query_id
stringlengths
32
32
passage_id
stringlengths
32
32
query
stringlengths
7
297
category
stringclasses
6 values
passage
stringlengths
137
5.93k
link
stringlengths
28
740
6781db55ceca9e2dfa261d4b909b8b30
2c8271ab2982e90d13978831b6019853
ሐምሌ 22 በአዲስ አበባ 3 ሚሊየን ችግኞች ለመትከል ቅድመ ዝግጅቶች ተጠናቀዋል
ቢዝነስ
ሐምሌ 22 በአዲስ አበባ ከተማ የሶስት ሚሊየን ችግኞች ተከላ ለማከናወን ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁ ተገለፀ፡፡ዛሬ በርካታ የከተማዋ ነዋሪዎች በተገኙበት የአረንጓዴ አሻራ የንቅናቄ መድረክ በሚሊኒየም አዳራሽ ተካሂዷል፡፡በንቅናቄ መድረኩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማን ጨምሮ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም በርካታ የከተማዋ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።ኢንጂነር ታከለ ኡማ በንቅናቄ መድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር ከተማ አስተዳደሩ በዚህ የአንድ አመት ጉዞው ካከናወናቸው በርካታ ተግባራቶች ውስጥ የክረምት በጎ ፈቃድ ሥራዎች ዋነኞቹ እንደሆኑ ጠቅሰው፣ በተለይ የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ ለተማሪዎች የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ማሰባሰብ እንዲሁም የችግኝ ተከላ ተግባራት መልካም ውጤት የታየባቸው ናቸው ብለዋል፡፡   ምክትል ከንቲባው አያይዘውም እንደገፁት ሐምሌ 22 በአገራቀፍ ደረጃ ለሚካሄደው የችግኝ ተከላ በአዲስ አበባ ደረጃ 3 ሚሊየን የሚሆኑ ችግኞች እንደሚተከሉና ለዚህም የሚሆን ከ2 ነጥብ 8 ሚሊየን በላይ ጉድጓዶች መቆፈራቸውንና ቀሪዎቹ በመጪዎቹ ጥቂት ቀናቶች ውስጥ እንደሚጠናቀቁም ነው የተናገሩት።ሐምሌ 22 በአገር አቀፍ ደረጃ ለሚካሄደው የችግኝ ተከላ ፕሮግራም ማስጀመሪያ ይሆን ዘንድ ከተለያዩ የከተማዋ ነዋሪዎች የተውጣጡ ተወካዮች ከምክትል ከንቲባው እጅ ችግኞች ተረክበዋል።   ትላንት “ለምለሚቱ ኢትዮጵያ” ትባል ነበር ያም የሆነው ትላንት አባቶች መሰዋእት ሆነው ሀገሪቱን ለዛሬዎቹ ትውልዶች ስላቆዩ መሆኑን የገለፁት ከንቲባው፣ ዛሬ እና ነገን መልካም ለማድረግ ልዩነታችንን ትተን አንድ በመሆን የተጣለብንን ኃላፊት ልንወጣ ይገባናል ሲሉም ለመላው የከተማዋ ነዋሪዎች ጥሪ አቅርበዋል።  
https://waltainfo.com/am/23881/
0a6ff88b171fc14756313d1799cea97e
4c503fe6e96d73976114920550e88a22
በሞቃዲሾ የሚገኘው የቱርክ ወታደራዊ ካምፕ 152 የሶማሊያ ወታደሮችን አሰለጠነ
ፖለቲካ
በሶማሊያ ሞቃዲሾ የሚገኘው የቱርክ ወታደራዊ ካምፕ 152 የሶማሊያ ወታደሮች ማሰልጠኑን አስታወቀ፡፡በቱርክ አጋዥነት በሶማሊያ የሚደረገው ወታደራዊ ስልጠና ሀገሪቱን ከሚያምሳት የሽብርተኝነት አደጋ ለመታደግ መሆኑንም ቱርክ ገልፃለች፡፡ቱርክ በአፍሪካ ከከፈተቻቸው ወታደራዊ ካምፖች መካከል በ2017 እ.አ.አ በሞካዲሾ የከፈተችው ይጠቀሳል፡፡ይህ ካምፕ ከ1 ሺህ 500 በላይ የሶማሊያ ወታደሮችን አሰልጥኖ ወደ ስራ ማሰማራቱን የቱርክ መከላከያ ሚኒስቴር ሁሉሲ አካር አስታውቀዋል፡፡ቱርክ በሶማሊያ አሰልጥና ካስመረቀቻቸው ወታደሮች መካከልም 81 የሚደርሱት በመቶ አለቃ ማዕረግና ከ71 በላይ የሚሆኑት ደግሞ በ50 አለቃ ማዕረግ እንደተመረቁ እና የሰላም ማስከበር ስራቸውን እንደሚሰሩ ነው ሚኒስትሩ ያስታወቁት፡፡የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሙሀመድ አብዱላሂ ፋርማጆ 152 የሶማሊያ ወታደሮችን በመገኘት ያስመረቁ ሲሆን÷ ቱርክ በሶማሊያ ሽብርተኝነትን ለማጥፋት እያደረገች ስላለው እገዛ ምስጋና አቅርበዋል፡፡በሞቃዲሾ ቱርክ ካስመረቀቻቸው ወታደሮች ጎን ወታደራዊ መጠለያዎችን እና ትምህርት ቤቶችን መገንባቷን የዘገበው ሲጂቲኤን ነው፡፡
https://waltainfo.com/am/33311/
631e889e052b10a76a2834e0bcd61dff
c8473d65f18a8c6fe8c2e30df1607600
የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤን ማካሄድ ጀመረ
ፖለቲካ
የጋምቤላ ህዝቦች ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት 5ኛ የምርጫ ጊዜ 4ኛ የስራ ዘመን መደበኛ ጉባኤን ዛሬ ማካሄድ ጀምሯል።የምክር ቤቱ አፈ-ጉባኤ ላክዴር ላክባክ በጉባዔው መክፈቻ እንደተናገሩት፤ ለህዝቦች ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚዊና ፖለቲካዊ ዕድገት ሰላም ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን በመገንዘብ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚፈጠሩ ግጭቶችን ጥበብ በተሞላበት መንገድ መፍታት ይገባዋል፡፡በክልሉ የተጀመረውን ለውጥ ለማደናቀፍ እየተንቀሳቀሱ ያሉ ግለሰቦችና ቡድኖችን በጋራ መታገል እንደሚገባም አፈጉባኤው አሳስበዋል፡፡የ2011 ዓ.ም በጀት አመት የልማትና የመልካም አስተዳደር እቅድ አፈፃፀም በክልሉ ርዕሰ-መስተዳደር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ የቀረበ ሲሆን፤ አሁን ያለውን የክልሉን ሰላም አስተማማኝ ለማድረግ ህብረተሰቡን ያሳተፉ ስራዎች ተሰርተዋል ተብሏል፡፡አቶ ኡሞድ አያይዘውም የክልሉን የፖለቲካ ምህዳር ለማስፋት በተደረገው ጥረትም በኤርትራ የሚገኙ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወደ ክልሉ መግባታቸውን አውስተዋል፡፡ምክር ቤቱ በሚኖረው የሁለት ቀናት ስብሰባ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤትና ዋና ኦዲት መስሪያ ቤት የ2011 እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት፤ የ2012 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት እንዲሁም ሌሎች አዋጆችንና ሹመቶችን መርምሮ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡በአረንጓዴ አሻራ ዘመቻው በአንድ ጀምበር 200 ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል በሚደረገው እንቅስቃሴ የምክር ቤት አባላት ህዝቡን በማስተባበርና አርአያ በመሆ እንዲሳተፉም ተጠይቋል። የጋምቤላ ክልል ፕሬስ ሴክሬታሪያት በላከልን መረጃ መሰረት።
https://waltainfo.com/am/31263/
829e11594f2d2a6ac0c1d5e4196ed64a
3db1fa7bfd34e9f97c064930816d03ee
የ2011 በጀት ዓመት የውጭ ዲሎማሲያዊ ተግባራት ስኬታማ እንደነበሩ ተገለጸ
ፖለቲካ
በ2011 በጀት ዓመት የተከናወኑ የውጭ ዲፕሎማሲያዊ ተግባራት ስኬታማ እንደነበሩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሂሩት ዘመነ የሚኒስቴሩን የ2011 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀም አስመልክተው ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ላይ እንደገለጹት የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ የትኩረት አቅጣጫ በሆኑት በኢኮኖሚ እና ዜጋ መር ዲፕሎማሲ፣ የአሜሪካ፣ አውሮፓ፣ እስያ አውስትራሊያ ዓለምአቀፍ ተቋማት እንዲሁም የሚኒሰቴሩ አዲስ የሰው ኃይል ስምሪት አንፃር ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡   የኢትዮ ኤርትራ የንግድ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ የንግድ ስምምነቶች እየተዘጋጁ መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታዋ ገልጸዋል፡፡ የሁለቱን ሀገራት የንግድ ልውውጥ ህጋዊ ማድረጉ በሁለቱ ሀገራት መካከል አሁን ላይ የታየውን ሰላማዊ ግንኙነት የሚያጠናክርና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ይሆናልም ነው ያሉት፡፡ኢትዮጵያ ባለፈው በጀት ዓመት ከጅቡቲ፣ ኬንያና ሌሎች የቀጠናው ሀገራት ጋር በቀጠናው ሰላምና በኢኮኖሚው መስክ ዙሪያም ሰፊ ስራ ማከናወኗን ገልጸዋል።በሱዳን ተፈጥሮ የነበረው ችግር ወደ ሰላማዊ ሁኔታ እንዲመለስ ኢትዮጵያ የበኩሏን ድርሻ መወጣቷንም አስታውሰዋል፡፡የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር አክሊሉ ሃይለሚካኤል በበኩላቸው ባሳለፍነው በጀት ዓመት በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲና ቆንስላ ጉዳዮች ዙሪያ ከእቅድ በላይ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡በበጀት ዓመቱ 168 ቢዝነስ ፎረሞች ተዘጋጅተው 1 ሺህ 150 ኩባንያዎች ኢትዮጵያን መጎብኘታቸውን የተናገሩት ሚኒስትር ዴኤታው፣ 225 ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመራቸውን ጠቁመዋል፡፡የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች ከውጭ ባለሃብቶች ጋር በሽርክና እንዲሰሩ ለማድረግ በተከናወነው ተግባርም 67 ትስስሮች መፈጠራቸውን ጠቅሰዋል።ያሳለፍነው በጀት ዓመት በተለያዩ ሀገራት በእስር ላይ የነበሩ ከ27 ሺህ በላይ ዜጎች ከእስር ተፈተው ወደ ሀገራቸው የተመለሱበት እንደነበርም ገልጸዋል። በተጨማሪም በውጭ ሀገራት የነበሩና የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው 112 ሺህ 615 ዜጎች ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል ብለዋል፡፡ አሁንም ከ4 ሺህ በላይ ዜች በተመሳሳይ ሆኔታ በተለያዩ የውጭ ሀገራት በእስር ላይ የሚገኙ ሲሆን ለማስመለስ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ አስገንዝበዋል፡፡የአህጉራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ዴኤታ ዶክተር ማርቆስ ተክሌ በበኩላቸው የኢትዮጵያ የገቢ አጋር እንደሆኑ የሚገለጽላቸው  የአሜሪካ፣ አውሮፓ እና እስያ አህጉራትና አገራትን ጨምሮ አለም አቀፍ ተቋማት በኢትዮጵያ ያለውን የለውጥ ሂደት እንደሚደግፉ የማስገንዘብ ሥራ ተከናውኖ አመርቂ ውጤቶች ተገኝተውበታል፡፡ አገራቱ ለውጡ ተቋማዊ ሆኖ እንዲቀጥል ጠንካራ ድጋፍ እንደሚያደርጉም ታውቋል፡፡    
https://waltainfo.com/am/31264/
2dadb2854a047f2ee30167b51a86ada7
9c1ae6d51b99e59bcdf97b372e1f607e
አቶ አገኘሁ ተሻገር የሰላም ግንባታና የሕዝብ ደህንነት ኃላፊ ሆነው ተሾሙ
ፖለቲካ
አቶ አገኘሁ ተሻገር የአማራ ክልል የሰላም ግንባታና የህዝብ ደህንነት ቢሮ ሃላፊ ሆነው ተሹመዋል።የአማራ ክልል ምክር ቤት እያካሄደ ባለው መደበኛ ጉባኤ የአቶ አገኘሁ ተሻገርን የክልሉ የሰላም ግንባታና የህዝብ ደህንነት ቢሮ ሃላፋነት ሹመትን በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።አቶ አገኘሁ ላለፉት 20 ዓመታት በክልሉ በልዩ ልዩ የኃላፊነት ቦታዎች መስራታቸው ተገልጿል፡ከሰላምና ጸጥታ ሥራዎች ጋር በተያያዘ ልምድ ያላቸው በመሆኑ ለወቅቱ የክልሉ የሰላምና ደኅንነት ሁኔታ መረጋጋት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱም አስተያየት ተሰጥቷል፡፡ዘገባው የአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት ነው፡፡
https://waltainfo.com/am/31259/
30c89e604385feffe84e785bc67b91d6
990a914b1377aa46f8e722fa90763cfb
የአማራ ክልል ምክር ቤት የ230 ዳኞችን ሹመት አጸደቀ
ፖለቲካ
የአማራ ክልል ምክር ቤት የ230 ዳኞችን ሹመት አጸደቀየአማራ ክልል ምክር ቤት በተለያዩ ደረጃዎች የሚመደቡ ዳኞችን ሹመት አጽድቋል፤ የሥነ ምግባር ጉድለት ያለባቸውን ደግሞ ከሥራ አሰናብቷል፡፡የአማራ ክልል ምክር ቤት 5ኛ ዙር፣ 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 13ኛ መደበኛ ጉባኤ ዛሬ በአራተኛ ቀን ውሎው ከሰዓት በፊት ከተመለከታቸው ጉዳዮች ውስጥ የዳኞች ሹመት ይገኝበታል፡፡በዕጩነት የቀረቡት ዳኞች በሥነ ምግባራቸው ጥሩ ስለመሆናቸው አስተያዬት የተሰጠባቸው፣ በመመልመያ መስፈርቱ ተወዳድረው የተመረጡ እና የትምህርት ደረጃውንም ያሟሉ ናቸው ተብሏል፡፡በዚህም መሰረት 10 ዳኞች ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኝነት፣ ሁለት ዳኞች ለከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንትነት፣ 18 ዳኞች ለከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኝነት፣ 200 ዳኞች ለወረዳ ፍርድ ቤት ዳኝነት ተሹመዋል፡፡የሁሉም ዳኞች ሹመት በሙሉ ድምጽ ነው የጸደቀው፡፡ምክር ቤቱ አምስት ዳኞችን በስነ ምግባር ጉድለት ከሥራ አሰናብቷል ሲልየዘገበው የአማራ መገናኛ ብዙሀን ነው።
https://waltainfo.com/am/31260/
95ef0df079dc26ff14af552343c92bab
2338fada671827af2294998468cc0468
ሃምሌ 22 ለሚካሄደው የችግኝ ተከላ መርሀ-ግብር 54 ሚሊየን ብር ተመድቧል
ሀገር አቀፍ ዜና
በዘንድሮ በጀት ዓመት ከ4 ቢሊዮን ችግኝ በላይ ለመትከል እቅድ መያዙ ይታወቃል፡፡ የዚህ አካል የሆነውና ሃምሌ 22 ቀን የሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ ቀን በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ አሰፈላጊ ቅድመ ዝግጅቶች እየተጠናቀቀ እንደሚገኝ ብሄራዊ የቴክኒክ ኮሚቴው አስታውቋል፡፡ሃምሌ 22 ቀን በአንድ ጀንበር 200 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል የተያዘው እቀድ የተሳካ እንዲሆን 54 ሚሊየን ብር መመደቡም ተገልጿል፡፡ለዚህም 46 ሚሊየኑ ለክልሎች 8 ሚሊየኑ ደግሞ ለፌደራል ከተሞች እንደተመደበ የብሄራዊ የቴክኒክ ኮሚቴው አስታውቋል፡፡በእለቱም ያጋጥማሉ ተብለው የታሰቡ ችግሮችን ቀድሞ በመለየት የመፍትሄ አቅጣጫም እንደተቀመጠላቸው የተነገረ ሲሆን÷ ይህም የተሳካ እንዲሆን ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በትብብር እየተሰራ ይገኛል፡፡ከማለዳው 12 ሰአት እሰከ ምሽት 12 በሚካሄደው በዚህ መርሃግብር ላይ እያንዳንዱ ዜጋም ሆነ ተቋማት በተዘጋጀለቸው ቦታ በመገኝት በባለሞያዎች በመታገዝ የችግኝ ተከላውን ማከናወን እንደሚገባቸውም ተገልጿል፡፡አሁን ላይ በሀገሪቱ ያለው የደን ሽፋን 15 ነጥብ 5 በመቶ መድረሱንና ይህንን ለማሻሻል የአረንጓዴ ልማት ፕሮጀከትን ለማሳካት ሁሉም ሃላፊነቱን እንዲወጣ ተጠይቋል፡፡
https://waltainfo.com/am/32585/
b2c60821584987ad168a72f0b1d283b7
f983c0c9e865969bb69c3410d6aa2173
ለህግ የበላይነት መከበር ሁሉም በጋራ መስራት እንዳለበት ተጠቆመ
ሀገር አቀፍ ዜና
የፍትህ እኩልነትን ለማረጋገጥ የህግ የበላይነትን የማክበርና የማስከብር ሃላፊነትን ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በጋራ እንዲወጣ ተጠየቀ፡፡መሰረቱን ህዝብ ያደረገ የፍትህ ስርዓት ለማፈን የፌዴራል የፍትህና ህግ መምሪያ እና ስልጠና ተቋም ከሚመለከታቸው የፍትህ አካላት ጋር እየሰራ መሆኑን አስታውቋል፡፡በሀገር አቀፍ ለውጡን የሚደግፍ እና የህዝብን እኩልነት የሚያረጋግጥ የፍትህ ስርዓት እንዲኖር የዘርፉ ተቋማት የህግ የበላይነትን ዋና ዓላማቸዉ አድርገው መስራትም አለባቸው ብሏል የስልጠና ተቋሙ ምክትል ዳይሬክተር፡፡ስልጠናው የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤህግ ከሆላንዱ በህግላት ትኩረቱን አድርጎ ከሚሰራው "ዘ ሄግ ኢንስቲቱዩት ፎር ኢኖቬሽን ኦፍ ሎው " ከተባለ ድርጅት ጋራ በመተባበር የተሰጠው ነው፡፡
https://waltainfo.com/am/32586/