query_id
stringlengths 32
32
| passage_id
stringlengths 32
32
| query
stringlengths 7
297
| category
stringclasses 6
values | passage
stringlengths 137
5.93k
| link
stringlengths 28
740
|
---|---|---|---|---|---|
f19fffecc6857bf94005a378992b12ed | 0de9578024a6b5778da7b591ef0b42fd | በአማራ ክልል ከአምደወርቅ- ተኬዜ-እብናት የገጠር መንገድ ፕሮጀክት ተመረቀ | ቢዝነስ | በአማራ ክልል የተገነባው አምደወርቅ-ተኬዜ-እብናት የገጠር መንገድ ፕሮጀክት በዛሬው ዕለት ተመርቆ ለትራፊክ ክፍት ሆነ፡፡በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ተመስገን ጥሩነህን ጨምሮ፤ የተለያዩ የክልሉ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡የ124 ኪ.ሜ የሚሸፍነው መንገዱ በአካባቢው ያለውን የእንስሳትና የተለያዩ የግብርና ምርቶችን ወደ ገበያ ለማቅረብ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡በአካባው በኢኮኖሚ መነቃቃት ረገድ ጉልህ ሚና ከመጫወቱም ባሻገር የሁለቱን ዞኖች ህዝቦች ማህበራዊ ግንኙነት እንደሚያጠናክርም ተገልጿል፡፡ | https://waltainfo.com/am/23921/ |
63b754c070d369ce4bc2094ba8309aa5 | 1fa2936c4df488ae70a537ea4b5437e2 | ኢትዮጵያ እና ብሪታንያ የ120 ሚሊየን ፓውንድ የድጋፍ ስምምነት ተፈራራሙ | ቢዝነስ | ኢትዮጵያ እና ብሪታንያ የ120 ሚሊየን ፓውንድ የድጋፍ ስምምነት ተፈራራሙ፡፡ስምምነቱን የኢፌዴሪ የገንዘብ ሚኒስትር ዲኤታ አቶ አድማሱ ነበበ እና የብሪታኒያ ዓለም አቀፍ የልማት ትብብር ሚኒስትር አሎክ ሻርማ በዛሬው እለት ተፈራርመውታል፡፡ከድጋፉ 95 ሚሊየን ፓውንዱ የፋይናንስ ተቋማትን ለማጠናከር፣ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ እና ለንጹህ ውሃ አቅርቦት እንደሚውል ተገልጿል፡፡ቀሪው 25 ሚሊየን ፓውንድ ለአራተኛው ዙር የሴፍቲኔት ልማት ፕሮግራም ማስፈጸሚያ የሚውል ነው ተብሏል፡፡የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ እና የውሃ ንጽህና አገልግሎት ድጋፉ ዓላማ በኢትዮጵያ በድርቅ በሚጠቁ አካባቢዎች የ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ያህል ዜጎችን የንጽህና እና የንጽህና አጠባበቅ ልምድ ለማሻሻል ያለመ መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡ቀሪው 25 ሚሊየን ፓውንድ የሴፍቲኔት ድጋፍ በገጠር አካባቢዎች የምግብ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች የምግብ ድጋፍ እና አደጋ ቅነሳ ስራ ለማከናወን የሚውል መሆኑም ተገልጿል፡፡ (ምንጭ፡-የገንዘብ ሚኒስቴር) | https://waltainfo.com/am/23919/ |
62ea3a699f046144f4679b09edfca6bd | 1bf23fa0c3d7bc7283e92b8035da3ce0 | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከእንግሊዝ ዓለም አቀፍ ልማት ትብብር ሚኒስትር አሎክ ሻርማ ጋር ተወያዩ | ፖለቲካ | ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከእንግሊዝ ዓለም አቀፍ ልማት ትብብር ሚኒስትር አሎክ ሻርማና ልዑካቸው ጋር ዛሬ ተወያይተዋል፡፡ሁለቱ ወገኖች እንግሊዝ ለኢትዮጵያ የልማት እንቅስቃሴዎች በምታደርገው ድጋፍ ዙሪያ ውይይት አድረገዋል፡፡የእንግሊዝ ዓለም አቀፍ ልማት ትብብር ሚኒስትር አሎክ ሸርማ፣ በኢትዮጵያ ያለው አገር በቀል ሪፎርምን አድንቀው፣ አገራቸው ለኢትዮጵያ ልማት የምታደርገውን ድጋፍ እንደምትቀጥል ተናግረዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እንግሊዝ ለኢትዮጵያ ለምታደርገው ድጋፍ አድናቆታቸውን ገልጸዋል፡፡(ምንጭ:-የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት) | https://waltainfo.com/am/31307/ |
38ad79399af19996eaa00dcfdf2a2c75 | 7b85823d1c597b0acad250a82fc39fdb | የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከፐብሊክ ዲፕሎማሲ ቡድን ካውንስል አባላት ጋር ተወያዩ | ፖለቲካ | የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከፐብሊክ ዲፕሎማሲ ቡድን የካውንስል አባላት ጋር በትናንትናው እለት ተወያይተዋል።በውይይቱ ወቅት ሚኒስትሩ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ባደረጉት ንግግር፥ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ በሌሎች ሀገራት ተሰርቶበት ለገፅታ ግንባታና ለመልካም ወዳጅነት በጎ ሚና መጫወቱን ጠቅሰዋል።በኢትዮጵያ ካለው አቅም ጋር ሲነፃፀር ግን ቨፐብሊክ ዲፕሎማሲ ዘፍር ብዙ እንዳልተሰራ ያመላክተዋል ሲሉም ተናግረዋል።ስለሆነም ያለውን አቅም በተሻለ ለመጠቀም ቀደም ብሎ በነበረው የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ቡድን ላይ አዳዲስ አባላት በመጨመርና መመሪያ በማዘጋጀት እንዲሁም ድጋፍ ሰጪ ተቃማትን በማስፋት ለአዲስ የዲፕሎማሲ ስራ ዝግጅቶች መጠናቀቁን አስታውቀዋል።የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ቡድን ካውንስል አባላቱ በበኩላቸው መመርያው ላይ ቢሻሻል የበለጠ ውጤት ያመጣል ያሉትን እንዲካተቱ ሃሳበ አቅርበዋል።ከበፊቱ የላቀ ስኬታማ ተግባራትን ማከናወን እንደሚችሉ ለዚህም ተግባር በመመረጣቸው ደስተኛ መሆናቸውን መግለፃቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ቡድን 75 አባላትን ያቀፈ ሲሆን፥ ከታዋቂ ሰዎች፣ ከሀይማኖት አባቶችና ተፅእኖ ፈጣሪ ግለስቦችን በማካተት ከስምንት አመት በፊት መዋቀሩ ይታወቃል። | https://waltainfo.com/am/31308/ |
6ca8330681b590f71d2b84fb570e08f3 | 0f35713bfb5b47d582ac313ac31d969a | ኢትዮጵያዊያን ሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርኃግብር ላይ ያሳዩትን ህብረት በሁሉም መስክ እንዲደግሙ ተጠየቀ | ቢዝነስ | ኢትዮጵያዊያን ሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርኃግብር ላይ ያሳዩትን ህብረት በሁሉም መስክ እንዲደግሙ ተጠየቀ፡፡የ2011 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የችግኝ ተከላ መርሃግብር የማጠቃለያ ፕሮግራም በዛሬው ዕለት በብሔራዊ ቤተመንግስት ተካሂዷል፡፡ በማጠቃለያ ፕሮግራሙ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በችግኝ ተከላ መርሃግብሩ ላይ የታየዉ ኢትዮጵያዊ ህብረትና ተሳትፎ ኢትዮጵያዊያን በሁሉም መስክ ላይ ከተባበሩ የማያስመዘግቡት ድል ላለመኖሩ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ሀገር አቀፍ የችግኝ ተከላ መረሃግብር ከታቀደለት በላይ ስኬታማ እንደነበርም ፕሬዝዳንቷ ጠቁመዋል፡፡በብሔራዊ ቤተመንግስት በተካሄደው የ2011 የችግኝ ተከላ መርሃግብር የማጠቃለያ ፕሮግራም ላይ በርካታ አርቲስቶች ችግኝ በመትከል አሻራቸውን አኑረዋል፡፡እንዲሁም ብሔራዊ አንድነት ጎልቶ በተስተዋለበት በአንድ ጀንበር ከ350 ሚሊየን በላይ ችግኞች በተተከሉበት የሐምሌ 22ቱ ሀገር አቀፍ የችግኝ ተከላ መርሃግብር በየክልሉ ተሰማርተው የነበሩ የአርቲስቶች ቡድን ከየክልሉ ይዘው የመጡትን ምልዕክት በማስተላለፍ ዘጠኙን ክልሎችንና ሁለት ከተማ አስተዳደሮችን የሚወክሉ አንዳንድ ችግኝ በቤተመንግስት ውስጥ ተክለዋል፡፡ክልሎቹንና ከተማ አስተዳደሮቹን ወክለው ከተተከሉ 11 ችግኞች በተጨማሪ በመሃከላቸው የኢትዮጵያ አንድነትን የሚወክል 12ኛው ችግኝ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴን በመወከል ተተክሎ የመርሃግብሩ ማጠቃለያ ተደርጓል፡፡ | https://waltainfo.com/am/23916/ |
956a648920531a808a71028b200ca50f | 0115a648be9afda87b54572cdeff4cd6 | ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገ/ስላሴ በዋግ ኽምራ ያስገነባው ትምህርት ቤት ተመረቀ | ሀገር አቀፍ ዜና | ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረ ስላሴ የቀድሞውን የዳስ ትምህርት ቤት ደረጃውን በጠበቀ መልኩ አስገንብቶ አስመርቋል፡፡አትሌቱ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ፃግብጂ ወረዳ ላይ ያስገነባው ገልኩ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ነው ለምረቃ የበቃው፡፡ትምህርት ቤቱ ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረ ስላሴ አጠቃላይ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተሰኝቷል፡፡ሁለት ብሎኮችና ስምንት የመማሪያ ክፍሎች ያሉትን ይህን ት/ቤት ኃይሌ በሦስት ወራት በማስገንባት ነው ለቀጣዩ የትምህርት ዘመን ማስተማሪያ ዝግጁ ያደረገው፡፡በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ነዋሪነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ አንድ ግለሰብ 8 ሺህ 500 የማጣቀሻ መጻህፍትን ለትምህርት ቤቱ መለገሳቸው ተገልጿል፡፡ | https://waltainfo.com/am/32670/ |
25eb36f1293d055528e522e6e3fb6704 | fcbde641862a1387162210ce632184fb | ፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በኢትዮጵያ የለውጥ ዙሪያ የሚወያይ ኮንፈረንስ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዳራሽ አስጀመሩ | ፖለቲካ | ፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በኢትዮጵያ የለውጥ ሂደት፣ ወቅታዊ ሁኔታ፣ መፃኢ እድል እና ስጋቶች ዙሪያ የሚወያይ ኮንፈረንስ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዳራሽ አስጀመሩ፡፡ፕሬዝዳንቷ ኢትዮጵያ በታሪኳ ወሳኝ የሚባል የለውጥ መንደርደሪያ ላይ እንደምትገኝ ገልፀዋል፡፡ይህ ወቅት ኢትዮጵያ የህዝቦቿን መሰረታዊ ጥያቄዎች ለመመለስና ፍላጎታቸውን ለማርካት ከፍተኛ የለውጥ እንቅስቃሴ ጅማሮ ላይ እንደምትገኝም አብራርተዋል፡፡በዚህ ሂደት ላይ የህዝቡን አንድነትና ተነሳሽነት ለማጠናከር ከቃላት ባለፈ በተግባር የሚገለፁ በርካታ መሰራት ያለባቸው ተግባራት ከፊት እንደሚጠብቁ ተናግረዋል፡፡እስካሁን ድረስ የታዩት ተስፋዎችን አጠናክሮ በመቀጠል ለሚፈለገው ድል ለመድረስ ከህዝቡ አቅም በላይ እንደማይሆን አምናለሁ ያሉት ፕሬዝዳንቷ ለዚህ ሂደት አቅጣጫ የሚያመላክት ፍሬያማ ውይይት ከኮንፈረንሱ እንደሚጠብቁ አብራርተዋል፡፡ መረጃው የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ነው፡፡ | https://waltainfo.com/am/31306/ |
3c0bf0c2d123f5382fcda29378f695a4 | 1bc359b3e11a3f2600964aac0160e9be | የእነ ብርጋዲየር ጄነራል ተፈራ ማሞን የክስ መዝገብ ለመመርመር ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠ | ሀገር አቀፍ ዜና | የባሕር ዳር እና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የእነ ብርጋዲየር ጄነራል ተፈራ ማሞ የምርመራን መዝገብ ለመመርመር ለነሐሴ 21 ቀን 2011 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ።ፍርድ ቤቱ በእነ ጄነራል ተፈራ ማሞ የክስ መዝገብ መርማሪ ፖሊስ በጠየቀው የጊዜ ቀጠሮ ይግባኝ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ለመመርመር በማስፈለጉ ነው ቀጠሮ የሰጠው።ብርጋዲየር ጄነራል ተፈራ ማሞ የብዙዎቻችን ተጠርጣሪዎች የባንክ ደብተሮች በመርማሪ ቡድኑ ስለተያዙብን፣ በቤት ኪራይ የሚኖሩ ቤተሰቦቻችን ለችግር ተዳርገዋል ሲሉ ለችሎቱ አቤት ብለዋል።የመርማሪ ቡድኑ በበኩሉ ከወንጀሉ ጋር የሚያያዝ ከሆነ የባንክ አካውንት የሚታገድበት እንጂ የባንክ ደብተሩ የሚያዝበት አግባብ እንደሌለ ለችሎቱ አስረድቷል።የተጠርጣሪዎቹ የባንክ ደብተር እና አልባሳት በቁጥጥር ስር በዋሉባቸው ፖሊስ ጣቢያዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም መርማሪ ቡድኑ ጠቁሟል።ፍርድ ቤቱም ተጠርጣሪዎቹ በምርመራ ሒደት በቁጥጥር ስር ሲውሉ ከሕግ አግባብ ውጭ የተያዙባቸው ንብረቶች እንዲመለሱላቸው ትእዛዝ ሰጥቷል።እንደ ኢቢሲ ዘገባ የተጠርጣሪ ጠበቆች በበኩላቸው ተጠርጣሪዎቹ በመታሰራቸው ምክንያት የሚያስተዳድሯቸው ቤተሰቦች ችግር ላይ ወድቀዋል በሚል ለችሎት ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት፣ ለችግር የተጋለጡ የተጠርጣሪ ቤተሰቦች ቀለብ እንዲሰጣቸው ትእዛዝ አስተላልፏል። | https://waltainfo.com/am/32671/ |
df82179f33eae1521e422e4d46225d8b | d17c0f7bd3ab09118c07f5672121f3ea | የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ መሠረት ማስፋት የሚያስችል የሦስት ዓመት ፕሮጀክት ይፋ ሆነ | ቢዝነስ | የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ መሠረት ማስፋት የሚያስችል ለሶስት ዓመታት የሚተገበር በአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ተራድኦ (ዩኤስ ኤይድ) የሚደገፍ እና በሀርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ጥናት የሚመራ ፕሮጀክት ይፋ ሆነ።ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ የጀመረችውን የኢኮኖሚ ሪፎርም ይደግፋል ሲሉ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ዶ/ር ይናገር ደሴ ተናግረዋል፡፡ፕሮጀክቱን ለማስፈፀምም መንግስት በሀርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ጥናት ታግዞ እንደሚሰራ የገለፁት ገዢው፤ በኢንቨስትመንት ማስፋፊያ፣ በስራ አጥነት ቅነሳ እና ጥናትን መሠረት ባደረጉ ፕሮጀክቶች ላይ ይሰራልም ብለዋል፡፡ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ በተጀመረው የኢኮኖሚ ሪፎርም የፖሊሲ ምክረ ሐሳብ በማፍለቅ በኩል እገዛ እንደሚያደርግ የብሔራዊ ባንክ ዋና ገዥ ዶ/ር ይናገር ደሴ ተናግረዋል።ኢትዮጵያ የወሰደችውን የኢኮኖሚ ማሻሻያ የአሜሪካ መንግስት እንደሚደግፍ የገለፁት በኢትዮጵያ የዐሜሪካ አምባሳደር ማይክ ራይነር ለማሻሻያው ተግባራዊነት እና ተፈፃሚነት መንግስታቸው ያላሰለሰ ድጋፍ እንደሚያደርግም ተናግረዋል፡፡አሜሪካ ላላፉት ሦስት ዓመታት በትምህርት፣ በጤና እና በኃይል ልማት ዘርፎች ከሦስት ቢሊየን ዶላር በላይ ኢንቨስት ማድረጓንም አምባሳደሩ ተናግረዋል።ፕሮጀክቱን ዩኤ ኤይድ በገንዘብ የሚደግፈው መሆኑም ተገልጿል። | https://waltainfo.com/am/23918/ |
acc542a097fe2c6c510091ce473b2c66 | cc6573b916461b69941b7ab611ff63c4 | የሻዳይ፣አሸንድዬ እና ሶለል ባህል ዓመታዊ ክብረ በዓል በባሕር ዳር ከተማ በድምቀት ተከበረ | ሀገር አቀፍ ዜና | የሻዳይ፣አሸንድዬ እና ሶለል ባህል ዓመታዊ ክብረ በዓል በባሕር ዳር ከተማ በድምቀት ተከበረ፡፡በዋግ ሹሞች መዲና ሰቆጣና አካባቢዋ ሻደይ፣ በቆቦ አካባቢ ሶለል እና በላስታ እና በአብዛኛው የክልሉ አካባቢዎች አሸንድዬ በሚል የሚከበረው የልጅ አገረዶች ጨዋታ በዓል ዛሬ በባህርዳር ከተማ በድምቀት ተከብሯል።በዚሁ በክልላዊው የሻደይ፣ አሸንድዬ እና ሶለል በዓል አከባበር ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ጥሩነህ፣ የፌዴራል ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ኂሩት ካሳው እና የተለያዩ የክልል እና የፌዴራል የስራ ሃላፊዎች ታድመዋል፡፡በስነ ስርዓቱ ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ከመገፋፋትና ከመጠላላት ወጥተን አንድ ስንሆን የጥበብ አውድማ እና የፍቅር ተምሳሌት እንሆናለን ብለዋል፡፡ዘመን ባልከለሰው አብሮነታችሁ አምራችሁና ደምቃችሁ ስትታዩ በእርግጥም ‘የአማራ ሕዝብ ታላቅ ነው’ ስንል ያለምክንያት አለመሆኑን ከመግለፁም ባሻገር ጥበብ፣ ኩራት፣ አብሮነትና ጀግንነት የክልሉ ህዝብ መገለጫዎች ማሳያ ጭምር እንደሆኑ ያሳያልም ብለዋል።የአብሮነታችን አሻራ፣ የአንድነታችን ተምሳሌት እና የፍቅራችን መገለጫ የሆነው የሻደይ፣ አሸንድየ እና ሶለል በዓል በዩኔስኮ በማይዳሰ ወካይ ቅርስነት ለማስመዝገብ ስራ መጀመሩንም ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል፡፡የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ጥሩነህ “ታላቅ ነን ስንል ራሳችንን አክብረንና አስከብረን ሌሎችንም የምናከብር ህዝቦች ነን ማለታችን ነው፤ ታላቅ ነን ስንል ችግር በገጠመን ጊዜ አንድ ሆነንና ተባብረን ከችግር የምንወጣ ብርቱ ህዝቦች ነን ማለታችን ነው፤ ታላቅ ነን ስንል በችግር አረንቋ ውስጥ ያሉ ሌሎች ህዝቦችን የምንታደግ ህዝቦች ነን ማለታችን ነው›› በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።የሻዳይ፣አሸንድዬ እና ሶለል ባህል በዩኔስኮ በማይዳሰ ወካይ ቅርስነት ለማስመዝገብ ስራ መጀመሩንም ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል፡፡የአማራ ክልል ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ግዛት አብዩ በበኩላቸው የሻደይ፣ አሸንድዬ እና ሶለል በዓል ራሱን የቻለ የቱሪስት መስህብ እንዲሆን እንደሚሰራ ገልጸዋል።በአማራ ክልል በርካታ ዘመን ተሻጋሪ ባህላዊ ሁነቶች እንዳሉ የገለጹት አቶ ግዛት፤ የሻደይ፣ አሸንድዬ እና ሶለል ባህላዊ ክዋኔዎቹ ሳይበረዙ እና ሳይከለሱ የባህሉ ባለቤት በሆነው ሕዝብ ተጠብቀው፣ ተናፍቀው እና ተወዳጅነታቸውን አጎልብተው እንዲዘልቁም ይደረጋል ብለዋል። | https://waltainfo.com/am/32674/ |
f59d5e18c7391d796aae5b8a6f1e1a4f | f07586f7201a7d2e776fed001b616d40 | ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ ለአዳዲሶቹ የሱዳን መሪዎች የመልካም ምኞት መግለጫ አስተላለፉ | ፖለቲካ | ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ለአዳዲሶቹ የሱዳን መሪዎች የመልካም ምኞት መግለጫ አስተላልፈዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በዛሬው እለት ባስተላለፉት መልእክት፥ ጀነራል አብዱል ፈታህ ቡርሀን 11 አባላት ያሉት ሉዓላዊ ምክር ቤት መሪ ሆነው በመመረጣቸው እንኳን ደስ አለዎት ብለዋል።እንዲሁም የነሐሴ 11 የሽግግር መንግስት ስምምነት ፊርማን ተከትሎ ጠቅላይ ሚንስትር ሆነው ለተመረጡት አብደላ ሀምዶክ የመልካም ምኞት መግለጫ ማስተላለፋቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል።ጄኔራል አብድል ፈታ ቡርሃን አዲስ የተቋቋመው እና 11 አባላት ያሉት የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት መሪ ሆነው በትናንትናው እለት ነው የተመረጡት።11 አባላት ያሉት የሱዳን ሉዓላዊ የሽግግር ሸንጎ ኦማር ሀሰን አል በሽር ከስልጣን ከወረዱበት ሚያዚያ 2019 ጀምሮ ሀገሪቱን ሲመራ የቆየውን ወታደራዊ የሽግግር ምክር ቤትን ተክቶ ትናንት ነው በይፋ ስራውን የጀመረው።ሌተናል ጄነራል አብደል ፈታህ አብደልራህማን ቡርሃን አዲስ የተቋቋመው የሱዳን ሉአላዊ ምክር ቤት መሪ በመሆን በትናንትናው እለት ቃለ መሃላ ፈጽመዋል።ጀኔራል ቡርሃን ከሶስት ዓመት በላይ የሽግግር ጊዜ ውስጥ የሉዓላዊ ሸንጎውን ለ21 ወራት በበላይነት የሚመሩት ሲሆን፥ የሲቪል ተወካዮች ደግሞ ቀጣዮቹን 18 ወራትን ይመራሉ።11 አባላት ያሉት ሉዓላዊ ምክር ቤት በትናንትናው እለት በይፋ ስራውን መጀመሩን ተከትሎም አብደላ ሀምዶክ የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን በትናንትናው እለት ቃለመሃላ ፈፅመዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚነታቸውን የለቀቁት ባለፈው ዓመት ነበር።አብደላ ሃምዶክ በኢኮኖሚ ተንታኝነት ከ30 ዓመት በላይ ልምድ ያላቸው ሲሆን፥ ከካርቱም ዩንቨርሲቲና ከታወቁ የእንግሊዝ ትምህርት ተቋሞት ዲግሪያቸውን አግኝተዋል።ወታደራዊ ምክር ቤቱና የነጻነትና የለውጥ ኃይሎች ጥምረት የአገሪቱን የሽግግር መንግሥት ለመጀመር ባለፈው ቅዳሜ መፈራረማቸው የሚታወስ ነው።(ምንጭ፦ ኤፍቢሲ) | https://waltainfo.com/am/31304/ |
87a0ba7482d6c850d92d233c6bc03f6a | c6ea3c48b2bb7b45bb31d952aec58b73 | በተያዘው ክረምት ወራት በጎርፍ አደጋ ከ1.3 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ሊጠቁ እንደሚችሉ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ | ሀገር አቀፍ ዜና | በክረምት ወራት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በሚከሰተው የጎርፍ አደጋ ከ1.3 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ሊጠቁ እንደሚችሉ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ፡፡የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን፣ ብሄራዊ ሜትዎሮሎጂ እና የተፋሰሶች ልማት ባለስልጣን በጋራ በመሆን በሀገሪቷ የክረምት ወቅት ሊፈጠር ይችላል ተብሎ በሚታሰበው ቅጽበታዊ ጎርፍ አደጋ እና ሊደረግ የሚገባውን ጥንቃቄ አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል፡፡በኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ በሚዘንብ ዝናብ፣ በወንዞች እና ግድቦች መሙላት ምክንያት በተለያዩ የሃገሪቷ አካባቢዎች የጎርፍ አደጋዎች እየተስተዋሉ ነው፡፡ በዚህም የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የጎርፍ አደጋው የሚያስከትለውን አደጋ ለመቀነስ እና ለመከላከል በፌደራል እና በክልል ደረጃ ግብረ ሃይል ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ ለቅድመ ጎርፍ መከላከል እና በጎርፍ ወቅት 1.3 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በጎርፍ ሊጠቁ እንደሚችሉ የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዳመና ዳሮታ ተናግረዋል፡፡በደቡብ፣ አማራ፣ ኦሮሚያ እና አፋር ክልሎች በሚገኙ ሰባት ወረዳዎች ከ23 ሺህ 900 በላይ ሰዎች ላይ በጎርፍ አደጋ ጉዳት እንደደረሰም ምክትል ኮሚሽነሩ ገልጸዋል፡፡የብሄራዊ ሜትዎሮሎጂ ኤጀንሲ የ2011 የክረምት የአየር ፀባይ አዝማሚያን በተመለከተ በግንቦት ወር መረጃውን ለህዝብ ተደራሽ ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡ በዚህም ባለፉት ሁለት የክረምት ወራት በአብዛኛው ሃገሪቷ ክፍል ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደነበር መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡በሚቀጥሉት የክረምት ወራት ደግሞ መደበኛ እና ከመደበኛ በላይ ዝናብ እንደሚከሰት እና በአንዳንድ አካባቢዎች ቅጽበታዊ ጎርፍ ያጋጥማል ተብሎ እንደሚጠበቅ የብሄራዊ ሜትዎሮሎጂ ኤጀንሲ ምክትል ዳይሬክተር አቶ ክንፈ ሃ/ማርያም ገልጸዋል፡፡በሀገሪቷ በተለያዩ አካባቢዎች በተለይ ቆቃ፣ መልከዋከና፣ ግልገል ጊቤ፣ ተከዘ እና ሌሎች ግድቦች ላይ እየተከሰተ ባለው የውሃ መሙላት ሳቢያ የጎርፍ አደጋ እንሚያጋጥማቸው ተገልጿል፡፡ግድቦቹ በመሙላታቸው በሰው እና በንብረት ላይ ከፍተኛ አደጋ እያስከተሉ እንደሚገኙ የገለጹት የተፋሰሶች ልማት ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ግዛው በግድቦቹ አካባቢ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ሊያጋጥም የሚችለውን የጎርፍ አደጋ ለመከላከል የጎርፍ ስጋት ወደሌለባቸው አካባቢዎች መሄድ እንደሚገባቸው ጠቁመዋል፡፡ | https://waltainfo.com/am/32669/ |
887da3e1283687824d0f5c10c810ddac | d135b5021d88f21e7de7c4d770ffd0d3 | 33 የምግብ አምራችና አስመጭዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ | ቢዝነስ | በ33 የምግብ አምራችና አስመጪ ድርጅቶች ላይ እርምጃ መውሰዱን የኢትዮጵያ የምግብና መድሃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን አስታወቀ፡፡ባለስልጣኑ የተቋሙን የ2011 እቅድ አፈፃፀም እና የ2012 እቅድ አስመልክቶ ትናንት መግለጫ ሰጥቷል።የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተሩ አቶ ሳምሶን አብርሃም እንደተናገሩት ህገ ወጥ ተግባራት ሲያከናውኑ በተገኙ ተቋማት ላይ እርምጃ ተወስዷል፡፡“ህገወጥ ተግባራትን በፈፀሙ አካላት ላይ ምርቶችን ከማስወገድ አንስቶ ተቋማቱን እስከ ማስዘጋት ደርሰናል” ያሉት የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው ከዘርፉ የማስወጣት እና በህግ የመጠየቅ ሥራ መሰራቱንም ተናግረዋል፡፡ተቋሙ ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የሚሰጡ ጥቆማዎችን መሠረት በማድረግ መድሃኒት እና ምግብ አስመጪዎች ላይ ፍተሻዎችን በማድረግ እርምጃ እየተወሰደ እንደሆነ ነው ያስታወቁት፡፡የታሸጉ ምግቦች በብዛት በበረሃማ አካባቢዎች ስለሚገቡ ወደ አደገኛ ኬሚካልነት እንደሚቀየሩና በኅብረተሰቡ ላይም ከፍተኛ የጤና ጉዳት፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ እንደሚያስከትሉ ተመላክቷል።እንደ አዲስ ዘመን ዘገባ በበጀት ዓመቱ በኅብረተሰቡ ጥቆማ እንዲሁም ድንገት በተደረገ ፍተሻ ከ4 ሺህ 763 ቶን በላይ ምግብ መያዙን አቶ ሳምሶን አስታውቀዋል። | https://waltainfo.com/am/23915/ |
f53636096d8beaea8c1c4c1086ae0c15 | 4de5ca4e5316cc7792b338bba250db7e | የኦሮሚያ ክልል የዜግነት አገልግሎት ምክር ቤት ምስረታ እየተካሄደ ነው | ፖለቲካ | የኦሮሚያ ክልል የዜግነት አገልግሎት ምክር ቤት ምስረታ መድረክ በአዲስ አበባ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት አዳራሽ እየተካሄደ ነው፡፡ጨፌ ኦሮሚያ በ4ኛ ዓመት 5ኛ የስራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ጉባኤው የዜግነት አገልግሎት አዋጁን በማጽደቅ የክልሉ መንግስት ስራ ላይ ያዋለው መሆኑ ይታወቃል፡፡በመድረኩ ላይ የኦሮሚያ ክልል ም/ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ አባገዳዎች፣ አርቲስቶችና ሌሎች ተሳታፊዎች መገኘታቸውን ከኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ | https://waltainfo.com/am/31305/ |
8866dd2963fce4d63d05340460f366cb | ca26afb0af01a9ca3955b8505350d3d3 | ሞቃዲሾ አዲስ ከንቲባ አገኘች | ፖለቲካ | የሶማሊያው ፕሬዚዳንት መሐመድ አብዱላሂ ፋርማጆ የቀድሞውን የጦር አበጋዝና የመንግሥት ሚኒስትር የነበሩት ኦማር መሐመድን የሞቃዲሾ ከንቲባና የባዲር ግዛት አስተዳደሪ አድርገው ሾመዋል።ሹመቱ ባለፈው ወር በአጥፍቶ ጠፊዎች ህይወታቸው ያለፈውን የቀድሞ ከንቲባ አብዱራህማን ኦማር ኦስማንን ለመተካት መሆኑ ተገልጿል፡፡አዲሱ ከንቲባ ኦማር መሐሙድ መሐመድ እ.አ.አ 2004 ላይ በተመሠረተው የሽግግር መንግሥት ውስጥ የሃይማኖት ጉዳዮች ሚኒስትር ከመሆናቸው አስቀድሞ ሞቃዲሾ ውስጥ የጦር አበጋዝ ነበሩ።እ.አ.አ እስከ 2009 ድረስም በሚኒስትርነት አገልግለዋል።ኦማር መሐመድ ለሞቃዲሾ ከንቲባነት የተመረጡት በመንግሥት ውስጥ ባላቸው ልምድ እንዲሁም የልማት ፕሮጀክቶችን ተግባራዊነት ማስቀጠል የሚያስችሉ በመሆናቸው ነው መባሉን የዘገበው ቢቢሲ ነው። | https://waltainfo.com/am/33328/ |
5bfea7ef5b0ae60f725e0b0e58b3ce9a | b631b6db6d36b1e96ad5355c4e49b48e | ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በመቐለ እየተከበረ በሚገኘው የአሸንዳ በዓል ላይ ተገኙ | ሀገር አቀፍ ዜና | ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የአሸንዳ ክብረ በዓል ላይ ለመገኘት በዛሬው ዕለት መቐለ ገብተዋል፡፡ፕሬዝዳንቷ አሉላ አባነጋ አየር ማረፊያ ሲደርሱ በትግራይ ክልል ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤልና በሌሎች የክልሉ አመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡የአሸንዳ በዓል በትግራይ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የሰላም፣ አንድነትና ልማት ተምሳሌት” በሚል መሪ ቃል እየተከበረ ይገኛል፡፡በትግራይ ክልል በነሃሴ ወር የሚከበረው የአሸንዳ፣ ማሪያ እና ዓይኒ-ዋሪ በዓላት የክልሉን ባህል፣ ትውፊትና የቱሪዝም መስህቦች በማስተዋወቅ ረገድ የላቀ ሚና እንዳለው ይነገራል፡፡ | https://waltainfo.com/am/32668/ |
3cf6744f9944f3194a4ac45001bc09b6 | f4015ddcd5b0006cef1b9d6873f7700a | የሻደይ፣ አሸንድዬ እና ሶለል የልጃገረዶች ጨዋታዎች ከዛሬ ጀምሮ ይከበራሉ | ሀገር አቀፍ ዜና | የሻደይ፣ አሸንድዬ እና ሶለል ጨዋታዎች በዋግ ኽምራ፣ በላል ይበላ እና በቆቦ ከዛሬ ነሐሴ 16 እስከ 21/2011 ዓ.ም ይከበራሉ።በበዓሉ ለመታደም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ተመስገን ጥሩነህ የተመራ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ልዑክ ትናንት ማምሻውን ሰቆጣ ከተማ ገብቷል።ለልኡካኑ የሰቆጣ ከተማና እና አካባቢዋ ነዋሪዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል። የየወረዳዎቹ ሻደይ ባህላዊ ተጫዋች ቡድኖችም በባህሉ ዜማና ጨዋታዎች ታጅበው ነው የአቀባበል ያደረጉላቸው። ሰቆጣም ከዋዜማው ጀምሮ የሻደይ ጨዋታን መከወን ጀምራለች።የዘንድሮው የሻደይ በዓል "ሻደይ ባህላችን ለዘላቂ ልማትና ሰላማችን" በሚል መሪ ሀሳብ ነው የሚከበረው።የሻደይ፣ አሸንድዬ እና ሶለል የልጃገረዶች ጨዋታዎች ባለፈው ዓመት በክልል ደረጃ ባሕር ዳር ላይ መከበሩ ይታወሳል። በዚህ ዓመት ደግሞ ከክልል ባለፈ አዲስ አበባ ላይም እየተከበረ ነው። በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎችም እንደሚከበር ታውቋል።በአዲስ አበባ በፓናል ውይይት በየክፍለ ከተሞች ሲከበር የቆየው በዓሉ የፊታችን ነሐሴ 19/2011 ዓ.ም በሚሊኒዬም አዳራሽ ይከበራል፤ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በማይዳሰሱ ቅርሶች መዝገብ ለማስፈርም ጥረቱ ቀጥሏል። | https://waltainfo.com/am/32666/ |
7dbeb8e1b66fe5a5a5427a849fde2be2 | fdf2e85a36298364562466351512d1e6 | ኢትዮጵያ በኢንዶኔዢያ- አፍሪካ የመሰረተ ልማት ዓለም አቀፍ ጉባኤ እየተሳተፈች ነው | ቢዝነስ | የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የከተማ ልማትና ኮንስራክሽን ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድ በባሊ ኢንዶኔዢያ በመካሄድ ላይ ባለው የኢንዶኔዢያ- አፍሪካ የመሰረተ ልማት ዓለም አቀፍ ጉባኤ ላይ በመሳተፍ ላይ ናቸው፡፡በጉባዔው በተካሄደው የፓናል ውይይት ማብራሪያ የሰጡት ኢንጂነር አይሻ ባለፉት አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ ጠንካራ የኢከኖሚ ዕድገት ማሰመዝገቧን ተናግረዋል፡፡በተለይም በመሰረተ ልማት ልማት ያላትን ተሳትፎ ይበልጥ ውጤታማና ተወዳዳሪ ለማድረግ እየሰራች መሆኗንም ገልፀዋል፡፡በመንገድ መሰረተ ልማት ፣ በባቡር ሐዲድ ፣ በብሔራዊ ሎጅስቲክስ ልማት ፣ በትራንስፖርት ዘርፍና በአየር ትራንስፖርት ዘርፎች የተመዘገቡት ውጤቶች አስደናቂ መሆናቸውን ሚኒስትሯ ለጉባኤው ተሳታፊዎች አብራርተዋል፡፡በተለይም የኢትዮጵያ የባቡር ኮርፖሬሽኑ ዋና ከተማዋን ከጂቡቲ ወደብ ጋር የሚያገናኝ የ 656 ኪሎ ሜትር የባቡር መስመር መዘርጋቱንና ይህም ወደ ጅቡቲ ወደብ ለመድረስ ይፈጅ የነበረውን የ 84 ሰዓታት ቆይታ ጊዜ ወደ 10 ሰዓታት ድረስ ለመቀነስ መቻሉንም አንስተዋል፡፡የኢትዮጵያ መንግስት የግንኙነት ትስስርን እና መሠረተ ልማቶችን ለማጎልበት ብሎም የአካባቢያዊ ና የአለም አቀፍ የንግድ እንቅስቃሴዎችን ለማሳደግ የኢትዮ-ቴሌኮም ፣ የኢትዮጵያ የመርከብና የሎጂስቲክስ አገልግሎት እንዲሁም የኢትዮጵያ አየር መንገድን የመሳሰሉ በመንግስት የተያዙ ኩባንያዎችን በከፊል በግል ለማዞር የሚያችል ዕቅድ መዘርጋቱን ገልጸዋል ፡፡የኢትዮጵያ መንግስት ከኢንዶኔዥያና ከህዝቧ ጋር በመሰረተ ልማትና በሌሎች ዘርፎች ለጋራ ብልፅግናና ልማት እንደምትሰራ መናገራቸውን ከኢፌዴሪ የኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡የኢንዶኔዢያ- አፍሪካ የመሰረተ ልማት ጉባኤ በየዓመቱ ኤንዶኔዢያ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትስሰስር ለማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳየች ላይ የሚመክር ጉባኤ ነው፡፡ | https://waltainfo.com/am/23913/ |
7e52d33d9aa03468f41a4fa45a4a3278 | bdaf23d19557d8524e71461dd4ad47ea | የአሸንዳ /አውርስ በዓል በትግራይ ክልል እየተከበረ ነው | ሀገር አቀፍ ዜና | የአሸንዳ /አውርስ በዓል በትግራይ ክልል በመከበር ላይ ይገኛል፡፡በዓሉ “አሸንዳ/አውርስ የሰላም፣ አንድነትና ልማት ተምሳሌት” በሚል መሪ ቃል በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች በመከበር ላይ ነው የሚገኘው።በዓሉ በክልሉ በሚገኙ ከተሞች እና የገጠር ወረዳዎች በሙሉ በመከበር ላይ የሚገኝ ሲሆን፥ በአሁኑ ሰዓትም በክልል ደረጃ በዓቢይ ዓዲ ከተማ እየተከበረ ነው።በበዓሉ ላይም የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ደኤታ ወይዘሮ ብዙነሽ መሰረት፣ በትግራይ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር ማእረግ የከተማ ልማት፣ ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ ዶክተር አብረሃም ተኸስተን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የክልል እና የፌደራል የስራ ሃላፊዎች እና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።በዓቢይ ዓዲ ከተማ በመከበር ላይ በሚገኘው በዓል ላይም ከሰቆጣ የመጡ ልኡካንም በመሳተፍ ላይ እንደሚገኙ ታውቋል።አሸንዳ/አውርስ በዓል ከ8 ሰዓት ጀምሮ በክልል ደረጃ ከፍተኛ የፌደራል እና የክልል አመራሮች በተገኙበት በመቐለ ከተማ በደማቅ ሁኔታ እንደሚከበርም ይጠበቃል።በትግራይ ክልል በነሃሴ ወር የሚከበረው የአሸንዳ፣ ማሪያ እና ዓይኒ-ዋሪ በዓላት የክልሉን ባህል፣ ትውፊትና የቱሪዝም መስህቦች በማስተዋወቅ ረገድ የላቀ ስራ የሚሰራበት ፕሮግራም ነው።አሸንዳ እና ማሪያ ከነሃሴ 16 ጀምሮ የሚከበር ሲሆን፥ ዓይኒ-ዋሪ ደግሞ ነሃሴ 24 2011 ዓ.ም በአክሱም ከተማ እና አካባቢው የሚከበር የልጃ ገረዶች በዓል ነው።በዓሉ በህዝቦች መካከል ሰላም፣ አንድነት እና ፍቅር እንዲኖር ከሚሰጠው ጠቀሜታ በተጨማሪ ለቱሪዝም መስህብነት በማገልገል ለኢኮኖሚው አስተዋዕኦ እንዳለው ይታወቃል።እንደ ኤፍቢሲ ዘገባ አሸንዳ/አውርስ በዓል የፊታችን ነሃሴ 26 2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃ የሚከበር ይሆናል። | https://waltainfo.com/am/32667/ |
ba6c19f1d97269672d2a877898d1bdb8 | b4543bd0ee5016fb9835a6b083fc6188 | አምስት የአውሮፓ ሕብረት ሀገራት ስደተኞችን ሊቀበሉ ነው | ሀገር አቀፍ ዜና | አምስት የሚሆኑ የአውሮፓ ሕብረት አባል ሃገራት፤ ስፔን፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ሉክዘምበርግ እና ፖርቹጋል በጣሊያን ደሴት ላምፔሱዳ የደረሱ ስደተኞችን ሊቀበሉ መሆናቸው ተገለፀ።ስደተኞቹን የጫነችው የእርዳታ መርከብ ተቀባይ በማጣቷ ለሳምንታት በሜዲትራኒያን ባህር ላይ ስትዋልል ቆይታ ጣሊያን ላምፔሱዳ የደረሰችው ባለፈው ማክሰኞ እንደነበር ተገልጿል።የአገሪቷ አቃቤ ሕግ መርከቧ እንድትለቀቅ ትዕዛዝ ማስተላለፈቻውን ተከትሎ ቁጥራቸው ወደ አንድ መቶ የሚጠጉ ስደተኞችን ያሳፈረችውና 'ባለሽበት ቆይ' የተባለችው መርከብ እንድትንቀሳቀስ ተፈቅዶላታል።ምንም እንኳን ከስደተኞቹ መካከል ህፃናትና በጠና የታመሙ ሰዎች ቢኖሩም የአገር ውስጥ ሚንስትሩ ማቴዎ ሳልቪኒ "ከዚህ በኋላ ወደቦቻችን ለስደተኞች ዝግ ናቸው።" በማለት ስደተኞቹ ከመርከቧ እንዳይወርዱ ለሦስት ሳምንታት ያህል ተከልክለው ቆይተዋል።ቀደም ሲል 10 ስደተኞች ደሴቷ ጋር በዋና እንደርሳለን በሚል ተስፋ ከመርከቧ ዘለው ባህር ውስጥ መግባታቸው ተጠቅሷል።በሥፍራው የሚገኙት ስደተኞችም ቆስለውና በፋሻ ተጥቅልለው ይታዩ እንደነበር ኤ ኤፍ ፒ የዜና ወኪል ዘግቧል።ከስደተኞቹ መካከል አንዱ "ልቀውስ ትንሽ ቀርቶኝ ነበር" ሲል የነበረበትን ሁኔታ ለዜና ወኪሉ ገልጿል።እንደ ሮይተርስ የዜና ወኪል ከሆነ የአውሮፓ ሕብረት ኮሚሽን እነዚህን ስደተኞችን የሚቀበሉ ሃገራትን ሲያፈላልግ ቆይቷል።በመጨረሻም ስደተኞችን የጫነችው ሁለተኛዋ የእርዳታ መርከብ፤ ለ13 ቀናት በሜዲትራኒያን ባህር ላይ ከቆየች በኋላ ሃገራቱ ከአደጋው የተረፉትን ከ100 በላይ ስደተኞች ለመቀበል ፈቅደዋል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል። | https://waltainfo.com/am/34129/ |
9e6ce4c7a2be1536c0b687a260eabf00 | 215677edc62de55e10b803b4ed2bd031 | ሊድ አሲድ ለአካባቢ አየር ንብረት ለዉጥ የሚያበረክተዉን አስተዋፅኦ ለመቀነስ የሚያስችል ፍኖተ ካርታ ለማዘጋጀት ዉይይት ተካሄደ | ቢዝነስ | ባገለገሉ ባትሪዎች ዉስጥ የሚገኘዉ ሊድ አሲድ ለአካባቢ አየር ንብረት የሚያበረክተዉን አስተዋፅኦ ለመቀነስ የሚያስችል ፍኖተ ካርታ ለማዘጋጀት ዉይይት ተካሄደ፡፡በአካባቢ ደንና አየር ንብረት ለዉጥ ኮሚሽን የፖሊሲ ፤ ደረጃዎች ጥናትና ዝግጅት ጀነራል ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር አየለ ሄገና በዉይይት መድረኩ ላይ እንዳሉት ኢትዮጵያ ባለፉት 30 አመታት የአየር ንብረት ለዉጥን ተፅዕኖ ለመከላከል የተለያዩ ተግባራትን ስታከናዉን ቆይታለች፡፡ባለፉት 2 አመታትም የተለያዩ ከጉዳዩ ጋር የተያያዙ አዋጆችና ደንቦች ማሻሻያ እንዲደረግባዉ መደረጉን አዉስተዉ በቀጣይ ወደተግባር ለሚገባዉ የፍኖተ ካርታ ዝግጅት መንግስት የበኩሉን እንደሚወጣ ገልፀዋል፡፡የሊድ አሲድ በአለም አቀፍ ደረጃ 977 ቢሊየን ዶላር በማሳጣት ተፅዕኖ እንደሚያደርስ ጥናቶች ያሳያሉ፡፡ በአፍሪካም 134.7 ቢሊየን ዶላር የሚገመት ጉዳት ማድረሱንና ይህም በአህጉሩ 4 በመቶ ለሚሆነዉ የምርት መቀነስ ምክኒያት መሆኑ ተመልክቷል፡፡ይህ አሲድ በኢትዮጵያም 4 በመቶ ሃገራዊ ምርት እንዲቀንስ የበኩሉን አስተዋጾ ማበርከቱ ተነግሯል፡፡ፍኖተ ካርታዉ በመጀመሪያ ዙር 1.1 ሚሊየን ዩሮ ከባለድርሻ አካላት ተመድቦለት ወደተግባር እንደሚገባ ተገለፀ፡፡በዉይይቱ ላይ የአዉሮፓ ህብረት፤ በሃይል አቅርቦት ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ባለሃብቶችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡ | https://waltainfo.com/am/23914/ |
c1bf7dd9cb763d1d5308fd24194ad98d | 14bb71eac3c86404534eae8ebb645af7 | ም/ቤቱ ባካሄደው 73ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ | ፖለቲካ | ም/ቤቱ ባካሄደው 73ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈምክር ቤት በቅድሚያ በማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር ተዘጋጅተው በቀረቡ ከፍተኛ ደረጃ የድንጋይ ከሰል ማዕድን እና አነስተኛ ደረጃ የክሮማይት ማዕድን ማምረት ፈቃድ ስምምነቶች ላይ የተወያየ ሲሆን፤ ስምምነቶቹ በህጉ መሰረት መሟላት የሚገባቸው ጉዳዮች ከተሟሉ በኋላ እንደተዘጋጁ ተገልጿል፡፡ምክር ቤቱም በቀረቡት የከፍተኛ እና የአነስተኛ ደረጃ የማዕድን ማምረቻ ፈቃድ ስምምነቶች ላይ ከተወያየ በኋላ በስራ ላይ እንዲውሉ መወሰኑ ተመልክቷል፡፡በመቀጠልም ምክር ቤቱ በሰው የመነገድና ሰውን በህገ ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በተዘጋጀ ረቂቅ አዋጅ ላይ ውይይት የተደረገበት ሲሆን፤ በዚህ ዙሪያ የሚደርሱ ወንጀሎች በዜጎች ላይ የከፋ ጉዳት እንዳያስከትሉ ጠቅላይ ዓቃቤ ህግ ወንጀሎቹን ለመከላከል የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ አዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ለውሳኔ አቅርቧል፡፡ምክር ቤቱም በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ በዝርዝር ከተወያየ በኋላ ማሻሻያዎችን በማዕከል ይፀድቅ ዘንድ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ ወስኗል፡፡እንዲሁም የማሪታይም ጉዳይ ባለስልጣን የተለያዩ የማሪታይም አገልግሎቶችን ለመስጠት የሚያወጣውን ወጪ ተመጣጣኝ በሆነ መልኩ የአገልግሎቱ ቀጥተኛ ተጠቃሚ የሆነው ተገልጋይ እንዲሸፍን ለማድረግ የሚያስችል የህግ መሰረት መኖሩ አስፈላጊ መሆኑን በመግለፅ፤ የገንዘብ ሚኒስቴር የአገልግሎት ክፍያውን ለመወሰን የሚያስችል ረቂቅ ደንብ አዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ ያቀረበ ሲሆን፤ ምክር ቤቱም ደንቡ ላይ ተወያይቶ በስራ ላይ እንዲውል መወሰኑን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ | https://waltainfo.com/am/31310/ |
31f897b3c77b7ac6e87e10d81f7a70fa | 222c77a2482855da801ae9f362f45559 | የኦሮሚያ ክልል ም/ፕሬዝዳንትና የእንግሊዝ የዓለም አቀፍ ልማት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዩኒሌቨር ኩባንያን ጎበኙ | ቢዝነስ | የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ የእንግሊዝ ዓለም አቀፍ ልማት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሎክ ሸርማ በኢስተርን እንደስትሪ ዞን የሚገኘውን የዩኒሌቨር ኩባንያን ጎብኝተዋል፡፡አቶ ሽመልስ አብዲሳና የብሪታኒያ የዓለም አቀፍ የልማት ትብብር ሚኒስትር አሎክ ሻርማ በኢንዱስትሪ ዞኑ ባደረጉት ጉብኝትም የዩኒሊቨር ኩባንያ ስራዎችን ተዘዋውረው መመልከታቸውን የኦሮሚያ ክልል የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታውቋል።ዓለም አቀፍ ተቋም የሆነው ዩኒሊቨር ኩባንያ በዱከም በሚገኘው ኢስተርን ኢንደስትሪያል ዞን ውስጥ ለምግብነት እና ለመዋብያነት የሚያገለግሎ ምርቶችን እያመረተ ለገበያ በማቅረብ ላይ ይገኛል።ኩባንያ ኢስተርን ኢንደስትሪያል ዞን ባለው ፋብሪካም ከዚህ ቀደም ክኖር የምግብ ማጣፈጫ፣ ላይፍ ቦይ የንፅህና መጠበቂያ ሳሙና እና ቫዝሊን ሎሽን እያመረተ ይገኛል። (ምንጭ:-የኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ0 | https://waltainfo.com/am/23912/ |
c62d22792111193c49d3c19d27c3af6a | 7c514a94a9050b17c85fce65ffe020d5 | የአዲሱ የትምህርት መዋቅር 6-2-4 በሚል ማሻሻያ መደረጉን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ | ሀገር አቀፍ ዜና | አዲሱ የትምህርት መዋቅር 6 ዓመት የአንደኛ ደረጃ፣ 2 ዓመት የመለስተኛ ትምህርት እንዲሁም 4 ዓመት የ2ኛ ደረጃ ትምህርት እንዲሆን መወሰኑን የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡የትምህርት ሚኒስትር ዶክተር ጥላዬ ጌቴ በዛሬው ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ከዚህ በፊት የነበረው የትምህርት ፖሊሲ የውጭ ናፋቂና ሀገር በቀል እውቀቶችን ከመስጠት አንፃር ውንነቶች እንዳሉ በመረዳት የትምህርት ስርዓቱ የሃገሪቱን አንድነት የሚያስቀጥል፣ ከማህበረሰቡና ከተማሪው ጋር የተጣጣመ እንዲሁም ሃገር በቀል እውቀቶችን መሰረት ባደረገ መልኩ እንደሚሰጥ ተናግረዋል፡፡ሚኒስትሩ በመግለጫቸው አዲሱ የትምህርት መዋቅር በሶስት ክፍሎች ተመድቦ እንደሚሰራ ጠቅሰው፥ 6 ዓመት የአንደኛ ደረጃ ትምህርት፣ 2 ዓመት የመለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እንዲሁም 4 ዓመት ደግሞ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት እንዲሆን ተወስኗል ብለዋል።ተማሪዎች 6ኛ ክፍልን ሲያጠናቅቁ ክልላዊ ፈተናን የሚፈተኑ ሲሆን፥ ከዚህ በፊት ክልላዊ ፈተና የነበረው 8ኛ ክፍል ደግሞ ሃገራዊ ፈተና ይሆናልም ተብሏል።ከዚህ ጋር ተያይዞ ከዚህ በፊት በግል ዘርፍ ተይዞ የቆየው የቅድመ መደበኛ ትምህርት (የህጻናት ማቆያን ጨምሮ እስከ ኬጂ) በግልና በመንግስት እንዲያዝ ይደረጋል ነው የተባለው፡፡ከዚህ ቀደም ሲሰጥ የቆየው የ10ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና አይኖርም የተባለ ሲሆን፥ የ12ኛ ክፍል ፈተና ለከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ሊሆንም ላይሆንም እንደሚችል ተጠቁሟል። በተጨማሪም የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠናዎች ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ትምህርታቸውን ከጨረሱ በኋላ እንደሚጀምሩ ተገልጿል።በዚህም ተማሪዎች በቴክኒክና ሙያ ትምህርት መርሃ ግብር ከደረጃ 1 እስከ ደረጃ 8 (እስከ ሶስተኛ ዲግሪ) ደረጃ ድረስ መማር እንደሚችሉም በመግለጫው ወቅት ተነስቷል።የመምህራን ድልድልን በተመለከተም መምህራኑ ያላቸውን የትምህርት ደረጃ መሰረት ባደረገ መልኩ ይተገበራልም ነው የተባለው።ለአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው መምህራን፣ ለሁለተኛ ደረጃ ደግሞ ሁለተኛ ዲግሪ (ማስተርስ) እንዲሁም ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሁለተኛ ዲግሪና ከዚያ በላይ ያላቸው መምህራን የሚመደቡ ይሆናል።ፍኖተ ካርታው ከ3 እስከ 5 አመታት የሚፈጅ በሆንም መሰረታዊ ተብሎ የተለዩ ጉዳዮች በቀጣይ አንድ ወር በመጨርስ ወደ ትምህርት ማዕቀፉ በእቅድ ደረጃ እንዲገባ ይደረጋል በ2012 አጠቃላይ ስራው አልቆ በ2013 ወደ ትግበራ ይገባል፡፡ፍኖተ ካርታው ከትምህርት ጋር በተያያዘ የሚነሱ ቅሬታዎችንና ያልተካተቱ ጠቃሚ ጉዳዮች ከማከተቱም በሻገር ትውልዱን ኢትዮጵያዊ አውቀት እንዲኖረው ያደርጋል ተብሎም ይታሰባል፡፡ለሀያ አራት ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ እንዲሁም እስትራቴጂ ያመጣቸው በጎ ለውጦች ቢበዙም ዘመኑን ያላማከለ እንዲሁም ከፍተቶች ያሉበት በመሆኑ ከ2007 ዓ.ም ጀምሮ በትምህርትና ስልጠናው ፍኖተ ካርታ ሲዘጋጅ ቆይቷል፡፡ፍኖተ ካርታውን የሚመለከታቸው አካላት ካዘጋጁት በኋላ ከአምስት አመት በፊት ለህዝብ ይፋ ሆኖ ምክክር ተደረጎበታል፡፡ከምክክሩና በኋላም ከ357 በላይ ቢሻሻሉ የተባሉ የመፍትሔ ሀሳቦች የተሰበሰቡ ሲሆን፣ በዋናነት 36ቱ መሰረታዊ ሆነው ተገኝተዋል፡፡ ከእነዚህም ባሻገር በትምህርትና ስልጠናው ፍኖተ ካርታ ከተቀመጡት 37 የመፍትሄ አቅጣጫዎች መካከል ከቀጣዩ የትምህርት ዘመን ጀምሮ በተመረጡት 13 የርብርብ መስኮች ላይ በትኩረት እንደሚሰራ የትምህርት ሚኒስቴሩ ዶ/ር ጥላዬ ጌቴ ገልፀዋል።የትምህርት ሚኒስትሩ መግለጫቸው ከቀጣዩ የትምህርት ዘመን ጀምሮ መንግስት በመልካም እሴት፣ ስነ ምግባርና በብቃት የታነጸ ዜጋን ለማፍራት እንደሚሰራ ተናግረዋል። | https://waltainfo.com/am/32664/ |
89bdb5d082c7a14820878f39fa1633b7 | 7a97772a530923523dee5ff782a0fb29 | ፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ የስራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን የአየርላንድ አምባሳደር ሚስ ሶንጃ ሃይላንድን አሰናበቱ | ፖለቲካ | ፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ የስራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን የአየርላንድ አምባሳደር ሚስ ሶንጃ ሃይላንድን አሰናበቱ፡፡አምባሳደሯ ባለፉት ሁለት ዓመታት ቆይታቸው በኢትዮጵያና በአየርላንድ መካከል የነበረው ግንኙነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ላደረጉት አሳተዋፅኦ ፕሬዝዳንቷ አመስግነዋል፡፡ በቀጣይ ለሚኖረው ግንኙነትም በተግባር ካዩት እውነታ ተነስተው በኢትዮጵያ ያለውን የሀገር ግንባታ እንቅስቃሴ እንዲደግፉ ጠይቀዋል፡፡ተሰናባቿ የአይርላንድ አምባሳደር ሚስ ሶንጃ ሃይላንድ በበኩላቸው፣ በቆይታቸው በኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት ለተደረገላቸው ሁለንተናዊ ድጋፍ አመስግነው በጤና፣ በትምህርት፣ በኢንቨስትመንትና ሌሎች ዓለም አቀፍ የጋራ ጉዳዮች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩላቸውን ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገብተዋል፡፡ መረጃው የፕሬዝዳንት ጽጽቤት ነው፡፡ | https://waltainfo.com/am/31303/ |
cd33325a6d8dfd6525f7ab1962b1b628 | 5a714a6d2038a0f972df06caf787fbd8 | ሱዳን ለሦስት ዓመታት ለሚቆየው የሽግግር መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር ሾመች | ፖለቲካ | ሱዳን ለሦስት ዓመታት ለሚቆየው የሽግግር መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር ሾመች።አዲስ የተሾሙት ጠቅላይ ሚንስትር አብደላ ሃምዶክ የሽግግር መንግሥቱ መሪ በመሆን ቃለ መሃላ የፈፀሙ ሲሆን፣ በቃለ መሃላቸው በአገሪቱ ያለውን ሰላም ማረጋገጥ እና ለምጣኔ ሐብታዊ ቀውሶች እልባት መስጠት ቅድሚያ የሚሰጡት ጉዳይ እንደሆነ ገልፀዋል።ሌተናንት ጄነራል አብደል ፈታህ አብደልራህማን ቡርሃን ለሉዓላዊ ምክርቤቱ መሪ ሆነው መምራት ከጀመሩ በኋላ የተሾሙት ጠቅላይ ሚንስትሩ እስከ ቀጣዩ የአገሪቷ ምርጫ ድረስ እንደሚያስተዳድሩ ተገልጿል።የሉዓላዊ ምክር ቤቱና ሃምዶክ በቃለ መሃላ ሥነስርዓቱ ላይ ሱዳን ኦማር አል በሽር ሥልጣን በኋላ ከወታደራዊ አገዛዝ ሥርዓት የተላቀቀችበት የመጀመሪያው ጊዜ ብለውታል።ተቃዋሚ ፓርቲዎችም በበኩላቸው አሁን የተመሰረተው መንግሥት በአገሪቷ የነበረውን የወታደራዊ አገዛዝ ሥርዓት እንዲያከትም ያደርገዋል በማለት ተስፋ ሰንቀዋል።ጠቅላይ ሚንስትር ሃምዶክ ከአውሮፓዊያኑ 2011 ጀምሮ በተባበሩት መንግሥታት ከፍተኛ የምጣኔ ሐብት ባለሙያ ሆነው አገልግለዋል።መንግሥት ቅድሚያ ሰጥቶ ከሚሰራቸው ተግባራት መካከል፤ ጦርነትን ማስቆም፣ ዘላቂነት ያለው ሰላም መገንባት፣ የምጣኔ ሐብት ቀውስን መፍታት እና ሚዛናዊነቱን የጠበቀ የውጭ ፖሊሲ መገንባት እንደሆኑ ሃምዶክ ለሮይተርስ ዜና ወኪል አስታውቀዋል።ባለፈው ዓመት ሃምዶክ የአገሪቷ የገንዘብ ሚኒስቴር እንዲሆኑ ከሥልጣን በተወገዱት ፕሬዚዳንት ኦማር አልበሽር የታጩ ሲሆን ጥያቄው ሳይቀበሉት መቅረታቸውን ኤ ኤፍ ፒ የዜና ወኪል ዘግቧል።በሱዳን የተፈጠረው ቀውስ የጀመረው ባለፈው ዓመት መጨረሻ አካባቢ ሲሆን አገሪቷን ለ30 ዓመታት ያስተዳደሩት ኦማር አል በሽር ከሥልጣን እንዲወርዱ በመጠየቅ ነበር።የሲቪል መንግሥት እንሻለን የሚሉ የአገሪቷ ዜጎች ለወራት ተቃውሟቸውን ያሰሙ ሲሆን በእነዚህ ጊዜያትም የበርካቶች ሕይወት ማለፉ ይታወሳል ሲል የዘገበው ቢቢሲ ነው። | https://waltainfo.com/am/33327/ |
04f0c276df0fd8e0d9d084c68f99609f | 9bca2fb52da29a04078ce44f5e4d4529 | ቻይና እና ሩሲያ የተመድ ጸጥታው ምክር ቤት በአሜሪካ ሚሳኤል ሙከራ ዙሪያ ስብሰባ እንዲጠራ ጠየቁ | ፖለቲካ | ቻይና እና ሩሲያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጸጥታው ምክር ቤት በአሜሪካ ሚሳኤል ሙከራ ዙሪያ ስብሰባ እንዲጠራ መጠየቃቸው ተገለጸ፡፡
አሜሪካ ባሳላፍነው ሰኞ የመካከለኛ ርቀት ሚሳኤሎችን የማልማትና የመጠቀም ፍላጎት እንዳላት መግለጫ መስጠቷ ይታወሳል፡፡
ቤጅንግ እና ሞስኮ ጉዳዩ ለዓለም አቀፉ ሰላምና መረጋጋት ስጋት በመሆኑ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት በጉዳዩ ላይ እንዲመክር ጥያቄ ማቅረባቸው ተገልጿል፡፡
በሳለፍነው ሰኞ የአሜሪካ መከላከያ በሰጠው መግለጫ የመካከለኛ ርቀት ሚሳኤል ሙከራ ማድረጉን አስታውቋል፡፡
ሙከራው ከ500 ኪሎ ሜትር ርቀት በላይ ኢላማውን መምታት መቻሉም ነው በመግለጫው የተመላከተው፡፡
የአሜሪካ የመከላከያ ሚኒስትር ማርክ ኢስፐር ለፎክስ ኒውስ በሰጡት ቃለ ምልልስም የሚሳኤል ሙከራው ለቻይና እና ሩሲያ ብሎም ለሰሜን ኮሪያ መልዕክት የሚያስተላልፍ ነው ማለታቸውን ዘገባው አስታውሷል፡፡
አሜሪካ በቀዝቃዛው ጦርነት ከተፈራረመችው የመካከለኛው ርቀት ሚሳኤል መጠቀም ከሚከለክለው ስምምነት መውጣቷን ይፋ ካደረገች በኋላ ሙከራው የመጀመሪያው መሆኑምን ዘገባው ያስረዳል፡፡ (ምንጭ፡-አልጀዚራ) | https://waltainfo.com/am/33988/ |
4c3d480b95c90f5fadf1051f7a8e3ffb | 2dd63f1560f4437a32cfcf106baff03f | ወ/ሮ ሂሩት ዘመነ አዲስ አበባ ከሚኖሩ የኢጋድ አባል አገራት አምባሳደሮች ጋር ተወያዩ | ፖለቲካ | የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሂሩት ዘመነ ዛሬ ነሀሴ 14 ቀን 2011 ዓም አዲስ አበባ ከሚኖሩ የኢጋድ አባል አገራት አምባሳደሮች ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል።የኢጋድ አባል አገራት አምባሳደሮች በቀጠናው ሰላምን በማስፈን ዘላቂ ልማት ለማስመዝገብ በሚደረገው እንቅሰቃሴ የሚያደርጉትን ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉ ሚኒስትር ዴኤታዋ አሳስበዋል።አምባሳደሮቹ በበኩላቸዉ በቀጠናው በተለይም በደቡብ ሱዳን ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፈን እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ ከግብ እንዲደርስ የሚያደርጉትን ጥረት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል፡፡ሚኒስትር ዴኤታዋ ውይይቱ በዋናነት የደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት ፈራሚ አካላት በነገው እለት በአዲስ አበባ ከሚያደርጉት ስብሰባ ጋር በተያያዘ ያለውን ቅድመ ዝግጅት ስራ በተመለከተ መረጃ መለዋወጥ ላይ ያተኮረ መሆኑን ነው የገለፁት።በውይይቱ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የሱዳን፣ የሶማሊያ፣ የጅቡቲ፣ የኬንያ እና የኡጋንዳ አምባሳደሮች መሣተፋቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ፅ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያሳያል። | https://waltainfo.com/am/31300/ |
298135669aeec01c5a9fc5cffc55db79 | fdb3957196db739cf771df7df9a9b579 | በአቶ አብዲ መሐመድ ዑመር የክስ መዝገብ የተከሰሱ ሰዎች ጉዳያቸው በሌሉበት እንዲታይ ተወሰነ | ፖለቲካ | የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት 4ኛ የወንጀል ችሎት በቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አብዲ መሐመድ ዑመር የክስ መዝገብ ተጠቅሰው ያልተገኙ 11 ተከሳሾች ጉዳያቸው በሌሉበት እንዲታይ ብይን ሰጠ።በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጥሪ ተደርጎላቸው ሳይቀርቡ በሌሉበት ጉዳያቸው እንዲታይ ከተበየነባቸው ተከሳሾች የክልሉ ልዩ ኃይል አዛዥ የነበሩት ጄኔራል አብዱራህማን አብዱላሂ፣ ሻለቃ ሼክ ሙክታር እና ሄጎ የተሰኘውን የአመፅ ቡድንን በምክትልነት ሲመሩ ነበር የተባሉት የወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ መሐመድ አህመድ ይገኙበታል።ችሎቱ ከነዚህ በተጨማሪ በክስ መዝገቡ የመኖሪያ አድራሻ ተፈልገው ያልተገኙ ሌሎች 7 ተከሳሾችም እንዲቀርቡ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጥሪ እንዲደርሷቸው ትዕዛዝ ሰጥቷል።በተሻሻለው ክስ ላይ 1ኛው ተከሳሽ የቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አብዲ ዑመር ከጠበቆች ጋር ተማክሬ የክስ መቃወሚያ አቀርላሁ ብለዋል።ጉዳያቸውን በአካል እየተከታተሉ ከሚገኙ 14 ተከሳሾች የተፋጠነ ፍትሕ ተጠቃሚ መሆን አልቻልንም፤ ጉዳያችንን ፍርድ ቤቱ በትኩረት ይመልከትልን በማለት አመልክተዋል።ችሎቱ የክስ መዝገቡ በጋራ የሚታይ በመሆኑ የተከሳሾች የግል አቤቱታ የክስ መቃወሚያ እና ከሌሎች መሰል ጉዳዮች ጋር በተያያዘ የተጠቀሰውን ጊዜ ሊቆጠር ችሏል ብሏል፡፡ | https://waltainfo.com/am/31296/ |
4df5c744c59e8be7206c45b89262410a | 982a1599277e8a4eb68e6e1495574875 | የመቐለ ከተማ ሴቶች የአሸንዳ በዓልን ምክንያት በማድረግ ችግኝ ተከሉ | ሀገር አቀፍ ዜና | የመቐለ ከተማ ሴቶች የአሸንዳ በዓልን ምክንያት በማድረግ ዛሬ በሰማዕታት ሐውልት ግቢ ችግኝ ተከሉ።
ሴቶቹ ችግኞቹን የተከሉት በዓሉን ከማድመቅ በተጨማሪ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የአረንጓዴ ልማት ፕሮግራምን ለማሳካት እንደሆነም ተገልጿል።ሴቶቹ ችግኞቹን ተንከባክበው ለማጽደቅ እንደሚሰሩም ተገልጿል።በተከላው ከተሳተፉት ሴቶች መካከል ወይዘሮ ፅጌ አብርሃ የሴቶች የነጻነት መገለጫ የሆነውን በዓል ለማድመቅና መነሳሳትን ለመፍጠር ያስችላል ብለዋል።እንዲሁም የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር የጀመሩትን የአረንጓዴ ልማት ፕሮግራም ከዳር እንደሚያደርሱ ተናግረዋል።ሌላዋ አስተያየት ሰጪ ኮማንደር አበባ ነጋሽ በበኩላቸው በችግኝ ተከላው የተሳተፉት በአረንጓዴ ልማት መርሐ ግብር ስኬት ተሳትፏቸውን ለማረጋገጥ መሆኑን ገልጸዋል።ሴቶች በሁሉም መስኮች ከተሰማሩ የማያሳኩት ሥራ እንደሌለ ለማሳየትና በዓሉን ለማድመቅ ነው ብለዋል።የትግራይ ክልል ሴቶች ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር የትምወርቅ ገብረመስቀል እንዳሉትም ችግኝ ተከላው የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ለአረንጓዴ ልማት ፕሮግራም ስኬት የነበራቸውን ታላቅ አስተዋጽኦ ለማስታወስ የተዘጋጀ ነው። | https://waltainfo.com/am/32662/ |
03f59ab317ffe5a3adf97c5f01ae6132 | a65963efea008799304d0a58c35de08b | ኮሚሽኑ የተሰጠውን ተልእኮ በብቃት ማስፈም እንዲችል አዋጅና ደንቦችን የሚያሻሽል ረቂቅ አዘጋጀ | ሀገር አቀፍ ዜና | የፌዴራል የስነምግባርና የጸረ ሙስና ኮሚሽን የተሰጠውን ተልእኮ በብቃት ማስፈም እንዲችል አዋጅና ደንቦችን የሚያሻሽል ረቂቅ አዘጋጅቷል፡፡አዲስ በመዘጋጀት ላይ ካለው የከፍተኛ መንግሥት ባለስልጣናት የስነ ምግባር ደንብ በተጨማሪ በሀብት ማሳወቅና ማስመዝገቢያ እንዲሁም የስነምግባር መኮንኖች አሰራርን ለመወሰን በወጣው ደንብ ላይ ረቂቅ ማሻሻያዎች መዘጋጀታቸውን ኮሚሽኑ ገልጿል።ኮሚሽኑ የባለፈውና የቀጣይ በጀት አመቱን እቅድና አፈጻጸም አስመልክቶ በጋራ ከሚሰሩ የጸረሙስና ጥምረት አካላት ጋር ውይይት አድርጓል፡፡በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሀብት ማስመዝገብ ላይ ያለው አፈጻጸም ደካማ መሆኑ በመድረኩ ተነስቶ ተገምግሟል።ኮሚሽኑ በስሩ የምርመራና አቃቤ ህግ ስራን አቀናጅቶ አለመስራቱ ውጤታማ እንዳይሆን አድርጎታል ተብሏል፡፡በሌላ በኩል ሙስና በሃገሪቱ ያለበትን ደረጃ ለማወቅ ያስችላል ተብሎ ተስፋ የተጣለበት 3ኛው ሃገር አቀፍ የሙስና ቅኝት ጥናት መጀመሩን ኮሚሽኑ አስታውቋል።ከዚህ በተጨማሪም ሀገራዊ የፀረ ሙስና ፖሊሲና ስትራቴጂ የዝግጅት ሂደት መጀመሩንም ነው ኮሚሽኑ የገለፀው።የስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አየልኝ ሙሉዓለም እንዳሉት የኮሚሽኑ ማቋቋሚያ አዋጅን ጨምሮ ተቋማዊ የውስጥ አሠራርን የተመለከቱ መመሪያዎች ተዘጋጅተው ውይይት እየተደረገባቸው ነው።ብልሹ ስነ ምግባርንና ሙስናን የመዋጋቱ ስራ በተቋማዊ አደረጃጀት ብቻ የሚሳካ ባለመሆኑ የህብረተሰቡንና የሚመለከታቸው አካላትን የተቀናጀ ተሳትፎ ለማሳደግ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡ | https://waltainfo.com/am/32663/ |
62d6584434ce1456f93982c8c59bcdfe | 242f77da3bfe3a0c0655cc4e8325e30c | የግብርና ሚኒስቴር ከቻይና አቻው 4 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የግብርና መሳሪያዎች ተበረከቱለት | ቢዝነስ | የቻይናው ግብርናና ገጠር ጉዳዮች ሚኒስቴር ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የግብርና መሳሪያዎችና ቁሳቁስ ለግብርና ሚኒስቴር አበርክቷል፡፡ርክክቡ ሲካሄድ የቻይናው አምባሳደር ሚስተር ታን ጄይን እንዲሁም በኢትዮጵያ በኩል የግብርናው ሚኒስትር አቶ ዑመር ሁሴን ተገኝተዋል፡፡ርክክብ ከተደረገባቸው መሳሪያዎች መካል ትራክተር፣ ዘር መዝሪያ ማሽን፣ የአፈር መከስከሻ ማሽን፣ የሩዝና ስንዴ መውቂያ ማሽን፣ የጥጥ ዘር መፈልፈያ፣ ጀነሬተሮች እና የቢሮ መገልገያ እቃዎች ይገኙባቸዋል፡፡መሳሪያዎቹ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ለማስተዋወቅና ግብርናን ለማዘመን ከፍተኛ ሚና ያላቸው መሆኑ ተገልጿል፡፡የቻይና መንግስት ለኢትዮጵያ ግብርና እድገት እያደረገ ላለው ድጋፍ የግብርናው ሚኒስትር አቶ ዑመር ሁሴን ከፍተኛ ምስጋና ማቅረባቸውን ከግብርና ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ | https://waltainfo.com/am/23911/ |
7c66cbe769e1cb45c356e261c0d563e5 | 459d7c28add12f1b09727b3888e6d82f | ኢትዮጵያና አሜሪካ የሕግ ማስከበር እና የወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ስምምነት ተፈራረሙ | ፖለቲካ | የሰላም ሚኒስትሯ ወ/ሮ ሙፈሪሀት ካሚልና በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ማይክል ሬይኖር መንግሥቶቻቸውን ወክለው የሕግ ማስከበር እና የወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ስምምነት ተፈራርመዋል።ስምምነቱም ለሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱና ለፌደራል ፖሊስ እንዲሁም ለፍትህና ሕግ ማስከበር አካላት ድጋፍ በመስጠት የሕግ ማስፈጸም እና የፍትሕ ዘርፉን ለማሻሻል ያለመ መሆኑን ከሰላም ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። | https://waltainfo.com/am/31298/ |
c44f5c7231468258f3743ebf4e82b982 | d69904632eba03cb6c2c7b324b02e290 | ዛምቢያ ቀረጥ ያልከፈሉ ተሽከርካሪዎችን በድሮን እያደነች ነው ተባለ | ቢዝነስ | የዛምቢያ ግብር ባለሥልጣናት ቀረጥ ያልከፈሉ ተሽከርካሪዎችን በድሮን እያደነች ነው ተባለ፡፡ባለሥልጣናቱ ቀረጥ ሳይከፍሉ እቃዎችን የሚያዘዋውሩ ከባድ መኪናዎችን ለመቆጣጠር ድሮኖችን መጠቀም መጀመራቸው ነው የተገለጸው፡፡ባሳለፍነው ቅዳሜና እሁድ የዛምቢያ ገቢዎች ባለሥልጣን በድሮኖች በመታገዝ ከዋናው መንገድ በመውጣት ተደብቀው የነበሩ ሰባት ተሽከርካሪዎች መያዛቸውን አስታውቀዋል።"ድሮኖቹ የፍተሻ ሠራተኞች በማይደርሱባቸው እንዲሁም አደጋ ባለባቸውና ጥንቃቄን በሚጠይቁ ቦታዎች ድረስ በመግባት አሰሳ ያደርጋሉ" ሲሉ የዛምቢያ ገቢዎች ባለስልጣን የኮሚዩኒኬሽን ሥራ አስኪያጅ ቶፕሲይ ሲካሊንዳ ለቢቢሲ ተናግረዋል።በዚህ ሰባት ተሽከርካሪዎች በቁጥጥር ሥር በዋሉበት ፍተሻ ድሮኖቹ 'ካፒሪ ስርነጅ' በተባለ መንገድ በመግባት ማሰስ የጀመሩ ሲሆን፣ ዋናው የተሽከርካሪ መንገድ ባዶ ሆኖ አግኝተውታል፤ ከዚያም ከዋናው መስመር 14 ኪሎሜትር በሚርቅ ጥሻ ውስጥ አመላክተዋል።በዛምቢያ ወደ ደቡብ አቅጣጫ የሚጓዙ ተሽከርካሪዎች በአብዛኛው ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ማላዊ፣ ወይም ታንዛኒያ የሚመጡ ናቸው።ኃላፊው ሲካሊንዳ እንዳስታወቁት አብዛኞቹ ተሽከርካሪዎች በጣም በርካታ እቃዎችን ይጭኑና ወደ ፍተሻ ጣቢያው ሲቃረቡ በትንንሽ መኪና ቀንሰው ይጭናሉ ይህም ባለሙያዎቹ ጥርጣሬ ውስጥ እንዳይገቡ ምክንያት ሆኗል።የዛምቢያ የገቢዎች መሥሪያ ቤት ቴክኖሎጂን በመጠቀም ገቢውን ለማሳደግ ተስፋ እንዳለው የቀረጥ ባለሥልጣናት ጨምረው ተናግረዋል። (ምንጭ፡-ቢቢሲ) | https://waltainfo.com/am/32902/ |
4d017611d6e72850179aca489eb27e6c | 471016ee9772f625f38647278297913d | የጦር መሳሪያ በተሽከርካሪ ሲያዘዋውር የተያዘው ተከሳሽ በ2 ዓመት ጽኑ እስራትና በገንዘብ ተቀጣ | ሀገር አቀፍ ዜና | ተከሳሽ አብዱራህማን ዩኑስ ከሚመከለተው የመንግስት ፈቃድ ውጪ ወደ ሀገር እንዳይገቡ ገደብ የተደረገባቸው የጦር መሳሪያዎችን በተሸከርካሪ ደብቆ ወደ ሀገር ሊያስገባ ሲል ተይዞ ዐቃቤ ሕግ በመሰረተው ክስ በእስራት ተቀጥቷል፡፡ተከሳሽ 53 ቱርክ ስሪት ሽጉጦችንና 35 ሺህ 766 ጥይቶችን የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-A50931 አ.አ በሆነ ላንድክሩዘር መኪና ደብቆ ወደ ሀገር ሊያስገባ ሲሞከር በተደረገው ክትትል በአዲስ አበባ የካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ክልል ልዩ ቦታው ጣፎ አደባባይ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በተሸከርካሪው ላይ በተደረገ ፍተሻ ተይዟል፡፡ተከሳሽ ክሱ በችሎት ተነቦለት እንዲረዳ ከተደረገ በኃላ ድርጊቱን ክዶ በመከራከሩ ዐቃቤ ሕግ እንደ ክሱ አቀራረብ ምስክሮች አሰምቷል፡፡ፍርድ ቤቱም መዝገቡን መርምሮ ተከሳሽ ሽጉጥና ጥይት በመኪና ደብቆ በፍተሻ ስለመያዙ በመረጋገጡና መከላከልም ባለመቻሉ በተከሰሰበት ድንጋጌ ጥፋተኛ መሆኑን በይኗል፡፡የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 8ኛ ወንጀል ችሎት መዝገቡን መርምሮ የግራ ቀኙን የቅጣት አስተያየት በመመልከት ተከሳሽ በ2 ዓመት ጽኑ እስራት እና በ5 ሺህ ብር መቀጮ እንዲቀጣ ወስኗል፡፡ምንጭ፡- ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ | https://waltainfo.com/am/32661/ |
bfaddc6489926597107a5a16b584bf5a | f094d0f1a768678f53f0869301d8de4e | ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከኳታር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ተወያዩ | ፖለቲካ | ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከኳታር ምክትል ጠ/ሚርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ተወያዩጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ ከኳታር ምክትል ጠ/ሚርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሼክ መሐመድ ቢን አብዱልራሕማን ቢን ጃሲም አል ታኒ ጋር ተወያዩ፡፡ሁለቱ ወገኖች ጠ/ሚሩ በመጋቢት ወር 2011 በኳታር ይፋዊ ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት የተጀምረውን ውይይት በማስቀጠል በቁልፍ የሁለትዮሽ ትብብር ጉዳዮች ላይ ተነጋግረዋል፡፡ሼክ መሐመድ ከዚህ ቀደም ስምምነት ላይ የተደረሰባቸው የኢንቨስትመንት ዘርፎች በተለይም በሆቴል፣ ስኳር ፋብሪካ፣ በቱሪዝም ልማትና አዳዲስ የኩላሊት ሕክምና ማዕከላት ግንባታን ለማስጀመር ዝግጁነት እንዳለ መግለጻቸውን ከጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያስረዳል። | https://waltainfo.com/am/31297/ |
d121ba09b55bfbdf66809442b0b8192b | fbdb68d7cc006275f5737ccefddba7d9 | በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የለውጥ ስራዎችን ማስጀመሪያ መድረክ እየተካሄደ ነው | ሀገር አቀፍ ዜና | በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የለውጥ ስራዎችን ማስጀመሪያ መድረክ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ሂሩት ወ/ማርያም በተገኙበት በአዲስ አበባ ሸራተን ሆቴል እየተካሄደ ነው፡፡የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በሀገራችን የመጀመሪያውን የትምህርትና ስልጠና ፍኖተ ካርታ ከሶስት አመታት በላይ ከፈጀ የዝግጅት ምዕራፍ በኋላ ከ 2012 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ያደርጋል፡፡ፍኖተ ካርታው እስከ 2022 ዓ.ም የሚተገበር ሲሆን፣ 2012 ዓ.ም የመጀመሪያው የትግበራ አመት ይሆናል፡፡ ፍኖተ ካርታው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ያሉ ችግሮችን ለይቶ መፍትሄዎችን አስቀምጧል፡፡የስርዐት ትምህርት አዘገጃጀት ይዘትና ትግበራ ችግር፣ የዩኒቨርሲቲዎች በተልእኮ አለመለየት፣ የትምህርት አደረጃጀት ችግር እና ሌሎችም አራት ችግሮች የተለዩ ሲሆን፣ በእነዚህ ችግሮች ምክንያትም የስነምግባርና የሞራል ውድቀት፣ ስርአት አልበኝነትና ምክንያታዊ አለመሆን፣ የስራ ጠባቂነትና ጥገኝነትን የመሳሰሉ ችግሮች በተማሪዎች ዘንድ ተስተውለዋል ተብሏል፡፡የአንደኛ አመት ተማሪዎችን የታሪክ፣ ጂኦግራፊና አንትሮፖሎጂ፣ የኮምፒውቴሽናል ክህሎት፣ የስነምግባር፣ የቋንቋ፣ የስነ ተግባቦት፣ ምክንያታዊነት፣ ቴክኖሎጂና አለምአቀፋዊ እውቀት ሊያስጨብጡ የሚችሉ ትምህርቶችን መስጠት፣ ዩኒቨርሲቲዎችን እንደ ተልዕኳቸው ትኩረት ማደራጀት ማለትም የምርምር፣ የአፕላይድ ሳይንስ እና ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲዎች አድርጎ ማደራጀት እና የዩኒቨርሲቲ ቆይታን አራት አመት እንዲሆን ማድረግ ለምህንድስና አምስት ለህክምና ስድስት አመት ለማስተርስ ዲግሪ ሁለት አመት እንዲሁም ለፒኤችዲ ዲግሪ ደግሞ አራት አመት ማድረግ ችግሮችን ከስር መሰረታቸው ለመፍታት በፍኖተ ካርታው የተቀመጡ የመፍትሄ ምክረ ሀሳቦች ናቸው ተብሏል፡፡ መረጃው የፕሬስ ኤጄንሲ ነው፡፡ | https://waltainfo.com/am/32658/ |
ea8bc39e6fa56245ad7a594943fb9d8f | e72410a74b877de7766614e73221e56a | በምዕራብ ኢትዮጵያ የሚገኙ ክልሎች የጋራ መድረክ እየተካሄደ ነው | ሀገር አቀፍ ዜና | የምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ መድረክ በአሶሳ እየተካሄደ ነው::የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ የአማራ፣የኦሮሚያና የጋምቤላ ክልሎች የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ መድረክ ሲሆን፤ የክልሎቹ አፈ ጉባኤዎች፣ የቢሮዎች ሀላፊዎች፣ እንዲሁም የአራቱ ክልሎች ተጎራባች ዞኖችና ወረዳዎች አመራሮች በመታደም ላይ ናቸው፡፡የፌዴሬሽን ምክር ቤት ከኦሮሚያ ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች የጋራ የሰላምና ልማት ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ጋር በትብብር መድረኩን አዘጋጅተዋል፡፡ፕሬስ ድርጅት እንደዘገበው የምዕራብ ኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ህዝቦች ሁለንተናዊ ሁኔታ፤ ፌዴራሊዝምና የሰላም እሴት ግንባታ፤ የቤኒሻንጉል ጉሙዝና የኦሮሚያ ዞኖችና ወረዳዎች የጋራ ልማትና ሰላም ስምምነት ይፈረማል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ | https://waltainfo.com/am/32659/ |
3146314a35ba1728df613058493da64e | 2f719718200252d4a70ce08dbde2f454 | በነብርጋዴር ጄነራል ተፈራ ማሞ የክስ መዝገብ ላይ ብይን ለመስጠት ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠ | ፖለቲካ | በእነ ብርጋዴር ጄኔራል ተፈራ ማሞ የክስ መዝገብ ላይ የምርመራ ቡድኑ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ በጠየቀው ይግባኝ ላይ የባሕር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውሳኔ ለመስጠት ለነሐሴ 16/2011 አ.ም የጊዜ ቀጠሮ ሰጠ።በእነ ብርጋዴር ጄኔራል ተፈራ ማሞ የክስ መዝገብ ላይ ሐምሌ 29/ 2011 ዓ.ም በነበረው የጊዜ ቀጠሮ የባህር ዳር ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ፖሊስ የጠየቀውን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ውድቅ ማድረጉ ይታወሳል ። ይህን ተከትሎም የምርመራ ቡድኑ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው የባህር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤትን ዛሬ ጠይቋል።የምርመራ ቡድኑ “አዳዲስ ተከሳሾች ተይዘዋል። ቃል እየተቀበልን ነው። በድርጊቱ ዋና ተከሳሾች ካልተያዙ ክስ መመስረት አንችልም። በህክምና ላይ ያሉትን ምስክሮች ቃል የመቀበል ስራ እየተከናወነ ነው። በፌዴራል ከሚካሄደው ምርመራም ጋር የሚያያዙ ጉዳዮች አሉ። የቀዳሚ ምርመራ የሚሰሙ ብዙ ምስክሮች እያሉን የቀረቡት ጥቂቶቹ ናቸው” በሚሉ ምክንያቶች ተጨማሪ የይግባኝ ጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠይቋል።የተከሳሾቹ ጠበቆች በበኩላቸው የጊዜ ቀጠሮው ይግባኝ የሚቀርብበት እንዳልሆነ እና ለምርመራ የተሰጠው የጊዜ ቀጠሮ በቂ መሆኑን በመግለጽ ይግባኙን ተቃውመዋል።ከፍተኛ ፍርድ ቤቱም ግራ ቀኙን ካደመጠ በኋላ በይግባኝ ክርክሩ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ለነሐሴ 16/2011 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ቀጠሮ ሰጥቷል።(ዘገባው የአብመድ ነው) | https://waltainfo.com/am/31295/ |
82be198ac448fbed60ef19c3d03e8c59 | b51ef2a18a3b2c813acf7160a7066921 | የሱዳን ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች አምስት የሉዓላዊ ምክር ቤት አባላትን ሰየሙ | ፖለቲካ | የሱዳን ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች አምስት የሉዓላዊ ምክር ቤት አባላትን ሰየሙ፡፡አባላቱ ዛሬ ቃለ መሀላ እንደሚፈፅሙ የተገለጸ ሲሆን፣ ከመሃላው በፊት ሀገሪቷን እያስተዳደረ የሚገኘው ወታደራዊው መንግስት ከሲቪል ተወካዮች በሁለት በልጦ አባል መርጦ አዘጋጅቷል፡፡አባላቱም በምክር ቤቱ ውስጥ ከፍተኛ ስልጣን የሚኖራቸው ይሆናሉ ነው የተባለው፡፡ሱዳን ሰላም አጥታ ለበርካታ ወራት ስትታመስ ከቆየች በኋላ ለህዝቡ ጥያቄ የመጨረሻ እልባት መፍትሄ ሰጭ የተባለለት የስምምነት ደረጃ ላይ ተደርሷል፡፡የሀገሪቷ የአስተዳደር አካል ከወታደራዊው አገዛዝ ይልቅ ህዝባዊ አካል ሀገሪቱን ሊያስተዳድር ይገባል የሚል ሀሳብ በተቃዋሚ የፖለቲካ አመራሮች ሲመራና ሲራመድ እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡በዚህ ሀሳብ በገዥው ወታደራዊው መንግስት እና በህዝብ መካከል ከፍተኛ መተራመስ በመፈጠሩ ከ127 በላይ ሱዳናዊያንም ሞት እና ለባርካቶች አካላቸው ጉዳት ምክንያት ሆኗል፡፡ ሱዳን ሰላም እንድታገኝ እና በገዢው አካል መካከል ሰላም እንዲወርድ ኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ ሀገራት እንዲሁም የአፍሪካ ህብረት ጥረት ሲያደርጉም ቆይተዋል፡፡በስተመጨረሻም ሁለቱ አካላት ስምምነት ላይ ደርሰው ዛሬ መቋጫዉን ሊያገኝ ስልጣን ላይ ያለው ወታደራዊው መንግስት እና የሱዳን ተቃዋሚ የፖለቲካ አባላት የስልጣን ክፍፍል ሊያደርጉ የሉዓላዊ ምክር ቤት አባሎቻቸዉን መርጠው አዘጋጅተዋል፡፡ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች አምስት ወታደራዊው መንግስት ከሲቪሊያኑ በሁለት ከፍ ብሎ ሰባት በምክር ቤቱ ውስጥ ከፍተኛ ስልጣን የሚኖራቸዉን አባሎቻቸዉን መርጠዋል፡፡በዘመነ አልበሽር ሱዳን በከፍተኛ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ የሴቶች ተሳትፎ ያን ያህል ነበር፡፡ ከዚህ አካሄድ ለየት ባለ መልኩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመረጧቸው አባላቶቻቸው ውስጥ ሴቶችን አካተዋል ነው የተባለው፡፡ሁለቱ አካላት ሰልጣን መጋራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ቅዳሜ ስምምነት ላይ የደረሱ ሲሆን፣ ዛሬ ደግሞ የመጨረሻ መሃላ ሊፈፅሙ የምክር ቤቱ አባላቶቻቸዉን አዘጋጅተዋል፡፡አባላቶቹ በምክር ቤቱ ከፍተኛ ስልጣን የሚኖራቸው ቢሆንም ትልቁ ኃላፊነታቸው ለካቢኒው የሚሰሩ ነው የሚሆነው፡፡ ሱዳን አጥታ ለነበረው ሰላም እና ህዝቡ ሲያነሳ ለነበረው ጥያቄ መልስ የሚሰጥ ነው የተባለው ይህ ስምምነት ዛሬ ላይ በርካታ ሱዳናዊያን በካርቱም እና በሌሎች ከተሞች ጎዳና እንዲወጡ ምክኒያት ሆኗቸዋል፡፡ ደስታቸዉን ለመግለጽ እና የፊርማ ስምምነቱን ለማክበር ሲባል፡፡ሁለቱ አካላት ዛሬ የመጨረሻ ቃለ መሃላ የሚፈጽሙ ሲሆን፣ በስምምነታቸውም መሰረት ወታደራዊው ሽግግር መንግስት ለ21 ወራት ስልጣን ላይ የሚቆይ ሲሆን የሲቪሉ አካል ደግሞ ለሚቀጥሉት 18 ወራት ስልጣን በመጋራት በጋራ ሱዳንን ያስተዳድራሉ፡፡(ምንጭ፡-ሚድል ኢስት እና አልጄዚራ) | https://waltainfo.com/am/33325/ |
0ca9d275c446783afdaed2dcab7bf279 | 92ccac663eae894c8ca1df1cb8e60e3f | የከተማ አስተዳደሩ ም/ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማ በከተማዋ እየታደሱ የሚገኙ የመንግስት ትምህርት ቤቶችን ጎበኙ | ሀገር አቀፍ ዜና | የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማ በከተማ አስተዳደሩና በባለሀብቱ እየታደሱ የሚገኙ የመንግስት ትምህርት ቤቶችን ጎበኙ፡፡በከተማ አስተዳደሩ 488 የመንግስት ትምህርት ቤቶች እየታደሱ የሚገኙ ሲሆን፣ አሁን ወደ መጠናቀቅ ምዕራፍ ላይ ደርሰዋል ነው የተባለው፡፡የትምህርት ቤቶቹ እድሳት ለተሻለ መማር ማስተማር እንዲኖር ከማድረግ ባሻገር ለተማሪዎችም ሆነ ለአስተማሪዎች የትምህርት ፍላጎት ማደግ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማ ተናግረዋል፡፡ከእድሳት እና ጥገና ስራዎች በተጨማሪ የከተማ አስተዳደሩ በየትምህርት ቤቶቹ ቅጥር ጊቢ ውስጥ ለተማሪዎች የአረንጓዴ ቦታ እና ምቹ የመመገቢያ አዳራሾች በአዲስ መልክ የሚደራጁ ይሆናልም ነው የተባለው፡፡ምክትል ከንቲባው በጉብኝታቸው ወቅት በየትምህርት ቤቶቹ በዩኒቨርሲቲ መግቢያ ከፍተኛ ውጤት ካመጡ ተማሪዎች ጋርም ቆይታ አድርገዋል፡፡ከንቲባው በዛሬ ጉብኝታቸው በአስሩ ክፍለ ከተሞች የሚገኙ የመንግስት ትምህርት ቤቶች እድሳት ሂዴትን ይጎበኛሉ ተብሏል፡፡ | https://waltainfo.com/am/32657/ |
8620ab35fd6596430e56fc2ef49a9879 | 7dd49c46bfb74798ea2255933bbae3a2 | በካቡል ከተማ አንድ ሠርግ ላይ የፈነዳ ቦንብ 63 ሰዎችን ሲገድል 180 ሰዎችን አቁስሏል | ሀገር አቀፍ ዜና | በአፍጋኒስታን ዋና ከተማ ካቡል አንድ ሠርግ ላይ የፈነዳ ቦንብ 63 ሰዎችን ሲገድል 180 ሰዎችን አቁስሏል፡፡የዓይን እማኞች አንድ አጥፍቶ ጠፊ ቦንቡን ተሸክሞ መጥቶ እንዳፈነዳው የተናገሩት፡፡ቦንቡ የፈነዳው ቅዳሜ ምሽት 4፡40 ገደማ ሲሆን ሥፍራው ደግሞ የሺያ ሙስሊሞች የሚያዘውትሩት የካቡል ምዕራባዊ ክፍል ነው ተብሏል።ታሊባን 'እኔ እጄ የበለትም' ሲል አስተባብሏል። እስካሁን ለጥፋቱ ኃላፊነት የወሰደ ቡድን የለም። ራሳቸውን ከሱኒ ሙስሊሞች ጋር የሚያቆራኙት ታሊባን እና አይ ኤስ ከዚህ በፊት የሺያ ሙስሊሞች ላይ ጥቃት መፈፀማቸው ይታወሳል።የአፍጋኒስታን ሃገር ውስጥ ሚኒስትር አደጋው ከደረሰ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ የሟቾችን እና የተጎጂዎችን ቁጥር ይፋ አድርገዋል።ወንዶች እና ሴቶች ለየብቻ ሆነው የሚስተናገዱበት የአፍጋኒስታን የሠርግ ሥነ-ሥርዓት በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎች ይታደሙበታል።'አጋጣሚ ሆኖ ቦንቡ ሲፈነዳ እኔ ከሴቶች ጎራ ነበርኩ' የሚለው ሞሐመድ ፋርሃግ 'ከፍንዳታው በኋላ ሰዎች ሁላ እግሬ አውጭኝ እያሉ ሲወጡ ተመልክቻለሁ' ሲሉ ኤኤፍፒ ለተሰኘው የዜና ወኪል ተናግሯል።ከ10 ቀናት በፊት ካቡል ውስጥ በሚገኝ አንድ ፖሊስ ጣብያ የፈንዳ ቦንብ የ14 ሰዎችን ሕይወት መቅጠፉ አይዘነጋም። ታሊባን ጥፋቱን የፈፀምኩት እኔ ነኝ ሲል ኃላፊነቱን ወስዷል።ባለፈው አርብ ደግሞ የታሊባን አለቃ ወንድም የሆነው ሂባቱላህ አኩንደዛዳ መስጅድ ውስጥ ሳለ በተመጠደ ቦንብ ሕይወቱ አልፏል።አፍጋኒስታን ውስጥ በርካታ ወታደሮች ያሏት አሜሪካ ከታሊባን ጋር ድርድር ውስጥ እንዳለች እና በጎ ጅማሬዎች እንደታዩ ዕለት አርብ ፕሬዝደንቷ ትራምፕ በትዊተር ገፃቸው ማወጃቸው አይዘነጋም። (ምንጭ፡-ቢቢሲ) | https://waltainfo.com/am/34128/ |
f526033c11de4c5875b696672c701e7e | ba9fb1c1781eb2ab5610add702dd8efa | የመንግስታቱ ድርጅት ለሱዳን ህዝብ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላለፈ | ፖለቲካ | በሱዳን ህዝባዊ መንግስት እንዲመሰረት መደላድል የሚፈጥር ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ጽሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ለአገሪቱ ህዝብ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላለፉ፡፡የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሱዳን የሽግግር መንግስት እንዲመሰረት ያደረገ ስምምነት መፈረሙን አስመልክቶ የድጋፍ መግለጫ አውጥቷል፡፡በዚህም የሱዳን ህዝብን የቆየ የዲሞክራሲና የሰላም ምኞት ለማሳካት ብሎም የአገሪቱን የሽግግር ጊዜ ለመደገፍ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቁርጠኛ መሆኑን የተቋሙ ዋና ጽሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ተናግረዋል፡፡አያይዘውም የአገሪቱን ኢኮኖሚ እንዲያገግም በማድረግ ዘላቂ ልማት ለማምጣት ምቹ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡በሱዳን ወታደራዊ ምክር ቤትና በተቃዋሚ ሀይሎች መካል የተፈረመው የስምምነት ሰነድ ሁለቱ ኃይሎች ስልጣን በመጋራት የሽግግር መንግስት መመስረት የሚያስችላቸው ነው፡፡ስምምነቱ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድና የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ በተገኙበት ትላንት በካርቱም መፈረሙ ይታወቃል፡፡ (ምንጭ፦ ሽንዋ) | https://waltainfo.com/am/33324/ |
b0e470079a9bd7a21e66229b4e571690 | ee4e8da8d63c8409821c3a8180eb38cc | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ከሳዑዲ አልጋወራሽ ሞሃመድ ቢን ሳልማን ጋር በስልክ ተወያዩ | ፖለቲካ | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ከሳዑዲ አረቢያ አልጋወራሽ ሞሃመድ ቢን ሳልማን ቢን አብዱላዚዝ ጋር በስልክ ተወያይተዋል፡፡በዚህን ወቅት የሳዑዲው አልጋወራሽ ኢትዮጵያ የሱዳን የፖለቲካ ፓርቲዎች ስምምነት እንዲፈፅሙ የነበራትን የሸምጋይነት ሚና አድንቀዋል።በተጨማሪም ኢትዮጵያ በቀጠናው ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን የምታደርገውን ጥረት ሳዑዲ እንደምትደግፍ መናገራቸውን የዘገበው የሳዑዲ ፕሬስ ኤጀንሲ ነው።የሱዳን ተቃዋሚዎችና ወታደራዊ ሃይል ስልጣን መጋራት የሚያስችላቸውን የመጨረሻ ስምምነት ከቀናት በፊት መፈራረማቸው ይታወሳል። | https://waltainfo.com/am/31294/ |
b80697cc1054d753174d598532d2293d | 78f92e9fa93023a528d9d494201ea1d0 | ሦስት ዓመት የነበረው የዩኒቨርሲቲ የዲግሪ መርሀ ግብር ቆይታ ወደ 4 ዓመት ከፍ እንዲል ተወሰነ | ሀገር አቀፍ ዜና | ሦስት ዓመት የነበረው የዩኒቨርሲቲ የዲግሪ መርሀ ግብር ቆይታ ወደ 4 አመት ከፍ እንዲል ተወሰነ፡፡በ2012 ዓ.ም ወደ መንግሥትም ሆነ የግል ዩኒቨርሲቲዎች የሚገቡ አዲስ የመጀመሪያ ዓመት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ትምህርት የሚጀምሩት በ15 አዳዲስ ትምህርቶች መሆኑን የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ አስታውቋል።በሦስት ዓመታት ይጠናቀቅ የነበረው የዲግሪ መርሀ ግብርም ወደ አራት ዓመት ከፍ እንደሚል ነው የገለጸው።በዚህ ሂደት እንዲያልፉ የሚደረጉትም በ2012 ዓ.ም ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚገቡ ተማሪዎች እንደሆኑ ነው የተገለጸው፡፡ዩኒቨርሲቲዎቹ በ2012 ዓ.ም ለመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች የሚሰጡት የትምህር ዓይነቶች ለሁሉም የትምህርት ክፍሎች የጋራ እንደሚሆኑ ታውቋል፡፡ትምህርቶቹም ተማሪዎች በአስተሳሰብ ምጡቅ እንዲሆኑ፣ ብዝሀነትን፣ የሀገርን ባህል፣ ሀገር በቀል ዕውቀቶችንና ታሪክ እንዲያውቁ የሚያደርጉ ናቸው ብሏል ኤጀንሲው፡፡የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የትምህርት ጥራት፣ ስነምግባር እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በሚመለከት የሀገሪቱ የትምህርት ስርዓት እንዴት ይቃኝ? በሚል ከ2007 ዓ.ም ጀምሮ በምሁራን ሰፊ ጥናት ሲደረግና ሕዝብም ሲወያይበት መቆየቱን የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አንዱአለም አድማሴ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ አስረድተዋል፡፡ በሂደቱም ማሻሻያ እና ለውጦች ተደርገዋል።በዚሁ መሰረትም በ2012 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ዩኒቨርሲቲ ለሚገቡ ተማሪዎች አዳዲስ የትምህርት ዓይነቶችን መስጠት እንዲችሉ ስምምነት ላይ ተደርሶ ለዚሁ ዝግጅት መደረጉን፣ አሁን ያለው ሁኔታም ትምህርቱን ለመጀመር የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ | https://waltainfo.com/am/32654/ |
9fbad3d43f70f3a59dfeae8f7c0b66eb | 251827161458c4b4f50a6eb12e1f9f62 | ጳጉሜ ‘ጳጉሜን በመደመር’ በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ መርሃ ግብሮች ይታሰባል | ፖለቲካ |
‘ጳጉሜን በመደመር’ በሚል መሪ ሀሳብ ሀገራዊ የመርሐ ግብር ቅድመ ዝግጅት እየተካሄደ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት አስታውቋል፡፡
የመደመር ስድስት ምሰሶዎችን ባማከለ መልኩ ጳጉሜን በመደመር ሀገር አቀፍ መርሃ ግብር መዘጋጀቱን ነው ፅህፈት ቤቱ ያስታወቀው፡፡
የተለያዩ የመንግስት አካላት የየዕለት እንቅስቃሴዎቹን ለማቀድ ፣ ለመምራት፣ ለማስተባበርና ለማስፈፀም ሀላፊነት ወስደው እየተንቀሳቀሱ መሆኑንም ጨምሮ ገልጿል እየፈፀሙ፡፡
በዚህም መሰረት የጳጉሜን ስድስቱ ቀናት ስያሜ እና አስተባባሪዎች ይፋ የሆኑ ሲሆን ጳጉሜን 1 ብልፅግናን የወከለ ሲሆን በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት አስተባባሪነት፣ ጳጉሜን 2 ደግሞ የሰላም ቀን ሲሰኝ በሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፊሪያት ካሚል እንደሚመራ ነው የተገለፀው፡፡
ጳጉሜን 3 ሀገራዊ ኩራት የሚል ስያሜን ሲሰጠው በማስተባበር በኩል የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማ ሀላፊነቱን ወስደዋል፡፡
ጳጉሜን 4 ዲሞክራሲ የሚል ስያሜን በትራንስፖርት ሚኒስትር ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ የተሰጠ ሲሆን ዕለቱን በአስተባባሪነት የሚመሩት ይሆናል፡፡
ጳጉሜን 5 የፍትህ ቀን ሆኖ እንዲታሰብና የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ እንደሚያስተባብሩት ተመልክቷል፡፡
የመጨረሻው እና የአዲስ አመት ዋዜማው ጳጉሜን 6 ደግሞ የሀገራዊ አንድነት ቀን ሆኖ ታስቦ እንዲውል ውሳኔ ተላልፏል፡፡
ህብረተሰቡም በእነዚህ ቀናት ሰፊ ተሳትፎ በማድረግ ወደ መጪው አዲስ አመት ተስፋን ሰንቆ ለመሻገር እንዲሰናዳ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ጥሪ አቅርቧል፡፡
| https://waltainfo.com/am/31302/ |
c25681405f265453af06484b8d0ce4dd | 1a89439c204a9510e7cab71e2ad13c08 | ጠ/ሚ ዐቢይ በሱዳን ወታደራዊ የሽግግር ሸንጎና የነፃነትና ለውጥ ኃይሎች መካከል በተደረገው የመጨረሻ የስምምነት ፊርማ ላይ ተገኙ | ፖለቲካ | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ነሐሴ 11 ቀን 2011 ወደ ሱዳን ካርቱም በመጓዝ በወታደራዊ የሽግግር ሸንጎና በነፃነትና ለውጥ ኃይሎች መካከል የተደረገውን የመጨረሻውን የስምምነት ፊርማ ተከታተሉ::ይህ የመጨረሻው ስምምነት ወታደራዊ ያልሆነ መንግስት ለመመስረት መንገድ ከፋች ነው ተብሏል::ከስምምነት ፊርማው ቀደም ብሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከነፃነትና ለውጥ ኃይሎች አባላት ጋር ተወያይተዋል:: አባላቱ ለዚህ ስምምነት መፈረም የተጫወተችውን ሚና በማድነቅ እነዚህ ሕገ መንግስታዊና ፖለቲካዊ ስምምነቶች ለዘላቂ ዴሞክራሲያዊና ልማት መሰረት ይጥላል ብለዋል::ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በበኩላቸው፣ ይቅርታንና አንድነትን በመንከባከብ እንዲተጉ በማበረታታት ስኬታማ ውይይት መልካም መነሻ እንጂ ብዙ ስራ የሚጠይቀው መንገድ ከዚህ ቀጣዩ ነው ብለዋል::ሴቶች በፖለቲካ አመራር ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ ለዚህም አካታች እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በተያያዘም የኢትዮጵያን ልምድ በማንሳት የነፃነትና የለውጥ ኃይሉ ይህንን 50-50 የፆታ አካታች ካቢኔ እንዲተገብሩ አስታውሰዋል::በሱዳን ስምምነት ፊርማው ስነስርዓት በማስከተል ባደረጉት ንግግር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሀገሪቱ በሚደረገው የዴሞክራሲ ግንባታ ሂደት ወቅት የሱዳን ህዝቦች የሰላማቸውና የክብራቸው ተንከባካቢዎች እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል::በሱዳን ጉዞአቸው ማብቂያም ከመቶ በላይ በህገወጥ የሰዎች ዝውውር ወደሌላ ሀገር ለመሻገር ሱዳን የቀሩ ኢትዮጵያውያን ሴቶችን ይዘው ተመልሰዋል:: ከነዚህም ውስጥ በተለያየ ጥፋት እስር ቤት የነበሩም ይገኙበታል ነው የተባለው፡፡ መረጃው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ነው፡፡ | https://waltainfo.com/am/31293/ |
08146dc22bf3e437baa507017471437e | f5e509c7d7e54b57753c6b3c6f677181 | ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ በሱዳን የሽግግር መንግሥትን ምስረታ ስነ ስርዓት ላይ ለመታደም ካርቱም ገቡ | ፖለቲካ | ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ የሚመሩት ልዑክ በሱዳን የሽግግር መንግሥትን ምስረታ ስነ ስርዓት ላይ ለመታደም ካርቱም ገብቷል።በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ በማኅበራዊ ገጹ እንዳስነበበው፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመሩት ልዑክ ዛሬ ወደ ሱዳን ያቀናው በሱዳን የሽግግር መንግሥትን በይፋ ለመመሥረት በሚከናወነው ሥነ-ሥርዓት ለመታደም ነው፡፡
የቀድሞው ፕሬዝዳንት ሐሰን ኦማር አልበሽር መንግሥት የሦስት አስርት ዓመታት ቆይታው በሕዝባዊ ተቃውሞ ተናግቶ ወታደራዊ የሽግግር ምክር ቤት ሲመሠረት ሱዳን ወደ ቀውስ እንደምትገባ ብዙዎች ገምተው ነበር፡፡ነገር ግን ኢትዮጵያና የአፍሪካ ሕብረት ባደረጉት ተከታታይ ጥረት ወታደራዊ የሽግግር ምክር ቤቱና ሲቪል የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሳተፉበት የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡
በዚህም ሱዳን ወደ መረጋጋት እንደምትገባ ተስፋ ተጥሎበታል፡፡ የሽግግር መንግሥቱ ምሥረታ ላይ ለመገኘትም የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ የሚመሩት ልዑክ ዛሬ ጠዋት ካርቱም ገብቷል፤ ደማቅ አቀባበልም ተደርጎለታል ሲል የአማራ መገናኛ ብዙሃን ነው፡፡ | https://waltainfo.com/am/31292/ |
0f10341103d746180e7c6d733f4f18e9 | a3f1423290663d9bde1897dd20ddc959 | ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ የ2019 የዓለም የቱሪዝም ሽልማት አሸናፊ ሆኑ | ሀገር አቀፍ ዜና | ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ በሀገሪቱ ቱሪዝም ዘርፍ ባበረከቱት ከፍተኛ አስተዋፅኦ የ2019 የዓለም የቱሪዝም ሽልማት አሸናፊ መሆናቸውን በብሪታኒያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል።ሽልማቱንም የፊታችን ህዳር ወር ላይ በለንደን ከተማ በሚካሄደው የዓለም የቱሪዝም ሽልማት ስነ ስርዓት ላይ የሚቀበሉ ይሆናል።የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ሀምሌ ወር መጨረሻ ላይ ከአለም የቱሪዝም ፎረም ፕሬዚዳንት ቡሉት ማግቺ ጋር መወያየታቸው ይታወቃል።በውይይታቸውም ተቋማቸው እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2020 የሚካሄደውን የአለም የቱሪዝም ፎረም በአዲስ አበባ ለማዘጋጀት ፍላጎት እንዳለው በሉት ማግቺ መናገራቸው በማስታወስ ኤፍ ቢሲ ዘግቧል። | https://waltainfo.com/am/32652/ |
9453d5723ec499b9f9b8bf8d3e640da6 | ca97aed92c4bd754f09b776913e8d3e7 | የፅዳት ዘመቻ ተግባር ባህል ሆኖ እንዲቀጥልና ህብረተሰቡ ለሀገራዊ ጥሪ የሚያሳየው ምላሽ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለፀ | ሀገር አቀፍ ዜና | የፅዳት ዘመቻ ተግባር ባህል ሆኖ እንዲቀጥል እና ህብረተሰቡ ለሀገራዊ ጥሪ የሚያሳየው ምላሽ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለፀ፡፡አራተኛው ዙር ሀገር አቀፍ የጽዳት ዘመቻ ፕሮግራም በዛሬው ዕለት ተከናውኗል፡፡በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ ይፋ በተደረገው እና ወር በገባ የመጀመሪያው እሁድ በመላ ሀገሪቱ የሚከናወነው የጽዳት ዘመቻ በአዲስ አበባ ከተማ ስቴድየም እና የኦሮሞ ባህል ማከል አካባቢ ተከናውኗል፡፡የኦሮሚያ ክልል የተለያዩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች የተሳተፉበት የፅዳት ዘመቻ በአዲስ አበባ ኦሮሞ ባህል ማእከልና አካባቢው የተካሄደ ሲሆን፣ በአዲስ አበባ ስቴድየም ደግሞ የከተማው ነዋሪዎች፣ የመንግስት ባለስልጣናትና የተለያዩ ተቋማት የጽዳት ስራውን አከናውኗል፡፡የኦሮሚያ ክልል ርአሰ መስተዳድር ጽህፈት ቤት ሀላፊ የሆኑት አቶ ሴፈዲን መሀዲ ንጽህናው በተጠበቀ አካባቢ የሚኖርና በጥሩ አስተሳሰብ የተገነባ ማህበረሰብ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡በጽዳት መረኃግብሩ የተሳተፉ አካላትም አካባቢን ከቆሻሻ ጽዱ በማድረግ ጥላቻና መጥፎ አመለካከቶችን ማስወገድ እንደሚገባ አንስተዋል፡፡ | https://waltainfo.com/am/32655/ |
725b024510f5a7cf8793af2462dcf7c2 | 800d2ecdc60dd0d85e55e49c2373241b | የኬንያው ፕሬዚደንት ኡሁሩ ኬንያታ በአዲስ አበባ በሚካሄደው የሰላም ፌስቲቫል ላይ ይሳተፋሉ | ሀገር አቀፍ ዜና | ፕሬዚደንት ኡሁሩ ኬንያታ ከሀገር አቀፍ የአንድነት፣ ይቅርታና ሰላም ኮሚቴ የበላይ ጠባቂ የቀድሞ የኢፌዲሪ ፕሬዚደንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ እና የኮሚቴው አባላት ጋር ባደረጉት ውይይት፤ ኢትዮጵያውያን በምንም ሁኔታ ውስጥ ሆነው የማይለወጡ እና ለድርድር የማይቀርቡ የኬንያውያን ወዳጆች ናቸው ብለዋል።ኢትዮጵያ ከቅድመ-ነጻነት ጊዜ ጀምሮ የኬንያ የቁርጥ ቀን ወዳጅ እንደሆነች ያስታወሱት ፕሬዝዳንት ኡሁሩ፤ በኢትዮጵያ በጳጉሜን 2 እና 3፣ 2011 ዓ.ም በሚካሄደው ሀገር አቀፍ የአንድነት፣ ይቅርታና ሰላም ፌስቲቫል ላይ "እንደ እንደራሳችሁ፤ እንደ ኢትዮጵያውያን ሆኜ እገኛለሁ" ብለዋል።መሪዎች ለሕዝቦቻቸው ሰላም እና ብልፅግናን እንጂ ውድቀትና ጥፋትን ማውረስ አይገባም ሲሉም ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል።የሀገር አቀፍ የአንድነት፣ ይቅርታና ሰላም ፌስቲቫሉን ያዘጋጀው እና በበጎ ፈቃድ የተቋቋመው የሀገር አቀፍ የአንድነት፣ ይቅርታና ሰላም ኮሚቴ አባላት ፕሬዚደንትዶ/ር ሙላቱ ተሾመ፤ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ በኢትዮጵያ በሚካሄደው የሰላም ፌስቲባል ላይ እንዲታደሙ ጋብዘዋቸዋል።ኬንያ የኢትዮጵያ ወዳጅ ሀገር መሆኗን ያወሱት ዶ/ር ሙላቱ፤ ከኬንያ ግጭትን የማስወገድ ተሞክሮ እንዲያጋሩም ጠይቀዋል።
ከፕሬዚደንቱ በተጨማሪ ለቀድሞ የኬንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ራኢላ ኦዲንጋ በፌስቲቫሉ ላይ እንዲሳተፉ ግብዣ የቀረበላቸው ሲሆን፤ ለመሳተፍ ቃል ገብተዋል።ሀገር አቀፍ የአንድነት፣ ይቅርታና ሰላም ኮሚቴ ሰላሟ እና ልማቷ የተረጋገጠ ኢትዮጵያን ለመፍጠር በሚል ዓላማ ከንግዱ ማህበረሰብ፣ ከኃይማኖት ተቋማት፣ ከስነ-ጥበብ ባለሙያዎች፣ ከወጣቶች እና ከሲቪል ማህበረሰብ አባላት የተዋቀረ ኮሚቴ ነው። | https://waltainfo.com/am/32653/ |
9a54309a7672d2a8939a91b341c147be | d54a1d029a704569740e10ea2dc331d6 | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የተሳተፉበት የጽዳት ዘመቻ በአርሲ ዞን ኢተያ ከተማ ተካሄደ | ሀገር አቀፍ ዜና | ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ባህል ሆኖ እንዲቀጥል ታስቦ የሚካሄደውን አገር አቀፍ የጽዳት ዘመቻ ዛሬ በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ኢተያ ከተማ በመገኘት አከናውነዋል፡፡የጽዳት ዘመቻው የመከላከያ ሚኒስትር አቶ ለማ መገርሳና የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ እንዲሁም ሌሎች የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ነው የተካሄደው።ከጽዳት ዘመቻው ቀጥሎም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከልዑካናቸው ጋር በመሆን በአርሲ ዞን ዲገሉና ጢጆ ወረዳ ሙኔሳ አካባቢዎች የኩታ ገጠም ግብርናን በመጎብኘት ላይ ይገኛሉ፡፡አገር አቀፍ የጽዳት ዘመቻው ዛሬ አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ተካሂደዋል፡፡ (ምንጭ:-ኢዜአ) | https://waltainfo.com/am/32656/ |
f2f8feb55d2d01f2f35cc7407c372881 | 9f6de2c79069c661157c8a872f9e13ce | አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የደቡብ ሱዳን የፖለቲካ ፓርቲዎች ከዚህ ቀደም የደረሱትን የሰላም ስምምነት ተግባራዊ እንዲያደርጉ ጥሪ አቀረቡ | ፖለቲካ | የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የደቡብ ሱዳን የፖለቲካ ፓርቲዎች ከዚህ ቀደም የደረሱትን የሰላም ስምምነት ተግባራዊ በማድረግ ወደ ተጨባጭ እንቅስቃሴ እንዲገቡ ጥሪ አቅርበዋል።ሚኒስትሩ ጥሪያቸውን ያቀረቡት የደቡብ ሱዳን የፖለቲካ ፓርቲዎቸ ከዚህ ቀደም የደረሱትን የቅድመ ሽግግር የሰላም ስምምነት አፈፃፀም ሂደት ለመገመገም የተጠራው ስብሰባ ዛሬ አዲሰ አበባ በሚገኘው ኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል በተጀመረበት ወቅት ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ነው።የቅድመ ሽግግር ጊዜው የደቡብ ሱዳን ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች በተገኙበት እኤአ ሜይ 12 ቀን 2019 ዓም በአዲስ አበባ ባደረጉት ውይይት በደረሱት ስምምነት መሰረት እስከ ኖቬምበር 2019 ዓም ድረስ ለ6 ወራት ያህል መራዘሙ ይታወቃል።ስምምነቱ እንዲራዘም መግባባት ላይ ከተደረሰ ጊዜ አንስቶ ወደ ሌላ አገር የተሰደዱ የደቡብ ሱዳን ህዝቦች እና ተቃዋሚ ሃይሎች ወደ ጁባ በመመለስ መኖር መጀመራቸው በፓርቲዎች መካከል መተማመን የፈጠረ መሆኑን እንዲሁም በደቡብ ሱዳን ያለው ግድያ እና ተኩስ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ በደቡብ ሱዳን ሰላምን ለማስፈን አበረታች ጅምር መሆኑን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው ገልጸዋል።ይሁን እንጂ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ተግባራዊ መደረግ ያለባቸው ዋና ዋና ጉዳዮች ማለትም የጋራ የፀጥታ ሃይል ምስረታ፣ የሰው ሃይል ስልጠናና ስምሪት፣ የክልላዊ መንግስታትን ቁጥር የመወሰንና መስል ስራዎች አፈፃፀም አዝጋሚና ዝቅተኛ መሆኑን በማስታወስ ሁሉም ፓርቲዎች ለደቡብ ሱዳን ህዝብ ጥቅም ሲሉ ስምምነቱን ተግባራዊ ለማድረግ ቁርጠኛ እንዲሆኑ ክቡር ሚኒስትሩ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።በዛሬው ውይይት የደቡብ ሱዳን የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የኢጋድ አባል አገራት፣ የኢጋድ ባለድርሻ አካለት ፎረም፣ የትሮይካ፣ የቻይና፣ የውሮፓ ህብረት፣ የአፍሪካ ህብረት፣ የተባበሩት መንግስታት እና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካለት ተወካዮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።ስብሰባው በደቡብ ሱዳን የፖለቲካ ፓርቲዎች የተደረሰውን ስምምነት ተግባራዊ ለማደረግ የተሰሩ ስራዎችን ሪፖርት በማዳመጥ እና ቀጣይ አቅጣጫዎችን በማመላከት በዛሬው እለት እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል። መረጃው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃልአቀባይ ጽ/ቤት ነው፡፡ | https://waltainfo.com/am/31301/ |
0ce38b93993ce9b149ecc4c8484fab49 | ed34024040bc7aa534d79fa9ccde6162 | ፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ የኳታር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሀመድ ቢን አብዱልራህማን አል-ታኒን ጋር ተወያዩ | ፖለቲካ | ፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ የኳታር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሀመድ ቢን አብዱልራህማን አል-ታኒን ጋር ተወያዩ፡፡ኢትዮጵያ ከኳታር ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ግንኙነት ለማሳደግ በትምህርት፣ የመካከለኛ አመራር ደረጃን የማሳደግ ስልጠና እና የሴቶችን ሁለንተናዊ አቅም በማጎልበት ረገድ በትብብር መስራት እንደምትፈልግ ፕሬዝዳንቷ በውይይቱ ወቅት ተናግረዋል፡፡የኳታር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሀመድ ቢን አብዱልራህማን አል-ታኒ በበኩላቸው፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት ዘርፈ ብዙ መሆኑን አንስተው ይህንን ለማጠናከር በትምህርት፣ በጤና እና በልዩ ልዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር ለመስራት ሀገራቸው ፍላጎት እንዳላት ገልፀዋል፡፡ሚኒስትሩ አያይዘውም ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላም መረጋገጥ እያደረገች ያለውን እንቅስቃሴ አድንቀው በተለይ በቅርቡ በሱዳን መረጋጋትና በሰላማዊ የስልጣን ክፍፍሉ ላይ የነበራትን ሚና ልዩ ቦታ የሚሰጠው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ መረጃው የፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ነው፡፡ | https://waltainfo.com/am/31299/ |
2c5faa21aa891b855d234a53f20e36a4 | 4cab5669c067b9bfa47b772023fa19b2 | በኬንያ ሠርግ ከታደሙ መካከል አንድ ሰው በኮሌራ ሲሞት 40 ሰዎች ሆስፒታል መግባታቸው ተገለጸ | ሀገር አቀፍ ዜና | በኬንያ መዲና ናይሮቢ ባለፈው ቅዳሜ በተከናወነ የሠርግ ሥነ ሥርዓት ላይ ከታደሙት መካከል አንድ ተጋባዥ በኮሌራ ሳቢያ ሕይወቱ ሲያልፍ ሌሎች 40 የሚሆኑት ለሕክምና ሆስፒታል መግባታቸውን ዘ ስታር የተባለው ጋዜጣ ዘገበ።ጋዜጣው ጭምሮ እንደገለፀው የሠርጉ ተጋባዦች የሕክምና ምርመራ ውጤት እንደሚያሳየው ተጋባዥ እንግዶቹ ሠርጉን ከታደሙ በኋላ ለኮሌራና የምግብ መመረዝ እንደተዳረጉ ያሳያል።አዲስ ተጋቢ ጥንዶቹ ግን ምንም ዓይነት የጤና መቃወስ ያልገጠማቸው ሲሆን፣ በሠርጋቸው ዕለትም ለጫጉላ ሽርሽር ወደ ዱባይ በረዋል።ይሁን እንጂ የሙሽራው አያት በዚሁ ምክንያት ባሳለፍነው ማክሰኞ ሕይወታቸው ማለፉ ተሰምቷል።በሠርግ ሥነ ሥርዓቱ ላይ 450 የሚሆኑ እንግዶች ተጋብዘው እንደነበር ጋዜጣው አስፍሯል።የሠርግ ሥነ ሥርዓቱ አሠናጅ ይህ ችግር እንዴት ሊከሰት እንደቻለ አስተያየት ከመስጠት ተቆጥቧል።ኮሌራ በዲያሪያ ኢንፌክሽን የሚመጣ ሲሆን ባክቴሪየም ቫይብሪኦ ኮሌራ በተባለ በሽታ አምጭ ተህዋስ ምግብና ውሃ ሲመረዝ ይከሰታል።በኬንያ የኮሌራ በሽታ መከሰት የተለመደ ባይሆንም ከሁለት ዓመታት በፊት ግን በመዲናዋ በአንድ ሆቴል በተካሄደ ዓለም አቀፍ የጤና ኮንፈረንስ ተሳታፊዎች ላይ ወረርሽኙ ተከስቶ እንደነበር ተነግሯል ሲል የዘገበው ቢቢሲ ነው። | https://waltainfo.com/am/33464/ |
7f6b39dbe30d9813a929aea245fe5c9c | da4160150eaafff4087ae1de41c0f564 | የተመድ ዋና ጸሐፊ እና ስምንት የአፍሪካ ሀገራት ርእሳነ መንግሥታት በሱዳን የለውጥ ስምምነት ላይ ይገኛሉ | ፖለቲካ | የተባበሩት መንግሥታት ድርጀት (ተመድ) ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ፣ ስምንት የአፍሪካ ሀገራት ርእሳነ መንግሥታት፣ የአውሮፓ ኅብረት ፕሬዚዳንት እንዲሁም የአረብ እና የምዕራባውያን ሀገራት መሪዎች ቅዳሜ ዕለት በሱዳን በሚደረገው የፖለቲካ ለውጥ እና ሕገ-መንግሥት የማፅደቅ ስምምነት ላይ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።የሱዳን የነፃነት እና የለውጥ ኃይሎች እና የወታደራዊ ሽግግር ምክር ቤት ታሪካዊ የተባለውን ስምምነት ለማድረግ መስማማታቸው ይታወሳል።በስምምነት ፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ይገኛሉ ተብለው የሚጠበቁት የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር የሆኑት የግብጹ ፕሬዚዳንት አብደል ፋታህ ኤል-ሲሲ፣ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፣ የኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ፣ የዩጋንዳው ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ፣ የቻድ ፕሬዚዳንት ኢድሪስ ዴቢ እና የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ሞሳ ፋቂ ናቸው።በዚህ ታሪካዊ ስምምነት ላይ የዩናይትድ ስቴትስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተወካዮች፣ ስድስት ሀገራትን ያከተተው የገልፍ ኅብረት ምክር ቤት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና ሌሎች የባሕረ-ሰላጤ ሀገራት መሪዎች እንደሚገኙም ይጠበቃል።ቅዳሜ ዕለት ለሚደረገው ሕገ-መንግሥት የማፅደቅ ስምምነት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፤ ስምምነቱ የወታደራዊ ሽግግር ምክር ቤት ሊቀበንበር አብዴል ፋታህ አል-ቡርሃንን የመጀመሪያው የሉዓላዊ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ያደርጋቸዋል ተብሏል።(ምንጭ፦አልሸርቅ አል-አውሳጥ) | https://waltainfo.com/am/33323/ |
0aeffd520b1af60282af97f0748a19d9 | a5c7f30cc9232a6d24006f3179d92370 | የፌዴራል ፖሊስ፣ ፀረ ሙስና ኮሚሽንና ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ | ቢዝነስ | የፌዴራል ፖሊስ፣ ፀረ ሙስና ኮሚሽንና ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ሙስና ጨርሶ እንዳይፈፀም በጋራ ለመከላከልና ተፈፅሞም ሲገኝ ለመመርመር የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ስምምነቱ በዋናነት የተደራጀ የፀረ ሙስና ዘመቻ ለማድረግ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡በተለይም በአገሪቱ የሚስተዋለውን ከፍተኛ የሆነ የሙስና ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያስችል ስምምነት መሆኑም ተገልጿል፡፡ሙስናን የሚፀየፍ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረገው አገራዊ ጥረት ሶስቱም ተቋማት ተጠናክረው ተግባሩን በጋራ ለመከላከል በቅንጅት እንደሚሰሩ ተገልጿል፡፡የምርመራውን ስራ ፌዴራል ፖሊስ፣ የመክሰሱን ስራ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ እንዲሁም ሙስናን የመከላከሉንና የማስተማሩን ስራ ፀረ ሙስና ኮሚሽን እንደሚሰሩ የሚታወቅ ሲሆን፣ ይህንኑ በቅንጅት ለመስራት ነው ስምምነቱ የተፈረመው፡፡ፀረ ሙስና ኮሚሽን ሙስናን ለመከላከል ደክሟል በሚል በህብረተሰቡ ዘንድ የሚነሳውን ቅሬታ በማስተካከል በቀጣይ ሙስናን ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመከላከል የሚያስችል ስራ እያከናወነ መሆኑን ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡ | https://waltainfo.com/am/23910/ |
90c6e80abfcf089746ce766265f4e53b | de54e50dad18307c066d422e514cd251 | የደቡብ ክልል አደረጃጀት ጥናት የምክክር መድረክ ማጠቃለያ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው | ፖለቲካ | የደቡብ ክልል አደረጃጀት ጥናት የምክክር መድረክ ማጠቃለያ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን) በአዲስ አበባ እና በአዳማ ሲያካህድ የቆየውን የክልል አደረጃጀት ጥናት ምክክር መድረክ ማጠቃለያ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል።በውይይት መድረኩ ላይ በፌደራል ደረጃ የሚገኙ አመራሮች እና የቀድሞ ነባር አባላት ከሰሞኑ በአዲስ አበባ ሲያካሄዱት የነበረው ውይይት እንዲሁም የአዳማው የአዲስ አበባ ከተማ የደኢህዴን አመራር መድረክ ሪፖርት ቀርቧል፡፡በዚሁም በውይይቱ ላይ የተንሸራሸሩ ሀሳቦች በየቡድን መሪዎች በሪፖርት መልክ ቀርበው ውይይት እየተካሄደባቸው ይገኛል፡፡መድረኩን እየመሩ የሚገኙ የደኢህዴን ሊቀ መንበርና የሰላም ሚኒስትሯ ወ/ሮ ሙፈርያት ካሚል፣ ውይይቶቹ አመራሮቹን በአንድነት ውስጥ ያለውን ሀይል እንዲገነዘቡ ያስቻለ ነው ብለዋል፡፡በዛሬው ውይይት ላይ በደቡብ ክልል የአደረጃጀት ጥናትና በመጨረሻው ምክረ-ሃሳብ ላይ የተስተዋሉ ክፍተቶች መኖራቸውንና ሌሎች የተለያዩ ወቅታዊ ጥያቄዎች ከተሳታፊዎች ተነስተዋል፡፡ሰሞኑ ከክልል ውጭ ባሉ የደኢህዴን አመራሮች ደረጃ የደቡብ ክልል የአደረጃጀት ጥናት ዙሪያ ውይይት ሲካሄድ መቆየቱ የሚታወስ ነው፡፡ | https://waltainfo.com/am/31291/ |
3e92fc15ebd5318f383cfd77091ee850 | a27204ab28e0341787f84046001856aa | በሀገሪቱ የሚፈጠሩ ግጭቶችንና አለመረጋጋትን ለመፍታት የሴቶችን ከፍተኛ ሚና መጠቀም እንደሚገባ ተገለጸ | ሀገር አቀፍ ዜና | በሀገሪቱ የሚፈጠረውን ግጭትና አለመረጋጋት ከመፍታት ረገድ ሴቶች ያላቸውን ሚና በሚመለከት ውይይት ተደረገ፡፡በኢትዮጵያ ሴቶች ፌደሬሽንና ሰላም ሚኒስቴር ባዘጋጀው በዚህ መድረክ ከሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ ሴቶች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡በውይይት መድረኩ ግጭቶችና አለመረጋጋቶች ሲፈጠሩ የመጀመሪያ ተጎጂዎች ሴቶች የመሆናቸውን ያህል ችግሮችን ለመፍታት ደግሞ ሴቶች ከየትኛውም የህብረተሰብ ክፍል በላይ ቅርበት አላቸው ተብሏል፡፡ሴቶች ልጆቻቸውን፣ ባሎቻቸውና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎችን በቅርበት የማግኘት ዕድሉ ስላላቸው ችግሮችን መፍታት እንደሚችሉም ተገልጿል፡፡በአንዳንድ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተፈጠሩ ችግሮችን ከመቅረፍ ረገድና ሰላም እንዲሰፍን ሴቶች ጉልህ ሚና እንደነበራቸውም ተጠቁሟል፡፡በውይይቱ ላይ የተገኙት የእርቀ ሰላም ኮሚሽን ምክትል ሰብሳቢ ሎሬት የትነበርሽ ንጉሴ፤ ቀደም ባሉት ጊዜያት በሀገሪቱ በነበረው አለመረጋጋት ሴቶች የሚጠበቅባቸውን ያህል ሚናቸውን አልተወጡም ብለዋል፡፡በመሆኑም ይህንን ታሳቢ በማድረግ በቀጣይ በሀገሪቱ ሰላን በማስጠበቅ በኩል ሴቶች ተፈጥሯዊ ፀጋዎችን በመጠቀምና ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት ድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ | https://waltainfo.com/am/32651/ |
fe4f087cd5e757b6303b97e2b88d032d | f14ee68c5392f001ea0b9c8fc181277b | የኬንያው ፕሬዚደንት ጳጉሜ 2 እና 3 በአዲስ አበባ በሚካሄደው የሰላም ፌስቲቫል ላይ እንደሚሳተፉ አስታወቁ | ሀገር አቀፍ ዜና | የኬንያው ፕሬዚደንት ጳጉሜ 2 እና 3 በአዲስ አበባ በሚካሄደው የሰላም ፌስቲቫል ላይ እንደሚሳተፉ አስታወቁፕሬዚደንት ኡሁሩ ኬንያታ ከሀገር አቀፍ የአንድነት፣ ይቅርታና ሰላም ኮሚቴ የበላይ ጠባቂ የቀድሞ የኢፌዲሪ ፕሬዚደንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ እና የኮሚቴው አባላት ጋር ባደረጉት ውይይት፤ ኢትዮጵያውያን በምንም ሁኔታ ውስጥ ሆነው የማይለወጡ እና ለድርድር የማይቀርቡ የኬንያውያን ወዳጆች ናቸው ብለዋል።ኢትዮጵያ ከቅድመ-ነጻነት ጊዜ ጀምሮ የኬንያ የቁርጥ ቀን ወዳጅ እንደሆነች አስታውሰው፤ በጳጉሜን 2 እና 3፣ 2011 ዓ.ም. በሚካሄደው ሀገር አቀፍ የአንድነት፣ ይቅርታና ሰላም ፌስቲቫል ላይ እንደ ኢትዮጵያውያን ሆኜ እገኛለሁ ብለዋል።መሪዎች ለሕዝቦቻቸው ሰላም እና ብልፅግናን እንጂ ውድቀትና ጥፋትን ማውረስ አይገባም ሲሉም ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል።የሀገር አቀፍ የአንድነት፣ ይቅርታና ሰላም ፌስቲቫሉን ያዘጋጀው እና በበጎ ፈቃድ የተቋቋመው የሀገር አቀፍ የአንድነት፣ ይቅርታና ሰላም ኮሚቴ አባላት ፕሬዚደንትዶ/ር ሙላቱ ተሾመ፤ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ በኢትዮጵያ በሚካሄደው የሰላም ፌስቲባል ላይ እንዲታደሙ ጋብዘዋቸዋል።ኬንያ የኢትዮጵያ ወዳጅ ሀገር መሆኗን ያወሱት ዶ/ር ሙላቱ፤ ከኬንያ ግጭትን የማስወገድ ተሞክሮ እንዲያጋሩም ጠይቀዋል።ከፕሬዚደንቱ በተጨማሪ ለቀድሞ የኬንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ራኢላ ኦዲንጋ በፌስቲቫሉ ላይ እንዲሳተፉ ግብዣ የቀረበላቸው ሲሆን፤ ለመሳተፍ ቃል ገብተዋል።ሀገር አቀፍ የአንድነት፣ ይቅርታና ሰላም ኮሚቴ ሰላሟ እና ልማቷ የተረጋገጠ ኢትዮጵያን ለመፍጠር በሚል ዓላማ ከንግዱ ማህበረሰብ፣ ከኃይማኖት ተቋማት፣ ከስነ-ጥበብ ባለሙያዎች፣ ከወጣቶች እና ከሲቪል ማህበረሰብ አባላት የተዋቀረ ኮሚቴ ነው። | https://waltainfo.com/am/33465/ |
abe52602ce28a0716ccbbdae2749d58d | 3d355d9ebb13246efb966885a8fbb81d | በ2045 ሁለቱ ኮሪያዎች የመዋሃድ እድል እንዳላቸው የደቡብ ኮሪያው ፕሬዚዳንት ሙን ጃ-ኢን ተናገሩ | ፖለቲካ | የሁለተኛው የዓለም ጦርነት 100ኛ ዓመት በሚከበርበት እ.አ.አ 2045 ላይ ሁለቱ ኮሪያዎች የመዋሃድ እድል እንዳላቸው የደቡብ ኮሪያው ፕሬዚዳንት ሙን ጃ-ኢን ተናገሩ፡፡ፕሬዚዳንት ሙን ይህንን ያሉት ኮሪያ እ.አ.አ ከ1910-1945 ባሉት ዓመታት ውስጥ ከነበረችበት የጃፓን አገዛዝ ነፃ የወጣችበትን 74ኛ ዓመት ክብረ በዓል አስመልክቶ ነው።ሙን በሰሜን ኮሪያው ኪም ጆንግ ኡን እና በአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ መካከል ከኒዩክሌር ነፃ መሆን በተመለከተ በአጭር ጊዜ ውስጥ አራተኛ ውይይት እንዲካሔድ እየገፋፉ ይገኛሉ።ከኒዩክሌር ነፃ መሆን እና ከሰሜን ኮሪያ ጋር ጠንካራ ኢኮኖሚያዊ ትብብር ማድረግ በሰላጤው ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የሚያስችል መሠረት ለመጣል ወሳኝ ነው ብለዋል።ሙን፣ ሴኡል እና ፒዮንግያንግ እ.አ.አ በ2032 በጋራ ኦሎምፒክን እንዲያዘጋጁ ለማድረግ እና እ.አ.አ በ2045 የሁለቱን ኮሪያዎች ውሕደት እውን ለማድረግ ቃል ገብተዋል።በመጨረሻም፣ “ለራሷ፣ ለምሥራቅ እስያ እና ለዓለም ሰላም እና ብልጽግና የምታመጣ አዲሲቷን የኮሪያ ሰላጤ እየጠበቅን ነው” በማለት ሐሳባቸውን ደምድመዋል። (ምንጭ:-ዘጋርዲያን) | https://waltainfo.com/am/33985/ |
cae22fa71658ebb09c91e7fdf9274274 | 8ca3ff3bad877a0c4ac54e826f11105f | በአዳማ ሲካሄድ የቆየው የደኢህዴን ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች መድረክ ተጠናቀቀ | ፖለቲካ | በአዲስ አበባ የሚገኙ የደኢህዴን ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በአዳማ ያካሄዱት መድረክ ተጠናቋል፡፡አመራሮቹ በደቡብ ክልል የክልል አደረጃጀት አስመልክቶ ይፋ በተደረገው ጥናት ላይ ተወያይተዋል፡፡በደቡብ ክልል የክልል አደረጃጀት ጥያቄዎችን ለመመለስ የተጠናዉ ጥናት የዜጎችን ህገ መንግስታዊ መብት የሚጥስ አለመሆኑም ተብራርቷል፡፡ የደኢህዴንና የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ ተስፋዬ በልጅጌ፤ ደኢህዴን የህዝቦችን ጥያቄ በግምት ሳይሆን በእውቀት ላይ ተመስርቶ በጥናት ለመመለስ በ10ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ በመነሳት በሀገር ደረጃ አዲስ ልምድ ይዞ የመጣና አማራጭ ሃሳቦችን እያበረከተ የሚገኝ መሆኑን ገልፀዋል፡፡የክልሉ 2011 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀም የተገመገመ ሲሆን፤መድረኩ ብሄራዊና ሀገራዊ ማንነትን አጣጥሞ ለመሄድ መግባባት የተፈጠረበት መሆኑ ተገልጿል፡፡ለአራት ቀናት በቆየው በዚህ መድረክ ከክልል አደረጃጀት ጥያቄ በተጨማሪ በወቅታዊ፣ አገራዊ፣ ክልላዊ እና በከተማው የፖለቲካዊና ፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ ምክክር አድርገዋል፡፡በምክክር መድረኩ ከ1 ሺህ በላይ በአዲስ አበባ የሚገኙ የድርጅቱ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ | https://waltainfo.com/am/31290/ |
69a117292e81bd5154f6819f7544f694 | c23a868419d7661bbd17adcd464c0f99 | ሰሜን ኮሪያ ከደቡብ ኮሪያ ጋር እንደማትደራደር አሳወቀች | ፖለቲካ | ሰሜን ኮሪያ "በደቡብ ኮሪያ ያልተገባ ድርጊት ምክንያት" በሚል ሰበብ ከደቡብ ኮሪያ ጋር ልታደርግ የነበረውን ቀጣይ ድርድር እንደማታካሂድ አሳወቀች።ሰሜን ኮሪያ እዚህ ውሳኔ ላይ መድረሷን ያሳወቀችው የደቡብ ኮሪያው ፕሬዝዳንት ሙን ጃኢን ትናንት ሐሙስ ያደረጉትን ንግግር ተከትሎ ነው።ይህ በእንዲህ እንዳለ ዛሬ አርብ ሰሜን ኮሪያ ሁለት ሚሳኤሎችን ወደ ምሥራቃዊ የባሕር ዳርቻዋ በመተኮስ ሙከራ ማድረጓን የደቡብ ኮሪያ ሠራዊት አሳውቋል። ይህም ሙከራ ከአንድ ወር ባነሰ ጊዜ ውስጥ ለስድስተኛ ጊዜ መሆኑ ታውቋል።ይህ ተከታታይ የሰሜን ኮሪያ የሚሳኤል ሙከራ የተደረገው ባለፈው ሰኔ ወር ላይ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ከሰሜን ኮሪያው መሪ ጋር ባደረጉት ውይይት የኒዩክሌር ጦር መሳሪያዎችን ለማስወገድ ውይይት ለመጀመር ከተስማሙ በኋላ ነው።የደቡብ ኮሪያው ፕሬዝዳንት ሃገራቸው ከጃፓን ነጻነቷን ያገኘችበትን ቀን በተከበረበት ወቅት ሁለቱ ኮሪያዎች በአውሮፓዊያኑ 2045 እንደሚዋሃዱ በመናገራቸው ነው ሰሜን ኮሪያ ቁጣዋ የተቀሰቀሰው።በቴሌቪዥን በተላለፈው ንግግር "ለራሱና ለምሥራቅ እስያ ብሎም ለዓለም ሰላምና ብልጽግናን የሚያመጣው አዲሱ የኮሪያ ልሳነ ምድር ከፊታችን እየጠበቀን ነው" ሲሉም ተናግረዋል- ፕሬዝዳንቱ።ሰሜን ኮሪያ፣ ደቡብ ኮሪያና አሜሪካ እያካሄዱት ባለው የጋራ ወታደራዊ ልምምድ ላይ ተቃውሞዋን ያሰማች ሲሆን፣ ይህም ከፕሬዝዳንት ትራምፕና ከሙን ጃኢን ጋር ቀደም ሲል ያደረጉትን ስምምነት የሚጥስ መሆኑን በመግለጫዋ ላይ ጨምራ ገልጻለች።የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት በጻፉት ደብዳቤ ላይ ከፍተኛ ወጪ ስለሚወጣበት የደቡብ ኮሪያና የአሜሪካ የጦር ልምምድ ቅሬታቸውን ገልጸው ነበር።የሰሜን ኮሪያ የውህደት ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እንደተናገሩት፣ አካባቢውን ከኒዩክሌር ጦር መሳሪያ ነጻ ለማድረግ የተጀመረው ንግግር መቋጫ እንዳያገኝ ደቡብ ኮሪያ ወታደራዊ ልምምዱን ማድረጓ ዋኛው ምክንያት ነው ሲሉ ተናግረዋል። (ምንጭ፡-ቢቢሲ) | https://waltainfo.com/am/33986/ |
83d48bc1725fa9f8ecee2f8ddce21dd1 | 7597f528c7bcfca44c5519bf11b446e7 | ህንድ ግዛቶቿን ወደ ነበረበት ለመመለስ በቁርጠኝነት እንደምትሰራ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ገለጹ | ፖለቲካ | ህንድ ግዛቶቿን በተመለከተ ወደ ነበረበት ታሪክ ለመመለስ በቁርጠኝነት እንደምትሰራ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ገለጹ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ የካሽሚር ጉዳይ በተለየ መልኩ የሚታይ እና ለሀገራቸው የህልውና ጉዳይ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡የካሽሚር ግዛት ህንድ በኢንግለዝ ቅኝ ግዛት ከመገዛቷ በፊት የህንድ እንደነበረች የሚነገር ሲሆን፣ ሀገሪቱ በቅኝ ግዛት ስር መውደቋን ተከትሎ በቀጠናው ላይ መበጣጠስ ሲመጣ ጊዛቲቱ በተለያዩ ሀገራት ማለትም በፓኪስታን እና በህንድ ስር ተከፋፍላለች፡፡ታዲያ ህንድ የካሽሚርን ግዛት በተመለከተ በተለያዩ ጊዜያቶች የተለያዩ እርምጃዎችን ስትወስድ የቆየች ብትሆንም በዘላቂነት ችግሩን ለመፍታት አልቻለችም፡፡ በዚህ ጉዳይ የካሽሚር ነዋሪዎች ለሚያነሱት ጥያቄ ህንድ መልስ ለመመለስ መጣር ብቻ ሳይሆን ከጎሮቤቷ ፓኪስታን ጋርም እሰጣ ገባ ውስጥ እንድትገባ አድርጓታል፡፡የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በሰጡት ጋዜጣዊ መግልጫ ሀገራቸው ህንድ ወደ ነበረችበት የቀድሞ ታሪክ መመለስ አለባት፤ ለዚህም መንግስታቸው በቁርጠኝነት ይሰራል ሲሉ መናገራቸው ተገልጸዋል፡፡ህንድ ከኢንግሊዝ ነፃ የወጣችብትን 70ኛ እና ከፓኪስታን የተለያየችበትን የነፃነት ዓመት ስታከብር ንግግር ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የካሽሚር ግዛት በህንድ ሉዓላዊነት እና ለእድገቷ ወሳኝ ሚና የምትጫወት ነች፤ ስለዚህም ሀገራቸው ከዚህ በኋላ ያለማመንታት ካሽሚር ወደ ቀድሞ ማንነቷ ትመለሳለች ማለታቸዉን የወጡት ዘገባዎች አስነብበዋል፡፡ናሬንደራ ሞዲ ሀገራቸው ሁሉን በልኩ ሊስተካክል የሚያስችል ህገ መንግስት እንዳላት ተናግረው ነገሮች ሁሉ በዛ ይስተካከላል ብለዋል፡፡ በጉዳዩ ከህንድ ጋር እሰጣ ገባ ውስጥ ያለችው ፓኪስታን ህንድ ለመውሰድ ለምተዘጋጀው እርምጃ አፀፋዊ መልስ ለመስጠት ዝግጁ ነኝ ብላለች፡፡የፓኪስታኑ ጠቅላይ ሚንስትር ኢምራን ካሃን እስከ መጨረሻው እስትንፋስ ድረስ ለመፋለም ተዘጋጅተናል ማለታቸዉን ቢቢሲ አስንበቧል፡፡የዓለም ሁሉ ዓይን በካሽሚር እና በፓኪስታን ላይ ነው፡፡ ህንድ ስለምታደርገው ነገር ሃይ ባይ ባጣችበት ውቅት ላይ እኛ ለእርምጃ ተዘጋጅተናል፡፡ ነገር ግን ለሚሆነው ሁሉ ኃላፊነቱን የዓለም ማህበረስብ ራሱ ይወስዳል ብለዋል ጠቅላይ መኒስትር ኢምራን ከሃን፡፡ በዚህ መልስ ግን ናሬንድራ ሞዲ ያሉት ነገር የለም ነው የተባው፡፡(ምንጭ፡-አልጀዚራ፣ ቢቢሲ እና ኢንዲያን ቱደይ) | https://waltainfo.com/am/33984/ |
237c8da9d98e1de2d149efd92780faf5 | d8505295959ad8070015440cef676843 | ሩዋንዳ በትምህርት የወጣቶችን ስብዕና በመገንባት ውጤታማ ሆናለች -ተመድ | ሀገር አቀፍ ዜና | በሩዋንዳ የተዘረጋው የትምህርት መርሀ ግብር የወጣቶችን ስብዕና በመገንባት ውጤታማ እየሆነ ስለመሆኑ ተነግሯል፡፡የዓለም ወጣቶች ቀን በዚህ ሳምንት በመላው አለም እየተከበረ ይገኛል፡፡ወጣቶችን በትምህርት በማብቃት ማህበራዊ ለውጡን ማገዝ በሚለው መርህ መሰረት ሩዋናዳ ይበል የሚያሰኝ ለውጥ ስለማስመዝገቧ ተዘግቧል፡፡የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ በማህበራዊ፤ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ረገድ ማስፋት ዓለም እየገጠማት ላለው ችግር ሁነኛ መፍትሄ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ትምህርት ዋነኛ የአመለካከት ለውጥ መሳሪያ መሆኑን ተከትሎም ሩዋንዳውያን ወጣቶች የለውጡን ፈር እየተከተሉ ስለመሆናቸው ነው የሀገሪቱ መንግስት ይፋ ያደረገው፡፡በዓለም አቀፍ ደረጃ 1 ነጥብ 8 ቢሊዮን ዜጎች እድሜያቸው ከ10 እስከ 24 ውስጥ እንደሚገኝ መረጃዎች የሚያመላክቱ ሲሆን፤ ከዚህ ውሰጥ 226 ሚሊየኑ በአፍሪካ ይገኛሉ፡፡ሩዋንዳም 60 በመቶ ዜጎቿ እድሜያቸው ከ 25 በታች መሆኑን ተከትሎ በትምህርት እንዲዘልቁ በማድረግ በኩል አበክራ በመስራቷ የተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ተቋም ዪኒስኮ እውቅና ችሯታል፡፡ባሁኑ ሰዓት ከዓለማችን 262 ሚሊዮን ህጻናትና ወጣቶች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጥናት ማመላከቱን ተከትሎ ሩዋንዳ ፍታዊ የትምህርት ተደራሽነትን ማሰካቷ ወደኋላ ለቀሩት ሀገራት ተምሳሌት እንድትሆን አሰችሏታል፡፡ከሁለት አመታት አስቀድሞ ይፋ ያደረገቸው የሰባት አመት የትምህርት ማሻሻያ ስትራቴጂ ለውጤቱ እንዳበቃት በመረጃው ተጠቅሷል፡፡ እየተመዘገብ ባለው ውጤት መሰረትም ተመድ አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ ነው ሲል ዘ ኒው ታይምስ ድረ ገጽ ዘግቧል፡፡ | https://waltainfo.com/am/33463/ |
e669c6ef1eb5fded780118e7c706412f | 4981696953999b5485cd44fe5469eeee | ሰላሟ የተረጋገጠ ሀገር ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የወጣቱ ሚና የጎላ ሊሆን ይገባል ተባለ | ሀገር አቀፍ ዜና | በኢትዮጵያ የአብሮነት እሴት ተጠብቆ እንዲቀጥልና ሰላሟ የተረጋገጠ ሀገር ለመገንባት በሚደረገው ጥረት 70 በመቶውን የሚሸፍነው ወጣት ሚና የጎላ ሊሆን ይገባል ተባለ፡፡ከሁሉም ክልሎችና ከሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የተወጣጡ 1 ሺህ 400 ወጣቶች የተሳተፉበት አገር አቀፍ የወጣቶች የሰላምና የአንድነት ኮንፈረንስ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ነው፡፡የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ አልማዝ መኮንንእንዳሉት፤ ወጣቱ በሰላም፣ ሀገር ግንባታ እና ዴሞክራሲ ያለውን ሚና በአግባቡ መወጣት አለበት ብለዋል፡፡ሰላምን እውን ለማድረግ ምንም አይነት ቅድመ ሁኔታ ሊቀመጥ አይገባም ያሉት ሚኒስትር ድኤታዋ፤ ሁሉም ጥያቄ በሰላም ማዕቀፍ ውስጥ ምላሽ ሊያገኝም እንደሚገባ ነው የገለጹት።የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ታረቀኝ አብዱልጀባር በበኩላቸው፤ ወጣቱ ሰላምን ለማስጠበቅ በሚደረገው ስራ ግንባር ቀደም መሆን ይኖርበታል ብለዋል።የሰላም እጦት ዋነኛ ሰለባ ወጣቱ እንደመሆኑ ለሰላም ዘብ ሊቆም እንደሚገባም የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ገልጸዋል፡፡ “ወንድማማችነትን በማጎልበት ዘላቂ ሰላምን እናረጋግጣለን” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው መድረክ በሰላም ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ ወጣቶች ፌዴሬሽን ትብብር በጋራ የተዘጋጀ ነው፡፡መድረኩ በውይይት የሚያምንና ጥያቄውን በሰላማዊ መንገድ የሚያቀርብ ትውልድ መፍጠርን ትኩረት አድርጎ መዘጋጀቱም ተገልጿል። | https://waltainfo.com/am/32650/ |
0ffb018e29bff545031f64e1c553d831 | b90cd6e26dda10b4a1cf867383d248c4 | የሚኒስትሮች ም/ቤት በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ተዘጋጅተው በቀረቡ ልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳለፈ | ቢዝነስ | የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 16ኛ አስቸኳይ ስብሰባ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ተዘጋጅተው በቀረቡ ልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡በዚህም መሠረት የመንግስት ሠራተኞች የሥራ መደቦች ምዘና፣ ደረጃዎች ምደባና የደመወዝ ስኬል ረቂቅ ደንብ፣ ወደ ነጥብ የሥራ ምዘና ሥርዓት ለማሸጋገር በቀረበ ውሳኔ የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ስኬል ጥናትና የውሳኔ ሃሳብ እና የጡረታ አበል ተመን በተመለከተ ለሚኒስትሮቸ ምክር ቤት በቀረቡ ጉዳዮች ላይ በዝርዝር ከተወያየ በኋላ አንዳንድ ማሻሻዎችን በማከል ከሀምሌ 1 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ በሥራ ላይ እንዲውሉ ወስኗል፡፡(ምንጭ፡-ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት) | https://waltainfo.com/am/23908/ |
78138d2ab2c32a8b7ff970c26f737023 | 7938058259f264f7a69f09d8aed9d35d | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ መልዕክተኛ ጋር ተወያዩ | ፖለቲካ | ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ሽንዞ አቤ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ዮሽፉሚ ኦካሙራ ጋር ዛሬ ተወያይተዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩና ልዩ መልዕክተኛው የሁለቱ አገራት ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከርና በአፍሪካ የአከባቢ ሰላም ጉዳዮች ላይ አብሮ መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡(ምንጭ:-ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት) | https://waltainfo.com/am/31289/ |
33f51806c0f8207ad4fd1530dabddb57 | f08618136a0c67a6bfe4dbc28f94380f | የሴት ልጅ ግርዛትና ያለ ዕድሜ ጋብቻ ሙሉ ለሙሉ ለማስቆም የተዘጋጀው ፍኖተ ካርታ ይፋ ሆነ | ሀገር አቀፍ ዜና | ፕሬዝደንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የሴት ልጅ ግርዛትና ያለ ዕድሜ ጋብቻ ሙሉ ለሙሉ ለማስቆም የተዘጋጀውን ፍኖተ ካርታ ይፋ አደረጉ፡፡ፕሬዝዳንቷ ኢትዮጵያ በ2025 የሴት ልጅ ግርዛትንና ያለ ዕድሜ ጋብቻን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የያዘችውን ዕቅድ ለማሳካት ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።ባለፉት አምስት አመታት ሲዘጋጅ የቆየውና በቀጣዮቹ አምስት አመታት የሚተገበር ሀገራዊ የጸረ ሴት ልጅ ግርዛትና ያለዕድሜ ጋብቻ ፍኖተ ካርታ በዛሬው ዕለት ይፋ ሆኗል፡፡በስነሥርዓቱ ላይ የተገኙት ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የሴት ልጅ ግርዛትና ያለዕድሜ ጋብቻ ሴቶችን ለዕድሜ ልክ ችግር የሚዳርግ በመሆኑ፤ አሁን የተዘጋጀው ፍኖተ ካርታ ኢትዮጵያ ችግሩን ለመፍታት ያላትን ቁርጠኝኘት ያሳያል ብለዋል፡፡ባለድርሻ አካትና ህብረተሰቡ ለፍኖተ ካርታው ስራ ስኬት የበኩላቸውን እንዲያበረክቱም ጥሪ አቅርበዋል፡፡የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ሚኒስትር ወ/ሮ ያለም ፀጋይ በበኩላቸው፤ የሴት ልጅ ግርዛትና ያለዕድሜ ጋብቻ በመላው ሀገሪቱ ያለ ችግር መሆኑን አንስተዋል። ፍኖተ ካርታውን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለማከናወን ሰፊ ማህበራዊ ንቅናቄ እንደሚደረግና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋርም በጋራ እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ፍኖተ ካርታውን ለማስፈጸም ሶስት ቢሊየን ብር እንደሚያስፈልግም በመድረኩ ላይ ተጠቁሟል፡፡ | https://waltainfo.com/am/32649/ |
35d11ef563b9f2a518820321a12c5c2b | 42229f56961a523ad2308444cce4bf4f | በግንባታ ላይ የሚደርስ አደጋን ለመከላከል የወጡ ህጎች ባለመተግበራቸው ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰ መሆኑ ተገለጸ | ቢዝነስ | በአዲስ አበባ በግንባታ ላይ የሚደርስ አደጋን ለመከላከል የወጡ ህጎች አለመተግበራቸው በሰራተኛው ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ከፍተኛ አድርጎታል ተብሏል፡፡የህጎቹ በትክክል አለመተግበርም የግንባታ ባለቤቶች ለሰራተኛው ደህንነት መጠበቅ ትኩረት እንዳይሰጡ አድርጓቸዋል ነው የተባለው፡፡ይህ የተባለው በአዲስ አበባ በተለይ በየካ፣ ቂርቆስ እና ቦሌ እንዲሁም የ20/80 እና የ40/60 የኮንዶሚኒየም መኖሪያ ቤቶች ግንባታ በስፋት በሚከናወኑባቸው አካባቢዎች የጤና እና ግንባታ ደህንነት ላይ የተሰራ የህዝብ አስተያየት እና ጥናት ይፋ በተደረገበት ወቅት ነው፡፡የግንባታ ባለቤቶች የደህንነት ቁሳቁሶችን አለመጠቀማቸው እና የሚጠቀሙትም ቢሆኑ ርካሽ ዋጋን ፍለጋ ጥራታቸውን እና ደረጃቸውን ያልጠበቁ መሳሪያዎችን ከውጭ አገር እያስገቡ ሰራተኛው እንዲጠቀምባቸው ማድረጋቸው በአዲስ አበባ ውስጥ በግንባታ ዘርፉ ላይ በየጊዜው የሚደርሰውን ጉዳት ከፍተኛ እንዲሆን አድርጎታል፡፡እንደ ኢቲቪ ዘገባ ዘርፉ በኢትዮጵያ ውስጥ ከ850 ሺህ በላይ የስራ ዕድል የሚፈጥር ቢሆንም፤ ለዘርፉ በቂ ትኩረት ባለመሰጠቱና እና ደህንነቱን እንዲጠብቅ ባለመደረጉ በሰራተኛው ምርታማነት ላይ ጉዳት እያስከተለ መሆኑ ተነግሯል፡፡ | https://waltainfo.com/am/23907/ |
10bde65ea9094b3b620b6856fb5bba72 | ec7443ed1e6e90bae0ddc7682902f862 | በሩሲያ በሮኬት ፍንዳታ የተከሰተ የጨረር መጠን ከመደበኛው በ16 እጥፍ ይልቃል ተባለ | ሀገር አቀፍ ዜና | በሩሲያ ለአምስት ሰው ሞት መንስኤ የሆነው የሮኬት ፍንዳታ በአከባቢ ያለውን የጨረር መጠን ከመደበኛው በ16 እጥፍ ከፍ እንዳደረገው ተገልጿል።የሩሲያ የኒውክሌር ኤጀንሲ በወደብ ከተማዋ ሴቬሮድቪንስክ የሮኬት ፍንዳታ ከተከሰተ በኋላ በአካባቢው ያለውን የጨረር መጠን በመለካት ይፋ አድርጓል።180 ሺህ ህዝብ በሚኖርባት ሴቬሮድቪንስክ ከተማ በሚገኙ ስድስት የሙከራ ጣቢያዎች የጨረር መጠኑ የተለካ ሲሆን፥ በዚህም የጨረር መጠኑ ከመደበኛው ከአራት እስከ 16 እጥፍ መጨመሩ ተነግሯል።መደበኛው የጨረር መጠን በሰዓት 0 ነጥብ 11 ማይክሮ ሲኤቨርት ሲሆን በአንድ ጣቢያ በሰዓት 1 ነጥብ 78 ማይክሮሲኤቨርት መመዝገቡ ተነግሯል።ይህ መጠን አደጋኛ ከሚባለው ደረጃ በታች መሆኑ የተገለፀ ቢሆንም፥ በሰው ላይ መጠነኛ ችግር ሊፈጥር እንደሚችል የኒውክሌር ባለሙያዎች ገልፀዋል፡፡ፍንዳታውን ተከትሎ የጨረር መጠኑ ከመደበኛው ከፍ ያለ እንደነበረ እና ከቆይታ በኋላ ግን ወደ መደበኛ ደረጃ መመለሱን የሴቬሮድቪንስክ ከተማ ባለስልጣናት አስታውቀዋል።ባለስልጣናት ፍንዳታው በተከሰተበት አከባቢ የሚገኙ ነዋሪዎች አካባውን ለቀው እንዲወጡ ማሳሰቢያ ቢሰጡም ሌሎች የሩሲያ ባለስልጣናት ግን ውሳኔውን መቃወማቸውን የዘገበው ቢቢሲ ነው፡፡ | https://waltainfo.com/am/34127/ |
15670f3e2f19f4503ce31e192f7cbeff | 2a2c10a99f7e0eaad971a368ca358304 | ሀምሌ 22 የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ በይፋ ተጀመረ | ሀገር አቀፍ ዜና | ሀምሌ 22 የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ በይፋ መጀመሩን የአካባቢ ደንና አየር ንብረት ለውጥ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡የኢትዮጵያ ፕረስ ድርጅት ዘገባ እንደሚያመለክተው ኮሚሽኑ በአረንጓዴ አሻራ ቀን የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብና የመተካካት ስራን ዛሬ በምስራቅ ሸዋ ዞን አደአ ወረዳ የረር የመትከያ ጣቢያ አስጀምሯል፡፡የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ፍቃዱ በየነ ለችግኞቹ እንክብካቤ በተደረገበት ወቅት በኮሚሽኑ ሰራተኞች የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራን አስጀምረዋል፡፡በስነስርዓቱ ላይ 100 የሚሆኑ ሰራተኞች ተሳታፊየሆኑ ሲሆን ሀገራችን ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ሀሳብ አመንጪነት አረንጓዴ አሻራ ቀን በሚል ሀምሌ 22 ቀን 2011 ዓ.ም በአንድ ጀምበር ከ 350 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል በአለም አቀፍ ደረጃ የተያዘውን ክብረወሰን መረከቧ ይታወሳል፡፡ | https://waltainfo.com/am/32647/ |
a072097c4f31f6147a1b475d9669efb9 | 322f8792140a270f5c563b4af6f94aa2 | “የክልል እንሁን” ጥያቄዎችን ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ ለመፍታት እየሰራ እንደሆነ ደኢህዴን አስታወቀ | ፖለቲካ | የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን) በደቡብ ክልል የሚነሱ “የክልል እንሁን” ጥያቄዎችን ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ እንደሚፈታ በአዲስ አበባ የሚገኙትን የድርጅቱን ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በአዳማ ከተማ አባ ገዳ አዳራሽ ሰብስቦ እያወያየ ባለበት ወቅት አስታዉቋል፡፡በስብሰባዉ ላይ ንግግር ያደረጉት የደኢህዴን ስራ አስፈፃሚ አባልና የአዲስ አበባ የኢህአዴግ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ በልጅጌ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተበራከተ የመጣዉን “የክልል እንሁን” ጥያቄ ለመፍታት 7 ወራት የፈጀ ጥናት መካሄዱን አስታዉሰዋል፡፡አቶ ተስፋዬ እንደተናገሩት 20 አባላት ባሉት ቡድን የተካሄደዉ ጥናት ይፋ መደረጉን ተከትሎ በየደረጃዉ የሚገኙ አካላት እንዲወያዩበት ተደርጓል፡፡የዛሬዉ ዉይይት የዚሁ አካል መሆኑን የተናገሩት ኃላፊዉ በጥናቱ ላይ ግብረ-ሀሳብ ዉይይት ማድረግ፣ በክልልና ሀገርአቀፍ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ዉይይት ማድረግና የአዲስ አበባ ደህዴን ቅርንጫፍ 2011ዓ.ም አፈፃፀም ግምገማ አጀንዳዎች ናቸዉ፡፡የዉይይቱ መድረኩ ከስሜት የፀዳ፣ እዉቀትን መሰረት ያደረገና ሀገራዊና ብሄራዊ ማንነትን ባገናዘበ መልኩ እየተካሄደ መሆኑን አቶ ተስፋየ ገልፀዋል፡፡ዉይይቱ ለ 3 ቀናት የሚቆይ ሲሆን ከ1005 በላይ በአዲስ አበባ የሚገኙትን የድርጅቱን ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች እየተሳተፉ ነዉ ተብሏል፡፡
| https://waltainfo.com/am/31287/ |
a5abbd7e973949a3d4cd89a53846282c | 915ed5ea3d96413c3e99899f486cc5da | በኦሮሚያ ከልል ከ80 ሺህ በላይ ለሚሆኑ አመራሮች ስልጠና ተሰጠ | ፖለቲካ | በስልጠናው 20 ሺህ ለሚሆኑ ከፍተኛ አመራሮች በአዳማና ጅማ ለአስራ አምስት ቀናት እነደተሰጠ የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ሀላፊ አቶ አድማሱ ዳምጠው አስታዉቀዋል፡፡ በ20 ዞኖች በተመረጡ አስራ ዘጠኝ ከተሞችና በሶስት መቶ ሀያ ሶስት ወረዳዎች በሰባት ሺ ስልሳ ስድሰት ቀበሌዎች ለሚገኑ ስልሳ ሺ አመራሮች በአጠቃላይ ከሰማንያ ሺ በላይ ለሚሆኑ አመራሮች ስልጠናው መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡የስልጠናው ዋና አላማም በፈጣንን በተቀላጠፈ መልኩ እየሄደ ያለውን ለውጥ ለማስቀጠል የአመለካከትና የአገልጋይነት ስሜት ተፈጥሮ የህበረተሰቡን የመልካም አስተዳደርና መሰረታዊ ችግሮችን ለመቅረፍ ታስቦ የተዛጋጀ ነው ተብሏል፡፡በአስተሳሰብና በአመራር ሂደት ወጥ የሆነ መዋቅር መፍጠር ለውጡን ታች ድረስ በማድረስ ለክልሉም ሆነ ለሀገር የሚሰሩ በጎ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል ያስፈልጋል፡፡ለዚህ ደግሞ በእውቀትና በክህሎት የዳበረ አመራር መፈጠር ያስፈልጋል ያሉት ሃላፊው ስልጠናው እጅጉን መጥቀሙን ጠቅሰዋል፡፡ከስልጠናው በኃላም በተገኘው ግብረ መልስና በተጨባጭ በመጣው ለውጥ ስልጠናው አመርቂ መሆኑም ተነግሯል፡፡ | https://waltainfo.com/am/31288/ |
d0c99b8dc04c0e9876278cb213915d92 | a933c107c9a7822b06d1b6812fb3dae8 | በታንዛኒያ ያላገቡ ሴቶችን ከመታለል ለመታደግ ያገቡ ወንዶች የመረጃ ቋት እንዲቋቋም ሃሳብ ቀረበ | ሀገር አቀፍ ዜና | በታንዛኒያ የዳሬሰላም ገዢ ያላገቡ ሴቶችን ከመታለል ለመታደግ ያገቡ ወንዶች የመረጃ ቋት እንዲቋቋም ሃሳብ አቅርበዋል፡፡በአጭበርባሪ ባለትዳር ወንዶች የሚሠቃዩ ሴቶችን ጉዳት መቀነስን ዓላማ ያደረገ እንደሆነ ገዢው ፖል ማኮንዳ ተናግረዋል፡፡ባለፈው ዓመትበርካታ ያላገቡ ሴቶች ወደ ቢሯቸው በመጡበት ወቅት የችግሩን ስፋት በመረዳት ሀሳቡ እንደመጣላቸው ፖል ማኮንዳ ገልጸዋል፡፡ሚስተር ማኮንዳ ስለ አዲሱ የመፍትሄ እቅድ ሂደት ምንም ዓይነት ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ግን ተቆጥበዋል፡፡ገዢው አወዛጋቢ መግለጫዎችን በመስጠት እንደሚታወቁ በዘገባው ያስታወሰው ቢቢሲ ነው፡፡ | https://waltainfo.com/am/33462/ |
f6ffcbbf9219873266a899fa71cb122c | 5bfa8c8f711a083f2f6d7534fcef40fd | የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ዉጤት ከ 11፡ 30 ጀምሮ ይፋ ይሆናል | ሀገር አቀፍ ዜና | የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ዉጤት ከ 11፡ 30 ጀምሮ ይፋ እንደሚሆን የሀገር አቀፍ የፈተናዎች ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡በዘንድሮዉ ፈተና የተቀመጡት ተማሪዎች ቁጥር በአጠቃላይ 319ሺህ 264 ሲሆን ፤ከነዚህ ዉስጥ 180ሺህ625 ወንደችና ቀሪዎቹ ደግሞ ሴቶች መሆናቸዉን ኤጀንሲ አስታዉቋል፡፡3453 ተማሪዎች በተለያየ ምክንያት ፈተናዉን አለመዉሰዳቸዉ ታዉቋል፡፡ከአጠቃላይ ተፈታኞች 48.59 ፐርሰንት የሚሆኑት ፈተናዉን ከግማሽ በላይ ያመጡ ሲሆን፤ አንድ ተማሪ ከአማራ ክልል 645 ነጥብ በማምጣት ከፍተኛ ዉጤት አስመዝግቧል፡፡ | https://waltainfo.com/am/32648/ |
e925db3a8f0c72945b60db22f250917a | e00cca2b5e0c74c9660f6a57fbbdbf82 | የተባበሩት መንስታት ድርጅት ተጠሪ ተቋማት ለኢትዮጵያዉያን ስራ ፈላጊዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጁ | ሀገር አቀፍ ዜና | የተባበሩት መንስታት ድርጅት ተጠሪ ተቋማት ከ1800 በላይ ለሚሆኑ ኢትዮጵያዉያን ስራ ፈላጊዎች ወደ ስራዉ አለም መቀላቀል በሚችሉበት ሁኔታ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጅተዋል፡፡በመድረኩ የተገኙ ከ26ቱ የመንግስታቱ ድርጅት ተጠሪ ተቋማት የመጡ ተወካዮችም ስራ ፈላጊዎች እንዴት ስራዉን አለም መቀላቀል እንደሚችሉና በቀጣይ በየተቋማቱ የስራ እድል ማግኘት በሚችሉባቸዉ ጉዳዮች ዙሪያ ገለፃ አድርገዉላቸዋል፡፡የኢትዮጵያ የህዝብ ቁጥር ከ100 ሚልዮን በላይ እንደሆነ መረጃዎች ያሳያሉ። ከዚህ ዉስጥም 11 ሚሊዮን የሚጠጋዉ የሀገሪቱ ዜጋ ስራ ፈላጊ እንደሆነ ይነገራል፡፡ ይህ ሳይበቃ በየዓመቱ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ስራ ፈላጊዉን ማሕበረሰብ እንደሚቀላቀሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ታዲያ ይህንን የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ መንግስት ጉዳዩን የሚከታተል የስራ ፈጠራ ኮሚሽን እስከማቋቋም ደርሷል፡፡ በተጨማሪ እስከሚቀጥለው ዓመት መጨረሻ ድረስ ለ3 ሚሊዮን ዜጎች የስራ እድል ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ መግለፃቸዉም ይታወሳል፡፡ | https://waltainfo.com/am/32646/ |
449c6c53038237f560ac03c9c17c4aea | c3510f23d562c110b1ec7d28ab023031 | የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ወደ መምህርነት ሙያ የሚገቡ ተማሪዎች ብቁ መሆን እንዳለባቸው ተገለፀ | ቢዝነስ | የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገቡና በመምርነት ሙያ የሚሰለጥኑ ተማሪዎችን ውጤት መሰረት በማድረግ መመልመል እንደሚገባ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ሰልጣኖች ለመምህርነት ለመመልመል ከፍተኛ ውጤትና ፍላጎት ሊኖራቸው እንደሚያስፈልግ ነው የትምህርት ሚኒስቴር የ2011 በጀት ዓመት ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት ያስታወቀው፡፡በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የቅድመ መደበኛ ትምህርትና የጎልማሶች ትምህርት ላይ በቂ ስራ አለመሰራቱም ተጠቁሟል፡፡በተለይም በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ምክንያቶች ወደ 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን የሚሆኑ ተማሪዎች ትምህርት ማቋረጣቸው የተገለጸ ሲሆን፤ በቀጣይ መፍትሄ እንደሚበጅለት የትምህርት ሚኒስትር ዶ/ር ጥላዬ ጌቴ ገልጸዋል፡፡በ2012 በጀት ዓመት መምህራን የሚያነሷቸውን ጥያቄዎች ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለመመለስ እንደሚሰራ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስታውቋል፡፡በተለይም የመምህራንን ጉዳይ በተመለከተ ከመምህራን ማህበር ጋር በመተባበር ጥናት እየተካሄደ መሆኑንና ጥናቱ እንዳለቀ ውጤቱ ይፋ እንደሚደረግ መገለፁን ኢቢሲ ዘግቧል፡፡ | https://waltainfo.com/am/23903/ |
d29e0f0b1b91ffaf2cd10da2e064ab02 | 2eacd5ebc6be3325f77847443354970b | ኢትዮጵያ እና ቻይና በ300 ሚሊየን ዶላር አዲስ የኢንዱስትሪ ፓርክ ሊገነቡ ነው | ቢዝነስ | ኢትዮጵያ እና ቻይና በ300 ሚሊየን ዶላር የጋራ ወጭ በአዳማ የኢንዱስትሪ ፓርክ ሊገነቡ ነው።በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ የኢኮኖሚ እና ንግድ ጉዳዮች ተጠሪ ሊው ዩ፣ በአዳማ የሚገነባው አዲሱ የኢንዱስትሪ ፓርክ በያዝነው የፈረንጆች 2019 ዓመት ከመጠናቀቁ አስቀድሞ ሊጀመር ይችላል ሲሉ ተናግረዋል።85 በመቶ የኢንዱስትሪ ፓርኩ ግንባታ ወጭ ከቻይና መንግሥት በሚገኝ ዝቅተኛና በተራዘመ ጊዜ በሚከፈል የብድር ወለድ የሚሸፈን መሆኑን ተናግረዋል። ቀሪው 15 በመቶ ደግሞ በኢትዮጵያ መንግሥት እንደሚሸፈን ተገልጿል።የሚገነባው ፓርክ በዋናነት መሣሪያዎችን የሚያመርቱ ኢንዱስትሪዎችን ታሳቢ ያደረገ ነው ያሉት ሊው፣ በአሁኑ ወቅት መሬት እና ገንዘብ ማግኘት ጋር የተያያዙ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል።በቻይና ድጋፍ እና ሞያዊ እገዛ የሚገነባው አዲሱ ፓርክ ለአዳማ ከተማ ሁለተኛው ይሆናል።የቻይና እና የኢትዮጵያ መንግሥት የኢንዱስትሪ ፓርኮች ግንባታ ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ውጤታማ የሆነ ጠንካራ ግንኙነት አላቸው ሲሉም ሊው ተናግረዋል። (ምንጭ:-ሽንዋ) | https://waltainfo.com/am/23905/ |
1937191123647ad2a6580151d7877838 | d484e2ab3c0336c8e2ddb2dd0564915f | በአዲስ አበባ ከመስመር ጥገና ጋር ሳምንቱን ሃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች ይፋ ተደረጉ | ቢዝነስ | የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በዚህ ሳምንት በመዲናዋ ከመስመር ጥገና ጋር በተያያዘ ሃይል የሚቋረጥባቸውን አካባቢዎች ይፋ አደርጓል፡፡በዚህም መሰረት ረቡዕ ነሃሴ 8 ቀን 2011 ዓ.ም በቸራልያ ፋብሪካ፣ በገነት መናፈሻ ኮንደሚኒየም፣ በማሩ ብረታ ብረት፣ በወህኒ ቤት ጀርባ፣ በቂሊንጦ ማረሚያ፣ በሳሪስ አቦ ቤተክርስቲያን፣ በቦሌ ቡልቡል ኮንዶሚኒየም፣ በቡልቡላ ማርያም ማዞሪያ፣ በክሬሸር፣ በባሌስትራ ፋብሪካ፣ በጎፋ ካምፕ ኮንደሚኒየም፣ በመካኒሳ፣ በከፍያለው መድሀኒት ማከፋፈያ፣ በቫቲካን ኤምባሲ፣ በመካኒሳ አቦ ቤተ ክርስቲያን፣ በቄራ ይመስገን ጋራዥ እና በአካባቢዎቻቸው ከጠዋቱ 1 ሰዓት እስከ ቀኑ 6 ሰዓት ድረስ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ይቋረጣል፡፡በተመሳሳይ ቀን ከጠዋቱ 1 ሰዓት እስከ ቀኑ 9 ሰዓት ድረስ በቡና ቦርድ፣ በምርጫ ቦርድ፣ በዳችያ፣ በጎፋ መብራት ኃይል፣ በአየር መንገድ፣ በቦሌ ሚካኤል፣ በቦሌ ካርጎ፣ በማዕድን ማሕበር እና በአካባቢዎቻቸው ሃይል እንደሚቋረጥ ተገልጿል፡፡በማግስቱ ሐሙስ ነሃሴ 9 ቀን 2011 ዓ.ም በእሕል በረንዳ፣ በአውቶብስ ተራ፣ በአዲስ ከተማ ትምህርት ቤት፣ በገነሜ ትምህርት ቤት፣ በአማኑኤል ቤተ ክርስቲያን፣ በሻወል ደማ ትምህርት ቤት፣ በሰባተኛ ትራፊክ መብራት፣ በዶሮ ተራ፣ በጦር ሀይሎች፣ በመኮንኖች ክበብ፣ በቶሎሳ ሰፈር፣ በገዳመ እየሱስ፣ በወንድማማቾች፣ በሜክሲኮ፣ በፍሬህይወት ትምህርት ቤትና አካባቢዎቻቸው ከጠዋቱ 1 ሰዓት እስከ ቀኑ 10 ሰዓት ድረስ ሃይል አይኖርም፡፡አርብ ነሃሴ 10 ቀን 2011 ዓ.ም ደግሞ በለቡ፣ በጆሞ 1 በከፊልና አካባቢዎቻቸው ከጠዋቱ 1 ሰዓት እስከ ቀኑ 9 ሰዓት ድረስ በከፍተኛ የኤሌክትሪክ መስመር የማሻሻያ ስራ ለማከናወን ሲባል የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሚቋረጥ በመሆኑ ደንበኞች ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ተቋሙ አሳስቧል። | https://waltainfo.com/am/23904/ |
6bb5edce8532d5d7bcb5c5e0fbd7267a | 916f153ec93c616eaa02be79001eb6bc | ትራምፕ ሕጋዊ ስደተኞች የሚያገኙትን የምግብ ድጋፍ ለማስቀረት አልመዋል ተባለ | ሀገር አቀፍ ዜና | የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ሕጋዊ ስደተኞች የሚያገኙትን የምግብ ድጋፍ ለማስቀረት አልመዋል ተባለ፡፡አስተዳደሩ ያጡ የነጡ ሕጋዊ ስደተኞች ቪዛቸውን ለማራዘም አልያም ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ (ግሪን ካርድ) ለማግኘት የሚያደርጉትን ጥረት ከባድ ለማድረግ እየሠራ መሆኑ ነው የተገለጸው።መመሪያው ታላሚ ያደረገው የምግብ፣ የመኖሪያ ቤት ድጋፍ ከአንድ ዓመት በላይ እያገኙ የሚቆዩ ሕጋዊ ስደተኞችን ነው።መንግሥት ከዚህ በኋላ እነዚህን ድጋፎች ማግኘት አትችሉም ብሎ ከወሰነ ማመልከቻቸው ውድቅ እንዲሆን ይደረጋል ተብሏል።ባለስልጣናት መመሪያው "ራስን መቻልን" ያበረታታል ሲሉ ተናግረዋል።ይህ አዲሱ መመሪያው "ፐብሊክ ቻርጅ ሩል" የሚሰኝ ሲሆን፣ በጥቅምት ወር አጋማሽ ሥራ ላይ መዋል ይጀምራል ነው የተባለው።በዚህ ሕግ በአሜሪካ በቋሚነት እየኖሩ ያሉ ስደተኞች ላይጎዱ ይችላሉ፤ እንዲሁም ጥገኝነትና መጠለያ የጠየቁትን አይመለከትም ተብሏል።ነገር ግን ቪዛቸው እንዲራዘምላቸው የጠየቁ፣ ግሪን ካርድ ወይንም የአሜሪካ ዜግነት ለማግኘት ያመለከቱ ላይ ተፈፃሚ የመሆን እድል አለው።የገቢ ደረጃቸው ከሚጠበቀው በታች የሆነ ወይንም እንደ መኖሪያ ቤትና ሕክምና የመሳሰሉ ጥቅማ ጥቅሞች ላይ ሕይወታቸውን የመሰረቱ ወደፊት ወደ ሀገሪቱ እንዳይገቡ ሊታገዱ ይችላሉ።በአሜሪካ ውስጥም ያሉ ግለሰቦች ማመልከቻቸው ውድቅ ሊደረግ እንደሚችልም ተገልጿል።በአሜሪካ 22 ሚሊየን ይሆናሉ ተብለው የተገመቱ ሕጋዊ ስደተኞች ያለ ዜግነት የሚኖሩ ሲሆን፣ ከእነዚህ አብዛኞቹ በዚህ መመሪያ መሰረት ሊጎዱ ይችላሉ ተብሏል።የመብት ተሟጋቾች መመሪያው ያጡ የነጡ ስደተኞች ላይ ፍትሀዊ ባልሆነ መልኩ ትኩረት ተደርጎባቸዋል ሲሉ ተናግረዋል።የብሔራዊ ስደተኞች የሕግ ማዕከል የተሰኘ ተቋም ይህ መመሪያ ስራ ላይ እንዳይውል የትራምፕ አስተዳደርን ከስሼ ሕግ ፊት አቆማቸዋለሁ ሲል ተናግሯል።ነገር ግን ዋይት ሐውስ ይህ ስርዓት "ራሳቸውን በገቢ የቻሉና የመንግሥትን ድጋፍ ከማይጠብቁ ይልቅ" አሜሪካ ቤተሰብ ያላቸው ስደተኞችን የሚደግፍ ነው ሲል ተናግሯል። (ምንጭ፡-ቢቢሲ) | https://waltainfo.com/am/34126/ |
168c09c90953d1f18442dd0668d4f3ad | 23458bd38566a80b1e008cc93ceb9587 | ተቋማት ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምር በማካሄድ አምራች ኢንዱስትሪውን መደገፍ እንዳለባቸው ተገለፀ | ቢዝነስ | ኢንስቲትዩቶች ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምር በማካሄድ አምራች ኢንዱስትሪውን መደገፍ አለባቸው ሲል ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ሚኒስቴር በመስሪያ ቤቱ የ2011 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸሙን በስሩ ካሉ 15 ተጠሪ ተቋማት አመራሮች ጋር በቢሾፍቱ ከተማ እየገመገመ ይገኛል፡፡የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/እግዚአብሔር ኢንስቲትዩቶች ኢንዱስትሪውን በሚፈለገው ደረጃ እየደገፉ አይደለም ብለዋል፡፡ኢንስቲትዩቶች ሲቋቋሙ ዋና ተልኳቸው ጥናት በማካሄድ ኢንዱስትሪውን ማሳደግ ስለሆነ ወደዚህ መደበኛ ስራቸው ገብተው ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምር ማካሄድ እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡የወጪ ንግድ ችግሮችን በመለየት የአገራትን የገበያ ፍላጎት እንዲሁም የአገር ውስጥ ምርቶች ገበያ የሚያገኙበትን አገራት መለየት የሚሉትን በማጥናት ለኢንዱስትሪው የመፍትሄ ምንጭ መሆን አለባቸው ብለዋል ሚኒስትሯ፡፡በሌላ በኩል ኢንስቲትዩቶች የራሳቸው ቢሮና የጥናትና ምርምር ቦታ እንዲኖራቸው ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ድጋፍ ያደርጋል ተብሏል፡፡በተጨማሪም የአገሪቷን አጠቃላይ ትራንስፎርሜሽን እውን ለማድረግ በአምራች ኢንዱስትሪው ሴክተር ለውጥ ማምጣት ይገባል የተባለ ሲሆን ለዚህም በዘርፉ ያላውን የስራ ባህል መቀየር እንደሚያስፈልግ ተነግሯል፡፡ምንጭ፦ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር | https://waltainfo.com/am/23906/ |
7823ee84864a9fd394601bc370104dea | 4cf59b6b3bc6440ca21fc649bd7ffa90 | የሱዳን የቀድሞ የመረጃና ደህንነት ኃላፊ ሳላህ ጎሽ ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ ታገዱ | ፖለቲካ | የሱዳን የቀድሞ የመረጃና ደህንነት ኃላፊ ሳላህ ጎሽ ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ መታገዳቸው ተገለፀ።የቀድሞ ኃላፊው ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ የታገዱት በሰብአዊ መብት ጥሰት እጃቸው አለበት በሚል ሲሆን፣ እርሳቸው ብቻም ሳይሆኑ ቤተሰባቸውም ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ እገዳው ተጥሎባቸዋል ነው የተባለው።የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያወጣው መግለጫ እንደሚያትተው የቀድሞ ኃላፊው ሳላህ፤ የሱዳን ብሔራዊ የፀጥታና ደህንነት ኃላፊ በነበሩበት ወቅት ሰዎችን በማሰቃየት እጃቸው እንዳለበት ተጨባጭ ማስረጃ አለኝ ብሏል።የቀድሞ የአገሪቷ ፕሬዝዳንት ኦማር አል በሽር ከሥልጣን እስከተወገዱበት ሚያዚያ ወር ድረስ ከመረጃና ደህንነት ኃላፊው ሳላህ ጋር ጥብቅ ግንኙነት እንደነበራቸው ተገልጿል።እርሳቸው ከሥልጣን ከወረዱ በኋላ በተቃዋሚዎች ግፊት ምክንያት ኃላፊነታቸውን ለቀዋልም ነው የተባለው።የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማይክ ፖምፔዮ፤ ሱዳን በሲቪል የሚመራ መንግሥት እንዲኖራት ድጋፋቸውን እንደሚያደርጉ በትዊተር ገፃቸው ላይ መልእክታቸውን አስፍረዋል።አሁን ሃገሪቷን እያስተዳደረ ያለው ምክር ቤት እና የተቃዋሚዎች ጥምረት በሦስት ዓመታት የሽግግር ጊዜ ስለሚኖራቸው ኃላፊነት ከአስር ቀናት በፊት መፈራረማቸው የሚታወስ ነው።በሚኖራቸው የሥልጣን ክፍፍል ላይም ለመጨረሻ ጊዜ በመጭው ቅዳሜ እንደሚፈራረሙ ይጠበቃል። (ምንጭ፡-ቢቢሲ) | https://waltainfo.com/am/33322/ |
39da955487cbf1bc13051130a1f782f9 | b4aed99dad09ad7d689b55a8e8a90d94 | የመከላከያ አባላት ያላቸውን የላቀ ስብዕና እና የአገር ፍቅር ለተተኪ ማስተላለፍ እንደሚገባቸው ተገለፀ | ፖለቲካ | የመከላከያ አባላት ያላቸውን የላቀ ስብዕና እና የሀገር ፍቅር ለተተኪ ማስተላለፍ እንደሚገባቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ገለፁ።የመከላከያ አዛዥነት ስታፍ ኮሌጅ ለ13ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን 100 የሚሆኑ ከፍተኛ መኮንኖች ዛሬ በታላቁ ቤተ መንግስት አስመርቋል።የመከላከያ አዛዥነት ስታፍ ኮሌጅ ዛሬ ካስመረቃቸው 100 ከፍተኛ መኮንኖች ውስጥ 92 ፖስት ስታፍ እና ስምንት የሁለተኛ ዲግሪያቸውን የተከታተሉ ሲሆኑ 21 ተመራቂዎች ከጎረቤት አገሮች መሆናቸው ተገልጿል።ኮሌጁ ዛሬ ካስመረቃቸው ተመራቂዎች የጎረቤት አገራት ጅቡቲ፣ ሶማሊያ እና ደቡብ ሱዳን የተውጣጡ ከፍተኛ መኮንኖች መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።በምርቃት ሥነ ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው የሥራ መመሪያ የሰጡት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዶክተር አብይ አህመድ የወታደር መኮንን መሆን ድርብ ኃላፊነት መሆኑን ተናግረዋል።በተለይም ለተመራቂ የኢትዮጵያ መኮንኖች የአገሪቱን ታሪክ የህዝቦችን ባህል፣ ማንነትና ድንበር ጠንቅቀው በማወቅ የላቀ ስብዕናን በመገንባት ለተተኪ ትውልድ ማስተላለፍ እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።የመከላከያ አባላት ያላቸውን የላቀ ስብዕና እና የአገር ፍቅር ስሜት ለተተኪ ማስተላለፍ እንደሚገባቸውም አክለዋል።አባላቱ የፖለቲከኞች ሽኩቻ ሳይወስዳቸው ከወረዱ ዘረኞችና ደካሞች ጋር ሳይወርዱ ለኢትዮጵያ አንድነት እና ለህዝቦች እኩልነትና ደህንነት እንደሚሰሩ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።በመጨረሻም መከላከያን የማዘመን ሥራ በሁሉም ተቋማቶች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለአብነትም ዘመናዊ ጀቶችና ሄሊኮፕተሮች፣ ሰው አልባ ሚሳኤል እና የሳይበር ስራዎች ላይ የማዘመን ስራ በፍጥነት እንደሚሰራ ጠቁመዋል።ለመከላከያ አባላት የሚሰጠው ከስልጠና እስከ ትጥቅ የማዘመን ሥራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተመራቂዎች ተረድተው ለቀጣይ አዳዲስ ስልጠና እና ትምህርት ራሳቸውን ዝግጁ እንዲያደርጉም ጠይቀዋል።የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄነራል አደም መሀመድ በበኩላቸው መከላከያ የሰራዊቱን ተልዕኮ የመፈፀም አቅም እና ብቃት ለማሳደግ የሚያስችለው የሪፎርም ሥራ ላይ እንደሚገኝ አንስተዋል።ከዚህ ውስጥ የመከላከያ አዛዥነት ስታፍ ኮሌጅ አንዱ በመሆኑ ዛሬ የተመረቁ ከፍተኛ መኮንኖች የተጀመረውን ተቋማዊ ሪፎርም ከግብ ለማድረስ ሚናቸው የጎላ መሆኑን አንስተዋል።ተመራቂ ከፍተኛ መኮንኖች በበኩላቸው የተሰጣቸውን ህገ መንግስታዊ ተልዕኮ ለመወጣት ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ ሆነው ለህገ መንግስቱና ህገ መንግስታዊ ሥርዓቱ ዘብ እንደሚቆሙ አረጋግጠዋል።ተመራቂ ከፍተኛ መኮንኖቹ በኮሌጁ ያገኙትን የወታደራዊ ሳይንስና አመራር ተጠቅመው ህገ መንግስታዊ ግዳጆችን በስኬት ለማጠናቀቅ ያላቸውን ዝግጁነት ገልፀዋል።/ኢዜአ | https://waltainfo.com/am/31286/ |
c1c8eada2bc0d2a79e99be4ac50ccbdd | 024a43f4b2b2937220217bbc64b7304b | የሊቢያ ተዋጊዎች የኢድ በአልን በማስመልከት ጊዜያዊ የእርቅ ስምምነት አደረጉ | ፖለቲካ | የሊቢያ ዋነኛ ተቀናቃኝ ተዋጊ ቡድኖች ለሶስት ቀናት የሚከበረው የኢድ አል አድሃ በዓልን በማስመልከት ጊዜያዊ ስምምነት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።ይህንንም ውሳኔ የተባበሩት መንግሥታት ይበል የሚያሰኝ ነው ብሎታል።ቅዳሜ እለት ቤንጋዚ ላይ በደረሰ የቦምብ ጥቃት ሶስት ሰራተኞቹን ያጣው የተባበሩት መንግሥት ድርጅት በዚህ የሰላም ስምምነትም እንደ አንድ አደራዳሪ ሆኖ ቀርቧል።በዚህ ስምምነት ላይ በሊቢያ መዲና ትሪፖሊ ከፍተኛ ጥቃትን ሲፈፅም የነበረው ወታደራዊ ኃይል ኃላፊ ጄኔራል ካሊፋ ሃፍተር ዋነኛ ተደራዳሪ ናቸው።የአለም ጤና ድርጅት እንደዘገበው ከሚያዝያ ጀምሮ በነበረው ጥቃት አንድ ሺ ሰዎች ተገድለዋል።"ጄኔራሉ ለእርቁ የተስማሙት ሊቢያውያን የኢድን በአል በሰላም እንዲያከብሩ ነው" በማለት ቃል አቀባያቸው አህመድ አል ሜስማሪ ገልጿል።እርቁ ቅዳሜ ከ9 ሰአት የጀመረ ሲሆን፣ ሰኞ እስከ ከሰአትም እንደሚቀጥል ቃል አቀባዩ አክለው ተናግረዋል።ኢድ አል አድሐ በመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ አምላክ ለአብርሃም በህልም ተገልፆ አንድ ልጁን እንዲሰዋ ትእዛዝ ካስተላለፈለት በኋላ፤ መስዋእቱን ለማድረግ በሚዘጋጅበት ወቅት በግ የላከበትን ቀን የሚታወስበት ነው።በመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ 1 ሺህ 440ኛው ዓመተ ሒጅራ የኢድ አል አድሐ አረፋ በዓል በትላንትናው ዕለት ተከብሮ ውሏል፡፡ (ምንጭ፡-ቢቢሲ) | https://waltainfo.com/am/33321/ |
e15862a02f9b735077bcb2015bde8723 | cd348ec86efbab2724ed4a846c717983 | በመዲናዋ 98 ሺ ለሚልቁ ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው | ሀገር አቀፍ ዜና | በአዲስ አበባ ከተማ በጎ ፈቃደኞች የማጠናከሪያ ትምህርትና በስፖርት፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂና በስነ ጥበብ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ ስልጠናዎችን ከ98 ሺህ በላይ ለሆኑ ተማሪዎች እየሰጡ መሆኑን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ቢሮ አስታወቀ።የቢሮ የበጎ ፈቃድ ዳይሬክተር አቶ አክሊሉ ትዕዛዙ እንደገለጹት÷ በ114 ትምህርት ቤቶች ከ5ኛ ክፍል እስከ 10 ክፍል ላሉ 62 ሺህ 700 ተማሪዎች በተለያዩ የትምህርት መስኮች የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ይገኛል።በተጨማሪም በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በኪነ ጥበብ፣ በስፖርትና ኢትዮጵያዊነት ዙሪያም ለ36 ሺህ ተማሪዎች ለሁለት ወራት ስልጠና እየተሰጠ ነው።ወጣቱ ትውልድ የኢትዮጵያ ታሪክና ባህላዊ እሴቶችን የሚያትቱ መፅሀፎችን ከማንበብ ይልቅ በማህበራዊ ሚዲያዎች ተጠምዶ የሚውል መሆኑን ዳይሬክተሩ አመልክተው ስለ ኢትዮጵያዊነት የሚሰጠው ስልጠናም ወጣቱ በስሜት የሚነዳ ሳይሆን ምክንያታዊ ትውልድ ለመፍጠር እንደሚረዳ አመልክተዋል።የበጎ ፈቃድ ትምህርትና ስልጠና ከሚሰጥባቸው ትምህርት ቤቶች መካከልም ዳግማዊ ምኒልክ፣ ጥቁር አንበሳ፣ ኮከበ ጽባህ እንደሚገኙባቸው ጠቅሰዋል።ትምህርቱ እስከ ነሀሴ 30 ቀን 2011 ዓ.ም ድረስ የሚሰጥ መሆኑ መገለፁን የኢትዮጵያ ፕረስ ድርጅ ዘገባ ያመለክታል፡፡ | https://waltainfo.com/am/32645/ |
7712f953b40851d6e95fc0f558b85a86 | 7478d39879e0dfe8162d281cd2577b97 | ሚኒስትሯ በአዲስ አበባ እየተሰሩ ያሉ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ | ቢዝነስ | የትራንስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ፣ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሙሉ ገ/እግዚአብሔር እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባና የትራንስፖርት የቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሰለሞን ኪዳነ እና ሌሎችም በመዲናዋ የትራንስፖርት ቢሮ እየተሰሩ ያሉ ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።በጉብኝቱ የመርካቶ አውቶብስ ተርሚናል በአንድ ጊዜ 20 አውቶብሶችን በማስተናገድ እስከ 2 ሺህ ሰው የመጫን አቅም ያለው መሆኑ ተገልጿል።ተርሚናሉ ለአካል ጉዳተኞች የሊፍት አገልግሎት እንዲሰጥ ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑም በጉብኝቱ ወቅት ተብራርቷል፡፡
ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅም በሰዓት 6 ሺህ ተጠቃሚዎችን ማስተናገድ እንደሚችልም ነው የተገለፀው።የሸጎሌ እና የቃሊቲ አውቶብስ ተርሚናሎችም በጥሩ አፈፃፀም ላይ እንደሚገኙና የአውቶብስ ዴፖዎቹ የራሳቸው የጥገና ማዕከል፣የነዳጅ ማደያ፣ ዘመናዊ የመኪና የማጠቢያ ቦታና ሰፊ የማቆሚያ ቦታ እንዳላቸው ተገልጿል፡፡ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ የከተማ አስተዳደሩ የትራንስፖርት ቢሮ ኘሮጀክቶችን በቅርበት በመከታተል በወቅቱ ተጠናቀው ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጡ ላደረጉት ከፍተኛ ጥረት ምስጋና አቅርበዋል።ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሙሉ ገ/እግዚአብሔርም በበኩላቸው ይህ ትልቅ ውጤትና ጅማሮ በሌሎች የሀገራችን ክፍሎችም ሊስፋፋና ህብረተሰቡም እንዲያውቀዉ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ ሊሰራ ይገባል ማለታቸውን ከትራንስፖርት ሚኒስቴር የተገኘነው መረጃ ያመለክታል። | https://waltainfo.com/am/23901/ |
f1f722ca3b44cf3af8faf8644b9da77a | 4879360e7096f36e9eb3b0f426787ea7 | በእስያ የደረሰው የጎርፍ አደጋ የበርካቶችን ህይወት ቀጥፏል ተባለ | ሀገር አቀፍ ዜና | በእስያ የደረሰው የጎርፍ አደጋ የበርካቶችን ህይወት መቅጠፉ ተገለጸ፡፡በ10ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችም በጊዜያዊ መቆያ ጣቢያዎች ኑሮአቸውን ለመመስረት ተገደዋል ነው የተባለው፡፡ምንም እንኳን ቻይና በጎርጎሮሳውኑ 2019 ብቻ 9 አውሎ ንፋስ ብታስተናግድም የቻይናው የዜና አውታር ሽንዋ ይዞት በወጣው መረጃ መሰረት ሊኪማ የተሰኘው የአሁኑ አውሎ ንፋስ ግን በሀገሪቱ ታሪክ በአመታት የታየው ከባዱ አውሎ ንፋስ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ በገንግ ዡ ከተማ ዤጀንግ ግዛት በአውሎንፋሱ ሳቢያ ተፈጥረው እንዳሻቸው የሚተሙ ወንዞች ያገኙትን እየጠራረጉ መውሰዳቸውን ቀጥለዋል፡፡በግዛቲቷ የተሰማሩ የነፍስ አድን ሰራተኞችም ሰዎችን ከጎርፍ አደጋው ለመታደግ ህይወትን እሰከማጣት የሚያደርስ ተግባር በጀግንነት ሲከውኑ ተስተውለዋል፡፡በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎችም ቤታቸውን ለቀው እንዲወጡ ተደርገዋልም የተባለው፡፡ምንም እንኳን ማእበሉ የመቀነስ አዝማሚያ ቢታይበትም ወደ ቻይናዋ ቅንጡ ከተማ ሻንጋይ ግን መገስገሱን አሁንም አላቆመም ተብሏል፡፡አስቸጋሪው የአየር ጸባይ በቻይና ብቻ ሳይገታ ጉዞውን ወደ ሌሎችም የእስያ ክፍሎች በማድረግ በፓኪስታኗ ካራቺም መዳረሻውን አድርጓል፡፡ጥቂት የማይባሉ ሰዎችም በሀገራቸው መንግስት ላይ ቁጣቸውን እየገለጹ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡በቻይና ሊኪሚያ በተሰኘው አውሎ ንፋሰአዝ ሳቢያ በትንሹ 36 ሰዎች ሲሞቱ፣ በፓኪስታን እና ህንድ ደግሞ መነሻውን ከውቂያኖስ ያደረገ ነፋስ ባስከተለው ከባድ ዝናብ ምክኒያት ከ160 በላይ ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡165ሺ የሚጠጉት ሰዎች ደግሞ ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለው መጠለያ ጣቢያ ውስጥ ለመጠለል መገደዳቸውን አልጀዚራ በዘገባው አመላክቷል፡፡ | https://waltainfo.com/am/34125/ |
e489522bbe940cb7588749fde642f730 | 3bc9ae773b775ca0df8d5e347aad23fd | 1 ሺህ 440ኛው የአረፋ በዓል በመላ ሀገሪቱ ተከበረ | ሀገር አቀፍ ዜና | የ1440ኛው የዒድ አልአድሀ (አረፋ) በዓል በመላ አገሪቱ በደማቅ ስነ ስርዓት ተከበረ፡፡የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ተወካይ ሼህ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ በበዓሉ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ለአገራችን አንድነትና ለሰላም፣ ለአብሮነት በጉልበታችን፣ በእውቀታችንና በገንዘባችን የሚፈለግብንን ሁሉ ማበርከት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡በበዓሉ ላይ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሱልጣን አማን ኤባ በበኩላቸው፣ የአረፋ በዓል ለመላው የሙስሊም ማህበረሰብ የሰላም፣ የፍቅርና የመተሳሳብ እንዲሆን ተመኝተዋል፡፡ሼህ ሱልጣን አማን ኤባ የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ አስተዳደር የሙስሊሙን ጥያቄ ለመመለስ የሚያደርገው ጥረት የሚያበረታታ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም በዘላቂነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡የአዲስ አበባ ከተማ ም/ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ተወካይ አቶ ዮሃንስ ምትኩ በዓሉ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ የዘንድሮን የዒድ አልአድሀ በዓል ልዩ የሚያደርገው የሙስሊሙ አንድነት ከወትሮው በተለየ መልኩ የተጠናከረበት፣ በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድና በሃይማኖት አባቶች ያጋራ ጥረት በሰላማዊ መንገድ ልዩነቶች የጠበቡበትና መቻቻል በታየበት ወቅት በድምቀት መከበሩ ነው ብለዋል፡፡(ኢቢሲ) | https://waltainfo.com/am/32644/ |
086a4d54244921a355d2014ffbcdf2a5 | ca5fe93a994865fe53497ca156b555e7 | የኢትዮጵያ መድን ድርጅት ለመቄዶንያ የ155 ሚሊየን ብር የአደጋ ስጋት የመድህን ሽፋን ሰጠ | ሀገር አቀፍ ዜና | የኢትዮጵያ መድን ድርጅት ለመቄዶንያ አረጋዊያንና አዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የ155 ሚሊየን ብር የአደጋ ስጋት የመድህን ሽፋን ሰጥቷል፡፡የድርጅቱ አመራሮችና ሰራተኞች የአረጋዊያኑን መርጃ ማዕከል በጎብኙበት ወቅት የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ነፃነት ለሜሳ እንዳሉት መርጃ ማዕከሉ ቀጣይነት ያለው አገልግሎት መስጠት እንዲችል ዘላቂ የመድህን ዋስትና ሽፋን እንዲያገኝ ጥረት እየተደረገ ነው ፡፡ማዕከሉ ለሚያስገነባው ሆስፒታል፣ ሰራተኞች እንዲሁም ተሽከርካሪዎች የሚሆን 155 ሚሊየን ብር የሚደርስ የአደጋ ስጋት የመድህን ሽፋን መስጠቱን አቶ ነፃነት ገልፀዋል፡፡የኢትዮጵያ መድን ድርጅት ከዚህ በፊትም ለመቄዶኒያ የአረጋዊያንና አዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የተለያዩ ድጋፎችንና የመድህን ሽፋን መስጠቱ ይታወሳል፡፡ | https://waltainfo.com/am/32641/ |
8f18389f882b70166507b69412d17a42 | de1f7f7d336274e4e7d6ab47a00a8652 | አዲስ ወግ ውይይት በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት እየተካሄደ ነው | ቢዝነስ | አዲስ ወግ የውይይት መድረክ “አንድ ጉዳይ የምጣኔ ሃብት ሪፎርም መነሻና አቅጣጫ” በሚል ርዕስ በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡በመድረኩ ባለፉት 17 ወራት የተተገበሩ አንኳር የማሻሻያ ስራዎችን በተመለከተ የፋይናንስ ሚኒስትሩ ከፍተኛ አማካሪ ብሩክ ታዬ ማብራሪያ ሰጥተዋል።ዘላቂ መፍትሄ የሚሹት እንደ የዋጋ ግሽበት፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረትና የብድር አከፋፈል ችግሮችንና ልሎችንም ለመፍታት የመንግስት የልማት ድርጅቶችን ወደ ግል ለማዞር እንቅስቃሴዎች መደረጋቸውን አስታውሰዋል።ለዚህም ሲባል ከአበዳሪዎች ጋር በመደራደር እፎይታ ለማግኘት የሚያስችሉ ስልቶችን ተግባራዊ ማድረግ፣ ያላለቁ የመንግስት የልማት ድርጅቶችን ማጠናቀቅ እንዲሁም ሕጎችን የማብላላትና የመከለስ ስራዎች መሰራታቸውን አንስተዋል።በወጭ ንግድ ላይ አለም አቀፍ አሰራርን የመረዳት ክፍተት ችግሮች ባጋጠሙ ወቅት ሙሉ በሙሉ መርምሮ የመረዳት አቅም ማዳበር አለመቻሉን ያነሱት የንግድ እንደራሴው አቶ ብሩክ ፍቅሩ÷የሕግና የአሰራር ማዕቀፎች ባለሃብቶችንና የተወሰኑ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ብቻ ሳይሆን ግለሰቦችንም መሰረት ያደረጉ እንዲሆኑ መስራት ይገባል ብለዋል፡፡አዲስ ወግ የውይይት መድረክ ከአዲስ አበባ ውጭ ለመጀመሪያ ጊዜ በድሬዳዋ ከተማ በቅርቡ መካሄዱ ይታወሳል፡፡ | https://waltainfo.com/am/23902/ |
6e1292a8d0fd2c5d37ed741f0124e14b | 719fb1741c7433e2c8939804642b0a56 | የወሳን ኩነት ምዝገባ የዜጎችን ህገ መንግስታዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ነው- ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ | ሀገር አቀፍ ዜና | ሁለተኛው ሃገር አቀፍ የወሳኝ ኩነት ምዝገባና ስታቲስቲክስ ቀን ከተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ሃላፊዎች እና የሚመለከታቻው አካላት በተገኙበት ተከብሯል፡፡“የልደት ምስክር ወረቀት ለሰብዓዊ መብቶች መከበርና አድሏዊ አሰራርን ለማስወገድ መሰረት ነው” በሚል መሪ ቃል ነው የተዘጋጀው፡፡በዝግጅቱ ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ የወሳን ኩነት ምዝገባ ዜጎች ህገ መንግስታዊ መብታቸውንና ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን የሚረጋግጥ ነው ብለዋል፡፡የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ዘይኑ ጀማል በበኩላቸው ከልደት እና ሞት ጋብቻ እና ፍቺ ምዝገባ የሚገኘው መረጃ ለሃገሪቱ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ተግባራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልፀዋል፡፡የኢሚግሬሽን፣ ዜግነት እና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙጂብ ጀማል በዓለም ከ1 ቢሊየን ሰዎች በላይ የማንነት መታወቂያ ሰርተፊኬት እንደሌላቸው በመግለፅ÷ በኢትዮጵያም 65 በመቶዎቹ ህጋዊ መታወቂያ እንደሌላቸው ነው የገለፁት፡፡ለሚቀጥለው የትምህርት ዘመን የሚመዘገቡ ተማሪዎችም ምዝገባቸው ያለምንም ክፍያ የሆኑ በልደት የምስክር ወረቀት እንዲመዘገቡ እንደሚደረግም አክለዋል፡፡በ2063 የተያዘው ዘላቂ የልማት ግቡን ለማሳካት በህብረተሰቡ ዘንድ ግንዛቤ መፍጠር እንደሚያስፈልግም ነው የገለፁት፡፡በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት የህፃናት መርጃ ድርጅት ዩኒሴፍ ዳይሬክተር አደል ሆደር በኢትዮጵያ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ከመጀመሩ በፊት የተወለዱ ጨቅላ ህፃናትን የማስመዝገብ ባህሉ 3 በመቶ ብቻ የነበረ ሲሆን÷ የወሳን ኩነት ምዝገባ ከተጀመረበት በሶስት ዓመታት ውስጥ ቁጥሩ ወደ 20 በመቶ ከፍ ማለቱን አንስተዋል፡፡በዝግጅቱልጆቻቸውን ለልደት ሰርተፊኬትያስመዘገቡ ወላጆችና አዲስ ጋብቻቸውን በወሳኝ ኩነት ያስመዘገቡ ጥንዶች ከፕሬዚዳንት ወ/ሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ የምስክር ወረቀት ተቀብለዋል፡፡ | https://waltainfo.com/am/32643/ |
1eda9f9c004de2e1ea700068b9f60aed | 45e8d4b246ef0790b961bd8f4dbb7ddf | ኢንጅነር ታከለ ኡማ ለቡ ቫርኔሮ አከባቢ ሰሞኑን በፈረሰው አሊፍ መስጅድ በመገኘት የሀይማኖት አባቶችን አነጋገሩ | ሀገር አቀፍ ዜና | የአዲስ አበባ ከተማ አስተደዳር ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማ ለቡ ቫርኔሮ አከባቢ ሰሞኑን በፈረሰው አሊፍ መስጅድ በመገኘት የሀይማኖት አባቶችን አነጋግረዋል፡፡ኢንጅነር ታከለ ኡማ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ከከተማ አስተዳደሩ እውቅና ውጪ የፈረሰውን የአሊፍ መስጅድ ጎብኝተዋል፡፡በዚሁ ጉብኝታቸውም ጥቂቶች በተንኮል ከሙስሊሙ ማህበረሰብ ጋር ሊያጋጩ እና በሴራ ሊበትኑ ቢያስቡም እኛ ግን ችግሮችን በተሻለ መንገድ እናልፋቸዋለን ሲሉ ተናግረዋል፡፡የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የማምለኪያ ቦታዎችን ችግር በዘላቂነት ለመቅረፍ ከሁሉም የእምነት ተቋማት ጋር በትብብር እየሰራ እንደሆነም ነው የተናገሩት፡፡መስጅዱን በማፍረስ የተሳተፉ አካላትን ተጠያቂ ከማድረግ ጎን ለጎንም መስጅዱን በተሻለ ሁኔታ ለመገንባትም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ 4 ሺህ ካሬ ሜትር ተለዋጭ ቦታም ለአዲስ አበባ መጅሊስ መተላለፉም ነው የተገለጸው፡፡ከተጀመረው የለውጥ ጉዞ የሚያስተጋጉሉንን ለመግታት አሁንም የጋራ ጥረታችን ሊቀጥል ይገባል ሲሉም መልዕክታቸውን ማስተላለፋቸውን ከከንቲባው ጽ/ቤት የተኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ | https://waltainfo.com/am/32640/ |
11277e57483664ef151377f8afb1c8e6 | 6b220bf48a36649c8313dcb57ae1e0bc | የግብርና ሚኒስቴር በ2011 በጀት ዓመት ለ1.3 ሚሊየን ዜጎች የገጠር ስራ ዕድል መፍጠሩን አስታወቀ | ቢዝነስ | የግብርና ሚኒስቴር በ2011 በጀት ዓመት ለ1.3 ሚሊየን የገጠር ስራ ዕድል መፍጠሩን አስታወቀ፡፡ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በ2011 በጀት ዓመት በግብርና፣ በማዕድን ማናፋክቸሪንግ እና በሌሎች አገልግሎት ሰጪ መስኮች ላይ 1.8 ሚሊየን የገጠር ስራ ዕድል ለመፍጠር አቅዶ 1.3 ሚሊየኑን ማሳካቱን አስታውቋል፡፡ሚኒስቴሩ በስራ እድል ፈጠራ ዙሪያ የ2011 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀምና የ2012 ዓ.ም የትኩረት አቅጣጫ ላይ በቢሾፍቱ ከተማ እየተወያየ ሲሆን፣ በባለፈው በጀት ዓመት በገጠር የስራአጥነት ችግርን ለመቅረፍ በተሰራው ስራ የእቅዱን 73 በመቶ ማሳካት አሳክቻለሁ ብሏል፡፡በዞን፣ ወረዳና ቀበሌ የአደረጃጀት እርከኖች ላይ የገጠር የስራ ዕድል ፈጠራ ባለቤት ማጣት በዘርፉ የሚታይ ዋነኛ ተግዳሮት እንደነበር በውይይቱ ላይ የተገለጸ ሲሆን፤ የአቅም ማነስ፣ ተደራሽ የሆነ የመረጃ አያያዝ ችግር፣ የገበያ ትስስር ማጣት እንዲሁም የባለድርሻ አካላት በቅንጅት አለመስራት በማነቆነት ተለይቷል፡፡በ2011 በጀት ዓመት የኦሮሚያ ክልል የዕቅዱን 83 በመቶ፣ የአማራ ክልል ደግሞ 81 በመቶ በማሳካት የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ ቀዳሚ ነበሩ ተብሏል።ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት በተግዳሮትነት የተመዘገቡ ማነቆዎችን በማቃለል በ2012 በጀት ዓመት በመላ ሀገሪቱ 1.7 ሚሊየን የገጠር ስራ ዕድል ለመፍጠር እንደሚሰራም አስታውቋል፡፡የግብርና ሚኒስቴር ከ2008 እስከ 2010 ዓ.ም በገጠር የስራ እድል ፈጠራ ዙሪያ ባደረገው የዳሰሳ ጥናት ስራ ፈላጊዎች በፍላጎታቸው ወደ ስራ ከመግባት ይልቅ መንግስት ባስቀመጣቸው አማራጮች መሳተፋቸው በውጤታማነታቸው ላይ ትልቅ ተጽዕኖ እንደፈጠረባቸውም ገልጿል፡፡በጥናቱ ከ2000 እስከ 2010 ዓ.ም በገጠር የስራ እድል ፈጠራ ከ3.8 ሚሊዮን በላይ የስራ እድል እንደተፈጠረም ተመላክቷል፡፡ | https://waltainfo.com/am/23899/ |
4c7868b0825318e0d526eee72fe5d565 | 3a5c448353b3182613eb201e15514ed3 | የአረፋ በዓል ሲከበር አቅመ ደካሞችን በማሰብና በመደገፍ ሊሆን ይገባል- ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጅ ዑመር | ሀገር አቀፍ ዜና | የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓል እምነቱ በሚያዘው መሰረት አቅመ ደካሞችን በማሰብና ያለው ለሌለው በማካፈል እንዲያከበር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጅ ዑመር ኢድሪስ አሳሰቡ።የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጅ ዑመር ኢድሪስ 1 ሺህ 440ኛውን የአረፋ በዓል አስመልክተው ለሕዝበ ሙስሊሙ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።ኢድ አል አድሃ አረፋ አላህ የነብዩ ኢብራሂምን ፍቅርና እምነት ለመፈተን ልጃቸውን ለመስዋዕትነት እንዲያቀርቡ ያዘዘበትን ዕለት ለማሰብ የሚከበር ሃይማኖታዊ በዓል ነው።ይህን ታሪክ ለመዘከር በዓሉ “የመስዋዕትነት በዓል” ተብሎ እንደሚጠራ የእምነቱ ሊቃውንት ያስረዳሉ፤ የእምነቱ ተከታዮችም የነብዩ መሃመድን ፈለግ ተከትለው በዕለቱ እርድ ይፈጽማሉ።ምዕመኑ በዓሉን ሲያከብርም እምነቱ በሚያዘው መሰረት አቅመ ደካሞችን በማሰብ፣ ያለውን በማካፈልና በማስደሰት መሆን እንዳለበት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።በአሁኑ ወቅት አንገብጋቢው ጉዳይ አንድነትና ሠላምን ማስጠበቅ መሆኑን የጠቀሱት ሃጅ ኡመር እድሪስ “በአገርም ሆነ በውጭ ያለን ሁሉ አንድነታችንንና ሠላማችንን ልንጠብቅ ይገባል” ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። (ምንጭ፡-ኢዜአ) | https://waltainfo.com/am/32638/ |
f78788af119e3c36a439c6ff430ee66e | 1da34c1e5f1b2d19dfde326b75b956df | የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ሲያካሂድ የነበረውን ስብሰባ አጠናቀቀ | ፖለቲካ | የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ሲያካሂድ የነበረውን ስብሰባ የተለያዩ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ አጠናቀቀ።የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው አባልና በኢህአዴግ ፅህፈት ቤት የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሲቪክ ጉዳዮች ሀላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ ለኢቢሲ እንደተናገሩት፥ ኮሚቴው በወቅታዊ የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የድርጅት ስራዎች እና የአመራር ቁመና ላይ ሀላፊነት በተሞላው መንገድ ህዝብና መንግስትን በሚያስቀጥል መልኩ ዝርዝርና ጥልቅ ግምገማዎችን አካሂዷል።በዚህ ድክመት ነው ያላቸውን በመለየት በዝርዝር መፍትሄዎችን ያስቀመጠው ኮሚቴው፥ ከሀገራዊ ለውጡ ጋር የመጡ በድክመት ያነሳቸውን ዝንባሌዎችን መመልከቱን ነው ያነሱት።ለውጡ ህዝቡ በሚፈልገው ደረጃ ወደፊት እንዲሄድ ህዝቡና ሀገሪቱ ወደሚፈለገው የከፍታ ደረጃ እንዲደርሱ የሚታትሩ እንዳሉ ሁሉ በለውጡ የቀድሞውን ይዞ የመቆዘም፣ ህዝበኝነት እና ወላዋይነት በአመረራር ደረጃ እንዳሉና ይህም የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች አንድ ሆነው በአንድ አቅጣጫና እና በተመሳሳይ ፍጥነት እንዳይሄዱ ማድረጉን በድክመት እንደገመገመ ገልፀዋል።በዚህ ላይም የጋራ ስምምነት መደረሱን በመጠቆም ከድርጅት በላይ ኢትዮጵያና ህዝቦቿ መቀጠል እንዳለባቸው በማንሳት ለውጡን በመምራት ሂደት በተሸለ መረጋጋት፣ መደማመጥ እና ሀላፊነት በሚሰማ አግባብ ግምገማውን መካሄዱን ነው አቶ ፍቃዱ የተናገሩት።በሀገር ደረጃ የሚስተዋለው የብሄር ፅንፈኝነት ለሀገራዊ አንድነት እና ለፌደራላዊትና ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ችግርና ተግዳሮት እንደሆነ በማንሳት መታገል እንደሚገባ ኮሚቴው ተመልክቷል።ማንነቶች መከበር ያለባቸው ቢሆንም ኢትዮጵያዊ ማንነትን አስታርቆና አቻችሎ ማስኬድ እንደሚገባ መነሳቱንና በማህበራዊ ሚዲያው ከሚንፀባረቁትና አመራሩም ከሚገዛቸው ፅንፈኝነት በመውጣት መታገል እንደሚገባ ዝርዝር ግምገማ ተካሂዷል ብለዋል።የህግ የበላይነትን ከማስከበር አንፃር ባለፉት ጊዜያቶች ህግና ስርዓትን ለማስከበር የህዝቡ የሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያው መብቶች ተገድበው እንደነበር ከዚህም ለመውጣት በህዝቡ ገፊነት ኢህአዴግ ለውጡን እዚህ ደረጃ ማድረሱን ተመልክቷል።ነገር ግን ህዝቡ ነፃነቱን አጠቃቀም ላይ ክፍተቶች መታየታቸውን በማንሳት ኮሚቴው በነፃነት እና በደህንነት መካከል ሚዛኑ መጠበቅ እንዳለበት በማንሳት ማንኛውም ጥያቄ በሰለጠነ እና በሰከነ መልኩ ለሀገር ያለውን ፋይዳ በመመልት የተሰጠውን መብት መጠቀም እንደሚገባ መገምገሙን ነው አቶ ፍቃዱ ያነሱት።ከዚህ ውጪ የሚሄዱ ህገውጥ፣ ስርዓት አልበኝነት እና በሀይል ማንኛውንም ለመፈፀም የሚደረጉ ነገሮች ዋጋ የሚያስከፍሉ በመሆናቸው እና ነፃነቱን የሚፈታተኑ በመሆናቸው እነዚህን ክፍተቶች ከህዝቡ ጋር በመሆን በውስጡም ያሉትን ጉድለቶች በማረም የህግ የበላይነትን ሳይደራደር ማስከበር አለበት የሚል ድምዳሜ በግምገማው መደረሱን አስታውቀዋል።በለውጡ ላይ ያለውን ብዥታ የተመለከተው ኮሚቴው ለውጡ በህዝብ ግፊት ኢህአዴግ በውስጡ በወሰዳቸው እርምጃዎች የመጣ መሆኑን በማስመር ሁሉም በለውጡ ውስጥ ድርሻ እንዳለው ተመልክቷል።ኮሚቴው በግምገማው የደረሰባቸውን ድምዳሜዎች ያብራሩት አቶ ፍቃዱ፥ አንዱ ድምዳሜ እንድነትን የሚንዱ ነገሮች መታረም እንዳለባቸው የሚመለከተው ነው ብለዋል።በብሄራዊ ድርጅቶች መካከል በጋራ ያሳለፏቸው መልካም ነገሮች በጋራ የከፈሏቸው መስዋእቶች እና ትግሎች እንዳሉ ያነሱት አቶ ፍቃዱ፥ ዛሬ ላይ አነስተኛ እና ስትራቴጂክ ያለሆኑ ጉዳዮች አይደለም መታየት ያለባቸው ብለዋል።ይህንንም ታሳቢ በማድረግ ኮሚቴው አንድነትን የሚጎዱ ነገሮችን በግልጽ በመገምገም አንዱ ድርጅት ሌላው ላይ ጣት መቀሰር ሳይሆን ራሱን ከለውጡ አንፃር እንዲመለከት ድምዳሜ ላይ ተደርሷል ብለዋል።በጋራ በመስማማት ድምዳሜ የተደረሰባቸውን ነገሮችን በሁሉም ደረጃ መተግበር ላይ ክፍተቶች እንዳሉ ኮሚቴው ተመልክቷል።ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው የደረሰባቸውን ድምዳሜዎች መሰረት በማድረግም ቀጣይ አቅጣጫዎችን እንዳስቀመጠ አቶ ፍቃዱተናገርዋል።በሁሉም የሀገሪተ አከባቢዎች የዜጎች የመዘዋወር እና ንብረት የማፍራት ህገ መንግስታዊ መብት መከበር እንዳለበት በመመለክት የደህንነት እና ነፃነት ሚዛን በተጠበቀ መለኩ የህግ የበላይነት እንዲከበር አቅጣጫ አስቀምጧል።የለውጡ ስራዎች ተቋማዊ እንዲሆኑ ከማድረግ አንፃር የሚያስፈልጉ ህጎች እና ደንቦችን በማውጣት ህዝቡን ባሳተፈ ሁኔታ እንዲተገበሩም የሚል አቅጣጫ ተቀምጧል።የለውጡን ትክክለኛ ምን ማለት እና ዓላማው ምንድነው በሚለው ላይ ግልፅነት መፍጠር ሌላው አቅጣጫ መሆኑን አንሰተዋል።መገናኛ ብዙሃን በህዝብ አብሮነትና መቻቻል እንዲሁም አንድነት እና የህግ የበላይነት ላይ እንዲሰሩ ለማስቻልም እንዲሰራ ኮሚቴው አቅጣጫ ማስቀመጡ ነው የተናገሩት።ቀጣዩ ሀገር አቀፍ ምርጫም ህገመንግስቱ ባስቀመጠው መሰረት 2012 ላይ መካሄዱ አስፈላጊነት ላይ አቋም በመያዝ እንደ ድርጅትም እንደ መንግስትም ዝግጅት እንዲደረግ ነው አቅጣጫ ያስቀመጠው።በደቡብ ክልል እየተነሱ ባሉት የክልልነት ጥያቄ በተመለከተ ኮሚቴው መምከሩን የተናገሩት አቶ ፍቃዱ፥ ደኢህዴን በክልሉ እየተነሱ ላሉት ጥያቄዎች ሳይንሳዊ መፍትሄ ለመስጠት ያከናወነውን ጥናት ተመልክቷል።በጥናቱ መሰረት ደኢህዴን ያቀረበውን የክልልነት መዋቅር የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በአወንታ መመልከቱን እና ለተግባራዊነቱም ድጋፍ ለማድረግ መስማማቱን ገልፀዋል።ከኢህአዴግ ውህደት አንጻር በሀዋሳው ድርጅታዊ ጉባኤ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ የተካሄደ ጥናት አልቆ ውይይት እየተደረገ መሆኑን እና ሁሉም ብሄራዊ ድርጅቶች መክረውበት ለስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው እንዲያቀርቡ አቅጣጫ መቀመጡን ተናግረዋል። | https://waltainfo.com/am/31285/ |
46c302a78d1822f0dbbf0f8a5149a136 | 0858e1d55de6a1418e89860915e7a0b5 | በሆንግ ኮንግ አዉሮፕላን ጣቢያ ለሶስት ቀናት የሚዘልቅ አዲስ ተቃዉሞ መቀስቀሱ ተሰማ | ፖለቲካ | በቻይናዋ እራስ ገዝ አስተዳደር ሆንግ ኮንግ አዉሮፕላን ጣቢያ ለሶስት ቀናት የሚዘልቅ አዲስ ተቃዉሞ መቀሳቀሱ ተሰማ፡፡በቻይናዋ እራስ ገዝ አስተዳደር ሆንግ ኮንግ ወንጀል ፈፅመዉ ጥፋተኛ የሚባሉ ዜጎች ለፈጸሙት ወንጀል ከቻይና መንግስት ፍርድ እንዲሰጣቸዉ የሚያስችል ህግ መዉጣቱን ተከትሎ የግዛቲቱ ነዋሪዎች ህጉን በመቃወማቸዉ ሆንግ ኮንግ ለወራት በህዝባዊ አመፅ ስትናወጥ ቆይታለች።ለሶስት ወራት የዘለቀዉ ህዝባዊ ተቃዉሞ ማብቂያዉ መች እንደሆነ ዛሬም በዉል የታቀወ ነገር የለም። አልጀዚራ ባስነበበዉ መረጃ በግዛቲቱ አዉሮፕላን ማረፊያ ጣቢያ ለሶስት ቀናት የሚዘልቅ አዲስ ተቃዉሞ ተቀስቅሷል። ተቃዋሚዎቹ በአዉሮፕላን ጣቢያዉ ድምፃቸዉን ያሰሙት በአዉሮፕላን ጣቢያዉ የሚመላለሱ አለም አቀፍ ተጓዦች የችግሩን መጠን እንዲረዱና አለም አቀፉ ማህበረሰብም በጉዳዩ ላይ የበኩሉን ተፅእኖ እንዲያሳድር በማሰብ ነዉ ተብሏል።የተቃዉሞዉ ዳግም መቀስቀስን ተከትሎ የሆንግ ኮንጓ ዋና አስተዳዳሪ ካሪ ላም መንግስታቸዉ ተቃዋሚዎችን የሚለማመጥበት ትዕግስት እንደሌለዉና አስፈላጊዉን እርምጃ ለመዉሰድ መሰናዳቱን አስታዉቀዋል።በቼክ ላፕ ኮክ አዉሮፕላን ጣቢያ የተሰባሰቡት ተቃዋሚዎቹ ጥቁር ቲሸርቶችን የለበሱና ቁጥራቸዉም በመቶዎች የሚቆጠር ስለመሆኑ ተነግሯል። ተቃዋሚዎቹ ከዚህ ቀደምም በተመሳሳይ ተቃዉሟቸዉን ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማድረስ መሰል ተቃዉሞ ያካሄዱ ሲሆን፣ የአሁኑም ለሁለተኛ ጊዜ ስለመሆኑ ተነግሯል።ተቃዉሞዉን ተከትሎም የአዉሮፕላን ማረፊያ ጣቢያዉ ኃላፊዎች በአከባቢዉ ያለዉ የፀጥታ ኃይል እንዲጠናከርና የአዉሮፕላን መሳፈሪያ ቅፅ ያልያዙ ሰዎች ወደ ቅጥር ግቢዉ እንዳይገቡ እግድ ጥለዋል።የአሁኑ ተቃዉሞ ከመንግስት አካላት እዉቅና የሌለዉ ቢሆንም ከዚህ ቀደም በአዉሮፕለን ጣቢያዉ የተደረጉ የተቃዉሞ ሰልፎች ግን በሰላማዊ መንገድ መጠናቀቃቸዉ ነዉ የተሰማዉ። በመሆኑም ምንም እንኳን ተቃዉሞዉ ቢኖርም የአዉሮፕላን ጣቢያዉ መደበኛ ስራዉን እያከናወነ ስለመሆኑ ተገልጿል።የአልጀዚራዉ ሰዉ ሮብ ማክብራይድ ከስፍራዉ እንደዘገበዉ የአዉሮፕላን ጣቢያዉ ተቃዉሞ ይልቅ የግዛቲቱን ባለስልጣናት ስጋት ዉስጥ የከተታቸዉ በቀጣይ ቀናት ሀመላዉ ሆንግ ኮንግ ይካሄዳል ተብሎ የተሰጋዉ የተቃዉሞ ሰልፍ ነዉ።በሆንግ ኮንግ የተቀሰቀሰዉ ተቃዉሞ ካስከተለዉ የፀጥታ መደፍረስ ባለፈ የግዛቲቱን ምጣኔ ሀብትም ክፉኛ እየጎዳዉ ስለመሆኑ መረጃዎች አመላክተዋል። በግዛቲቱ ኃላፊዎች ይፋ የተደረገ መረጃ እንዳመላከተዉ ባለፈዉ ወር መጨረሻ ላይ የነበረዉ የቱሪስት ፍሰት ከባለፈዉ አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ26 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል። ይህ ደግሞ በግዛቲቱ ነዋሪወፖች ላይ የሚያስከትለዉ ምጣኔ ሀብታዊ ቀዉስ የከፋ እንደሚሆን ነዉ የሚጠበቀው። በሆንግ ኮንግ ለ250ሺ ሰዎች የስራ እድል የፈጠረዉ የቱሪዝም ዘርፉ 4.5 በመቶ የሚሆነዉን የግዛቲቱን ምጣኔ ሀብት ዘርፍም ይሸፍናል።የግዛቲቱ አስተዳዳሪ ካሪ ላምም ለወራት የዘለቀዉ ህዝባዊ ተቃዉሞ ያስከተለዉን ምጣኔ ሀብታዊ ቀዉስ ሱናሚ ሲሉ ከአስከፊዉ የአዉሎ ንፋስ ወጀብ ጋር አመሳስለዉታል።የሆንግ ኮንጉ ተቃዉሞ ግዛቲቱ በፈረንጆቹ 1997 ከእንግሊዝ ለቻይና ተላልፋ ከተሰጠች ወዲህ ከፍተኛዉ ስለመሆኑ አልጀዚራ በዘገባዉ አስታዉሷል። | https://waltainfo.com/am/33982/ |
e6389c9697486466de36b9997c09ed17 | 4af5692063bccf1137789060860fb8d7 | ሰሜን ኮሪያ የአጭር ርቀት የባልስቲክ ሚሳኤል ሙከራ አደረገች | ፖለቲካ | ሰሜን ኮሪያ ሁለት የባልሰቲክ ሚሳኤሎችን ወደ ባህር ማስወንጨፏ ተነግሯል፡፡ይህም ሀገሪቱ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ያደረገቻችውን የሚሳኤል ሙከራዎች አምስት አድርሶታል፡፡ከደቡብ ሃምግዮንግ ግዛት ሃምሁን ከተማ እንደተተኮሱ የተነገረላቸው ሁለቱ ሚሳኤሎች በጃፓን ባህር የኮሪያ ባህረ ሰላጤ አካባቢ ማረፋቸው ተነግሯል፡፡የባሊስቲክ ሚሳኤሎቹ የመካከለኛ ርቀት ተወንጫፊዎች ሊሆኑ እንደሚችልም የደቡብ ኮሪያ ወታደራዊ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከሰሜን ኮሪያ ሰላማዊ መልዕክት እንደደረሳቸው ከገለጹ በኋላ ሰሜን ኮሪያ ወደ ባልስቲክ ሚሳኤል ሙከራ ተመልሳ ገብጻለች፡፡የሰሜን ኮሪያው አቻቸው ኪም ጆንግ ኡን በበኩላቸው የደቡብ ኮሪያና አሜሪካ የጋራ ወታደረዊ ልምምድ እንዳልተዋጠላቸው ገልጸው እንደነበረም ቢቢሲ በዘገባው አስታውሷል፡፡ | https://waltainfo.com/am/33983/ |
0d62bb28a790a3494d82450bc3ffa874 | 431d51d5129c3c37cab6131b2ee74e6b | መቀንጨርን ዜሮ ለማድረግ መንግሥትና ባለድርሻ አካላት በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ ም/ጠ/ሚ ደመቀ መኮንን አሳሰቡ | ሀገር አቀፍ ዜና | መቀንጨርን ዜሮ ለማድረግ የመንግሥት እና የባለድርሻ አካላት ቁርጠኝነት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን አሳሰቡ።የሰቆጣ ቃል ኪዳን የሙከራ ምዕራፍ ትግበራን አስመልክቶ የተዘጋጀ ከፍተኛ የምክክር መድረክ በሸራተን ሆቴል ተካሂዷል።በመድረኩ ላይ የፌደራል እና የክልል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡ተሳታፊዎቹ የመቀንጨር ችግርን በሚፈለገው ደረጃ ለመፍታት በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል፡፡በቀጣይ የሰቆጣ ቃልኪዳን አፈፃፀም ላይ የሚታዩ የበጀት፣ የግብዓት እና ተያያዥ ችግሮችን በመፍታት በተያዘው በጀት ዓመት ውጤታማ ስራ መስራት እንደሚገባ የጋራ አቅጣጫ ተቀምጧል። (ምንጭ፡-የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት) | https://waltainfo.com/am/32635/ |
f334b9e57bc2250d99c5976d660de7eb | c17c6702144a001c11a3994ad428c447 | ፓኪስታን ከህንድ የካሽሚር ውሳኔ ጋር በተያያዘ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯን ወደ ቻይና ላከች | ፖለቲካ | የፓኪስታኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሻህ ሙሀሙድ ህንድ በካሽሚር ግዛት ያሳለፍችውን ውሳኔ እንድትቀለብስ ለመድረግ ያለመ ጉዞ ወደ ቻይና አድርገዋል፡፡በቻይና ቆይታቸውም ከሀገሪቱ ባለስልጣናት ጋር በጉዳዩ ላይ ውይይት እንደሚያደርጉም ነው የሚጠበቀው።የአሁኑ የህንድ ውሳኔ ከፍተኛ የፖለቲካ ትኩሳት በነገሰበት አካባቢ ባለፉት ሰባት አስርት ዓመታት ከተላለፉ ውሳኔዎች መካከል ጠንካራው እንደሆነም ፖለቲከኞች ይናገራሉ፡፡ይህን ተከትሎም ፓኪስታን ጉዳዩን ወደ ዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት ለመውሰድ መዘጋጀቷን ገልጻለች።ህንድ በቅርቡ የሻረችው አንቀፅ 370 የካሽሚር ግዛት የነበረውን የራስ ገዝ አስተዳደር እና ህግ የሚያግድ ሲሆን፤ ውሳኔውን ተከትሎ ህንድ በርካታ ወታደሮችን ወደ አካባቢው በማሰማራት ፖለቲከኞችን አስራለች፣ የኢንተርኔት እና የስልክ ግንኙነትም እንዲቋረጥ አድርጋለች፡፡ይህ ውሳኔ ወትሮም ሻክሮ የቆየውን የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ይበልጥ ወደ ውጥረት ከቶታል፡፡ ህንድ ለካሽሚር ግዛት ልዩ መብት የሚሰጠውን ህገ መንግስታዊ ውሳኔ እንዲሻር ማድረጓ የሚታወስ ነው፡፡ምንጭ፦ አልጀዚራ | https://waltainfo.com/am/33981/ |
Subsets and Splits