query_id
stringlengths
32
32
passage_id
stringlengths
32
32
query
stringlengths
2
300
passage
stringlengths
78
8.98k
category
stringclasses
7 values
link
stringlengths
28
740
⌀
negative_passages
listlengths
5
5
608823f9f4635381c68222501123b2ed
465525198bd3bf4e5b137fe927e34ee1
የኦሊምፒክ ማጣሪያ ተሳታፊዎች የሚለዩበት ቻምፒዮና እየተካሄደ ይገኛል
ብርሃን ፈይሳየኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን በየዓመቱ የሚያዘጋጀው የክለቦች ቻምፒዮና በአዲስ አበባ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተሻለ ብቃት ያሳዩ ቦክሰኞች ለቶኪዮ ኦሊምፒክ ማጣሪያ ተሳታፊ እንደሚሆኑም ታውቋል።በቦክስ ስፖርት ከሚካሄዱት ዓመታዊ ቻምፒዮናዎች መካከል አንዱ በክለቦች መካከል የሚካሄደው ነው፤ የዚህ ውድድር የመጀመሪያው ዙር በአዲስ አበባ ከተማ ተጀምሯል። የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን ከአዲስ አበባ ቦክስ ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር በተዘጋጀው በዚህ ቻምፒዮና፤ ከኮቪድ 19 ወረርሽኝ መከሰት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደ ውድድርም ነው። በውድድሩም ላይ አምስት ክለቦች ከአዲስ አበባ (ፌዴራልፖሊስ፣ ፌዴራል ማረሚያ ቤቶች፣ አዲስ አበባ ፖሊስ፣ የኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ እና ኦሞቲክ ቦክስ)፣ ሁለት ክለቦች ከአማራ ክልል (ጎንደር ከነማ እና ደሴ ከነማ) እንዲሁም ድሬዳዋ ከነማ በድምሩ ስምንት ክለቦች ተሳታፊ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያሳያል። በአጠቃላይ ክለቦቻቸውን ወክለውም 12 ሴትና 76 ወንድ ቦክሰኞች በጥቅሉ 88 ተወዳዳሪዎች ተሳታፊ ይሆናሉ። ውድድሩ የሚካሄደው በራስ ኃይሉ ስፖርት ትምህርትና ስልጠና ማዕከል ሲሆን፤ በ10 ክብደቶች በ49፣ 52፣ 57፣ 60፣ 63፣ 69፣ 70፣ 81፣ 89 እና 91 ኪሎ ግራሞች እየተካሄደም ይገኛል። የቦክስ ስፖርት ከንክኪ ስፖርቶች መካከል አንዱ እንደመሆኑ ጨዋታው በሚካሄድበት ወቅት ቦክሰኞቹ አካላዊ ቅርርብ ሊያደርጉ እና ሊነካኩ ይችላሉ። በመሆኑም በዚህ ረገድ ውድድሩ ሙሉ ለሙሉ የኮቪድ 19 ጥንቃቄን በተላበሰ መልኩ እየተካሄደ መሆኑን ነው ፌዴሬሽኑ ያረጋገጠው። ይኸውም ተወዳዳሪዎችና አሰልጣኞች የኮቪድ ምርመራ እንዲያደርጉና ከሌሎች ሰዎች ጋር እንዳይገናኙ በካምፕ እንዲቆዩ በማድረግ ነው። ከዚህ ባሻገር ውድድር የሚደረግበት ሪንግ ቶሎ ቶሎ በኬሚካል እንዲጸዱ እንዲሁም ተመልካቾች ውድድሩ ላይ እንዳይገኙም ተደርጓል። ኮቪድ 19 ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ እንደመሆኑ በመላው ዓለም ስፖርታዊ ውድድሮች ተቋርጠው መቆየታቸው የሚታወስ ነው። ከእነዚህ ውድድሮች መካከል ለቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ የቦክስ ስፖርት ማጣሪያ የሚካሄደው ውድድር ይጠቀሳል። ውድድሮች ወደ እንቅስቃሴ መግባታቸውን ተከትሎም ማጣሪያው የሚቀጥል ይሆናል። ኢትዮጵያም በዚህ ቻምፒዮና (በመጀመሪያው ዙር) የተሻለ ብቃት ያሳዩ ቦክሰኞችን በማጣሪያው የምታሳትፍ መሆኑ ታውቋል። ቻምፒዮናው አራት ዙሮች ያሉት ሲሆን፤ ሁለተኛው ዙር ከአማራ ክልል ቦክስ ፌዴሬሽን ጋር በመሆን ጎንደር ላይ፣ ሶስተኛውን ከደቡብ ክልል ቦክስ ፌዴሬሽን ጋር በመሆን ወላይታ እንዲሁም የመጨረሻውና የማጠቃለያው ውድድር አዲስ አበባ ላይ የሚካሄድም ይሆናል። ቻምፒዮናው ጥር 4/2013 ዓም የተጀመረ ሲሆን እስከ ጥር 7/2013 ዓም ድረስም ይቆያል።
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=39481
[ { "passage": "12 ኛው የመላ አፍሪካ ጨዋታ ከነሐሴ 13 እስከ 25 ቀን 2011 ዓ.ም በሞሮኮ ራባት ከተማ የሚካሄድ ሲሆን ኢትዮጵያም ተሳታፊ ከምትሆንባቸው 13 የስፖርት አይነቶች አንዱ ካራቴ ነው። በውድድሩ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ካራቴ ብሄራዊ ቡድን ልኡክ ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅቱን እያደረጉ እንደሚገኙና በውድድሩም ጥሩ ውጤት ያስመዘግባሉ የሚል እምነት መያዙ ተጠቁሟል። ተሳታፊ ስፖርተኞችም ውጤታማ ለመሆን እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ካራቴ ፌዴሬሽን ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሠፋ አንጀሎ ዝግጅቱን አስመልክተው እንደተናገሩት ፤ ለውድድሩ ትኩረት በመስጠት ከግንቦት ወር ጀምሮ ዝግጅት መጀመሩንና ሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተሳተፉበት ሻምፒዮና በማካሄድ ውጤታማ ሊሆኑ ይችላሉ ተብሎ የታመነባቸው 25 ወጣት ስፖርተኞች ዕጩ የብሔራዊ ቡድን አባል የማድረግ ስራ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡ ከተመለመሉት ዕጩ የብሔራዊ ቡድን አባላት ውስጥም አስፈላጊውን ማጣሪያ በማድረግ 3 ሴትና 6 ወንድ ስፖርተኞች ለውድድሩ ተመርጠዋልⵆ ስፖርተኞቹም በቀን 2 ጊዜ የስልጠና መርሃ ግብር ወጥቶላቸው ዝግጅታቸውን በማድረግ ላይ ሲሆኑ መንግስትም በቂ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ በውድድሩ የተሻለ ውጤት እንደሚመዘገብ ፍላጎት ማሳየቱን ተናግረዋል። እገዛው ጥሩ ቢሆንም ብሄራዊ ቡድኑ በተወሰነ መልኩ ውስንነቶች እንዳሉበት ጠቁመዋል። ከውስንነቶቹ መካከል ዓለም አቀፉ የካራቴ ፌዴሬሽን ያረጋገጠው የመወዳደሪያ ልብስ “ቲሞኖ” በሀገር ውስጥ አለመኖሩ ነው ያሉት አቶ አሰፋ ይህን ችግር ለመፍታትና ለውድድሩ ሙሉ ሆኖ ለመገኘት ከአንዳንድ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመጻጻፍ ላይ ነን ብለዋል፤ ጥረቱ ተሳክቶም ለውድድሩ እንደሚደርስ ያላቸውን እምነት ጠቁመዋል። የብሄራዊ ቡድኑ ዋና አሠልጣኝ ኢንስትራክተር ዮሴፍ ተበጀ በበኩላቸው ዝግጅቱ ጥሩ መሆኑን ተናግረው ተወዳዳሪ ስፖርተኞች የሚሰጣቸውን ስልጠና በአግባቡ እየተቀበሉ መሆኑን እና በስነ ልቦና ፣ በታክቲክ እና በቴክኒክ በመዘጋጀት ሙሉ የማሸነፍ አቅምም መፍጠራቸውን ተናግረዋል ፡፡ ኢንስትራክተር ዮሴፍ እንደሚሉት ቡድኑ እየተደረገለት ያለው ድጋፍ ከወትሮው የተለየ ነው ተወዳዳሪዎችም በድጋፉ ልክ ውጤት ለማስመዝገብ ጥረት እያደረጉ መሆኑን ገልፀዋል ፡፡ በዝግጅቱ ዙሪያ አስተያየቱን የሰጡት የነጠላ ካታና የቡድን ካታ ተወዳዳሪ የሆኑት ሄዋን እና ሰለሞን እንደገለፁት ፤ በፌዴሬሽኑ እየተደረገ ያለው ድጋፍ እና በአሠልጣኙ እየተሰጣቸው ባለው ስልጠና ደስተኞች መሆናቸውን በመግለጽ ለሀገራቸው ውጤት በማስመዝገብ አዲስ ታሪክ ለመስራት መዘጋጀታቸውን አብራርተዋል፡፡ በሞሮኮ\nራባት በሚካሄደው 12ኛው መላ አፍሪካ ጨዋታ በካራቴ ስፖርት ኢትዮጵያ በ 3 ሴት በ 6 ወንድ ስፖርተኞች ተወክላ የምትሳተፍ ሲሆን በነጠላ ካታ እና ኩምቴ (fight) በወንድ እና በሴት እንዲሁም በቡድን ካታ በወንድ ትካፈላለች ፡፡አዲስ ዘመን ነሃሴ 2/2011", "passage_id": "41c10d66bddeabdcf4513522a4366d4a" }, { "passage": "በተያዘው ዓመት መጨረሻ በሚካሄደው የቶኪዮ ኦሊምፒክ ዝግጅት አካል የሆነው ችቦ የመለኮስ ስነ-ስርዓት በመጪው እሁድ የሚጀመር ይሆናል።በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ የሚጀመረው ችቦ ማብራት በዕጣው መሰረት በተለያዩ ክልሎች የሚዘዋወርም ይሆናል፡፡ ለቶኪዮ ኦሊምፒክ ቅድመ ዝግጅት የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ‹‹ከቶኪዮ\nእስከ ቶኪዮ›› በሚል ርዕስ በብሄራዊ ኮሚቴው አማካኝነት ከተለያዩ ባለ ድርሻ አካላት ጋር እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ\nይታወቃል።ከዝግጅቶቹ መካከል አንዱ የኦሊምፒክ ደጋፊ ማህበር አባላትን ማፍራት ሲሆን፣ ለዚህ ንቅናቄም በመላው የሃገሪቷ ክፍል የሚካሄድ\nየችቦ ማብራት ስነስርዓት ከመጪው እሁድ የካቲት 08/2012ዓም ጀምሮ የሚካሄድ ይሆናል። የመጀመሪያው ችቦም በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ የመንግስት\nኃላፊዎች፣ የከተማው ነዋሪዎች፣ ስፖርተኞች፣ ቀጣይ የሃገር ተረካቢ የሆኑት ተማሪዎች እንዲሁም ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት\nየሚበራ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በድረ ገጹ አስነብቧል።ስነ- ስርዓቱ በሌሎች ክልሎችም የሚቀጥል ሲሆን፤ በወጣው\nእጣ መሰረት የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ሁለተኛው ነው።ሶማሌ፣ ትግራይ፣ ጋምቤላ፣ አፋር፣ ሐረሪ፣ ኦሮሚያ፣ አማራ፣ ደቡብ እና ቤኒሻንጉል\nጉሙዝ ክልሎችም የሚዘዋወር ይሆናል። ከዝግጅቱ ጋር በተያያዘም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽነር ዮናስ አረጋይ፤ ከቶኪዮ 2020\nብሔራዊ ዝግጅት ኮሚቴ አባላት ባቀረቡት መርሃ ግብር እና መሪ ዕቅድ ላይ ውይይት በማድረግ ማጽደቃቸውንም በድረ ገጹ ተጠቁሟል።በውይይቱ\nላይም የቀድሞ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤና የብሔራዊ ዝግጅት ኮሚቴ ሰብሳቢው አባዱላ ገመዳ፣ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ\nፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ እንዲሁም የኮሚቴው አባላቶች ተገኝተዋል፡፡ ኦሊምፒክ ለሰው ልጆች የላቀ ቦታ የሚሰጥ፣ አንድ የሚያደርግና ሰላምን የሚሰብክ በመሆኑ ዝግጅቱ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ\nተሳትፎ ይፈል ጋል። በመሆኑም የተለያዩ አካላትን ያካተተ ብሄራዊ የኦሊምፒክ ዝግጅት ኮሚቴ በማዋቀር እንቅስቃሴ ማደረግ የተጀመረው\nቀደም ብሎ ነው።ኮሚቴው ለጃፓኑ ኦሊምፒክ እንዲሁም ሌሎች የልማት ስራዎች የሚውል 1ቢሊየን ብር ለማሰባሰብ፣ ከ12ሚሊየን በላይ\nየሚሆኑ የኦሊምፒክ ደጋፊ ማህበር አባላትን ለማፍራት፣ የአትሌቶች ሽኝትና ሽልማት እንዲሁም በመድረኩ የሃገሪቷን መልካም ገጽታ መገንባትም\nዋነኛ ክንዋኔዎቹ ናቸው። ለዚህ ስራ የሚውል ህዝባዊ ንቅናቄ ችቦ በማብራት የሚጀመር ሲሆን፤ የተለያዩ የገቢ ማሰባሰቢያዎችን ማካሄድም\nበቀጣይ የሚተገበር ይሆናል።ለዚህ ስኬትም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በጋራ በመነሳት አሻራቸውን እንዲያኖሩም ጥሪ ቀርቧል። ሁሉም ኢትዮጵያዊ\nበጋራ በመነሳት አሻራውን በኦሊምፒክ ላይ እንዲያኖር ጥሪ ቀርቧል፤አዲስ ዘመን ረቡዕ የካቲት 4/2012  ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "8a04d224c4328a24ad6a906e9d2e6856" }, { "passage": "የዘንድሮውን ከ20 ዓመት በታች የዓለም ሻምፒዮና በኬንያ ናይሮቢ ከመካሄዱ በፊት ውድድሩ በሚካሄድበት አካባቢ ያለው የአየር ጥራት እንደሚለካ የዓለም አትሌቲክስ ተቋም አስታውቋል፡፡\nባለሙያዎቹ ፈረንሳይ ሞናኮ ከሚገኘው ዋና መስሪያ ቤቱ ትናንት ኬንያ መግባታቸውን ያስታወቀው ተቋሙ “ኩናክ” የተሰኘ የአየር ጥራት መለኪያ መሳሪያ ሻምፒዮናው በሚካሄድበት የካሳራኒ ስታዲየም መተከሉንም ገልጿል፡፡\nመሳሪያው ባለፈው ዓመት በአዲስ አበባ ተተክሎ ነበር፡፡\nይህን ያስታወሰው ሲ.ጂ.ቲ.ኤን አፍሪካ የናይሮቢው የታዳጊዎቹ ሻምፒዮና የአየር ጥራት የሚለካበት የመጀመሪያው ዓለም ቀአፍ ውድድር መሆኑን ዘግቧል፡፡\nሻምፒዮናው በመጪው ሰኔ ወር መጨረሻ የሚካሄድ ነው፡፡\nኬንያ ከሶስት ዓመታት በፊት በዚሁ በካሳራኒ ስታዲየም ከ17 አመት በታች የዓለም ሻምፒዮናን ማስተናገዷ የሚታወስ ነው፡፡\n", "passage_id": "5812a107b5ae2f1f1f7b1c4b2bd0509d" }, { "passage": "የዓለም ታላቁ ስፖርታዊ ውድድር ኦሊም ፒክ፤ በየወቅቱ አዳዲስ የውድድር ዓይነቶችን በማካተት ይታወቃል። ፓሪስ\nበታሪኳ ለሶስተኛ ጊዜ እአአ በ2024 በምታስተናግደው ኦሊምፒክ ላይም አዳዲስ ውድድሮች የሚጨመሩ መሆኑ ታውቋል። የመጀመሪያው በማራቶን\nስፖርት ላይ መሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውንም ሰው ማካተት ሲሆን፤ «ብሬክ» በመባል የሚታወቀው ዳንስ፣ በ«ስኬት ቦርድ» መንሸራተት፣\nበውሃ ላይ መንሳፈፍ እንዲሁም ተራራ መውጣት የኦሊምፒኩ የውድድር ዓይነቶች ናቸው።ከአትሌቲክስ ስፖርቶች ረጅሙን ርቀት የሚሸፍን ውድድር እንደመሆኑ ከፍተኛ ጽናትና ጥንካሬን ይጠይቃል፤ ማራቶን።\n42ኪሎ ሜትር መሸፈኑ ከባድ ቢያደርገውም በተለያዩ የዓለም ከተሞች በየሳምንቱ የሚካሄድ የውድድር ዓይነት በመሆኑ ብዙዎች ይሳተፉበታል።\nበተለይ በዚህ ርቀት እንደ ኦሊምፒክ ባሉ የውድድር መድረኮች ተሳትፎ የሜዳሊያ ባለቤት መሆን ከፍተኛ ክብርን ያስገኛል። በዚህም\nምክንያት በኦሊምፒክ የርቀቱ ተካፋይ የሚሆኑት፤ ታዋቂና ልምድ ያላቸው አትሌቶች ናቸው። በፓሪስ ኦሊምፒክ ላይ ግን የትኛውም መሮጥ የሚፈልግ ሰው ተካፋይ መሆን እንደሚችል የዓለም ኦሊምፒክ ኮሚቴ\nአስታውቋል። ይህንን ዜና ተከትሎም የኦሊምፒኩን አስተባባሪ ኮሚቴ በፕሬዚዳንነት የሚመሩት ቶኒ ኢስታንጉዌት «ውድድሩን ልዩ ለማድረግ\nአንድ እርምጃ ተራምደናል። በርካቶችን የሚያሳትፉ የተለያዩ ውድድሮችም እንዲካተቱ አድርገናል። ተሳ ታፊዎች በየትኛውም ደረጃ ላይ\nቢገኙም በኦሊምፒኩ የተለየ ልምድ እንዲኖራቸው ማድረግ እንፈልጋለን» ሲሉ ገልጸዋል።በአሜሪካዋ የኒው ዮርክ ከተማ እአአ ከ1970 እንደተጀመረ የሚነገረው «ብሬክ» የተባለው የዳንስ ዓይነት፤\nባሳለፍነው ዓመት በቦነስ አይረስ በተካሄደው የወጣቶች ኦሊምፒክ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደ አንድ የውድድር ዓይነት ተካሂዶ ነበር።\nይህንን ተከትሎም በዋናው የኦሊምፒክ ውድድር ላይም ለማካተት መወሰኑን ፕሬዚዳንቱ ይጠቁማሉ።  ሊቀመንበሩ አክለውም\nከዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እንዲሁም የስፖርት ማህበራት ጋር በመስራት ላይ እንደሚገኙና ልምዱ በሌሎች ስፖርቶችም እንዲንጸባረቅ\nእንደሚሹም ገልጸ ዋል።አዲስ ዘመን የካቲት\n18/2011ብርሃን ፈይሳ __\n  ", "passage_id": "f353ba31d75c252e4f49b91071931a2d" }, { "passage": "የዓለም የዩኒቨርሲቲዎች ቻምፒዮና የእግር ኳስ ውድድር ትናንት በቻይናዋ ጂንጃንግ ከተማ ተጀምሯል።አፍሪካን በመወከል በውድድሩ ላይ የሚካፈለው ብቸኛው የኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲም ትናንት ከታይላንድ አቻው ጋር የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል፡፡ባለፈው ዓመት በመቐለ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት 9ኛው የአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ቻምፒዮና መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን በቻምፒዮናው ላይ በእግር ኳስ ስፖርት አሸናፊ የነበረው የኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ በመሆኑ አፍሪካን በመወከል በዓለም ቻምፒዮናው ላይ ለመሳተፍ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ወደ ቻይና አቅንቷል።በዚህ ቻምፒዮና ላይም ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች የተውጣጡ 16 የወንድ ቡድኖች እንዲሁም አራት የሴት ቡድኖች ይካፈላሉ፡፡በወንዶች በኩል ጨዋታው በአራት ምድብ ተከፍሎ የሚካሄድ ሲሆን፤ በምድብ አንድ የቻይና፣ አውስትራሊያ፣ ጀርመን እና ስፔን ዩኒቨርሲቲዎች ተደልድለዋል።በምድብ ሁለት ደግሞ ኢትዮጵያ፣ ከታይላንድ፣ ከቻይና እና ከሜክሲኮ ጋር ተደልድላለች።በሦስተኛው ምድብ ብራዚል፣ ኮሪያ፣ ዩክሬን እና ጣሊያን እንዲሁም በመጨረሻው ምድብ ላይም ክሮሺያ፣ ሩሲያ፣ ሆንግ ኮንግ እና ኡራጓይ ይገኛሉ።በሴቶች ደግሞ ቻይና፣ ብራዚል፣ አውስትራሊያ እና ስዊዘርላንድ በመጀመሪያው ምድብ የተካተቱ ሲሆን፤ ታይላንድ፣ ቻይና፣ ሩሲያ እና ፈረንሳይ በሌላኛው ምድብ ተደልድለዋል።ኢትዮጵያን እና አፍሪካን የሚወክለው ኮተቤም ለዚህ ውድድር ሁለት አሰልጣኞችንና 18ተጫዋቾችን በመያዝ ዝግጅት ሲካሄድ ቆይቷል።ቡድኑ በዋና አሰልጣኙ ዶክተር ወገኔ ዋልተንጉስ እየተመራ በኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ ልምምዳቸውን ሲያደርጉ የቆዩ ሲሆን፤ በተለያዩ የስፖርት አመራሮች ማበረታቻ ሲደረግላቸው ቆይቷል።ቡድኑ ወደ ቻይና ከማቅናቱ አስቀድሞም በብሔራዊ ቤተመንግሥት የባንዲራ ርክክብና ሽኝት ተደርጎላቸዋል።ጂንጃንግ በደቡባዊው የቻይና ክፍል የምትገኝ ሲሆን፤ በተለይ በእግር ኳስ ስፖርት ታዋቂ ከተማም ናት።በከተማዋ 14 እግር ኳስ ስታዲየሞች የሚገኙ ሲሆን መሰል ውድድሮችን ለማሰናዳትም ተመራጭ ናት። አዲስ ዘመን ኅዳር 12/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "477a78e354a95820c0fc37ac8e747437" } ]
65a4d23f1b9eedcdc2e06f1f3c9c4718
8cbcc5f269b0b8b7a519f07006145508
አዲስ ዘመን ድሮ
 የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ቀደምት ዘገባዎች በእጅጉ ተነባቢ ዛሬም ላገኛቸው በእጅጉ ተነባቢ ናቸው።እኛም ከእነዚህ ዘገባዎች ጋዜጣው በ1950ቹ ያስነበባቸውን ወጣ ያሉ ዘገባዎች ለዛሬ ይዘንላችሁ ቀርበናል። በዛሬው የአዲስ ዘመን ዱሮ አምዳችን አዲስ ዘመን ጋዜጣ በ1950ዎቹ ይዟቸው ከወጣ ዘገባዎች በአዘጋገባቸውና በይዘታቸው ተነባቢ ናቸው ያልናቸውን እና ሌሎች አስደናቂ ዘገባዎችን ይዘን ቀርበናል። ማገጃ ምልክት ይሰጠውማንኛውም የሥራ ድርጅት በብዙ ድካም ከተቋቋመ በኋላ አስፈላጊው ጥንቃቄ ካልተደረገለት የተሠራው እንዳልተሠራ የነበረው እንዳልነበር መሆኑ የማይጠረጠር ነው።በሲዳሞ ጠ/ግዛት ዋና ከተማ ይርጋዓለም የቴሌኮሙኒኬሽን ቦርድ ያቋቋመው ከፍተኛ መሥሪያ ቤት ይገኛል። የተቋቋመውም በትልቁ መኪና መንገድ አጠገብ ስለሆነ ፤ተሽከርካሪዎች የሚመላለሱበት ቦታ ነው።አንዳንድ ጊዜም ከባድ ጭነት የያዙ መኪናዎች ለምሳሌ አውቶቡስን የመሳሰሉት በሁለተኛው መንገድ እንዲያልፉ የሚታዘዙበት ቀን ስለሚያጋጥም በተጠቀሰው መሥሪያ ቤት አደባባይ የሚገኙትን ሽቦዎች ሳይመለከቱ ለማለፍ ሲሞክሩ በብዙ መጯጯህ ስልኩ ሽቦ ከመጣስ የዳነበትና መኪናውንም ለመመለስ የቻለበትን ጊዜ ለማታወስ የማይችል የለም፤ ታናናሽ መኪናዎችን ለማሳለፍ የቦታው ስፋት ይፈቅዳል።ስለ ታላላቅ መኪናዎች ግን የክፍሉ ባለሥልጣን የማገጃ ምልክት ቢያደርግበት የሚሻል መሆኑን አስታውሳለሁ። አቧራ አዋዜ አይደለም። በዚሁ ከተማ ትልቁን መንገድ በመከተል አልፎ አልፎ በሚገኙት ሰፈሮች ብዙዎች የልኳንዳ ሥጋ የተሰቀለባቸውና   ፉርኖ ይህንንም የመሳሰሉት ምግቦች የተደረደረባቸው ቤቶች ይገኛሉ። ሥጋው የሚገኝበት ብዙ ቦታ በረንዳ ስለሆነ ማናቸውም ተንቀሳቃሽና ይልቁንም በማይቋረጠው የመኪና ኃይል ከመንገዱ ላይ የሚነሳው አቧራ በሥጋውና በማናቸውም ምግብ ላይ ሲሰፍርበት ይታያል።ለማስረጃ ያህል በመንገዱ ዳር የሚገኘውን የቡና የሌላውንም ቅጠል የተመለከትን እንደሆነ በአንዱ ቅጠል ላይ ብቻ አንድ ጥርኝ የሚሞላ አቧራ ስለምናገኝ በየቀኑ በያንዳንዱ ብልት ሥጋ ላይ ተደባልቆ ወደ ሆድ የገባውን አቧራ ለመገመት እንችላለን። ስለዚህ ሥጋና ፉርኖ ይህንንም የመሳሰለ ምግብ የሚያሰናዱ ነጋዴዎች ለዚሁ አገልግሎት በዘመናዊ ዕቅድ በተሰናዳው መስታወት ውስጥ ማኖር ይገባቸዋል።ይህም ባይቻል አቧራ ወደሌለበት ሁለተኛው መንገድ እንዲዛወሩ ማድረግ ስለሚገባ ፤ሥራው የሚመለከተው ባለሥልጣን ያስብበት ዘንድ ሳስታውስ በትሕትና ነው። መመሳሰል ይገባዋልበዚሁ ከተማ የሚገኘው የጠቅላይ ግዛቱ በጅሮንድ ጽ/ቤት በሦስት ቦታ ተከፋፍሎ የሚገኝ ከመሆኑም በላይ ቤቱም በጠላት ጊዜ የተሠራ አሁን መፍረስ የጀመረ ነው።ስለ የውስጥ ዕቃውም አጠባበቅ ከቤቱ ይልቅ ዘበኞቹንና ካዝናውን ማመን ግድ ሳይሆን አይቀርም። ይኸውም ሆኖ ለሥራው የተመጠነ ስፋት ያለው አይደለም። በአካባቢው የሚገኙት ቢሮዎች በአማረና በጥሩ ሕንፃ የተሠሩ ሲሆኑ፤ የተጠቀሰው መሥሪያ ቤት እርጅና የእነሱን ውበት ግርማ አሳንሶታል።ስለዚህ ጓደኞቹን እንዲመስል የክፍሉ ባለሥልጣን ይተጋበት ዘንድ ማሳሰብ የጋዜጣው ፋንታ ነው። የሲዳሞ ጠ/ግዛት አዣንስ ኃይለ መስቀል ወልደየስ (የካቲት 20 ቀን 1951 የወጣው አዲስ ዘመን) ሁለት ወንዶች ልጆችእናት በአስር ቀን ልዩነት ሁለት ወንዶች ልጆች ወለደች። በወቅቱ ዜናው ጋዜጣችን ላይ ሲወጣ ርዕሰ ዜናው ከላይ እንደተጠቀሰው ሁለት ወንዶች ልጆች ብቻ ነበር የሚለው በሚከተለው መልኩ ተዘግቦ ስለነበር እንድታነቡት እንጋብዛለን። በደብረ ታቦር ከተማ ዙሪያ ቃናት ማርያም ከተባለው አገር የአቶ መኰንን ካሳ ባለቤት ያልጋነሽ አድማሱ የተባለችው ፤ጥር 22 ቀን 51ዓ.ም ከሌሌቱ 8 ሰዐት ሲሆን አንድ ወንድ ልጅ ከወለደች በኋላ 10 ቀን ቆይታ የካቲት 2 ቀን 1951 ዓ.ም ከጥዋቱ 1 ሰዐት ሲሆን አንድ ወንድ ልጅ ደግማ መውለዷንና ሁለቱም ልጆች እስካሁን በሕይወታቸው መኖራቸውን የነዚሁ ልጆች አባት አቶ መኰንን ካሳ አስታውቀውናል። የደብረ ታቦር ከተማው ዙሪያ ምክትል ገዥ ባላምባራስ ኃይሌ ታምራት በቁጥር100/1951የካቲት 10 ቀን በተጻፈ ደብዳቤ አረጋግጠውልናል።እኒህ የምክትል ወረዳ ገዥ እንደዚህ ያለው ሁኔታ በጋዜጣ እንዲገለጥ በቶሎ ለአውራጃው ግዛት አዣንስ ጽ/ቤት በማስተላለፋቸው እናመሰግናለን። ሌላዎችም ምክትል ገዥዎች የርሳቸውን አርአያ ተከትለው ይህን የመሰለ ጉዳይ ሲያጋጥማቸው በፍጥነት የሚያስታውቁን ቢሆን ከፍ ያለ ምስጋና የሚያገኙበት መሆኑን እንገልጻለን።የደብረ ታቦር አውራጃ አዣንስ አሰፋ ረታ (የካቲት 17 ቀን 1951 የወጣው አዲስ ዘመን)
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=38334
[ { "passage": "መኳንንት ጌጡ በከብት ንግድ ላይ ከተሰማራ ከአሥር ዓመት በላይ አልፎታል። በጎችና ፍየሎችን ከገበሬዎች እየገዛ ለአዲስ አበባ ነጋዴዎች የሚያከፋፍለው መኳንንት በሥራው ላይ ብዙ ጊዜያትን ቢያሳልፍም፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ገበያው ተገማች ባለመሆኑ ኪሳራ ውስጥ እየወደቀ መሆኑን ይናገራል። ለአብነትም ባለፈው የአዲስ ዓመት በዓል ገበያ ይኖራል በሚል ዕሳቤ በከፍተኛ ዋጋ በጎችና ፍየሎችን ከገበሬዎች ገዝቶ የነበረ ቢሆንም፣ ሸማቾች ዋጋ በመወደዱ እንዳልገዙት ያስታውሳል። ‹‹ገበሬዎች ዋጋ በመጨመራቸው የተነሳ እኔም ይህንን ማካካስ ነበረብኝ፤›› የሚለው መኳንንት፣ ዋጋ በመጨመሩ ምክንያት ሸማቾች ፍላጎት የነበራቸው ቢሆንም፣ ሊገዙት እንዳልቻሉ፣ ምንም እንኳን በጎቹን ከበዓል በኋላ በአነስተኛ ዋጋ ቢሸጣቸውም፣ ከፍተኛ ኪሳራ ደርሶበት እንደነበር ያወሳል። ታዲያ ለዘንድሮ ገና በዓል ከአዲስ ዓመት ገጠመኙ ትምህርት በመውሰድ ረከስ ባለ ዋጋ ከገበሬዎች ቢገዛም፣ የሸማቾች ፍላጎት በጣም ወርዷል ይላል። ‹‹ከጊዜ ወደ ጊዜ ገበያውን መገመት አዳጋች እየሆነ ነው፤›› የሚለው መኳንንት፣ በተለይ በአገሪቱ የሚስተዋለው አለመረጋጋት ሸማቾች በተረጋጋ መንፈስ እንዳይሸምቱ እንዳደረጋቸው ምልከታውን ያጋራል። የገና ገበያ ምን ይመስላል?በዘንድሮ የገና በዓል ገበያ ከአዲስ ዓመት አኳያ የምግብ ምርቶች ዋጋና የአቅርቦት መረጋጋት ቢያሳዩም፣ የሸማቾች ቁጥር ብዙም ጭማሪ አለማሳየቱን ነጋዴዎች ይናገራሉ። የሪፖርተር ዘጋቢዎች በቦሌ፣ ሾላ፣ መርካቶና ቄራ በሚገኙ ገበያዎች ባለፉት ሁለት ቀናት ያደረጉት ዳሰሳ እንደሚያሳየው፣ በተለይም የዶሮ፣ የበግና የፍየል አቅርቦት ካለፈው በዓል አንፃር ጭማሪ አሳይቷል። በአዲስ ዓመት ወቅት እስከ 550 ብር ሲሸጥ የነበረው የዶሮ ዋጋ በገና ወደ 400 ብር የወረደ ሲሆን ከወላይታ፣ ከአርባ ምንጭ እንዲሁም በአዲስ አበባና ዙሪያ ከተሞች የዶሮዎች ቁጥር መጨመሩ እንደ ምክንያት ተነስቷል። ከበግና በፍየል ገበያ መረጋጋት ታይቷል። ‹‹ባለፈው በዓል (አዲስ ዓመት) ከኦሮሚያ አንዳንድ ከተሞች ይመጡ የነበሩ በግና ፍየሎች በነበረው አለመረጋጋት የተነሳ ቁጥራቸው ቀንሶ የነበረ ሲሆን፣ በገና በዓል ይህ ችግር ተቀርፏል፤›› የሚለው በቄራ አካባቢ የሚሠራው ሰዒድ መሐመድ የተባለ ነጋዴ ነው፡፡ ይህም ዋጋ እንዲረጋጋ ትልቅ ሚና እንደተጫወተ አስረድቷል። የሸማቾችም አስተያየት ከዚህ ብዙ የተለይ አይደለም። ‹‹በአዲስ ዓመት ሁሉ ነገር ተወዶ ነበር፤›› የሚሉት ተመሥገን ቢተው የሚባሉ ሪፖርተር በቦሌ አካባቢ ያገኛቸው ሸማች፣ የበግና የፍየል ዋጋ ከፍተኛ ቅናሽ ማሳየቱንና የተሻሉ አማራጮቹም በዘንድሮ በዓል መታየታቸውን ተናግረዋል።በአዲስ ዓመት ወቅት እስከ 6,000 ብር ሲሸጥ የነበረው መካከለኛ መጠን ያለው በግ በዘንድሮ ገበያ ወደ አራት ሺሕ ብር ዝቅ ያለ ሲሆን፣ ሙክት የሚባል የሰባ በግ ከ9,000 ብር ወደ 6000 ዝቅ እንዳለ ነጋዴዎች ተናግረዋል። በተመሳሳይ ከፍተኛው የፍየል ዋጋ ከ12,000 ብር ወደ 8,000 ብር ዝቅ ማለቱን፣ አነስተኛ ክብደት ያለው የፍየል ዋጋ ከአንድ ሺሕ ብር በላይ ቅናሽ በማሳየት በ3,000 ብር ሲሸጥ ተስተውሏል። እንደ ገበያው ቅርበት ቢለያይም በአዲስ አበባ ሲሸጡ የነበሩ ፍየሎችና በጎች በብዛት ከደብረ ብርሃን፣ ከዱበር፣ ከጊንጪ፣ ከደሴና ከጅማ የመጡ ናቸው፡፡ ሠንጋዎች በአብዛኛው ከምሥራቅ ኦሮሚያ በተለይም ሐረርጌ ዞን ውስጥ ከሚገኙ አነስተኛ ከተሞች የመጡ እንደሆኑ ሪፖርተር በከተማው ያደረገው ዳሰሳ አመላክቷል። በተጨማሪ ቅልብ ሠንጋዎች በአብዛኛው ከአዳማ፣ ከባሌና ከአርሲ የገቡ ሲሆን ከጎንደርና ከወለጋ የመጡ ሠንጋዎች ቁጥር ላይ ቅናሽ መታየቱን ለማወቅ ተችሏል። በግና ፍየል ላይ የታየው የዋጋ መቀነስ ሠንጋዎች ላይ የታየ ሲሆን፣ እስከ 5,000 ብር የሚደርስ ቅናሽ ተስተውሏል። የሐረር ሠንጋዎች ከ34,000 ብር አንስቶ እየተሸጡ የነበረ ሲሆን፣ ዝቅተኛ ዋጋ ያላቸው ሠንጋዎች ደግሞ ከ10,000 ብር እስከ 12,000 ብር ድረስ ሲሸጡ ተስተውሏል። ያላቸው ክብደት መካከለኛ የሚባሉት ሠንጋዎች ደግሞ ከ12,000 ብር እስከ 18,000 ብር ሲሸጡ ተስተውሏል። ይሁን እንጂ በአዲስ አበባ በቅርጫ ሠንጋ የመግዛት ልማድ እየቀነሰ በመምጣቱ፣ በብዛት ሠንጋዎችን የሚገዙት ልኳንዳዎች መሆናቸውን ማወቅ ተችሏል። በሌላ በኩል ከአቅርቦት አኳያ ከአዲስ ዓመት መሻሻል ቢታይም፣ የገዥዎች ቁጥር ላይ እምብዛም ለውጥ እንዳልታየ አሸናፊ ሽፈራው የተባሉ የከብት ነጋዴ ለሪፖርተር ተናግረዋል። ለዚህም እንደ ምክንያት ያነሱት፣ ‹‹በዓሉ በሐሙስ ቀን መዋሉን›› ሲሆን፣ በማግሥቱ የፆም ቀን በመሆኑ የገዥዎች ፍላጎት ቀንሷል ብለዋል፡፡ የሠንጋ ዋጋ መረጋጋት ቢያሳይም ልኳንዳ ቤቶች በሥጋ ዋጋ ላይ ቅናሽ ማድረጋቸው አልታየም። በአንዳንድ አካባቢዎች ከወዲሁ ጭማሪዎች እየታዩ ሲሆን፣ በአሁኑ ጊዜ የአንድ ኪሎ ሥጋ ዋጋ ከ200 ብር እስከ 600 ብር እየተሸጠ መሆኑን ሪፖርተር ያደረገው ዳሰሳ ያሳያል፡፡  በሌላ በኩል በዓልን ተከትሎ በስፋት በጥቅም ላይ ከሚውሉ ምርቶች መካከል የሆነው ቅቤ ዋጋ ላይ እስከ 20 ብር ጭማሪ የታየ ሲሆን፣ በመርካቶና በሾላ ገበያዎች በኪሎ እስከ 290 ብር ሲሸጥ ተስተውሏል። ከአቅርቦት አኳያ ካለፈው በዓል አንፃር የተሻለ ሁኔታ እንደነበር ነጋዴዎች ተናግረዋል። በተመሳሳይ በኮረሪማ አቅርቦት ላይ መሻሻል መታየቱን ተከትሎ ከአዲስ ዓመት አኳያ እስከ 80 ብር የሚደርስ ቅናሽ ታይቷል። በሾላና በመርካቶ ሪፖርተር ባደረገው ዳሰሳ በኪሎ እስከ 170 ብር ሲሸጥ ተስተውሏል። በአዲስ ዓመት ወቅት እስከ 38 ብር ሲሸጥ የነበረው የሽንኩርት ዋጋ ወደ 17 ብር የቀነሰ ሲሆን፣ የነጭ ሽንኩርት ዋጋም ከ160 ብር ወደ 100 ብር ወርዷል፡፡በምግብ ምርቶች ላይ የታየው መረጋጋት ምግብ ነክ ያልሆኑ ምርቶች ላይ ሊታይ አልቻለም። ለአብነት አልባሳቶችን ማንሳት ይቻላል።በመርካቶ፣ በፒያሳና በሃያ ሁለት አካባቢዎች የሪፖርተር ዘጋቢ ባደረገው ዳሰሳ መሠረት፣ ከውጭ የሚገቡ ሱሪዎች ላይ ከ100 ብር እስከ 200 ብር የሚደርስ ጭማሪ የታየ ሲሆን፣ የወንድና የሴት ጫማዎች ላይ ከ50 ብር እስከ 150 ብር ጭማሪ ታይቷል። ከቻይና የሚገቡ ምርቶች በውጭ ምንዛሪ እጥረት የተነሳ አቅርቦታቸው መቀነሱ እንደ ምክንያት ተወስቷል። በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከውጭ ከሚገቡ አልባሳት ውስጥ 90 በመቶ ከቻይና በመሆናቸው፣ ያለው የአቅርቦት ችግር ካልተፈታ የታየው የዋጋ ጭማሪ ከፍተኛ ሽያጭ ይኖራል ተብሎ በሚገመትበት የጥምቀት በዓል ላይ የበለጠ ሊጨምር እንደሚችል፣ አብሽሮ አወል የተባሉ በልብስ ንግድ ላይ የተሰማሩ ነጋዴ ተናግረዋል። ባለፉት ሦስት ወራት የታየው የምርት እጥረት በዓይነቱ የከፋ መሆኑን ሪፖርተር ያነጋገራቸው ነጋዴዎች የተናገሩ ሲሆን ከዱባይ የሚገቡ ምርቶች ላይ የሚጣለው ቀረጥ ከፍ ማለቱም ለታየው የዋጋ ጭማሪ ምክንያት እንደሆን አስረድተዋል፡፡የታየው የዋጋ ግሽበት በዚህ አያበቃምበአገር ውስጥ የሚመረቱ ጫማዎች የችርቻሮ ዋጋ ላይ እስከ 100 ብር የሚደርስ ጭማሪ ታይቷል። በተለይም ጫማ ለማምረት የሚውሉ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች አቅርቦት በመቀነሱና የፋብሪካዎች የማምርት አቅም በመውረዱ የጫማ ዋጋ ሊጨምር እንደቻለ፣ አማኑኤል መንግሥቱ የተባሉ በአመዴ አካባቢ የጫማ ንግድ ላይ የተሰማሩ ነጋዴ ተናግረዋል። የሸማቾች ልበ ሙሉነትበኢትዮጵያ በተደጋጋሚ የሚታየው አለመረጋጋት፣ የሸማቾች ልበ ሙሉነት (consumers’ confidence) ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚያሳድር ግልጽ ነው። በተለይም አለመረጋጋቶች በሚከሰቱ ጊዜ ሸማቾች የምግብ ምርቶች ይጠፋሉ በሚል ፍራቻ በብዛት ሲገዙ ማየት የተለመደ ሲሆን፣ በእንዲህ ዓይነት ወቅቶች እንደ አልባሳት ላሉ ምግብ ነክ ላልሆኑ ምርቶች ያለው ፍላጎት ሲቀንስ ይስተዋላል። በገና በዓል የዋዜማ ገበያ ላይ የታየው ከዚህ የተለየ እንዳልሆነ ነጋዴዎች ያስረዳሉ፡፡ በአገሪቱ ያለው አለመረጋጋት በከፋ ቁጥር ሸማቾች ልበ መሉነታቸው ስለሚቀንስ የሚያወጡት ገንዘብ ይቀንሳል የሚሉት የጫማ ነጋዴው አማኑኤል፣ አለመረጋጋቶች በተከሰቱ ቁጥር የሽያጭ ገቢያቸው ወዲያውኑ እንደሚቀንስ ይናገራሉ፡፡ የኮሮና ወረርሽኝ የተከሰተ ሰሞን ሸማቾች በመደናገጣቸው ምግብ ነክ ያልሆኑ ምርቶችን መግዛት አቁመው እንደነበር ያወሱት አማኑኤል፣ ከዚያም የሃጫሉን ሞት ተከትሎ በተከሰተው የፖለቲካ አለመረጋጋትና በትግራይ በነበረው ግጭት የተነሳ ተመሳሳይ ችግር ገጥሟቸው እንደነበር ተናግረዋል። ይሁን እንጂ አሁን በአገሪቱ አንፃራዊ ሰላም እየታየ በመሆኑ የሸማቾች ልበ ሙሉነት ስለጨመረ የንግድ እንቅስቃሴው የተሻለ መሆኑን የሚናገሩት አማኑኤል፣ በገና በዓል ገበያ ከአዲስ ዓመት የተሻለ ሽያጭ ማስመዝገባቸውን አውስተዋል። በሌላ በኩል በአገሪቱ አንፃራዊ ሰላም ቢታይም ሸማቾች ከፍተኛ ገንዘብ ለማውጣት ያላቸው ፍላጎት ብዙም አላደገም የሚሉት በከብት ንግድ ላይ የተሰማሩት መኳንንት፣ አሁንም መንግሥት ይህንን ለመቅረፍ መሥራት እንደሚገባው አውስተዋል። በተመሳሳይ የሸማቾች ልበ ሙሉነት ወሳኝነት እንዳለው የሚናገሩት የምጣኔ ሀብት ባለሙያው አቶ አየለ ገላን ሲሆኑ፣ ለኢኮኖሚ ዕድገት ሞተር በመሆን እንደሚያገልግል ያስረዳሉ። ‹‹ሸማቾችና ነጋዴዎች በምጣኔ ሀብት ላይ ያላቸው መተማመን የተሻለ ሲሆን፣ የኢኮኖሚው ዕድገትም የተሻለ ይሆናል። ይህንን ማድረግ ካልተቻለ ደግሞ አገሪቱ የምታሳየው ዕድገት ይቀንሳል፤›› በማለት፣ የሸማቾች ልበ ሙሉነት ለኢኮኖሚ ዕድገትና መረጋጋት ያለውን የማይተካ ሚና የመንግሥት የፖሊሲ አውጪዎች ሊረዱት ይገባል ሲሉ አቶ አየለ ሐሳባቸውን ለሪፖርተር አጋርተዋል። በሳምሶን ብርሃኔ", "passage_id": "a5b7e6e5832e7a77d46647633ddc3e72" }, { "passage": "የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ተመስገን ጥሩነህ የ2012 አዲስ ዓመት ዋዜማ ልዩ ዝግጅት መልዕክትሙሉ መልዕክቱን ያንብቡትየተከበራችሁ የአማራ ክልል ህዝቦች፤የተከበራችሁ መላው የአገራችን ህዝቦች፤ክቡራን የሃይማኖት አባቶች፤የተከበራችሁ የፌዴራልና የክልል የስራ ኃላፊዎች፤የተከበራችሁ የዞን፣ የከተማ፣ የወረዳና የቀበሌ አመራሮች፤ክቡራን የባህር ዳር ነዋሪዎች፤ክቡራን ጥሪ የተደረገላችሁ ምሁራንና ባለሃብቶችክቡራትና ክቡራንበቅድሚያ ሁላችንንም እንኳን ከዘመን ዘመን በሰላም አሸጋገረን፡፡ መልካም አዲስ ዓመት፤ እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን ለማለት እወዳለሁ፡፡ በዚህ አይነቱ ለየት ባለ ሁኔታ በተዘጋጀ የአዲስ ዓመት ዋዜማ ዝግጅት ተገኝቼ መልዕክት ማስተላለፍ በመቻሌ የተሰማኝ ደስታ እጥፍ ድርብ መሆኑን እየገለፅኩ ‹‹ማቅ አውልቀን፤ ግምጃ እንልበስ›› በሚል መሪ ሃሳብ በተዘጋጀው በዚህ የዋዜማ ክብረ በዓል ላይ ጥሪ ስናስተላልፍላችሁ ፈቅዳችሁ የአዲስ ዓመት ዋዜማ ክብረ በዓላችን ተካፋይ ለመሆን በመምጣታችሁ በክልሉ መንግስት፣ በህዝቡና በራሴ ስም ላቅ ያለ ምስጋናዬን እያቀረብኩ የአማራ ክልል ርዕሰ መዲና ወደ ሆነችው ውቢቷ ከተማችን ባህር ዳር እንኳን ደህና መጣችሁ ለማለት እወዳለሁ፡፡ክቡራትና ክቡራን፡-ኢትዮጵያ የፍጥረታት ሁሉ መነሻ ምድረ ቀደምት፣ የጥንታዊ ታሪክ ባለቤት፣ የገናና ስልጣኔ አምባ፣ የአኩሪ ተጋድሎ እና ድል ባለቤት ሀገር ስትሆን ኢትዮጵያዊነት ደግሞ የኩራት ምንጭ ነው፡፡ ኢትዮጵያዊነት የኩራት ምንጭ ነው ስንል ሀገሪቱ ጥንታዊነት እና የገናና ስልጣኔ ባለቤት የነበረች መሆኑ ብቻ ሳይሆን የበርካታ ውብ ባህሎች ሀገር በመሆኗም ጭምር ነው፡፡ የኢትዮጵያውያን ባሕሎች ዘርፈ ብዙ እና ውቦች ናቸው፡፡ ከባሕላችን መገለጫዎች መካከል አንዱ የበዓል አከባበር ስርዓታችን ነው፡፡ በዓላት ለእኛ ለኢትዮጵያውያን ልዩ ቦታና ትርጉም አላቸው፡፡ በተለያዩ በዓላቶቻችን እንደ ሕዝብ ትዝታችን ተጽፎባቸዋል፤ ህብረታችን ታትሞባቸዋል፣ ማህበራዊ ትስስራችን ተገምዶባቸዋል፤ ተስፋችን ተበስሮባቸዋል፡፡ የዘመን መለወጥን ማብሰሪያው የአዲስ ዓመት በዓልም ሁላችንም ኢትዮጵያውያን በጋራ የምናከብረው፤ ከከረምንበት ጭጋጋማ ብርዳማ ክረምት፣ ተስፋን ወደምትፈነጥቀው የጸደይ ፀሀይ፤ ማብሰሪያ ወቅት የሚከበር በመሆኑ፤ ልዩ ስሜት ይሰጣል፤ ለዚህም ነው ብዙዎቻችን የአዲስ ዓመት በዓል ትዝታ የሚናፍቀን፡፡አገራችን ኢትዮጵያ የተገነባችበት ሁኔታ፤ እንደ ታሪኳ ሁሉ ረዥም ጊዜ የፈጀ፣ በጥልቅ ጥበብ የተበጀ ነው፡፡ ይህቺ ድንቅ አገር የተገነባችው በቅድመ አያቶቻችን ብርቱ ታታሪነት፣ደም እና አጥንት ነው፡፡ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስከበር እና ክብሯን ለማስጠበቅም፤ የአማራ ክልል ሕዝቦች ከሌሎች እህት እና ወንድም ኢትዮጵያውያን ጋር በመሆን ሳይሰስቱ ፊት ለፊት ግንባራቸውን ሰጥተዋል፡፡ ለዚህም ቅዱስ ተግባራቸው ለዘላለም ስናከብራቸው፣ ስናመሰግናቸው እና ስንመካባቸው እንኖራለን፡፡ዓለም የሚመሰክረው እኛም የምናውቀው ሀቅ የአማራ ክልል ሕዝቦች መነሻ እና መድረሻቸው፤ የኢትዮጵያ ጥንካሬ እና ታላቅነት ነው፡፡ ይህም ዕውን የሚሆነው፤ በሁሉም የኢትዮጵያውያን ሕብር እና እኩልነት እንደሆነ በጽኑ ያምናሉ፡፡ የአማራ ክልል ሕዝቦች፤ በኢትዮጵያ አገር ግንባታ ሂደት ውስጥ የተለያዩ ፈተናዎችን አልፈዋል፡፡ በተለይም ኢትዮጵያን ለማፍረስ የፈለገ ጠላት ሁሉ፤ የመጀመሪያ ኢላማ አድርጎ ግፍና መከራ የሚያደርስበት፣ ባህሉን ለማጥፋት የሚረባረብበት፤ ወጉን ለማኮስመን የሚታትርበት የአማራ ክልል ሕዝቦችን ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ይህ የሆነበት አበይት ምክንያ የአማራ ክልል ሕዝቦች ለኢትዮጵያ እና ለህብረ ኢትዮጵያዊነት ቀናኢ በመሆናቸው ነው፡፡በመሆኑም ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን ለመካድና ለመርሳት ወይንም ለመጥራት እና በውስጣቸው ለመኖር መስጋት፤መጠራጠር፤ መዘንጋት ለሚሹ አካላት ከላይ የጠቀስኳቸውን የኩራት ምንጮች የሆኑ ውብ የአባቶቻችን ባህል፣ ወግ፣ ወኔና ጀግንነት አለማወቅ፤ ወይንም እያወቁ ሆነ ብሎ ማጥፋት በመሆኑ የእንዲህ አይነት አባዜ የተጠናወታቸው አካላት ሁሉ፤ በአዲሱ ዓመት ፈጣሪ ቅን ልቦና እንዲሰጣቸው እንመኛላቸዋለን፡፡ክቡራንና ክቡራት፡-ባለፉት በርካታ ዓመታት በመጣንበት ጉዞ ውስጥ ያጋጠሙ ፈተናዎች እና ሳንካዎች እጅግ ብዙ እና ውስብስብ ቢሆኑም ከፊሉን ተገዳድረን እያለፍን ብዙውን ግን በአሸናፊነት እየተወጣን እዚህ ደርሰናል፡፡ በየጊዜው ያጋጠሙንን ፈተናዎች እንዴት ማለፍ እንደቻልን ልምድ እና ተሞክሮ ያለን ህዝቦች ስለሆን፤ ባለፉት ጊዜያት በአገራችን በተለይም በክልላችን ያጋጠሙንን ፈተናዎችም፤ በአሸናፊነት መወጣት ጀምረናል፡፡ ችግር ሲያጋጥመን እንዴት መፍታት እንዳለብን የተማርነው፤ ከቀደምት አባቶቻችን ነው፡፡ እኛ የጠበብት አባቶች ልጆች ነን፡፡ አይደለም በጥንታዊቷ ይቅርና በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እንኳ የኢትዮጵያንም ሆነ የአማራን ሕዝብ በእጅጉ ህልውናውን የሚፈታተኑ፣ አያሌ ጉድጓዶች ተምሰዋል፡፡ ይሁንና፤ በፈተና ወቅት ወደ ኋላ መንደርደር ማለት ለባለ ራዕይ ወደ ፊት እንዴት እንደሚያስወነጭፍ አባቶቻችን አስተምረውናል፡፡ እኛም የአባቶቻችን ልጆች ነንና፤ ዛሬም ብዙ የችግር አረንቋዎች አልፈን እዚህ ደርሰናል፡፡ አበው እንደሚሉት ችግር ሲገጥመው የሚደነግጥ ከዚህ ቀደም ያለ ችግር የኖረ ሰው ነው፡፡ በብዙ ችግር ያለፈ ሰው ግን የሚያጋጥመውን ፈተና በብቃትና በአሸናፊነት ይወጣዋል፡፡ እኛም እንደ ሕዝብ የብዙ ተግዳሮቶች ውል የሚፈታበትን ጥበብ የያዝን ስለሆነ ባለፈው ጊዜ በክልላችነ አጋጥሞን የነበረውን አስጨናቂና ከባድ ጊዜ ተቋቁመን ይኸው እዚህ ደርሳል፡፡ ይህ ክስተት ያደረሰብን የህይወት የንብረትና የስነ ልቡና ጉዳት ከባድ ቢሆንም በደረሰብን ሀዘን እየቆዘምን እንደ ዶሮ አንገት ደፍተን መሬት ስንጭር የምኖር ደካሞች አይደለንም፡፡ክቡራንና ክቡራት፡-አጋጥሞን የነበረው ጉዳት ጥልቅ ሀዘን ውስጥ ቢያስገባንም ለሕዝባችን ስንል ከሀዘን ቶሎ መውጣት ነበረብን፡፡ ሀዘን ማብዛት ትረፉ የበለጠ ለችግር መጋለጥ ነው፡፡ መሪ በደስታ ጊዜ ብቻ ሳይሆን በሀዘን ጊዜም ጭምር ሕዝቡን እየመራ ማሻገር አለበት፡፡ በሀዘን በመቆዘም የምናተርፈው ነገር የለም፡፡ የሚሻለን የወንድሞቻችንን ህልም እውን ማድረግ ነው፡፡ ስለሆነም ያጋጠመን ጉዳት ወደ ባሰ ችግር ሳይሸጋገር ከሕዝባችን ጋር ሆነን በጥበብ በመወጣት ከማቅ ወደ ግምጃ ከምንሻገርበት ቀን ደርሰን፤ ይኸው ዛሬ በእናንተ ፊት ግምጃ ለብሰን መቆም ችለናል፡፡የማያሳፍረንና የማያሳንሰን የክልላችን ሕዝብ፤ ከጎናችን ሁኖ ስለደገፈን በሕዝባችን አይዞህታ ተረጋግተንና ተበረታተን፤ ይኸው ዛሬ ማቅ አውልቀን ግምጃ ለብሰን ለተጨማሪ ተስፋ እና ድል ወደ መጪው ብሩህ ዓመት እንሸጋገር ዘንድ ቆርጠን ተነስተናል፤ አዲሱን ዓመት ስንቀበል ከሕዝባችን ጋር ጣትና ጥፍር ብቻ ሳይሆን ደምና የደም ስር ሆነን የምናከናውናቸውና ውጤት የምናስመዘግብባቸው በርካታ ተግባራት ሰንቀናል፡፡ በአዲሱ ዓመት “ማቅ አውልቀን ግምጃ እንለብሳለን” ስንል ከመቼውም ጊዜ በላቀ መንገድ ለሁለንተናዊ ልማትና ለፍትሃዊ ተጠቃሚነት እንሰራለን ማለታችን ነው፡፡በመሆኑም በመጪው ዓመት የተስፋ ግምጃችንን ለመልበስ ጠንካራ የመንግስትና የፓርቲ አደረጃጀትና ተቋማዊነት እንፈጥራለን፡፡ ህግን የማስከበርና የሕዝብን ደህንነት ዋስትና የሚሰጥ የፀጥታ እና ፍትህ መዋቅሮችን ተደራሽና ጠንካራ እናደርጋለን፡፡ ለዘመናት ስር ሰዶ ያለውን ድህነት የመቀነስ ትግል አጠናክረን የልማትና የኢንቨስትመንት ተግባራትን ከምንጊዜም በተሻለ ቁርጠኝነት ለማሳካት እንረባረባለን፤ ግብርና ትልቁ የትኩረት ማዕከላችን ይሆናል፤ የሥራ ዕድል ፈጠራ በሁሉም ዘርፎች በተለይም ደግሞ በግብርና ኢንቨስትመንት፣ በቱሪዝም ዘርፎች በተለየ ሁኔታ ትኩረት ሰጥተን እንሰራለን፤ በመጪው ዓመት ክልላችንን ብቻ ሳይሆን ሀገራችንንም ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያላቸው ፋብሪካዎችን ስራ ለማስጀመር ጥረት ይደረጋል፤ በእነዚህም ትርጉም ያለው የሥራ ዕድል ለመፍጠር በትኩረት እንቀሳቀሳለን፡፡ ከክልል ውጭ የሚኖሩ የአማራ ክልል ተወላጆች ሁለንተናዊ መብታቸው እንዲከበር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራና በትብብር እንሠራለን፡፡ በአገራችንና መላው ዓለም ከሚገኙ ምሁራን ባለሀብቶችና ከመላው ሕዝብ ጋር በመቀራረብና በመመካከር የልማት የሰላምና የዴሞክራሲ ትግላችንን በትብብር ለመሥራት ከምንጊዜውም በላይ እንተጋለን፤ በተለያዩ አካባቢዎች የሚነሱ የማንነትና የአስተዳደር ወሰን ጥያቄዎች የሕዝባችንን ደህንነት እና ሕገ መንግስታዊ መብት በሚያረጋግጥ ሕጋዊና ዴሞክራሲያዊ አግባብ የሕዝቦችን ፍትሐዊ ተጠቃሚነት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ እና አገራዊ አንድነት ለመፍጠር እየተሠራ ነው፡፡ክቡራትና ክቡራን፡-በዚህ ልዩ የዋዜማ ዝግጅት በሀዘናችን ወቅት ከጎናችን ለነበሩ ሁሉ ምስጋናና በእግረ መንገዱም አደራ አቀርብ ዘንድ እንድትፈቅዱልኝ እጠይቃለሁ፤እናንት የእውነተኛ ህብረ መገለጫ የሆናችሁ የአማራ፣ የአገው፣ የኦሮሞ፣ የአርጎባ፣ የቅማንት በጥቅሉ የክልላችን ሕዝቦች፣ በተለይም ደግሞ የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዎች በዚያ የማቅ ወቅት ከጎናችን ባትሆኑ ኖሩ ዛሬ ለዚህ ግምጃ አንደርስም ነበር፡፡ ለአስተዋይነታችሁና ለአርቆ ተመላካችነታችሁ ክብር ይገባችኋልና የክልሉ መንግሥት በእጅጉ ያመስግናል፡፡ እናንተን ይዘን የማናሳካው እቅድ አይኖረንም፡፡ በመሆኑም መላው የክልላችን ሕዝቦች ከክልሉ ወጪና በተለያየ የዓለም አካባቢ የምትኖሩ ወገኖቻችን እኛ ህልማችን በሁለንተናዊ መልኩ የለማና ያደገ ሕዝብና ከባቢ መፍጠር ነውና፤ ለዚህ እውን መሆን ከመቼውም በላይ ቆርጠን እንደተነሳን አውቃችሁ ከጎናችን በመሆን እንድታግዙን ስንደክም እንድታበረቱን ስንሳሳት እንድታርሙን በዚህ አጋጣሚ ጥሪ ለማቅረብ እወዳለሁ፡፡ እናንተ የዕምነት ተቋማት የሃይማኖት አባቶች፤ የአገር ሽማግሌዎች ያለ እናንተ ተግሳፅና ምክር፤ ያለ እናንተ ቡራኬና ፀሎት፤ እንዲሁም ያለ እናንተ ግልግልና እርቅ አገር አይረጋም፡፡ በሃገራችን ያሉ ሁሉንም ሃይማኖቶች አስተምህሮ ስንመረምረው ሁሉም ሰላምን፣ ፍቅርን፣ መቻቻልን፣ መተባበርንና አንድነትን የሚያስተምሩ ናቸው፡፡ የኛ ህዝብ እንኳን የሰው ሊወስድ የወደቀ ቢያገኝም አንስቶ ለባለቤቱ የሚሰጥ፣ ጠብ ቢያጋጥመው በህግ አምላክ የሚል፣ እንግዳ ቢመጣበት እግር አጥቦና ከአልጋው ወርዶ የሚያስተናግድ፣ ምን ይሉኝ የሚገደው ሆኖ የዘለቀው በእናንተ አስተምህሮ ነው፡፡በተለይም የክርስትናም ይሁን የእስልምና አስተምህሮት በሀገራችን ኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ትውልድን በጥሩ ስነ ምግባር በመኮትኮትና በማሳደግ ፊደል ቀርፆና ብራና ፍቆ አሁን ለደረስንበት ዘመናዊ ትምህርት መሰረት የጣለ ሃገራችን ኢትዮጵያ በተለያዩ ጊዜ በገጠማት የውጭ ወረራም ይሁን የውስጥ ችግሮች ለሃይማኖታቸውና ለሃገራቸው ክብር ሲሉ ክርስቲያኖች መስቀላቸውን፣ ሙስሊሞች ኪታባቸውን ይዘው ተፋልመዋል፡፡ አኩሪ መስዋዕትነትና ገድል ፈፅመዋል፡፡ በመሆኑም ሃገራቸውንና ሃይማኖታቸውን ለዚህ ትውልድ አስረክበዋል፡፡ ይህ ሃይማኖትንና ሃገርን የመከፋፈል ጥቃት በተለያዩ ጊዜያት በውስጥም ይሁን በውጭ ሴራ ተሞክሮ የከሸፈና ያልተሳካ የደካሞች እኩይ ዕቅድና ድርጊት ነው፡፡ ባሳለፍነው ወርም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ የተቃጣው ሃይማኖትን የመከፋፈል ሴራ ፈፅሞ ተቀባይነት የሌለው እና መንግስት ከእምነቱ ተከታዮችና ከመላው የኢትዮጵያ ህዝቦች ጋር በመሆን በጋራ ልንመክተው የሚገባ ጉዳይ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ ባሳለፍነው ከባድ ወቅትም በፀሎትና በምክር ከጎናችን እንዳልተለያችሁን ሁሉ መጭው ዘመን ያሰብነውን የምንተገብርበት ይሆንልን ዘንድ ፀሎታችሁ፣ ምክራችሁ፣ አይዞህ ባይነታችሁ እንዳይለየን፣ በትህትናና በታላቅ አክብሮት እጠይቃለሁ፡፡የክልላችን ሆነ የአገራችን የዛሬም ሆነ የነገ ተስፋ የሆናችሁ ወጣቶቻችን፣ እኛ ከእናንተ የምንፈልገው ነገር እንዳለ ሁሉ፣ እናንተም ከእኛ ብዙ ነገር እንደምትፈልጉ እናውቃለን፡፡ የእናንተ ፍላጎት አቅም በፈቀደ መጠን ለሟሟላት፣ ሌት ከቀን እየሰራን እንደሆነ አውቃችሁ፣ ለእቅዶቻችን ስኬት ግንባር ቀደም ሆናችሁ ተሰለፉ እኛንም ደግፉን፡፡ ምክንያታዊ ሆናችሁ ሞግቱን እንጂ አታደናቅፉን፡፡ እናንተ ክፍተቶቻችንን ማሳየት አንዳንዱን ደግሞ እናንተም መሙላት ይጠበቅባችኋል፣ ለእናንተ በተለይም ለመላው ህዝባችን ህልውና ብለን፣ ህግና ስርአት ለማስከበር በምንንቀሳቀስበት ጊዜ፣ ለሰላም ስትሉ አግዙን እንጂ አታስተጓጉሉን፡፡ ይልቁንስ ተከባብረን ስለነጋችን በመነጋገር እና በመመካከር የክልላችንን ብሎም የአገራችንን ልዕልና በማስጠበቅ ወደ ተሻለ ምዕራፍ የማሸጋገር ታሪካዊ ኃላፊነታችንን እንድንወጣ ምክሬን እለግሳለሁ፡፡የክልላችን አርሶ አደሮች፣ በአዲስ አመት አዲስ ተስፋ ሰንቃችሁ፣ አርሳችሁ እና አለስልሳችሁ የዘራችሁት ሰብል መልካም ቡቃያ እያያችሁ፣ በምትገኙበት በዚህ ጥሩ ወቅት ላይ ትገኛላችሁ፡፡ እናንተ ምንጊዜም ከእርሻ ስራችሁ ማንም አይነጥላችሁም፣ ሊነጥላችሁ የሞከረም አልተሳካለትም ፤ አሁንም ይህን ተግባራችሁን አጠናክራችሁ እንደምትቀጥሉ እምነቴ የጸና ነው፡፡ በመጪው አመት ግብርናን ለየት ባለ የአሰራር ሁኔታ በሙከራ ደረጃ በአንዳንድ አካባቢዎች ለመጀመር አቅደናል፡፡ ይህ አሰራርም ስኬታማነቱ ከተረጋገጠ ደረጃ በደረጃ የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን ይረዳል፡፡ በትንሽ መሬት ብዙ ማምረት እና ሰፊ ገቢ ማግኘት የሚያስችል ፕሮጀክት በመሆኑ ለልጆቻችሁም መልካም የስራ እድል አማራጭ ሆኖ ያገለግላል፡፡በአትክልት እና ፍራፍሬ እንዲሁም የእንስሳት ሀብት ላይ ያተኮረ በመሆኑ የአመጋገብ ስርዓታችንንም ለማሻሻል ይረዳናል፤ ሰላማችሁን ነቅታችሁ ጠብቁ፡፡ አዳዲስ የአሰራር ዘዴዎችን ጠቃሚነት ተረድታችሁ ተግብሩ፡፡ የመንግስት ድጋፍ በመጪው አመት ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ አደራ የምላችሁ ነገር ትርፍ አምርቱ፤ እናተ እያላችሁ ክንዳችሁ ሳይዝል ኢትዮጵያውያን መራብ የለባቸውም፡፡እናንት የአማራ ክልል ምሁራን፡- የክልላችንን ኢኮኖሚያዊ፣ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎችን ለመደገፍ የምሁራን ሚና የማይተካ መሆኑን እንረዳለን፡፡ ስለሆነም የክልሉን ሁሉን አቀፍ እንቅስቃሴ እንድትደግፉ ፣ችግር ፈቺ የሆኑ ጥናት እና ምርምሮችን እየሰራችሁ ፣ሳይማር ያስተማረ ወገናችሁን ወደ ብልጽግና ለማሻገር፣የመፍትሔ አካል ሆናችሁ እንድታገለግሉና የማህበረሰብ አገልግሎት ኃላፊነታችሁን በተግባር እና በቅርበት እንድትወጡ ጥሪ አቀርብላችኋለሁ፡፡የክልላችን ባለሀብቶች፣ ዳኞች፣ የፍትህ እና የጸጥታ አካላት፣የመንግስት እና የግል ዘርፍ ሙያተኞች፣የሚዲያ አካላት፣ የሲቪክ ማህበራት፣ባለጥበቦች፣የማህበረሰብ አንቂዎች፣ተማሪዎች በጥቅሉ ሁላችሁም ወገኖቻችን በየተሰማራችሁበት ሙያ በኃላፊነት መንፈስ ፣ በንጹህ ሰብዕና፣በተቆርቋሪነት እና በቁጭት ለሰላም፣ለዕድገት እና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ታገለግሉ ዘንድ ጥሪ አቀርብላችኋለሁ፡፡ በምታደርጉት ህግ እና ስርዓትን የተከተለ እንቅስቃሴያችሁ ሁሉ ለሚያጋጥማችሁ ተግዳሮት የክልሉ መንግስት በየትኛውም ቦታና ሰዓት ከጎናችሁ መሆኑን ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ፡፡ክቡራት እና ክቡራን፡-የአማራ ህዝብ ከጥንት ጀምሮ በየትኛውም የኢትዮጵያ አካባቢዎች በብዛት እንደሚኖር ይታወቃል፡፡ ተጋብቶ እና ተዋልዶ እንደጠፍር አልጋ ከሁሉም ጋር ተጋምዶ ይኖራል፡፡ ይህን አጋጣሚ ተጠቅሜ ጥሪ ማቅረብ የምፈልገው ለመላው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ብሔረሰቦች እና ህዝቦች የአማራ ህዝብ በየአካባቢያችሁ የሚኖረው አንድም ሀገሩ ስለሆነ እንደ ኢትዮጵያዊነቱ፣ በሌላ በኩል ደግሞ እናንተ ወንድሞቹ እና እህቶቹ ስለሆናችሁ፣ እንደ ትናንቱ ነገም አብራችሁ ተሳስባችሁ በፍቅር እንደትኖሩ፣ በመካከላችሁ የሚገባውን አሜካላ ጊዜ ሳትሰጡ እንድትነቅሉ እያሳሰብኩ ከእናንተ በላይ ስለእናንተ መስተጋብር የሚያውቅ እና የሚረዳ የሌለ መሆኑን ተረድታችሁ በቆዬው የኢትዮጵያዊነት መንፈስና ስሜት በሰላም እንደትኖሩ ጥሪዬን አቀርብላችኋለሁ፡፡", "passage_id": "573ce324b398d83369010f3754f91d8f" }, { "passage": "አንዱ በሌላው ላይ፣ ወገን በወገኑ ላይ ፈጸመ የሚባለውን ጉድና ደባ ሰምቶ ዝም ማለት አልሆንላት ብሎ፤ እውነቷን ነው ማንስ ቢሆን እንዴት ዝም ይላል። ተለጉመው የነበሩ የስሜት ሕዋሳት ነጻነት በተቀዳጁበት ዘመን ላይ ነው የምንገኘዋ። ‹‹የማሰብ ነጻነት፣ የመናገር ነጻነት፣ የመሰብሰብ ነጻነት፣ የመጻፍ ነጻነት….ወዘተ›› አንደኛ ዓመት ክብረ በዓል ብንለውስ? እንደው ማን ይሙት! ልብ ብሎ ለተመለከተን ‹‹ከገመዱ አፈትልኮ የወጣ እንቦሳ›› መስለን አርፈነዋልሳ። በጨዋ ወግና ባህል ተኮትኩቶ ያደገ ኢትዮጵያዊ ሲናገርም ልክ አለው፤ ሲጽፍም ልክ አለው፤ ሲጠላም ልክ አለው፤ ኧረ ሲወድም ልክ አለው። እንዲህ እንደ አሁኑ ልካችን ልኩን ከማጣቱ በፊት ለሁሉም ነገር ከልክ በታች ነበረ አይደል እንዴ? ‹‹አንድ ሰው ነጻነት በሰጠኸው ቁጥር የበለጠ ኃላፊነት በትከሻው እንዳረፈ ይሰማዋል›› ብሎ የተናገረው ምሁር፣ ፈላስፋ፣ ተመራማሪ፣ ሳይንቲስት ማን ነበር? ብዬ ቀና አልኩና ከቅርብ ጓደኛዬ ምስክርነት ተማጸንኩ። እሱም ‹‹ባውቀው ምን አስደበቀኝ ብሎኝ እርፍ!›› ከት ከት ከት ብዬ ሳቅኩኝ። ትናንት የፕሬስ ነጻነትን ልክ ለማስረዘም ረጅም መዘዝ በራሳቸው ላይ ያስከተሉ ሰዎች ቁጥራቸው ቀላል አይደለም። ዛሬ ያስረዘሙትን ነጻነት ወርዱ ከቁመቱ ተስተካክሎ በልክ እንድናምርበት የማድረጉ ኃላፊነት ከእነሱ በላይ ባለቤት የት ይመጣለታል። ካልተመጠነ ለሌላው እንቅፋት መሆኑ የት ይቀራል። እያንዳንዱ ነገር ልክ ከሌለው ለእልክ ይዳርጋል ይላሉ አባቶች ሲመክሩ።መቼም ‹‹ወሬን ወሬ ያነሳዋልና›› የድሮው ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ሚኒስቴር በሕይወት እያለ ‹‹መብትና ግዴታውን ጠንቅቆ የተረዳ፣ የሕዝብ አገልጋይነት መንፈስ መላበስ›› የሚሉ ነገሮች መለጣጠፍ ያበዛ ነበር። እንደው በጥናት የተረጋገጠ ባይሆንም በርካታ ሰዎች ‹‹የአገልጋይነት ሳይሆን የአጎብዳጅነት መንፈስን የተላበሰ›› ሰራተኛ ነው የተፈጠረው ሲሉ ይደመጣሉ። ለዚህ መገለጫው ‹‹መረጃ የማግኘት መብት››ን ብቻ ማየቱ በቂ ማሳያ ነው ይላሉ። ሠራተኛው በራሱ ተማምኖ ሙያው የሆነውን ጉዳይ እንኳን መረጃ ሊሰጥህ አይደፍርም። በሥራው ተማምኖ ከመኖር ይልቅ አጎብድዶ መኖር ጥቅም እንደሚያስገኝ ይነገራል። ስለዚህ ‹‹የአገልጋይነት መንፈስ ተላብሷል›› ሳይሆን ‹‹ክፉ መንፈስ ተዋርሷል›› ቢባል የተሻለ ይሆናል። ያው እንደልብ መተንፈስ ተችሏል፤ በተነፈሱት ልክ ያውም በልጥ አድርጎ ማስተንፈስም ቀርቷል ብዬ ነው የተነፈስኩላችሁ። አለበለዚያማ የተነፈሱትን ትንፋሽ ያስቆጥር ነበር ያ የትናንቱ ክፉ ቀን። እርግጥ ነው ዶክተሩ የመረጃን ዋጋ አሳምረው ያውቃሉ። መረጃ የመሸጥ ጥበብንም ተክነውበታል። በመረጃ ነጻነት ግኡዝ አካሉ ውስጥም ነፍስ ሊዘሩበት እየጣሩ ነው። ከሥልጣን ዕድሜያቸው አኳያ የመገናኛ ብዙኃንና የመረጃ ነጻነትን ከቀብር አፋፍ ታድገውታል። ቁርጠኝነታቸውን አለማድነቅ አይቻልምና። ትናንት ሐሳብ በማፍለቃቸው፣ በመጻ ፋቸው፣ በመናገራቸው ለመከራ የተዳረጉ ወጣቶችና ጋዜጠኞች ብዙ ናቸው። ዛሬ በማጎሪያ ቤት የሉም። የተለየ ሐሳብ ይዞ መምጣት የሚያኮራ እንጂ የሚያሳፍር፣ የሚያሳስር መሆኑ ያከተመ ይመስላል። ዓለም እኛን የሚመለከትበት የተንሸዋረረ ዓይን ወደ መስተካከል ተጠግቷል። ይልቁ ንስ እኛ ራሳችንን የምናይበት ዓይን፣ እኛ ዜጎቻችንን የምንመዝንበት ሚዛን፣ የምናቀ ርብበት የሜትር ልክ መስተካከል ተስኖት እንደተንጋደደ ይሄው እያገዳደለ ቀጥሏል። የነጻነት ልኩን ማወቅ ተስኖን፣ የመናገር ወሰኑ ጠፍቶን ይሄው እርስ በርሳችን የሰላማችን ፀር ሆነናል። ገዳይ ወንድም፣ ሟች ወንድም፣ አፈናቃይ ወንድም፣ ተፈናቃይ ወንድም ሆኖ ቀጥሏል። ዕድሜ ለሚዲያ ነጻነት እንጂ የቀረርቶ፣ የፉከራና የሽለላ ጫካው በእጃችን ላይ ሆኗል፤ ፌስቡክ። ኢትዮጵያ ለረጅም ዘመናት ስሟን ጥላሸት ሲቀቡ የነበሩ ድርጊቶቿ በአንድ ዓመት ከስመዋል። በሰብዓዊ መብት አያያዝ፣ በሐሳብ ብዝሃነት ማስተናገድ፣ በሚዲያ ነጻነት አጠባበቅ ከፍተኛ ለውጥ መታየታቸውን አሁን ላይ መስካሪዎቹ እኛ አይደለንም። ሌሎቹን ለማሳመን የተመናመነ የሃሳብ ጥይት ከመፈለግ ተገላግለናል። ስለ እኛ የሰብዓዊ መብት አያያዛችን ላይ ‹‹እትፍ እትፍ ይልመድባችሁ›› የሚሉ መስካሪዎች ፍለጋ ከጫፍ ጫፍ መኳተንና ማሰልጠን ቀርቷል። አልሆን ሲልም ረብጣ ገንዘብ ለእጅ መንሻ በቀዳዳ ልኮ አፍ ማዘጋት ዛሬ የለም፤ አንዳንድ ያልጠራ ሁኔታ ግን ሊኖር ይችላል። ሆሆይ ጉድ እኮ ነው። አልሰማንም እንዳትሉ! ለሥራ ከምናውለው ገንዘብ በላይ ቆሻሻ አመላችንን አለያም ገመናችንን ለመሸፈን እንከፍል እንደነበር ከውስጥ አዋቂዎች ውስጡን ጠይቁ። እኛ ተንፍሰናል። የመገናኛ ብዙኃን አቅም በማቆጥቆጥ ላይ ነው። በዘርፉ የሚሰማሩ የሚዲያ ሰዎች በሙያዊ ሥነምግባር እንጂ በፖለቲካ ርዕዮት ዓለም የተሞረዱ መሆናቸው ታሪክ ሊሆኑ እየተቃረበ ይመስላል። የሚዲያ ተቋማት መጡልን እንጂ መጡብን በሚል መብቀላቸውን ለማክሰም በጎሪጥ የሚመለከት ባለሥልጣን የለም። ተወዳዳሪነት እንጂ አቋራጭ እርምጃዎች መጥበብ ጀምረዋል። የመንግሥትን ካዝና በማለብ ዕድሜያቸውን የሚያራዝሙ የግል ሚዲያ ጣቢያዎች ልሳናቸው (ደማቸው) ደርቋል። ሕዝብን ረስቶ የፓርቲን እስትንፋስ እየተከተሉ ማላዘን አሁን ላይ ሳንቲም አለመውለድ ላይ ለመድረስ እየተጠጉ ይመስላል። የሚዲያው ባለቤት ባለሥልጣን፣ ጋዜጠኛው ወፍዘራሽ አለያም የእህት ልጅ፣ ፈቃድ ሰጪው አጎት፣ ሸላሚው የሚስት ወንድም፣ የገንዘብ ምንጭ (ስፖንሰር) መንግሥት፣ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚስት ሆነው በሕዝብ ላብ ጅምላ ንግድ አሁን አይሰራ ይሆናል፤ ይህ በሩ እየጠበበ ነው። ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ስለህጸጻችን ምን ያወሩብን ይሆን? ምን ይናገሩብን ይሆን? እያሉ መርበትበት ታሪክ ሊሆን ተቃርቧል። ይልቁንስ የእኛ ሚዲያዎች አቀንቃኝ እነሱ አስወንጫፊ ሆነው አብረው በመዘመር ላይ ናቸው። ኢትዮጵያ እንዲህ የዓለምን ቀልብ ስባ የታየችበት አጋጣሚ ምናልባትም ከአድዋ ድል ቀጥሎ ሁለተኛው ሳይሆን አይቀርም። የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪዎች፣ የዓለም ጋዜጠኞች መብት ተሟጋቾች፣ አክቲቪስቶችና የዓለም ሚዲዎች በኢትዮጵያ መዲና በቅርቡ ይከትማሉ። እንደከዚህ በፊቱ የክስ አቤቱታ ለማሰማት አይምሰላችሁ።ልምድ ለመቅሰም እንጂ። የለውጡ የአንድ ዓመት ፍሬ የሩብ ምዕተ ዓመት ስብራትን መጠገን ችሏል። ኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙሃንና የመረጃ ነጻነት የዓለም የፕሬስ ቀን የዘንድሮ ተሞሻሪ ናት።ከዚህ በፊት በዘርፉ ደረጃ ደልዳዮች ከነበረችበት 150ኛ ደረጃ በአንድ ዓመት ውስጥ 40 ደረጃዎችን ማሻሻል ችላለች። እሰይ ሀገሬ። በዚህ ብቻ የሚወሰን አይምሰላችሁ። እየተውተረተረ ያለው የሚዲያዎቻችን አቅም መለወጥ ይኖርበታል። ጋዜጠኞቻችን ለሙያው ሥነምግባርና ለእውነት የሚቆሙ ብሎም ለህዝብ ጥቅም የሚፋለሙ ሊሆኑ ይገባል። ከግል ሚዲያ ተቋማት እስከ ሕዝብ ሚዲያዎች በጥቅም ትስስር የግለሰቦችን ሥም ለማጥፋት ዘመቻ ይውላሉ የሚሉ አሉባልታዎች ቢነሱም ከአሉባልታ አይዘሉም። በአጠቃላይ የፕሬስ ነጻነቱን በደስታ ስናከብር በምንጠቀምባቸው ሚዲያዎች በኩል የጥላቻ ንግግርን ከማስተላለፍ ብንቆጠብ ከእኛነታችን የሚቀነስ ነገር ይኖር ይሆን? ሁሉም ነገር ትናንትን ስቦ የእኛ ነገር አጃኢብ እንዳያሰኝ ስጋት አለኝ። ምክንያቱም ‹‹ሲለጉሙን እዳ ሲፈቱንም እዳ፣ ተቻችሎ መኖር አሁን ማንን ጎዳ›› እንዳለችው ሴትዮ እንዳይሆንብን ነዋ።አዲስ ዘመን ሚየዝያ 24/2011ሙሐመድ ሁሴን ", "passage_id": "9c3312e8ae66f77e8b451d5187507a91" }, { "passage": "የሩቅ ጊዜ እውነተኛ ታሪክ ነው።ምን ለብሼ ልሳቅ የሰውየው እውነተኛ ስሙ አይደለም።በነገር አገደም አግራሞት የሚያጭርበት ጉዳይ ሲያገኝ ከት ብሎ እየሳቀ ምን ለብሼ ልሳቅ ስለሚል ነበር አካባቢው መንደርተኛው በሩቅ የሚያውቁትም ጭምር በዚህ ስያሜ የሚጠሩት።መለያው መጠሪያ ስም ሆኖ ጸደቀለት። አዳሩ\nበዚያን ዘመን ይሰሩ ለነበሩ ቤቶች ከአሰሪዎቹ ከባለቤቶቹ ጋር ተዋውሎ ጭቃውን በጭድ እያቦካ በደንብ በተለያየ ቀናት አገላብጦ ፈርመንትድ ሲሆን (ሲበስል) እንበለው የተማገረውን አዲስ ቤት ደህና አድርጎ በጭቃ ይመርገዋል።በኋላም የልስን ስራ ይሰራል።የእኛ ሀገር የቀደመው ዘመን ሲሚንቶአችን መሆኑ ነው።ዛሬም በስፋት ይሰራበታል፡፡ ብዙዎቹ የሀገራችን ቤቶች\nየሕዝቡ የመሳፍንቱና መኳንንቱ ሳይቀር ምሰሶው ቆሞ ወጋግራው ከተዋቀረና ከተገደገደ በኋላ የሣር ክዳን ይደረግለታል።ዙሪያውን የሚለሰነው ምርጥ ብቃት በነበራቸው የሀገራችን ጭቃ አቡኪና ለሳኞች ነው።ስንቱን ከተማ መንደር ሰፈር አብረው እንደቆረቆሩ፤ ስንቱን ቤት እንደሰሩ፤ የሚናገርላቸው የሚጽፍላቸው ጠፍቶ እንጂ ሰዎቹስ ምርጥ ባለሙያዎችና ባለታሪክም ነበሩ። እነ ምን ለብሼ ልሳቅን የመሰሉ ብዙ ሺዎች ፡፡ ምን\nለብሼ ልሳቅን ለየት የሚያደርገው ለየት ያለ ባህርይና አስገራሚም ስለነበረ ይመስለኛል። ግጥም የለውም። መንደርተኛና ሰፈሩ በአለባበሱ ይደመማል። ትልቁም ትንሹም።ሲመጣ ሕጻናት ይከቡታል። ያውካካሉ።ሱሪ 2 ኮት 3 ሸሚዝ 2 ከረባት 4 ሁልጊዜም መነጽሩ ባዶና መስታወት የሌለው፤ በሸሚዞቹ ኪሶች ላይ የሚሰሩና የማይሰሩ ብዙ እስክሪቢቶዎች የሚደረድር ሰው። ጸጉሩ በዘመኑ ፋሽን ኤልቪስ።ዘመኑም የእነ ኤልቪስ የዝነጣ ዘመን ነበር። በጫማ ላይ ጫማ ስለማይደረግ እንጂ እሱንም ለማድረግ አይመለስም ነበር። በዚያን ዘመን\nእንዲያ ለብሶ ከገጠር መንደር ብዙም በማትለየው የአዲስ አበባ ጥርጊያ መንገዶች ላይ ሽር ብትን እያለ በቄንጥ ሲራመድ የሁሉንም ቀልብ ይስባል።‹‹ኧረ ሳቄ መጣ›› ያሠኛል።እሱ ማንንም ከቁብ አይቆጥርም። ይህ ሰው ማነው ለሚለው ማንም መልስ አላገኘለትም።ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ ወይንም ለመጠላት ወይ ለመወደድ እንዲሉ ሆነና። አዕምሮው ልክ\nአይደለም ባዮች ብዙ ነበሩ።እነሱ እንጂ እሱማ ልክ ነኝ ብሎ ነው የሚኖረው፤ የሚሰራው።የተዋዋለውን ስራ ጭቃ ማቡካቱንና መለሰኑን አሳምሮ ይሰራል።ስራ ሲሰራ ይዘፍናል።ሰው ሰማ አልሰማ ደንታ የለውም።ዘፈኑ ሁሌም ‹‹አንቺ ልጅ›› ነው። ‹‹አሀሀሀ አንቺ ልጅ፡፡›› ምናልባት ምናልባት ይሄ ስለሚሰራው ስራ እንጂ ስለማንነቱ ብዙ የምይታወቀው ሰው ከጀርባው ምን ታሪክ ተሸክሞ ይሆን የሚለው ጥያቄ የብዙዎች ነበር። የት ተወለደ፤ አደገ፤ ተማረ፤ ቤተሰቡስ የት ነበር? ምንም ፍንጭ የለም።ብዙ ሰዎች ለማወቅ ጥረዋል።ሲጠይቁት መልሱ አጭር ነው ምን ለብሼ ልሳቅ ይልና ይንከተከታል።ምናልባት በሰዎቹ በመገረም አሊያም ዓለምን በመናቅ ሊሆን ይችላል።እኛ ያላየነው የማናውቀው የለም በሚል ውስጣዊ ምፀት ይሆናል ከት ብሎ የሚስቀው። አዛውንቶቹ ወጣቱ ሁሉም ሰው ያውቀዋል። አብዝተው ይገረሙበታል። በማይታወቀው ማንነቱ። በዚህ ሰው ማንነት ውስጥ ሌላ የተሰወረ የተደበቀ ማንነት አለ።ግን ለምን እንዲያ ሆነ ቢባል የመልሱ ባለቤት እሱና እሱ ብቻ ነው። ብዙ ሰዎች ደሞ ‹‹ምን ለብሼ ልሳቅ ይላል እንዴ፤ ይሄን ሁሉ የሀገር ልብስ ደራርቦ እየለበሰ›› ይሉና ይሽኮመኮማሉ። የሚገርመው የስራ ልብስ አለው።ለብሶ የሚመጣው ንጹህ ልብሶች ናቸው። ስራውን ሲጨርስ ተጣጥቦ ሲያበቃ ያንኑ ደራርቦ ይለብስና ሽክ ይላል። ‹‹አሀሀሀሀሀሀ አይ ምን ለብሼ ልሳቅ።›› ዛሬ ከስንትና ስንት ዓመታት በኋላ ታወሰኝ በል፡፡ ‹‹በጤናው አይደለም›› ቢሉም ‹‹እኔ እብድ አይደለሁም፤ እናንተ ናችሁ እብድ›› ይላል።‹‹ጤነኛ ነኝ›› የሚል ስንት እብድ እንዳለ መንፈሱ ሹክ የሚለው ይመስላል።ልብሱ፤ ከረባቱ፤ ሸሚዙ ኮቶቹ ይቀያየራሉ።ወይ ሰዎች ይሰጡታል ወይ የራሱ የሆነ የተከማቸ አለው።ለስራ ተዋውሎ ሲመጣ እንጂ መኖሪያው አይታወቅም የምን ለብሼ ልሳቅ።እንደሌሎቹ የእሱን አይነት ስራ እንደሚሰሩት ሰዎች ጠላ፤ ጠጅ፤ አረቄ፤ ቤት አይታይም።ቢሰጡትም አይጠጣም፡፡ አንዳንድ ሰዎች ግን እንደዛው ለብሶ አልፎ አልፎ ግሮሰሪ እንደሚገባ በሥርዓቱ ቁጭ ብሎ አዞ የተወሰነ አልኮል እንደሚጠጣ ይናገራሉ።አንድ ጊዜ ቁምጣ ሱሪውን አድርጎ በባዶ እግሩ ጭቃውን ሲለውስ ከቤታቸው ውሀ ልክ ላይ ቁጭ ብለው ሁለት የተማሩ ወጣቶች ምስጢራቸውን በእንግሊዝኛ ቋንቋ ያወራሉ። ማንም ሰው አይሰማንም ነው ነገሩ።መቼም ምንም ቢያስቡ ሊጠረጥሩ አይችሉም። እሱ ስራውን ይሰራል። ሰማ፤ ሰማ ፤ሰማና መጨረሻ ስራውን ከውኖ ተጣጥቦ ሲያበቃ ያንኑ አስገራሚ ልብሱን ከረባቱን ባዶ መነጽሩን አድርጎ ለማረፍ በሚመስል መልኩ ተማሪዎቹ አጠገብ ቁጭ አለ።እየሳቁ ምን ለብሼ ልሳቅ ታዲያስ አሉት።በተለመደው ሳቁ አውካካ።አይ እናንተ አሁን ምስጢራችሁ እንዳይሰማ ነው አይደል በወፍ ቋንቋ የምታወሩት አላቸው።‹‹ልክ ነህ ማንም እንደማይሰማ እርግጠኞች ነን›› አሉት።የተነጋገሩት ስለአብዮትና ለውጥ ስለንጉሱና ሥርዓታቸው የእኛስ በምን መልኩ ነው መሄድ ያለበት የሚል ነበር፡፡ የወጣቶቹን አፍ ያዘጋ ድንጋጤ ውስጥ የከተተ ድንገተኛ ምትሀት የመሰለ ጉዳይ ተከሰተ።በጠራ እንግሊዝኛ የተወያዩበትን ዘርዝሮ ጥያቄአቸውን በመለሰ መልኩ ነገራቸው ጭቃ አቡኪውና ለሳኙ ምን ለብሼ ልሳቅ።ደነገጡ።ማመን ተሳናቸው።እሱ ነው ሌላ ሰው እስኪሉ ድረስ።መጽሐፍቶችን በስም እየጠራ ይሄን ይሄን አንብቡ ሲላቸው ድንጋጤአቸው ሽቅብ ጎነ።ግን አላቸው ለማንም አትናገሩ ቃል ግቡልኝ። እኔ በዚህ መልኩ የምሰራው የምኖረው የእራሴን ኑሮ ነው።ደስተኛ ነኝ።ዓለምን ንቄ ሰውንም እርቄ ነው ብሎ በረዥሙ ተነፈሰ። እንዴት ብዙ የተማረ ሰው በሌለበት ሀገር የዚህ እውቀት ባለቤት አንዱ ጋ ተቀጥሮ መኖር\nሲችል ይሄንን አይነት ኑሮ ለመኖር መረጠ በሚል ወጣቶቹ በእጅጉ አዘኑ።ተደናገጡ።እሱ ግን አላቸው።ለእኔ አታስቡ አትጨነቁም።በጉልበቴ ሰርቼ እኖራለሁ።ስራ አከብራለሁ።የሰው እጅ አላይም።ልመና አልወድም።ዓለምን ስትረሳት ትረሳሀለች። ሁሉን ከረሳህ በትላንት ውስጥ ካልቆዘምክ ትኖራለህ በሉ ቻው አለና ተነስቶ ግቢውን ጥሎ ወጣ።ጉድ ጉድ ሲሉ ውለው አደሩ።ምን ለብሼ ልሳቅ ማነው።ከአሁኑ ትንሽ መገለጥ በቀር ስለዚህ ሰው ማንም ምንም አያውቅም። ሌላ ሰፈር ሄዶ ያንኑ ጭቃ ማቡካት ሲሰራ እንዲሁ የ11ኛ\nክፍል ተማሪዎች በራፋቸው ላይ ቁጭ ብለው በተሰጣቸው የታሪክ ትምህርት የቤት ስራ ላይ በእንግሊዝኛ እያወሩ ይከራከራሉ።የያኔ ተማሪ ብርቱና የቀለም ቀንድ ነበር።ለወረቀት ሳይሆን ለእውቀት የሚተጋ።ለእውቀት የሚታትር ንብ።አንባቢ፤ተከራካሪ፤ሞጋች።ብርቱ የቀለም ደቀመዝሙርና ካህን።መምህሮቹም በእውቀት የላቁ የረበቡ።እሱ ጭቃውን ጭድ እየነሰነሰ ይለውሳል።ተማሪዎቹ በጥያቄው መልስ ላይ አልተስማሙም።ተነታረኩ።አጠገባቸው ወትሮም የሚያውቁት የሚስቁበት ምን ለብሼ ልሳቅ ብቻ ነበር።ሌላ ሰው የለም። አከራካሪው ጥያቄ በፈረንሳይ አብዮት ላይ ያተኮረ ነው።ምን ለብሼ ልሳቅ አካፋውን ይዞ ጭቃውን እያገላበጠ ይሰማቸዋል። አላስቻለውም። ዝምታውን በድንገት ሰበረና ከት ብሎ ሳቀ።አንዱ ተማሪ ይሄ እብድ ምን ይስቃል ሲል አዎን እብድ ነኝ። ዘመን ያሳበደኝ በራሴ ዓለም የምኖር እብድ አለው። መልሱ ልጁን አስደነገጠው። ምን ለብሼ ልሳቅ ለጠቅ አደረገና በጠራ እንግሊዝኛ ምንድነው የምትጨቃጨቁት ሲላቸው በተቀመጡበት ክው ብለው ቀሩ። እሱ ነው የተናገረው ሌላ ሰው በሚል ጥርጣሬ።ደገመላቸው። የተከራከሩበትን ነጥብ በነጥብ እያነሳ ከመነሻው እስከ መድረሻው አካፋውን ይዞ ቆም እንዳለ አነበነበላቸው።መልሱ ይሄ ነው አለና በረዥሙ ተነፈሰ፡፡ ተማሪዎቹ አብዝተው ተደመሙ።ግን አላቸው ስለእኔ ለማንም አታውሩ ።ስለእኔም አትጨነቁ።አትመራመሩ።እኔ በራሴ የሕይወት መንገድ ደስተኛ ነኝ። ከማንም ምንም እርዳታ አልፈልግም። እስካለሁ በጉልበቴ ሰርቼ እኖራለሁ። ስራዬን አከብራለሁ።እናንተ ግን በርትታችሁ ተማሩ።አንብቡ። ለወረቀት ሳይሆን ለእውቀት ትጉ አላቸው። በተቀመጡበት በድንጋጤ ተመቱ። ከጭቃው ውስጥ ወጥቶ ተጣጥቦ ልብሱን በተለመደው ሁኔታ ለባብሶ ቻው ብሎአቸው መንገዱን ቀጠለ። ግዜው የ1966 አብዮት ዋዜማ\nነበር።ምን ለብሼ ልሳቅ ማነው? እውነተኛ ስሙና ታሪኩስ? ምን ገጥሞት ምንስ ሆኖ ይሄን የሕይወት መንገድ መረጠ? አዲስ ዘመን ሀምሌ 18/2011", "passage_id": "304fd91821603631b9bad2d841cc81b3" }, { "passage": "የ2009  ዓም  የአዲስ  ዘመን  መለወጫ  በዓል በሰላም፣ በደስታና በድምቀት እየተከበረ መዋሉን  የተለያዩ   የአዲስ አበባ  ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ ።   \nዋኢማ ተዘዋውሮ ያነጋገራቸው የተለያዩ የአዲስ አበበ ከተማ ነዋሪዎች እንደገለጹት የ2009 የአዲስ  ዘመንን  በሰላም ፣ በደስታና በፍቅር  ማክበራቸውን ።\nአዲሱ ዘመን ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የደስታ፣ የሰላም፣ የፍቅርና የመከባባር   እንዲሆንለት መልካም  ምኞታቸውን ገልጸዋል ።  \nበከተማዋ  የካራ ቆሬ አካባቢ ነዋሪ የሆኑት አቶ ወይሳ ጥርአይሎ እንደገለጹት ከዋዜማው አንስቶ  የአዲስ ዘመን  መለወጫ በዓሉን ለማክበር ዝግጅት ሲያደርጉ መቆየታቸውንና በሰላም ማክበራቸውን ገልጸው አዲሱ ዓመት  ለኢትዮጵያና ህዝቦቿ የሰላም ፣ የደስታና የዕድገት እንዲሆን ተመኝተዋል።  \nወጣት ዳናዊት  ለምለም በበኩሏ  አዲሱን ዓመት ካለፉት ዓመታት በህይወቷ ላይ የተሻለ ለውጥ  በማምጣት የምትጥርበት መሆኑን ጠቁሟ   ወጣቶች  እራሳቸውን  በመለወጥ  ለአገር ዕድገት  አስተዋጽኦ የሚያበረክቱበት ዘመን እንዲሆን ተመኝታለች ።\nበአዲስ አበባ ከተማ የኮልፌ ቀራንዮ አካባቢ  ነዋሪ  የሆነው ከበደ እሸቱ የዘንድሮ የአዲስ ዓመት በዓል በአዲስ መንፈስ  እንደተቀበለው በመግለጽ ሁሉም  ዜጋ  በአዲሱ ዓመት ለሰላም ፣ ለዴሞክራሲና ለልማት  የሚቆምበት  እንዲሆን ተመኝቷል ።\nሌላዋ  የአዲስ አበባ ከተማ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ነዋሪ  የሆነቺው  ዓለም  ተሰማ   አዲሱን  ዓመት  የምትቀበለው   ከባለፉት ዓመታት  በተሻለ  መልኩ ኑሮዋን  የማሻሻል  የያዘችውን ዕቅድ ለማሳካት ከልብ በመነሳት ነው ብላለች ።   \n   ", "passage_id": "6d19e2aa379bbdaeddf54c58376df9e3" } ]
524ddf103c1b646d02bab34958c46ee4
e3564bee4dc397f060bc0d8c4a9a3ed4
የአረንጓዴ ጎርፍ በጎ አድራጎት አምባሳደሮች ተሰየሙ
ቦጋለ አበበየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽን ከኢትዮጵያ አረንጓዴ ጎርፍ የአትሌቲክስ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር‹‹የገና በዓልን ከአንጋፋ አትሌቶች ጋር እናሳልፍ›› በሚል ትናንት በኢትዮጵያ ሆቴል በተዘጋጀው የእውቅናና የሽልማት መድረክ የበጎ አድራጎት ድርጅቱ ሁለት አምባሳደሮች ተሰይመዋል፡፡ በዚህም ከሴት ፈር ቀዳጇ የአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር የቀድሞ ኮከብ አትሌት ኮማንደር ቁጥሬ ዱለቻ የተሰየመች ሲሆን በወንድ ፋና ወጊው የኦሊምፒክ የሦስት ሺ ሜትር መሰናክል የነሐሴ ሜዳሊያ ባለቤትና የርቀቱ አሰልጣኝ ሻምበል እሸቱ ቱራ የዕውቅና አምባሳደርነት የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።አምባሳደሮቹ በተሰየሙበት መርሃግብር በህይወት ዘመናቸው ለኢትዮጵያ ስፖርት የላቀ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ግለሰቦች የዕውቅናና የምስጋና ካባ እንዲሁም የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል፡፡ አንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ሐኪም ዶክተር አያሌው ጥላሁን እንዲሁም አንጋፋው የስፖርት ጋዜጠኛ ሰለሞን ገብረእግዚያብሔር የዕውቅናና የምስክር ወረቀት ከተቀበሉ በኋላ በሞሀ ለስላሳ መጠጦች እንዱስትሪ አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጌታቸው ቢርቦ የክብር ካባ ተጠልቆላቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ጎርፍ አትሌቲክስ የበጎ አድራጎት ድርጅት መስራችና ዋና ስራ አስኪያጅ አትሌት መልካም ተገኝ፣ ‹‹መረዳዳት በህይወት›› በሚል ሀሳብ ለአገራቸው የሰሩ፣ የለፉ ፣ የደከሙና ለአገር ክብር የተጉ አትሌቶችንና ቀጣይ ተተኪዎችን በማንኛውም ማህበራዊ ህይወታቸው ለመታደግ በጎ አድራጎት ድርጅቱ መመስረቱን ጠቅሰው ለዚህ የተቀደሰ አላማ ሁሉም አካላት ትብብር እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽነር በላይ ደጀን በበኩላቸው ‹‹መረዳዳት በህይወት›› የሚለው መሪ ቃል በጎ አድራጎት ድርጅቱን እንደሚወክል በመግለፅ፣ ለአገራቸው ክብር ፣ ህዝብና ባንዲራ የለፉ አንጋፋ አትሌቶችና ጋዜጠኞች እንዲሁም ሌሎች ባለሙያዎች በዚህ ደረጃ ዕውቅና ማግኘታቸው ተገቢ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡ በቀጣይ በጎ አድራጎት ድርጅቱ የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን በጋራ እንደሚሰሩም ቃል ገብተዋል፡፡ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ዱቤ ጅሎ በበኩላቸው ይህን በጎ አላማ እውን ላደረጉና መርሃግብሩን ላዘጋጁና ለዚህ ያበቁ የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን አመራሮችን አመስግነዋል። በርካታ አንጋፋ አትሌቶች በመርሃግብሩ ታድመውም የእውቅናና የምስክር ወረቀት ተቀብለዋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 28/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=39010
[ { "passage": "የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስቴር የአንደኛ ዓመት መታሰቢያ አስመልክቶ በተካሄደው ችግኝ ተከላ ላይ የንግድ ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋማት የሆኑት የኢትዮጵያ እህል ንግድ፣ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለሥልጣንና የንግድ አሠራርና ሸማቾች ጥበቃ ባለሥልጣን ተካፍለውበታል፡፡የንግድ ሚኒስትር አቶ ከበደ ጫኔ ለዋልታ እንደተናገሩት ተከላው በአንድ በኩል የሃገሪቱን ልምላሜ የሚያመጣ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ የመለስ ራዕይን በሁሉም ሰራተኛ ውስጥ በማስረጽ የእድገትና ተራንስፎርሜሽን እቅዱን ለማሳካት በቁርጠኝነት ለመንቀሳቀስ አጋጣሚ ይፈጥራል፡፡ተከላው ለዚሁ ዓላማ ሲባል በጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በተመረጠው የውንጌት ቀለበት መንገድ አደባባይ ላይ በሚገኙ የአረንጓዴ ስፍራዎች ላይ ሲሆን በእለቱ በ350 ሰዎች ተሳትፎ እስከ 1 ሺህ 100 ችግኞች ተተክለዋል፡፡ ", "passage_id": "d08c3d48c61da21fbd75ee90af19bead" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 14 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የጤና ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት  ጋር  በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ- ግብር በአገር አቀፍ ደረጃ 6 ነጥብ 5 ሚሊዮን ችግኞችን እንደሚተክል አስታወቀ።በዚህም ሚኒስቴሩ ዛሬ በሥሩ ያሉ ተጠሪ ተቋማት ሠራተኞች ጋር በመሆን በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ 5ሺህ ችግኞችን በመትከል መርሃ ግብሩን  አስጀምሯል።መርሃ ግብሩም “ከኮሮና ቫይረስ ራሳችንን እየተከላከልን አረንጓዴ አሻራችንን እናሳርፍ” በሚል መሪ ሃሳብ እንደሚከናወን ነው የተገለጸው።በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ  ላይ የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያን ጨምሮ የስራ ሃላፊዎች እና ሰራተኞች በመሳተፍ አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል፡፡የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በዚህ ወቅት÷መርሃ-ግብሩ አካበቢን ከመጠበቅ በተጓዳኝ ለማህበረሰብ ጤና ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል።ችግኞች በሚተከሉበት ወቅት የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚወሰዱ ጥንቃቄዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም ዶክተር ሊያ ታደሰ  ጥሪ አቅርበዋል።በመርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፉ አመራሮች እና ሰራተኞች  የሚተከሉ ችግኞች የአየር ንብረትን በመጠበቅ  ለዜጎች ጤና  ያላቸው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡በመለሰ ምትኩ#FBCየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።", "passage_id": "2c5cd5aac652a11c6f96537a7d7129a0" }, { "passage": "ዓምና በተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ በአንድ ጀምበር ከ350 ሚሊዮን እንዲሁም በክረምቱ መርሃግብር ከአራት ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል በሕንድ ተይዞ የነበረውን የዓለም ክብረ ወሰን ኢትዮጵያ መስበሯ ይታወሳል። ይህንኑ ተግባር በዚህ ዓመት በተሻለ መነቃቃት እና ነገን ታሳቢ ባደረገ ጥንቃቄ ለመድገምም ቅድመ ዝግጅቶች ተጠናቀው እነሆ በዛሬው እለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በአገር አቀፍ ደረጃ የሚከናወነውን የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር በደቡብ ክልል ያስጀምራሉ። በዚህ ዓመት በመላው አገሪቱ አምስት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል በችግኝ ዝግጅቱም በአስተሳሰብም በተግባርም በቂ ቅድመ ዝግጅት መደረጉ ተነግሯል።በዚህም የአገሪቷን አረንጓዴ ሽፋን ከማሳደግ ባለፈ የአርሶ አደሩን ህይወት መለወጥ የሚችሉ የፍራፍሬ ዛፎች በስፋት መዘጋጀታቸውን የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ኡመር ሁሴን ገልጸዋል። ከአምስት ቢሊዮኑ ችግኞች 60 በመቶ የሚሆኑት ለምግብነት ሊውሉ የሚችሉ የአትክልትና የፍራፍሬ ተክሎች መሆናቸውን ያስታወቁት ሚኒስትሩ፤ ከቀሪው 40 በመቶ ውስጥ ደግሞ ትልቁ ድርሻ ያላቸው የአገር በቀል ተክሎች መሆናቸውንም ጠቁመዋል። ለዚህም በአገር አቀፍ ደረጃ ከተዘጋጁት 24ሺ የችግኝ ጣቢያዎች በትግራይ ክልል አንድ በመቶ፤ በአማራ ክልል 32 በመቶ፣ በኦሮሚያ ክልል 42 በመቶ እንዲሁም በደቡብ ክልል 25 በመቶ እንደሚሸፍን ተናግረዋል። በችግኝ ተከላ ወቅት የኮቪድ 19 ተጽእኖ ተግዳሮት ሊሆን እንደሚችል የጠቆሙት አቶ ኡመር፤ ሂደቱም ችግኝ በመጫንና በማውረድ፤ አካላዊ ርቀትን በመጠበቅ ራስን የመጠበቂያ መሳሪያዎችን በማቅረብና በብዛት ወጣቶችን ተሳታፊ በማድረግ እንደሚካሄድ ገልጸዋል። አቶ ኡመር፤ ችግኝ ለፈጣን ልማት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት፤ የህዝቡን ኑሮና ለማሻሻል እንዲሁም አገርን ለማበልጸግ እንደሚረዳና ከዛሬው የአረንጓዴ አሻራ ይፋዊ የችግኝ ተከላ ዕለት ጀምሮ ተመሳሳይ የችግኝ ተከላ ዘመቻዎች እንደሚካሄዱና ለዚህም በቂ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል። የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ በበኩላቸው ችግኞቹ አገሪቷን በግብርና ኢኮኖሚ መጥቀም የሚችሉ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ እያንዳንዱ ሳይት ላይ ምን ያህል አለ የሚለው በቴክኖሎጂ በመታገዙ ለመንከባከብ እንደሚያግዝና ይህም አምስት ቢሊዮን የመድረሱን ዓላማ ለማሳካት ውጤታማ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።ህዝቡ በየዓመቱ የሚያከናውነው የችግኝ ተከላ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ እንዳይተላለፍ በሚያግዝ ስልት መንግስት ተገቢውን ዝግጅት ማድረጉን የጠቆሙት ሚኒስትሩ፤ ከይፋዊው የተከላ እለት ጀምሮ እስከ ሀምሌ ወር መጨረሻ ተግባራዊ ክንዋኔው እንደሚቀጥል ተናግረዋል። በመሆኑም ዝናብን ሳይጠብቁ በመስኖ በማልማት ምርታማነትን ማስፋፋትና አገሪቷ ወደ ኋላ በቀረው ግብርናዋ በዘመናዊ መንገድ ታግዛ ውጤታማ እንድትሆን ማድረግ እንደሚገባም ሚኒስትሩ ገልጸዋል። “ችግኝ ከተፋሰስ አጠባበቅ አኳያ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። አገር በቀል የሆኑ የዛፍ አይነቶች ቢተከሉ ምርት ሊሰጡ የሚችሉና አፈሩን መንከባከብን የሚችሉ ስላሉ የዝናብ መጠንን ለመጨመር ያስችላል። ይህም የውሃ በጀት እንዲያድግ ያደርጋል። ከዚህም ባሻገር ደለል በወንዞች ውስጥ አልፎ ወንዞች እንዳይሞሉ ይከላከላል። የተሻለ የምንጭና የከርሰ ምድር ክምችት እንዲኖር ያግዛል። የአካባቢንና የዓለም ሙቀትን ለመቀነስም ያስችላሉ” በማለት ችግኝ ከዛፍነቱ ባሻገር ብዙ ሚና እንዳለው አብራርተዋል። የአረንጓዴ አሻራ ብሄራዊ ኮሚቴ አባል አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ፤ በችግኝ ማፊያ ማዕከላት የሚታዩት ተግባራት ጥሩ ደረጃ ላይ መሆናቸውንና ከዚህም በላይ ብዙ ሥራ እንደሚጠበቅ፤ ጅማሮው ያማረ እንደሆነ ሁሉ በዘላቂነት የሚከናወነው ተግባርም እንዲሁ ታሳቢ መደረግ እንዳለበት ተናግሯል። ምርት በተገቢው ሁኔታ ለማግኘት በባለቤትነት እንክብካቤ ማድረግ እንደሚገባና ምርቱን ለተፈለገው ዓላማ ለማዋል ከፍተኛ ጥረት እንደሚያስፈልግ አመላክቷል። የተራቆቱ አካባቢዎችን በማልማት አዳዲስ ምርቶችን የማስተዋወቅ ሥራው ቀጣይነት ያለው እንዲሆን የአረንጓዴ አሻራ ብሄራዊ ኮሚቴ አባላት በሚገባ መስራት እንዳለባቸው አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ተናግሯል። ድምጻዊ ስለሺ ደምሴ (ጋሽ አበራ ሞላ) “በባለሙያዎች አማካኝነት የተደረገው ችግኝ የማፍላት ሥራው በመስክ ጉብኝት መልካም ነገሮችን አይተናል። በተለይ የሚተከሉ ችግኞች በዓይነት መብዛታቸው ደግሞ የማህበረሰቡን የአኗኗር ባህሪ መሠረት ያደረጉ በመሆናቸው የአካባቢን ስነምህዳር ከመጠበቅ አልፈው በፋይናንስ በኩል ከፍተኛ ጠቀሜታ ይሰጣሉ። ለመትከል የታሰበውን ቁጥር ለማሳካት ተክሎች ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆኑ በአእምሮ ውስጥ ቀድሞ መትከል ይገባል’’ ይላሉ። እርሳቸውን ጨምሮ ያሉ የኮሚቴ አባላት እንዲሁም ታዋቂ ግለሰቦች ይህንን ግንዛቤ ለህብረተሰቡ ማድረስ እንዳለባቸው ድምጻዊ ስለሺ ደምሴ ተናግሯል። በተከላው ላይ የሚደረገው ዘመቻ ኃላፊነት ወስዶ በመንከባከብም ሊቀጥል እንደሚገባ ያመላክታሉ። አዲስ ዘመን ግንቦት 28/2012 አዲሱ ገረመው", "passage_id": "b2464022e5e0160a67da350cc00c734f" }, { "passage": "ለኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ውጥኖች ስኬት የደን ሽፋን መጨመርና የተራሮች ወደ አረንጓዴነት መለወጥ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው የአካባቢ የደንና የአየር ንብረት ለውጥ ሚኒስቴር አስታወቀ።የሚኒስቴሩ ሠራተኞች የዛሬውን \"የአረንጓዴ ልማት ቀን\" በአዲስ አበባ-አዳማ የፍጥነት መንገድ ላይ የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ አክብረዋል።ከአዲሱ ዓመት መቀበያ ዝግጅቶች አንዱ የሆነው ዕለቱ \"የአረንጓዴ ልማት ጠበቆች ነን\" በሚል መሪ ሃሳብ ነው የተከበረው።ሚኒስትሩ ዶክተር ገመዶ ዳሌ የአረንጓዴ ልማቱን ቀጣይነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።በዓሉ በየክልሉና በየተቋማቱ የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብና አካባቢን በማፅዳት እየተከበረ መሆኑን ገልፀዋል።የችግኝ እንክብካቤና የአካባቢ ፅዳት ስራው ዓመቱን ሙሉ ሊሰራ እንደሚገባም አሳስበዋል።በተጨማሪም የደኖችን ቁጥር በመጨመር ኢትዮጵያ ላላት የአረንጓዴ ልማት ጥብቅናና ታዳሽ ኢኮኖሚ ስኬት አስተዋፅኦ ማድረግ ይገባል ብለዋል።የደን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ከበደ ይማም በበኩላቸው ደኖችን ማልማት ወደ ታቀደው የኢኮኖሚ አማራጭ ለመሰማራት ቅድሚያ የሚሰጠው ስራ መሆኑን አስረድተዋል።ደኖች ሲለሙና የደን ሽፋኑ በተራሮች አካባቢ ሲበዛ የአፈር መሸርሸርን ከመከላከል ባለፈ ውሃ በብዛት እንዲታቆር ያደርጋል ብለዋል።ይህም ለእርሻ ልማትና አገሪቱ እንደ ትልቅ አማራጭ እየተጠቀመችበት ያለውን በውሃ የሚመነጭ ኃይል ለመፍጠር ያስችላታል።የኃይል አቅርቦቱ ደግሞ ለተጀመረው የኢንዱስትሪ ልማት አቅርቦት ይሆናል ሲሉ አስረድተዋል።የደን ልማቱ ከኢትዮጵያ አልፎ ለጎረቤት አገራት የውሃ ፍላጎትና ተስማሚ የአየር ንብረት ምክንያት በመሆኑ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ እንደሆነም ነው የተናገሩት።የኢትዮጵያ የፍጥነት መንገዶች ኢንተርፕራይዝ ስራ አስኪያጅ አቶ ሙስጠፋ ከድርም የአገሪቱን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ለማሳካት ኢንተፕራይዙ የበኩሉን ድርሻ በመወጣት ላይ መሆኑን ገልፀዋል።ኢንተርፕራይዙ በቀን በአማካይ ከ21 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችን የሚያስተናግድ ሲሆን ከእነሱ የሚወጣውን የጭስ ልቀት ለማካካስ ዘንድሮ 21 ሺህ ችግኞችን ተክሎ በመንከባከብ ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።ኢትዮጵያ በ2025 አገራዊ የደን ሽፋኗን 20 በመቶ ለማድረስ እየሰራች ትገኛለች-ኢዜአ)። ", "passage_id": "4efbd148f29894ee6c5d2b11c326aed8" }, { "passage": "ሰኞ ሐምሌ 22 ቀን 2011 ዓ.ም. በመላ አገሪቱ 200 ሚሊዮን ችግኞች የሚተከሉበት መርሐ ግብር ተይዟል፡፡ ‹‹አገራዊ የአረንጓዴ ልማት ድርጊት መርሐ ግብር›› በመባል በሚታወቀው አረንጓዴ አሻራ የማኖር ሥነ ሥርዓት፣ በችግኝ ተከላ የዓለም ክብረ ወሰን ለመስበር ዕቅድም ተይዟል፡፡ በመላ አገሪቱ በአጠቃላይ አራት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታስቦ እስካሁን 2.7 ቢሊዮን ችግኞች መተከላቸውን የውኃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር በቅርቡ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡፡ ለማኅበራዊ ምርታማነት፣ ተጋላጭነትን ለመቋቋም፣ ለአየር ንብረት ተፅዕኖ መቀነስና መላመድ፣ ጤናን ለማሻሻል፣ ለዱር እንስሳት ከለላ፣ ለብዝኃ ሕይወት ከለላ፣ ለውኃ ማንፃትና ከለላ፣ እንዲሁም ለኢኮኖሚ ጠቀሜታ (ደንና ግብርና) ሲባል በሚከናወነው መርሐ ግብር በመላ አገሪቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ይሳተፉበታል ተብሏል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ለችግኝ ተከላው 2.8 ሚሊዮን ጉድጓዶች መዘጋጀታቸው ተገልጿል፡፡ ነዋሪዎች በ116 ወረዳዎች በችግኝ ተከላው የሚሳተፉ ሲሆን፣ ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡም የመትከያ ቦታ መዘጋጀቱ ታውቋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በተለያዩ ጊዜያት ችግኞችን ሲተክሉ መሰንበታቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ከተለያዩ የውጭ አገር እንግዶች ጋርም ሲተክሉ ነበር፡፡ ሰኞ ሐምሌ 22 ቀን 2011 ዓ.ም. ደግሞ በደቡብ ክልል በወላይታ ዞን በሶዶ ከተማ ዳሞት  ተራራ ላይ፣ ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ችግኝ እንደሚተክሉ ታውቋል፡፡ በምሥሉ ላይ የሚታየው የዳሞት ተራራ ሲሆን፣ ችግኞቹ ደግሞ በሶዶ የደንና ዕፅዋት ልማት ፕሮጀክት የፈሉ ናቸው፡፡", "passage_id": "c7d304018c47a16935952018ba248631" } ]
841356db06403e817a5278c53afc2643
01c3a5732d6f5bdd77714d572c7bdf9f
የሊጉ በቢዝነስ ሞዴል መመራት አበረታች ጅምር መሆኑ ተገለጸ
ብርሃን ፈይሳአዲስ አበባ፡- የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ በሼር ካምፓኒ እንዲተዳደር መደረጉና የቴሌቪዥን ሽፋን ማግኘቱ ለሌሎች ስፖርቶችም አበረታች ጅምር መሆኑ ተገለጸ። በብሄራዊ ስፖርት ምክር ቤት የ2013ዓም የስፖርት ዘርፍ አፈጻጸም ሰነድ ላይ እንደተመለከተው፤የሃገሪቷ ስፖርት በቢዝነስ ሞዴል እንዲመራ በማድረግ ረገድ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሪሚየር ሊጉን (ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ) በሼር ካምፓኒ እንዲመራ ማድረጉ መልካም ጅማሬ ነው። በአጭር ጊዜ ውስጥ የተደራጀው ካምፓኒው ውድድሩን የቴሌቪዥን መብት እንዲያገኝ እና የውድድር ስያሜውንም መሸጥ መቻሉ በስፖርት ላይ ትልቅ ተስፋን እና መነቃቃት ፈጥሯል። የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር፤ ሃገር አቀፍ የስፖርት ማህበራት ስፖርቱን በቢዝነስ ሞዴል ከመምራት አንጻር ሰፊ ስራ መሰራቱን ጠቅሰው፣ ለእዚህም በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሊግ ካምፓኒው መቋቋም ተጠቃሽ መሆኑን አመላክተዋል። የውድድሩ መሸጥ በተለይ ክለቦች በገቢ ራሳቸውን እንዲችሉ የሚያደርግ፣ ለተጫዋቾችም መልካም ዕድል የፈጠረና የሃገርን ገጽታ ለመገንባት ትልቅ አስተዋጽኦ ያደረገ ነው ነው ያሉት ኮሚሽነሩ፣በተመሳሳይ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብም ወደ አክሲዮን የተለወጠበት ሁኔታ ሌሎች ክለቦች ልምድ የሚወስዱበት ነው ብለዋል። ይህም በቢዝነስ ሞዴል ከመመራት አንጻር የተጀመሩ ስራዎች እንዳሉ ማሳያ መሆኑንም ጠቅሰዋል።የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው በበኩላቸው፤ በዓመቱ (2012ዓም) የሊግ ኮሚቴ በመፍጠር እግር ኳስ የስፖርታዊ ጨዋነትና የስፖርት መርህን የሚያከብር ዘርፍ እንዲሆን መደረጉ መልካም መሆኑን ጠቁመዋል። የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ራሱን መቻልም ለሌሎች እንዴት ራስን በገቢ መቻል ይቻላል የሚለውን ያሳየ መሆኑን ተናግረው፣ ጥሩ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ጠቋሚ ነው ብለዋል። ይህንንም አጠናክሮና ተባብሮ ማስኬድ ከተቻለ በስፖርቱ የሚነሱ ጥያቄዎችና ችግሮች ይቀረፋሉ ሲሉም ተስፋቸውን አንጸባርቀዋል። ብሔራዊው የስፖርት ሪፎርም ክለቦችና የስፖርት ማህበራት በገቢ ራሳቸውን ችለው ከመንግስት ድጎማ እንዲላቀቁ እንዲሁም ሃብት እንዲያፈሩ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ያመላክታል። እንደ ኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን የአፈጻጸም ሪፖርት፤ መንግስት እስካሁን ከክልል እስከ ፌዴራል ባለው ደረጃ 163 ሚሊዮን 177ሺ 165 ብር ድጋፍ አድርጓል። ይህንን ለመቅረፍም ሃገር አቀፍ የስፖርት ማህበራት ያሉበት ሁኔታና ቁመና ለማወቅ ቅኝት በማድረግ ያሉበትን ደረጃ ለመለየት ጥረት ተደርጓል። የስፖርት ማህበራት ስፖርቱን በቢዝነስ ሞዴል በመምራት ከድጎማ የሚላቀቁበትና የራሳቸውን አቅም በማጎልበት የ10 ዓመቱን የስፖርት ልማት እቅድ ግቦች የሚያሳኩበትን ቁመና መፍጠርም በተያዘው ዓመት የኮሚሽኑ እቅድ መሆኑም ተጠቁሟል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 28/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=39011
[ { "passage": "የ2011 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከወትሮው በተለየ አጨቃጫቂ ሁኔታ፣ በተደጋጋሚ መቆራረጥ እንዲሁም በአሰልቺ የውድድር መርሐ ግብር ተጠናቋል፡፡ የዘንድሮው የፕሪሚየር ሊግ ከዚህ ቀደም ይታዩ ከነበሩ ስፖርታዊ ባላንጣነት ይልቅ ‹‹ብሔር ተኮር›› መጠቃቃቶችና ግጭቶችን አስተናግዶ አልፏል፡፡ በሊጉ በተፈጠሩ አለመግባባቶች ምክንያት በተለይ የአዲስ አበባ ክለቦች የተለየ አቋም እንዲይዙ አድርጓል፡፡ አንጋፋው ቅዱስ ጊዮርጊስ የሊጉን የመጨረሻ ሦስት ጨዋታዎች ሳያከናውን የውድድር ዓመቱ መርሐ ግብር ተጠናቋል ቢባልም፣ የክለቡ ቀጣይ ዕጣ ፋንታ እንዴት ሊሆን ነው? የሚለውና ሌሎች ከስፖርት መርህና ባህል ባፈነገጠ መልኩ ሲሰጡ የነበሩ ውሳኔዎች፣ ፌዴሬሽኑ ከፊት ለፊቱ የተደቀኑበት ጥያቄዎችን ሳይፈታና የሊጉን ቀጣይ አካሄድ እንዴት እንደሚሆን ሳይወስን የ2012 ዓ.ም. የውድድር ዘመን በወርሃ ጥቅምት አልያም ህዳር ለመጀመር ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ሽር ጉድ እያለ መሆኑን እየተሰማ ይገኛል።ከአዲስ አበባ ክለቦች በኩል የተያዘው አቋም ገፍቶ መሄድ የፕሪሚየር ሊጉ ህልውና ጥያቄ ውስጥ መሆኑን ምልክት እያሳየም ይገኛል። ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ የሊጉን አደረጃጀት እንዲቀየር አጥብቀው ሲጠይቁና ሲሞግቱ የሰነበቱት ክለቦቹ ይህንን መንገድ በመተው በራሳቸው በመጓዝ ውጤታማ ለመሆን ከጫፍ ደርሰዋል። ከብሄራዊ እግር ኳስ ፌዴሬሽኑ በኩል ቅቡልነት ያጣው የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጥያቄም ጥናትን መሰረት በማድረግ ተቀብሎ ተግባራዊ ሊያደርገው መሆኑ ታውቋል። የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በኢትዮጵያ እግር ኳስ የሚታየውን የሊግ ውድድር የአደረጃጀት ችግሮች በመለየትና የመፍትሔ ሀሳቦች በማስቀመጥ ላይ ያተኮረ የአውደ ጥናት መድረክ ከትናንት በስቲያ በሸራተን ሆቴል አዘጋጅቷል።በመድረኩ ላይ\nዋነኛ ትኩረት የነበረው የሊግ አደረጃጀት ጉዳይ ሲሆን፤ «በኢትዮጵያ አሁን ያለው የሊግ አደረጃጀት በፋይናንስ ረገድ ክለቦች ላይ ያለው ተጽእኖ ምንድ ነው? » በሚል ጥናታዊ ጽሁፍ ቀርቦ ነበር። የጥናቱ አቅራቢ የአዲስ አበባ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ሥራ አስኪያጅ አቶ ገዛኸኝ ወልዴ እንዳሉት በኢትዮጵያ የሊግ ውድድር ፕሪሚየር ሊግ፣ ከፍተኛ ሊግና አንደኛ ሊግ ናቸው፤ በእነዚህ ውድድሮች ላይ በየዓመቱ ሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር ወጪ ይደረጋል። አብዛኞቹ ክለቦች የከተማ ቡድኖች በመሆናቸው ከዚህ ውስጥ 95 በመቶ ከመንግስት ካዝና ወጪ የሚሸፈን ነው። ገንዘቡም ለተጫዋቾች ወርሃዊ ደሞዝ፣ ለምግብ፣ ለመኝታ፣ ተዟዙሮ ለመጫወትና ለትራንስፖርት እንደሚውል ተናግረዋል።የወጪውን ከፍተኝነት ከትራንስፖርት ጋር ተያይዞ ያለውን ሁኔታ አቶ ገዛኽኝ ሲገልጹ ፤ « በዋናነት ተዟዙሮ መጫወት በሁሉም እርከኖች ለትራንስፖርት ብቻ\nግማሽ ቢሊዮን (490 ሚሊዮን 800 ሺህ) ብር በየዓመቱ ወጪ ይሆናል። ይህ ሁሉ ወጪ ወጥቶ አንድ በፕሪሚየር ሊግ ውድድር የሚሳተፍ ቡድን ሲያሸንፍ 150 ሺህ ብር የገንዘብ ሽልማት ያገኛል። ከዚህ አኳያ ወጪና ገቢው የማይመጣጠን የገንዘብ ቀውስ ያለበት የሊግ አደረጃጀት እንደሚገኝ ማሳያ ነው» ሲሉ ተናግረዋል። የጥናቱ አቅራቢ እንዳሉት የፊፋ የክለቦች ፈቃድ የሚለው በምንም መንገድ የአንድ ክለብ ወጪና ገቢ መበላለጥ የለበትም ነው፤ ሆኖም በኢትዮጵያ ያለው ነባራዊ ሁኔታ ይሄንን የሚያሳይ አለመሆኑን ገልጸዋል።ሌላው የሊግ አደረጃጀቱ ከጸጥታና ደህንነት፣ ከፋይናንስ አኳያ ያለበት ሁኔታ ምን እንደሚመስል ያቀረቡ ሲሆን ችግሮች መኖራቸውን አስረድተዋል። የሊጉ አደረጃጀት ስፖርታዊ ጨዋነት እንዲጓደል በር ከፋች መሆኑን አመላክተዋል። አሁን ያለው የሊግ አደረጃጀት ከክልሎችና ከከተማ አስተዳደሮች ተሳትፎ አንጻር ሲመዘን ሁሉንም ውድድር የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጠቅልሎ የያዘ መሆኑ አቅም ያላቸው ተጫዋቾች እድል እንዳይኖራቸው አድርጓል። የክልሎችን የውስጥ ውድድር አዳከሟል ሲሉ አደረጃጀቱ በሌላ ማዕዘን ያለበትን ክፍተት በጥናቱ አስረድተዋል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ እግር ኳስ የሊግ አደረጃጀት ከፋይናንስ አንጻር ሲታይ ከፍተኛ ችግር ያለበት፣ የመንግስትን ገንዘብ ጥቅም በሌለው መንገድ የሚያስወጣ፣ ስፖርታዊ ጨዋነትን በአጉል መንገድ እንዲጓዝ ያደረገም በመሆኑ ያሉትን ክፍተቶች መስመር በማስያዝና የወደቀውን እግር ኳስ ለማዳን አዲስ የሊግ አደረጃጀት ተግባራዊ ማድረግ አስፈላጊ እንደሚሆን አሳስበዋል።በአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የቀረበውን ጥናትና የሊጉ አደረጃጀት እጣ ፈንታ መሰረት በማድረግ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማኅበር ቦርድ ሊቀመንበር አቶ አብነት ገብረመስቀል እንዳሉት የአዲስ አበባ ክለቦች እስከ ዛሬ ድረስ በየክልሉ ስንሄድ ያልደረሰበን ዛቻና ድብደባ የለም። የእኛ አንድ አለመሆንና ምስቅልቅሉ የወጣ ስራ አስፈጻሚ መምረጣችን ነው ዋጋ እየከፈልን ያለው በመሆኑም ከዚህ በኋላ የአዲስ አበባ እግር ካስ ፌዴሬሽን ከጎናችን ቆሞ አንድ መሆንና ያለው የውድድር አደረጃጀት (ፎርማት) መቀየር አለብን ብለዋል ። “እንደ አዲስ አበባ አንድ ሆነን በራሳችን ውድድር እናካሂድ። በዚህ ምክንያት ጉሮሯቸው የሚዘጋ ጥቅማቸው የሚቀር ግለሰቦች የተለያየ ስም ሊሰጡን ይችላሉ። እኛ የፖለቲካ እና የብሄር ቡድኖች አይደለንም። ለሃገራችን ሰላም የሚጠቅመውን እያሰብን ነው ያለነው” ብለዋል።የኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ መሥራችና የቦርድ ሰብሳቢ መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ በበኩላቸው፤ ባለፉት ጊዜያት የተለያዩ ውይይቶችን ስናደርግ ቆይተን አሁን ወሳኝ ጊዜ ላይ ደርሰናል። እስከ ዛሬ የሊግ አደረጃጀት ( ፎርማት) የኢትዮጵያ እግር ኳስ ውስጥ ከፍተኛ ሃብት ያካበቱ ግለሰቦች ምን አይነት ሀብት እንዳፈሩ ከነመረጃው በጥናት የምናቀርብ ይሆናል ብለዋል። መቶ አለቃ ፈቃደ አክለው፤ እነዚህ ግለሰቦች የራሳችንን ውድድር ስናካሂድ ከፍተኛ ጥቅም ስለሚቀርባቸው ቡናና ጊዮርጊስ የራሳቸውን ውድድር ብቻቸውን ያድርጉ እያሉ ይሳለቃሉ። አሁን ጉዳዩ የቡናና የቅዱስ ጊዮርጊስ ብቻ አይደለም። የኢትዮጵያን እግር ኳስ ከውድቀት፣ ከሞት የማዳን ነው። ከዚህ በኋላ ለአንድ ቀን ማደር አንችልም። ይህን የመግባቢያ ሰነድ መፈረም አለብን ሲሉ በተደጋጋሚ ጥያቄን ሲያቀርቡበት የነበረውን የሊግ አደረጃጀት እንዲሻር ተማጽኖን አቀረቡ። በመድረኩ ላይ ተሳትፎ ያደረጉ 22 የአዲስ አበባ ክለቦችም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ህልውና በአዲስ የሚቀይረውን የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተቀበሉ። ከፌደራል ፖሊስ ክለብ በቀር በስብሰባው ላይ የተገኙ ለእግር ኳሱ እድገት ሆነ አላግባብ የሚወጡ የመንግስት የገንዘብ ወጪን ለማስቀረት በሚል ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ስር በመሆን ለመወዳደር በጋራ ተስማምተው ተፈራርመዋል። ስምምነታቸውም የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለሚመለከተው አካላት በሙሉ እንዲያደርስ ወስነው ጉባኤው ተጠናቋል።የዚህ አይነቱ\nየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ህልውና\nመንታ መንገድ ላይ እንዲቆም\nያደረገው ሆኗል። በጉዳዩ\nላይ ከብሄራዊ እግር\nኳስ ፌዴሬሽኑ በኩል\nምንም አይነት ምላሽም\nሆነ አስተያየት ያልቀረበ\nሲሆን፤ የአዲስ አበባ\nክለቦችን ውሳኔ ተከትሎ\nሌሎች ክልሎችም ተመሳሳይ\nአቅጣጫን እንደሚከተሉ ይጠበቃል።አዲስ ዘመን ነሃሴ 1/2011ዳንኤል ዘነበ ", "passage_id": "daaac1af515db4246ce68f63ca0bff14" }, { "passage": "አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 13/2006 (ዋኢማ) – ሁሉንም የልማት ሃይሎች አቀናጅቶ በመንቀሳቀሱ የ2006 በጀት አመት የድርጅትና የመንግስት እቅድ አፈጻጸም ውጤታማ መሆኑን የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አስታወቀ።የኢህአዴግ ም/ቤት ጽ/ቤት ለዋልታ በላከው እንዳስታወቀው ኮሚቴው በዛሬው እለት  ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው እንደገመገመው  በገጠርና በከተማ የልማትና መልካም አስተዳደር ስራዎች በድርጅት መሪነት ስኬቶችን ማስመዝገብ ተችሏል።በገጠር ልማት  ከአካባቢ አካባቢ  አንጻራዊ ልዩነት መኖሩን የጠቆመው መግለጫው በተለያዩ መስኮች ያለው የሰራዊት ግንባታ እድገት ማሳየቱንም ገልጿል።የለማውን ተፈጥሮ ሃብት ጥቅም ላይ በማዋልና ችግኞችን በመትከልም ሆነ   በመንከባከብ ረገድ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለማስወገድ  ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው አሳስቧል፡፡በ2006/2007 የምርት ዘመን የሰብል ልማት ምርትን ከ20 በመቶ በላይ ለማሳደግ የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም መግለጫው ጠቁሟል።በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ልማት ሰፋ ያለ እንቅስቃሴ የተደረገ ቢሆንም ኢንተርፕራይዞች በማኑፋክቸሪንግ መስክ በስፋት በማሳተፍና  የተፋጠነ ሽግግር እንዲያካሂዱ በማድረግ በኩል የታዩ  ክፍተቶችን ለመሙላት ርብርብ እንደሚደረግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ገልጿል።በገጠር  ለ2 ነጥብ 2 ሚሊየን ወጣቶች  የሥራ እድል ለመፍጠር ታቅዶ 85 በመቶ መከናወኑን የጠቆመው መግለጫው በከተሞችም ከ2 ሚሊዮን 600 ሺሕ በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሮላቸዋል።በትምህርት፤ በጤናና ሌሎች ማህበራዊ ዘርፎች የአመቱ አፈፃፀም ስኬታማ እንደሆነም ስራ አስፈጻሚው ተመልክቷል። ", "passage_id": "75dcf9ddf12343c9d3ad1772ca70eaab" }, { "passage": "በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ባለው የመካከለኛ አመራር ጥልቅ ተሃድሶ የውይይት መድረክ ላይ ሊቀመንበሩ እንደገለጹት በክልሉ የሚስተዋሉ ዋና ዋና ችግሮች በመፍታት የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን ማጠናከር ይገባል።\"በጥልቅ ተሃድሶው ድርጅቱ ያለውን አሰራር፣ ጥንካሬና ድክመትን በመገምገም የህብረተሰቡንና የአካባበውን ነባራዊ ሁኔታ ለመረዳትና ከወቅቱ ሁኔታ ጋር እራሱን እያመዛዘነ ለማስተካከል እጅግ አስፈላጊና ተገቢ ነው \"ብለዋል።ድርጅቱ የመጀመሪያውን ተሃድሶ ሲያደርግ 15 ዓመታት ማስቆጠሩን ጠቆሙት አቶ ለማ በዚህ ጊዜ ውስጥ በርካታ ለውጦች መገኘታቸውን ተናግረዋል።በእዚኒህ ዓመታት እየጨመረ የመጣውን የህዝብ ቁጥር ታሳቢ በማድረግ በልማት ዘርፉ አንፀባራቂ ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰው \"የወጡ ፖሊሲዎች፣ህጎችና የምንሰራቸው የየእለት ስራችን ከህዝብ ፍላጎት ጋር በማነፃፀር እንዲገመገሙ ይደረጋል\" ብለዋል ።ጥልቅ ተሃድሶው የህዝብን ጥቅም በማስከበር ረገድ ያሉ ጉድለቶችንና መልካም ነገሮችን በመመርመር መስተካከል የሚገባቸውን በዚሁ አግባብ ተፈጻሚ ለማድረግ ዓይነተኛ መሳሪያ ነው።ባለፉት ሦስት አምስት ዓመታው በህብረተሰቡ ውስጥም በርካታ ለውጦች እንዳሉ የተናገሩት ሊቀመንበሩ የህዝብ የልማት ፍላጎት መጨመሩን፣የመንግስት ስራ መስፋቱንና ውስብስብ ከመሆኑ ነባራዊ ሁኔታ አንፃር እየታየ የውስጥ አቅምን መለካት የተሃድሶው ዋነኛ ማጠንጠኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ከዚህ በመነሳት የህዝቡን ፍላጎት አሁን ያለው አቅም፣ ስፋትና ሀብት እንዲሁም የህዝቡን ጥያቄ ለመመለስና ለማሳካት ድርጅቱ ራሱን ለመፈተሽ መዘጋጀቱ ተገቢ መሆኑን ጠቁመዋል።የድርጅቱ ሊቀመንበር እንዳመለከቱት ከጥልቅ ተሃድሶው በፊት የተሰሩ ማህበራዊ፣ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊ ለውጦች ቢኖሩም በዚያው ልክ የሚታዩ ጉድለቶች ስላሉ ህብረተሰቡን ለቅሬታ ዳርገውታል፡\"ቅሬታው የተባላሹ ነገሮች እንዲስተካከሉለት ከመፈለግ የመነጨ በመሆኑ እንደ ድርጅትና እንደ መንግስት ተስተካክለን እንድንገኝ የሚያግዝ ነው \"ብለዋል ።ፍትህ በገንዘብ ሳይሆን በአግባቡ ለዜጋ እንዲሰጥ ከመፈለግ የመነጨ ቅሬታ በመሆኑ ድርጅቱ አንድ በአንድ ችግሮቹን ነቅሶ በማውጣት የማስተካከል እርምጃ እንደሚወስድ አቶ ለማ ተናግረዋል፡፡ ሥርዓቱን ለማስቀጠል የመልካም አስተዳደርና የኪራይ ሰብሳቢነት አደጋን እልባት መስጠት ተገቢ መሆኑን ጠቁመው \" ሁላችንም ቆም ብለን ራሳችንን እያየን ልንፈትሽ ግድ ነው \"ብለዋል።ድርጅቱ አስፈላጊውን አስተዳደራዊና ህጋዊ እርምጃ ጭምር ለመውሰድ አቋም ወስዶ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ መግባቱንም አስታውቀዋል።የህዝቡን ጥያቄ በጋራ በመነጋገርና በመመካከር ለመመለስ ታስቦ የተዘጋጀ ተሃድሶ መሆኑን ያመለከቱት አቶ ለማ “እኛው በእኛው ህዝብ ላይ የፈጸምናቸውን በደሎች አመራሩ አንድ በአንድ እያነሳ ሂስና ግለ ሂስ ያደርጋል” ብለዋል።\"የጀመርነውን ተሃድሶ እስከ ታች በማውረድ ህብረተሰቡ ተሳታፊ እንዲሆን ካደረግን የገባንባቸው ችግሮች አስተካክለን የተሻለና ተስፋ ያለው ስራ እንሰራለን ብለን እንጠብቃለን\" ብለዋል።ከጥቅምት 25 እሰከ ሕዳር 3/2009 ዓም ድረስ በአዳማ፣ ሀረር፣ ሻሸመኔ፣ ነቀምትና ጅማ ከተሞች እየተካሄደ ባለው የጥልቅ ተሃድሶ መድረክ ላይ ከ5 ሺህ 350 በላይ መካከለኛ አመራሮች እየተሳተፉ ናቸው። የመድረክ ዋና አላማ በክልሉ የተጀመረውን የመስመር ማጥራት እርምጃ ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋር ያለመ መሆኑም ቀደም ብሎ ተገልጿል -(ኢዜአ) ።", "passage_id": "1fa552c1beb0dcdd2259d3c930a94cd3" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ስኬታማ ያደረጉትን ሚስጥሮች በሌሎችም ትላልቅ የአገሪቱ ፕሮጀክቶች ላይ መድገም ይቻል ዘንድ ተሞክሮውን እንዲያሰፋ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ አሳሰቡ።የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በዛሬው እለት ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚገኘውን የመንገደኞች ማስተናገጃ (ተርሚናል) ጨምሮ የተለያዩ የአየር መንገዱ የሥራ እንቅስቃሴዎችን ጎብኝተዋል።በጉብኝቱ ላይ የተገኙት የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ እና የምክር ቤቱ አባላት በሰጡት አስተያየት፤ የአየር መንገዱ የአፍሪካና የዓለም ኩራትነቱን አጠናክሮ መቀጠል መቻሉን ማረጋገጣቸውን ተናግረዋል።ይህ ታላቅ ስኬት ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በሚያንቀሳቅሱ የሀገሪቱ የተለያዩ የልማት ተቋማት ላይም መጠቀም ይቻል ዘንድ የስኬት እውቀቱ ወደሌሎችም የሚተላለፍበትን መንገድ አየር መንገዱ እንዲዘይድ አፈ ጉባኤው ጠይቀዋል።የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረማሪያም በበኩላቸው ኩባንያው እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር እስከ 2025 ድረስ ለማሳካት ይዞት የነበረውን ህልም ከወዲሁ እውን ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።በአሁኑ ወቅት የኢትጵያ አየር መንገድ ደንበኞችን በማጓጓዝም ሆነ በካርጎ ጭነት ማመላለስ በአፍሪካ ከሚገኙ አየር መንገዶች ሁሉ ቀዳሚው እንደሆነ ጠቁመዋል።አክለውም አየር መንገዱ በተጠናቀቀው የአውሮፓዊያን ዓመት 12 ሚሊየን መንገደኞችንና ከ432 ሺህ ቶን በላይ ዕቃዎችን አጓጉዟል ሲሉም አስረድተዋል።በዚህ አገልግሎቱም በዓመቱ አራት ቢሊየን ዶላር ማስገባት መቻሉንም ይናገራሉ።በማንኛውም የፖለቲካ ሁኔታ ጣልቃ አለመግባቱ፤ እስከ አሁን ሀገሪቱን የመሩ መንግሥታትም በአየር መንገዱ አሠራር ላይ ጣልቃ አለመግባታቸው አየር መንገዱ ስኬታማ እንዲሆን ካስቻሉት ምክንያቶች መካከል ናቸው ብለዋል።የማኔጅመንቱ ተጠያቂነትንና ግልጸኝነትን መሰረት ያደረገ የአሠራር ሥርዓት መከተሉም ለስኬቱ ቁልፍ እንደሆነ ጠቁመዋል።የምክር ቤቱ አባላት በአየር መንገዱ የአሠራር ሥርዓትና የስኬት ሚስጥር ላይ ጥያቄና ማብራርያ ጠይቀው ከዋና ሥራ አስፈጻሚው መልስ ተሰጥቶባቸዋል።ምክር ቤቱ አየር መንገዱ ለያዘው ቀጣይ ስኬት እውን መሆን አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም አባላቱ ቃል ገብቷል።የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአምስት አህጉራት ከ127 በላይ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎች ላይ የሚበር ሲሆን፤ በሳምንት ከ2 ሺህ በላይ መንገደኞችን ያስተናግዳል፤ በየቀኑ ደግሞ ከ300 በላይ በረራዎችን እንደሚያደርግም በዚሁ ጊዜ ተጠቅሷል።ምንጭ፦ ኢዜአ", "passage_id": "7b15b00c0009147fb4a8ff827f6108b2" }, { "passage": "የኢህአዴግ ም/ቤት ጽ/ቤት ለዋልታ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ለእቅዱ እንደ መነሻ የተቀመጠውን የመጀመሪያውን የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ያለፉት አራት አመታት አፈጻጸም ከእቅዱ አላማዎች፣ አቅጣጫዎችና እና ዋና ዋና ግቦች አኳያ ገምግሟል፡፡የእቅድ አፈጻጸሙም በኢኮኖሚ እድገት፣ በመሰረተ ልማት፣ በማህበራዊ ልማት፤ በአቅም ግንባታና በመልካም አስተዳደር እንዲሁም በባለብዙ ዘርፎች ዙሪያ የህዝቦችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስኬታማ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው ብሏል፡፡ በእቅዱ የትግበራ ሂደት ቁልፍ በሆኑ ሀገራዊ የልማት ጉዳዮች ዙሪያ ከፍተኛ ህዝባዊ መነሳሳት የተፈጠረበት እንደነበረና ይህም ለቀጣይ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች የተደራጀና የተጠናከረ አቅም እንደሚሆን ኮሚቴው አስምሮበታል፡፡በመጀመሪያው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ከተቀመጡት ግቦች ውስጥ በመሰረታዊ አማራጭ በየአመቱ በአማካይ የ11.2 በመቶ እድገት ማስመዝገብ አንዱ የነበረ ሲሆን ያለፉት አራት አመታት አፈጻጸም ሲታይም ኢኮኖሚው በአመት 10.1 በመቶ በማደግ ባለሁለት አሃዝ የኢኮኖሚ እድገቱን አስቀጥሏል፡፡ አፈጻጸሙ ከተቀመጠው ግብ አኳያ የተወሰነ ጉድለት ቢኖረውም የአለም ኢኮኖሚ ከፍተኛ ችግሮችና ውጣ ውረዶች በነበሩበት ወቅት ችግሩን በመቋቋም በዚህ ደረጃ ማደጉ በጣም ከፍተኛ እድገት እንደሆነ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ገምግሟል፡፡በአገራችን የተመዘገበው እድገት በተመሳሳይ ወቅት ከሰሃራ በታች ባሉ አገሮች ከተመዘገበው የ5 በመቶ እድገት አኳያ ሲታይም በጣም ከፍተኛና ፈጣን እድገት እንደሆነ ታይቷል፡፡ እድገቱ አገራችንን በአለም አቀፍ ደረጃ እጅግ ከፍተኛ ፍጥነት ካስመዘገቡ ጥቂት አገሮች አንዷ እንድትሆን ያደረገ የትክክለኛ መስመርና ፖሊሲ ውጤት መሆኑም ተመላክቷል፡፡ ኮሚቴው ከግምገማው በመነሳት ፈጣንና ተከታታይ እድገቱን አጠናክሮ ማስቀጠል የሁለተኛው እድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱ አንዱ የትኩረት አቅጣጫ እንደሚሆን አስምሮበታል፡፡ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው በመጀመሪያዊ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱ አፈጻጸም የነበሩ ስኬቶችን፣ እጥረቶችንና ፈታኝ ሁኔታዎችን እንዲሁም የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን በዝርዝር ከፈተሸ በኋላ ለሁለተኛው የእድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅድ እንደ መነሻ እንዲሆኑ አስቀምጧል ፡፡ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ለሁለተኛው የአምስት አመት የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱ በተቀመጡ አቅጣጫዎችና ግቦች ላይ ከተወያየ በኋላ ዝርዝር እቅዱ እንዲዘጋጅ የሚያስችሉ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው እለት ማጠናቀቁን የኢህአዴግ ም/ቤት ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡ ", "passage_id": "e998294aa8798f32a7283a0938bf1bd4" } ]
9f0d6f3852caca37e94c2b2a90b869e7
8f8010b037e30c19d8f3afa6d45e4f21
የኦሊምፒክ ሥራ አስፈፃሚው እስከ ቶኪዮ ኦሊምፒክ ማግስት ይቀጥላል
ቦጋለ አበበ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አርባ አምስተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ባለፈው እሁድ በሐዋሳ ከተማ ሲያካሂድ የተለያዩ ውሳኔዎች ተላልፈዋል፡፡ ባለፉት አራት ዓመታት ሲያገለግል ቆይቶ ዘንድሮ ይጠናቀቅ የነበረው የኮሚቴው የስራ አስፈፃሚና የፕሬዚዳንት የስልጣን ዘመን በመጪው ክረምት እስከሚካሄደው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ማግስት ድረስ እንዲቀጥል ጉባዔው ወስኗል፡፡ የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ባለፈው ዓመት ሊካሄድ የነበረ ቢሆንም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ለአስራ ስድስት ወራት ተራዝሞ በመጪው ክረምት ሊካሄድ ቀን ተቆርጦለታል፡፡ ኮሚቴውን ሲመራ የነበረው ሥራ አስፈፃሚ በኦሊምፒኩ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የተለያዩ ዝግጅቶችን ሲያደርግ የቆየ ሲሆን ዘንድሮ የስራ ዘመኑን አጠናቆ በጠቅላላ ጉባዔ ምርጫ ይካሄድ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ኦሊምፒኩ በመራዘሙ ሲዘጋጅ የቆየው ስራ አስፈፃሚ የልፋቱን ውጤት እንዲመለከት እስከ ኦሊምፒኩ ማግስት እንዲቀጥል ጠቅላላ ጉባዔው ውሳኔ አስተላልፏል፡፡ ጉባዔውን በንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ፣ ኢትዮጵያ የአኖካን ጉባኤ ባስተናገደችበት ማግስት አስረኛ ክልል ሆኖ እንደ አዲስ በተዋቀረው የሲዳማ ክልል ጉባዔው መካሄዱ ልዩ እንደሚያደርገው ገልፀዋል፡፡ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ግዜ የአፍሪካ ወጣቶች ኦሊምፒክን በ2022 ለማስተናገድ እድል ባገኘችበት ማግስት በሲዳማ ክልል ዘንድሮ የኢትዮጵያ ወጣቶች ኦሊምፒክ ጨዋታ እንደሚካሄድም ጠቁመዋል፡፡ ኮሚቴው በቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ የአበበ ቢቂላን የ1964 የቶኪዮ ኦሊምፒክ ገድል ለመድገም በምትዘጋጅበት ወቅት ጉባዔውን ማካሄዱና በኮቪድ-19 ስጋት ውስጥ ሆኖ መከናወኑ ጉባዔውን የተለየ እንደሚያደርገውም ተናግረዋል፡፡ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው፣ ስፖርት የማህበራዊና ተፈጥሯዊ ሳይንስ ዘውግ መሆኑን ጠቅሰው ማህበራዊ ትስስርን በእጅጉ የሚፈጥር በመሆኑ ህብረተሰቡ ስፖርትን ባህሉ እንዲያደርግ የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል። እስካሁን ድረስ በስፖርት ዘርፍ የተፈጠረው ተወዳዳሪነት ዝቅተኛ መሆኑን በመጥቀስም በአትሌትክስ ስፖርት ኢትዮጵያ ያስመዘገበችው ውጤት በሌሎችም እንዲደገም መሠራት እንዳለበት አብራርተዋል። ሚኒስትሯ የህብረተሰብ ስፖርትንም ለማስፋፋት በትምህርት ቤትና በስራ ቦታ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ መሠራት እንዳለበት ገልፀዋል። የኢፌዲሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሸነር ኤሊያስ ሽኩር በበኩላቸው፣ 45ኛው የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የተካሄደው በስፖርት ህብረተሰቡ ዘንድ መነቃቃት በተፈጠረበት ወቅትና በብሔራዊ የስፖርት ምክር ቤት መደበኛ አንደኛ ስብሰባ ትላልቅ ውሳኔዎች በተላለፈበት ወቅት መሆኑን አስታውሰዋል፡፡ የአኖካ ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ የተካሄደ መሆኑን ጠቅሰውም ሠላማዊና አስተማማኝ ሁኔታ በኢትዮጵያ መኖሩን አኖካ በማረጋገጡ ቀጣይ ስብሰባዎችን በራሱ ሙሉ ወጪ በኢትዮጵያ ለማካሄድ መነሳሳት እንዳሳየ አብራርተዋል። ለቶኪዮ 2020 የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ዝግጅት ማድረግ በተጀመረበት ወቅት ላይ ጉባዔው በስፖርት ምክር ቤት በተቀመጡ ወሳኔዎችና አቅጣጫዎች መሠረት በጥልቀት መምከር እንዳለበት አስረድተዋል፡፡ ስፖርት ለሠላም፣ ለወዳጅነት፣ ለአንድነት፣ለወንድማማችነትና ለብልፅግና መሆኑን በመገንዘብ ጠቃሚ ውይይት እንዲደረግ አሳስበዋል፡፡ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ፕሬዚዳንት አቶ ደስታ ሌዳሞ ጉባኤውን በንግግር የከፈቱ ሲሆን፣በዕለቱ በስፖርት ላይ በመስራት እውቅና ለተሰጣቸው ፈርጦች ምስጋና አቅርበዋል። በጉባኤው በስፖርት አመራርነት በፌደራልና በክልል ደረጃ አገልግሎት ሲሰጡ ቆይተው በአሁኑ ጊዜ በተለያዩ አመራር ቦታዎች ላይ ለሚገኙ አካላት የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።ከነዚህም መካከል የቀድሞ የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትር የነበሩትና በአሁኑ ወቅት የደቡብ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ርስቱ ይርዳው፣ የቀድሞ ወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትር ዴዔታ ወይዘሮ ሃቢባ ሲራጅ፣ የቀድሞ ወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትር ዴዔታ የነበሩትና አሁን የደቡብ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆን እያገለገሉ የሚገኙት አቶ ተስፋየ ይገዙ፣ የቀድሞ የኢፌዴሪ ምክትል ስፖርት ኮሚሽነርና አሁን የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ ጌታቸው ባልቻ የእውቅና ሽልማት ከተበረከተላቸው መካከል ዋነኞቹ ናቸው። ጠቅላላ ጉባዔው የ44ኛው መደበኛ ጉባኤ ቃለ ጉባኤ ፣ የ2012 ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርትና የውጪ ኦዲተር ሪፖርት መርምሮ ያፀደቀ ሲሆን የ2013 ዓ.ም ዕቅድና የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ቀጣይ 46ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔን በተመለከተ መክሮ ውሳኔ አስተላልፏል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 28/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=39012
[ { "passage": "የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ለአስራ ስድስት ወራት በመራዘሙ ምክንያት የአዘጋጅ አገሯ ጃፓን መንግሥትና የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ገና ከጅምሩ በርካታ ውስብስብ ችግሮች ውስጥ መዘፈቃቸው ሲነገር ቆይቷል። የኦሊምፒክ ውድድሩ በዓለም ላይ ከፍተኛ ስጋት በፈጠረው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ጋር ተያይዞ ወደ ቀጣዩ ዓመት መራዘሙ ግድ መሆኑ ከታመነበት ወቅት አንስቶ አዘጋጆቹ በርካታ ፈተናዎችን መጋፈጣቸው የማይቀር ሆኗል። በተለይም ላለፉት ሰባት ዓመታት የበለጠ ዝግጅት ሲደረግበት የቆየው የኦሊምፒክ ውድድር መራዘሙ ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ ማስከተሉ የአዘጋጆቹ ራስ ምታት እንደሚሆን ቀድሞም የታወቀ ነው። \nይህ ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ የጃፓን መንግሥትንም ይሁን ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴን በእጅጉ ሊፈትን እንደሚችል በባለሙያዎች አስተያየት ሲሰጥበት የቆየ ሲሆን ሁለቱ አካላት ኪሳራውን ለማካካስ እንደሚደጋገፉና ሌሎች ባለድርሻ አካላትም ለዚህ እንዲዘጋጁ ጥሪ ሲያቀርቡ ቆይተዋል። \nየዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እንዲህ ዓይነት ችግሮች ሲገጥሙት ትልቅ ተቋም እንደመሆኑ የመድህን ዋስትና እንዳለው ይታወቃል። አሁን የገጠመው ግን ካለው የመድህን ዋስትና አቅም በላይ በመሆኑ ነው እዚህ ችግር ውስጥ የተዘፈቀው። ስለዚህ የመድህን ዋስትናው በሕጉ መሠረት የሚሸፍነው ኪሳራ እንዳለ ሆኖ ተጨማሪ ኪሳራውን የሚያካክስበት አንድ ነገር መፈጠሩ የግድ ይሆናል። ይህንን ተጨማሪ ኪሳራ የጃፓን መንግሥት እንደሚሸፍን ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ ቀደም ሲል በተለያዩ አጋጣሚዎች መስማማታቸው ቢገለፅም አሁን የሃሳብ ለውጥ እንዳደረጉ የሚጠቁሙ መረጃዎች መውጣታቸውን ተከትሎ ውዝግቦች ተነስተዋል። \nየዓለም አቀፍ ኮሚቴው ፕሬዚዳንት ቶማስ ባኽ ሰሞኑን ከአንድ የጀርመን ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቃለምልልስ እንደጠቆሙት፣ ዓለም አቀፍ ኮሚቴው ከጃፓን መንግሥት ጋር በተስማማው መሠረት ለሚደርሰው በመቶ ሚሊዮን ዶላሮች የሚገመተውን ኪሳራ ለመሸፈን የራሱ ድርሻ አለው። ተጨማሪ የተባለውን ኪሳራ የመሸፈን ግዴታ ያለበት ደግሞ የጃፓን መንግሥት ነው። ይህን ስምምነት ሁለቱ አካላት እአአ 2013 ላይ እንዳደረጉ ቢገለፅም የጃፓን ካቢኔ አባላት ዋና ፀሐፊው ዮሺሂዴ ሱጋ ስምምነቱ እንዳልተደረገ አስተባብለዋል። \nይህንንም ተከትሎ በሁለቱ አካላት መካከል ውዝግብ የተፈጠረ ሲሆን ተጨማሪ የተባለው ኪሳራ እስከ ሦስት ቢሊዮን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል የጃፓኑ ክዮዶ ኒውስ ዘግቧል። የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ አዘጋጅ ቃል አቀባይ ማሳ ታካያ በበኩላቸው የጃፓን መንግሥት፣ የኦሊምፒኩ አዘጋጅ ኮሚቴና ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ውድድሩ በመራዘሙ ሊገጥሙ የሚችሉ እንቅፋቶችን በጋራ እንደሚወያዩና መፍትሄ እንደሚያስቀምጡ ተናግረዋል። \nኦሊምፒኩ በመራዘሙ ብቻ የጃፓን መንግሥትን ጨምሮ በርካታ ባለድርሻ አካላት ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ ውስጥ እንደሚገቡ ቀደም ሲል ተዘግቧል። የጃፓኑ ኦሊምፒክ አዘጋጅ ኮሚቴም ገና ከመጀመሪያው ከፍተኛ ኪሳራ ሊገጥም እንደሚችል መናገሩ ይታወሳል። ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ለዚህ ኪሳራ ስጋት ሰላሳ ሦስቱንም ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኖች የሚመለከት መድህን የገባ ቢሆንም በቂ እንደማይሆን ታምኖበታል። ፕሬዚዳንቱ ቶማስ ባኽም ኦሊምፒኩ መራዘሙን በገለፁበት ወቅት ከባድ ኪሳራ እንደሚኖር በማመን ሁሉም ባለድርሻ አካላት መስዋዕትነት መክፈል እንደሚጠበቅባቸው ለመጠቆም ሞክረዋል። ከባዱን መስዋዕትነት ማን እንደሚከፍልና ጫናው በየትኛው ወገን ትከሻ ላይ ሊወድቅ እንደሚችል ግን ከመጀመሪያውም ግልፅ አልነበረም። አሁን ላይ ገና ኦሊምፒኩ አስራ አምስት ወራት ገደማ እየቀሩትም ሁለቱ አካላት ውድድሩ በመራዘሙ የገጠማቸውን ውስብስብ ችግሮች ከመፍታት ይልቅ ከገንዘብ ጋር በተያያዘ ባለው ጉዳይ ላይ መነታረ ክ ጀምረዋል። \nየተለያዩ ተንታኞች እንደሚናገሩት ከሆነ የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በዓለም ላይ ሙሉ ለሙሉ እስከ ቀጣዩ ዓመት በቁጥጥር ስር ካልዋለ ኦሊምፒኩ በተራዘመበት 2021ም ላይካሄድ ይችላል። ከዚህም በዘለለ የመሰረዝ ዕድል ሊገጥመው ይችላል። ኦሊምፒኩ በመራዘሙ ብቻ በሚገጥመው ኪሳራ ትልቅ ውዝግብ የሚነሳ ከሆነ ከነጭራሹ ከተሰረዘ የሚገጥመው ኪሳራም በቀላሉ የሚሰላ እንደማይሆን ይታመናል። አዲስ ዘመን ሚያዝያ 17 / 2012 ቦጋለ አበበ", "passage_id": "c6132eb1ae8632b1cb425d11c6f98a83" }, { "passage": "የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ወራት ብቻ ለሚቀሩት የሪዮ ኦሊምፒክ በአፋጣኝ ወደ ስልጠና ለመግባት ሁኔታዎች እንደሚመቻቹ አመለከተ፡፡ ፌዴሬሽኑ በዝግጅቱ ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ምክክር አድርጓል፡፡ ጃፓን አስተናጋጅ የሆነችበት የቶኪዮ\n2020 ኦሊምፒክ ሊካሄዱ የቀሩት ከስድስት ወራት ያነሰ ጊዜ ብቻ ነው፡፡ በመሆኑም ካለፉት የሪዮ ኦሊምፒክና የዶሃው የዓለም አትሌቲክስ\nቻምፒዮና ተሞክሮ በመውሰድ ስልጠና እንዲታቀድና በአፋጣኝ ወደ ትግበራ እንዲገባ ሁኔታዎች እንዲመቻቹ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡ ለተግባራዊነቱም\nፌዴሬሽኑ ለሚያወጣው የምልመላና የስልጠና ዝግጅት ሚናውን እንደሚወጣ አስታውቋል፡፡ ለውድድሩ ታስበው የሚከናወኑ እንዲሁም ታቅደው\nየሚመሩና የሚፈጸሙ እንዲሆኑ ጥብቅ ክትትልና የድጋፍ ስርዓት ተዘርግቶ ችግሮች ሲያጋጥሙ በወቅቱ ተቀራርቦና ተረባርቦ መፍታት የሚያስችል\nቀልጣፋ ስርዓት እንዲዘረጋና እንዲተገበርም ፌዴሬሽኑ አሳስቧል፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከቶኪዮ\nኦሊምፒክ ጋር በተያያዘ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ትናንት ባደረገው የምክክር መድረክ ላይ ከኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን፣ ከኢትዮጵያ\nኦሊምፒክ ኮሚቴ፣ የክልልና ከተማ አስተዳደር ፌዴሬሽኖች፣ አንጋፋ አትሌቶችና የሙያ ማህበራት፣ ክለቦች፣ ማሰልጠኛ ተቋማት፣ አሰልጣኞች፣\nማናጀሮች እንዲሁም የማናጀር ተወካዮችና ሌሎችም ባለሙያዎች ተሳታፊ መሆናቸው ታውቋል፡፡ በውይይቱም ላይ አገሪቷ በተለይ በኦሊምፒክ\nውጤታማ በሆነችበት የአትሌቲክስ ስፖርት እንደተለመደው ውጤት በማስመዝገብና የአገርን መልካም ገጽታ በመገንባት ላይ ያጠነጠኑ ሃሳቦች\nተነስተዋል፡፡ የምልመላ፣ የስልጠና የአሰራር፣ ቅንጅት፣ ተግባቦት፣ ትብብር፣ ተፈጥሯዊና ንጹህ ውድድር ማድረግ እንዲሁም\nከግል ፍላጎት ይልቅ የአገርን ክብር ማስቀደም የሚሉ ሃሳቦችም ጎልተው ተንጸባርቀዋል፡፡ ትግበራውም በፌዴሬሽኑ መሪነትና አስተባባሪነት\nከባለ ድርሻ አካላት ጋር ተግባብቶና ተቀናጅቶ በመስራት ረገድ የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ የአቋም መግለጫ በማውጣት የምክክር\nመድረኩ ተጠናቋል፡፡ በአቋም መግለጫው የአትሌቶችና አሰልጣኞች ምላመላ በተሻሻለው የፌዴሬሽኑ የውስጥ አሰራር መመሪያ መሰረት\nግልጽ፣ ፍትሃዊና ተጠያቂነት የሰፈነበት እንዲሆንና ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እንዲከናወን ተጠቁሟል፡፡ አትሌቶች ዘመናዊና\nሳይንሳዊ ስልጠና ከመስጠት አንጻር የሚመረጡ አሰልጣኞች ወቅቱንና ሁኔታው የሚጠይቀውን የስልጠና ዕቅድ እንዲዘጋጅ፣ በአፈጻጸሙም\nላይ በተገቢው መንገድ ክትትል እንዲደረግበትና የማስተካከያ እርምጃዎችም በወቅቱ እንዲወሰዱ እንዲሁም የቶኪዮን የአየር ሁኔታን ያገናዘበ\nስልጠና እንደሚካሄድም ቃል ተገብቷል፡፡ ፌዴሬሽኑ ከኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጋር በመተባበር የገንዘብና የግብዓት አቅርቦት ወቅቱን ጠብቆ\nእንዲቀርብና በሥራ ላይ እንዲውልም ከስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡ ስለ አበረታች ቅመሞች ግንዛቤ ያለውና ንጹህ የሆነ አትሌት እንዲሁም\nበዓለም አቀፉ ጸረ አበረታች ቅመሞች ኤጀንሲ መመሪያ መሰረት ምርመራ ሂደቱን በአግባቡ የሚያልፉ አትሌቶች በመድረኩ እንደሚካፈሉም\nተረጋግቷል፡፡ ከዚህ ባሻገር ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለውጤታማነት እንደሚሰራም ተጠቁሟል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፣ አዲስ ዘመን ረቡዕ ጥር 27/2012 ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "2bd802a362001fb9b97203a341d7206b" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ መጋቢት 15፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ የ2020ቱን የቶኪዮ ኦሎምፒክ ውድድር በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ለአንድ ዓመት እንዲራዘም የቀረበውን ምክረ ሃሳብ መቀባሉ ተገልጿል። ", "passage_id": "af985e57b58d499356918c60d0f8bb43" }, { "passage": "ለአንድ አገር ስፖርት ውጤታማነት ማንሰራሪያና የትንሳኤ ማብሰሪያ መላና ምክንያት ከሆኑት ውስጥ በተለይ በዋና ከተሞች የሚካሄዱ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ተጠቃሾች ናቸው። የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን በአዲሱ ዓመት – የዓመታት ቁጭቴን በእርካታና በተስፋ ለመሙላት እንዲሁም ለስፖርቱ ትንሳኤ የምችለውን ለማከናወን ቆርጬ ተነስቻለሁ” ብሏል፡፡ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል ጋር ቆይታ ያደረጉት አቶ ዮናስ አረጋይም የኮሚሽኑን ተግባራትና መፃኢ ተስፋ አብራርተዋል፡፡ አዲስ ዘመን፡- የከተማ አስተዳደሩ\nበ2011 ዓ.ም በስፖርቱ ዘርፍ ካከናውናቸው ተግባራት መካከል እንደ ስኬት ያስመዘጋባቸው ምን ምን ጉዳዮች ነበሩ? አቶ ዮናስ፡- በስኬት ደረጃ ያስቀመጥናቸው አምስት ጉዳዮች ናቸው፡፡ የመጀመሪያው አጠቃላይ መዋቅሩን ከታች እስከ ላይ እንዲለወጥ\nአድርገነዋል፡፡ የማያስፈልጉ መዋቅሮችን አስነስተናል፡፡ የተሻሉ መዋቅሮችን ደግሞ ወደፊት እንዲሄዱ አድርገናል፡፡ ለምሳሌ፤ የማያስፈልገው\nአንዱ የኮንስትራክሽን ዘርፉ ነው፡፡ እሱን አንስተን ኮንስትራክሽን ቢሮ ይመለከተዋል ብለን ሰጥተነዋል፡፡ ስፖርት ኮሚሽኑ የማዘውተሪያ\nስፍራ ያስፈልገናል የሚል ጥያቄ ማቅረብ እንጂ፤ መሐንዲስ በሌለበት የማዘውተሪያ ግንባታ ማካሄድ አይደለም፡፡ ኮሚሽኑ በስፋት የስፖርት ከፍተኛ ባለሙያዎች አልነበሩትም፡፡ ስለዚህ\nከሚሽኑ በሚያስተዳድራቸው እንደ ራስ ኃይሉ፤ አበበ ቢቂላ፤ ጃንሜዳ፤ አራት ኪሎ ሥልጠና ማዕከላት ሁለት ሁለት ከፍተኛ ባለሙያዎች\nእንዲመደቡ አድርገናል፡፡ እነዚህ ማዕከላትም አብዛኞቹ ስፖርትንና የስፖርትን ሥራ ትኩረት አድርገው እንዲሰሩ ሆኗል፡፡ ይህም በተሻለ\nደረጃ ተተግብሯል፡፡ የማያሰሩ ማነቆዎች የተባሉትን በጠቅላላ በባለሙያ በተደገፈ ጥናት ፈትሸን ለማየት ጥረት አድርገናል፡፡ ከዚህ\nጋር ተያይዞ ለውጥ ባደረግንበት ልክ የሰው ሃይላችንን የመደልደል ሥራም ሠርተናል፡፡ የዚህ ውጤትም የስፖርት ኮሚሽን ከዚህ በፊት\nየነበረውን እንደ ልብ እንዳይሠራ ያደረገውን አሠራር ለማረምና አዲስ አበባ ያጣቸውን የስፖርት ማዕከልነቷን ለመመለስ ነው፡፡ ይህንን\nትኩረት አድርገን ስንሰራም በመዋቅሩ ዙሪያ ምን መደረግ አለበት ብለን ከፍተኛ ግምገማ አድርገናል፡፡ ሌላኛው፤ እንደ መንግሥትም ሊበራታታ የሚገባው ጉዳይ በቀደመው አደረጃጀት የወጣቶች ጉዳይና ስፖርት በጋራ የነበረ\nሲሆን፤ ስፖርት ራሱን ችሎ ይሂድ የሚል መዋቅር የመጣውም በዚህ ዓመት ነው፡፡ ሁለተኛው፤ የስኬት ተግባር የማዘውተሪያ ሥፍራን የተመለከተ ነው፡፡ ምንም እንኳን የአዲስ አበባን ጥያቄ በሚመጥን\nመልኩ ተመልሷል ባይባልም ትናንት የነበሩትንና ያደሩትን ውዝፍ ሥራች ግን ማገባደድ ችለናል፡፡ ለምሳሌ፤ የአበበ ቢቂላ ስታዲየም\nየረጅም ጊዜ የግንባታ ችግር ነበረበት፡፡ የማስፋፊያ ችግር ነበረበት፡፡ ከተማዋንም የሚመጥን አልነበረም፡፡ አሁን ግን ከተማዋን\nበሚመጥን መልኩ የወንበር፤ የትራክና የጣራ ሥራዎች ተጠናቅቀው አጠቃላይ ሥራው ወደ 95 በመቶ ያህል አልቋል፡፡ ከ105 ሚሊዮን\nብር በላይም ወጭ ተደርጎበታል፡፡ ከህዳሴ ግድብ እኩል የተጀመረው የሜዳ ቴኒስና የዓለም አቀፍ መዋኛ ገንዳውም በአጭር ጊዜ ውስጥ ቀንና ሌሊት\nእየተሠራ እንዲጠናቀቅ ተደርጓል፡፡ የቀረን ውሃ መሙላትና መሞኮር ብቻ ነው፡፡ ሁለቱም የመዋኛ ስፍራዎች፤ ማለትም የህፃናቱም የአዋቂውም\nተጠናቅቀዋል፡፡ ይህም ከ500 ሚሊዮን በላይ ወጭ ተደርጎበታል፡፡ ከዚህ በፊት የተጀመሩትን ሥራዎች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ ከማድረግ\nአኳያ በርካታ ሥራዎች የተሰሩበት ወቅት ነበር፡፡ እዚህ ላይ ሊታሰብ የሚገባው ቁምነገር ግዙፍ የሆኑ ሜጋ ፕሮጀክቶችን መሥራት አይደለም\nትልቁ ነገር፤ ዋናው ነገር ተደራሽ በሆነ ሁኔታ አነስ አነስ ያሉ ማዘውተሪያ ቦታዎችን መሥራት ነው የሚያዋጣው፤ በመሆኑም፤ በ2012\nዓ.ም የምንሰራቸው እንዳሉ ሆነው በአፈጣኝ ግን በ117ቱም ወረዳዎች የጥርጊያ ሜዳ መሥራት አለብን ብለን ተነስተን 61 ቦታዎች\nተሳክተውልናል፡፡ አዲስ አበባ የነበራትን ነባር ሜዳ በማጣት ነው እንጂ የምናሳልፈው አዲስ ሜዳዎች ሲጨመሩ ብዙም የተለመደ አልነበረም።\nይህ በሁለተኛው የዕቅድና ትራንስፎርሜሽን ዘመን ያልሠራነውን ነው በዚህ ዓመት ማሳካት የቻልነው፡፡ ከዚህ ውጭ 63 ቦታዎች የይዞታ\nማረጋገጫ ካርታም አስወጥተናል፡፡ አንዳንዱ ቦታ ካርታ ስለሌለው ማንም ባዶ ቦታ ሲያይ መጥቶ ይገነባል፡፡ ይህ እንዲቀርም ተደርጓል፡፡\nሦስተኛው፤ የታዳጊዎችን ፕሮጀክቶች ከአዲስ አበባና\nከኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በዝርዝር እንዲገመገሙ አድርገናል፡ ፡ ገልለተኛ አካላቱ ፕሮጀክቱን ሲያጠኑ እስከዛሬ\nበነበረው አሠራራችን ላይ ችግር እንደነበር አመላክተዋል፡፡ በእርግጥ የተወሰኑ ፕሮጀክቶች የተሻሉ መሆናቸውም ታይቷል፡፡ በድምር\nውጤቱ ግን በአዲስ መንገድ መሄድ እንዳለብን ያመላከቱ ናቸው፡፡ ወደ 132 የሚሆኑ ጣቢያዎች ላይ በነበሩ እንቅስቃሴዎች ከአራት\nሺህ አምስት መቶ  በላይ ልጆች የታቀፉበት ሥራ ግን በስኬት\nየሚታይ ነው፡፡ እነዚህም አጠናክረን እንቀጥላለን፡፡ ስለዚህ ታዳጊዎች ላይ በአዲስ ዓመት አዲስ ሐሳቦች ተግባራዊ ይደረጋሉ፡፡\nበተመረጡ ቦታዎች ላይ ብቻ ለመስራት ነው ዕቅድ የተያዘው፤ በዚህ ዓመት በዘጠኝ የስፖርት ዓይነቶች እስከ ሦስት ዓመት ድረስ ካልሰራን\nመወዳደሩ አይጠቅምም የሚል አቋም ላይ ነን፡፡ በነገራችን ላይ፤ አዲስ አበባ ላለፉት ስድስት ዓመታት ከስፖርት ማዕከልነቷ ወጥታ\nበአገር አቀፍ ውድድሮች ስድስተኛና ሰባተኛ ደረጃ ነበር ይዛ የምታጠናቅቀው፤ ስህተታችንን ስላወቅን በትክክል በሰራነው ላይ ብቻ\nበመሳተፍ ያልሰራነውን በመተው ጥራት ላይ ት ኩረት ማድረግ ጀምረናል፡፡ በአራተኛ ደረጃ፤ ለአጠቃላይ ባለሙያዎች ሠፋፊ ዓለም አቀፍ ይዘታቸውን\nየጠበቁ ሥልጠናዎች ተሰጥተዋል፡፡ የመጨረሻና ትልቁ ሥራ ደግሞ የማስ ስፖርትን የማጠናከሩ ተግባር ነው፡፡ ስፖርት መሰረቱ ማስ ስፖርት\nነው። ይህም በኢትዮጵያ የስፖርት ፖሊሲ ላይ በግልጽ ተቀምጧል፡፡ ማስ ስፖርት ባህል ሆኖ እንዲቀጥልም የተሻለ ሥራ ተሠርቷል፡፡\nአዲስ ዘመን፡- እነዚህን\nስኬታማ ተግባራት ስታከናውኑ ምንም ሳንካ አልነበረም ማለት ነው? አቶ ዮናስ፡- ቀላል የማይባሉ ችግሮች ነበሩብን፡፡ መዋቅር ሲስተካከል በክፍለ ከተማ ላይ በስፖርት የሰለጠኑ ብቻ ናቸው የስፖርት\nዘርፍ ዳይሬክተር መሆን ያለባቸው ስንል በማኔጅመንትና በኢኮኖሚክስ የጨረሱ ነበሩ የተመደቡት፤ ይህንን ለማስተካከል ችግር ፈጥሮ\nነበር፡፡ በሌላ በኩል፤ ታዳጊዎች ላይ አሁንም ቀላል የማይባሉ ማነቆዎች አሉ፡፡ ለምሳሌ፦ አንዱ ችግር የእድሜ ማጭበርበር ነው፡፡\nአሾልኮ የሚያስገባውም የሚገባውም ትስስር ያላቸው ናቸው፡፡ ልምምድ በአግባቡ ያለመስራት፤ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በተሻለ ፍጥነት\nየፍፃሜ ሥራዎችን አለማከናወን፣ በቢሮ በኩል ደግሞ ትጥቅ አለማድረስ፤ አበልና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞችን ማዘግየት፤ እልፍ ሲል ደግሞ\nየጥራት ጉድለቶችም እንዳሉ አስተውለናል፡፡ በፈፃሚዎች መካከል ያሉ ድክመቶችም ተስተውለዋል፡፡ ከዚህ ውጭ አዲስ አበባ ላይ የማዘውተሪያ\nሥፍራ ችግር ቀላል አይደለም፡፡ በተለይ በልማት ምክንያት ተነሽ በሆኑ አካባቢዎች አንድ ስንዝር መሬት እንኳን ማግኘት ችግር ነበር፡፡\nማስ ስፖርቱን ቁልፍ ጉዳይ አድርጎ አለመግምገም እንዲሁ እንደ ክፍተት የሚታይ ነው፡፡ እንደ ካርኒቫልና ፌስቲቫል ከማየት በዘለለ\nበእያንዳንዱ ወረዳ ላይ እንዲተገበር በማድረግ ረገድ ችግር አለ፡፡ የመጨረሻው አንዱ ችግር የአዲስ አበባ ስታዲየም ጉዳይ ነው፡፡ እንደሚታወቀው ሁሉም ክልሎች ስታዲየም አላቸው፡፡\nበፌዴራል የሚተዳደር ስታዲየም የላቸውም፡፡ የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን መሥራት ያለበት በስትራቴጂክ ጉዳዮች ላይ ነው እንጂ ክልሎች\nበሚሰሩት ጉዳዮች ላይ መካተቱ ስፖርቱን ያዳክመዋል የሚል እምነት ነው ያለኝ፤ እኛም የአዲስ አበባ ስታዲየም ሜዳው ይሰጠን ብለን\nአመልክተናል፡፡ ይህንን እየጠበቅን ነው፡፡ በተለይ በስታዲየሙ ዙሪያ ያለው የአልኮል መጠጥ ንግድ ቤቶች በስፖርቱ ላይ ከፍተኛ ማነቆ\nእንዲፈጠር አድርገዋል፡፡ በመሆኑም ስታዲየሙን ተረክበን አልምተን ለከተማዋ ማህበረሰብ አገልግሎት እንዲሰጥ እናደርጋለን፡፡ ይህ\nሲሆን ደግሞ የሚገጥመውን የፋይናንስ ችግር ለመቅረፍ ያግዛል፡፡ አዲስ ዘመን፡- ወርሐዊው\nየማስ ስፖርት ተሳትፎ ለፖለቲካ ፍጆታ እንጂ ስፖርታዊ መሠረት የለውም የሚሉ አካላት አሉ። አርስዎ በዚህ ጉዳይ ላይ ምን ይላሉ?\nስፖርታዊ ክንዋኔውስ ከታለመለት ዓላማ አንፃር ምን ያህል ውጤታማ ነበር? አቶ ዮናስ፡- በመሰረቱ ስፖርት ከዘር፤ ከሃይማኖትና ከፖለቲካ የፀዳ ነው፡፡ የኦሊምፒክ ውድድሮችን ብዙ ጊዜ በከተማችን ውስጥ\nስናካሄድ ቆይተናል፡፡ ስፖርትን የሚያጠናክረው ሠላም ነው፤ የሚያፈርሰውም የሰላም እጦት ነው። አገራችን ውስጥ በሚፈጠር ችግር የስፖርቱ\nቤተሰብ ለሰላሙ አቅም ካልሆነ ስፖርት ምንም አይጠቅመንም፡፡ ስፖርት ለአገራችን አንድነትና ፍቅር ጠንካራ የሆነ መሠረት መፍጠሪያ\nነው፡፡ ኦሊምፒክን የመሰረተው እኮ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት የፈጠራቸው ችግሮች ናቸው፡፡ በነገራችን ላይ ኦሊምፒክ ውድድር አይደለም።\nአሁን አሁን የውድድር መልክ ያዘ እንጂ አንድነትና ፍቅር የሚገለፅበት መድረክ ነበር፡፡ ስለዚህ የማስ ስፖርቱ በህዝባችን ውስጥ\nእንዲሰርፅ ማድረግ አንድነትን ማጠናከሪያ እንጂ በሌላ እይታ የሚታይ አይደለም፡፡ ስፖርቱ ያቀራርባል እንጂ የፖለቲካ ተልዕኮ አይደለም፡፡\nበአሁን ወቅት በስፖርት ቤት የገባው አንዱ ነገር ዘረኝነት ነው፡፡ ለዚህ ነው “ዘረኝነት ይብቃ” የሚል መሪ\nቃል/ሞቶ እየተጠቀምን ያለነው፤ ስፖርት የፖለቲካው ትኩሳት ጥሩ ሲሆን ጥሩ የምንሆንበት፤ መጥፎ ሲሆን መጥፎ የምንሆንበት አካሄድ\nአይደለም፡፡ ፖለቲካው ጥሩም ሳይሆን ወደ ሠለም መመለሻ አቅም መሆን አለበት፡፡ ስፖርት ሠላም ነው ካልን ሰላም የሚያደፈርሱ ሃይሎችንም\nከእኩይ ተግባራቸው የሚያወጣ ነው፡፡ ትኩሳትን የሚያበርድ እንጂ ለመንግሥትና ለህዝብ ራስ ምታት መሆን የለበትም፡፡ ከዚህ አንፃር፤ ምንም የፖለቲካ አጀንዳ የለውም። የፖለቲካ አመራሮች በማስ ስፖርት ላይ ተገኙ ማለት አጀንዳው\nፖለቲካ ነው ማለት አይደለም። መቀራረብና መፈቃቀር ግን አጀንዳው ነው፡፡ ሁሉም ተጋግዘው ነው እየሠሩ ያሉት፤ የሚተላለፈው መልዕክት\nእንዴት መሥራት እንዳለብን የሚጠቁም ነው፡፡ የስፖርት ቤተሰቡም የመገኘትም ያለመገኘትም መብት አለው፡፡ የማስ ስፖርት መርሐ ግብር ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ዓላማውን እያሳካ ነው፡፡ በማህበረሰቡ ዘንድ\nመቀራረብ ፈጥሯል፡፡ ሰዎች በጉጉት እንዲጠብቁት ሆኗል፡፡ የተሳታፊዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል። ከጤና አኳያም ብዙ\nሰው ባህል አድርጎት እየተሳተፈበት ነው፡፡ የማስ ስፖርት ከጀመርን በኋላ 21 ወረዳዎች በተጠናከረ መልኩ እየሠሩ ይገኛሉ፡፡ አዲስ ዘመን፡- በመዋቅር ለውጡ ስፖርት ኮሚሽን ራሱን ችሎ\nእንዲቆም ቢደረግም ተጠሪነቱ ግን ለወጣቶችና በጎ ፈቃድ ማስተባሪያ ቢሮ መሆኑ አሉታዊ ተጽዕኖ አይኖረውም? አቶ ዮናስ፡- ክልሎች የተለያየ አደረጃጀት ይኖራቸዋል፡፡ አዲስ አበባ ላይ አሁን ባለው ሁኔታ ለስፖርቱ ትልቅ ትኩረት ከተሰጠው\nተጠሪነቱ ለከንቲባው መሆን አለበት የሚል እምነት አለኝ። ይህንንም ምክትል ከንቲባው በተገኙበት በዓመታዊ ግምገማ ላይ ተናግሬያለሁ፡፡\nአሁንም ራሱን ችሎ እየሄደ ነው ለማለት ግን የሚጎድለን ነገር የለም፡፡ ቡድን መሪ፣ ዳይሬክተሮችና አመራሩ ነው ወሳኙ፡፡ ሥራውን\nአጠናቅቆ የመሥራት አቅም ካለ የተጠሪነቱ ጉዳይ አያሳስብም፡፡ ስለዚህ በአሁኑ ወቅት ራሱን የቻለ ተቋም ነው ብለን እየመራን ነው፡፡\nከድጋፍ ጋር በተያያዘ ግን ከከንቲባው ጽህፈት ቤት ጋር መሠራት አለበት የሚል አቋም ነው ያለኝ፤ ይህም የሚወሰነው እንደ አመራር\nሚና ይሆናል ብዬ አስባለሁ፡፡ አዲስ ዘመን፡- ኮሚሽኑ በአዲሱ\nዓመት በዋናነት ምን ምን ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ ሊሠራ አቀደ? አቶ ዮናስ፡- ከሚሽኑ የራሱ ስትራቴጂክ ዕቅድ አለው፡፡ ዋና ፍኖተ ካርታውም መነሻው ከዚህ ነው። የስትራቴጂክ ዕቅዱ ዋና\nራዕይ “አዲስ አበባ ላይ ያለው ትውልድ በተክለ ሰውነትም ሆነ በአዕምሮው የዳበረ፤ በአስተሳሰቡ የተሻለ ጠንካራ ዜጋ በስፖርት ዘርፉ\nመገንባት” ነው፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን ደግሞ በአገራዊ ጥሪዎች ላይ ከዓለም የጎላ ተወዳዳሪነት መንፈስን ተግባራዊ ማድረግ ነው፡፡\nበዚህ አዲስ ዓመት የጥርጊያ ሜዳዎቻችንን ማስፋፋት፣ ጥርጊያ ሆነው የተሰሩትን ደግሞ ወደ ሣር ማሸጋገርና ወጣቶችን\nአደራጅተን የተሻለ ሥራ ለመሥራት አቅደናል፡፡ 32 ሦስት በአንድ የሆኑ ሜዳዎችን መስራትም አንዱ ዕቅድ ነው። የተጀመሩትን ፕሮጀክቶች\nሙሉ ለሙሉ እንዲጠናቀቁ ማድረግም ሌላኛው ሥራ ነው፡፡ ሌለኛው ደግሞ የተለዩ የማዘውተሪያ ሥፍራዎችን የመረከብና የማከል ሥራ ነው፡፡\nየማስ ስፖርቱን በተጠናከረ መልኩ በማስቀጠል በሁሉም ወረዳ ተግባራዊ ማድረግ የኮሚሽኑ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ\nነው፡፡ የታዳጊ ፕሮጀክቶችን በተመረጡ ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች ላይ በሚታይና በሚቆጠር ሥራ ላይ ትኩረት እናደርጋለን፡፡ ለዚህም\nለትምህርት ቤቶች በር እንከፍታለን፡፡ ዋናው ነገር በተመረጡ ስፖርቶች ብቻ ውድድር እያደረግን በአዲሱ ዓመት አዲስ አበባ የስፖርት\nማዕከልነቷን እንድትመልስ ማድረግ ነው፡፡ ለዚህም የስፖርቱን ቤተሰብ አቅም ከመገንባት አኳያም የተጀመሩትን ተግባራት እናስቀጥላለን፡፡\nአዲስ ዘመን፡- የከተማ አስተዳሩ በስፖርቱ ዘርፍ ከሌሎች ዓለም\nአቀፍ እህት ከተሞች ጋር ተሞክሮ የመቅሰም ልምድ ካለው ቢጠቅሱልኝ፤ አቶ ዮናስ፡- እስካሁን አለነበረም፡፡ ከአሁን በኋላ ለመጀመር ግን ከተለያዩ አገራት አምባሳደሮች ጋር ተናጋግረናል፡፡\nየአርጀንቲና፣ የጃፓን፣ የፈረንሳይና የኮሪያ ተጠቃሾች ናቸው። ስለዚህ በ2012 ዓ.ም ከእህት ከተሞች ጋር በከተማ አስተዳደሩ አማካኝነት\nትስስር ፈጥረን በማስ ስፖርትና በታዳጊዎች ላይ እንሠራለን፡፡ ከሚበልጡን ለማማር ዕቅድ ይዘናል፡፡ አዲስ ዘመን፡- አዲስ አበባ የአገሪቷ ርዕሰ መዲና ሆና ሳለች\nዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ስታዲየም ማጣቷ ለምንድነው? ወደፊትስ ምን ታስቧል? አቶ ዮናስ፡- ስታንዳርዱ በምን ደረጃ ነው መሆን ያለበት የሚለው ነገር እንዳለ ሆኖ፤ በአጠቃላይ ግን ባዳ መሆናችንን\nያሳያል፡፡ ምክንያቱም “የአዲስ አበባ ስታዲየም ለምንድነው ደረጃውን ያላሟላው?” የሚለውን ነገር አናውቀውም፡፡ ከሚመለከታቸው አካላት\nጋር አብረን ሆነን በምክክር እንዳንሠራ ችግር አለ፡፡ በግብረ መልሶች ላይ ከኮሚሽነሮች ጋር ተቀምጠን አልተወያየንም፡፡ ነግር ግን፤\nበዚህ ዙሪያ በርከታ ሥራ መሥራት እንዳለብን እረዳለሁ፡፡ ችግሩ እንዳይደገምም እየሠራን ነው፡፡ አዲስ ዘመን፡- የባህል ስፖርቶችን በከተማዋ እንዲስፋፉ ለማድረግስ\nምን እየተሠራ ነው? አቶ ዮናስ፡- በቅርቡ አምቦ ላይ በተደረገው የባህል ስፖርት ውድድሮች በከተማ ደረጃ የተሻለ አፈፃፀም ታይቷል፡፡\nበቀጣይም ከባህልና ቱሪዝም ጋር በመተባበር ሥልጠና እንዲሰጥና የባህል ስፖርቱን አጠናክረን መሄድ እንዳለብን ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡\nበአዲሱ ዓመት ከምንሠራቸው ተግባራትም አንዱ ትውልዱ አገሩን እንዲወድ በባህል ስፖርት ላይ ትኩረት ማድረግ ነው፡፡ ነባር የሆኑ\nየባህል ስፖርቶች እንዳይጠፉ ግን በከተማዋ ላይ በርካታ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ነው፡፡ አዲስ ዘመን፡- ለሰጡኝ ሰፊ ማብራሪያ አመሰግናለሁ! አቶ ዮናስ፡- እኔም በጣም አመሰግናለሁ!አዲስ ዘመን መስከረም 2/2011አዲሱ ገረመው ", "passage_id": "a9110a474f2eb59073e6aad97829a75a" }, { "passage": "የአፍሪካ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማኅበር (አኖካ) እ.ኤ.አ. በ 2022 ሌሴቶ እንድታስተናግድ ተወስኖ የነበረውን አራተኛውን የአፍሪካ ወጣቶች ውድድር ከሀገሪቱ ነጥቆ ወደ ኢትዮጵያ አዛውሯል፡፡\nሌሴቶ ለውድድሩ በቂ ዝግጅት እያደረገች ባለመሆኑ ውድድሩ ከማሴሩ ወደ አዲስ አበባ መዛወሩን ማህበሩ ስለማሳወቁ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የቶኪዮ ኦሊምፒክ ብሔራዊ ዝግጅት አባል አራያት ራያ ለአል ዐይን እንዳረጋገጡት ኢትዮጵያ ውድድሩን እንድታስተናግድ የተመረጠች ሲሆን ከአፍሪካ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማኅበር ጋር በወጪ መጋራት እና መሰል ጉዳዮች ላይ ውይይት እየተደረገ ነው፡፡\n“የ 2022 የአፍሪካ ወጣቶች ጨዋታዎች ለኢትዮጵያ አዲስ አበባ ከተማ ተሰጥቷል፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት ይህንን ዝግጅት በጥሩ ሁኔታ ለማስተናገድ ቁርጠኛ ነው” ሲል አኖካ በመግለጫው ይፋ አድርጓል፡፡\nውድድሩን እንድታስተናግድ በ2018 ዕድሉ ተሰጥቷት የነበረችው ሌሴቶ በኢኮኖሚ ችግር ምክንያት ላለፉት 2 ዓመታት ምንም ዝግጅት ሳታደርግ ስለመቆየቷ ነው ማኅበሩ የገለጸው፡፡\nከሁለት ዓመታት በኋላ የሚካሔደውን 4ኛውን የወጣቶች ውድድር የተነጠቀችው ሌሴቶ በምትኩ በቂ ዝግጅት በማድረግ ከአራት ዓመታት በኋላ በ2026 የሚካሔደውን 5ኛውን የአፍሪካ ወጣቶች ጨዋታዎች እንድታስተናግድ ተወስኗል፡፡\nየአፍሪካ ወጣቶች ጨዋታዎች የመላው አፍሪካ ጨዋታዎችን በመተካት በየአራት ዓመቱ በተለያዩ የስፖርት አይነቶች የሚካሔድ ውድድር ሲሆን ከዚህ ቀደም የተካሔዱትን 3 ውድድሮች ሞሮካ ፣ ቦትስዋና እና አልጄሪያ በቅደም ተከተል አስተናግደዋል፡፡\nኢትዮጵያ ከሁለት ወራት በኋላ በአውሮፓውያኑ ታህሳስ 6 የአፍሪካ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማኅበር ጉባዔን እንደምታስተናግድም ከአል ዐይን ጋር ቆይታ ያደረጉት በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የቶኪዮ ኦሊምፒክ ብሔራዊ ዝግጅት አባል አራያት ራያ ተናግረዋል፡፡ ለዚህም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ ነው የገለጹት፡፡\n", "passage_id": "71ae6a3bf08411890767101849fdbfbd" } ]
011166bfa21097cce9355a345d96d1ab
3b9c93b94fd66f9cc1b902020a88e47d
‹‹ሃገራዊ ችግሮችን ለማረምና አብሮነትን ለማጠናከር ስፖርት ወሳኝ ነው››- አቶ ደመቀ መኮንን የብሄራዊ ስፖርት ምክር ቤት ሰብሳቢ
 ብርሃን ፈይሳ አዲስ አበባ፡- እንደ ሃገር እየታዩ ያሉትን ስብራቶችና ችግሮች ለማረምና የአብሮነትን ጉዞ ለማጠናከር ስፖርት ወሳኝ ሚና አለው ሲሉ የብሄራዊ ስፖርት ምክር ቤት ሰብሳቢ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን አስታወቁ። ለስፖርቱ ዘርፍ ተገቢው ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተጠቆመ። የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር የውጪ ጉዳይ ሚኒስትርና የብሄራዊ ስፖርት ምክር ቤት ሰብሳቢ ደመቀ መኮንን ትናንት የብሄራዊ ስፖርት ምክር ቤት የመጀመሪያ መደበኛ ጉባኤ በተካሄደበት ወቅት እንዳስታወቁት፤ ስፖርት የሰላምና የአብሮነት መሰረት፤ ሰላም ደግሞ ለስፖርት ሁነኛ ነባራዊ ሁኔታ ነው። በመሆኑም እንደ ሃገር ያሉትን ስብራቶችና በተለያየ መልክ የሚታዩ ችግሮችን ለማረምና የአብሮነት ጉዞን ለማጠናከር ስፖርት ወሳኝ ነው። አሁን ባለው ሃገራዊ ሁኔታ በጣም ብዙ ስብራቶች መኖራቸውን የምክር ቤቱ ሰብሳቢ ጠቅሰው፣ እነዚህን ከመጠገንና አብሮነትን ከማጠናከር አኳያ ስፖርት ሁነኛ መስተጋብር መሆኑን አመልክተዋል። የስፖርቱ መርሆዎች በአንድም ሆነ በሌላ መልክ በአስር ዓመት ሃገራዊ ዕቅድ መሪ ሃሳብ ውስጥ የተንጸባረቁ መሆናቸውን ተናግረው፣ ከየትኛውም ተቋም በላይ ሃገሪቷ በመጪዎቹ ዓመታት በሚሰራው ስራ አፍሪካዊ የብልጽግና ተምሳሌት ትሆናለች የሚል መሪ ሃሳብ ተይዟል ብለዋል። በዚህ ጭብጥ ውስጥም ዋና ዋና የስፖርት መርሆዎች ይገኛሉ ያሉት የምክር ቤት ሰብሳቢው፣ ‹‹የስፖርት መርሆዎች ከብልጽግና እንዲሁም የስፖርት መርሆዎች ከአብሮነት አኳያ፣ የስፖርት መርሆዎች በወንድማማችነት፣ በወዳጅነት፣ ጤናማ ማህበረሰብን በመፍጠር አብሮነትን የሚያስተሳስሩ እሴቶችን የተላበሱ ናቸው። በመሆኑም ለእዚህ ኢንዱስትሪ ትኩረት መስጠትና ማጠናከር ለራሳችንና ለሃገራችን ስንል ትውልዱ የሚታወቅባቸውን ስፖርቶች ለማስቀጠል ኃላፊነትና አደራም አለብን። የበለጠ ሆኖ ለመገኘት ስንልም በጣም መሰረታዊውንና ስፖርትን ከዚህ አኳያ ትርጉሙን ከፍ አድርጎ መመልከት ያሻል›› ሲሉም  አብራርተዋል። ስፖርት ተገቢው ትኩረት ሊሰጠው ይገባል የሚለው በምክር ቤቱ የተለመደ አባባል መሆኑን ጠቅሰው፣ ወደ ተግባር ተሟልቶ እስካልተገባ ድረስ አጉልቶ መያዝ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ‹‹ታላላቅና የኩራታችን ምንጭ የሆኑ ስፖርተኞች በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና እያስገኙ በመጡበት ሂደት አሁን ላይ ሆነን ሌጋሲውን እንዴት ማስቀጠል እንችላለን፤ ስፖርትስ እንዴት በሃገሪቷ ብልጽግና ጉዞ ውስጥ ሁነኛ ቦታ ይዞ ይሄዳል በሚለው ላይ ኃላፊነት አለብን›› ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፣ ስፖርት በተወሰኑ አካላት ብቻ የሚታጠር መሆን እንደሌለበትም አስገንዝበዋል። ከታዳጊ ህጻናት እስከ ብሄራዊ እንዲሁም ዓለም አቀፍ ድረስ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚገባም ሰብሳቢው አመላክተዋል።በብዙ ትውልዶችና በጀግኖች ጥረት ስፖርቱ ዓለም አቀፋዊ ሆኗል፤ እነዚህ ጀግኖችም ሃገራቸውንም አስተዋውቀዋል፤ አሁንም በብዙ መልኩ ስፖርቱ ዓለም አቀፋዊ መሆን ይኖርበታል፤ ለዚህ ደግሞ ምቹ ሁኔታ ያስፈልጋል፤ በተለይ በታዳጊ ህጻናት ላይ ከተሰራ መጪው ዘመን በስፖርት ያለውን አቅም ወደ ውጤት መመንዘር ያስችላል ብለዋል።አዲስ ዘመን ታኅሳስ 21/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=38512
[ { "passage": "አዲስ አበባ፡-ወጣቱ የአድዋ ድል ለአገ ራዊ አንድነት የማያልቅ ስንቅ መሆኑን በመገንዘብ  የአባቶቹን \nለአገራዊ አንድነት በጋራ የመቆም  እሴትን ጠብቆ መራመድ እንዳለበት ምሁራን\nገለጹ፡፡በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ ጥናትና\nምርምር ተቋም ዋና ዳይሬክተርና የታሪክ ተመራማሪው ዶክተር አህመድ ሀሰን \nእንደገለጹት፣ ከወታደራዊ ድል ባሻገር አገራዊም ሆነ ታሪካዊ እሳቤው ትልቅ ነው፡፡ዘላለማዊ ነጻነት፣ኢትዮጵያዊ አንድነት\nበማጠናከር በኩል ጉልህ ሚና አበርክቷል፡፡ወጣቱ አያቶቼና ቅድመ አያቶቼ በአንድነት\nታግለው የውጭ ወራሪውን ድል መንሳታቸውን የገለጹት ዶክተር አህመድ፣ የአድዋን ድል ታሪካዊ አሻራውን ጠብቆ እንዲሄድ መንግስት የህዝብ\nለህዝብ ግንኙነትን ማጠናከር፣የወጣቱን መልካም ሰብዕናን መገንባት፣ታታሪ መሆንና አገራዊ አንድነትን ማላበስ ይገባል፡፡በሀረማያ ዩኒቨርስቲ  የታሪክ ምሁሩ ዶክተር መሀመድ አሊ የአድዋ ድል የፖለቲካ አመለካከት፣የሀይማኖትና\nየብሄር ልዩነቶችን ወደ ጎን ትተው አንድ የምታደርገቸውን አገር ኢትዮጵያን ብለው የዘመቱበት ነው፡፡ድሉም የአገራዊ አንድነት ትልቁ\nማሳያ በመሆኑ አሁን ያለው ትውልድ በድል በዓሉን ከማክበር በተጓዳኝ አንድነቱን ጠብቆ የጋራ ጠላታችን በሆነው ድህነት ላይ በጠንካራ\nየስራ መንፈስ መዝመት አለበት ብለዋል፡፡በአገሪቱ ብዙ ችግር ሲያጋጥም እንኳ ኢትዮጵያዊነት\nበጠንካራ መሰረት የተገነባ በመሆኑ ኢትዮጵያ ፈተናዎችን አልፋለች ያሉት ምሁሩ፣ ይህም የህዝቦች  መስተጋብር የማይበጠስ መሆኑን ያሳያል፡፡በቀጣይም ህዝቦች የሚከባበሩበትና\nየሚፈቃቀሩበት ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ከመገንባት አኳያ ሁሉም ዜጋ የድርሻውን መወጣት ይኖርበታል፡፡የአሁኑ ትውልድ ከአባቶቹ የተረከበውን\nለውጭ ሃይል የማይደፈር ጠንካራ አገር ለመጪው ትውልድ ጠብቆና አበልጽጎ ማስተላለፍ ይጠበቅበታል ሲሉ ተናግረዋል፡፡በአክሱም ዩኒቨርስቲ የታሪክና ቅርስ አስተዳደር\nመምህር አቶ ግርማይ ሀላፎም፣  የአድዋ ድል ለኢትዮጵያ አገራዊ አንድነት\nየጎላ አስተዋጸኦ  እንዳለው አውስተው፣ ጀግኞች አባቶቻች ከደቡብ፣ከምስራቅ፣ከሰሜን፣ከምዕራብና\nከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ልዩነታቸውን በመተው ለአገር ሉዓላዊነት በአንድነት የተሰለፉበት የጦር ግንባር ነው፡፡የአድዋ ድል ለኢትዮጵያዊያን\nብሄራዊ መግባባትና አገራዊ አንድነት አንዱ  ስንቅ ነው ሲሉ አመልክተዋል፡፡‹‹ የአድዋ ድል አባቶቻችን የተራቀቀ ቴክኖሎጂ\n፣ትራንስፖርት፣መረጃና መሳሪያ ሳይኖር ከሀረር ፣ከሶማሌ ፣ከሞያሌ፤ከወለጋ፣ ከጅማና ከሁሉም የአገሪቱ ክፍል ሳይቀር ረጅም ኪሎ ሜትር\nበእግራቸው ተጉዘው ከወራሪ ሀይል ጋር ጦርነት በመግጠም ድል የነሱበት \nመሆኑን ገልጸው ድሉም የዓላማ ፅናታቸውን፣ ቁርጠኝነታቸውን፣ አንድነታቸውንና የአገር ፍቅር ስሜታቸውን  በተግባር ያረጋገጡበት ነው፡፡ የአሁኑ ትውልድም ከአባቶቹ በመማር  በተሰማራበት መስክ ሁሉ ለአገሩ ብልፅግና መትጋት ይኖርበታል ሲሉ መክረዋል፡፡የአድዋ ድል ለኢትዮጵያ አንድነት ስንቅ ብቻ\nሳይሆን በቅኝ ግዛት ለነበሩ ሀገሮች   የነጻነት ተምሳሌት ነው ያሉት\nምሁሩ፣ጦርነቱ የተካሄደው ለእኩልነት፤ ለፍትህ፣ ለሉዓላዊነትና ለነጻነት በመሆኑ አገራዊ አንድነትን ማምጣቱ እንደ ተጠበቀ ሆኖ ለአፍሪካ\nአንድነትም የበኩሉን ሚና ተጫውቷል ፡፡ወጣቱም የአድዋ ድል ታሪኩን አውቆና አጥንቶ ለመጪው ትውልድ የማስተላለፍና የኢትዮጵያ አንድነትና\nብልጽግን አረጋግጦ በመሄድ የራሱን ታሪክ አሻራ ማስቀመጥ ይኖርበታል ብለዋል፡፡የዛሬ 123 ዓመታት በፊት በአድዋ ጦርነት\nጊዜ  ከንጉሱ ጋር የተጣሉና  ያኮረፉ የኢትዮጵያ ህዝቦች ሳይቀር ለሀገር ልዕልና አንድነት በጋራ ዘምተው\nወራሪውን የውጭ ኃይል ድል አድርገዋል። አዲስ ዘመን ቅዳሜ የካቲት 23/2011", "passage_id": "3d82d5ef93f855f7d5e9f5e51db08b91" }, { "passage": "በ1990 ዓ.ም. በአገር አቀፍ ደረጃ የወጣው የስፖርት ፖሊሲ ሕዝቡ በሚኖርበት፣ በሚማርበትና በሚሰራበት አካባቢ ስፖርት እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚገባው ይደነግጋል። ህብረተሰቡ በሚኖርበት፣ በሚማርበትና በሚሠራበት አካባቢ በስፖርት እንቅስቃሴ ተሳታፊ የሚሆንበት መንገድ መመቻቸት እንዳለበት ያስቀምጣል። ከመንግሥት ተቋማት እስከ ታችኛው የኅብረተሰብ ክፍል በየደረጃው ኅብረተሰቡ ለሚሳተፍባቸው መድረኮች ትኩረት በማድረግ ልሂቃን (ኤሊቶች) የሚፈጠሩበት ዕድል እንዳለም ፖሊስው ያመለክታል። በሌላ በኩል አምራች ዜጋ ለመፍጠር፣ የኅብረተሰቡ ማኅበራዊ ግንኙነት የሚዳብርበት፣ ከዚያም ሲያልፍ ዜጎች ጤንነታቸውን ለመጠበቅና ለመዝናናት እንዲሁም አካላቸውን ለማጎልበትና አዕምሯዋቸውን ለማበልጸግ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ታምኖበታል። የስፖርት ፖሊሲውን መሰረት በማድረግ የሕብረተሰቡን ተሳትፎ በማስፋት ረገድ እየተሄደበት ያለው መንገድ አጥጋቢ አለመሆኑ ተደጋግሞ ይነሳል። በመንግስትም ሆነ በህብረተሰቡ በኩል እንደሚነሳው «ሕዝቡ በሚኖርበት፣ በሚማርበትና በሚሰራበት አካባቢ የስፖርት እንቅስቃሴ ማድረግ አለበት»በሚል በፖሊሲ ደረጃ ቢቀመጥም ወደ ተግባር ከመለወጥ አንጻር ከፍተኛ ክፍተት መኖሩ ይታመናል። በተለይ በመንግስትና በግል ተቋማት ህብረተሰቡ በሚሰራበት ቦታ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ እንዲያደርግ እድል በመፍጠር ረገድ የፍላጎትም ሆነ የግንዛቤ ክፍተቶች እንዳሉ በስፖርቱ አዋቂዎች በኩል ይነገራል። በተቋማት የስፖርቱን ማህበራዊም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳን በመረዳት ስፖርታዊ ክንውኖችን የማዘጋጀት ባህሉ በእጅጉ አናሳ መሆኑም አብሮ ይነሳል። መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት በኩል የስፖርቱን ዘርፈ ብዙ ፋይዳ በመረዳት የስፖርት ፌስቲቫል የማዘጋጀት ልምድ ባለቤት የሆኑ ተቋማት በጣት የሚቆጠሩ ናቸው። ከእነዚህ ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳል። የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫሉ ዘንድሮ ለ5ኛ ጊዜ ከመስከረም 26 ጀምሮ ለአስር ቀናት ያክል «የኋላውን እያደስን የወደፊቱን ለመገንባት እንተጋለን »በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ይገኛል። የኮርፖሬሽኑ የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫል በ2002 ዓ.ም እንደተጀመረ መረጃዎች ያመላከታሉ ። ኮርፖሬሽኑ በሚያከናውነው የስፖርት ፌስቲቫል፤ አገር አቀፍ የስፖርት ፖሊሲውን ተግባራዊ ከማድረግ ባሻገር በሰራተኞች መካከል መቀራረብን እንደሚፈጥር ታምኖበታል። የስፖርት ፌስቲቫሉ ጤናው የተጠበቀና አምራች ዜጋን በማፍራት ውጤታማ መሆን እንደሚቻል ማሳያ መሆኑም ተጠቁሟል። የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫል አስተባባሪ አብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጥንፉ ሙጬ፤ የስፖርት ፌስቲቫሉ በአገር አቀፍ ደረጃ የወጣውን የስፖርት ፖሊሲ መሰረት በማድረግ የተጀመረ መሆኑን ይናገራሉ። ህዝቡ በሚኖርበትና በሚሰራበት አካባቢ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በማድረግ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን ማጉላት እንደሚችል መሰረት ባደረገ መልኩ ተቋሙ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑንም ይገልጻሉ። እንደ አቶ ጥንፍ ገለጻ፣ ስፖርት በተለይ ደግሞ በሰራተኞች መካከል እርስ በእርስ እንዲተዋወቁ፣ ጤናው የተጠበቀና አምራች ዜጋን ለማፍራት እንዲቻል፣ የሰራተኞችን አንድነት ለማጠናከር ፋይዳው ግዙፍ መሆኑን ያብራራሉ። በመሆኑም ኮርፖሬሽኑ የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫሉን እነዚህን ውጤቶች መሰረት በማድረግ ትኩረት ሰጥቶ እንደጀመረ ይናገራሉ። «ፌስቲቫሉ በየሁለት ዓመቱ ቢደረግ የበለጠ ዝግጅት ተደርጎ በጠንካራና ባማረ ሁኔታ ማከናወን ይቻላል »በሚል አስተዳደሩ ወስኖ በየሁለት ዓመቱ ሊካሄድ እንደቻለም ያስታውሳሉ። የኮርፖሬሽኑ የቤተሰብ ስፖርት በዚህ መልኩ በመቋቋም ባለፉት አስር ዓመታትን መጓዝ ችሏል። በስፖርት ክንውኑ ተቋሙ ውጤታማ መሆን ችሏል? ስንል ጥያቄ ሰንዝረናል። አቶ ጥንፍ ባለፉት አስር ዓመታት በነበረው ስፖርታዊ ክንዋኔ ተቋሙ ውጤታማ መሆኑን ይገልጻሉ። በመጀመሪያ ደረጃ አመራሩና ሰራተኛው መልካም የሆነ ግንኙነት እንዲፈጥሩ አድርጓል። እያደረገም ይገኛል። በአካልም፣ በአዕምሮም የበለፀገ ሰራተኛና አመራር እንዲኖር አስችሏል። ጤናማ ሰራተኛ በመፍጠር ረገድ ውጤት ማምጣት ተችሏል። መታወቅ ያለበት ያለ ጤናማ ሰራተኛ የኮንስትራክሽን ስራ የሚታሰብ እንዳልሆነም ያብራራሉ። የስፖርት ፌስቲቫሉ ሠራተኛውም ሆነ አመራሩን የበለጠ የሚያቀራርብ፣ ሠራተኛው ትርፍ ጊዜውን አዕምሮውንና አካላዊ ብቃቱን የሚያዳብርበት፣ ለተቋሙ ያለውን ወገናዊነት የሚያሳይበት፣ በሌሎች ፕሮጀክቶች ከሚገኙ ሠራተኞች ጋር ለመቀራረብና ለመተዋወቅ መንገድ እየከፈተ እንደሚገኝ ይገልጻሉ። እንደ አቶ ጥንፍ ማብራሪያ፤ የዘንድሮ መድረክ ከእስከ ዛሬው ለየት የሚያደርገው የተሳታፊነቱን ኮታ ለአመራሩ አንድ ሶስተኛውን በመስጠት ዋና ሥራ አስፈጻሚውን ሳይቀር ተሳታፊ ማድረጉ ነው። ስፖርት ፌስቲቫሉ ለአመራሩና ለሰራተኛው እኩል እድል ከመስጠት ባሻገር፤ በሁለቱ አካላት መካከል መቀራረብ እንዲፈጠርና የበለጠ ቀረቤታን መፍጠር እንዲያስችል ነው። ይህን በተግባርም ለመመልከት ተችሏል። የዘንድሮው ውድድር ሴቶችን የበለጠ ተሳታፊ እንዲሆኑ አድርጓል። በመድረኩ ያለፉት ዓመታት ጉዞ ሴቶች ቡድን አልነበራቸውም፤ ዘንድሮ ሁለት ቡድኖች ተቋቁመው በመረብ ኳስና በጠረጴዛ ቴኒስ ስፖርቶች ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ተደርጓል። «የዘንድሮው ፌስቲቫል ልዩ ገጽታው የለውጥ አስተሳሰቦችን ለማስረጽ ጥረት መደረጉ ነው። በውድድሩ ያሉትን ቡድኖች ስያሜን በዚህ ሁኔታ እንዲቃኙ የተደረገ ሲሆን ስያሜዎቹም አሸናፊ፣ ብቁ፣ ታዋቂ፣ ድንቅ፣ ባለራዕይ እና ተስፋ በሚል እንዲሰየሙ ተደርጓል›› ያሉት አስተባባሪው ከዚህ በተጨማሪም ቀደም ሲል ዘርፎች በቡድን ተደራጅተው እርስ በዕርስ የሚያደርጉት ውድድር እንደነበር ተናግረዋል። አደረጃጀቱ እንደ ኮርፖሬሽን ውህደት ባለማምጣቱ አዲስ አደረጃጀት በመፍጠር ወድድሩ እየተካሄደ ሲሆን፤ በመድረኩ የበለጠ መቀራረብና ተቋማዊ ስሜት መፍጠር እንደተቻለ በውድድሩ የአምስትና ስድስት ቀናት ቆይታ ወቅት ለመታዘብ ተችሏል። የስፖርት ፌስቲቫሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ ተቋማዊ ፋይዳውን እያሳደገ መምጣቱን የ5ኛው የቤተሰብ ስፖርት ውድድር እያሳየም ይገኛል። አቶ ጥንፍ ኮርፖሬሽኑ ግዙፍና በርካታ ፕሮጀክቶች ያቀፈ እንደመሆኑ በስፖርት ፌስቲቫሉ ሁሉም ፕሮጀክቶች ተሳታፊ እንዲሆኑ በመስራት የስፖርቱን ግዙፍ ፋይዳ በተቋሙ ምሉእ እንዲሆን ለማድረግ በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም አስቀምጠዋል። በ5ኛው የኮርፖሬሽኑ የቤተሰብ ስፖርት ሲሳተፍ ያገኘናቸው በኮርፖሬሽኑ የፋሲሊቲ ሰራተኛ የሆኑት አቶ ዜናው ደነቀው በበኩላቸው፤ የስፖርት ክንውኑን እንደ ኮርፖሬሽኑ ሁሉ ሌሎች ተቋማት ተግባራዊ ማድረግ ቢችሉ ያለውን ፋይዳ ይናገራሉ። «በእኛ ተቋም ያለውን ተሞክሮ በሌሎች የመንግስትና የግል መስሪያ ቤቶች ተግባራዊ ማድረግ ቢቻል፤ በአገር አቀፍ ደረጃ ተጠቃሚ መሆን ይቻላል። ከስፖርቱ የሚገኘውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ማግኘት ይቻላል። በተጨማሪም ኢሊት ስፖርተኞች የሚፈሩበትን አጋጣሚ በማስፋት ረገድ የራሱ የሆነ ድርሻ ይኖረዋል። የአገራችንን ስፖርት በማሳደግ ረገድም የመንግስት ተቋማት ድርሻቸውን እንዲወጡ አጋጣሚውን መፍጠር ይቻላል» ሲል ያብራራል። በኮርፖሬሽኑ የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫል ላይ ከአሰልጣኝነት እስከ ዳኝነት የተሻገረ ተሳትፎን ከመጀመሪያው ጀምሮ ሲያደርጉ እንደነበረ የገለፁልን የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ሰራተኛ የሆኑት አቶ አለማየሁ ገብሬ፤ የኮርፖሬሽኑ ተሞክሮን ሌሎች ተቋማት መውሰድ ቢችሉ ያለውን ነጥብ በማሳት ተመሳሳይ ሃሳብ ይጋራሉ። የቤተሰብ ስፖርቱን ከመጠንሰስ እና ቀጣይነት እንዲኖረው ከማድረግ አካያ በተቋሙ የነበሩና ያሉ አመራሮች ትልቅ ድርሻ እንደነበራቸውም ይናገራሉ። የኮርፖሬሽኑ አመራሮች የስፖርት ፌስቲቫሉ ሳይቋረጥ እንዲቀጥል ከማደርግ አኳያ ያሳዩት ቁርጠኝነት በተለይ ደግሞ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ዮናስ አያሌው ትልቅ ስራን መስራታቸውን ያስረዳሉ። አቶ አለማየሁ ዋና ስራ አስፈፃሚው ስፖርታዊ ክንውኑ ቀጣይነት ኖሮት በጠንካራ መስመር እንዲጓዝ ከመስራት ባሻገር፤ በውድድሩ ተጫዋች በመሆን የስፖርቱ ተሳታፊ መሆናቸው የሚያስመሰግናቸው መሆኑን ይገለጻሉ። ስፖርቱ ትኩረት እንዲያገኝ ከማድረግ አኳያም አመራሩ ያሳየው ቁርጠኝነት በሌሎች ተቋማት እንደ አርዓያ ሊወስዱት ይገባል ባይናቸው። ኮርፖሬሽኑም በየሁለት ዓመቱ ይህ የስፖርት ባህል ተጠናክሮ እንዲቀጥል ማድረግ እንደሚገባው ያስቀምጣሉ። በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫል ተሞክሮ በሌሎች መንግስታዊና መንግስታዊ ባልሆኑ ተቋማት መውሰድ ቢቻል ዘርፈ ብዙ ውጤቶች እንደ አገር ማትረፍ እንደሚቻል መመስከር ይቻላል። ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በህብረተሰቡ ዘንድ ትኩረት እንዲሰጠው ፖሊሲ ከመቅረጽ ባሻገር ተግባራዊ እንዲሆን እንደ ኮርፖሬሽኑ ሌሎች ተቋማት መስራት አለባቸው።አዲስ ዘመን  ረቡዕ ጥቅምት 5/2012ዳንኤል ዘነበ ", "passage_id": "6d84cfd7c86d1084995b22e46a54eca8" }, { "passage": "ከጥር 5 እስከ 12 ቀን 2011 ዓ.ም የሚካሄደው የአዲስ አበባ ከተማ 7ኛው ከተማ አቀፍ የተማሪዎች ስፖርት  ውድድር  ብሄራዊ መግባባትን ለመፍጠር እንደሚያግዝ  የከተማዋ ስፖርት ኮሚሽን አመለከተ።የአዲስ አበባ ከተማ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዮናስ አረጋይ ትናንት በተሰጠው መግለጫ ላይ እንደተናገሩት፤በአዲስ አበባ ከተማ ለ7ኛ ጊዜ የሚካሄደው ከተማ አቀፍ የተማሪዎች ስፖርታዊ  ውድድር ብሄራዊ መግባባትን ለመፍጠር እየተደረገ ባለው እንቅስቃሴ ውስጥ አሻራውን በማሳረፍ የበኩሉን ሚና ይወጣል ብለዋል።የውድድሩ አስፈላጊነት የተማሪዎች እርስ በእርስ ግንኙነትን በማጠናከር ሀገራዊ ስሜትን ብሄራዊ መግባባትን ለማበልጸግ የሚያስችል ተከታታይና የማያቋርጥ የውድድር መድረክ ለመፍጠር መሆኑን ጠቁመው፤በሰባተኛው የከተማ አቀፍ የውድድር መድረክ በስፖርት ሰላምን አንድነትን ለማምጣት ለሚደረገው አገራዊ እንቅስቃሴ እርሾ በመሆን ያገለግላል። በተጨማሪም በከተማችን የሚገኙ ተማሪዎችን በተደራጀ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ለማሳተፍና ተሳትፏቸውን እንዲያሳድጉ ለማድረግ የሚያስችል እንደሆነ ገልጸው፤ የመደበኛ የሰውነት ማጎልመሻ ትምህርት የተግባራዊ እንቅስቃሴ ሂደት ለመፍጠርም የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል።በየሁለት ዓመቱ የሚካሄደው  ከተማ አቀፍ የተማሪዎች ውድድሩ ጥር አምስት ቀን በእንጦጦ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በይፋ የሚጀመር ሲሆን በ20 የስፖርት አይነት እንደሚከናወን ተነግሯል። በዚህ መሰረት በውድድሩ  65 ቡድኖች 467 ወንድ እና 409 ሴት በድምሩ 876 ስፖርተኞች እንዲሁም 130 አሰልጣኞች ተሳታፊ እንደሚሆኑ ኮሚሽኑ አስታውቋል።በውድድሩ ጥሩ እንቅስቃሴ ያሳዩ ተሳታፊ ተማሪዎች በመቀለ ከተማ ለሚካሄደው ሀገር አቀፍ የተማሪዎች የስፖርት ውድድር አዲስ አበባን እንዲወክሉ የሚመረጡ ይሆናል። በየሁለት ዓመቱ የሚካሄደው አገር አቀፍ የተማሪዎች የስፖርት ውድድር  ከመጋቢት 14  እስከ 29 ቀን 2011 ዓ.ም በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ ይካሄዳል። የሀገር አቀፍ የተማሪዎች ውድድር የዝግጅት ሂደት ያለበትን ሁኔታ ከአስተናጋጇ ክልል ጋር ለመገምገም ወደ መቀሌ የሚመለከተው ቡድን መጓዙ ይታወሳል።አዲስ ዘመን ጥር 21/2011ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "85aadc607dcb9bb8acea5ed6dfa79bc9" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ህዳር 7/ 2006 (ዋኢማ) – የተጀመረውን የህዳሴ ጉዞ ከግብ ለማድረስ የኢህአዴግ ሴቶችና ወጣቶች ሊጎች አባላት ግንባር ቀደም ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ የኢህአዴግ ሊቀመንበርና ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ገለጹ፡፡የኢህአዴግ ሴቶችና ወጣቶች ሊጎች 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያምን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የአገር ውስጥና የውጭ እንግዶች በተገኙበት ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ ተጀምሯል፡፡ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም እንዳሉት ሴቶችና ወጣቶች ሊጎች ከ75 ፐርሰንት በላይ የሚሆነውን የብረተሰብ ክፍል የሚወክሉ በመሆናቸው የተጀመረው የህዳሴ ጉዞ እንዲሳካ የማይተካ ሚና አላቸው፡፡  በመሆኑም  በሁሉም ደረጃ የሚገኙ የሁለቱም ሊጎች አባለት በእድገትና ትራንስፎርሜሽን ሥራዎች እንዲሁም በጸረ ኪራይ ሰብሳቢነት ትግል ውስጥ ግንባር ቀደም ተዋናይ ሊሆኑ ይገባል ብለዋል፡፡የየሊጎቹ አባላት እንዲሁም መላው ወጣቶች በጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት ግንባታ ላይ ሁነኛ ተሳታፊዎች በመሆን አገሪቱ ወደፊት ልታረጋግ ጠው ለምትፈልገው የበለፀገ ኢንዱስትሪያዊ አገራዊ ኢኮኖሚ ግንባታ እውን መሆን ከማንም በላይ መንቀሳቀስ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡የኢህአዴግ ሴቶችና ወጣቶች ሊግ አባላት በሥነ ምግባር አበለጸጉ፣ ከኪራይ ሰብሳቢነትና ፀረ-ዴሞክራሲ የፀዱ፣ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ሁሉ ለሌላው የህብረተሰብ ክፍል ዓርአያ ሊሆኑ እንደሚገባቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ተናግረዋል፡፡  ሊጎቹ አገራዊ ሀላፊነታቸውን ለመወጣት ለሚያደርጉት ጥረት ኢህአዴግና በየደረጃው የሚገኙ የመንግስት አካላት አስፈላጊውን ድጋም እንደሚያደረጉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አያይዘው ገልጸዋል፡፡    በጉባኤ መክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ የሱዳን ብሄራዊ ኮንግረስ ፓርቲ፣ የደቡብ ሱዳን ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ፤ የሩዋንዳ አርበኞች ግንባር፣ የደቡብ አፍሪካው ኤ ኤን ሲና የቻይናው ኮሚኒስት ፓርቲ የድጋፍ መግለጫቸውን በተወካዮቻቸው አማካይነት  አቅርበል፡፡“በመለስ አስተምህሮ የተደራጀ የሴቶችና የወጣቶች ተሳተፎና ተጠቃሚነት ለህዳሴያችን” በሚል መሪ ቃል ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት በሚካሄደው ጉባኤ ላይ ከመላው አገሪቱ የተውጣጡ ወጣቶችና ሴቶች ተሳታፊ ናቸው፡፡ጉባኤው የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ሴቶችና ወጣቶች ሊግ ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀመንበር  በመምረጥ የተለያዩ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡", "passage_id": "f78d0933fbfbcf994b94418d05f20c24" }, { "passage": "የስፖርት መድረኮች ለማህበራዊ፣ ለኢኮኖሚያዊ፣ ለፖለቲካዊ፣ ለባህላዊና ተፈጥሯዊ ልማት አወንታዊ ተፅዕኖ እንዳላቸው ተደጋግሞ ይነሳል። ከነዚህም ጠቀሜታዎቹ ውስጥ የምጣኔ ሃብት እድገት፣ የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ ጤናማና ታታሪ ትውልድን ማፍራት፣ የመዋዕለ ንዋይ ፍሰት መጨመር፣ የስራ እድልን መፍጠርና የከተሞች መስፋፋት በዋናነት ሲጠቀሱ ስፖርት ለሰላም ያለው ፋይዳም በጉልህ የሚጠቀስ እውነታ ነው። ይህንንም በተለያዩ የታሪክ አጋጣሚዎች ለመመልከት ችለናል።ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአገራችን እየታየ ያለውን ፖለቲካዊ ለውጥ ተከትሎ በተለያዩ አካባቢዎች የፀጥታ ችግሮች ይስተዋላሉ። ከዚህም ጎን ለጎን በተለይም በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ላይ በየስቴድየሞቹ የሚስተዋለው የፀጥታ ችግር አሳሳቢነቱ ቀጥሏል። ስፖርት የሰላም ማስፈኛ መድረክነቱ ተዘንግቶም የሁከትና የግጭት መንስዔ ሲሆን በተደጋጋሚ ተስተውሏል። በየስቴድየሞቻችን በሚካሄዱ ጨዋታዎችም የስፖርት ትልቅ አላማ የሆነው «ሰላም» ተግባራዊ ከመሆን ይልቅ በተቃራኒው ሲመነዘር እያየን ነው።የኢትዮጵያ ቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽን ግን ዓመታዊ የክለቦች ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ከመጀመሩ አስቀድሞ ክለቦች «ስፖርት ለሰላም» በሚል መርህ የአቋም መለኪያ ጨዋታ እንዲያካሂዱ በማድረግ ከወዲሁ የውድድር አውድማዎች ሰላማዊ አየር እንዲተነፍሱ ለማስቻል እየሰራ እንደሚገኝ አሳውቋል።ስድስተኛው አገር አቀፍ የቅርጫት ኳስ ፕሪሚየር ሊግ ከመጀመሩ አስቀድሞ ከታህሳስ 15 እስከ 19 ቀን 2011 ዓ.ም በትንሿ ሁለገብ ስፖርት ማዕከል የሚካሄደው የአቋም መለኪያ ውድድር ሁለት አላማዎችን የሰነቀ ነው። የመጀመሪያው ስፖርት የሰላም መሳሪያ መሆኑን በማሳየት ክለቦች ወደ ውድድር ከመግባታቸው በፊት ለሰላም ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳዩበት ነው። በሌላ በኩል ክለቦች ወደ ዋናው ውድድር ከመግባታቸው አስቀድመው ያሉበትን አቋም የሚመዝኑበት ነው።ይህን መሰረት በማድረግ ውድድሩ ከትናንት በስቲያ ሲጀመር ሁለት ጨዋታዎች በወንዶች ተከናውነዋል። ሐዋሳ ከተማ ከየካ ክፍለ ከተማ የመጀመሪያውን ጨዋታ ያካሄዱ ክለቦች ሲሆኑ ሐዋሳ ከተማ ስልሳ ስድስት ለሃያ ዘጠኝ በሆነ ቅርጫት ጨዋታውን በአሸናፊነት አጠናቋል። በተመሳሳይ ሁለተኛውን ጨዋታ የኢትዮጵያ ውሃ ስፖርት ክለብ ፓንተርስ ክለብ ላይ ሃያ ቅርጫት በማስቆጠር አንድም ሳይቆጠርበት ጨዋታውን ደምድሟል።ሁለቱ ተሸናፊዎች ማለትም ፓንተርስና የካ ክፍለ ከተማ ዛሬ እርስበርስ የሚገናኙ ሲሆን፤ በተመሳሳይ አሸናፊዎቹ ሐዋሳ ከተማና ኢትዮጵያ ውሃ ስፖርት ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።ውድድሩ ሲጀመር በሴቶች ጨዋታቸውን ያደረጉት የኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚና ቢጂአይ ኢትዮጵያ ሲሆኑ የአካዳሚው ታዳጊዎች ሰላሳ አምስት ለሃያ ሰባት በሆነ ቅርጫት ማሸነፍ ችለዋል።አዲስ ዘመን  ታህሳስ 28/2011ቦጋለ አበበ", "passage_id": "191be45aa118971671fcefb20ed06445" } ]
969a1adb3c275dfcb72c9a19b262ffbc
bd78535bcffacfe1ae1b0f84cba42cf0
በውድድር ወቅት በወረርሽኙ መከላከያ መመሪያዎች አተገባበር ላይ ስጋት እንዳለው ሚኒስቴሩ ጠቆመ
ብርሃን ፈይሳ አዲስ አበባ፡- ስፖርታዊ እንቅስቃሴና ውድድሮች በሚከናወኑበት ወቅት የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ለመከላከል የተቀመጡ መመሪያዎች አተገባበር ላይ ስጋት እንዳለው የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ትናንት በተካሄደው በብሄራዊ የስፖርት ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን በጤና ሚኒስትር እንዲሁም በባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር የወጡ የኮቪድ 19 መከላከያ መመሪያዎችን ታሳቢ አድርጎ ውድድሮችንና እንቅስቃሴዎችን ለማከናወን ጥረት እየተደረገ መሆኑ መገለጹን አስታውቀው፣ የጤና ሚኒስቴር ግን በአተገባበሩ ላይ ስጋት እንዳለው ጠቁመዋል። በዚህ ወቅት የቫይረሱ ስርጭት ያለበት ምጣኔ ከ9-10 በመቶ ነው ያሉት ሚኒስትሯ፣ ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት ከፍተኛ ስጋት አለባቸው በሚል ካስቀመጣቸው ሃገሮች ውስጥ ትመደባለች ብለዋል። መመሪያዎቹም ይህንን ተከትለው የወጡ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ አተገባበራቸው ላይ ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ አሳስበዋል። እንደ ዶክተር ሊያ ገለጻ፤ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ከተከሰተ ጀምሮ በስፖርት ዘርፍ ወረርሽኙን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የተወሰዱ እርምጃዎች በርካታና የሚያስመሰግኑ ናቸው። በማህበረሰቡ ዘንድ የሚታየው በሽታውን የማቃለል ሁኔታ የሚስተዋል ሲሆን፣ ይህም በሁሉም ዘርፍ እየታየ ይገኛል፤ ይህን ችግር ለመፍታት አመራሮች ትኩረት ሊሰጡ ይገባል። መመሪያውን መከተልና ውድድሮችን ያለተመልካች ማካሄድ ያስፈልጋል ሲሉም አስገንዝበዋል። ሚኒስቴሩ በዚህ በኩል ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፣ ለእዚህም ከታላቁ ሩጫ አዘጋጆች ጋር እየተሰራ ያለውን በአብነት ጠቅሰዋል። ታላቁ ሩጫን ለማካሄድ በሚደረገው ዝግጅት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከአዘጋጆቹ ጋር እየሰራ መሆኑንም ጠቅሰው፣ በውድድሩ የታቀደው ብዙ ቁጥር ያላቸው ተሳታፊዎችን ለማካተት መሆኑን አመልክተዋል። ይህን አሀዝ ለመቀነስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ውድድሩን ከዚህ ቀደም ከነበረው ለየት ባለ ሁኔታ ለማድረግም ፈቃደኝነት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በአዲስ አበባ ያለው የወረርሽኝ መጠን በጣም ከፍተኛ የሚባል መሆኑን አመልክተው፣ መመሪያዎቹን ብቻ ማዘጋጀት ሳይሆን ለተግባራዊነቱም መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።አዲስ ዘመን ታኅሳስ 21/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=38515
[ { "passage": "አዲስ አበባ፡- በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በኢኮኖሚው፣ በድርጅቶች ቀጣይነትና ህልውና እንዲሁም በሰራተኞች ላይ የሚፈጥረውን አሉታዊ ተጽዕኖ ለመቀነስ ይረዳል የተባለ የስራ ቦታ ምላሽ የሶስትዮሽ ፕሮቶኮል ይፋ ተደረገ። የስራ ቦታ ምላሽ የሶስትዮሽ ፕሮቶኮሉን የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን፣ የኢትዮጵያ አሰሪዎች ኮንፌዴሬሽን፣ የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ አሰሪዎች ኮንፌዴሬሽን በጋራ ይፋ አድርገውታል። በወቅቱ የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ እንደገለጹት፤ ፕሮቶኮሉ ህጋዊና አስተዳደራዊ ዕርምጃዎችን ለመውሰድ እንዲቻል ከወረርሽኙ ጉዳት አኳያ ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት ለማድረግ በመንግስት፣ በአሰሪ እና ሰራተኛው እየታዩ የሚወሰዱ አቅጣጫዎችን ይዟል። ወረርሽኙን በአስተማማኝ መልኩ ለመከላከል እና በድርጅቶችና በሰራተኛው ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ለመቀነስ ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀ ነው። እንደ ዶክተር ኤርጎጌ ገለጻ፤ ቀውስን የመቋቋም ችሎታ እና ምላሽ አቅም ከድርጅት ድርጅት እንዲሁም ከዘርፍ ዘርፍ የሚለያይ በመሆኑ መፍትሄዎች ከየድርጅቶች እንዲመነጩ በማድረግ በፕሮቶኮሉ የቀረቡ ምክረሃሳቦችን አሰሪውና ሰራተኛው የጋራ እንዲያደርጉት ይጠበቃል። በዚህም ደረጃ በደረጃ ሊወሰዱ ከሚገባቸው ህጋዊና አስተዳደራዊ ዕርምጃዎች መካከል ያልተቋጩ አዲስ የህብረት ስምምነት ድርድሮች ለሚቀጥሉት 12 ወራት እንዲቋረጡ የሚል ተካቷል። ተግባራዊ ያልተደረገ የደመወዝ ጭማሪ ለሚቀጥሉት 12 ወራት ተግባራዊ እንዳይደረግ የሚል አቅጣጫ በፕሮቶኮሉ ተቀምጧል። እንደ ሚኒስትሯ ከሆነ፤ በተጨማሪ ሰራተኞች ያልተጠቀሙበት የዓመት ዕረፍታቸውን እንዲጠቀሙ ማድረግ እና እረፍታቸውን ተጠቅመው የጨረሱ ካሉ ከቀጣይ ዓመታት የእረፍት ጊዜ ቢያንስ ግማሹን እየተጠቀሙ በክፍያ እንዲቆዩ የሚለው ተካቷል። እንደየተቋማቱ የኪሳራ ሁኔታ የሚለያይ ሆኖ እና የችግሩ መጠን እየታየ ተግባራዊ ሲደረጉ የነበሩ የተለያዩ አበሎች፣ ጉርሻ እና ኮሚሽን እንዲሁም እንደደመወዝ የማይቆጠሩ ክፍያዎች ችግሩ ሙሉ በሙሉ እስኪቀረፍ እንዳይፈጸሙ ቢደረግ የሚል ሃሳብም ፕሮቶኮሉ አካቷል። እጅግ አስፈላጊ ባልሆኑ የድርጅት ስራዎች ላይ የተሰማሩ ሰራተኞች ለጊዜው የተወሰነ ብድር በመስጠት ሁኔታዎች ሲሻሻሉ ወደስራ እንዲመለሱ የጽሁፍ ማረጋገጫ መስጠት እንደሚገባ በፕሮቶኮሉ ሰፍሯል። ፕሮቶኮሉ በአሰሪዎች ሊወሰዱ የሚገቡ ጥንቃቄዎችን መያዙን የገለጹት ዶክተር ኤርጎጌ፤ የአፍና የአፍንጫ ማስክ ማቅረብ እና ስለአጠቃቀሙ ግንዛቤ ማስያዝ፣ በድርጅቱ ሃላፊ የሚመራና ሰራተኞች አባል የሚሆንበት የኮና ቫይረስ ቁጥጥርን የሚመራና የሚከታተል ኮሚቴ ማቋቋም እንዲሁም የሰራተኞችን የጥግግት ሁኔታ ማስቀረት እንደሚገባ አቅጣጫ መቀመጡን ተናግረዋል። ሰራተኞች በበኩላቸው ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው በማስታወስ፣ የሴፍቲ ኦፊሰሮች በስራ ቦታዎች እየተንቀሳቀሱ ለኮሮና ቫይረስ የሚያጋልጡ ሁኔታዎችን እየተከታተሉ እርምጃ መውሰድ እንደሚገባቸው በፕሮቶኮሉ መካተቱን አስረድተዋል። በፕሮቶኮሉ የቀረቡ ሃሳቦች በእያንዳንዱ ድርጅት እንደየሁኔታው የሚወሰን መሆኑን የተናገሩት ሚኒስትሯ፣ ፕሮቶኮሉ ከአንድ ሰው በላይ ለቀጠሩ ድርጅቶች በሙሉ እንደሚሰራ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ አሰሪዎች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ በበኩላቸው፣ ከጥንቃቄ እርምጃዎች ባሻገር አብዛኛዎቹ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃዎች ተብለው የሰፈሩትን ጉዳዮች ኪሳራ ባጋጠማቸው ድርጅቶች ላይ እንጂ ትርፋማ የሆኑትን እንደማያካትት ገልጸዋል። በቀጣይም እንደየችግሩ መጠን እና ሁኔታ ደረጃ በደረጃ መንግስት፣ ሰራተኛ እና አሰሪዎችን ባካተተ መልኩ የፕሮቶኮሉ ይዘት ሊስተካከል እንደሚችልም አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ አሠሪዎች ኮንፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ታደለ ይመር በበኩላቸው ከችግሩ ለመውጣት አሰሪውም ሆነ ሰራተኛውም ሳይጎዳ ለመጓዝ ፕሮቶኮሉ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል። በሌላ በኩል ግን ያላስፈላጊ ጥቅም ለማጋበስ የሚሰሩ ነጋዴዎችም ሱቃቸውን መዝጋት ብቻ ሳይሆን በአደባባይ ተጋልጠው ለፍርድ ሊቀርቡ እንደሚገባ ገልጸዋል። ዓለም አቀፉ የሰራተኞች ድርጅት የቀውስ ጊዜ አስተዳደርን ምላሽ በተመለከተ ባሰፈረው መመሪያ መሰረት በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ሳቢያ የስራ ሁኔታ ጉዳት ሲደርስበት በቀውስ ለተጎዱ ሰራተኞች መሰረታዊ ገቢያቸው እንዳይቋረጥ ማገዝ ይገባል። አዲስ ዘመን መጋቢት19/2012 ጌትነት ተስፋማርያም", "passage_id": "11728b5bac740a2abaf8adfab26da3e3" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ታህሳስ 27 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የገና በአል አስመልክቶ ህብረተሰቡ በግብይት ሂደት ለኮቪድ 19 ወረርሺኝ ከሚያጋልጡ ሁኔታዎች ራሱን መጠበቅና ከአላስፈላጊ መዘናጋቶች ራሱን መጠበቅ እንደሚገባው የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።ሚኒስትሩ መልዕክቱን ያስተላለፉት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ባዘጋጀው የኮቪድ 19 ወረርሺኝ መከላከያ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ድጋፍ ድርጊት መርሃ ግብር ላይ ነው።አቶ መላኩ በወቅቱም በዓሉን አስመልክቶ በኢንዱስትሪዎች በርካታ ሰራተኞች እና በገበያ ቦታዎች በርካታ የግብይት ተዋንያኖች አሉ ብለዋል።ስለሆነም እነዚህ ቦታዎች ለወረርሺኙ መስፋፋት ምክንያት በመሆናቸው ህብረተሰቡ በዓሉን ለማድመቅ በሚያደርጋቸው ማንኛውም እንቅስቀሴ ወቅት የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል ማድረግ ይኖርበታል ብለዋል።ከዚያም ባለፈ በጤና ባለሞያዎች የሚሰጠውን መመሪያ በመተግበር ራሱን ከበሽታው በመከላከልና ለበሽታው ስርጭት መገታት በሚደረገው ጥረት የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ጥሪያቸውን ማስተላለቻውን ከሚኒስቴሩ ያገኘኘው መረጃ ያመላክታል።ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!", "passage_id": "a5a121389eeac4cf316b619d7e183edd" }, { "passage": "ተሽከርካሪዎች የፍጥነት መገደቢያ እና ጂፒኤስ ሳይገጠምላቸው ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ ያዘጋጀውን መመሪያ ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩን የትራንስፖርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡መመሪያው ታህሳስ ፣2011 ዓ.ም አጋማሽ የፀደቀ ቢሆንም ተግባራዊ መሆን የጀመረው  ከሀምሌ 2011 ዓ.ም አጋማሽ ጀምሮ ነው ተብሏል፡፡መመሪያው ከመውጣቱ በፊት የግዥ ጥያቄ ያቀረቡና የግዥ ሂደት የጀመሩ የተሸከርካሪ አስመጪዎች  መመሪያው አይመለከታቸውም ተብሏል፡፡አዲሱ ቴክኖሎጂ በትራፊክ አደጋ ምክንያት እየተከሰተ ያለውን የሞት፣ የአካል ጉዳትና የንብረት ውድመት ለመከላከል እንደሚረዳ የትራንስፖርት ሚኒስቴር የኮሙኒኬሽን ምክትል ዳይሬክተር አቶ ሙሴ ይሄይስ ገልጸዋል፡፡በዜጎች ላይ እየደረሰ ያለውን የትራፊክ አደጋ ለመከላከል መንግስት ግንዛቤ ማስጨበጥን ጨምሮ መሳሪያውን በፍጥነት ወደ ስራ ለማስገባት እየሰራ መሆኑንም ነው አቶ ሙሴ የገለፁት፡፡መንግስት ከባለሀብቶች ጋር በመተባበር የፍጥነት መገደቢያ እና ጂፒኤስ ቴክኖሎጂው ተገጥሞ ወደ ሃገር ለማስገባት እየሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ባለሃብቶች የፍጥነት መገደቢያና ጂፒኤስ መሳሪያውን በተሽከርካሪዎች ላይ አስገጥመው በማስገባት በተመጣጣኝ ክፍያ ደንበኞቻቸውን የሚያስከፍሉበት ሁኔታ ላይ መግባባት ላይ ተደርሶ ወደ ስራ መገባቱም አቶ ሙሴ መናገራቸውን ኢቢሲ ዘግቧል፡፡", "passage_id": "8e92f49213e5be390db2c68917382e40" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ መስከረም 25 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የጤና ሚኒስቴር ኮቪድ-19 በመከላከል ዜጎች በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የሚያደርጉበትን መመሪያ ይፋ አደረገ። በኢትዮጵያ መጋቢት 2012 ዓ.ም የተከሰተው የኮሮና ወረርሽኝ የሚያደርሰው ጉዳት እየጨመረ መጥቷል።በአሁኑ ወቅት 79 ሺህ ያህል ዜጎች በቫይረሱ የተያዙ ሲሆን፣ ከ1ሺህ 200 በላይ ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል። በጽኑ ሕሙማን ክፍልም 285 ሰዎች ይገኛሉ።የጤና ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በዓዋጅ የተሰጣቸውን ሥልጣን በመጠቀም በጋራ መመሪያ አዘጋጅተዋል።የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ የመመሪያውን ይዘት በሚመለከት ዛሬ ማብራሪያ ሰጥተዋል።መንግሥት ኮቪድ-19 በአገሪቱ መከሰቱን ተከትሎ የስርጭቱን መጠን ለመቀነስና ለመግታት የኮቪድ መከላከል ግብረ ኃይልን ከማቋቋም በተጨማሪ የአስቸኳይ ጊዜ ዓዋጅ ታውጆ እንደነበር አስታውሰዋል።የዓዋጁን መነሳት ተከትሎ ህብረተሰቡ መዘናጋት ውስጥ ከመግባቱ ባሻገር የስርጭት ምጣኔው በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች በመስፋፋት ስጋት መፍጠሩን ገልጸዋል።በዚህም ኮቪድ-19ን በመከላከል ረገድ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ እያደረገ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴው መመሪያውን እንዲተገብር ሚኒስትሯ አሳስበዋል።መመሪያው ኮቪድ 19 እንዳለበት በምርመራ የተረጋገጠ ማንኛውም ሰው ወደ አገር መግባት፣ቫይረሱን ሊተላለፍ በሚችልበት ሁኔታ ከሰዎች ጋር ንኪኪ ማድረግ፣ለሰላምታም ሆነ ለሌላ ዓላማ እጅ ለእጅ መጨባበጥና መተቃቀፍ ፈጽሞ ይከለክላል።ከአምስት ዓመት በታች ከሆኑ ህጻናት በስተቀር የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ (ጭምብል) ሳይጠቀሙ በማንኛውም ቦታ ላይ መንቀሳቀስ በሕግ እንደሚያስቀጣም ሚኒስትሯ ተናግረዋል።በክፍት ገበያዎች፣በትራንስፖርት መሳፈሪያ ቦታዎች፣ሕዝባዊ አገልግሎት በሚሰጥባቸው ስፍራዎች ሌሎች መሰል ቦታዎች ላይ ሁለት የአዋቂ እርምጃ ርቀት መጠበቅና የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል) መጠቀም ግዴታ መሆኑን ይደነግጋል።ማንኛውም የግልም ሆነ የመንግሥት የትምህርት ተቋማት ትምህርት የሚጀመርበትን ትክክለኛ ወቅትና መመሪያ ሳይደርሳቸው ትምህርት መጀመር እንደማይችሉ ዶክተር ሊያ አስታውቀዋል።የህጻናት ማቆያ ማዕከላትም አገልግሎት የሚሰጡበት መመሪያ እስኪወጣላቸው ዝግ ሆነው እንደሚቆዩ ገልጸዋል።የመንግሥትም ሆነ የግል የሥራ ተቋማት ሰራተኞቻቸው ወረርሽኙን ለመከላከል የሚከናወኑ ተግባራትን መከታተልና ማስተግበር እንደሚጠበቅባቸው ሚኒስትሯ አስገንዝበዋል።ምን ዓይነት የበሽታውን ምልክት የማያሳይ የኮቪድ-19 ታማሚ በቤት ውስጥ የሚደረግለት ሕክምና እንደሚቀጥል ገልጸው፣ታካሚው ቢያንስ ለ14 ቀናት ከማህበረሰቡ ራሱን አግልሎ መቆየት ግዴታ ነው ብለዋል።የኳረንቲንና የድንበር ላይ ጤና ቁጥጥርን በሚመለከት ከትራንዚት መንገደኛ በስተቀር ከ10 ዓመት ዕድሜ በላይ የሆነ ማንኛውም ተጓዥ ከመጣበት አገር ነጻ መሆኑን የሚያሳይ የምርመራ ውጤት ማሳየት ይጠበቅበታል።በቀጣይም በአውሮፕላን ማረፊያው ምርመራ ከተደረገለት በኋላም አድራሻውን በማስመዝገብ በቤቱ ለሰባት ቀናት ለይቶ የመቆየት ግዴታ እንደተጣለበት ገልጸዋል።ከመጣበት አገር ፖዘቲቭ የሆነ ውጤት ይዞ የሚመጣ መንገደኛ ኢትዮጵያ ውስጥ መግባት እንደማይችልም ዶክተር ሊያ አመልክተዋል።በየብስ የሚገባ መንገደኛ ከበሽታው ነጻ መሆኑን የሚያረጋግጥበት የምርመራ ውጤት ቢኖረውም፤ ለሰባት ቀናት በቤቱ መቆየት ግዴታ እንዳለበት አብራርተዋል።የቀብር ሥነ-ሥርዓት፣ የሰርግና የቤት ውስጥ ማህበራዊ ዝግጅቶች ከ50 ሰዎች ባልበለጠ እንደሚከወኑና የጥንቃቄ መርሆዎች እንደሚተገበሩ መመሪያው ያስገድዳል።የሰዎችን በአንድ ቦታ መሰባሰብ ለማስቀረት ስብሰባዎች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተደግፈው ይካሄዳሉ ያሉት ሚኒስትሯ፣ አስገዳጅ ከሆነ ከ50 ሰዎች ባልበለጠና ርቀትን በጠበቀ መልኩ ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ ማካሄድ ይቻላል ብለዋል።አገልግሎት የሚሰጥባቸው ካፌዎች፣ባርና ሬስቶራንቶች፣መጠጥ ቤቶች፣የመዝናኛና የመጫወቻ ስፍራዎች በጠረጴዛ ሶስት ሰዎችን ብቻ ማስተናገድና ጥንቃቄ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ነው ያሉት።ሲኒማ ቤቶች፣ትያትር ቤቶችና የሥዕል ጋለሪዎች ያላቸውን ቦታ ከግምት ውስጥ በማስገባት አንድ አራተኛ ተመልካቾችን ብቻ በመለየትና በሽታውን መከላከል መርሆዎችን በማስተግበር ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆኑ ተናግረዋል።በተጨማሪም የስርጭቱ ምጣኔ እየታየ በድጋሚ ሌላ መመሪያ እስኪወጣ ድረስ ከማረሚያ ቤት በስተቀር በማዕከላትና ማገገሚያ ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን መጠየቅ ክልክል መሆኑን ዶክተር ሊያ አብራርተዋል።ይሁን እንጂ ማረሚያ ቤቶች ላይ የጥየቃ አገልግሎቱ ርቀትን በጠበቀና ምንም ንኪኪና ግንኙነት በሌለው መልኩ ማድረግ ይችላሉም ነው የተባለው።ስፖርታዊ ውድድሮች በተለይም የእግር ኳስ፣የእጅ ኳስ፣ቅርጫት ኳስ፣ቴኒስና አትሌቲክስ ታዳሚ በሌለበት መከናወን እንዳለባቸው አመልክተዋል።ዜጎች መመሪያዎችን በመተግበርና በማስተግበር ወረርሽኙን በመከላከል ድርሻቸውን እንዲወጡ ሚኒስትሯ ጥሪ አቅርበዋል፡፡", "passage_id": "6cb37594a4ef3f0534429e39d7fe1e5e" }, { "passage": "የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን በበኩሉ በስር የሚገኙ ማዕከላትና የስፖርት ማዝወተሪያ ስፍራዎች በኮሮናቫይረስ ምክንያት ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት መስጠት ማቆማቸውን ገልጿል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዮናስ አረጋይ ዛሬ ለዝግጅት ከፍላችን በሰጡት መግለጫ ከዛሬ ጀምሮ በአራት ኪሎ ስፖርት ትምህርት ስልጠና ማዕከል፣ በጃንሜዳ ስፖርት ትምህርትና ስልጠና ማዕከል፣ በራስ ሀይሉ ስፖርት ትምህርት ስልጠና ማዕከል እና በአዲስ አበባ ሜዳ ቴኒስ ማዕከል እንዲሁም በ117 ወረዳዎች በሚገኙ የስፖርት ማዝወተሪያዎች ማንኛውም ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ላልተወሰነ ጊዜ መቆሙን ተናግረዋል።መንግስት የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ከዛሬ ጀምሮ ትምህርት ቤቶች እንዲዘጉ፣ ታላላቅ ስብሰባዎች እንዲዘጉ እና ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች እንዳይካሄዱ ለ15 ቀናት መወሰኑ ይታወሳል።አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 7 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን በሀገር ውስጥ የሚካሄዱ ስፖርታዊ ውድድሮች፣ ጨዋታዎች፣ የስፖርት ፌስቲቫል፣ ስልጠናዎች፣ ጉባኤዎች እና ትላልቅ ስብሰባዎች ለ15 ቀናት በየትኛውም ቦታ እንደማይካሄዱ አስታወቀ።ከዚህ በተጨማሪም ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ውድድሮች እና የስልጠና መድረኮች ለህዝቡ ደህንነት ሲባል በቫይረሱ ዙሪያ ተጨማሪ መረጃ በመንግስት እስከሚሰጥ ድረስ እንደማትሳተፍም አስታውቋል።ከዛሬ ጀምሮም በመንግስት አስፈላጊው መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ምንም ዓይነት ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረግ እንደማይቻል መግለጹን ከኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።ከዚህ ጋር ተያይዞ በኮሚሸኑ አዘጋጅነት በማህበረሰብ ስፖርት ተሳትፎ እና በስፖርታዊ ጨዋነት ማስፈን ዙሪያ መጋቢት 9 እና 10 ቀን 2012 ዓ.ም ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው የባለድርሻ አካላት መድረክ ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙም ተገልጿል። ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!\nhttps://t.me/fanatelevision", "passage_id": "2c135e90230580b74ad18792fe83c3e4" } ]
417d669827e164060f52c003b36785ba
d99a3fe0fff3173d45bf256751d61f8b
ስፖርትን ከፖለቲካ የመለየት ፈተናዎች
ቦጋለ አበበ‹‹ስፖርትና ፖለቲካ አንድ ናቸው ወይም ጠንካራ ግንኙነት አላቸው›› ብለው የሚያምኑ በርካቶች የመሆናቸውን ያህል ‹‹ስፖርት ከፖለቲካ ነፃና ገለልተኛ ነው ወይም መሆን አለበት›› ብለው በምክንያት የሚሞግቱ ጥቂት አይደሉም።ከዚህ በተለየ መልኩ በዘመናዊው ዓለም ስፖርት የፖለቲካ መጠቀሚያ ዋነኛ መሳሪያ እየሆነ በመምጣቱ ነፃ ሊወጣ እንደሚገባ የሚሞግቱ አልጠፉም።እነዚህ ሞጋቾች ግን ስፖርትን ከፖለቲካ ሙሉ በሙሉ ነፃ ለማውጣት ወይም የመሰንጠቅ ፈተናዎች እንዳሉባቸው በርካታ ማሳያዎችን በመደርደር የሚከራከሩ የየዘርፎቹ ተንታኞች በዓለም ዙሪያ ድምፃቸውን ሲያሰሙ መገንዘብ ይቻላል።ባለፈው ዓመት በሞንቴ ካርሎ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የሰላምና የስፖርት ኮንፍረንስ ላይ ስፖርትን ከፖለቲካ የመነጠል ጉዳይ ብዙ ክርክር አስነስቷል። ‹ስፖርትና ሰላም› በሚል እኤአ 2007 ላይ በፈረንሳዊው የቀድሞ አትሌትና የዓለም ኦሊምፒያኖች ማህበር ፕሬዝዳንት ጆኤል ቦዞ የተመሰረተው ተቋም በሞንቴ ካርሎ የተካሄደው የስፖርትና ሰላም ኮንፍረንስ አዘጋጅ ነበር።ይህ ተቋም ‹‹ቻምፒዮኖች ለሰላም›› በሚል መርህ የስፖርቱ ዓለም ከዋክብቶችን በአምባሳደርነት በመያዝ ተፅዕኖው ከዓመት ዓመት እየጨመረ ይገኛል። ኮትዲቯራዊው የእግር ኳስ ኮከብ ዲዲየር ድሮግባ፣ ሰርቢያዊው የሜዳ ቴኒስ ኮከብ ኖቫክ ጆኮቪችና እንግሊዛዊቷ ስመ ጥር አትሌት ፓውላ ራድክሊፍ ከዚህ ተቋም አምባሳደሮች መካከል ይገኙበታል።ተቋሙ በሚያዘጋጃቸው ኮንፍረንሶች የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች፣ የፆታ እኩልነት፣ ስፖርትና ቴክኖሎጂ እንዲሁም ስደተኞችና የበጎ አድራጎት ስራዎች አጀንዳ ሆነው ይነሳሉ።ከዓለም ዙሪያ በርካታ ባለሙያዎች፣ የዓለም አቀፍ ስፖርት ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንቶችና ተወካዮቻቸው እንዲሁም መንግስታዊ ያልሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማት ኮንፍረንሱ ላይ ተገኝተውም በአጀንዳዎቹ ላይ ይወያያሉ።ስፖርትን ከየትኛውም አይነት የፖለቲካ ተፅዕኖ ነፃ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በሚደረጉ ሰፊ ውይይቶች ቀልብ ከመሳባቸው ባሻገር መደምደሚያ ያልተበጀላቸው አጀንዳዎች ስፍር ቁጥር የላቸውም።የስፖርትና ሰላም ተቋም መስራቹ ቦዞ ስፖርትን ከፖለቲካ ተፅዕኖ መነጠል በሚቻልበት አከራካሪ ሁኔታ ላይ በሰጠው አስተያየት ‹‹ሁል ጊዜም ቢሆን የስፖርትን ገለልተኝነት እናከብራለን፣ ስፖርት ከሰላም ጋር እንዲቆራኝም ምክኒያታዊ ሆነን እንሰራለን›› በማለት ይናገራል።ቦዞ ስፖርት ከተለመደው ፖለቲካ ነፃ እንደሆነ በማመን ተቋሙ ስፖርትን ከፖለቲካ ጋር በማይገናኝበት በማንኛውም ሁኔታ ከተለያዩ አካላት ጋር ለመስራት ጥረት እንደሚያደርግም ያስረዳል።ይህም በየትኛውም የዓለም ክፍል ከሚገኝ አገር ጋር በመስራት የስፖርትን ዓለም አቀፋዊነት እስከ ማረጋገጥ እንደሚደርስ እምነቱ ነው።የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ስራ አስፈፃሚዎች በቅርቡ በሉዛን ባደረጉት ስብሰባ አትሌቶች የኦሊምፒክ መድረክ ላይ በፍፁም የፖለቲካ ተቃውሞ፣ የሐይማኖትና የዘረኝነት መልዕክት ማስተላለፍ እንደሌለባቸው ውሳኔ ላይ መድረሳቸው ይታወሳል። የኮሚቴው ፕሬዝዳንት ቶማስ ባኽ በቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ አትሌቶች የትኛውንም አይነት የፖለቲካ፣ የሐይማኖት፣ የዘርና መሰል ተቃውሞና መልዕክት እንዳያስተላልፉ ማሳሰቢያ መስጠታቸውን ተከትሎም ስፖርት ከፖለቲካ ነፃ መሆን አለበት የለበትም? የሚሉ ሙግቶች ፍጥጫ ፈጥረዋል። በኦሊምፒኩ ወቅት በየትኛውም ስፍራ አትሌቶች ለተፎካካሪዎቻቸው ክብር ማሳየት እንዳለባቸውም ፕሬዝዳንቱ ደጋግመው ሲናገሩ ይደመጣል። ቶማስ ባኽ ስፖርትን የፖለቲካ መጠቀሚያ የማድረግ አዝማሚያ እየሰፋ በመጣበት በዚህ ወቅት በኦሊምፒክ መድረክ አላስፈላጊ መልዕክቶችን ማስተላለፍ ምንም ጥቅም እንደሌለውና የዓለምን ሕዝቦች ከመነጣጠል የዘለለ ፋይዳ እንደማይኖረው ያምናሉ። ‹‹የኦሊምፒክ መድረክ ዓለም አቀፋዊ ይዘት ያለው አትሌቶች ስፖርታዊ ብቃታቸውን የሚያሳዩበት እንጂ የፖለቲካ ወይም ሌላ ፕሮፓጋንዳ የሚያስተላልፉበት አይደለም›› የሚሉት ቶማስ ባኽ፣ ስፖርትን የፖለቲካ መጠቀሚያ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት ለመታገል በመድረኩ እንደዚህ አይነት ማሳሰቢያዎችን ቀድሞ ማሳወቅ እንደሚገባ ይናገራሉ።የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የአትሌቶች ኮሚሽን ሊቀመንበር ኪርስቴይ ኮቬንትሪ ከዓመት በፊት በርካታ አትሌቶች ኦሊምፒክ መድረክ ላይ የፖለቲካ ተቃውሞ ለማድረግ ተገቢው ቦታ መሆኑን እንደሚያምኑ በመናገር የአትሌቶቹን ሃሳብ መደገፋቸው በዓለም አቀፉ ኮሚቴ ውስጥ የተከፋፈለ ሃሳብ እንዳለ አሳይተዋል። ይህንንም ተከትሎ አትሌቶች በኦሊምፒክ መድረክ የፖለቲካ ተቃውሞ ማድረግ፣ የሐይማኖትና የዘረኝነት መልዕክት ማስተላለፍ አለባቸው የለባቸውም የሚለው ሃሳብ አከራካሪ ሆኖ ቆይቷል፡፡የዓለም መንግስታት ስፖርትን ለፖለቲካ መጠቀሚያ የሚያደርጉበት አጋጣሚ እንዳለ ሁሉ ከፖለቲካው ትርፍ ጎን ለጎን በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ከሰላም ጋር ተያይዞ ለአገርና ለሕዝብ የሚጠቅሙ ክስተቶች ሲፈጠሩ ይታያል።ለአብነት ያህል የቦስኒያና ሄርዝጎቪኒያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ከዓመት በፊት በሳራጄቮና ምስራቅ ሳራጄቮ ከተሞች የአውሮፓን ወጣቶች ኦሊምፒክ በጥምረት በማዘጋጀት ተሸላሚ ሆነዋል። ይህም እኤአ ከ1992 እስከ 1995 በቦስኒያ ተካሂዶ ከነበረው ደም አፋሳሽ ጦርነት ወዲህ ሁለቱ የተከፋፈሉ አገራት የዲፕሎማሲ ግንኙነት እንዲሻሻል አድርጓል።በሌላ መልኩ የወርልድ ቴኳንዶና ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ፌዴሬሽኖች በግልፅ የሚታወቅ የተቀናቃኝነት ታሪክ ቢኖራቸውም ጥቂት ልዩነቶቻቸውን ወደ ጎን ትተው ውድድሮችን አንድ ላይ ያካሄዱበት አጋጣሚ ከስፖርትም የዘለለ ትርጉም ነበረው።ወርልድ ቴኳንዶ መሰረቱን በደቡብ ኮሪያ ሲዎል ከተማ ያደረገ ሲሆን ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ መሰረቱ የሰሜን ኮሪያ ነው። ሁለቱ አካላት መቀመጫቸው በአውስትራሊያ ቬና ቢሆንም ሰሜን ኮሪያና ደቡብ ኮሪያን የመሰንጠቅ አቅም እንደነበራቸው ይታወቃል። በተመሳሳይ እንደ ጠላት የሚተያዩት ሰሜን ኮሪያና ደቡብ ኮሪያ ጉዳይ እስካሁን መቋጫ ያላገኘ ቢሆንም በ2018 የፒዮንግያንግ የበጋ ኦሊምፒክ የሁለቱ አገራት የሴቶች የሆኪ ስፖርት ቡድኖች አንድ ሆነው በመድረኩ መሳተፋቸው በሁለቱ አገራት መካከል የነበረውን የፖለቲካ ውጥረት ወደ ተሻለ የዲፕሎማሲ ደረጃ ያሸጋገረ ነበር። ከዚህ ኩነት አኳያ ፖለቲካና ስፖርትን ሙሉ በሙሉ እንዴት መነጠል እንደሚቻል ግልፅ እንዳልሆነ ብዙዎች ይስማማሉ።ስፖርትን ለሰላም መጠቀም ማንም የሚቃወመው ጉዳይ እንዳልሆነ ሁሉ በስፖርት ሽፋን የማይሆን የፖለቲካ ትርፍ ማጋበሻ የማዋል አዝማሚያም በተለያዩ አገራት ይስተዋላል።ዓለም አቀፋዊ ውድድሮችን ማዘጋጀት የሁሉም አገራት መንግስታት ፍላጎት የሚሆነው በዋናነት የአገርን ገፅታ ለመገንባት በማሰብ ነው። አምባገነን መንግስታት ይህን በመጠቀም የአገራቸውን የፖለቲካ ገፅታ ለመቀየር ሲሞክሩ ግን ይታያል።ለዚህ በርካታ ምሳሌዎችን መጥቀስም ይቻላል።በቅርቡ እንግሊዛዊው ቦክሰኛ አንቶኒ ጆሹአ ከሜክሲኳዊው ቦክሰኛ አንዲ ሩይዝ ጋር በሳውዲ አረቢያ ያደረገው የክፍለ ዘመኑ ምርጥ የተባለለት ግጥሚያ መነጋገሪያ ነበር።ሳውዲ አረቢያ በሰብዓዊ መብት አያያዝ ተወቃሽ አገር ከመሆኗ ባሻገር ከዓመት በፊት ቱርክ ኢስታንቡል በሚገኘው ኤምባሲዋ የተገደለው ጋዜጠኛ ጀማል ካሾጊ ጉዳይ አሁንም ድረስ መነጋገሪያ ነው።ያም ሆኖ ቦክሰኛው ጆሹአ በሳውዲ አረቢያው የቡጢ ፍልሚያ ወቅት የጀማል ካሾጊን ግድያ አዘዋል በሚል ሲ አይ ኤ ከፈረጃቸው የሳውዲው ልዑል ሞሐመድ ቢን ሳልማን ጋር ፎቶ በመነሳት በማህበራዊ መገናኛዎች መልቀቁ ውድድሩ በሳውዲ ከመካሄዱ በበለጠ ብዙ ቁጣን የቀሰቀሰ ነበር።ከዓመት በፊት ሁለተኛው የአውሮፓ ጨዋታዎች በቤላሩስ መዲና ሚኒስክ መካሄዱ ይታወሳል።ከአራት ዓመት በፊትም ይህ ውድድር በአዘርባጃን መዲና ባኩ ተካሂዶ ነበር።በሩሲያ የ2018 የዓለም ዋንጫን ጨምሮ በርካታ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ተካሂደዋል።በነዚህ አገራት የተጋነነ ባይሆንም ከሰብዓዊ መብት አያያዝ ጋር በተገናኘ ጥያቄዎች የሚነሱ በመሆናቸው አገራቱ ስፖርትን ለፖለቲካ ገፅታ መገንቢያነት ተጠቅመውታል የሚል ወቀሳ ይነሳል።ወደፊትም ቤጂንግ 2022 የበጋ ኦሊምፒክን የምታዘጋጅ ከተማ እንደመሆኗ በቻይና ሰሜን ምዕራብ ክፍል በዢንጃንግ የሚኖሩ የሙስሊም ማህበረሰቦች ላይ ከሚደርሰው የሰብዓዊ መብት ረገጣ ጋር ተያይዞ አወዛጋቢ ነገሮች መፈጠራቸው እንደማይቀር ተንታኞች ከወዲሁ ስጋታቸውን ይገልፃሉ። በተመሳሳይ ዓመት ከዚሁ ከሰብዓዊ መብት አያያዝ ጋር የምትታማው ኳታር የዓለም ዋንጫን ታስተናግዳለች። ሚድል ኢስተርን ኒውስ የተባለ ተቋም ያወጣው ሪፖርት እንደሚያመለክተው 1400 ስደተኞች ኳታር በምታስገነባቸው ስቴድየሞች ስራ ላይ እያሉ በችልተኝነት ሕይወታቸው አልፏል። ኳታር ምናልባት የተሳካ የዓለም ዋንጫ ካስተናገደች ግን ይህ ሁሉ ሊረሳ ይችላል።ኳታር ከሰብዓዊ መብት አያያዝ ጋር በተገናኘ በዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ዘንድ የጎደፈ ስሟንና ገፅታዋን ለመገንባት ታላላቅ ስፖርታዊ ውድድሮች በስፋት እያዘጋጀች የምትገኝ ሲሆን፣ የአገሪቱ ባለሃብቶችና መንግስት በአውሮፓ ታላላቅ ሊጎች ክለቦችን ከፍተኛ ገንዘብ በማውጣት ሲገዙ ማየት እየተለመደ መጥቷል።አገሪቱ እኤአ የ2027 መላው ኤሽያ ጨዋታዎችን ለማዘጋጀት ከሌሎች የአካባቢው አገራት ጋር ጨረታ ውስጥ የገባች ሲሆን ይህንኑ ውድድር ከሦስት ዓመታት በኋላ በ2030 ለማዘጋጀት ፅኑ ፍላጎት እንዳላት መግለጿ ይታወቃል።ይህንንም የዲፕሎማሲ ቀውስ ውስጥ ከገባችው ጎረቤቷ ሳውዲ አረቢያ ጋር ጡንቻ ለመለካካት ያደረገችው እንደሆነ ተቺዎቿ ደጋግመው ያነሱታል፡፡ሳውዲ አረቢያና ኳታር የ2030 የመላው ኤሽያ ጨዋታዎችን ለማዘጋጀት ጨረታ ውስጥ ከገቡ በኋላ የዓለም አቀፉ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ለኤሽያ ኦሊምፒክ ምክር ቤት አገራቱ በሰብዓዊ መብት ላይ ያላቸውን መጥፎ ስም በተግባር አሻሽለው እስካልተገኙ ክልከላ እንዲያደርግ መጠየቁ ይታወቃል፡፡ከወር በፊት ኳታር ይህን ውድድር ማስተናገድ የአገሪቱ ቀዳሚ ትኩረት መሆኑን የገለፀች ሲሆን ዋነኛ ተቀናቃኟ የሆነው የሪያድ መንግስትም ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ትኩረት ሰጥተው ሲዘግቡ ቆይተዋል። በነዳጅ ሃብት የበለፀጉት ሁለቱ የመካከለኛው ምስራቅ አገራት የዲፕሎማሲ ቀውስ ውስጥ መግባታቸውን ተከትሎ ድንበሮቻቸውን የዘጉ ቢሆንም ከአስር ዓመታት በኋላ የሚካሄድ የስፖርት ውድድርን ጡንቻ መለካኪያ ማድረጋቸው ትዝብት ላይ ጥሏቸዋል፡፡የኤሽያ ኦሊምፒክ ምክር ቤት ከሳምንት በፊት በሙስካት ባደረገው ጠቅላላ ጉባዔ የሁለቱን አገራት ውድድር የማዘጋጀት ፉክክር ምላሽ ለመስጠት መፍትሄ ያለውን ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል። በዚህም ዶሃ የ2030ን መላ ኤሽያ ጨዋታ እንድታዘጋጅ የወሰነ ሲሆን ከአራት ዓመት በኋላ በ2034 የሚካሄደውን ተመሳሳይ ውድድር ሪያድ እንድታዘጋጅ መርጧል። እዚህ ውሳኔ ላይ ለመድረስ የኤሽያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዘዳንት ሼክ አሕመድ አል ፋሃድ አል ሳባህ፣ ሁለቱንም አገራት ሊያስማማ ይችላል ብለው ባሰቡት መንገድ መሰረት በጠቅላላ ጉባዔው ብዙ ድምፅ ያገኘ አገር ቀድሞ ውድድሩን እንዲያዘጋጅ ማድረጋቸው ታውቋል። ውሳኔው ሁለቱን አገራት ያስማማል ተብሎ ቢታመንበትም በምርጫ ወቅት በተፈጠረ የቴክኒክ እክል ድራማ ሳይሰራ እንዳልቀረ መረጃዎች መጠቆማቸው ይታወቃል፡፡ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የዓለም መንግስታት በስፖርት ውስጥ እጃቸውን እንዳያስገቡ ፍላጎቱን ከመግለፁ ባሻገር አገራት በበጎም ይሁን በመጥፎ ጎኑ ስፖርትን እንዴት የፖለቲካ መጠቀሚያ ከማድረግ እንደሚቆጠቡ ያስቀመጠው ግልፅ አቅጣጫ የለም። ወይም መንግስታት ለፖለቲካ ፍጆታ እጃቸውን ከስፖርት በምን መልኩ መሰብሰብ እንዳለባቸው የመቆጣጠሪያ ቁልፉን ያገኘ አይመስልም። በዓለም አቀፍ መድረኮች በሚሊየን የሚቆጠሩ አትሌቶችም ቢሆኑ እንደየአመለካከታቸው የፖለቲካ፣ የሐይማኖትና የዘረኝነት መልዕክትን ከማስተላለፍ የሚቆጠቡበትን መንገድ ለመቆጣጠር እንደሚከብደው የበርካቶች እምነት ነው።
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=38578
[ { "passage": "በእግር ኳሱ የሚስተዋለው ችግር ካልታረመ ውድድርን እስከ ማቆም የደረሰ እርምጃ ሊወሰድ እንደሚችል ሚኒስቴሩ አስጠነቀቀ። በቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማኅበር አዘጋጅነት ለሁለት ቀናት «የስፖርት ጨዋነት ምንጮች» በሚል መሪ ቃል ከሚያዚያ 14 እስከ 15 ቀን 2011 ዓ.ም የምክክር ጉባዔ በሸራተን ሆቴል ተካሂዷል። የባህል ቱሪዝምና ስፖርት ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው እንደተናገሩት፤ በሀገራችን በስፖርታዊ ሁነቶች ላይ ስፖርታዊ ጨዋነት ሲጓደልና በርካታ ያልተገቡ ድርጊቶች ሲፈጸሙ እየተስተዋለ ይገኛል። በተለይ በእግር ኳሱ ከደጋፊዎች ጋር ተያይዞ የሚስተዋለው መስመር የለቀቀ ባህርይ እየተስተዋለ ነው፡፡ ችግሩ ካልታረመ ውድድርን እስከ ማቆም የደረሰ እርምጃ ሊወሰድ ይችላል። እንደ ዶክተር ሂሩት ገለጻ ፤ ስፖርት ለሰላም መሆኑ\nቀርቶ ውድድሮች ዘርንና ማንነት መሰረት ባደረገ መልኩ የግጭት ምንጭ እየሆኑ ይገኛሉ። ስፖርት አለ በተባለ ቁጥር ሰው መረበሽ የለበትም። ህዝቡ ተረጋግቶ መኖር መቻል አለበት። ህብረተሰቡ ጨዋታ አለ በተባለ ቁጥር ለከፋ ስነ ልቦና ረብሻ መዳረግ የለበትም፤ አይገባውምም። ስለዚህ በእግር ኳሱ የሚታየው ስፖርታዊ ጨዋነት ችግር እስከሚስተካከል ውድድሩን እስከማቆም የሚደርስ እርምጃ ሊወሰድ የሚችል ይሆናል። ስፖርት ለወንድማማችነት የሚለው ብሂል ተረስቶ፤ በስፖርት ሁነቶች ላይ አጀንዳዎች እየተፈጠሩ እርስ በእርስ ወደ መጠቃቃት የመግባት ሁኔታዎች በስፋት እንደሚስተዋሉ አመልክተዋል። በስፖርት ማህበረሰቡ መካከል መጠራጠርና ጥላቻን ከመዝራት ባሻገር ኢትዮጵያዊ ባህልን፣ እኛነታችንን የሚያዋርድና የስፖርቱን እድገት የሚያቀጭጭ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ ረገድ ክለቦችና ደጋፊ ማህበራት ሰፊ ስራ መስራት አለባቸው። በተለይ ክለቦችና የደጋፊ ማህበራትን የሚመሩ አካላት ለሚመሩት ወገን አርዐያ ሆነው መገኘት እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል።«ጨዋ ተጫዋች ከጨዋ አሰልጣኝ ይፈጠራል፤ ጨዋ ደጋፊ ከጨዋ የደጋፊ ማህበራት፣ ክለብና የክለብ አመራር ይፈጠራሉ። ወጣቱ የሚማረው በዙሪያ ከሚታዩት ነባራዊ ሁኔታዎች በመሆኑ አመራር ላይ የምትገኙ አባላትና አካላት ተነባቢ መጽሀፍት መሆናችሁን አውቃችሁ መልካም አርዐያ በመሆን ቆርጣችሁ ልትነሱ ይገባል። ባለድርሻ አካላትም በመመካከርና በመወያየት ችግሩን መፍታትና እልባት ለመስጠት መስራት ይገባል» ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። የብሄራዊ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳይያስ ጂራ በበኩላቸው፤ ‹‹እግር ኳሱ የሌላ ነገር አጀንዳ መናኸርያ ከማድረጋችን ባሻገር ቂም እያወረስን እንገኛለን። እከሌ ሲያሸንፍ ከስፖርት መርህ ውጭ እከሌ ዘር ተሸነፈ፣ አሸነፈ በሚል ጤናማ ያልሆነ አስተሳሰብ ላይ ደርሰናል። ከስፖርታዊ ጨዋነት መጓደል የተነሳ ሙሉ ጤና ይዞ መጥቶ ጤናውን አጉድሎ የሚመለስበት ጊዜ ላይ ደርሰናል›› ብለዋል። እንደ አቶ ኢሳያስ ገለጻ ፤ ችግሮችን ለመቅረፍ ጥረት\nእየተደረገ ቢሆንም ይህ በቂ አይደለም። እግር ኳሱን ከዚህ ስፖርታዊ ካልሆነ ተግባር ለመታደግ እንዲህ አይነት ውይይቶች ሊጎለብቱ ይገባል ። የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ፕሬዝዳንት አቶ አብነት ገብረመስቀል ፤ ‹‹በሀገራችን እግር ኳስ ውስጥ ሥርዓት አልበኝነት እግር ኳሱን እየጎዳው በመሆኑ በርካታ የስፖርት ቤተሰቦችን ከስፖርት ማዘውተሪያ እያራቀ ይገኛል። በጊዜ መስራት የሚገባውን የቤት ስራ ባለመስራታችን ችግሩ እየተባባሰ መጥቶ በዘር ፣ በጎሳ፣ በሃይማኖት እና በፖለቲካ አመለካከት ያተኮሩ ልዩነቶች እዚም እዛም እየታዩ ይገኛሉ። ስለሆነም ይህ እየተባባሰ የመጣውን ችግር ለመቅረፍ የውይይት መድረኩ የራሱ ድርሻ አለው የሚል እምነት አለኝ» ብለዋል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 16/2011በ", "passage_id": "70f6c6e6c5695a4670b36a2f580f32b9" }, { "passage": "የኢትዮጵያ እግር ኳስ በደጋፊዎች መካከል ለሚቀሰቀስ ግጭትና እሱን ተከትሎ ለሚፈጠር ጩኸት ባይተዋር ባይሆንም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሚስተዋሉ ክስተቶች ከስፖርትም በዘለለ የአገሪቱን ፖለቲካዊ ነባራዊ ሁኔታ እያንፀባረቁ መጥተዋል። የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ባለፈው ሰኞ የ2011 በጀት ዓመትን አፈፃፀም ሪፖርት ለተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡበት ወቅት ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሳላቸው ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡ የፖለቲካው ትኩሳት ስቴድየም ሰተት ብሎ መግባቱን መስክረዋል። ከዚህ ቀደም በመሪዎች ደረጃ የተለመደ አለመሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአጠቃላይ በስፖርቱ ጉዳይ ማብራሪያ መስጠታቸው በራሱ የሚያስመሰግናቸው ነው። ይሁንና ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአገሪቱ እግር ኳስ ዙሪያ ያሉትን ቁስሎች ነካክተው አለፉ እንጂ ቁስሉን አፍረጥርጦ የሚድንበትን አቅጣጫ አላስቀመጡም። ከአገሪቱ እግር ኳስ ጋር በተያያዘ ከስቴድየም ግጭቶች በተጨማሪ ያሉትን አንገብጋቢ ችግሮች ጥልቀት በተለያዩ ማዕዘኖች መመልከት መንግስት አፋጣኝ መፍትሄ ማስቀመጥ እንደሚገባው ይረዳል ተብሎ ይታመናል። የአገራችን እግር ኳስ ውስብስብ ችግሮች የሞሉበት እንደመሆኑ መጠን ሁሉንም በስፋት ለመመልከት ከባድ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመጠኑም ቢሆን ጠቅሰው ያለፏቸው ሁለት አንኳር ነጥቦች የስቴድየም ግጭትና ክለቦች በመንግስት ላይ ያላቸውን የምጣኔ ሀብት ጥገኝነት እንዲህ በቀላሉ መታለፍ የሌለባቸውና አፋጣኝ ፈውስ የሚሹ ቁስሎች በመሆናቸው የችግሮቹን ስፋትና ጥልቀት መመልከት ተገቢ ነው። የስቴድየም ሁከትና ግጭትበ2009 ዓ.ም በርካታ ቁጥር ያለው የስቴዲየም ሁከት በተለይም በፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ቢከሰቱም ከብጥብጦቹ ጀርባ እግር ኳስን የሚሻገሩ ገፊ ምክንያቶች እምብዛም እንዳልነበሩ ይጠቀሳል። ከዚያ ወዲህ ግን በልዩ ልዩ ምክንያቶች የሚለኮሱ የስቴድየም ግጭቶችና ረብሻዎች ቁጥር አይሏል።በ2010 የውድድር ዓመት ሐዋሳ፣ ድሬዳዋ፣ አዲግራት፣ ጅማና ወልዲያ ከተሞች ውስጥ የስቴድየም ሁከትና ግጭቶች ተበራክተው እንደነበር ይታወሳል። በተለይም በውድድር ዓመቱ በወልዲያ ስፖርት ክለብና በመቐለ ሰብዓ እንደርታ መካከል ሊደረግ የነበረው የእግር ኳስ ጨዋታ ከመጀመሩ ከሰዓታት በፊት በሁለቱ ቡድኖች ደጋፊዎች መካከል በተቀሰቀሰው ግጭት ህይወት የጠፋ ሲሆን፣ የንብረት ዘረፋና ውድመት ተከስቷል። በዕለቱም ማገባደጃ ላይ በመቐለ ከተማ መንገዶች ላይ ክስተቱን ለመቃወም በርካታ ሰዎች ወጥተው እንደነበር አይዘነጋም። ጨዋታው ካለመካሄዱ በተጨማሪም የግጭቱ አሻራ እስከ ቀጣይ ቀናት ሲሻገርና ከእግር ኳሳዊ ምክንያት ይልቅ ፖለቲካዊ አንደምታው ሚዛን ሲደፋ ታይቷል። በወቅቱ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት የነበሩት አቶ ጁነዲን ባሻ ክስተቱ ከእግር ኳስ የሚሻገር ገፅታ እንዳለው ተናግረው ነበር።የ2010 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሃ ግብር ከረብሻዎች ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በተለያዩ ክለቦች ላይ የጣለው ቅጣት ግማሽ ሚሊዮን ብር ገደማ መሰብሰብ መቻሉ ግጭቶች በምን ያህል ደረጃ እንደተበራከቱ ማሳያ ነው። በእንቁላሉ ጊዜ ያልተቀጣው እግር ኳስ ዛሬ ላይ ከፖለቲካም በላይ ጦዞ ለፀጥታ አስከባሪዎች ፈተና ከመሆን አልፎል እንደ አገርም ስጋት የሆነበት ደረጃ ላይ ደርሷል። ሰላም በራቃቸው የስፖርት ማዘውተሪያዎች መደበኛ የውድድር መርሐ ግብሮች መተማመኛ ማግኘት እየቻሉ አይደለም። በክልል የሚካሄዱ ጨዋታዎች በፖለቲካ ትኩሳት ሳቢያ ተጨማሪ ራስ ምታት እየሆኑ መምጣታቸውን በተለይም በዚሁ የውድድር ዓመት ለመታዘብ ተችሏል።በስፖርቱ ዓለም የተመልካቾች ነውጠኝነት ምክንያቶች ብዙ መሆናቸውን በስፖርቱ ጥልቅ እውቀት ያላቸው ባለሙያዎች ሲናገሩ ይደመጣል። ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ ወይንም ምጣኔ ሀብታዊ ብሶቶች ስቴዲየም ላይ ሊያጠሉ እንደሚችሉም ይታመናል። በኢትዮጵያ እግር ኳስን የታከከ ግጭትና ሁከት ሲከሰት የመጀመሪያው ባይሆንም አሁን ቀይ መስመር እያለፈ ይገኛል። የቅርብ ጊዜ ክስተቶችን ስናጤን ደግሞ ከእግር ኳስ ባሻገር ከነዚህ ምክንያቶች ሁሉ ለስፖርት ጠንቅ የሆነ የፖለቲካ አጀንዳ መኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ራሳቸው አስተውለውታል። እግር ኳስ ማኅበረሰባዊ መሰረት ከሌለው በስተቀር የጠነከረ የእኔነት ስሜት ሊፈጥር አይቻለውም የሚሉ ተንታኞች ፤ ክለቦች ከማኅበረሰባዊ መሰረታቸው በዘለለ ብሔር ተኮር መልክን እየተላበሱ የመምጣታቸው አዝማሚያ አደገኛ መሆኑ የበርካታ ስፖርት ቤተሰቦች እምነት ነው።ክለቦች ሲቋቋሙ ወይንም ሲዋቀሩ አካባቢያዊ መገለጫ ወይንም ከተማዊ ስያሜ ሊኖራቸው ቢችልም ከብሔር፣ ከዘር ወይንም ከሃይማኖት ጋር በተቆራኘ መልኩ መደራጀት ክልክል መሆኑን የስፖርት ኮሚሽን የስፖርት ማኅበራት ማደራጃ መመሪያ አንቀፅ 50 ቁጥር 2 ይገልፃል። ነገር ግን ባለፉት ዓመታት ብቻ ፌዴሬሽኑ በሚያስተዳድራቸው ሊጎች የብሔር ስም የተቀጠላላቸው በርካታ ክለቦች ውድድር እያደረጉ ይገኛሉ። እግር ኳሱ ከአንዳንድ ሁከቶች አልፎ እጅግ ወደተደራጀ ነውጠኛነት እያመራ ስለመሆኑ ለማንም የተደበቀ አይደለም። ቀስ በቀስም የቡድናዊ መንፈስ እየተጓዘ ነው። ራሳችንን መከላከል እና ማዘጋጀት አለብን በሚል ደጋፊዎች ራሳቸውን ማደራጀት ከጀመሩ የሚያሰጋ ዓይነት እውነታ ሊፈጠር እንደሚችል ከወዲሁም እየተመለከትን ነው።በደጋፊዎች መካከል የእኔነቱ መንፈስ ከሮ ከኳስ ወዳጅነት አፈንግጦ በብሔርተኝነት ጎዳና መጓዝ ተጀምሯል። ከዚህ ቀደም ብጥብጡ ተጀምሮ የሚያልቀው ስቴዲየም ነው፤ ከዚያ አያልፍም። አሁን አሁን እየታየ ያለውን ግን ማብራሪያ የማይፈልግ የአደባባይ ሃቅ ነው። ክለቦች የማንነት ማግነኛና የራስ ኩራት መገለጫ መድረኮች እየሆኑ የመምጣታቸውን ሃቅ በየአካባቢው እየጎመራ ከመጣው ብሔርተኛነት ጋር የሚያስተሳስሩትም ጥቂት አይደሉም። ክለቦች መጠሪያው ባይኖራቸውም ከሚመጡበት ክልል ጋር ተያይዞ የእገሌ ብሔር ነው የሚል እምነት አሳድረዋል። ከዚህም በተጨማሪ ክለቦች የተለያዩ የአገሪቱን ክልሎች እንደሚወክሉ መታሰቡ፤ ክልሎች ብሔርን መሰረት አድርገው እንደመዋቀራቸው ብሄርን እንደሚወክሉ ወደመታሰብ አድጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ ፌዴሬሽኑ መስራት እንዳለበት ጠቁመዋል። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እንደ ብሔራዊ ተቋም በሙሉ እግሩ ረግጦ መንቀሳቀስ እየቻለ እንዳልሆነ በግልፅ እየታየ ነው። ፌዴሬሽኑ ከውይይት የዘለለ ፋይዳ ያለው ነገር እየሰራ እንዳልሆነ የሚጠቁሙ የስፖርት ቤተሰቦች ከዚህም በኋላ ችግሩን ይቀርፋል የሚል እምነት ማሳደር ተቸግረውበታል። መንግስት ይህን ስጋት ከተመለከተ ‹‹ጣልቃ የሚገባው ምን እስኪፈጠር ነው?›› የሚሉ ወገኖች መንግስት በእግር ኳሱ ጉዳይ ማሳሰቢያ ከመስጠት አልፎ ውሳኔ ማስተላለፊያ ትክክለኛው ወቅት ላይ እንደሆነ ፅኑ እምነት አላቸው። ቅጥ ያጣው የክለቦች የምጣኔ ሃብት ብክነትበማለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ የአገራችን ክለቦች ምጣኔ ሀብት ምን ያህል በመንግስት ጫንቃ ላይ እንደተንጠለጠለ ተናግረዋል። እነዚህ ክለቦች የመንግስት የምጣኔ ሀብት ጥገኛ ከመሆናቸው ባሻገር ቅጥ ያጣው የገንዘብ ብክነታቸው በጥልቀት ታይቶ ርምጃ ሊወሰድበት እንደሚገባ መናገር አያስፈልግም። መንግሥት ለእግር ኳሱ የሚመድበው በጀትና የተጫዋቾች ክፍያ ነባራዊውን የአገር ኢኮኖሚ ያላገናዘበ፣ የክለቦች የፋይናንስ ሥርዓት የሌለበት፤ ዘመናዊ የእግር ኳስ አመራርና አደረጃጀት የሌለበት ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ሊጉ በተለመደው መንገድ እንዲቀጥል መፍቀድ የአገርና የሕዝብ ገንዘብ በከንቱ ሲባክን እንደመመልከት ይቆጠራል።ብዙዎቹ ክለቦች ቋሚ ገቢ የሌላቸው ሲሆኑ ከከተማ አስተዳደሮችና በመንግሥት ተቋማት በቀጥታ በጀት የሚመደብላቸው ናቸው። የተጫዋቾች ዝውውርና ሌሎች ክፍያዎቻቸውም ከዚሁ በጀት ላይ የሚታሰብ ሲሆን የሊጉ ተወዳዳሪዎች በየዓመቱ ከ30 እስከ 80 ሚሊዮን ብር የሚያንቀሳቅሱበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል። የተጫዋቾች የዝውውር ገንዘብ በየዓመቱ እየናረና እያደገ መምጣቱን ተከትሎም በአማካኝ ከ50 እስከ 100 ሺ ብር ወርሃዊ ደመወዝ ከአንዱ ክለብ ወደ ሌላኛው እየተዘዋወሩ ይገኛሉ። ዘንድሮ እንኳን በተጫዋቾች የዝውውር መስኮቱ አማካኝ ገንዘብ 100 ሺ ብር ሲሆን አነስተኛው 25 ሺ ብር ነው። አንድ ክለብ በዓመቱ በሚያስፈርማቸውና ውላቸውን የሚያድስላቸው የውጭና የአገር ውስጥ ተጫዋቾች ከአስር እስከ አስራ ሁለት ቢገመቱ፤ ሃያ ሚሊዮን ብር በተጫዋቾች ዝውውር ብቻ እንደሚያወጣ መገንዘብ ይቻላል። ክለቦች ከመንግስት በጀት ተላቀው የራሳቸውን ገቢ ማመንጨት አልቻሉም። የገቢ መንገዶች እየቀነሱ ወጪያቸውም ከዚህ በኋላ ይበልጥ እየተመነደገ እንደሚሄድ ከሁኔታዎች ተነስቶ ቢተነበይ ደግሞ ችግሩ ይበልጥ ጥርስ ያወጣ ይመስላል። የፕሪምየር ሊጉ ከከተማ ከተማ ተዟዙሮ የመጫወት መርሐግብር ከሊጉ ተሳታፊ ክለቦች መልክዓምድራዊ አቀማመጥ መራራቅ ጋር በተያያዘ ወጪያቸው በዚያው ደረጃ የሚደፈር ባይሆንም በድሃው ሕዝብ ገንዘብ እየተደፈረ ይገኛል።ከሁለት ዓመት በፊት አንድ የአዲስ አበባ ክለብ ለሊጉ ውድድር አንድም ጊዜ ወደ ትግራይ ክልል አይጓዝም ነበር። ዘንድሮ ግን አራት ጊዜ መጓዝ ግድ ይለዋል። ባለፉት ሦስት የውድድር ዘመናት በየዓመቱ አንዳንድ የአዲስ አበባ ክለቦች ከሊጉ መውጣታቸውን ተከትሎ (አዲስ አበባ ከተማ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ኢትዮ ኤሌክትሪክና ደደቢት) ከአምና እና ከካቻምና ይልቅ የአዲስ አበባ ክለቦች ለበለጠ ጊዜያት ወደ ክልሎች እየተጓዙ ለመጫወት ተገድደዋል። የክልሎችም ወደ አዲስ አበባ እየተጓዙ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።ክለቦቹ ብዙ በተጓዙ ቁጥር ወጪያቸው እየጨመረ መሄዱን ማስተዋል ይቻላል። በቀጣይ ዓመታትም ፕሪሚየር ሊጉን የሚቀላቀሉ ሦስት አዳዲስ ክለቦች ከአዲስ አበባ ውጪ መሆናቸው ከግምት ውስጥ ማስገባት ያስፈልጋል። ይህ ደግሞ ለብዙሃኑ የመንግስት በጀት ላይ የተንጠለጠሉ የክልል ክለቦች ችግሩ ይበልጥ ብርቱ እንዲሆን ያደርገዋል።እነዚህ ክለቦች የህዝብ ሀብት የሚፈስባቸው እንደመሆናቸው «ሚሊዮኖችን ዘርተው ምን አጨዱ?» ብለን ብንጠይቅ መልሱ በቀላሉ ምንም ይሆናል። አሳዛኙ ነገር በእግር ኳሱ ይህን ያህል ገንዘብ እየተረጨ ከፋይናንስ ዕድገቱ ጋር ኳሱ አብሮ መራመድ ይቅርና በግማሽ መንገድ እንኳን ሊከተለው አቅሙ አለመፍቀዱ ነው። ከአስር ጨዋታ ዘጠኙ አንድ ለዜሮ በሆነ ውጤት በሚጠናቀቅበት አሰልቺ ሊግ፣ በሰላሙ ጊዜ እንኳን የስፖርት ቤተሰቡ ለመዝናናት ካምቦሎጆ ገብቶ ፀያፍ ስድብ ሰምቶ ከመመለስ የዘለለ ያገኘው ነገር የለም። ይህ ሁሉ የገንዘብ ክምር ብሔራዊ ቡድኑ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳታፊ አገራት ከአስራ ስድስት ወደ ሃያ አራት አድጎ እንኳን ተወዳጁ መድረክ ጋር ሊያደርሰው የሚችል አቅም አልፈጠረለትም። የዘወትር ጩኸት ለሆነው የታዳጊ ወጣቶችና ተተኪዎች ላይ ገንዘቡ ባክኖ ቢሆን ኖር እሰየው ነበር። ኳስና መጫወቻ ጫማ አጥተው እግራቸው እየቆሰለ ለስፖርቱ ፍቅር ብቻ ድንቅ ብቃት ይዘው በየሰፈሩ የሚባክኑ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ታዳጊዎች ባላት አገር የነገ ተስፋቸው በደላላና በጥቅም ሰንሰለት በተሳሰሩ ግለሰቦች ጨልሟል። የሕዝብ ገንዘብ በገፍ የሚፈስባቸው ክለቦች ግን ከሌሎች አፍሪካ አገራት በወር ሦስት መቶ ሺ ብር ደመወዝ እየተከፈሉ ከኛ አገር ታዳጊዎች የማይሻል ተጫዋች ማስመጣትን ፋሽን አድርገውታል። ይህ ሁሉ ገንዘብ ባክኖ የሰናፍጭ ቅንጣት ታህል የእግር ኳስ ፍላጎት ተሳክቶ ቢሆን የስፖርት ቤተሰቡ አሜን ብሎ በተቀበለም ነበር። ምክረ ሃሳብክለቦች በክልሎች ተዟዙረው የሚያደርጉት ጨዋታ ከወጪውም አኳያ ቀድሞውንም ባይደግፉትም ፖለቲካው ባመጣው ጣጣ አንዳንዶቹ እየተዟዟሩ ለመጫወት ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቆይተዋል። እግር ኳሱን ምክንያት በማድረግ የሚስተዋለውን አደገኛ አዝማሚያ መቀነስ የሚቻለው ውድድሮችን በዞን ማከናወን ሲቻል ብቻ እንደሆነ በርካታ የስፖርት ቤተሰቦች ያምናሉ። ይህ የሚስተዋለውን አምባጓሮ ከመቀነሱም በላይ ተዟዙሮ በመጫወት ይባክን የነበረውን የክለቦች ፋይናንስ ይታደጋል የሚል ጠንካራ እምነትም በብዙዎች ዘንድ አለ። ፌዴሬሽኑ ግን የዚህን የውድድር ዓመት ቀሪ ሦስት ጨዋታዎች በጊዜው ማጠናቀቅ ተስኖት እንኳን በቀጣይ ዓመት የፕሪሚየር ሊጉን ፎርማት በተመሳሳይ መንገድ የመቀጠል እንጂ የመለወጥ አዝማሚያ አይታይበትም። መንግስት ከአደረጃጀትና ከክለቦች የፋይናንስ ሥርዓት ጋር በተያያዘ እግር ኳሱን ውስጥ ቢገባ ፊፋ ቅር እንደማይሰኝ ህጎቹን ጠንቅቀው የሚያውቁ ይመሰክራሉ። ፌዴሬሽኑ ቀጣዩን የውድድር ዓመት በተመሳሳይ መልኩ እንዳይጀምር መንግስት አንድ ጠንካራ ትዕዛዝ ማስተላለፍ ካለበት ጊዜው አሁን ነው። የስቴድየም ሁከቶችን አደብ ማስያዝ ካለበትም ሙሉ በሙሉ ማጥፋት ባይቻል እንኳን በከፍተኛ ደረጃ እንዲቀንስ አደረጃጀቱን የቤት ስራው አድርጎ መያዝና አስፈላጊውን ማስተካከያ ማድረግ እንደሚኖርበት የበርካቶች ምክር ነው። ይህ ካልሆነ ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደተናገሩት ‹‹ወጣትም ገንዘብም እየከሰርን›› ላለመሄዳችን ማስተማመኛ የለም።አዲስ ዘመን ሰኔ 29/2011ቦጋለ አበበ", "passage_id": "874c954e22d3021b2e9ccc277693bdc3" }, { "passage": "ስፖርት የማይካተትበት ዘርፍ የለም፤ ቴክኖሎጂም እንዲሁ።ሁለቱም ዘርፎች በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እንዲሁም ሌሎች ጉዳዮች ጋር በመቆራኘት ህይወትን በማቅለል ለዘመናዊው ዓለም የጎላ ሚና በመጫወት ላይ ይገኛሉ።ከዚህ ባለፈ አንዱ ለሌላኛው ቁልፍ ጉዳይ መከወኑም አልቀረም።በልምድ ይካሄድ የነበረው ስፖርት በሳይንስና ቴክኖሎጂ በመደገፉ፤ ዘመናዊውን ስፖርት ከሳይንስና ቴክኖሎጂ ለይቶ ማሰብ በዚህ ወቅት አዳጋች ሆኗል።በቴክኖሎጂ የታገዙ ፈጠራዎች መበራከትም የስፖርተኞችን ብቃት በማሳደግ እንዲሁም የስልጠና ሂደቱን በማቃለልም ዘርፉን ትርፋማ ማድረግ ችሏል።የዘመኑ ስትንፋስ የሆነው ቴክኖሎጂ በ19ኛው ክፍለ ዘመን ስፖርትን ተቀላቅሎ በቁጥር የማይተመኑ ለውጦችን አስገኝቷል።በስፖርት ትጥቅና የስልጠና ቁሳቁስ፣ ውድድሮችን በቀጥታ ለደጋፊዎች በማስመልከት፣ በውድድር ሜዳዎች ተገኝቶ ለመመልከት ትኬት የመቁረጫ አማራጭ፣ የስፖርት ሜዳዎች ሁለገብና ዘመናዊ እንዲሆኑ፣ ከውድድር አጨራረስ እንዲሁም ዳኝነት፣ የስፖርተኞችን መረጃና ውጤትን በመመዝገብ፣ ከዚህ ቀደም የነበረን ውድድርና ብቃት ለመገምገም፣ ስለ ስፖርቱ የሚወጡ አዳዲስ መረጃዎችን ለመከታተል፣ ስፖርተኞችን ከደጋፊዎቻቸው በማገናኘት፣ ንጹህ ስፖርትን ለማካሄድና በስፖርት የሚፈጸሙ የረቀቁ ወንጀሎችን ለማጣራት (ከአበረታች ቅመሞች ጋር በተያያዘ)፣ ከጉዳት ለማገገም (ስፖርት ህክምና)፣ በትልልቅ ጨዋታዎችና ውድድሮች ከአየር ሁኔታ ጋር በተያያዘ ችግር እንዳይገጥም እንዲሁም ዘርፈ ብዙ ግኝቶችንም አበርክቷል። በዋናነት እነዚህ ተጠቀሱ እንጂ ቴክኖሎጂ በእያንዳንዱ ስፖርት ለእያንዳንዱ ሂደት እየተወጣ ያለው አስተዋጽኦ ይዘርዘር ቢባል አዳጋች ነው የሚሆነው።ለአብነት ያህል ግን ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት በጉልህ ከታዩ የቴክኖሎጂ ውጤቶች መካከል በሁለት ተወዳጅ ስፖርቶች የታዩትና የስፖርት ቤተሰቡን ቀልብ የሳቡትን ማንሳት ይቻላል።በአትሌቲክስ ስፖርት በመሮጫ ጫማ ላይ የነበረው የቴክኖሎጂ እገዛ የሰው ልጅ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ማራቶንን ከሁለት ሰዓት በታች በመሮጥ አዲስ ታሪክ እንዲያስመዘግብ አድርጓል።በቪዲዮ የታገዘ ዳኝነት በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ መተግበሩም እስካሁን በእግር ኳሱ ነጥረው ያልወጡ ጉዳዮች እንዲስተዋሉ ያደረጉ ሆነዋል። የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ዓለምን በእጅጉ እያስጨነቀ ባለበት በዚህ ወቅት ደግሞ ቴክኖሎጂ ለስፖርቱ እጅጉን አስፈላጊ መሆኑ በተግባር እየታየ ይገኛል።በተለይ ከስፖርታዊ ውድድሮች መሰረዝና ‹‹ከቤት አትውጡ›› ትዕዛዝ ጋር በተያያዘ ስፖርተኞች እንዲሁም ስፖርት ወዳዶች ቴክኖሎጂን እንደ አማራጭ ይዘውታል።የስፖርት መገናኛ ብዙሃን እንዲሁም ድረ ገጾችም የውድድሮች አለመኖርን ተከትሎ ከዚህ ቀደም የተካሄዱ ውድድሮችን በድጋሚ በማስታወስ ላይ ይገኛሉ።ስፖርተኞች በበኩላቸው በግላቸው የሚያደርጓቸውን እንቅስቃሴዎች በተለያዩ ድረ-ገጾች ለሌላው ህዝብ በማጋራት ላይ ናቸው።አሰልጣኞችም ስፖርተኞች በቤታቸው ሲቆዩ እንዳይዘናጉ በተለያዩ ቴክኖሎጂ አፈራሽ መንገዶች ስልጠናቸውን ቀጥለዋል።የውድድር አዘጋጅ አካላት ደግሞ በአካል ስፖርተኞችን ማፎካከር ባይችሉም በስልኮች ላይ በሚጫን መተግበሪያ ውድድሮችን እያካሄዱ ይገኛሉ።የ ‹‹በቤት ቆዩ›› ቻሌንጆችም በዓለም ላይ እየተበራከቱ መሆኑ በግልጽ የሚታይ ነው። ይህ ሁኔታ በኢትዮጵያም እየተለመደ ያለ ሲሆን፤ ስፖርተኞች፣ ባለሙያዎች፣ የስፖርት ማህበራት እንዲሁም ስፖርቱን የሚመሩ አካላት የብዙሃን መገናኛዎችንና ድረገጾችን በመጠቀም ህዝቡን ተደራሽ እያደረጉ ናቸው።አሰልጣኞችም በማህበራዊ ድረ-ገጾች ከሰልጣኞቻቸው ጋር ግንኙነት ያደርጋሉ። የስፖርትና የስልጠና ባለሙያዎችም የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እንዴት እንደሚከወን ህብረተሰቡን ግንዛቤ እያስጨበጡና እያነቁም ይገኛሉ።የኢትዮጵያን ስም ከገነኑ አትሌቶች እኩል የሚያስነሳው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያም በተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያ አማካኝነት የሩጫ ውድድር እያካሄደ ይገኛል።‹‹ቨርቹዋል ሬይስ›› የሚሰኘው ይህ የውድድር ዓይነት እየተለመደ ያለና በርካቶች ተሳታፊ እየሆኑበትም ይገኛሉ፡፡በወቅታዊው ሁኔታ ስፖርት ለጊዜውም ቢሆን ከአካላዊ እንቅስቃሴ ጋር መለያየቱን ተከትሎም ከስፖርት ቴክኖሎጂ ጋር በተያያዘ የሚሰሩ ድርጅቶች ገበያቸው እየደራ መሆኑም ተስተውሏል።ፎርብስ በዚህ ጉዳይ ላይ የሰራው ዘገባ፤ ስፖርተኞች በቤት ውስጥ ከመቆየታቸው ጋር በተያያዘ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መከወኛ መሳሪያዎች ፍላጎትና ግዢ ጭማሪ አሳይቷል።በእንግሊዝ የሚገኝ አንድ የስፖርት ቁሳቁስ አምራች ከድረ-ገጹ ጋር በነበረው ቆይታ፤ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ባልታየ መልኩ የፈረንጆቹ\n2020 ከገባ በኋላ ጥያቄው መበርታቱን ጠቁሟል።በተለይ የኦሊምፒክ ተሳታፊ አትሌቶች፣ ቡድኖች እና ታዋቂ አትሌቶች ደግሞ ቀዳሚ ፈላጊዎች መሆናቸው ታውቋል። ዘ ኢኮኖሚክስ ደግሞ የዓለም ስፖርት በኮሮና ቫይረስ ምክንያት በወራት ውስጥ ከአካላዊ እንቅስቃሴ ወደ ዲጂታል (በቴክኖሎጂ የታገዘ) መቀየሩን አመላክቷል።ይህ ‹‹ኢ-ስፖርት›› የተሰኘው ውድድር በኮምፒዩተር የሚካሄድ ሲሆን፤ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ የሚያሸልም ነው።በዚህም ምክንያት የተሳታፊዎቹ ቁጥር በእጥፍ እያደገ መሆኑ ተረጋግጧል።ቁጥራዊ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከሆነም፤ እአአ በ2019 የተሳታፊዎች ቁጥር 443 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን፤ ይህም ከ2018 ጋር ሲነጻጸር በ12 ከመቶ ጭማሪ ያሳየ ነው።በዚህ ዓመት ደግሞ በዚህ ጨዋታ ተሳታፊ ከሆኑ ሰዎች አንድ ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱም ታውቋል።አዲስ ዘመን ግንቦት 17/2012 ብርሃን ፈይሳ አጫጭር ዜናአትሌቷ\nእርዳታ አድርጋለች ኢትዮጵያን በኦሊምፒክ፣\nበዓለም ቻምፒዮና፣ በዳይመንድ\nሊግ እንዲሁም በሌሎች\nውድድሮች በ5 እና\n10 ሺ ሜትሮች የሜዳሊያ\nባለቤት ያደረገችው አትሌት\nአልማዝ አያና እርዳታ\nአድርጋለች።አትሌቷ ከባለቤትዋ ጋር\nበመሆን ከአሁን በፊት\nየጀመረችውንና ከ30 በላይ\nየሚሆኑ አቅመ ደካማ\nአዛውንቶችን ለሁለተኛ ጊዜ\nየለገሰች ሲሆን፤ ከ50\nለማያንሱ ገቢያቸው አነስተኛ\nለሆነና ወደፊት ሀገራቸውን\nሊያስጠሩ ለሚጥሩ አትሌቶችም\nእርዳታውን ማበርከቷን የኢትዮጵያ\nአትሌቲክስ ፌዴሬሽን በድረ\nገጹ አስነብቧል።ተረጂዎች እያንዳንዳቸው\nእንዳንድ ካርቶን ፓስታ፣\n5 ሊትር ዘይት እና\n50 ኪሎ ዱቄት አግኝተዋል።ከዚህ\nባሻገር የኮሮና ወረርሽኝን\n(ኮቪድ 19) ለመዋጋት\nበሚደረገው ጥረት የሚውል\n150 ሺህ ብር ለድጋፍ\nአስተባባሪው አምባሳደር ምስጋኑ\nአረጋ አስረክበዋል።አትሌቷ በጥቅሉ\n267ሺ ብር እርዳታ\nነው ያደረገችው።ሁለተኛ ዙር የምገባ መርሃ ግብር ተጀመረ የኢፌዴሪ\nስፖርት ኮሚሽን፣ ከኢትዮጵያ\nአትሌቲክስና እግር ኳስ\nፌዴሬሽኖች እንዲሁም ቢጂአይ\nጋር በመሆን ለአንድ\nወር የሚቆይ የምገባ\nመርሃ ግብር ማካሄዳቸው\nየሚታወስ ነው።አሁን ደግሞ\nለአንድ ወር የሚቆይና\nበአዲስ አበባ ስቴድዮም\nዙሪያ የሚገኙ ችግረኞችን\nየሚያቅፍ ሁለተኛ ዙር\nየምገባ መርሃ ግብር\nበይፋ ተጀምሯል።ምገባውን የኢፌዴሪ\nስፖርት ኮሚሽን፣ ከኢትዮጵያ\nአትሌቲክስና እግር ኳስ\nፌዴሬሽኖች፣ ከኢትዮጵያ ጸረ\nአበረታች ቅመሞች ጽህፈት\nቤት፣ ከወጋገን ባንክ፣\nከቢጂአይ ኢትዮጵያ እና\nከአቶ አብነት ገብረመስቀል\nጋር በመተባበጀር የሚካሄድ\nመሆኑም ታውቋል። የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ በቀጣዩ ወር ይመለሳል\nበኮሮና\nቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት\nየተቋረጡ የሊግ ውድድሮች\nእየተመለሱ መሆኑ ይታወቃል።ከእነዚህ\nመካከል አንዱ የሆነው\nተወዳጁ የእንግሊዝ ፕሪምየር\nሊግም በቀጣዩ ወር\nየሚቀጥል መሆኑን ቢቢሲ\nአስነብቧል።ባሳለፍነው ሳምንት መጀመሪያ\nልምምድ የጀመሩት ክለቦቹ\nከ17 ቀናት በኋላ\nውድድር የሚጀምሩ መሆኑን\nየፕሪምየር ሊጉ ዋና\nስራ አስፈጻሚ ሪቻርድ\nማስተር አረጋግጠዋል።በሊጉ ከሚሳተፉ\n20 ክለቦች ውስጥ ባሉ\nተጫዋቾች በተደረገው የኮቪድ\n19 ምርመራ በሶስት ክለቦች\nውስጥ የሚገኙ ስድስት\nተጫዋቾች ላይ መገኘቱም\nየሚታወስ ነው።አዲስ ዘመን ግንቦት 17/2012", "passage_id": "4a980366ef66ea523c47939ecb1a465e" }, { "passage": "በ1990 ዓ.ም. በአገር አቀፍ ደረጃ የወጣው የስፖርት ፖሊሲ ሕዝቡ በሚኖርበት፣ በሚማርበትና በሚሰራበት አካባቢ ስፖርት እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚገባው ይደነግጋል። ህብረተሰቡ በሚኖርበት፣ በሚማርበትና በሚሠራበት አካባቢ በስፖርት እንቅስቃሴ ተሳታፊ የሚሆንበት መንገድ መመቻቸት እንዳለበት ያስቀምጣል። ከመንግሥት ተቋማት እስከ ታችኛው የኅብረተሰብ ክፍል በየደረጃው ኅብረተሰቡ ለሚሳተፍባቸው መድረኮች ትኩረት በማድረግ ልሂቃን (ኤሊቶች) የሚፈጠሩበት ዕድል እንዳለም ፖሊስው ያመለክታል። በሌላ በኩል አምራች ዜጋ ለመፍጠር፣ የኅብረተሰቡ ማኅበራዊ ግንኙነት የሚዳብርበት፣ ከዚያም ሲያልፍ ዜጎች ጤንነታቸውን ለመጠበቅና ለመዝናናት እንዲሁም አካላቸውን ለማጎልበትና አዕምሯዋቸውን ለማበልጸግ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ታምኖበታል። የስፖርት ፖሊሲውን መሰረት በማድረግ የሕብረተሰቡን ተሳትፎ በማስፋት ረገድ እየተሄደበት ያለው መንገድ አጥጋቢ አለመሆኑ ተደጋግሞ ይነሳል። በመንግስትም ሆነ በህብረተሰቡ በኩል እንደሚነሳው «ሕዝቡ በሚኖርበት፣ በሚማርበትና በሚሰራበት አካባቢ የስፖርት እንቅስቃሴ ማድረግ አለበት»በሚል በፖሊሲ ደረጃ ቢቀመጥም ወደ ተግባር ከመለወጥ አንጻር ከፍተኛ ክፍተት መኖሩ ይታመናል። በተለይ በመንግስትና በግል ተቋማት ህብረተሰቡ በሚሰራበት ቦታ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ እንዲያደርግ እድል በመፍጠር ረገድ የፍላጎትም ሆነ የግንዛቤ ክፍተቶች እንዳሉ በስፖርቱ አዋቂዎች በኩል ይነገራል። በተቋማት የስፖርቱን ማህበራዊም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳን በመረዳት ስፖርታዊ ክንውኖችን የማዘጋጀት ባህሉ በእጅጉ አናሳ መሆኑም አብሮ ይነሳል። መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት በኩል የስፖርቱን ዘርፈ ብዙ ፋይዳ በመረዳት የስፖርት ፌስቲቫል የማዘጋጀት ልምድ ባለቤት የሆኑ ተቋማት በጣት የሚቆጠሩ ናቸው። ከእነዚህ ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳል። የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫሉ ዘንድሮ ለ5ኛ ጊዜ ከመስከረም 26 ጀምሮ ለአስር ቀናት ያክል «የኋላውን እያደስን የወደፊቱን ለመገንባት እንተጋለን »በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ይገኛል። የኮርፖሬሽኑ የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫል በ2002 ዓ.ም እንደተጀመረ መረጃዎች ያመላከታሉ ። ኮርፖሬሽኑ በሚያከናውነው የስፖርት ፌስቲቫል፤ አገር አቀፍ የስፖርት ፖሊሲውን ተግባራዊ ከማድረግ ባሻገር በሰራተኞች መካከል መቀራረብን እንደሚፈጥር ታምኖበታል። የስፖርት ፌስቲቫሉ ጤናው የተጠበቀና አምራች ዜጋን በማፍራት ውጤታማ መሆን እንደሚቻል ማሳያ መሆኑም ተጠቁሟል። የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫል አስተባባሪ አብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጥንፉ ሙጬ፤ የስፖርት ፌስቲቫሉ በአገር አቀፍ ደረጃ የወጣውን የስፖርት ፖሊሲ መሰረት በማድረግ የተጀመረ መሆኑን ይናገራሉ። ህዝቡ በሚኖርበትና በሚሰራበት አካባቢ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በማድረግ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን ማጉላት እንደሚችል መሰረት ባደረገ መልኩ ተቋሙ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑንም ይገልጻሉ። እንደ አቶ ጥንፍ ገለጻ፣ ስፖርት በተለይ ደግሞ በሰራተኞች መካከል እርስ በእርስ እንዲተዋወቁ፣ ጤናው የተጠበቀና አምራች ዜጋን ለማፍራት እንዲቻል፣ የሰራተኞችን አንድነት ለማጠናከር ፋይዳው ግዙፍ መሆኑን ያብራራሉ። በመሆኑም ኮርፖሬሽኑ የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫሉን እነዚህን ውጤቶች መሰረት በማድረግ ትኩረት ሰጥቶ እንደጀመረ ይናገራሉ። «ፌስቲቫሉ በየሁለት ዓመቱ ቢደረግ የበለጠ ዝግጅት ተደርጎ በጠንካራና ባማረ ሁኔታ ማከናወን ይቻላል »በሚል አስተዳደሩ ወስኖ በየሁለት ዓመቱ ሊካሄድ እንደቻለም ያስታውሳሉ። የኮርፖሬሽኑ የቤተሰብ ስፖርት በዚህ መልኩ በመቋቋም ባለፉት አስር ዓመታትን መጓዝ ችሏል። በስፖርት ክንውኑ ተቋሙ ውጤታማ መሆን ችሏል? ስንል ጥያቄ ሰንዝረናል። አቶ ጥንፍ ባለፉት አስር ዓመታት በነበረው ስፖርታዊ ክንዋኔ ተቋሙ ውጤታማ መሆኑን ይገልጻሉ። በመጀመሪያ ደረጃ አመራሩና ሰራተኛው መልካም የሆነ ግንኙነት እንዲፈጥሩ አድርጓል። እያደረገም ይገኛል። በአካልም፣ በአዕምሮም የበለፀገ ሰራተኛና አመራር እንዲኖር አስችሏል። ጤናማ ሰራተኛ በመፍጠር ረገድ ውጤት ማምጣት ተችሏል። መታወቅ ያለበት ያለ ጤናማ ሰራተኛ የኮንስትራክሽን ስራ የሚታሰብ እንዳልሆነም ያብራራሉ። የስፖርት ፌስቲቫሉ ሠራተኛውም ሆነ አመራሩን የበለጠ የሚያቀራርብ፣ ሠራተኛው ትርፍ ጊዜውን አዕምሮውንና አካላዊ ብቃቱን የሚያዳብርበት፣ ለተቋሙ ያለውን ወገናዊነት የሚያሳይበት፣ በሌሎች ፕሮጀክቶች ከሚገኙ ሠራተኞች ጋር ለመቀራረብና ለመተዋወቅ መንገድ እየከፈተ እንደሚገኝ ይገልጻሉ። እንደ አቶ ጥንፍ ማብራሪያ፤ የዘንድሮ መድረክ ከእስከ ዛሬው ለየት የሚያደርገው የተሳታፊነቱን ኮታ ለአመራሩ አንድ ሶስተኛውን በመስጠት ዋና ሥራ አስፈጻሚውን ሳይቀር ተሳታፊ ማድረጉ ነው። ስፖርት ፌስቲቫሉ ለአመራሩና ለሰራተኛው እኩል እድል ከመስጠት ባሻገር፤ በሁለቱ አካላት መካከል መቀራረብ እንዲፈጠርና የበለጠ ቀረቤታን መፍጠር እንዲያስችል ነው። ይህን በተግባርም ለመመልከት ተችሏል። የዘንድሮው ውድድር ሴቶችን የበለጠ ተሳታፊ እንዲሆኑ አድርጓል። በመድረኩ ያለፉት ዓመታት ጉዞ ሴቶች ቡድን አልነበራቸውም፤ ዘንድሮ ሁለት ቡድኖች ተቋቁመው በመረብ ኳስና በጠረጴዛ ቴኒስ ስፖርቶች ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ተደርጓል። «የዘንድሮው ፌስቲቫል ልዩ ገጽታው የለውጥ አስተሳሰቦችን ለማስረጽ ጥረት መደረጉ ነው። በውድድሩ ያሉትን ቡድኖች ስያሜን በዚህ ሁኔታ እንዲቃኙ የተደረገ ሲሆን ስያሜዎቹም አሸናፊ፣ ብቁ፣ ታዋቂ፣ ድንቅ፣ ባለራዕይ እና ተስፋ በሚል እንዲሰየሙ ተደርጓል›› ያሉት አስተባባሪው ከዚህ በተጨማሪም ቀደም ሲል ዘርፎች በቡድን ተደራጅተው እርስ በዕርስ የሚያደርጉት ውድድር እንደነበር ተናግረዋል። አደረጃጀቱ እንደ ኮርፖሬሽን ውህደት ባለማምጣቱ አዲስ አደረጃጀት በመፍጠር ወድድሩ እየተካሄደ ሲሆን፤ በመድረኩ የበለጠ መቀራረብና ተቋማዊ ስሜት መፍጠር እንደተቻለ በውድድሩ የአምስትና ስድስት ቀናት ቆይታ ወቅት ለመታዘብ ተችሏል። የስፖርት ፌስቲቫሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ ተቋማዊ ፋይዳውን እያሳደገ መምጣቱን የ5ኛው የቤተሰብ ስፖርት ውድድር እያሳየም ይገኛል። አቶ ጥንፍ ኮርፖሬሽኑ ግዙፍና በርካታ ፕሮጀክቶች ያቀፈ እንደመሆኑ በስፖርት ፌስቲቫሉ ሁሉም ፕሮጀክቶች ተሳታፊ እንዲሆኑ በመስራት የስፖርቱን ግዙፍ ፋይዳ በተቋሙ ምሉእ እንዲሆን ለማድረግ በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም አስቀምጠዋል። በ5ኛው የኮርፖሬሽኑ የቤተሰብ ስፖርት ሲሳተፍ ያገኘናቸው በኮርፖሬሽኑ የፋሲሊቲ ሰራተኛ የሆኑት አቶ ዜናው ደነቀው በበኩላቸው፤ የስፖርት ክንውኑን እንደ ኮርፖሬሽኑ ሁሉ ሌሎች ተቋማት ተግባራዊ ማድረግ ቢችሉ ያለውን ፋይዳ ይናገራሉ። «በእኛ ተቋም ያለውን ተሞክሮ በሌሎች የመንግስትና የግል መስሪያ ቤቶች ተግባራዊ ማድረግ ቢቻል፤ በአገር አቀፍ ደረጃ ተጠቃሚ መሆን ይቻላል። ከስፖርቱ የሚገኘውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ማግኘት ይቻላል። በተጨማሪም ኢሊት ስፖርተኞች የሚፈሩበትን አጋጣሚ በማስፋት ረገድ የራሱ የሆነ ድርሻ ይኖረዋል። የአገራችንን ስፖርት በማሳደግ ረገድም የመንግስት ተቋማት ድርሻቸውን እንዲወጡ አጋጣሚውን መፍጠር ይቻላል» ሲል ያብራራል። በኮርፖሬሽኑ የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫል ላይ ከአሰልጣኝነት እስከ ዳኝነት የተሻገረ ተሳትፎን ከመጀመሪያው ጀምሮ ሲያደርጉ እንደነበረ የገለፁልን የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ሰራተኛ የሆኑት አቶ አለማየሁ ገብሬ፤ የኮርፖሬሽኑ ተሞክሮን ሌሎች ተቋማት መውሰድ ቢችሉ ያለውን ነጥብ በማሳት ተመሳሳይ ሃሳብ ይጋራሉ። የቤተሰብ ስፖርቱን ከመጠንሰስ እና ቀጣይነት እንዲኖረው ከማድረግ አካያ በተቋሙ የነበሩና ያሉ አመራሮች ትልቅ ድርሻ እንደነበራቸውም ይናገራሉ። የኮርፖሬሽኑ አመራሮች የስፖርት ፌስቲቫሉ ሳይቋረጥ እንዲቀጥል ከማደርግ አኳያ ያሳዩት ቁርጠኝነት በተለይ ደግሞ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ዮናስ አያሌው ትልቅ ስራን መስራታቸውን ያስረዳሉ። አቶ አለማየሁ ዋና ስራ አስፈፃሚው ስፖርታዊ ክንውኑ ቀጣይነት ኖሮት በጠንካራ መስመር እንዲጓዝ ከመስራት ባሻገር፤ በውድድሩ ተጫዋች በመሆን የስፖርቱ ተሳታፊ መሆናቸው የሚያስመሰግናቸው መሆኑን ይገለጻሉ። ስፖርቱ ትኩረት እንዲያገኝ ከማድረግ አኳያም አመራሩ ያሳየው ቁርጠኝነት በሌሎች ተቋማት እንደ አርዓያ ሊወስዱት ይገባል ባይናቸው። ኮርፖሬሽኑም በየሁለት ዓመቱ ይህ የስፖርት ባህል ተጠናክሮ እንዲቀጥል ማድረግ እንደሚገባው ያስቀምጣሉ። በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫል ተሞክሮ በሌሎች መንግስታዊና መንግስታዊ ባልሆኑ ተቋማት መውሰድ ቢቻል ዘርፈ ብዙ ውጤቶች እንደ አገር ማትረፍ እንደሚቻል መመስከር ይቻላል። ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በህብረተሰቡ ዘንድ ትኩረት እንዲሰጠው ፖሊሲ ከመቅረጽ ባሻገር ተግባራዊ እንዲሆን እንደ ኮርፖሬሽኑ ሌሎች ተቋማት መስራት አለባቸው።አዲስ ዘመን  ረቡዕ ጥቅምት 5/2012ዳንኤል ዘነበ ", "passage_id": "6d84cfd7c86d1084995b22e46a54eca8" }, { "passage": "በዓለማችን ላይ\nተወዳጅነትን ያተረፉ ስፖርቶች እንደየ ባህሪያቸው እና እንደሚፈልጉት የማዘውተሪያ ስፍራ አይነት በቤት ውስጥና ከቤት ውጪ (indoor and outdoor) ይካሄዳሉ፡፡ አንዳንድ የውድድር አይነቶች ለምሳሌ የአትሌቲክስ በሁለቱም የመወዳደሪያ ስፍራዎች እንደሚደረጉት ሁሉ በጅምናዚየም ውስጥ ወይም ከቤት ውጪ ብቻ ሊዘወተሩ የሚችሉ የስፖርት አይነቶችም በርካታ ናቸው፡፡በቴክኖሎጂ ድጋፍ\nየሰው ልጅ ኑሮ እጅጉን በረቀቀበት በዚህ ጊዜ ተወዳጅነትን ያተረፉ የስፖርቶች አይነቶችም በተመሳሳይ እያደጉና እየዘመኑ ነው። ይህን ተከትሎ ደግሞ አገራት እንደ አካባቢያቸው ነባራዊ ሁኔታና እንዳላቸው እምቅ አቅም ውጤታማ ሊሆኑ የሚችሉባቸውን ስፖርቶች ለይተው ለስኬታማነት እና ድልን ለመጎናፀፍ ተግተው ይሰራሉ፡፡ አንዳንዶቹ ያላቸውን የአየር ፀባይ አሊያም ልዩ ችሎታ መሰረት አድርገው ይሰራሉ፡፡ ሌሎች\nደግሞ ለረጅም ዘመናት ሲከውኗቸው የቆዩትን ስፖርቶች ሳይበረዙ ዘመናዊ ቅርፅ እንዲኖራቸው በማድረግ ዓለም አቀፍ ይዘት ያላብሷቸዋል፡፡ እነዚህ ከላይ ለማንሳት የሞከርናቸው ስፖርቶች ደግሞ እንደየ ባህሪያቸው የመወዳደሪያ እና የማዘውተሪያ ስፍራቸው ቅርፃቸው የተለያየ ይሆናል፡፡ አንዳንዶቹ የቤት ውስጥ ስፖርት (indoor game) ሲሆኑ ቀሪዎቹ ደግሞ ከቤት ውጪ የሚዘወተሩ (outdoor game) ይሆናሉ፡፡ የረጅም ዓመታት ልምድ\nያካበቱ የስፖርቱ ዘርፍ ባለሙያዎች ቤት ውስጥም ከቤት ውጪም መዘውተር የሚችሉ ስፖርቶችን በማነጻጸር ከቤት ውጪ የሚደረጉት የተሻሉ እንደሆነ የተለያዩ የመከራከሪያ ነጥቦችን በመሰንዘር ይሞግታሉ፡፡ ስፖርትን ቤት ውስጥ ማዘውተር የተሻለ መሆኑን የሚያምኑ ደግሞ ከአየር ፀባይ ጋር በተያያዘ የሚያነሱት ሞጋች ሃሳብ አለ፡፡ እነዚህ ምሁራን ስፖርትን ቤት ውስጥ ማዘውተር ከአየር ፀባይ ጋር በተያያዘ ከሙቀት ወይም ከቅዝቃዜ ተፅዕኖ ማምለጥ እንደሚቻል ያስቀምጣሉ፡፡ውድድሮችና ልምምዶች በአየር ፀባይ መለዋወጥ የተነሳ የመሰረዛቸው እድል ጠባብ መሆኑን በመዘርዘር ቤት ውስጥ ስፖርትን ማዘውተር ለስፖርተኞች፣አሰልጣኞች ከዚያም ሲያልፍ ስፖርቱን ለሚታደሙ ተመልካቾች ምቹ መሆኑን ያብራራሉ፡፡ ከወጪ አኳያም የቤት ውስጥ ስፖርቶች መሰረተ ልማት አንዴ መገንባት ከተቻለ ለረጅም ጊዜ ተጨማሪ ወጪና ልፋት እንደማይጠይቅ ያምናሉ፡፡ ለዚህም ቤት ውስጥ ስፖርትን ማዘውተሪያ (ጅምናዚየም) አንድ ጊዜ መገንባት ከተቻለ መሰረተ ልማቱን ለመንከባከብ ግፋ ቢል ፅዳት መጠበቅ እንጂ ከቤት ውጪ የሚገነቡ ማዘውተሪያዎች በአየር ፀባይ መለዋወጥ በየጊዜው እንደሚፈልጉት ተጨማሪ የጥገና ወጪ እንደማይሹ ነው የሚያስረዱት፡፡ከቤት\nውጪ የሚገኙ የመወዳደሪያ ስፍራዎች የተሻሉ መሆናቸውን የሚያምኑት ወገኖች በበኩላቸው ስፖርትን ቤት ውስጥ ለማዘውተር በዋናነት ጅምናዚየም የመገንባት ወጪው በራሱ የተጋነነ መሆኑን በማስቀመጥ ሀሳቡን ይቃወማሉ፡፡ ከዚህ ባሻገር ስፖርትን ቤት ውስጥ ከማዘውተር ይልቅ ከቤት ውጪ መከወን የተሻለ ነፃነት እንደሚሰጥ በማንሳት ጠንካራ የመከራከሪያ ነጥብ ያስቀምጣሉ፡፡ ሁለቱም ወገኖች ግን በቂ የፋይናንስ አቅም ካለ የቤት ውስጥም ሆነ ከቤት ውጪም ያሉ የስፖርት መሰረተ ልማቶቹ መሟላታቸው ተገቢ መሆኑ ላይ ልዩነት የላቸውም፡፡ ይሁን እንጂ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ታዳጊና አቅም የሌላቸው አገራት አቅማቸውን አሳድገው ሁሉንም ማሟላት እስኪችሉ አዋጭ ለሆነው መንገድ ቅድሚያ መስጠት የግድ እንደሚላቸው ነው ባለሙያዎቹ ጎራ ለይተው ሃሳባቸውን የሚሰነዝሩት፡፡ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ለስፖርት መሰረተ ልማት ግንባታዎች ትኩረት በመስጠት በተለያዩ ክልሎች ግዙፍ ስቴድየሞችን ጨምሮ ሌሎች መሰረተ ልማቶችን በብዛት እየተገነባ ይገኛል። ከነዚህ መካከል በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍለ አገራት ጎልተው የወጡት ግዙፍ ስቴድየሞች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ከነዚህ መካከል አብዛኞቹ ሁለገብ ሲሆኑ የቤት ውስጥ ስፖርቶች የሚባሉትን ጭምር ከቤት ውጪ ማዘውተር እንዲያስችሉ ሆነው እየተገነቡ ይገኛሉ፡፡ ግንባታቸው የተጠናቀቀም በርካታ ናቸው፡፡ በመግቢያችን ላይ በስፋት ለመጥቀስ እንደሞከርነው እነዚህ ግንባታዎች ለቤት ውስጥ ስፖርቶች (indoor game) ትኩረት አለመስጠታቸውን ለመለየት ብዙ የሚከብድ ነገር የለውም፡፡ አብዛኞቹ የስፖርት መሰረተ ልማቶች እግር ኳስና አትሌቲክስ ስፖርቶች ብቻ ትኩረት የሰጡ ስለመሆናቸው በተለያዩ አጋጣሚዎች ተዘዋውሮ የማየት እድሉ የገጠመው ማንኛውም ሰው በቀላሉ እውነታውን መታዘብ ይችላል፡፡ እነዚህ ግንባታዎች አገሪቷ ካላት እምቅ አቅም አኳያ ‹‹ስፖርትን በቤት ውስጥ ወይም ከቤት ውጪ ማዘውተር የተሻለ ይሆናል›› የሚሉ ጥናቶች ተደርጎባቸው ይሰሩ አሊያም ደግሞ በዘፈቀደ በግብታዊነት ተግባራዊ ተደርገዋል የሚለው ጉዳይ እስካሁን በቂ ምላሽ አላገኘም፡፡ በተለይ ለየትኛው ስፖርት ትኩረት ሰጥተው ነው? በምንስ መስፈርት? የሚለው ጉዳይ አነጋጋሪ ይመስላል፡፡ባለፉት በርካታ ሳምንታት አዲስ ዘመን የተለያዩ ብሔራዊ የስፖርት ፌዴሬሽኖችን በተመለከተ በሰሯቸው ዘገባዎች የቤት ውስጥ ስፖርቶች ትልቁ እንቅፋታቸው የማዘውተሪያ ስፍራ ወይም ጅምናዚየም መሆኑን አስተውሏል፡፡ የቦክስ ፌዴሬሽን የፅሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጳውሎስ ማዳ የቦክስ መፋለሚያ ሪንግ የሚቀመጥበት ጅምናዚየም የስፖርቱ ትልቅ ችግር መሆኑን ነግረውናል። ፌዴሬሽኑ በዚህ ምክንያት ጥራት ያላቸው ውድድሮችን እንደ ልብ ማድረግ አለመቻሉ ስፖርቱን ወደ ኋላ እየጎተተው ሲሆን ከቤት ውጪ ምቹ ባልሆነ ሁኔታ ውድድሮችን ለማድረግም አማራጮቹ ትንሽ ናቸው፡፡ ወደ ፊትም ቢሆን አዲስ አበባ ላይ እየተገነባ ከሚገኘው ብሔራዊ ስቴድየም ጎን ለጎን ይገነባል የተባለው ጅምናዚየም እንጂ ሌላ ተስፋ እንደ ሌለ የፅሕፈት ቤት ሃላፊው መናገራቸውን ዘግበናል፡፡ የብሔራዊ ስቴድየም ግንባታው የእግር ኳስና አትሌቲክስ ስፖርቶችን ብቻ በሚያገለግል መልኩ ግንባታው እየተፋጠነ እንደሚገኝ ያስተዋሉ የስፖርት ቤተሰቦች የጅምናዚየሙ ግንባታ በቅርቡ እውን እንደማይሆን ጥርጣሬ አላቸው፡፡ ከብሔራዊ ስቴድየሙ ጎን ለጎን እንደሚሰራ እቅድ የተያዘለት ጅምናዚየም በአዲስ አበባ ደረጃ ለበርካታ የአገራችን የቤት ውስጥ ስፖርት ፌዴሬሽኖች ተስፋ ነው፡፡ ከቤት ውጪ ለማዘውተር የማይቻለው ‹‹የባድሚንተን›› ስፖርት ከብሔራዊ ስቴድየሙ ጎን ለጎን የሚገነባውንም ይሁን ሌላ ጅምናዚየም በተስፋ ከሚጠባበቁት ግንባር ቀደሙ ነው፡፡ አቶ ዮሴፍ ለታ የኢትዮጵያ ባድሚንተን ፌዴሬሽን የፅሕፈት ቤት ሃላፊ ናቸው፡፡ የባድሚንተን ስፖርት በባህሪው ከቤት ውስጥ ስፖርቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የተሟላ መሰረተ ልማት የሚጠይቅ መሆኑን ባለፈው ሳምንት ባስነበብነው ዘገባ መናገራቸው ይታወሳል። ይህን ስፖርት ለመጫወት አዳራሹ ወይንም ጅምናዚየሙ ቢያንስ ሰባት ሜትር ከፍታ ያለውና ሁለት ጨዋታዎችን በአንድ ጊዜ ማካሄድ የሚያስችል መሆን እንዳለበት ዓለም አቀፍ ህጉም ይደነግጋል። በእርግጥ የባድሚንተን ስፖርትን እንደ ቮሊቦልና ቅርጫት ኳስ አይነት ስፖርቶች ከቤት ውጪ ማዘውተር እንደሚቻል አቶ ዮሴፍ ያምናሉ፡፡ ይሁን እንጂ ባድሚንተንን ከቤት ውጪ ማዘውተር ስፖርቱን በፕሮፌሽናል ደረጃ ለማሳደግና ውጤታማ ለመሆን አያስችልም፡፡ እንደ ባድሚንተንና ቦክስ ስፖርቶች ሁሉ በብሔራዊ ፌዴሬሽን የሚመሩት በርካታ ስፖርቶች ጅምናዚየም የተራቡ ናቸው፡፡ እንደ ቴኳንዶ፣ ጁዶ፣ ካራቴና ጅምናስቲክ ያሉ የፍልሚያ ስፖርቶች የዚህ ችግር ተጋሪ ናቸው፡፡ ከእግር ኳስ በስተቀር ኳስን መሰረት ያደረጉ በርካታ ስፖርቶችም ጅምናዚየም የሚሹ ቢሆንም በአገራችን ካለው ችግር አኳያ ከቤት ውጪ መዘውተራቸው የተለመደ ነው። በእርግጥ ለጊዜውም ቢሆን አንዳንድ የቤት ውስጥ ስፖርቶች ከቤት ውጪ ቢዘወተሩ ችግር ላይኖረው ይችላል። የግዴታ በቤት ውስጥ መዘውተር ያለባቸው ስፖርቶች ችግርን ለመቅረፍ ከወዲሁ ካልታሰበ ግን የሚፈለገውን ውጤት ለማግኘት የማይታሰብ ከመሆኑ ባሻገር ኦሊምፒክን በመሳሰሉ ታላላቅ መድረኮች በአትሌቲክስ ላይ ብቻ ተስፋ አድርጎ መቆየቱን የግድ ያደርገዋል። አትሌቲክሱም ቢሆን ኦሊምፒክና ዋናው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ላይ እንጂ በራሱ የቤት ውስጥና ከቤት ውጪ ተብሎ የተከፈለ በመሆኑ ተጨማሪ የማዘውተሪያ ስፍራ የግድ አስፈላጊ የሚሆንበት ጊዜም መምጣቱ አይቀሬ ነው፡፡በፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን የስፖርት ፋሲሊቲ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኢንጂነር አስመራ ግዛው፣ ‹በኢትዮጵያ እየተገነቡ የሚገኙ የስፖርት መሰረተ ልማቶች በዋናነት ከቤት ውጪ ስፖርቶችን መሰረት ያደረጉ ናቸው› የሚለው ሃሳብ ከተሳሳተ ግንዛቤ የመነጨ መሆኑን ይናገራሉ። ግዙፍ ስቴዴየሞች በአገራችን ሲገነቡ ከቤት ውጪ ስፖርቶችን ብቻ መሰረት አድርገው እንዳልሆነም ያብራራሉ፡፡ የነዚህ ግንባታዎች ዲዛይን በትንሹ አምስት ወይም ስድስት ስፖርቶችን መሰረት ያደረገ ነው፡፡ ትናንሽና ትላልቅ አዳራሽና ጅምናዚየሞች አብረው እየተገነቡ መሆኑን በቀላሉ ማየት እንደሚቻል ያስረዳሉ፡፡ በአደይ አበባ ቅርፅ በሚገነባው ብሔራዊ ስቴድየም ውስጥ ሁለት ደረጃቸውን የጠበቁ ጅምናዚየሞችና ከ2500 ሰው በላይ ማስተናገድ የሚችሉ ሁለት አዳራሾች እየተገነቡ መሆኑንም በምሳሌነት ያስቀምጣሉ፡፡ ይህም የስፖርት መሰረተ ልማቶች ከቤት ውጪ ስፖርቶች ላይ ብቻ ትኩረት አድርገው እንደማይገነቡ ማሳያ አድርገው ያነሳሉ፡፡ በነዚህ ማዘውተሪያዎች ውስጥ ጅምናስቲክ፣ክብደት ማንሳትና ሰውነት መገንባት፣ ባድሚንተንና በርካታ የቤት ውስጥ ስፖርቶችን ማካሄድ እንደሚቻል ኢንጂነር አስመራ ያምናሉ፡፡ አገሪቷ ካላት አቅም፣የስፖርት ባህልና ነባራዊ ሁኔታ አኳያ ጥናት ተደርጎባቸው ነው የሚገነቡት ለማለት ግን ሌላ ጥናት ያስፈልጋል የሚል ሃሳብ ይሰነዝራሉ፡፡ ‹‹እያንዳንዱ ክልል የየራሱን አንድ ዘመናዊ ስቴድየም ለመገንባት ይነሳል፣ በዛም መሰረት ዲዛይን ያደርጋል፣ነገር ግን ያለውን እምቅ የስፖርት አቅም ለይቶ ለሚያስፈልገው ስፖርት ማዘውተሪያ ይሰራል የሚለው ጥናት ይፈልጋል፣እንደ ችግርም የታየው ይሄ ነው፣ የቅንጅት ስራም የሚጠይቅ በመሆኑ እኔ በግሌ እንደ ክፍተት ወስደዋለሁ›› የሚሉት ኢንጁነር አስመራ፤ በሁሉም ግንባታዎች ዲዛይን ለቤት ውስጥ ስፖርቶች የሚሆኑ ማዘውተሪያዎች መካተታቸውን ያነሳሉ፡፡ ነገር ግን በዲዛይናቸው መሰረት ግንባታዎቹ እየተጠናቀቁ አለመሆናቸውን ይቀበላሉ፡፡ በአንዳንድ ክልሎች ከእግር ኳስ እና አትሌቲክስ ማዘውተሪያዎች በተሻለ ጅምናዚየሞች ተጠናቀው ውድድሮችን እያስተናገዱ መሆናቸውን የጠቆሙት ኢንጂነር አስመራ፣የሐዋሳ ስቴድየም ኳስ ሜዳው እንደገና ፈርሶ እየተሰራ በመሆኑ ጎን ለጎን የተገነባው ጅምናዚየም በአንፃሩ በርካታ የቤት ውስጥ ስፖርቶችን እያስተናገደ እንደሚገኝ በምሳሌነት ያስቀምጣሉ፡፡ የቤት ውስጥ ስፖርቶች ትኩረት እንዳልተነፈገው፣ የጂም እቃዎች በዲዛይን መሰረት ተሟልቷል ከተባለ ግን ከበጀት ጋር የሚያያዝ ክፍተት መሆኑን፣ ችግሩ ከትኩረት ጋር የተያያዘ ሳይሆን ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ ስለማይጠናቀቁ እንደሆነ በዝርዝር አብራርተዋል፡፡ በተጨማሪም ከአብዛኞች ስቴድየሞች ጎን ለጎን ጅምናዚየሞች ከሩቅ ጎልተው ስለማይታዩ እንጂ እየተጠናቀቁ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን አስረድተዋል።‹‹ብሔራዊ ስቴድየም የሚገነባበት ዋና አላማ አንድ መገለጫ ስቴድየም እንዲኖር በማሰብ እንጂ የቤት ውስጥ ስፖርቶችን ለማካተት በማሰብ አይደለም›› የሚሉት ዳይሬክተሩ፤ መንግስት ብዙ ገንዘብ አውጥቶ ይሄን ሲያደርግ ደግሞ ግንባታው ለአንድ እግር ኳስ ብቻ እንዲውል እንደማይፈልግ ይናገራሉ። ስለዚህ ስቴድየሙ ገፅታውንና ነባራዊ ሁኔታውን ሳይቀይር ሌሎች ስፖርቶችን እንዲያስተናግድ እንደሚደረግ ይገልፃሉ። ብሔራዊ ስቴድየሙ የቤት ውስጥ ስፖርቶችን ማዘውተር የሚችሉ ነገር ግን ከቤት ውጪ የተገነቡ በርካታ መሰረተ ልማቶች አካቶ የያዘ ነው፡፡ ዳይሬክተሩ ከላይ ከጠቀሱት ሀሳብ በተቃራኒ የግዴታ በቤት ውስጥ መዘውተር ያለባቸው ስፖርቶች ችግር ጅምናዚየም መሆኑን ይናገራሉ፡፡ አሁን እየተገነቡ የሚገኙት ጅምናዚየሞችም በቂ አለመሆናቸውንም ያምናሉ፡፡ ይህን ክፍተት ለመቅረፍ ግን የግል ባለሃብቶች ተሳትፎ እያደረጉ መሆኑን አንስተው መንግስትም የቤት ውስጥ ስፖርቶች ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት አለበት የሚለው ቀጣይ የቤት ስራ እንደሆነ ያብራራሉ። መንግስት ትላልቅ የስፖርት መሰረተ ልማቶችን እየገነባ በሚገኝበት በዚህ ወቅት ግን ትላልቅ ጅምናዚየሞችን መገንባት ከበጀት እጥረት አኳያ ተገቢ ነው የሚል እምነት የላቸውም፡፡ በጊዜያዊነት ያሉትን በጋራ ተናቦና አብቃቅቶ መጠቀም አስፈላጊ መሆኑንም ነው በምክረ ሃሳብ ደረጃ የሚያነሱት፡፡ ለዚህም በቂ መሰረተ ልማት አለ ብለው ያምናሉ፡፡መንግስት በተለያዩ ክልሎች የስፖርት መሰረተ ልማቶች እየገነባ መሆኑ እሙን ነው፡፡ ለጊዜውም ቢሆን አስገዳጅ ሁኔታዎች በመኖራቸው የቤት ውስጥ ስፖርቶችም ከቤት ውጪ ባሉ ማዘውተሪያዎች እንዲከወኑ በማድረግ ግንባታዎችን እንደሚያከናውን መካድ አይቻልም፡፡ ከግዙፍ ስቴድየሞች ጎን ለጎን የጅምናዚየምና ሌሎች ስፖርቶች ማዘውተሪያ ግንባታዎች በዲዛይን መካተትም ግን ‹‹ለቤት ውስጥ ስፖርቶች ትኩረት ተሰጥቷል›› ማለትም አይደለም፡፡ ያሉትን መሰረተ ልማቶች አብቃቅቶና ተናቦ መጠቀም ሌላ ጉዳይ ነው፡፡ በቂ መሰረተ ልማት አለ ማለት ግን ወደ ፊት መንግስት ለቤት ውስጥ ስፖርቶች ትኩረት አድርጎ መስራት ይኖርበታል ከሚለው ሃሳብ ጋር አይጣጣምም፡፡ በቂ መሰረተ\nልማት ካለ መንግስት\nትኩረት ሰጥቶ የሚሰራበት\nምክንያት አይኖርምና፡፡ ስለዚህ\nየኢንጂነር አስመራ አስተያየት\nእርስበራሱ የሚጣረስ ነው።\nመንግስት ትላልቅ የስፖርት\nመሰረተ ልማቶችን እየገነባ\nበሚገኝበት በዚህ ወቅት\nትላልቅ ጅምናዚየሞችን መገንባት\nከበጀት አኳያ አያስኬድም\nማለትም በግልፅ የመንግስት\nትኩረት አሁን ላይ ወዴት\nእንዳዘነበለ ያሳያል፡፡ ኢትዮጵያ\nካላት አቅም አኳያ\nየጀመረቻቸውን የስቴድየም ግንባታዎች\nአጠናቃ በቀጣይ ለቤት\nውስጥ ስፖርት ማዘውተሪያዎች\nትኩረት መስጠት ይኖርባታል\nየሚለው ሃሳብ ግን በርካቶችን\nየሚያስማማ ይመስላል፡፡አዲስ ዘመን ቅዳሜ ሰኔ 1/2011", "passage_id": "d9804552fa4ad66c91b4fc59af7b2384" } ]
fd7e7687d7041a2b2aaf7fbf9e3ab5f6
fa5997abb25501d92753abc953d0c38c
የዓለም አትሌቲክስና 2020 የውድድር ዓመት
ቦጋለ አበበ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት የዓለም ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ገፅታ ዝብርቅርቁ በወጣበት የፈረንጆች 2020 ዓመት የዓለም ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችም ቀላል የማይባል አሉታዊ ተፅዕኖ አርፎባቸዋል። ኦሊምፒክን ጨምሮ ታላላቅ ዓለም አቀፋዊና የአገር ውስጥ ስፖርታዊ ውድድሮች በተሰረዙበትና በተራዘሙበት የውድድር ዓመት የአትሌቲክስ ስፖርት በርካታ ፈተናዎችን ማሳለፉ ይታወቃል። በዓለም ሕዝብ ዘንድ ጥሩ ትውስታን ጥሎ ያላለፈው 2020 ተሸኝቶ ዛሬ በ2021 የውድድር ዓመት አንድ ብሎ የሚጀምርበት ቀን ነው። በአብዛኛው መጥፎ ትዝታውን ጥሎ ባለፈው ዓመት የአትሌቲክሱ ዓለም በርካታ አሉታዊ ተጽእኖዎች አርፈውበታል፤ በርካታ አዎንታዊ ክስተቶችንም አስተናግዷል። ከእነዚህ መካከልም አበይት ክስተት የሆኑት እንደሚከተለው ተዳሰዋል። ጥር የ2020 የውድድር ዓመት በጀመረበት ታህሳስ መጨረሻና ጥር ወር ላይ የአትሌቲክሱ ዓለም በርካታ የዓለም ክብረወሰኖችን አስተናግዷል። ኬንያዊው አትሌት ሮኔክስ ኪፕሩቶ የአስር ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የዓለም ክብረወሰንን ቫሌንሲያ ላይ 26፡24 በሆነ ሰዓት ያስመዘገበው በዚህ ወር ሲሆን፣ ሌላኛዋ ኬንያዊት ሼላ ቺፕኪሩይ በተመሳሳይ ውድድር የሴቶቹን የዓለም ከገጽ 46 የዞረክብረወሰን 29፡46 በሆነ ሰዓት በማሻሻል የውድድር ዓመቱን በስኬት ጀምራለች። በዚሁ ወር የማራቶን ቁጥር አንድና ቁጥር ሁለት የሆኑት ኢትዮጵያዊና ኬንያዊ አትሌቶች ቀነኒሳ በቀለና ኢሉድ ኪፕቾጌ በለንደን ማራቶን እንደሚፋለሙ ይፋ መደረጉም የውድድር ዓመቱ ትልቅ ክስተት ነበር። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በየዓመቱ የሚደምቁበት የዱባይ ማራቶን በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፈው ኦሊካ አዱኛ አሸናፊ ሲሆን፣ በሴቶች ወርቅነሽ ደገፋ የኢትዮጵያውያንን የተለመደ ድል ማስቀጠል ችላለች። በቻይና ናጂንግ ባለፈው መጋቢት ወር ሊካሄድ ቀጠሮ የተያዘለት የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ቻምፒዮና መራዘሙ የተሰማው በዚሁ ወር ነበር፤ ይህ ወድድር በኮቪድ-19 ስጋት የተራዘመ የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ ውድድርም ሆኗል። የካቲት ያለፈው የካቲት ወርም በዓለም አትሌቲከስ የተለያዩ የዓለም ክብረወሰኖች የተሻሻሉበት ሆኖ ይታወሳል። በተለይም ስዊድናዊው ምርኩዝ ዘላይ ሞንዶ ዱፕሌንቲስ 2014 ላይ በፈረንሳዊው ሪናውድ ላቪሌኒ ተይዞ የቆየውን የዓለም ክብረሰወን 6 ነጥብ 17 ሜትር በመዝለል በአንድ ሴንቲሜትር ያሻሻለበት አጋጣሚ ትልቁ ክስተት ነበር። ላቪሌኒ በተመሳሳይ ወር ግላስጎ ላይ 6 ነጥብ 18 ሜትር በመዝለልም ተጨማሪ የዓለም ክብረወሰን በአንድ ወር ውስጥ ያሻሻለበት አጋጣሚ የሚዘነጋ አይደለም። የውድድር ዓመቱን በበርካታ የዓለም ክብረወሰኖች ታጅቦ ያጠናቀቀው ዩጋንዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቺፕቴጌ የዓመቱን የስኬት ጉዞ ሞናኮ ላይ የአምስት ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የዓለም ክብረወሰንን 12፡51 በሆነ ሰዓት በማሻሻል የጀመረው በዚሁ የካቲት ወር ነበር። ኢትዮጵያዊቷ አትሌት አባብል የሻነህ የግማሽ ማራቶን የዓለም ክብረወሰንን በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ራስ አል ካይማህ 64፡31 በሆነ ሰዓት ያሻሻለችበትም አጋጣሚ በጉልህ የሚጠቀስ ነው። ቬንዙዌላዊቷ ስሉስ ዘላይ ዩሊማር ሮጃስ በማድሪድ በተካሄደው የቤት ውስጥ ውድድር ለአስራ ስድስት ዓመታት በታትያና ሌቢዴቫ ተይዞ የቆየውን የዓለም ክብረወሰን 15 ነጥብ 43 ሜትር በመዝለል ያሻሻለችበት አጋጣሚም ይታወሳል። መጋቢት የውድድር ዓመቱ ሦስተኛ ወር በሆነው መጋቢት ሕዝብ ባልተሳተፈበት የቶኪዮ ማራቶን ብርሃኑ ለገሰ ባለድል የሆነበት አጋጣሚ ሳይጠቀስ አይታለፍም። ቀነኒሳ በቀለም በለንደን ግማሽ ማራቶን አስደናቂ ብቃት አሳይቶያሸነፈበት ውድድርም አይዘነጋም። በዚህ ወር የኮቪድ-19 ስርጭት እየተስፋፋ መሄዱን ተከትሎ የዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮናም የመራዘም ዕድል ገጥሞታል። በተመሳሳይ ታላላቅ የሚባሉት የለንደንና የቦስተን ማራቶን ውድድሮችም በዚሁ የካቲት ወር እንደተራዘሙ ታውቋል። እንዲካሄድ በርካታ ጥረቶች ሲደረጉ ከቆዩ በኋላ የውድድር ዓመቱ ታላቅ የስፖርት መድረክ ቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ የተራዘመውም በዚሁ ወር ነበር። ሚያዝያ-ግንቦትበአሜሪካ ኦሪገን በሰኔ ወር ሊካሄድ የነበረው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ቻምፒዮና በ2022 እንዲካሄድ ውሳኔ ላይ የተደረሰው በሚያዝያ ወር ነበር። የሚያዝያ ወር ምናልባትም በአትሌቲክሱ ዓለም ውድድሮችና ክብረወሰኖች የተመዘገቡበት ሳይሆን በርካታ ተጠባቂ ውድድሮች የተራዘሙበትና የተሰረዙበት መጥፎ ትዝታ ጥሎ ያለፈ ነው ማለት ይቻላል። ከቤት ውስጥ ቻምፒዮናው በተጨማሪ በፓሪስ ሊካሄድ የነበረው የአውሮፓ አትሌቲክስ ቻምፒዮና በዚህ ወቅት ለመሰረዝ በቅቷል። ጥቁር አሜሪካዊው ጂዮርጅ ፍሎይድ ሜይዌዘር በፖሊስ በአሰቃቂ ሁኔታ መገደሉን ተከትሎ የዓለም አትሌቲክስ ‹‹የጥቁር ሕይወት ዋጋ አለው›› በሚል በዓለም አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን እንቅስቃሴ የተቀላቀለበት ወቅት ነው። የዓለም አትሌቲክስ አዲስ የኦሊምፒክ ተሳትፎ ማረጋገጫ ሂደትን ይፋ ያደረገውም በዚህ ወቅት ነበር። የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስፖርቱን እያዳከመው በመምጣቱም የዓለም አትሌቲክስ ስፖርቱን ለመደገፍ አዲስ ስትራቴጅክ ፕላን ይፋ አድርጓል። ተጠባቂው የኒውዮርክ ማራቶንም መሰረዙ የተሰማው በዚሁ ወቅት ነው። ሰኔ-ሐምሌ ውድድሮች ለወራት በዓለም ላይ አለመካሄዳቸውን ተከትሎ የስፖርቱ ዓለም በዘርፉ ፖለቲካ ተጠምዶ የቆየበት ጊዜ ነበር። በዚህም ከውድድርና ውጤቶች ይልቅ የተለያዩ ጉዳዮች የስፖርቱ ቤተሰብ መነጋገሪያ ሆነው ሰንብተዋል። በሰኔ ወር ትልቅ መነጋገሪያ ከሆኑ የአትሌቲክስ ጉዳዮች የቀድሞው የማራቶን ባለክብረወሰን ኬንያዊው ዊልሰን ኪፕሳንግ አበረታች ንጥረነገር ተጠቅሞ በመገኘቱ ለአራት ዓመታት ከስፖርቱ መታገዱ ትልቅ ትኩረት ስቦ ነበር። ተቋርጠው የቆዩ የዳይመንድ ሊግ ውድድሮች በወሩ መጨረሻ እየተመለሱ መምጣታቸው ግን በወረርሽኙ ሳቢያ ድብርት ውስጥ ለነበረው የስፖርቱ ቤተሰብ ተስፋ ሆነው ነበር። በዚህም በዙሪክ የተካሄደው የዳይመንድ ሊግ ውድድር ተጠቃሽ ነው። ያም ሆኖ እንደ ቺካጎ ያሉ ታላላቅ የማራቶን ውድድሮች በዚህ ወር ከመሰረዝ አልዳኑም። ወሩ ከመጠናቀቁ አስቀድሞም የዓለም አትሌቲክስ በመሮጫ ጫማዎች ላይ አዲስ ሕግ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። ውድድሮች ከወራት በኋላ በሂደት መመለሳቸውን ተከትሎ ለረጅም ዓመታት ያልተደፈሩ የዓለም ክብረወሰኖች ጭምር ሐምሌ ወር ላይ ተሰብረዋል። በተለይም ዩጋንዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቺፕቴጌ ሞናኮ ላይ በቀነኒሳ በቀለ ለአስራ አምስት ዓመታት ተይዞ የቆየውን የዓለም ክብረወሰን በ12፡35፡36 ማሻሻሉ ያልተጠበቀ የዓመቱ አበይት ክስተት ነበር። ነሐሴ ሐምሌ ወር ላይ የታየው ትልልቅ የዓለም ክብረወሰን የማሻሻል ሂደት በነሐሴም ተደግሟል። በተለይም በኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ኃይሌ ገብረስላሴና ድሬ ቱኔ ለረጅም ዓመታት ተይዘው የቆዩት የአንድ ሰዓት ውድድር የዓለም ክብረወሰኖች መሰበራቸው ያልተጠበቀ ነበር። ትውልደ ሶማሊያዊው የእንግሊዝ አትሌት ሞ ፋራህ የወንዶቹን ክብረወሰን ሲያሻሽል ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ የኔዘርላንድስ አትሌት ሲፈን ሃሰን የሴቶቹን ክብረወሰን መጨበጥ ችላለች። ኬንያዊቷ አትሌት ፒርስ ጂፕቺርቺር በፓራጓይ ግማሽ ማራቶን የርቀቱን የሴቶች ብቻ የዓለም ክብረወሰን ያሻሻለችበት አጋጣሚም አይዘነጋም። የቀድሞው የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ፕሬዚዳንት ሴኔጋላዊው ላሚን ዲያክ በሙስና ቅሌት በፓሪስ ለዓመታት በቁም እስር ቆይተው ፍርድ የተበየነባቸውም በዚሁ ወር ነው። የውድድር ዓመቱን በክብረወሰኖች ታጅቦ ያሳለፈው ስዊድናዊው ምርኩዝ ዘላይ ሞንዶ ዱፕሌንቲስ ከቤት ውጪ ባሉ ውድድሮች በዩክሬናዊው ታሪካዊ አትሌት ሰርጌ ቡካ ተይዞ የቆየውን የዓለም ክብረወሰን በ6 ነጥብ 15 ሜትር ያሻሻለበት አጋጣሚም ትልቅ ነው። የዓለም የማራቶን ክብረወሰን ባለቤት የሆነችው ኬንያዊት አትሌት ብሪጊድ ኮስጌ የለንደን ማራቶንን ለሁለተኛ ጊዜ አሸንፋለች። በዚህ ውድድር ለወራት ሊፋለሙ ቀጠሮ ይዘው ትልቅ ትኩረት የተሰጣቸው ቀነኒሳ በቀለና ኢሉድ ኪፕቾጌ ፍልሚያ አንድ ቀን ሲቀረው ቀነኒሳ በጉዳት ከውድድር ውጪ መሆኑ አሳዛኝ ነበር። ያም ሆኖ የርቀቱ የክብረወሰን ባለቤትና ባለፉት ዓመታት ሽንፈት ያልገጠመው ኪፕቾጌ ባልተጠበቀው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሹራ ቂጣታ ከመሸነፉ ባሻገር ሰባተኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ አስገራሚ ነበር።ዩጋዳዊው ቺፕቴግ ቀነኒሳ ለአስራ ስድስት ዓመታት ይዞት የቆየውን የአስር ሺ ሜትር የዓለም ክብረወሰን ቫሌንሲያ ላይ ሲያሻሽል ኢትዮጵያዊቷ ለተሰንበት ግደይ በጥሩነሽ ዲባባ ለአስራ ሁለት ዓመታት የተያዘውን የአምስት ሺ ሜትር የዓለም ክብረወሰን ማሻሻሏ የውድድር ዓመቱ ግንባር ቀደም አበይት ክስተት ሆኖ አልፏል። ኬንያዊቷ ፒርስ ጂፕቺርቺር በፖላንድ ጊዲኒያ የዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮና የርቀቱን የሴቶች ብቻ የዓለም ክብረወሰን መስበሯም ወሩን አስደናቂ አድርጎት አልፏል። መስከረም -ታህሳስ የ2023 የአውሮፓ አትሌቲከስ ቻምፒዮናን ቱርክ ኢስታንቡል ላይ እንድታዘጋጅ ዕድል ባገኘችበት መስከረም ወር በአየርላንድ ደብሊን ሊካሄድ የነበረው የ2020 የአውሮፓ አገር አቋራጭ ቻምፒዮና ከመሰረዙ በቀር በአትሌቲክሱ ዓለም ብዙም አነጋጋሪ ጉዳዮች ሳይፈጠሩ አልፈዋል። ከዚያ በኋላ ባሉት ሦስት ወራት ግን የዓለማችን ፈጣኑ አትሌት ጃማይካዊው ዩዜን ቦልት እንዲሁም የረጅም ርቀት ንግስቷ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ በእውቁ የእንግሊዝ የአትሌቲክስ መፅሔት የምን ጊዜም ምርጥ አትሌት ተብለው መሰየማቸው አብይ ጉዳይ ነበር። ቬንዙዌላዊቷ አትሌት ዩሊማር ሮጃስ እንዲሁም ስዊድናዊው ሞንዶ ዱፕሌንቲስ የዓመቱ ምርጥ አትሌቶች ተብለው ተሸልመዋል። ኬንያዊው ኪቢዎት ካንዲም በዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮና ሲያሸንፍአዲስ ዘመን ታህሳስ 23/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=38650
[ { "passage": "ያልተጠበቁ አስደናቂ አሸናፊዎች፣ ለአሸናፊነት ጥቂት የቀራቸው የሚያስቆጩ ሽንፈቶች፣ አሳዛኝና አስደንጋጭ አጋጣሚዎች፣ በስፖርታዊ ጨዋነት የታጀቡ ክስተቶች፣ ለቀጣዩ ትውልድ ለታሪክ የሚዘልቁ ሁነቶች ባለፉት አስር ቀናት ተስተናግደውበታል። ሁለት ዓመታትን የጠበቀው 17ኛው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ከ10 ቀናት ቆይታ በኃላ ለቀጣይ ሁለት ዓመታት በቀጠሮ ተሰናብቷል። ከጅማሬውም በእስያ መካከለኛው ምስራቅ አቅጣጫ የምትገኘው አገር ከስፔኗ ባርሴሎና እና ከአሜሪካዋ ኦሪጎን ግዛት በልጣ ለዚህ ውድድር መታጨቷ አነጋጋሪ ነበር። በርካታ አስደናቂ ጉዳዮች እና ጥቂት ጉድለቶች ከአስቸጋሪው የአየር ሁኔታ ጋር አጣምሮ ሲካሄድ የቆየው የዶሃው ዓለም ቻምፒዮናም ከትናንት በስቲያ መቋጫውን አግኝቷል። 200 አገራት በሺዎች የሚቆጠሩ አትሌቶቻቸውን ባሳተፉበት ቻምፒዮና፤ 43 አገራት የሜዳሊያ ሰንጠረዡ ውስጥ ሲገቡ 68 የሚሆኑት ደግሞ እስከ 10ኛ ደረጃ ባለው ውጤት ውድድራቸውን አጠናቀዋል። ይህም እ.ኤ.አ በ2017 ለንደን ላይ ከተመዘገቡ ክብረወሰኖች እጥፍ የሚሆኑትም በዶሃ ሊሰበሩ መቻላቸውን ማህበሩ በድረገፁ አስነብቧል። በከሊፋ ስታዲየም በተካሄደው የመዝጊያ መርሀ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ፕሬዚዳንት ሰባስቲያን ኮ የዶሃውን ዓለም ቻምፒዮና በታሪክ ምርጡ እንደነበር መስክረዋል። ኮ በንግግራቸው «ስፖርታችንን ለምትከታተሉና ለስፖርቱ ቅርብ ለሆናችሁ ሁሉ የአትሌቶቻችንን እና አሰልጣኞቻችንን ስኬት በቻምፒዮናው መመዘን ችለናል። በዓለም ላይ ያሉ አትሌቶች ሁሉ በቻምፒዮናው ታሪክ የሚልቀውን አቋማቸውን አሳይተዋል፤ ይህም አስደናቂ ነበር። ለውድድሩ የሚሆነውን ሁሉ ያሟላችው አዘጋጇ አገርም በዚህ መመስገን ይገባታል» ብለዋል። የኳታር ዓለም ቻምፒዮና\nአዘጋጅ ኮሚቴ ምክትል ፕሬዚዳንት ዳሃላን አል ሃማድ በበኩላቸው፤ የቻምፒዮናው አዘጋጅ በመሆናቸው የኳታራዊያን ህልም እንደሰመረ ነው የገለፁት። በአስተያየታቸውም «ለአዘጋጅነት ፍላጎት ያሳየነው ከ1997 ጀምሮ ነበር፤ ለዓመታት ፍላጎታችንን ስናቀርብ ቆይተንም በ2010 የዓለም የቤት ውስጥ ቻምፒዮናን ለማሰናዳት እንዲሁም የዳይመንድ ሊግ አንድ መዳረሻ ለመሆን በቃን። ይህ ጥሩ ቢሆንም መሰል ውድድርን በአገራቸው ሲካሄድ ለመመልከት የሚፈልጉ ትውልድ ላይ በመድረሳችን ለማዘጋጀት በቅተናል» ማለታቸውን ዘገባው ጠቁሟል። በዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር እስካሁን ከተደረጉት የዓለም ቻምፒዮናዎች በተሰጠው ደረጃ መሰረትም ዶሃ ቀዳሚውን ስፍራ መቆጣጠር ችላለች። ለንደን ሁለተኛ ስትሆን፤ የሴቪላ፣ የቤጂንግ እና የበርሊን ቻምፒዮናዎች ከአንድ እስከ አምስት ያለውን ደረጃ ይዘዋል። በዚህ ቻምፒዮና ላይ በርካታ ወጣት አትሌቶች የታዩ ሲሆን የሜዳሊያ ባለቤቶችም ሆነዋል። ከእነዚህ ስኬታማ አትሌቶች መካከል ደግሞ ኢትዮጵያዊያኑ ሰለሞን ባረጋ እና ለሜቻ ግርማ ተጠቃሽ ሆነዋል።አዲስ ዘመን  መስከረም 27/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "e89e3596cf846fe32929f8ef7b64ad76" }, { "passage": "ዓመቱን ሙሉ አትሌቶችን የሚያፋልመው ዳይመንድ ሊግ ውድድር ከአዲሱ የፈረንጆቹ ዓመት 2020 ጀምሮ ስምንት ውድድሮችን እንደቀነሰ አስታውቋል፡፡ የ3ሺ ሜትር መሰናክል እና ረጅሙ የሩጫ ውድድር የሆነው 5ሺ ሜትር እንደማይካሄድም ታውቋል፡፡ ውድድሩ ትኩረቱን በአጫጭር እና መካከለኛ እንዲሁም በሜዳ ተግባራት ላይ የሚያደርግም ይሆናል፡፡ በተያዘው ሳምንት የውድድሩ አዘጋጆች ዕቅዳቸውን ሲያሳውቁ 5ሺ ሜትር አለመካተቱ ተረጋግጧል፡፡ በዚህ ዓመት በዳይመንድ ሊጉ የሚካሄዱት ውድድሮች ቀድሞ ከነበረው 14 አንሶ 12 ብቻ ይሆናል፡፡ ከእነርሱም መካከል ሰባቱ ብቻ የሩጫ ውድድሮች ሲሆኑ ረጅሙ ርቀት ደግሞ 3ሺ ሜትር ይሆናል ማለት ነው፡፡ ይህ የሆነውም አዘጋጁ አካል ከአትሌቶች፣ አሰልጣኞች፣ ደጋፊዎች እንዲሁም ከመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ጋር በተደረገ ምክክር እና ጥናት መሰረት እንደሆነም ፍሎ ትራክ የተባለ ድረገጽ አስነብቧል፡፡ ዓመቱን ሙሉ በአስራ አራት ዙር በተለያዩ ሃገራት ከተሞች በመዘዋወር የሚካሄደው ይህ አትሌቲክስ ውድድር ከአዲሱ ዓመት ጀምሮ ረጅሙን ርቀት እንደሚያስቀር ቀደም ብሎ ማስታወቁ ይታወሳል፡፡ ይህንን ተከትሎም በተለይ በርቀቱ ስኬታማ የሆኑት የምሥራቅ አፍሪካ ሃገራት የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ተቃውሟቸውን ሲያቀርቡ ቆይተዋል፡፡ ኢትዮጵያም በሃሳቡ እንደማትስማማ በፌዴሬሽኑ አመራሮች በኩል ለዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ማስታወቋ አይዘነጋም፡፡ ይሁን እንጂ ዓለም አቀፉ ማህበር በውሳኔው በመስማማት በርቀቶቹ መሰረዝ ላይ ያለውን ድጋፍ አንጸባርቋል፡፡ ውሳኔው እውን መሆኑን ተከትሎ ከኢትዮጵያ በኩል የተሰማ አስተያየት ባይኖርም ሌሎች አገራት ተቃውሟቸውን በማሰማት ላይ ይገኛሉ፡፡ በ3ሺ ሜትር መሰናክል የዓለምን ክብረወሰን የሰበረችው ኬንያዊቷ ባትሪስ ቼፕኮች፤ ውሳኔው ውድድሮቹን እንደ መግደል እንደሚቆጠር ተናግራለች፡፡ በአዲሱ የዳይመንድ ሊግ መርሐግብር መሰረት በሁለቱም ፆታ አስራ ሁለት አስራ ሁለት ውድድሮች ሲካሄዱ የመቶ ሜትር፣ የመቶና መቶ አስር ሜትር መሰናክል፣ አራት መቶ ሜትር፣ አራት መቶ ሜትር መሰናክል፣ ስምንት መቶ ሜትር፣ አንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር፣ ርዝመት ዝላይ፣ ከፍታ ዝላይ፣ ምርኩዝ ዝላይ፣ ጦር ውርወራና መዶሻ ውርወራ ውድድሮች ብቻ የዳይመንድ ሊጉ አካል ይሆናሉ፡፡ አዲስ ዘመን ጥቅምት28/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "df5b5d1d48000416cbffa53d38f2d214" }, { "passage": " ኢትዮጵያ በአትሌቲክስ ስፖርት በተለይ ከምትታወቅባቸውና ውጤታማም ከሆነችባቸው ርቀቶች መካከል ይጠቀሳል፤ 5ሺ ሜትር። ከሁለት ዓመታት በፊት በለንደን በተካሄደው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ኢትዮጵያ በአትሌት ሙክታር እንድሪስ አማካኝነት የርቀቱ ቻምፒዮን መሆኗ ይታወሳል። በቅርቡ በተጠናቀቀው የዳይመንድ ሊግ ውድድር ላይም በተመሳሳይ የዓለም ፈጣኑ ሰዓት የተመዘገበው በኢትዮጵያዊ አትሌት መሆኑ ይታወቃል። ይህም ከተጀመረ ዛሬ አራተኛ ቀኑን ባስቆጠረው የዶሃ ዓለም ቻምፒዮና ላይ የርቀቱን ቀዳሚ የአሸናፊነት ግምት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች እንዲያገኙ አድርጓል። በዚህ ውድድር ተጋባዥ ከሆነው ቻምፒዮኑ ሙክታር ባሻገር፤ ጥላሁን ኃይሌ፣ ሰለሞን ባረጋ፣ እንዲሁም አባዲ ሃዲስ አገራቸውን የሚወክሉ አትሌቶች ናቸው። ይሁን እንጂ አባዲ ሃዲስ ማጣሪያውን ማለፍ አልቻለም። ቀሪዎቹ አትሌቶች በግላቸው ያስመዘገቧቸው ሰዓቶች በርቀቱ ከሚሳተፉት አትሌቶች ሁሉ ፈጣን መሆኑ፤ የርቀቱ ክብር ዘንድሮም ከምሥራቅ አፍሪካውያኑ እጅ እንደማይወጣ ያመላከተ ሆኗል። በሦስት ቻምፒዮናዎች ላይ በተከታታይ መንገስ የቻለው እንግሊዛዊው አትሌት ሞ ፋራህ ዘመን ከማብቃቱ ጋር በተያያዘም ሜዳሊያው የኢትዮጵያውያን ስለመሆኑ ግምታቸውን የሚያስቀምጡም በርካታዎች ናቸው። ኢትዮጵያ በቻምፒዮናው እስካሁን ድረስ ወርቅ አለማስመዝገቧን ተከትሎም እነዚህ ወጣት አትሌቶች የመጀመሪያው የወርቅ ሜዳሊያ ተስፋ ሆነዋል። ሞ ፋራህን በመጨረሻው\nየመም ውድድሩ የረታው\nየዓለም ቻምፒዮኑ ሙክታር\nእድሪስ በዚህ ቻምፒዮና\nላይ ተጋባዥ ቢሆንም\nበጉዳት ምክንያት በዛሬው\nውድድር ተሳታፊ ላይሆን\nእንደሚችል ተገምቶ ነበር።\nይሁን እንጂ ሙክታር\nማጣሪያውን አልፎ ዛሬ\nበፍፃሜ ተፋላሚ እንደሚሆን\nአረጋግጧል። የሁለት ጀግና አትሌቶችን ስም አጣምሮ የያዘው ወጣቱ አትሌት ጥላሁን ኃይሌ በቀለ ለአሸናፊነት ከሚጠበቁት መካከል አንዱ ሲሆን፣ በሮም ዳይመንድ ሊግ ያስመዘገበው\n12:52.98 የሆነ ሰዓት በዛሬው ውድድር ላይ የሚካፈሉት አትሌቶች ሁሉ ፈጣኑ ነው። በለንደኑ ቻምፒዮና በርቀቱ\nአምስተኛ ደረጃን በመያዝ\nያጠናቀቀው ሌላኛው ወጣት\nአትሌት ሰለሞን ባረጋም\nበዚህ ውድድር የአሸናፊነት\nቅድመ ግምት ያገኘ አትሌት ነው። አትሌቱ እአአ በ2018 ያስመዘገበው ፈጣን ሰዓት 12:43.02 ከርቀቱ ተሳታፊዎች ሁለተኛው ምርጥ ሰዓት ነው። ሰለሞን የዓለም ቻምፒዮና ተሳትፎው ይህ ሁለተኛው መሆኑ የተሻለ ልምድ እንደሚያስገኝለት የሚታመን ሲሆን፤ ለፈጣኑ ሰዓት ያለው ቅርበትም የወርቅ ሜዳሊያውን ለማጥለቅ የሚሮጥ ያሰኘዋል። ባህሬናዊው ብርሃኑ ባለው\n12:56.26 ሰዓት በማስመዝገብ ኢትዮጵያውያኑን አትሌቶች የሚከተል ከመሆኑ ባሻገር ለኢትዮጵያውያኑ ፈተና እንደሚሆንባቸውም ይጠበቃል። ኮማንደር ቶሌራ ዲንቃ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የ5ሺ እና 10ሺ ሜትር አሰልጣኝ፤ ርቀቱ በዓለም ላይ ፈጣን ሰዓት ባላቸው አትሌቶች የተዋቀረ መሆኑን ይጠቁማሉ። አዳዲስና ጥሩ ሰዓት ያላቸው ወጣት አትሌቶች ተሳታፊ የሚሆኑበትም ነው። በተጨማሪም ሁሉም አትሌቶቹ በዓመቱ ዳይመንድ ሊግ ላይ ርቀቱን በደንብ የሸፈኑ አትሌቶች መሆናቸው ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ እንደሚረዳቸው በዝግጅታቸው ወቅት ለአዲስ ዘመን ገልጸዋል። በዓለም ቻምፒዮና በ5ሺ ሜትር የኢትዮጵያ ታሪክ እ.አ.አ 1991 ቶኪዮ ላይ ይጀምራል፤ በወቅቱ ፊጣ ባይሳ ኬንያዊውን አትሌት ተከትሎ በመግባት የብር ሜዳሊያ ነበር ያገኘው። ከሁለት ዓመታት በኋላም በስቱትጋርት ኃይሌ ገብረስላሴ እና ፊጣ ባይሳ ተከታትለው በመግባት የብርና የነሐስ ሜዳሊያ ተሸላሚዎች ሆነዋል። እ.አ.አ 2001 ኤድመንተን ላይ በተካሄደው ቻምፒዮና ሚሊዮን ወልዴ ሦስተኛውን የብር ሜዳሊያ እስካስመዘገበበት ጊዜ ድረስም ኢትዮጵያ በሦስት መድረኮች ከሜዳሊያ ሰንጠረዥ መግባት አልቻለችም ነበር። እ.አ.አ 2003 ቀነኒሳ በቀለ የነሐስ፣ ሄልሲንኪ በስለሺ ስህን የብር፣ በርሊን በቀነኒሳ የወርቅ፣ ዴጉ በደጀን ገብረመስቀል የነሐስ፣ ሞስኮ እና ቤጂንግ ሐጎስ ገብረሕይወት ብርና ነሐስ እንዲሁም ለንደን ላይ ሙክታር እድሪስ የወርቅ ሜዳሊያ ያጠለቁ አትሌቶች ናቸው። በርቀቱ ምሥራቅ አፍሪካዊቷ አገር ኬንያ በርካታ ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ ቀዳሚ ስትሆን፤ 14ሜዳሊያዎችን ወደ ካዝናዋ አስገብታለች። አምስት ሜዳሊያዎች ያሏት እንግሊዝ ደግሞ በወርቅ ሜዳሊያ ብዛት ሁለተኛ ስትሆን፤ በተከታይነት ኢትዮጵያ 2የወርቅ፣ 5የብር እና 4የነሐስ በጥቅሉ 11ሜዳሊያዎችን በወንድ አትሌቶች በማግኘት ሦስተኛ ስፍራ ላይ ተቀምጣለች። በዓለም ቻምፒዮናው የርቀቱ ክብረወሰን እ.አ.አ በ2003 የተመዘገበው\n12:52.79 ሲሆን፤ ኬንያዊው አትሌት ኢሉድ ኪፕቾጌ ደግሞ የሰዓቱ ባለቤት ነው። ሌላው ዛሬ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚካፈሉበት ርቀት የ3ሺ ሜትር መሰናክል ሴቶች ምድብ ነው። ኢትዮጵያ በዚህ ውድድር እ.አ.አ 2013ቱ የሞስኮ ቻምፒዮና ነበር የነሐስ ሜዳሊያ በአትሌት ሶፊያ አሰፋ ያስመዘገበችው። ሶፊያ በዚህ ርቀት በ2012ቱ የለንደን ኦሊምፒክም ሦስተኛ የወጣች ቢሆንም፤ ቀድማት የገባችው አትሌት የአበረታች ቅመም ተጠቃሚነቷ በመረጋገጡ የብር ሜዳሊያውን ሶፊያ እንድትወስድ ተደርጓል። በዘንድሮው ቻምፒዮና ላይ አትሌት መቅደስ አበበ፣ ሎሚ ተፈራ፣ ዘርፌ ወንድምአገኝ እና አገሬ በላቸው ኢትዮጵያን ይወክላሉ። የ3ሺ ሜትር መሰናክል አሰልጣኝ ተሾመ ከበደ፤ አትሌቶቹ በራባት የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች ላይ ተሳታፊ በመሆናቸው ረዘም ላለ ጊዜ በሳምንት ስድስት ቀን በቀን ደግሞ ለሁለት ጊዜ በዝግጅት ላይ መቆየታቸውን ተናግሯል። በሄንግሎ በተካሄደው የሰዓት ማሟያ ውድድር ላይ የተመዘገበው ጥሩ ሰዓት መሆኑን የጠቆሙት አሰልጣኙ፤ በርቀቱ ያለውን ታሪክ ለመቀየር ቡድኑ ወደ ዶሃ ያመራ መሆኑንም አስረድተዋል። በዚህ ርቀት ኬንያውያን አትሌቶች ስኬታማ ሲሆኑ ባትሬክ ቼፕኮች ደግሞ በለንደን ቻምፒዮን መሆኗ አይዘነጋም። አትሌቷ ከ2018 ጀምሮ በተሳተፈችባቸው 17 ውድድሮች 15ቱን ያሸነፈች ጠንካራ አትሌት ስትሆን፤ በተያዘው ዓመት ያስመዘገበችው 8:55.58 የሆነ ሰዓት ደግሞ ፈጣኑ ነው። 9:03.71ሰዓት ያላት ኖራህ ጀሩቶ በ3ሺ ሜትር መሰናክል የአሸናፊነት ግምት እንዲሁም ፈጣን ሰዓት ያላቸው ኬንያውያን አትሌቶች ሁለተኛዋ ናት። እ.አ.አ የ2015 ቻመፒዮኗ ሃይቪን ኪያንግ 9:03.83 በሆነ ሰዓት ሦስተኛዋ ፈጣን አትሌት ናት። ለንደን ላይ ቻምፒዮን የነበረችው አሜሪካዊቷ ኤማ ኮቡርን አራተኛው ፈጣን ሰዓት ያላት ስትሆን፤ ከኬንያውያኑ አትሌቶች ጋር ብርቱ ፉክክር እንደምታደርግም ይጠበቃል።አዲስ ዘመን  መስከረም 19/2012 ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "8783d01e57a66da3bce79909914663e3" }, { "passage": " በተለያዩ የዓለም ከተሞች በመዘዋወር የሚካሄደው የዳይመንድ ሊግ ውድድር፤ ዘጠነኛውን ዙር በሞናኮ ያካሂዳል። በተያዘው ሳምንት መጨረሻ በዕለተ አርብ የሚካሄደው ይህ ውድድር፤ ዘንድሮ መታሰቢያነቱን ለአንድ አትሌት አድርጓል። በቅርቡ በሞት የተለየችውን በ1ሺ 500 ሜትር እና 5ሺ ሜትር ሩጫዎች ታዋቂዋን አሜሪካዊት አትሌት ጋብሬሌ ግሩንዋልድ። ባለፈው ወር በካንሰር ህመም ለህልፈት የተዳረገችው አትሌቷ፤ በተያዘው ወር 33ኛ ዓመት የልደት በዓሏን ታከብር ነበር። ይህንን እና አትሌቷ እአአ በ2013 በ1ሺ500 ሜትር የግሏን ምርጥ ሰዓት ማስመዝገቧን ምክንያት በማድረግ ሩጫው መታሰቢያ እንዲሆናት መደረጉን ዳይመንድ ሊግ በድረገጹ አስነብቧል። ከዚህ ባሻገር በሴቶች መካከል የሚካሄደው የማይል ውድድር የጋቤ ማይል በሚል ተሰይሟል። ይህ ውድድርም ሦስት ሴት የዓለም ክብረወሰን ባለቤት አትሌቶችን የሚያገናኝ ሲሆን፤ እአአ በ2015 የ1ሺ500 ሜትር ውድድር ክብረወሰን የሰበረችው ገንዘቤ ዲባባን፣ ያለፈው ዓመት የ3ሺ ሜትር መሰናክል ባለ ክብረወሰኗ ባትሬስ ቼፕኮች እንዲሁም በዚህ ዓመት የ5ኪሎ ሜትር ክብርን የተቀዳጀችው ሲፈን ሃሰን የሚያደርጉት ፍልሚያ ተጠባቂ ሆኗል። ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ገንዘቤ ዲባባ ደግሞ በርቀቱ የሴቶች ቁጥር አንድ አትሌት በመሆኗ ለአሸናፊነት ትጠበቃለች። ገንዘቤ እአአ በ2015 በሞናኮ ርቀቱን ያሸነፈችበት 3:50:07 የሆነ ሰዓት እስካሁንም ሊደፈር ያልቻለ የዓለም ፈጣኑ ሰዓት ሲሆን፤ አትሌቷ የዓለም ሻምፒዮናም ነበረች። በዓለም ሻምፒዮናው በ5ሺ ሜትርም ሜዳሊያ ያጠለቀችው አትሌቷ የዓመቱ ምርጥ ሴት አትሌት በሚል መመረጧም የሚታወስ ነው። በቤጂንጉ ዓለም ሻምፒዮና ሻምፒዮን ስትሆንም በሪዮ ኦሊምፒክ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ነበር ያጠናቀቀችው። ከዚህ ባሻገር በዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና የ1ሺ500 ሜትር ለንግስናዋ ተስተካካይ አልተገኘላትም። የርቀቱን ክብረወሰን የጨበጠችበት የዚህ ርቀት ሰዓት የተመዘገበው በሞናኮ መሆኑ እንዲሁም በርቀቱ ያላት ልምድ ደግሞ በዚህ ውድድር ላይም አግዟት እንደምታሸንፍ በአትሌቲክስ ቤተሰቡ ዘንድ ተስፋ ተጥሏል። በዚህ ርቀት ታዋቂ የሆነችውና በቤጂንግ እና የለንደን የአትሌቲክስ ዓለም ሻምፒዮናዎች ላይ ሁለት የነሐስ ሜዳሊያዎችን ማጥለቅ ችላለች። አትሌቷ በተለያዩ አህጉር አቀፍ ውድድሮችና ሌሎች ውድድሮች ላይም በ1ሺ 500ሜትር የተሻለ ውጤት ካስመዘገቡ አትሌቶች መካከል ትጠቀሳለች። አትሌቷ ከወራት በፊት በዚሁ በሞናኮ በተካሄደ የ5ኪሎ ሜትር ሩጫ ላይ14:44 የሆነ ክብረወሰን አስመዝግባለች። አትሌቷ የርቀቱን የመጨረሻ መስመር የረገጠችበት ሰዓት ክብረወሰን ሊባል የቻለው 15:48 የነበረውን የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻሉ ነው። ይህም ሲፈንን ለባለ ክብረወሰኗ አትሌት ገንዘቤ ዲባባ ፈተና እንደሚሆንባት ይጠበቃል። ኬንያዊቷ አትሌት የመሰናክል ስፔሻሊስት የምትባል ሲሆን፤ በሪዮ ኦሊምፒክና በለንደኑ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናዎች ላይ አራተኛ ደረጃን በመያዝ ነበር ያጠናቀቀችው። ከዚያ በኋላ ባሉት ጊዜያት ግን በርቀቱ ወደ አሸናፊነት ከመምጣትም ባለፈ የክብረወሰን ባለቤት ልትሆን ችላለች። ርቀቱን 8:50 የነበረውን ሰዓት 8:45 በማሻሻል የመጀመሪያዋ ሴት አትሌት ናት። አትሌቷ ከመሰናክል ባሻገር በ1ሺ500 ሜትርም የምትሮጥ ሲሆን፤ እአአ በ2015 በተሳተፈችበት የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች የነሐስ ሜዳሊያ ባለቤት ነበረች። ባለፈው ዓመት በተካሄደው የኮመን ዌልዝ ጌምስ ርቀቱን ሁለተኛ በመውጣት ርቀቱን ሸፍናለች። በዚያው ዓመት በተካሄደው የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ተሳትፎዋም ሰባተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች። ይህ ውጤቷም አትሌቷን በዚህ ርቀት የተሻለ ውጤት ታመጣለች በሚል እንድትጠበቅ አድርጓታል። በወንዶች በኩል ደግሞ በቅርቡ ለረጅም ዓመታት ተይዞ የቆየውን ክብረወሰን መስበር የቻለው ወጣቱ አትሌት ሳሙኤል ተፈራ ተሳታፊ እንደሚሆን ታውቋል። በዚህ ውድድርም በተመሳሳይ ጠንካራ አትሌቶች የሚሳተፉበት እንደመሆኑ የአሸናፊነት ግምቱ አዳጋች ሆኗል። ኢትዮጵያዊው አትሌት በቅርቡ በበርሚንግሃም በተካሄደው የቤት ውስጥ የዓለም ሻምፒዮና፤ 1ሺ500 ሜትሩን ለመሸፈን የፈጀበት ጊዜ 3:31.04 ነበር። ይህም በውድድሩ አሸናፊ ይሆናል በሚል እንዲጠበቅ ቢያደርገውም፤ የዓለም ሻምፒዮኑ ኤልጃህ ማናንጎይ እና የኦሊምፒክ ሻምፒዮኑ ማቲው ሴንትሮዊትዝ ለውድድሩ ከባድ ፈተና እንደሚሆኑ ተገምቷል።አዲስ ዘመን ሀምሌ 1/2011 ", "passage_id": "4c4d78e5ad8be6855a25b83661664340" }, { "passage": "የዓለም አትሌቲክስ የፕላቲነም ደረጃ በሚሰጠው የቶኪዮ ማራቶን እስካሁን ከተደረጉ 13 ውድድሮች በወንዶች 4 በሴቶች 6 ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸንፈዋል፡፡ የቦታው ክብረ ወሰን የተያዘው ግን በኬንያውያን አትሌቶች ነው፡፡\nበመጪው የአውሮፓውያኑ መጋቢት 1 በሚጀመረው በዚህ የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያኑ ብርሃኑ ለገሰ እና ሩቲ አጋ ያሸንፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የዓለም አትሌቲክስ ዘገባ ያሳያል፡፡\nብርሃኑ ለገሰ በ2019 ቶኪዮ ላይ ርቀቱን በ2፡04፡48 በማጠናቀቅ ሲያሸንፍ በዚሁ አመት በርሊን ማራቶን ላይ ኤሉድ ኪፕቾጌን 2፡02፡48 በሆነ ሰዓት ተከትሎ ገብቷል፡፡ ይህም ምርጥ የግል ሰዓት ሆኖ ተመዝግቦለታል፡፡ሆኖም በቶኪዮው ውድድር ልክ እንደ ብርሃኑ ሁሉ ርቀቱን ከ2 ሰዓት ከ05 ደቂቃ በታች የገቡ ስምንት አትሌቶች መኖራቸው ፉክክሩን ከፍ እንደሚያደርገው ይጠበቃል፡፡\nየዱባይ ማራቶን አሸናፊው ጌታነህ ሞላ፣ሲሳይ ለማ፣አሰፋ መንግስቱ እና ኃይሌ ለሚ ኢትዮጵያውያን የብርሃኑ ተቀናቃኞች ናቸው፡፡የውድድሩ የሁለት ጊዜ አሸናፊ ኬንያዊው ዴክሰን ቹምባ በተመሳሳይ የአሸናፊነቱን ቅድመ ግምት አግኝቷል፡፡የዓለም ሻምፒዮና የነሃስ ሜዳሊያ ባለቤቱ አሞስ ኪፕሩቶ እና ቤዳን ካሮኪምም የውድድሩ ተሳታፊዎች ናቸው፡፡\nልክ እንደ ብርሃኑ ሁሉ ኢትዮጵያውያኑ ሴት አትሌቶችም በፉክክሩ ይጠበቃሉ፡፡ የውድድሩ የባለፈው ዓመት አሸናፊ ሩቲ አጋ ክብሯን ለማስጠበቅ እንደምትሮጥ ይጠበቃል፡፡ሩቲ 2፡20፡40 ነበር ርቀቱን ያጠናቀቀችው፡፡ ከ2 ዓመት በፊት በበርሊን ማራቶን 2፡18፡34 በመግባት ሁለተኛ ወጥታ ነበረ፡፡ ሰዓቱም ምርጥ የግል ሪከርዷ ነው፡፡\nየውድድሩ የ2015 እና 2018 አሸናፊዎቹ ብርሃኔ ዲባባ እና ትርፌ ጸጋዬ ሩቲን ለመፎካከር ቅድመ ግምትን አግኝተዋል፡፡ ብርሃኔ ባሳለፍነው ወር ስፔን ቫሌንሺያ ላይ ሶስተኛ ስትወጣ የገባችበት 2፡18፡46 ምርጥ የግል ሰዓቷ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ በውድድሩ የኢትዮጵያ የግማሽ ማራቶን የክብረ ወሰን ባለቤት ሰንበሬ ተፈሪም ትሳተፋለች፡፡\nየቶኪዮ ማራቶን ከባድ ፉክክር የሚጠበቅበት ብቻም ሳይሆን የተሻለ ሰዓት የሚያስመዘግቡ ጃፓናውያን አትሌቶች ለኦሎምፒክ የሚመለመሉበት ነው ተብሏል፡፡\n", "passage_id": "d15ffe2ac0bf7fe94a03944f0f1b5f8e" } ]
3937ddb483244f33d24e7d8e99f63c58
d7ff0b5545f060e154c21078eb959f90
ለራስ ሲባል ሌላውን …
ኧሯ! እንዴት ሆኖ እንዴት ሆኖ እኛንማ አይደፍርም! ብለን ነበር ደፈረን። በሩቅ ሆኖ የሰማነው ዜና ገስግሶ መጥቶ አጠገባችን ከደረሰ የወራት እድሜን አስቆጠረ። በሰው ሀገር ሲነገር፤ ሲወራ እኛ ዘንድ የማይደርስ መስሎን ተዘናግተንማል። እኛ ሀገር አይገባም ፤ ጥቁሮችን አይነካም በማለት እራሳችንን በማይሆን ተስፋ እያታለልን ቆይተናል። ቁርጡ ቀን ደርሶ በሀገራችን የቫይረሱን መገኘት እውነታ ሲነገር ሰምተን ላለማመን ያመነታነው ስንቶቻችን እንሆን? ታዲያ አስፈሪ ዝናውን አስቀድሞ በርካቶቻችንን ኮርኩሮ ሃሳብ በማሰንዘር ፤ ከሃሳባችን መደምደሚያ ሳንደርስ ከች ብሎ ጉድ ያደረገን እሱም አይደል ወይ ኮሮና። ስለ ቫይረሱ ያለን እውቀት እንደ ግንዛቤ የሚለያይ ነው። አንዳንዱ ህይወቱ ግድ ሰጥቶ ለራሱ ኖሮ ሌላውን ለማትረፍ የሚጥረው ነው። ሌላው ደግሞ ለራሱም ሆነ ለሌላው ግድ የሌለው ቢነገረው ቢዘከር ሰምቶ እንዳልሰማ አይቶ እንዳላየ የሚሆን ነው። ራሱን በመኖርና ባለመኖር መካከል ከቶ በደመነፍስ እንደሚኖር ሰው ቫይረሱ ምንም እንደሚያመጣ የሚናገርም ዛሬ ድረስ አልጠፋም። ሰውን ለማዳን ራሱን ያልሰሰተውን ተመልክተን እሰየው በርታልን ጓድ እንዳላልን ሁላ ፤ በግዴለሽነት የሚኖረውን ደግሞ በትዝብት እያየን ከማለፍ ለመምከር የሞከርን እንኖራለን። የሚጠነቀቀውም ሆነ ግዴለሹ፤ የአንዱ ጤንነት የሌላው መኖር ዋስትና ነው ። የሰው ልጅ በምድር ላይ የሚኖረው ለራሱ ብቻ አይደለም፤ ለሌሎችም ነው። አንዱ ከሌለ የሌላው መኖር ትርጉም አልባ ነውና ። ህይወት ጣዕም የሚኖራት በመኖር ነው። መኖር ትርጉሟ ሙሉ የሚሆነው አንዳችን ለአንዳችን በሚኖረን አብሮነት ፤ መረዳዳትና መደጋገፍ ነው። ለዚህ ዋንኛው ደግም የኔ ጤንነት ሲጠበቅ የጎረቤት፤ የአካባቢዬ ፤ የሀገር፤ የሁሉም ጤና መሆን ግድ ይላል ። ታዲያ አለመታዘዛችን ከምን የመነጨ ይሆን? ለመኖር ራሳችን ከመጠበቅ ሌላው አማራጭ ይኖር ይሆን። ታላላቆቻችን፤ አባቶቻችን ማድመጥ፤ መደማመጣችንን እሴቶቻችንን ማን ነጠቀን? ለምን ረሳነው? በራሳችን ፈርደን በሌሎችም የመጨከን አባዜን ከየት አመጣነው? የሰውን ልጅ ሳይመርጥ ከምድረ ገጽ እያጠፋ ያለው ይህ ጨካኝ ቫይረስን እንዴት ልባችንን ሊያደነድን ቻለ። ሰው የሚችለውን ነውና የሚታዘዘው እራሳችንን እንመርምር ለመለወጥ መትጋት አለብን። የማንችለውን ትተን የምንችለውን መምረጥ ፤ ዛሬን መኖር ለነገ ተስፋ ነው። የእኛ ጥንቃቄ ለወገን መሆኑ ማመን አለብን። ነጭ፤ ጥቁር፤ ዘመድ፤ ባዕድ እያልን ራሳችንን ሳንከፋፈል ከስጋት ራስን ጠብቆ በማስመለጥ አብሮ ማምለጥ ይቻላልና ነው። ካለበለዚያ ግን “ከኑግ ጋር ያለህ ሰሊጥ አብረህ ተወቀጥ” ከሆነ ጉዳይ የታሪክ ተወቃሽ መሆናችን አይቀርም። መቼም ቫይረስ በሀገራችን ከተከሰተ ማግስት ጀምሮ ብዙ ለውጦችን፣ አዳዲስ ነገሮችን ታዝበናል። ለመከላከል የሚረዱን እጅን በሳሙና ቶሎ ቶሎ በደንብ መታጠብን ፤ ፊት በእጅ አለመንካት፤ አካላዊ ርቀትን መጠበቅ በዋናነት ከህክምና ባለሙያዎች የሚሰጡትን ምክሮች ተግባራዊ ለማድረግ ተሞክሯል። ለራሱ ያለ ራሱ ተጠንቅቆ ሌላውን ለማዳን እየጣረ እየተጋ ታይቷል። ይገርማችኋል! ለዛሬ ትዝብቴ መነሻ የሆኑት ይህንን የሰሙ የማይመስሉ የሰፈሬ ወጣቶች ናቸው። በከተማችን የሚገኙ በርካታ ወጣቶች በጎ ተግባራት ላይ በመሳተፍ ከወገናቸው ጎን የቆሙበትን አይተናል፤ ሰምተናልም። የነገ የሀገሪቱ ተስፋዎች መሆናቸውንም አስመስክረዋል። የኔ ሰፈር ወጣቶች ግን ቫይረስ መኖሩን አልሰሙም!! በአንድ ላይ በጋራ በመሆን መጠጥ ይጠጣሉ ፤ ጫት ይቅማሉ፤ መንገድ ዳር ተዛዝለው በሚባል ሁኔታ ሆነው ያወጋሉ። የቫይረሱ የተከሰተ ሰሞን አልነበሩም፤ ጠፍተው ነበር ። እሰየው አልኩኝ፤ ራሳቸውን ለመከላከል ወስነው ቤት ለመቀመጥ የከተሙ መስሎኝ። አልሰሜን ግባ በለው አሉ። ለካ የቦታ ለውጥ በማድረግ ከሰው አይን ዞር ብለው ነበር። ታዲያ እኔም የግዴታዬን ለመወጣት ወደእነሱ አመራሁ። በእግዜር ስላምታ ተቀላቀልኳቸው። ስለቫይረሱ አስከፊነት የነሱ መጠንቀቅ ለሚወዷቸው ሁሉ ፤ ለወላጆቻቸው፤ ለሰፈራችን ሁሉም እንደሆነ አስረዳኋቸው። ለማዳመጥ ፈቃደኛ ባልሆነ ጆሮ ሰሙኝ ። መልስ አልሰጡኝም። አንደኛው እሺ አለኝ ቀልድ በተሞላበት ፌዝ ። በእውነት አመመኝ። ለምን አትተሳሰቡም እርስ በርሳችሁ እንኳን አትዋደዱም አልኳቸው። እሺ ሌላው ቢቀርስ ለምን አትታዘዙም አልኩት? አቀርቀረው ስልካቸውን መጎርጎር ተያያዙት ። ትቻቸው ስሄድ መታዘዝ ከመሰዋዕትነት ይበልጣል አልኩ ሰምተውኛል፤ ግን ዝምታን መርጠዋል። ለብቻዬ እንዳስብበት የቤት ስራ የሰጡኝ ወጣቶች ዞር ብዬ በማየት ጉዞዬን በሃሳብ ቀጠልኩ። “ለምን ይሆን የተከለከለ ነገር የሚያምረን?” አልኩኝ ለራሴ ። ወደ አፈጣጣራችን ተመለስኩ ለካ አዳምን ከገነት ያስባረረው አታድርግ የተባለው በማድረጉ ነው። እኛም ዛሬ ለመቅጽበት ለሚያልፍ ቀን ብለን አታደርጉ የተባልነውን በማድረግ በጎ ተግባር እንደፈጸመ ጀግና በየአደባባዩ እንታያለን። ማንንም መስማት አንፈልገም፤ እራሳችንን ብቻ ካልሆነ በስተቀር ፤ ራሳችንን በቅጡ አውቀን ብናዳምጥ ጥሩ ነው። በዓለም ያሉ ሀገራት እንደኛ አይነት ተው ተብለው የማይሰሙ ዜጎች በመያዛቸው ነው። ዛሬ ለመስማት የሚቀፍ ዜና እየሰማን የምንገኘው። እነሱ ቢጸጸቱም ወደ ኋላ ሊመልሱት የማይችሉት ነገር ሆኖባቸዋል። ለኛ ትምህርት መሆን አለባቸው። እኛ ላይ በቅድሚያ ያልተፈጸመብን መሆኑን እያመሰገን ከሰማነው፣ ካየነው ቀድሞ መገኘት የግድ ይለናል። ጊዜው ፈጣን ነው ፤ ዛሬ ላይ እንኳን ቆመን ነገን ለማየት በተሰጠን መልካም እድል መጠቀም አለብን። ያለመታዘዛችን ዋጋ እንዳያስከፍል መበርታት ያስፈልገናል። ለዚህም ቀኑ ዛሬ እንጂ ነገ አይደለም። የቤት ስራን ከወዲሁ በመፈጸም ለወገን አለኝታነታችን በመግለጽ እራስን ሆኖ መገኘት፤ ታዝዞ መታዘብ ማስተማር ፤ቀዳሚ ሆኖ ለሌሎች አርአያ በመሆን መስመሩን በመጥረግ ከመስመሩ ያፈነገጡትን መመለስ ይገባል። የዛሬ ሁላችንም አብሮነትና ትብብርን አንዱ ለአንዱ መኖር ግድ ይሆናል። ታላላቆቻችንን በማስቀደም እነሱን አድምጠን ከዚህ አስከፊ አደጋ ማምለጥ ይኖርብናል። አብረን ስንሆን፣ ስንተባበር፣ ስንደማምጥ፤ ስንረዳዳ ያምርብናል። ባህሩን አቋርጠን መሻገር እንችላለን። የሰው ልጆችን እየጠረገ ያለውን አስከፊ ወረርሽን ለመከላከል ወኔ አቅም ጉልበት ይኖረናልና ። መጪው ጊዜ መልካም ዜና የምንሰማበት ጊዜ ይሁንልን ። አዲስ ዘመን ሚያዝያ 19/2012 ወርቅነሽ ደምሰው
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=31198
[ { "passage": "መልካም አስበን፣ መልካም ነገር ሰርተንና መልካም ሆነን መኖር ምን ይጎዳል? ማንን ይጎዳል? በእርግጠኝነት ሁሉም ሰው ይሄ ማንንም አይጎዳ ፤ እንዳውም መልካምነት እድሜን ያረዝማል፤ ክፋትና ተንኮልን ለማሰብ ጊዜ ያሳጣል ከዚያ ሲያልፍ ደግሞ እድሜ የሚያረዝመውን ደስታ ይጨምራል። ታዲያ ደስተኛ ሆነን ዕድሜያችንን ብናራዝም አይሻልም የክፋት ሶፍት ዌር ጭኖ ዕድሜን ከማሳጠር ። መልካምነት ለሌሎች አርአያ ያደርጋል፤ መልካምነት ብዙ መልካም ነገሮች አሉት እኔም አምናለሁ። መልካም ሰው ነው የሚባለው ግን ምን አይነት ነው? ምን የሰራ? ሌላው ሲሰርቅ ዝም ያለ? ስራ ማሰራት ወይም መስራት እያለበት ያንን ያልተወጣ? አጥፊ ሲያጠፋ የደበቀ የተባበረ …? ወይስ ደግሞ ሌላ። ይሄንንና መሰል ለሀገርና ለህዝብ የማይጠቅሙ ነገሮችን አይቶ እንዳለየ ያለፈ፤ ያላረመ ከሆነ ይሄ መጥፎ ሰው ነው ። ምናልባት ያ ሰው ጥፋቱ ለጊዜው ስላልታወቀበት ወይም ጥፋቱ ስለተደበቀለት ከመጋለጥ ድኗል እንበል ። ይሄ ግን በዚሁ አይቀጥልም ውሎ አድሮ ፤ ከርሞም ቢሆን መጥፎ የሰራ ሰው መጋለጡ አይቀርም ወይም ደግሞ ተመሳሳይ ድርጊት ሲፈጽም መያዙ አይቀሬ ነው። ለዚህ ሰው ታዲያ ጠላቱ ያ መጀመሪያ አይቶ ያለፈው ፤ ከጥፋቱ ያልገሰጸው ነው። በስራ ላይም ይሄው ነው ። የማይሆን ጥቅም ለማግኘት ብሎ የሚታትረውን ሳይሰራ በወሬ ጊዜውን የሚያጠፋውን ሰው እንዲሁም ባለስልጣንን መከታ አድርጎ ደረቱን የነፋ የኋላ ኋላ መውደቂያው የከፋ ሲሆን፤ የሚያማርረው በወቅቱ ያልገሰጸውን ሰው ነው ። በተቃራኒው ስራውን በተገቢው መንገድ በቅንነት የተወጣ ሰው ግን ይዋል ይደር እንጂ ስራው ያስከብረዋል፤ በጉብዝናው ፣በደግነቱና በቅንነቱ ይነሳል ፤ ይወደሳል… ። መልካምነትን ሁሉም ሰው በተለያየ መልኩ እንደሚገልጸው አምናለሁ። አንዳንዱ ከሀብቱ አካፍሎ የሰጠውን ሰው ቅን፣ ደግ፣ ለጋስ… ሲለው ሌሎች ደግሞ ስጦታ የትም አያደርስም እንዳውም ሰጪውንም በጊዜ ሂደት ያደኸያል ። ስለዚህ የሰዎችን ህይወት የማይለውጥ እርጥባን አይነት ስጦታ ተገቢ አይደለም ይላሉ። እነዚህ ሰው አይተው ወቅትን ቆጥረው በዘመቻ መልክ ለጋሾች ለመምሰል የሚሞክሩትን ለማለት አይደለም። እነሱ ለአንድ ወቅት እዩኝ እዩኝ የሚሉ ናቸው። ለማንኛውም ፍቀዱልኝ እኔ ይሄንን ልበል ። ( ከተሳሳትኩ እታረማለሁ) ። ለእኔ መልካምነት ለሚያውቀውም ሆነ ለማያውቀው ቀና ሆኖ የሚቀርብ፣ ቀና አመለካከት ያለው ፣ በዘር በብሄር የማይሸነፍ፣ ለሰው በሰላም ወጥቶ መግባት የሚመኝ ነው ። በተሰማራበት የስራ መስክ ለስራው ታታሪ፣ ስራውን አክባሪ ፣ የስራ ሰዓቱን ለስራው የሚጠቀም፣ የመንግስት ንብረትን ለመንግስት ስራ ብቻ የሚያውል፣ በተገልጋይ ክቡርነት የሚያምን … እሱ ለእኔ መልካም ሰው ነው። ይሄንን ስል ብዙ ጊዜ የመጥፎ ምሳሌ የምናደርጋቸው ሆኖም ግን አልፎ አልፎም ቢሆን በጣም ጥሩ የሚሰሩ የታክሲ አሽከርካሪዎችንና ረዳቶችን (“ወያላ አላልኩም” እሱም ከቅንነት መጉደል ያወጣነው ወይም የምንጠራበት ስያሜ ነው ) ላነሳ ነው። የተሳፈርኩበት ታክሲ “ እንኳን ደህና መጡ፤ እርሶን በማገልገላችን ደስ ብሎናል “ የሚል ጽሀፍ ከአሽከርካሪው ፊት ለፊት ይነበባል። ያልተለመደ የደንበኞች አቀባበል በመሆኑ የተጻፈውንና አይኔ የሚያየውን ፊደል በመጠራጠር ደግሜ ለማንበብ ሞከርኩ ቃሉ ይሄው ነው ። ራሴን ታዘብኩት ። ለምን ያነበብኩትን አልቀበልም አልኩ ፤ ይሄ እኮ በአእምሯችን ያለው የክፋት ሶፍት ዌር ነው። ለምን ይሄ ተጻፈ ብዬ ሌላ እንዳላስብ ያደረገኝ አልኩ ።ቅን ካለማሰብ የመጣ መሆኑን ተቀብያለሁ። የሌሎቹም ተሳፋሪዎች ሀሳብ ከሆዳቸው አልወጣም እንጂ ግርምቱ ግን ጭንቅላታቸው ውስጥ መኖሩ አይቀርም። መልካም ነገር ሲሰሩና ሲናገሩ አላየንምና ይሄንን ብናስብ አይፈረድብንም ። የታክሲ አሽከርካሪና ረዳቶችን በምንድነው የምናውቃቸው ማለቴ ከሚሰጡን አገልግሎት ባሻገር፤ በተለይ ከስነ ምግባር ጋር ተያይዞ ያለውን የታሪፍ መቆራረጥ፣ የዋጋ መጨመር፣ጠጋ ጠጋ ፣ ትርፍ አልጫንም አላስጭንም ያለ ይውረድ ፣በአቋራጭ …. በሚሉ ተግባራትና ንግግሮች ነው። አሁንም ቢሆን አልፎ አልፎ ጥሩ የሚባሉ መኖራቸውን ያዙልኝ። ይሄኛው በሌላ ቀን ነው ፤ መቼም የታክሲ ላይ ወግ ሞልቷል። ሁላችሁም ማለቴ የታክሲ ተሳፋሪዎችን ማለቴ ነው ብዙ ጊዜ ገጠመኞች አታጡም። የመጻፈ እድሉን አጥታችሁ እንደሆን እንጂ ከምለው በላይ ይኖራችኋል። ወደ ገጠመኜ። ተሳፋሪው መልከ መልካም አይነት ነው። ደርበብ ያለ፤ ደግሞም አንዳንድ ነገሮቹ ንግግሩን ጭምር ጆሮ ሰጥቶ ላደመጠ ውጪ ቀመስ ይመስላል። ብቻ ምንም አይነት ጉስቁልና አይታይበትም ልላችሁ ነው ።ከዚህ ወጣት ጋር ከመገናኛ 22 በሚለው ታክሲ ነው የተሳፈርነው ። የጉዞው ታሪፉ ደግሞ አንድ ብር ከሃምሳ ሳንቲም ነው ። ሁላችንም ሂሳብ ስንሰጥ ሁለት ብር የሰጠ የሃምሳ ሳንቲም መልስ አይሰጠውም። አስር እና አምስት ብር እያወጡ የከፈሉት ሽርፍራፊ ሳንቲም ሳይሆን የብር መልሶች ይመለስላቸዋል። ብቻ ረዳቱ ሂሳቡን ሲሰበስብ ተሳፋሪው ወጣት አምስት ብር አውጥቶ ሰጠ። ረዳቱም ሶስት ባለ ሳንቲም ብር ሊመልስለት እጁን ሲዘረጋ “ያዘው“ ይለዋል። ረዳት በቁጣ እንካ እኮነው የምልህ ሲል እጁን እንደዘረጋ ስራ አስፈታኸኝ በሚመስል ንግግር ተመነጫጨቀ። ተሳፈሪ ደግሞ “ችግር የለም ያዘው” ። በሁለቱ መካከል አልተግባቡም ብሎ ያሰበው ሌላው ተሳፋሪ ታዲያ “ቲፕ ነው“ አለ። በዚህ መካከል ተሳፋሪው መውረጃው ደርሶ ነበርና ወራጅ ሲል ተደፈርኩ ባዩ ረዳት “ለማኝህን ፈልግ… “ ሌላም ሌላም መጥፎ ቃላቶችን ተናግሮ ገንዘቡን ወደ ውጪ ወረወረለት። በሆነው ነገር ሁላችንም በአንድነት በሚመስል አስገራሚ አባባል እነሱ መች የሚያከብራቸውን ይፈልጋሉ፤ ሰውን አያከብሩ፤ እነሱም አይከበሩ ስንል ወረድንባቸው። በሁኔታው አንዳንዶች አዝነናል። አንድም ባለማወቅ ሌላው ደግሞ ከቅነነት ማጣት ይሆናል በሚል ። በውጪው አለም እንዳየነውና እንደሰማነውም ለታክሲ አሽከርካሪም ሆነ ለሌሎች መስተንግዶዎች ቲፕ ይሰጣል። ደረሰኝ በሚቆረጥባቸው የአገልግሎት መስጫ ቦታዎችም እንዲሁ ቲፕ ይቀመጣል። በእኛም ሀገር በተለይ ሆቴሎች፣ ኬክ ቤቶች፣ መዝናኛ ቦታዎች … ይሄ ሲደረግ አይተናል፤ አድርገናል። ያ ወጣትም ባደገበት ወይም በኖረበት ሀገር ለታክሲ አሽከርካሪ ወይም ለረዳት ቲፕ ቢሰጥ ክፋቱ ምን ላይ ነው። ሳስበው ሳስበው የተገጠመልን የክፋት ሶፍት ዌር የሚያሳስበን መጥፎ መጥፎውን ብቻ መሰለኝ ያ ረዳት እኮ ቲፕ ብለን ሳንሰጠው ከእያንዳንዳችን ተሳፋሪዎች ሃምሳ ሃምሳ ሳንቲም ነጥቆናል ፤ ወይም ሶስት ብር ቲፕ ሰጥተነዋል ያለፈቃዳችን ። በስህተት አንድ የተሳሳተ ጥሪ በእጅ ስልኩ ላይ የተደወለበት ሰው “ይቅርታ ወንድም ወይም እህት ተሳስተዋል “ ብሎ ከመመለስ ይልቅ ይሄ የእገሌ ስልክ አይደለም ከአሁን በኋላ ደግመህ /ደግመሽ እንዳትደውይ/ አትደውል ብሎ መዝጋትን ምን ይሉታል? ማንም ሰው ለመሳሳት ብሎ አይሳሳትም። ሳንቲሙን ለማውጣት ብሎ የማያውቀው ሰው የእጅ ስልክ ላይ አይደውልም። የሚሆነው ነገር በስህተት ነው ይሄንን በቅንነት ማየትና በትህትና መልስ መስጠት ማንን ገደለ? ቁጣን፣ መመናጨቅ፣ ማስጠንቀቅና ማስፈራራትስ ምን አመጣው ! አመል ወይስ ቅንነት ማጣት? ብቻ ክፉ ክፉውን እንድናስብና እንድንሰራ ሆነን እንጂ አለማወቅንም አለመፈለግንም በትህትና በቀናነት መመለስና መነጋገር ይቻል ነበር ። ኧረ የክፋት ሶፍት ዌራችንን እንቀይር!አዲስ ዘመን ሀምሌ 14/2011 ", "passage_id": "c64b37fc8d0b35d9632c12aeb0d9b0b7" }, { "passage": "እንዴት\nሰነበታችሁልኝ? እናተዬ የሕይወት ሩጫ ፋታ አይሰጥም አይደል? የሚገርመው ደግሞ ሩጫችን ሲጨምር የምንሮጥለት ነገር እየቀነሰ መሄዱ የሩጫችንን ያህል የሮጥንለት ነገር አለመሙላቱ የስገርማል፡፡ ወይ ጉድ ከሰው ጋር ለየን፤ ከወዳጅ ጋር አራራቀን እኮ፡፡ ግለኝነቱ ጠንክሮ የእርስ በእርስ ግንኙነታችንን ያላላው፤ ማህበራዊ ትስስራችንን ያሳሳውና አብሮነታችንን የሸረሸረው ምን ይሆን? አሁንማ አብረን ቁጭ ብለን የምናወራው መጓጓዣ መኪና ውስጥ ብቻ ሆኗል እኮ ጉድ ነው። ሰብስቦ ሳንፈልግ በጋራ አስቀምጦ የሚያስጉዘን ታክሲ የወጋችን መጠንሰሻ፣ የገጠመኞቻችን መነሻና የትዝብታችን መዳረሻ ሆኗል ታክሲ፤ ከቀናት በፊት ታክሲ ተሳፍሬ ስጓዝ የሰማሁት ገጠመኝ መነሻነት ትዝብቴን እያነሳሁ ላወጋችሁ ወደድኩ፡፡ “እማዬ እኔ ትልቅ ስሆን ቢራ እጠጣና መኪና ይደርሰኛል! ከዚያ ሁሌም አንቺን በመኪናው ይዤሽ ወደፈለግሽበት እወስድሻለሁ፡፡” ታክሲ ውስጥ አንድ የ4 ዓመት ሕፃን ከእናቱ ጋር በሚያደርገው ውይይት መሀል ከልጁ የሰማሁት ለዛሬ ጽሑፌ መነሻ ሆነኝ፡፡ ሐፃን\nነውና እሱን አልታዘብኩትም፤ ለሕፃናት የማያስቡትን ሚዲያዎች ለትውልድ ግድ የሌላቸውን ምርት አቅራቢያዎችና ገቢያቸውን ብቻ የሚያስቡትን የማስታወቂያ ድርጅቶች ታዘብኳቸው እንጂ፤ ይገርማል! እዚህ ሀገር ላይ ህግ አክባሪ ተቋም፣ መመሪያና መተዳደሪያ አክባሪ ሠራተኛ፣ ደንብ አስከባሪ መስሪያ ቤት ጠፍቶ ይሆን እንዴ? ስለኛ ግድ ሳይኖራቸው እዩን የሚሉን በቴሌቪዥን የሚተላለፉ ማስታወቂያዎቻችን ግን ወዴት ይሁን የሚያደርሱን? “ማን ይመለከታል? ምነስ ያስከትላል?” ተዘንግቷል። ይሄ ማህበራዊ ሀላፊነት ይሉት ነገር አፈር ደቼ በልቷል። ምን አገባኝ እኔ ብሩን ልሰብስብ እንጂ በምን መልክ ልሰብስብ አያሳስባቸውም፡፡ በብሄራዊ\nጣቢያዎቻችን ብሄራዊ ስካር ስከሩ እንባላለን፡፡ ወዳጆቼ አባት ከሕፃን ልጁ ጋር ቁጭ ብሎ የሚመለከታቸው ማስታወቂያዎች እናት ከሴት ልጇ ጋር የምትሰማቸው ስርዓት አልባ ምናምናችንን ገዝተው ይጠቀሙ ባዮች ነፃነት ነሱን፤ሃያ አራት ሰዓት ባልተገደበ ሁኔታ እንዳሻቸው የሚያስተዋውቁት ተገቢነት የሌለው ማስታወቂያ ልጁን እንዲህ እንዲያስብ ህልሙ እንዲዛባ አደረገው፡፡ በትንሽ አዕምሮው የሚያስበው የምኞቱ ጥግ ጠጥቶ መሸለም ሆነ፡፡ የሚመጥነው ተለክቶ አልተሰጠውማ ምን ያድርግ ተገኝ ብሩ የሚያየውን የሚሰማውን ተመኘ፤ የሚመኘውንም ተናገረ፡፡ ደሞ እኮ የተገረምኩት ያሳሰበን የልጁ እንደዚያ ማለት ብቻ አይደለም የናትየዋም ምላሽ እንጂ፡፡ የልጁ እናት በተናገሩት ነገር ተከፋሁ። በእነዚያ\nየስካር መንፈስ በሚጣሩ ማስተወቂያዎች የተጸነሰ ህልሙን ለተነፈሰው ልጅ እናቱ የሰጠችው ምለሽ እቅፍ አድርጋ ጉንጩን እየሳመች ጎሽ የኔ አንበሳ አንተ እኮ መኩሪያዬ ነህ! ብትለውስ? እም እሱን ነው የምፈልገው፤ እ… መኩሪያዬ ጉድ! እናት በልጅዋ የስካር ሽልማት መኩራትን ፈለገች፡፡ ልጁ ምን እያሰበ መሆኑ ተዘንግቷት ይሆን? ቆዩኝማ ዕድሜ አያስተምርም? ከፍ ሲባል ከፍ ያለ አተያይ አይለመድም? ዕድሜ ሲጨምር መገሰጫና ማረሚያ አይለይም? እናትነት በራሱ ምንም ሳይጨመር በጎና ክፉ ምኞት አያስለይም? የልጁ እናት ቅር አሰኘችኝ፤ ልጅማ አልኮል ጠጥቶ ከሚያመጣው ድሎት በትምህርት በርትቶ፤ ቀለም ጠጥቶ የሚያወራው ተረት በስንት ጣዕሙ፤ ስካሩ ውስጥ የሞላ የጤና መቃውስ ዘግናኝ አደጋ ሲብስም ሞት እኮ ነው ያለው እናትየዋ አላሰበችውም፡፡ እኔ\nምለው የኛዎቹ መገናኛ ብዙሃን ግን ምን ነካቸው? ለትውልድ አይታሰብም? የሚሠራው ሀገር ለመለወጥ፤ ሀገር ለማነጽ አይደል እንዴ? ኧረ ተው አንተዛዘብ ተው፡፡ የሚገርመው ይሄን ያለ ልክ የሚሰበከውን የአልኮል መጠጥ ማስታወቂያ ያሳሰበው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አንድ አዋጅ አውጥቶ አጽድቋል። ይበል የሚያሰኝ ነው። ያለ ልክ እንዲፈነጩ ተፈቅዶላቸው ከኢትዮጵያዊነት መለያ ከሆኑ እሴትና መልካም ልምዶች ጋር እየቀላቀሉ፣ ከጀግንነት፣ ከአብሮ መኖርና መተሳሰብ ውብ ባህላችን ጋር አዛንቀው ሀበሾች ውብ ናችሁ! ባህላችሁም ደስ ይላል! ስካርም ደንባችሁ ነው፡፡ እያሉን ነው፡፡ ከታሪካችን ጋር እየቀየጡ ለአደጋ ምክንያት ለጤንነት ጠንቅ መሆኑን ረስተው ማዋረዱን ደብቀው አስካሪ መጠጣቸው የደስታና የፌሽታ ምንጭ መሆኑን በተከሸኑና ሲሰሙዋቸው በሚያሰክሩ ቃላት ይሰብኩናል፡፡ ወዳጆቼ የአልኮል መጠጦችን ስያሜ ልብ ብላችሁ ታውቃላችሁ፡፡ በማስታወቂያቸው ስካርን የእኛ ባህል እንዳስመሰሉት ሁሉ ስያሜያቸውንም ከኛ ቀምተዋል፡፡ ሀበሻ ባህሉንና ታሪኩን እንደሚወድ ገብቷቸዋል፡ ፡ በተፈጥሮ ሀብቱ እንደሚማረክ ተረድተዋል፡፡ የጋራችን መጠሪያችንን ቀምተው፤ የተፈጥሮአዊ ሀብቶቻችንን ስም ነጥቀው፣ የታሪካዊ ቦታዎቻችን ስያሜ ወስደው በማን አለብኝነት ለራሳቸው መጠሪያ አደረጉት፡፡ በነገራችን ላይ በቅርቡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሚዲያ በሚታየው የአልኮል መጠጥ ማስታውቂያ አግባብነት ላይ መክሮ ስርዓት ለማስያዝ የሚያስችል አዋጅ አፅድቋል፡፡ በኢትዮጵያ\nየምግብ መድሀኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን ቀርቦ በምክር ቤቱ አባላት በሙሉ ድምፅ የጸደቀው አዋጅ አሁን ላይ በአንዳንድ የሚዲያ ተቋማት ሙሉ በሙሉ መተግበር ባይችልም ቀድሞ ለትውልድ ግድ ሳይሰጣቸው ባሻቸው መልክ ያቀርቡት የነበረውን ማስታወቂያ ሳይወዱ እንዲያቆሙ ተገድደዋል፡፡ ይህንን ተከትሎ ትላንት በአንድ ሬዲዮ ጣቢያ ላይ የአየር ሰዓት ተከራይቶ በመጠጥ ማስታወቂያ ሁለት ሰዓታት ሙሉ ያ …ዬ… ዩ….እያለ አንድ የረባ ቁም ነገር የሌለው ፕሮግራም ሲያቀርብ የነበረ የባህር ማዶ ዘፈን ጋባዥ “በዓለም ላይ የሌለ ህግ ወጣብን…አልኮል አታስተዋውቁ ተባልን፤ የትም ሀገር ተሰምቶም አይታወቅም..” እያለ ወሬና ቁም ነገር የጠፋበት በሬዲዮ ሞገዱ ላይ ድምፁን የሚያስተጋባውን ሰው ስሰማ ይበልጥ አዘንኩበት፡፡ አያችሁ ወዳጆቼ ለሱ መብት ጥያቄ ማለት ያላግባብ ትውልድን በሚያነትብ መልክ የሚቀርበውን ማስታወቂያ እያስተላለፈ ያለገደብ የሚያገኘውን ገቢ ቀነሰ ብሎ መጮህ ነው፡፡ ባይገርማችሁ የዚያን ቀን የሬዲዮ ፕሮግራሙ ሙሉው “እንዴት እንከለከላለን ሌላ ዓለም ላይ የሌለ ህግ ነው” ብሎ ዘራፍ ሲል ነበር ሰዓቱ ያለቀበት፤ እኔ ምለው የትኛው ሀገር ላይ ሰምቶ ይሆን ስርዓት በሌለው መልክ የሚተላለፍ ማስታወቂያ የማያውቁትን መናገር ለዚያውም ለራስ ጥቅም ብሎ፤ አያስተዛዝብም? ወይኔ አሳዘነኝ ይሄኔ እሱ ከራሱ ውጪ የሚመለከተው ዓለም ስለሌለ ይሆናል እኮ ዓለም ላይ የሌለ ህግ ነው ብሎ የተሟገተው፤ ሌላው ዓለም በእንደዚህ ዓይነት ማስታወቂያች ላይ የሚታየውን ጠንከር ያለ ክለከላ ቀድመን ተግብረን ቢሆን ኖሮ ወዳጆቼ ይህ ሰው ፈጽሞ ፕሮግራሙን ለአየር ማብቃት አይችልም ነበር፡፡ ግለሰቡ በራሱ የእነዚህ ማስታወቂያዎች ውጤት ሁሉ ይመስለኛል፤ ለማንኛውም ወዳጆቼ አነሰም በዛ አምላክ ለኛ የፈቀደውን፤ ወደኛም ያቀረበውን መብላታችን በዚያም መኖራችን አይቀሬ ነው። አይደል? በኑሯችን ለወገን አስበን፤ ለትውልድ ተጨንቀን፤ መልካም ነገር ዘርተን ማለፍ መቻል ደግሞ አቻ የሌለው ሰናይ ተግባር ነውና ጉዟችንንና ሥራችንን ሀገር በሚገነባ፤ ትውልድ በሚያንጽ መልኩ ብናደርግ ባይ ነኝ፡፡ ቸር ይግጠመን፡፡አዲስ\nዘመን መጋቢት 4/2011በተገኝ\nብሩ", "passage_id": "de934c4fd3dd07579bfe5067b337820b" }, { "passage": "ዲስ ላይ ኑሮ ተወዷል፤ ሸገር ላይ ህይወት ከብዷል። መዲናችን ለኔ ቢጤ ድሃ ጥሩን ለብሶ ማጌጥ ድንቁ፤ እህል ጎርሶ ማደር ብርቁ ሆኗል። ወገን በወገን ላይ ጨክኗል። ነጋዴው ደንበኛው (ሸማቹ) እንጀራው መሆኑን ረስቶ ዛሬ ኪስህን ካላጠብኩ እንቅልፍም አይወስደኝ፤ ተኝቼም አላድር ብሏል። ከገበሬው 1 ሺህ 500 ብር የገዛው ጤፍ ከተማ አምጥቶ ከ3,500 ብር ፍንክች አልልም ይላል። “ምነው ወዳጄ! ይሄ ደግም አይደል እንተዛዘን እንጂ ይሄን ያህል መጨካከን ተገቢ ነው?” ስትለው “ዶላር ጨምሮ ነው። ምን እናድርግ?” ይልሃል። ጤፉን በውጭ ምንዛሬ ከሩቅ ምስራቅ አስጭኖ ያስመጣው ይመስል። ነጋዴው ሸምሱ ከወይዘሮ ጫልቱ በ100 ብር የገዛው ቅቤ በ300 ብር መሸጡ ከዶላር መጨመር ጋር ምን አገናኘው? በሞቴ እስቲ አስረዱኝ። ነጋዴዎች ኧረ ተዉ! ወዴት እንሄድባችዋለን? ቀስ እያላችሁ ብትነጥቁን አይሻልም? ከበረገግን እኮ ለእናንተም መጥፎ ነው። የኛ ገቢ አድሮም ውሎም መድረሻው ወደ እናንተው ነው፤ ምን መሄጃ አለው ? ቆዩማ! እጀራችሁ እኛ መሆናችንን እየዘነጋ ችሁ ይሆን እንዴ? እኛ ከሌለን እናንተስ በምን ታድራላችሁ? ሰው እንጀራውን ይገፋል? እንጀ ራው ላይ ይጨክናል? ጭካኔያችሁ ደግሞ መክ ፋቱ ደግማችሁ እንዳትደርሱብኝ የማለትን ያህል “ስንት ነው?” ብለን ስጠይቅ ለመቁጠር ቀርቶ ለመጥራት የሚከብድ የገንዘብ መጠን መንገራችሁ አያስተዛዝበንም? ለኛ ባታዝኑ ለወገን ባትራሩ እንኳን ይሄ ለኛ ብረቅ የሆነው ገንዘብ እንዴት ነው የናቃችሁት? ቢያንስ ያስከበራችሁ ያህል ክብር ሰጥታችሁት አብሮዋችሁ እንዲቆይ ብታደርጉ አይሻልም? ገንዘብ አንዴ ካኮረፈ አኮረፈ ነው እንደኛ መሄጃ ያጣ አይደለም ጥሎዋችሁ እብስ ይላል። ንገሩኝማ ውድ ነጋዴዎች የወገንስ ኪስ ማጠብ፤ ያለአግባብ በትርፍ ላይ ትርፍ መሰብሰብ እንደው ደስታን ያጎናፅፍ ይሆን? እኔ አይመስለኝም። እውነተኛ ደስታ የራስን አሳልፎ ከመስጠት ጋር የሚያያዝ በመቸር የሚገኝ ልዩ ጉዳይ ነው። ይህ በድርሰት አለም ውስጥ የሚሰበክ አይደለም እውን ነው። እውነተኛ ደስታ በውስጣችን ለመፍጠር ቀድመን ማስደሰትን እንወቅ። እናም ነጋዴዎች ለወገን ማሰብ መልካም ነው፤ እንተሳሰብ። የደንበኛዬን እድሜ ያቆይልኝ ገቢውንም ያሳድግልኝ እያላችሁ ፀሎት አድርጉ እሱ ነው የሚያዋጣችሁ። የኔ ቢጤ ለፍቶ አዳሪዎች\nበነጋዴዎች የተፈጠረብን ጫና እያንገዳገደን ነው። እንደኔ አይነቱማ ብቻ መኖሩ አልቻል ሲለው አጋር ፍለጋ መባዘን ጀምሯል። ኣኣ..አጋር ያልኩት ትዳርን አይደለም ወዳጆቼ እሱማ አከራዮች ማቀብ ጥለዋል! መባሉን ሰምቶ የማግባት ሀሳቡን ተከራይ ሰርዟል። አከራዮች ለባለ ትዳር አናከራይም ለላጤ እንጂ ብለዋል አሉ። ጉድ ነው ላጤ አድርገው ሊያስቀሩን እኮ ነው። እናም የማወራው\nከትዳር ውጪ የሆነ ደባልነትን ነው። እናላችሁ እኔና የኔ ቢጤው የኑሩን ዳገት ለብቻ አልገፋ ቢለው አብሮ የሚያጋፋው መላ በመዘየድ ላይ ነው። እኔም ከሌሎች ጋር አብሮ በመሆን ኑሮን ለማሸነፍ አሰብኩ። መኖር ቢያቅተኝ\nጓደኞቼን ጠራው ለመመካከር፤ እንደው ምን ይሻል ይሆን ብሎ ስለ መፍትሄው ለማውራት። እነሱም እንደኔው ከጫፍ ደርሰው ነበርና “ባንድ አፍ!” አሉኝ። ሀሳቤን ቅዱስ ብለው ተቀበሉት። እናም ኑሮው ትንሽ ቢቀለን\nብለን አንድ ላይ በመኖር ወጪም ለመጋራት ተስማማን። አራት ባራት በሆነች አንድ ክፍል ቤት ውስጥ ለመኖር። አራት ነን በአንድ ቤት የምንኖር፤ አንድ ክፍል የምንጋራ፤ መሆን ሳንፈልግ የኑሮ መወደድ ያቆራኘን፤ ነፃነታችንን ማወጅ እየፈለግን ችግር ያዋደደን ጓደኛሞች። አስማተኛ\nሆነን ምናዘግምባት አዲስ አበባ (የምናወጣው ወጪ ገቢያችንን ስለሚበልጥ አመጣጡ እንዲሁ ግርም ስለሚለኝ ነው)፣ ኑሮን ማየት እንጂ ማኖር በማትፈቅደው በዚህች ጉደኛ ከተማ አዲስ አበባ (ለደሃ ማለቴ ነው) አንዱን በጠኔ ክርችም ሌላውን በተቃራኒው በቁንጣን በምታጨናንቀው አዲስ አበባ እንኖራለን ኣኣ…ተሳሳትኩ እንኖራለን ነው ያልኩት ማለቴ እናኗኑራለን። ሰሞኑን\nብርድም አይደል? ሲበርደን አንድ ሀሳብ መጣልንና ጃኬት ለመግዛት ተስማማን። አንድ ጃኬት ለአራት ነው። እንግዲህ ለመግዛት ያሰብነው። አንድ ጃኬት ለአራት በተራ ለመልበስ። በአንድ ጃኬት በተራ ለአራት ለማጌጥ። አራታችንም በጃኬቱ መገዛት ላይ ድምፅ ለመስጠት ተሰባሰብን በሙሉ ድምጽ ጸደቀና በመዋጮ ተገዛ። በነገራችን\nላይ የኛ ቤት ይለያል። አንድ ሰው ቢጎልም ምላዕተ ጉባዔው ስለተሟላ ስብሰባው ይደረግ ወይም ድምፅ ይሰጥ የሚለው ፍልስፍና እኛ ቤት አይሰራም። ምክንያቱም የጎደለው ሰው ሙሉ የቤቱ አባል ካልተሟላ ምንም ርእስ ተነስቶ ውይይት አይደረግበትም። ምክንያቱ ብዙውን ጊዜ የምንወያየው በመዋጮ ጉዳይ ስለሆነ ስብሰባው ላይ ያልተገኘው አላዋጣም እንዳይለን በመስጋት ነው። እኔ ነኝ ጃኬቱ እንዲገዛ\nሀሳብ ያቀረብኩ። ምክንያት ስጠየቅ አንድም ብርድ ነው በሚል ሁለትም አብሮን በተማረ የሌላ መስሪያ ቤት ሰራተኛ (ጥሩ ደመወዝ የሚከፈልበት መስሪያ ቤት የሚሰራን ሰው ጠቅሼ) ተለብሶ ማየቴን እንዳማረበትና እኛም በዙር ቢያምርብን ብዬ መሆኑን አስረዳሁ። “አዎ እኛ ከሱ በምን እናንሳለን\nአራት ሆነን መግዛት እንዴት ያቅተናል።” በሚል ፉከራ ይገዛ ተባለ። “አዎ በእርግጥ በደመወዝ እንጂ በጋራና በፍቅር በመኖርም እኛ የተሻልን ነን” አንዱ ጓደኛችን የጃኬቱ መገዛት እርግጥ እንዲሆን ለማፅናት በዛቻ መሰል መልክ ያሰማው ፉከራ ነበር። በዚህ እልህ የተገዛው\nጃኬት ለመልበስ እጣ ወጣና ለገረመው ደረሰው። በመዋጮ ለአራት የተገዛው ጃኬት የመጀመሪያ ሳምንት የገረመው ማጌጫ ሊሆን በቃ። ድምጽ የሚከበርበት ቤት ነውና ጸደቀለት። አይናችን እያቁለጨለጭን ፈቀድንለት። ኦ በነገራችን ላይ ይቅረታ ጓደኞቼን (ደባሎቼን) ሳላስተዋውቃችሁ። የኛ ቤት ልዩ ነገር የሁላችንም ስምና ባህሪ መመሳሰሉ ነው፤ ካንዱ በቀር። ጓደኞቼ ስማቸውና ባህሪያቸው በትንሹ ልንገራችሁ። ዜና፡- ቤታችንን\nበመረጃ ሙሉ የሚያ ደርግልን ጓደኛችን ነው። እኛ ቤት የመረጃ ችግር የለም። ዜና ባይኖር ከመረጃ ርቀን ቀርተን ነበር። ሬድዮ የለን፤ ቴሌቪዥን የለን። እናም ዜና መረጃዎችን እያነፈነፈ እንደ ጉድ ያዘንብልናል። ችግሩ ዜናዎቹ አብዛኛውን ጊዜ ሲግናላቸው በተበላሸ ሳተላይት ቲቪ እና ጣቢያቸው ባልተሰናሰለ ሬድዮ እየሰማ ነው መሰለኝ የተሟላ መረጃ አይነግረንም። ብዙው ዜና ጀምሮ ይተወዋል። ለነገሩ እኛም አሟላ ብለን አናስጨንቀውም። ባልተሟላ ኑሮ የተሟላ መረጃ ምን ያደርጋል። ገረመው፡-\nአቤት ነገሮች ሁሉ የሚገርሙት ሰው፤ ገረመው መገረም ዋንኛ ስራው ነው። በአንደኛው ጓደኛችን የሺጥላ የሺጥላ ተብሎ እራሱን እንኳን ማስጠለል ተስኖት ከኛ ጋር ተጠግቶ መኖሩ ያስገርመዋል፤ በእኛ ደህነትና በቢል ጌት ሀብታም መሆን ይደነቃል፤ በኤሊ መንቀርፈፍና በዩዜን ቦልት ፍጥነት ሲደነቅ፤ በጨርቆስና በቦሌ ልጆች የኑሮ ልዩነት ሲመሰጥ ብዙ ጊዜውን ይፈጃል። እኛም እየተመለከትነው ባለነው የገረመው መገረም ይገርመናል። አንዳንዴ ሳስበው ገረመው ለመገረም የተፈጠረ ሁሉ ይመስለኛል፤ ተገራሚው ገረመው። የሺ ጥላ ምስኪን\nራሱን የማይችለውን ሰው የሺ ሰው ጥላ አሉት። እኔም እንደገረመው በየሺ ጥላ በጣም እገረምበታለሁ። አራት ወራት በጋራ ስንኖር አንድ ቀን ምግብ የማብሰል ተግባር ብቻውን ተወጥቶ አያውቅም። አድርግ የተባለውን ሁሉ ገረመው እስኪገርመው ድረስ አልችልም ብሎ ያልፋቸዋል። ለነገሩ እሱ ምን ያድርግ ቤተሰቦቹ ናቸው የማይችለውን ያሸከሙት። እኔን ጓደኞቼ በሰኔ ይሉኛል፤ ሰኔን አልወደውም፣ ደጋግሞ ሰኔ ላይ መጥፎ ገጠመኝ ስለገጠመኝ ሰኔን እጠላለው። ከ13ቱ ወራት ሰኔን ቀንሰው አኔን ከመሳቀቅ ቢታደጉኝ እላለው። ምንም ነገር በሰኔ ቢጠይቁኝ እለፉኝ ባይ ነኝ። ጓደኞቼም በሰኔ ያሉኝ ለዚያም ነው። በቃ እኔ እና ሰኔ እንዲህ ነን፤ የተወለድኩት በሰኔ ነው። ምን አልባትም እንትን የምለው በሰኔ ይመስለኛል። እንትን ያልኩት አስፈሪ ቃል ሰኔ ላይ ማውራት ስለማልወድ ይቅርታ እለፉኝ ሰኔ ባይሆን ኖሮ አወራችሁ ነበር። ለዛሬ ይብቃኝ ሰላማቹሁ ይብዛልኝ።አዲስ ዘመን ሰኔ 21/2011 ", "passage_id": "c64f4c4228d89f5e45ae65bc72daa601" }, { "passage": "ተማሪዎች ናቸው የምስኪን ቤተሰብ ልጆች። ትምህርታቸውን የሚከታተሉት በመንግሥት ትምህርት ቤት ነው። ጠዋት ማልደው ሲሄዱና ተምረው ሲመለሱ ለተመለከተ በገፅታቸው ላይ የሚታየው ፈገግታ የሌላውንም ልብ ያሞቃል። የተማሏ ያልተቀዳደደ ዩኒፎር ለብሰዋል። ሁሉንም እኩል አንድ የሚያደርግ የትምህርት ቤት ዩኒፎርም፤ በመሐከላቸው ያለው ልዩነት የልብሱ ቀለም ብቻ ነው። ምን አልባት የክፍል ደረጃቸው የተለያየ ስለሆነ ይሆን ? ይሄን በውስጤ ያሰብኩት ነው። የቅድመ መደበኛ ፣ የአንደኛ ደረጃ፣ የመለስተኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ተብሎ የልብሱ ቀለም (ከለር) እንደዛ መልኩ የተለያየ ይሆናል። በትክክል ይሄ ነው ብዬ ልቀበል ምክንያቱም እኔ የተነሳሁት ከልብሱ ቀለም ላይ አይደለም፤ ትኩረቴ በልጆቹ ደስታ ላይ ነው። እኩል ያወራሉ፤ ማለቴ ሁሉም በሚነጋገሩበት ጉዳይ ተሳታፊ ናቸው። ፊቱን ቅጭም አድርጉ፣ አንገቱን ደፍቶ የሚቆዝም አላየሁም።\nይሄ ትልቅ ደስታን ፈጥሮብኛል። የሰው ልጅ ተደስቶ ከማየት የበለጠ ምን ደስታ አለ። ክብር ይግባው ላከበራቸው፤ ምስጋናዬ ከውስጥ\nነው።የሆነ ሆኖ ግን እኔም የ‹‹ምስኪን›› ቤተሰብ ልጆች እንድል የገፋፋኝ የተጫሙት ጫማ ብቻ ነው። የተቆራረጠች ‹‹ኤርጌንዶ››\nነው የለበሱት። እኔ እንጂ እነሱ ይሄንን እንደማያስተውሉት እገምታለሁ ። ምክንያቱም ብዙ ይጉድልባቸው የነበረው ነገረ ዛሬ ከሞላ\nጎዳል ተስተካክሎላቸዋል። ዓለም መቼም ‹‹ሞልታ አታውቅም አይደል›› የሚባለው። ሁላችንም የሚጎልብን ብዙ ነገር አለ። ፍላጎታችን\nእንደ አኗኗራች በመሆኑ። ከሁሉም በላይ ግን ሰው የማይመለከተው “እንዴት ውለህ አደርክ” የማይባለው ሆድ ሰዓቱን ጠብቆ መሙላት\nችሏል። አሁንም እላለሁ ክብር የሚገባቸው ይክበሩ፣ ይመስገኑ።እስክሪብቶ፣ ደብተር፣\nእርሳስ ሳይሉ ሳይጨነቁና ወደ ስርቆትም ሳያመሩ የራሳቸውን የትምህርት መሣሪያ አሟልተው ወደ ትምህርት ገበታ ገብተዋል። ብዙዎቹ\nበችግር ትምህርታቸውን ሲያቋርጡ ሌሎቹ ደግሞ ከትምህርት ቤት መልስ ኑሮን ከቤተሰባቸው ጋራ ለመግፋት ሳንቲም በምታስገኝ ሥራ ላይ\nይሰማሩ ነበር። በጫማ ማሳመር፣ በመላላከ፣ ልጅ በመጠበቅ፣ በቤት ሠራተኛነት… እናም የማጥኛ ጊዜ የላቸውም። ትኩረታቸው ዛሬ ምን\nበልቼ እሄድ ይሆን የሚል እንጂ ዛሬ ይሄንን ትምህርት አጥንቼ፣ ፈተናውን ደፍኜ የሚል አይደለም። ምክንያቱም ቀዳሚው ሆድ ነዋ\n! ሆድ አማርጦ ባይሞላም የተገኘውን መቅመስ ግን የግድ ነው። ብዙ ጊዜ አሁን ሳይሆን\nቀደም ባሉት ጊዜያት ልጆች በየትምህርት ቤቱ ሰልፍ ላይ እየወደቁ ነው፤ ይዝለፈላፋሉ፤ በዴስክ ላይ ይተኛሉ፤ ትምህርት ያቋርጣሉ፣….\nየሚባሉ በርካታ ችግሮች በየትምህርት ቤቱ ይሰማ ነበር። ይሄንን የሰሙ በጋራ ገንዘብ በማዋጣት ለተማሪዎቻቸው አይዝዋችሁ ባናጠገባችሁ\nበቀን አንዴም ቢሆን እንመግባችኋለን ብለው ሲሰሩ ከርመዋል። እነዚህም ሊመሰገኑ ይገባል። መፍትሄ አመላካች ፈር ቀዳጀ ናቸው። እዚህ\nላይ መመስገን አለባቸው ስል የመምህራኖችን ውለታ በመርሳት አይደለም። በተማሪዎቻቸው ላይ ችግር ሲገጥም ገንዘብ አዋጥተው በመመገብ፣\nየራሳቸውን ምሳ አሳልፈው በመስጠት፣ ችግሩን አደባባይ በማውጣት ኧረ አልፈው ተርፈው ቤተ እምነቶች ደጃፍ ብቅ እያሉ ዕርዳታ እንዲያደርጉ\nጭምር ሲማፀኑ የነበሩትን ተመልክቻለሁ። ህዝብ በተሰባሰበበት\nቦታ ላይ ተገኝተው ‹‹ዛሬ የተቸገሩ ተማሪዎች የሁላችን ልጆች ናቸው እርዱ›› ብለው ሲያሳስቡ በጆሬዬ መስማቴን ልመሰክር እችላለሁ።\nእናም የመምህራንን ውለታ ለእነሱ የሚገባውንም ምስጋና ከማንም ይቀድም ይሆናል እንጂ አይታጠፍም። የመምህራኑ ጥረት መልካም አሳቢነት፣\nአስተዋይ አመራር ታክሎበት ዛሬ ለደረሱበት ደረጃ ላይ አድርሷቸዋል። ነገርን ነገር ያነሳዋል\nብዬ እንጂ ለዛሬው ያስተዋልኩት በተማሪዎች ላይ ያየሁትን የተለየ ደስታ ነው። ማስደሰት ያስደስታል፤ ምን ማስደሰት ብቻ የተደሰተ\nሰውን መመልከትም በራሱ ያስደስታል። አንድ የናጠጠ ሀብታም ቤቱ ሙሉ ቢሆን፣ መርጦ አማርጦ መኪና ቢነዳ፣ ፎቅ ቢደረድር፣ በሀገር\nላይ ከሀገር ውጭ ቢንሸራሸር ከአጠገቡ ሁሌ የሚሰማው የሰዎችን ችግር፣ ረሃብ፣ ሰቆቃ፣ ለቅሶ ከሆነ፤ የሚመለከተው ጎስቋሎችን፣ ለልመና\nየሚዘረጉ እጆችን ከሆነ… ደስታው ሁሉ ይጠፋል። ነገር ግን በአጠገቡ ያሉ ሰዎች ሀብታም ባይሆኑም ደስተኛ ከሆኑ፤ ራሳቸውን ለማሸነፍ\nየሚታትሩ ብሎም ሃሴት ከቤታቸውም የማይርቅ ከሆነ እርሱም ይደሰታል። በሰራው ሥራ፣ ባደረገው ጥረት፣ በፈጠረው የሥራ ዕድል የተገኘ\nደስታ ከሆነ ደግሞ ከተደረገላቸውም በላይ የሚደሰተውና የሚረካው እሱ ነው። በእነዚሁ ተማሪዎች\nላይ ሰሞኑን ያየሁትን ፈንጠዝያ ታዲያ ያደረገላቸው አካል ቢያየው በምላሹ ምን ያህል እንደሚደሰት አሰብኩት። ጉዳዩ እንዲህ ነው፤\nተማሪዎች ከትምህርት ቤት ተለቀው ወደ ቤታቸው እየተመለሱ ናቸው። በጀርባቸው አንዳንዶች ደግሞ በደረታቸው የተሸከሙት አዲስ ቦርሳ\nነው። በቦርሳው ውስጥ የተለያየ የመማሪያ ቁሳቁስ አለ። እሱን አንድ በአንድ እያወጡ ይተያያሉ። አንዳንዶቹ ልጆች ይህን አይነት\nቦርሳና የትምህርት መሣሪያ ቁሳቁስ እንኳን በእጃቸው ነክተው፣ በጀርባቸው ተሸክመው በአይናቸው ስለማየታቸውም እጠራጠራለሁ። በጣም\nውድ እና ዘመናዊ ነው። ዛሬ ግን ይሄም ለእናንተ\nይገባል ተብለው እጃቸው መድረሱ ያልጠበቁት እንግዳ ነገር ጭምር ነውና ቀደም ብዬ እንደገለፅኩት በፊታቸው ሙሉ ጥርሳቸው ጭምር ነው\nየሳቀው። ወተት እንደጠገበች ጥጃ እምቦር እምቡር እያሉ የሚሯሯጡትም ቤታቸው ገብተው ለቤተሰቦቻቸው እስከሚያሳዩ በመቸኮል ጭምር\nእንደሆነም አስቤያለሁ። እኔ የዚህ ስጦታ አካል ባልሆንም በተደረገላቸው ተማሪዎች ደስታ በመደሰት አንዱ አካል ሆኜ አምሽቻለሁ።\nመስጠት ‹‹መሰጠት›› ቢሆንም\nለመስጠት ልባችንን በቅንነት ከከፈትን ለብዙዎች እንደርሳለን። ዛሬ በህይወት የሌሉት አለቃዬ በሚሉት ንግግር ሐሳቤን ልቋጭ ‹‹ለሰጫችን\nይስጥልን፤ ለንፉግ ልብ ይስጥልን››። ሰላም!አዲስ ዘመን ህዳር 28/2012አልማዝ አያሌው", "passage_id": "89523c13b0688087ca2c4fd5bee16750" }, { "passage": "ምንም እንኳን እያደረሰ ካለው የህይወት መቅጠፍ ተግባር ጋር ባይወዳደርም ኮቪድ ወረርሽኝ ያመጣቸው በርካታ ሰብአዊ ፋይዳ ያላቸው ቁም ነገሮች በአገራት፤ እንደ አጠቃላይም በዓለም ላይ በርካታ ናቸው። ከእነዚህም መካከል አንዱ የአንድ ማህበረሰብ እንደ ማህበረሰብ የሚገለፅባቸው እሴቶቹ ተጠቃሽ ሲሆኑ፤ መተሳሰብ ደግሞ ከሁሉም አንጋፋ፣ ቀዳሚና የአብሮነትና ወሳኝ የህዝቦች የእርስ በርስ ግንኙነት ማሰሪያ ገመድ ነው። በመሆኑም በአገራችን የኮቪድ ወረርሽኝ መከሰትን ተከትሎ በስፋት ከተስተዋሉት ተግባራት አንዱ ይሄው የመተሳሰብ፣ መረዳዳትና መደጋገፍ የቆየ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበረሰባዊና ባህላዊና የማንነት እሴት ነው። ስለሆነም በየመስኩ፣ ዘርፉና አቅጣጫው ተግባሩ በተግባር ሲረጋገጥ፤ አንዱ የአንዱን ሸክም ሌላው ሲራዳ፤ ሲያቃልልና ወረርሽኙን በጋራ በመከላከል፣ በመቆጣጠርና ከወረርሽኙ ባሻገር ያለውን ተስፋ ሲያለመልም ይታያል። ኮቪድ 19 ይዞት የመጣው ሞትን ብቻ ሳይሆን በአሁኑ ዘመን መስፈርት ከሱ ያልተናነሰውን የኢኮኖሚ ድቀት ጭምር በመሆኑ ችግሩ የአንድና ሁለት ሰዎች ሳይሆን የሁላችንም ነው። በመሆኑም የሁላችንንም የጋራ መፍትሄ ይሻል። ይህም በጥቅል ስያሜው መረዳዳት፤ መደጋገፍ መሆኑ ነው። ይህ መደጋገፍ፣ መረዳዳትና መተሳሰብ ከታየባቸውና አሁንም ድረስ በመዝለቅ እየተስተዋለ ካለባቸው ዘርፎች መካከል አንዱ የኢኮኖሚ አውታር በመሆን የሚታወቀው የንግዱ ዘርፍ በመሆኑ፤ በዘርፉ በርካታ መመሰቃቀሎች ተከስተዋል፤ በርካቶችም ከጨዋታው ውጪ ሆነዋል። የዜጎች ከሥራ መፈናቀል፣ የንግዱ እንቅስቃሴ “ጭራሽ የለም” እስከ መባል ድረስ መቀዛቀዝ… ቀዳሚ ተጠቃሽና በግልፅ የሚታይ ኮቪድ ወለድ ወረርሽኝ ነው። በመሆኑም ከግለሰብ ጀምሮ እስከ መንግሥት ጣሪያ ድረስ የመነጋገሪያ ርእሰ-ጉዳይና ለመፍትሄ ፍለጋውም እያመራመረ የሚገኘው። በቤት፣ ሱቅና መደብሮች ኪራይ ቅነሳ (እስከ ወራት ክፍያ መሰረዝ ድረስ የዘለቀ)፣ የግብርና መሰል ክፍያዎችን መቀነስና የእፎይታ ጊዜን መስጠት፣ ለተጎዱ ተቋማት ድጎማ፣ ድጋፍ፣ ብድር… መፍቀድ፤ ክፍያን ማራዘም ድረስ እርምጃዎች እየተወሰዱ ሲሆን ኢኮኖሚውንና አንቀሳቃሾቹን ከድቀት የመታደግ ሰናይ ተግባር እየተሰራ የሚገኘው። ይሁን እንጂ አልፎ አልፎ ችግሮች የሉም፤ ክፍተቶች በሙሉ ተደፍነዋል ማለት አይደለም። የንግዱ ዘርፍ ከሚንቀሳቀስባቸው ቢዝነሶችና ማከናወኛ ስፍራዎቹ በአብዛኛው የግለሰቦች ህንፃዎች ሲሆኑ እነዚህም በተለይ ኮሮናን በመሳሰሉ ጊዜያት ክፍያቸው ወገብ ያንቀጠቅጣል። በመሆኑም ይመስላል ብዙዎቹ ባለሀብቶች በተለያየ መልኩ ለብዙዎች ምህረት ያደረጉት። ይህንኑ ጉዳይ አስመልክተን በከተማው ተዘዋውረን የተለያዩ አስተያየቶችን ለማሰባሰብ የሞከርን ሲሆን ለየት ብሎ ያገኘነው ወደ አራት ኪሎ አካባቢ ነው። በአራት ኪሎ የሁለት ወር ኪራይን የማሩ የመኖራቸውን ያህል ምንም ያላሉም አሉ። ምንም እንኳን ጉዳዩ የግል ጉዳይ ቢሆንም የጋራ የሚያደርገው ቀደም ሲል እንደጠቀስነው ጉዳዩ ዓለም አቀፍና በማናችንም ላይ ያነጣጠረ መሆኑ ነው። በድንቅ ሥራ ሀ/የተ/የግ/ማህበር ስር በሚገኘው ድንቅ ስራ ህንፃ ውስጥ የተከራዩ ነጋዴዎችን አግኝተን እንዳነጋገርነው ከሆነ እስካሁን ከሚመለከታቸው አከራዮች ምንም አይነት ሀሳብ የመጣም ሆነ ምን ማድረግ እንዳለባቸው የጠቆመ አካል የለም። በመሆኑም ከበሽታው ስጋት፣ ከገበያው ድቀት በተጨማሪ የኪራይ መክፈሉ ጉዳይ እያስጨነቃቸው መሆኑን ይናገራሉ። በህንፃው ውስጥ የአንደኛው ሱቅ ሥራ አስኪያጅና ስማቸው እንዳይጠቀስ የሚፈለጉት በወር 30 ሺህ ብር ኪራይ የሚጠበቅባቸው ተከራይ እንደሚሉት ከሆነ እስካሁን አንድም ነገር ያናገራቸውም ሆነ ትከፍላላችሁ/አትከፍሉም ያላቸው አካል የለም። ከቃል አልፈው በፅሁፍ ቢያመለክቱም ማንም ትንፍሽ የሚል አልተገኘም። “ከሁሉም እኛን የሚያሳስበን እንዴት አንድ ነገር አይሉንም የሚለው ነው። ምናለበት ቢያወያዩን። ምንም ሳይከፍል ሶስት ወር የሞላው አለ። ሁለት ወር የሆነው አለ። በኋላ አምጣ ቢሉት ከየት ሊያመጣ ነው?” የሚሉት አስተያየት ሰጪው ባለሀብቶቹ ቢያወያዩአቸውና አንድ ነገር ላይ ቢደርሱ ከብዙ ሀሳብ እንደሚገላገሉ ይናገራሉ። “ብንነጋገር እኮ ጥሩ ነው። ወይ በእረጅም ጊዜ ክፍያም ከተስማማን፤ ወይ እንደ ጎረቤት ህንፃ ባለቤቶች ምህረት የሚያደርጉልንም ከሆነ… ብንነጋገር ጥሩ ነው። አሁን ብዙ ሰው እኮ ሀሳብ ገብቶታል። ተጨንቋል።” ሲሉም የህንፃውን አስተዳዳሪዎችና ባለሀብቶች ያሳስባሉ። ሌላው በማርኮ ሚላኖ ሱቅ ውስጥ አግኝተን ያነጋገርናቸው የሱፍ አልባሳትና መጫሚያ ነጋዴ አቶ ኡሽራ ሰይድ ሲሆኑ እንደሚሉት ከሆነ የኮሮና መከሰት እጅግ እጅግ አንገድግዷቸዋል፤ እንደዚህ ዘመንም ተፈትነው አያውቁም። ሰርግ፣ ምርቃት፣ ስብሰባና የመሳሰሉት ባለመኖራቸው ሥራቸው በር መክፈትና በር መዝጋት ብቻ ሆኗል። በአሁኑ ሰዓትም እንኳን ለኪራይ የሚሆን ለግል ወጪ እንኳን እየተንገዳገዱ ነው። እንዲቀንሱላቸውም ተፈራርመው ቢያስገቡም እስካሁን ምንም ምላሽ አላገኙም። ይህ ደግሞ ከፍተኛ ስጋትን ፈጥሮባቸዋል። “ባለሀብቶቹ አንድ ነገር ቢሉን ጥሩ ነው። እነሱም እኛም ሳንጎዳ ቤተሰባዊ ትብብራቸውን እንጠይቃለን” በማለትም ይጠይቃሉ። ምናልባትም ጥሩ አስበውልንም ሊሆን ይችላል አናውቅም ሲልም መልካም ሀሳቡን አካፍሎናል። የአዲስ አበባ መስተዳድርም ያስበናል ብለው እንደሚያስብም ነግሮናል። ሌሎች ከቡና ማፍላት ጀምሮ ያሉትንም አነጋግረን ያገኘነው ተመሳሳይ አስተያየቶችን ሲሆን ሁሉም ከሥራው ውጪ ከመሆናቸው በፊት ባለሀብቶቹ አንድ ነገር ቢሏቸው እንደሚወዱ ነግረውናል። ጉዳዩን በተመለከተ ከሚመለከታቸው ጋር ለመነጋገር ያደረግነው ጥረት አድካሚ ቢሆንም የቦርድ ሰብሳቢ የሆኑትን አቶ ሙሉጌታ ነጋሽን አግኝተን ያነጋገርናቸው ሲሆን በሥራ ምክንያት ሊሰባሰቡ ባለመቻላቸው ምክንያት ሊወስኑ እንዳልቻሉና ተከራዮች ምንም ሊያሳስባቸው እንደማይገባ ነግረውናል።አዲስ ዘመን ግንቦት 28/2012 ግርማ መንግሥቴ ", "passage_id": "724d7f9d60f09d102f2891f01f81d341" } ]
faf8930d1795c69c309e5553a518ca52
949e7538c3640ef47ac37addfddefb84
የ2023 አፍሪካ ዋንጫ ዝግጅት ቀጥሏል
 ቦጋለ አበበ ምዕራብ አፍሪካዊቷ አገር ኮትዲቯር የ2023 አፍሪካ ዋንጫን ለማስተናገድ የምታደርገው ዝግጅት በሚፈለገው ደረጃ ቀጥሏል።የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ባለፈው ዓመት ከተከሰተ ወዲህ በርካታ የዓለማችን አገራት ስፖርታዊ ውድድሮችን ከማቆም ባለፈ ዓለም አቀፍና አህጉር አቀፍ ውድድሮችን ለማስተናገድ የሚያደርጉት ዝግጅት ተስተጓጉሏል።የ2023 አፍሪካ ዋንጫን ለማስተናገድ ዕድሉ የተሰጣት ኮትዲቯር ግን ወረርሽኙ ሳያግዳት ዝግጅቷን በተገቢው መንገድ እንደቀጠለች ኢንሳይድ ዘጌምስ አስነብቧል። የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የግምገማ ቡድን ከሳምንት በፊት ወደ ኮትዲቯር አቅንቶ አገሪቱ እያደረገች የሚገኘውን ዝግጅት የተመለከተ ሲሆን ምዕራብ አፍሪካዊቷ አገር ለአፍሪካ ዋንጫው ተገቢውን ዝግጅት በማድረግ ሂደት ላይ እንደምትገኝ አሳውቋል።በዝግጅት ግምገማ ቡድኑ ውስጥ የካፍ ምክትል ዋና ፀሐፊ አንቶኒ ባፎይ፣ የውድድር ዳይሬክተሩ ሳምሶን አዳሙ፣ የብሔራዊ ቡድን ውድድሮች ማኔጀሩ ኢስማሊ ዋሊ እንዲሁም የአገልግሎትና የጉዞ ዋና ሃላፊው ራንዳ ሚትዋሊ ተካተው ወደ ስፍራው አቅንተዋል። የግምገማ ቡድኑ ከኮትዲቯር ከተመለሰ በኋላ ለኢንሳይድ ዘጌምስ አስተያየታቸውን የሰጡት ምክትል ዋና ፀሐፊው ባፎይ ምንም እንኳን የኮቪድ-19 ወረርሽኝ የዓለም ሕዝብ የጤና ቀውስ በመሆን ቢቀጥልም ያሳደረውን ጫና ተቋቁማ ኮትዲቯር በጥሩ ሁኔታ ዝግጅቷን እንደቀጠለች ማረጋገጫ ሰጥተዋል። ‹‹ጉብኝቱ በደንብ የታሰበበት ነው፣ በጉዟችንና የውድድሩ አዘጋጆች እየሠሩ በሚገኙት ሥራ ረክተናል›› ያሉት ባፎይ አብዛኛው ለውድድሩ የሚገነቡት ስቴድየሞች በ2021 አጋማሽ እንደሚጠናቀቁ ጠቁመዋል።ይህም አዘጋጆቹ እስከ ውድድሩ ድረስ በቂ ጊዜ እንዳላቸው የሚያሳይ ሲሆን ለሙከራ የተለያዩ ጨዋታዎችን የማካሄድ ዕድልም እንደሚኖራቸው ባፎይ አብራርተዋል። የውድድሩ አዘጋጆች በዕቅዳቸው መሰረት እየተመሩ ትክክለኛ ሰዎችን በትክክለኛው ቦታ በማሰራት ተጨባጭ ነገር እንዳሳዩ የጠቆሙት ባፎይ‹‹ ሁሌም የምናገረው ነገር አንድ ነው፣ ትክክለኛውን ሰው በትክክለኛው ቦታ ማስቀመጥ›› በማለት አዘጋጆቹን አድንቀዋል።ኮትዲቯር እ.ኤ.አ 2014 ላይ የ2021 አፍሪካ ዋንጫን እንድታዘጋጅ ዕድሉን ያገኘች አገር መሆኗ ይታወሳል።ይሁን እንጂ የ2019 አፍሪካ ዋንጫን ለማዘጋጀት ዕድሉ የተሰጣት ሌላኛዋ ምዕራብ አፍሪካዊት አገር ካሜሩን 2018 ላይ ውድድሩን ለማዘጋጀት የምትገነባቸው ስቴድየሞች በመጓተታቸውና በወቅቱ በአገሪቱ የነበረው የፖለቲካ አለመረጋጋት ከደህንነነት አኳያ ስጋት ስለፈጠረ የአዘጋጅነት ዕድሉ ለግብጽ ተሰጥቷል።ካሜሩንም በምትኩ የ2021 አፍሪካ ዋንጫን እንድታዘጋጅና ኮትዲቯር የ2023 አፍሪካ ዋንጫን እንድታሰናዳ ሽግሽግ ተደርጓል። በዚህም መሰረት ኮትዲቯር የአፍሪካን ትልቁ የስፖርት መድረክ በተሳካ ሁኔታ ለማዘጋጀት በቂ ጊዜና ዕድል ማግኘት ችላለች።ውድድሮቹንም ከ2023 ሰኔ ወር መጨረሻ አንስቶ በመዲናዋ አቢጃን፣ ቦኬ፣ ኮርሆጎ፣ ሳን ፔድሮ እና ያሙሱክሮ ከተሞች እንደ ምታከናውን ይጠበቃል።
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=37905
[ { "passage": "የኢትዮጵያ ከ20 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን በዛምቢያ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ የማጣርያ ጨዋታውን በመጪው እሁድ ከሶማልያ ጋር ያደርጋል፡፡ ለጨዋታው የሚያደርገውን ዝግጅትም ቀጥሏል፡፡ቡድኑ ከ2 ሳምታት በፊት ለ38 ተጫዋቾች ጥሪ በማድረግ ዝግጅት የጀመረ ቢሆንም በሂደት በርካታ ተጫዋቾች ቡድኑን በመቀላቀላቸው የመለየት ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡ በአሁኑ ሰአት 25 ተጫዋቾች በቡድኑ ውስጥ ሲቀሩ በትላንትናው እለት ለጨዋታው የሚያደርገውን ዝጅግት በተሟላ ሁኔታ ጀምሯል፡፡አሰልጣኝ ግርማ ሃብተዮሃንስ በዛሬው የልምምድ ፕሮግራም ተጫዋቾችን ለሁለት በመክፈል ቋሚ ተሰላፊ ሊሆኑ የሚችሉ ተጫዋቾችን በሚለይ መልኩ ረጅም ደቂቃዎች የፈጀ የልምምድ ጨዋታ አጫውተዋል፡፡ከ20 አመት በታች ብሄራዊ ቡድናችን ከፕሪሚየር ሊግ ፣ ከፍተኛ ሊግ ፣ ብሄራዊ ሊግ እና ተስፋ ቡድኖች የተውጣጡ 25 ተጫዋች ሲኖሩት ከሁለት በላይ ተጫዋች ያስመረጡ የከፍተኛ ሊግ ክለቦች በዚህ ሳምት የሚያደርጉት ጨዋታ ለሌላ ጊዜ ይዛወራል ተብሏል፡፡ብሄራዊ ቡድናችን በመጨው እሁድ የመጀመርያውን ጨዋታ አዲስ አበባ ስታድየም ላይ ሲያደርግ ሩዋንዳዊያን ዳኞች ጨዋታውን ይመሩታል፡፡ የመልሱ ጨዋታ ደግሞ ሚያዝያ 15 ወይም 16 ሲደረግ ጨዋታው በሶማልያ አልያም በገለልተኛ ሃገር እንደሚካሄድ ካፍ እስካሁን አላሳወቀም፡፡በ20 አመት በታች ቡድኑ ዙርያ የአሰልጣኝ ግርማ እና የተጫዋችን አስተያየቶች ከጨዋታው በፊት የምናቀርብላችሁ ይሆናል፡፡", "passage_id": "4f766e9ca912d5ead4ad429d7974cf5d" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለወትሮው ለትልልቅ ውድድሮች ቢያንስ አንድ ወር ዝግጀት የማድረግ ልማድ ቢኖረውም በ2014 መጀመርያ በሀገር ውስጥ ሊግ ውስጥ በሚጫወቱ ተጫዋቾች ብቻ በሚዋቀር ስብስብ ለሚደረገው ውድድር (ቻን) እስካሁን ዝግጅት አልጀመረም፡፡ውድድሩ ሊጀመር የ23 ቀናት እድሜ የቀሩት ቢሆንም ኢትዮጵያ እስካሁን ተጫዋቾቿን አላሳወቀችም (በምድባችን የምትገኘው ጋና ከወዲሁ 23 ተጫዋቿን አሳውቃለች)፡፡ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው በመጪው ሳምንት ሰኞ ዝግጅት ለመጀመር ጥያቄ ቢያቀርቡም የሊጉ ውድድር እንዳይቋረጥ በሚል በፌዴሬሽኑ ውድቅ ተደርጎባቸዋል፡፡ኢትዮጵያ በቻን ምድብ ሦስት ከኮንጎ ሪፐብሊክ (ብራዛቪል)፣ ሊቢያ እና ጋና ጋር መደልደሏ ይታወሳል፡፡", "passage_id": "6c5f8b58b6a6c92160461c73c4065dbf" }, { "passage": "በአራት ሀገሮች ተሳታፊነት በኤርትራ አዘጋጅነት ከሚያዚያ ሦስት ጀምሮ ይካሄዳል ተብሎ ቀጠሮ የተያዘለት “የሠላም እና ወዳጅነት ዋንጫ” በተባለበት ጊዜ ላይጀምር እንደሚችል ቢገመትም የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ዝግጅቱን አጠናክሮ እየሰራ ይገኛል።ኢትዮጵያ ፣ ጁቡቲ ፣ ሱማሊያ እና አዘጋጇ ሀገር ኤርትራ ይካፈሉበታል ተብሎ የታሰበው ” የሠላም እና የወዳጅነት ” ጨዋታ ከሚያዚያ ሦስት ጀምሮ ለአንድ ሳምንት በአስመራ ከተማ ውድድሩ እንደሚካሄድ ከዚህ ቀደም መገለፁ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ከ20 አዓመት በታች ብሔራዊ ቡድንም የመጨረሻ 25 ተመራጭ ተጫዋቾችን በመያዝ ዝግጅቱን በተጠናከረ ሁኔታ እያካሄደ ይገኛል። ዛሬ 04:00 ላይ በአዲስ አበባ ስታድየም ከመከላከያ የ20 ዓመት በታች ቡድን ጋር ባደረገው የአቋም መፈተሻ ጨዋታ በመጀመርያው አጋማሸ እዮብ ዓለማየሁ ባስቆጠረው ብቸኛ ጎል 1-0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።ይሁን እንጂ ከተሳታፊ ሀገራት መካከል በተለይ ኤርትራ እና ኢትዮጵያ ተጫዋቾችን በመምረጥ ሆነ ለውድድሩ አስፈላጊውን ዝግጅት በማድረግ ላይ ቢገኙም የተቀሩት ሁለት ሀገራት ሶማሊያ እና ጁቡቲ እስካሁን ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ እያደረጉ አለመሆኑ እና በውድድሩ ላይ እንደሚሳተፉ እስካሁን ማረጋገጫ የሰጡ ባለመሆኑ ውድድሩ አስቀድሞ በወጣለት መርሐግብር መሠረት ላይካሄድ እንደሚችል ተገምቷል።\nበቀጣዩ ሁለት ቀናት የሚለወጥ አዳዲስ ነገሮች ካሉ እየተከታተልን የምናቀርብ ይሆናል።", "passage_id": "9f2352da051fff89f1feb0855e1f61bb" }, { "passage": "አራት የምዕራብ አፍሪካ ሃገራት የያዘው የመጨረሻው ምድብ ከሞት ምድብ ቀጥሎ አጓጊ ምድብ ነው። ሻምፒዮናዋ ካሜሩን፣ ጋና፣ ቤኒን እና ጊኒ ቢሳዋን የሚያገናኘው ይህ ምድብ ጠንካራ እና እልህ አስጨራሽ ፉክክር ይታይበታል ተብሎ እንደሚጠበቅ ሶከር ኢትዮጵያ ዘግቧል። በቀድሞ የኤስሚላን ጀግና ክላረንስ ሲዶርፍ የሚመሩት የባለፈው ውድድር አሸናፊ ካሜሩን ይሄ ውድድር እንደባለፈው ፉክክር አልባ አፍሪካ ዋንጫ አልጋ በአልጋ እንደማይሆንላቸው የታወቀ ነው። በማጣሪያው በምድብ ‘B’ ከሞሮኮ፣ ኮሞሮስና ማላዊ ተደልድለው በደካማው ምድብ ሳይፈተኑ ወደ ውድድር ያለፉት ካሜሩኖች የፓሪ ሰን ጀርመው አጥቂ ቾፓ ሞቲንግን ይዘው ወደ ግብፅ ሲያመሩ ቡድኑ ሻምፒዮና በሆነበት ዓመት በፍፃሜው ጨዋታ የቡድኑ የነብስ አዳኝ የነበረው ቪንሰንት አቡበከር እና ባለፈው የውድድር ዓመት ከሊቨርፑል ጋር ድንቅ ዓመት ያሳለፈውና የሃገሩን ጥሪ አልቀበልም በማለቱ በሃገሩ ልጆች እንደ ከሃዲ የታየው ቀውላላው ተከላካይ ዮኤል ማቲፕ በክላረንስ ሲዶርፍ ጥሪ አልደረሳቸውም። የቅድመ ዝግጅታቸው በስፔን እና ኳታር ያደረጉት ካሜሩኖች በአቋም መለኪያ ጨዋታ ዛምቢያ እና ኤዲ ኮርኮን የተባለ የስፔን ክለብ ሲያሸንፉ ከማሊ ጋር አቻ ተለያይተዋል። የማይበገሩት አናብስት ከአያክስ ጋር ድንቅ ዓመት ያሳለፈው ግብጠባቂው አንድሬ ኦናና እና በሃገሩ ማልያ ጥሩ የጎል ክብረወሰን ያለው ማክሰም ቾፓሞቲንግ ላይ ተስፋ ጥለዋል። ሃገራችን\nኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ሴራሊዮን ከነበሩበት ምድብ ‘F’ ምድቡን በበላይነት በማጠናቀቅ በቀላሉ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፉት ጥቋቁር ከዋክብቶች በውድድሩ በተከታታይ አምስት ጊዜ ለፍፃሜ በመድረስ ባለ ታሪክ ናቸው። አንድሬ አየው አምበልነት ወደ ግብፅ የሚያቀኑት ጥቋቁር ከዋክብቶች በዱባይ በቆዩባቸው የዝግጅት ቀናት ሦስት የአቋም መለኪያ ጨዋታዎች አድርገው አንድ ድል ፣ አንድ አቻ እና አንድ ሽንፈት ቀምሰዋል። ሁሌም በውድድሩ\nተጠባቂ ከሆኑት ሀገራት ተርታ ብትሰለፍም 37 ዓመት ያስቆጠረችው ሀገር ታሪኳን ለማደስ አስር ለውድድሩ እንግዳ የሆኑ ተጫዋቾችን ከማካተት ባሻገር እንደ አትሌቲኮ ማድሪዱ ቶማስ ፓርተይ፣ ባለልምዶቹ ክዋዱ አሳሙሃ፣ አንድሬ አዬው እና አሳሞሃ ጅያን ባሉ ተጫዋቾች ላይ ተስፋ ጥለዋል። ሳይጠበቅ\nአዳዲስ ፊቶች ይዞ ወደ ውድድሩ ለማቅናት የወሰነው ክዌሲ አፒያ እነ ባባ ኣህማን ፣ ጆናታን ሜንሳህ ፣ ጆሴፍ አይዶ እና ዓብዱልመጅድ ዋሪስ ወደ መጨረሻው ስብስቤ ሳያካትት ወደ ግብፅ ያመራል። አልጀርያ\n፣ ቶጎ እና ኮሞሮስ ከነበሩበት ምድብ ‘ D’ ከምድቡ መሪ አልጀርያ በአንድ ነጥብ ዝቅ ብላ በሁለተኛነት በማጠናቀቅ ከዘጠኝ ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው የተመለሰችው ቤኒን የማጣርያ ጉዞዋን መሰረት በማድረግ ቀላል ተጋጣሚ እንደማትሆን መገመት አያዳግትም። በማጣርያው\nጨዋታዎች ላይ አምስት ግቦች ብቻ ያስቆጠሩት ቤኒኖች እንደ አብዛኞቹ የአፍሪካ ሃገራት ግብ የማስቆጠር እና ንፁህ የግብ ዕድል በመፍጠር ረገድ ቀላል የማይባል ክፍተት አለባቸው። ለቅድመ\nዝግጅት ሞሮኮ የቆዩት ቤኒኖች ሦስት ጨዋታዎች አድርገው ሦስቱም በድል ተወጥተዋል። በርከት\nያሉ ተጫዋቾች ከፈረንሳይ የመረጡት ቤኒኖች በአንጋፋው ስቴፈን ሴሴኞ እና በሃደርስፊልዱ ስቲቭ ሞውኔ ላይ ተስፋ ጥለዋል። ዛምቢያ\n፣ ናሚቢያ እና ሞዛምቢክ ከነበሩበት ምድብ ‘ k ‘ ሳትጠበቅ ምድቡን በበላይነት ያጠናቀቀችው ጊኒ ቢሳው ትላቋን ዛምቢያ ጨምሮ ሌሎቹን ሁለት ሃገራት ረምርማ ወደ ውድድሩ ታልፋለች ብሎ የገመታት አልነበረም። ከሞዛምቢክ ጋር በነበረው ድራማዊ ክስተት በተሞላበት ጨዋታ በአስደናቂ ብቃት አቻ ከተለያየች በኋላ የብዙዎች ትኩረት ስባ የነበረችው ጊኒ ቢሳው ሽንፈት ሳትቀምስ ነበር ወደ ውድድሩ ያለፈችው። በአሰልጣኝ\nካንዴ እየተመራች ለሁለተኛ ጊዜ በውድድሩ የምትሳተፈው ጊኒ ቢሳው በማጣርያው ሦስት ግብ ያስቆጠረላት ፍሬድሪክ ሜንዲ ኮከብ ተጫዋቿ ነው። የምድቡ\nተጠባቂ ጨዋታ – ካሜሩን ከ ጋና ሁለቱ በውድድሩ\nትልቅ ታሪክ ያላቸው የምንጊዜም ተቃናቃኞች የሚያገናኘው ይህ ጨዋታ በታሪክም በወቅታዊ አቋም ረገድም ተጠባቂ ጨዋታ ነው። ተመሳሳይ\nአጨዋወት የሚከተሉት ሁለቱ ቡድኖች የሚያገናኘው ይህ መርሐ ግብር የምድቡ ሁለተኛ ጨዋታ ነው።ከምድብ\nስድስት የሚጠበቀው ተጫዋች ጋናዊው የአትሌቲኮ ማድሪዱ ወሳኝ አማካይ ቶማስ ፓርተይ ነው። በምድቡ በርካታ የማጥቃት ባህሪ ያላቸው እና ከዚ በፊት በውድድሩ ልምድ ያላቸው እንደነ አሳሞሃ ጅያን የመሳሰሉ ተጫዋቾች ቢኖሩም እንደ የሃያ ስድስት ዓመቱ ውጤታማ አማካይ የሚያክል ግን አይጠበቁም። በአትሌቲኮ በበርካታ ሚናዎች ላይ የሚጫወተው አይደክሜው ተጫዋች በጋናም ተመሳሳዩ ሚና ከተሰጠው እንደሚያንፀባርቅ ይጠበቃል። ካሜሩን\nከጊኒ ቢሳው 2:00 ካሜሩን\nከጋና 2:00 ጋና ከቤኒን\n5:00 ቤኒን ከኢኳቶርያል\nጊኒ 5:00 ቤኒን 1:00 ካሜሩን\nጊኒ ቢሳው\n1:00 ጋናአዲስ ዘመን ሰኔ 16/2011 ", "passage_id": "260548f5c05c65f4a743d7cb9a8f5916" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ከ17 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን ከግብፅ ጋር ለሚያደርገው የአፍሪካ ከ17 አመት በታች ዋንጫ ማጣርያ የሚያደርገውን ዝግጅት አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ከሐምሌ 1 ጀምሮ በሀዋሳ ሴንትራል ሆቴል በመክተም ዝግጅት እያደረገ የሚገኘው ብሄራዊ ቡድኑ በመለማመጃ ሜዳ እጦት እንደተቸገረ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በከተማው በርካታ ሜዳዎች ቢገኙም የሚመለከተው አካል ትኩረት በመንፈጉ ለዝግጅት መሰናክል ፈጥሮባቸዋል ተብሏል፡፡የፌዴሬሽኑ አመራሮች በጉዳዩ ላይ ከቡድኑ ጋር ከተወያዩ በኋላ ችግሩን ለመፍታት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እንደሚነጋገሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡26 ተጫዋቾች በመያዝ ወደ ሀዋሳ ያቀኑት አሰልጣኝ አጥናፉ ስብስባቸውን ወደ 20 ቀንሰዋል፡፡በዝግጅት ላይ የሚገኘው ስብስብ ይህን ይመስላል:-ኦኛ ኦሜኛ ፣ እሸቱ ተሾመ ፣ ፋሲል ገብረሚካኤል ፣ ረመዳን የሱፍ መሃመድ ፣ እሱባለው ጌታቸው ፣ ማትያስ ወልደአረጋዊ ፣ ሚኪያስ መኮንን ፣ አቡበከር ናስር ፣ ዳዊት ሳህሌ ፣ ጫላ ተሸታ ፣ እዮብ አለማየሁ ፣ ዳግማዊ አርአያ አምበፍርድ ፣ ሳሙኤል ተስፋዬ ፣ አማኑኤል አዲሱ ፣ ሉክ ፖውልን ፣ ሀቢብ ከተማ ፣ አላዛር ሽመልስ ፣ ጌታሰጠኝ ሸዋ ፣ አክሊሉ ለአሙ ፣ ቃልኪዳን ዘላለም", "passage_id": "0cf4c160f24ebb862b9203beab986e7f" } ]
07b0726cc39d3266376163a049b694ff
7e0a41e5a412b3fe6695933745a8541e
የባለሀብቶች ተሳትፎ ያልታከለበት የማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ
ብርሃን ፈይሳወቅቱ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ በዓለም አቀፍ ደረጃ እጅግ የሰፋበት መሆኑን ጥናቶች ያመላክታሉ። የማዘውተሪያዎች ዘመናዊነትና ጥራት የሰለጠኑ ከተሞች አንዱ መለያ እየሆነ ከመምጣቱም ባሻገር ኦሊምፒክ፣ ዓለም ዋንጫ እና የተለያዩ ስፖርት ቻምፒዮናዎችን ለማሰናዳት ዋነኛው መስፈርትም ነው። ሀገሮች ዜጎቻቸው በአእምሮና በአካል የተዋጣላቸውና ብቁ እንዲሆኑም በማዘውተሪያ ስፍራዎች አስፈላጊነትም እምነት ጥለዋል። በመሆኑም የከተሞቻቸውን ዲዛይን ሲያዘጋጁም ሆነ ግንባታውን ሲያከናውኑ ነዋሪዎቻቸው በቂ የጊዜ ማሳለፊያና ስፖርታዊ እንቅስቃሴ የሚከውኑባቸው ስፍራዎች ስለመኖራቸው ያረጋግጣሉ። የአፍሪካ መዲናዋ አዲስ አበባም በዓለም ላይ ካሉና ታላላቅ ጉባኤዎችን ለማስተናገድ ከሚመረጡ እንዲሁም የአህጉር አቀፍ ተቋማት መቀመጫ እንድትሆን ተመራጭ ከሆኑት መካከል ትገኛለች። ይህም ስፖርታዊ ውድድሮችን ለማስተናገድ ምቹ ሁኔታን ቢፈጥርላትም እስካሁን ግን ጉባኤዎችን ብቻ በማካሄድ ተወስናለች። ምክንያቱ ደግሞ ደረጃውን የጠበቀ የማዘውተሪያ ስፍራ የሌላት በመሆኑ ነው። አዲስ አበባ ከተማም ደረጃቸውን የጠበቁ የማዘውተሪያ ስፍራዎች ብቻም ሳይሆኑ በየአካባቢው ለነዋሪዎቿ የሚበቃ የማዘውተሪያ ስፍራ ማግኘትም ፈተና ሆኖባታል። በመሆኑም የየከተማ አስተዳደሩ ስፖርት ኮሚሽን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ትኩረቱን በማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ ላይ አድርጓል። ከሰሞኑ ጉባኤውን ያከናወነው የከተማዋ ስፖርት ምክር ቤትም አትኩሮቱን በተለይ በስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ላይ አድርጎ ነበር። ምክር ቤቱ በጉባኤው ላይ ባቀረበው የ2012 በጀት ዓመት የአፈጻጸም ሪፖርት የአዳዲስና ነባር የማዘውተሪያ ስፍራዎች ያሉበትን ደረጃ በዝርዝር አመልክቷል። በዚህም በበጀት ዓመቱ ብቻ 95 የሚሆኑ 3በ1 እንዲሁም የጥርጊያ ሜዳዎች እንዲገነቡና እንዲታደሱ ተደርጓል። እነዚህም በክፍለ ከተሞች እንዲሁም በ14 የጋራ መኖሪያ ስፍራዎች ላይ የተገነቡና የታደሱ ናቸው። ከፍተኛ ወጪ ተደርጎባቸው የሚገነቡ ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን በተመለከተም በዚህ ዓመት ተጠናቀው ወደ አገልግሎት የሚገቡና አዳዲስ የሚጀመሩ መሆኑም ተጠቁሟል። በዚህም የራስ ኃይሉ የመዋኛ ገንዳ እና የአበበ ቢቂላ ስታዲየም የግንባታ ምዕራፍ 99 ከመቶ የተጠናቀቀ ሲሆን፤ በተያዘው በጀት ዓመት ወደ ሥራ ይገባሉ በሚል ይጠበቃል። በሁለቱም የማዘውተሪያ ስፍራዎች የውሃ እጥረት በመኖሩ ምክንያት የከርሰ ምድር ውሃ ለማውጣት እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል። የአቃቂ ስታዲየም ግንባታም 70 ከመቶ ደርሷል፤ የአራት ኪሎ እና የጃንሜዳ ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ በቴክኒክ ችግር ተቋርጦ ቆይቷል። በዚህ ዓመት ዕቅድም በዋናነት የማዘውተሪያ ስፍራ ቁጥርን ማሳደግና ሕጋዊነታቸውን ማረጋገጥ ላይ ትኩረት መሰጠቱ በመድረኩ ላይ ተጠቁሟል። በዚህም መሠረት የአቃቂና የአበበ ቢቂላ ስታዲየሞች እንዲሁም የራስ ኃይሉ የመዋኛ ገንዳዎች ግንባታን በዚህ ዓመት ሙሉ ለሙሉ በማጠናቀቅ አገልግሎት ለማስጀመር ታቅዷል። ግንባታው 67 ከመቶ ደርሶ የተቋረጠው የጃንሜዳ ጂምናዚየም እና ወደ ግንባታ ያልገባው የአራት ኪሎ ትምህርትና ስልጠና ማዕከል ሕንፃም በዓመቱ ወደ ግንባታ የሚገቡ ይሆናል። በተለያዩ ክፍለ ከተማዎች አንድ የአትሌቲክስ መንደር እና ሦስት ዞናል ስታዲየሞችን አስገንብቶ ለኅብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግም የበጀት ዓመቱ ዕቅድ መሆኑም ተጠቁሟል። የቀረበውን ሪፖርትና ዕቅድ ተከትሎም የምክር ቤቱ አባላት የተለያዩ ሃሳቦችን አንጸባርቀዋል። አጸንኦት የተሰጠው ሃሳብ ግን ከስፖርት ኢንቨስትመንት አንጻር በከተማዋ ባለሀብቱን የማሳተፍ ሂደት የሌለ መሆኑ ነው። የግል ባለሀብቱ በተለይ እጥረት ባለበት የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ ላይ የማሳተፍ አስፈላጊነት ተጠቁሟል። በዚህም ባለሀብቱን ከመጥቀም አልፎ ነዋሪውንም ተጠቃሚ ማድረግ ይቻላል።በከተማዋ የሚስተዋለው የግሉ ተሳትፎ ጂምናዚየሞች ላይ የተወሰነ ነው። በመሆኑም የኦሊምፒክ ስፖርት በሆኑ ሌሎች የቤት ውስጥ ስፖርቶች ላይም ተሳታፊ ለመሆን የሚፈልጉ ባለሀብቶችን በማበረታታት ስፖርቱን መደገፍ ይገባል። ለግል ባለሀብቶች ለስፖርቱ በዋናነት ግብዓት የሚሆኑ ቁሳቁስ ከቀረጥ ነፃ እንዲገቡ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑንም በመድረኩ ተጠቁሟል። ከባለሀብቱ ባሻገር የስፖርት ክለቦችም በማዘውተሪያ ስፍራ ልማት ቢሰማሩ ለመንግሥት ላይ ብቻ የተተወውን ዘርፍ ሊደግፉ እንደሚችሉም ተነስቷል። ጉባኤተኞቹ የሚገነቡ ማዘውተሪያዎች ሁሉንም ስፖርቶች ያማከሉ መሆን እንደሚገባቸውም አመልክተዋል። በከተማዋ ከ30 በላይ የሚሆኑ የአትሌቲክስ ቡድኖች እያሉ ለስፖርቱ የሚሆን ማዘውተሪያ ያለው በአዲስ አበባ ስታዲየም ብቻ መገኘቱ ሌላው አሳሳቢ ችግር መሆኑ ተጠቁሟል። ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት የከተማ አስተዳደሩ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር በላይ ደጀን፤ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መንግሥታዊ በሆኑና ባልሆኑ አካላት በየአካባቢው ሊጠናከሩ እንደሚገባ ነው ያመለከቱት። እንደ ኮሚሽነሩ ገለጻ፤ የታዳጊ ፕሮጀክት ስልጠናን ለማስፋፋትም ሆነ ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት የሚቻለው ማዘውተሪያዎችን ማስፋትና ማልማት ሲቻል ነው። የመዘውተሪያ ስፍራዎች ጉዳይ የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ርብርብ የሚጠይቅ ቁልፍ ሥራ በመሆኑ በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል። ከሚሽነሩ ትምህርት ቤቶች በአካልም በአእምሮ የበለጸገ ዜጋ ለማፍራት የሚያስችል ስፍራ እንደመሆናቸው 300 የሚሆኑ የሰውነት ማጎልመሻ መምህራን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ስልጠና እንዲያገኙ መደረጉን ጠቅሰው፣ ይህንን ተከትሎ የመጣው ጥያቄ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን የሚመለከት መሆኑን ይጠቅሳሉ። ስለዚህም ማዘውተሪያዎቹን በትምህርት ቤቶች ውስጥ ማልማት እንዲሁም ተማሪዎች ከሚጠቀሙበት ሰዓት በኋላ በሚኖረው ጊዜ የአካባቢው ወጣቶችና ታዳጊዎች የሚጠቀሙበትን ሁኔታ ማመቻቸት እንደሚያስፈልግ ያብራራሉ። ከዚህ ባሻገር በከተማዋ የሚገኙ ነባር ማዘውተሪያዎችን በማደስና አዳዲሶችንም በጥራትና በፍጥነት ለማስገንባት ቢሮው በእንቅስቃሴ ላይ መሆኑንም ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል። ለዓመታት ጥያቄ ሲነሳባቸው የቆዩ የማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሞከረ ነው። ከባድ የሆነው ግን ከዚህ ቀደም የተጀመሩና በግንባታ ላይ የቆዩ ነባር ማዘውተሪያዎችን የጥራት ጉድለት እያለባቸው ወደ ሥራ ማስገባት ነው ሲሉ ያመለክታሉ። ለአብነት ያህል የአበበ ቢቂላ ስታዲየም ሜዳውን ለእግር ኳስ መሙን ደግሞ ለአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች መስጠት ይቻላል ነገር ግን አሁን የጥራት ጉድለት አለ ይላሉ። በሌሎችም እንዲሁ የዲዛይን ችግር፣ የግንባታ ክፍተት፣ የክትትልና ቁጥጥር ድጋፍ የሚጎድላቸው እንዲሁም በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ያልተጠናቀቁም እንዳሉም ይናገራሉ። በእነዚህ ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶበት የሚሰራ ይሆናል ብለዋል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የስፖርት ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አዳነች አቤቤም፤ በከተማዋ ታዳጊዎች የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች በማጣታቸው ባልተገባ ስፍራ እንደሚውሉ ጠቅሰዋል። ይህንን በመረዳትም በየአካባቢው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ያመለክታሉ። ምክትል ከንቲባዋ ይህ ግን በቂ እንዳልሆነ ተናግረው፣ ከዚህም በላይ መስራት እንደሚገባም ይጠቁማሉ። የጠቅላላ ጉባኤው አባላት በተናጠልም ሆነ በጋራ ኃላፊነትን በመወጣት የተጀመሩትን ውጤታማ ማድረግና በሁሉም አካባቢ ማዳረስ እንደሚገባም አሳስበዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=38041
[ { "passage": "የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ከሚያስገነባቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መካከል አንዱ የጃንሜዳ ጂምናዚየም ነው። ይህ ጅምናዚየም በጃንሜዳ መከናወኑም፣ ጃንሜዳ፣ የከተማዋን ነዋሪዎች በስፖርታዊ እንቅስቃሴ ከሚያሳትፉ ቦታዎች ዋነኛው እንደመሆኑ ግንባታው ተጨማሪ ጠቀሜታ እንደሚሰጥ ስለታመነበት ነበር። ነገር ግን በዚህ ወቅት ግንባታው ሙሉ ለሙሉ ተቋርጦ ባለበት ቆሟል። «ግንባታው በምን ምክንያት ተቋረጠ?» በሚለው ላይም አዲስ ዘመን ጋዜጣ የሚመለከታቸውን አካላት አናግሮ በዛሬው እትሙ እንደሚከተለው አሰናድቷል።አቶ ማቲዎስ ኦልቀባ፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የማዘውተሪያ ስፍራዎች ዳይሬክተር ተወካይ ናቸው። ሰኔ 10 ቀን 2005 ዓ.ም ቢሮው ለጂምናዚየሙ ግንባታው ውለታ ሲገባ በ540 ቀናት (ታህሳስ 9 ቀን 2007 ዓ.ም) ይጠናቀቃል በሚል ነበር። ይሁን እንጂ ከግንባታው መጓተት ባለፈ ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ ስራው ሙሉ ለሙሉ በመቋረጡ ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት እለት ድረስ ግንባታው በጅምር ቀርቷል፡፡ ለግንባታው መቋረጥ ምክንያት የሚሆነውም የመዋቅር ስራው ሙሉ ለሙሉ ከተጠናቀቀ በኋላ ጣሪያ ለማልበስ የማይቻል በመሆኑ ነው። ግንባታው በዚህ መልክ ከመቋረጡ አስቀድሞ የጂምናዚየሙ ዲዛይን በተዘጋጀው መልኩ ለመገንባት መሰረቱ ስለማይችል ባለ አንድ ፎቅ መሆኑ እንዲቀር መደረጉንም ተወካዩ ያስታውሳሉ።እንደ አቶ ማቲዎስ ማብራሪያ፤ ዲዛይኑ እንዲስተካከል ከተደረገ በኃላ በድጋሚ ወደ ግንባታ የተገባ ቢሆንም፤ ጣሪያውን የሚይዙት ምሰሶዎች ላይ ሌላ ችግር መኖሩን ተቋራጩ አስታወቀ። ለሁለተኛ ጊዜም ዮሃንስ አባይ የተባለው አማካሪ ድርጅት ዲዛይኑን ማስተካከል እንዳለበት በተቋራጩ ጥያቄ በመቅረቡ፣ የማጣራት ስራው ለሶስተኛ አካል ሊሰጥ ችሏል። በማጣራቱ ላይ የተሳተፈው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም ችግሩ መኖሩን በደብዳቤ በማረጋገጡና አማካሪውም በማመኑ በድጋሚ ማሻሻያ ለማድረግ ተስማማ። በዚሁ መሰረት አማካሪው ድርጅት ማሻሻያ ያደረገበት ዲዛይንም 10 ሚሊዮን ብር ተጨማሪ ወጪ የሚጠይቅ ነበር።የማዘውተሪያ ስፍራዎች ዳይሬክቶሬትም የገንዘቡን መጠን ለፋይናንስ ቢያሳውቅም ፍቃደኛ አልነበረም። የመንግስት ግንባታን በበላይነት የሚከታተለው የአዲስ አበባ ኮንስትራክሽን ቢሮም ይህ ሊሆን እንደማይችል አቋም አሳየ። የስራ ተቋራጩም በበኩሉ በተሻሻለው ዲዛይን የቀረበው ጥሬ ዕቃ ውድ በመሆኑ በዚህን ያህል ዋጋ ግንባታውን ሊያከናውን እንደማይችል አሳወቀ። በእነዚህ ምክንያቶችም የኮንስትራክሽን ህጉ በሚፈቅደው መሰረት ውሉ ተቋርጦ በጃንሜዳ የተጀመረው ጂምናዚየም ግንባታ ላለፉት ስድስት ዓመታት ከሚጠበቅበት የጥራትና የአፈጻጸም ደረጃ በታች ሆኖ የቆየው ሥራ ባለበት ሊቆም ተወስኖበታል።ግንባታው እዚህ ደረጃ ከመድረሱ አስቀድሞ ዲዛይኑ ችግር እንዳለበት ተቋራጩ እንዲሁም ተቆጣጣሪ መሃንዲሶች በደብዳቤ ሲያሳውቁ እንደነበር ተወካዩ ያስታውሳሉ። በዚሁ ምክንያትም ባለ አንድ ፎቅ መሆኑ ቀርቷል፡፡ በዚህም ቢሮው ከመስማማት በቀር አማካሪውን ተጠያቂ የማድረግ ስራ አላከናወነም ነበር። አሁን ግን ዲዛይኑ ችግር እንዳለበት አማካሪው በማመኑ ለደረሰው ኪሳራ ኃላፊነቱን ይወስዳል። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ላደረገው ማጣራትም 200ሺ ብር ከአማካሪው እንዲከፈለው የሚያደርግ ውሳኔም ተላልፎበታል።ከዚህ ባሻገር ከላይ ሆኖ ስራውን የሚቆጣጠረው መንግስታዊው አካል ጣልቃ ገብቶ ችግር መኖሩን፤ በዚሁ ምክንያትም መዘግየት መፈጠሩን ለቢሮው አለማሳወቁም በክፍተትነት እንደሚታይ ተወካዩ ይገልጻሉ። ቢሮው ለደረሰበት የገንዘብ፣ የጊዜ እና ሌሎችም ኪሳራዎች አማካሪውን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ የኮንስትራክሽን ቢሮው የኮንስትራክሽን ህጉን ማጣቀስ ስለሚገባው በእነርሱ በኩል የሚከናወን ይሆናል።ስለ ግንባታው ግንባታውን በበላይነት የሚቆጣጠረው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮንስትራክሽን ቢሮ በባለሙያዎች (መሃንዲሶች) የሚከተለውን ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በቢሮው የሳይት ሱፐርቫይዘር ታደለ ደንደና፤ ሁለተኛ የዲዛይን ማሻሻያ በተደረገበት ወቅት (2008 ዓ.ም) ወደ ስራ እንደገባ ይገልጻል። በወቅቱ ተቋራጩ ችግር መኖሩን ቢያሳውቅም አማካሪው ሊቀበል ባለመቻሉ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንዲያጣራ መደረጉን ያስታውሳል። በዲዛይኑ ላይ ችግር መኖሩ ከተረጋገጠ በኃላም ተቋራጩ ውሉ እንዲቋረጥ በ2009 ዓ.ም በጠየቀው መሰረት በ2010 ዓ.ም ግንባታው እንደቆመ ያረጋግጣል።በቢሮው የውለታ አስተዳደር ባለሙያ መቆያ አለማየሁ በበኩሉ፤ በከተማዋ ያሉ የመንግስት ግንባታዎችን በበላይነት የሚቆጣጠረው ኮንስትራክሽን ቢሮው ቢሆንም፤ ከአቅሙ በላይ የሆኑ ስራዎችን ግን ለሌሎች አማካሪዎች እንደሚሰጥ ያስረዳል። በዚህ መሰረትም የጃንሜዳ ጂምናዚየም ግንባታ በበርካታ ፕሮጀክቶች ላይ እየተሳተፈ ላለው ዮሃንስ አባይ ለተባለ አማካሪ ድርጅት በጨረታ ተላልፎ ተሰጥቷል፡፡ ወደ ስራው ከተገባ በኋላ ግን የተለያዩ ችግሮች አጋጥመዋል፤ ተቋራጩም ውሉ ይቋረጥልኝ ሲል ባቀረበው ጥያቄ መሰረት ግንባታው 54 በመቶ ላይ እያለ ሊቋረጥ እንደቻለም ባለሙያው ያስረዳል።ዲዛይን በባህሪው ሙሉ ሊባል የማይችልና በየጊዜው ሊሻሻል የሚችል ሲሆን፤ በመጀመሪያ ያጋጠመውም ትንንሽ ማሻሻያ ሊባሉ ከሚችሉት የሚመደብ ነበር። ከዚያ በኋላ ያለውና ፕሮጀክቱንም ያስቆመው ትልቁ ምክንያትም የቆሙት ምሰሶዎች ጣሪያውን መሸከም ስላልቻሉ ነው። ተቋራጩ በአማካሪው ችግር ፕሮጀክቱ ላይ አንድ ነገር ቢደርስ ተጠያቂ ስለሚሆን፣  ባለቤትንም ካሳ መጠየቅ ስለሚችል፤ እንዲሁም ከአማካሪው ጋር አለመግባባት ውስጥ በመግባቱ በስምምነት ውሉ እንዲቋረጥ ባለቤትን በመጠየቅ መቋረጡንም ባለሙያው ይገልጻል።እስካሁን ለደረሰው ብክነትም በዋናነት ተጠያቂ የሚሆነው አማካሪው ቢሆንም፤ ለተጓተተው ጊዜ ግን ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተጋሪ ይሆናሉ። በዚህ መሰረትም ኮንስትራክሽን ቢሮው አማካሪው መቀጣት ይኖርበታል ከሚል ውሳኔ ላይ ደርሶ  ለባለቤቱ ደብዳቤ ጽፏል። ከገንዘብና ከሌሎች ጉዳዮች ጋር የደረሰበትን ተከታትሎ የሚያስቀጣውም ባለቤት መሆኑን ይጠቁማል።ውስብስብ ችግሮች ካሉባቸው ፕሮጀክቶች መካከል ከራስ ኃይሉ ስፖርት ማዕከል ቀጥሎ የጃንሜዳ ጂምናዚየም መሆኑን የሚጠቅሰው ደግሞ፤ የስፖርት ፕሮጀክቶች ተባባሪ መሃንዲስ ፍቃዱ አለሙ ነው። ቢሮው ከዚህ ቀደም ፕሮጀክቱ ይቋረጥ በሚል ሃሳቡን ቢያሳውቅም ባለቤት ግን ባለው ይቀጥል የሚል ምላሽ መስጠቱንም ይጠቁማል።በዚህ ሃሳብ የማይስማሙት ተወካዩ አቶ ማቲዎስ በበኩላቸው፤ ቢሮው ውል የማቋረጥ ኃላፊነት እንደሌለውና ይህ ስራ የሚመለከተውም ኮንስትራክሽን ቢሮውን መሆኑን ነው የሚጠቅሱት። ግንባታውን የመከታተል ስራ የኮንስትራክሽን ቢሮ እንደመሆኑ ውሉን አቋርጦ ለቢሮው ማሳወቅ ይችል እንደነበርና ውሉ ይቋረጥ በሚል በቅድሚያ ደብዳቤ የጻፈውም ቢሆን ተቋራጩ መሆኑን ይገልጻሉ። ነገር ግን ከዚህ ቀደም ከዲዛይን ጋር በተያያዘ የአማካሪ ድርጅቱ ውል ይቋረጥ የሚል ደብዳቤ ከኮንስትራክሽን ቢሮ ለስፖርት ቢሮ መጻፉን አልሸሸጉም። የቢሮው ምላሽም እስካሁን ለደረሰው ነገር ተጠያቂ ይሁን የሚል እንደነበርና ከዚያ በኋላ ኮንስትራክሽን ቢሮው ተመልሶ ወደ ድርድር መግባቱንም ያስታውሳሉ።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ በጂምናዚየሙ መዘግየት፤ የጊዜ፣ የገንዘብና የጥራት ብክነት ደርሶበታል። ተወካዩ ይህንን ሲያብራሩም ጊዜው በጨመረ ቁጥር ገንዘቡም በዚያው ልክ የሚጨምር ይሆናል። በወቅቱ ውል የተገባው በ48 ሚሊዮን ብር ቢሆንም፤ እስካሁን ለመዋቅር ስራው ብቻ 36 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጓል። አሁን ላለበት ደረጃ ከ50 በመቶ በላይ መውጣቱም ቢሮውን ተጎጂ ያደርገዋል። ግንባታው በጥራት ሳይሰራ ቢጠናቀቅ ኖሮም የሰውን ህይወት አደጋ ላይ ሊጥል የሚችል ኪሳራ ያደርስ ነበር።ሆኖም ጃንሜዳ እንደሚታወቀው በርካታ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች አካላዊ እንቅስቃሴ የሚያደርጉበት ቦታ እንደመሆኑ ጂምናዚየሙ በጉጉት የሚጠበቅ ነበር። ነገር ግን ቦታው ለህብረተሰቡ ግልጋሎት ሳይውል፤ ግንባታውም ሳይጠናቀቅ ዓመታትን ማስቆጠሩ ማህበራዊ ጉዳትና ኪሳራ አስከትሏል። በዚህ ግንባታ ምክንያትም ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ ሊደርስ ችሏል።ኮንስትራክሽን ቢሮ ባለቤትን ወክሎ የሚሰራ እንደመሆኑ ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜ ተገንብቶ ባለመጠናቀቁ፤ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እንዲሁም ከሃገራዊ ገጽታ አንጻር ችግር ማስከተሉን የፕሮጀክት አስተባባሪው ያመላክታል። እንደ ኮንስትራክሽን ቢሮም ለከተማዋ የተሻለ ገጽታ በማላበስ ረገድ የተሰጠውን ኃላፊነት በተወሰነ መልኩ ይቀንሳል። አማካሪው ላደረሰው ኪሳራም በህጉ መሰረት እስከ ሁለት ሚሊዮን ብር እንዲቀጣ ተወስኖበት ለባለቤት ተላልፏል። ከዚህ በኃላም መሰል ጥፋት እንዳይደርስ አማካሪዎች ምን ሰርተዋል የሚለውን በቴክኖሎጂ አስደግፎ ለመስራትና ተቋራጩ ደረጃ አንድ እንዲሆን መወሰኑንም ያክላል።ግንባታውን በበላይነት የሚቆጣጠረው ኮንስትራክሽን ቢሮ ለከተማው ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሂደቱን በማሳመን ውሉን ካቋረጠ በኃላም ቀሪ ስራዎች ተለቅመው ወደ ስራ እንዲገባ ተወስኗል። በዚህም መሰረት የማዘውተሪያ ስፍራዎች ዳይሬክቶሬት ፋይናንስን የጠየቀ ሲሆን፤ ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ ተጠንቶና ውስን ጨረታ ተደርጎ ወደ ስራ ይግባ በሚል መፍቀዱን ተወካዩ አቶ ማቲዎስ ያስረዳሉ። ይህንንም ለኮንስትራክሽን ቢሮ በማሳወቅ ቀሪ ስራዎችን ለቅመው እንዲያመጡ ተጠቁሟል። በመሃል የባለሙያዎች መቀያየር ስለነበር መዘግየት ቢኖርም በቅርቡ ይጨርሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።የውለታ አስተዳደር ባለሙያው በበኩሉ፣ አሁን ባለበት ሁኔታ ቀሪ ስራዎችን በመያዝ እንደ አዲስ ጨረታ የተዘጋጀ መሆኑን ይገልጻል። ጨረታው የወጣውም ጣሪያውን በራሱ ዲዛይን አድርጎ መስራት የሚችል ነው፤ ይህም ከዚህ ቀደም ያጋጠመውን ጨምሮ በርካታ ጉዳዮችን ለማስቀረት ይችላል። በዚህም መሰረት በአዲስ ውለታ በቅርብ ጊዜ ወደ ስራ ይገባል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፤ ስራውም በ6 ወራት ይጠናቀቃል የሚል እቅድ ተይዟል።ቢሮው አሁንም የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን በመገንባት ላይ ይገኛል፤ ከዚህ በኋላም በእቅድ የያዛቸው ግንባታዎች አሉ። በመሆኑም ተመሳሳይ የዲዛይንና ሌሎች ችግሮች እንዳይገጥሙት እንደ ባለቤት ምን ለመስራት አቅዷል በሚለው ላይም ተወካዩ እንዳሉት፤ ቁጥጥሩን ከስራው ጎን ለጎን እንዲሄድ ይደረጋል፤ ቢሮውን በባለሙያ በማጠናከር ላይ ይሰራል። ቢሮው ጥናት አድርጎ ባለሙያዎችን ለመቅጠር ማሰቡም የተሻለ ስራ ለመስራት ያስችላል፡፡", "passage_id": "50d4c6ee47d7928c28c1716572663abb" }, { "passage": "አዲስ\nአበባ፡- 52 ኪሎ ሜትር ከሚሸፍነው የአዲስ አበባ ከተማ የወንዝ ዳርቻዎችን ለመናፈሻ የማዋል ሥራ ውስጥ ሁለት ኪሎ ሜትሩን የጣሊያኑ ቫርኔሮ ኩባንያ ስራ መጀመሩን የተፋሰስና አረንጓዴ አካባቢዎች ኤጀንሲ አስታወቀ። በሸራተን ማስፋፊያ አካባቢ የሚሰራው ሁለገብ አገልግሎት ያለው የመናፈሻ ፓርክ ሥራም ከኩባንያው ጋር የውል ስምምነት ለመፈጸም በሂደት ላይ መሆኑም ተጠቁሟል። የኤጀንሲው\nዳይሬክተር ዶክተር ስለሺ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት የአዲስ አበባ ከተማ የወንዝ ዳርቻዎችን ለመናፈሻ የማዋል ሥራ አጣዳፊ የጎርፍ ችግር ሲያጋጥምና የአካባቢውን ነዋሪዎች ለአደጋ ሲያጋልጥ አደጋውን ከመከላከል ጎን ለጎን ወንዞችን ለመናፈሻ የማዋል ሥራ ቀድሞም ሲከናወን የቆየ ነው። ይህ የሚለየው የፕሮጀክቱ ግዝፈትና ከላይኛው እስከ ታችኛው ተፋሰስ ድረስ ወጥ በሆነ መልኩ መከናወኑ ነው ብለዋል።በፕሮጀክቱ\nአምስት ገባር ወንዞችንና ሰባት የከተማዋን የወንዝ ዳርቻዎች ለመናፈሻ ለማዋል በጥናት ተለይተዋል የሚሉት ዳይሬክተሩ የሁለት ኪሎ ሜትሩ ሥራ ቢጀመርም ቀሪው ጥናት ላይ መሆኑንና በምዕራፍ ተከፋፍሎ አጠቃላይ ሥራውን በሶስት አመት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ መታቀዱን አመልክተዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ማብራሪያ የአካባቢውን ነዋሪ ብዛት ታሳቢ በማድረግና የልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል ከእንጦጦ፣አፍንጮ በርና ቡልቡላ አድርጎ አቃቂ የሚሄደው ወንዝ በፕሮጀክቱ በቅድሚያ ተካትቷል፡፡ ፕሮጀክቱ\nበፌዴራል መንግሥት፣በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣በብድር፣በገቢ ማሰባሰብና በተለያዩ ድጋፎች የሚከናወን ሆኖ በአጠቃላይ 29 ቢሊዮን ብር እንደሚፈጅ አስረድተዋል፡፡ ቻይና መንግሥት ከእንጦጦ እስከ ቡልቡላ ያለውን በገንዘብ ለመደገፍ ፍላጎት ማሳየቱን አስታውሰው በተመሳሳይ መንገድ ፕሮጀክቱን ለመደገፍ ፍላጎት ያላቸው ዓለምአቀፍ ድርጅቶች መኖራቸውንም ጠቁመዋል፡፡ የልማቱ ሥራ ከሚከናወንበት አካባቢ 32ሺ ተነሽዎች እንደሚኖሩት የሚጠበቀው ይህ ፕሮጀክት ለሚነሱ ነዋሪዎች ምትክ ቦታና አስፈላጊውን ካሳ አሟልቶ ከቦታው አስነስቶ ወደ ሥራ ለመግባት የተባባሪ አካላት ድጋፍ ወሳኝ እንደሆነ ዶክተር ስለሺ አስረድተዋል፡፡ የፕሮጀክት መጓተት እንዳይኖርም በቅድ መዘጋጀቱ ትኩረት መደረጉን ገልጸዋል፡፡ በሸራተን ማስፋፊያ አካባቢ በሁለት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር ወጪ የአረጓዴ ቦታ፣ የልጆች መጫወቻ፣አንፊ ቲያትር፣ የገበያና የተለያየ አገልግሎት መስጫ ያለው የፓርክ ሥራም የወንዝ ዳርቻና መናፈሻ ሥራው አካል መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ የፕሮጀክቱ የአዋጭነት ጥናት መካሄዱንም ይናገራሉ፡፡ በወንዞች\nዳር መናፈሻ ፕሮጀክት ጥናቱ ላይ የተሳተፉት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአካባቢ ሳይንስ መምህር ፕሮፌሰር ተሾመ ሶሮምሳ እንደገለጹት ጥናቱ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት አማካኝነት እኤአ በ2016 የተጀመረ ሲሆን፣ በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ መጠናቀቁን ያስታውሳሉ፡፡ ጥናቱ\nሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን የዳሰሰና አምስት ዋና ዋና ጉዳዮችን ያካተተ ነው ያሉት ፕሮፌሰሩ በከተማዋ የ127 አመት ታሪክ ውስጥ ሰፊ የሆነ የወንዝ ዳር ልማት ሥራ በመሆኑ አዲስና ሥር ነቀል ለውጥ እንደሚያመጣ አመልክተዋል፡፡ በጥናቱ ግኝት በከተማዋ 607 ኪሎሜትር ርዝመት ያላቸው 76 ወንዞች ይገኛሉ፡ ፡ አሁን በተጀመረው የልማት ሥራ በ20 አመት ጊዜ ውስጥ ሁሉንም መናፈሻ ማድረግ የሚቻልበት ዕድል መኖሩን ፕሮፌሰሩ አመልክተዋል፡፡አዲስ\nዘመን መጋቢት 19/2011በለምለም\nመንግሥቱ", "passage_id": "6de2d9d2797b70545a95cb7f2eb406c0" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- በአዲስ አበባ ከተማ በውጭ እና በሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ ዘመናዊ መንደሮች ግንባታ መካሄድ ከተማዋን ወደ ተቀናጀ የከተማ ልማት የሚያሸጋግርና ኢኮኖሚያዊ ትሩፋቱም የላቀ መሆኑን የከተማ ፕላን ባለሙያዎች አስታወቁ፡፡በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ\nየከተማ ልማት ምህንድስና\nኮሌጅ ዲንና የአዲስ\nአበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር፣\nዶክተር ዳንኤል ሊሬቦ\nበተለይ ለአዲስ ዘመን\nእንደገለፁት፣ የአፍሪካ መዲና\nየዓለም አቀፍ ተቋማትና\nዲፕሎማቶች መቀመጫ የሆነችው\nአዲስ አበባ አሁን\nባለችበት ገፅታ ዓለምአቀፍ\nመስፈርቶችን ከማያሟሉት ከተሞች መካከል ትመደባለች። ይህም በሚያሳዝንና በሚያስተዛዝብ መልኩ ከተማዋን ለነዋሪዎችም ሆነ ለእንግዶች በሚመች መልኩ በዘመናዊ መንገድ የማልማት ፕሮጀክት ትግበራ እጦት ውጤት ነው። «ይህ ታሪክ ተለውጦ በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ከተማ የተጀመሩ የዘመናዊ መንደር ግንባታ ፕሮጀክቶች ከተማዋን ዳግም የሚወልዱና ህዳሴዋን የሚያስጀምሩ ናቸው» ያሉት ዶክተር ዳንኤል፣ ከተማዋ ስሟን በሚመጥን መልኩ ተወዳዳሪ፣ ለነዋሪዎች ተስማሚና ለጎብኚዎች አማላይ እንድትሆን የሚያስችሉና ኢኮኖሚያዊ ትሩፋታቸውም የላቀ መሆኑን አብራርተዋል።ፕሮጀክቶቹ የከተማዋን አጠቃላይ ገጽታ በመቀየር በተለይ ለነዋሪዎችና ቱሪስቶች ምቹ ከባቢን በመፍጠር የጎብኚዎች መናኸሪያ መሆን እንደሚያስችላት አመልክተው፣ ግንባታው የመሬት ጥበት ባለባቸው አገራት በተለይ በትንሽ ቦታ ላይ በርካቶችን ለማስፈር የሚያስችል መሆኑንም ገልጸዋል። «ውስን የሆነውን የከተማዋን የመሬት ሀብት በአግባቡ ለመጠቀም ፋይዳው የላቀ ነው፤ ፕሮጀክቶቹ የግሉን ዘርፍ ተሳታፊ ማድረጋቸውም ጠቀሚታውን ያገዝፈዋል» ብለዋል። እንደ ዶክተር ዳንኤል ገለጻ፤ ፕሮጀክቶቹ ሜጋ ፕሮጀክቶች እንደመሆናቸውም ምቹ መኖሪያዎችን ገንብቶ ዜጎችን ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ይፈጥራል፤ የተደራጀ የመሠረተ ልማት ዝርጋታ እንዲኖርም ያግዛል።የዘመናዊ መንደሮቹ ግንባታ ቅይጥ በሆነ መልኩ የመኖሪያ አፓርትመንቶችን የመዝናኛና የንግድ ማዕከል፣ አረንጓዴ ስፍራዎች የሚያካትት መሆኑም በተለይ ማታ ላይ እንቅስቃሴ የምታቆመውንና ወደ ጭለማ የምትቀየረውን ከተማ፣24 ሰዓት ደማቅ እንድትሆን ያስችላል። መሰል ፕሮጀክቶች ሲተገበሩም\nበዋነኝነት ጥንቃቄ ማድረግ\nየግድ መሆኑን ያስገነዘቡት የከተማ ልማት ባለሙያው፣ ግንባታዎቹ በሕግና ሥርዓት መመራት እንዳለባቸውም አመልክተዋል። ለባለሀብቶች መሬት ከማስተላለፍ ጀምሮ በሌሎችም ሂደቶች መንግሥት ኃላፊነቱን በአግባቡ በመከወን ልማቱን ማስቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል።በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የድህረ ምረቃ ትምህርት ቤት ዳይሬክተርና አርክቴክት ፕላነር ዶክተር ፍሬው መንግስቱ በበኩላቸው፣ መሰል ግዙፍ ፕሮጀክቶች በከተማ ልማት ላይ የሚያበረክቱት ፋይዳ ዘርፈ ብዙ መሆኑን በመጠቆም፣ በተለይ የተቀናጀ የከተማ ክልል ልማትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆናቸውን አስታውቀዋል።ባለሀብቶችን በማቀናጀት በመሰል ፕሮጀክቶች ላይ ማሳተፍ ሊደነቅና ሊበረታታ የሚገባው እርምጃ መሆኑን ጠቁመው፣ «ፕሮጀክቶቹ ሲተገበሩም ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል» ሲሉ ዶክተር ፍሬውም አስገንዝበዋል። ከሕዝብ ትብብር አንስቶ የባለድርሻ አካላትን ቅንጅት ለመፍጠር የጋራ ራእይ እንዲኖር ማድረግና ይህንንም በአግባቡ መፈፀም እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል።አዲስ አበባ ስሟን እንድትመጥን በሚያደርጉ ተመሳሳይ ፕሮጀክቶች በተለይ «የተቀናጀ የከተማ ክልል ልማትን ለመምራትና ለማስተባበር በሌሎች አገራት እንደሚደረገው በዘርፉ ብቃት ካላቸው ባለሙያዎች ጋር በቅርበት መስራት ያስፈልጋልም» ብለዋል።በአሁኑ ወቅት የተለያዩ የውጭ እና የሀገር ውስጥ ኩባንያዎች በአዲስ አበባ ከተማ ዘመናዊ መንደሮችን ለመገንባት እየተንቀሳቀሱ መሆናቸው ይታወቃል። የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች ባለሀብቶች በለገሀር ግንባታ የጀመሩ ሲሆን፣ የአፋር ባለሀብቶች የአሚባራ መንደር ግንባታን በጎተራ አካባቢ በይዞታቸው ላይና ከከተማ አስተዳደሩ በሚገኝ ተጨማሪ ቦታ ላይ ተመሳሳይ ግንባታ ለማካሄድ የመሰረት ድንጋይ አስቀምጠዋል። የቻይና ኩባንያዎችም በጎተራ አካባቢ ተመሳሳይ ግንባታ እንደሚያካሂዱ ይጠበቃል።አዲስ ዘመን የካቲት 17/2012ታምራት ተስፋዬ ", "passage_id": "13d13df440ca73269c1ae43a4c8513d4" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 3፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ታሪካዊ ቅርሶችን የመጠበቅ እና የህዝብ መዝናኛ ስፍራዎች የማስፋፋት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለፀ።", "passage_id": "626cb357ab37cd78c8b5fd0207ab07fa" }, { "passage": "አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ብሎም የአፍሪካ ህብረትና የበርካታ አለም አቀፋዊ ድርጅቶች መቀመጫ ብትሆንም ዘመኑን የሚመጥን የመሰረተ ልማት እና የቱሪስት መስህብ ስፍራዎችን አልያዘችም። ከተማዋ ካለባት የፅዳት ጉድለት እና ንፁህ አየር ችግር የተነሳ በነዋሪዎቿና ለአጭርም ይሁን ረዘም ላለ ጊዜ ሊጎበኟት በሚመጡ እንግዶቿ ስትተች ኖራለች። የወንዝ ዳርቻዎቿ የቆሻሻ ማራገፊያና ማጠራቀሚያሆነው በአካባቢው ለሚያልፍ ነዋሪ በሽታን እንካችሁ ሲሉ ከቆዩ ከራርመዋል።ይህ የከተማዋ መለያ የሆነው የቆሻሻ ጉዳይ እና የመዝናኛ ቦታዎች እጥረት ታሪክ ሊሆን የሶስት አመታት ጊዜ የተያዘለት ሸገርን የማስዋብ ፕሮጀክት 48 ሄክታር ስፋት ያላቸው የማዕከላዊ ፓርኮች ግንባታ እና 51 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ያላቸው ከእንጦጦ ተራራ እስከ አቃቂ ወንዝ የሚደርሱ ሁለት ትላልቅ ወንዞችን የማልማት ስራ ተጀምሮ ግንባታዎች በፍጥነት እየተከናወኑ ነው። የፕሮጀክቱ ሰራተኞችም ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ደፋ ቀና ሲሉ ተመልክተናል።የዚሁ ፕሮጀክት አካል የሆነው የማዕከላዊ ፓርክ ግንባታ እና 12 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳር ልማት ፕሮጀክት በመስከረም ወር 2012 ዓ.ም በይፋ የማስጀመር ስነ ስርዓት በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ እና በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ታን ጂያን የመሠረት ድንጋይ በማስቀመጥ መጀመሩ ይታወሳል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የሸገርን ማስዋብ ፕሮጀክት አካል የሆነውን የአዲስ አበባ ወንዝ ዳርቻ አረንጓዴ ልማት ስራ ትናንት ሸራተን አካባቢ ባለው የግንባታ ቦታ ተገኝተው በጎበኙበት ወቅት በብልፅግና ዘመን ለአዲስ አበባ ከተማ ፀሀይ እየወጣላት እንደሆነ ተናግረዋል። ይህ ፕሮጀክት ከሚጠበቀው በላይ እየተከናወነ እንደሆነ የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በመንግስት የፕሮጀክቶች ማስፈፀም ላይ እየተስተዋለ ያለውን ችግር እየቀረፈ ያለ ማሳያ ተደርጎ ሊታይ የሚችል እንደሆነም ጠቁመዋል።ፕሮጀክቱ እንጦጦ እና አንድነት ፓርክ ላይ እየተሰራ ያለውን ስራ እንዲሁም ከእንጦጦ እስከ ፒኮክ ያለውን የወንዝ ዳር ማልማት ፕሮጀክት የሚያገናኝ እና የአዲስ አበባን ገፅታ በብዙ መልኩ የሚቀይር ነው ተብሏል። ‹‹በብልፅግና ጉዞ ዘመን አንዱ ማረም የምንፈልገው ነገር የምናስበውን መፃፍ፣ የምንፅፈውን ለህዝብ መናገር እና የተናገርነውን ደግሞ ተግባራዊ አድርጎ መገኘት ነው›› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህ አንፃር ፕሮጀክቱ አርአያ ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል እንደሆነም ተናግረዋል።ኢትዮጵያ ውስጥ ስራ ተጀምሮ በታለመለት ጊዜ ሲጠናቀቅ እንደማይስተዋል የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ 47 ሄክታር ገደማ ስፋት ያለውና በውስጡ ምግብ ቤቶች፣ ካፍቴሪያዎች፣ መዝናኛ ማዕከላትና ሌሎችንም ያካተተው ይህ ስራ በሶስት ወራት ውስጥ 45 በመቶ መጠናቀቁን ገልፀዋል። በመጪው ግንቦት ወር ተጠናቆ ሙሉ በሙሉ ክፍት እንደሚሆን የተገለፀ ሲሆን ከእንጦጦ እስከ ፒኮክ ያለው የወንዝ ዳር ማልማት ፕሮጀክት ደግሞ በሚቀጥለው አመት እንደሚሰራ ተገልጿል።አዲስ አበባን እንደ ስሟ አዲስ አበባ በማድረግ የአፍሪካ ካፒታል እንድትሆን ሰፊ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የችግኝ መትከል፣ ማጽዳት፣ ፓርኮችን ማስፋፋትና መሰል ስራዎች በሚቀጥሉት ሶስት አመታት በትኩረት እንደሚከናወኑ ተናግረዋል።አዲስ አበባን ድንቅ ከተማ በማድረግ ለነዋሪዎቿ ብሎም ለጎብኝዎች የተመቸች እና ሳቢ እንድትሆን መላው የከተማዋ ነዋሪዎች እንዲሁም ወዳጆች ዛፎችን በመትከል፣ በማፅዳት እና ልማቶችን በመንከባከብ አርአያ ሊሆኑ እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።‹‹የነዋሪዎቿን ኑሮ ማሻሻል፣ ስራ አጥነትን መቀነስና የማልማት ስራ መስራት አዲስ አበባ የእኛ መሆኗን የምናረጋግጥባቸው መንገዶች ናቸው›› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ገፅታዋን በመቀየር ተቆርቋሪነትን ማስመስከር እንደሚገባም ገልፀዋል። በፕሮጀክቱ ለ1 ሺህ 300 ያህል ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር የተቻለ ሲሆን ከሁለት ወራት በኋላ 4 ሺህ ሰዎች እንደሚቀጠሩ ይህም የስራ እድል ፈጠራውን ስራ እንደሚያግዝ ተነግሯል።እነዚህና መሰል ፕሮጀክቶች አዲስ አበባ በብልፅግናው ዘመን ፀሀይ እየወጣላት ስለመሆኑ ማሳያዎች ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ፣ ፀሀዩን ወደ ሌሎች የክልል ከተሞች በማስፋትና ስራዎችን በመስራት የኢትዮጵያን የቱሪስት ፍሰት ማሳደግና እውነተኛ ብልፅግናን ማየት እንደሚቻልም አረጋግጠዋል። በቻይና መንግስት ሙሉ ወጪ እየተከናወነ ላለው ይህ ፕሮጀክት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የቻይናን መንግስት እና በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲን አመስግነዋል። ፕሮጀክቱ በሁለት ምዕራፎች የሚከናወን ሲሆን በመጀመሪያው ምዕራፍ 32 ሄክታር ጠቅላላ ስፋት ያለው የማዕከላዊ ፓርክ ግንባታ እና አንድ ነጥብ ሁለት ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራን በ2020 እኤአ አጋማሽ ለማጠናቀቅ ውጥን ተይዞ እየተሰራ ነው።ሁለተኛው ምዕራፍ ቀሪውን 16 ሄክታር ማዕከላዊ ፓርክ እና 10 ነጥብ ስምንት ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻ ልማትን የሚያጠቃልል ሲሆን በውስጡ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሙዚየም፣ የልጆች መጫወቻዎች እና ኪነጥበባዊ የአትክልት ስፍራዎች ይኖሩታል፤ በ2021 እኤአ ይጠናቀቃል ተብሎም ይጠበቃል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወንዝ ዳርቻና አረንጓዴ ልማት አስተዳደር ኤጀንሲ የፕሮጀክቱ ባለቤት ሲሆን ሲሲሲሲ ፈርስት ሀይዌይ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የተባለው የቻይና ድርጅት ደግሞ ግንባታውን እያከናወነ የሚገኝ ተቋራጭ ነው። በጉብኝቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ታን ጂያን ተገኝተዋል።አዲስ ዘመንታህሳስ 23/2012  በድልነሳ ምንውየለት", "passage_id": "35b9d81cb3a7da42d9e433e898cc6332" } ]
15bbe34e97927377b646d5f183751009
f9449b088f1a08d6bf35cd59620085c8
ቡናን ያለዛፍ ጥላ – በቀርጫንሼ ደበቃ
አስቴር ኤልያስስፍራው ሞቃታማ ቢሆንም ቅጥር ጊቢው ግን በቡና ችግኞችና በተለያዩ የፍራፍሬ ዛፎች በመሙላቱ ለአይን አርንጓዴነቱ ደምቆ፤ ለአፍንጫ ደግሞ መልካም መዓዛው ዘልቆ ስለሚመጣ ለጎብኚው ማየትም መማግም ግዴታ ሳይሆን በውዴታ የሚያጣጥመው ነገር ነው። ወዲህ ለቡና ተክሉ የተስተካከለ ውሃ ይደርሰው ዘንድ አዲስ የሆነና የውሃው ልክ በኮምፒውተር የሚታዘዝበት ቴክኖሎጂ ያለበት አንድ ክፍል ይታያል፤ ወዲያ ደግሞ ወደ 750 ሜትር ኪዩብ ውሃ የሚይዝ የውሃው ሪዘርቫይር ይስተዋላል ፤ ቦታው በምዕራብ ጉጂ ዞን አባያ ወረዳ ልዩ ስሙ ደበቃ እርሻ ልማት ነው። የቀርጫንሼ እርሻዎች አስተባባሪ ስራ አስኪያጅ አቶ ደጀኔ ዳባ እንደሚሉት፤ በቀርንጫንሼ ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ቀደም ሲል ጥራቱን የጠበቀ ቡና ወደ ውጭ አገር በመላክ ለአገሪቱ የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት ረገድ በግንባር ቀደምትነት እየሰራ ነው። ከንግዱ በተጨማሪ ከቅርብ ጊዜ ወደዚህ ጎን ለጎን በቡና እርሻ ልማት ተሰማርቷል። ድርጅቱ፣ በዓለማችን ላይ ዘመናዊ የሆነ በቡና ማምረት ቴክኖሎጂ ጫፍ ከደረሱ እንደብራዚል ካሉት አገራት ባልተናነሰ ዘመናዊ ቴክሎጂን ወይም ዲሪፕ እሪጌሽንን በመጠቀም ወደቡና ልማት እርሻ የገባ ነው። የቡና እርሻው የሚገኘው በምዕራብ ጉጂ ዞን አባያ ወረዳ ልዩ ስሙ ደበቃ እርሻ ልማት ሲሆን፣ያረፈው ደግሞ በ72 ሄክታር መሬት ላይ ነው። በዚህም ላይ 110 ሺህ የቡና ችግኞችን በመተክል ወደ ስራ መግባታቸውን ጠቅሰው፤ በቀጣይም በአንድ ሄክታር ላይ ዘመናዊ የቡና ማፍያ የችግኝ ጣቢያ ወይም ዲጂታል ስፕሪንግ ክለር እሪጌሽ በመጠቀም 600 ሺህ ችግኞችን በማፍላት ለአካባቢው ህብረተሰብም ጭምር ለማደል ወደ ስራ መግባታቸውን ይናገራሉ። ቀደም ሲል በአገራችን ያለው አስተሳሰብ ቡናን ያለጥላ ዛፍ ማልማት አይቻልም የሚል ኋላ ቀር አስተሳሰብ ሲሆን፣ ይህን አስተሳሰብ በአዲስ አስተሳሰብ ለመቀየር እየሰራን ነው ሲሉ ያስረዳሉ። በድርጅቱ አግሮኖሚስት ሆነው የሚሰሩት የሆርቲካልቸር ባለሙያው አቶ ጉተማ ጎቤ በበኩላቸው፤ በድሪፕ እሪጌሽን (ጠብታ መስኖ) በአንድ አይነት መልኩ ውሃ ለቡናው እንዴት ሆኖ ይሰራጫል የሚለውን እንደሚከታተሉ ይናገራሉ። ውሃው ለችግኙ ሲደርሰው ለእያዳንዱ ቡና እኩል የሆነ የውሃ መጠን ነው በሜትር ኪዩብ የተለቀቀው ውሃ ወደ ቡናው ሲሄድ የሚደርሰው በሚሊ ሊትር ተቀይሮ መሆኑን ይጠቅሳሉ። ይህ ቴክኖሎጂ የነበረውን ተልምዷዊ አሰራር ያለዛፍ ቡና መብቀል አይችልም የሚል አስተሳሰብን የሰበረ ነው። ቀደም ሲል ዛፍ ያስፈልግ የነበረው ብዙ ውሃ ስለማይጠጣ የዛፍ ጥላው ያለውን ውሃ እርጥበቱን ጠብቆ እንዲሄድ ስለሚያርገው ነው ይላሉ። አጠቃላይ የቀርጫንሼ ካምፓኒ ስራ አስፈጻሚ አቶ እስራኤል ደገፋ፣ ካምፓኒው የሚሰራው አጠቃላይ የአገራችን ኢኮኖሚ በሚፈልግበት በግብርናና ማኑፋክቸሪንግ ላይ መሆኑን ይገልጻሉ። በግብርናው ላይ ወደ 26 ሺህ የስራ እድሎችን በመፍጠር እንዲሁም ከ56 ሺህ አርሶ አደሮች ጋር የገበያ ትስስር በመፍጠር የሚሰራ ድርጅት እንደሆነም ያመለክታሉ። አቶ እስራኤል እንደሚሉት፤ ላለፉት አራት አምስት ዓመታት ትልቁን የአገሪቱን የቡና ኤክስፖርት ከሁለት አኃዝ በላይ ድርሻ በመውሰድ የሚልከው ይኸው የቀርጫንሼ ኩባንያ ነው። በየትኛውም የኢትዮጵያ ቡና አብቃይ ክልሎችም ሆነ ወረዳዎች ይገኛል። አጠቃላይ ወደ 57 ኢንዱስትሪዎች እንዲሁም ደግሞ ወደ አምስት እርሻዎችን በቡናው ሴክተር ላይ ማኔጅ ያደርጋል። ጉብኝት የተደረገበት የደበቃ እርሻ ጣቢያ፣ ኩባንያው ካሉት እርሻዎች ሁሉ አነስተኛው ነው ያሉት አቶ እስራኤል፣ ነገር ግን እንዴት አድርገን ግብርናን ከተለምዶ አሰራራችን መቀየር አለብን ሲሉ በማሰብ በቡናው ፋርም ትልቅ ደረጃ ላይ የደረሱ አገሮችን ተሞክሮ ከእነእስራኤልና ብራዚል መውሰድ ላይ መሆናቸውን ያመለክታሉ። የወሰዱትም ቴክኖሎጂ ድሪፕ ኢሪጌሽን ሲሆን፣ በአሁኑ ሰዓት በዓለም ላይ የመጨረሻው የሚባለው በግብርናው ዘርፍ የተገኘና ውጤታማ የሆነ የመስኖ ሲስተም ነው ይላሉ። ከዚህ አንጻር በደበቃ ያለው የተሻለው ቴክኖሎጂ  እንደሚያሰኘው ያስረዳሉ። አርሶአደሩ በተለምዶ በሄክታር ቡና የሚያገኘው ከስድስት ኩንታል የዘለለ አይደለም የሚሉት አቶ እስራኤል፣ እኛ በዚህ ቴክኖሎጂ ተጠቅመን ግን በሄክታር እስከ 35 ኩንታል ማሳካት ችለናል ብለዋል። ይህ ሙከራ ደግሞ የመጀመሪያው ሲሆን፣ የሚጠበቀው በሄክታር እስከ 65 ኩንታል ድረስ ነው ብለን እየሰራን ነው ሲሉ ተናግረዋል። ያንን ማሳካት ከቻልን የአገራችንን የውጭ ምንዛሬ ማሳደግ እንዲሁም የአርሶ አደሮችን ገቢ ከፍ ማድረግ ይቻላል ብለዋል። የእኛ ትልቁ እቅዳችን የራሳችን ማሳ ላይ ትልቁን ምርት ማምረት ላይ ብቻ አይደለም። በአቅራቢያው የሚገኙ የአርሶ አደሮችንም ማሳዎች ወደእኛ ቴክኖሎጂ በመቀየር እነርሱም ተጠቃሚ የሚሆኑበትን መሰረት ማደላደልና በፋይናንስም ለመደጎም ሲሆን፣ ይህን ተግባራዊ ለማድረግ ዲዛይን አድርገን ጨርሰናል ይላሉ። በዕለቱ ቀርጫንሼ ትሬዲግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ኤክስፖርት ስታንዳርድ የቡና ላቦራቶሪን የመረቁት የግብርና ግብአትና ግብይት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ አይናለም ንጉሴ እና የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበላ ሲሆኑ፣ ሚኒስትር ዴኤታዋ በዕለቱ እንደተናገሩት፤ የድርጅቱን የቡና ማዘጋጃ መጋዘንና የቡና መቅመሻ ላቦራቶሪ እንዲሁም እርሻዎቹን ጎብኝተናል። ከዚህ ደርጅት ባለቤት ጋር አርሶ አደሮችም አብረው ነው ያሉት። ለምርት መሻሻል ደግሞ ዋናው አርሶ አደሮቻችን ከባህላዊ የቡና አመራረት ዘዴ በመጠኑም ቢሆን በመቀየር የቡናን ምርታማነት ሊቀየሩ የሚችሉ አሰራሮችን ተግባራ እያደረጉ ነው ያሉት። ቡሌ ሆራ ላይ እንደማየውና ሞዴል አርሶአደሮችም እንዳረጋገጡልን በምርትም፣በአቅርቦትም ሆነ በገበያ ትስሰርም የተሻለ እድል ያለበት አካባቢ መሆኑን ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፣ እዚህ የሚሰሩ ባለሀብቶች የአርሶአደሩንም ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ስለመሆናቸው ማስተዋል መቻላቸውን ይናገራሉ። እርሳቸው እንደሚናገሩት፤ እንደግብርና ሚኒስቴር የበለጠ ምርትና ምርታማነትን ሊያሳድግ የሚችል ስራ ይሰራሉ። ቡና ወደውጭ በመላክ ረገድ በተለይ ቀርጫንሼ ላለፉት ሁለትና ሶስት ዓመታት የቀዳሚነት ድርሻውን እየተወጣ ነው። በመጋዘን ውስጥ የተመለከትነውም ደረጃውን የማያስለቅቅ ለአገርም ኢኮኖሚ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሊያደርግ የሚችል ክምችት የያዘ ቡና መኖሩን ነው፤ ለዚህም በጣም ደስተኞች ነን። አርሶአደሮቹ ጥሩ የቴክኖሎጂ ስራ ካላቸው ከግል ሴአልሚዎች ጋር በመቀናጀት ምርታቸውን እንዲያሳድጉ ለማድረግ የሚያስችል የአሰራር ማዕቀፍ መዘርጋት ነው። የተሻለ ገበያ እንዲያገኝ ከማድረግ አኳያ የተዘረጉ አሰራሮች አሉ፤ ትልቁ ነገር አርሶ አደሩ ያመረተውን ምርት ቀጥታ ወደ ገበያ ለማድረስ የሚያስችለው አቅም ገበያ የማፈላለግ ችሎታ የማዳበር ስራ መሰራት ይኖርበታል። እንዲህ ከሆነ በለፋው ልክ ጥቅም እንዲያገኝ ያችለዋልና በዚህ ደረጃ እንቅስቃሴዎች ተጀምረዋል ብለዋል። ዶክተር አዱኛ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ ባለስልጣኑ ቡና ከማብቀል ጀምሮ ውጭ አገር እስከ መላክ ድረስ ያለውን ሂደት በማገዝ እንዲሁም ገበያ በማፈላለግ ረገድ በመስራት ላይ ይገኛል። አርሶ አደሮቻችን እስከ ውጭ አገር በራሳቸው እንዲልኩ ይሰራል። 500 ያህል አርሶ አደሮች ወደውጭ አገር መላክ የሚያስችላቸውን ሰነድ አውጥተዋል። በዚህም እየሄዱበት ነው። ቀርጫንሼ የሰራው ስራ በአርአያነት መጠቀስ የሚያስችል ስራ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፣ በቦታው ተገኝተን ያስተዋልነው ነገር ቢኖር ይህን ነው ብለዋል። ይህም ወደሌሎቹም መስፋፋት ያለበት ቴክኖሎጂ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህ ስራው ደግሞ እንደ መንግስት ድጋፍ እናደርግለታለን ብለዋል።አዲስ ዘመን ጥር 10/2013 ዓ.ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=39687
[ { "passage": "ዲስ ላይ ኑሮ ተወዷል፤ ሸገር ላይ ህይወት ከብዷል። መዲናችን ለኔ ቢጤ ድሃ ጥሩን ለብሶ ማጌጥ ድንቁ፤ እህል ጎርሶ ማደር ብርቁ ሆኗል። ወገን በወገን ላይ ጨክኗል። ነጋዴው ደንበኛው (ሸማቹ) እንጀራው መሆኑን ረስቶ ዛሬ ኪስህን ካላጠብኩ እንቅልፍም አይወስደኝ፤ ተኝቼም አላድር ብሏል። ከገበሬው 1 ሺህ 500 ብር የገዛው ጤፍ ከተማ አምጥቶ ከ3,500 ብር ፍንክች አልልም ይላል። “ምነው ወዳጄ! ይሄ ደግም አይደል እንተዛዘን እንጂ ይሄን ያህል መጨካከን ተገቢ ነው?” ስትለው “ዶላር ጨምሮ ነው። ምን እናድርግ?” ይልሃል። ጤፉን በውጭ ምንዛሬ ከሩቅ ምስራቅ አስጭኖ ያስመጣው ይመስል። ነጋዴው ሸምሱ ከወይዘሮ ጫልቱ በ100 ብር የገዛው ቅቤ በ300 ብር መሸጡ ከዶላር መጨመር ጋር ምን አገናኘው? በሞቴ እስቲ አስረዱኝ። ነጋዴዎች ኧረ ተዉ! ወዴት እንሄድባችዋለን? ቀስ እያላችሁ ብትነጥቁን አይሻልም? ከበረገግን እኮ ለእናንተም መጥፎ ነው። የኛ ገቢ አድሮም ውሎም መድረሻው ወደ እናንተው ነው፤ ምን መሄጃ አለው ? ቆዩማ! እጀራችሁ እኛ መሆናችንን እየዘነጋ ችሁ ይሆን እንዴ? እኛ ከሌለን እናንተስ በምን ታድራላችሁ? ሰው እንጀራውን ይገፋል? እንጀ ራው ላይ ይጨክናል? ጭካኔያችሁ ደግሞ መክ ፋቱ ደግማችሁ እንዳትደርሱብኝ የማለትን ያህል “ስንት ነው?” ብለን ስጠይቅ ለመቁጠር ቀርቶ ለመጥራት የሚከብድ የገንዘብ መጠን መንገራችሁ አያስተዛዝበንም? ለኛ ባታዝኑ ለወገን ባትራሩ እንኳን ይሄ ለኛ ብረቅ የሆነው ገንዘብ እንዴት ነው የናቃችሁት? ቢያንስ ያስከበራችሁ ያህል ክብር ሰጥታችሁት አብሮዋችሁ እንዲቆይ ብታደርጉ አይሻልም? ገንዘብ አንዴ ካኮረፈ አኮረፈ ነው እንደኛ መሄጃ ያጣ አይደለም ጥሎዋችሁ እብስ ይላል። ንገሩኝማ ውድ ነጋዴዎች የወገንስ ኪስ ማጠብ፤ ያለአግባብ በትርፍ ላይ ትርፍ መሰብሰብ እንደው ደስታን ያጎናፅፍ ይሆን? እኔ አይመስለኝም። እውነተኛ ደስታ የራስን አሳልፎ ከመስጠት ጋር የሚያያዝ በመቸር የሚገኝ ልዩ ጉዳይ ነው። ይህ በድርሰት አለም ውስጥ የሚሰበክ አይደለም እውን ነው። እውነተኛ ደስታ በውስጣችን ለመፍጠር ቀድመን ማስደሰትን እንወቅ። እናም ነጋዴዎች ለወገን ማሰብ መልካም ነው፤ እንተሳሰብ። የደንበኛዬን እድሜ ያቆይልኝ ገቢውንም ያሳድግልኝ እያላችሁ ፀሎት አድርጉ እሱ ነው የሚያዋጣችሁ። የኔ ቢጤ ለፍቶ አዳሪዎች\nበነጋዴዎች የተፈጠረብን ጫና እያንገዳገደን ነው። እንደኔ አይነቱማ ብቻ መኖሩ አልቻል ሲለው አጋር ፍለጋ መባዘን ጀምሯል። ኣኣ..አጋር ያልኩት ትዳርን አይደለም ወዳጆቼ እሱማ አከራዮች ማቀብ ጥለዋል! መባሉን ሰምቶ የማግባት ሀሳቡን ተከራይ ሰርዟል። አከራዮች ለባለ ትዳር አናከራይም ለላጤ እንጂ ብለዋል አሉ። ጉድ ነው ላጤ አድርገው ሊያስቀሩን እኮ ነው። እናም የማወራው\nከትዳር ውጪ የሆነ ደባልነትን ነው። እናላችሁ እኔና የኔ ቢጤው የኑሩን ዳገት ለብቻ አልገፋ ቢለው አብሮ የሚያጋፋው መላ በመዘየድ ላይ ነው። እኔም ከሌሎች ጋር አብሮ በመሆን ኑሮን ለማሸነፍ አሰብኩ። መኖር ቢያቅተኝ\nጓደኞቼን ጠራው ለመመካከር፤ እንደው ምን ይሻል ይሆን ብሎ ስለ መፍትሄው ለማውራት። እነሱም እንደኔው ከጫፍ ደርሰው ነበርና “ባንድ አፍ!” አሉኝ። ሀሳቤን ቅዱስ ብለው ተቀበሉት። እናም ኑሮው ትንሽ ቢቀለን\nብለን አንድ ላይ በመኖር ወጪም ለመጋራት ተስማማን። አራት ባራት በሆነች አንድ ክፍል ቤት ውስጥ ለመኖር። አራት ነን በአንድ ቤት የምንኖር፤ አንድ ክፍል የምንጋራ፤ መሆን ሳንፈልግ የኑሮ መወደድ ያቆራኘን፤ ነፃነታችንን ማወጅ እየፈለግን ችግር ያዋደደን ጓደኛሞች። አስማተኛ\nሆነን ምናዘግምባት አዲስ አበባ (የምናወጣው ወጪ ገቢያችንን ስለሚበልጥ አመጣጡ እንዲሁ ግርም ስለሚለኝ ነው)፣ ኑሮን ማየት እንጂ ማኖር በማትፈቅደው በዚህች ጉደኛ ከተማ አዲስ አበባ (ለደሃ ማለቴ ነው) አንዱን በጠኔ ክርችም ሌላውን በተቃራኒው በቁንጣን በምታጨናንቀው አዲስ አበባ እንኖራለን ኣኣ…ተሳሳትኩ እንኖራለን ነው ያልኩት ማለቴ እናኗኑራለን። ሰሞኑን\nብርድም አይደል? ሲበርደን አንድ ሀሳብ መጣልንና ጃኬት ለመግዛት ተስማማን። አንድ ጃኬት ለአራት ነው። እንግዲህ ለመግዛት ያሰብነው። አንድ ጃኬት ለአራት በተራ ለመልበስ። በአንድ ጃኬት በተራ ለአራት ለማጌጥ። አራታችንም በጃኬቱ መገዛት ላይ ድምፅ ለመስጠት ተሰባሰብን በሙሉ ድምጽ ጸደቀና በመዋጮ ተገዛ። በነገራችን\nላይ የኛ ቤት ይለያል። አንድ ሰው ቢጎልም ምላዕተ ጉባዔው ስለተሟላ ስብሰባው ይደረግ ወይም ድምፅ ይሰጥ የሚለው ፍልስፍና እኛ ቤት አይሰራም። ምክንያቱም የጎደለው ሰው ሙሉ የቤቱ አባል ካልተሟላ ምንም ርእስ ተነስቶ ውይይት አይደረግበትም። ምክንያቱ ብዙውን ጊዜ የምንወያየው በመዋጮ ጉዳይ ስለሆነ ስብሰባው ላይ ያልተገኘው አላዋጣም እንዳይለን በመስጋት ነው። እኔ ነኝ ጃኬቱ እንዲገዛ\nሀሳብ ያቀረብኩ። ምክንያት ስጠየቅ አንድም ብርድ ነው በሚል ሁለትም አብሮን በተማረ የሌላ መስሪያ ቤት ሰራተኛ (ጥሩ ደመወዝ የሚከፈልበት መስሪያ ቤት የሚሰራን ሰው ጠቅሼ) ተለብሶ ማየቴን እንዳማረበትና እኛም በዙር ቢያምርብን ብዬ መሆኑን አስረዳሁ። “አዎ እኛ ከሱ በምን እናንሳለን\nአራት ሆነን መግዛት እንዴት ያቅተናል።” በሚል ፉከራ ይገዛ ተባለ። “አዎ በእርግጥ በደመወዝ እንጂ በጋራና በፍቅር በመኖርም እኛ የተሻልን ነን” አንዱ ጓደኛችን የጃኬቱ መገዛት እርግጥ እንዲሆን ለማፅናት በዛቻ መሰል መልክ ያሰማው ፉከራ ነበር። በዚህ እልህ የተገዛው\nጃኬት ለመልበስ እጣ ወጣና ለገረመው ደረሰው። በመዋጮ ለአራት የተገዛው ጃኬት የመጀመሪያ ሳምንት የገረመው ማጌጫ ሊሆን በቃ። ድምጽ የሚከበርበት ቤት ነውና ጸደቀለት። አይናችን እያቁለጨለጭን ፈቀድንለት። ኦ በነገራችን ላይ ይቅረታ ጓደኞቼን (ደባሎቼን) ሳላስተዋውቃችሁ። የኛ ቤት ልዩ ነገር የሁላችንም ስምና ባህሪ መመሳሰሉ ነው፤ ካንዱ በቀር። ጓደኞቼ ስማቸውና ባህሪያቸው በትንሹ ልንገራችሁ። ዜና፡- ቤታችንን\nበመረጃ ሙሉ የሚያ ደርግልን ጓደኛችን ነው። እኛ ቤት የመረጃ ችግር የለም። ዜና ባይኖር ከመረጃ ርቀን ቀርተን ነበር። ሬድዮ የለን፤ ቴሌቪዥን የለን። እናም ዜና መረጃዎችን እያነፈነፈ እንደ ጉድ ያዘንብልናል። ችግሩ ዜናዎቹ አብዛኛውን ጊዜ ሲግናላቸው በተበላሸ ሳተላይት ቲቪ እና ጣቢያቸው ባልተሰናሰለ ሬድዮ እየሰማ ነው መሰለኝ የተሟላ መረጃ አይነግረንም። ብዙው ዜና ጀምሮ ይተወዋል። ለነገሩ እኛም አሟላ ብለን አናስጨንቀውም። ባልተሟላ ኑሮ የተሟላ መረጃ ምን ያደርጋል። ገረመው፡-\nአቤት ነገሮች ሁሉ የሚገርሙት ሰው፤ ገረመው መገረም ዋንኛ ስራው ነው። በአንደኛው ጓደኛችን የሺጥላ የሺጥላ ተብሎ እራሱን እንኳን ማስጠለል ተስኖት ከኛ ጋር ተጠግቶ መኖሩ ያስገርመዋል፤ በእኛ ደህነትና በቢል ጌት ሀብታም መሆን ይደነቃል፤ በኤሊ መንቀርፈፍና በዩዜን ቦልት ፍጥነት ሲደነቅ፤ በጨርቆስና በቦሌ ልጆች የኑሮ ልዩነት ሲመሰጥ ብዙ ጊዜውን ይፈጃል። እኛም እየተመለከትነው ባለነው የገረመው መገረም ይገርመናል። አንዳንዴ ሳስበው ገረመው ለመገረም የተፈጠረ ሁሉ ይመስለኛል፤ ተገራሚው ገረመው። የሺ ጥላ ምስኪን\nራሱን የማይችለውን ሰው የሺ ሰው ጥላ አሉት። እኔም እንደገረመው በየሺ ጥላ በጣም እገረምበታለሁ። አራት ወራት በጋራ ስንኖር አንድ ቀን ምግብ የማብሰል ተግባር ብቻውን ተወጥቶ አያውቅም። አድርግ የተባለውን ሁሉ ገረመው እስኪገርመው ድረስ አልችልም ብሎ ያልፋቸዋል። ለነገሩ እሱ ምን ያድርግ ቤተሰቦቹ ናቸው የማይችለውን ያሸከሙት። እኔን ጓደኞቼ በሰኔ ይሉኛል፤ ሰኔን አልወደውም፣ ደጋግሞ ሰኔ ላይ መጥፎ ገጠመኝ ስለገጠመኝ ሰኔን እጠላለው። ከ13ቱ ወራት ሰኔን ቀንሰው አኔን ከመሳቀቅ ቢታደጉኝ እላለው። ምንም ነገር በሰኔ ቢጠይቁኝ እለፉኝ ባይ ነኝ። ጓደኞቼም በሰኔ ያሉኝ ለዚያም ነው። በቃ እኔ እና ሰኔ እንዲህ ነን፤ የተወለድኩት በሰኔ ነው። ምን አልባትም እንትን የምለው በሰኔ ይመስለኛል። እንትን ያልኩት አስፈሪ ቃል ሰኔ ላይ ማውራት ስለማልወድ ይቅርታ እለፉኝ ሰኔ ባይሆን ኖሮ አወራችሁ ነበር። ለዛሬ ይብቃኝ ሰላማቹሁ ይብዛልኝ።አዲስ ዘመን ሰኔ 21/2011 ", "passage_id": "c64f4c4228d89f5e45ae65bc72daa601" }, { "passage": "“በተደጋጋሚ ወተት የምወስደው ከአንድ ሰው ቤት ነው። እንደልማዴ አንድ ቀን ጠዋት ሁለት ሊትር ወተት ወስጄ፤ አንዱን ሊትር ለራሴ ሌላውን ደግሞ ነፍሰጡር ለሆነች ጎረቤቴ ሰጠሁ። ከቆይታ በኋላ ግን የተፈጠረው ነገር ምነው እጄን በሰበረው ያሰኘ ነበር። ወተቱን የጠጡት ልጆቼ ባጋጠማቸው የጤና ችግር ታመው ለሆስፒታል በቁ ፤ ልጆቼን አሳክሜ ከመጣሁ በኋላ በፍጥነት ያመራሁት ወተቱን ወደ ሰጠኋት ጎረቤቴ ነው። እሷም ’ወደላይ ወደታች‘ ሲላት ውላ በመጨረሻ ህክምና ተቋም በመሄድ የተወሰነ እፎይታ ማግኘቷን ነገረችኝ። እኔም ያጋጠመኝን ነግሬያት ያመራሁት ወተት ወደምገዛበት ቤት ነበር። በንዴትና በደምፍላት ’ምን አይነት ወተት ነው የሰጠሽኝ?‘ ስል ጠየቅኳት። ጥያቄዬ ምንም አልመሰላትም ‘እኔም ሁልጊዜ ከማመጣበት አምጥቼ ነው ያከፋፈልኩት‘ የሚል ነበር መልሷ። ያጋጠመኝን ችግር ነገርኳት ‘ ከአንቺ በቀር ሌላ ሰው በእዚህ መልኩ የመጣ የለም ’ ስትል ከደሙ ንጹህ መሆኗን ለራሷ መሰከረች…” እኔም ምንም ሳልመልስላት ወጣሁ፡፡ ጠዋት ይህንኑ ወተት ላመጣ ስወጣ የሰማሁት ለቅሶ ሰለነበር ልደርስ ሄድኩኝ። ያው እንደምታውቁት ለቅሶ ቤት ከማስተዛዘን ባሻገር ትላልቅ ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም ፖለቲካዊ ጉዳዮች የሚነገሩበት መድረክም አይደል! እኔም የገጠመኝን ለገበያ አዋልኩት፡፡ ኧረ ጉድ እኮ ነው ምን ያልሆንነው ነገር አለ! ጨዋታ በዚህ በተጀመረው አጀንዳ ሞቅ ብሎ ቀጠለ ፤ ቤቱ\nሰዎች ሀዘንተኞችን ለማስተዛዘን የተሰባሰቡበት ነበርና ከወ ዲያ ከወዲህ ሀሳቦች መውጣታቸው ለጨ ዋታው ድምቀት ሆኗል። አንደኛው ከወዲህ ጥግ “በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ከጀሶ ጋር የተቀላቀለው እንጀራ እና ስምንት በርሜል ሊጥ ለኤግዚቢት ተይዞ በወረዳው ጽህፈት ቤት አይተናዋል። ይሄንንም ድርጊት ሲፈጽሙ ነበር የተባሉት 3 ግለሰቦችም በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአካባቢው ህብረተሰብ አይቷል ፤ ታዝቧል። ይሄ የህግ አካላት እርምጃ እና ቅጣት ግን ከሳምንት በላይ የዘለለ አልነበረም ማለት ይቻላል። ድርጊቱን ፈጽመዋል የተባሉት ግለሰቦችም የቅጣት ዜና ሳይሆን የመለ ቀቃቸው ዜና ሳምንት ባልሞላው ጊዜ እውን ሆነ። ፍትህ የት ነህ ልበል? ወይስ …” ሌላኛው ከወዲያኛው ጥግ “የሚገርም እኮ ነው! በቀደም ዕለት አንድ የህጻናት አልሚ ምግብ የሚያስመጣ ድርጅት እንዲሁ ባዕድ ነገር በመቀላቀል መያዙን ሰምቻለው፤ በፍራቻ እና በስጋት ቦዝዞ….” እንዲያ በደራው ጨዋታው መሀል እኔም ባልደረባዬ የነገረችኝ ትዝ አለኝ። “ከአገር ውስጥ አልፎ ተርፎም የጀሶ እንጀራ አሜሪካ ገባ “ ስትለኝ ማመኑ ቢከብደኝ እንኳን አይሆንም ብሎ ለመሟገት ድፍረቱ አልነበረኝም። ምክን ያቱም ወንጀሉን የሚሰሩት፣ የሚያ ቀናባብሩት፣ የሚያሰራጩት የእኛው እህትና ወንድም አይደሉም። ባህር ማዶ ይሄንን አይልኩም ብሎ ለማለት ምን ይከብዳል ። ደግሞ እኮ “ ነጋዴ” ብር ያግኝ እንጂ አይን የለውም፤ ገንዘብ እንጂ ሰብአዊነት አልፈ ጠረበት ለማለት አሰብኩና ደግሞ እነዛን ንጹህ ነጋዴዎች አስቤ ከአንደበቴ ቆጠብ አልኩ ። ልጽፈው ግን ግድ ሆነ። መረጃ እንደ መረጃ ማገልገሉ ያው ከጉዳት ማዳኑ አይቀርማ። ከተዳፈርኩ ይቅር በሉኝ! እንዲያ በደራው ጨዋታው መሀል እኔም ባልደረባዬ የነገረችኝ ትዝ አለኝ። “ከአገር ውስጥ አልፎ ተርፎም የጀሶ እንጀራ አሜሪካ ገባ “ ስትለኝ ማመኑ ቢከብደኝ እንኳን አይሆንም ብሎ ለመሟገት ድፍረቱ አልነበረኝም። ምክን ያቱም ወንጀሉን የሚሰሩት፣ የሚያ ቀናባብሩት፣ የሚያሰራጩት የእኛው እህትና ወንድም አይደሉም። ባህር ማዶ ይሄንን አይልኩም ብሎ ለማለት ምን ይከብዳል ። ደግሞ እኮ “ ነጋዴ” ብር ያግኝ እንጂ አይን የለውም፤ ገንዘብ እንጂ ሰብአዊነት አልፈ ጠረበት ለማለት አሰብኩና ደግሞ እነዛን ንጹህ ነጋዴዎች አስቤ ከአንደበቴ ቆጠብ አልኩ ። ልጽፈው ግን ግድ ሆነ። መረጃ እንደ መረጃ ማገልገሉ ያው ከጉዳት ማዳኑ አይቀርማ። ከተዳፈርኩ ይቅር በሉኝ! ለወንጀለኛ ከዚህ ተመለስ ማለት እኮ አይቻልም። የትም መድረስ ይችላል። በማንም ላይ ምንም ነገር ማሰብና መስ ራትም ይችላል። ሁሉም በእነሱ እጅና በእነሱ አእምሮ የሚታሰብ አይደል? በቃ የሚፈለገው ገንዘብ ብቻ ነው። ግን ግን ገንዘብ ህሊና ይሆናል? ማለቴ ከምንም በላይ እኮ ህሊና የሚባለው ይሄ ሰዎችን የሚጎዳ ህጻናትን የሚገድል የእድሜ ልክ በሽተኛ የሚያደርግ ስራ ሰርቶ ገንዘብ አግኝቶ ጥሩ ኑሮ እየኖርኩ ነው ማለት ይቻላል? አይቻልም! እንዳልል እማ ተችሎ አየነው አይደል ? ይሄ ነው እንግዲህ ለዜጋው የማያስብ የንግድ ህብረተሰብ፣ የእሱ ተባባሪ። እንዳው በንዴት ብዙ ክፉ ክፉ ነገር ወጣኝ እንዴ? ህጋዊውን ፣ለወገንና ለአገሩ የሚቆረቆረውን የንግድ ህብረተሰብ ማለቴ እንዳልሆነ ይያዝልኝ! እነሱን ስማቸው ያስከብራቸዋል፤ እጃቸው ያሸልማቸዋል፤ ያሾማቸዋል። ለምን ብትሉ የሁሉም ነገር ፈራጁ ስራ ነዋ። በሀቅ መስራት በታማኝነት ማገልገል የልፋት ውጤት የሆነውን ሀብት ብቻ ሳይሆን ስም፣ ዝና ሁሉ ያስከትላል። ስም ደግሞ ከመቃብርም በላይ ነው። ምን ያልሆንነው ነገር አለ ? ያለው አንድ የህግ ምሁር ለፅሁፌ ርዕስ መነሻ ሆነኝ እና እኔም ምን ያልሆነው ነገር አለ! ብዬ ይሄን አልኩ። እውነት እኮ ነው ምን ያልሆነው ነገር አለ። እንጀራን ከጀሶ፣ እንጀራን ከሰጋቱራ ተቀየጠ ምግብ ሆኖ በላነው ፤ወተት ከሳሙና አረፋ ተቀየጠ ጠጣነው፣ ቅቤ ከሙዝ፣ ከድንች፣ ከረጋ ዘይት፣ ከውሀ ተቀላቅሎ ተከሸነ ሸመትነው፤ በርበሬ ከሸክላ አፈር ፣ ከቀይ\nስር ተቀየጠ በተመሳሳይ ጥቅም ላይ አዋልነው፤ … ሌላም ሌላም ባዕድ ነገሮች ተቀይጠው ወደ ገበያ ገቡ ሸመትናቸው። ግን እኮ ይሄ ሁሉ ሰው ወገቤን፣ እግ ሬን፣ ጨጓራዬን… የሚለው ምናልባት የእነዚህ የባዕድ ነገሮች ቅይጥ የረጅም ጊዜ ውጤት ይሆን? መጠርጠር ደግ ነገር ነው ብዬ ነው ፡፡ይህን ማለቴ እውነቱን ግን የሚያውቀው የደረሰበት ብቻ ነው። አሁን ደግሞ ከውስኪ ጋር የተቀየጠ አደገኛ ነገር መያዙን እንዲሁ ከጨዋታው መሀል ወደ ጆሮዬ ገባ፤ ይሄ ግን ብዙም የተጫዋቹን ቀልብ የገዛ አልነበ ረም፤ “እስከዛሬው በደሀው ወገን ላይ ነበር፤ አሁን ወደ ሀብታሙም ሊዘመት ነው“ ከሚል ያለፈ አልነበረም። ምንም ቢሆን ውስኪ የቅንጦት መጠጥ ነው ሊቀር ይችላል፤ ዳቦ እና እንጀራ ገዝቶ የሚበላው ግን ሌላ አማራጭ የለውም! ለእነዚሁ አረመኔ ነጋዴዎች ተላልፎ የተሰጠ ሚስኪኑ ነው የሚለው ጨዋታ ጎላ ብሎ ወጣ ። ውስኪ አቅራቢውም ሆነ ጠጪው ምን እንደሚሉ ባላውቅም ለረጅም ጊዜ ግን ”የተወጋ ውስኪ“ ገበያውን እንደያዘው መስማቴን አስታውሳለሁ። አሁን ግን ኧረ ውስኪ ጠጪዎች ከመወጋት ከፍ ያለ ችግር ውስኪም አረገዘች የሚለው ጥቆምታ ሊያነቃቸው ይገባል። አይደል? ሁሉም ወገን ነዋ! ነጋዴ ወገን አያውቅም፤ የነጋዴ ወገኑ ገንዘብ ብቻ ነው ብላችሁ ግን አትጠይቁኝ ንጹህ ነጋዴዎችን ማስቀየም ይሆንብኛል። ግን እስኪ አስቡት ማን ማንን ነው የሚያጠቃው ፤ በማን\nላይ ነው ሀብት የሚሰበስበው? ወንጀል ሰርቶስ ምን አይነት ህሊና ነው የሚኖረው ? ይሄንን ሰርቶ እንቅልፍ የሚተኛውስ ምን አይነት አእምሮ ቢኖረው ነው ? ብቻ ምላሹን ለአንባቢው ልተው። ይህን ሳነሳ ህጉስ? የፍትህ አካላትስ ምን እየሰሩ ናቸው ? የሚል ጠያቂ አይጠፋም። አዎ! አሁን ዲሞክራሲ ፣ነፃነት፣ ገለመሌ … እያልን የምናወራበት ነው። መጠየቅ የሚገባንን ብቻ ሳይሆን ማንሳት የሌለብንን ወይም ደግሞ አሁን ወቅቱ ያልሆነውን ጥያቄ የምናነሳበት ሰዓት አይደል? ። ጠያቂ\nትውልድም አፍርተናል ። ይሄንን ጥያቄ\nቢያነሳ ይገባል። ኧረ እንዳውም ተገቢ ነው። ከመስመሬ ወጣሁ መሰለኝ ልመለስ። አንዳንዱ ነጋዴ በፍጥነት ሀብታም መሆን በመሻት፣ በአቋራጭ ለመክበር የማይወጣው ዳገት፣ የማይፈነቅለው ድንጋይ አይኖርም። የፍትህ አካሉንም ሆነ የጸጥታ ሀይሉን ሲችል አጭበርብሮ ካልሆነም በእግሩ ሳይሆን በእጁ ብሎ የራሱ ያደርገዋል። ዓላማውን ቃልኪዳኑን ሁሉ ያስተወዋል። ስለዚህ በወገኑ ፣ በሀገሩ ላይ ምንም የከፋ ነገር አይሰራም ብሎ ማለት አይቻልም ፤ ምክያቱም ግቡ ሀገር ወገን አይደለም። ግቡ ገንዘብ ነው፤ ገንዘቡ ከተገኘ ሌላው የእሱ ጉዳዩ አይደለም። አሁን አሁን ተባብሰው አይነታቸውን አስፍተው የምናያቸው የወንጀል ድርጊቶች የሚያሳዩት ለገንዘብ ተብሎ ምንም ክፉ ነገር እንደሚሰራ ነው። ህጉም አስተማሪ ቀጪ ሳይሆን ልል፤ ፈፃሚና አስፈፃሚው በእዛው መስመር መጓዛቸው ችግሩን አገዘፈው መሰለኝ። እኔ እንዲህ ተሰማኝ የእናንተን ግን እንጃ! ።አዲስ ዘመን ሰኔ 9/2011 ", "passage_id": "5bd811f732d7652de74d11f465171f08" }, { "passage": "አከራዬ “ጤፍ ጨመረ፤ ኑሮ ተወደደ” ብለው የቤት ኪራይ ጨመሩብኝ።እኔ የተወደደውን ጤፍ የምበላ አይመስላቸውም መሰለኝ።አዎን! ከስቼ ሲያዩኝ ምግብ የተውኩ መስሉዋቸው ይሆናል።ኮስምኜ ሲመለከቱኝ የኑሮ ክብደት መለከያ ሚዛን መስያቸው ይሆናል።ለሳቸው የከበደው ኑሮ ለኔ የረከሰ ይመስላቸዋል መሰለኝ፤ ብቻ ኑሮ አጠውልጎኝ አንገቴን ሰብሬ ሲያዩኝ የኑሮ መወደድ ምክንያት እኔ መስያቸው ይሆን እንዴ ብዬ አስባለሁ።አከራዬ የኑሮን መወደድ በምን ሊያውቁት ይችላሉ።ምንያም ሱቅ ሄደው የ5 ብር ሻማ 6 ብር ሆነ ሲሏቸው የአራት ሺህ ቤታቸው “ከዛሬ ጀምሮ አምስት ሺህ ሆኗል፡፡” የሚሉት አከራዬ የኑሮ መወደድ ለሳቸው ጭማሪ እንጂ ኪሳራ እንዴት ሊሆን ይችላል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግልምጫቸው ሲጨምርብኝ አጎንብሼ “ሰላም ዋሉ?”\nስል ዝም በማለት ያልፉኝ የነበሩት አከራዬ ማልጎምጎም ሲጀምሩ ጭማሪ አስበው እደሆነ ሊገባኝ ይገባ ነበር።“ጨምሯል” የሚቀላቸው\nተጨምሮብዎታል የሚነዳቸው አከራዬ የሚቀላቸውን ነገር ሲተገብሩ እኔም የቀለለ ቤት ፍለጋ በረፍቴ ቀን ማልጄ ወጥቼ አምሽቼ መግባት\nአዘውትሬያለሁ።ከስራ ወጥቼ ሌላ ኑሮ የሚያቀልል ቤት፤ ለመቆየት የሚበቃ ማረፊያ ለማግኘት ስማስን ረፍት አጥቻለሁ። ውዶቼ የሰሞኑ ትርፍ ስራዬ ቤት መፈለግ ሆኗል።ይህ አጋጣሚ ብዙ\nደላሎች ለማወቅ አጋጣሚ ሆነኝና በአዲስ አበባ የተለያዩ መንደሮች ውስጥ ያሉ ቤት አከራዮች አመልና በተለያየ መልኩ ለኪራይ ያዘጋጁዋቸው\nቤታቸው በደላሎች አስጎብኚነት አዳረስኩ።ከውካዋ …..”ምንድ ነው?” ከውስጥ የአከራይ ቤተሰብ፤ “ተከራይ ይዤ መጥቻለሁ ክፈቱ….”\nከውጭ እኔን ይዘው ይዞሩ የነበሩት ደላሎች ተደጋጋሚ የቃላት ልውውጥ የመሰንበቻዬ ማጀቢያ ሙዚቃዎች ሆነውኝ ከረሙ። ቤት ለመከራየት ስዞር ስንቱን አከራይ ታዘብኩ! “ብቻህን ነህ?”\n“አዎን”፣ “ታመሻለህ?” “አይ” “ትቅማለህ? ታጨሳለህ?” “ኧረ ፈጥሞ”፤ “ብዙ ጓደኛ አለህ?” “አዎን …” የተለያዩ ጥያቄዎች\n፤ብዙ አዎን፤ አንዳንዱ ደግሞ አይ የሚያሰኙ ይጠይቃሉ አከራዮች።አዎን እና አይ አስከትላው እኔ።ብቻ ብዙ የማይገባ ጥያቄና አሰልቺ\nንግግር ይሰማል።ለመግባባት ስደርስ ሌላ ጥያቄ ያስከትላሉ።ይሄን ጥያቄ መሞገት ያምረኛል።ሰው ሆኖ ከሰው ጋር መኖር ክልክል ነው\nባይን እሞግታለሁ።ሰው ሆኖ ሰውን አታቅርብ የሚልን እከሳለሁ።ለዚያውም ራቅ ብዬ።ታዲያ ነግሬያቸው ነው ’ማልፈው።“ሰው ወይም ጓደኞችህ\nማምጣት አይቻልም ሲሉኝ” ተቃውሞዬን ማሰማት እጀምራለሁ፡፡ እኔ ምለው ተከራዮች ጓደኛ የሌላቸው ያህል የተከራይ ጓደኛ አጥብቀው የሚጠሉበት ምክንያት ምን ይሆን? ከሰው\nጋር መኖር ክልክል ነው ማለት እንዴት ይቀላል? ትዳርን መስርቶ፤ ልጅ ወልዶ በደስታ ለመኖር እየታሰበ ለሌላው አያገባኝም በሚል\n“ለባለትዳርና ልጅ ላለው ቤት አላከራይም” እንዴት ይባላል? ትዳሩን የሚያስተዳድሩት እነርሱ፤ ልጁን የሚያሳድጉት እነርሱ፤ ቤተሰቡን\nየሚመግቡት እነርሱ ይመስል።ብቻውን የሚኖር፣ ሰው የማያምረው፣ የማይስቅ የማይጫወት፣ ማህበራዊ ህይወት የራቀና የጠላ ሊያደርጉን\nቆርጠዋል አከራዮች፡፡ ውዶቼ አከራዮች ተከራይ በቤት ላይ እንደዜጋ መብት እንዳለው አስበን እናውቃለን።መሬቱ በምንም መለኪያ የሀገር\nሀብት ነው።ያ ሀብት ደግሞ በአጋጣሚ ወይም በሆነ መንገድ የአከራዩ ሆኖ ተገኘ።ነገር ግን፤ ተከራዩ በሀገሩ ያለን ማንኛውም ሀብት\nበእኩል የማግኘት ኢኮኖሚያዊ መብቱ ነውና ቢያንስ በተከራይነት መብቱ ሳይነጠቅ በሰላም የመኖር ህጋዊ መብት ይኖረዋል።የኑሮ ጉዳይ\nየሰብዓዊ መብት ጉዳይም ነውና አከራይ የተከራይን ሰብዓዊ መብት የማክበር ህጋዊ ግዴታ አለበት።ተከራይም የአከራይ መብት መጠበቅ\nእንዳለበት ሳይዘነጋ፤ እናም ሰው ሆኖ “ሰው አትቅረብ ሰው አትጥራ” ማለት ተገቢነት የለውም።ያራዳ ልጆች እንዲህ አይነቱ ገጠመኝ\nተገቢ ያለመሆኑን መንገር ሲፈልጉ ወይም ሲወርፉ “አይነፋም” ማለት ያዘወትራሉ።እናም ይሄ ተግባር ‘አይነፋም፡፡’ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በቅርቡ ባደረጉት የፓርላማ ንግግራቸው “የቤት ኪራይ ጉዳይ በጥናት\nእልባት ይበጅለታል፤” ማለታቸውን በሰማሁ ጌዜ ለተግባራዊነቱ ፍጥነት ጸሎት ጀምሬ ነበር።ምን ዋጋ አለው ጸሎቴ አልሰመረም መሰለኝ፤\nየአጥኚዎቹን ድምፅ እስካሁን መስማት አልቻልኩም።እንደአከራይ ካልሆነ በቀር ተከራይ ሆኖ ይሄን የማይናፍቅ ይኖራል።የኪራይ ገደብ\nተቀምጦ ህጋዊ የሆነ ምቹ ስርዓት ተዘርግቶ ተከራዮች መበዝበዛቸው ቢቆም ምን አለ።የቤት አከራዮችና ደላሎች የሚስማሙበትን ያህል ተከራዮች ከደላሎች ጋር ቢስማሙ የቤት ኪራይ ዋጋ ከመጨመር ይልቅ\nበወረደ ነበር።አቤት የደላሎችና የአከራዮች ፍቅር፤ በነገራችን ላይ ውዴታቸው በጥቅም ላይ የተመሰረተ ነው።ደላላው አዳዲስ ተከራዮችን\nበማቅረብና ዋጋ ከፍ አድርጎ በመንገር የአከራይን ገቢ ማሳደግና አከራይ ደግሞ ተከራይን ቶሎ ቶሎ በመለዋወጥ የደላላውን ገቢ በማሳደግ\nየንግድ ስምምነት አድርገው እቅድ አውጥተው ተከራይን የመበዝበዝ ስራ በጋራ ለመስራት ቃል ኪዳን አስረዋል። የቃላቸውን ያህል ታምነው የማይገኙት ደላሎችም ምግባርና ቃላቸው የተነጣጠለ፤ ተግባርና እውነታቸው የተራራቀ\nሆኗል።ደላሎቹ ቤት ተጠይቀው ሲያወሩ ሲያስተዋውቁ ለጉድ ነው።የቤቱን ሁኔታ በአንደበታቸው ባለ ምርጥ ቃል ሁሉ አጣፍጠው ይናገራሉ።ቤቱ\nየተሰራው ከምርግ ጭቃ ሆኖ አስሩ ቦታ ተነድሎ እየታየ ሳለ በእምነበረድ ተገጥግጦ የተሰራ ነው።የተነደለው ደግሞ በባህሪው ቤቱ ስለሚሞቅ\nለንፋስ መውጫ ሆን ተብሎ የተሰራ ነው፤ በአፈር የተደመደመ ወለል ልስልስ በሆነ ሲሚንቶ ተሰርቶ ነው እያሉ ሲተረተሩ የሚተረትሩትን\nእየሰሙ ከመታዘብ ውጪ ምን ሊባል ይችላል።እኔ ’ምለው ደላላና ውሸት እስከ መቼ ነው አብረው ተከባብረው ወዳጅ ሆነው የሚዘልቁት?\nበነገራችን ላይ ውዶቼ፤ አሁን ላይ ያለው የኑሮ መወደድና የዋጋ ንረት ምክንያት ሸማቹን ከተጠቃሚ ጋር የሚያገናኙት\nደላሎች ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን ብዙ ማሳያዎችን መጥቀስ ይቻላል።የቤት ኪራይ ጉዳይ አይደል መነሻዬ? እሱን መሰረት አድርጌ አንድ\nገጠመኜን ላንሳ። እዚሁ አዲስ አበባ ከተማ አራት ኪሎ አካባቢ የሚገኝ አንዱ ኮንዶሚኒየም ግቢ ቤት ጥየቃ ገብቼ ከደላሎቹ የተሰጠኝ\nምላሽ ላስከትል።የሚከራይ ቤት መኖሩን የጠየኩት ደላላ መኖሩ ነገረኝ።የዋጋ ጥያቄ ሲያቀርብልኝ የምችለውን ነገርኩት። ባልኩት ዋጋ አሁን ላይ የተያዘ ቤት መኖሩንና እኔ የተሻለ ዋጋ የምከፍል ከሆነ አሁን ያለው ተከራይ ከቤቱ\nባለቤት ጋር በመነጋጋር ማስወጣት እንደሚችል ነገረኝ።የኔን የነገ እጣ አሰብኩት።እሺ ብዬ ተደራድሬው ብገባ ሌላ ከፍ ያለ ተከራይ\nሲመጣ ልቀቅ የማልባልበት ምንም ምክንያት የሌለኝ ተገፍታሪ ነኝና መገፍተርን ጠላሁ። ምቾት ፈልጎ የሰውን ሰላም መንፈግ፤ መደላደልን ተመኝቶ\nድሎትን ከሰው ማራቅ አይከብድም!? የደላሎች ስራ ተጠቃሚን ከአገልግሎት ሰጪ ጋር አገናኝቶ ተገቢ በሆነ መልኩ ገቢ ማግኘት፤ በሰጡት\nልክ መገልገል መሆን ሲገባው ተገቢ ያልሆነ ጥቅም መቃረም አግባብ አይደለም።አገልግሎት ሰጪው ከአገልግሎት ፈላጊው ጋር የሚያገናኝ\nመላ ሲፈጠር ደላላው ምን ይል ይሆን? አከራዩስ “ሰው አይረባህም፤ ብቻህን ከሆንክ፣ እየሳቅህ የማታወራ ከሆነ፤ ከሰው ጋር የማትኖር\nከሆነ ግባ” ማለቱን ሰው ሲያስፈልገው ሰው ከየት ያስገኝለት ይሆን እንጃ? ምድር ለሁላችንም የኪራይ ቤት ናትና እርስ በርስ ሳንበዳደል\nእንለፍባት።ኪራያችን እስኪያበቃ ብንፋቀርባት ትሰፋናለች። አበቃሁ ቸር ያሰማን! አዲስ ዘመን ነሀሴ 17/2011 ተገኝ ብሩ", "passage_id": "99b179bb2697ea564dd7b28d6a7ca3f6" }, { "passage": " ከቢሮዬ ብዙም ራቅ ባላለው ህንፃ በየፎቁ ላይ ባለው የማረፊያ ቦታ የሚታየው የቡና ጠጡ ሥነ ሥርዓት ፣ የሚቆላ ቡና መዓዛ ፣ የሻይ ቅመም ብቻ ምን አለፋችሁ በአካባቢው ለማለፍ ይፈታተናል። በተለይማ “ሱስ አለብኝ “ ለሚል ይሄን አልፎ መሄድ ከበድ ይላል። እናም አብረውኝ ከነበሩት መካከል አንደኛዋ ኧረ ይሄንን ቡና ጥሎ ማለፍ … የሆነ ቃላት ወረወረች። ሁላችንም ተያይተን ፈገግ አልን። ምክንያቱም ቀሪዎቹ የማኪያቶ እንጂ የቡና አፍቃሪዎች አይደለንም። ቢሆንም ግን ቡናን ፉት አንልም ማለት አይደለም። ስለዚህ የምንጠጣውን ቁጭ ብለን ለመወሰን ግብዣውን ግን መቀበል ግድ ነውና ተስማማን ። ረፋድ ላይ ከዚህም ከዛም በሚመጣው ሰው ወንበሮቹ ተይዘዋል። አነስ አነስ ብለው ቁጢጥ በሚያስደርጉ ወንበሮች ላይ ከበብ አድርገን ተቀመጥን ሁሉም የየራሱን ጨዋታ ይጨዋወታል። ወንድ ሴቱ ተደበላልቆ የሚታይበት በርከት ብለው አጠገባችን የተቀመጡት ወጣቶች ጨዋታ ግን ልቤን ሰረቀው። ከጓደኞቼ ጋር ልቀመጥ እንጂ በቆይታዬ የነበርኩት ከጎናች ካሉት ጋር ነው። በአካል እዚህ በጨዋታ እዛ። ቀልቤን የሳበው ጭውታቸው አሁን አሁን የከተማውን ነዋሪ እያነጋገረ ያለው ነው። እዚህ አካባቢ እንዲህ ሆነ እዛ ደግሞ እንደዚህ ተፈጠረ በሚል በሬ ወለደ ወሬ ወይም ደግሞ “ትንሽ ቆሎ ይዞ ወደ… “ እንደሚባለው ትንሽ እውነት ይዞ አገር አተራማሽ ውሸት ማለቴ ነው። እናም ከአጠገቤ ያሉት ወጣቶች የሚያወሩት ዩኒቨርሲቲዎቻችንን የሚመለከት ነው። ባሳለፍነው ሳምንት በየዩኒቨርሲቲዎች ይሰማ የነበረውን ግጭት ነው። በግጭቱ ደረሰ የሚሉትን ወሬ ከዚህ አንዱ ሲያወራ ሌላው የሌላውን ዩኒቨርሲቲ ያለውን ያክላል። በዚህ ብቻ ያቆመ አይደለም ሞቱ ስለተባሉት ተማሪዎች አሟሟት፣ ገዳይ፣ የግድያው ሁኔታ ጭምር ይፈተፈታል። ምን አልባትም በቦታው ላይ ነጥብ መዝጋቢ ሆነው የተሰለፉ ይሁኑ ይሆን ያሰኛል። ኧረ ተው እንዲህ አይደለም ብዬ እያንዳንዱን በማስረጃና እና በመረጃ አስደግፌ መናገርና ማሳመን ብችል ደስ ባለኝ ነገር ግን አልቻልኩምና ወድጄ ጆሮዬን አውሼ በፈጠራ ወሬ ታመምኩ። ከሁሉም ከሁሉም ደግሞ አይ የሰው ነገር የፌስቡክን መረጃ ይዘው ብዬ እንድታዘባቸው ያደረገኝ እዛ እንቶኔ ዩኒቨርሲቲ በጣም የሚያሳዝነው መምህራቸውን ሳይቀር ነው “ፈነካክተው የጣሉት “ሲሉ የሰማሁት ነው። አንድ እውነት ግን አለ የፌስቡክ አርበኞች ዶክተር እንቶኔ የተባሉት የዩኒቨርሲቲው መምህር ብለው የውጭ ሀገር የተፈነከተ ሰው ለጥፈው ነበር። መለጠፉ እውነት ነው፤ ነገር ግን መምህር ዶክተር እንቶኔ ናቸው ወይ? በተባለው ዩኒቨርሲቲ የሚያስተምሩ ሰው ናቸው ወይ? በዩኒቨርሲቲው እንዲህ የሚባሉ ሰው አሉ ወይ … የመሳሰሉ መረጃዎችን መመርመር ላይ የፌስ ቡክ ተጠቃሚዎች ችግር አለ። የተለጠፈን ነገር እውነት ብሎ ማመን ተጠናውቶናል። በቴክኖሎጂ ዘመን ግን ሁሉንም ነገር አምኖ መቀበል ሳይሆን መመርመር ፣ እውነታውን ማረጋገጥ ቀዳሚ ተግባር መሆን እንዳለበት ብንስማማስ፤ ካልተስማማን ያው እንደተለመደው በሸዋጆች መሸወድ ይቀጥላል። ማጣራት በማይቻልበት ቦታ ላይ ደግሞ ለሌላው የተሳሳተ መረጃ ከማድረስ መቆጠብም የአጥፊዎች ተባባሪ ከመሆን ያድናል። እንዳው ነገርን ነገር ያነሳው የለ። ይሄ ወር አንድ ነገር አስታወሰኝ። የህዳር ወር ሲነሳ መቼም የማይዘናጋው ህዳር 12 (ህዳር ሲታጠን) የሚባለው ነው። ህዳር ሲታጠን ሲባል በአይኔ ድቅን የሚለው ጢሱ ነው። ግቢው፣ መንደሩ፣ ከተማው ሁሉ ጢስ ታጥኖ በጢስ ድባብ ውስጥ መታየት። በሀገር ላይ አንድ ክፉ እንደ ተስቦ ያለ በሽታ ገብቶ ብዙዎችን ጎድቶ ነበር እና በወቅቱ የነበሩት ሰዎች በሽታው እንዲጠፋ የአካባቢያችሁን ቆሻሻ ሁሉ ሰብስባችሁ አጥፉ ተባሉ አሉ። እናም ሁሉም ሰው ቆሻሻውን ሰብሰቦ አቃጠለ። በሽታውም እየጠፋ ሄደ። ይሄ የሰማሁት ነው ። ከእዛን ጊዜ ጀምሮ ሁሉም ሰው በከተማ በገጠሩ ህዳር 12 ቆሻሻን ሁሉ ከግቢው ከሰፈሩ በመሰብሰብ ያቃጥላል። ያን ዕለት እኮ መቼም ከተማችንን ለታዘበ ጢሱ ከማዶ ማዶ አያስተያይም በርቀት ቀርቶ በቅርብ ርቀትም መተያየት ከባድ ነው። አሁን ታዲያ ለምን ህዳር 12 ቆሻሻ እናቃጥላለን ? ስል አካባቢያችንን ለምን እናጸዳለን ለማለት ግን አይደለም ። አሁን በአመት አንዴ ሳይሆን ቶሎ ቶሎም ባይሆን መንግስት ሲያጸዳም ቢሆን በወር አንዴ እናጸዳለን። ማለቴ ዓመት እስኪሞላን አንጠብቅም ።ኧረ እንዳውም የከተሞች የምግብ ዋስትና እና የስራ ዕድል ፈጠራ የታቀፉ ሰዎችም የጸዳውን አካባቢም ቢሆን ደግመው በማጽዳት ላይ እንዳሉ ታዝቤያለሁ። ታዲያ በልቤ ይሄ ሁሉ ሰው (ብዙዎቹ ሴቶች ናቸው) አንድ ቦታ ላይ ተሰባስበው ደግሞ በጸዳና አስፋልት ዳር ሲንገዋለሉ ቆይተው የከተማውን ጽዳት ሰርተዋል ተብሎ ከምግብ ዋስትና ገንዘብ ተከፋይ መሆናቸው አስገርሞኛል። ደግሞ ተቆጣጣሪው ከፍ ያለ ድንጋይ ወይም ዳገታማ ቦታ ላይ ቆሞ የመጡና ያልመጡ ለመቆጣጠር ስም ይጠራል። የመጡትም ስማቸው ሲጠራ አቤት ለማለት ካልሆነ የሰሩትን ብዙም አላየሁም። በጭራሽ አልሰሩም እንዳልል ግን ክረምቱ እንደወጣ አካባቢ በየመንገዱ ዳር ያለውን እፀዋት (አረም) በአካፋ ሲጨፈጭፉ እንደነበርም ያየሁትን ልመስክር። አሁን ታዲያ በየቦታው የተመነጠረውን በማቃጠል ህዳር ሲታጠንን እናስታውሳለን። ህዳር ሲታጠን ታዲያ ስንቱን ከበሽታ ሲያወጣ ምነው የእኛን ዘመነኛ የጥላቻ በሽታ ከስር ከመሰረቱ መንቅሎ ቢያወጣልን ስል ተመኘሁ። አሁን እኛ ምንም አይነት በሽታ ቢኖርብን የጥላቻ ያህል ሀኪምም መድሀኒትም የማይፈውሰው በሽታ የለብንም። ስፖርት ሲነሳ ጥላቻ፣ ከስልጣን ሲነሳ ብሄር፤ ተማሪና አስተማሪ… ሲባል ብቻ በእያንዳንዱ ጨዋታና አጋጣሚ ሁሉ የለከፈን ጥላቻን መሰረት ያደረገ የብሄርተኝነት በሽታ ነውና የዘንድሮው የህዳር ጢስ ቢታደገን ብላችሁ አልተመኛችሁም። እኔ ይሄንን ተመኘሁ ። የዛን ዘመን የዋሆችን ከበሽታ የታደጋቸው ጢስ እኛንም ከያዘን በሽታ ይፈውሰን።አዲስ ዘመን ኅዳር 14/2012በጋዜጣው ሪፖርተር ", "passage_id": "749968149aefefa24e6823c4b97d0f89" }, { "passage": "“ሞዬ” በቀጣዩ ዓመት እስከ 155ሺ ኪሎ የተቆላ ቡና ለውጭ ገበያ ያቀርባል የኢትዮጵያ መንግሥት ምርት ገበያን ማቋቋም ፈለገና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራምን (UNDP) ስለጉዳዩ አማከረው፡፡ ዩኤንዲፒም በሐሳቡ ተስማማና ድጋፍ ለማድረግ ወሰነ፡፡ በዚሁ መሰረት ምርት ገበያውን እንዲያቋቁሙ ኤክስፐርቶችንና አማካሪዎችን ከውጭ አገር በማስመጣት ለ5 ዓመት ቀጠረ፡፡ በዚህ አጋጣሚ የዛሬው እንግዳችን በ2001 ዓ.ም ወደ አገሩ የመመለስ ዕድል አገኘና የምርት ገበያን ካቋቋሙ 7 ሰዎች አንዱ ሆነ፡፡ የኦፕሬሽን መምሪያ ኃላፊም በመሆን አገልግሏል፡፡ ዋነኛው የተቋሙ ምርት ቡና ነበር፡፡ ያኔ ቡና አልገባም ነበር፡፡ ከዚያ በፊት አሻሻጩ እንዴት መሆን አለበት? የጥራት ደረጃው እንዴት ነው የሚወጣው? አቀማመጡስ እንዴት መሆን አለበት? … የሚሉ ጥናቶችን በማድረግ ሲያደራጁ ቆዩና ምርት ገበያው ሥራ ጀመረ፡፡ ከምርት ገበያው ከለቀቀ በኋላ፣ ምርት ገበያውን ሲያደራጁ ያስተዋላቸውን ችግሮች አሰበ፡፡ ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ ቡና ወደ ውጭ አገር የምትልከው በባህላዊው አዘገጃጀት ጥሬውን ነው፡፡ ቡናው እሴት ከተጨመረበት (ቫሊዩ አድ ከተደረገበት) ትልቅ አማራጭ ነው፡፡ እንዴትስ ነው ለየት አድርጎ ማቅረብ የሚቻለው? ትርፉስ ምን ያህል ነው? ገበሬዎቹስ እንዴት ነው ከምርታቸው መጠቀም የሚችሉት? ጉድለቱ የት ነው ያለው? እስካሁን ባልተሰራ ሁኔታ እንዴት ነው ቫሊዩ አድ አድርጌ ማቅረብ የምችለው?የኢትዮጵያ ቡና በዓለም የማይታወቅበት አገር የለም፡፡ የይርጋጨፌ፣ የሊሙ፣ የሲዳሞ… ቡና በአሜሪካም ሆነ በአውሮፓ በስፋት ይታወቃል። እነዚህ አገሮች የኢትዮጵያን ቡና የሚያውቁት በጥሬው ነው፡፡ ለምንድነው ቆልተንና ፈጭተን የማንልከው? በማለት አሰበ አሰላሰለ፡፡ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ እያለ ቡና ኤክስፖርት ተደርጎ የሚሸጥበትን ዋጋ ያውቃል፡፡ ትልልቆቹ ቡና ሻጮች እነስታር ባክስ ከኢትዮጵያ ጥሬውን ገዝተው ቆልተውና ፈጭተው ከ15 እና ከ16 እጥፍ በላይ አትርፈው እንደሚሸጡ አሜሪካ በኖረበት ጊዜ ያውቀዋል፡፡ በኢትዮጵያ፣ ጥሬውን ቡና፣ ኡኡ ተወደደ እያሉ አንዱን ኪሎ በ3 ዶላር ይገዛሉ። ቆልተው ወቅጠውና አሽገው ለገበያ ሲያቀርቡ ከ23 እስከ 30 ዶላር እንገዛለን፡፡ በኢትዮጵያ ትላልቅ ቡና ላኪዎች ቢኖሩም ቆልተው መላክ ያልቻሉበት ምስጢር፣ ችግርና ምክንያት ምንድነው? መፍትሔውስ? በማለት ማስተንተን ያዘ፡፡ ቡና፣ በኢትዮጵያ ገበያ በብዛት የሚገኝ ሀብት ነው፡፡ ቀደም ሲል የነበሩት ችግሮች ትኩረት ተሰጥቷቸው በጥንቃቄ ከተሰራ ቡና ብዙ ጥቅምና አማራጮች አሉት፡፡ ባለፉት ሁለትና ሦስት ጊዜያት የቡና ገበያ እየተቀየረ ነው፡፡ እነዚህን ነገሮች ሁሉ እንዴት ነው አቀናጅቼ ወደ ላቀ ደረጃ የማሸጋግረው? በማለት አሰበና ተቆልቶ የተፈጨ ቡና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ በማቀድ “ሞዬ የተቆላ ቡና ኢንዱስትሪ”ን አቋቋመ - አቶ አሐዱ ውብሸት ወርቃለማሁ፡፡ አቶ አሐዱ የተወለደው በአዲስ አበባ ከተማ ነው። ትምህርቱን በቅዱስ ዮሴፍ ት/ቤት እስከ 10ኛ ክፍል ከተከታተለ በኋላ ወደ አሜሪካ ሄደ፡፡ እዚያም የ2ኛ ደረጃ ትምህርቱን አጠናቅቆ የመጀመሪያ ዲግሪውን በኢኮኖሚክስ፣ሁለተኛ ዲግሪውን በማስተርስ ኦፍ ቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን (ኤምቢኤ) አግኝቷል፡፡ በኒውዮርክና በዋሽንግተን ዲሲ ከተሞች ኖሯል፡፡ በሥራ ዓለም ወደ ትውልድ አገሩ እስከተመለሰበት እስከ ማርች 2008 ድረስ የአሜሪካ ድርጅቶችና ባንኮችን በትላልቅ ኃላፊነቶች ሲመራ ነበር፡፡ ስለ ሞዬ የተቆላ ቡና ኢንዱስትሪና ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ከአዋሽ ወይን ጠጅና ከሙልሙል ዳቦ ጋር ስለፈጠሩት የኢትዮጵያ ለግዤሪ አሊያንስ (እሴት) አውግቶናል፡፡   አቶ አሐዱ ባደረገው ጥናት፣ ኢትዮጵያ ቡና ቆልታ ወደ ውጭ እንዳትልክ ያገዳት የውጭ ገበያ የማግኘት ችግር ነው፡፡ እንደ ስታር ባክስ ያሉ ትላልቅ ቡና ቆይዎች በቀን እስከ ሚሊዮን ኪሎ ቡና ይቆላሉ፡፡ ይህን ያህል ኪሎ ቡና ሲቆሉ ወጪያቸው ይቀንሳል፤ ብዙ ትርፍ ያገኛሉ፡፡ ስለዚህ አንድ ምርት ባወጡ ጊዜ 20 እና 30 ሚሊዮን ዶላር ከገበያ ማፈስ ይችላሉ፡፡ ሌላው ደግሞ መቀላቀል (ብሌንዲንግ) ነው፡፡ የኢትዮጵያ ቡና ጥሩ ስለሆነ በውድ ዋጋም ቢገዙ፣ ከኮሎምቢያ ወይም ከቬትናም በርካሽ ዋጋ ከገዙት ጋር ይቀላቅላሉ፡፡ ቡና ስፔሻሊቲ አለው፡፡ በደንብ ከተሰራበት ብዙ ዓይነት ቡና አለ፡፡ ደረጃ አወጣጡ፣ አመዳደቡ፣ አቀማመሱ፣ አሰራሩ ሁሉ ሳይንስ ነው፡፡ ለምሳሌ ኒውዮርክ አካባቢ ያሉ ተጠቃሚዎች ስፔሻሊቲ ቡና የሚፈልጉ ይሆናል፡፡ ስለ ቡና የሚያውቁት ሰዎች ይህ ቡና ከየት የመጣ ነው? ብለው ይጠይቃሉ። የተጠቃሚውን ፍላጎት ስለሚያውቁት በፈለገው አካባቢ ስም ቆልተው ያቀርባሉ፡፡ ጥያቄው፣ ከእነዚህ ቡና ቆይዎች ጋር እንዴት መወዳደር ይቻላል? የሚለው ነው፡፡ ሌላው ችግር ደግሞ የአቀራረቡ ሳይንስ ነው። እንዴት ነው የአሜሪካና የአውሮፓ ገበያ በሚፈልገው የጥራት ደረጃ ማቅረብ የሚቻለው? እነዚህን ችግሮች ስንመረምራቸው፣ አንደኛው የካፒታል ችግር ነው። ሁለተኛው የባለሙያ ወይም የሰለጠነ የሰው ኃይል፣ ሦስተኛ ደግሞ ገበያ የማግኘት ችግር ነው፡፡ ገበያ በማግኘቱ ዙሪያ አንድ ዘዴ ቀየስን፡፡ በውጪው አሠራር ኦርጋኒክ ቡና፣ ፌር ትሬድ፣ አከፋፈሉ እንዴት ይሆን? የሚልና ትራንስፓረንስ የሚባሉ ነገሮች አሉ፡፡ እኔ ፌርትሬድ የሚለውን ፌር ቼይን በማለት ቀየርኩት፡፡ የኢትዮጵያ ገበሬ ከምርቱ ሽያጭ የሚደርሰው ከ3.5 – 4 በመቶ ነው። ገበሬው የሚያገኘውን እንዴት ነው የምንቀይረው? እንዴት ነው ለገበያው የምናስተዋውቀው በማለት ዓለም አቀፍ ፌር ቼይን ፈጠርኩ፡፡ የገበያ ሰንሰለቱ ቀንሶ አንድ ኪሎ የሚሸጥበትን 30 ዶላር እንዴት ነው ወደ አገራችን ማምጣት የሚቻለው? ማለት ነው፡፡ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በዓመት ወደ ውጭ ከምትልከው ቡና የምታገኘው ከ5500 እስከ 700 ሚሊዮን ዶላር ነው፡፡ ይህ ቁጥር የዛሬ 10 ዓመትም ከፍ አይልም፤ እዚያው ገደማ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ቡና ጥሩ ነው ይባላል፡፡ ነገር ግን ተደራድረን መሸጥ አንችልም፡፡ የሰጡንን ዋጋ ተቀባይ ነን፡፡ 10 በመቶ ይሰጠናል፣ እሱኑ ተቀብለን እንሄዳለን፡፡ እንዴት ነው በዓለም ገበያ ተከራክረን መሸጥ የምንችለው? እንዴት ነው ኤክስፖርት የምናደርገውን የቡና መጠን ከፍ ማድረግ የምንችለው? … በማለት እየሰራን ነው፡፡ ቡና እየቆላን ወደ ውጭ አገር ለመላክ ስናስብ፣ በትንሹ እየቆላን፣ በሚሊዮን ኪሎ ከሚቆሉ ትላልቅ ኩባንያዎች ጋር መወዳደር አንችልም፡፡ ቡና የሚቆላ ትልቅ መሳሪያ ሊኖረን ይገባል፡፡ ስለዚህ ትልቅ ገንዘብ አውጥተን በዓመት እስከ 2 ሚሊዮን  ኪሎ ቡና የሚቆላ መሳሪያ ገዝተናል። ሌላው ደግሞ የቡና ሳይንሳዊ አሰራር የሚያውቁ 3 ባለሙያዎች ከውጭ አገር ቀጥረን እያሰራን ነው፡፡ ሌላው የአይኤስኦ የምስክር ወረቀት ነው፡፡ በኢትዮጵያ እስካሁን የጥራት መቆጣጠሪያ ያለው ድርጅት የለም፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ የቡና አይኤስኦ አግኝተን ለዓለም እያስተዋወቅን ነው፡፡ ሌላው የገበያ ማፈላለግ ሥራ ነው፡፡ በእግራችን መቆም እስከምንችል ትልቅ አቅም ካለው ድርጅት ጋር መስራት ይሻላል በማለት በሆላንድ ትልቅ አቅም ካለው ድርጅት ጋር በ50፣50 እኩል ድርሻ ሸጠን እየሰራን ነው። አሁን የገበያ ማስተዋወቁን እየሰራን ያለው በሦስት የአውሮፓ አገሮች ማለትም በኔዘርላንድ፣ በቤልጂየምና ፈረንሳይ ነው፡፡ በሆላንድ ሁለተኛ ቡና ቆይ (እስከ 2.5 ሚሊዮን ቡና ከሚቆላ) ለመጀመሪያ ጊዜ የተቆላ ቡና ለማቅረብ ተወዳድረን ጨረታውን አሸንፈናል፡፡ በ2016 ሁለት ሚሊዮኑን ባይሆንም እስኪ እንያችሁ በማለት 10 በመቶውን 200ሺህ ኪሎ ቡና አቅርቡ ብለዋል፡፡ እኛ 2000 ኪሎ ለማቅረብ እየሰራን ነው፡፡ አሁን በሦስት የአውሮፓ አገሮች ነው እየሰራን ያለነው፡፡ በ7 እና 8 አገሮች ለመስራትና ወደ ሰሜን አሜሪካ ገበያዎች ለመግባት ዕቅድ አለን፡፡ አብዛኛው ኢንቨስትመንታችን ማርኬቲንጉ ላይ ነው፡፡ በሆላንድ 700 ሺህ ዩሮ አጥፍተናል፡፡ በኢትዮጵያ ደግሞ እስካሁን ድረስ 1.8 ሚሊዮን ዶላር አውጥተናል። ከሸሪኮቻችን ጋር በመሆን በሚቀጥለው ሁለት ዓመት የዚህን እጥፍ ኢንቨስት በማድረግ 4 ሚሊዮን ዩሮ ለማድረስ አቅደናል፡፡ ቡናችንን ለአገር ውስጥ ገበያም እናቀርባለን፡፡ በአሁኑ ወቅት ዓለም አቀፍ ደረጃ ያሟሉ ሆቴሎች እየተከፈቱ ነው፡፡ በእነዚህ ሆቴሎች የሚያርፉ እንግዶች ቡና አዘው እስኪመጣላቸው ድረስ ሊቆይና ሊቀዘቅዝ ይችላል። ስለዚህ እንግዳው ራሱ አፍልቶ የሚጠጣበትን ዘዴ እያዘጋጀን ነው፡፡ ካፌይን የሌለው ቡናም እናዘጋጃለን። ቡና ሌሎች በርካታ አሰራሮች ስላሉት እነሱን እንተገብራለን፡፡ ሞዬ የተቆላ ቡና በአሁኑ ወቅት ለ22 ሰራተኞች የሥራ ዕድል ፈጥሯል፡፡ በሚቀጥለው ዓመት መጨረሻ 53 ለማድረስ ታቅዷል፡፡ 500 ሄክታር መሬት የቡና እርሻም አለው፡፡ በሚቀጥለው ዓመት የ100 ኪሎ ኮንትራት በእጃቸው አለ፡፡ አሁን እየሰሩ ያለ 60 ኪሎ አለ፡፡ በአጠቃላይ በሚቀጥለው ዓመት ከ100 ሺህ እስከ 155 ሺህ ኪሎ ቡና ያቀርባሉ፡፡ * * *ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ምሽት፣ በምርት ጥራታቸው የታወቁ ሦስት ድርጅቶች፡- ሞዬ የተቆላ ቡና፣ አዋሽ ወይን ጠጅና ሙልሙል ዳቦ የኢትዮጵያ ላግዠሪ አሊያንስ የፈጠሩበትን ኅብረት ይፋ አድርገዋል፡፡ አቶ አሐዱ ስለዚህ ኅብረት ሲናገር፣ “ሜድ ኢን ጀርመኒ፣ ሜድ ኢን ኢታሊ፣ ዝቅ ሲልም ሜድ ኢን ቻይና … ይባላል፡፡ ጥሩ ምርት በኢትዮጵያ ሲሰራ ለምንድነው ሜድ ኢን ኢትዮጵያ፤ በአገሬ ምርት እኮራለሁ”  የማይባለው? ዛሬ ኅብረት የፈጠርን ሦስት ድርጅቶች ነን፡፡ በሚቀጥለው ዓመት ሌሎች ድርጅቶች ተጨምረው ሰባትና ስምንት እንሆናለን፡፡ የዚህ ዓይነት አሰራር በውጭ አገር የተለመደ ነው፡፡ አንድ ዓይነት ምርት ብቻ ከመስጠት የሦስትና የሰባት ድርጅቶች ምርት አንድ ላይ አድርጎ በስጦታ ማበርከት መለመድ አለበት፡፡ ጥራት ያለው ምርት የሚያመርቱም ድርጅቶች ኅብረት መፍጠር አለባቸው” ብሏል፡፡  ", "passage_id": "cb7d36ef5e7aadf086f2173797b04932" } ]
d257408849ea5210d2920a7680699b15
1dd6701861055b016f1ec03cf6a04fb5
ኮቭድ-19- ዳግም የቶኪዮ ኦሊምፒክ ሥጋት
ቦጋለ አበበ ጃፓን ከሰባት ዓመታት በላይ ብዙ የለፋችበት የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ዝግጅት ካለፈው ዓመት ጀምሮ የዓለም ሕዝብ የጤና ጠንቅ በሆነው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ለአስራ ስድስት ወራት ተራዝሞ ዘንድሮ ሊካሄድ ቀጠሮ ተይዞለታል። ኦሊምፒኩ በተራዘመው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት እንደሚካሄድም እርግጠኛ ሆነው የውድድሩ አዘጋጆች መናገር ከጀመሩ ሰነባብተዋል። የተለያዩ አገራትም በአዘጋጆቹ ተማምነው የስፖርት ልዑካን ቡድኖቻቸውን እያዘጋጁ ይገኛሉ።የዓለም አቀፉን ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጨምሮ የውድድሩ አዘጋጆች አሁንም ድረስ ውድድሩ እንደሚካሄድ እርግጠኛ የሆኑት ወረርሽኙ ኦሊምፒኩ እስኪቃረብ አንድ መፍትሄ ያገኛል በሚልና በሙከራ ላይ የሚገኙትን የተለያዩ ክትባቶች ተማምነው ነው። ያም ሆኖ ሰሞኑን እየወጡ የሚገኙ መረጃዎች ወረርሽኙ እየቀነሰ ከመሄድ ይልቅ በፍጥነት እየተስፋፋ እንደሚገኝ ያመላክታሉ። ጃፓን ውድድሩን በምታካሂድበት ወቅት ከወረርሽኙ ጋር በተያያዘ ከአገሪቱ ዜጎች በበለጠ ብዙ ቁጥር ያላቸው እንግዶች ስጋት ሊሆኑ እንደሚችሉ የገመተች ቢሆንም፣ በተቃራኒው ራሷ ጃፓን የእንግዶቿ ስጋት ልትሆን እንደምትችል በቅርብ የወጡ መረጃዎች እየጠቆሙ ነው።ወረርሽኙ ለዓለም ስጋት ከሆነ ወዲህ ኦሊምፒኩን በዋናነት የምታስተናግደው ከተማ ቶኪዮ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ ወር ውስጥ ብቻ በቫይረሱ የተጠቁ አስር ሺህ ሰዎች የተገኙባት ሆናለች። ይህም በቀጣዩ ክረምት በሚካሄዱት የኦሊምፒክና የፓራሊምፒክ ውድድሮች ላይ ዳግም ተመሳሳይ ስጋት እንዲፈጠር ያደረገ ሲሆን በብዙዎች ዘንድ ጥያቄ እየተነሳበት ይገኛል።ኦሊምፒኩ ሊካሄድ ስድስት ወራት በቀሩበት በዚህ ወቅት ባለፈው ሐሙስ ብቻ ቶኪዮ በሃያ አራት ሰዓት ውስጥ ስምንት መቶ ሃያ ሁለት ሰዎች በቫይረሱ የተያዙባት ከተማ ሆናለች። ይህም ወረርሽኙ በሀገሪቱ ከተከሰተበት ወቅት ወዲህ የታየ ከፍተኛው ቁጥር ሆኖ ተመዝግቧል። የቶኪዮ ከተማ አስተዳዳሪ ዩሪኮ ኮኢኬ ከጃፓን ታይምስ ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስም የቶኪዮ የጤና ተቋማት ከአቅማቸው በላይ ሕመምተኞችን እያስተናገዱ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ‹‹ሆስፒታሎች ተዘግተዋል፣ በዚህ ወሳኝ ወቅት በቅርቡ መሰረታዊ አገልግሎት መስጠት ሊያቆሙም ይችላሉ›› በማለትም በከተማዋ ያለውን ሁኔታ ገልፀዋል።ቶኪዮ ወረርሽኙ ከተከሰተ ወዲህ እስካለፈው ሳምንት መጨረሻ ብቻ ሃምሳ ሁለት ሺህ ሰዎች በቫይረሱ የተጠቁባት ከተማ ስትሆን አምስት መቶ ያህል ሰዎችም ሕይወታቸው አልፏል። በአጠቃላይ በጃፓን ደግሞ እስካፈው ሰኞ ድረስ በአማካይ ከሁለት ሺህ በላይ ሰዎች በቫይረሱ እየተጠቁ እንደሚገኙ መረጃዎች ይጠቁማሉ፤ እስካሁን ከሁለት ሺህ ዘጠኝ መቶ በላይ ሰዎች በቫይረሱ መሞታቸው ታውቋል።የቶኪዮ ተላላፊ በሽታዎች መቆጣጠሪያ ማዕከል ዳይሬክተር ኖሮዪ ኦማጋሪ በበኩላቸው ‹‹የቫይረሱ ሥርጭት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል፣ ከዚህ የበለጠ ብዙ ሰዎች በቫይረሱ እንዳይጠቁ ጠንካራ እርምጃዎች መወሰድ አለባቸው›› በማለት ለአገሪቱ ጋዜጣ ተናግረዋል።ጥቂት ቀናት በቀሩት የፈረንጆቹ አዲስ ዓመትና የገና በዓል አከባበር ወቅት በርካታ የአውሮፓ አገራት የወረርሽኙን ሥርጭት ለመቀነስ ጠንካራ መመሪያዎችን ከማውጣት ባሻገር በአገር አቀፍ ደረጃ እንቅስቃሴዎችን እስከ መግታት ደርሰዋል። ይህን በመመልከትም ጃፓን በአንፃራዊነት የተሻለ ሁኔታ ላይ እንደምትገኝ የሚናገሩ አሉ። ከቀናት በፊት የእንግሊዝ መንግሥት የጤና ቢሮ ሃላፊ ክሪስ ዊቲይ በአይነቱ ልዩ የሆነና በፍጥነት የመዛመት ባህሪ ያለው የኮቪድ-19 ቫይረስ በአገሪቱ እንደተገኘ ለዓለም ጤና ድርጅት ጭምር በማሳወቅ ጥንቃቄ እንዲደረግ ማሳሰቡ ይታወቃል። በአገሪቱ የቫይረሱ ሥርጭት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በመምጣቱም ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን በአዲስ ዓመትና በገና በዓል ዋዜማዎች ወቅት በሚደረጉ መዝናኛዎች ላይ ጠንካራ እግድ አስቀምጠዋል። መዲናዋ ለንደንን ጨምሮ ቫይረሱ በስፋት በተሰራጨባቸው የደቡብ እንግሊዝ ከተሞችም ጠንካራ የተባሉ ገደቦች ተጥለዋል።አስቀድሞ በቫይረሱ ከፉኛ የተጠቃችው ጣሊያንን ጨምሮ ኔዘርላንድስና ጀርመን እስከ አዲሱ ዓመት ድረስ ማንም ከቤቱ እንዳይወጣ እግድ አስቀምጠዋል። አውስትራሊያም ከገና በዓል በኋላ ተመሳሳይ እርምጃ እንደምትወስድ መረጃዎች ጠቁመዋል። በቅርቡ በቤልጂየም ብራሰልስ የተካሄደውን የአውሮፓ ሕብረት ስብሰባ ከተካፈሉ በኋላ የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑዔል ማክሮንና የስሎቫኪያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኢጎር ማቶቪች እንዲሁም ሌሎች የአገር መሪዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ይታወቃል። ባለፈው ዓመት በቫይረሱ ሥርጭት ስጋት የገባቸው የኦሊምፒክ አዘጋጆች ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ታላቁን የስፖርት መድረክ ለማራዘም መገደዳቸው ይታወቃል። በዚህም የተነሳ አዘጋጅ ኮሚቴው ሁለት ነጥብ ስምንት ቢሊየን ዶላር ኪሳራ እንደደረሰበት ከወር በፊት አሳውቋል። ወረርሽኙ ዳግም በከፍተኛ ሁኔታ ማገርሸቱን ተከትሎም የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ላይ ጥያቄ ተነስቷል። የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ቶማስ ባኽን ጨምሮ የተለያዩ ሃላፊዎች ግን አሁንም ውድድሩን በጥንቃቄ ለማካሄድ ሃሳብ አለወጡም።ቶኪዮ በኦሊምፒኩ ወቅት ወረርሽኙን ለመቆጣጠር በምትወስደው እርምጃ ከዘጠኝ መቶ ስልሳ ሚሊየን ዶላር በላይ ወጪ እንደምታደርግ የተዘገበ ሲሆን፣ የውድድሩ አዘጋጆች ቫይረሱን ለመዋጋት ከአገሪቱ መንግሥት ጋር በየጊዜው ውይይት እያደረጉ ይገኛሉ። በኦሊምፒኩ የሚሳተፉ አትሌቶችና የስፖርት ልዑካን ቡድኖች የፊት ጭምብል ማጥለቅና ርቀትን መጠበቅ እንደሚገባቸው አዘጋጆቹ በቅርቡ ጠቁመዋል፤ ከውድድሩ በኋላ በጃፓን የሚቆዩበት ጊዜ አጭር እንደሚሆንም አሳውቀዋል።እንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ ቻይናና ሩሲያን የመሳሰሉ የተለያዩ አገራት ለወረርሽኙ መፍትሄ ይሆን ዘንድ የተለያዩ ክትባቶችን በማምረት የተሳካ ሙከራ እንዳደረጉ መናገር ከጀመሩ ሰንብተዋል። ክትባቱ በምን አይነት ፍጥነት ለዓለም ሕዝብ ተዳርሶ የቶኪዮ ኦሊምፒክ ከስጋት ነፃ በሆነ መልኩ ይካሄዳል የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ነው። በኦሊምፒኩ ለመሳተፍ ወደ ቶኪዮ የሚያቀኑ ከቫይረሱ ነፃ የሆኑ አትሌቶች ክትባቱን ለማግኘት ቅድሚያ ይሰጣቸዋል አይሰጣቸውም የሚሉ ጥያቄዎችም ከወዲሁ እየተነሱ ይገኛሉ።የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ቶማስ ባኽ ባለፈው ወር በጃፓን ባደረጉት ጉብኝት ወቅት የተሳካ የኮቪድ-19 ክትባት ተገኘ መባሉን ተከትሎ እንኳን ስፖርተኞች የስፖርቱ አፍቃሪዎች ስቴድየም ገብተው የኦሊምፒክ ውድድሩን ካለ ስጋት እንደሚመለከቱ እርግጠኛ ሆነው ሲናገሩ ተደምጠዋል።የጃፓን መንግሥትና የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አትሌቶች የወረርሽኙን ክትባት እንዲያገኙ የተለያዩ ጥረቶችን እያደረጉ ይገኛሉ። ከዚህ ባሻገር በኦሊምፒኩ የሚሳተፉ አትሌቶችና የስፖርት ቤተሰቦች ወረርሽኙን ለመከላከል የተለያዩ ጥብቅ መመሪያዎችን ማክበር እንደሚገባቸው ቀደም ሲል አዘጋጆቹ አሳውቀዋል።ባለፈው ዓመት ወረርሽኙ በኦሊምፒኩ አዘጋጅ ጃፓንም ይሁን በሌሎች አገራት እንዲህ እንዳሁኑ ባልጠነከረበት ወቅት ለመራዘም የተገደደውን ይህን ውድድር፣ ዘንድሮ ወረርሽኙ ‹‹ክትባት ተገኝቶለታል›› እየተባለም መልኩን እየቀያየረ የብዙዎች ስጋት በሆነበት ጊዜ እንዲካሄድ መወሰን ለብዙዎች አልተዋጠም። ዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴውም ይሁን የጃፓን መንግሥት ውድድሩን ለማካሄድ እርግጠኛ ሆነው እየተንቀሳቀሱ የሚገኙትም ኦሊምፒኩ ካልተካሄደ የሚደርስባቸውን ትልቅ ኪሳራ በማስላት ሊሆን እንደሚችል ትችቶች ይሰነዘራሉ።ኦሊምፒኩ ባለፈው ዓመት መካሄድ ሲገባው ወደ ዘንድሮ በመራዘሙ ብቻ ሁለት ነጥብ ስምንት ቢሊየን ዶላር ኪሳራ እንዳደረሰ የቅርብ ጊዜ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ይህን ኪሳራ ለመሸፈን የቶኪዮ ከተማ አንድ ነጥብ አንድ ቢሊየን ዶላር ወጪ እንዳደረገ ተዘግቧል፤ የውድድር አዘጋጅ ኮሚቴው አንድ ቢሊየን ዶላር ወጪ አድርጓል። ቀሪውን ሰባት መቶ ሚሊየን ዶላር ደግሞ የጃፓን መንግሥት እንደሚሸፍን ታውቋል። ኦሊምፒኩ ከመራዘሙ አስቀድሞ አስራ ሦስት ቢሊየን ዶላር ወጪ እንደሚጠይቅ ተገልጿል።በዘንድሮው ዓመት ሳይካሄድ ከተራዘመ ወይም ከተሰረዘ ቀድሞ ከተያዘለት በጀት እስከ አራት እጥፍ ኪሳራ ሊያደርስ እንደሚችል መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=38136
[ { "passage": "የኮሮና ቫይረስ(ኮቪድ 19) በዓለም ላይ በከፍተኛ ፍጥነት መሰራጨቱን ተከትሎ የሁሉም ዓለም አቀፍ የስፖርት መርሐግብሮች እንዲቋረጡ አድርጓቸዋል። የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱ ተከትሎ የስፖርቱ ዓለም ካለፉት ሁለት ወራት በላይ ተቋርጦ እንዲቆይ አድርጎታል። የውድድሮቸ መቋረጥና መርሐ ግብሮች መራዘማቸውን ተከትሎ የስፖርቱን ኢንዱስትሪ ክፉኛ እንደጎዳው ዓለም አቀፍ ጥናቶች ከወዲሁ ያመላክታሉ። ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በመቆማቸው ምክንያት የሚደርሰውን ኪሳራ በመጠኑም ቢሆን ለማዳን ውድድሮችን በዝግ ስታዲየም ማድረግ አማራጭ ተደርጓል። ከቫይረሱ ስጋት ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆን ባይችሉም ታላላቆቹን አውሮፓ እግር ኳስ ሊጎች ጨምሮ አንዳንድ አገራትም ስፖርታዊ ውድድሮቻቸውን ከሰሞኑ አስጀምረዋል። ውድድሮችን በዝግ ስቴድየሞች በማድረግ የውድድር ዓመቱ ከመጠናቀቁ በፊት መርሐግብሮቻቸውን ለማጠናቀቅ ጨዋታዎችን እያደረጉ ይገኛሉ። \nበአውሮፓ እግር ኳስ ሊጎች የተወሰደውን መፍትሔ የዓለም አቀፍ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተግባራዊ ሊያደርገው እንደሚችል ቢቢሲ ዘግቧል። የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሰባስቲያን ኮዬ ፤ የአትሌቲክስ ስፖርት ሲመለስ በባዶ ሜዳዎች ሊካሄድ እንደሚችል ማስጠንቀቃቸውን መሰረት ያደረገው ዘገባው፤ «በታላላቆቹን አውሮፓ እግር ኳስ ሊጎች ከሰሞኑ እንደተመለከትነው ዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድሮችም በቅርቡ ሊመለሱ ይችላሉ »ሲል አስነብቧል የዓለም አቀፍ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የአትሌቲክስ ስፖርት ሲመለስ በባዶ ሜዳዎች ሊካሄዱ እንደሚችሉ ከማስገንዘብ በተጨማሪ ፤ውድድሮች ስለሚመለሱባቸው ሁኔታዎች በተመለከተ ሃሳብ መስጠታቸውን አመልከቷል። በዚሁ ላይም «ዓመታዊው የዳይመንድ ሊግ እንዲሁም የተለያዩ የአትሌቲክስ ውድድሮች ሁኔታዎች ከተገመገሙ በኋላ በመጪው ነሐሴ አጋማሽ እንዲካሄዱ እቅድ ተይዟል። በነሐሴ እንዲካሄዱ እቅድ የተያዘላቸው አስራ አንዱ የተለያዩ የአትሌቲክስ ውድድሮች በዝግ ሜዳ ይሆናሉ » ሲሉ መናገራቸውን ጽፏል። \nቢቢሲ በዘገባው ፕሬዚዳንቱ በተለይ ጌምስ ለተባለው ድረገፅ በሰጡት ማብራሪያ «በመጪዎቹ ቅርብ ጊዜያት የሚካሄዱ ውድድሮች ላይ ለደህንነት ስንል ልንደራደርባቸው የማይገቡ ጉዳዮች አሉ። በተደጋጋሚ በጤና ባለሙያዎችም ሆኑ በአካባቢው ማህበረሰብ የተነገረንን ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ ያስገባና ችላ የማንላቸውም ናቸው። ሁላችንም ቢሆን ይህ የረዥም ጊዜ መፍትሔ ነው ብለን አናስብም። ስፖርታዊ ውድድሮች ያለታዳሚ ይጠፋሉ። ሆኖም በአሁኑ ወቅት የአትሌቲክስ ውድድሮችን ለመመለስ መክፈል ያለብን መስዋዕትነት ይሄ ነው» ሲሉ መናገራቸውን በዘገባው አካቷል።አዲስ ዘመን ግንቦት 11/2012ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "7880ef43a81ab343f810d54366a6043d" }, { "passage": "\nየአለም ጤና ድርጅት በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክን መሰረዝ ወይንም የውድድር ቦታውን መቀየር እንደማያስፈልግ መግለጹን የአለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቲ አስተባበሪ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡\n የድርጅቱ ከፍተኛ የአስቸኳይ ጊዜ ባለሙያ የሆኑት ዶ/ር ማይክ ርያን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ “ከአደጋ ዜሮ የሆነ የብዙሀን ስብስብ የለም”፤ ስለሆነም አዘጋጆቹና የአካባቢው የጤና ባለሙያዎች ችግር ሲያጋጥም መፍትሄ ለመስጠት መዘጋጀት አለባቸው ብለዋል፡፡\nየ17 ቀናት ቆይታ የሚኖረው የጃፓን ኦሎምፒክ ሐምሌ 17 ይደመራል ተብሏል፡፡\nበተለየ መግለጫ ጃፓን በቫይረሱ ምክንያት አንድ ዶክተርና የታክሲ ሹፌር ከሞቱ በኋላ የቫይረሱን መስፋፋት ለመግታት ምርመራ አጠናክራ መቀጠሏን አስታውቃለች፡፡\nእየተስፋፋ ያለውና መነሻውን በቻይናዋ ውሀን ከተማ ያደረገው የኮሮና ቫይረስ በቻይና ሊካሄዱ የነበሩትን የ2020 ኦሎምፒክ የጨዋታ የማጣሪያዎችን፤ የቦክስና የባድሜንተን ጨዋታዎች እንዲሰረዙ አድርጓል፡፡\n የቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ አዘጋጅ ኮሚቴ ዋና ስራ አስፈፃሚ በጥር መጨረሻ ቫይረሱ ምናልባት ውድድሩ ላይ ተፅዕኖ ሊያሳድር ይችላል በሚል በጣም ተጨንቀው የነበሩ ቢሆንም፣ በሚቀጥለው ቀን ውድድሩ በተያዘለት ቀን እንደሚካሄድ ቃል ገብተዋል፡፡\n እካሁን ድረስ በኮሮና ቫይረስ 1,490 በላይ የሞቱ ሲሆን ከ60,000 በላይ ሰዎች ደግሞ በኮሮና ቫይረስ ተይዘዋል፡፡\n\n\n\n\n\n\n\n\n", "passage_id": "9971020fb3d5a373c4427bc6d211fc15" }, { "passage": "የአፍሪካ አትሌቲክስ ቻምፒዮና ከኦሊምፒክ ቀድሞ ይካሄዳል የኮሮና ቫይረስ(ኮቪድ 19) በዓለም ላይ በከፍተኛ ፍጥነት መሰራጨቱን ተከትሎ የሁሉም ዓለም አቀፍ የስፖርት መርሃግብሮች ዝብርቅርቅ መውጣቱ ይታወቃል፡፡ ይህንንም ተከትሎ በርካታ ታላላቅ የስፖርት መርሃግብሮችን ዳግም መከለስ አስፈላጊ ሆኗል፡፡ በዚህም መሰረት ክለሳ የተደረገባቸው የተለያዩ መርሃግብሮች ውዝግብ ሲያስነሱ ማየት እየተለመደ መጥቷል፡፡ \nከተያዘለት መርሃግብር እንዲራዘም የተደረገው የአፍሪካ አትሌቲክስ ቻምፒዮና በ2021 እንዲካሄድ ከተራዘመው የቶኪዮ ኦሊምፒክ አስቀድሞ እንዲካሄድ የአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን ውሳኔ ላይ መድረሱን ከሁለት ቀናት በፊት አሳውቋል፡፡ የኮንፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ሐማድ ካልካባ በአልጄሪያ የሚካሄደው የአፍሪካ አትሌቲክስ ቻምፒዮና ከቶኪዮ ኦሊምፒክ ከአንድ ወር ቀደም ብሎ እንደሚካሄድ ማረጋገጫ ሰጥተዋል፡፡ የዓለም አትሌቲክስ ምክትል ፕሬዚዳንት የሆኑት ካልካባ የውድድሩ አዘጋጅ አገርም አዲሱን መርሃግብር የመቀበል ግዴታ እንዳለባት ገልፀዋል፡፡ \nካልካባ ቻምፒዮናው ከተራዘመው ኦሊምፒክ በፊት መካሄዱ ለአትሌቶች ጥቅም እንደሚኖረው የገለፁ ሲሆን ውድድሩ በተከለሰው የኦሊምፒክ ማጣሪያ መርሃግብር ውስጥ እንደሚካተት ጠቁመዋል፡፡ ‹‹ውድድሩ የኦሊምፒክ ማጣሪያ(ሚኒማ) ለሚፈልጉ አትሌቶች ጠቃሚ ይሆናል›› ያሉት ካልካባ የዓለም አትሌቲክስ የኦሊምፒክ ማጣሪያ መርሃግብር እስከ ቀጣዩ ዓመት ሰኔ ወር እንዲራዘም ግፊት ማድረጉን አስታውሰዋል፡፡ \nበኮሮና ቫይረስ ስጋት የተነሳ የአትሌቲክስ ስፖርት የኦሊምፒክ ማጣሪያ ውድድሮች እስከ መጪው ታህሳስ ወር ድረስ እንዳይካሄዱ የዓለም አትሌቲክስ ውሳኔ ማሳለፉን ተከትሎ እስከ ተጠቀሰው ጊዜ የሚካሄዱ ማንኛቸውም ውድድሮችና ውጤቶች የኦሊምፒክ ማጣሪያም ይሁን እውቅና እንደማያገኙ ማስጠንቀቁ ይታወሳል፡፡ ይህ የዓለም አትሌቲክስ ውሳኔ በበርካታ ታላላቅ የዓለማችን አትሌቶች የሰላ ትችት ሲሰነዘርበት እንደሰነበተ ይታወቃል፡፡ \nበኮሮና ቫይረስ ስርጭት ምክንያት የስፖርቱ ዓለም ካለፉት ሁለት ወራት በላይ እንቅስቃሴው ተገድቦ ቢቆይም ከቅርብ ቀናት ወዲህ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው ለመመለስ ሲፍጨረጨሩ እየተስተዋለ ነው፡፡ ታላላቆቹን አውሮፓ እግር ኳስ ሊጎች ጨምሮ አንዳንድ አገራትም ስፖርታዊ ውድድሮቻቸውን ለማስጀመር ከቫይረሱ ስጋት ነፃ ሳይሆኑ ጥረት እያደረጉ ሲሆን አብዛኞቹ ውድድሮችን በዝግ ስቴድየሞች በማድረግ የውድድር ዓመቱ ከመጠናቀቁ በፊት መርሃግብሮቻቸውን ስለመፈፀም እየተጨነቁ ይገኛሉ፡፡ \nበርካቶቹ የዓለም አቀፍ ውድድሮች ግን ቀደም ሲል ቫይረሱ በቀጣዩ ዓመት ይጠፋል ወይም በቁጥጥር ስር ይውላል በሚል ተስፋ ወደ ቀጣይ ዓመት እንዲዞሩ መወሰናቸው ይታወሳል፡፡ ከነዚህ መካከል በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ዘግይቶም ቢሆን በቫይረሱ ስርጭት ስጋት የተነሳ ታላቁን የስፖርት መድረክ ለአስራ ስድስት ወራት እንዲራዘም ማድረጉ ይታወሳል፡፡ ይህም እንደሌሎቹ ውድድሮች ሁሉ ቫይረሱ በቀጣዩ ዓመት በቁጥጥር ስር ይውላል ከሚል ተስፋ እንጂ በተጨባጭ መረጃና ማስረጃ አልነበረም፡፡ በርካቶቹ ይህን ተስፋ የሙጥኝ ብለው እያንዳንዱ ቀን እንደ ዓመት እየረዘመባቸውም ቢሆን ቀጣዩን ዓመት በጉጉት እየተጠባበቁ ይገኛሉ፡፡ \nየቫይረሱ ስርጭት ግን በተቃራኒው እየቀነሰ ከመሄድ ይልቅ በአስደንጋጭ ፍጥነት እየተስፋፋ ይገኛል፡፡ ይህንን ያስተዋሉ የጤና ባለሙያዎችም ለአስራ ስድስት ወራት የተራዘመው የቶኪዮ ኦሊምፒክ በቀጣዩ ዓመት ላይካሄድ እንደሚችል ከወዲሁ እየተናገሩ ይገኛሉ፡፡ የኦሊምፒኩ አዘጋጅ የሆነችው ጃፓን የተላላፊ በሽታዎች ፕሮፌሰር የሆኑት ኬንታሮ ዋታ የቫይረሱ ስርጭት ኦሊምፒኩ በተራዘመበት ወቅት በቁጥጥር ስር ስለመዋሉ አጠራጣሪ በመሆኑ ውድድሩ ላይካሄድ እንደሚችል ስጋታቸውን ለመገናኛ ብዙሃን መግለፃቸው ይታወሳል፡፡ \nበዓለም ላይ አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታ ከተስፋ በስተቀር የቫይረሱ ስርጭት በጊዜ የሚገታ ወይም ፈውስና ክትባት በዚህ ጊዜ እውን ይሆናል የሚያስብል እንዳልሆነ መታዘብ ይቻላል፡፡ ይህንን ከግምት ያስገቡት የቶኪዮ ኦሊምፒክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ቶሺሮ ሙቶ ኦሊምፒኩ የቫይረሱን ስጋት ለማምለጥ በአስራ ስድስት ወራት ቢራዘምም ከቫይረሱ ተፅዕኖ ሊያመልጥ እንደማይችል ሰሞኑን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ማመልከታቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ማስነበቡ ይታወሳል፡፡ የአፍሪካ አትሌቲክስ ቻምፒዮናም ከዚህ የተለየ እድል እንደማይገጥመው ማንም እርግጠኛ አይደለም፡፡አዲስ ዘመን ግንቦት 8/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "d9a6c910e351136919c0b9932f8b36b6" }, { "passage": "የ1982 የዓለም ዋንጫ ለኤሽያዊቷ አገር ኩዌት የእግር ኳሷ ወርቃማ ዘመን ሆኖ ይታወሳል። የዓለም ዋንጫ በመጣ ቁጥር ግን ይህ የኩዌት ወርቃማ የእግር ኳስ ዘመን ሲታወስ አይታይም። እግር ኳስ በተለያዩ ቴክኖሎጂዎች እየረቀቀ ሲመጣ፤ በይነ መረብ ዓለምን ሲያቀራርብና ቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭቶች እንደ ልብ እየሆኑ ሲመጡ እኤአ ከ199oዎቹ ጀምሮ በዓለም ዋንጫ የታዩ ወርቃማ ብሔራዊ ቡድኖች፤ በርካታ ከዋክብቶችና አይረሴ አጋጣሚዎች አሁንም ድረስ በእግር ኳስ አፍቃሪው ዘንድ ይታወሳሉ። ያም ሆኖ ከ1978 የዓለም ዋንጫ አስቀድሞ ከጣሊያንና አርጀንቲና ውጪ ያሉ የእግር ኳስ አፍቃሪዎች ዘንድ ፓውሎ ሮሲና ማሪዮ ኮምፐስን የመሳሰሉ ተጫዋቾች ትልቅ እውቅና ነበራቸው። ከዚህ የዓለም ዋንጫ በኋላም መረጃዎች እንደ ልብ በሌሉበት ዘመን የዲያጎ አርማንዶ ማራዶና ለመጀመሪያ ጊዜ ለአርጀንቲና ተሰልፎ ቤልጂየምን እስከ ገጠመበት ጨዋታ በበርካታ የዓለማችን እግር ኳስ አፍቃሪዎች በቴሌቪዥን መስኮት የመመልከት እድላቸው ጠባብ ቢሆንም ስምና ዝናው ይታወቅ ነበር።የዓለም ዋንጫ አይረሴዎቹ ኮከቦች ሚካዔል ላውድሩፕ፤ ህሪስቶ ስቶቺኮቭ፤ ጂዮርጅ ሃጂና ሌሎችም የጀገኑበት ዘመን ሩቅ ቢሆንም የዓለም ዋንጫ በመጣ ቁጥር ሳይታወሱ የማይታለፉበት ታሪክ አኑረዋል። በተመሳሳይ በብሔራዊ ቡድን ደረጃም የ1966 የሰሜን ኮሪያ፤ በ1982 የአልጄሪያና በ199o የካሜሩን ብሔራዊ ቡድኖች የሚዘነጉ አይደሉም። የኩዌት የ1982 ብሔራዊ ቡድንም ከነዚህ ብሔራዊ ቡድኖች እኩል የሚታወስ ነው። በዛሬው የስፖርት ማህደር አምዳችንም ይህን ብሔራዊ ቡድን ለማስታወስ ወደድን፡፡የ1982 የስፔን የዓለም ዋንጫ የኤሽያን እግር ኳስ አንገት ቀና ያደረገ ድንቅ የብሔራዊ ቡድን ስብስብ ከኤሽያ አልፎ በመካከለኛው ምስራቅና የገልፍ አገራት እግር ኳስ ላይ ትልቅ መነቃቃትን ፈጥሮ ነበር። ይህ ከ197o መጀመሪያ እስከ 198oዎቹ መጀመሪያ ላይ ትልቅ የእግር ኳስ አብዮት የፈጠረ የኩዌት ወርቃማ የእግር ኳስ ትውልድ ኤሽያ እስካሁንም መልሳ ያላየችው ስብስብ ይዞ ነበር። ከ1976 እስከ 1978 በታሪካዊው ብራዚላዊ ማሪዮ ዛጋሎ እንዲሁም ከ1978 እስከ 1982 በሌላኛው ብራዚላዊ ካርሎስ አልቤርቶ ፔሬራ እየሰለጠነ ዓለምን ጉድ ያሰኘ የብሔራዊ ቡድን ስብስብ በድንቅ ባለ ተሰጥኦ ተጫዋቾች የተሞላም ነበር። ከግብ ጠባቂው አህመድ ታራቡልሲ አንስቶ እስከ አብዱላዚዝ አል አንባሪ፤ አህመድ አቡ ሐማድና ግብ አፈንፋኙ ጃሴም ያቆብ እንዲሁም አምበሉ ሳድ አል ሆቲና ፋሳል አል ዳክሂል ድረስ በከዋክብት የተሞላው የኩዌት ብሔራዊ ቡድን ስብስብ ከእግር ኳስ በላይም ትልቅ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ተጽዕኖዎች ነበሩት። ይህ ስብስብ በዓለም እግር ኳስ ላይም በትልቅ ደረጃ ተፅዕኖ መፍጠር የቻለ የመጀመሪያው የገልፍ አገራት ብሔራዊ ቡድን ሆኖ ይታወሳል።የኩዌት ወርቃማ የእግር ኳስ ትውልድ በአንድ ጊዜ ተፈጥሮ በዓለም እግር ኳስ ላይ ድንገት ተፅዕኖ የፈጠረ ሳይሆን በሂደት እየተገነባ የመጣ ነው። ለዚህም በኤሽያና በገልፍ አገራት የእግር ኳስ ቻምፒዮና ሃያል የሆኑትን እንደ ኢራን አይነት አስደናቂ የቡድን ስብስብ ያላቸውን አገራት በሂደት አሸንፎ ዋንጫ በማንሳት ነው። ከዚህ በዘለለም ለ198o የሞስኮ ኦሊምፒክ አልፎ እስከ ሩብ ፍፃሜ ድረስ በመጓዝ በርካቶችን አሳምኖ ነው ወደ ዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጣው።በኤስያ አገራት የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች ኩዌት ኒውዘላንድ፤ ቻይናና ሳውዲ ዓረቢያ ከሚገኙበት ምድብ በፔሬራ አሰልጣኝነት እየተመራች በቀላሉ ወደ 1982 የዓለም ዋንጫ ማምራት ችላለች። እንደ አጋጣሚ ሆኖ ግን ኩዌት በዓለም ዋንጫው ጠንካራ በሚባል ምድብ ውስጥ ተደለደለች። ይሁን እንጂ በቡድኑ ውስጥ የነበረው ጠንካራ ስነ ልቦና ጠንካራውን ምድብ አልፈው ወደ ጥሎ ማለፍ እንደሚገቡ ትልቅ ተስፋ የሰጠ ነበር።«ግመሎቹ» በሚል ቅጽል ስም የሚታወቀው የኩዌት ብሔራዊ ቡድን የመጀመሪያቸው በሆነው የዓለም ዋንጫ በምድብ ድልድሉ ከሦስቱ አውሮፓውያን አገራት ቺኮስላቫኪያ፤ ፈረንሳይና እንግሊዝ ጋር ነበር የተደለደሉት። ይህ ምድብ ከቺኮስላቫኪያ በስተቀር ፈረንሳይና እንግሊዝ ያላቸው ትልቅ ስም ለግመሎቹ ስጋት ቢሆንም የፔሬራ ልጆች ወደ ቀጣዩ ዙር የማለፍ ትልቅ ተስፋን ሰንቀው ነበር። በተለይም በመጀመሪያው የቺኮስላቫኪያ ጨዋታ ሙሉ ሦስት ነጥብ ይዘው ለመውጣት ግምት የተሰጣቸው ቢሆንም ጨዋታው አንድ ለአንድ በሆነ አቻ ውጤት መጠናቀቁ ያልተጠበቀ ነበር። ይሁን እንጂ ጠንካራዋ ፈረንሳይ በእንግሊዝ ሦስት ለአንድ መሸነፏን ተከትሎ ግመሎቹ ወደ ቀጣዩ ዙር የማለፍ ተስፋቸው እንደገና ነብስ ዘራበት። ያም ሆኖ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታ ሚሼል ፕላቲኒ፤ አሊያን ጊረስና ጄን ቲጋና ለፈረንሳይ ግቦችን አስቆጥረው ፈረንሳይ በቀላሉ መምራት ቢችሉም ግመሎቹ ወደ ጨዋታው ተመልሰው ወይ ለማሸነፍ ወይንም የአቻ ውጤት ይዘው ለመውጣት ተስፋ አልቆረጡም። በዚህም ፈረንሳይን ተጭነው በመጫወት በአብዱላህ አል ቦኑሺ የግንባር ኳስ ሦስት ለአንድ መሆን ቻሉ። ይህም ተነሳሽነታቸውን ጨምሮ ሌላ ግብ ለማስቆጠር ጥረት በሚያደርጉበት ሰዓት አንድ ተስፋ አስቆራጭ ክስተት ተፈጠረ። ይህም አለን ጊረስ ከጨዋታ ውጪ የሆነ ግብ ኩዌት ላይ አስቆጥሮ ዳኛው ይሽሩታል ተብሎ ሲጠበቅ ማፅደቃቸው ነበር።ይህች ቅፅበት ግመሎቹን ተስፋ ከማስቆረጧም በላይ በወቅቱም የኩዌት ተጫዋቾች ውሳኔውን በመቃወም ጨዋታውን ሳይጨርሱ ሜዳውን ለቀው ወጥተዋል። በወቅቱ የኩዌቱ ኤሚር ወንድምና የአገሪቱ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት የነበሩት ሼክ ፋሃድ አል አህመድ አል ጃበር አል ሳባህ ከክብር ወንበራቸው ተነስተው ወደ ሜዳ በመግባት በዳኛው ውሳኔ ላይ ያላቸውን ቅሬታ ከተጫዋቾቹ ጋር የገለፁበት አጋጣሚ አይረሳም። በዚህም ዳኛው አሁንም ድረስ የዓለም ዋንጫ አስገራሚ ክስተት ተብሎ እንዲታወስ ያደረገውን አጋጣሚ ያፀደቁትን ግብ በመሻር ጨዋታው እንደገና እንዲጀመር ማድረጋቸው ነበር። ያም ሆኖ ግን ግመሎቹ ወደ ጨዋታው ቢመለሱም ወደ ቀድሞው ተነሳሽነታቸው ሳይመለሱ ቀርተው ፈረንሳይ በመጨረሻ ሰዓት ሌላ ግብ አስቆጥራ አራት ለአንድ ማሸነፍ ቻለች። ከዚህም ቅፅበት በኋላ የኩዌት እግር ኳስ የተሰበረ ቅስም አሁንም ድረስ ሳይጠገን ደብዛው ሊጠፋ ችሏል።የ1982 የስፔን የዓለም ዋንጫ ለኩዌት እግር ኳስ ወርቃማ ዘመን እንደመሆኑ መጠን ደብዛው የጠፋበት አጋጣሚም ሆኖ ይታወሳል። አብዛኞቹ የኩዌት ተጫዋቾች እድሜያቸው የገፋ እንደመሆኑ ከዚያ የዓለም ዋንጫ በኋላ ሌላ ተዓምር ሳያሳዩ ጫማቸውን ለመስቀል ተገደዋል። በእርግጥ የተወሰኑ ተጫዋቾች ከዚያም ወዲያ የተወሰኑ ዓመታትን ተጫውተዋል። እነዚህ ተጫዋቾች ከዓለም ዋንጫው በኋላ በገልፍ አገራት ቻምፒዮና እኤአ 1986ና 1990 ላይ ዋንጫ ማንሳት ቢችሉም ኩዌት የዓለም ዋንጫ ማጣሪያን ለማለፍ የተቃረበችበት ወቅት እንኳን አልተከሰተም። ከዚህም በኋላ እኤአ በ1990 ኩዌት በኢራቅ የተወረረችበትና ቀጥሎም የገልፍ አገራት ጦርነት የተከሰተበት አጋጣሚ የአገሪቱን እግር ኳስ ከተነቃቃበት ወደ ገደል ገፍትሮታል። በፖለቲካ ጣልቃ ገብነት ብሔራዊ ቡድኑ በተደጋጋሚ በፊፋ እገዳ እየተጣለበትም ከድጡ ወደ ማጡ ሲገባ ታይቷል። የኩዌት እግር ኳስ አፍቃሪዎችም የወርቃማ ትውልዳቸው ከዋክብቶችን አል ዳክሂል፤ ያቆብ እንዲሁም አል አንባሪን በማስታወስ የዓለም ዋንጫ በመጣ ቁጥር ይደሰታሉ።አዲስ ዘመን ሐምሌ 26/2012  ቦጋለ አበበ", "passage_id": "cfdb45e3039b64b45e3682ea59b31759" }, { "passage": "ቦጋለ አበበ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት የዓለም ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ገፅታ ዝብርቅርቁ በወጣበት የፈረንጆች 2020 ዓመት የዓለም ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችም ቀላል የማይባል አሉታዊ ተፅዕኖ አርፎባቸዋል። ኦሊምፒክን ጨምሮ ታላላቅ ዓለም አቀፋዊና የአገር ውስጥ ስፖርታዊ ውድድሮች በተሰረዙበትና በተራዘሙበት የውድድር ዓመት የአትሌቲክስ ስፖርት በርካታ ፈተናዎችን ማሳለፉ ይታወቃል። በዓለም ሕዝብ ዘንድ ጥሩ ትውስታን ጥሎ ያላለፈው\n2020 ተሸኝቶ ዛሬ በ2021 የውድድር ዓመት አንድ ብሎ የሚጀምርበት ቀን ነው። በአብዛኛው መጥፎ ትዝታውን ጥሎ ባለፈው ዓመት የአትሌቲክሱ ዓለም በርካታ አሉታዊ ተጽእኖዎች አርፈውበታል፤ በርካታ አዎንታዊ ክስተቶችንም አስተናግዷል። ከእነዚህ መካከልም አበይት ክስተት የሆኑት እንደሚከተለው ተዳሰዋል። ጥር የ2020 የውድድር ዓመት በጀመረበት ታህሳስ መጨረሻና ጥር ወር ላይ የአትሌቲክሱ ዓለም በርካታ የዓለም ክብረወሰኖችን አስተናግዷል።\nኬንያዊው አትሌት ሮኔክስ ኪፕሩቶ የአስር ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የዓለም ክብረወሰንን\nቫሌንሲያ ላይ 26፡24 በሆነ ሰዓት ያስመዘገበው በዚህ ወር ሲሆን፣ ሌላኛዋ ኬንያዊት\nሼላ ቺፕኪሩይ በተመሳሳይ\nውድድር የሴቶቹን የዓለም ከገጽ 46 የዞረክብረወሰን 29፡46 በሆነ ሰዓት በማሻሻል የውድድር ዓመቱን በስኬት ጀምራለች። በዚሁ ወር የማራቶን ቁጥር አንድና ቁጥር ሁለት የሆኑት ኢትዮጵያዊና ኬንያዊ አትሌቶች ቀነኒሳ በቀለና ኢሉድ ኪፕቾጌ በለንደን ማራቶን እንደሚፋለሙ ይፋ መደረጉም የውድድር ዓመቱ ትልቅ ክስተት ነበር። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በየዓመቱ የሚደምቁበት የዱባይ ማራቶን በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፈው ኦሊካ አዱኛ አሸናፊ ሲሆን፣ በሴቶች ወርቅነሽ ደገፋ የኢትዮጵያውያንን የተለመደ ድል ማስቀጠል ችላለች። በቻይና ናጂንግ ባለፈው መጋቢት ወር ሊካሄድ ቀጠሮ የተያዘለት የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ቻምፒዮና መራዘሙ የተሰማው በዚሁ ወር ነበር፤ ይህ ወድድር በኮቪድ-19 ስጋት የተራዘመ የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ ውድድርም ሆኗል። የካቲት ያለፈው የካቲት ወርም በዓለም አትሌቲከስ የተለያዩ የዓለም ክብረወሰኖች የተሻሻሉበት ሆኖ ይታወሳል። በተለይም ስዊድናዊው ምርኩዝ ዘላይ ሞንዶ ዱፕሌንቲስ 2014 ላይ በፈረንሳዊው ሪናውድ ላቪሌኒ ተይዞ የቆየውን የዓለም ክብረሰወን 6 ነጥብ 17 ሜትር በመዝለል በአንድ ሴንቲሜትር ያሻሻለበት አጋጣሚ ትልቁ ክስተት ነበር። ላቪሌኒ በተመሳሳይ ወር ግላስጎ ላይ 6 ነጥብ 18 ሜትር በመዝለልም ተጨማሪ የዓለም ክብረወሰን በአንድ ወር ውስጥ ያሻሻለበት አጋጣሚ የሚዘነጋ አይደለም። የውድድር ዓመቱን በበርካታ የዓለም ክብረወሰኖች ታጅቦ ያጠናቀቀው ዩጋንዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቺፕቴጌ የዓመቱን የስኬት ጉዞ ሞናኮ ላይ የአምስት ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የዓለም ክብረወሰንን 12፡51 በሆነ ሰዓት በማሻሻል የጀመረው በዚሁ የካቲት ወር ነበር። ኢትዮጵያዊቷ አትሌት አባብል የሻነህ የግማሽ ማራቶን የዓለም ክብረወሰንን በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ራስ አል ካይማህ 64፡31 በሆነ ሰዓት ያሻሻለችበትም አጋጣሚ በጉልህ የሚጠቀስ ነው። ቬንዙዌላዊቷ ስሉስ ዘላይ ዩሊማር ሮጃስ በማድሪድ በተካሄደው የቤት ውስጥ ውድድር ለአስራ ስድስት ዓመታት በታትያና ሌቢዴቫ ተይዞ የቆየውን የዓለም ክብረወሰን 15 ነጥብ 43 ሜትር በመዝለል ያሻሻለችበት አጋጣሚም ይታወሳል። መጋቢት የውድድር ዓመቱ ሦስተኛ ወር በሆነው መጋቢት ሕዝብ ባልተሳተፈበት የቶኪዮ ማራቶን ብርሃኑ ለገሰ ባለድል የሆነበት አጋጣሚ ሳይጠቀስ አይታለፍም። ቀነኒሳ በቀለም በለንደን ግማሽ ማራቶን አስደናቂ ብቃት አሳይቶያሸነፈበት ውድድርም አይዘነጋም። በዚህ ወር የኮቪድ-19 ስርጭት እየተስፋፋ መሄዱን ተከትሎ የዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮናም የመራዘም ዕድል ገጥሞታል። በተመሳሳይ ታላላቅ የሚባሉት የለንደንና የቦስተን ማራቶን ውድድሮችም በዚሁ የካቲት ወር እንደተራዘሙ ታውቋል። እንዲካሄድ በርካታ ጥረቶች ሲደረጉ ከቆዩ በኋላ የውድድር ዓመቱ ታላቅ የስፖርት መድረክ ቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ የተራዘመውም በዚሁ ወር ነበር። ሚያዝያ-ግንቦትበአሜሪካ ኦሪገን በሰኔ ወር ሊካሄድ የነበረው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ቻምፒዮና በ2022 እንዲካሄድ ውሳኔ ላይ የተደረሰው በሚያዝያ ወር ነበር። የሚያዝያ ወር ምናልባትም በአትሌቲክሱ ዓለም ውድድሮችና ክብረወሰኖች የተመዘገቡበት ሳይሆን በርካታ ተጠባቂ ውድድሮች የተራዘሙበትና የተሰረዙበት መጥፎ ትዝታ ጥሎ ያለፈ ነው ማለት ይቻላል። ከቤት ውስጥ ቻምፒዮናው በተጨማሪ በፓሪስ ሊካሄድ የነበረው የአውሮፓ አትሌቲክስ ቻምፒዮና በዚህ ወቅት ለመሰረዝ በቅቷል። ጥቁር አሜሪካዊው ጂዮርጅ ፍሎይድ ሜይዌዘር በፖሊስ በአሰቃቂ ሁኔታ መገደሉን ተከትሎ የዓለም አትሌቲክስ ‹‹የጥቁር ሕይወት ዋጋ አለው›› በሚል በዓለም አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን እንቅስቃሴ የተቀላቀለበት ወቅት ነው። የዓለም አትሌቲክስ አዲስ የኦሊምፒክ ተሳትፎ ማረጋገጫ ሂደትን ይፋ ያደረገውም በዚህ ወቅት ነበር። የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስፖርቱን እያዳከመው በመምጣቱም የዓለም አትሌቲክስ ስፖርቱን ለመደገፍ አዲስ ስትራቴጅክ ፕላን ይፋ አድርጓል። ተጠባቂው የኒውዮርክ ማራቶንም መሰረዙ የተሰማው በዚሁ ወቅት ነው። ሰኔ-ሐምሌ ውድድሮች ለወራት በዓለም ላይ አለመካሄዳቸውን ተከትሎ የስፖርቱ ዓለም በዘርፉ ፖለቲካ ተጠምዶ የቆየበት ጊዜ ነበር። በዚህም ከውድድርና ውጤቶች ይልቅ የተለያዩ ጉዳዮች የስፖርቱ ቤተሰብ መነጋገሪያ ሆነው ሰንብተዋል። በሰኔ ወር ትልቅ መነጋገሪያ ከሆኑ የአትሌቲክስ ጉዳዮች የቀድሞው የማራቶን ባለክብረወሰን ኬንያዊው ዊልሰን ኪፕሳንግ አበረታች ንጥረነገር ተጠቅሞ በመገኘቱ ለአራት ዓመታት ከስፖርቱ መታገዱ ትልቅ ትኩረት ስቦ ነበር። ተቋርጠው የቆዩ የዳይመንድ ሊግ ውድድሮች በወሩ መጨረሻ እየተመለሱ መምጣታቸው ግን በወረርሽኙ ሳቢያ ድብርት ውስጥ ለነበረው የስፖርቱ ቤተሰብ ተስፋ ሆነው ነበር። በዚህም በዙሪክ የተካሄደው የዳይመንድ ሊግ ውድድር ተጠቃሽ ነው። ያም ሆኖ እንደ ቺካጎ ያሉ ታላላቅ የማራቶን ውድድሮች በዚህ ወር ከመሰረዝ አልዳኑም። ወሩ ከመጠናቀቁ አስቀድሞም የዓለም አትሌቲክስ በመሮጫ ጫማዎች ላይ አዲስ ሕግ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። ውድድሮች ከወራት በኋላ በሂደት መመለሳቸውን ተከትሎ ለረጅም ዓመታት ያልተደፈሩ የዓለም ክብረወሰኖች ጭምር ሐምሌ ወር ላይ ተሰብረዋል። በተለይም ዩጋንዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቺፕቴጌ ሞናኮ ላይ በቀነኒሳ በቀለ ለአስራ አምስት ዓመታት ተይዞ የቆየውን የዓለም ክብረወሰን በ12፡35፡36 ማሻሻሉ ያልተጠበቀ የዓመቱ አበይት ክስተት ነበር። ነሐሴ ሐምሌ ወር ላይ የታየው ትልልቅ የዓለም ክብረወሰን የማሻሻል ሂደት በነሐሴም ተደግሟል። በተለይም በኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ኃይሌ ገብረስላሴና ድሬ ቱኔ ለረጅም ዓመታት ተይዘው የቆዩት የአንድ ሰዓት ውድድር የዓለም ክብረወሰኖች መሰበራቸው ያልተጠበቀ ነበር። ትውልደ ሶማሊያዊው የእንግሊዝ አትሌት ሞ ፋራህ የወንዶቹን ክብረወሰን ሲያሻሽል ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ የኔዘርላንድስ አትሌት ሲፈን ሃሰን የሴቶቹን ክብረወሰን መጨበጥ ችላለች። ኬንያዊቷ አትሌት ፒርስ ጂፕቺርቺር በፓራጓይ ግማሽ ማራቶን የርቀቱን የሴቶች ብቻ የዓለም ክብረወሰን ያሻሻለችበት አጋጣሚም አይዘነጋም። የቀድሞው የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ፕሬዚዳንት ሴኔጋላዊው ላሚን ዲያክ በሙስና ቅሌት በፓሪስ ለዓመታት በቁም እስር ቆይተው ፍርድ የተበየነባቸውም በዚሁ ወር ነው። የውድድር ዓመቱን በክብረወሰኖች ታጅቦ ያሳለፈው ስዊድናዊው ምርኩዝ ዘላይ ሞንዶ ዱፕሌንቲስ ከቤት ውጪ ባሉ ውድድሮች በዩክሬናዊው ታሪካዊ አትሌት ሰርጌ ቡካ ተይዞ የቆየውን የዓለም ክብረወሰን በ6 ነጥብ 15 ሜትር ያሻሻለበት አጋጣሚም ትልቅ ነው። የዓለም የማራቶን ክብረወሰን ባለቤት የሆነችው ኬንያዊት አትሌት ብሪጊድ ኮስጌ የለንደን ማራቶንን ለሁለተኛ ጊዜ አሸንፋለች። በዚህ ውድድር ለወራት ሊፋለሙ ቀጠሮ ይዘው ትልቅ ትኩረት የተሰጣቸው ቀነኒሳ በቀለና ኢሉድ ኪፕቾጌ ፍልሚያ አንድ ቀን ሲቀረው ቀነኒሳ በጉዳት ከውድድር ውጪ መሆኑ አሳዛኝ ነበር። ያም ሆኖ የርቀቱ የክብረወሰን ባለቤትና ባለፉት ዓመታት ሽንፈት ያልገጠመው ኪፕቾጌ ባልተጠበቀው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሹራ ቂጣታ ከመሸነፉ ባሻገር ሰባተኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ አስገራሚ ነበር።ዩጋዳዊው ቺፕቴግ ቀነኒሳ ለአስራ ስድስት ዓመታት ይዞት የቆየውን የአስር ሺ ሜትር የዓለም ክብረወሰን ቫሌንሲያ ላይ ሲያሻሽል ኢትዮጵያዊቷ ለተሰንበት ግደይ በጥሩነሽ ዲባባ ለአስራ ሁለት ዓመታት የተያዘውን የአምስት ሺ ሜትር የዓለም ክብረወሰን ማሻሻሏ የውድድር ዓመቱ ግንባር ቀደም አበይት ክስተት ሆኖ አልፏል። ኬንያዊቷ ፒርስ ጂፕቺርቺር በፖላንድ ጊዲኒያ የዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮና የርቀቱን የሴቶች ብቻ የዓለም ክብረወሰን መስበሯም ወሩን አስደናቂ አድርጎት አልፏል። መስከረም -ታህሳስ የ2023 የአውሮፓ አትሌቲከስ ቻምፒዮናን ቱርክ ኢስታንቡል ላይ እንድታዘጋጅ ዕድል ባገኘችበት መስከረም ወር በአየርላንድ ደብሊን ሊካሄድ የነበረው የ2020 የአውሮፓ አገር አቋራጭ ቻምፒዮና ከመሰረዙ በቀር በአትሌቲክሱ ዓለም ብዙም አነጋጋሪ ጉዳዮች ሳይፈጠሩ አልፈዋል። ከዚያ በኋላ ባሉት ሦስት ወራት ግን የዓለማችን ፈጣኑ አትሌት ጃማይካዊው ዩዜን ቦልት እንዲሁም የረጅም ርቀት ንግስቷ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ በእውቁ የእንግሊዝ የአትሌቲክስ መፅሔት የምን ጊዜም ምርጥ አትሌት ተብለው መሰየማቸው አብይ ጉዳይ ነበር። ቬንዙዌላዊቷ አትሌት ዩሊማር ሮጃስ እንዲሁም ስዊድናዊው ሞንዶ ዱፕሌንቲስ የዓመቱ ምርጥ አትሌቶች ተብለው ተሸልመዋል። ኬንያዊው ኪቢዎት ካንዲም በዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮና ሲያሸንፍአዲስ\nዘመን ታህሳስ 23/2013", "passage_id": "fa5997abb25501d92753abc953d0c38c" } ]
7ce6c012eb7aa2a7b8eff02d931ac55e
c97201fbb4638ada9cefa378d21a4d0d
ምክር ቤቱ አቅጣጫና ውሳኔ እንደሚያሳልፍ ይጠበቃል
ብርሃን ፈይሳ አዲስ አበባ፡- ብሄራዊ የስፖርት ምክር ቤት ነገ የመጀመሪያ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን እንደሚያከናውን ተገለጸ። በጉባኤው ላይም አቅጣጫዎችን እንደሚሰጥና ውሳኔዎችንም እንደሚያስተላልፍ ይጠበቃል። የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን በሰጠው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ብሄራዊ የስፖርት ምክር ቤቱ ባለፈው ዓመት ህዳር 4 ቀን 2012 ዓ.ም መስራች ጉባኤውን ማካሄዱ ይታወሳል፤ ይሁን እንጂ ኮቪድ 19 በኢትዮጵያ መከሰትን ተከትሎ የመጀመሪያ ጠቅላላ ጉባኤውን በተያዘለት ወቅት ማካሄድ አልተቻለም። በመሆኑም ነገ የመጀመሪያ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ያከናውናል። በጉባኤው ላይም የጉባኤው አባላት የሆኑት፤ የክልልና ከተማ አስተዳደር ርዕሳነ መስተዳድሮች ከንቲባዎች፣ ከዘጠኝ ሚኒስትር መስሪያ ቤቶች የተወጣጡ ሚኒስትሮች፣ የስፖርት ኮሚሽነሮች፣ የሃገር አቀፍ ስፖርት ማህበራት አመራሮች፣ የስፖርት ተቋማት እንዲሁም ለስፖርት ጉልህ ሚና ያላቸው የክብር እንግዶች ይገኛሉ። የጉባኤው አጀንዳዎችም የመስራች ጉባኤውን አጀንዳ ማጽደቅ፣ በወቅቱ የተሰጡ አቅጣጫዎችን አፈጻጸም መገምገም፣ በቀጣይ በትኩረት የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፣ የ10 ዓመቱ መሪ እቅድና የ2013 በጀት ዓመት እቅድ እንዲሁም ልዩ ልዩ መመሪያዎችን አቅርቦ ማጸደቅ የሚሉት መሆናቸው ተጠቁሟል። አጀንዳዎቹን ተከትሎ አቅጣጫ እንደሚሰጥና ውሳኔዎችም እንደሚያስተላለፉ ይጠበቃል።የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር ጉባኤው ትኩረት የሚሰጥበት አጀንዳም ምክር ቤቱ በመስራች ጉባኤ ወቅት ያስቀመጣቸው ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች አፈጻጸምን በዝርዝር ተመልክቶ መገምገምን የተመለከተ መሆኑን አስታውቀዋል። የሃገሪቷ ስፖርት መሰረታዊ ችግሮችና መፍትሄ የሚል ጥናት በማካሄድ በተዘጋጀው የሪፎርም ሰነድ ምክር ቤቱ ተወያይቶ በዝርዝር እንዲከናወኑ አቅጣጫ የሰጣቸው ጉዳዮች ላይ ግምገማ የሚያካሂድም መሆኑን ተናግረዋል። እንደ ኮሚሽነሩ ገለጻ፤ከአቅጣጫዎቹ መካከል አንዱ ባለድርሻ አካላትን በማወያየት ሰነዱ እንዲዳብር ነበር፤ ይህም እስከ ታችኛው እርከን በመውረድ የማዳበር ስራው ተከናውኗል። ሰነዱ ሲዘጋጅ የተቀመጡት ምክረ ሃሳቦች በእቅድ እንዲካተቱ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በ10 ዓመቱ ስትራቴጂክ እና የዓመቱ እቅድ ላይ እንዲካተት ተደርጓል። አሰራሮችን ከመፈተሽና አዳዲስ የአሰራር ማኑዋሎችን ከመፍጠር ረገድም የስፖርት ፖሊሲውን የማሻሻል ስራ ተጀምሯል፣ ሃገሪቷ የሌላት የስፖርት ህግም እየተረቀቀ ነው፣ ሃገር አቀፍ የስፖርት ማህበራት የሚመዘኑበት ስታንዳርድ የማዘጋጀት፣ የማዘውተሪያ ስፍራዎች ስታንዳርድና የስፖርት ፈንድ ሰነድ ማዘጋጀት እንዲሁም የስፖርት መመሪያ በማሻሻል ረገድ ያሉትን ፈትሾ በማስተካከልና የሌሉትን አዳዲስ በማዘጋጀት የተሳካ ስራ ማከናወን ተችሏል። ተጠናቀው ወደ ስራ የገቡ መኖራቸውንና ሌሎች ደግሞ እርከኑን ጠብቆ በሌሎች አካላት መጽደቅ ያለባቸውም በሂደት ላይ ይገኛሉ።የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን፣ የስልጠና ማዕከላትና የስፖርት ቁሳቁስን በሚመለከትም ትልልቅ ግንባታዎች በተያዘላቸው ጊዜና በጥራት እንዲጠናቀቁ እየተሰራም መሆኑም በመግለጫው ተጠቁሟል። ከጥርጊያ ሜዳ ጀምሮ በየአካባቢው ያሉ ማዘውተሪያዎችም የባለቤትነት ማረጋገጫ እንዲኖራቸውና እጥረት ባለባቸውም ተጨማሪ እንዲያገኙም እየተደረገ ነው። ያሉት የስልጠና ማዕከላትም በሙሉ አቅማቸው እንዲሰሩ የማድረግ ስራ እየተሰራ ከሚሽነሩ ጠቅሰው፣ በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ከማስፋፋት አኳያ ያለው ተነሳሽነትም መልካም የሚባል መሆኑን ኮሚሽነሩ ይጠቁማሉ። የህዝብ ተሳትፎን በሚመለከትም ኮቪድን እንደ ምክንያት በመጠቀም በህብረተሰቡ ዘንድ መነሳሳትን በመፍጠር ረገድ የተሻለ ጅማሮ ታይቷል ብለዋል። በጉባኤው ላይ በህብረተሰቡ የስፖርት ተሳትፎ ፍትሃዊነትና ተደራሽነት ላይም ውይይት ይደረጋል ተብሏል። በስፖርት አደረጃጀት ላይ ሕዝባዊ አካሉ በምን መልክ ሊደራጅ ይገባዋል የሚለውም ሌላው ውይይት የሚደረግበት መሆኑ ተጠቁሟል። በመግለጫው ላይ እንደተመለከተው፤ በ2011 ዓም አሳሳቢ የነበረው የስፖርታዊ ጨዋነት መጓደልም በወረርሽኙ መከሰት ውድድሮች እስከተቋረጡ ድረስ ውጤታማ ስራዎችን ማከናወን ተችሏል። ኮቪድ 19 በኢትዮጵያ ከተከሰተ ወዲህም በስፖርቱ ላይ ያስከተላቸው ጉዳቶችን እና ቫይረሱ እያለ እንዴት ወደ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ መገባቱን ተከትሎ ክትትል ለሚያደርገው ኮሚቴ አቅጣጫ የሚሰጥም ይሆናል። በቀጣይ የሚካሄዱ ሃገር እና ዓለም አቀፍ ውድድሮችን በሚመለከትና ለሚቀጥለው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ በምን መልክ ውጤት ማስመዝገብ ይቻላል በሚለው ላይም ምክር ቤቱ ይመክራል።
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=38365
[ { "passage": "የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌደሬሽን ምክር ቤት የጋራ መክፈቻ ስነ ስርዓት ሰኞ መስከረም 26/2012 ይካሔዳል። አምስተኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌደሬሽን ምክር ቤት አምስተኛ ዓመት የስራ ዘመን የጋራ መክፈቻ ስነ ስርዓት የኢፌዲሪ ፕሬዘዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በተገኙበት ይጀመራል።ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ከፋና ብሮድካስቲንግ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ በ2011 በጀት ዓመት በዋና ኦዲተር አማካኝነት ኦዲት ግኝት የታየባቸውን ድርጅቶች የተጓደሉ ስርኣቶችን ፈትሾ በማስተካከል አገራዊ ሀብቱ በትክክለኛው መንገድ ጥቅም ላይ መዋሉን ለማረጋገጥ በትኩረትእየተሰራ እንደሆነ አስታውቀዋል።ምክር ቤቱ በአራተኛ ዓመት የስራ ዘመኑ ከዚህ ቀደም ባልተለመደ መንገድ በበርካታ ተቃውሞ እና ድምፅ ተኣቅቦ ውሳኔዎች መፅደቃቸው የዲሞክራሲ ስርኣቱ እየጎለበተ የመምጣቱ ማሳያ እንደሆነ አፈጉባኤው ገልፀዋል።", "passage_id": "7e9367e51b5a942f7a68ae5970e3d96e" }, { "passage": "የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የካቲት 5/2012  አስቸኳይ ጉባኤውን የሚያደርግ ሲሆን  ምክር ቤቱም የኤክሳይዝ ታክስ እንዲሁም የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የቀረበ ረቂቅ አዋጅን እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል፡እሁድ ከየካቲት 1/2012 ጀምሮ  የአንድ ወር እረፍት የነበሩት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ከአራት ቀን በኋላ ለአስቸኳይ ጉባኤ የተጠሩ ሲሆን በጉባኤው ላይም በ10 አጀንዳዎች ላይ ውሳኔዎችን ያሳልፋሉ ተብሎም ይጠበቃል፡፡ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትን ህጋዊ ሰውነት ለመስጠት የቀረበ ረቂቅ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መምራት፣  የኤክሳይዝ ታክስ፣ የፌደራል የአስተዳደር ሥነ ሥርዓት፣ በውጭ አገራት ለተሰጡ የግልግል ዳኝነት ውሳኔዎች እውቅና የመስጠት እና የመፈጸም ስምምነትን ለማጽደቅ የሚቀርቡ ረቀቅ አዋጆችን ያጸድቃሉ ተብሎም ይጠበቃል፡፡ ", "passage_id": "a678af4eb2fff6d439dc90fda21e4a7e" }, { "passage": "የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ከማግሰኞ ጥር 7 ቀን 2011 ዓም ጀምሮ መደበኛ ስብሰባውን እንደሚያካሂድ የኢህአዴግ ምክር ቤት ጽ/ቤት ገልጿል፡፡ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው በ11ኛው ድርጅታዊ ጉባዔ የተቀመጡ አቅጣጫዎች አፈጻጸም፤ በሀገራችን ወቅታዊ ሁኔታ እና የለዉጥ እንቅስቃሰ ሂደት፤ እንዲሁም የድርጅት እና የመንግስት የስራ አፈጻጸም ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ በጥልቀት ተወያይቶ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ እንደሚጠበቅም የኢህአዴግ ምክር ቤት ጽ/ቤት ለዝግጅት ክፍላችን በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡  ", "passage_id": "4b7fdf7e2e47f9981507242fa6706281" }, { "passage": "የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ከነገ ጀምሮ ስብሰባውን ያካሂዳልየኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር(ኢህአዴግ) ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ከነገ ነሓሴ 2 ቀን 2011 ም ጀምሮ ስብሰባውን የሚካሂድ ሲሆን፤ በተለያዩ አጀንዳዎች እንደሚመክር ይጠብቃል፡፡ኮሚቴ የድርጅት ስራዎች አፈጻጸም እና በሌሎች ሀገራዊ ወቅታዊ አጀንዳዎች ላይ ውይይት እንደሚያካሄድ የኢህአዴግ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው የድርጅት ስራዎችና ወቅታዊ ሁኔታዎችን በጥልቀት ከገመገመ በኃላ ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል::", "passage_id": "5ebc53ff254f396ed5484b25c2607cef" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 30 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 18ኛ አስቸኳይ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። የምክር ቤቱ ውሳኔዎች እንደሚከተለው ቀርበዋል፦ 1. ምክር ቤቱ በመጀመሪያ የተወያየው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ሥርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠር እና የሚያስከከትለውን ጉዳት ለመቀነስ በወጣው ረቂቅ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ላይ ነው። ኮቪድ-19 ክትባትም ሆነ መድሃኒት የሌለው፣ በፍጥነት የሚዛመት እና በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ሰብዓዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ ቀውስ እያስከተለ የሚገኝ ዓለም ዓቀፍ ወረርሽኝ መሆኑን በመገንዘብ፤ የቫይረሱ ስርጭት በተለያዩ ሃገራት በሚልዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን እያጠቃ እና ለብዙ ሺዎች መሞትም ምክንያት መሆኑ እንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ሲፈጠር በተለመደው የጤና አጠባበቅ ዘዴ እና አካሄድ የዜጎችን ደህንነት ማስጠበቅ አዳጋች በመሆኑ፥ በሃገራችን ተጨባች ሁኔታም የቫይረሱ ስርጭት እና በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ችግሮችን እያስከተለ የሚገኝ ሲሆን ለነዚህ ችግሮች ምላሽ ለመስጠት የአስችኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጅ አስፈላጊ ሆኗል። በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ሕገ-መንግሥት እንዲህ ዓይነት ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለማወጅ የሚያስችል ሥርዓት በአንቀጽ 93 ተደንግጓል። በአንቀጽ 93 (1) (ሀ) መሰረት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ መነሻ ከሚሆኑ ሁኔታዎች አንዱ “የሕዝብን ጤንነት አደጋ ላይ የሚጥል በሽታ መከሰት” መሆኑም ሰፍሯል። የኮቪድ-19 የሕዝብን ጤንነት በከፍተኛ ደረጃ አደጋ ላይ የሚጥል በሽታ ከመሆኑም በላይ የአለም ጤና ድርጅት አለም አቀፍ ወረርሽ መሆኑን ማወጁን ተከትሎ ከ70 የማያንሱ አገሮች ወረርሽኙን ለመቆጣጠርና ህዝቦቻቸውን ለመታደግ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጥተዋል። በአገር ደረጃ ይህን ወረርሽኝ ለመከላከል፣ ለመቆጣጠር እና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ የሚወሰዱ እርምጃዎችን ለማሳለጥ እና ውጤታማ ለማድረግ ሲባል ከተለመደው አሠራር ወጥቶ በልዩ ሁኔታ መንቀሳቀስ የሚያስፈልግ በመሆኑ የአስቸኳይ ጊዜ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል። ምክር ቤቱን በረቂቅ አዋጁ ላይ በስፋት ከተወያየ በኋላ ጥቂት ማስተካከያዎችን በማከል ከዛሬ 29/07/2012 ዓም ጀምሮ ስራ ላይ እንዲውል ወስኗል። በተጨማሪም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በሚኒስትሮች ምክር ቤት የታወጀው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በስራ ላይ ባለበት ወቅት በመሆኑ በህገ መንግስቱ አንቀጽ 93(2(ሀ)) መሰረት በአስቸኳይ ለምክር ቤቱ እንዲላክ ጭምር ተወስኗል። 2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው ከአለም አቀፍ ልማት ማህበር ጋር የተደረጉ 3 የብድር ስምምነቶች ላይ ነው፡። የመጀመሪው ለኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ አስቸኳይ ጊዜ ምላሽ ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል የ41 ነጥብ 3 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ብድር ስምምነት ሲሆን፥ ሁለተኛው ለአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል ክፍለ አህጉራዊ ኢንቨስትመንት ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል የ54 ነጥብ 9 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ብድር ስምምነት ነው። ሶስተኛው ለሁለተኛው የኢትዮጵያ የዕድገት እና የተወዳዳሪነት የልማት ፖሊሲ ፋይናንስ ፕሮግራም ማስፈፀሚያ የሚውል 1346 ነጥብ 4 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ሲሆን፥ ምክር ቤቱም ሁሉም ብድሮች 0 ነጥብ 5 በመቶ ወለድ የሚታሰብባቸው፣ የ6 ዓመት የእፎይታ ያላቸው እና በረጅም ጊዜ ተከፍለው የሚጠናቀቁ በመሆናቸው በአገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያስከትሉት ጫና የሌለ መሆኑን እና የኮቪድ 19 ቫይስ ወረርሽኝን ለመከላከል ለሚደረገው አገራዊ ርብርብ ፋይዳው የላቀ መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት በሙሉ ድምጽ አዋጆቹ ይጸድቁ ዘንድ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ ወስኗል።", "passage_id": "9ec044c32e6f46efe41d9a7667c3f41e" } ]
8e4190b129f67d7639b1a6de7b8363b7
f90f3d408a2558dc0ea944a6e2cdb6f2
የከተማ አቀፍ አካል ብቃት እንቅስቃሴ ተመልሷል
ቦጋለ አበበ ከተማ አቀፍ የአካል ብቃት ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ አዲሱ ለሚ ኮራ ክፍለ ከተማ በደማቅ ሁኔታ በይፋ ተጀምሯል። የአካል ብቃት እንቅስቃሴው ‹‹ለሀገሬ ሰላም ዘብ እቆማለሁ፤ ለመከላከያ ሰራዊት ቅድሚያ እሰጣለሁ›› በሚል መሪ ቃል በየካ አባዶ የጋራ መኖሪያ ቤቶች አደባባይ ከትናንት በስቲያ የተካሄደ ሲሆን በርካታ ቁጥር ያላቸው የአካባቢው ነዋሪዎችም ተሳታፊ ሆነዋል ። በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የመንግሥት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር አባይ፣ ‹‹በስፖርት የተገነባ ኃይል የትኛውንም ጠላት መመከት ይችላል፤ በመሆኑም በየትኛውም አካባቢ በተገኘው ቦታ ሁሉ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በማድረግ እራሳችንን ከበሽታ ልንከላከል ይገባል›› ብለዋል። ለዚህም ከተማ አስተዳደሩ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል። ‹‹መከላከያችን ባደረገው የሰላም ማስከበር ተልዕኮ በአጭር ጊዜ ውስጥ ድል የተቀዳጀው በስፖርት የተገነባ ስለሆነ ነው፣ መከላከያችንን እያሰብን ሁሌም ስፖርትን ባህላችን ልናደርግ ይገባል›› በማለትም አቶ ጃንጥራር  ተናግረዋል::የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ኤሊያስ ሽኩር በበኩላቸው፣ የማህበረሰብ አቀፍ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች በፍታሐዊነት ተደራሽ እና ባህል እስኪሆን ድረስ ከሚመለከታቸው አካላት በጋራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል::በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ለረጅም ወራት ተቋርጦ ከትናንት በስቲያ የተጀመረው ከተማ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መርሃ ግብር በየሳምንቱ በአስራ አንዱም የአዲስ አበባ ክፍለ ከተሞች በወጣው መርሃ ግብር መሠረት ለአንድ ወር የሚቀጥል ሲሆን በሚቀጥለው ሳምንት በየካ ክፍለ ከተማ እንደሚካሄድ ታውቋል።በአካል ብቃት ስፖርታዊ እንቅስቃሴው ላይ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር በላይ ደጀን፣ የለሚ ኩራ፣ የቦሌና የየካ ክፍለ ከተሞች ዋና ስራ አስፈፃሚዎች እንዲሁም በርካታ ቁጥር ያላቸው የየካ አባዶ የጋራ መኖሪያ ቤት ነዋሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽን የከተማዋን ሁለንተናዊ የስፖርት ልማት፣ የስፖርት ንቅናቄ ፣ የስፖርት ተሳታፊነትና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝ የተገለጸ ሲሆን ስፖርት ለሰላም፣ ለአንድነት፣ ለፍቅር፣ ለጤንነት፣ ለመቻቻል፣ ለአብሮነት፣ ለልማትና ለትብብር ያለው ፋይድ ታላቅ መሆኑን ስፖርት በተግባር እያሳየ እንደሚገኝም ተጠቁሟል፡፡አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 20/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=38442
[ { "passage": "ስፖርት\nበስርዓት የሚመራ ውብ ክዋኔ መሆኑ ለተወዳጅነቱ በምክንያትነት ይጠቀሳል። ከአደረጃጀቱ ጀምሮ የትኛውም ዓይነት ስፖርታዊ እንቅስቃሴ የራሱ የሆነ ሂደትና ስርዓት አለው። ይህ ስርዓት ተጥሶ በዘፈቀደ ሲከወን ደግሞ የተወዳጅነቱን ያህል በአደገኛ አካሄድ ላይ ሊገኝ ይችላል። በኢትዮጵያ ስፖርት አደረጃጀት የሚስተዋለውም ይኸው ነው። የተቀመጠለትን አቅጣጫ በመሳቱም፤ ስልጠናው፣ ሰልጣኞች፣ ሃብት፣ ጉልበት፣ ጊዜ፣ … ለብክነትና ለአሰራር ድርርቦሽ ተዳርገዋል። ለውጤት ማጣትም የራሱን ሚና ሲጫወት ቆይቷል። በአገሪቷ ስፖርቱን በበላይነት የሚመራው የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን፤ የታዳጊ ማሰልጠኛ ፕሮጀክት፣ የስፖርት ማሰልጠኛ ማዕከላት፣ አካዳሚዎች፣ ክለቦች እንዲሁም ብሄራዊ ቡድን የሚል መስመር በመዘርጋት እየሰራ መሆኑ ይታወ ቃል። ነገር ግን ይህ አሰራር በቅብብሎሽ ከመከናወን ይልቅ ሁሉም በራሱ መንገድና አካሄድ ሲመራው ቆይቷል። ይህም ለብክነት ምክንያት ሲሆን፤ ማሰልጠኛ ማዕከላቱ ሚናቸው ተመሳሳይ በመሆኑ የሰልጣኞች ሽሚያ እና የእርስ በርስ ቅሬታ ውስጥ እንዲገቡ ሲያደርጋቸው ቆይቷል። ይህንን የተመለከተው ኮሚሽኑ አገር አቀፍ ስፖርት ስልጠና ጣቢያዎች፣ ማዕከላትና አካዳ ሚዎች አደረጃጀትና ስርዓት መተግበሪያ ረቂቅ ሰነድ በማዘጋጀት፤ ግብዓት የሚሆኑ ሃሳቦችን በመሰብሰብ ላይ ይገኛል። ረቂቁ አምስት ክፍ ሎች ያሉት ሲሆን፤ የመጀመሪያው ክፍል በማዕከ ላትና ፕሮጀክቶች መዋቅራዊ አደረጃጀት ላይ ትኩረቱን ያደርጋል። ቀጣዩ ክፍል ምዘና እና ውድድርን የሚመለከት ሲሆን፤ ሦስተኛው የሰል ጣኞችን የቅብብሎሽና ዝውውር፣ አራተኛው የባለቤትና ባለድርሻ አካላትን ተግባርና ኃላፊነት እንዲሁም በመጨረሻው ክፍል የክትትል፣ ድጋፍና ግምገማ ስርዓትን የሚያጠቃልል ነው። የሰነዱ አስፈ ላጊነትም፤ በየደረጃው በሚገኙ ፕሮጀክቶች፣ ማሰል ጠኛ ማዕከላት፣ አካዳሚዎችና ክለቦች መካከል ወጥ እና ቅንጅታዊ አሰራርን መዘርጋት ነው። በዚህም መሰረት ለሁሉም የየራሳቸው የሆነ የአሰራር ስርዓት ተበጅቶላቸዋል። በየአካባቢውና ትምህርት ቤቶች ከ13ዓመት በታች (11እና12) በሆነ ዕድሜ ስልጠናው የሚጀመር ሲሆን፤ በዚህም በርካታ ፍላጎት ያላቸው ታዳጊዎችን በተመሳሳይ ዕድሜ ማግኘት ይቻላል። ሁለት ዓመታትን በሚሸፍነው በዚህ ስልጠናም በዋናነት ሥራው የተሰጥኦ ፍለጋ ይሆናል። በቀጣይም ታዳጊዎቹ በ15 ዓመት በታች (13እና14) የስልጠና ጣቢያዎችን በመቀላቀል ለሁለት ዓመታት ይሰለጥናሉ። በዚህ የተሰጥኦ ልየታ ወቅትም ከአሰልጣኞቻቸው እገዛ ባሻገር በምዘና ያላቸውን ተሰጥኦ ለመለየት ይቻላል። በ17\nዓመት በታች (15እና16) ወደ ስልጠና ማዕከላት በመግባት የተለየውን ተሰጥኦአቸውን ማልማት የሦስት ዓመታት ሥራ ይሆናል። በዚህ ወቅት የስልጠና ጫናን የመሸከም ብቃታቸው የሚ መዘን ሲሆን፣ በማዕከላት መካከል የሚደረገውን ውድድር ጨምሮ በአገር አቀፍ ሻምፒዮናዎች እንዲሁም በዕድሜ በሚካሄዱ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይም ተሳታፊ ይሆናሉ። ይህንን ሲያጠናቅቁ ወደ አካዳሚዎች የሚገቡ ሲሆን፤ ከ3- 4ዓመታት በሚዘልቀው ቆይታቸው ለኦሊምፒክ ብቁ እንደሚሆኑ ስለሚታመን ክለቦችን እንዲሁም ብሄራዊ ቡድኖችን ይቀላቀላሉ። የዚህ\nሂደት ባለቤቶችም የተለዩ ሲሆን፤ ከ13-17ዓመት በሚዘልቀው የስልጠና ወረዳ እና ዞኖች ኃላፊነት አለባቸው። የስፖርት ማሰልጠኛ ማዕከላትን በባለቤትነት ክልሎች ሲያስተዳድሩ፤ አካዳሚዎች ደግሞ በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ስር ይገኛሉ። የትምህርት ሚኒስትር፣ የጤና ሚኒስትር፣ ኦሊምፒክ ኮሚቴ፣ ወላጅ፣ አሰልጣኝ፣ ክለብ፣… ደግሞ ባለድርሻ አካላት እንደመሆናቸው ሥራውን በቅንጅት ያከናውናሉ። በዚህ ሂደትም ለዓመት ለሦስት ጊዜያት የመስክ ምልከታ፣ የብቃት ምዘና፣ ዓውደ ጥናት፣ ወቅታዊ ሪፖርት እና የዳሰሳ ጥናቶች እንደሚካሄድም ሰነዱ ይጠቁማል። ሰነዱ ገለጻ ከተደረገበት በኋላም ከተሳታፊዎች በርካታ አስተያየት ተሰጥቷል። የስልጠና ቁሳቁስ፣ የምግብ አቅርቦትና የላብ መተኪያ ላይ ቢታሰብበት፣ ሰልጣኞች ከክለቦች ብቻም ሳይሆን ከማናጀሮች ጋር በምን መልኩ ይሰራሉ፣ ወደ ውጭ አገራት ክለቦች የሚኖራቸው ዝውውር እንዴት ይሆናል፣ ስልጠናው ሳይጠናቀቅ ወደ ክለቦች የሚያደርጉት ዝውውር፣ በምልመላ ላይ መስፈርት ቢቀመጥ፣ እንደየ ስፖርት ዓይነቱ የምልመላ ዕድሜው ቢቀነስ፣ የስልጠናውን ጊዜ በዕድሜ ከመገደብ ይልቅ በሰዓት ማድረግ ቢቻል፣ ማስተግበሪያውን ወደ ሥራ ለማስገባት መመሪያ ማዘጋጀት አስፈላጊ መሆኑ፣ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የስፖርት ማሰልጠኛ ሥፍራዎች አጠቃቀምን በተመለከተ፣ ማዕከላት ትኩረታቸውን በአትሌቲክስ ላይ ያደረጉ እንደመሆኑ የሌሎች እጣፋንታ ምን ይሆናል፣ እንደየ ደረጃው የአሰልጣኞች ደረጃ ቢወሰን፣… የሚሉ ሃሳቦች ተንጸባርቀዋል። በኢፌዴሪ\nስፖርት ኮሚሽን የትምህርትና ስልጠና ዳይሬክተር ሲሳይ ሳሙኤል፤ ለሰነዱ ግብዓት የሚሆኑ አስተያየቶችን ማሰባሰቡ ቀጣይነት ያለው መሆኑን ይጠቁማሉ። ክልሎች፣ ፌዴሬሽኖች እን ዲሁም የሚመለከታቸው አካላት በአጠቃላይ አስተያየታቸውን በመስጠት ረቂቁ ዳብሮ ወደ ተግባር ይገባል። ይህ ሰነድ በትክክል ወደ ሥራ የሚለወጥ ከሆነም በስልጠናውና በአገሪቷ ውጤት ላይ ትልቅ ድርሻ እንደሚኖረውም እምነታቸው ነው። ሰነዱ ሲዘጋጅ በአገሪቷ ያሉትን የማሰልጠኛ ማዕከላትና አካዳሚዎች ልምድ እንዲሁም ጠን ካራና ደካማ ጎኖች በመያዝ ነው። ከዚህም ባሻገር በዘርፉ የተሻለ ተሞክሮ ካላቸው አገራት እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ማዕከል እና አካዳሚ ለመባል መስፈርቶች በመነሻነት ተይዘዋል። አሰራሩ በወጥ አደረጃጀት፣ ደረጃ እና በተመሳሳይ አቅርቦት የሚካሄድ እንደመሆኑም በአንድ ቀን አዳር ይሳካል ለማለት እንደማያስደርም ዳይሬክተሩ ይጠቁማሉ። ነገር ግን ማዕከላቱ በምን መልኩ መስራት እንደ ሚገባቸው ራሳቸውን ይመለከቱበታል፤ እንዲሁም ከዚህ በኋላ የሚከፈቱ የማሰልጠኛ ማዕከላት እንደ መስፈርት በመሆን የሚያግዛቸው መሆኑን አስረድተዋል። የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚ ሽነር ጌታቸው ባልቻ፤ ሰነዱ በዘርፉ በምን መልኩ ውጤታማ መሆን ይቻላል የሚለውን ለማመላከት የተዘጋጀ መሆኑን ይገልጻሉ። ከሰነዱ\nየሚጠበቀውም፤ ማዕከላት ተሳስረው ውጤታማ ሥራ በማከናወን በዓለም አቀፍ ደረጃ ውጤት ማግኘት ነው። በስፖርት ላይ በሚሰሩ አካላት 50ሺ እና ከዚያ በላይ የሆኑ ስፖርተኞች ሰልጥነዋል ይባላል፤ የሚታየው ግን ለአብነት ያህል በእግር ኳስ ስፖርት11 ተጫዋቾችን ማፍራት አለመቻሉን ነው። በርካታ የማሰልጠኛ ጣቢያዎችና ማዕከላት ኖሮን ሰልጥነው የሚወጡት ውጤት ማስመዝገብ ካልቻሉ አሰራሩንና አደረጃጀቱን ቆም ብሎ መመልከት አስፈላጊ ይሆናል። ይህ ሰነድ ዳብሮ ወደ ተግባራዊነት እንዲገባም ህግና መመሪያ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች እንደሚኖሩም ምክትል ኮሚሽነሩ ይጠቁማሉ።አዲስ\nዘመን መጋቢት 16/2011ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "47b43da4d0a7ec84c955c2256ff82e36" }, { "passage": " ብርሃን ፈይሳ አዲሱ የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ከወራት በፊት ራሱን ችሎ በክልል ደረጃ መቋቋሙ ይታወቃል:: በዚህ ሂደትም እንደ አዲስ በመዋቀር ላይ ካሉ ዘርፎች መካከል አንዱ ስፖርት ነው:: ክልሉ በተለይ በእግር ኳስ የተሻለ አቅም ያለው እንደመሆኑ የክልሉን የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ምስረታና እስካሁን የተጓዘባቸውን በተመለከተ አዲስ ዘመን ጋዜጣ ከሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ብሩ ወልዴ ጋር ቆይታ አድርጓል:: የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ወደ ስራ ከገባ ስድስት ወራትን አስቆጥሯል፤ ፌዴሬሽኑም ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እውቅና አግኝቶ ወደ ስራ ገብቷል:: በመሰረታዊነትም የ2013 ዓ.ም እቅድን በማዘጋጀት ስራው የተጀመረ ሲሆን፤ በቅድሚያ የሚከናወኑ ተግባራትም ተለይተዋል:: በዚህ መነሻነትም የቢሮና ሌሎች የአደረጃጀት፣ የሰው ኋይልን ማሟላትን የመሳሰሉ ስራዎች እየተከናወኑ ነው:: በተጨማሪም በክልሉ እየተካሄደ ያለውን የሴቶች ፕሪምየር ሊግ በመደገፍና ከብሄራዊው ፌዴሬሽን ጋር በቅንጅት በመስራት ላይ ይገኛል:: በዚህ ዓመት ለመስራት ከታቀዱ ስራዎች መካከል ዋነኛው ታዳጊ ወጣቶችን በፕሮጀክት በመያዝና ልዩ ትኩረት በመስጠት ማጠናከር ነው:: ሃዋሳ ከተማ፣ በንሳ፣ ዳራ እና አለታ ጩኮ የተለዩት ስፍራዎች ሲሆኑ፤ ከ13-16 ዓመት ያሉ ታዳጊዎችን ለማሰልጠንም ነው የታቀደው:: በእነዚህ አካባቢዎች የፕሮጀክት እንቅስቃሴ ካለ ለማጠናከር የቴክኒክና የግብዓት ድጋፍ እንዲሁም አሰልጣኞች እንዲጠናከሩ ይደረጋል::ለፕሮጀክቶቹ የሚያስፈልገውን ሃብትና\nድጋፍ እየተሰባሰበ ሲሆን፤\nአንዱን ፕሮጀክት ሊደግፍ\nየሚችል አካል ተገኝቷል::\nበተለይ በኢንዱስትሪው አካባቢ\nያሉ ባለሃብቶችና በኢንቨስትመንት\nላይ የተሰማሩ ሰዎች\nድጋፍ እንዲያደርጉም እየተሰራ\nነው:: በመሆኑም ሁለቱን\nበዚህ  ዓመት\nስራ ለማስጀመር ታቅዷል::\nይርጋለም ላይም የታሰበ\nሲሆን ቀስ በቀስም\nበየአካባቢው ቁጥሩ ይጨምራል::\nሌላው በክልሉ ያሉ ሁለት የፕሪምየር ሊግ ተሳታፊ ክለቦች (ሃዋሳ ከተማ እና ሲዳማ ቡና እግር ኳስ ቡድኖች) መደገፍ ነው:: ከስፖርት ቤተሰቡም ጋር በተያያዘ የደጋፊ ማህበራትን ማጠናከር ሌላኛው ስራ ሲሆን፤ የሃዋሳ ከተማ ክለብ ደጋፊዎች ማህበር በአዲስ መልክ እየተደራጀ ይገኛል:: በጥሩ ሁኔታ ላይ የሚገኘውን የሲዳማ ቡና ክለብ እግር ኳስ ደጋፊ ማህበርም ይበልጥ ለማጠናክር ይሰራል:: በዓመቱ ልዩ ትኩረት ከሚሰጣቸው ተግባራት መካከል በክለቦቹ ያሉትን ተግዳሮቶች በመለየት የሚመለከተው አካል እንዲያውቀው በማድረግ መፍትሄ መስጠት ነው:: ለአብነት ያህል በሁለቱ የሊጉ ክለቦች ውስጥ ባሉ ታዳጊ ቡድኖች ላይ ውስንነቶች ይታያሉ:: ታዳጊዎቹ ወደ ዋናው ክለብ እንዲያድጉ ቢደረግም ጨዋታዎች ላይ ግን ሲሰለፉ አይስተዋልም:: ብቃቱ እና ተሰጥኦው እያላቸውም ውጤታማ ሲሆኑ አይታይም::በመሆኑም በቴክኒክ አካላት ጉዳዩ በመጠናት ላይ ይገኛል:: በሲዳማ ክልል ያለውን\nየእግር ኳስ አቅም\nማጥናት፣ ሁለቱ ክለቦች\nጋር ያሉትን ችግሮች\nመለየት እንዲሁም የክለቦቹ\nስራ አመራር ቦርድ\nአውቆ ትኩረት እንዲሰጣቸው\nማድረግም አንዱ ነው::\nአብዛኛውን ጊዜ የሚስተዋለው\nተጫዋቾችን በከፍተኛ ገንዘብ\nወደ ክለቦች ማምጣት\nነገር ግን ውጤታማ\nያለመሆን ችግር  ነው::\nበአንጻሩ ያለ ምንም ክፍያ ከፕሮጀክቶች የሚያድጉ ታዳጊዎች ቦታ አይሰጣቸውም:: በገንዘብ ከመጣው ተጫዋች አንጻር ሲታይ የተሻለ አቅም ያላቸው ናቸው፤ እነዚህ ታዳጊዎች እድል ቢያገኙና በትክክል ቢያዙ ለዋናው ቡድን ብቻም ሳይሆን ለሌሎች ቡድኖችም የሚሆኑ ናቸው:: በእርግጥ ይህ በክልሉ ብቻም ሳይሆን እንደ ሃገር የሚስተዋል ችግር ነው:: በቅድሚያ ይህ ኃላፊነት እንደተሰጠን በሲዳማ ያለውን የእግር ኳስ እንቅስቃሴ ከሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ባለሙያዎችን በቴክኒክ ቡድን በማዋቀር ጥናት እንዲጠና አድርገናል:: ጥናቱ ሲጠናቀቅም ለክልሉ ስፖርት ምክር ቤት ይቀርባል:: እንደሚታወቀው በሃዋሳ ከተማ ብቻ በኮረም፣ በቄራ እና ሌሎች ሜዳዎች ተጫውተው ያደጉ ተጫዋቾች ለብሄራዊ ቡድን እንዲሁም ለክለቦች ግብዓት ሆነዋል:: ነገር ግን አቅሙን በትክክል መለየትና መጠቀም አስፈላጊ ነው፤ ይህም በትንሽ ስራ ከፍተኛ ውጤት ለመሰብሰብ የሚያስችል እድል ነው:: ከክለቦችና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀናጅቶ ለመስራትም ፌዴሬሽኑ በማስተባበር ላይ ይገኛል:: እንደሚታወቀው ስታዲየሙ በፊፋ ስታንዳርድ መሰረት የተገነባና በመጠናቀቀ ላይ ያለ ነው:: በእስካሁኑ ስራም ሌሎች ስታዲየሞች ላይ የሌሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን የያዘ እንዲሁም ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት ነው:: ስታዲየሙ ከዚህ ቀደም ይተዳደር የነበረው በደቡብ ክልል እንደመሆኑ ሙሉ ለሙሉ ወደ ሲዳማ ክልል ባለመተላለፉ ምክንያት በመካከል ክፍተት ተፈጥሮ ችግር ውስጥ ወድቆ ነበር:: በመሆኑም ለሁለቱም ክልሎች በስታዲየሙ ላይ እየደረሰ ያለውን ችግር በማሳየት ውሳኔ እንዲያገኝ ለማድረግ ተሞክሯል:: ሲዳማ ክልልም ስታዲየሙን ተረክቦ ግንባታውን ለማጠናቀቅ ስራዎች ተጀምረዋል:: በአሁኑ ወቅትም የርክክቡ ስራ በሂደት ላይ ይገኛል:: ከዚህ በኋላ የሚሆነውም ቀሪ ስራዎች ተለቅመው ከአማካሪው ድርጅት በሚሰጠው አስተያየት መሰረት ስራዎችን ማጠቃለል ላይ ይሰራል::በሜዳው ላይ የሳር ተከላው እስካሁን አልተጠናቀቀም፤ ውሃ በመቋጠሩ ምክንያት ሳሩን ሙሉ ለሙሉ በማንሳት በድጋሚ ልምድ ባለው ባለሙያ ተከላ እየተደረገ ይገኛል:: በቅርቡ ተጠናቆ አገልግሎት እንዲሰጥም ታስቧል፤ ምክንቱም ብዙ ሃብት የፈሰሰበትና ዓለም አቀፍ ጨዋታዎችን የማስተናገድ አቅም ያለው እንደመሆኑ ወደ ስራ አለመግባቱ በርካታ ጉዳቶች አሉት:: ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አመራሮች ጋር በተደረገው ውይይትም ስታዲየሙ እንደ ክልል ሳይሆን እንደ ሃገራዊ ፕሮጀክት ታስቦ ሃብት በማፈላለግ እንዲጠናቀቅ ማድረግ ነው:: ይህም ለስፖርቱ ብቻም ሳይሆን ለከተማው የቱሪዝም እንዲሁም ሌሎች ትሩፋቶችንም የማስገኘት አስተዋጽኦ ይኖረዋል:: እስካሁንም ጉዳት የደረሰበትን መታደግ ሲቻል በቶሎ ለማጠናቀቅ በልዩ ትኩረት እየተሰራ ይገኛል:: የተቀሩትን ሁለት ሜዳዎች የሲዳማ ክልል ተረክቦ በአነስተኛ ወጪ በማንቀሳቀስ ወደ ስራ እንዲገቡ ተደርጓል:: በእነዚህም ልምምዶችና አነስተኛ ጨዋታዎች የሚካሄዱ ይሆናል:: በየወረዳውና በየትምህርት ቤቶቹ የሚገኙ የእግር ኳስ ሜዳዎችንም ለማጠናከር ድጋፍ እየተደረገ ነው:: በኮንስትራክሽን ላይ የተሰማሩ ድርጅቶችን ድጋፍ በመጠየቅ ሜዳዎቹን ማዘጋጀት ደግሞ ከስራዎቹ መካከል ዋነኛው ነው:: በመሆኑም በአጭር ጊዜ ውስጥ ለውጥ ይኖራል ብዬ አስባለሁ:: ክልሉ አዲስ እንደመሆኑ እንዲሁም ከወቅታዊው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ ባለሃብቶችን ለማንቀሳቀስ ቢሞከርም ውስንነቶች አሉ:: የቀረበው ተደጋጋሚ የሃብት ማሰባሰብ ስራም በሚፈለገው ልክ ሊጓዝ አልቻለም:: በስራ አስፈጻሚ ኮሚቴውም ከልምድ ማነስ ጋር የተያያዘ ችግር በመኖሩ የአቅም ግንባታ አስፈላጊ ነው:: ስለዚህም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የአቅም ግንባታ ስልጠና እንዲሰጠን እንዲሁም ከሌሎች ክልሎች ጋር የልምድ ልውውጥ በመውሰድ በቀጣይ የሚገጥሙትን ችግሮች እየፈቱ ለመሄድ ታቅዷል:: አዲስ ዘመን፡- በመጨረሻም ማለት የሚፈልጉት ነገር ካለ:: አቶ ብሩ፡- ፌዴሬሽኑ መስራት ይፈልጋል፤ ይህንንም ለማገዝ ከክልሉ ውጪ ያሉ አካላትም አብረውን ቢሰሩ እላለሁ:: በግብዓት ለማገዝና ፕሮጀክቶችን መደገፍ ለሚፈልጉ በራችን ክፍት ሲሆን፤ ቀደም ብለው ወደ ስራ የገቡ ፌዴሬሽኖች ቢደግፉንና ልምዳቸውን ቢያካፍሉን ደስተኞች እንሆናለን:: እኔም አመሰግናለሁ::", "passage_id": "a881aebae3d11421c995872241e16305" }, { "passage": "የሞተር ስፖርት ውድድሮች ከአፄ ሃይለ ስላሴ ዘመነ መንግስት ጀምሮ ይካሄድ ነበር። በወቅቱ ከአዲስ አበባ አስመራ ድረስ የሚዘጋጁ «የራሊ» የመኪና ፍልሚያዎች እንደነበሩ የሚያሳዩ መረጃዎች አሉ። ሆኖም በደርግ ዘመነ መንግስት ስፖርቱ «የቡርዥዋ» ስፖርት ነው በሚል እንዲቋረጥ አድርጎት ነበር። ይህ ስፖርት ረጅም ዓመታትን ይቆይ እንጂ ይህ ነው የሚባል አመርቂ ለውጥ ማምጣት አልቻለም። የደርግ ዘመን ማብቃቱን ተከትሎም ለስፖርቱ ፍቅር እና ቅርበት ያላቸው ሰዎች በማህበር ደረጃ በመሰባሰብ መሰረት ለመጣል ጥረት ከማድረጋቸው በዘለለ በኢትዮጵያ ውስጥ በልዩ ትኩረት እንዲታይ ማድረግ አልቻሉም። አቶ ኤርሚያስ አየለ የኢትዮጵያ ሞተር ስፖርት አሶሲዬሽን ቦርድ ፕሬዚዳንት ነው። ከሞተር ስፖርት አሶሴየሽን የቦርድ ፕሬዚዳንትነቱ በተጨማሪ የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ስራ አስኪያጅም በመሆን አገልግሏል። ለአራት ዓመታት ማህበሩን ሲመራ በቆየበት ወቅት የኢትዮጵያ ስፖርት ላይ የጎላ ሚና እንዲኖረው ጥረት አድርጓል። በዚህ ማህበር ላይ ተሳታፊ እንዲሆንና ውድድሩ ላይ ልክ እንደ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ተጨባጭ ለውጥ እንዲያመጣ በሚል ነበር በአባላቱ ፍላጎት የመጣው። ሆኖም ግን ይህ ስፖርት ከሚጠይቀው ልዩ ትኩረት እና ኢንቨስትመንት አንፃር ውጤታማ ስራዎች ማከናወን እንዳልተቻለ ነው የነገረን። «ስፖርቱ በሚገባ ከተሰራበት ለአገር ኢኮኖሚ ያለው አበርክቶ ከፍተኛ ነው» የሚል እምነት ያለው አቶ ኤርሚያስ መንግስትም ሆነ የሚመለከተው አካል አስፈላጊ በሆነ መንገድ ድጋፍ ሊያደርግለት ይገባል። በተለይ የማስፋፊያ ቦታ ወሳኝነት አለው በማለት ይገልፃል። አሁን ባለው ሁኔታ ግን ፈታኝ የሆኑ እንቅፋቶች የበዙበት እና በቀላሉ ውጤታማ መሆን ያልተቻለበት እንደሆነ ይናገራል። በመሆኑም የማህበሩ ፕሬዚዳንት ሆኖ የመቀጠል ፍላጎት እንደሌለውም ይገልጻል። በተመረጥኩበት የስራ ዘመን ማህበሩ ዓለም አቀፍ ግንኙነቱ እንዲጠናከር ሆኗል። አፍሪካ የሞተር ስፖርት ማህበር ጉባኤ በኢትዮጵያ ተደርጓል። መንግስት ከቀረጥ ነፃ ድጋፍ እና የውድድር ማዘጋጃ ቦታዎችን ማመቻቸት ቢችል ወደፊት ስፖርቱን የሚመሩት አካላት ስኬታማ ውጤት ያስመዘግባሉ የሚል እምነቱን ገልጿል። አቶ እዮብ ገብረ ሚካኤል የኢትዮጵያ ሞተር ስፖርት አሶሲዬሽን የቴክኒክ ክፍል ሃላፊ እና የቦርድ አባል ነው። ስፖርቱ ከተጀመረ ረዘም ያሉ አመታትን ማስቆጠሩንና እድገት አለማሳየቱን ጠቅሰን ምክንያቱን እንዲያብራራልን ጠይቀነው ነበር። በጉዳዩ ላይ በሰጠው ምላሽ «ውድድሩ እስካሁንም ይህ ነው የሚባል ለውጥ እንዳያሳይ ያደረገው በባህሪው ከፍተኛ ወጪ የሚያስወጣ ስፖርት በመሆኑ ነው» በማለት ሃሳቡን ይሰነዝራል። ከላይ አቶ ኤርሚያስ ያነሳውንም ሃሳብ ይጋራል። አቶ እዮብ መንግስት የሞተር ስፖርትን ለማበረታታት ድጋፍ ያደርግ እንደነበር ይናገራል። ድጋፉም ከቀረጥ ነፃ የመወዳደሪያ መኪናዎች እንዲያስገባ ማህበሩ ይፈቅድ እንደነበርም ይገልፃሉ። ሆኖም ይህ ድጋፍ ግን አሁን ላይ ባልታወቀ ምክንያት ተቋርጧል። «በአገራችን ስፖርቱን ማስፋፋት ብንችል በከፍተኛ ደረጃ\nየቱሪስት ፍሰቱን መጨመር እንችላለን» የሚለው አቶ እዮብ በአፍሪካ ውስጥ በሚደረጉ ተመሳሳይ ውድድሮች ከፍተኛ ተጠቃሚ መሆናቸውን በምሳሌነት ያነሳል። መንግስት አሁንም ቢሆን ከቀረጥ ነፃ መኪኖች እንዳይገቡ መከልከሉ ግልፅ ሊሆንላቸው እንዳልቻለ ነው የሚናገረው። በዚህ ሂደት ውስጥ ሌሎች ችግሮች እንዳይከሰቱ የቁጥጥር ስልት በመንደፍ ቀድሞ የነበረውን ድጋፍ መቀጠል ይኖርበታል ይላል። «ድጋፍ\nለማድረግ የሚችሉ አካላት ውድድሩ ቢካሄድ እና ስፖርቱ ቢያድግ ይዞት የሚመጣውን ጥቅም ሊረዱት የቻሉ አይመስለኝም» የሚለው አቶ እዮብ፤ የቀረጥ ነፃ ማበረታቻው ቢደረግ እና ስፖርቱ ቢያድግ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች እንደሚኖሩት ይናገራል። በተለይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪዎችን ለማፍራት፣ ቱሪስት ለመሳብ እና ሰፊ የስራ እድል ለመፍጠር እንደሚቻል ይገልፃል። የስፖርት ማህበሩ ከዓለም አቀፉ የስፖርት ፌዴሬሽን ጋር መልካም ግንኙነት እንዳለውና እገዛ እንደሚያደርግላቸውም ይገልፃል። መሳሪያዎችን በማቅረብ እና ስልጠናዎችን በመስጠት ላይ እንደሚደግፋቸውም ይናገራል። ማህበሩ ለፌዴሬሽኑ የአባልነት ክፍያ ይፈፅማል። ለበርካታ ዓመታትም ሳያቋርጥ ከፍሏል። ስለዚህ ጉዳይ የቴክኒክ ሀላፊው ሲገልፁ «ለረጅም ዓመታት የፊያ አባል ሆነን ቆይተናል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት ግን በገንዘብ ምንዛሬ እጥረት ምክንያት የአባልነት ክፍያ ለመፈፀም ተቸግረን ነበር» በማለት ዓለም አቀፍ ግንኙነታቸው በመልካም ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ይገልፃሉ። ፌዴሬሽኑ ለማህበሩ ወጣቶች እንዲያሰለጥንበት «ጎካርት» በመባል የሚታወቀውን የመወዳደሪያ መኪና እንደለገሳቸው ተናግረዋል። ማህበሩ በመላው ኢትዮጵያ የሞተር ስፖርት እንዲስፋፋ እየሰራሁ ነው ይላል። በኢትዮጵያ ስፖርት ላይ እንደሌሎቹ ሁሉ ፌዴሬሽን እንዲሆን ጥረት በማድረግ ላይ መሆኑንም ይገልፃል። በባህርዳር ሃዋሳ እና ሌሎች ከተሞች ላይም የሞተር ስፖርት ማህበር በማቋቋም ወደ ፌዴሬሽን እንዲያድግ የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ስራዎች እየተከናወነ መሆኑንም ይፋ አድርጓል። ማህበሩ አሁን ላይ እንቅፋቶች ከሆኑበት መካከል የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ አለመኖር መሆኑን ይናገራሉ። ስፖርቱ በባህሪው ከሚፈልገው ሰፊ ማዘውተሪያ አንፃር አሁን ላይ ይህን ማሟላት አስቸጋሪ እንደሆነባቸውም አቶ እዮብ ይገልፃሉ። ሳንሱሲ አካባቢ ማህበሩ ማዘውተሪያ ስፍራ ቢኖረውም አሁን ላይ በተለያየ ምክንያት ከእጁ የመውጣት ስጋት እየተደቀነበት ነው። ይህንን ችግር መንግስት ከግምት አስገብቶ የማዘውተሪያ ስፍራ ለማህበሩ እንዲያመቻች ፍላጎታቸው ነው። በኢትጵያ ውስጥ በሚካሄዱ የሞተር ስፖርት ውድድሮች ላይ በብዛት ተሳታፊ የሚሆኑት የውጭ አገር ዜግነት ያላቸው እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ናቸው የሚለውን ትችት አቶ እዮብ ይቀበሉታል። ይህ ሊሆን የቻለው ስፖርቱ በባህሪው ከፍተኛ ወጪን ስለሚጠይቅ ነው በማለትም ምላሽ ይሰጣሉ። አሁን ላይ ግን የዓለም አቀፉ ፌዴሬሽን በሚያደርግላቸው ድጋፍ እና በማህበሩ ጥረት ችግሩን ለመቅረፍ እንደሚሰሩ ይናገራሉ። የጣሊያኖች እና የግሪክ ተወዳዳሪዎችን የሚፎካከሩ ወጣት ኢትዮጵያውያን እየተፈጠሩ መሆኑንም ያነሳሉ። አቶ እዮብ «አሁን በአገር ደረጃ ጥሩ መነቃቃት እየተፈጠረ ነው» ይላሉ። ይህንን እድል ማህበራቸው ለመጠቀም ተግቶ እንደሚሰራ ይገልፃሉ። «ፊያ» ከደቡብ አፍሪካ ከፍተኛ የሞተር ስፖርት ዳኝነት ባለሙያዎችን በመላክ ለአገር ውስጥ ዳኞች ስልጠና ሰጥቷል። ባለሙያዎቹ በውድድር ጊዜ ትክክለኛ ዳኝነት የሚሰጡበትን ቴክኖሎጂዎች እንዴት መጠቀም እንደሚችሉ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ስልጠና እንዲወስዱ አድርጓል። የከፍተኛ ዳኝነት ስልጠናውን በተግባር ታግዘው የወሰዱት ባለሙያዎቹ ከ20 በላይ\nይሆናሉ። የቴክኒክ ሃላፊው ማህበሩ በቅርቡ ከአዲስ አበባ ወደ አስመራ የሚደረገውን ውድድር ለማዘጋጀት ማሰቡንና በጉዳዩ ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየሰራ መሆኑን ከዝግጅት ክፍላችን ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልፀውልናል። ፊያ ዳኞችን በማሰልጠን እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደራጁ መሳሪያዎችን በመደገፍ ስለተባበራቸው በቀጣይ የሚያዘጋጁት ውድድር ስኬታማ ይሆናል የሚል ተስፋ አላቸው። በአጠቃላይ የሞተር ስፖርት በኢትዮጵያ ውስጥ መሰረት እንዲኖረው ለማድረግ ግን ከዓለም አቀፍ ባለድርሻ አካላት ባሻገር መንግስት በቀናነት ድጋፍ ያድርግልን የሚል ጥሪ ያስተላልፋሉ።አዲስ ዘመን  ሐምሌ 21/2011  ዳግም ከበደ", "passage_id": "53ab7d1a131bbe1c7665af3d0c05a93b" }, { "passage": "ሰላም ፣ፍቅር ፣ አንድነትና ብሄራዊ ኩራት ከአዲስ አበባ እንዲጀምር እንፈልጋለን ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ ተናገሩ፡፡ ኢ/ር ታከለ ኡማ ይህንን ያሉት በትናንትናው እለት በአዲስ አበባ ከተማ የስፖርቱን ዘርፍ ለማሳደግ የላቀ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በተዘጋጀው የዕውቅና እና የምስጋና መድረክ ላይ በተገኙበት ወቅት ነው፡፡ እንደ\nምክትል ከንቲባው ገለፃ አዲስ አበባ የሀገራችን ዋና ከተማ እንደመሆኗ መጠን ብዙ መልካም ነገሮችን በመጀመር ለክልል ከተሞችም አርአያ መሆን አለባት፤ ለአብነትም የዛሬ አመት የተሰራውን የችግረኞች ቤት እድሳትና በጠቅላይሚኒስትሩ ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የችግኝ ተከላ ጅማሮውን በአዲስ አበባ አድርጎ ወደ ክልልም መውረዱን በማውሳት አሁንም በከተማ አስተዳደሩ በመንግስት ትምህርት ቤቶች የተጀመሩት ስራዎች ወደክልልም ይወርዳሉ የሚል እምነት እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ ‘’የከተማውን\nወጣት ማገልገል ግዴታችን ነው’’ ያሉት ምክትል ከንቲባው የወጣቱን ፍላጎት ለሟሟላት እንደሚሰሩ በመግለፅ ፤ ስፖርትም የልማቱ አንድ አካል ስለሆነ ወጣቶችን በስፖርት ለማሳደግና ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል ብለዋል፡፡ ምክትል\nከንቲባው በከተማዋ የስፖርቱን ዘርፍ ለማሳደግ የላቀ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት የተዘጋጀላቸውን የምስጋናና የእውቅና የምስክር\nወረቀት አበርክተዋል፡፡ በእውቅና አሰጣጥ ስነስርአቱ ላይ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትም በስፖርት ዘርፍ ዘገባ ላበረከተው አስተዋፅኦ የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበርክቶለታል፡፡ በመድረኩ\nላይ በቀጣይነት በከተማዋ የስፖርቱን ዘርፍ ይበልጥ ለማሳደግ ሊሰሩ በሚገቡ ስራዎች ዙሪያ ከስፖርት ማህበረሰብ እና ጋዜጠኞች ጋር ምክክር ተደርጓል፤ የፌደራልና የመስተዳደሩ ባለስልጣናት ተገኝተዋል፡፡ኢንተርናሽናል\nዳኞች ባምላክ ተሰማና ሊዲያ ታፈሰም በዕለቱ እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡በዳግማዊት\nግርማ", "passage_id": "83f47aadfdfca581ababded7a7a4c131" }, { "passage": "፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፈው አንድ ዓመት በርካታ ውጤቶችን ቢያስመዘግብም አሁንም የሚቀሩ ሥራዎች መኖራቸውን የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ።አዲስ ዘመን ጋዜጣ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች በሰጡት አስተያየት በዓመቱ በርካታ ሥራዎች ቢከናወኑን አሁንም በአፋጣኝ መሰራት ያለባቸው ሥራዎች እንዳሉ ተናግረዋል። አቶ ዘላለም አያሌው በሰጡት አስተያየት፣ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በዚህ አንድ ዓመት በርካታ መልካም ሥራዎች መሰራታቸውን ጠቁመው፣ ለበርካታ ዓመታት በሕገወጥ መንገድ በተለያዩ አካላት ተይዘው የነበሩ መሬቶች ወደ መንግሥት መመለሳቸውን አንስተዋል።እነዚህ ልማት\nላይ ያልዋሉ በከተማዋ ያሉ መሬቶች መመለሳቸው ለከተማዋ ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለው የተናገሩት አቶ ዘላለም፣ በከተማዋ ሰላምን ለማምጣት የተሰሩ ሥራዎችም አበረታች ውጤት ነበሩ ብለዋል።የከተማዋን ንፅህና ከመጠበቅና ለነዋሪዎቿ ምቹ\nከማድረግ አንፃር የተሰራው ሥራ እንዲሁም አሁን በቋሚነት እየተከናወነ ያለው ወርሀዊ የፅዳት ዘመቻ እንዲሁም ከተሽከርካሪ ነፃ ቀንን በማወጅ ለአካል ብቃት እንቅስቃሴ የተሰጠው ትኩረት በስኬትነት ከሚጠቀሱት ውስጥ የሚካተቱ እንደሆኑም አቶ ዘላለም ተናግረዋል።እንደ አቶ ዘላለም አስተያየት የከተማ አስተዳደሩ በዚህ አንድ ዓመት ውስጥ በከተማዋ ያሉ ክፍት ቦታዎችን ወደ ልማት ማስገባት፣ የግንባታ ሥራዎች ሲሰሩ ለዛፎች መትከያ ስፍራ እንዲኖራቸው አስገዳጅ ሕግ ማውጣትና ተግባራዊ ማድረግ፣ ለወጣቶች የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን መገንባት፣ በከተማዋ የሥራ አጥ ቁጥርን መቀነስ እና ለወጣቱ የሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ክፍተት ስላለበት ይህንንና ሌሎችም ችግሮችን ተመልክቶ ወደፊት ቢሰራ መልካም መሆኑን ገልፀው፣ በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጭነት መኪናዎች ላይ የተጣለው የመንቀሳቀሻ ሰዓት ገደብ ሀገሪቱን ለአላስፈላጊ ወጪ ስለሚዳርግና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ስለሚያስነሳ እንደገና ቢታይ ተገቢ ነው ብለዋል።በየካ ክፍለ ከተማ የመኪና ግብር ለመክፈል ተራ ሲጠብቁ ያገኘናቸው አቶ እንዳለ ደረጀ ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ በለውጡ ሂደት በአካባቢ ፅዳት፣ በጎ አድራጎት ሥራዎች እና መሰል ተግባራት ላይ ውጤት ቢያስመዘግብም በገቢ አሰባሰብ ላይ ሰፊ ክፍተት እንደነበረበት ለዚህም በክፍለ ከተሞች ገቢ ሰብሳቢ መስሪያ ቤቶች የሠራተኞች ቁጥር አናሳ መሆኑን የየካ ክፍለ ከተማን ለአብነት በማንሳት ተናግረዋል።መብራት፣ ውሃ፣ መንገድና ሌሎችም መሠረተ ልማቶችን በበቂ ሁኔታ ለነዋሪዎች ከማቅረብ አንፃር በዓመቱ ክፍተት እንደነበር የተናገሩት አቶ እንዳለ፣ ያልተጠኑ ውሳኔዎችም ሌሎቹ ችግሮች እንደነበሩ ጠቁመዋል።በደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ላይ የተጣለው የሰዓት ገደብ ሳይጠና የተተገበረ ነው የሚሉት አስተያየት ሰጪው፣ ለመንግሥት ግብር ለመክፈልና ሰርቶ ለመለወጥ የሚደረግ ጥረትን የሚያደናቅፍ ከመሆኑም ባሻገር በዘርፉ በተሰማሩ ባለሀብቶች ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ በመሆኑ እንደገና ሊፈተሽና ሊስተካከል ይገባዋልም ብለዋል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአንድ ዓመት ውስጥ ብዙ ሥራዎችን መስራቱን የተናገረችው ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወጣት ለኢላ አብደላ፣ ለአብነትም በበጎ አድራጎት ሥራዎች ዝቅተኛ የኅብረተሰብ ክፍሎችንና የጎዳና ተዳዳሪዎችን ተጠቃሚ በማድረግ በኩል ትልቅ ሥራ ተሰርቷል ብላለች።አሁንም በከተማዋ ለሚገኙ ሁሉም የመንግሥት ትምህርት ቤት ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስና የደንብ ልብስ ለማሟላት የተጀመረው እንቅስቃሴ ትልቅ ስኬት ነው ያለችው ወጣት ለኢላ፣ በከተማዋ ሰላም እንዲሰፍን የተሰራው ሥራም አበረታች እንደነበር ጠቁማለች። በከተማዋ እየጨመረ የመጣው ሕገወጥ ንግድ እና የስርቆት ወንጀል እንዲሁም ከጊዜ ወደጊዜ እያሻቀበ ያለው የኑሮ ውድነት ላይ አስተዳደሩ በትኩረት እንዳልሰራ የተናገረችው ወጣት ለኢላ፣ ይህ በኢኮኖሚው ላይ ተፅዕኖ ስለሚያሳድር ወደፊት በትኩረት ሊሰራበት የሚገባ ጉዳይ ነው ብላለች።በከተማዋ ሕገወጥ ተግባራት በስፋት ይታያሉ ለዚህ ደግሞ ሰዎች መብትና ግዴታቸውን ማወቅ አልቻሉም። ከዚህ ጋር በተያያዘ በከተማዋ በሞተር ሳይክል ስርቆት ተስፋፍቶ ነበር አሁን ላይ እንዳይንቀሳቀሱ መደረጉ ጥሩ ሆኖ ሳለ ለመልካም ተግባር የሚጠቀሙበት አካላት ተደራጅተው ቢሰሩ ሥራ አጥነትን ይቀንሳሉ።አስተያየት ሰጪዎቹ\nበከተማዋ አስተዳደሩ ላይ በርካታ\nቅሬታዎች ቢኖሩም፣ ቅሬታ\nማንሳት ብቻ ሳይሆን\nለውጥ ለማምጣት ሁሉም\nዜጋ የራሱን ኃላፊነት\nእንዲወጣና አስተዳደሩን እንዲያግዝ\nጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 11/2011", "passage_id": "9b971aa05357a9600372f083ca8c9f9f" } ]
fd72453b45e97e412963a264d04ba723
ece7d77687d255e3d1e9c80aca73b820
አዳዲስ የአትሌቲክስ ማዘውተሪያዎች ግንባታ ይከናወናል
ብርሃን ፈይሳአዲስ አበባ፡- ለአትሌቲክስ ስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ የሚሆኑ ቦታዎች ምልከታ ተደረገ። ማዘውተሪያዎቹ በአዲስ አበባ አቅራቢያ በሚገኙ አራት ከተሞች ላይ የሚገኙ መሆኑም ታውቋል። በቅርቡ በለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ አስተዳደር የተመረቀውን የአትሌቲክስ ስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ ተከትሎ ሌሎች ግንባታዎችም እንደሚከናወኑ ተጠቁሞ ነበር። በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ፤ ከለገዳዲ ለገጣፎ ባሻገር በተለያዩ ከተሞች በአጭር ጊዜ ቦታ በማዘጋጀት ተጨማሪ ማዘውተሪያ ስፍራዎች እንደሚገነቡ ጠቁመው ነበር። የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን በድረገጹ እንዳስታወቀው፤ለማዘውተሪያ ስፍራዎቹ ግንባታ በሚሆኑ ስፍራዎች ላይ ሰሞኑን ምልከታ ተከናውኗል። በመልክታው መሰረት ማዘውተሪያዎቹ የሚገነቡት በአዲስ አበባ አቅራቢያ በሚገኙት አራት ከተሞችም ቡራዩ ፣ ሰበታ ፣ ዱከም እና ሱልልታ ይሆናል። ለግንባታውም በቡራዩ 50 ሄክታር፣ በሰበታ 8 ነጥብ 5 ሄክታር፣ በዱከም 23 ሄክታር እንዲሁም በሱልልታ 20 ሄክታር መሬት ተዘጋጅቷል። በምልከታው ላይም የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው፣ ሚኒስትር ዲኤታው ሃብታሙ ሲሳይ፣ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር፣ ምክትል ኮሚሽነር ዱቤ ጂሎ፣ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ደራርቱ ቱሉ እና ምክትል ፕሬዚዳንቱ ገዛኸኝ አበራ እንዲሁም የኦሮሚያ ስፖርት ኮሚሽን አመራሮች ተገኝተዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=38042
[ { "passage": "አዲስ\nአበባ፡- 52 ኪሎ ሜትር ከሚሸፍነው የአዲስ አበባ ከተማ የወንዝ ዳርቻዎችን ለመናፈሻ የማዋል ሥራ ውስጥ ሁለት ኪሎ ሜትሩን የጣሊያኑ ቫርኔሮ ኩባንያ ስራ መጀመሩን የተፋሰስና አረንጓዴ አካባቢዎች ኤጀንሲ አስታወቀ። በሸራተን ማስፋፊያ አካባቢ የሚሰራው ሁለገብ አገልግሎት ያለው የመናፈሻ ፓርክ ሥራም ከኩባንያው ጋር የውል ስምምነት ለመፈጸም በሂደት ላይ መሆኑም ተጠቁሟል። የኤጀንሲው\nዳይሬክተር ዶክተር ስለሺ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት የአዲስ አበባ ከተማ የወንዝ ዳርቻዎችን ለመናፈሻ የማዋል ሥራ አጣዳፊ የጎርፍ ችግር ሲያጋጥምና የአካባቢውን ነዋሪዎች ለአደጋ ሲያጋልጥ አደጋውን ከመከላከል ጎን ለጎን ወንዞችን ለመናፈሻ የማዋል ሥራ ቀድሞም ሲከናወን የቆየ ነው። ይህ የሚለየው የፕሮጀክቱ ግዝፈትና ከላይኛው እስከ ታችኛው ተፋሰስ ድረስ ወጥ በሆነ መልኩ መከናወኑ ነው ብለዋል።በፕሮጀክቱ\nአምስት ገባር ወንዞችንና ሰባት የከተማዋን የወንዝ ዳርቻዎች ለመናፈሻ ለማዋል በጥናት ተለይተዋል የሚሉት ዳይሬክተሩ የሁለት ኪሎ ሜትሩ ሥራ ቢጀመርም ቀሪው ጥናት ላይ መሆኑንና በምዕራፍ ተከፋፍሎ አጠቃላይ ሥራውን በሶስት አመት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ መታቀዱን አመልክተዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ማብራሪያ የአካባቢውን ነዋሪ ብዛት ታሳቢ በማድረግና የልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል ከእንጦጦ፣አፍንጮ በርና ቡልቡላ አድርጎ አቃቂ የሚሄደው ወንዝ በፕሮጀክቱ በቅድሚያ ተካትቷል፡፡ ፕሮጀክቱ\nበፌዴራል መንግሥት፣በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣በብድር፣በገቢ ማሰባሰብና በተለያዩ ድጋፎች የሚከናወን ሆኖ በአጠቃላይ 29 ቢሊዮን ብር እንደሚፈጅ አስረድተዋል፡፡ ቻይና መንግሥት ከእንጦጦ እስከ ቡልቡላ ያለውን በገንዘብ ለመደገፍ ፍላጎት ማሳየቱን አስታውሰው በተመሳሳይ መንገድ ፕሮጀክቱን ለመደገፍ ፍላጎት ያላቸው ዓለምአቀፍ ድርጅቶች መኖራቸውንም ጠቁመዋል፡፡ የልማቱ ሥራ ከሚከናወንበት አካባቢ 32ሺ ተነሽዎች እንደሚኖሩት የሚጠበቀው ይህ ፕሮጀክት ለሚነሱ ነዋሪዎች ምትክ ቦታና አስፈላጊውን ካሳ አሟልቶ ከቦታው አስነስቶ ወደ ሥራ ለመግባት የተባባሪ አካላት ድጋፍ ወሳኝ እንደሆነ ዶክተር ስለሺ አስረድተዋል፡፡ የፕሮጀክት መጓተት እንዳይኖርም በቅድ መዘጋጀቱ ትኩረት መደረጉን ገልጸዋል፡፡ በሸራተን ማስፋፊያ አካባቢ በሁለት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር ወጪ የአረጓዴ ቦታ፣ የልጆች መጫወቻ፣አንፊ ቲያትር፣ የገበያና የተለያየ አገልግሎት መስጫ ያለው የፓርክ ሥራም የወንዝ ዳርቻና መናፈሻ ሥራው አካል መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ የፕሮጀክቱ የአዋጭነት ጥናት መካሄዱንም ይናገራሉ፡፡ በወንዞች\nዳር መናፈሻ ፕሮጀክት ጥናቱ ላይ የተሳተፉት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአካባቢ ሳይንስ መምህር ፕሮፌሰር ተሾመ ሶሮምሳ እንደገለጹት ጥናቱ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት አማካኝነት እኤአ በ2016 የተጀመረ ሲሆን፣ በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ መጠናቀቁን ያስታውሳሉ፡፡ ጥናቱ\nሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን የዳሰሰና አምስት ዋና ዋና ጉዳዮችን ያካተተ ነው ያሉት ፕሮፌሰሩ በከተማዋ የ127 አመት ታሪክ ውስጥ ሰፊ የሆነ የወንዝ ዳር ልማት ሥራ በመሆኑ አዲስና ሥር ነቀል ለውጥ እንደሚያመጣ አመልክተዋል፡፡ በጥናቱ ግኝት በከተማዋ 607 ኪሎሜትር ርዝመት ያላቸው 76 ወንዞች ይገኛሉ፡ ፡ አሁን በተጀመረው የልማት ሥራ በ20 አመት ጊዜ ውስጥ ሁሉንም መናፈሻ ማድረግ የሚቻልበት ዕድል መኖሩን ፕሮፌሰሩ አመልክተዋል፡፡አዲስ\nዘመን መጋቢት 19/2011በለምለም\nመንግሥቱ", "passage_id": "6de2d9d2797b70545a95cb7f2eb406c0" }, { "passage": "የበርካታ ዓመታት የኢትዮጵያዊያን ስፖርት ወዳዶች ጥያቄ ነው፤ ዘመናዊ ስታዲየም። ይህንን ተከትሎም በርካታ ክልሎች ደረጃቸውን የጠበቁና ግዙፍ ስታዲየሞችን በማስገንባት ላይ ይገኛሉ። በአዲስ አበባ ከተማ የሚገነባው ብሔራዊ ስታዲየምም ለዚህ ጥያቄ መንግሥት የሰጠው ሌላኛው ምላሽ ነው። እ.ኤ.አ በ2016 የመጀመሪያው ወር የተጀመረው የስታዲየሙ ግንባታ፤ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ መሰረት ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት አጋማሽ የመጀመሪያው ምዕራፍ መጠናቀቅ ነበረበት። አዲስ ዘመን «ግንባታው የት ደርሷል?» ሲል ጠይቋል። በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ስፖርት ኮሚሽን የስፖርት\nፋሲሊቲ ዳይሬክተር ኢንጂነር አዝመራው ግዛው፤ ከዚህ ቀደም ለህዝብ ይፋ የተደረገው የመጀመሪያ ዙር ግንባታው 95 በመቶ ላይ መድረሱን\nሲሆን፤ አሁን ባለበት ደረጃ 98 ነጥብ 89 በመቶ ደርሶ ሥራው መቆሙን ይገልፃሉ። ይህም ሊሆን የቻለው ውስጣዊው የመም(ትራክ)\nአካል ሥራ ተጠናቆ ሴንቴቲኩ ከመነጠፉ በፊት ክረምቱ በመግባቱ ለመሥራት አመቺ ባለመሆኑ ነው። በተመሳሳይ የእግር ኳስ መጫወቻ ሜዳ\nግንባታው ቢጀመርም ሣሩ እስካሁን አልተተከለም። ለዚህም ምክንያት የሆነው ሁለተኛው ዙር ግንባታ በቅርቡ የሚጀመር ከመሆኑ ጋር ተያይዞ\nከ900 ቀናት እስከ ሁለት ዓመት ከግማሽ ሊፈጅ ይችላል። በዚህ የግንባታ ሂደትም ሣሩ ሊበላሽ እንደሚችል ግምት ውስጥ በማስገባት\nእንዲዘገይ ተደርጓል። በቀጣይም ቀሪ ግንባታዎች ከተጠናቀቁ በኋላ በመጀመሪያ በተገባው ውል የሣር ተከላ ሥራው የሚቀጥል መሆኑን\nዳይሬክተሩ ተናግረዋል። በዚህ ወቅት የግንባታው ሁለተኛ ምዕራፍ\nለማስጀመር ጨረታ ተከፍቶ ቴክኒካዊ ጉዳዮች በአማካሪው ድርጅት በመገምገም ላይ ይገኛሉ። በህጉ መሰረት የጨረታ ሂደቱ 15ቀናት ቢፈጅም፤\nአማካሪው ከውጭ ድርጅት ጋር የሚሠራ በመሆኑ ዶክመንቶችን መላላክ የግድ ብሏል፡፡ የግምገማው ውጤት ከተጠናቀቀ በኋላ ያለው ቀሪ\nሥራ ስለማያቆይ ሁለተኛው ዙር ግንባታው የሚጀመር ይሆናል። ሁለተኛው ዙር ግንባታም በስታዲየሙ፤\nየአደይ አበባ ቅርጽ ያለውን ዙሪያ ጣራ ማልበስ፣ የደህንነትና የድምጽ ሲስተሞችን መዘርጋት፣ የወንበርና ስክሪኖች ገጠማ እንዲሁም\nየተለያዩ ክፍሎች፣ ቢሮዎችና የመገናኛ ብዙሃን መገልገያ ክፍሎች ሥራን ያጠቃልላል። ከስታዲየሞ ውጭም፤ ቢሮዎች፣ የዕቃ ማከማቻ ክፍሎች፣\nየመኪና ማቆሚያና ሄሊኮፕተር ማረፊያ ስፍራዎች፣ ቲያትር ቤት፣ የባድሜንተን እና ሦስት በአንድ መጫወቻ ሜዳዎች፣ ሁለት የመለማመጃ\nሜዳዎች እንዲሁም በስታዲየሙ አጠገብ የሚያልፈውን ወንዝ አልምቶ ለመዝናኛ ማዋልን የያዘ ሰፊ ሥራ ይከናወናል። ከመጀመሪያው ምዕራፍ በበለጠ እጅግ ከፍተኛ ሥራዎችን ላካተተው ለዚህ ሥራም በባለሙያዎች ግምታዊ ዋጋ\nተተምኖ በጀት መዘጋጀቱን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ በዚህም መሰረት የጨረታ ሂደቱ ተጠናቆ አሸናፊው ሲታወቅ ምን ያህል ወጪ እንደሚጠይቅ\nይፋ ይደረጋል። በተለያዩ ክልሎች የተገነቡ ስታዲየሞች የመጀመሪያ ዙር ግንባታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ሁለተኛውን ምዕራፍ ለመጀመር\nሲቸገሩና ለዓመታትም ባሉበት ግንባታቸው ቆሞ ሲቀር ማየት የተለመደ ነው፡፡ የብሔራዊው ስታዲየም ግንባታ ግን ይህ ዕጣ እንዳይደርሰው\nመንግሥት በቂ በጀት መመደቡን እና በልዩ ሁኔታ የተያዘ ፕሮጀክት መሆኑን ኢንጂነር አዝመራው አብራርተዋል፡፡ ለዚህ ዓመት ሥራ የሚውለውና\nለሁለትና ሦስት ክፍያዎች የሚሆነው በጀትም ፀድቋል። ከዚህ ባሻገር ፕሮጀክቶች ሊዘገዩ ከሚችሉባቸው ምክንያቶች መካከል አንዱ ቴክኒክ ነው፤ ለዚህም ከአማካሪው\nጋር በመሆን ሥራውን እንደሚከታተሉ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። የጨረታ ሂደቱ በቶሎ ተጠናቆ ወደ ሥራ ከተገባ በኋላም ከአቅም በላይ\nየሆነ ችግር ካላጋጠመ ግንባታው አይቆምም። ከተያዘለት የጊዜ ገደብ በላይ የቆየው የመጀመሪያው ዙር ግንባታ፤ የውጭ ምንዛሬ እጥረት\nመግጠሙ ለመዘግየቱ እንደምክንያት የሚነሳ ነው። ተቋራጩ ውል ከገባ በኋላም በቦታው የነበሩ ህገወጥ ግንባታዎች እስኪነሱ ድረስ ጊዜ\nመውሰዱንም ዳይሬክተሩ ያስታውሳሉ። በዚህም ጊዜው ሁለቴ የተራዘመ ሲሆን አሁን የቀሩት ሥራዎች ግን በስምምነት የሚቆዩ ናቸው። ከዚህ በኋላ ለሚኖረው ሥራ ፈታኝ ሊሆኑ የሚችሉ ሁኔታዎች አሉ። ከእነዚህም መካከል አንዱ ከትራንስፖርት\nጋር በተያያዘ መንግሥት ያወጣው ሕግ ነው። ግንባታው በ480ሺ ሜትር ስኩዌር ቦታ ላይ የሚያርፍ ሲሆን፤ በዚህም እስከ 1 ሚሊየን\nሜትር ኪዩብ አፈር በቁፋሮ ሊወጣ ይችላል። ይህንን አፈር የሚያወጡት ከባድ ተሽከርካሪዎች ደግሞ በምሽት ብቻ እንዲሠሩ መደረጉ ጊዜውን\nሊያራዝመው ይችላል። በመሆኑም በልዩ ሁኔታ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጋር በመነጋገር ማስፈቀድ አስፈላጊ ይሆናል። ሌላው አሁንም\nድረስ ከግንባታው ስፍራ ያልተነሱ ቤቶች መኖራቸው ነው። ከሚመለከታቸው አካል ጋር በመሆን ቤቶቹ የማይነሱ ከሆነ አሁንም ከውል በኋላ\nበድጋሚ ችግር ሊገጥም ይችላል የሚል ሥጋት አለ። በመጨረሻም፤ የሁለተኛው ዙር ግንባታ ቅድመ ዝግጅት በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝና መንግሥትም በልዩ\nሁኔታ ድጋፍ ማድረጉን ዳይሬክተሩ ይገልፃሉ። ፕሮጀክቱ የኢትዮጵያ ህዝብ በመሆኑ እንዲሁም ከተማዋን አዲስ ገጽታ ስለሚያላብስ መንግሥትና\nደጋፊ ተቋማትም ድጋፋቸውን አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ አዲስ ዘመን  መስከረም 13/2012ብርሃን ፈይሳ ", "passage_id": "d93c0a06783ad2cece3cfee92dd96ff1" }, { "passage": "የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ4.8 ቢሊዮን ብር ካፒታል በእንጦጦ ተራራ ላይ ደረጃውን የጠበቀ የቱሪስት ማዕከል ለመገንባት ዕቅድ ነደፈ፡፡በሰሜን አዲስ አበባ በሚገኘው እንጦጦ ተራራ በ4,200 ሔክታር ቦታ ላይ የሚያርፈውን የቱሪስት ማዕከል ግንባታ ለማስጀመር በከንቲባ ድሪባ ኩማ የሚመራ ሥራ አመራር ቦርድ ተሰይሟል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤትና ማዕከሉን ማቋቋም የሚያስችሉ የሕግ ማዕቀፎች ተዘጋጅተዋል፡፡የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ገብረ ጻዲቅ ሐጎስ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የቱሪስት ማዕከሉ አራት ማዕቀፎች አሉት፡፡ከእነዚህ ማዕቀፎች ውስጥ የመጀመሪያው የብሔርና ብሔረሰቦች ማዕከል ግንባታ ነው፡፡አዲስ አበባ የብሔርና የብሔረሰቦች ከተማ ብትሆንም፣ የብሔሮችና ብሔረሰቦች ማዕከል የላትም ያሉት የቢሮ ኃላፊው፣ ‹‹ማንኛውም ዓይነት ቱሪስት አዲስ አበባ ቢገባ የሚገነባውን የባህል ማዕከል በመጐብኘት ኢትዮጵያን መመልከት እንዲችል ማድረግ ይቻላል፡፡ በዚህም አንድ ቱሪስት ስለኢትዮጵያ ሙሉ መረጃ እንዲኖረው ያደርጋል፤›› ሲሉ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ሁለተኛው ማዕቀፍ የመዝናኛ ማዕከላት ግንባታ ነው፡፡ በዚህ ፕሮጀክት ሎጆችና አምስት መቶ ሜትር ርዝመት ያለው ማማ (ታወር) ይገነባል፡፡ ማማው የተለያዩ ሬስቶራንቶችን ከመያዙ በተጨማሪ እየተሽከረከረ ከተማውን ማሳየት ያስችላል ብለዋል፡፡‹‹በዕረፍት ቀናት የከተማው ነዋሪዎች ከአዲስ አበባ ወጥተው ይዝናናሉ፣ እዚሁ እንዲዝናኑ አማራጭ ሊፈጠር ይገባል፡፡ የቱሪስቶች የመቆያ ጊዜም እንዲጨምር ያደርጋል፤›› ሲሉ አቶ ገብረ ጻዲቅ የመዝናኛ ማዕከላት መገንባት ያለውን ጠቀሜታ ገልጸዋል፡፡ሦስተኛው ማዕቀፍ እንጦጦን የአትሌቶች የመለማመጃ ማዕከል ማድረግ ነው፡፡ እንጦጦ ያለው የአየር ፀባይ ለአትሌቲክስ ስፖርት የተመቸ በመሆኑ፣ የአገር ውስጥና የሌሎች አገሮች አትሌቶች ጥያቄ ሲያቀርቡ መቆየታቸው ተገልጿል፡፡‹‹ጉዳዩ በመታመኑ የአትሌቲክስ ስፖርት የልምምድ ማዕከል ግንባታ ይካሄዳል፤›› ሲሉ አቶ ገብረ ጻድቅ ተናግረዋል፡፡ አራተኛው ማዕቀፍ ደግሞ የኢትዮጵያ ብሔርና ብሔረሰቦች የራሳቸውን ሙዚቃ፣ ወግ፣ ሥርዓትና ባህል ለታዳሚዎች በቀጥታ የሚያቀርቡባቸው ግንባታዎች ይካተታሉ፡፡ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት ወደ ተግባር ከመለወጡ በፊት የከተማው አስተዳደርና ሕዝቡ የሚመክርባቸው መድረኮች ይዘጋጃሉ ተብሏል፡፡የእዚህን ፕሮጀክት አዋጪነት ጥናት የዓለም ባንክ ፋይናንስ አድርጎ ያስጠናው በመሆኑ፣ ግንባታውንም የዓለም ባንክ ፋይናንስ እንዲያደርገው ንግግር እየተደረገ መሆኑን ከንቲባ ድሪባ ኩማ ገልጸዋል፡፡ ይህንን አዲስና ግዙፍ ግንባታ ለማካሄድ የአምስት ዓመታት ስትራቴጂካዊ ዕቅድ መነደፉ ታውቋል፡፡   ", "passage_id": "0880a867b156e0eec7ea26ed7a762361" }, { "passage": "በኢትዮጵያ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች አስተዳደር አዋጅ በ2004ዓ.ም ቢወጣም፤ ደንብና መመሪያ ስላልነበረው በስራ ላይ ማዋል እንዳልተቻለ ይታወቃል። የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽንም ችግሩን ለመቅረፍ መመሪያውን በረቂቅ ደረጃ ያዘጋጀ ሲሆን፤ የሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል። በ1990ዓ.ም\nየወጣው የኢትዮጵያ ስፖርት\nፖሊሲ፤ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ\nማከናወን የዜጎች መብት\nመሆኑን ይጠቁማል። በመሆኑም\nህብረተሰቡ በሚኖርበት፣ በሚማርበትና በሚሰ ራበት\nአካባቢ በስፖርት እንቅስቃሴ\nተሳታፊ የሚሆንበትን ሁኔታ\nማመቻቸትና ለዚህ ዓላማም\nየስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች\nእንዲስፋፋ ማድረግ አስፈላጊ\nነው። በዚህ መሰረትም በአሁኑ\nወቅት በመላ ሀገሪቷ\nየስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራዎች\nበተለያየ ደረጃ በስፋት\nበመገንባት ላይ ይገኛል።\nይሁን እንጂ የማዘውተሪያ ሥፍራዎቹ ወጥ\nበሆነ መንገድ እንዲተዳደሩ እየተደረገ አይደለም።\nአንዳንድ ማዘውተሪያዎች በስፖርት\nምክር ቤት እየተዳደሩ\nየራሳቸውን ገቢ ሲያመነጩ፤\nሌሎች ደግሞ በመንግስት\nመዋቅር እንዲሁም ባስገነቧቸው ተቋማት ሥር\nነው የሚገኙት። የማዘውተሪያ ስፍራዎቹ ወጥ\nበሆነ መንገድ እንዲተዳደሩ እንዲሁም የባለቤትነት መብት እንዲኖራቸው የመተዳደሪያ አዋጁ\nቢወጣም አዋጁን ተግባራዊ\nለማድረግ ደንብና መመሪያ\nባለመዘጋጀቱ እንዲሁም ለአስፈጻሚ\nአካላት በቂ ግንዛቤ\nባለመፈጠሩ የስፖርት ማዘውተሪያ\nየነበሩ ስፍራዎች ለሌላ\nዓላማ እየዋሉ ይገኛሉ።\nይህ መሆኑ ደግሞ\nበህብረተሰቡ ዘንድ ከፍተኛ\nቅሬታ መፍጠሩን እና\nአሉታዊ ተጽእኖም ሲፈጥር\nመቆየቱን ኮሚሽኑ በድረገጹ\nአስነብቧል። የኢፌዲሪ ስፖርት ኮሚሽን\nችግሩ እልባት እንዲያገኝና ህብረተሰቡም በቂ\nየማዘውተሪያ ስፍራዎችን በማግኘት\nጤንነቱን እንዲጠብቅ፣ ሀገሪቷ\nከስፖርት የምትጠብቀውን ውጤት\nእንድታገኝ እንዲሁም የስፖርት\nማዘውተሪያ ስፍራዎች በቂ\nጥበቃ እንዲኖራቸው አዋጁን\nተግባራዊ ማድረግ የሚያስችል\nረቂቅ ደንብ በማዘጋጀት\nበአዳማ ከተማ ለውይይት\nማቅረቡ ታውቋል። በውይይቱ ላይ የህዝብ\nተወካዮች ምክር ቤት\nማህበራዊ ዘርፍ ቋሚ\nኮሚቴ፣ ከክልል አስተዳደር\nጽህፈት ቤት፣ ከክልል\nምክር ቤት ማህበራዊ\nዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ\nአባላት፣ ከክልል የገጠርና\nከተማ ልማት አስተዳደር\nቢሮ ኃላፊዎች፣ ከከተማ\nልማት ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ፣ ከፍትህ\nእና መሬት አስተዳደር\nየሚመለከታቸው ባለሙያዎች፣ የክልል\nስፖርት ኮሚሽን እና\nየስፖርት ማህበራት አመራሮች\nተሳታፊዎች ሆነዋል። በመድረኩ ላይ ንግግር\nያደረጉት የኢፌዴሪ ስፖርት\nኮሚሽን ኮሚሽነር ርስቱ\nይርዳ፤ የስፖርት ማዘውተሪያ\nስፍራዎችና መዝናኛ ቦታዎች\nአልፎ አልፎ እንደ\nአላስፈላጊ እና ትርፍ\nአድርጎ የማየት እንዲሁም\nበሰበብ አስባቡ ለሌሎች\nአገልግሎቶች እንዲውሉ የማድረግ\nዝንባሌዎች የሚታይ በመሆኑ\nበአርቆ አሳቢነትና በሰለጠነ\nአስተሳሰብ መምራት የሁሉም\nየጋራ ኃላፊነት ነው\nማለታቸውም ተጠቅሷል። እንደ ኮሚሽነሩ ገለጻ ረቂቅ አዋጁ በባለ ሙያዎች ከተገመገመና ሃሳብ ከተሰጠበት በኋላም ወደ ሚኒስትሮች ምክር ቤት የሚመራ ይሆናል። ጸድቆ ወደ ሥራ ሲገባም፤ የይዞታ ማረጋገጫ ባለማግኘታቸው በርካታ ህብረተሰብ የሚሳተፍባቸውና ስመ ጥር ስፖርተኞችን ያፈሩ ታዋቂ ማዘውተሪያዎች ለግል ባለ ሃብቶችና ሌሎች ግንባታዎች ተላልፈው ሲሰጡ የነበረውን አሰራር ያስቀራል። የማዘውተሪያ ሥፍራዎች ከተገነቡ በኋላ፤ ለመጠበቅ፣ ለማደስ፣ ለማስፋፋት እንዲሁም ለማልማት የመንግሥት በጀት መጠበቅ ይቀራል። ረቂቅ አዋጁ የራሳቸውን ገቢ ማመንጨት እንዲችሉ የሚያደርግና በዚህ ረገድ ያለውን ችግር እንደሚፈታም ተስፋ ተጥሎበታል።አዲስ ዘመን መጋቢት 26/2011 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "657f707a24995c07c02d603c535134af" }, { "passage": "በእግር ኳስ ሶስት የአፍሪካ ዋንጫዎችን፣ አራት ሴካፋ፣ የአፍሪካ ከ21 ዓመት በታች ሻምፒዮና፣ በርካታ ኢንተርናሽናል የማጣሪያ እንዲሁም የክለብ ጨዋታዎችን አስተናግደዋል። አህጉር አቀፉን እንዲሁም የታዳጊዎች የአትሌቲክስ ሻምፒዮናም በዚሁ ስታዲየም ተከናውነዋል። ይህ በርካታ አህጉር አቀፍ ውድድሮችን እንዲሁም ሃገር አቀፍ ሁነቶችን ሲያስተናግድ የኖረው አንጋፋው የአዲስ አበባ ስታዲየም አሁን ግን ዘመኑን ከማይመጥንበት ደረጃ ደርሷል። እንደሚታወቀው ከተማዋ ዓለም ዓቀፍ ሁነቶችን ለማስተናገድ ተመራጭ ናት። ከእነዚህ ሁነቶች መካከል አንዱ ስፖርት እንደመሆኑ፤ አህጉርና ዓለም ዓቀፍ ውድድሮች በተለይም ለእግር ኳስና አትሌቲክስ ውድድሮች ከአዲስ አበባ ስታዲየም ውጪ አማራጭ ሳያገኙ ቆይተዋል። በዚህ ወቅት ግን የኢትዮጵያ ዋና ከተማ እና የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባ ከተማ ስሟን የሚመጥን ስታዲየም የላትም በሚል ትታማለች። የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽንም (ካፍ) «ከደረጃ በታች» ሲል መፈረጁም በዚሁ ምክንያት ነው። ከአዲስ አበባ ስታዲየም በተጓዳኝ በከተማዋ በሚካሄዱ ስፖርታዊ ሁነቶች አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው የአበበ ቢቂላ ስታዲየምም ለሁለት ዓመታት እገዛውን አቋርጦ ቆይቷል። በታላቁ ኢትዮጵያዊ አትሌት አበበ ቢቂላ የተሰየመው ስታዲየሙ በ1995 ዓ.ም ነበር ተገንብቶ ወደ ስራ የገባው። ይሁን እንጂ ስታዲየሙ ደረጃውን ያልጠበቀ በመሆኑ ምክንያት እንደሚጠበቀው ዘርፈ ብዙ አገልግሎት መስጠት አልቻለም። ስታዲየሙ 30ሺ ሰው ይይዛል ቢባልለትም፤ ከትሪቡኑ ውጪ ያለው ስፍራ ከኮንክሪት የተሰራ ከመሆኑ በዘለለ ወንበር አልነበረውም። በትሪቡኑ የሚገኘው ጣራና ወንበርም ቢሆን ከአገልግሎት ብዛት ምቹ የሚባል አልነበረም። የእግር ኳስ መጫወቻ ሜዳው ከፊፋ በተገኘ ድጋፍ ሰው ሰራሽ ሳር የለበሰ ቢሆንም በዙሪያው የሚገኘው ኮሮኮንች በመሆኑ፤ በአጋጣሚ ከሜዳ ወጥቶ የወደቀ ተጫዋች ላይ ጉዳት ያስከትል ነበር። በተለይ የስታዲየሙ መም አልባነት በከተማ አስተዳደሩ ለሚገኙ የአትሌቲክስ ክለቦች መለማመጃም ሆነ በፌዴሬሽኑ አዘጋጅነት ለሚካሄዱ ውድድሮች ፈተና በመሆኑ፤ በአዲስ አበባ ስታዲየም ለመስራት ይገደዱ ነበር። ከተማ አስተዳደሩ ለስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች በሰጠው ትኩረት መሰረትም ስታዲየሙ ሙሉ እድሳት ሊደረግለት ችሏል። በእድሳቱ ምክንያት ያለፉትን ሁለት ዓመታት የቆየው ስታዲየሙ አሁን አብዛኛው ስራው በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል። በተያዘው አዲስ ዓመት የውድድር ዘመን እስከሚጀመርበት ጊዜም ሙሉ ለሙሉ ስራው ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆንም ይጠበቃል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በዚህ ወቅት ደረጃውን የጠበቀ የመሮጫ መም እንዲሁም የተመልካቾች መቀመጫ ሙሉ ለሙሉ ተገንብቶ ተጠናቋል። ዋናውና የስራውን ከፍተኛ ድርሻ የሚይዘው የዙሪያ ጣራ ማልበስ ስራውም አብዛኛው ተጠናቆ ጥቂት ቋሚዎች ብቻ ናቸው የሚቀሩት። ከዚህ በኋላም ጣራውን የሚሸከሙትን ቋሚዎች ተመልካቾች እንዳይወጡባቸው የመሸፈን ስራ ብቻ ይቀራል። ከዚህ በኋላም ዙሪያውን ያሉት ሱቆች ጥቂት የማጥራት ስራ ብቻ ሲቀራቸው፤ የውሃ ታንከር ማቆሚያ፣ የኤሌክትሪክ ስራዎች፣ የስክሪን ገጠማ እንዲሁም የማጽዳት ስራዎች ብቻ የሚሰሩ መሆኑን የአበበ ቢቂላ ትምህርት እና ስልጠና ማዕከል ስራ አስኪያጅ አቶ ብርሃኑ ባዩ ይጠቁማሉ። እነዚህ ቀሪ ስራዎችም በቅርቡ የሚጠናቀቁ ሲሆን፤ በሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ መደበኛ አገልግሎቱን እንደሚሰጥ በከተማው ስፖርት ኮሚሽን ታቅዷል። ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ የግንባታ ሂደቱ 105ሚሊዮን ብር የፈጀ ሲሆን፤ በውለታው መሰረት ለተቋራጩ የሚከፈለው 60 በመቶ በብር እንዲሁም 40 በዶላር ነው። ነገር ግን እስካሁን ክፍያው ተጠቃሎ ለተቋራጩ አልተሰጠም፤ ለዚህም ምክንያት የሆነው እንደ ሃገር ያለው የምንዛሬ እጥረት ነው። ይህንንም ለሚመለከተው አካል በማሳወቅ ምላሽ በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኙ ስራአስኪያጁ ጠቁመዋል። የስታዲየሙ እድሳት ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ ለከተማዋ ተጨማሪ ብስራት እንደሚሆን ይጠበቃል። ከዚህ ባሻገር በከተማ ደረጃ ያለውን የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እጥረት እንደሚቀርፍ ይታመናል። የከተማዋ የፕሪምየር ሊግ ክለቦችስ ጨዋታዎችን ያስተናግዱባቸው ይሆን በሚል ለተነሳው ጥያቄ ስራ አስኪያጁ፤ ማዕከሉ የትምህርትና ስልጠና ማዕከል እንደመሆኑ ታዳጊ ወጣቶችን ለማፍራት የሚውል መሆኑን በምላሻቸው ጠቁመዋል። እንደሚታወቀው በሃገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄዱ የአትሌቲክስ ውድድሮች ላይ ከተማ አስተዳደሩ የሚያስመዘግበው ውጤት እየቀነሰ መምጣቱ ይታወቃል። በተለይ በአትሌቲስ ስፖርት በርካታ ክለቦች በከተማዋ ቢገኙም አትሌቶች ሲቸገሩና ለአደጋም ሲጋለጡ ቆይተዋል። ይህ የሆነበት ምክንያትም በከተማዋ ለስልጠና የሚሆን ስፍራ ባለመኖሩ ነው። በመሆኑም የስታዲየሙ መታደስ ፍላጎቱና ችሎታው ያላቸውን ታዳጊዎች ለማፍራት እንደሚያስችልም ያክላሉ ስራ አስኪያጁ። በተመሳሳይ የእግር ኳስ ሜዳው እንዲሁም የሶስት በአንድ(እጅ ኳስ፣ መረብ ኳስ እና ቮሊቦል) ሜዳውም ታዳጊዎች በኳስ ስፖርቶች ተተኪ ለመሆን የሚያስችላቸውን ስልጠና የሚያገኙበት ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። በቀጣይም የእግር ኳስ ሜዳውን እንዲሁም ስታዲየሙ በሃገሪቷ አሰራር መሰረት ደረጃው እንዲለይም ለሚመለከተው አካል እንደሚያሳውቁም ስራ አስኪያጁ ያመላክታሉ። ከዚህ ባሻገር የአካባቢውን ህብረተሰብ በማሳተፍና ተጠቃሚ በማድረግ የራሱን ገቢ ማመንጨት እንዲችልም ይደረጋል። በዚህም በዓመት ከ20ሚሊዮን ብር በላይ ለምክር ቤቱ ለማስገባት ታቅዷል፤ ይህ ብርም በየአካባቢው ላሉ ታዳጊዎች ድጋፍ የሚውልም ይሆናል። በእድሳት ስራው ላይ በስታዲየሙ የሱቅ ተከራዮች በቶሎ አለመልቀቅ፣ የውጪ ምንዛሬ እጥረት እንዲሁም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባለሙያዎች የተሳተፉበት የጣራ ናሙና መረጣ ላይ ጥቂት መዘግየቶች ገጥመዋል። ሌላው የስታዲየሙ እድሳት ለከተማዋ ነዋሪዎች የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ዘርፈ ብዙ መሆኑ ባያጠያይቅም የአካባቢው ለተጠቃሚዎች ምቹ መሆን አጠራጣሪ ነው። በተለይ ወደ ስታዲየሙ የሚወስዱት መንገዶች በእጅጉ መጎዳት እንዲሁም ለመኪና ማቆሚያ የሚሆን ምቹ ቦታ አለመኖር በችግርነት ተጠቃሽ ነው። ይህንን ጉዳይም ኮሚሽኑ ከዓመታት በፊት ለአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ቢያሳውቅም እስካሁን ለውጥ አለመኖሩን የማዕከሉ ስራ አስኪያጅ ያመለክታሉ። ከዋና መንገዱ ጋር የሚገናኘው እንዲሁም ሌሎች ወደ ስታዲየሙ የሚያደርሱ መጋቢ መንገዶች ጥናትና ይደረግባቸው በሚልና በሌሎች ምክንያቶች መዘግየቶች ቢኖሩም ኮሚሽኑ ጥያቄውን አላቋረጠም። በመጨረሻም በስታዲየሙ እድሳት ወቅት የአካባቢው ነዋሪ ላደረገው ከፍተኛ ድጋፍ ስራ አስኪያጁ ምስጋና አቅርበዋል።አዲስ ዘመን መስከረም 5/2012ብርሃን ፈይሳ ", "passage_id": "b88fe84ed204ee81605a960ed3aebca6" } ]
ecbb555d181c6a738856bfd0cebba93a
45eada520b80135f2da51e6ad708b565
የአገር አቋራጭ ሩጫና የፆታ እኩልነት ሙግቶች
በታሪክ አጋጣሚ ቀደም ባሉት ዓመታት በተለያዩ የአትሌቲክስ ውድድሮች ወንድና ሴት አትሌቶች በተለያዩ ርቀቶች በተመሳሳይ ውድድር ላይ ሲሮጡ መመልከት የተለመደ ነው። ‹‹ወንዶች የሚሮጡትን ርቀት ሴቶች መሮጥ አይችሉም›› የሚል አስተሳሰብ በነበረበት ዘመን በተመሳሳይ ውድድር ላይ ሴቶች ከወንዶች ያነሰ ርቀት ለመሮጥ ይገደዱ ነበር። እንዲያውም በአንዳንድ ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች ላይ ወንዶች በሚሮጡበት ርቀት ሴቶች እንደማይወዳደሩ ከታሪክ መረዳት ይቻላል። ለምሳሌ ያህል በታላቁ የዓለማችን የስፖርት መድረክ ኦሊምፒክ ማራቶን አንጋፋና ምናልባትም ከመጀመሪያ አንስቶ የሚካሄድ የውድድር አይነት ቢሆንም ሴቶች በርቀቱ መወዳደር የጀመሩት ዘግይተው ነው።በኦሊምፒክ መድረክ ብቸኛው የጎዳና ላይ ውድድር በሆነው ማራቶን ወንዶች መሳተፍ የጀመሩት እኤአ 1896 ላይ ነው። የሴቶች ማራቶን የኦሊምፒክ ውድድር ውስጥ የተካተተው ግን ዘጠና ዓመታትን ዘግይቶ በ1984 ኦሊምፒክ ነበር። ከማራቶን በተጨማሪም በርካታ በተለይም ረጅም ርቀት ውድድሮች በኦሊምፒክም ይሁን በዓለም ቻምፒዮና ሴቶችን ማካተት የጀመሩት ዘግይተው ነው። ይሁን እንጂ በዘመናዊው የአትሌቲክስ ዓለም ሴቶች ወንዶች በሚወዳደሩበት ርቀት ሙሉ በሙሉ ለማለት በሚያስችል ደረጃ ተወዳዳሪ ናቸው።ከአታካቹ ማራቶን አንስቶ እስከ ተለያዩ የጎዳና ላይ ውድድሮች ሴቶች ወንዶች የሚሮጡትን ርቀት በመሮጥ ብቃታቸውን አስመስክረዋል። ርቀቶቹን ሮጠው  ለማጠናቀቅ የሚፈጅባቸው ሰዓት ከተፈጥሮ ጋር በተያያዘ ከወንዶች የዘገየ ቢሆንም የትኛውንም ርቀት ሴቶች አይሮጡም ብሎ የሚያምን ሰው ፈልጎ ማግኘትም ከባድ የሚመስልበት ዘመን ላይ ተደርሷል። ይሁንና ሴቶች በአገር አቋራጭ ውድድሮች ላይ ከወንዶች ያነሰ ርቀት እንዲሮጡ መደረጉ በአትሌቲክሱ ቤተሰቦች መከራከሪያ አጀንዳ ከሆነ ዓመታት ተቆጥረዋል።እንግሊዛዊቷ የቀድሞ የአገር አቋራጭ ቻምፒዮና የሜዳሊያ ባለቤት አትሌት ጆ ፓቬይ «በአገር አቋራጭ ውድድሮች ሴቶች ከወንዶች ባነሰ ርቀት መወዳደራቸው የፆታ እኩልነትን አያሳይም» የሚል አስተያየት ከሁለት ዓመት በፊት ለስካይ ኒውስ መስጠቷን ተከትሎም የአገር አቋራጭ ውድድር አዘጋጆች ከአትሌቲክስ ቤተሰቡ ጋር ሙግት ገጥመው እንደነበር ይታወሳል። በርካታ የስፖርቱ ባለሙያዎችና የውድድር አዘጋጆችም በጉዳዩ ላይ ሲሟገቱ ይስተዋላል። አገር አቋራጭ ውድድሮች በየዓመቱ በተለያዩ ከተሞች በተለይም በአውሮፓ ይካሄዳሉ። የዓለም አትሌቲክስም በየሁለት ዓመቱ የዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና ያዘጋጃል። በእነዚህ ውድድሮች ሴትና ወንድ አትሌቶች በእኩል ርቀት ሲወዳደሩ አይታይም። እኤአ ከ2017 በፊት በዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና የሚካሄደው ፉክክር በአራት አይነት መንገድ ተከፍሎ ነው። የመጀመሪያው አዋቂ ወንዶች የሚወዳደሩበት የአስራ ሁለት ኪሎ ሜትር ውድድር ሲሆን አዋቂ ሴቶች ስምንት ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ርቀት ላይ ብቻ ተፎካካሪ ነበሩ። በወጣት ወንዶች መካከል የሚካሄደው ውድድር ደግሞ ስምንት ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን ወጣት ሴቶች ስድስት ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ፉክክር ያደርጋሉ። እነዚህ ርቀቶች በዓለም ቻምፒዮናም ይሁን በግል አገር አቋራጭ ውድድሮች በብዛት የተለመዱ ናቸው። አልፎ አልፎ ግን በዓለም ቻምፒዮናም ይሁን በግል ውድድሮች እንደየሁኔታው ወንዶች ከሴቶች እኩል ርቀቶችን የሚሮጡበት አጋጣሚ ሲፈጠር ይታያል። ለአብነት ያህልም በ2017 በዩጋንዳ ካምፓላ ተካሂዶ የነበረው የዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮናን ማንሳት ይቻላል። በዚህ ቻምፒዮና ለመጀመሪያ ጊዜ አዋቂ ሴቶችና ወንዶች እኩል አስር ኪሎ ሜትር የሸፈነ ውድድር ማድረጋቸው ይታወሳል። «ታዲያ ሴቶች በዚህ ውድድር ከወንዶች እኩል መሮጥ እየቻሉ አነስተኛ ርቀት እንዲሮጡ መደረጋቸው ለመጪው ትውልድ ምን አይነት መልዕክት ያስተላልፋል?» የሚል ከጾታ እኩልነት አኳያ ጥያቄ የሚያነሱ ቁጥራቸው ብዙ ነው።በምስራቅ ለንደን የአትሌቶች ማህበር አባል የሆነችው ማዑድ ሆድሰን በዚህ ውድድር የጾታ እኩልነት መረጋገጥ ካለበት ሴትም ወንድም እኩል ርቀት መሮጥ አለባቸው የሚል አቋም ይዛ ባለፉት ዓመታት ስትከራከር ቆይታለች። ይህን ሃሳቧንም በርካቶች ደግፈውታል። ሆድሰን በጉዳዩ ላይ ለራነርስ ዌብ ከዓመታት በፊት እንደገለፀችው፣ በአገር አቋራጭ ውድድሮች ሴትና ወንድ እኩል ርቀት እስካልሮጡ ድረስ መጪው የአትሌቲክስ ትውልድ በሩጫው ዓለም ሴትም ወንድም እኩል መሆናቸውን ሊረዳ አይችልም። ወንዶች ከፍ ያለውን ርቀት መሮጣቸው በአገር አቋራጭ ውድድሮች የሴቶቹ ፉክክር ከወንዶቹ ያነሰ የሚመስል ትርጉም ይሰጠዋልም ትላለች። ሆድሰን በዚህም ሳታበቃ በጉዳዩ ላይ አንድ መፍትሄ ለማምጣት በኤሌክትሮኒክስ መንገድ ፊርማ አሰባስባ በቀናት ውስጥ ከአንድ ሺ በላይ ተከታዮችን አግኝታለች። ይህ ሃሳብ በፌስ ቡክ ገፅም«አይ ወዝ ኦር አም ራነር» በሚል በተፈጠረ የቡድን ገፅም በርካታ ወንዶች የደገፉት ሲሆን ብዙ ተከታዮች አግኝቶ መነጋገሪያነቱ እየጨመረ መጥቷል።አዳጋች በሆነው የአገር አቋራጭ ውድድር አትሌቶች በጭቃ፤ በዳገትና ቁልቁለት አልፎ አልፎም በበረዶ ይፈተናሉ። ይህን ከግምት የሚያስገቡ በርካታ ሰዎች ሴቶች በውድድሩ እንደ ወንዶች ረጅም ኪሎ ሜትር መሮጥ አይችሉም የሚል አስተሳሰብ እንዲይዙ ያደርጋቸዋል። አንዳንድ ጥናቶች እንደሚያመላክቱት ግን ሴቶች በሌሎች ፈታኝ በሚባሉ ማራቶንና ግማሽ ማራቶን ውድድሮች ላይ ከወንዶች እኩል ርቀት ሮጠው ከሚያስመዘግቡት የሰዓት ልዩነት የተጋነነ አያስመዘግቡም። በቢኬት ዩኒቨርሲቲ የስፖርት ሳይንስና ባዮሜካኒክስ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ብሬን ሃንሌይ ጥናታዊ ፅሁፍ ግን በአገር አቋራጭ ውድድር ሴቶች ከወንዶቹ ባልተናነሰ ተመሳሳይ ርቀት መወዳደር እንደሚችሉ ይጠቁማል። ጥናቱ ልክ እንደ ወንዶቹ የሴቶቹም ውድድር መጀመሪያ ላይ ቀዝቃዛ ፉክክር የሚታይበት ቢሆንም መጨረሻው በፉክክር የታጀበ እንደሚሆን አረጋግጧል። አብዛኞቹ የውድድር አዘጋጆች ግን ሴቶች በዚህ ውድድር ከወንዶች እኩል ርቀት ቢሮጡ መጨረሻው በፉክክር እንደማይታጀብና አሰልቺ እንደሚሆን ስለሚያምኑ ሴቶች አነስተኛ ርቀት እንዲወዳደሩ ያደርጋሉ የሚል ክርክር ይነሳል። ይህ ግን ዞሮ ዞሮ ከፆታ እኩልነት ጋር ባይያያዝ እንኳን በርካታ ወጣት አትሌቶችን ወደ ውድድሩ እንዳይመጡ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል መላ ምቶች ይቀመጣሉ። ይህም ርቀቱ በረዘመ ቁጥር በርካታ አትሌቶች እንደ ጎዳና ላይ ረጅም ርቀት ውድድሮች ሁሉ የመወዳደራቸው አጋጣሚ ሰፊ ይሆናል የሚል ነው።የአርባ ስድስት ዓመቷ ጆ ፓቬይ አትሌቲክስን ካቆመች በርካታ ዓመታት ቢቆጠሩም ሴቶች በአትሌቲክሱ ዓለም አስደናቂ ታሪኮችን ከወንዶች እኩል መስራታቸውን በማስታወስ በአገር አቋራጭ ውድድሮችም ከወንዶች እኩል ርቀት መሮጥ እንዳለባቸው ከስካይ ኒውስ ጋር በነበራት ቆይታ ገልፃለች። «ለበርካታ ዓመታት በአስቸጋሪው የማራቶን ውድድር ሴቶች ከወንዶች እኩል ርቀት ሲወዳደሩ ቆይተዋል፤ በአገር አቋራጭ ውድድሮች እኩል ርቀት ያለመሮጣቸው ሴቶች ከወንዶች እኩል አቅም የላቸውም የሚል አመለካከትን ይፈጥራል» በማለትም ፓቬይ አቋም ይዛለች።የማራቶን ባለክብረወሰኗና የቀድሞ የዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮኗ አትሌት ፓውላ ራድክሊፍ ሰሞኑን በጉዳዩ ላይ በማህበራዊ ሚዲያው የሚደረገውን ክርክር ተቀላቅላ ‹‹ርቀቶች መመሪያ ናቸው፣ የአገር አቋራጭ መወዳደሪያ ቦታዎች ጥሩ ከሆኑ በሁለቱም ፆታ ተመሳሳይ ርቀት ቢሮጥ ችግር የለውም፣ የውድድሩ ተፈጥሯዊ ባህሪ ሆኖ አንዳዶች አጭር ርቀት መሮጥ ሲፈልጉ ሌሎች ረጅም መሮጥ ሊፈልጉ ይችላሉ፣ ወንድም ሴትም ተመሳሳይ ርቀት መሮጥ እንደሚችሉ ግን አምናለሁ›› በማለት ፅፋለች። የአገር አቋራጭ ውድድር አዘጋጆች ይህ ልዩነት ለምን እንደተፈጠረ አሳማኝ ምክንያት ማቅረብ ባይችሉም በተለምዶ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ በመሆኑ ብቻ አሁን ላይ እየተገበሩት እንደሚገኙ ይታመናል። ይህ ግን በአንዳንድ የስፖርት ቤተሰቦች የፆታ ልዩነት እንዳለ ለማሳየት ሆን ተብሎ የተደረገ ሳይሆን የሴቶቹን ፉክክር ረዘም ላለ ሰዓት መመልከት ስለማይፈለግ ነው የሚል ትችት ይቀርባል። የእንግሊዝ አገር አቋራጭ ውድድር ማህበርም ይህ ልዩነት በተለምዶ አሰራር የመጣ መሆኑን በማመን በአገር አቀፍ ውድድር ላይ ሴቶች ከወንዶች እኩል ርቀት መሮጥ እንዳለባቸው ሲከራከርና ተፅዕኖ ሲያሳድር ቆይቷል። በዚህም የእንግሊዝ አትሌቲክስ ማህበርን ድጋፍ ማግኘት ችሏል። የእንግሊዝ አትሌቲክስ ማህበርም ጥያቄውን ወደ ፊት በማምጣት የተለያዩ ሙግቶችን ሲያደርግ ቆይቷል። ለረጅም ጊዜ ጉዳዩ የተዘነጋና ተድበስብሶ ያለፈ ቢመስልም የእንግሊዝ አትሌቲክስ ማህበር ከቀናት በፊት ዳግም ጉዳዩን በማንሳት በጥናት ጭምር አስደግፎ እየተሟገተ ይገኛል። አትሌቲክስ ማህበሩ በፈጠረው ተፅዕኖ በአገሪቱ በሚደረጉ የአገር አቋራጭ ውድድሮች ላይ ለውጦች ማምጣት ቢችልም በዓለም አቀፍ ደረጃ የተለያዩ የውድድር አዘጋጆችን ለማሳመን ተጨማሪ ስራዎች ይቀሩታል። ለዚህም የአውሮፓ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ላይ የሰራውን ጥናት ሰሞኑን ይፋ አድርጓል። 2016 ላይ ከሃምሳ አንድ የአውሮፓ አገራት አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ሰላሳ ሰባቱ ለጥናቱ ምላሽ የሰጡ ሲሆን ከሰላሳ ሰባቱ ሃያ አንዱ ሴቶችና ወንዶች በአገር አቋራጭ ውድድሮች እኩል ርቀት መሮጥ አለባቸው የሚል እምነት እንዳላቸው ጠቁሟል። አገር አቋራጭ ውድድር እንደ ረጅም ርቀት ውድድሮች ሁሉ በስፋት የሚታወቁት ምስራቅ አፍሪካውያኑ ኢትዮጵያና ኬንያ ቢሆኑም በጉዳዩ ላይ የተነሳው ሙግት ከወደ ምዕራባውያኑ መሆኑ አስገራሚ ነው። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቴክኒክ ዳይሬክተር የነበሩትና አሁን የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር የሆኑት አቶ ዱቤ ጂሎ በአንድ ወቅት ከአዲስ ዘመን ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስ በዚህ ጉዳይ ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያለውን አቋም አሳውቀው ነበር። አቶ ዱቤ ይህ በሴቶችና በወንዶች አገር አቋራጭ ውድድሮች ላይ ያለው የመወዳደሪያ ርቀት በተለምዶ ሲሰራበት ስለመጣ እንጂ ሴቶች ወንዶች የሚሮጡትን ርቀት መሮጥ ስለማይችሉ የተፈጠረ እንዳልሆነ ያብራራሉ። የርቀቱ ልዩነት የመጣው ቀደም ሲል በውድድሩ ደንብ ላይ የተቀመጠ በመሆኑ እንጂ ከጤናም አኳያ ይሁን ከሌሎች ነገሮች ሴቶች በአገር አቋራጭ ውድድር ከወንዶች ያነሰ ርቀት እንዲሮጡ የሚያደርጋቸው ምንም አይነት አሳማኝ ምክንያት እንደሌለ ገልፀው ነበር። «ሴቶች ከወንዶች እኩል በአገር አቋራጭ ውድድር መሮጥ አለባቸው፤ ማራቶንም ይሁን ግማሽ ማራቶን እኩል እስከ ሮጡ ድረስ በአገር አቋራጭም እኩል ርቀት መሮጥ አለባቸው፤ ይህ ካልሆነ ማራቶንም እኩል ኪሎ ሜትር መሮጥ የለባቸውም» በማለትም አቶ ዱቤ ሃሳባቸውን ሰንዝረው ነበር። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በየዓመቱ ጃን ሜዳ ኢንተርናሽናል አገር አቋራጭ ውድድሮችን በክልሎችና በክለቦች መካከል እንደሚያካሂድ ይታወቃል። በነዚህ ውድድሮች ወንዶቹም ሴቶቹም እኩል ርቀት የሚሸፍን ውድድር እንዲያካሂዱ ማድረግ ይቻላል ያሉት አቶ ዱቤ፣ ይህን ጥያቄ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለዓለምአቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ሊያቀርብ እንደሚችልም ጠቁመዋል። ከዚያም ዓለምአቀፍ ማህበሩ አሁን ያለውን ህግ አሻሽሎ በተመሳሳይ ርቀት እንዲወዳደሩ ከፈቀደ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም በእኩል ርቀት ውድድሮቹን ለማካሄድ የሚያግደው ነገር እንደሌለ አብራርተዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 17/2013 ዓ.ም
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=38194
[ { "passage": "1953 ዓ.ም ከአዲስ አበባ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው አቃቂ ከተማ ጋርዱባ 06 አካባቢ ነበር የተወለደው፤ በልጅነቱ ፈጣንና አስተዋይ እንደነበር ይነገራል። የታዳጊው ሁኔታ በቤተሰቦቹም ሆነ በአካባቢው ሰዎች ዘንድ ከፍተኛ ደረጃ እንደሚደርስ ተስፋ እንዲጣልበት አድርጎታል። የታዳጊው ብሩህ አዕምሮ በቀለም ትምህርት ቢታገዝ ደግሞ እኛንም አገሩንም ያኮራል ብለው አስበዋል።ተሻጋሪ ተስፋ ማድረግ ብቻም ሳይሆን በአካባቢው በሚገኘውና ፊት አውራሪ በሚባለው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት አስመዘገቡት። በአስኳላ ውሎው በጥሩ ተማሪነትና በፈጣን ሯጭነቱም ጭምር ለመታወቅ የቻለው የትናንቱ ታዳጊ የቀድሞ አትሌት ሸምሱ ሀሰን ነው። የትምህርት ቤት ቆይታውን እየወደደው ቢመጣም፤ የቤተሰቦቹ ሁኔታ ግን ሊያራምደው አልቻለም።የቤተሰቡን ችግር ለማቃለል እርሱ ቢያንስ ራሱን ማስተዳደር ቢችል ትልቅ ብርታት እንደሚሆናቸው ሃሳቡ ነበር። በቀለም ትምህርቱ ብዙ ርቀት መጓዝ ቢያልምም አልቻለም። ከቤተሰብ ጥገኝነት ለመላቀቅ ከስድስተኛ ክፍል አቋርጦ ወደ ውትድርና ለማቅናት ወሰነ። አደረገውም፤\nሸምሱ፤ በብሄራዊ ውትድርና ውስጥ ለስልጠና የተመደበለትን ጊዜ አጠናቀቀ። አዲስ አበባ ማዕከላዊ ዕዝ ተመድቦ የህይወቱን ሌላኛውን ምዕራፍ ማጣጣሙን ያዘ። ሸምሱ የልጅነት ህልሙ በዚህ መልኩ እንዲሆን ፍላጎት ባይኖረውም፤ የሆነውን ግን ተቀብሎ ቀጠለ። በትምህርት ቤት ውስጥ ፈጣንና ተስፈኛ እግሮቹ በጦሩ ቤት ያለውን ቆይታ ወደ ስፖርት እንዲገባ አስችለውታል። በማዕከላዊ ዕዝ ውስጥ የሚያደርገው የስፖርት እንቅስቃሴ በጦሩ ውስጥ ለእጩነት አበቃው።የእርሱን የዕጣ ጎዳና በአትሌቲክሱ ያደረገው አጋጣሚም በዚህ መልክ ተወለደ። የስፖርት አጀማመሩ በ1500 ሜትርና በ800 ሜትር ነበር። በእነዚህ ርቀቶች በተለያዩ ውድድሮች በመሳተፍ ሁለት ጊዜ ሦስተኛ ደረጃ ይዟል። አትሌቱ እግሮቹን ያሟሸው በእነዚህ ርቀቶች ይሁን እንጂ፤ እስከመጨረሻ የዘለቀው ግን በእርምጃ ውድድር ነበር። አጋጣሚው እንዲህ ነበር። አንድ ቀን በማዕከላዊ ዕዝ ስፖርት ውስጥ ብዙም ባልተለመደው የእርምጃ ሩጫ እንዲሳተፍ ይጠየቃል። ጥያቄው ለተሳትፎ ያህል የነበረ ቢሆንም፤ በውድድሩ ባለድል መሆን ቻለ። በ1974 ዓ.ም በአገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደ ውድድር ተሳትፎ አሸናፊ ሆነ። አትሌቱ በእርምጃ ውድድሩ አሸናፊነቱ በአሰልጣኞቹ የመመረጥ እድል አገኘ። አገሩን ለማስጠራት በብዙዎች ዘንድ ተስፋ እንዲጣልበት ያደረገም ነበር።በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ውስጥ ስማቸው ተጠቃሽ ከሆኑት መካከል ሻለቃ ባሻ ዋሚ ቢራቱ የሸምሱን ተስፈኝነት ከመሰከሩ ታላላቅ የስፖርት ሰዎች መካከል ተጠቃሽ ነበሩ። የእርሱ የእርምጃ ሩጫ የተለየ ክህሎት በመገንዘብና አርቀው በማስተዋል በደንብ እንዲሰራ ይመክሩት ነበር። ይህም በስፖርቱ ጉዞውን የጀመረበትን ርቀት በመተው ወደ እርምጃ ሩጫው ብቻ እንዲያዘነብልም ጭምር ሀሳብ እስከ መለገስ ደርሰዋል። እርሱም በእርምጃ ስፖርት ውድድር መጽናቱን ነው የሚናገረው፤ አገራችን በእርምጃ ውድድር ግን በማትታወቅበት ሁኔታ ገፍቶ ለመሄዱ የዋሚ ቢራቱ ምክር ለእርሱም ብቻም ሳይሆን በወቅቱ ለነበሩት ወንዴ ጦሬ፣ ተከስተ ዮሃንስ፣ ጥላሁን ሸገና በጽናት እንዲቆዩ ያደረገ ጭምር እንደነበር ሸምሱ ያስታውሳል።እርሱ እንደሚለው፤ «በአገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄዱ ውድድሮች እይታ ውስጥ ለመግባት የቻልኩበትን አጋጣሚ መፍጠር ቻልኩ። ይህ ሁኔታ ደግሞ የተሳትፎዬን ደረጃ ተሻጋሪ የሚያደርግልኝን አጋጣሚ ይዞ ብቅ አለ። በአገር ውስጥ የእርምጃ ውድድር ብቃቴ ተለክቶ በዓለም አቀፍ መድረክ ታጨሁ። በ1975 ዓ.ም በኬኒያ ናይሮቢ ላይ በተካሄደው የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ውድድር ላይ በእርምጃ ሩጫ ለአገሬ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ ማምጣት ቻልኩኝ። በዚህ ድል ለራሴም ሆነ ለእናት አገሬ አኩሪ ድል ያመጣሁበት ትልቅ የህይወት አጋጣሚዬ ነበር። ይህም አሸናፊነት ገና ጅምር እንጂ የሚያበቃ እንዳልሆነም ለራሴው ቃል የገባሁበት አጋጣሚም ነው»።የልጅነት ህልሙ መስመሩ በስፖርት ውስጥ ይሆናል የሚል ቅንጣት ያህል ፍላጎት ያልነበረው ወጣቱ ከስኬት ወደ ስኬት መሸጋገር ጀመረ። ከአንድ ዓመት ቆይታ በኋላ ግብጽ ውስጥ የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በመሳተፍና በአንደኝነት በማጠናቀቅ የወርቅ ሜዳሊያ እንዳሸነፈ ይናገራል። ከዚህ በኋላም፤ በተለይ በኬኒያ እና በግብጽ በተዘጋጁ ውድድሮች ላይ በተደጋጋሚ የመሳተፍ እድል እንደነበረው ያስታውሳል። «በኬኒያም ሆነ በግብጽ በተካሄዱ ውድድሮች አሸናፊ መሆን ችያለሁ። ኬኒያ ውስጥ በተካሄዱ ውድድሮች አራት ጊዜ ተሳትፌያለሁ። በሁሉም አንደኛ ሆኜ ነው ያሸነፍኩት፤ በግብጽ በተመሳሳይ የመሳተፍ አጋጣሚዎች ነበሩኝ። ከነበሩት አራት ውድድሮች በአንዱ ብቻ ሁለተኛ ስወጣ የተቀሩትን በአሸናፊነት ነበር ያጠናቀኩት» ይላል ሸምሱ።የወጣቱ የድል ጉዞ ከፍ በማለት በአራት ዓመት አንዴ በሚዘጋጀው ኦል አፍሪካ ጌምስ ላይ ሦስት ጊዜያት የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት ለመሆን በቅቷል። ፈጣኑና ትንታጉ አትሌት የድል አድማሱን ከፍታ ከአህጉር አፍሪካ ተሻግሮ ለኦሎምፒክ ውድድር ወደባርሴሎና መጓዙን የሚያስታውሰው ሸምሱ በውድደሩ አምስተኛ ደረጃ በመያዝ ነበር ያጠናቀቀው፤ ሩሲያ በመጓዝ ደግሞ ስምንተኛ ወጥቶ ማጠናቀቁን ያስታውሳል። «በጊዜው እኔ ትኩረት የማደርገው ሰዓቴን ማሻሻሌን ነው» ይበል እንጂ፤ አገራችን ብዙም ባልታወቀችበት የእርምጃ ውድድር በድሉ ከአገር ውስጥ እስከ አህጉር፤ ከዚያም እስከ ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች የተሻገረ ስኬት ያስመዘገበ የአገር ባለውለታ ነው። ሸምሱ በአትሌቲክሱ እያደገ የመጣው ውጤቱ በማዕረግ የታጀበም ሲሆን፤ ከአስር አለቅነት እስከ ሻለቃነት የደረሰ ነበር።የሸምሱ የስፖርት ጉዞው ብቻም ሳይሆን የህይወት ኡደቱ ከ1974 እስከ 1992 ወርቃማ ዓመታት ናቸው ለማለት ያስደፍራል። አትሌቱ በእነዚህ 18 ዓመታት በስፖርቱ እራሱንም ሆነ አገሩን አስጠርቷል። ቤተሰብ በማፍራትም ህይወቱን በደስታ አጣጥሟል። የዚህ ሁሉ ታሪክ ባለቤት የሆነውና የቀድሞው የእርምጃ ውድድር ባለድሉ ጎልማሳ የአዕምሮው ሁኔታ በመታወኩ ምክንያት እጅና እግሩን አጣጥፎ ከቤት ለመዋል ተገደደ። ከእርሱ በኋላም በመስኩ አሸናፊ ሆኖ የወጣ አትሌት አለመኖሩን ባገላበጥናቸው የተለያዩ መረጃዎች ለመገንዘብ ችለናል። በአሁኑ ወቅት ግን ለአገሩ የሰራው ገድል ተረስቶ፤ እርሱም አስታዋሽ አጥቶ በአዕምሮ ህመም እየተሰቃየ ይገኛል። ከኬኒያ እስከ ሩሲያ በእርምጃ ብቻ ሜዳሊያዎችን ያስገኙ እግሮች፤ የሚመራቸው ጤናማ አዕምሮ አጥተው ተሳስረው ቁጭ ለማለት ተገድደዋል። በከባድ ህመም ውስጥ ከመሰቃየት በቀር አማራጭ ያጣው ሸምሱ፤ በተለያዩ ውድድሮች አሸናፊ ቢሆንም ዘመኑ ስፖርተኞች እንዲህ እንደዛሬው የማይሸለሙበት ነበርና በስፖርቱ ተጠቃሚ መሆን እንዳልቻለ ይናገራል። «በአሁን ሰዓት አላውቅም እንጂ እኔ በነበርኩበት ጊዜ የገንዘብ ሽልማት ሳይሆን የአበባ ጉንጉን ነበረ ወደ አገራችን ስንመለስ የሚበረከትልን፤ መንግሥት በእርምጃ ውድድር አሸንፌ ስመጣ ይሰጠኝ የነበረው ከብር 1500 ያልበለጠ ገንዘብ ነበር» በማለት በጊዜው ከስፖርቱ ተጠቃሚ እንዳልነበር ያስታውሳል። የአገር ባለውለታ የሆነው የቀድሞው አትሌት ሸምሱ ሀሰን በስፖርቱ ያገኘው ጥቅም ያለመኖሩ ብቻም ሳይሆን ጤናው መታወኩ ደግሞ ቤተሰብ ይዞ በችግር ለመቆራመት እንደዳረገው ይናገራል።አትሌቱ ሲጀመር ስምንት መቶ፤ በአሁኑ ወቅት ደግሞ 1400 ብር በሚያገኛት የጡረታ ገንዘብ በችግር መኖር እጣው ሆኖበታል። የተገኘውን ሥራ ለመስራት እንዳይችል ህመሙ ጋሬጣ ሆኖበት የሚያገኛትን የጡረታ ገንዘብ አጠገቡ ከሚገኙት ባለቤቱና ሁለቱ ልጆቹ ጋር በመቋደስ የችግር ህይወት ለመግፋት ግድ እንደሆነበት ይገልጻል። የሥራ ፍላጎት ቢኖረውም የህመሙ ሁኔታ ሰርቼ እንኳን ለመብላት እንዳልችል አድርጎኛል ሲል ይናገራል። በአንድ ባንክ ውስጥ በጥበቃ ስራ ተቀጥሮ መስራት ቢጀምርም የጤናው ሁኔታ የሚያሰራ አይደለምና መቀጠል አልቻለም። የመንፈስ ከፍታው በዚህ ደረጃ የሆነው ሸምሱ ከአንዴም ሁለት ሦስቴ የተለያዩ ስራዎችን ለመስራት ጥሯል። የእርሱ ሁኔታ አላላውስ ያላት ባለቤቱም የህይወት አጋሯን በቤት ውስጥ ሆና ከማስታመም በስተቀር ወጥታና ሰርታ ተጨማሪ ገቢ ለማምጣት እንዳትችል ሳንካ እንደፈጠረባት ሲቃ እየተናነቀው ይናገራል።ሸምሱ፤ የጤናው መቃወስ ይሄንን ጠንካራ የመንፈስ ከፍታውን የናደበት ሲሆን፤ «አሁን ካለሁበት የችግር አረንቋ እንድወጣ እጃችሁን ዘርጉልኝ» ሲል ጥሪውን ለአገሩ ህዝብ ለማቅረብ ተገድዷል። ለርዳታ ጥያቄ የተዘረጋውን እጁን ተከትሎ የሁለት ኢትዮጵያዊያን ወገኖቹን ምላሽ እንዳገኘ አጫውቶናል።«እስካሁን የሁለት ኢትዮጵያዊያን ወገኖቼን መጎብኘት አስገኝቶልኛል። አንዷ ሁለት ሺ ብር አንደኛዋ ደግሞ አንድ ሺ ብር ሰጥተውኛል። ይሁን እንጂ፤ የእነዚህ ወገኖች ድጋፍ አሁን የደረሰበትን የጤና ችግርና ባዶውን ማጀት ለመሙላት አይችልም። አሁንም ጥያቄ የሆነብኝ ነገር አትሌቲክስ ፌዴሬሽኑ ስለምን በእኔ ላይ ጨከነ? ምን በድየው ይሆን!? ሊያስታውሰኝ እንዴት አቅም አጣ? ምን ላይ ወደክ እንኳን አላለኝም። እንዴት ነህ መባሉ የተሰበረን መንፈስ ያክማል። የገንዘብ ድጋፍ ይቅርና እስካሁን የት ወደክ አላለኝም። ይህ ሁሌም ጥያቄ የሚያጭርብኝና የዘወትር ብስጭቴ ነው» ሲል ሃሳቡን ይቋጫል።አገራችን ብዙም ስሟ በማይነሳበት በእርምጃ ውድድር በግሉ ጥረት ከፍ ብሎ የነበረውን የቀድሞ አትሌት ሸምሱ ሀሰን በአሁን ወቅት ካጋጠመው የጤና ቀውስና ከገባበት የችግር አረንቋ እንዲወጣ ድጋፍ ሊደረግለት ይገባል። በአሁን ወቅት በአዕምሮ ህመም መሰቃየት ብቻም ሳይሆን በጡረታ በሚያገኛት አንድ ሺህ አራት መቶ ብር ስድስት ቤተሰብ እያስተዳደሪ እንደሚገኝ ተናግሯል። ሸምሱ እንዲህ እንደዛሬው ህይወት ፊቷን ሳታዞርበት የጤናው ሁኔታም ባልተቃወሰበት ወቅት በአትሌቲክሱ በተወዳዳሪነት ብቻ ሳይሆን በአሰልጣኝነት አገልግሏል።የአገር መከላከያ ሰራዊት አባል በመሆንም ለአገሩ ለመድማትና ለመሞት እራሱን አሳልፎ ሰጥቷል። ሸምሱ አነሰም በዛም እናት አገሩን ለማገልገል የተቻለውን ያህል ርቀት እንደመሄዱ፤ ከዛሬው ሰቆቃው እንዲወጣ ሁሉም የበኩሉን ሊያግዘው ይገባል። በተለይ፤ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቀድሞውን አትሌት ማስታወስ ይጠበቅበታል። የአገር ባለውለታ የሆነውና የተረሳው የቀድሞው አትሌት የዚህ ባለታሪክ ሆኖ ይቅረብ እንጂ፤ አስታዋሽ የማጣት ቁጭት፤ የጤና መቃወስ፣ የወገን አይዞህ ባይነት ማጣት እንደ ሸምሱ ሁሉ በበርካታ የአገር ባለውለታዎች ላይ የደረሰ በደል ነው። በጉብዝናቸው ወቅት ለአገራቸው ታሪክ የሰሩትን በቁም እያሉ ለመርዳትና ለማዳን ርብርብ አለማድረግ ሲያልፉ ቁጭትን ሲያጭር በተደጋጋሚ ይስተዋላል። በተለያዩ ዘርፎች ተሰማርተው የነበሩ የአገር ባለውለታዎችን ተረባርቦ በህይወት ለማቆም ሳይሆን ከሞቱ በኋላ ኃውልት ለማቆም መሯሯጥ መገለጫችን ይመስለኛል።የአገር ባለውለታዎችን ማሰብ ጥቅሙ ለአገር ነው። በተለያዩ ዘርፎች ለአገር የአቅማቸውን የሚበረክቱ ጀግኖችን ማፍራት ብቻ ሳይሆን፤ ከከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ጀግኖችን የመርሳት አባዜም ባለቤት ነን። በተጨማሪም በቁም ሳለ ከችግሩ፣ ከበሽታው ለማዳን ርብርብ ከማድረግ ይልቅ ለመቅበር የሚደረገው ርብርብ «አጃኢብ»ያሰኛል። ለዚህም ትልቁ ማሳያ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ነው። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በአትሌቲክሱ ብዙ አስተዋጽኦ ያደረጉ ጀግኖችን ማስታወስና መዘከር የማይሆንለት እንደሆነ በተለያዩ አጋጣሚዎች ታዝበነዋል። በተለያዩ አለም ዓቀፍ ውድድሮች ላይ በእርምጃ ውድድር ሜዳሊያዎችን ያገኘው የቀድሞው አትሌት ሸምሱ፤«አትሌቲክስ ፌዴሬሽኑ ስለምን በእኔ ላይ ጨከነ? ምን በድየው ይሆን? ሊያስታውሰኝ እንዴት አቅም አጣ?» ሲል ቁጭቱን ሲገልጽ ታዝበናል።በኦሊምፒኮችና በዓለም ሻምፒዮናዎች ላይ ኢትዮጵያን ወርቅ በወርቅ ያደረጉ ጀግኖች አትሌቶች ዋና አሠልጣኝ የነበሩት ዶ/ር ወልደ መስቀል ኮስትሬን፣ ሻምበል ምሩፅ ይፍጠርን በህይወት ሳሉ በመርሳት፤ ህይወታቸው ካለፈ በኋላ ኃውልት ለማቆም ሲታትር ነበር። ይህም ፌዴሬሽኑ አንጋፋዎቹ የአገር ባለውለታዎች ህይወታቸው ሳይቃወስ ድጋፍ ከማድረግ ይልቅ፤ ሲሞቱ ለሙሾና ለሀውልት ከመሮጥ አባዜው ዛሬም እንዳልተላቀቀ ከተለያዩ ወገኖች የተሰነዘረ ትችት ነው።ፌዴሬሽኑ ትናንት ከሰራው ስህተት ከመማር ይልቅ፤ ሌላ ታሪካዊ ስህተት ለመፈጸም እደማይመለስም አብሮ የተነሳ ሃሳብ ነበር። በአትሌቲክስ ፌዴሬሽን በኩል የአገር ባለውለታዎችን እጀ ሰባራ የማድረጉ ስንኩሉ ልምድ በስፖርቱ ብቻም ሳይሆን፤ በተለያዩ የሙያ መስኮች የዜግነት ግዴታቸውን የተወጡ የአገር ባለውለታዎች የመደገፍ ልምዱ ኢምንት ነው። የአገር ባለውለታዎቹ ምናልባትም የሚታወሱት ወይ ታመው አልጋ ሲይዙ፣ ወይም ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ ነው፡፡ አንጋፋዎች ሲዘነጉ ተከታዩ ትውልድ ተስፋ ይቆርጣል፡፡ ለባለውለታዎች ዕውቅና ለመስጠት በሕግ ማዕቀፍ የሚመራ የሜዳሊያና የኒሻን፣ በአገልግሎት ዘመን መጠን የሚበረከት ሽልማትና የምሥጋና ሥነ ሥርዓት ሊኖር ይገባል፡፡ አገርን በፍቅር ማገልግል የውዴታ ግዴታ ቢሆንም፣ አስመስጋኝ ተግባር ላከናወኑ አኩሪ ዜጎች ዕውቅና መስጠት የአገር ባህል መሆን ይገባል ባይ ነን፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2011ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "7aa562443d19f2caff6421e1e336ad9b" }, { "passage": "ስፖርት አንድ ትልቅ ማሕበራዊክንውን ነው።በተለይ በዚህ ዘመን ስፖርት ትልቅ የገቢ ምንጭም ነው፡፡ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአገራችን በተለይም በእግር ኳሱ መንደር እየተከሰቱ የመጡ ሁከቶችን ተከትሎ ስፖርትና ፖለቲካን ምን አገናኛቸው? በሚል በርካታ የስፖርት ቤተሰቦች ሙግት ሲገጥሙ ይታያል፡፡ በአንድ ወገን ስፖርትና ፖለቲካ አይገናኙም የሚሉ ሞጋቾች ፖለቲካና መንግሥት በስፖርቱ አካባቢ መድረስ የለባቸውም የሚል አቋም ሲያንፀባርቁ ይስተዋላል፡፡ በሌላ በኩል ስፖርት ብቻም ሳይሆን ሁሉም ነገር ፖለቲካ መሆኑን የሚያስቀምጡ ወገኖች ስፖርት ከፖለቲካ ተፅዕኖ ነፃ ሊሆን እንደማይችል ያስቀምጣሉ፡፡ከዚህ በተለየ መልኩ ስፖርት በመሰረታዊ ፅንሰ ሃሳቡ ከፖለቲካ ነፃ መሆን እንዳለበት ወይም ነፃ ቢሆን ይመረጣል፣ ነገር ግን ከፖለቲካ ተፅዕኖ ነፃ እንደማይሆን በርካታ ማሳያዎችን የሚያስቀምጡ ምሁራን በርካታ ናቸው፡፡ስፖርት በተለያዩ የታሪክ አጋጣሚዎች ሁነኛ የፖለቲካ መሳሪያ ሆኖ ማገልገል እንደቻለ ማስተዋል ይቻላል፡፡ስፖርት በጥሩ ከተጠቀምንበት ምላሹ ጥሩ እንደሚሆን ሁሉ ለመጥፎ ፖለቲካ አላማ ከተጠቀምንበት በተቃራኒው የሚያስከትለው ጉዳት በቀላል የሚታይ እንዳልሆነ ከታሪክ ማህደሮች መማር ይቻላል፡፡ ለዚህም በዓለማችን በሩቅና በቅርብ ዓመታት ስፖርት ከፖለቲካ ጋር እንዴት እየተሳሰረ እንደመጣ የተለያዩ አጋጣሚዎችንና የአገራትን ተሞክሮ በመዘርዘር መመልከት ይቻላል፡፡አሜሪካበሃያሏ አገር አሜሪካ እጅግ ተወዳጅና ሰፊ ተቀባይነት ባለው የአሜሪካን እግር ኳስ ውስጥ ስፖርት በበርካታ አጋጣሚዎች ከፖለቲካ ጋር ሲተሳሰር ማየት የተለመደ ነው፡፡ በአሜሪካ እግር ኳስ ውስጥ የሚሳተፉ ሃብታምና ዝነኛ ጥቁር ተጫዋቾች በአሜሪካዊያን ጥቁሮች ላይ የሚደረገውን የዘር መድልዎ በመቃወም ከጨዋታ በፊት የአሜሪካ ብሔራዊ መዝሙር ሲዘመር መንበርከካቸው ዛሬ የመጣ ነገር አይደለም፡፡ በአሜሪካ እግር ኳስ ብቻም ሳይሆን በቅርጫት ኳስና ሌሎች ስፖርቶች ላይ የሚሳተፉ ታዋቂ ጥቁር ስፖርተኞች አሁንም ተመሳሳይ ነገር ሲያደርጉ ይታያል፡፡ ይህ የጥቁር ተጫዋቾች ተቃውሞ የዋይት ሃውስን በር እያንኳኳም ተፅዕኖ ማሳረፍ ሲችል በግልፅ ታይቷል፡፡ በቅርብ ሰሞን እንኳን የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት ማይክ ፔንስ ይህን የተጫዋቾችን ድርጊት በመቃወም ስቴድየም ጥለው ለመውጣት እስከ መገደድ የደረሱበት አጋጣሚ ይታወሳል፡፡ስፔንበስፔን ታላቁ ውድድር ላሊጋ የዓለማችን ሃያል የእግር ኳስ ክለቦች ባርሴሎናና ሪያል ማድሪድ በሚጫወቱበት ወቅት የሚፈጠረው ድባብ ከስፖርት ይልቅ ወደ ጦርነት የሚያደላ መሆኑን የእግር ኳስ አፍቃሪዎች ያውቁታል፡፡ ጨዋታው በተገንጣዩ የካታላን ግዛት ወኪል ባርሴሎናና በማእከላዊያን ወኪል ሪያል ማድሪድ መካከል የሚደረግ መሆኑ እያንዳንዱ ጨዋታ ከፖለቲካ ትኩሳት ነፃ ሆኖ አያውቅም፡፡ የባርሴሎናው የተከላካይ መስመር ተጫዋች ጄራርድ ፒኬ በአንድ ወቅት ‹‹ከአሁን በኋላ ካታላን ለሚባል አገር እንጂ ስፔን ለሚባል አገር አልጫወትም›› ብሎ በአደባባይ ማወጁ ጨዋታው የሚካሄድበትን ድባብ ይገልጻል። ከስፔን ሳንወጣ በሁለቱ የማድሪድ ክለቦች ሪያል ማድሪድና አትሌቲኮ ማድሪድ መካከል የሚደረገው ጨዋታም ስፖርታዊ አይደለም። ፍጹም የፖለቲካ መንፈስ የሚንጸባረቅበት ነው። በአምባገነኑ ጀነራል ፍራንኮ ዘመን ከሪያል ማድሪድ ይልቅ አትሌቲኮ ማድሪድ መንግሥታዊ ድጋፍ ያገኝ ነበር ተብሎ ስለሚታመን የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ዘወትር ከፖለቲካ ተፅዕኖ ወጥቶ አያውቅም።ደቡብ አፍሪካኔልሰን ማንዴላ በአፓርታይድ ስርዓት ምክንያት የተቃቃረውን ደቡብ አፍሪካዊ ሁሉ አንድ ያደረጉት የራግቢን ስፖርት ተጠቅመው ነበር። ማዲባ ደቡብ አፍሪካ የዓለም ራግቢ ዋንጫን አዘጋጅ የነበረችበትን መልካም አጋጣሚ ተጠቅመው የራሳቸውን የተለየ መርሐግብር በማውጣት ቡድናቸውን እያበረታቱ ደቡብ አፍሪካ ብታሸንፍም ባታሸንፍም በስፖርት አማካኝነት የአገሪቱ ህዝብ ወደ አንድ ሊመጣ እንደሚችል ቀድመው ተረድተዋል፡፡ የነፃነት ታጋዩ እድል ሲቀናቸው ቡድናቸው ዋንጫ ወሰደ፡፡ ይህም የተቃቃረው ህዝብ በደስታ ስሜት ቂሙን ረስቶ ተቃቅፎ በአንድ ላይ ይቅር የሚባባልበትን አጋጣሚ እንዲፈጠር አደረገ፡፡የነፃነት ታጋይና የሰላም አባት የሆኑት ማንዴላም በዓለም አቀፉ የስፖርት መድረክ ለሰው ልጆች ነፃነትና መብት ባደረጉት ትግል፣ ስፖርታዊ ውድድሮች በረጅሙ ዘመን የእርሳቸውና ሕዝባቸው እልህ አስጨራሽ የፀረ-አፓርታይድ የነፃነት ተጋድሏቸው ወቅት ‹‹ሰላማዊ የትግል ስልት›› መሆኑን ላሳዩበት ፖለቲካዊ ብቃታቸው በተሰጣቸው ዓለም አቀፍ ሽልማት ላይ ባደረጉት ንግግር ‹‹ ስፖርት ዓለምን ለመቀየርና ህዝቦችን አንድ ለማድረግ ትልቅ ሃይል አለው›› በማለት ገልፀውታል፡፡እንግሊዝና አርጀንቲናታላላቆቹ የእግር ኳስ አገራት እንግሊዝና አርጀንቲና በዓለም ዋንጫም ይሁን በሌሎች አጋጣሚዎች ሲጫወቱ ከኳስነቱ ይልቅ ፖለቲካነቱ እንደሚያመዝን በተደጋጋሚ ታይቷል፡፡ እኤአ በ1982 ለአስር ያህል ሳምንታት በፎክላንድ ደሴቶች ምክንያት ሁለቱ አገራት የገጠሙት የውጊያ ታሪክ አሁንም ድረስ በሰላማዊው ጦርነት በኳስ ሜዳ ይከተላቸዋል፡፡ ከፍተኛ የሆነ ጦርነት ውስጥ ገብተው የነበሩት ሁለቱ አገራት ሲገናኙ ከኳሱ ውጤት ጀርባ የሚመነዘር ፖለቲካዊ አስተሳሰብ ይራመዳል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ኳሳዊ ሽንፈት የክብር፣የማንነት፣የሐገር፣የፖለቲካ ጉዳይ በመሆኑ ነው። በይበልጥ የሁለቱ አገራት የኳስ ፉክክር መክረር የጀመረውም ከጦርነቱ በኋላ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ሴኔጋልና ፈረንሳይፈረንሳይ ባስተናገደችው የዓለም ዋንጫ በመክፈቻው ጨዋታ በሴኔጋል አንድ ለዜሮ መሸነፏ ከኳሱ ውጤት ይልቅ ፖለቲካዊ አንደምታው ትልቅ እንደነበር ይታወሳል፡፡ሴኔጋል ፈረንሳይን አሸነፈች፣ አፍሪካውያን ሁሉ በአንድ እግር ቆመው አጨበጨቡ፣ጨፈሩ፡፡ ምክንያቱም ሴኔጋል በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ውስጥ ወድቃ ነበር። ስለዚህ የሴኔጋል ፈረንሳይን ማሸነፍ ከኳስ በላይ ሊተረጎም የቻለ የመላውን አፍሪካውያን ስነልቦና የቀየረ ፖለቲካዊ አንድምታ ነበረው ማለት ነው፡፡ቻይናቻይና በ2050 አካባቢ የዓለምን እግር ኳስ መቆጣጠር እንደምትፈልግ ይታወቃል፡፡ለዚህም በመላው ቻይና በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሕጻናት እጅግ ዘመናዊ የሆኑ የስፖርት አካዳሚዎች ተከፍቶላቸው ከሕጻንነታቸው ጀምሮ ተመልምለው የኳስ ስልጠና እየወሰዱ ነው። የቻይና ክለቦች ልጆቻቸው ብቁ እስከሚሆኑ ድረስ የዓለምን ቀልብ ለመሳብ ከስፔን እና እንግሊዝ ተጫዎቾችን እጅግ ውድ በሆነ ዋጋ እየገዙ የሚወስዱት ስፖርትን ብቻ አስበው እንዳልሆነ ብዙዎች ይመሰክራሉ፡፡ አንድ አገር በዓለም ላይ የበላይነትን ለማሳየት ስፖርትም አንዱ አማራጭ መሆኑ ቻይናውያን ዘግይተውም ቢሆን ገብቷቸዋል፡፡ ጀርመንጀርመን ከሌላ አገር ጋር ገጥማ ስትሸነፍ በኳስ ብቻ የተሸነፈች አይመስልም፡፡ ይህም የሆነው ጀርመናውያን በኳስ የሚመጣ ሽንፈትን የክብር፣የፖለቲካና የስነልቦና ሽንፈት አድርገው ስለሚመለከቱት መሆኑ ይገለፃል፡፡ ይህንን የሚያደርጉት ኳስ የፖለቲካ ዋና መሳሪያ እንደሆነ በአግባቡ ስለሚረዱ መሆኑንም የሚናገሩ በርካታ ናቸው፡፡አሜሪካና ኢራንየ1998ቱ በፈረንሳይ አስተናጋጅነት የተካሄደው የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ በዓለም አቀፉ የፖለቲካ መድረክ ስፖርት ለሰላም፣ ለወንድማማችነት፣ ለአንድነት … ወዘተ ያለው አዎንታዊ ፋይዳ በግልፅ የታየበት መድረክ ሆኖ ነበር ያለፈው። በአንድ ምድብ ተደልድለው የተገናኙት በጥንታዊ ስልጣኔዋ የምትታወቀው ኢራን ከዘመናችን ሃያሏ አገር አሜሪካ ጋር ነበር። እነዚህ ሁለት የፖለቲካ ባላንጣ አገሮች በአንድ ቡድን ተደልድለው የተገናኙበትን ጨዋታና ፉክክር ‹‹የጨዋታዎች ሁሉ እናት›› በማለት ነበር የአሜሪካው እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት በአጭር ቃል የገለጹት፡፡ በወቅቱም ስለ ሁለቱ አገራት ጨዋታ የዘገቡ ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙኃን፣ የሁለቱ አገራት ፖለቲከኞች፣ ዲፕሎማቶች፣ የእግር ኳስ ባለሙያዎችና ተንታኞች ጨዋታው ከስፖርታዊ ውድድር ባለፈ ጠንከር ያለ ፖለቲካዊ አንድምታ እንዳለው ሲዘግቡ ቆይተዋል፡፡ ከእግር ኳስ ፉክክሩ ባሻገር ፖለቲካዊ አንድምታው ጎልቶ በተነገረበት በዚህ የአሜሪካንና የኢራን ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታ፣ ሁለቱ አገሮች በስፖርቱ መድረክ ለሰላምና ለመልካም ግንኙነት ያላቸውን አዎንታዊ ፍላጎትና ስሜት የገለጹበት መልካምና ልዩ አጋጣሚ ሆኖ ይታወሳል፡፡በተጨማሪም የሁለቱ አገሮች ደጋፊዎች በውድድሩ ወቅት ያሳዩት ሰላማዊነትና ስፖርታዊ ጨዋነት ‹‹ስፖርት ለሰላም፣ ለፍቅር፣ ለአንድነት፣ ለትብብር፣ ለወንድማማችነት›› የሚለውን የስፖርት መርህ ከፍ አድርጎ ለዓለም ሕዝብ ያሳየ ነበር። ጥቂት የማይባሉ የሁለቱ አገራት እግር ኳስ አፍቃሪያንና ደጋፊዎች አንድ ጉንጫቸውን በአሜሪካን አንድ ጉንጫቸውን ደግሞ በኢራን ሰንደቅ ዓላማ ቀለማት በማስዋብ የእግር ኳስ ስፖርት በአገሮችና በሕዝቦች መካከል መቀራረብና ሰላም እንዲፈጠር የሚያስችል መድረክ መሆኑን በተግባር ለዓለም አሳይተውበታል። ይህን የወቅቱን እውነታ ያስተዋለው የኢራኑ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የሆነው አፍሺህን የእግር ኳስ ስፖርት አገራትን በሰላምና በፍቅር መንፈስ ለማስተሳሰር ያለውን ጉልበት እንዲህ በማለት ነበር የገለጸው ‹‹ይህችን ዓለም በአንድ ላይ ለማምጣት ሁለት ነገሮች ብቻ ቁልፍ ናቸው፣ እነሱም እግር ኳስና ፍቅር ይባላሉ››፡፡ማጠቃለያየተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ የነበሩት ባንኪሙን በስዊዘርላንድ ጄኔቫ እ.ኤ.አ ግንቦት 11 ቀን 2011 ዓ.ም\n‹‹ስፖርት ለሰላምና ለልማት ያለው አስተዋጽዖ›› በሚል ባደረጉት ንግግራቸው እንዳረጋገጡት፤ ስፖርት በዓለም አቀፍ ደረጃ የአገሮችን ድንበር ተሻግሮ የዘር፣ የጎሳና የኃይማኖት ልዩነቶች ሳይገድበው፣ የዓለም አቀፍ ቋንቋ መሆን እንደቻለና ስፖርታዊ ውድድሮች ለሰው ልጆች ሰላም፣ አንድነትና እድገት እየተጫወቱ ያለውን ቁልፍ ሚና መናገራቸው ይታወሳል፡፡ ስፖርታዊ ውድድሮች የሰላም፣ የወንድማማችነትና የፍቅር መድረክ ናቸው ቢባሉም አልፎ አልፎም ቢሆን የዘረኝነት መንፈስ የሚንጸባረቅባቸው፣ የሌሎችን ክብርና ነፃነት የሚጋፋ ኃይማኖታዊ መልዕክቶች፣ ፖለቲካዊ ተቃውሞች፣ ጠብና ግጭት ድረስ የሚዘልቁ ክስተቶችን ማስተናገዳቸው አልቀረም።እንግሊዝና አርጀንቲና፣\nየላቲን አሜሪካኖቹ የኤልሳልቫዶርና\nሆንድራስ በእግር ኳስ ጨዋታ\nምክንያት የተፋጠጡበትንና ጦር የተማዘዙበት አጋጣሚዎች ሲታሰቡ\nየስፖርቱ መድረክ አልፎ\nአልፎም ቢሆን የፖለቲካ\nአጀንዳዎች እንደማያጣው ያስገነዝበናል።አዲስ ዘመን ቅዳሜ ሰኔ 22/2011ቦጋለ አበበ", "passage_id": "38f48767cc66dc61e9c6ff1dae46b8ab" }, { "passage": " ብስራቱን ለመንገር የመጀመሪያውን ማራቶን ከአቴንስ እስከ ስፓርታ የሮጠው ወታደሩ ፊዲፒደስ ከ30 ሰዓታት በላይ ፈጅቶበታል። ከዘመናት በኋላ ደግሞ 42 ኪሎ ሜትሩ በሁለት ሰዓት ውስጥ የሚጠናቀቅ ሆኗል፡፡ ነገር ግን በቅርቡ ከዚህም በታች በሆነ ሰዓት መግባት እንደሚቻል ኬንያዊው አትሌት አረጋግጧል። ይህንን ሃሳብ በመያዝ ሲንቀሳቀስ የቆየው ናይኪ የተባለው የስፖርት ትጥቅ አምራችም በጫማዎቹ አማካኝነት ርቀቱ እስካሁን በሰው ልጅ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅበት ሁኔታ ከሁለት ሰዓት በታች መግባት እንደሚቻል አሳይቷል። ነገር ግን የማራቶን ሰዓት እዚህ ከመድረሱ ናይኪም በዘመን አመጣሽ ጫማዎቹ ሳይራቀቅ በፊት ፊዲፒደስ ርቀቱን በምን ሸፈነው በማለት የታሪክ ማህደርን ማገላበጥ አስፈላጊ ይሆናል። ሩጫ መለያዋ የሆነው ኢትዮጵያም የተከበረውን የኦሊምፒክ መንደር አሃዱ ያለችው በምን መልኩ ነው ለሚለውም ታሪክን መለስ ብሎ ማስታወስ በቂ ነው። ባለሙያዎች «ተፈጥሮአዊ ሩጫ» ሲሉ የሚጠሩትና በተለምዶ በባዶ እግር መሮጥ ለማራቶን ስፖርት መሰረት ነው ለማለት ይቻላል። በዘመነው ዓለም የማይታሰበው የባዶ እግር ሩጫ በአፍሪካ እና በደቡባዊው አሜሪካ ግን እስካሁንም በስፋት ይስተዋላል። በኢትዮጵያም ይህ አሯሯጥ የተለመደ ቢሆንም ምርጫ በማጣት (ከድህነት ጋር በተያያዘ ምክንያት) አሊያም በአስገዳጅ ሁኔታ የሚከወን ስለመሆኑ ዋቢ መጥቀስ አያሻም። በአንጻሩ ከሃብት ማማ ላይ በሚገኙት ምዕራባዊያን ዘንድ ይህ ዓይነቱ ሩጫ ጥቅሙን በመረዳት ይዘወተራል። ከጊዜ ወደ ጊዜም እየታወቀና እየተስፋፋ የመጣ የአሯሯጥ ዓይነት ሆኗል። በተለይ በሃይቅና ውቅያኖስ ዳርቻዎች እንዲሁም በሳር በተሸፈኑ መስኮች ላይ ባዶ እግርን መሮጥ እያደገ ያለ ተግባር ነው። በዚህ የሩጫ ዓይነት ስሙ ጎልቶ የሚነሳው ኢትዮጵያዊው ታላቅ አትሌት አበበ ቢቂላ ቢሆንም ከእርሱ አስቀድመውም ሆነ በዚያው ዘመን በርካቶች ባዶ እግራቸውን በውድድሮች ላይ ይካፈሉ ነበር። ከታዋቂዎቹ መካከልም ደቡብ አፍሪካዊቷ የሁለት ጊዜ የሃገር አቋራጭ ሻምፒዮና ዞላ ቡድ፣ አውስትራሊያዊው የ1ሺ500 ሜትር እና 800 ሜትር አትሌት ኸርብ ኤሎት እንዲሁም እንግሊዛዊው የ3 ማይል ሻምፒዮን ብሩች ቱሎህ ጥቂቶቹ ናቸው። ጀግናውን አትሌት ከሌሎቹ ልዩ የሚያደርገውም በባዶ እግር ቀርቶ በጫማም የማይደፈረውንና እህል ውሃ የማያሰኘውን ማራቶንን በመሮጡ ነው። እርግጥ ነው ከረጅም ዓመታት በኋላም ሌላ ኢትዮጵያዊ አትሌት በዚህ መልክ 42 ኪሎ ሜትሮችን በማቋረጥ ዓለምን አጀብ ማሰኘት ችሏል። ከሰው ልጅ ስልጣኔ እና የአኗኗር ሁኔታ ጋር በተያያዘ የሰው ልጅ ሩጫን በባዶ እግሩ አሊያም ከድብ እና ከሌሎች እንስሳት ቆዳ በሚሰራ ጫማ ሲከውነው እንደነበረ ጥንታዊያን ታሪኮች ያስረዳሉ። ግሪካዊያንም በጥንታዊው ኦሊምፒክ ጭምር በሩጫ ብቻም ሳይሆን በተለያዩ ስፖርቶች የሚካፈሉ ተወዳዳሪዎች ባዶ እግራቸውን ነበር የሚቀርቡት። እንደሌላው ዘርፍ ሁሉ የስፖርት ቁሳቁሶችም ከዘመን ጋር እየዘመኑና በረቀቁ ቴክኖሎጂዎች ታግዘው እየተካሄዱ ይገኛሉ። ለዚህም በቅርቡ ኬንያዊው አትሌት ኢሉድ ኪፕቾጌ በ1ሰዓት ከ59 ደቂቃ ከ40ሰከንድ በሆነ ሰዓት ማራቶንን የሮጠበትን ጫማ ማንሳት ይቻላል። ናይኪ ቫፖርፍላይ የተባለው ይህ የመሮጫ ጫማ ከተፈጥሮአዊው አቅም ባሻገር አትሌቶችን ወደፊት በማፈናጠር ተጨማሪ ፍጥነት የሚሰጥ ነው። በርካቶች ግን 250 ዶላር ዋጋ የተተመነለት ናይኪ ቫፖርፍላይን በህግ ከሚያስቀጣው የአበረታች ቅመሞች ተጠቃሚነት ለይተው አያዩትም። ይህ ከዘመናዊው ዓለም ጋር ከመራመድ እና ከተፈጥሯዊው ልማድ ጋር የመቀጠል እሳቤም የአትሌቲክስ ቤተሰቡን ከሁለት የከፈለ አድርጎታል። በተፈጥሯዊ መንገድ በባዶ እግር መሮጥ ግን ላለንበት ወቅት የማይመጥን ተግባር ተደርጎ ይወሰድ እንጂ የጤና ባለሙያዎች እንዲተገበር የሚመክሩት የአሯሯጥ ዓይነት ነው። ሳይንስም በባዶ እግር መሮጥን ከጉዳት ማገገምን ጨምሮ በርካታ ጥቅሞችን እንደሚያስገኝ ያረጋግጣል። ነገር ግን ተግብሮት ለማያውቅ ሰው በመጀመሪያ ፈታኝ እንደሚሆን እና የሚሮጡበትን ስፍራ ደህንነትም አስቀድሞ ማረጋገጥ እንደሚገባም ያሳስባል። የመጫሚያዎች ምቾት ከሳምባ፣ ከአእምሮ፣ ከደም ዝውውር እንዲሁም ከነርቭ ጋር ይያያዛል። በመሆኑም ከባድ፣ ጠባብ፣ ከተረከዛቸው ከፍ ያሉ፣… ጫማዎች ያደረገውን ሰው ምቾት ከመንሳት ባሻገር ጤናም ላይ ተያያዥ እክሎችን ማድረሱ አይቀርም። በመሆኑም አልፎ አልፎም ቢሆን ባዶ እግርን መጓዝ እና መሮጥን መለማመድ ጠቃሚ ይሆናል። የደም ዝውውርን ለማስተካከል ተመራጭ መንገድ ሲሆን፤ በተለይ ለልብ ህመም እንዲሁም በደም ውስጥ የሚኖሩ መርዘኛ ንጥረ ነገሮችን ለማስወገድ እንደሚረዳ ተመራማሪዎች በሳይንስ ጆርናሎች ያሳተሟቸው ጽሁፎች ያስነብባሉ። በሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ዳንኤል ሊበርማን እንደሚገልጹት ከሆነ፤ (cushioned\nshoes) በመባል የሚታወቁትን የስፖርት ጫማዎች የሚያዘወትሩ አትሌቶች ተረከዛቸው በመዶሻ የመቀጥቀጥን ያህል ጉዳት ይደርስባቸዋል። በመሆኑም አሰልጣኞች አንዳንዴም አትሌቶቻቸውን ባዶ እግራቸውን በሳር ላይ እንዲሮጡ ቢያደርጉ፤ የእግራቸውን ጤንነት ከመንከባከብም በላይ ከደረሰባቸውም ጉዳት እንዲያገግሙ እንደሚረዳቸው ያስረዳሉ። በጫማ መሮጥ በባዶ እግር ከመሮጥ ይልቅ የኦክስጅን ፍጆታን በሁለት እጅ ይጨምራል፤ ይህም አትሌቱ (ሯጩ ግለሰብ) ከሚያወጣው ጉልበት የሚያያዝ በመሆኑ በሚሸፍነው ርቀት ላይ የራሱን ተጽእኖ ማሳረፉ አይቀርም። በእግር ጤንነት፣ ሚዛን፣ ነርቮችን በማነቃቃት፣ የእግር ቅርጽ እና እድገት ላይም በጫማ እና ያለጫማ እንቅስቃሴ ማድረግ ሚናው ይለያያል። በተለይ ደግሞ በሽንጥ፣ ባት፣ ተረከዝ፣ ቁርጭምጭሚት፣ ጅማት፣ አጥንት እና ጡንቻዎች ጤና ላይ የራሱን አሻራ ያሳርፋል። ከዚህ ባሻገር ሰው ከተፈጥሮ ጋር ያለውን ቁርኝትም በማስፋትና ተፈጥሮን በመንከባከብ ረገድ የራሱን ስነ-ልቦናዊ በረከት ያስገኛል።አዲስ ዘመን ጥቅምት24/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "721145480b76984363e8a73c5bcf2259" }, { "passage": "በእግር ኳሱ ዓለም በደጋፊዎች መካከል ግጭትና ሁከት ሲፈጠር ማየት የተለመደ ነው። የኢትዮጵያ እግር ኳስም በደጋፊዎች መካከል ለሚፈጠር ግጭት እና እሱን ተከትሎ ለሚፈጠር የስቴድየም ሁከት ባይተዋር አይደለም። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን በአገራችን ስቴድየሞች የሚከሰቱ ግጭቶችና ሁከቶች ስፖርታዊ ብቻ እየመሰሉ አይደለም። በተለይም ባለፉት ሁለትና ሦስት ዓመታት በተለያዩ የአገራችን ስቴድየሞች እየተስተዋሉ የመጡት የስቴድየም ሥርዓት አልበኝነት ጉዳዮች ከስፖርታዊ አንድምታ ይልቅ ወቅታዊ አገራዊ የፖለቲካ ጥላ ያንዣበበባቸው ስለመሆኑ ማሳያዎችን ማስቀመጥ ይቻላል። በተለያዩ የእግር ኳስ ደጋፊዎች በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ስፖርትና ፖለቲካን ደበላልቀውት በየስታዲየም ውስጥ ተጽፈው የሚታዩት ባነሮች፣ ወረቀቶች ተጽፈው የሚታዩት አዎንታዊና አሉታዊ መፈክሮች የዚህን ድብልቅልቆሽ ፍንትው አድርገው የሚያሳዩ ናቸው። ስፖርትና ፖለቲካ ምንና ምን ናቸው? የሚለውን ጥያቄ ዛሬም ድረስ ምላሽ አለማግኘቱን እዚህ ጋር ገታ እናድርግ። የሀገራችን የፖለቲካ ፓርቲዎች ወቅታዊ ሁኔታና የእግር ኳስ ክለቦቻችን ወቅታዊ ቁመና በእጅጉ ተመሳስሏል። የሁለቱ ዘውጎች ተመሳስሎን ከአደረጃጀት፣ ከስያሜ፣ በተተኪ ካለማመን አኳያ ያለውን እውነታ አፍታተን እንመልከት።የሀገራችን እግር ኳስ ክለቦችና ፖለቲካ ፓርቲዎች የአደረጃጀት ሁናቴ ተመሳስሎ ከሚታይባቸው አንኳር ጉዳይ ይጠቀሳል። ይህንኑ እግር ኳሱ መነሻ አድርገን እንመልከት። የእግር ኳስ ክለቦች የተደራጁበት ሁኔታ መሠረት ያደረጉት አካባቢን፣ ማንነትን፣ ከተማን፣ ክልልን … ያደረጉ ናቸው። በስያሜያቸው ያዘሉት ማንነት «ስፖርት ለወዳጅነትን የሚለውን ገልብጦ ለጦርነት» እንዲውል ምክንያት እስከመሆን ደርሷል። ለዚህ አመክንዮ የስፖርት ሳይንስ ምሁሩ ፒተር አልጊ/Peter እኤአ 2009 ያሳተመው ጆርናል እንደ ማሳያ እንጥቀስ። ፒተር በተለያዩ የስፖርት ዓይነቶች ብሔርተኛ ክለቦች መበራከት ብሔራዊ ስሜትን ወደ ፈተና የሚከቱ መሆናቸውን የሚያትት ሲሆን፤ ስፖርት የአንድነት ስሜት እንዲያደበዝዝ በተለየ መልኩ በቅኝ ገዥዎች ተግባራዊ ሲደረግ ነበር።የፒተር ሃተታ፤ ብሔርተኛ ክለቦች በአንድ ብሔር፣ ብሔረሰብ፣ጎሳ እና ዘር ተለይቶ እንዲታወቅ ብሎም እንዲደገፍ ተደርጎ የሚመሰረት የእግር ኳስ ክለብ ሲሆን በዘመነ ቅኝ ግዛት በተለይም በአፍሪካ ተስፋፍቶ የነበረ የክለብ አደረጃጀት ነው። ቅኝ ገዥዎች ስፖርትን በተለይም ደግሞ እግር ኳስን በመጠቀም የዘር እና የባህል ልዩነቶችን በአፍሪካውያን ላይ እንዲሰርጽ ለማስቻል በነገድ ላይ የሚያጠነጥኑ ቡድኖች በሥራ ቦታዎች (በፋብሪካ፣በማዕድን ቁፋሮ) ላይ ያቋቁሙ ነበር። በዚህ መልኩ ክለቦችን በመመስረት የአንድ አገር ሕዝቦችን በልዩነትና በብሔርተኝነት፣ በጎሰኝነት፣ በጎጠኝነት…አስተሳሰብ እንዲወጠሩ በማድረግ ብሔራዊ ስሜታቸውን በመሸርሸር የሀብት ብዝበዛውን ያለ ጥያቄ ሲያከናውኑ ቆይተዋል። ልዩነቱን ለመፍጠር በነገድ ላይ የሚያጠነጥኑ ቡድኖች እንዲስፋፉ በማድረግ ስፖርትን የአንድነት ፀር ለማድረግ ተጠቅመውበታል።በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በተለይ የእግር ኳስ ክለቦች በአብዛኛው ማለት ይቻላል ህልውናቸው ከተማን መሠረት ያደረጉ ቢሆንም የስፖርት ሜዳውን የጦርነት አውድማ ሲያደርጉት ታዝበናል። የእግር ኳስ ክለቦች አደረጃጀት መሠረቱን የልዩነትን ሚዛንን የማጉላቱ ሀቅ፤ በፖለቲካው ላይ ትልቅ ተመሳስሎ የሚስተዋልበት ነው።በሀገራችን ያሉ 107 ፓርቲዎች በፖለቲካ ሜዳው በቡድንነት ራሳቸውን ከማስመዝገብ ባሻገር፤ ከመንግሥት የሚደረገውን ድጎማ ለመቀራመት ከመሻት በዘለለ፤ የቡድናቸውን ስያሜ የተጠቀሙለትን አካል ፖለቲካዊ ባለ ድል ከማድረግ አኳያ ምንያህል ውጤታማ ያደርገን ይሆን? በሚል እሳቤ የተቃኘ አይመስልም። እውነታውን መካድ «ግመል ሰርቆ አጎንብሶ መሄድ አይቻልም» እና ሕዝብም እውነታ በገሃድ የሚናገረው ነው።የክለቦች መጠናከርና መብዛት ግቡ ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መፍጠር ሲሆን፤ በፖለቲካ ፓርቲዎች በኩል ደግሞ ዴሞክራሲያዊ ሀገርን መገንባትና ሕዝብን የሥልጣን ባለቤት ማድረግ ነው። የእግር ኳሱ ክለቦች የአደረጃጀት መሠረታቸውን ያልተቃና መሆኑ ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን ለመፍጠር ዋልታና ማገር የመሆን ሚናቸውን አጥተውታል።መሰንበት ደጉ መቼም ብዙ ያሳየናል። «ምን አየን ደግሞ» መባሉ አይቀርምና ወደ ማብራሪያዬ ልግባ። የእግር ኳስ ክለቦች ሆኑ ፓርቲዎች አደረጃጀት መሠረቱ ልዩነት እንጂ አንድነትን የሚጋብዝ መሆኑ ለመጥቀስ ተሞክሯል። በሁለቱም ማዕዘን በኩል ያለው ስያሜ አካባቢን፣ ከተማን…መሠረት ባደረገ መልኩ እንደሆነ ተገልጿል። «ታዲያ ክፋቱ ምንድነው?» የሚል ጥያቄ መነሳቱ አይቀርም። ክፋቱማ በግልጽ እየታየ ይገኛል፤ከእግር ኳስ ክለቦች በኩል ካለውን እውነታ ስንነሳ፤የብሔራዊ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከወራት በፊት «በስፖርታዊ ጨዋነት፣ የተመልካቾች ረብሻ፣ ሁከትና ብጥብጥ በኢትዮጵያ እግር ኳስ» በሚል ያስጠናውን ጥናት በመነሻነት እንጥቀስ። ፌዴሬሽኑ ጥናቱ በማሳያነት እንዳቀረበው፤ ቁጥራቸው ትንሽ የማይባል ስያሜ ቅጽል ስያሜ፣ አርማ፣ ዜማ ከተፈጥሯዊ አሰፋፈር ጋር ተዳብሎ በአንድም ይሁን በሌላ ምክንያት ከብሔር/ፖለቲካ ጋር ተያያዥነት ኖሮት እንዲቀርብ መደረጉ ጠቅሷል።በስፖርት ውስጥ ልዩነት ለመፍጠር መንገድ የሆነውን እንዲህ ዓይነቱን አደረጃጀትን ተመልክቶ መፍትሄ መስጠት የሚገባ መሆኑን በጥናቱ ውጤት በመፍትሄነት ቀርቧል። ከክለቦቻችን ስያሜ ጀርባ ለምንዛሬው ወደ ማንነት የቀረቡ መሆናቸው በስፖርት ተፈጥሯዊ ሕግ ውስጥ «ማሸነፍና መሸነፍ» መሆኑን እንዲረሳ ሲያደርግ ለመታዘብ ተችሏል። የሀገራችንን ነባራዊ ሀቅ ወደ ጎን ትተን እስቲ ወደ ስፔን እናቅና። በስፔን ፕሪሚየር ሊግ የባርሴሎና እና የሪያል ማድሪድ ጨዋታ ወቅት የሚፈጠረው ድባብ የስፖርት ሳይሆን የጦርነት ነው። ምክንያቱም ጨዋታው በተገንጣዩ የካታላን ግዛት ወኪል ባርሴሎና እና በማዕከላውያን ወኪል ማድሪድ መካከል የሚደረግ ስለሆነ። የባርሴሎናው ተከላካይ ጀራርድ ፒኬ በአንድ ወቅት ከአሁን በኋላ ካታላን ለሚባል ሀገር እንጂ ስፔን ለሚባል ሀገር አልጫወትም ብሎ በአደባባይ ማወጁ ጨዋታው የሚካሄድበትን ድባቡ መለወጡ ይገልጻል። በዚህ ስሜት ውስጥ ሆነን የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን እንመልከት።በፕሪሚየር ሊጉ አሁናዊ ሁኔታ የጨዋታው ድልና ሽንፈት ከስፖርት አውድ አርቆ ወደማንነት ድል በማድረግ ወደ ጸብና ወደ ዱላ ማሻገር እየተለመደ መጥቷል። የስፖርቱን መልክም በግልጽ ፖለቲካዊ መልክ ብቻም ሳይሆን የብሔር አንድምታን በመስጠት ሌላ የጦርነት አውድ ሊሆን ሲከጅለው መታዘብ «መሰንበት ደጉ ብዙ ያሳየናል» ከሚለው አባባል ላይ ይጥለናል። ክለቦች የተደራጁበት ሁኔታ የመጣመም ክፋትን እንደተመለከትነው ሁሉ የፓርቲዎቹን እንመልከት።የእግር ኳስ ክለቦች ስያሜ በፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ላይም ያለውን ተጽእኖ ተመሳሳይ ነው። የብሔር፣ የአካባቢ፣ ጥቂት ቡድንና ቤተሰብ መሠረት ያደረጉ ፓርቲዎች መፈልፈል፤ «ስያሜህ እኔን አይመስልምና አካባቢዬ ድርሽ ትልና….» የሚሉ ቅድመ ማስጠንቀቂያዎች እስከ መስጠት ሲደረስ ለመታዘብ ተችሏል። የቤተሰቡን ህልውና ለማስከበር የተቋቋመው ፓርቲ እኔ ለእኔ ቤተሰብ ብቸኛው ወኪል ነኝና «ዋ ቤቴ ትመጣና» እስከ መባባል ተደርሷል። የፓርቲዎቹ ደጋፊዎችም ቢሆኑ ብደግፈው ይበጀኝ፣ ይጠቅመኝ ይሆን በሚል ሚዛን ሰርቶ ሳይሆን «ብሔሬን፣ሰፈሬን…»ተሸክሟልና ልደግፈው የሚል ጭፍን ጉዞ ውስጥ እንዲጓዙ ሲያደርጋቸው ለመታዘብ ተቸሏል። ሃሳብ ትቶ ማንነት ላይ ያተኮረ የድጋፍ ስልት ለመኖሩ ደግሞ ትልቁ ምክንያት ከፓርቲዎች ስያሜው ጀርባ ያለው መዘዝ እንጂ ሌላ አይደለም። በፖለቲካው አካባቢ ያለውን መዘዝ በስፖርቱም ሲመዘዝ ምን እንደሚፈጠር አሳይቶ ማለፍ ይገባል።አሰልጣኝ ዘማሪያም ወልደጊዮርጊስ ከቀናት በፊት በጄቲቪኢትዮጵያ በነበረው ቃለ ምልልስ «በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውስጥ እኮ ከውጪ የመጡ ተጫዋቾች ያለምንም ስጋት እየተጫወቱ የኛ ተጫዋቾች ግን ዘራቸው እየተነሳ የመጡበት አካባቢ እየተጠቀሰ እንዲሳቀቁ መደረጉ ያሳፍራል…»ሲል የተናገረውን ማስታወስ ተገቢ ይሆናል። አሰልጣኙ የገለጸው እንዳለ ሆኖ የሁኔታው አደገኝነት ከዚህ ከፍ ሲል ደግሞ ክለቦች የሚቀጥሯቸው ተጫዋቾች፣ በተለይ አሰልጣኞች ከአካባቢውና ነዋሪ ተመሳስሎ መኖርን እንደ ቅድሚያ መስፈርትነት እስከ መመልከት የደረሰ መሆኑ ነው። ደጋፊዎች ክለቦችን የሚደግፉት የራሳቸውን አካባቢና አካባቢ ብቻ ሆኗል። በመሠረታዊነት ደግሞ እግር ኳሱን ሳይሆን ማንነቴን ያንጸባርቅልኛል የሚል መስፈርት መኖሩ ችግሩን ያገዝፈዋል። በተጨማሪም ለብሔራዊ ቡድን የሚመረጡ ተጫዋቾች ለመመልመል እዚሁ ስሌት ውስጥ እስከ መግባት የተደረሰ መሆኑ ይህቺ ሀገር ወዴት እየሄደች ይሆን የሚለውን የግርምት ጥያቄን ለመሰንዘር ያስገድዳል። እግር ኳሱም ሆነ ፖለቲካው በዚህ ደረጃ የመውረዱና እንዘጭ የማለቱ ሀቅ ሁለቱም የተደራጁበት መንገድ የተጣመመ ከመሆኑ ጋር እንደሚያያዝ ጥሬ ሀቅ ነው።የፖለቲካውና እግር ኳስ የጨዋታ ተስፋ ቢስ ካደረጉ ምክንያቶች አንዱና ዋነኛ ተደርጎ ቢነሳ ድፍረት አይሆንም፤ የተተኪ ችግር። ከተተኪ ጋር ተያይዞ ያለውን ችግርንና ተመሳስሎ ከእግር ኳሱ በመነሳት እንመልከት። ክለቦች ተጫዋቾችን ከታች ኮትኩተው በማሳደግ ወደ ዋናው ቡድን የማስገባት ዝንባሌን ብዙም አይታይባቸውም። ከዚህ ይልቅ ተጫዋቾችን ከሌላ ክለብ በማዘዋወር (በከፍተኛ የዝውውር ገንዘብ) ራሳቸውን መገንባት የተለመደ ነው። በተለይ አንጋፋ የሚባሉ ተጫዋቾች በአንድ ክለብ ለረጅም ዓመት ከተጫወቱ በኋላ ጫማ ከመስቀል ይልቅ እታች ወዳለ ክለብ በመዘዋወር የጡረታ ዕድሜያቸውን ሲያጣጥሙ መታዘብ አዲስ አይደለም። በክለቦች በኩል ልምድ የሆነው ተተኪዎችን ያገለለ የተጫዋቾች ዝውውር፤ አሁን አሁን ደግሞ ቅኝቱን ቀይሯል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ብቻም ሳይሆን በብሔራዊ ሊጉ ሳይቀር የውጭ ሀገራትን ተጫዋቾች የማስፈረሙ ልምድ ቦታውን ይዟል። የተጫዋቾች ዝውውር ሂደቱ በዚህ መልኩ መሆኑ ታዳጊዎችን በእግር ኳሱ ለማየት መታደል እንዳይቻል ሳንካ ሲፈጥር ለመታዘብ ተችሏል። በእግር ኳሱ እንደሚታየው የተተኪ ድርቅ ሁሉ በፖለቲካ ፓርቲዎች ውስጥ በተመሳሳይ ይስተዋላል።በሀገራችን ከ107 በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች ይገኛሉ። ከፓርቲዎቹ ዘጠና በመቶ በሚባል መልኩ በ60 ዎቹ ትውልዶች ተመስርተው በራሳቸው የሚመሩ ናቸው። የፓርቲዎቹ ርዕዮት ይሄኛውን ትውልድ ገሸሽ የሚያደርግ ሲሆን፤ ፖለቲካውንም እንዲዘውሩ ለሚያስችል የአመራርነት ዕድልን ያልጋበዘ መሆኑ፤ በፓርቲዎቹ ውስጥ የሚንጸባረቀውን በተተኪ ያለማመን ዝንባሌ ፍንትው አድርጎ ያሳያል። በዚህ እሳቤ ውስጥ የመዳከሩ ጉዳይ ደግሞ የፖለቲካውን ሜዳ ደጋፊ አልባ በማድረግ፤ የፓርቲዎች ቁጥር ብቻ ሆኖ እንዲጓዝ አድርጎታል። የሀገራችን ፖለቲካና እግር ኳስ የሜዳ ላይ ቆይታን በእጅጉ አሰልቺና ውጤት አልባ በመሆን ለመጓዙ ምክንያት ሆኗል።በአጠቃላይ የሀገራችን አሁናዊ የፖለቲካውና የስፖርቱ ጭብጫቦና ድጋፍ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴንና የጨዋታ አሰላለፍን መሠረት ያደረገ ሳይሆን ማንነትን በመመዘን የሚደረግ መሆኑ ስፖርቱን ከስታዲየም፤ ዴሞክራሲውንም ከሀገር እንዲወጣ ሲታገለው ለመታዘብ ችለናል። ሃሳብና ችሎታ ከሚዛን ርቀው፤ የክለቡንና ፓርቲውን ስያሜ ብቻ ዋነኛ መስፈርት በሆነበት ሜዳ ላይ መቼም ቢሆን፤ ፖለቲካው ሆነ የስፖርቱ እርካብ ከስኬት መንበር ለመድረስ አይቻለውም። በመሆኑም ኢትዮጵያ እንደ አገር ልትቀጥልና ሕዝቧም በልዩነት በሰላም መኖር የሚችለው የታጠቀውም ያልታጠቀውም በጎሳና በዘር የተደራጁት ድርጅቶች በአዋጅ ሲታገዱ፤ ብሎም የፖለቲካ ፓርቲዎች ማቋቋሚያ አዋጅ ማሻሻያ ማድረግን እንደ ዋነኛ መፍትሄ መመልከት ይገባል። በስፖርቱም በተመሳሳይ በእግር ኳሱ በተመሳሳይ ክለቦች የተደራጁበት መንገድ ብሔርን፣ አካባቢን፣ ቡድንን መሠረት ያደረጉ እንደመሆናቸው ይሄንኑ ዓይነት ስያሜን በማስተካከል ስፖርቱ ከገባበት ህመም ማዳን ይገባል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 16/2011", "passage_id": "c685e42169a7344cbe9e862cdf04a476" }, { "passage": "ስፖርት ለሰላም ትልቅ ዋጋ የሚሰጥ ማህበራዊ ክንውን እንደሆነ ይታመናል። ስፖርት ብሄራዊ ስሜትን በመገንባት፤ ወዳጅነትን፣አንድነት፣አብሮነትን በማጠናከር ረገድ ከፍትኛ ሚና አለው። ይህም የሰላም ዘብነቱ የጎላ መሆኑ እንዲታመን አድርጓል። ስፖርት ወደ ሰላም የሚያደርስ አሳንስር መሆኑን ከመሰከሩት ታላላቅ ሰዎች ውስጥ የስፖርት ሳይንስ ልሂቁ ፒተር አልጊ ይጠቀሳል። ፒተር፤ ስፖርት በእርስ በእርስ ጦርነት ምክንያት በልዩነት የምትታመስ አገርን ወደ ሰላም ለመመለስ፤ ህዝቡ ወደ አንድነት እንዲመጣ ዋነኛ መፍትሄ እንደሆነ ይናገራል። ‹‹ስፖርት ለሰላም ሁለንተናዊ ግልጋሎቱን በአንድ አገር ውስጥ ለሚኖሩ ዜጎች የግንኙነት ሰንሰለት ከማጥበቅ አኳያ ትልቅ ሚና ያለው ዘርፍ ነው» ሲልም ይሄንኑ ምስክርነት ሰጥቷል። የስፖርት ሊሂቁን አባባል እውነትነት ለማረጋገጥ ሰላምን፣ መቻቻልን፣ አንድነትን፣ ወንድማማችነትን የሚሰብኩ የውድድር መድረኮችን ቀርጾ ወደ ተግባር መግባት ቢቻል ውጤቱን በተጨባጭ ማየት ይቻላል። በአገር አቀፍ ደረጃ ሰላምን አጀንዳቸው ያደረጉ ስፖርታዊ ውድድሮችን በማዘጋጀት ብሄራዊ ስሜት መገንባት እንደሚቻል ደግሞ ደቡብ ሱዳን ምስክር ናት። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በደቡብ ሱዳን የእርስ በእርስ ግጭቱን ለመፍታት ከተጠቀመባቸው ዋነኛ መንገዶች ስፖርት አንዱ ነበር። ስፖርቱን እንደ መፍትሄ ለመጠቀም ምክንያት የነበረው ክስተት ከሶስት ዓመት በፊት ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በደቡብ ሱዳን እና በጋቦን መካከል የተደረገው ጨዋታ ነበር። የደቡብ ሱዳን ብሄራዊ ቡድን የጋቦን አቻውን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል። የጨዋታው ውጤት ግን ያልተጠበቀ ክስተት ይዞ ነበር የመጣው። በደቡብ ሱዳን እርስ በእርስ ጦርነት የቆሸሸውን የአንድነት ስሜት ከተቀበረበት ገንፍሎ እንዲወጣ ሲያደርግ ለመታዘብ ተችሏል። የአገሪቱ ህዝቦች በብሄር፣በጎሳ ተመዳድበውና በጠላትነት\nተፈራርጀው እርስ በእርስ ከመጋደል በአንድነት ስለ ደቡብ ሱዳን እንዲያዜሙ ያደረገ ክስተት በጨዋታው ተፈጠረ። የልዩነት ቀለም ደብዝዞ\nየአንድነትና የወንድማማችነት ስሜቱን ከፍታ ያስመለከተ የማይታመን ሁኔታ የፈጠረም ነበር። ከእግር ኳስ ድል የሚቀዳ ድብቅ የብሄራዊ\nስሜት ሲፍለቀለቅ ያስመለከተ ትልቅ አጋጣሚም የተፈጠረ ሲሆን፤ ለተባበሩት መንግስታት በደቡብ ሱዳናዊያንን መካከል እርቅ የመፍጠሪያው\nዘዴ ስፖርቱና የስፖርቱ ዘርፍ ብቻ የመሆኑን ብልሀት ያቀበለም ነበር። በአገሪቱ የነበረውን የልዩነት ስሜት ወጣቶችን ማዕከል ያደረገ\nየእግር ኳስ ውድድር በማዘጋጀት ወደ አንድነት ስሜት ለማሸጋገር ተራምዷል። የደቡብ ሱዳን የጸጥታ ጉዳዮች ልዩ ተወካይ ስፖርት ለሰላም\nበሚል ያደረገው እንቅስቃሴ ውጤታማ መሆኑን ነበር የረጋገጠው። የተባበሩት መንግስታት በደቡብ ሱዳን ወጣቶች መካከል የጎሣ መከፋፈል\nጥቃት ለማስወገድ እና ጥላቻን ለመዋጋት አስደናቂ አማራጭ መንገድ አድርጎ እየሰራ መሆኑን በወቅቱ አስረድቷል። ይሄም የፈጠረው የወንድማማችነት\nስሜት የተሳካ መሆኑንም ለዓለም ተናግሯል። በደቡብ ሱዳን በስፖርት መሳሪያነት የልዩነት ታሪክ ወደ አንድነት ተለውጦ ለሰላም መሰረት\nበመሆን የነበረውን ደም አፋሳሽ ሂደት በማርገብ ረገድ ሚናው እንደ ማሳያ ይቀርባል። በዚህ ደረጃ የስፖርትን የሰላም አሳንሰርነት በማሳያ ታግዞ ለማቅረብ የተሞከረው ያለምክንያት አይደለም። በኢትዮጵያ አሁናዊ\nሁኔታ በህዝብ ለህዝብ ዘንድ ያለመተማመን፣ ብሄርን መሰረት ያደረጉ ግጭቶች፣ አስተማማኝ ያልሆነ የሰላም ሁኔታ መኖራቸውን ታሳቢ\nበማድረግ እንጂ። በእርግጥ በሀገሪቱ ሰላምን፣ አንድነትን፣ ወዳጅነትን፣ ብሄራዊ ስሜትን ለመፍጠር በመንግስትም ሆነ በግሉ ዘርፍ\nየሚገኙ ማህበራት የተለያዩ ስልቶችን እየተከተሉ ይገኛሉ። የሰላም ማዕከል የሆነውን የስፖርት ዘርፍን ግን ዘንግተውት እንደቆዩ ይታመናል።\nየስፖርት ዘርፍን እንደ ቁልፍ መፍትሄ ተጠቅሞ ሰላምን ፣ አንድነት፣ ወዳጅነትን፣ ወንድማማችነትን በመስበክ ወደተሻለ ደረጃ ማድረስ\nየመቻሉን ሚስጥር ለብዙዎች ሳይገለጥ ቆይቷል። ፍቅር ያሸንፋል የበጎ አድራጎት ማህበር ግን ዘግይቶም ቢሆን እውነታው ተገልጦለታል።ማህበሩ\n‹‹ለፍቅር እንሩጥ ጥላቻን እናምልጥ ››በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ የሩጫ ውድድር ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ይገኛል። የ‹ፍቅር ያሸንፋል›በጎ አድራጎት ማህበር ዋና ሥራ አስኪያጅና መስራች አቶ ሚስባህ ከድር ለአዲስ ዘመን እንደገለፁት፣\nሰላምን፣ አንድነትን፣ ወዳጅነትን፣ ፍቅርን ለመስበክ የሚችሉ ስፖርታዊ ሁነቶች በማዘጋጀት፤ በአገር ሰላምና ፍቅር ለመፍጠር የሚያስችል\nስፖርታዊ መድረክ የማዘጋጀት መነሻው ማህበሩ የተመሰረተበት አላማ ነው። ‹ፍቅር ያሸንፋል› በጎ አድራጎት ማህበር ቀደም ሲል በማረሚያ\nቤቶች እስራት ላይ በነበሩ ግለሰቦች የተመሰረተ ማህበር ነው። የማህበሩ መስራቾች ለዓመታት ጨለማ ቤት ውስጥ በግፍ ታስረው በማይተካ\nዕድሜያቸው የቀለዱባቸውንና ተነግሮ የማያልቅ ግፍ ሲሰራባቸው የነበሩ ሰዎች ናቸው። ‹‹በግፍ ሲያሰቃዩን የነበሩትን አካላት ለፈጣሪና\nለአገር ሠላም ቀጣይነት ይጠቅማል በሚል ፍቅር ያሸንፋል ማህበር ተመሰረተ›› በማለት አቶ ሚስባህ ይናገራሉ። በ2011 ዓ.ም ማህበሩ ዕውቅና አግኝቶና ሌሎች የማህበር አባላትን በማካተት እንቅስቃሴ መጀመሩን አቶ ሚስባህ ያስታውሳሉ።\nማህበሩ የክብር አምባሳደር አርቲስት ቻቺ ታደሰ እና አርቲስት ዳዊት ፅጌን በማድረግ ባለፉት 12 ወራት የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውን\nነበር። በዚህም ሰላምን፣ አንድነትን፣ ፍቅርን የሚዋጁ እንቅስቃሴ ሲያደርግ መቆየቱን ይናገራሉ። ማህበሩ ባለፉት ጊዜያት ባከናወናቸው\nበጎ ተግባራት መነሻ በማድረግ ትልቅ አላማ ያነገበውን የኢትዮጵያውያን የፍቅር ሩጫና ፌስቲቫል ማዘጋጀቱን ያመላክታሉ።ስፖርቱን እንደ\nመሳሪያ በመጠቀም ከአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ በመነሳት በህዝቦች መካከል ሰላምን፣ አንድነትን፣ ፍቅርን ለመፍጠር የኢትዮጵያውያን የፍቅር\nሩጫና ፌስቲቫል ሊዘጋጅ መቻሉን ይናገራሉ። «በአገራችን የተለያየ የሀሳብ ልዩነት ያላቸውን የተፎካካሪ ፓርቲ መሪዎችን እና ተፅዕኖ\nፈጣሪ ግለሰቦችን በማናገር ለአገር አንድነትና ለፍቅር እንሮጣለን የሚል መልካም ምላሾችን ማግኘት ተችሏል። በኢፌዴሪ ሰላም ሚኒስቴር\nበኩልም እውቅና ተሰጥቶታል። በመሆኑም ውድድሩ «ለፍቅር እንሩጥ ጥላቻን እናምልጥ»በሚል መሪ ሃሳብ የካቲት 15 ቀን 2012 ዓ.ም\nበአዲስ አበባ መነሻና መድረሻውን መስቀል አደባባይ በማድረግ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ እንገኛለን»ይላሉ። በእለቱ ከሩጫ ውድድሩ ባሻገር ከተለመደው እንጀራ በተለየ በመጠኑ ትልቅ እንጀራ ተጋግሮ ለታዳሚዎች እንደሚቀርብ የጠቆሙት\nአቶ ሚስባህ፤ እንጀራውን የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ሌሎች ታዳሚዎች በጋራ በመመገብ ለሰላም ያላቸውን አዎንታዊ ምላሽ\nእንደሚያሳዩ አስረድተዋል። ይህም የሚሆነው ኢትዮጵያውያን ከተሳሰብንና አንድ ከሆንን አገራችን ለሁላችንም ትበቃለች የሚል መልዕክት\nለማስተላለፍ በማሰብ መሆኑን ያስረዳሉ። ሰላምን፣ፍቅርን፣ አብሮነትን ባስቀደመው በዚህ የኢትዮጵያውያን የፍቅር ሩጫና ፌስቲቫል ላይ\nከ40 ሺ ተሳታፊዎች በላይ ይኖራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ይገልፃሉ። በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ በርካቶች\nየቲሸርት ኩፖን እየገዙ ይገኛል። የቲሸርት ሽያጩ እስከ ውድድሩ ጊዜ የሚዘልቅ ሲሆን በ250 ብር ዋጋ በሁሉም የዳሸን ባንክ ቅርንጫፎች፣\nበኦን ላየን የመገበያያ መንገዶች አሞሌ ቻት ቦት፣ ሸክላ አፕ፣ሜዳ አፕ የቲሸርት ኩፖኖቹ ሽያጭ እየተፈጸመ እንደሚገኝም አመልክተዋል።\n«ማህበሩ ለአገሪቱ አንድነትና አብሮነት የአቅሙን ለመወጣት እየታገለ ይገኛል›› ያሉት አቶ ሚስባህ ከአዲስ አበባ ባሻገር በቀጣይም\nአድማሱን አስፍቶ ለመንቀሳቀስ እቅድ መያዙን ይናገራሉ። አዲስ ዘመን ጥር 26/2012 ዳንኤል\nዘነበ", "passage_id": "4cdd37360207b78ab81fec7932bee285" } ]
90060745ec4e5be8a95c97dce4e79d9d
7d83b6b49f33f187012a3db986a60c93
የዓለም አትሌቲክስ በዶፒንግ ጉዳይ ጥርስ አውጥቷል
ቦጋለ አበበ ኢትዮጵያ አበረታች ንጥረ ነገሮችን በመጠቀም በስፖርቱ ዓለም በተለይም በአትሌቲክስ ትልቅ ስጋት ካንዣበበባቸው የዓለማችን አምስት አገራት አንዷ እንደሆነች ጉዳዩ የሚመለከታቸው ዓለም አቀፍ ተቋማት ሲያሳስቡ ቆይተዋል። በተቃራኒው ኢትዮጵያ ይህን ስጋት ለመቀነስ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በብሔራዊ ደረጃ የፀረ አበረታች ንጥረ ነገሮች ፅሕፈት ቤት አቋቁማ አበረታች ለውጥ ማምጣቷንም የዓለም አቀፉ ፀረ አበረታች ንጥረ ነገሮች ኤጀንሲ መስክሮላታል። ይሁን እንጂ ስጋት አለባቸው ከተባሉት አምስት አገራት ተርታ ለመውጣት ብዙ ስራ እንደሚጠብቃት ይታወቃል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ፀረ አበረታች ንጥረ ነገሮች ጽሕፈት ቤት አትሌቶች አውቀውም ይሁን ሳያውቁ የችግሩ ሰለባ እንዳይሆኑ የተለያዩ ግንዛቤዎችን ከማስጨበጥ ባሻገር የችግሩ ሰለባ ሆነው የተገኙ በርካታ አትሌቶች ላይ የቅጣት ውሳኔዎችን ሲያስተላልፍ ቆይቷል። ባለፈው ሳምንት አጋማሽ እንኳን አትሌት ወንድወሰን ከተማ ማሞና አትሌት እዮብ ኃብተስላሴ ጎሳ የስፖርት አበረታች ቅመሞች (ዶፒንግ) የሕግ ጥሰቶችን በመፈፀም ተጠርጥረው ላለፉት ጊዜያት ጊዜያዊ እገዳ ላይ ሆነው ጉዳያቸውን ሲያጣራ መቆየቱን ገልጿል። በዚህም መሰረት በተካሄደው ተጨማሪ ምርመራ አትሌት እዮብ ኃብተስላሴ ጎሳ እ.ኤ.አ የካቲት 02/2020 ዓ.ም ታይላንድ በተካሄደ ውድድር ላይ (Cathinone) የተባለውን የተከለከለ የስፖርት አበረታች ቅመም መጠቀሙ ተረጋግጧል። በዚህም አትሌቱ እ.ኤ.አ ከሚያዝያ 03/2020 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ አራት ዓመታት በማንኛውም ውድድር ላይ እንዳይሳተፍ ቅጣት ተጥሎበታል። በውድድሩ የተገኘው ውጤትና ውጤቱን ተከትሎ የሚሰጥ የእውቅና ሽልማትም እንዲሰረዝ ተወስኗል። በተመሳሳይ መልኩ አትሌት ወንድወሰን ከተማ ማሞ ቀደም ሲል (Cathinone) የተባለውን የተከለከለ የስፖርት አበረታች ቅመም መጠቀሙ በመረጋገጡ እ.ኤ.አ እስከ የካቲት 01/2024 ድረስ በማንኛውም ውድድር ላይ እንዳይሳተፍ እገዳ የተጣለበት መሆኑ ይታወቃል። ይሁን እንጅ አትሌቱ የተሳሳቱ የሰነድ ማስረጃዎችን በማቅረብ የህግ ጥሰት የማጣራት ሂደቱን በተለያየ መልኩ በማስተጓጎልና በድጋሚ ለማጭበርበር በመሞከር ተደራራቢ የህግ ጥሰት በመፈፀም ተጠርጥሮ ጉዳዩ ሲጣራ ቆይቷል። በመሆኑም አትሌት ወንድወሰን ያቀረባቸው ሰነዶች የሐሰት መሆናቸው በመረጋገጡና በፀረ- ዶፒንግ ህጉ አንቀፅ 2ነጥብ5 ላይ የተደነገገውን የፀረ-ዶፒንግ እንቅስቃሴውን የማስተጓጎልና አቅጣጫ የማሳት የህግ ጥሰት መፈፀሙ በመረጋገጡ ቀደም ሲል ከተጣለበት የአራት ዓመት የእገዳ ቅጣት በተጨማሪ የመጀመሪያው ቅጣት ከሚያበቃበት የካቲት 01/2024 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ ስምንት ዓመታት እስከ የካቲት 01/2032 ዓ.ም በማንኛውም ስፖርታዊ ውድድር  ላይ እንዳይሳተፍ የእገዳ ቅጣት ተላልፎበታል።የኢትዮጵያ ብሔራዊ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ጽሕፈት ቤት በቀጣይም የምርመራና ቁጥጥር ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል። የዓለም አትሌቲክስም ከዶፒንግ ጋር በተያያዘ በስፖርቱ ትልቅ ክብርና ዝና ያተረፉ አትሌቶች ላይ ሳይቀር ጥርስ እንዳወጣ የሚጠቁም አቋም በሳምንቱ መጨረሻ ይፋ አድርጓል። ኢትዮጵያን ጨምሮ የዓለምን አትሌቲክስ በበላይነት የሚመራው ተቋምና ሌሎች አገራት ባለፉት ዓመታት ከዶፒንግ ጋር በተያያዘ በስፖርቱ ትልቅ ክብርና ዝና ካላቸው አትሌቶች ይልቅ እምብዛም በማይታወቁና በአንፃራዊነት በትንንሽ ውድድሮች በሚካፈሉ አትሌቶች ላይ ትኩረት እንዳደረጉ ወቀሳ ሲቀርብባቸው መቆየቱ ይታወቃል።ማህበሩ በተለይም የዓለም አትሌቲክስ የስፖርቱ ስም እንዳይጠለሽና የተለያዩ አጋሮቹን ላለማጣት ሲል በስፖርቱ ትልቅ ስምና ዝና ላላቸው አትሌቶች ሽፋን እንደሚሰጥ ምክንያታዊ ሙግቶችን የሚያቀርቡ በርካታ ናቸው። ለዚህም በስፖርቱ ትልቅ ስም ያላቸው የኦሊምፒክና የዓለም ሻምፒዮን የሆኑ በርካታ የዓለማችን አትሌቶች እምብዛም የችግሩ ሰለባ ሆነው ቅጣት ሲተላለፍባቸው እንደማይስተዋል ያስቀምጣሉ። የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንት ሴባስቲያን ኮ ሰሞኑን በዶፒንግ ጉዳይ አትሌቶች ትልቅ ስምና ዝናቸው ከጥፋተኝነት እንደማያስጥላቸው አስገንዝበዋል። ለዚህም ባለፉት ዓመታት አሜሪካዊው የመቶ ሜትር የዓለም ሻምፒዮን ክርስቲያን ኮሊማንን ጨምሮ በስፖርቱ ትልቅ ዝናና ስኬት ያላቸው አትሌቶች እንደተቀጡ አስታውሰዋል። እንደ ኮ ገለፃ፣ በአበረታች ንጥረ ነገሮች ላይ የሚደረገው ምርመራ እየተሻሻለ በሄደ ቁጥር ዶፒንግ ተጠቅመው ለሚወዳደሩ አትሌቶች ነገሮች ከባድ እየሆኑ ቢሄዱም የችግሩ ሰለባ ላለመሆን እንዲጠነቀቁ ያደርጋቸዋል። በተለይም በመጪው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ቁጥጥሩ ከምን ጊዜውም በላይ የጠበቀ እንደሚሆን ጠቁመዋል። የኮሊማ ቅጣት አትሌቶች የቱንም ያህል በስፖርቱ ስምና ዝና ቢገነቡ አበረታች ንጥረ ነገር ተጠቅመው ከተገኙ ከቅጣት እንደማያመልጡ ማሳያና የዓለም አትሌቲክስ የሚፈራው ነገር እንደሌለ ማረጋገጫ መሆኑንም የእንግሊዝ የቀድሞ የአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር የሁለት ኦሊምፒኮች አሸናፊው ኮ ለአገራቸው መገናኛ ብዙሃን ገልፀዋል። የዓለም አትሌቲክስ እንደ አበረታች ንጥረ ነገሮች ያሉ ጉዳዮችን የሚያጣራ ገለልተኛ ቡድን አቋቁሞ ባለፉት ዓመታት ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበ እንደሚገኝ የገለፁት ኮ፣ ዓለም አቀፍ ተቋሙ በራስ መተማመኑን በመገንባት ካለአንዳች ፍርሃት አበረታች ንጥረ ነገር የተጠቀሙ የትኞቹንም የዓለማችን አትሌቶች ለማጋለጥ ከልቡ እየሰራ መሆኑን አክለዋል።
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=38366
[ { "passage": "የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የወርቅ ደረጃ ከሰጣቸው ታላላቅ የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድሮች አንዱ የሆነው የፎኮካ ማራቶን ከሳምንት በኋላ በጃፓን ይካሄዳል፡፡ በዚህ ውድድር የሚፎካከሩ የዓለማችን ጠንካራ አትሌቶች ስም ከወዲሁ ይፋ እየተደረገ የሚገኝ ሲሆን፤ የርቀቱ ኮከቦች የሆኑት ምሥራቅ አፍሪካውያን አትሌቶች የተለመደ የአሸናፊነት ግምት ተችሯቸዋል፡፡እኤአ በ2015 የቤጂንግ የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በማራቶን ተከታትለው በመግባት የወርቅና የብር ሜዳሊያ ማጥለቅ የቻሉት ኤርትራዊው ግርማይ ገብረሥላሴና ኢትዮጵያዊው የማነ ፀጋዬ ትልቅ የአሸናፊነት ግምት ከተሰጣቸው አትሌቶች ግንባር ቀደም ናቸው፡፡ግርማይ ገብረሥላሴ በዓለም ቻምፒዮናው በአስራ ስምንት ዓመቱ ሳይጠበቅ ለታላቅ ድል በመብቃት ለኤርትራ በመድረኩ የመጀመሪያ የወርቅ ሜዳሊያ ማጥለቁ የሚታወስ ሲሆን፤ በአንፃሩ በርቀቱ የተሻለ ልምድ የነበረው የማነ የብር ሜዳሊውን ለኢትዮጵያ ማስመዝገቡ አይዘነጋም፡፡ ሁለቱ የማራቶን ፈርጦች ከዓለም ቻምፒዮናው በኋላ በትልቅ ውድድር ዳግም ፎኮካ ማራቶን ላይ የሚያደርጉት ፉክክር የሚጠበቅ ይሆናል፡፡የማነ በበርካታ የማራቶን ውድድሮች በማሸነፍ ስማቸው ከሚጠቀስ የዓለማችን ድንቅ የማራቶን አትሌቶች አንዱ ሲሆን፤ ከሁለት ዓመት በፊት በዚሁ በፎኮካ ማራቶን 2:08:48 ሰዓት ማሸነፉ ይታወሳል፡፡ ይህም ሰዓቱ እኤአ 2012 ላይ በሮተርዳም ማራቶን ሲያሸንፍ ካስመዘገበው የራሱ ምርጥ ሰዓት በአራት ደቂቃ የተሻለ ሆኖ ተመዝግቦለታል፡፡ የማነ በዓለም ቻምፒዮናው የብር ሜዳሊያውን ካጠለቀ ወዲህ ጉልበቱ ላይ በገጠመው ጉዳት የ2016 ሪዮ ኦሊምፒክን ጨምሮ በርካታ ውድድሮች ያመለጡት ሲሆን፤ ያለፈውንም ዓመት በጥሩ አቋም ላይ አልነበረም፡፡ ይሁን እንጂ በ2018 ወደ ጥሩ አቋም መመለሱን ባለፈው ሰኔ ወር የኦታዋ ማራቶንን 2:08:52 በሆነ ሰዓት በማሸነፍ አሳይቷል፡፡ግርማይ ገብረሥላሴ በበኩሉ ከዓለም ቻምፒዮናው ድሉ በኋላ በሪዮ ኦሊምፒክ ሌላ ታሪክ ይሠራል ተብሎ ሲጠበቅ ሜዳሊያ ውስጥ መግባት ሳይችል ቀርቷል፡፡ ይሁን እንጂ በዚህ ታላቅ መድረክ አራተኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ እንደ ወጣት አትሌት መጥፎ የሚባል አልነበረም፡፡ከኦሊምፒኩ ስድስት ሳምንታት በኋላ በጠንካራው የኒውዮርክ ማራቶን ዳግም ሳይጠበቅ ለድል የበቃው ግርማይ በአጭር ጊዜ ውስጥ ስሙን በርቀቱ ማግነን ችላል፡፡ 2:07:46 የሆነ የራሱ ምርጥ ሰዓት ያለው ግርማይ ባለፉት ሁለት ውድድሮቹ አቋርጦ መውጣቱ ምናልባትም ወደ ጥሩ አቋሙ ካልተመለሰ በዘንድሮው የፎኮካ ማራቶን ከየማነ ጋር የሚጠበቀውን ጠንካራ ፉክክር እንዳያሳይ ስጋት ሊሆን ይችላል፡፡በዚህ ውድድር የማነ ከግርማይ ባሻገር ከሌላ አትሌት ጠንካራ ፉክክር እንደሚገ ጥመው ይጠበቃል፡፡ ይህም ውድድሩ ላይ ከየማነ ቀጥሎ ሁለተኛውን ፈጣን ሰዓት ይዞ የሚወዳደረው ኬንያዊው ቪንሰንት ኪፕሩቶ ሲሆን፤ በርቀቱ 2:05:13 የሆነ የራሱ ምርጥ ሰዓት ያለው አትሌት ነው፡፡\nበሌላ በኩል በዘንድሮው የፎኮካ ማራቶን ትኩረት ሳይሰጠው መታለፍ የሌለበት አትሌት ጃፓናዊው ዩኪ ካዉቺ ነው፡፡ ይህ አትሌት ካለፉት ዘጠኝ የፎኮካ ማራቶን ውድድሮች በስምንቱ ላይ በመሳተፍ ከሌሎቹ አትሌቶች የተሻለ ልምድ ማካበት ችሏል፡፡ ዩኪ ልምድ ማካበቱ ብቻ በውድድሩ አስፈሪ ወይንም ጠንካራ ተፎካካሪ ባያደርገውም በርቀቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያስመዘገበ ያለው ውጤትና ጥሩ አቀም ለምሥራቅ አፍሪካውያኑ አትሌቶች አስፈሪ ያደርገዋል፡፡ ዩኪ በዚህ ውድድር እኤአ በ2011፣2013እና 2016 ሦስተኛ ደረጃን ይዞ ሲያጠናቅቅ በሦስቱም ውድድሮች ርቀቱን ከ2፡10 ሰዓት በታች በማጠናቀቅ ጥንካሬውን ማሳየት ችላል፡፡ ዩኪ ምሥራቅ አፍሪካውያን ደጋግመው ያሸነፉትን የቦስተን ማራቶን በቅርቡ ማሸነፉም በአገሩና በደጋፊዎቹ ፊት በሚያደርገው ውድድር ቀላል ግምት እንዳይሰጠው ያደርጋል፡፡", "passage_id": "ba0a2da0290d0ea00dd0d72866a0b83f" }, { "passage": "ባለፉት አስር ዓመታት በአትሌቲክስ ስፖርት ውስጥ በርካታ ክስተቶች ተስተናግደው አልፈዋል። ለቁጥር የሚታክቱ ክብረወሰኖች ከመሻሻላቸውም ባለፈ በሰው ልጅ ሊደፈሩ ይችላሉ በሚል የማይጠበቁና የማይገመቱ ታሪካዊ ክንውኖችም ታይተዋል። ከእነዚህ መካከል በተለይ በስፖርቱ አጭር ርቀት ውድድር (100ሜትር) እና በረጅሙ ርቀት (ማራቶን) የተመዘገቡት ስኬቶች የሰውን ልጅ አቅም በትክክልም ማሳየት የሚያስችሉ ሆነዋል። ታዲያ በአስሩ ዓመታት ከታዩና ክብረወሰንም ካስመዘገቡ አትሌቶች መካከል የተሻለው ማን ነው? በዚህ ጥያቄ ላይ ተንተርሶ ምርጫውን\nያካሄደው ደግሞ እአአ በ1940 መሰረቱን በአሜሪካ በማድረግ የተቋቋመውና ትኩረቱን በመምና ሜዳ ተግባራት ስፖርቶች ላይ ያደረገው\nመጽሄት ነው። መጽሄቱ እአአ ከ2010-2019 ድረስ ባሉት ዓመታት ከጎዳና ላይ ውድድሮች ባሻገር ባሉት ውድድሮች አስር አትሌቶችን\nበእጩነት በማቅረብ ምርጫውን በአዲሱ የፈረንጆች ዓመት መጀመሪያ ነበር የጀመረው። በተሰጠው ድምጽ መሰረትም ኬንያዊው የ800 ሜትር\nአትሌት ዴቪድ ሩዲሽያ ተመራጭ ሊሆን ችሏል። በእጩነት ከቀረቡት አትሌቶች መካከል\nአንዱ በአጭር ርቀት የአትሌቲክስ ተጽእኖ ማሳደር የቻለው ጃማይካዊ አትሌት ዩሲያን ቦልት ነው። አሁን ራሱን ከተወዳዳሪነት ያገለለው\nቁመተ መለሎ አትሌት በ100 ሜትር የሸፈነበት 9ሰከንድ ከ63 ማይክሮ ሰከንድ የምንጊዜም የርቀቱ ምርጥ አትሌት ያደርገዋል። በውድድር\nተሳትፎው ከደረጃ ወርዶ የማያውቀው አትሌት አራት የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያዎችን ከማጥለቅ ባሻገር የዓለም ቻምፒዮን በመሆንም ክብረወሰኑን\nአርቆ የሰቀለ አትሌት መሆኑ ምርጫውን በአሸናፊነት ያጠናቅቃል በሚል ይጠበቅ ነበር። በረጅም ርቀት የመም ላይ ውድድሮች በኢትዮጵያዊያኑ ጀግና አትሌቶች እግር የተተካው እንግሊዛዊ አትሌት\nሞሃመድ ፋራም በእጩነት ከቀረቡት መካከል ነበር። የዓለም ቻምፒዮናው በኦሊምፒክ አራት የወርቅ ሜዳሊያዎችን ያሳካ ሲሆን፤ በ5ሺ\nእና 10ሺ ርቀቶች ሃገሩን በተደጋጋሚ ለማስጠራት ችሏል። አትሌቱ ምንም እንኳን ከመም ወደ ጎዳና ላይ ውድድሮች ባደረገው ሽግግር\nእንደሚጠበቀው ውጤታማ ባይሆንም ያለፉት አስር ዓመታት ግን ለእርሱ አስደሳች ነበሩ። ከመም ይልቅ በማራቶን ስሙ የገነነውና የዚህ ወቅት የርቀቱ ቁጥር አንድ አትሌት የሆነው ኬንያዊ ኢሉድ\nኪፕቾጌም ቀዳሚ ተመራጭ ይሆናል በሚል ከሚጠበቁት እጩዎች መካከል ነበር። የዓለም ክብረወሰን ባለቤቱ እንዲሁም ማራቶንን ከ2 ሰዓት\nበታች የመግባት ሙከራውን ያሳካው አትሌት በሮጠበት ጫማ ምክንያት ውዝግቦችን ያስተናግድ እንጂ የጎዳና ላይ ሩጫዎች ንጉስነቱን ማንም\nሊቀማው እንደማይችል ነው አዘጋ ጆቹ ያረጋገጡት። አሜሪካዊያኑ ክርስ ቲያን ቴይለርና አሽተን ኢትን፣ ደቡብ አፍሪካዊው ዋይዴ ቫን ኔኬርክ፣ ፈረንሳ\nዊው ሬናውድ ላቪሌኔ፣ የኳታሩ ሙታዝ ባርሺም እንዲሁም ጀርመናዊው ሮበርት ሃርቲንግም ከአስሩ እጩዎች መካከል ይገኙበታል። ከእጩዎቹ መካከል በተለይ ‹‹የዓለም ፈጣኑ ሰው›› በሚል የሚታወቀው ጃማይካዊ አትሌት አብላጫውን\nድምጽ ያገኛል የሚል ግምት ያግኝ እንጂ አሸናፊ የሆነው ግን ዴቪድ ሩዲሽያ ነው። የለንደንና ሪዮ ኦሊምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤቱ\nእንዲሁም የዴጉና ቤጂንግ የዓለም ቻምፒዮናው አትሌት፣ በተለይ እአአ በ2012ቱ የለንደን ኦሊምፒክ ርቀቱን ያጠናቀቀበት ሁኔታ በአስር\nዓመታት ከማይዘነጉ ትዝታዎች መካከል ቀዳሚው በሚል በዓለም አትሌቲክስ መመረጡ የሚታወስ ነው። አትሌቱን አስደናቂ ከሚያደርጉት ምክንያቶች\nመካከል አንዱ፣ በርቀቱ የዓለም ክብረወሰንን ለሶስት ጊዜያት(1:41.09፣ 1:41.01፣ 1:40.91) መስበር መቻሉ ነው። መጽሄቱ መሰል ምርጫዎችን ማካሄድ የጀመረው እአአ በ1960ዎቹ ሲሆን፣ የመጀመሪያው አሸናፊም ኒውዝላንዳዊው\nፒተር ስኔል ነበር። እአአ የ1970ዎቹን ክብር ደግሞ የሶቬት ህብረት አትሌት የሆነው ቪክቶር ሳኔይቭ ነበር የወሰደው። በ1980ዎቹ\nአሜሪካዊው ካርል ሉዊስ ምርጥ ሲሰኝ፤ የ90ዎቹንም ሌላኛው የሃገሩ ልጅ ሚካኤል ጆሃንሰን አሸናፊ ሆኗል። እአአ ከ2000-2009\nባሉት ዓመታት ምርጥ አትሌትነት ምርጫ ወደ ኢትዮጵያ የመጣ ሲሆን፤ አንበሳው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ቀዳሚ ሊሆን ችሏል። አዲስ ዘመን የካቲት 2/2012ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "c1a3934ef128e2c24bafaf397641a09b" }, { "passage": "በአትሌቲክሱ ዓለም\nረጅም ርቀት ውድድሮች\nየስፖርቱ ድምቀቶች ናቸው።\nበተለይም አምስትና አስር\nሺ ሜትር ውድድሮች\nበዓለም ላይ ከፍተኛ\nተቀባይነትን እያገኙ ለመጡ\nየማራቶን ውድድሮች መሰረት\nናቸው። እንደ አጠቃላይ\nለአትሌቲክስ ስፖርትም ቢሆን\nየጀርባ አጥንቶች ናቸው።\nበታላቁ የስፖርት መድረክ\nኦሊምፒክም ቢሆን የረጅም\nርቀት ውድድሮች የማይረሳ\nታሪክ ያላቸውና ከስፖርት\nቤተሰቡ ምናብ ወደ\nፊትም ቢሆን የማይፋቁ\nናቸው።እአአ 2000 ሲድኒ ኦሊምፒክ ላይ\nጀግናው አትሌት ኃይሌ\nገብረስላሴና ኬንያዊው ድንቅ\nአትሌት ፖል ቴርጋት\nበአስር ሺ ሜትር\nቁጭ ብድግ የሚያደርግ\nግሩም ፉክክር ማን\nይረሳዋል? ይህን ከህሊና\nየማይፋቅ ውድድር ጨምሮ\nበርካታ የአምስትና አስር\nሺ ሜትር ውድድሮች\nየኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮና\nመገለጫዎች መሆናቸውን የሚክድ\nይኖራል ብሎ ማሰብ\nከባድ ነው። በእነዚህ\nውድድሮች ላይ ምሥራቅ\nአፍሪካውያን ፍፁም የበላይነት\nእየጎላ መምጣቱም ለምዕራባውያን ምቾት እንዳልሰጣቸው ምልክቶች መታየት\nየጀመሩት ዛሬ አይደለም።\nለዚህም ጠንክረው ሠርተው\nየበላይነት ከመያዝ ይልቅ\nበሴራ ለማመናቸው በርካታ\nማሳያዎችን ማስቀመጥ ይቻላል።\nእኛ ብቻ በሁሉም\nነገር የበላይ እንሁን\nየሚል ክፉ አባዜ\nየተጠናወታቸው ምዕራባውያን በመጀመሪያ\nየአገር አቋራጭ ሩጫን\nከኦሊምፒክ ድራሹ እንዲጠፋ\nአደረጉ። ቀጥሎም ቀስበቀስ\nየአስር ሺ ሜትር\nየመም(ትራክ) ውድድሮችን\nከገበያ ጋር በማስተሳሰር ‹‹አዋጭ አይደሉም››\nበሚል በዓመት አንድ\nጊዜ እንኳን የሚካሄዱበትን መንገድ ጥርቅም\nአድርገው ዘጉ። በዚህም\nበርካታ የምሥራቅ አፍሪካ\nአትሌቶች በለጋ ዕድሜያቸው\nፊታቸውን ወደ ጎዳናና\nማራቶን ውድድሮች አዙረው\nሮጠው ሳይጠግቡ ከፉክክር\nውጪ እንዲሆኑ አደረጉ።\nየምሥራቅ አፍሪካ አትሌቶች\nአስር ሺ ሜትርን\nእርግፍ አድርገው በጎዳና\nውድድር በተጠመዱበትና በተዘናጉበት ወቅት ግን\nየቤት ሥራቸውን ውስጥ\nለውስጥ ሠርተው በሞፋራህና\nበጋለን ሩፕ አማካኝነት\nስንት የኦሊምፒክና የዓለም\nቻምፒዮና ሜዳሊያዎችን እንደሰበሰቡ የምንዘነጋው አይደለም።\nየሞፋራህና ጋለን ሩፕ\nየጀግንነት ጀምበር እየጠለቀ\nሲመጣም ችላ ብለውት\nየቆየውን አምስትና አስር\nሺ ሜትር ከኦሊምፒክ\nየማስወጣት አጀንዳ ዳግም\nአራገቡት። ‹‹ውጣ አትበለው\nእንዲወጣ አድርገው›› እንደሚባለው አስር ሺ\nሜትርን እንዳኮላሹት ሁሉ\nየቀራቸውን አምስት ሺ\nሜትር ውድድርን ለመቅበር\nከሰሞኑ ሌላ ስልት\nይዘው ከች ብለዋል።\nየዓለም አቀፉ አትሌቲክስ\nፌዴሬ ሽኖች ማህበር\n(አይ.ኤኤ.ኤፍ)\nባለፈው ማክሰኞ ኳታር\nዶሃ ላይ አምስት\nሺ ሜትር ውድድር\nከ2020 ጀምሮ ከዳይመንድ\nሊግ ፉክክሮች እንዲሰረዙ\nወስኗል። ይህ ውሳኔ\nአምስት ሺ ሜትር\nየአስር ሺ ሜትር\nዕጣ ፋንታ እንዲደርሰው የሚያደርግ በመሆኑ\nከአፍሪካውያን የስፖርት ቤተሰቦች\nተቃውሞና ወቀሳ እየቀረበበትም ይገኛል። የኢትዮጵያና ኬንያ አትሌቲክስ\nፌዴሬ ሽኖችን ጨምሮ\nጀግናው አትሌት ኃይሌ\nገብረስላሴ ውሳኔውን ከተቃወሙት\nመካከል ይገኙበታል። ባለፉት\nሁለት ቀናትም አንዳንድ\nየጃማይካ የቀድሞ አትሌቶች\nድምፃቸውን ማሰማት ጀምረዋል።\nይህ ውሳኔ አፍሪካ\nበዓለም አቀፉ አትሌቲክስ\nፌዴሬሽኖች ማህበር ተሰሚ\nየሆነ ወካይ እንደሌላት\nአሳይቶናል። ያም ቢሆን\nረጅም ርቀት ውድድሮች\nየበለጠ አፍሪካውያንን ተጠቃሚ\nየሚያደርጉ በመሆኑ የአፍሪካ\nአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር\n(ሲ ኤኤ)፤\nየአፍሪካ ኦሊምፒክ ኮሚቴ(አኖካ) ውሳኔውን ለማስቀየር\nአልረፈደባቸውም። የአበበ ቢቂላ ታሪካዊ\nድል የኢትዮ ጵያውያን\nብቻ እንዳልሆነው ሁሉ\nይህ ጉዳይ የምሥራቅ\nአፍሪካውያኑ ጎረቤታሞች ብቻ\nአይደለም። አፍሪካውያን በታላቁ\nየኦሊምፒክ መድረክ ሰንደቅ\nዓላማቸው ከፍ ብሎ\nሲውለበለብ፣ ብሔራዊ መዝሙራቸው\nበክብር ሲዘመር ማየት\nከፈለጉ ይህን ውሳኔ\nለማስቀየር በአንድ ላይ\nመቆም አለባቸው። ረጅም ርቀት የአፍሪካውያን ታሪክ በወርቅ\nቀለም የተፃፈበት ዛሬም\nነገም መገለጫቸው ሆኖ\nየሚኖር ህልውናቸው ነው።\nእንደ ኃይሌ ሁሉ\nሌሎች ተፅዕኖ ፈጣሪ\nአፍሪካውያን አትሌቶች ድምፃቸውን\nማሰማት ይኖርባቸዋል። በኬንያዊው\nድንቅ አትሌት ፖል\nቴርጋት የሚመራው የአፍሪካ\nአትሌቶች ኮሚሽንም እዚህ\nጋር አቅሙን ማሳየት\nአለበት።ምዕራባውያኑ እንዲህ ዓይነቱ\nአጋጣሚ በራሳቸው ላይ\nእንዲደርስ ማድረግ አይደለም\nበኦሊምፒክ እንዲስፋፋና የበላይነታቸውን ይዘው እንዲዘልቁ\nያገኙትን ዕድል ከመጠቀም\nወደኋላ አይሉም። አሁንም\nበቀጣዩ የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ እንኳን የነሱ\nፍላጎት ያለባቸው ወይም\nሜዳሊያ ያስገኝልናል ብለው\nያሰቡትን ማንኛውንም እንቅስቃሴ\nየኦሊምፒክ ስፖርት እንዲሆን\nእያደረጉ ነው።በቀጣዩ ኦሊምፒክ ብሬክ\nዳንስ ሳይቀር እንዲካተት\nአድርገዋል። አፍሪካውያንም ከምዕራባውያን ጋር በኦሊምፒክ\nተፎካካሪ ሆነው ለመገኘት\nእንደ አገር አቋራጭ\nሩጫ ዓይነት ውድድሮችን\nከመጠቀም ባለፈ ረጅም\nርቀቶች ላይ ያንዣበበውን አደጋ ለማስቀረት\nበጋራ መጋፈጥ ግድ\nይላቸዋል። የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ፕሬዚዳንትና የቀድሞ የአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር የኦሊምፒክ አሸናፊ እንግሊዛዊው ሴባስቲያን ኮ ወደ ስልጣን ሲመጡ እዚሁ አዲስ አበባ ላይ የረጅም ርቀት የቀድሞ ዝናና ስም ለመመለስ እንደሚሠሩ ቃል ቢገቡም አሁን ቃላቸውን አጥፈዋል። አፍሪካውያን በአንድነት ካሁኑ ካልታገሉም እንደ አገር አቀራጭ ውድድር ሁሉ አስርና አምስት ሺ ሜትር ውድድሮች በቅርቡ ከኦሊምፒክ ላለመሰረዛቸው እርግጠኛ መሆን አይቻልም።አዲስ ዘመን\nመጋቢት 6 /2011ቦጋለ\nአበበ ", "passage_id": "6d6589aa4c0a66d90450b044e54ca629" }, { "passage": "የመጨረሻ ክፍልባለፈው ሳምንት የስፖርት ማህደር አምዳችን በኢትዮጵያ ስፖርት ታሪክ ትልቅ ስፍራ የሚሰጣቸውን የ1960 እና 1964 የሮምና ቶኪዮ ኦሎምፒኮችን በተመለከተ ከአበበ ቢቂላ ታሪካዊ የማራቶን ተከታታይ ድሎች ባሻገር ያልተሰሙና ያልተነገሩ ወጎችን ማንሳታችን ይታወሳል። በተለይም ከሮም ኦሎምፒክ የአበበ ቢቂላ የባዶ እግር ገድል ባሻገር የኦሎምፒክ ቡድኑ ገና ከስፍራው ከማቅናቱ አንስቶ በድል እስኪመለስ ድረስ ከመድረክ ጀርባ የነበሩትን ወጎችና ቡድኑ የገጠመውን አጠቃላይ ፈተና በስፋት ዳሰናል። ቀጣዩን የቶኪዮ 1964 ኦሊምፒክን የተመለከቱ ወጎችን ለማቅረብም ለዛሬ ቀጠሮ በያዝነው መሰረትም እንደሚከተለው ለንባብ አሰናድተናል። ቶኪዮ ኦሎምፒክ 1964 ወደ 1964 የቶኪዮ\nኦሎምፒክ የሚጓዘው ቡድን\nበቢሾፍቱ ከተማ አየር\nሃይል በትብብር በሰጠው\nካፕ በተለየ መልኩ\nሲዘጋጅ ቢቆይም ወደዚህ\nኦሎምፒክ ለመጓዝ ምክኒያት\nየሆነው የሮም ኦሎምፒክ\nባለድሉ አበበ ቢቂላን\nችግሮች ይፈታተኑት ነበር።\nበዚሁ ዝግጅት ወቅት\nአበበ ወድቆ በእጁ\nላይ ጉዳት ደርሶ\nነበር። ይህን ዜና\nየሰሙ የውጪ አገር\nመገናኛ ብዙሃንም ወሬውን\nተቀባበሉት። አበበ ቢቂላ\nበቶኪዮ ኦሎምፒክ እንደማይወዳደርም\nፃፉ። ይሁን እንጂ\nአበበ ቀላል ጉዳት\nእንደደረሰበት ፊት ለፊት\nወጥቶ አስተባበለ። የኦሎምፒክ\nጉዞው መዳረሻ ላይ\nግን ሌላ ከባድ\nችግር ገጠመው። አሰልጣኙ\nኦኔ ኔስካነን በአበበ\nላይ የተለየ ነገር\nማስተዋል ከጀመሩ ሰነባብተዋል።\nአበበ ልምምድ ጀምሮ\nያቋርጣል፣ ሲቀመጥና ሲነሳ\nወንበር ይደገፍም ነበር፣\nከመኝታውም እንደ ቀድሞው\nቀልጠፍ ብሎ መነሳት\nአልሆነለትም፣ ይባስ ብሎም\nውድድር እያቋረጠ እስከ\nመውጣት ደረሰ። ይህንን\nያስተዋሉት ቡድን መሪው\nይድነቃቸው ተሰማና ስዊድናዊው\nአሰልጣኝ ኦኔ ኔስካነን\nአበበ ቢቂላ ሕክምና\nመሄድ እንዳለበት ተስማምተው\nወደ ምኒልክ ሆስፒታል\nወሰዱት። የጤና ምርመራው\nውጤት ግን ብዙዎችን\nያስደነገጠ ሆነ። አበበ\nትርፍ አንጀት እንዳለበትና\nበአስቸኳይ የቀዶ ጥገና\nካላደረገ ሕይወቱ አደጋ\nላይ እንደሚወድቅ መነገሩ\nስጋት ፈጠረ። ይህ\nጉዳይ በሚስጥር ቢያዝም\nእያደር ገሃድ መውጣት\nጀመረ። ይድነቃቸውና ኔስካነን\nበጉዳዩ ላይ መከሩ።\nአበበም ቀዶ ጥገናውን\nለማድረግ ተስማማ። የሕክምና ክፍሉና ሌሎች ወገኖች ግን ሦስት ሳምንት ለቀረው ውድድር አበበ ቀዶ ጥገና ማድረግ እንደሌለበት አቋም ያዙ። ይድነቃቸውና ኔስካነን ግን በራሳቸው ሃላፊነት ወስደው ቀዶ ጥገናው እንዲደረግ ወሰኑ። በሁለቱ ሰዎች ላይ ‹‹ኢትዮጵያ በቶኪዮ ኦሎምፒክ የምታገኘውን ወርቅ አስነጠቁ›› በሚል ክስና ወቀሳ ተሰነዘረባቸው። አበበ በሆስፒታል ተኝቶ የሚያሳይ ፎቶ ግራፍ በመውጣቱም የዓለም መገናኛ ብዙሃን አበበ በውድድሩ እንደማይሳተፍ መዘገብ ጀመሩ። በአዲስ አበባ የነበሩ የዜና ወኪሎች አበበ ከቡድኑ ጋር በዝግጅት ላይ ስለሌለ በውድድሩ እንደማይሳተፍ ማረጋገጫ አገኙ። በጉዞው መጨረሻ አበበ ከቡድኑ ጋር ቢጓዝም ህመም ላይ ስለነበረ ጋቢ ለብሶ የተሻለ ህክምና ለማድረግ እንጂ በውድድሩ ላይ ይሳተፋል የሚል እምነት አልነበረም። በቶኪዮ ኦሎምፒክ የተጓዘው 16 ሰው ሲሆን ለዝግጅት የወጣው 80ሺ ብር ብቻ ነው። ማራቶን የሚካሄደው በውድድሩ መዝጊያ ዕለት በመሆኑ አበበ ከህመሙ ለማገገም በቂ ጊዜ አገኘ። አበበ በውድድሩ መሳተፉ እንደታወቀ ብዙዎችን አስገረመ። ቀዶ ጥገና አድርጎ ቁስሉ ሳይጠግ መወዳደሩ ማሸነፍ ከመቻሉ ሌላ በጤናው ላይ ትልቅ ጉዳት እንደሚያመጣ ተዘገበ። የጤና ባለሙያዎች የኢትዮጵያን ልዑካን ቡድን አበበን ለውድድር ማቅረባቸው በሕይወቱ ላይ እንደፈረዱ ሆኖ ተነገረ። በዚህ መሃል ደግሞ አንድ ሰው ብቅ አለ። ሰውየው አሴክ የተባለ የስፖርት ጫማ አምራች ድርጅት ባለቤት ናቸው። ድርጅቱ ግን የሚታወቅ አልነበረም። ይህ ድርጅት ለአበበ ጫማ ሰርቶ እንደሚያቀርብ ነገራቸው። የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ግን ለጫማ መግዣ የሚሆን ገንዘብ እንደሌላቸው ገለፁ። ባለቤቱ ግን በነፃ መሮጫ ጫማውን እንደሚያቀርብ ተናገረ። ነፃ መሆኑን የሰሙት የኛ ሰዎች ‹‹እንደዚያማ ከሆነ ልኩን ውሰድና ሰርተህ ስጠን›› አሉት። ብዙ መላምት ሲሰጥበት የነበረውና ከሕመሙ በቅጡ ያላገገመው አበበ ውድድሩን ማሸነፉ ተዓምር ሆነ። በሽተኛው ሰው ጤነኞቹን ማሸነፉ ብቻ ሳይሆን የዓለም ክብረወሰን ማሻሻሉ ‹‹ ይሄ ሌላ ፍጡር እንጂ ሰው አይደለም›› እስኪባል ተደነቀ። የጤና ባለሙያዎቹም ያዩትን ነገር ማመን ከብዳቸው መጀመሪያም ቢሆን አልታመም ወደሚል ድምዳሜ ደርሰው ቀዶ ጥገና ማድረጉን እስከመጠራጠር ደረሱ። የቶኪዮውን ኦሎምፒክ ለየት\nየሚያደርገው አፍሪካውያን የነፃነት\nአየር መተንፈስ በጀመሩበት ወቅት ላይ መደረጉ ነው። ብዙ የአፍሪካ አገራት ከቅኝ ግዛት ወጥተው በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት፣ ለመወዳደር ብቻ ሳይሆን ወደ ነፃነት ሜዳ የመጡበትም መድረክና ዓለምን የተቀላቀሉበት ስፍራ ነበር። በኦሎምፒክ መድረክ የመጀመሪያቸው በመሆኑ የጥቁር ኩራትና ተምሳሌት በሚሉት አበበ ቢቂላ የይቻላል መንፈስ ተቀርፀው ነበር። ብዙዎቹ የአፍሪካ አገራት የመጀመሪያቸው ኦሎምፒክ በመሆኑ በማራቶን ውድድር እንደ አበበ ቢቂላ በባዶ እግር የሮጡበት አጋጣሚም በታሪክ ይታወሳል። በቶኪዮ ኦሎምፒክ ከአበበ ቢቂላ ሌላ ማሞ ወልዴ በአስር ሺ ሜትር ወርቅ ማምጣት የሚችልበት እድል በቀላ የቴክኒክ ስህተት ሳይሳካ ነገር ግን ትልቅ ትምህርት የተገኘበት ነበር። በፍፃሜው ውድድር የተጠበቁት የአሜሪካና የአውስትራሊያ አትሌቶች ነበሩ። ማሞ ስለተፈጠረው ነገር ሲናገር‹‹ እንደማሸንፋቸው እርግጠኛ ነበርኩ፣ እስከ መጨረሻ ዙር አብረን ነበርን፣ ሁለቱ ከእኔ ፊት ነበሩ፣ የቱኒዚያው ጋሙዲ ከእኔ ቀጥሎ ነው፣ ከእኔ ፊት የነበሩት ሁለቱም ትንፋሽ ጨርሰዋል፣ የመጨረሻ መቶ ሜትር ላይ ደርሰን አምልጬ ለመሄድ ተዘጋጀሁ፣ አሜሪካዊው አትሌት የመጨረሻው መቶ ሜትር መታጠፊያ ላይ እየተጠመዘዝኩ አውስትራሊያዊው አትሌት በክርኑ ደቆስ አድርጎ ወደ ኋላ እንድቀር በማድረግ አምልጦ ለመውጣት ነበር የተዘጋጀው፣ እኔ ደግሞ በሁለቱ መሃል በተፈጠረው ክፍተት አምልጬ ለመሄድ ስል ለእነሱ የተሰነዘረው ክርን እኔን መቶኝ ተደናቅፌ ወደኩኝ፣ ያን ጊዜ ሁሉንም አጣሁ፣ ከኋላ የነበረው ቱኒዚያዊ አትሌት የነሐስ ሜዳሊያውን ወሰደ፣ ከውድድሩ በኋላ ከአበበ ጋር ስነጋገር ስህተት መስራቴን አወኩኝ፣ እኔ መሄድ የነበረብኝ በሦስተኛው መስመር ነበር። ›› ይላል። በአስር ሺ ሜትር የማሞ ስህተት ለኢትዮጵያውያን ማስተማሪያ የሆነው የቶኪዮው ኦሎምፒክ ሆኖ ከዚያ በኋላ በርቀቱ ቅርፅ ማስያዝ የተቻለበት አጋጣሚ ተፈጥሯል። የቶኪዮ ኦሎምፒክ ከተጠናቀቀ\nበኋላ ቡድኑ ወደ\nአዲስ አበባ ከመመለሱ\nበፊት ጃፓኖች ማወቅ\nየፈለጉት የአበበን የአሸናፊነት\nሚስጥር ነበር። በሽተኛ\nሆኖ አርባ ሁለት\nኪሎ ሜትር የሮጠበት\nሚስጥር። በዚህ የተነሳ\nበጃፓን ስርዓተ ትምህርት\nበሞራል ትምህርት ውስጥ\nአበበ ቢቂላን የሚመለከት\nምዕራፍ እንዲካተት አደረጉ።\nይህም ማኛውንም ነገር\nከግብ ለማድረስ ፅናት\nማስፈለጉን ለዚህም አበበን\nምሳሌ ማድረጋቸው ነው።\nበሮም ኦሎምፒክ በባዶ\nእግሩ ማሸነፉ፣ በቶኪዮ ከሕመሙ ሳያገግም ጤነኞቹን ማሸነፉ ተምሳሌት መሆኑን ‹ፅናት› ካለ ሁሉንም ነገር ማድረግ እንደሚቻል ጃፓኖች ያስተምሩበታል። ከውድድሩ በኋላ አበበን የሚመለከቱ ሁለት ነገሮች ተከስተዋል። አበበ ህመምተኛ በመሆኑ ጋቢ ለብሶ ነበር ወደ ጃፓን የተጋዘው። በወቅቱ በአገራችን አንድ ሰው ከታመመ ጋቢ መልበሱ የተለመደ ነው። ጃፓናውያንም ከውድድሩ በኋላ ለማስታወሻነት ጋቢውን አስቀርተውታል። ለዚህም ምክኒያት ነበራቸው፣ እነሱ ቱሪዝምን በአግባቡ ስለሚጠቀሙበትና አበበም በውድድሩ መነጋገሪያ ስለነበረ ቱሪስቶች ጋቢውን ለብሰው ፎቶ ግራፍ እንዲነሱ ያደርጉበታል። ሌላው አስገራሚ ነገር አበበ የጣት ቀለበቱ ባረፈበት ሆቴል መጥፋቱ ነበር። ቀለበቱ ከሮም ድል በኋላ ከቀዳማዊ ሀይለስላሴ የተበረከተለት ነበር። የቀለበቱ መጥፋት በመገናኛ ብዙሃን ጭምር ተነገረ። በቀለበቱ ላይ የተፃፈው ‹‹ሮም 1960›› የሚልና የንጉሱ ፊርማ ያረፈበት መሆኑ በመገለፁ ለፈላጊዎቹ ብዙም አላስቸገረም። አበበ የወቅቱ ዝነኛና የእነሱም እንግዳ በመሆኑ ጃፓናውያን ወርቁን አፈላልገው መገኘቱን አበሰሩት። የቶኪዮ ልዑካን ቡድን ወደ አገሩ ሲመለስ በአበበ ቢቂላ ድል አዲስ አበባ በአቀባበሉ ደምቃ ነበር። የክቡር ዘበኛ ኦኬስትራ (የአበበ ክፍል) ዝነኛ ሙዚቀኞች ጥላሁን ገሰሰና እሳቱ ተሰማ ‹‹በጣም ደስብሎናል ምኞታችን ሞላ፣ አሸንፎ መጣ አበበ ቢቂላ›› በሚል ያዜሙት ለአቀባበሉ ትልቅ ድምቀት ነበር። የቶኪዮ ኦሊምፒክ ማራቶን የተካሄደው ጥቅምት 11 ቀን 1957 ነበር። ሕዝቡ ድሉን በሬዲዮ ዜና ሰማ እንጂ ምንም ያየው ነገር አልነበረም። ነገር ግን ሚያዝያ 23 1957 የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ስርጭት የጀመረበት ጊዜ በመሆኑ በጃፓን ኤምባሲ ትብብር አበበ ሲሮጥና ሲያሸንፍ የታየበት አጋጣሚ ተፈጥሯል። ቶኪዮ አበበን ምን ጊዜም አትረሳውም። ዘንድሮ ሊካሄድ ቀጠሮ ተይዞለት በኮሮና ቫይረስ ስጋት የተራዘመው የቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ የአዘጋጅነት እድሉን ለማግኘት ጃፓን አበበ ቢቂላን ‹ዳግም አበበን ለማግኘት› በሚል ለቅስቀሳ ተጠቅማበታለች። የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ በትምህርት ቤት ሩጫ ተሳታፊ በነበሩበት ወቅት የአበበ አድናቂና በአበበ ቅፅል ስም የሚጠሩ እንደነበሩም ከራሳቸው አንደበት ተሰምቷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአራትና አምስት ዓመታት በፊት አዲስ አበባ በመጡበት ጊዜም የአበበን ቤተሰቦች ጎብኝተዋል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 12/2012", "passage_id": "5147af55bab3a9bb76e821f976a100e1" }, { "passage": "በ25 ዓመታት የውድድር ዘመኑ፤ በርካታ የኦሊምፒክና የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ሜዳሊያዎችን እንዲሁም 27 የዓለም ክብረወሰኖችን በእጁ አስገብቷል። በረጅም ርቀት የመም ተወዳዳሪዎችም ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል፤ ከገጹ ፈገግታ የማይነጥፈው ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ። በስድስት ዓለም ቻምፒዮናዎች ተሳትፎው አራት የወርቅ፣ ሁለት የብርና አንድ የነሃስ በጥቅሉ ሰባት ሜዳሊያዎችን ለሃገሩ አበርክቷል። እአአ 1993 የስቱትጋርት ቻምፒዮና የመጀመሪያ ተሳትፎው ሲሆን፤ በ10ሺ ሜትር የወርቅ በ5ሺ ሜትር ደግሞ የብር ሜዳሊያ ነበር ያጠለቀው። ከሁለት ዓመታት በኋላም ጉተንበርግ በተዘጋጀው ቻምፒዮና በ10ሺ ሜትር የወርቅ ሜዳሊያውን መድገም ችሏል። በአቴንስ እና ሴቪላ በተካሄዱት ውድድሮችም በተመሳሳይ የወርቅ ሜዳሊያውን የግሉ አድርጓል። እአአ የ2001 የኤድመንተን ቻምፒዮና የመጀመሪያውን የነሃስ ሜዳሊያ ሲወስድ፤ በመድረኩ የመጨረሻ ተሳትፎውን ያደረገበት የፓሪሱ ቻምፒዮናም አትሌቱን በብር ሜዳሊያ ነው ያሰናበተው። አሁን ኃይሌ ራሱን ከውድድሮች ካገለለ ዓመታትን አስቆጥሯል። ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንትነት መንበሩን በቃኝ ብሎ ቢያስረክብም አገራቸውን ወክለው ለመሮጥ ከተዘጋጁ አትሌቶች ጎን አይጠፋም። በስድስት ጊዜ የዓለም ቻምፒዮና ተሞክሮውን ነገ በሚጀምረው የኳታር የዓለም ቻምፒዮና ኢትዮጵያን ለሚወክሉ አትሌቶች እንደሚከተለው ያካፍላል። «ዓለም ቻምፒዮናን፤ በዓለም ላይ ያሉ ምርጥ አትሌቶች የሚሳተፉበት መሆኑ ለየት ያደርገዋል። በዳይመንድ ሊግ እና ሌሎች ውድድሮች ላይ የሚገኙት ጥቂቶች ሊሆኑ ይችላሉ፤ በዓለም ቻምፒዮና ግን በዓለም ላይ ‘አሉ’ የተባሉ አትሌቶች የሚሰባሰቡበት ነው»። ጠንካራ አትሌቶች\nየሚገናኙበትና የምርጦች\nምርጥ የሚመረጥበትም\nይኸው ውድድር\nበመሆኑ በአትሌቶች\nዘንድ በልዩነት\nይታያል። አትሌቶች\nሃገራቸውን የሚወክሉበት\nእንዲሁም ሃገራት\nባስመዘገቡት ውጤት በዓለም\nአቀፉ የአትሌቲክስ\nፌዴሬሽኖች ማህበር\nደረጃ የሚያገኙበት\nበመሆኑም፤ ስፖንሰር\nአድራጊ ተቋማትም\nጭምር ከፍተኛ\nትኩረት እንደሚሰጡት አንጋፋው አትሌት ይጠቁማል። ሃገሩን ወክሎ\nበጥረቱ ውጤት ካስመዘገበባቸው\nቻምፒዮናዎች ሁሉ እስካሁንም\nከትውስታው ያልተሰረዙ\nገጠመኞችም አሉት።\n«ከተካፈልኩባቸው ቻምፒዮናዎች\nሁሉ እስካሁንም\nየማዝንበት አጋጣሚ\nየደረሰው በስቱትጋርት\nነው። እአአ የ1993ቱ\nቻምፒዮና በ5ሺ\nሜትር አሸናፊነት\nአምልጦን የብር ሜዳሊያ\nነበር ያገኘነው»\nሲል ቁጭቱን\nይናገራል። ገጠመኞቹ\nእነዚህ ብቻም አይደሉም\nኃይሌ ይቀጥላል፤\n«እአአ 2001 ኤድመንተን\nላይ እኔና አሰፋ\nመዝገቡ ማሸነፍ\nበምንችለው ውድድር\nላይ የፈጸምነው\nስህተት ነው። በተለይ\nእኔ ለአምስተኛ\nጊዜ አሸናፊ\nእንደምሆን በማመኔ\nመዘናጋት አሳይቼ\nነበር፤ ባልተጠበቀ\nሁኔታ ግን አንድ\nኬንያዊ አትሌት\nአሸነፈን። ይህም እስካሁን\nእንደ እግር እሳት\nነው የሚለበልበኝ»\nበማለት በድንገት\nከመሃላቸው ፈትልኮ\nወርቁን ስላጠለቀው\nጥርሰ ፍንጭቱ\nኬንያዊ አትሌት\nቻርልስ ካማቲ ያስታውሳል። ከተካፈለባቸው ቻምፒዮናዎች ሁሉ አንጋፋውን አትሌት በተለየ የሚያስደስተው እአአ 1995 በስዊድን ጉተንበርግ የነበረው ተሳትፎ ነው። በዚህ ውድድር ላይ የመጨረሻውን 200ሜትር፤ የወቅቱ ጠንካራ አትሌቶች ከነበሩት፤ ፖል ቴርጋት፣ ካሊድ ካህ እና ሳላ ኢሱ ለማምለጥ ያደረገው ጥረት ያስደስተዋል። አጨራረሱን ሲያስታውስም ምናልባት ከ800ሜትር ሯጮች በላይ የፈጠነ እንደነበር ነው የሚገልጸው። ከትውስታው መልስም\nነገ በዶሃ በሚጀመረው\nቻምፒዮና ስለሚሳተፈው\nየኢትዮጵያ ብሄራዊ\nቡድን አስተያየት\nሰጥቷል። ከዳይመንድ\nሊግ ውድደሮች\nበመነሳት በወንድም\nበሴትም በተለይ\nበ10ሺ ሜትር\nጥሩ ጥሩ አትሌቶች\nአሉ። በዚህ ውድድር\nላይ ግን ብልጠት\nበጣም አስፈላጊ\nነገር ነው። በተለይ\nየመጨረሻዎቹ ሜትሮች\nላይ የተለየ\nነገር ካላደረጉ\nልፋታቸው ሁሉ ገደል\nነው የሚገባው።\nየመጨረሻው 100ሜትር\nቀላል አይደለም\nበጣም ብዙ ነገር\nነው የሚያበላሸው፤ በመሆኑም እዚህ ላይ አእምሯቸውንና ሰውነታቸውን መጠቀም አለባቸው። ብልጠት ካልታከለበት ሰውነት ብቻውን አሸናፊ አያደርግም፤ ብልጥ ከሆኑ ግን ሰውነትም ቢደክም ማሸነፍ ይቻላል በማለት የይቻላል ተምሳሌቱን ይናገራል። ቡድኑ ወደ ዶሃ ከመጓዙ ከሁለት ቀናት አስቀድሞም የብዙዎች ተምሳሌት የሆነው አትሌቱ ልምምድ በሚያደርጉበት አዲስ አበባ ስታዲየም ተገኝቶ ምክርና ተሞክሮውን አካፍሏል። «ውድድር ‘እንዲህ ነው፤ እንዲያ ነው’ አይባልም ሁሉም የሰራውን ነው የሚያመጣው። ስታዲየሙ የሚያቀዘቅዝ መሳሪያ ስለተገጠመለት እዚህ ካለው አየር የተለየ አይሆንም። ከዚህ ባለፈ በአትሌቶችም ሆነ አሰልጣኞች መካከል አብሮነት አስፈላጊ ነው፤ የእናንተ አብሮ መሆን ብዙ ነገር ይቀይራል። የእናንተ በጋራ መስራት ከውጤትም በላይ ነው፤ ህዝቡም የሚፈልገው ይሄንኑ ነው። ሁሌም ሩጫ ስትሮጡ መጠንቀቅ ያለባችሁ የመጨረሻዎቹን 500 እና 600ሜትሮች ነው። ሌላውን ርቀት ሳትጨናነቁና ሳትፈሩ ዘና ብላችሁ ሸፍኑ። በመካከለኛ ርቀትም ቢሆን ሩጫውን ማንበብ የግድ ነው፤ መዘናጋት አያስፈልግም» ሲልም አስገንዝቧል። ቀጥሎም፤ «አንዳችሁ ለሌላችሁ ውጤት አስፈላጊ እንደሆናችሁ እንዳትዘነጉ። ልብ አድርጉ፤ አሰልጣኞችም ሆናችሁ አትሌቶች ‘እኔ ውጤት ላምጣ እንጂ ስለሌላው አያገባኝም’ ማለት የለባችሁም። ሌላው ማስታወስ ያለባችሁ እናንተን የሚመለከቱ ብዙ ሺ ታዳጊዎች አሉ፤ ውጤት ሁለተኛ ነገር ነው ዋናው እርስ በእርሳችሁ የምታሳዩት ስነ-ምግባር ነው። እናንተ ውጤት ስላመጣችሁ ብቻ መደሰት ሳይሆን ሌላውንም መደገፍ በተመሳሳይ አስፈላጊ ነገር ነው። አሰልጣኞች፣ የቡድን መሪዎችና ቴራፒስቶችም ከልምምዱ ባሻገር ስነ-ምግባር ላይም ማተኮር አለባችሁ»ም ብሏል። በመጨረሻም ለብሄራዊ ቡድኑ መልካም ውድድር እንዲሆን ተመኝቷል።አዲስ ዘመን  መስከረም 15/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "50f62ba170ff10bda28e8097fbd8bf73" } ]
e9c85591b5f0c51554d9fd285af332c7
553a04fff8da84e1fd944eaeedfeedc2
በቻን ውድድር ስቴዲየሞች በከፊል ለተመልካች ክፍት ይሆናሉ
ቦጋለ አበበ በአገር ውስጥ ሊጎች ብቻ የሚሳተፉ ተጫዋቾች የሚሳተፉበት የአፍሪካ ሁለተኛው ትልቁ የእግር ኳስ ውድድር(ቻን) ላይ ደጋፊዎች ስቴድየም ገብተው ጨዋታዎችን እንደሚመለከቱ ተገለፀ። ከመጪው ጥር አጋማሽ ጀምሮ በካሜሩን በሚካሄደው ውድድር የኮቪድ- 19 ወረርሽኝ ቅድመ ጥንቃቄ እርምጃዎችን ተግባራዊ በማድረግ ተመልካቾች ስቴድየም እንዲገቡ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን(ካፍ) ማሳወቁን ኢንሳይድ ዘ ጌምስ ዘግቧል። ባለፈው ሚያዝያ ወር ሊካሄድ የነበረው የቻን ውድድር በኮቪድ- 19 ስጋት ወደ ዘንድሮው ዓመት መራዘሙ ይታወሳል። የውድድሩን ዝግጅት ለመገምገም ወደ ካሜሩን አማዶ አሂጆ ስቴድየም ያቀኑት የካፍ የግምገማ ቡድን አባላት ለአገሪቱ ስፖርት ሚኒስትር ናርሲስ ሞውሌ ኮምቢ እንደገለፁት ከወር በኋላ በሚካሄደው የቻን ውድድር ወረርሽኙ የሚፈልገውን ጥንቃቄ በማድረግ ተመልካች ስቴድየም እንዲገባ ካፍ ውሳኔ ላይ ደርሷል። እንደ ስፖርት ሚኒስትሩ ገለፃ፣ በውድድሮች ወቅት ጨዋታዎችን የሚያስተናግዱ ስቴድየሞች ከመያዝ አቅማቸው ሃያ አምስት በመቶውን ብቻ ተመልካች እንዲያስተናግዱ ይደረጋል። ካሜሩን በውድድሩ ወቅት በፊፋና በጤና ባለስልጣናት የተቀመጡ መስፈርቶችን ተግባራዊ በማድረግ ተመልካች ስቴድየም እንዲገባ ባደረገችው ጥረት ከካፍ ፍቃድ ማግኘቱንም ጠቁመዋል። ውድድሩ በሚካሄድባቸው የተለያዩ ስቴድየሞች በምድብ ጨዋታዎች ወቅት ስቴድየሞች ተመልካች ከመያዝ አቅማቸው ሃያ አምስት በመቶውን ብቻ እንደሚጠቀሙ የገለፁት ሚኒስትሩ፣ ከምድብ ጨዋታዎች በኋላ በጥሎ ማለፍ ውድድሮች ስቴድየሞች ተመልካች የመያዝ አቅማቸው ወደ ሃምሳ በመቶ ከፍ ሊል እንደሚችል አስረድተዋል። በዱዋላ ከተማ የሚገኘው ስቴድየም በተጎበኘበት የካሜሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆሴፍ ኢኦን ንጉቴ ‹‹ውድድሩ ካለፈው ዓመት ተራዝሞ ዘንድሮ በሚካሄድበት ወቅት የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ጉዳይ በአፍሪካ እንደሚሻሻል እርግጠኛ ነኝ›› በማለት መናገራቸው ይታወቃል። የቅርብ ቀናት መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በካሜሩን ከሃያ ስድስት ሺ በላይ ሰዎች በኮቪድ-19 የተያዙ ሲሆን አራት መቶ ሃምሳ ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል። የካሜሩን ከተሞች መዲናዋ ያውንዴን ጨምሮ ዱአላና ሊምቤ ውድድሩን የሚያስተናግዱ ይሆናል። በዋናው የአፍሪካ ዋንጫ ጨዋታ በሌሎች አገራት ትልልቅ ሊጎች በሚጫወቱ ተጫዋቾች ተሸፍነው የመታየት እድል ያላገኙ በአገር ውስጥ ሊጎች ብቻ የሚጫወቱ ተጫዋቾች እንዲሳተፉ ለማድረግ ካፍ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ተግባራዊ ያደረገው የቻን ውድድር በኮቪድ-19 ምክንያት ካለፈው ዓመት ወደ ዘንድሮው ዓመት ከተሸጋገሩት አንዱ ነው። ካሜሩን በመጪው ሰኔ አጋማሽ ዋናውን የ2021 አፍሪካ ዋንጫ ጨዋታን የምታስተናግድ አገር መሆኗም ይታወቃል። የ2019 አፍሪካ ዋንጫን ለማዘጋጀት 2014 ላይ እድሉ የተሰጣት ምዕራብ አፍሪካዊት አገር ካሜሩን 2018 ላይ ውድድሩን ለማዘጋጀት የምትገነባቸው ስቴድየሞች በመጓተታቸውና በወቅቱ በአገሪቱ የነበረው የፖለቲካ አለመረጋጋት ከደህንነነት አኳያ ስጋት ስለፈጠረ የአዘጋጅነት እድሉ ለግብፅ ተሰጥቷል። ካሜሩንም በምትኩ የ2021 አፍሪካ ዋንጫን እንድታዘጋጅና ኮትዲቯር የ2023 አፍሪካ ዋንጫን እንድታሰናዳ ሽግሽግ መደረጉ ይታወቃል።አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 20/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=38441
[ { "passage": "ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሃገራት ቻምፒየንሺፕ (ቻን) በጥር ወር ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባለች መባሉን ፌዴሬሽኑ ቢያስተባብልም የአፍሪካ እግርኳስ ኮንፌድሬሽን ግን ጥያቄው እንደደረሰው የካፍ የሚዲያ ኦፊሰር ጁኒየር ቢንያም በተለይ  ለሶከር ኢትዮጵያ ገልፀዋል።የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌድሬሽን ፕሬዝደንት ጁነይዲ ባሻ ለሶከር ኢትዮጵያ ራዲዮ ኢትዮጵያ የቻን 2018 ውድድርን ለማስተናገድ ለካፍ ጥያቄ አለማቅረባቸውን መግለፃቸው ይታወሳል። ቢሆንም የካፍ ሚዲያ ኦፊሰር ጁኒየር ቢኒያም ለሶከር ኢትዮጵያ በሰጠው አስተያየት ከፌድሬሽኑ የአዘጋጅነት ጥያቄ መቅረቡን አስታውቋል። “ኦፊሳላዊ የሆነ ጥያቄ ከኢትዮጵያ እግርኳስ ፌድሬሽን ደርሶናል። ደብዳቤው የደረሰን አርብ መስከረም 19 ነበር።” ሲሉ ለምን ካፍ ኢትዮጵያን የአዘጋጅነት ጥያቄ ካቀረቡ ሃገራት ተርታ እንዳስቀመጠ አስረድተዋል።ፕሬዝደንት ጁነይዲ የአዘጋጅነት ጥያቄ መቅረቡን ቢያስተባብሉም ሶከር ኢትዮጵያ እንዳገኘችው መረጃ ከሆነ ከአንድ የፌድሬሽኑ አመራር የተፈረመ የአዘጋጅነት ጥያቄ ለካፍ አርብ ደርሷል። ሆኖም ልክ እንደሞሮኮ እና ኤኳቶሪያል ጊኒ ከመንግስት የተገኘውን ድጋፍ የሚገልፅ ደብዳቤ ከኢትዮጵያ በኩል አለመላኩን ለማወቅ ችለናል። ይህ ደግሞ የኢትዮጵያን የአዘጋጅነት ጥያቄ ሙሉ እንዳይሆን ያደርገዋል።በፌድሬሽኑ ውስጥ ባለው የአሰራር እና የአስተዳደር ክፍተት ምክንያት መሰል ጉዳዮች ሲከስቱ ማየት እና መስማት በኢትዮጵያ እግርኳስ ውስጥ የተለመደ ነው።", "passage_id": "33904191a4f38d72dc920d62ef94b4d9" }, { "passage": "ኢትዮጵያ የሴካፋ ሲኒየር ቻሌንጅ ዋንጫን በህዳር ወር እኝደምታዘጋጅ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌድሬሽን ፕሬዝደንት ጁነዲ ባሻ በግል የትዊተር ገፃቸው አስተውቀዋል፡፡ የሴካፋ ዋንጫን በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የክልል ከተሞች ለማዘጋጀት መታሰቡን ጁነዲ ጨምረው አስታውቀዋል፡፡ ኢትዮጵያ የሴካፋ ዋንጫን ስታዘጋጅ ይህ ለአራተኛ ግዜ ነው፡፡ ከዚህ በፊት በታህሳስ 1980፣ በህዳር 1997 እና 1999 ውድድሩን አዘጋጅታለች፡፡ የቻን 2020ን ለማዘጋጀት የእግርኳስ ፌድሬሽኑ ከጫፍ መድረሱን ጁነዲ ጨምረው ገልፀዋል፡፡", "passage_id": "2b55bd6db7250182e44dd82fff1fd544" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለወትሮው ለትልልቅ ውድድሮች ቢያንስ አንድ ወር ዝግጀት የማድረግ ልማድ ቢኖረውም በ2014 መጀመርያ በሀገር ውስጥ ሊግ ውስጥ በሚጫወቱ ተጫዋቾች ብቻ በሚዋቀር ስብስብ ለሚደረገው ውድድር (ቻን) እስካሁን ዝግጅት አልጀመረም፡፡ውድድሩ ሊጀመር የ23 ቀናት እድሜ የቀሩት ቢሆንም ኢትዮጵያ እስካሁን ተጫዋቾቿን አላሳወቀችም (በምድባችን የምትገኘው ጋና ከወዲሁ 23 ተጫዋቿን አሳውቃለች)፡፡ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው በመጪው ሳምንት ሰኞ ዝግጅት ለመጀመር ጥያቄ ቢያቀርቡም የሊጉ ውድድር እንዳይቋረጥ በሚል በፌዴሬሽኑ ውድቅ ተደርጎባቸዋል፡፡ኢትዮጵያ በቻን ምድብ ሦስት ከኮንጎ ሪፐብሊክ (ብራዛቪል)፣ ሊቢያ እና ጋና ጋር መደልደሏ ይታወሳል፡፡", "passage_id": "6c5f8b58b6a6c92160461c73c4065dbf" }, { "passage": " በሚቀጥለው ዓመት የአፍሪካ ዲዛይነሮችና ሞዴሎች ጭምር ይሳተፋሉ ባደጉ አገሮች በዓለም አቀፍ ደረጃ ‹‹የፋሽን ሳምንት›› በሚል ርዕስ የፋሽን ትርዒትን ጨምሮ ኤግዚቢሽንና ባዛር ይካሄዳል፡፡ ለአብት፣ የኒውዮርክ-አሜሪካ፣ የፓረስ-ፈረንሳይ፣ የሚላን- ኢጣሊያ፣ የቶኪዮ- ጃፓን፣…. የፋሽን ሳምንት መጥቀስ ይቻላል። እነዚህ ባዛርና ኤግዚቢሽኖች ለአገር ኢኮኖሚ ማደግና መበልፀግ የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ ነው፡፡ በፋሽን አንዲስትሪው የተሰማሩ ዲዛይነሮች፣ አርቲስቶች፣… ምርቶቻቸውን ይዘው ባዛርና ኤግዚቢሽኑ ወደሚካሄድበት አገር ይጓዛሉ፡፡ ‹‹በኤግዚቢሽኑ ላይ ምን ዓይነት አዲስ ዲዛይናና ፋሽን ቀረበ›› በማለት ለማየት፣ ለማድነቅ አዳዲስ ምርቶችን ለመግዛት የሚሄዱ ሰዎችና ቱሪስቶች፣… ብዙ ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች ሁሉ ሆቴል ይይዛሉ፣ ምግብ ይመገባሉ፣ ውሃ (መጠጥ) ይጠጣሉ፤ ከተማውን ይጎበኛሉ፤ ከባዛርና ኤግዚቢሽኑ ዕቃ ይገዛሉ፣ የልምድ ልውውጥ ያደርጋሉ፣ የገበያ ትስስር ይፈጥራሉ፣…. መስተጋብሩ ብዙ ነው፤ ተቆጥሮ አያልቅም፡፡ ሆቴል ሲያዝ፣ ምግብና መጠጥ ሲገዛ፣ ከተማው ሲጎበኝ - ለትራንስፖርት፣ ከባዛር ዕቃ ሲገዛ…. ገንዘብ ያወጣሉ፡፡ ያ ገንዘብ በኢኮኖሚው ውስጥ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው፡፡ ለዚህ ነው የፋሽን ኢንዱስትሪው እንደ አንድ የኢኮኖሚ ዘርፍ የሚቆጠረው፡፡ በዚህ ረገድ አገራችን ገና ናት- ብዙ መሥራት ይጠበቅባታል፡፡ ከሦስት ዓመት በፊት በ2006 ዓ.ም የተመሠረተውና ‹‹ዳዴ›› እያለ የሚገኘው የፋሽን ዲዛይነር ማኅበር፤ እንደ በለፀጉት አገሮች በሳምንት ሳይሆን ከግንቦት 27 እስከ 28 ለሁለት ቀን ‹‹የኢትዮጵያ የፋሽን ሳምንት›› ለማካሄድ ዝግጅቱን እያጠናቀቀ መሆኑን ማኅበሩ፣ በሳምንቱ መጀመሪያ፣ በዮዲ አቢሲኒያ ኢንተርናሽናል ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቋል፡፡ “የኢትዮጵያ ፋሽን ሳምንት” የሚካሄደው በታሪካዊው የምድር ባቡር ጣቢያ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ከ3 ዓመት በፊት በ11 ዲዛይነሮች  የተመሠረተው የፋሽን ዲዛይነር ማኅበር፤ በአሁኑ ወቅት 102 አባላት እንዳሉት የጠቀሱት የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ዲዛይነር እጅጋየሁ ኃ/ጊዮርጊስ፣ ዝግጅቱ የኢትዮጵያ ዲዛይነሮች ሳምንት ስለሆነ የማኅበሩ አባል ያልሆኑ ዲዛይነሮችም በትርዒት እንዲሳተፉ ተጋብዘዋል፡፡ በሁለቱ ቀን ቅዳሜና እሁድ የራሳቸው አዲስ የፈጠራ ውጤት የሆነ የቆዳና የሸማ፣ ዲዛይንና ፋሽን የሚያቀርቡ 30 ዲዛይነሮች ተመርጠዋል ብለዋል፡፡ ውበት በሰውነት ቅርፅ ብቻ አይለካም ብለን ስለምናምን፤ የእኛ ማኅበር አካል ጉዳተኞችን ያሳትፋል፡፡ ውበት በራስ መተማመንና ራስን ሆኖ መቅረብ ነው፡፡ አካል ጉዳተኞች ደግሞ በራሳቸው ይተማመናሉ ያሉት ፕሬዚዳንቷ፤ ከ10 ቀናት በኋላ በሚቀርበው ‹‹የኢትዮጵያ ዲዛይነሮች ሳምንት›› 8 የአካል ጉዳተኛ ሞዴሎች፣ ከጀማሪና ልምድ ካላቸው 30 ፕሮፌሽናል ሞዴሎች ጋር እኩል ትርዒት እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል፡፡ዲዛይነር እጅጋየሁ፣ ከሸማኔዎች ጋር የጠበቀ ቁርኝት እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡ “ማኅበሩ ከ3 ዓመት በፊት በ11 አባላት ሲቋቋም፣ የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ችግር ነበረበት፡፡ ሜዳ (ሜኖናይት ኢኮኖሚክ ደቬሎፕመንት አሶሴሽን- (Menonight economic Development Association) የተባለ የካናዳ ድርጅት፣ ያኔ በጨርቃጨርቅ ዙርያ ከሸማኔዎች ጋር ይሠራ ስለነበር፣ ዲዛይነሮችን፣ ከሸማኔዎች ጋር በማገናኘት የገበያ ትስስር እንድንፈጥር አድርጓል፡፡” “የፋሽን ዲዛይነሮች ለሸማ የሚሆን ጥሬ ዕቃ የምናገኘው ከሽማኔዎች ስለሆነ በጥብቅ ትስስር ነው አብረውን የምንሠራው፡፡ እንደተመሠረትን በኦሮሞ ባህል ማዕከል፣ አምና ደግሞ ከባህልና ቱሪዝም ሚ/ር ጋር በመተባበር ባቀረብነው ትርዒት፣ ሽማኔዎች እንዴት እንደሚያመርቱ፣ ምን ዓይነት ጥሬ ዕቃ እንደሚጠቀሙ፣ የምንለብሰው ሸማ የጥራት ደረጃ ምን እንደሆነ፣ እየሠሩ እንዲያሳዩ አድርገናል።” ብለዋል፡፡ ባህልና ኢንዱስትሪ ሚ/ር፣. የፋሽን ኢንዱስትሪ አድጎና ታውቆ ለአገር ኢኮኖሚ የበከሉን ድርሻ እንዲያበረክት ድጋፍ እያደረጉልን ነው፡፡ የህፃናት ጉልበት ብዝበዛን ለመከላከል ከማኅበራዊ ጉዳይ ሚ/ር ጋር እየሠራን ነው፡፡ የእኛ ዲዛይነሮች የጉልበት ብዝበዛ ውጤት እንዳይጠቀሙ እየሠራን ነው፡፡ በሁለቱ ቀን፣ ከጧት 3-12 ሰዓት ኤግዚቢሽንና ባዛር፣ ማታ ደግሞ የፋሽን ትርዒት ይቀርባል በማለት አብራርተዋል፡፡የኢትዮጵያ ፋሽን ሳምንት ዘንድሮ የሚካሄደው ለመጀመሪያ ጊዜ ቢሆንም በቀጣይ በየዓመቱ እንዲደረግ ተወስኗል ያሉት ፕሬዚዳንቷ፤ቀንና ወሩ በባዛሩ ወቅት ይገለጻል ብለዋል፡፡ በዘንድሮው ኤግዚቢሽንና ባዛር ኢትዮጵያውያን ዲዛይነሮች ቢቀርቡም ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ የአፍሪካ አህጉር ዲዛይነሮችና ሞዴሎች ጭምር እንዲሳተፉ ይደረጋል ብለዋል፤ ዲዛይነር እጅጋየሁ ኃ/ጊዮርጊስ፡፡  ", "passage_id": "fe5e002abe69b6bab883e06601d97af1" }, { "passage": " አዲስ አበባ፡- አስረኛው አዲስ ቢዩልድ ዓለም አቀፍ የኮንስትራክሽን ግብአቶችና የመሰረተ ልማት ኤግዚቢሽን ከመስከረም 28 እስከ ጥቅምት 1 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ እንደሚካሄድ ተገለጸ። በኢትኤል ማስታወቂያና ኮሚዩኒኬሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር እና በቱርክ አጋሩ (Ladin Inter­natinal Fair and Congress Organization INC) አዘጋጅነት በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽንትብብር የሚካሄደው የኮንስትራክሽን ግብዓቶችና መሰረተ ልማት ኤግዚቢሽን፤ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በሚገኙበት በደማቅ ሥነሥርዓት መስከረም 28 ቀን 2012 ዓ.ም ከቀኑ 5 ሰዓት እንደሚከፈት ከዝግጅቱ አስተባባሪዎች የተውጣጡ አመራሮች ትናንት በዌስተርን ቤስት ፕላስ ሆቴል በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ገልጸዋል። በመግለጫው እንደተመለከተው፣ በኤግዚቢሽኑ ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከቱርክ ፣ ከጀርመን ፣ ከሳውዲ አረቢያ ፣ ከህንድ ፣ ከኦማን ፣ ከታይላንድ ፣ ከኩዌት ፣ ከኢራን ፣ ከኳታር ፣ ከፓኪስታን ፣ ከዩክሬንና ቻይና በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ የግብዓት አቅርቦትና በቴክኖሎጂ ሽግግር ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሱ 97 ኩባንያዎች ይሳተፋሉ። የሲሚንቶና ኮንክሪት ምርቶች ፣ ኬብሎች ፣ የኢነርጂ ስርዓትና የቴሌኮም ሥራዎች ፣ የብረታ ብረት ፍሬሞችና ፣ የብረት ሥራ ውጤቶች ፣ ቀለም ፣ የፊኒሽንግ እቃዎች ፣ የውሃ ማስተላለፊያ ቱቦዎች፤ እንዲሁም አዲስ ቴክኖሎጂ የሆነው post-tension and\npre-stress steel technology እና ሌሎች ከ 22 በላይ የግንባታ ግብዓትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ውጤቶች ለዕይታ ይቀርባሉ። የኢትዮጵያን የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ እየፈተኑ ባሉት የጥራት መጓደል ፣ የዋጋ መናርና የማጠናቀቂያ ጊዜ መጓተት ተግዳሮቶች ላይም ውይይት ይደረጋል። በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር የኮንስትራክሽን ዘርፍ ተወዳዳሪነት ማበልጸጊያ ክፍል ኃላፊው አብዱ ጀማል የብረታ ብረት የአገር ውስጥ ምርት የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ከሚፈልገው 40 ከመቶ እንደማይበልጥ ጠቅሰው በዘርፉ የሚስተዋሉ መሰል ችግሮችን ለመቅረፍ የአገር ውስጥ አቅምን ለመጠቀም መንግሥት አልሞ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ኤግዚቢሽኑ የውጭ ኩባንያዎች ወደ አገራችን ገብተው ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂና ጥበቦች አገር ውስጥ ላሉ የዘርፉ ባለሙያዎች እንዲያስተዋውቁ ያደርጋል ያሉት አቶ አብዱ የአገር ውስጥ ድርጅቶችም በውጭ አገራት ያለውን የቴክኖሎጂ እድገት ተረድተው ራሳቸውን ለዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት እንዲያዘጋጁ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል። ለውጭና አገር ውስጥ የዘርፉ ተዋንያኖች የልምድ ልውውጥ ማድረጊያና የገበያ ትስስር መፍጠሪያ መድረክ እንደሚሆን የታመነበትን ኤግዚቢሽን 6 ሺ ጎብኚዎች ይመለከቱታል ተብሎ ይጠበቃል።አዲስ ዘመን  መስከረም 26/2012 የትናየት ፈሩ", "passage_id": "a6f16ea142a957a151a54c9b14fe677c" } ]
f8e86eaab16ed29170a5480a3e889a25
b8f3a3b3e8c4b13e79ea4fbcbe95f8f5
ከተራ – የጎንደር ልዩ ውበት
ክፍለዮሐንስ አንበርብርጎንደር አሸብርቃለች:: ተፈጥሮም ሰውም አጅቧታል:: ከተራ ለጎንደር፤ ጎንደርም ለከተራ ውበት ናቸው:: ቆነጃጅት ሽሩባቸውን በባህላዊ አሠራር አስውበው፣ በሐበሻ አለባበስ አምረውና ደምቀው ወደ ማደሪያው የሚሸኙትን ታቦታት ይከተላሉ:: ወጣት ወንዶች በሀገርኛ አለባበስ አምረውና ደምቀው፣ ሽመል ይዘው በሆታ እያደመቁ፤ በእግራቸው መሬት ረግጠው  እየነቀነቁ አቧራው ወደ ላይ ቡን! ቡን! ብሎ በሰዎች መሐል ወደ ላይ ቦለል ሲል እንደ ሰኔ ደመና እየተቆራረጥ ወደ ላይ ሲወጣ አንዳች የተለየ ውበት አለው::ጎንደር ከተማን በዙሪያ የከበበው ተራራ ታቦታቱን ያጅብ ይመስል ደረቱን ነፍቶ የቁልቁሊት እየተመለከተ የተለየ ውበት አላብሷል ለአካባቢው::የጎንደር ታቦታት በሰዎች ብቻ ሳይሆን ተራራ የሚታዘዝላቸው፤ ተራራ የሚከተላቸው ይመስላል::አንዳንዶቹ ደግሞ ፈረስ ላይ ሆነው ጎፈሬ አበጥረው እና በጃኖ ተሞሽረው እየተገማሸሩ፤ ጎንደር እሽሩሩ በሚለው ሙዚቃ ታጅበው ከፈረሶቹ ወገብ ላይ ሆነው እዩኝ እዩን በሚል ሁኔታ በታቦታቱ በቅርብ እርቀት ይጓዛሉ::የሰንበት ተማሪዎች በመለከት፣ በገና እና ከበሮ በታጀበ ህብረ ዝማሬ እያሰሙ ከታቦታቱ ኋላ ኋላ እየተከተሉ ወደ ማደሪያው ሥፍራ ሲሸኙ የጎንደር ከተራ በዓልን ውበት በእጁጉ ያጎላዋል::ካሜራቸውን ደቅነው ወዲህ ወዲያ ዝርው ዝርው የሚሉት ቱሪስቶች የታሪክ አካል ለመሆን የሚያደርጉት ሽሚያ በራሱ ዕይታን ይስባል::ቀሳውስቱ ግራ ቀኝ እያዘመሙ፣ ጽናጽል እየጸነጸሉ ታቦታቱን አጅበው ወደማደሪያው ሥፍራ ሲሸኙ ውበቱን በቃላት ለመግለፅ መሞከር አዳጋች ያደርገዋል::በአራቱም ነፋሳት የሚታጠነው ዕጣን አካባቢውን እንደ ናርዶስ ሽታ እያወደው ጥሩ መዓዛ አላብሶታል::ከተራ በጎንደር አንዳች የማይገለፅ መግነጢሳዊ ኃይል አለው::የአማራ ልዩ ኃይል በየአቅጣጫው ሆነው ከበጎ ፈቃድ ወጣቶች ጋር በመቀናጀት የአካባቢውንና የከተማዋ ሠላምና ፀጥታ ለማስከበር የሚያደርጉት መውተርተር ምንኛ የሀገር ፍቅርና የበዓል ክብር እንዳላቸው ያሳብቃል::እንደ ንሥር አሞራ ዓይናቸውን በርቀት በቅርበት እየላኩ አካባቢውን ይቃኛሉ::የከተራ ውበት በጎንደር፤ የጎንደር ከተማም ውበትም በከተራ ይገለፁ ዘንድ ተዋህደው የተሠሩ ይመስል አንዳቸው ካለአንዳኛው ምሉዕ አይመስሉም::ከተማዋ በዓል በዓል በሚሸቱ ሙዚቃ እና ዝማሬ ተንጣለች::በየህንፃዎቹ አናት ላይ የተሰቀሉት ሰንደቅ ዓላማዎች የከተማውን ድባብ በጠላት ጦር ላይ ድል በተቀዳጀ ማግስት የተገኘ ልዩ ድል አስመስለውታል::ጎንደር በሽለላ እና ቀረርቶም ለምን ይቅርብኝ ያለች ይመስላል::በርካታ ወጣቶች በአፄ ቴዎድሮስ አደባባይ እያቅራሩና እየፎከሩ በሐውልቱ ዙሪያ እየተሽከረከሩ ኢትዮጵያዊ ወኔ የሚቀሰቅሱና ለበዓሉ ድምቀት የሆኑ አያሌ ትዕይንተ ህዝብ ያሳያሉ::ሁሉንም እንቅስቃሴ በአንክሮ ለተመለከተው አንዳች ንዝረታዊ ኃይል አለው::በቃ ጎንደር ድምቅ! ብላለች::ወጣት ይድነቃቸው ታደሰ ከተራ ለእኔ ልዩ ስሜት ይሰጠኛል:: በዓሉ ነብስና ሥጋዬ ተዋህደው ደስታዬ እጥፍ ድርብ የሚሆንበት ነው::በተለይም ደግሞ በጎ አድራጎትን በመከወን ስለማሳልፍ ነብሴ በሐሴት ትረሰርሳለች ይላል::እርሱ ከከተራ እና ጥምቀት መቅረት አይሆንለትም::ጎንደር አፍ አውጥታ ትጠይቀው፤ በአሽሙር ወጋ ታደርገው ይመስል በዓሉን ሌላ ሥፍራ ማሳለፍ አይፈልግም::ወጣት ተረፈ መልካሙ ባለፈው ዓመት የምዕምናን መቀመጫ ደረጃ ተደርምሶ ጉዳት በማድረሱ በከተራውም ሆነ በጥምቀት በዓል ላይ ጥቁር ጥላ አጥልቶ ያላፈ በመሆኑ፤ መሰል ችግሮች እንዳይደገሙ ከከተማው ወጣቶች ጋር በመቀናጀት በጎ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል::በበዓሉ ወቅት ባህረ ጥምቀት ሄዶ መጠመቅና ከተራ በዓል ላይ መታደም ለእርሱ የፍሰሐ ጥግ ነው:: ከተራና ጥምቀትን በጎንደር ማሳለፍና መታደም የሁልጊዜ ዕቅዱ ነው::ከተራ ብሎም ጥምቀት በዓል የነፍስ የሥጋም በዓል እንደሆነ የሚናገሩት የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሊቀህሩያን አባ ዮሴፍ ደስታ ናቸው:: በዚህ በዓል በርካታ የአገር ውስጥና የአገር ውጭ ታዳሚዎች ወደ ጎንደር የሚመጡ ሲሆን ይህም ለጎንደርና ለአካባቢው ነዋሪዎች ፀጋ ይዞ የሚመጣ እንደሆነ ያብራራሉ::ማህበራዊ እሴቶችን በማጠናከር፣ መንፈሳዊ ሕይወትን በማደስና ነብስን በማረስረስ የሚሰጠው ስሜት ልዩ ስለመሆኑም ያስገነዝባሉ::ሊቀህሩያን አባ ዮሴፍ ደስታ እንደሚሉት፤ የጎንደር ከተራ እና ጥምቀት በዓል ሁሌም አዲስ ሰርክ ልዩ እየሆኑ ዘመናትን አስቆጥረዋል::በቀጣይም የበዓሉ ድምቀት በዚሁ ድባብ እንደሚቀጥል ተስፋ አላቸው::ለዚህም የወጣቶች፣ የምዕምናን ትግስትና ፅናት፣ የሀገር ታሪክ ወዳድነት፣ ለቤተክርስቲያንና የባህል እሴቶች ያላቸው ክብር ህያው ምስክር ስለመሆናቸውም ይገልፃሉ::በዚህ ዓመት የሚከበረው የከተራ እና ጥምቀት በዓል ከመቼውም በላይ ደስታየው የተለየ ስለመሆኑም ይናገራሉ::አገሪቱ ሠላም ሰፍኖባት የኤርትራ ወንድምና እህቶች በበዓሉ ታዳሚ የሚሆኑበት መሆኑም ታላቅ ፍስሐ እንደሆነም ይጠቁማሉ::የከተራ በዓል ሠላማዊና ፍሰሐ እንዲሆንም የመንግሥት አካላት ከአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ከሃይማኖት አባቶች፣ ከወጣቶችና ከሌሎች የሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመናበብ ስለሚሠሩ ሁሉም ነገሩ ሸጋ ነው ይላሉ:: ከተራ እና ጥምቀት በጎንደር ልዩ ስሜትና እንደሚሰጥ በመጠቆም፤ የተቻላቸው ኢትዮጵውያን እንዲታደሙት ይመክራሉ::አዲስ ዘመን ጥር 11 ቀን 2013 ዓ.ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=39749
[ { "passage": "ሰቆጣ ስያሜዋን አገኘች ተብለው ከሚነገሩ መላምቶች አንዱ ‹‹ሳ ቊጠ›› የሚለው ይገኝበታል፡፡ ፋጥዝጊ ከሚባል ከፍታ ቦታ ሆኖ ቁልቁል ስትታይ ‹ከታች ያለች እርጥበታማ ቦታ› የሚል ትርጎሜን ያስገኛል፡፡ ይህ ደግሞ ሰቆጣን ለሁለት ከሚከፍላት ወንዝ የሚመነጭ ነው፡፡ በአጼ ካሌብ ዘመነ መንግሥት በአምስተኛው ክፍለ ዘመን ለተመሠረተችው ከተማ ይህ ወንዝ ለከተማዋ መመሥረት የራሱ ሚና አለው፡፡ ወንዙ ከ16ኛው ክፍለ ዘመን በኋላ እስከ ባለፉት ጊዜያት የከተሜነት መስፋፋት ማዶ ለማዶ የተመሠረቱ መንደሮች ቆሻሻ መድፍያ ሁኖ አገልግሏል፡፡ ለንፁህ መጠጥ ውኃ መገልገያ እና ለንፅህና መጠበቂያ ሲያገለግል የነበረው ወንዙ የቆሻሻ መጣያ፣ ሽሽግ የመጸዳጃ ቦታ መሆን ሲጀምር ለጤና ጠንቅ የሆነ ሽታ የሚፈጠር አስቸጋሪ ቦታ መሆን ጀመረ፡፡ ለከተማዋ ውበትም እንቅፋት ሆነ፡፡  ለ20 ዓመታት በመንግሥት ሥራ አዲስ አበባ፣ ባሕር ዳር እና ሰቆጣ ሲሠሩ የነበሩት አቶ አዲሴ ሁሴን ስፍራውን ሲመለከቱ እንደመንገደኞች ሁሉ ዝም ብለው ማለፍ አልወደዱም፡፡በጎርፍ የተቦረቦረውን የከተማዋን አማካይ ወንዝ ድንጋዩን ከአፈሩ ጋር እያዋደዱ ለአምስት ዓመታት እርከን መሥራት ቀጠሉ፡፡ በክረምት ወቅት ችግኝ እየተከሉ እርከኑን አስተማማኝ አደረጉት፡፡ ዛፎቻቸውን አንድ ጊዜ ከቤታቸው ሌላ ጊዜ ከወንዙ እየቀዱ ውኃ ማጠጣት የሁልጊዜ የቤት ሥራቸው ሆነ፡፡ወንዙን በግንብ አጥረው ችግችን፤ አበቦችንና አትክልትና ፍራፍሬ መደቦችን አዘጋጅተው ማልማታቸውን ቀጠሉ፡፡ የመንግሥት ሥራቸውንም ከወንዙ ባዩት ተስፋ ምክንያት አቋረጡት፡፡ አፍንጫቸውን ይዘው ይሻገሩ የነበሩ ነዋሪዎች ከጥቂት አፈርና ድንጋይን የማከም የቤት ሥራ በኋላ ንፁህ አየር ከመልካም መዓዛ ጋር መተንፈሱ አስደስቷቸዋል፡፡ ‹‹ጋሽ አዲሴ በርታ›› እያሉ የሚሄዱት ሰዎች ዓላማቸውን ለማሳካት ኃይል እንደሆኗቸው ያስታውሳሉ፡፡ይህን ጅምር ሁነት የከተማ አስተዳድሩ ፈቅዶ ወደ መናፈሻነት ሲቀየር በከተማዋ አዲስ የመናፈሻ ዘውግን ተቆናጥጧል፡፡ ንፁሁን አየር ያለበት ነፋሻ ቦታው ለተማሪዎች ለንባብና መዝናናት ለሚፈለጉ ደግሞ በከተማዋ ባልተለመደው መልኩ አረንጓዴ መናፈሻ የመጀመሪያ ምርጫቸው ሆኗል፡፡ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የቀለበት፣ የሠርግ፣ የልደት እና ልዩ ልዩ ዝግጅቶች ማድመቂያ ሁኗል፡፡ ይህ የአቶ አዲሴ ተግባር ለከተማዋ አረንጓዴ ልማት መነቃቃት አብነት ሁኗል፡፡ አቶ አዲሴን ተከትሎ በሰቆጣ ከተማ ወንዝ ላይ የሚሠሩ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች በተለያዩ ሰዎች በመዘውተሩ የከተማዋን አየር ንብረት እንዲቀየር ዕድል ፈጥሯል፡፡አቶ አዲሴ አካባቢውን ያለመሰልቸት ሌሊት እና ቀን አስውበው እና አሳምረው፤ የተጎዳን መሬትም እንዴት ማልማት እንደሚቻል ሠርተው በማሳየታቸው ‹ታታሪ ጀግና› በመባል የተለያዩ ሽልማቶች ተበርክተውላቸዋል፡፡ ለራሳቸው ትልቅ የገቢ ምንጭ፤ ከ35 ሺህ ሕዝብ በላይ ለሚኖሩባት ሰቆጣ ከተማ ደግሞ ከከንፈር መምጠጫነትና ከአፍንጫ ማፈን ወጥቶ ንፁህ አየር መቀበያ፣ ለአዕምሮ መቀየሪያ ምቹ ቦታ ሁኗል፡፡ትዝብታቸውን ያጋሩን ግለሰቡ ‹‹በአጼ ካሌብ ዘመነ መንግሥት በ410 እንደተቆረቆረች የሚነገርላት የሰቆጣ ከተማ ከአክሱም ጋር የተያያዘ ታሪክም እንዳላት ይነሳል፡፡ በአጼ ካሌብ ዘመነ መንግሥት (ከ495-525 ዓ.ም) ከአንድ አለት ተፈልፍሎ እንደተሠራ የሚነገርለት ከላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ከ500 ዓመታት በላይ የሚቀድመው ውቅር መስቀለ ክርስቶስ ቤተ-ክርስቲያን መገኛም ናት ሰቆጣ፡፡ ለዚህች ታሪካዊት ከተማ አንድ ውለታ ማድረግ እንዳለባቸው በማመን ነበር ወደ ወንዝ ልማት የገቡት፡፡‹‹የሰቆጣን ከተማ ከበረሃማ አካባቢዎች ጋር አስተሳስሮ ለመናገር አይቻልም፤ የከርሰ ምድር ውኃው ብዙ እንድትለማ የሚያደርግ ነው›› ያሉት አቶ አዲሴ በእንደዚህ ዓይነት አካባቢዎች የአረንጓዴ ልማት መዝናኛዎች ለቱሪስቶች እና ለነዋሪዎች የደስታ ምንጭ እንዲሆኑ በማለም እየተጉ ነው፡፡ሰፊውን ሸለቆ በዛፍ እና በአትክልቶች ውበት አድምቆ፣ የተቃጠለውን አየር አቀዝቅዞ ለአካቢው የደስታ በረከትን የረጨው የአቶ አዲሴ መናፈሻ ሥራ ከመጀመሩ በፊት የነበሩትን ሁለት አስተያየቶች ዛሬም ያስታውሱታል፡፡ልፋቱን ዓይተው በውስጣቸው ‹‹እንዲያው ምን ሊያገኝ ይሆን በቆሻሻ ቦታ ሲደክም የሚኖረው? አንዳች ነገርም ሳይመታው አይቀርም›› እያሉ በአንደበታቸው ደግሞ ‹‹በርታ!›› እያሉ የሚያጀግኑ ሰዎችን የሥራቸውን ውጤት በማሳየት ሐሳባቸውን እንዲቀይሩ አድርገዋል፤ በምፀት ሲሳለቁባቸው ለነበሩ ሁሉም ነገር እንደሚቻል በማሳየታቸው ደስታ እንደተሰማቸውም ተናግረዋል፡፡ስለአቶ አዲሴ የሚያውቁት የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው አቶ ፍስሐ ሀብቱ ‹‹መቀመጥ መቆመጥ›› ነው የሚል  አመለካከት ያላቸውን የግለሰቡን አይደክሜነት እያስታወሱ ‹‹ይህ ቦታ እንዲህ አምሮ እና ደምቆ  ከመታየቱ በፊት በአካባቢው ለማለፍ አፍንጫን አፍኖ በፈጥነት ነበር፡፡ በዓይን ለማየት ዘግናኝ ነው የነበረው፤ይህ አካባቢ አዝኖ የደረሰለት የቁርጥ ቀን ልጅ  ስላገኘ ታክሞ ዳነ እንጂ ወላጆች ለልጆቻቸው ወደ አካባቢው እንዳይሄዱ ከሚመክሩባቸው ለደኅንነት እና ለጤንነት አስጊ እና አስታዋሽ ካጡ  ቦታዎች ውስጥ ነበር›› ብለዋል፡፡ አቶ ፍስሀ ‹‹እርሱ ግማሽ ዕድሜውን ከዚህ ቦታ ነው ያሳለፈው፡፡ በዚህ ሰዓት በዚህ የመዝናኛ ሎጂ ተገናኝተን ስናወራ ከዚህ በፊት በፌዝ ሳልፍ እንደነበር ስነግራቸው የብዙ ሰዎች ሐሳብ እንደሆነ ያጫውቱኛል›› ብለዋል፡፡", "passage_id": "2344cbd4cc4957910f0eea1f7a59c10a" }, { "passage": "ጎንደር የጥምቀት በዓልን ለማክበር እንዴት እየተዘጋጀች ነው?\\nለበዓሉ ዝግጅት የሚጀመረውም ቀደም ተብሎ ነው። በዘንድሮው ደግሞ ከሃይማኖታዊ ክብረ በዓል በተጨማሪ ሌሎች ባህልንና ታሪክን የሚያስተዋውቁ ትዕይንቶችም እንደተዘጋጁ ተነግሯል። \n\nበዓሉን በተለያየ ቦታ የማክበር አጋጣሚ የነበረው ኤርሚያስ ዘመነ፤ በጎንደር ሲያከብር ግን የተለየ ስሜት እንደሚሰማው ይናገራል። \"በሌሎች ከተሞች ከሚከበረውም ለየት ይላል\" ይላል።\n\n\"ታቦታቱ በጠቅላላ በአንድ ሥፍራ ማረፋቸው፣ በፋሲለደስ መዋኛ ገንዳ መከበሩ፤ ምዕመናኑም እየዋኙ የሚጠመቁበት፤ ከገንዳው ዳር ላይ የቆሙ ቀሳውስት ካባ ለብሰው ፀበሉን የመባረክ ሥነ ሥርዓቱ፣ ዝማሬው፣ አልባሳትና ትዕይንት መቼም ከአዕምሮዬ አይጠፋም\" ሲል ስለ በዓሉ ድምቀት ይናገራል።\n\nየዘንድሮውን የጥምቀት በዓል ለማክበርም ጎንደር የገባው ቀደም ብሎ ነው፤ ለበዓሉም ጃኖ አሰፍቶ ተሰናድቷል።\n\nከተማው እየተፀዳ፤ እየተጌጠ ነው። ከጎንደር ዙሪያ ካሉ አካባቢዎች የመጡ የባህል ቡድኖች ከተማው ገብተዋል። \n\nኤርሚያስ እንደነገረን ጎንደር ጥር 6 ቀን የአፄ ቴዎድሮስን ልደት ካከበሩ በኋላ የጥምቀት ዋዜማ ሆኖ መከበር ይጀመራል። እለቱም በተለያዩ ትዕይንቶች ተከብሮ ይውላል። \n\n\"ከተማዋ ሞቅ ደመቅ እንዳለች ነው፤ በርካታ ጎብኝዎችም ወደ ከተማዋ እየገቡ ነው፤ ካፍቴሪያም ሆነ ሆቴሎች ላይ ጎብኝዎች በርከት ብለው ይታያሉ\" የሚለው ኤርሚያስ፤ የባህል ልብሶች መሸጫ አካባቢዎችም በጣም የተጨናነቁ ናቸው ብሎናል።\n\nየጎንደር ከተማ ባህል ቱሪዝም የባህል ኢንዱስትሪ ልማት ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ልዕልና ገ/መስቀል በፊታችን በሚከበረው የጥምቀት በዓል ወቅት ታሪክንና ባህልን የሚያጎሉ ተግባራትን በማከናወን ለጎብኝዎች ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።\n\nየጥምቀት በዓል አከባበር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየደመቀ መምጣቱን የሚናገሩት አቶ ልዕልና፤ በዚህ ወቅት ወደ ከተማዋ የሚገቡ ጎብኝዎች ቁጥርም እየጨመረ እንደሆነ አስረድተዋል።\n\nወደ 30 ሺህ የሚጠጉ የውጭ ጎብኝዎችም ጎንደር ይገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ነግረውናል።\n\n'የነገሥታቱን ታሪክ የሚያሳይ ወካይ ትዕይንት'\n\nአቶ ልዕልና እንደገለፁልን ቢያንስ በሳምንት ሁለት ቀን፤ ሐሙስና ቅዳሜ የነገሥታት እራት ይዘጋጃል።\n\nበበዓሉ ወቅት ለእራቱ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይጋበዛሉ። ይህ ዝግጅት ቀጣይነት ያለው ሲሆን፤ ጎብኝዎች ታሪካዊ የሆነውን ቤተ መንግሥት ከጎበኙ በኋላ እራቱን በክፍያ እንዲመገቡ ይሆናል።\n\nባህልና ቱሪዝም ከሌሎች ጋር በመተባባር ምግብና መጠጡን ያቀርባሉ። ይህም ለቱሪዝሙ ተጨማሪ ገቢ እንደሚያስገኝ አስረድተዋል። \n\nከዚህ በተጨማሪም ነገሥታቶቹ ምን ያከናውኑ ነበር?፣ እንዴት አገር ይመሩ ነበር?፣ ምን ዓይነት ባህል ነበራቸው? የሚለው የነገሥታቱ ወካይ ትዕይንት ይቀርባል። በዚህም ጎብኝዎች ስለጎንደር ታሪክና ባህል በቀላሉ እንዲረዱ የሚያስችላቸውን አጋጣሚ ይፈጥርላቸዋል ብለዋል- አቶ ልዕልና።\n\n• በታሪካዊው ቤተ መንግሥት ውስጥ ምን አለ?\n\nበጎንደር አካባቢ ተፈጥረው የነበሩት የፀጥታ ችግሮች በቱሪዝሙ ላይ ያሳደሩት አሉታዊ ተጽዕኖ እንዳለ የጠየቅናቸው አቶ ልዕልና፤ እዚህ ግባ የሚባል ተፅእኖ አለማድረሱን ገልፀውልናል።\n\nበዘንድሮው ዓመት በአጠቃላይ 2 ሚሊየን ሕዝብ በዓሉን ያከብራሉ ተብሎም ይጠበቃል ይላሉ።\n\nበተለያዩ የአገሪቷ ክፍል ያሉ ከተሞች ተወካዮች እንዲገኙም እየተደረገ ነው የሚሉት አቶ ልዕልና፤ ከጋሞ ተነስተው በሚመጡ አባቶችና ታዋቂ ግለሰቦች በበዓሉ እንዲታደሙና በጋራ ኢትዮጵያዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ቃል የሚገቡበት በዓል እንዲሆን ግብዣ መደረጉን አክለዋል።\n\nያነጋገርናቸው የጎንደር ከተማ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር እንየው፤ በዓሉን በሰላም ለማክበር እቅድ ተዘጋጅቶ...", "passage_id": "11252c5c1753d8dd7f10544da8bf2765" }, { "passage": "የአማራ ክልል “የባህል ስፖርት አባት” እየተባለ ይጠራል። በተደጋጋሚ በሚደረጉ ሀገር አቀፍ የባሕል ስፖርት ውድድሮች በቀዳሚነት ሲያጠናቅቅም ይስተዋላል። ለአብነት ያህልም በ2011ዓ.ም ኦሮሚያ ክልል አምቦ፣ በትግራይ ክልል-መቀሌ እና በሶማሌ ክልል- ጅግጅጋ በተደረጉ ሀገር አቀፍ የባህል ስፖርት ውድሮች በሦስቱም የቀዳሚነቱን ደረጃ ይዞ ነበር ያጠናቀቀው። ቀዳሚ ሆኖ ማጠናቀቁ ብቻ ሳይሆን ከተከታዮቹ ክልሎች እና ከተማ አስተዳድሮች ያለው የነጥብ ልዩነትም ሰፊ ነበር። ክልሉ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተሻለ የባሕል ስፖርት እንቅስቀሴ ቢኖረውም ባለው ሀብትና አቅም ልክ ግን ባሕሉን ማሳደግ አልቻለም።", "passage_id": "3b2cf87e450425d68f889c035959afa1" }, { "passage": "ባሕር ዳር፡- ጥር 14/2012ዓ.ም (አብመድ) 7ኛው የመላው ሰሜን ጎንደር ወረዳ አቀፍ የባህልና ዘመናዊ ስፖርቶች ውድድር በደባርቅ ወረዳ አሸናፊነት ተጠናቅቋል ።", "passage_id": "afa48e785a8208eb295945ce34751507" }, { "passage": "ባሕር ዳር፡ መስከረም 09/2013ዓ.ም (አብመድ)  ዘመነ ኢሕአዴግ ‘ከተደገፈው የተነቀፈው፣ ከሠራው ያፈረሰው፣ ከሰበሰበው የበተነው፣ ካቀራረበው ያራራቀው፣ ካፋቀረው ያጣላው ይበዛል’’ ይሉታል፡፡ ‘‘ኢትዮጵያዊነት እንዲሸረሸር፣ ዘረኝነት እንዲስፋፋ፣ አንድነት እንዲቀበርም ሠርቷል’’ ተብሎም ይወቀሳል፡፡ በዘመነ ኢሕአዴግ ኢትዮጵያውያን ከአንድነታቸው ይልቅ ልዩነተቻው ከፍ ብሎ እንዲታያቸው እና ‹‹እኛ›› ከማለት ይልቅ ‹‹እኔ›› ማለት እንዲቀድምባቸው እንደተደረገ ይህም በኪነ ጥበቡ ውስጥም እንደገባ ሐያሲዎች ይናገራሉ፡፡ወታደራዊው መንግሥት ኃይልን በዋና መሣያነት ቢጠቀምም በኢትዮጵያዊነት ግን ለድርድር ተቀምጦ እንደማያውቅ ይገለጻል፡፡ ለኢትዮጵያ እንድነትና ለመንግሥቱ አብዮት ደግሞ ኪነ ጥበብን በሚገባ ይጠቀምበት ነበር፡፡ ለዚህም ይሆነው ዘንድ በየክፍለ አገራቱ ጠንካራ የሆኑ የኪነ ጥበብ ቡድኖች እንዲመሠረቱ አድርጎ ነበር፡፡ በዚያነው ‘‘የሕዝብ ለሕዝብ’’ አገራዊ ሥራው ዓለምን እየዞረ የኢትዮጵያን ብዝኃነትና አንድነት ያስተዋወቀ የሥርዐቱ ወቅት የኪነ ጥበብ ጉልላት እንደነበር ብዙዎች ይስማማሉ፡፡በደርግ ዘመነ መንግሥት ጊዜ በአማራ ክልል ሦስት ታላላቅ የኪነ ጥበብ ቡድኖች ተቋቁመው አጀብ ያስባሉ የጥበብ ሰዎች ተፈጥረዋል፡፡ ወሎ ላልይበላ፣ ግሽ ዓባይና ፋሲለደስ የባህል ቡድኖች ስማቸው ከፍ ብሎ ከሚነሱት የባህል ቡድኖች ነበሩ፡፡ ዛሬ የፋሲለደስ የባሕል ቡድንን ጉዞ ለመቃኜት ወደድን፡፡የቀድሞው ፋሲለደስ ባህል ኪነት የአሁኑ ፋሲለደስ ባህል ቡድን በኢትዮጵያ የኪነ ጥበብ ታሪክ ዝናቸው ከፍ ካሉ የኪነ ጥበብ ቡድኖች መካከል ከግንባር ቀደሞቹ ይገኝበታል፡፡በዚህ የኪነ ጥበብ ቡድን አስደናቂ የጥበብ ሰዎች ተገኝተውበታልና፡፡ በዘመነ ደርግ የአገሪቱ የባህል ሚኒስቴር የኪነ ጥበብ ዘርፉ እንዲያድግ ፍላጎት ነበረው፡፡ ይህን ጥበብ ከፍ ለማድረግም ከወትሮውም በቡድን ሳይደራጅ በተሰጥዖ ጥበብ በሚንቆረቆርበት የጎንደር ክፍለ አገር የበለጠ ለማዳበር የኪነ ጥበብ ቡድን ለመመሥረት ታሰበ፡፡ኪነ ጥበብ በጎንደር ዘመን ጀምሮ ከፍተኛ ትኩረት ይሰጠው እንደነበር ይነገራል፡፡ ከጎንደር ነገሥታት መካከል ዮሐንስ ሦስተኛ የጥበብ ፍቅር ስለነበራቸው ‘‘የጥበብ ሰዎችን ወደቤተ መንግሥት እያሰባሰቡ በጥበብ ይመሰጡ ነበር’’ ይባላል፡፡ ይህ ጥበብ ሲወርድ ሲወራረድ ቀጥሏል፡፡ በዘመነ ኃይለሥላሴም የፖሊስ ኪነት በመባል በጎንደር ከፍ ያለ የኪነ ጥብብ ድግስ ይደገስ እንደነበር ይነገራል፡፡ የዙፋን ዘመን አልቆ የደርግ ዘመን ተተካ፡፡ የወቅቱ የባህል ሚኒስቴር ታወቂውን አውላቸው ደጀኔን በመላክ ጎንደር ላይ አንድ የጥበብ ቡድን እንዲመሠረት ወሰነ፡፡አውላቸው ደጀኔ ከታዋቂው የባህል ሙዚቀኛ ጋሽ ይርጋ ዱባለ ጋር በመሆን በመጠጥ፣ በሠርግ፣ በዓመት በዓልና በተለያዩ አጋጣሚዎች እየተገኙ ከያኒያንን ማሰባሰብ ጀመሩ፡፡ ዘጠና የሚሆኑ አዝማሪዎችንም ሰብስበው በበጎ ፈቃደኛነት በማኅበር አደራጇቸው፡፡ ከእነዚህ መካከል ከማሲንቆ ተጫዋችነት ባለፈ በድምጽ የሚያንጎራጉሩና ውዝወዜ የሚችሉ 33 ሰዎች ተመርጠው በአውላቸው አማካኝነት ስልጠና ይሰጣቸው ጀመር፡፡ በአጭር ጊዜም ‘‘ታግሎ አታጋይ’’ በሚል ስያሜ በ1969 ዓ.ም የኪነት ቡድን ተመሠረተ፡፡ ከያንያኑም በጥቂት ጊዜያት ከበርካታ ሰዎች ጋር የመላመድና ሙያውን የማጎልበት ዕድል ገጠማቸው፡፡ የመወዝ ጉዳይ ግን ለኪነት ቡድኑ ፈታኝ ነበር፡፡ይህ የኪነት ቡድን አንድነትን ከሚያጠናክሩና ኢትዮጵያዊነትን ከሚሰብኩ የሙዚቃ ሥራዎች በተጨማሪ የቲያትር ሥራዎች በመሥራት በአጭር ጊዜ ውስጥ አንቱታን አተረፈ፡፡ የኪነት ቡድኑ በተመሠረተ በሁለት ዓመቱ ጅግጅጋ ላይ በተዘጋጄው የእናት አገር ጥሪ በዓል ላይ ተሳታፊ ነበር፡፡ በዚህ በዓልም አንደኛ በመሆን ተሸላሚ መሆን ቻለ፡፡ዕድገቱ ከፍ እያለ ሄደ፡፡ ከጥቂት ዓመታት በኃላ ስሙን ‘የራስ ደጀን ኪነት’ ወደሚል ቀዬረ፡፡ የኪነት ቡድኑ በርካታ መልካም የሚባሉ ሥራዎችን ቢሠራም የአባላቱ ዘመናዊ ትምህርት አለመማር ኪነቱን ይፈትነው ነበር፡፡ የኪነት ቡድኑ ዘመናዊ ትምህርት እንዲቀስሙ የባህል ሚኒስቴር ጋሽ ቀለመወርቅ ደበበን ወደጎንደር ላከ፡፡ ጋሽ ቀለመወርቅ ደበበ በተለያዩ አውራጃዎች ተዝዋውረው 32 ሰዎቸን መረጡ፡፡ የተመረጡትን የጥበብ ሰዎች ለዘጠኝ ወራት ተውኔት፣ ሙዚቃና ሌሎች ስልጠናዎችን ሰጥተው ሕዳር 2 ቀን 1976ዓ.ም አስመረቁ፡፡ በዚህ ጊዜ የኪነት ቡድኑ ስሙ የበለጠ የታወቀበትን ‘ፋሲለደስ ኪነት’ የሚል ስያሜ ያዘ፡፡የኪነት ቡድኑ በጋሽ ቀለመወርቅ ደበበ የተደረሰ ‘መረዋ’ የተሰኜ ተውኔት አዘጋጅቶ አሰብን ጨምሮ በያኔው የኢትዮጵያ ክፍለ ሀገራት በመዘዋወር በማቅረብ ስሙን ከፍ አድርጓል፡፡ የኪነት ቡድኑ የመጀመሪያ የተውኔት ሥራው ‘ጎራው ብቅ በል’ የሚል እንደነበር ታሪኩ ያሳያል፡፡ ከዚህ ተውኔት በመቀጠል ‘ቢሮ›› የተሰኜው ተውኔት ከጎንደር ውጪ ለአራት ወራት በአስራ አንድ ክፍለ ሀገራት ተዘዋውሮ በማሳዬትም በሕዝብ ዘንድ ተወዳጅነትን አትርፎ ነበር፡፡በዚህ የኪነት ቡድን ጋሽ ይርጋ ዱባለ፣ ታማኝ በዬነ፣ አሰፉ ደባልቄ፣ እንዬ ታከለ፣ አበበ ብርሃኔ፣ አበበ በለው፣ ሡራፌል ተካ፣ ሳሊህ አብደላ እና ሌሎችም እንቁ ሰዎች ወጥተውበታል፡፡ ይህ የኪነት ቡድን ዕድሜው የሰነበተው ግን ኢሕአዴግ ሥልጣነ መንበሩን እስኪረከብ ድረስ ነበር፡፡ ኢሕአዴግ ስልጣኑን እንደያዘ አብዮተኛን ሲኮንን ‘‘ጥበበኞችም የአብዮቱ ፍሬዎች ናቸው’’ በሚል ቡድኑን አፈረሰ፣ የኪነ ጥበብ ሰዎችም በነጻነት እንዳይንቀሳቀሱ ተደረገ፡፡ ልብ ይበሉ ፍቅርና ኢትዮጵያዊነትም መጎዳት የጀመረው እዚህ ላይ መሆኑ ይነገራል፡፡ በነገራችን ላይ ሙዚቀኞች አልበም ሲያወጡ ስለእናት ሀገር አንድ ሙዚቃ ማካተት በደርግ ዘመነ መንግሥት የኪነ ጥበብ ሰዎች ግዴታ እንደነበር ይነገራል፤ ብዙዎቹ በዚህ ዘመን የሚደመጡ ሀገራዊ ስሜት ያላቸው ሙዚቃዎች ውልደትም ያኔ ነው፡፡የክራርና የድምጽ ተጫዋቹ፣ የዜማና የግጥም ደራሲውና የቀድሞው የጎንደር ባህል ማዕከል ሥራ አስኪያጅ ጋሽ ስለሺ መስፍን ከአብመድ ጋር በነበራቸው ቆይታ ‘‘የኪነት ቡድኑ ምንም እንኳን አብዮቱ እንዲቀጣጠል ታስቦ የተቋቋመ ቢሆንም የአገር ፍቅር እንዲጎለብት ከፍተኛ ድርሻ ነበረው’’ ብለዋል፡፡ ‘‘ፋሲለደስ በመፍረሱ የአገር ፈቅር ስሜትና የጥበብ ሥነ ምግባርቀንሷል’’ ነው ያሉት፡፡ በዚህ ዘመን የፈረሰው ፋሲለደስ ብቻ ሳይሆን ሌሎችም ስለነበሩ ነው የአገር ፍቅር ስሜቱና ጥበቡ እንዲንሸራተት የሆነው፡፡ ‘‘ደርግለጥበብ ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ ነበር’’ ያሉት ጋሽ ስለሺ በዚህ ዘመን ግን ኪነ ጥበብ መቀዛቀዙን እንደታዘቡ ነግረውናል፡፡ ‘‘የኪነት ቡድኖችን ማፍረስ ሳያንሳቸው ማሲንቆ የያዘ ሁሉ እንዲያፍርና ከጥበብ እንዲርቅ ይደረግ ነበር’’ ነው ያሉኝ፡፡ እንዲህ መሆኑ አሁን ላይ ዘመን ተሸጋሪ የኪነ ጥበብ ሥራዎች እንዳይሠሩና አቅም የነበራቸው ሰዎች ተሸማቅቀው እንዲቀሩ እንዳደረገ ተናግረዋል፡፡የባህል ተጫዋቾች በመቀነሳቸውና በመሸማቀቃቸው ባህል እንዲበረዝ ምክንያት መሆኑንም ያስረዳሉ፡፡ ‘በዚያ ዘመን የተሠሩ የጥበብ ታሪኮች እንዲጠፉ ተደርገዋል’’ ነው ያሉት ጋሽ ስለሺ፡፡ ደርግ ሥርዓቱ አስፈሪ ቢሆንም ስለአገር ፍቅር ይሠራ እንደነበርም ተናግረዋል፡፡ በእርግጥ ደርግ ጥበቡ ከአገር ፍቅሩ ጎን ለጎን አብዮቱን ለማቀጣጠል ስለተጠቀመበት ያስተቸዋል፡፡ በየክፍለ አገራቱ የሚገኙ የኪነት ቡድኖች እርስ በርስ እየተገናኙ የባህል ትውቅቅ ያደርጉ እንደነበር ያስታወሱት ጋሽ ስለሺ በዚያ ዘመን የነበሩ ባህላዊ ጭውውቶች አሁን ላይ እንደጠፉም ተናግረዋል፡፡ከዓመታት ቆይታ በኋላ በጎንደር ግንቦት 19/2008 ዓ.ም ‘‘ፋሲለደስ የባሕል ቡድን’’ ተብሎ እንደገና ተቋቁሟል፡፡ ለዚህም የሙዚቃ ባለሙያው ሡልጣን ኑሪ ታላቅ ድርሻ ነበረው፡፡ ይህ ቡድን በአጭር ጊዜ ውስጥ ብዙ መልካም የሚባሉ ሥራዎች ቢሠራም ያልተበረዘውን ባህል በመሥራት ረገድ ግን ክፍተት እንዳለበት ነው ጋሽ ስለሺ የነገሩኝ፡፡ ያልተበረዘውን ባህል ለማቅረብም የባህል ቡድኑ ገጠር ሄደው ባህሉን እንዲያዩ እንደተደረገ ሥ ነቃል፣ ዜማና ውዝዋዜ እንዲያዩና እንዲያመጡ እየተደረገ መሆኑንም ሰምቻለሁ፡፡ ቀደም ባለው ጊዜ የኪነ ጥበብ ሰው እንደጦር ሠራዊት ጥንቃቄ ያደርግ እንደነበር ያስታወሱት ጋሽ ስለሺ ለዓመታት ትኩረት ስለተነፈገው የኪነ ጥበብ ሥነ ምግባሩ እንደቀነሰ ነው የተናገሩት፡፡ የጥበብ ሰው ለጥበብና ለማኅበራዊ ግዴታ መሥዕዋት መሆን እንዳለበትም ይመክራሉ፡፡ የደከመውን የጥበብ አብዮት ለመመለለስ በትኩረት መሥራት እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ ‘‘በጥበብ ያደገ ሰው አገራዊ ፍቅሩ ከፍ ያለ ነው፤ ጥበብንና አገሩን የማድመቅ ዕድሉም ከፍ ያለ ነው’’ ብለዋል፡፡ መንግሥትም ለሥራው ምቹ ሁኔታ መፍጠር እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡ ባህሉን ያልጠበቀ ሙዚቃና ማናቸውም የኪነ ጥበብ ሥራ መገሰጽ እንዳለበትም መክረዋል፡፡የአሁኑ የፋሲለደስ የባህል ቡድን ዋሽንት ተጫዋች፣ የዜማና የግጥም ደራሲና ድምጻዊ አስፋው መለሰ ‘‘ከድሮው የተሻለ ነገር አሁን ላይ አለ፤ ከድሮው ያልተሸለ ነገርም አሁን ላይ አለ፤ አሁን ላይ መሣሪያው ያደገ ነው፤ ይህ የተሻለው ነው፡፡ የድሮው ትክክለኛ ባህሉን ይሠራ ነበር፤ አሁን ላይ እንዲቀዬጥ ሆኗል፤ ይህ ደግሞ ያልተሻለው ምሳሌ ነው’’ ብሏል፡፡ በመካከል ላይ ተቋርጦ መቆዬቱ የባህል ጨዋታዎች እንደነውር እንዲቆጠሩ ማድረጉንም አንስቷል፡፡ ተተኪው ትውልድ ባህሉን እንዳያውቅ መደረጉንም እንዲሁ፡፡ ‘‘ኪነጥበብ አገር አፈራሽም አገር ሠሪም ነው’’ ያለው አስፋው ከሌሎች ጋር ሳይሆን ራሱን የቻለ ተቋም ሆኖ የኪነ ጥበብ ሰው እንዲመራው መደረግ እንደሚገባውም አሳስቧል፡፡", "passage_id": "8570e489e8e9e47657594c9a881494e4" } ]
52ca0e09b18a40176a11892e27e0734d
b53972c39b090222a1e3a9ce90d1b72e
” የሱዳን ሃይል በተጠናከረ ሁኔታ ወደ ውስጥ እየተስፋፋ መሄዱ የግድቡን ግንባታ ለማስተጓጎል ነው‘ – ብርጋዴል ጀነራል ዋሲሁን ንጋቱ
ዘላለም ግዛው  አዲስ አበባ:- የሱዳን ሃይል በተጠናከረ ሁኔታ ወደ ውስጥ እየተስፋፋ መሄዱ የግድቡን ግንባታ ለማስተጓጎል የተደረገ መሆኑን ብርጋዴል ጀነራል ዋሲሁን ንጋቱ አስታወቁ። ትዕግስቱ ከበቂ በላይ በመሆኑ የሃይል አጸፋ እንደሚያስፈልግ አመለከቱ። የቀድሞ መከላከያ ሰራዊት ባልደረባ ብርጋዴል ጀነራል ዋሲሁን በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት ፤ የሱዳን አሁናዊ የመሬት ወረራ ዋናው ግብ በማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ የሚገኘውን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ለማስቆም፣ ወደ ሃይል ማመንጨት ሂደቱ ከመሸጋገሩ አስቀድሞ ለማስተጓጎል የተወጠነ ሴራ መሆኑን ነው። ኢትዮጵያ የግድቡን ግንባታ ለማጠናቀቅ ተርባይኖቹንም   ተክሎ ሃይል እንዲያመነጩ ስራ ለማስጀመር እያደረገች ያለው ሂደት በምንም ሁኔታ የማይቆም ነው ያሉት ብርጋዴል ጀነራሉ፤ ከሱዳን ድርጊት ጀርባ የግብጽ እና የሱዳን ተባባሪ የሆኑ አንዳንድ የአረብ አገራት እጅ ሊኖርበት እንደሚችል ጥርጣሬያቸውን ገልጸዋል። በመንግስት በኩል እየታየ ያለው ትእግስት ከበቂ በላይ መሆኑን አመልክተዋል። ሱዳን በኃይለስላሴ አገዛዝና በደርግ ሥርዓትም የመስፋፋት አዝማሚያ ታሳይ እንደነበር ያስታወሱት ብርጋዴል ጀነራል፣ በአሁኑ ወቅት ድንበር ጥሶ የገባውን ሃይሏን በሰላም የሚወጣ ከሆነ መልካም፣ ካልሆነ ግን የሃይል አማራጭን መጠቀም እንደሚያስፈልግ አስታውቀዋል። ለሰላም አማራጩ ተገዢ ካልሆኑ ወታደራዊ አቅምን በመጠቀም ማባረር እንደሚገባም ጠቁመዋል። እንደርሳቸው ማብራሪያ፤ ኢትዮጵያ መሬቷ ተወርሮ አሁንም ችግሩን በዲፕሎማሲ ለመፍታት እያደረገች ያለው ጥረት የሚደነቅ ነው። ለጎረቤት አገራት ያላትን ፍቅር፣ የሰላም ፍላጎቷንና ለቀጠናው ሰላም መጠበቅ ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል። ትዕግስቱ፣ ስምምነት ላይ ለመድረስ መሞከሩና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ድርጊቱን ለማስቆም እና ለማስመለስ መንቀሳቀሱ ተገቢ ነው። መንግስት በከፍተኛ ጥንቃቄ ጉዳዩን ለመያዝ ያለውን ፍላጎት የሚያመለክት እንደሆነም አመልክተዋል። የሱዳን ሉአላዊ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሌተናል ጀነራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን እና የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ጉብኝት እና ውይይት ማድረጋቸውን፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶክተር) እንዲሁም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ወደ ሱዳን ተጉዘው ተመሳሳይ ጥረት እያደረጉ ባለበት ሁኔታ ፣ ወረራ ማካሄድ ተገቢ አይደለም ብለዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ትዕግስት ማድረጉ ከዚህ በላይ አያስኬድም ትዕግስትም ወሰን አለው ያሉት ብርጋዴል ጀነራል ዋሲሁን ፣ፍቅርና የሰላም ፍላጎት ያልገዛውን ሃይል እንደሚገዛ አስታውቀዋል።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=39619
[ { "passage": "በኢትዮ-ኤርትራ መካከል ሰላም በመስፈኑና ስጋት በመወገዱ ፣ በመከላከያ በተካሄደው ሪፎርም ስድስት የነበሩት ዕዞች ወደ አራት ዝቅ በማለታቸው በሰሜን ድንበር አካባቢ የነበረውን የተወሰነው የመከላከያ ሰራዊት ወደ ሌሎች የኢትየጵያ ክፍሎች የማንቀሳቀስ ስራ እየተሰራ  መሆኑን በቅርቡ የኢፌዴሪ የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር ይፋ አድርጓል፡፡የልዩ ዘመቻዎች ሀይል አዛዥ ሌተናል ጀነራል ሞላ ሀይለማርያም፣ በኤርትራ በኩል ያለው ስጋት በመወገዱ ምክንያት በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ከነበረው ሰራዊት የተወሰነው ወደ ሌሎቹ የአገሪቱ ክፍሎች የሚንቀሳቀሰው ህዝቡ ያለ ስጋት መኖር እንዲችልና የሜጋ ፕሮጀክቶችን ደህንነት ለማረጋገጥ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል  በብዛት ተሰባስቦ የሚገኘውን የመከላከያ ሀይል ወደ ሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች የማንቀሳቀስ ስራዎች የሚሰሩባቸው ምክንያቶችም የኢትዮ-ኤርትራ የሰላም ሁኔታ በአብዛኛው የተሻለ ሁኔታ በመድረሱ፣የሁለቱ ህዝቦችና መንግስታት የሰላም ፍላጎታቸው የተረጋገጠ በመሆኑ፤ የክልሎችን የጸጥታ ሀይሎች አቅም ለማጠናከር፣ የሁሉንም የአገሪቱ ክፍሎች ደህንነት ለማስጠበቅ መሆኑንም ይገልጻሉ፡፡ይህ ማለት ግን ከባድሜና ሌሎች አካባቢ ሰራዊቱ ሙሉ ለሙሉ ይወጣል ማለት እንዳልሆነ ሊታወቅ ይገባል፣በሁሉም የአገራችን አካባቢዎች ሊገጥም የሚችለውን የጸጥታ አደጋ መከላከል በሚያስችል መልኩ አሰፋፈሩ ተወስኖ ወደ ስራ መገባቱን ሌተናል ጀነራል ሞላ ጠቅሰዋል፡፡መንግስት ሰራዊቱን ሲያንቀሳቅስ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ገምግሞና ሌላ ዓላማ የለውም የሚል እምነት ስላለኝ እንደ ትልቅ ስጋት አላየውም የሚሉት የቀድሞው አየር ሀይል አዛዥ ሜጀር ጄነራል አበበ ተክለሀይማኖት፣ ነገር ግን ስጋት አላቸው፡፡‹‹ፕሬዚዳንት ኢሳያስ  ነገ ምን ሊያደርግ እንደሚችል ባህሪውን አውቀዋለሁ ፡፡ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ መናገር የሌለበት ቢሆንም አሁንም በኢትዮጵያ ውስጣዊ ጉዳይ እንደፈለገ ነው እየተናገረ ያለው›› የሚሉት ሜጀር ጄነራል አበበ፤ ከኤርትራ ጋር ሙሉ ለሙሉ ሰላም መጥቷልና ሰራዊት ላንቀሳቅስ ማለቱ ተገቢ አይደለም ሲሉ ሞግተዋል፡፡‹‹ሌሎቹ እንደሚሉት የእኛን ጠቅላይ ሚኒስትር የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ እየመራው ነው የሚል እምነት ባይኖረኝም፡፡ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ላይ ግን እንደፈለገ እንዲናገር መፈቀድ የለበትም የሚል እምነት አለኝ፡፡ እርግጥ ነው ሙሉ ለሙሉ ሰላም ከተፈጠረ ድንበሩ በሚሊሻም ሊጠበቅ ይችላል፡፡ አሁን ግን ሙሉ ለሙሉ ተማምኖ ሰራዊትን ማንቀሳቀስ ተገቢ አይደለም ብለዋል፡፡ ምክንያቱም ፕሬዚዳንቱ ከህወሓት ጋር ባላቸው ቁርሾ ምክንያት  ስጋት ሊፈጥር ይችላል፡፡ ስለዚህ ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡‹‹ሌሎቹ  ወገኖች ሰራዊቱ መንቀሳቀስ የለበትም የሚሉትና ስጋት የፈጠረባቸው  ከጥርጣሬና ከፌዴራል መንግስቱ ጋር ካላቸው የሻከረ ግንኙነት ጋር አስተሳስረው ነው ፡፡ ይህ ስህተት ነው፡፡ ባድመ ሲወረር ሚሊሻ ብቻ ነው በአካባቢው የነበረው፡፡ እዚህ ላይ ጥንቃቄ አድርጎ የተከማቸ ሰራዊት ካለ ወደ ሌላው ማንቀሳቀስ ችግር የለውም›› ሲሉ ሃሳባቸውን ቋጭተዋል፡፡‹‹በአሁኑ ወቅት መንግስት ዋና ስጋቴ ነው የሚለው ከውጭው ይልቅ አገር ውስጥ እየሆነ ያለው ነገር ነው፡፡ ምክንያቱም የውጭው ስጋት የአገሪቱ ውስጣዊ ሁኔታ ላይ ተመስርቶ  የሚመጣ ነው›› የሚሉት ሌተናል ጄነራል ባጫ ደበሌ፣በተለያዩ ግለሰቦች አቀናባሪነትና ፈጣሪነት የጎሳ ግጭት የሚመስል ግን ደግሞ መደበኛ የሰራዊት ውጊያ አይነት ክስተት እየታየ ነው፡፡ ለምሳሌ ሞያሌ የተደረገውን ውጊያ ማየት ይቻላል፡፡ይህ የጎሳ ግጭት ወይንም የቦረና ኦሮሞና የገሪ ሱማሌዎች ውጊያ አይደለም፡ ፡ምክንያቱም የሚጠቀሙበት መሳሪያና የውጊያው አይነት ፈጸሞ የጎሳ ግጭት አለመሆኑን ያረጋግጣል፡፡ ቤኒሻንጉል ጉሙዝም ተመሳሳይ ነው፡፡ ከዚህ አኳያሰላም የማስፈንና የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ጉዳይ ውስጣዊ ስጋታችን ነው ሲሉ ይናገራሉ፡፡ይህን ስጋት ለማስወገድ ደግሞ ከሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ያለውን ሀይል አንስቶ ወደ ሌሎቹ የአገሪቱ ክፍል ማሰማራት እንደሚያስፈልግ የሚገልጹት ሌተናል ጄነራል ባጫ ደበሌ በኢትዮ-ኤርትራ ድንበር ሰፍሮ የነበረው ሰራዊት የማንቀሳቀስ ርምጃ ስጋት ሊፈጥር የቻለበት ምክንያት አንደኛው የኢትዮ-ኤርትራን ግንኙነት የተፈጠረውን ሰላም በመጠርጠር ሊሆን ይችላል፡፡ መነሻውም ‹‹በቀን እባብ ያየ ለሌት በቅርፊት ይሸሻል›› እንደሚባለው ተደጋጋሚ የሆነ አለመተማመኖች ስላሉ፣አሁንም ከኤርትራ በኩል ጦርነት ስለሚነሳብን ሰራዊቱ እዚህ አካባቢ መነሳት የለበትም ከሚል ቅን አስተሳሰብ የተነሳ ሊሆን ይችላል፡፡ሆኖም በአሁኑ ጊዜ ኤርትራ ኢትዮጵያን በጦርነት አትፈልጋትም ነው ያሉት፡፡ምክንያቱም ኢትዮጵያና ኤርትራ የሰላማቸውን ዋጋ ገና እያጣጣሙት ነው፡፡ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱም ተጧጡፏል፡፡ሌላው ኤርትራ ሰላም እየፈጠረች ያለችው ከኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ከጂቡቲና ከሶማሊያም ጭምር ነው፡፡ በኤርትራ ላይ የተጣለው ማዕቀብ እንዲነሳም ኢትዮጵያ ጉልህ ሚና ተጫውታለች ሲሉ ነው ኤርትራ የኢትዮጵያ ስጋት አለመሆኗን ያስረዱት፡፡ሁለተኛው ምክንያት ግን ሰራዊቱ ከሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል መንቀሳቀስ የለበትም የሚሉት ወገኖች የራሳቸውን ድብቅ ፍላጎት ሊያስፈጸሙ በማሰብ ነው ይላሉ ሌተናል ጄነራል ባጫ፤ እዚህም እዚያ ብሄር ብሄረሰቦችን ለማጋጨት የሚፈልጉ ሰዎች ሰራዊቱ ወደ ሌሎች አገሪቱ ክፍሎች የሚንቀሳቀስ ከሆነ የማጋጨት ዕድሉ አይኖራቸውም፡፡ ከዚህ ተነስተው ሰራዊቱ መነሳት የለበትም ሊሉ ይችላሉ፡፡ስጋቱ ከማንኛውም ሆነ ከየትኛውም ወገን ይነሳ ሰራዊቱን የማንቀሳቀሱ ውሳኔው ግን በጣም ትክክለኛና አገራችን ውስጥ ያሉ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ታስቦ የተወሰደ ዕርምጃ በመሆኑ ማንንም ስጋት ውስጥ የሚጥል አይደለም በሚል ሃሳብ አላቸው፡፡‹‹የመከላከያ ሰራዊት ትግራይ ላይ የሰፈረው ድንበሩን እንጂ ማንኛውንም የፖለቲካ ፓርቲ ለመጠበቅ አይደለም›› ያሉት ሌተናል ጄነራሉ፣ሰራዊቱን ስጋት ወደ አለባቸው አካባቢ አስገብቶ ሰላም እንዲያመጣ ማሰማራት ተገቢና ኃላፊነት የተሞላበት ርምጃ ነው፡፡እንዲያውም ዘግይቷል ብለዋል፡፡ሚያዝያ 28 ቀን 1990 ዓ.ም  የተቀሰቀሰው የኢትዮ-ኤርትራ የድንበር ጦርነት ተከትሎ ሰራዊቱ ላለፉት 20 ዓመታት ያህል በድንበር አካባቢ ሰፍሮ ቆይቷል። አሁን የሁለቱ አገሮች መሪዎች የፈጠሩት ግንኙነት በስጋት ተወጥሮ የነበረው አካባቢ እፎይታ አግኝቷል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 17/2011በጌትነት ምህረቴ", "passage_id": "437ceb6f74fdd9d260e62fb87249b701" }, { "passage": "በሱዳን የኢትዮጵያ ባሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሙሉጌታ ዘውዱ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ 65 በመቶ መድረሱን ገልጸዋል ፡፡ሶስቱ ሀገራት በቅርቡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ በውሀ ሚኒስትሮች እና በከፍተኛ የደህንነት ሀኃፊዎች የተመራውን የሶስትዮሽ ስብሰባ በአዲስ አበባ ባካሄዱት ወቅት በግድቡ ውሀ አሞላል ሂደት፣ በግድቡ የወደፊት ስራ እና  በቴክኒካዊ ጥናቶች ዙሪያ የነበራቸውን አለመግባባት በመቅረፍ ከስምምነት መድረሳቸው የሚታወስ ነው፡፡ይህ ስምምነቱም በግድቡ ዙሪያ የሚነሱ ስጋቶች እልባት እንዲያገኙ ማስቻሉን የገለጹት አምባሳደሩ፤ ሶስቱም ሀገራት ከግድቡ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ አረጋግጠዋል፡፡ስምምነቱ ሶስቱ ሀገራት በመጀመሪያው የቴክኒካል ሪፖርት ላይ ያላቸውን አስተያየቶች እና ጥያቄዎች በግድቡ ዙሪያ የቴክኒካል ጥናት ለሚያደርገው ገለልተኛ አካል በደብዳቤ እንዲያቀርቡ ጋብዟል፡፡ የቴክኒካል ኮሚቴው በካይሮ በሚያደርገው ስብሰባም ሀገራቱ በሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ግብጽ ቀደም ሲል በአማካሪ ድርጅቱ በቀረበው ምክረ ሀሳብ ላይ ኢትዮጵያ እና የሱዳን  የሚያነሱትን ጥያቄ ውድቅ ስታደርግ መቆየቷ የሚታወስ ነው፡፡አሁን ላይ ግን ሶስቱ ሀገራት የጋራ ብሄራዊ ቴክኒካል ኮሚቴ ለማቋቋም ከስምምነት የደረሱ ሲሆን የሚቋቋመው ቴክኒካል ኮሚቴም የግድቡን ውሃ አሞላል እና የወደፊት ስራ በሚመለከት ጥናት የሚያካሂድ ሲሆን ከእያንዳንዱ ሀገር አምስት አባላት ይኖሩታል፡፡ይህን ተከትሎም ግብጽ ከዚህ በፊት በጉዳዩ ላይ ሶስተኛ ወገን ሆኖ እንዲያደራድር ጥያቄዋን ለአለም ባንክ ለማቅረብ አቅዳው የነበረውን ውሳኔ ሰርዛለች፡፡ኢትዮጵያ እና ሱዳን ሶስተኛ ወገን ሳይሳተፉ ልዩነቶችን መፍታት እንደሚቻል በመግለጽ ግብጽ ይዛው የነበረውን አቋም በጥብቅ ሲቃወሙ እንደነበር የገለጹት አምባሳደር ሙሉጌታ እርምጃ ከአንድ ዓመት በላይ የቆየውን የግብጽን አቋም ያለሳለሰ ተደርጎ ሊወሰድ እንደሚችልም ጠቁመዋል፡፡  ሀገራቱም በፈረንጆቹ ሰኔ 18 እና 19 ሁለት የተለያዩ ስብሰባዎችን በግብጽ ካይሮ ለማካሄድ ከስምምነት ደርሰዋል፡፡የመጀመሪያው ስብሰባ በብሔራዊ የቴክኒክ ኮሚቴ እና አማካሪው መካከል የሚካሄድ ሲሆን በሚኒስትሮች ደረጃ የሚካሄደው ሁለተኛው ስብሰባ ደግሞ በመጀመሪያው ስብሰባ በተነሱ ምክረሀሳቦች ላይ የአማካሪው ቡድን ምላሽ በመስማት የቀረበውን ሪፖርት ለማጽደቅ እንደሚካሄድ ታውቋል፡፡የካይሮን ስብሰባ ተከትሎ አማካሪ ቡድኑ በግድቡ ዙሪያ ያሉ ማህበራዊ፤ ሥነ ምህዳራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጥናቶችን እንደሚጀምር የሚጠበቅ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም የግድቡ ውሃ አሞላል እና የስራ ሂደት የሚያሳድረውን ተጽእኖ በሚመለከት የሃይሮሎጂካል ጥናት ማዘጋጀት እንደሚጀምር ታውቋል፡፡ኢትዮጵያ ሱዳን እና ግብጽ እ.አ.አ በ2015 የግድቡን ግንባታ የሚያረጋግጥ መግባቢያ ሰነድ መፈረማቸው የሚታወስ ሲሆን የሶስቱን የተፋሰሱ ሀገራት የውሃ ኮታ ባስጠበቀ መልኩ እንዲሆን የቴክኒካል ጥናት እንዲካሄድ ጥያቄ አቅርበው እንደነበር ተገልጸል፡፡በአውሮፓዊያኑ 2016 የፈረንሳዩ የኢንጂነሪንግ ኩባንያ አርቴሊያ እና ቢአርኤል አማካሪ ድርጅት ግድቡ የሚያደርሰውን ተጽዕኖ በሚመለከት ጥናት እንዲያካሂድ የተመረጠ ሲሆን የሶስትዮሽ ኮሚቴውን የህግ ጉዳዮች ለማስተዳደር ደግሞ የእንግሊዙ ኮርቤት እና ኮ የተሰኘው የህግ ተቋም መመረጡ ይታወቃል፡፡ከሱዳን ድንብር በ20 ኪሎሜትሮች ርቀት ላይ በ80 ቢሊየን ብር ወጭ እየተገነባ ያለው የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ሲጠናቀቅ 74 ቢሊየን ኪዩብክ ሜትር ውሃ የመያዝ አቅም እንደሚኖረው የተገለጸ ሲሆን 6 ሺህ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት እንደሚችልም ይጠበቃል፡፡ግብጽ የግድቡ ግንባታ ከናይል ወንዝ የምታገኘውን የ55 ነጥብ 5 ቢሊየን ኪዩብክ ሜትር ውሃ ይቀንሰዋል የሚል ስጋት ቢኖራትም ኢትዮጵያ ግን የግድቡ ግንባታ በዋነኛነት የኤሌክትሪክ ሀይል ለማመንጨት የሚውል በመሆኑ ግብጽንም ሆነ ሱዳንን የሚጎዳበት አግባብ እንደሌለ ማስታወቋን የሱዳን ትሪቡን ዘገባ አስነብቧል፡፡", "passage_id": "c6c22feefa863fc66bd5d504887f95e6" }, { "passage": "በሱዳን እየተደረገ ያለው አድማ ሁለተኛውን ቀን መያዙን ተከትሎ ጥበቃው ተጠናክሯል ሲል ወታደራዊ ምክር ቤቱ አስታውቋል፡፡በዚህም የተለያየ ተቋማት፣ የንግድ ቤቶችና የትራንስፖርት አገልግሎት በዋና ከተማዋ ካርቱም ዝግ ሆነው ቀጥለዋል፡፡የሱዳን ወታደራዊ ምክር ቤት ህዝባዊ ተቃውሞውን የሚመሩ አካላት የቀረበላቸውን የእንወያይ ጥያቄ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲቀበሉ ጥሪ አቅርቧል፡፡የምክር ቤቱ ቃል አቀባይ ሻማስ ኤልዲን አልካባሽ አሳሳቢ የሆነውን የሱዳን አካሄድ ለማረጋጋት ሁሉም አካል ቀድሚያ መስጠት አለባቸው ብለዋል፡፡የተቃውሞ መሪዎች የቀረበላቸውን ጥያቄ የማይቀበሉ ከሆነ ወታደራዊ ምክር ቤቱ ብቻውን መንግስት ለመመስረት እንደሚገደድም ቃል አቀባዩ አስታውቀዋል፡፡በሀገሪቱ እየተካሄደ ያው ተቃውሞ ወታደራዊ ምክር ቤቱ ስልጣኑን ለህዝባዊ አካል እንዲያስረክብ የሚጠይቅ ነው፡፡ሰሞኑን እየተካሄደ ባለው ተቃውሞ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሱዳናውያን መሞታቸውን ተቃዋሚ ኃይሎች ተናግረዋል፡፡ወታደሩ ስልጣኑን እስኪያስረክብ ድረስ ተቃውሞውና አድማው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አክቲቪስቶች ገልጸዋል፡፡(ምንጭ፡-ቢቢሲ) ", "passage_id": "b5c376f8bea3ced9aa7892021bc516be" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 4 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የተከዜ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ምንም አይነት ጉዳት እንዳልደረሰበትና ሃይል በማመንጨት ስራ ላይ እንደሚገኝ የጣቢያው ስራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ የጣቢያው ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ከማል አህመድ በስፍራው ለተገኙ ጋዜጠኞች እንደገለጹት፤ ከሰሞኑ መንግስት ከወሰደው ህግ የማስከበር እርምጃ ጋር ተያይዞ ማመንጫው ጉዳት ደርሶበታል መባሉ ሀሰት ነው ፡፡ የተከዜ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ አሁንም ሃይል እያመነጨ መሆኑን ገልጸው፤ በግድቡ ላይ የአውሮፕላን ጥቃት ደርሶበታል የሚለውን ዜና እንደማንኛውም ሰው በድምጸ ወያኔ እና በትግራይ ቴሌቪዢ የሰሙ መሆናቸውን ነው ያስታወቁት፡፡ የተከዜ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ 300 ሜጋ ዋት ሃይል የማመንጨት አቅም ያለው ሲሆን፤ በተጠቃሚ ማነስ ምክንያት አሁን ላይ 225 ሜጋ ዋት እያመነጨ መሆኑን ኢፕድ ዘግቧል፡፡ ጁንታው ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም በሀገር መከላከያ ሰራዊት ላይ ጥቃት ከፈጸመ በኋላ ከተከዜ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ የሚመነጨው ሃይል ወደ ብሔራዊ ቋት እንዳይጓዝ በማድረግ ለትግራይ ክልል ብቻ እንዲያገለግል ለማድረግ በክልሉ የሚገኙ ከፍተኛ የሀይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ጉዳት ማድረሱንም ገልጸዋል፡፡", "passage_id": "c8eddf086d1824d8de28923f5fbab48a" }, { "passage": "የኢትዮጵያ መንግስት በኢትዮ-ሱዳን ድንበር የተፈጠረውን ግጭት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እየሰራ እነደሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ገልጸዋል፡፡በትግራይ ክልል ሰላማዊ እንቅስቃሴ ተጀምሮ ባለበት በዚህ ወቅት የቀጠናውን አለመረጋጋት የሚፈልጉ አካላት የተሳሳተና አሉታዊ ነገሮችን በአለም አቀፍ መገናኛ እያሰራጩ ነው ተብሏል፡፡አምባሳደር ዲና የኢትዮጵያ መንግስት በኢትዮ-ሱዳን ድንበር የተፈጠረውን ግጭት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እየተሰራ እነደሆነም ተናግረዋል፡፡ምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ደመቀ መኮንን ወደ ሱዳን ካርቱም አቅንተው በሰላማዊ መንገድ መፍታት በሚቻልበት መንገድ ላይ ተወያይተዋል ያሉት አምባሳደር ዲና፣ ሱዳን ኢትዮጵያ በትግራይ ክልል ህግ በምታስከብርበት ወቅት ሱዳን የዲፕሎማሲ ድጋፏን አሳይታለች፤ ዜጎች ሲሰደዱም አስተናግዳለች፤ ይሄም እንደ በጎ ሊታይ የሚገባው ተግባር ነው ብለዋል፡፡አሁን ላይ በሁለቱ ሀገራት ድንበር ላይ ውጥረቱ ቢቀንስም ሙሉ በሙሉ እንዲፈታ መንግስት እየሰራ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተፈጠረው ግጭት የሁለቱን ሀገራት የቀደመ ታሪክ የማይመጥን ነው ተብሏል፡፡በቀጠናው አለመረጋጋት የሚያተርፉ አካላት ሁኔታዎች እንዲባባሱ እየሰሩ ነው የተባለ ሲሆን ሱዳናውያኑንም መሬቱ የናንተ ነው የሚል ቅስቀሳ በማድረግ በሀገራቱ መካከል ግጭት እንዲፈጠር ስለማድረጋቸው ተነስቷል፡፡በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ ከመካከለኛው ምስራቅ 328 ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው መመለስ መቻሉን አምባሳደሩ ተናግረዋል፡፡በሳምንቱ የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ የዲፕሎማሲ ስራዎች መሰራታቸው የተነገረ ሲሆን ከተለያዩ ሀገራት ከመጡ በኢትዮጵያ መዋዕለ ነዋያቸውን ማፍሰስ ከሚፈልጉ አካላት ጋር ውይይት መደረጉም ተነግሯል፡፡ለአንድ ወር ተቆርጦ የነበረው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድርድር በመጪው እሁድ እንደሚጀመርም ታውቋል፡፡(በመስከረም ቸርነት)", "passage_id": "b7b7a56fd66707e21e43c2cea4dfb367" } ]
25866e765997537f98dff658591bfaf7
114152130feb8e8599c38dc8d8e383ca
የአትሌቶችን ጥያቄ የሚመልስ ማዘውተሪያ
 ብርሃን ፈይሳበኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በኦሮሚያ ክልል ለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ የተገነባው የአትሌቲክስ ማዘውተሪያ የአሸዋ ትራክ ተመረቀ። በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎችም ተመሳሳይ ማዘውተሪያዎች እንደሚገነቡ ታውቋል።በኦሮሚያ ክልል ለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ የተገነባው የአትሌቲክስ ማዘውተሪያ ስፍራ ትናንት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል። ግንባታው ለረጅም ርቀትና አጭር ርቀት አትሌቲክስ ስፖርት መለማመጃ የሚውለው የአሸዋ ትራክ እንዲሁም የአትሌቶች ልብስ መቀየሪያ፣ የማረፊያና የንጽህና መጠበቂያ ስፍራን ያጠቃልላል። ከለገዳዲ ለገጣፎ ባሻገር በክልሉ ባሉ የተለያዩ ከተሞችም ተመሳሳይ ማዘውተሪያዎች የሚገነቡ መሆኑም ተጠቁሟል። በምረቃ ስነስርአቱ ላይ የፌዴሬሽኑ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ ከአትሌቶች ወቅታዊና አንገብጋቢ ጥያቄዎች አንጻር ለአትሌቲክስ ስፖርት ምቹ ከሆኑት አካባቢዎች መካከል አንዱን በመምረጥ ለምረቃ የበቃውን የለገጣፎ ለገዳዲ የአሸዋ ትራክ ለማስገንባት እንደተቻለ ገልጻለች። ፌዴሬሽኑ ለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ አስተዳደር ጋር በተደረሰው ስምምነት መሰረት የዲዛይን ስራ በማሰራትና ለግንባታውም ፌዴሬሽኑ 18 ሚሊየን ብር ወጪ በማድረግ ግንባታው ተካሂዶ ለምረቃ በቅቷል። ትራኩ 1ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን፤ ወደ 2ኪሎ ሜትር እንዲያድግ ለቀረበው ጥያቄም የክልሉ መንግስት ፈቃደኝነቱን በመስጠቱ ምክትል ፕሬዚዳንቷ ምስጋና አቅርባለች። ግንባታው ፌዴሬሽኑን ብቻም ሳይሆን ከተማ አስተዳደሩን፣ ክልሉንና ኢትዮጵያንም ጭምር በማበልጸግና የስፖርት ቱሪዝምን በመሳብ ከሃገር ገጽታ በተጨማሪ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታም እንደሚኖረው ጠቅሳ፣ ከፌዴራል መንግስት ጀምሮ ሁሉም አካላት የማዘውተሪያ ስፍራ ችግርን ለመቅረፍ በትኩረትና በርብርብ የሃገር በጎ ገጽታ መገንባት እንደሚኖርባቸው አስገንዝባለች። ማዘውተሪያውን የመረቁት የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ ፌዴሬሽኑ ማዘውተሪያውን በመገንባት በጎ ተግባር መስራቱን አስታውቀዋል። በፌዴሬሽኑ የቀረበውን 1ነጥብ6 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ትራክ ወደ 2 ኪሎ ሜትር ለማሳደግ የክልሉ መንግስት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። ከለገዳዲ ለገጣፎ ባሻገር በሱሉልታ፣ በቡራዩ፣ ሰበታ እና ገላን ቦታዎችን በአጭር ጊዜ በማዘጋጀት፤ የማዘውተሪያ ስፍራዎች በፌዴሬሽኑ እና በክልሉ መንግስት ድጋፍ እንደሚገነቡም ጠቁመዋል። ይህም አትሌቶችን ከመኪና አደጋ እና ከመሳሰሉት ጉዳቶች ተጠብቀው ልምምዳቸውን እንዲያደርጉ እና ለሃገራቸው ክብር እንዲቆሙ እንደሚያስችሉ አስታውቀዋል።ለእዚህም የክልሉ መንግስት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። የለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ወይዘሮ ሃቢባ ሲራጅ፤ በርካታ አትሌቶች ከከተማው የአትሌቲክስ ክለብ በመውጣት በዓለም አቀፍ ደረጃ ውጤት ማስመዝገባቸውን እንዲሁም ለቶኪዮ ኦሊምፒክ ስድስት አትሌቶችንና ሁለት አሰልጣኞች ለብሄራዊ ቡድን መመረጣቸውን ጠቅሰዋል። ይህ ውጤት ሊገኝ የቻለውም በመንግስት በተደረገለት ድጋፍ መሆኑን ተናግረው፤ ፖሊሲው ስፖርት በህዝባዊ አካል እየተመራ በመንግስት እንዲታገዝ ቢሆንም፤ በርካታ የማዘውተሪያ ስፍራዎች የተገነቡት በመንግስት ነው ብለዋል። በዚህም አትሌቶች የመለማመጃ ስፍራ አንድ ለእናቱ ከነበረው የአዲስ አበባ ስታዲየም ወደ አጎራባች ከተሞች በመውሰድ አትሌቶች አማራጭ መሮጫዎችን እንዲያገኙ ተደርጓል ያሉት ከንቲባዋ፤ እንደ ከተማም በስፖርቱ ምክንያት ወደ ማዘውተሪያው የሚጓዙ የሃገር ውስጥና የውጪ ሃገራት አትሌቶች ሰላማቸው ተጠብቆ ማዘውተሪያው ለታለመለት ዓላማ እንዲውል እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። መዋዕለ ነዋያቸውን በስፖርት ላይ ለማፍሰስ ለሚፈልጉ ባለሃብቶችም ከምንጊዜውም በላይ ድጋፍ እንደሚሰጥም ገልጸዋል። በእለቱ ከተካሄደው ምረቃ ስነስርአት ጎን ለጎን ፌዴሬሽኑ ለሚያስገነባው ባለ 12 ወለል ህንጻም የመሰረተ ድንጋይ በእለቱ ተቀምጧል። ይህም ጂምናዚየም፣ የህክምና እና የማገገሚያ ማዕከል፣ ከአትሌቲክስ ጋር የተያያዙ አገልግሎቶችን የሚሰጥ እንዲሁም ገቢ የሚያስገኝ እንደሚሆንም ታውቋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 4/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=37292
[ { "passage": "ስለ ኢትዮጵያ ማወቅ የሚፈልግ ማንኛውም ሰው ሰነዶችን ቢበረብር፣ መረጃዎችን ቢያገላብጥ፣ ወይም በይነ መረቦችን ቢያስስ ከተፈጥሮና ሰው መሰራሽ ሀብቶቿ መካከል አንዱ አትሌቲክስ መሆኑን ይገነዘባል። ኢትዮጵያ በዓለም ሕዝብ ዘንድ ከእውቅናም በላይ ከበሬታን እንድታገኝ ካደረጉ ጉዳዮች መካከል በኦሊምፒክ ማራቶን የወርቅ ሜዳሊያ ያጠለቀ የመጀመሪያው ጥቁር አትሌት የአበበ ቢቂላ አገር መሆኗ ትልቅ ድርሻ አለው። መረጃዎች አበበ ቢቂላ በባዶ እግሩን ሮጦ ከማሸነፉም በላይ ከአራት ዓመታት በኋላም ከዓለም ክብረወሰን ጋር ድርብ ድል መቀዳጀቱን ሳያስታውሱ አያልፉም። ስፖርቱን፣ አሸናፊነቱንና ክብሩን ትውልድ እየተቀባበለ ለዘመናት ማኖሩም በወርቅ ቀለም የተጻፈ የታሪክ አካል ነው። አትሌቲክስ ለኢትዮጵያ በቻምፒዮናዎች እና የኦሊምፒክ መድረኮች ላይ በመም፣ በጎዳና ወይም በሀገር አቋራጭ ውድድር ሜዳሊያ የምታስመዘግብበት ዘርፍ ብቻም አይደለም። ከኩራትና የአንድነት ስሜት ምንጭነቱ ባሻገር ሀገር ትለማና ትበለጽግ ዘንድ የበኩሉን በማድረግ እየተረባረበ ነው። ብርቅየ አትሌቶች በሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ፤ የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት፣ በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ፣ በአግሮ ኢንዱስትሪ፣ በኮንስትራክሽን፣ በአውቶሞቲቭና በመሳሰሉት ዘርፎች በመግባት ለወጣቱ የስራ እድል በመፍጠር ረገድ የራሳቸውን አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ። ስፖርቱ መዋዕለ ንዋዩን በማፍሰስ የድርሻውን ከመወጣት ባለፈም ሀገራዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይም ቅድሚያና ቀጥተኛ ተሳታፊ መሆኑም እሙን ነው። በተለያዩ ጊዜያት በፌዴሬሽኑ፣ በአትሌቶችና በሙያ ማህበራት በተናጠልና በቡድን የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ለማውሳትም፤ ከወቅታዊው የኮሮና ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ የተከናወነውን ስራ በምሳሌትነት ማንሳት ይቻላል። የገንዘብና የቁሳቁሰ ድጋፍ ከማድረግም ባለፈ በማዕድ ማጋራት ላይም ፌዴሬሽኑ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከት ችሏል። አሁንም መንግስት በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታና የውሃ ሙሌት ላይ የያዘውን አቋም በጽኑ እንደሚደግፍ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ግንባታው እስኪጠናቀቅ ድረስም የአትሌቲክስ ቤተሰቡ ከመንግስትና ከህዝብ ጎን የሚቆም መሆኑንም በድረገጹ ባወጣው መግለጫ አስነብቧል። ለረጅም ዓመታት ሲጓተት የቆየው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሂደቱ እየተፋጠነና የውሃ ሙሌቱም በተያዘው\nክረምት  የሚጀመር መሆኑን መንግስት ይፋ ማድረጉን ተከትሎ ነው ፌዴሬሽኑ የድጋፍ መግለጫውን ያወጣው። በዚህም የፌዴሬሽኑ አመራሮችና ሰራተኞች፣ አትሌቶች፣ የአትሌት ተወካዮችና አሰልጣኞች፣ የአትሌቲክስ ዳኞች እንዲሁም በስፖርት ቤተሰቡ በቁርጠኝነት እንደሚደግፍ ጠቁሟል። ፌዴሬሽኑ ከዚህ ቀደም ቦንድ በመግዛትና ድጋፍ በማሰባሰብ፣ ከዚሁ ጎን ለጎን የፌዴሬሽኑ አመራሮችና የአትሌቲክሱ ቤተሰብ በስፍራው በመገኘት ግንባታውን መመልከቱ ይታወሳል። ከ40ሺ በላይ ሯጮችን ያሳተፉ የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድሮችን በማካሄድም የግድቡን ግንባታ የሚደግፉ አካላትን የማነቃቃት ስራም አከናውኗል። በቅርቡም ፌዴሬሽኑ ለሕዳሴው\nግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ\nጽህፈት ቤት የገንዘብ\nድጋፍ አበርክቷል። አባይና የህዳሴ ግድቡ ለአትሌቶችና የኢትዮጵያ\nአትሌቲክስ ፌዴሬሽን እንደማንኛውም\nየህብረተሰብ ክፍል የህልውና\nጥያቄ በመሆኑም በአካል በቦታው  በመገኘት፣ ለግንባታው በማስተባበር፣ አቅም የፈቀደውን የገንዘብ አስተዋጽኦ በማድረግ እንዲሁም በግልና በቡድን ለግንባታው የሚያግዙ የዲፕሎማሲ ስራዎችም በተጨማሪነት እየተሰሩ እንደሚገኙም በመግለጫው ተመልክተዋል። ይህ ሂደት የአንድ ወቅት ብቻ ባለመሆኑ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኑ ድጋፉን አጠናክሮ በመቀጠል፤ ስራው እንደ ድል አድራጊ አትሌቶች በጽናትና በቁርጠኝነት እንደሚጠናቀቅም እምነት ተጥሎበታል። ፌዴሬሽኑ ከግድቡ ባሻገር የደም ልገሳና አረንጓዴ አሻራን ለማሳረፍ የችግኝ ተከላ በቅርቡ ለማካሄድም በዝግጅት\nላይ ይገኛል። በዓለምና\nሀገር አቀፍ ደረጃ እየተስፋፋ በሚገኘው\nየኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ\n(ኮቪድ 19) ምክንያት እየተከሰተ\nያለውን የደም እጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት የደም ልገሳ መርሃ ግብር በማዘጋጀት\nፌዴሬሽኑ ለስፖርቱ ቤተሰቦች\nጥሪ አድርጓል። በቀጣይ ሳምንት ሰኔ  16/2012 ዓም ከማለዳው ሶስት ሰዓት ጀምሮ የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት፣ የቢሮ ሰራተኞች፣ አንጋፋ አትሌቶች፣ አሰልጣኞች፣ የአትሌት ተወካይ ማናጀሮች፣ ሁሉም የአትሌቲክስ ማህበራት አመራሮች፣ የክለብ አመራሮች በአጠቃላይ የአትሌቲክሱ ቤተሰብ በፌዴሬሽኑ አስተባባሪነት የደም ልገሳውን ለማካሄድ ቀጠሮ ይዛል። ፌዴሬሽኑ ከኢትዮጵያ ደም ባንክ አገልግሎት ጋር በመተባበር ባዘጋጀው ታሪካዊና አገራዊ ጉዳይ ላይ ሁሉም የድርሻውን እንዲያበረክትም ጥሪውን አስተላልፏል። በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተመናመነ ያለውን የሀገሪቷን የደን ሽፋን እንዲያገግም ለማድረግም ከመንግስት ጎን በመቆም የአረንጓዴ አሻራን በችግኝ ተከላ ለማሳረፍም እቅድ ይዟል። የአትሌቶች የህይወት ምንጭ የሆኑትን የዛፍ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የትና መቼ እንደሚከናወን በቅርቡ እንደሚያሳውቅም ጠቁሟል።  አዲስ ዘመን ሰኔ10/2012ብርሃን ፈይሳ ", "passage_id": "d8d94b43638fd2e8af912cafe5230dad" }, { "passage": "የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) በቅርቡ ባደረኩት ግምገማ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ ሜዳዎች ዓለም አቀፍ ውድድሮችን የማስተናገድ አቅም የላቸውም ሲል ከሰሞኑ ይፋ አድርጓል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን «ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ ሜዳዎች አንዳንቸውም የካፍን መመዘኛ አያሟሉም ተብለናል» ሲል ለዚሁ ማረጋገጫ ሰጥቷል። የካፍ የግምገማ ውጤት ሰሞነኛ ጉዳይ በመሆንም ሰንብቷል። በሀገሪቱ የተለያዩ ክልሎች ስታድየሞች እየተገነቡ ባሉበት ወቅት እንዴት አንዱ እንኳን የካፍን መመዘኛ ማሟላት አቃተው? ሲሉም በርካቶች እየተጠየቁ ይገኛል። ጥያቄው ተገቢና መሰረታዊ መሆኑ የሚያሻማ አይደለም። የካፍ ግምገማን ተከትሎ ብዙ ብዙ የተባለላቸው ስታዲየሞቻችን አሁናዊ ቁመናን መፈተሽ ደግሞ ለዚህ ምላሽ ይሰጣል።በኢትዮጵያ በየዓመቱ ሲከበር የቆየውን የብሔር ብሔረሰቦችን በዓልን መሰረት በማድረግ በመላ ሀገሪቱ ግዙፍ የሚባሉ ስታዲየሞች በመገንባት ላይ ቢሆኑም አንዳቸውም ሙሉ ለሙሉ አልተጠናቀቁም። ለአብነትም በአዲስ አበባ ከሚገኘውና የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታው እየተጠናቀቀ ካለው ብሔራዊ ስታድየም አንስቶ በባህርዳር፣ ሐዋሳ፣ መቐለ ላይ ያሉት በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ። ከተመልካቾች መቀመጫና ውጫዊ ገጽታ ባሻገር የመጫወቻ ሜዳ ጥራት፣ አስፈላጊ ውስጣዊ ግንባታዎች ላይ የሚሰጠው ትኩረት አናሳ መሆኑም ዋጋ እያስከፈለ መጥቷል። ብሄር ብሄረሰቦች የወለዷቸው ስታዲየሞችበብሔር ብሔረሰቦች ቀን አማካኝነት ግንባታቸው ከተጀመሩ ታድየሞች መካከል በጋምቤላ ፣አፋር ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝና ሐረሪ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስታት የሚገነቡት ዋነኞቹ ናቸው፡፡ የስታዲየሞቹ ግንባታ ትልቅ ቁም ነገር ያለው ቢሆንም ፤ፕሮጀክቶቹ ሲታቀዱ “ማን ከማን ያንሳል” በሚል ስሜታዊነት በመሆኑ ፍጻሜያቸው እንዳጀማመራቸው ሳይሆን ቀርቷል። አንዳንዶቹ ባሉበት ቁመና የአገር ውስጥ ውድድሮች በማስተናገድ ላይ ይገኛሉ፡፡ ጥቂቶቹ ደግሞ መሠረታቸው ተጥሎ ግንባታቸው ከተጀመረ ሁለት አስርታት ዓመታት ሊሞላቸው ተቃርቧል።የስታዲየሞቹ ግንባታ መሰረት የተደረገው ስፖርትን ሳይሆን ፖለቲካን በመሆኑ ክብረ በዓሉ እንዳለፈ አስታዋሽ በማጣታቸው ምክንያት ቆመው ቀርተዋል። ለምሳሌ በጋምቤላ ክልል ብሄር ብሄረሰቦች በዓልን ምክንያት በማድረግ የተጀመረው ስታዲየም ግንባታው የካቲት 12 ቀን 2007 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን በሁለት ዓመታት ውስጥ ተገንብቶ በ 2009 ዓ.ም ላይ ይጠናቀቃል ተብሎ ነበር፡፡ ለግንባታውም 648 ሚሊዮን 776 ሺ አምስት መቶ ዘጠና ብር ተበጅቶለትም ነበር፡፡ ምን ዋጋ አለው አሁን ላይ አርባ ዘጠኝ በመቶ ብቻ ተሰርቶ በፋይናነስ እጥረትና ተጓዳኝ ምክንያቶች ቆሞ ይገኛል። ሌላው የብሄር ብሄረሰቦችን ቀንን መሰረት አድርገው መሰረታቸውን ከጣሉት ግዙፍ ስታዲየሞች አንዱ ደግሞ «አሕመድ ነስር» መታሰቢያ ስታዲየም ነው። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እየተገነባ የሚገኘው ይህ ስታዲየም ግንባታ የካቲት 23 ቀን 2006 ዓ.ም ነበር የተጀመረው። ጥቅምት 2011 ዓ.ም ይጠናቀቃል ተብሎ ነበር፡፡ አሁን ላይ የግንባታው ሂደቱ ሃምሳ በመቶ ላይ ነው የቆመው። የግንባታው ሂደት ከመጓተቱ ባሻገር የፋይናንስ አፈጻጸሙም ደግሞ ሌላ ተጨማሪ ጥያቄን የሚያስነሳም ሆኗል። በ 460 ሚሊዮን ብር ወጪ ይገነባል የተባለው ይህ ስታዲየም ፤ እስከ አሁን 50 በመቶ ላይ ይገኝ እንጂ 340 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጎበታል፡፡ ይህ ገንዘብ የሙሉ ግንባታ ወጪን የሚስተካከል በመሆኑ ከስራው መጓተት ባሻገር የፋይናንስ አፈጻጸሙም ምርመራን የሚሻ መሆኑን ጠቁመን ወደ ሐረር ተሻገርን ።በሐረሪ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሚገነባው አባድር ስታዲየም ሚያዝያ 2008 ዓ.ም ነው የተጀመረው፤ ጥቅምት 2011 ዓ.ም ይጠናቀቃል ተብሎ ነበር፡፡ ግንባታውን በታሰበበት ጊዜ እንዲጠናቀቅ በ2010 ዓ.ም ሦስት መቶ ስልሳ ሚሊዮን ብር ተመድቦ የነበረ ቢሆንም አሁንም 600 ሚሊዮን ብር አስወጥቶ ከ65 በመቶ ላይ ግን ፈቅ ማለት አልቻለም ተብሏል። በአሁኑ ወቅት ግንባታው እንደቆመ የሚነገርለት ስታዲየሙ ሙሉ በሙሉ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ 1 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር እንደሚፈጅ ታውቋል። የግንባታው መቋረጥ መንግስትን ለተጨማሪ ወጪ መዳረጉ የማይቀር መሆኑም ሊሰመርበት ይገባል።የብሄር ብሄርሰብ በዓልን መሰረት አድርገው ከተገነቡና ክብረ በዓሉ ሲያልፍ ከተዘነጉ ከፍተኛ ወጪ ከወጣባቸው ስታዲየሞች አንዱ የሆነው የሰመራ ስታዲየም ሌላው የትኩረታችን አቅጣጫ ነው። ግንባታው ሐምሌ 18 ቀን 2009 ዓ.ም ነበር የተጀመረው በአራት ዓመት ውስጥ ለማጠናቀቅም እቅድ ተይዞለት ነበር። አንድ ቢሊዮን ብር የሚጠጋ በጀት የተያዘለት ስታዲየሙ፤ በሶስት ዓመት ለማጠናቀቅ ውል ተገብቶ ቢጀመርም ፤ በአሁኑ ወቅት 44 በመቶ ላይ ደርሶ ቆሟል። ይህም ስታዲየምም እንደሌሎቹ ሁሉ መጀመርን እንጂ መጨረስን መሰረት ያደረገ አልነበረም። ከላይ በማሳያነት የቀረቡትም ሆነ ይሄንኑ ዓላማ ማነጣጠሪያ አድርገው የተጀመሩት ሁሉ ግንባታቸው ከክብረ በዓሉ ማግስት ጀምሮ ተረስቷል። ምክንያቱ ደግሞ አነሳሱም ስፖርቱን ሳይሆን ፖለቲካውን የያዘ ከዛ ባለፈ ደግሞ የእርስ በእርስ ፉክክር የወለዳቸው ስለነበሩ ጣሪያ አልባ ሆነው የህዝብና መንግስትን ሀብት አላግባብ ሲባክንባቸው ቆይቷል። መቋጫ አልባው ጅማሮ በሀዋሳ ፣መቐለ፣ ባህርዳርና አዲስ አበባ የሚገኙ ስታዲየሞች የግንባታ ሂደት ምንም እንኳን ከላይ እንዳልነው ፖለቲካዊ አጀንዳን መሰረት አድርገው መጀመራቸው ለመጓተታቸው ምክንያት ቢሆንም ስፖርቱን ታሳቢ በማድረግ ግንባታቸው የተጀመሩቱም የችግሩ ሰለባ ከመሆን ካለመዳናቸውም በላይ ሙሉ ለሙሉ አለመጠናቀቃቸው ከካፍ መስፈርት ውጪ አድርጓቸዋል። ለዚህ ማሳያ ይሆን ዘንድ በባህር ዳርና መቐለ ከተማ እየተገነቡ የሚገኙት ስታዲየሞች የግንባታ ሂደት ዘርዘር አድርጎ መመልከቱ አስፈላጊ ይሆናል። ማቱ ሳላህ ትግራይ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ በ2003 ዓ.ም ነበር የተጀመረው። የስታዲየሙን ግንባታ ውጥን ከአስር ዓመት በፊት ቢጀመርም ቅሉ ዛሬም ግንባታው አልተጠናቀቀም። ህብረተሰቡ የግንባታው ሂደት መጓተቱን አስመልክቶ «ማቱሳላ» የሚል መጠሪያ ሰጥቶታል፡፡ በእርግጥ ከህዝብና መንግስት በተገኘ ገንዘብ የሚሰራ ግንባታ በዚህን ያህል ጊዜ ሲቆይ ስሙ ከዚህም በላይ ቢባል ያንሰዋል።የትግራይ ክልል ስፖርትና ወጣቶች ጽህፈት ቤት የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ገብረማርያም ዘሚካኤል ከወራት በፊት ለአዲስ ዘመን የሰጡት መረጃ እንደሚያመለክተው ፤ስታዲየሙን በ530 ሚሊዮን ብር ገንብቶ ለማጠናቀቅ ታስቦ ነበር ፤ የተለያዩ ችግሮች በማጋጠማቸው ግንባታው ተጓቷል ወጪውም ከታሰበው ከፍ ብሏል። በአሁኑ ወቅት የግንባታው የመጀመሪያው ምዕራፍ 90 በመቶ መድረሱንና ስድስት መቶ 57 ሚሊዮን ብር ወጪ መደረጉን ነበር የነገሩን። የግንባታው የመጀመሪያው ምዕራፍ አስር በመቶ የቀረው ቢሆንም ፤ ከ127 ሚሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ ወጪ አስወጥቷል። አቶ ገብረማርያም ፤የግንባታው ቀሪ 10 በመቶ ስራ «የፊኒሺንግ» ስራ ነው። ይሄውም የወንበር ገጠማና የሼድ ስራ ይቀራል፣ የመብራትና የድምጽ ሥርዓት፣ የካሜራ ሲስተም ዝርጋታና ጣሪያ የመግጠም ስራን ያጠቃልላል። ለዚህ ደግሞ የሚያስፈልገው ገንዘብ ግን ከ600 ሚሊዮን ብር ያላነሰ ነው። የግንባታው ሂደት መጓተት በህዝብና መንግስት ሀብት ላይ ጎትቶ ያመጣው ብክነት ግን ለትውልድ እዳ ይሆናል። የትግራይ ስታዲየምን መቋጫ አልባ የግንባታ ሂደት ተመለከትን እስቲ ወደ ባህር ዳር እንውረድ። ጣሪያ አልባው ስታዲየም የባህር ዳር ስታዲየም ግንባታ ታህሳስ 2 ቀን 2002 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን ፤የግንባታ ሂደቱ እንደሌሎቹ ሁሉ መጓተት ተስተውሎበታል። የባህርዳር ሁለገብ ስታዲየምን ለመገንባት በአማራ ክልል የቀድሞው ርዕሰ መስተዳድር አቶ አያሌው ጎበዜና በሚድሮክ ኢትዮጵያ ባለቤት በሼህ መሃመድ አላሙዲን አማካኝነት የውል ስምምነት ተፈርሞ በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ሙሉ ለሙሉ ይጠናቀቃል ቢባልም ይኸው እስከ አሁን አለ፡፡ 60ሺ ተመልካቾችን የመያዝ አቅም እንደሚኖረውም የተነገረለትና በሁለት ምዕራፍ ተከፍሎ በ700 ሚሊዮን ብር ሊገነባ ጉዞው የጀመረው ስታዲየሙ የመጀመሪያውን ምዕራፍ በ380 ሚሊዮን ብር ወጪም ነበር የተጀመረው።ስታዲየሙ ለክልሉ ብቻ ሳይሆን ሀገሪቱ ዓለም አቀፍና አህጉር አቀፍ ውድድሮችን ለማዘጋጀት የሚያስችል መሆኑ ብዙዎች እንዲናፈቁት ያደረገ ቢሆንም ከስድስት ዓመት በላይ ሳይጠናቀቅ አስቆጠረ። የአማራ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ጉዳይ ቢሮ የግንባታው ሂደት መዘግየቱን አምኖ ሁኔታው ግንባታው ሲጀምር በዕቅዱ ያልተካተቱ ተጨማሪ ማሻሻያዎች በመኖራቸው ነው ሲል ምላሽ ሰጠ። ያልተጠናቀቁ ሥራዎች ላይ ብቻ ሳይሆን በተጨማሪም ሁለት የእግር ኳስ ሜዳዎችን ሊገነቡ መታቀዳቸው ተናገረ፡፡በመሆኑም ከተቋራጮች ጋር የነበረው የስምምነት ዕድሳት እና ከስድስት ዓመታት በፊት የነበረው የግንባታ ግብዓት ወጪ ተመጣጣኝ ያለመሆኑ እንዲዘገይ አድርጎታል። ቢሮው ይሄንን ሲል መጓተቱን ተከትሎ የደረሰውን ያለ አግባብ ወጪ ሳይሸሽግ ተናገረ 2003 ዓ.ም የስታዲየሙ ግንባታ ሲጀመር በ380 ሚሊዮን ብር ቢሆንም አሁን ላይ 589 ሚሊዮን ብር ደርሷል። እንደምንም ብሎም ስታዲየሙ በ2009 ዓ.ም 86 በመቶ ላይ መድረስ ቻለ። በዚሁ ዓመት ደግሞ የስታዲየም ዋና አካል የሆነው የጣራና የወንበር ተከላ ሳይጠናቀቅ የአማራ ክልላዊ መንግስት ርክክብ መፈጸሙ ተሰማ። የአማራ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ጉዳይ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙሉአዳም ጌታነህ በወቅቱ፤ የተመልካች ወንበር ዝርጋታ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2009 ዓ.ም. ድረስ እንደሚጠናቀቅና በ2010 ዓ.ም የሽፋን ግንባታ በሚድሮክ ኢትዮጵያ ለማከናወንም ስምምነት መደረሱንና በቀሪው ግንባታ ተጨማሪ 400 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ ተናግረው ነበር። የጣሪያውም ሆነ የተመልካች ወንበር በተባለው ጊዜው ሳይጀመር ይኸው ሁለት ዓመት ተቆጠረ። የባህር ዳር ስታዲየም ግንባታ በከፊል ከተጠናቀቀ በኋላ ከሰባት ያላነሱ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ሲያከናውን ቆይቷል። ኢትዮጵያ ለምታስተናግደው እግር ኳሳዊ ውድድሮች ከዓለም አቀፍም ሆነ ከአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ዕውቅናና ተቀባይነት በማግኘት እነዚህ ጨዋታዎችን ማድረግ ቢቻልም፤ቀጣይ ጨዋታዎችን ለማድረግ ማሟላት የሚገባው መስፈርት መኖሩን ካፍ ከሰሞኑ በደብዳቤ አስታውቋል። የትግራይ ስታዲየምም በተመሳሳይ እጣ ፈንታ ላይ ተቀምጧል። ትኩረት ይሰጥ ዘንድ በአጠቃላይ በመላው አገሪቱ የሚገነቡት ስታዲየሞች አንዳቸውም ሙሉ ለሙሉ አልተጠናቀቁም። ከተመልካቾች መቀመጫና ውጫዊ ገጽታ ባሻገር የመጫወቻ ሜዳ ጥራት፣ አስፈላጊ ውስጣዊ ግንባታዎች አለመጠናቀቅ ዋጋ እያስከፈለ መጥቷል። በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች ተገንብተዋል የሚባሉትንና በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙት በአጭር ጊዜ ማጠናቀቅ ከተቻለ ለስጋቱ ምላሽ የሚሰጥ ይሆናል። በተለይ ደግሞ ዋነኛ አማራጭ ሆነው የቀረቡትን የትግራይና ባህር ዳር ስታዲየሞች ቀሪ ስራዎቹን በከፍተኛ ትኩረትና ርብርብ መስራትን የግድ ይላል ። ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ እስካሁን ለዚህ ችግር ዘላቂ የሆነ መፍትሄ ለማምጣት ያሰበው ነገር ከመናገር ይልቅ ትግራይና ባህርዳር ስታዲየም ጊዜያዊ ፍቃድ ማግኘታቸውን አጉልቶ ማውራትን ነው የመረጠው። ሆኖም ሀገሪቱ ከገባችበት ምጥ ለመውጣት የሚቻለው ዘለቄታዊ መፍትሄ ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት ነው የሚያስፈልገው::በሌላ በኩል ከወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ጋር በመቀናጀት ለመፍትሄው በአብሮነት መስራቱ በይደር መተው የለበትም። በየክልሉ ግንባታቸው ተጀምረው በትኩረት እጦት ቆመው የቀሩትን ስታዲየሞች በማስቀጠል በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቁ መስራት ያስፈልጋል። አዲስ\nዘመን ረቡዕ ነሐሴ\n8 / 2011 ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "c3a031b762f6a7cbdcc1b5162838e12e" }, { "passage": "የወቅቱ የዓለማችን ራስ ምታት የሆነው የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ወረርሽኝ ምክንያት ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በግል እንዲከወኑ ሁኔታዎች አስገድደዋል። ወረርሽኙ በኢትዮጵያ መሰራጨት መጀመሩን ተከትሎም ውድድሮች፣ ስልጠናዎችና ሌሎች ስፖርት ነክ ክንዋኔዎች ተቋርጠዋል። ስፖርተኞችን የሚያሰለጥኑ ክለቦችና ማዕከላትም ስፖርተኞቻቸውን በትነዋል። ከእነዚህ መካከል አንዱ የሆነውና ታዳጊ ወጣቶችን የሚያሰለጥነው ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ሰልጣኞቹን ወደ የመጡበት ከመለሰ ወራትን አስቆጥሯል። በስመ ጥሯ አትሌት የተሰየመውና የኢትዮጵያን አትሌቲክስ ከነ ክብሩ እንዲቆይ ለማድረግ የሚጥረው ማዕከል፤ በሌሎች ስፖርቶችም ታዳጊዎችን ሲያሰለጥን ቆይቷል። በዚህ ወቅት ሰልጣኞቹ ወደየመጡበት ቢመለሱም ስልጠናውን ሳያቋርጥ ቀጥሏል። ይህ እንቅስቃሴውም ለሌሎች የማሰልጠኛ ማዕከላትና ክለቦች መልካም ተሞክሮ ሆኖ ይነሳል::ቅድመ ዝግጅት ወረርሽኙ ወደ ኢትዮጵያ መግባቱን ተከትሎ በመንግሥት መመሪያ ከተሰጠበት ጊዜ አንስቶ የማሰልጠኛ ማዕከሉ ቀዳሚ ሥራ ስልጠናውን በማቋረጥ ከ14-17 ለሚሆኑ ቀናት ሰልጣኞችን በየመኖሪያ ካምፓቸው እንዲቆዩ ማድረግ መሆኑን የማዕከሉ ዳይሬክተር ዶክተር አመንሲሳ ከበደ ይናገራሉ። የማዕከሉ ሰልጣኞች ባሉበት ሆነውም በእጅ ስልኮቻቸው በሚላክላቸው መልዕክት መሠረት በየግላቸው እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ቆይተዋል። ከዚህ ጎን ለጎን ስለ ወረርሽኙ ምንነት እንዲሁም በምን መልኩ ሊከላከሉ እንደሚችሉ በማዕከሉ የጤና ባለሙያዎች ለሰልጣኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጥቷል። በመንግሥት በኩል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲሁም የስፖርት ሰልጣኞች ወደየመጡበት እንዲመለሱ ውሳኔ ላይ መደረሱ ሲሰማም ተቋሙ ሰልጣኞችን ወደየቤታቸው ሊሸኝ ችሏል። ሰልጣኞች ወደየመጡበት እንዲመለሱም ማዕከሉ የራሱን አስር ተሽከርካሪዎች ያዘጋጀ ሲሆን፤ የጤና ባለሙያዎችን በመመደብ፣ የፊት መሸፈኛ ጭምብል፣ ጓንት እንዲሁም ሳኒታይዘር በማቅረብ ሙሉ ጥንቃቄ በማድረግ እንደነበር ዳይሬክተሩ ያስታውሳሉ። በጉዟቸውም ከሌሎች ሰዎች ጋር ሳይገናኙ ወደ ቤተሰቦቻቸው እንዲቀላቀሉ ጥረት ተደርጓል። ከዚህ ባሻገር ሰልጣኞች የትምህርት ማስረጃዎቻቸውን እንዲሁም የስልጠና ቁሳቁሶቻቸውን ይዘው በመሄድ ባሉበት ሆነው ከእንቅስቃሴ እንዳይርቁ የሚያደርግ ስልጠናም ወስደዋል። ወርሐዊው የኪስ ገንዘባቸውም በባንክ ቁጥራቸው በኩል እንዲደርሳቸው እየተደረገም ነው።ድጋፍና ክትትሉ በምን መልኩ ቀጠለ? ሰልጣኞች ወደየመጡበት ከተመለሱ በኋላም ስልጠናው መቆም ስለሌለበት ማዕከሉ በቴክኖሎጂ የታገዘ (ቨርቹዋል) ስልጠናን ቀዳሚ አማራጭ አድርጎ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። በተለያየ ደረጃ ያለው አፈፃፀም የተለያየ ቢሆንም በሁሉም የስልጠና ክፍሎች ስልጠናውን ማስቀጠል እንደተቻለም ዳይሬክተሩ ያስረዳሉ። ከአንድ ወር ቆይታ በኋላም ሰልጣኞች ያሉበትን ሁኔታ ለመገምገም የሚያስችል ቅኝት በሁሉም የአገሪቷ አቅጣጫዎች በባለሙያዎች እየተደረገ ይገኛል። ይህ ዘገባ በተዘጋጀበት ወቅትም ሶስተኛ ዙር ጉዞ የተደረገ ሲሆን፤ ወደ አርባ ምንጭ፣ ወላይታ ሶዶ እና ሃላባ እንዲሁም በባህርዳር መስመር የተጓዙ የአሰልጣኞች ቡድን መኖሩንም ዳይሬክተሩ ይጠቁማሉ። ማዕከሉ የሰልጣኞች ምልመላ የሚያደርገው በመላ አገሪቷ እንደመሆኑ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ውስጥ 280 ሰልጣኞች ይገኛሉ። በቅኝቱም 22 አሰልጣኞች፣ ስድስት የሚሆኑ የህክምና ባለሙያዎች እንዲሁም የህዝብ ግንኙነትና የትምህርት ክፍል ባለሙያዎች በቡድን እየተከፋፈሉ ወደየስፍራው ይዘው በመጓዝ ድጋፍ ሊደርጉላቸው ችለዋል። ከቁሳዊው ድጋፍ ባለፈ በቅኝቱ ወቅት የተለዩና መሰል ችግር ያሉባቸው 13 ሰልጣኞችን ከቤተሰቦቻቸው ድረስ በመሄድ ውይይት በማድረግ ችግራቸውን ለመፍታትም ተሞክሯል። ከሰልጣኞች ባለፈ በማዕከሉ የስልጠና፣ የህክምና፣ የአስተዳደር እንዲሁም ሌሎች በርካታ ሥራዎችን የሚያከናውኑ ባለሙያዎች ይገኛሉ። በመሆኑም ወረርሽኙን ሊስፋፉ የሚችሉ ምንያቶችን ለማስወገድ ጥረት ተደርጓል።የማዕከሉ የማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት ስፖርት ሁሉንም ማህበረሰብ የሚያሳትፍ እንደመሆኑ ከስፖርተኞችና ባለሙያዎቹ ባለፈ ማህበረሰቡንም ያቀፈ እንቅስቃሴ ላይ በስፋት ይሠራል። ማዕከሉም ከሰልጣኞቹና ከማዕከሉ ማህበረሰብ ባሻገር በአካባቢው ለሚገኙ ነዋሪዎች በእውቀት እንዲሁም በቁሳቁስ እገዛዎችን በማድረግ ላይ ይገኛል። የጥሩነሽ ዲባባ ትምህርትና ስልጠና ማዕከል በሚገኝበት አርሲ ዞን በሚገኙት ሁሉም ወረዳዎች በማዕከሉ የህክምና ባለሙያዎች የታገዘ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ በስፋት እየተሠራ እንደሚገኝ ዳይሬክተሩ ይናገራሉ። ግንዛቤ ማስጨበጫውም ወረርሽኙን ከመከላከል ባለፈ አካላዊ እንቅስቃሴ የማድረግ ጠቀሜታ፣ በሽታን የመከላከል አቅምን ለማጎልበት ስለሚያስችሉ የአመጋገብ ሥርዓት እንዲሁም የንጽህና አጠባበቅን አስመልክቶ ስልጠና ይሰጣል። ከትምህርት ሰጪው መርሃ ግብር ውጭ የማዕከሉ ሠራተኞች ከሚያገኙት ላይ በመቀነስ ግምቱ 287 ሺህ ብር የሚያወጣ ቁሳቁስ አቅመ ደካማ ለሆኑ ነዋሪዎች በማበርከት፣ ደም በመለገስ፣ ችግኞችን በመትከልና መሰል እገዛዎችን በማድረግ ላይም ይገኛል። ቀጣይ አቅጣጫ በዓለም ላይ የተሰራጨው ይህ ወረርሽኝ በቅርብ ጊዜ ይጠፋል የሚል ግምት እንደሌለ ይታወቃል። ነገር ግን ምልመላ፣ ምዘና እና ስልጠናው በቀድሞው፣ ሁኔታ ባይሆንም መቀጠሉ አይቀርም። በመሆኑም ወረርሽኙን ታሳቢ ባደረገ መልኩ ይህንን እንዴት ማከናወን ይቻላል የሚል ሰነድ በባለሙያዎች እየተዘጋጀ መሆኑን ዶክተር አመንሲሳ ይጠቁማሉ። አሰልጣኞች በዚህ ወቅት እያደረጉ ያሉት የሰልጣኞች ቅኝት ይህንንም ታሳቢ ያደረገና ግብዓት የሚገኝበትም ነው። ከወረርሽኙ ጋር በተያያዘም በቀጣይ አሁን ካለው በባሰ ሁኔታ የሚስፋፋ ከሆነ የተቋሙ ህክምና ባለሙያዎች ለማህበረሰቡ እገዛ ለማድረግ እንዲሁም ማዕከሉ ለማገገሚያነት እንዲውል ካስፈለገ ዝግጁ ሆኖ በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኝም ዳይሬክተሩ ያስረዳሉ። አዲስ ዘመን ሰኔ 8/2012ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "07b3ce4afce78621205c8033e6b869c0" }, { "passage": "ስፖርት ብሄራዊ ስሜትን በማጠናከር አሊያም በማደብዘዝ ረገድ ሚናው ግዙፍ የሆነ ትልቅ ማህበራዊ ክንውን ነው። በብሄራዊ ስሜት ግንባታ ውስጥ የስፖርቱን የተለያዩ ሚናዎችን ያሳዩ በርካታ አጋጣሚዎች ይጠቀሳሉ። ስፖርት ብሄራዊ ስሜትን የመገንባት አቅምን ለመፍጠር የሚያ ስችል ስለመሆኑ እ.ኤ.አ የ2013ቱ የደቡብ አፍሪካ ዋንጫ ትልቁ ማሣያ ይሆናል። የዋልያዎቹ ከ31 ዓመታት በኋላ በአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ላይ መሳተፍ በእግር ኳሱ ውስጥ የብሄራዊ ስሜት ማነሳሳትን ሲፈጥር ታዝበናል። ኢትዮጵያዊነትን ከገባበት የተቀዛቀዘ ስሜት ውስጥ አውጥቶ ከዳር እስከ ዳር በሞቀ የአንድነት መንፈስ ሲያስፈነጥዝም ተመልክተናል። የልዩነት ነጋሪት ጉሰማውን ድምጽ የዋጠና የአንድነቱን ድምፀት ያጎላም ጭምር እንደነበር አይተናል። ይህ አጋጣሚ ስፖርት የወንድማማችነት፣ የወዳጅነትና የአንድነት ማጠናከሪያ አብነት ነው እየተባለ ሲነገር የነበረውን በተጨባጭ አሳይቷል። ከሰሞኑ አዲስ አበባ ውስጥ አንጋፋው የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ የተንፀባረቀው ሁኔታም ይህንኑ የሚያጠናክር ነው። «የስፖርት ጨዋነት ምንጮች» በሚል መሪ ቃል በሸራተን ሆቴል ለሁለት ቀናት በተካሄደው የምክክር ጉባዔ ላይ በርካታ ቁምነገሮች ተነስተዋል። በዚሁ ወቅት የሠላም ሚኒስትር ዴኤታ አልማዝ መኮንን እንዳሉት ስፖርት ለሠላም ዘብ የመሆኑን ጉዳይ በተገቢው መጠቀም ካልተቻለ በተቃራኒው ሲውል የሠላም ፀር መሆኑ አይቀሬ ይሆናል። «ስፖርት ትልቅ የሠላም ምንጭ ነው። ስፖርት በአንድ አገር ሠላም ሲደፈርስና መረጋጋት ሲታጣ ወደ ቀደመው ሁኔታ ለመመለስ ትልቅ አቅም አለው። ስፖርት የታመመን ፖለቲካ የማከም ከፍ ያለ ስጦታም አለው» ብለዋል። ሚኒስትር ዴኤታዋ የዓለም ነባራዊ ሁኔታን መሠረት በማድረግ ይህንን ይበሉ እንጂ፤ በኢትዮጵያ እየተስተዋለ ያለው አሁናዊ ሁኔታ ከዚህ ፍጹም ተቃራኒ ሲሆን እየተስተዋለ ነው። በተለይ በእግር ኳሱ ስፖርት ለሠላምና ለጤንነት የሚለው መርህ ተገልብጦ ለሁከትና ብጥብጥ ምንጭ ከሆነ ሰንበትበት ብሏል። ይህንኑ መነሻ በማድረግ ሚኒስትር ዴኤታዋ ለችግሩ ዘላቂ የሆነ መፍትሄ በመስጠት ሂደቱን መስመር ማስያዝ እንደሚገባ አሳስበዋል። የአገሪቱ እግር ኳስ ክፉኛ በሆነ መልኩ «ዘረኝነት» በሚባል ወቅት አመጣሽ በሽታ ሽምድምድ ብሎ ከስታዲየም ውጪ ተኝቷል። በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ክፉኛ ታሟል። ይህ ሁኔታ በዚህ ደረጃ ከቀጠለ እስከ ሞት ሊያደርሰው እንደሚችል በመድረኩ ላይ የታደሙ የዘርፉ ባለሙያዎች ምክረ ሃሳባቸውን ለግሰዋል። ኢንተርናሽናል ዳኛ ሊዲያ ታፈሰ በአገሪቱ እግር ኳስ ውስጥ ከዳኝነት ጋር ተያይዞ ዘርፈ ብዙ ችግሮች ይስተዋሉበታል። እነዚህም ለስፖርታዊ ጨዋነት መጓደል መንስዔ ይሆናሉ ሲሉ ገልፀዋል። ፖለቲካ እና እግር ኳሱ መለያየት እንዳለበት አፅንኦት የሰጡት ኢንተርናሽናል ዳኛዋ ዘረኞችን፣ ጎሰኞችን፣ ፖለቲከኞችን ከስፖርቱ ለይቶ መዳኘት አቅቶናል ሲሉ ችግሩ የቱን ያህል ውስብስብ ደረጃ ላይ መገኘቱን ጠቁመዋል። የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር የቦርድ ሊቀመንበር አቶ አብነት ገብረመስቀል የሥነ ምግባር መጓደልና ሥርዓት አልበኝነት እግር ኳሱን ከመጉዳት አልፎ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በጎሣ፣ በዘር፣ በሃይማኖትና በፖለቲካ አመለካከት ላይ ያተኮሩ ልዩነቶችና መቆራቆዞች እዚህም እዚያም እየተበራከቱ መጥተዋል፤ ስፖርት ከፍ ያለ የሞራል ልዕልናን የመጠየቁን ያህል በአግባቡ ካልተመራ በተቃራኒው ነውጠኝነትና ሥርዓት አልበኝነት ሊነግስበት ይችላል ብለዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ኢሣይያስ ጂራ በሰጡት አስተያየት እግር ኳሱ የሌላ አጀንዳ መናኸሪያ እየሆነ መጥቷል። ከስፖርታዊ መርህ ውጪ «የእከሌ ዘር ተሸነፈ፣ ይኸኛው ብሔር አሸነፈ» በሚል ጤናማ ያልሆነ አስተሳሰብ ላይ ደርሰናል ሲሉ የችግሩን አሳሳቢነት ገልፀዋል። አሰልጣኝ መሠረት ማኔ በበኩላቸው በስፖርቱ አደረጃጀት ላይ ትልቅ ክፍተት መኖሩን በመጥቀስ፤ ስፖርቱ በሙያተኞች አለመመራቱ ሌላው መሠረታዊ ችግር እንደሆነ ጠቁመዋል። የባህል ቱሪዝምና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሐብታሙ ሲሳይ «የመንግሥት የስፖርት ተቋማት ግንኙነት እስከምን ድረስ» በሚል ርዕስ ባቀረቡት ጽሁፍ ክለቦች በፖሊስ፣ በመከላከያ፣ በከተማ አስተዳደር፣ በማህበር እና መሰል አደረጃጀቶች እየተመሩ መገኘታቸው ለስፖርታዊ ጨዋነት መጓደል ተፅዕኖ ፈጥሯል ብለዋል። አንድ ክለብ ምን ምን መስፈርቶችን ማሟላት እንዳለበት በግልፅ ተለይቶ መቀመጥ ይገባዋል። ወጥ የሆነ ሕግም ያስፈልገዋል፤ ይህም አለመኖሩ ክፍተት መፍጠሩን አስረድተዋል። የዘረኝነትና ብሄርተኝነት\nበሽታ ውስጥ የሚገኘው\nየኢትዮጵያ እግር ኳስን\nለመታደግ በስፖርታዊ እንቅስቃሴ\nውስጥ የዘር ልዩነት\nእንዲጠፋ፣ የኦሊምፒክና የዓለም\nአቀፍ የስፖርት ማኅበራት\nደንብና መመሪያዎች እንዲከበሩ፣\nብሔርን መሠረት አድርገው\nየሚቋቋሙ ክለቦች ስማቸውን\nእንዲቀይሩ፣ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ\nኮሚቴን ጨምሮ ሌሎችም\nብሔራዊ ፌዴሬሽኖች መሪዎቻቸውን\nበችሎታና ብቃት ላይ ተመሥርተው\nእንዲመርጡ፣ ስፖርት በትምህርት\nቤቶችና ዩኒቨር ሲቲዎች\nእንዲስፋፋ የመድረኩ ተሳታ\nፊዎች ጠይቀዋል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 23/2011 በዳንኤል\nዘነበ", "passage_id": "b2493c458f0cd6efe1d08212c7749a73" }, { "passage": "የስፖርት ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው በእጅጉ እየጨመረ እንደመጣ ይታወቃል። የዓለም አገራት የስፖርት ሴክተሩን ዘርፈ ብዙ ፋይዳ በመረዳት ብቻ የሚቆሙ እንዳልሆኑ በዘርፉ ያስመዘገቡት ውጤት ማሳያ ነው። በዓለማችን በበርካታ አገራት ከሌሎች ሴክተሮች ባልተናነሰ መልኩ ለስፖርት ልማቱ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይን በማፍሰስ ስማቸውን በዓለም አቀፍ መድረክ ከፍ ብሎ እንዲጠራ ከማድረግ አልፈው ብዙ ማትረፍ ችለዋል፡፡ ለስፖርት ሴክተሩ ትልቅ ትኩረት መስጠት በማህበራዊ ፋይዳው አምራችና ጤናማ ዜጋን በማፍራት\nረገድ ያለውን ውጤት ከመረዳት ይመነጫል። በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚካሄዱ ትላልቅ ውድድሮች በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ከሚገኘው ድል ጀርባ\nለአገር ፖለቲካዊ ትርፍ ማጣጣም ማስቻሉንም መታዘብ ይቻላል፡፡ ስፖርተኞች ከውድድር ድል በኋላ የሚያገኙት ረብጣ የሽልማት ገንዘብና\nየአገር ኢኮኖሚን በማንቀሳቀስ የሚገኘው ትርፍም ቀላል አይደለም፡፡ የስፖርቱን ዘርፈ ብዙ ፋይዳን በጥልቅ በመረዳት የስኬት ማማ\nላይ የወጡ እንደ ጀርመን ያሉ አገራትን ማንሳት ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ለስፖርት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ረገድ ጀርመን\nበግንባር ቀደምነት ተጠቃሽ ናት። ይህች አገር ስፖርቱ በጠንካራ የፋይናንስ መሠረት ላይ ማቆም መቻሏ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ መሠረቱን\nሳይለቅ መጓዝ የቻለ አደረጃጀት መፍጠሯ ለስኬቷ ምክንያት ተደርጎ ይነሳል፡፡ የጀርመን መንግሥት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ከሚያፈስባቸው\nዘርፎች ዋነኛው ስፖርት ሊሆን የቻለውም ለዚህ ነው፡፡ ስፖርት በጀርመን ኢኮኖሚ ውስጥ 2 ነጥብ 2 በመቶ ድርሻ ይይዛል። ስፖርቱን በፋይናንስ\nአቅም እንዲጎለብት ከማድረግ በተጓዳኝ፤ ጠንካራ አደረጃጀት የተዘረጋለት ነው። በጀርመን የስፖርት ዘርፍ ይህን መልክ መላበሱ ከዘርፉ\nየሚገኘው ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ፋይዳ እንዲጎላ ማድረጉ ይነሳል። በኢትዮጵያ ለስፖርቱ ዘርፍ የተሰጠውን ትኩረትና ውጤት\nከሌሎች አገራት አንጻር እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡ በቀደሙት ጥቂት ዓመታት ለስፖርቱ ቅርብ ከሆኑ ሰዎች፣ ከመንግሥትና ከሌሎች\nባለድርሻ አካላት በኩል ኢትዮጵያ ለስፖርቱ ዘርፍ ተገቢ ትኩረት መስጠቷ ይነገራል፡፡ ለስፖርት ዘርፍ በተገቢው ደረጃ ትኩረት ተሰጥቶት\nእየተሰራ አለመሆኑንና የዘርፉ እድገት በቁልቁለት ጉዞ ውስጥ መሆኑም በሌላ ወገን ይነሳል። የስፖርት ሴክተሩ ውጤት አልባ መሆኑ\nግን ሁለቱንም ወገኖች እንደሚያስማማ ለመታዘብ ይቻላል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህም በመንግሥት ደረጃ ይኸው እውነታ ታምኖበት እየተሰራ\nስለመሆኑ በተደጋጋሚ እየተነገረ ይገኛል። በኢፌዴሪ ስፖርት\nኮሚሽን የዕቅድ በጀት ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እንድሪስ አብዱ፤ በአገሪቱ ባለፉት ሁለት የዕድገትና\nትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመናት ዘርፉ ለአገሪቱ ማበርከት ካለበት ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጠቀሜታዎች አንፃር በሚፈለገው\nደረጃ ላይ አለመገኘቱና ውጤቱም በመላ አገሪቱ ተደራሽነት ላይ ክፍተቶች መኖራቸው እንደታመነበት ይናገራሉ:: ለዚህም የስፖርት ሴክተሩን\nመሠረታዊ ችግር በተረዳ መልኩ የ10 ዓመት የስፖርት ሴክተር ስትራቴጂክ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እንዲሆን በኮሚሽኑ በኩል እንቅስቃሴ\nከተጀመረ መሰንበቱን ያስረዳሉ፡፡ ስፖርቱን ወደፊት\nለማራመድ እንቅፋት ከሆኑ መሠረታዊ ምክንያቶች መካከል በዋነኛነት ከአደረ ጃጀት፣ ከፋይናንስ፣ ከሰው ኃይል ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮች\nመሆናቸውን የጠቆሙት የኮሚሽኑ ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ምክትል ዳይሬክተር አቶ እንየው አሊ፤ የ10 ዓመቱ ስትራቴጂክ እቅድ የተጠቀሱትን\nክፍተቶች በጥናት እንዲመልስ ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑን ያስቀምጣሉ፡፡ ስትራቴጂክ ዕቅዱ አገራዊ የስፖርት ሪፎርምን መነሻ በማድረግ\nበስፋት የተዘጋጀ መሆኑንም ይገልፃሉ። በመሆኑም በአገሪቷ ቀጣይ የስፖርት እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ለውጥና ውጤት ማምጣት እንደሚያስችል\nታምኖበታል፡፡ የስፖርት ሴክተሩ ሪፎርም ፕሮግራም ዘርፍን መለወጥ የሚችሉ ብዙ ያመላከታቸው ነጥቦች እንዳሉም ያስረዳሉ። በዚህም\nከአደረጃጀት ፣ ከፋይናንስ፣ ከሰው ኃይልና ሌሎችም ጉዳዮች አንፃር ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት እንደሚቻል ተስፋ የተጣለበት መሆኑን\nይጠቅሳሉ፡፡ በሪፎርሙ ላይ የሴክተሩ ችግሮች የተለዩ ሲሆን በተመሳሳይ መፍትሄዎች መመላከታቸውንም ያክላሉ። ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ\nተግባራዊ የሚደረገውና ከስፖርት ሪፎርሙ የሚቀዳው የ10 ዓመቱ ስትራቴጂክ እቅድ ዘርፍን የተሻለ እንደሚያደርገውም ያላቸውን እምነት\nይገልፃሉ፡፡ አቶ እንድሪስ በበኩላቸው፤\nበቀጣይ ዓመት ተግባራዊ የሚደረገው ስትራቴጂክ ዕቅድ ትኩረት ያደረጋቸው አንኳር ጉዳዮች መኖራቸውን በመጥቀስ በሴክተሩ በቀጣይ\n10 ዓመታት በትኩረት የሚሰራባቸው ተብለው የቀረቡት ቁልፍ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች እንዳሉ ይናገራሉ:: በመጀመሪያ መንግሥታዊ የስፖርት\nአደረጃጀቶችን የመፈፀም እና የማስፈፀም አቅም በማጎልበት፤ የተለያዩ የሕግ ማዕቀፎችን እና የአሠራር ሥርዓቶችን ተግባር ላይ ማዋል\n፤ ሕዝባዊ የስፖርት አደረጃጀቶችን በዓለም አቀፍ እና በአገር አቀፍ መስፈርቶች መሠረት ማደራጀት የስትራቴጂክ እቅዱ ትኩረት መሆናቸውን\nያስቀምጣሉ:: በሁለተኛ ደረጃ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የማሰልጠኛ ማዕከላት ተደራሽነት፣ ሕጋዊነት እና ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን\nመሠረት በማድረግ በጥራት የሚገነቡበትን ስልት ሥራ ላይ ማዋል ትኩረት የሚሰጠው መሆኑን ያስረዳሉ። በአህጉር እና ዓለም አቀፍ የውድድር\nመድረኮች በተፈጥሮ ብቃታቸውን መሠረት በማድረግ አገራችንን የሚወክሉ እና ውጤታማ የሆኑ ተተኪ ስፖርተኞችን በሳይንሳዊ ስልጠናዎች\nማፍራት ትኩረት ተደርጎ የሚሰራበት ጉዳይ መሆኑንም ያብራራሉ፡፡ ስፖርት ለማህበራዊ ልማትና ለአገር ብልፅግና ፣ ለሕዝቦች መቀራረብ\n፣ ለገፅታ ግንባታ እና ለቱሪዝም ዕድገት መሣሪያ ሆኖ እንዲያገለግል ትኩረት ሰጥቶ መስራትም የስትራቴጂክ እቅዱ ቁልፍ ጉዳዮች ናቸው።\nበስትራቴጂክ ዕቅዱ የተጠቀሱትን አንኳር ጉዳዮች መሠረት አድርጎ የተዘጋጀው ግብ ወደ ተግባር መቀየር ከተቻለም የስፖርት ሴክተሩ\nውጤታማ መሆን እንደሚችል እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡የባህልና ቱሪዝም\nሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሀብታሙ ሲሳይ፤ በአገር አቀፍ የስፖርት ፖሊሲ ባለፉት ሁለት አስር ዓመታት የተመዘገቡ በርካታ አበረታች\nውጤቶች ቢኖሩም የአገራችን የስፖርት ዕድገት ከዕድሜው አኳያ ሲመዘን በሚፈለገው ደረጃ ባለማደጉ ብዙ መስራት እንደሚጠበቅ ያመላክታሉ።\nበአሁኑ ወቅት መንግሥት ስፖርቱን እንደ አንድ የልማትና ብልፅግና መሣሪያ አድርጎ በመውሰድ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ እየሰራ እንደሚገኝ\nየሚናገሩት አቶ ሃብታሙ ፤ የስፖርት ዘርፍ በታሪኩ በዚህ ደረጃ ትኩረት ተሰጥቶት እንደማያውቅ ያብራራሉ:: የብሔራዊ የስፖርት ምክር\nቤት በኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ሰብሳቢነትና የበላይ ጠባቂነት መመራቱ መንግሥት ለስፖርቱ ሴክተር የሰጠውን\nትኩረት እንደሚያሳይም ያስቀምጣሉ፡፡ በመሆኑም የስፖርት ዘርፍን ከትናንት በተሻለ መልኩ ዛሬ ትኩረት በማግኘቱ ዕድሉን በአግባቡ\nበመጠቀም ጠንክሮ መስራት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል፡፡አዲስ ዘመን አርብ ጥር 22/2012ዳንኤል ዘነበ\n", "passage_id": "03113203decaadfcc71b27a06362f673" } ]
e14c4527370b170a67dc2a94b63df019
3407396a6333f1b62dae159ed6064b4b
ከቅጣት ያመለጠው ታሪካዊ ጥፋት
ቦጋለ አበበእግር ኳስን በመሳሰሉ ተወዳጅና ንክኪ በሚበዛባቸው ስፖርቶች ተጫዋቾች በእንቅስቃሴ ውስጥ እያሉ አውቀውም ይሁን ሳያውቁ በተቃራኒ ቡድን ተጫዋቾች ላይ ጥፋት(ፋውል) ይሰራሉ። እነዚህ ጥፋቶች ከቀላል እስከ ከባድ የአካል ጉዳት ሊያስከትሉ የሚችሉና ያስከተሉበት አጋጣሚም በርካታ እንደነበር መመልከት ይቻላል። በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ወቅት ስፖርተኞች መሰል ጥፋት ሲሰሩ ውድድሩን በሚመሩ ዳኞች ከቢጫ የማስጠንቀቂያ ካርድ አስከ በርካታ ጨዋታዎች መታገድ ሊያደርሱ የሚችሉ ቅጣቶች ይከተሏቸዋል። ዳኞች አውቀውም ይሁን ሳያውቁ ከትንሽ እስከ ትልቅ ጥፋቶች በዝምታ ሲያልፉ የሚታይበት አጋጣሚም ጥቂት አይደለም። በዛሬው የስፖርት ማህደር አምዳችንም እኤአ በ1982 የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ ጨዋታ ወቅት የተከሰተውን ከባድና ታሪካዊ ጥፋት ከቅጣት የዳነበትን አጋጣሚ እንደሚከተለው እንዳስሳለን።ታሪካዊው ፈረንሳዊ ተጫዋች ሚሼል ፕላቲኒ ያሻገራት ኳስ ፓትሪክ ባቲስቶን ከጀርመኑ ግብ ጠባቂ ጋር አገናኘችው። በአጠገቡ ተከላካዮች የሉም፣ ከጨዋታ ውጭ አይደለም። የተከላካይን መስመር ሰንጥቆ ያለፈ ለጎል የተመቻቸ ያለቀለት ዕድል ነበር። ሄራርድ ሹማኸር ኳሷን ማዳን አለበት። አለበለዚያ ጀርመን ለዓለም ዋንጫው ፍፃሜ ላትደርስ ትችላለች። ከባቲስቶ ጋር ፊት ለፊት ተጋፈጠ። በረኛው እየተንደረደረ ኳሷን ተከትሎ ወደ ፈረንሳዊው መጣ። ሁለቱም ወደ አንድ አቅጣጫ ፈጠኑ። ሁለቱም የሀገሮቻቸው ጀግና ለመሆን በየፊናቸው እየሮጡ ነው…።የ1982ቱ የዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ነበር፣ ፈረንሳይ ከምዕራብ ጀርመን። ውጤቱ 1-1 እያለ ባቲስቶ ተቀይሮ ገባ። ከመግባቱ በፊት በተጠባባቂዎች ወንበር ላይ የምዕራብ ጀርመኑ በረኛ ባህሪይ አልተመቸውም ነበር። ከፈረንሳይ ተጫዋቾች ጋር ሲናቆር ታዝቦታል። የበዛ ግልፍተኛነት ይታይበታል። ከደቂቃዎች በኋላ አሰልጣኙ ወደ ጨዋታው አስገቡት። ከሰባት ደቂቃ በኋላም ከሹማኸር ጋር ተፋጠጠ። ፈረንሳዊያን ጎል ሲጠብቁ ሹማኸር ባለ በሌለ ጉልበቱ እንደ ፊጋ በሬ ተንደርድሮ በትከሻውና ዳሌው ተላተመው። ባቲስቶ ከሹማኸር ጉልበት ጋር አልተመጣጠነም። ከወገቡ በላይ ወደኋላው ተገፍትሮ አካሉን ሊቆጣጠር በማይችልበት ኃይል በጀርባው ከመሬት ተደባለቀ። በክርኑ መሬቱን የተደገፈው የቀኝ እጁ፣ ጣቶቹ እንደታጠፉ ቀና ብሎ ቀስ እያለ መሬቱ ላይ አረፈ። ከዚያም ተጫዋቹ በወደቀበት ሳይነቃነቅ በድን ሆነ። ግጭቱ እጅግ ከባድ ስለነበር ባቲስቶ ራሱን ሳተ። ሁለት ጥርሶቹ ወለቁ፣ ሶስት የጎድን አጥንቶቹ ተሰበሩ። በሜዳ ላይ የህክምና እርዳታ ሲደረግለት በተጫዋቹ ዙሪያ ሆነው አሰቃቂውን ጉዳት በቅርበት የሚከታተሉ የፈረንሳይ ተጫዋቾች ፊታቸውን ወደ ሹማኸር መለስ ቀለስ እያደረጉ ቁጣቸውን ይገልፃሉ። በረኛው ግን ከቁብም አልቆጠራቸው። በመጀመሪያ ወገቡን በእጆቹ ይዞ ባለበት ቆሞ ቆየ። ከዚያም ከሌላ የቡድን ጓደኛው ጋር ኳስ እየተቀባበለ ሰውነቱ እንዳይቀዘቅዝ ማድረጉን ቀጠለ። በኦክስጅን ጭምብል ከሜዳ እንዲወጣ ያስገደደ ከባድ ጥፋት ቢፈጽምም አርቢትር ቻርልስ ኮርበር ለሹማኸር ቀይ ካርድ ቀርቶ የማስጠንቀቂያ ካርድ እንኳን አልመዘዙበትም። ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ በረኛው በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የባቲስቶ ጥርሶች መውለቃቸውን ሲነግሩት ‹‹እኔ ወጪውን እሸፍናለሁ›› በሚል ስላቅ እብሪተኛነቱን ጨምሮ አሳየ። በወቅቱ አንድ ቡድን መቀየር የሚችለው ሁለት ተጫዋቾችን ብቻ በመሆኑ ሁለተኛው ተቀያሪ በጉዳት ከሜዳ የወጣበት የፈረንሳይ ቡድን አጋጣሚው ለፍፃሜ የመድረስ አቅሙን ክፉኛ አዳከመበት። በጭማሪ ሰዓት ፈረንሳይ አከታትላ ባስቆጠረቻቸው ሁለት ጎሎች 3-1 መምራት ብትችልም፣ አልሞት ባዮቹ ጀርመናዊያን ሁለት ጎሎች አግኝተው በ3-3 የመጨረሻ ውጤት ወደ መለያ ምት ሄዱ። ከዚያም የሹማኸር ምዕራብ ጀርመን ለፍፃሜው በቃች። አጋጣሚው በፈረንሳይ ህዝብ ዘንድ ፀረ-ጀርመን ጥላቻን ፈጠረ። ሹማኸር የፈረንሳይ ቁጥር አንድ ጠላት ሆነ። አንድ የሀገሪቱ ጋዜጣ በሰበሰበው የህዝብ መጠይቅ ሹማኸር ከናዚው አዶልፍ ሂትለር በላይ በዚያች ሀገር እንደተጠላ ተረጋገጠ። የጀርመኑ መራሔ መንግስት ሄልሙት ሽሚድት ቁጣውን ለማቀዝቀዝ ለፈረንሳዩ አቻቸው ፍራንሷ ሚቴሯ የቴሌግራም መልዕክት ላኩ። የጋራ መግለጫ ሊያወጡም ተገደዱ። ተጫዋቾቹም እንዲገናኙ ለማድረግ ሞከሩ። በሰዎች ግፊትም ይሁን ዘግይቶ በመጸጸቱ፣ ሹማኸር ተጎጂው ባለበት ሄዶ ይቅርታ ሊጠይቀው ቢሞክርም በጋዜጠኞች መገኘት ምክንያት ያሰበውን ያህል ሳይሳካለት ቀረ። አሁን ባቲስቶ ከስልሳ ዓመት ያለፈው ጎልማሳ ሆኗል። ጉዳቱ በጀርባ አጥንቱ ላይ የፈጠረው አደጋ እስካሁንም የህመም ስሜት እንዳለው ይናገራል። ራስ ምታት ልማዱ ነው። በቃሬዛ ከወጣ በኋላ የተከናወነውን ቀሪ የጨዋታ ፊልም ላለማየት ወስኖ ቢቆይም በመጨረሻ ከሰላሳ ዓመታት በኋላ ተመልክቶታል። ወደ እርጅናው የተጠጋው ሹማኸርም አሁን ደርሶ በአጋጣሚው መጸጸቱን ይናገራል። ከጨዋታው ሁለት ዓመት በኋላ፣ በ1984፣ ፈረንሳይና ምዕራብ ጀርመን በወዳጅነት መርሃ ግብር ተገናኙ። ከጉዳቱ በኋላ ወደ ጨዋታ የተመለሰው ባቲስቶ በድጋሚ በብሔራዊው ማሊያ ከሹማኸር ጋር በተቃራኒ ቆመ። በመጨረሻ ሁለቱ ሰዎች ማሊያ ተቀያየሩ። ቅይይሩ ግን በህዝብና በሚድያው ፊት ሳይሆን በተጫዋቾች መልበሻ ቤት ውስጥ፣ ብቻቸውን ያደርጉት ነበር።አዲስ ዘመን ታህሳስ 4/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=37293
[ { "passage": " የመከላከያው ድንቅ አማካይ ተክለወልድ ፍቃዱ ከቢሾፍቱ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በደረሰበት የመኪና አደጋ ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል፡፡ በአደጋው የተክለወልድ ወንድም አብሮት የነበረ ሲሆን እሱም ህይወቱ አልፏል፡፡አደጋው ሲደርስ በቦታው የነበረ ያሬድ የተባለ የአይን እማኝ ለኤፍኤም 97.1 የተናገረው እንዲህ ባለ መልኩ ነበር ‹‹ አደጋው የደረሰው ትላንት ከምሽቱ 2፡00 አካባቢ ነበር፡፡ በመኪናው ውስጥ 5 ሰዎች የነበሩ ሲሆን ተክለወልድ እና ወንድሙ ጋቢና ውስጥ ነበሩ፡፡ መኪናው መንገዱን ስቶ ከግንድ ጋር ሲላተም ጋቢና የነበሩት ወንድማማቾች ወድያው ሲሞቱ ከኋላ ተቀምጦ የነበረው አንደኛው እግሩ ተቆርጧል፡፡ ›› ሲል ስለ አደጋው አብራርቷል፡፡የ24 አመቱ የቀድሞው የአየር ኃይል አማካይ በቅርብ አመታት ከታዩ ባለ ድንቅ ክህሎት አማካዮች አንዱ የነበረ ሲሆን በመልካም ባህርዩ በርካቶች የሚያወድሱት ድንቅ ተጫዋች ነበር፡፡ሶከር ኢትዮጵያ ለቤተሰቦቹ ፣ ለአድናቂዎቹ እና ለመከላከያ ስፖርት ክለብ አባላት መፅናናትን ትመኛለች፡፡", "passage_id": "1b31fbbc2e0ccd75828585008dfec28e" }, { "passage": "በአዲስ አበባ ከተማ ሲኤምሲ አካባቢ ወደ ሰሚት ለስላሳ ፋብሪካ በሚያመራው መንገድ ላይ ሐሙስ መጋቢት 1 ቀን 2008 ዓ.ም. በዩሮትራከር ከባድ የጭነት ተሽከርካሪ አደጋ ያደረሰ ሾፌር፣ ሰሚት ፔፕሲ አደባባይ ሲደርስ ከየረር ጎሮ ወደ ሰሚት የተገነባ የመንገድ መከለያ ግንብ በመደርመስ በአራት ሰዎች ሕይወት ማጥፋት በመጠርጠሩ እጁን ለፖሊስ ሰጠ፡፡አሽከርካሪው የመንገዱን ግንብ ሲገጭ ከየረር ጎሮ በኩል አራት ሰዎችን አሳፍሮ ወደ ሰሚት አደባባይ በመጓዝ ላይ በነበረ አንድ ባጃጅ ላይ በመገልጠቡ፣ የባጃጁ አሽከርካሪና ሦስት ተሳፋሪዎች ወዲያውኑ ሕይወታቸው ማለፉ እንደተረጋገጠ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ ምክትል ኢንስፔክተር አሰፋ መዝገቡ ገልጸዋል፡፡አሰቃቂው የትራፊክ አደጋ ሊደርስ የቻለው በተሽከርካሪው የቴክኒክ ችግር ይሁን ወይም በአሽከርካሪው ብቃት ማነስ ለማረጋገጥ ገና እየተሠራ መሆኑን የገለጹት የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያው፣ ከአደጋው አደራረስ ለመገመት እንደተቻለው ተሽከርካሪው ከፍተኛ ፍጥነት ላይ ሳይሆን እንዳልቀረ ግምት መወሰዱን አስረድተዋል፡፡ አደጋው በደረሰበት ወቅት የከባድ ተሽከርካሪው ሾፌር ለጊዜው ተሰውሮ የነበረ ቢሆንም፣ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ሄዶ እጁን መስጠቱን ምክትል ኢንስፔክተር አሰፋ ጠቁመዋል፡፡በአካባቢው የነበሩ የዓይን እማኞች ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ በግምት ከቀኑ 9፡30 ሰዓት ሲሆን ከአያት መንገድ ወደ ቀኝ ታጥፎ በከባድ ፍጥነት ሲሽከረከር የነበረው ከባድ የጭነት ተሽከርካሪ ሾፌር ቀጥ ብሎ ነው አደባባዩ ላይ የወጣው፡፡ ሰሚት ፔፕሲ አደባባይ ሲደርስ ወደ ሰሚት ኮንዶሚኒየም፣ ወደ አያት፣ ወደ ተባበሩትና ወደ የረር ጎሮ የሚታጠፉ መንገዶች መኖራቸውን የጠቆሙት እማኞቹ፣ የጭነት ተሽከርካሪው ከላይ እየበረረ መጥቶ አራት አቅጣጫ ያለው መንገድ ላይ ሲደርስ ወደሚፈልገው መታጠፍ ባለመቻሉ፣ ከፊት ለፊቱ ያገኘውን የመንገድ መከለያ ግንብ ደርምሶ መገልበጡን አስረድተዋል፡፡ በወቅቱ ከየረር ጎሮ ወደ ሰሚት ፔፕሲ አደባባይ ለመታጠፍ የደረሰው ባጃጅ ግንቡ ሥር ደርሶ ስለነበር፣ ግንቡ እንደተደረመሰበት ተናግረዋል፡፡ዩሮትራክተሩ ሲገጨው የተደረመሰው የመንገድ መከለያ ግንብ የተገነባው በሚድሮክ ኮንስትራክሽን ሲሆን፣ ግንባታው ረጅም ጊዜ ወስዶ በ2001 ዓ.ም. ተጠናቆ መመረቁ ይታወሳል፡፡የመንገድ መከለያ ግንቡ ሲደረመስ ለጥንካሬ የሚረዳው ምንም ዓይነት ብረት እንዳልተካተተበት ለማየት ተችሏል፡፡ የመንገድ መከለያ ግንብ ከመከለያነት በተጨማሪ ጥንካሬ ኖሮት ግጭት መከላከል እንዳለበት ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ ስለግንባታውና ስለሚጠቀሙት የግንባታ ማቴሪያል ሁኔታ ማብራሪያ እንዲሰጡ፣ የአዲስ አበባ መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ፍቃዱ ኃይሌን ለማነጋገር ሪፖርተር ያደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡በኢትዮጵያ እየደረሰ ያለውን የትራፊክ አደጋን በሚመለከት መጋቢት 1 ቀን 2008 ዓ.ም. የመንግሥትን የስድስት ወራት ሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ፣ ‹‹በዓለም ደረጃ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ የአገራችን ሕዝቦች ሕይወት በመኪና አደጋ እየተቀጠፈ ነው፡፡ ይህንን እጅግ አሳሳቢ የሆነና ኢትዮጵያን ከዓለም ሕዝቦች የተለየች ሆና እንድትታይ ማድረጉንና ማንኛውም ወረርሽኝ በሽታ እንኳን የማይቀጥፈውን ሕዝብ እየቀጠፈ ያለ አደጋ ለመቀነስ መሥራት ይገባል፤›› ማለታቸው ይታወሳል፡፡", "passage_id": "fc897969a21c8e69f4f4991ab1c2167b" }, { "passage": "ያልተጠበቁ እና ተጫዋቾች ከሚሳተፉበት ውድድሮች ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ውጪ የሆኑ ጉዳቶች በማንኛውም ቦታ እና ጊዜ ሊያጋጥሙ ይችላሉ። ግብ ከተቆጠረ በኋላ ከሚደረጉ የደስታ አገላለፅ ትዕይንቶች ጀምሮ ወደ መጫወቻ ሜዳ ጥሰው በገቡ እንስሳት ምክንያት በሜዳ ውስጥ ተጫዋቾችን ላልተለመዱ ጉዳቶች ሲዳርጉ ተመልክተናል። ከእግርኳስ ሜዳ ውጪም በተለያዩ የዕለት ተለት ተግባሮች ላይ የሚገኙ ተጫዋቾች በአስገራሚ አጋጣሚዎች ለረጅም ጊዜ ከጨዋታ እንዲገለሉ ያስገደዷቸውን ጉዳቶች ሲያስተናግዱ ተመልክተናል። ከእግርኳስ ጋር የተያያዙ የህክምና ጉዳዮችን በምንዳስስበት የሶከር ሜዲካል አምዳችን የዛሬ ዕሁፍ ከሜዳ ውጭ ያጋጠሙ እና በወቅቱም የመገናኛ ብዙሃንን ትኩረት ስበው የነበሩ ጉዳቶችን የሚያስታውስ ይሆናል። ለዚህም ‘The Secret Footballer: What the physio saw’ የተሰኘውን መጽሃፍ በዋቢነት ተጠቅመናል።ስፔናዊው ግብ ጠባቂ ሳንቲያጎ ካኒዛሬስ በክለቡ ቫሌንሲያ ባሳየው ጥሩ ብቃት በ2002ቱ የዓለም ዋንጫ የብሔራዊ ቡድኑ ቋሚ ተሰላፊ እንደሚሆን በሚጠበቅበት ወቅት ዕድለቢስ ያደረገውን ጉዳት አስተናግዷል። ተጫዋቹ ፂሙን በሚላጸጭበት ሰዓት ወድቆ በተሰበረ መስታወት እግሩ ላይ ጉዳት ስለደረሰበት ከውድድሩ ለመቅረት ተገዷል።እንግሊዛዊዉ ግብ ጠባቂ ዴቪድ ጄምስ ደግሞ ሪሞት ኮንትሮል ለማንሳት ሲንጠራራ የጀርባ ጡንቻዉ በመሳቡ ጉዳት አጋጥሞታል። አሌክስ ስቴፕኒ የተባለው በ1970ዎቹ ሲጫወት የነበረ የማንችስተር ዩናይትድ ግብ ጠባቂ በሚጮህበት ወቅት የአገጩ መገጣጠሚያ ተላቆ ለጉዳት ተዳርጎም ነበር። አሜሪካዊው ግብ ጠባቂ ኬሲ ኬለር በበኩሉ የጎልፍ መጫወቻ ዱላ በሚያወጣበት ሰዓት አፉን በመምታቱ የፊት ጥርሱ ረግፏል።ኬቨን ካይል እና አደም ቻፕማን የተባሉት ተጫዋቾች ያጋጠማቸው ጉዳት ደግሞ ከህፃናት ልጆቻቸው ጋር የተያያዙ ነበሩ። የስኮትላንዱ ኪልማርኖክ ክለብ አጥቂ የነበረው ኬቨን እ.ኤ.አ. በ2006 የ8 ወር ህጻን ልጁ በደፋበት የሞቀ ውሃ በመቃጠሉ አንድ ሌሊት በሆስፒታል ተኝቶ ለማሳለፍ ተገዶ ነበር። እንግሊዛዊው የአማካይ ስፍራ ተጫዋች አደም ቻፕማን በበኩሉ ለህጻን ልጁ ወተት በሚያዘጋጅበት ጊዜ የጡጦውን ክዳን መክደን በመዘንጋቱ ትኩስ ወተት ተደፍቶበት ተመሳሳይ ጉዳት ደርሶበታል፡፡ታዎቂው የቀድሞ የእንግሊዝ እንደዚሁም ማንችስተር ዩናይትድ ተከላካይ ሪዮ ፈርዲናንድ ለሊዲስ ዮናይትድ በሚጫወትበት ጊዜ በቤቱ ለረጅም ሰዐት በአንድ አይነት አቀማመጥ ሆኖ የቪድዮ ጌም በመጫወቱ የጉልበቱ ጅማት ላይ ጫና በዝቶበት ለሳምንታት ከሜዳ ያራቀው ጉዳት አስተናግዷል።ኢኳዲሪያዊው አጥቂ ኤነር ቫሌንሺያ የተሰበረ ሲኒ በመርገጡ የእግር ጣቱ ላይ ጉዳት አጋጥሞት ነበር። ዲሪክ ላይል የተሰኘው የስኮትላንዱ ክለብ ደንዲ ዩናይትድ ተጫዋች ቤቱ ውስጥ የነበረ የመስታወት ጠረጴዛ ላይ በመውደቁ ወሳኝ የሆነ የግማሽ ፍጻሜ ግጥሚያ እንዲያመልጠው ሆኗል።  በ1960ዎቹ የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች የነበረው አለን መሪ ሀገር ሰላም ብሎ ጥርሱን በሚፍቅበት ወቅት በጡንቻ መሳሳብ ምክንያት ጀርባው ላይ ጉዳት ገጥሞታል።ከላይ ከተጠቀሱት ምሳሌዎች ማየት እንደምንችለው ለወራት ከሜዳ ሊያርቁ የሚችሉ ጉዳቶች በማንኛውም ሰዓት ሊያጋጥሙ ይችላሉ። ተጫዋቾቻችንም ከሜዳ ውጭ በሚኖረው ህይወታቸው በእያንዳንዱ እንቅስቃሴያቸው አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ፤ በተለይም ከባድ ዕቃዎችን እንደመሸከም ያሉ ስራዎችን ባለመስራት፣ እንቅስቃሴ ሳያደርጉ በአንድ አቀማመጥ ለረጅም ጊዜ ባለመቆየት እና የመቁረጥ እና የመውጋት ጉዳት ሊያደርሱ የሚችሉ ቁሶችን በጥንቃቄ በመጠቀም ራሳቸውን ከተለያዩ ጉዳቶች መጠበቅ ይኖርባቸዋል። እግርኳስ ተጫዋቾች ሰዉነታቸው እና የአካል ብቃታቸው ገንዘባቸው ስለሆነ የቻሉትን ሁሉ እንክብካቤ እንደዚሁም ጥንቃቄ ሊያደርጉለት ይገባል።", "passage_id": "7eda7514e042f4d7ef5ae32c279ccf1f" }, { "passage": "\nበዚህ በዩናይትድ ስቴትስ በቦስተን ማርቶን ከአንድ ዓመት ተኩል በፊት በሁለቱ ወንድማማቾች Dzhokhar እና Tamerlan Tsarnaev ከደረሰው የቦምብ ፍንዳታ ጋር በተያያዘ “ለመርማሪዎች ዋሽቷል፤” በሚል ተወንጅሎ ለሳምንታት ጉዳዩ ሲታይ የቆየው ሮቤል ፊሊጶስ በሁለት ወንጀሎች ጥፋተኛ ሆነ።የከሳሽ አቃቤ ኅግና የተከሳሹ ሮቤል ፊልጶስ የኅግ ጠበቆች ለሁለት ሳምንታት ያቀረቧቸውን መከራከሪያዎች የሰማውና አሥራ ሁለት ሠዎች ያሉበት ለዳኝነቱ ከነዋሪው ሕዝብ የተመረጠው ቡድን በዛሬው እለት ብያኔውን ለችሎቱ አሰምቷል። ብያኔውንና ቀጣዩን ሂደት በተመለከተ የተከሳሹን ዋና ጠበቃ አቶ ደረጀ ሰምሴ ቡልቶን አነጋግረናል።", "passage_id": "c42bb57e2581c4d0d967a596eafa82aa" }, { "passage": "እኤአ 1995 ጃፓን ዋና ከተማ ቶኪዮ የምድር ውስጥ ባቡር ተሳፋሪዎች ላይ የሳሪን መርዝ ጥቃት አድርሶ ሰዎች የገደለው አምልኮ ቡድን መሪ ዛሬ በስቅላት መቀጣቱ ተሰማ።“ሾኮ አሳሃራ” በሚል ተለዋጭ ስም የሚጠራው ቺዞ ማትሱሞቶ ዛሬ መሰቀሉን የጃፓን መንግሥት ቃል አቀባይ አስታውቋል።በዘገባዎች መሰረት ሌሎችም የዚሁ የምጽዓት ቀን አምልኮ በርካታ አባላት እንደተሰቀሉ ነው ዘገባዎች ያመለከቱት። ምን ያህል እንደሆኑ አልታወቀም።ባለቤታቸው ከሃያ ሦስት ዓመታት በፊት በደረሰው በመርዝ ጥቃቱ የሞቱባቸው አንዲት ሴት ቅጣቱ ይህን ያህል ዘመን መዘግየቱ ያሳዝናል ብለዋል።ቶኪዮን ባሽመደመዳት የመርዝ ጥቃት ከአሥራ ሁለት የሚበልጡ ሰዎች ሲሞቱ ከስድስት ሺህ የሚበልጡ ሰዎች እንደታመሙ ይታወሳል።", "passage_id": "04df162fce5d4372e810158cdbb07db3" } ]
e482a9b918a1d06c463ec3ea3436d092
bd9d938962843a2319cf059722b904bd
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተሰበሩ ከሚገኙ የዓለም ክብረወሰኖች ጀርባ
ቦጋለ አበበበኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስጋት ለበርካታ ወራት ተቋርጠው የቆዩ ዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድሮች ካለፈው ሐምሌ መጨረሻ ጀምሮ በሂደት ወደ መደበኛ መርሃግብራቸው እየተመለሱ ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ውድድሮች በተመለሱበት ጥቂት ወራትም በተለይም የረጅም ርቀት የዓለም ክብረወሰኖች ለማመን በሚቸግር መልኩ ሲሰበሩ እየተስተዋለ ይገኛል፡፡ ይህም የስፖርቱን አፍቃሪዎች ከማነጋገሩ ባሻገር ተንታኞች ጭምር ግራ እንዲጋቡ ያደረገ ክስተት ሆኗል፡፡ በተለይም የዓለም ግማሽ ማራቶን ክብረወሰን ከወረርሽኙ በፊትም ቢሆን ከሌሎች ርቀቶች በተለየ በሁለቱም ፆታ በተደጋጋሚ ሲሰበር መስተዋሉ አነጋጋሪ አድርጎታል፡፡ የዓለም ግማሽ ማራቶን ክብረወሰን በዓለም አትሌቲክስ እኤአ ከ2004 አንስቶ እውቅና እየተሰጠው ከመጣ ወዲህ በወንዶች አምስትና በሴቶች ስድስት የዓለም ክብረወሰኖች ተመዝግበዋል፡፡ ከዚህ ዓመት በፊት በርቀቱ የተመዘገቡ ሰዓቶች በዓለም አትሌቲክስ ‹‹የዓለም ፈጣን ሰዓት›› በሚል ይታወቅ ነበር፡፡ የወንዶች ግማሽ ማራቶን የዓለም ክብረወሰን ባለፈው እሁድ በቫሌንሲያ የተመዘገበ ሲሆን ኬንያዊው አትሌት ኪቢዎት ኬንዲ 57፡32 በሆነ ሰዓት የክብረወሰኑ ባለቤት ሆኗል::የሴቶቹ ደግሞ ባለፈው የካቲት በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች የራስ አል ኪማህ ግማሽ ማራቶን ውድድር ላይ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት አባብል የሻነህ በ1፡04፡31 በሆነ ሰዓት ያስመዘገበችው ነው፡፡ ይህም በጥቅምት 2017 ኬንያዊቷ ጆይስሊን ጂፕኮስጌ በቫሌንሲያ ግማሽ ማራቶን ካስመዘገበችው የቀድሞው የዓለም ክብረወሰን በሃያ ሰከንድ የተሻለ ነበር፡፡ በመስከረም 2019 ሌላኛዋ  ኬንያዊት ብሪጊድ ኮስጌ በኒውካስትል ታላቁ ሩጫ 64፡28 በሆነ ሰዓት ከቀድሞው ክብረወሰን በሃያ ሦስት ሰከንድ የተሻለ ፈጣን ሰዓት ብታስመዘግብም የዓለም አትሌቲክስ ለክብረወሰኑ እውቅና አልሰጠውም። እኤአ ከ2011 ጀምሮ የዓለም አትሌቲክስ የሴቶች ግማሽ ማራቶን ክብረወሰኖችን በሴትና በወንድ አሯሯጭ የተመዘገቡ ብሎ በሁለት ከፍሏቸዋል።  በሴት አሯሯጮች የተመዘገበው የርቀቱ ክብረወሰንም በኬንያዊቷ አትሌት ፔርስ ጂፕቺርቺር 1፡05፡16 በሆነ ሰዓት ከወር በፊት በፖላንድ ጊዲኒያ የዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮና የተመዘገበ ነው። ባለፈው ሐምሌ መጨረሻ ለአስራ ስድስት ዓመታት ያልተደፈረው የቀነኒሳ በቀለ የአምስት ሺ ሜትር ክብረወሰን በዩጋንዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቺፕቴጌ ሞናኮ ላይ ከተሰበረ ወዲህ የዓለም ክብረወሰኖች በተለይም በረጅም ርቀት ውድድሮች እንደልብ የሚሰበሩ ሆነዋል። ከዩጋዳዊው ያልተጠበቀ ክብረወሰን በኋላ አንድ ወር ባልሞላ ልዩነት ትውልደ ሶማሊያዊው የእንግሊዝ አትሌት ሞ ፋራህ እኤአ 2007 ላይ በጀግናው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ተይዞ የቆየው ‹የአንድ ሰዓት ውድድር› የዓለም ክብረወሰን ብራሰልስ ዳይመንድ ሊግ ላይ ከ21፡330 ወደ 21፡285 ተሻሽሏል። በተመሳሳይ ርቀት እንዲሁም በተመሳሳይ ቀንና ውድድር በኢትዮጵያዊቷ አትሌት ድሬ ቱኔ 18፡930 ተይዞ የቆየው የዓለም ክብረወሰን በትውልደ ኢትዮጵያዊቷ የኔዘርላንድስ አትሌት ሲፈን ሃሰን 18፡517 በሆነ ሰዓት ተሻሽሏል። የሁለቱ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የአንድ ሰዓት ውድድር የዓለም ክብረወሰኖች በተሰበሩ በአንድ ወር ልዩነት ዩጋንዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቺፕቴጌ ለአስራ አምስት ዓመታት ያልተደፈረውን የቀነኒሳ በቀለ የአስር ሺ ሜትር ክብረወሰን በ6፡53 ሰከንድ መስበር ችሏል። በተመሳሳይ ቀን ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ለተሰንበት ግደይ በሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌትና የረጅም ርቀት ንግስት ጥሩነሽ ዲባባ ለአስራ ሁለት ዓመታት ተይዞ ሳይሰበር የቆየውን የአምስት ሺ ሜትር ክብረወሰን 14፡06 በሆነ ሰዓት ሰብራዋለች። ኬንያውያን አትሌቶችም ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ በኋላ ባንሰራራው የአትሌቲክስ ውድድር የክብረወሰን ተቋዳሽ ናቸው። ለዚህም በዓለም ግማሽ ማራቶን በአርባ ሁለት ቀናት ልዩነት ሁለት የዓለም ክብረወሰኖችን የጨበጠችው ኬንያዊቷ ፔስር ጂፕቺርቺር ትክክለኛ ማሳይ ናት። መስከረም ላይ በፓራጓይ ግማሽ ማራቶን የሴቶችን ብቻ የርቀቱን የዓለም ክብረወሰን በ1፡05፡24 ሰዓት ያሻሻለችው ኬንያዊት አትሌት ከአርባ ሁለት ቀናት በኋላ በፖላንድ ጊዲኒያ የዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮና የራሷን ክብረወሰን በአስራ ስምንት ሰከንድ ማሻሻል ችላለች። እነዚህ ሁሉ ክብረወሰኖች ሲሰባበሩና አትሌቶች በተለየ መልኩ አስደናቂ ብቃት ሲያሳዩ አብዛኛው የስፖርት ቤተሰብ ሁለት ነገሮችን ጠርጥሯል። ይህም በወረርሽኙ ምክንያት አትሌቶች ለረጅም ጊዜ ከውድድር በመራቃቸው ሰፊ የዝግጅት ጊዜ በማግኘት ወደ ውድድር ሲመለሱ ምርጥ ብቃት ሊኖራቸው እንደቻለና በነዚያ የረፍት ጊዜያት በጉዳት ላይ የነበሩ አትሌቶች በበቂ ሁኔታ ማገገም በመቻላቸው እንደሆነ ይታሰባል። ስፖርቱን በጥልቀት የሚመለከቱ በርካታ ተንታኞች ግን ከዚህም የበለጡ ገፊ ምክንያቶች ከክብረወሰኖቹ መሰባበር ጀርባ እንዳሉ ያምናሉ። የልምምድ ስነልቦናና ሂደት በወረርሽኙ ምክንያት እየተለወጠ መምጣቱ ለክብረወሰኖቹ መሻሻል አንድ ምክንያት ተደርጎ ይወሰዳል። ይህም የወረርሽኙ ስጋት ቀደም ብሎ አትሌቶች በርከት ብለው በአንድ አሰልጣኝና በአንድ ካምፕ ውስጥ ሆነው የሚያደርጉትን የተለመደ ዝግጅት ወደ ጎን ትተው በተናጠል በሚመቻቸው ስፍራና በቤታቸው ሆነው እንዲዘጋጁ እድል መስጠቱ ነው። ይህ አጋጣሚ አትሌቶች አንዱ አንዱን ሳይጠብቅ በራሳቸው መርሃግብር መሰረት ወጥ በሆነ መልኩ እስከ አቅማቸው ጥግ ድረስ እንዲዘጋጁ ያስቻላቸው ሲሆን በስነልቦናውም ረገድ ጠንካራ እንዲሆኑ አድርጓል። ለዚህም ከወረርሽኙ በኋላ ክብረወሰኖችን ያሻሻሉ አትሌቶች ቀደም ሲል ይከተሉት የነበረው የልምምድ መልክ በወረርሽኙ ሳቢያ መቀየሩ ለክብረወሰኖች መሻሻል ቁልፍ ሚና እንዳለው የሚያስቀምጡ ባለሙያዎች በርካታ ናቸው። በሌላ መልኩ አትሌቶች በወረርሽኝ ምክንያት ውድድሮች ቢቆሙም የሆነ ጊዜ ላይ እንደሚቀጥሉ አውቀው ዝግጅታቸውን ሳያቋርጡ ተግተው መስራታቸው የክብረወሰን ባለቤት እንዳደረጋቸው ይታመናል። አትሌቶች ወረርሽኙ የጤና ስጋት ቢሆንም መጥፎን አጋጣሚ ወደ ጥሩ ለውጠው ተጠቅመዋል። አቋማቸው እንዳይወርድ በመጠንቀቅ መዘጋጀታቸው ኋላ ላይ ለስኬት አብቅቷቸዋል። በተለይም እቤት የመቀመጥ አስገዳጅ ሁኔታው ቀደም ሲል የነበረባቸውን የተጣበበ የልምምድና የውድድር ጫና በማስቀረቱ በበቂ ሁኔታ እንዲዘጋጁ በር ስለከፈተላቸው በደህናው ጊዜ ማሳካት ያልቻሉትን ክብረወሰን እንዲያሳኩ አድርጓቸዋል። ከወረርሽኙ ጋር በተያያዘ የተፈጠሩ መልካም አጋጣሚዎች እንዳሉ ሆነው የስፖርት ቴክኖሎጂ እየዘመነ መምጣት ለተመዘገቡት ክብረወሰኖች የአንበሳውን ድርሻ እንደሚይዝም ዓለም አቀፍ የስፖርቱ ምሁራን የሚስማሙበት ጉዳይ ነው። ባለፉት ጥቂት ወራት ሲመዘገቡ ያየናቸው በርካታ ክብረወሰኖች አትሌቶች የሚያስመዘግቧቸው ሰዓቶች ላይ ሰፊ ልዩነት በሚፈጥሩ ዘመናዊ የመሮጫ ጫማ እንዲሁም አሯሯጮች በተለይም በመም ውድድሮች ከሰው ይልቅ ቴክኖሎጂ ሆኖ አትሌቶችን እስከ መጨረሻ ድረስ በሚፈለገው ደረጃ በማገዝ የተመዘገቡ ናቸው። ግዙፉ የስፖርት ትጥቅ አምራች ኩባንያ ናይኪ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሚያቀርባቸው የመሮጫ ጫማዎች ቀደም ሲል የዓለም ክብረወሰን ሲመዘገብባቸው ከቆዩ የመሮጫ ጫማዎች አንፃር በአትሌቶች ፍጥነት ላይ የጎላ ተፅዕኖ እንዳላቸው አትሌቶችም ይሁን የስፖርት ቤተሰቡ ይስማማሉ። ከዚህ በላይ የጥሩነሽ ዲባባ የአምስት ሺ ሜትር ክብረወሰን በሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ለተሰንበት ግደይ እና የቀነኒሳ በቀለ የአምስትና አስር ሺ ሜትር ክብረወሰኖች በዩጋዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቺፕቴጌ ሲሰበሩ አትሌቶቹን በአሯሯጭነት ያገዛቸው በመሮጫው መም ዙሪያ የተገጠመው መብራት(Wave-lights) እንደነበር ይታወቃል። ይህ ቴክኖሎጂ አትሌቶቹ በምን ያህል ፍጥነት እያንዳንዱን ዙር ሮጠው ክብረወሰን እንደሚጨብጡ አስልቶ በማሯሯጥ እስከ መጨረሻ ድረስ ደግፏቸዋል። አሯሯጭ በአትሌቲክሱ ዓለም ክብረወሰኖችን ለማስመዝገብ ወሳኙ ነገር እንደሆነ ይታወቃል። አንዳንድ ጊዜ ሴት አትሌቶች በወንድ አሯሯጮች ታግዘውም አሯሯጮች በሚፈለገው ፍጥነት መጓዝ ካልቻሉ ክብረወሰን የማይሰበርበት አጋጣሚ ጥቂት እንዳልሆነ ይታወቃል። አሯሯጩ ቴክኖሎጂ ሆኖ እስከ መጨረሻ ድረስ ወጥ በሆነ ስሌት አትሌቶችን ሲያግዝ ግን የተለየ እንደሚሆን የቅርቦቹ ክብረወሰኖች ምስክር ናቸው።አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 5/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=37367
[ { "passage": "የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የወርቅ ደረጃ ከሰጣቸው ታላላቅ የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድሮች አንዱ የሆነው የፎኮካ ማራቶን ከሳምንት በኋላ በጃፓን ይካሄዳል፡፡ በዚህ ውድድር የሚፎካከሩ የዓለማችን ጠንካራ አትሌቶች ስም ከወዲሁ ይፋ እየተደረገ የሚገኝ ሲሆን፤ የርቀቱ ኮከቦች የሆኑት ምሥራቅ አፍሪካውያን አትሌቶች የተለመደ የአሸናፊነት ግምት ተችሯቸዋል፡፡እኤአ በ2015 የቤጂንግ የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በማራቶን ተከታትለው በመግባት የወርቅና የብር ሜዳሊያ ማጥለቅ የቻሉት ኤርትራዊው ግርማይ ገብረሥላሴና ኢትዮጵያዊው የማነ ፀጋዬ ትልቅ የአሸናፊነት ግምት ከተሰጣቸው አትሌቶች ግንባር ቀደም ናቸው፡፡ግርማይ ገብረሥላሴ በዓለም ቻምፒዮናው በአስራ ስምንት ዓመቱ ሳይጠበቅ ለታላቅ ድል በመብቃት ለኤርትራ በመድረኩ የመጀመሪያ የወርቅ ሜዳሊያ ማጥለቁ የሚታወስ ሲሆን፤ በአንፃሩ በርቀቱ የተሻለ ልምድ የነበረው የማነ የብር ሜዳሊውን ለኢትዮጵያ ማስመዝገቡ አይዘነጋም፡፡ ሁለቱ የማራቶን ፈርጦች ከዓለም ቻምፒዮናው በኋላ በትልቅ ውድድር ዳግም ፎኮካ ማራቶን ላይ የሚያደርጉት ፉክክር የሚጠበቅ ይሆናል፡፡የማነ በበርካታ የማራቶን ውድድሮች በማሸነፍ ስማቸው ከሚጠቀስ የዓለማችን ድንቅ የማራቶን አትሌቶች አንዱ ሲሆን፤ ከሁለት ዓመት በፊት በዚሁ በፎኮካ ማራቶን 2:08:48 ሰዓት ማሸነፉ ይታወሳል፡፡ ይህም ሰዓቱ እኤአ 2012 ላይ በሮተርዳም ማራቶን ሲያሸንፍ ካስመዘገበው የራሱ ምርጥ ሰዓት በአራት ደቂቃ የተሻለ ሆኖ ተመዝግቦለታል፡፡ የማነ በዓለም ቻምፒዮናው የብር ሜዳሊያውን ካጠለቀ ወዲህ ጉልበቱ ላይ በገጠመው ጉዳት የ2016 ሪዮ ኦሊምፒክን ጨምሮ በርካታ ውድድሮች ያመለጡት ሲሆን፤ ያለፈውንም ዓመት በጥሩ አቋም ላይ አልነበረም፡፡ ይሁን እንጂ በ2018 ወደ ጥሩ አቋም መመለሱን ባለፈው ሰኔ ወር የኦታዋ ማራቶንን 2:08:52 በሆነ ሰዓት በማሸነፍ አሳይቷል፡፡ግርማይ ገብረሥላሴ በበኩሉ ከዓለም ቻምፒዮናው ድሉ በኋላ በሪዮ ኦሊምፒክ ሌላ ታሪክ ይሠራል ተብሎ ሲጠበቅ ሜዳሊያ ውስጥ መግባት ሳይችል ቀርቷል፡፡ ይሁን እንጂ በዚህ ታላቅ መድረክ አራተኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ እንደ ወጣት አትሌት መጥፎ የሚባል አልነበረም፡፡ከኦሊምፒኩ ስድስት ሳምንታት በኋላ በጠንካራው የኒውዮርክ ማራቶን ዳግም ሳይጠበቅ ለድል የበቃው ግርማይ በአጭር ጊዜ ውስጥ ስሙን በርቀቱ ማግነን ችላል፡፡ 2:07:46 የሆነ የራሱ ምርጥ ሰዓት ያለው ግርማይ ባለፉት ሁለት ውድድሮቹ አቋርጦ መውጣቱ ምናልባትም ወደ ጥሩ አቋሙ ካልተመለሰ በዘንድሮው የፎኮካ ማራቶን ከየማነ ጋር የሚጠበቀውን ጠንካራ ፉክክር እንዳያሳይ ስጋት ሊሆን ይችላል፡፡በዚህ ውድድር የማነ ከግርማይ ባሻገር ከሌላ አትሌት ጠንካራ ፉክክር እንደሚገ ጥመው ይጠበቃል፡፡ ይህም ውድድሩ ላይ ከየማነ ቀጥሎ ሁለተኛውን ፈጣን ሰዓት ይዞ የሚወዳደረው ኬንያዊው ቪንሰንት ኪፕሩቶ ሲሆን፤ በርቀቱ 2:05:13 የሆነ የራሱ ምርጥ ሰዓት ያለው አትሌት ነው፡፡\nበሌላ በኩል በዘንድሮው የፎኮካ ማራቶን ትኩረት ሳይሰጠው መታለፍ የሌለበት አትሌት ጃፓናዊው ዩኪ ካዉቺ ነው፡፡ ይህ አትሌት ካለፉት ዘጠኝ የፎኮካ ማራቶን ውድድሮች በስምንቱ ላይ በመሳተፍ ከሌሎቹ አትሌቶች የተሻለ ልምድ ማካበት ችሏል፡፡ ዩኪ ልምድ ማካበቱ ብቻ በውድድሩ አስፈሪ ወይንም ጠንካራ ተፎካካሪ ባያደርገውም በርቀቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያስመዘገበ ያለው ውጤትና ጥሩ አቀም ለምሥራቅ አፍሪካውያኑ አትሌቶች አስፈሪ ያደርገዋል፡፡ ዩኪ በዚህ ውድድር እኤአ በ2011፣2013እና 2016 ሦስተኛ ደረጃን ይዞ ሲያጠናቅቅ በሦስቱም ውድድሮች ርቀቱን ከ2፡10 ሰዓት በታች በማጠናቀቅ ጥንካሬውን ማሳየት ችላል፡፡ ዩኪ ምሥራቅ አፍሪካውያን ደጋግመው ያሸነፉትን የቦስተን ማራቶን በቅርቡ ማሸነፉም በአገሩና በደጋፊዎቹ ፊት በሚያደርገው ውድድር ቀላል ግምት እንዳይሰጠው ያደርጋል፡፡", "passage_id": "ba0a2da0290d0ea00dd0d72866a0b83f" }, { "passage": " የዓመቱ የምርጥ አትሌቶች ሽልማት እጩዎች ከሦስት ሳምንት በፊት ይፋ ሲደረግ አንድም ኢትዮጵያዊ አትሌት ከምርጥ አስር እጩዎች ውስጥ መካተት አልቻለም ነበር። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይህን ክብር ደጋግመው ማግኘት ቢችሉም ባለፉት ሁለት ዓመታት በሁለቱም ፆታ ከእጩዎቹ መካከል እንኳን ሳይካተቱ መቅረታቸው አስገራሚ ነበር። ያም ሆኖ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በዋናው ሽልማት በእጩነት ያልተካተቱበት አጋጣሚ በወጣቶች ወይም ከሃያ ዓመት በታች በእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ አትሌቶች በሚሳተፉበት ሽልማት ሁለት ወንዶችና አንድ ሴት አትሌት መካተት ችላለች። ከእጩነት ባሻገርም ወጣቱ አትሌት ሰለሞን ባረጋ ሽልማቱን ማሸነፍ ችሏል። ባለፈው ቅዳሜ በሞናኮ በተካሄደው የሽልማት ስነስርዓት ላይ ኢትዮጵያውያን በኮማንደር ደራርቱ ቱሉ አማካኝነት ተጨማሪ ዓለም አቀፍ ሽልማት ማግኘት ችለዋል። እኤአ 1992ና 2000 ላይ በተካሄዱት\nየባርሴሎናና የሲድኒ ኦሊምፒኮች በአስር ሺ ሜትር የወርቅ ሜዳሊያዎችን ያጠለቀችው ጀግናዋ አትሌት ደራርቱ ቱሉ በዓለም አትሌቲክስ\n‹‹ዘንድ የዓመቱ ምርጥ ሴት›› በሚል ሽልማት አግኝታለች። ደራርቱ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን በተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንትነት\nእየመራች ላሳየችው የላቀ አስተዋፅኦ ይህ እውቅና ተችሯታል። ደራርቱ በአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን የምክር ቤት አባል ስትሆን\nየምስራቅ አፍሪካ አትሌቲክስ ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆንም እያገለገለች መገኘቷ ለሽልማቱ አብቅቷታል። የአስራ ዘጠኝ ዓመቱ ኢትዮጵያዊ አትሌት\nሰለሞን ባረጋ የዘንድሮውን ዓመት የወጣትና ተስፈኛ አትሌቶች ሽልማት ለመጀመሪያ ጊዜ ማሸነፍ ችሏል። ሰለሞን በዶሃ በተካሄደው የዓለም\nቻምፒዮና በአምስት ሺ ሜትር የብር ሜዳሊያ ከማጥለቁ በተጨማሪ በዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና አምስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል።\nበውድድር ዓመቱ የዓለም ከሃያ ዓመት በታች የአምስትና አስር ሺ ሜትር ርቀቶችን 12፡53፡04ና 26፡49፡46 በሆነ ጊዜ መሪ ሰዓቶች\nማስመዝገቡ ለሽልማቱ አብቅቶታል። ባለፉት ሁለት ዓመታት በመካከለኛና ረጅም ርቀቶች ድንቅ ብቃት እያሳየ የሚገኘው አትሌት ሰለሞን\nባረጋ ባለፈው ዓመትም ከመጨረሻዎቹ አምስት እጩዎች ስም ዝርዝር ውስጥ መካተቱ ይታወሳል።የደቡብ ፖሊሱ ክለብ አትሌት የሆነው ሰለሞን\nባረጋ ከእድሜው ከፍ ብሎ ከታላላቆቹ ጋር በመወዳደር እያስመዘገበ ላለው ስኬት ባለፈው ዓመት ክለቡ የኢንስፔክተርነት ማዕረግ የሰጠው\nሲሆን ባለፉት ሦስት ዓመታት እያሳየ ያለው አስደናቂ ብቃት ወደ ፊት ተስፋ እንዲጣልበት አድርጓል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ወደ ታላላቅ የውድድር መድረኮች መጥቶ በአጭር ጊዜ ውስጥ የስፖርት ቤተሰቡ\nአይን ማረፊያ የሆነው ወጣት አትሌት ሰለሞን ባረጋ ውጤቱና አስደናቂ ብቃቱ ኢትዮጵያ በቅርቡ በታላላቅ መድረኮች አረንጓዴውን ጎርፍ\nዳግም የማየት ብሩህ ተስፋ እንዳላት ማሳያ መሆኑን በርካቶች ይመሰክሩለታል። ድንቅ የሩጫ ተሰጥኦው በመካከለኛና ረጅም ርቀቶች በቅርብ\nጊዜ ውስጥ ዙፋን ላይ እንደሚወጣ የስፖርቱ ባለሙያዎች በተደጋጋሚ መስክረውለታል። በ2018 የውድድር ዓመት የአምስት ሺ ሜትር አጠቃላይ የዳይመንድ ሊግ አሸናፊ መሆን የቻለው ሰለሞን\nባረጋ በርቀቱ ከሃያ ዓመት በታች የዓለም ክብረወሰንን 12፡ 43፡02 በሆነ ሰዓት ከመጨበጡ ባሻገር እኤአ 2005 ላይ ቀነኒሳ\nበቀለ በርቀቱ ካስመዘገበው ሰዓት ወዲህ ፈጣን ሰዓት ሆኖ መመዝገቡ ይታወሳል። በዶሃው የዓለም ቻምፒዮና ኢትዮጵያ በታሪክ ለመጀመሪያ\nጊዜ በሦስት ሺ ሜትር መሰናክል የብር ሜዳሊያ እንድታገኝ ያስቻለው አትሌት ለሜቻ ግርማ ከአምስቱ ተስፈኛ እጩዎች መካከል አንዱ\nበመሆን ከሰለሞን ጋር ሽልማቱን ለማሸነፍ ተፎካክሯል። ለሜቻ በውድድር ዓመቱ በርቀቱ ከሃያ ዓመት በታች መሪ የሆነውን ሰዓት በ8፡01፡36\nያስመዘገበ ሲሆን የኢትዮጵያን ክብረወሰንም የግሉ ማድረግ ችሏል። በዓለም ቻምፒዮናውም የወርቅ ሜዳሊያ ያመለጠው በ0ነጥብ01 ማይክሮ\nሰከንድ ተቀድሞ እንደነበረ አይዘነጋም። ከሁለቱ ኢትዮጵያን እጩዎች ጎን ለጎን ብራዚላዊው የአራት መቶ ሜትር መሰናክል ተወዳዳሪ\nአሊሰን ዶስ ሳንቶስ፣ ኖርዌያዊው አትሌት ጃኮብ ኢንግብሪትሰን፣ ዩክሬናዊው መዶሻ ወርዋሪ ማይክሃይሎ ኮክሃን በሽልማቱ ተፎካካሪ\nነበሩ። በወጣት ሴቶች ዘርፍ ከሰለሞን ባረጋ ጋር ተመሳሳይ ሽልማት ማሸነፍ የቻለችው ዩክሬናዊታ ያሮስላቫ\nማሁቺክ ናት። ይህች አትሌት በከፍታ ዝላይ የተሻለ አቅም ያላት አትሌት ስትሆን 2 ሜትር ከ04 ሳንቲ ሜትር በመዝለል የክብረ ወሰን\nባለቤት ናት። በዶሃው የዓለም ቻምፒዮናም የብር ሜዳሊያ አግኝታለች። ከዚህም ባሻገር አውሮፓ ቻምፒን መሆን የቻለች ጠንካራ አትሌትም\nናት። ይህን ሽልማት ለማሸነፍ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ለምለም ኃይሉ ከመጨረሻዎቹ አምስት እጩዎች ውስጥ ተካታ ተፎካካሪ መሆን ችላለች።\nጃማይካዊቷ ብሪታኒ አንደርሰን፣ የኢኳዶሯ እርምጃ ተወዳዳሪ ግሌንዳ ሞርጆን፣ አሜሪካዊቷ 100 ሜትር የወጣቶች ባለክብረወሰን ሻካሪ\nሪቻርድሰን የመጨረሻዎቹ ተፎካካሪዎች ነበሩ። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከእጩዎች መካከል ያልተካተቱበት የዓመቱ የምርጥ አትሌቶች ሽልማት በወንዶች\nዘርፍ ኬንያዊው ኢሉድ ኪፕቾጌ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ ማሸነፍ ችሏል። የማራቶን ፈርጡ ኢሉድ ኪፕቾጌ በውድድር ዓመቱ ሁለት ፉክክሮች\nላይ ብቻ ቢታይም ያስመዘገበው ታሪክ ሽልማቱን ለማሸነፍ አብቅቶታል። ኪፕቾጌ በውድድር ዓመቱ የለንደን ማራቶንን ክብረወሰን በማሻሻል\nበ2፡02፡37 ሰዓት ማሸነፉ ይታወሳል። ከዚህ በላይ ግን ከወር በፊት በቬና ማራቶን የሰው ልጅ የብቃት ጥግ ወሰን እንደሌለው ያሳየበት\nውድድር አይዘነጋም። ኪፕቾጌ ከትጥቅ አምራች ኩባንያው ናይኪ ጋር በመሆን በተለያዩ ቴክኖሎጂዎች ታግዞም ቢሆን ማራቶንን ከሁለት\nሰዓት በታች ማጠናቀቅ እንደሚቻል አስመስክሯል። 1፡59፡40 በሆነ ሰዓት ማራቶንን በማጠናቀቅ በታሪክ የመጀመሪያው አትሌት ለመሆን\nቢበቃም የተመዘገበው ሰዓት በዓለም ክብረወሰንነት እንዳልተያዘ ይታወሳል።ያም ሆኖ ዓለም ዓቀፍ ሽልማቱን ከማሸነፍ አላገደውም። ባለፈው የዶሃ የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና የአስር ሺ ሜትር ቻምፒዮን የሆነው ዩጋንዳዊው ጆሹአ ቺፕቴጌ\nየመጨረሻዎቹን አምስት እጩዎች መቀላቀል የቻለ ሲሆን፣ አሜሪካዊው ምርኩዝ ዘላይ ሳም ኬንድሪክስ በውድድር ዓመቱ ካደረጋቸው አስራ\nሰባት ከቤት ውጪ ውድድሮች አስራ ሁለቱን በድል በማጠናቀቅ የሽልማቱ ተፎካካሪ ነበር።አሜሪካዊው የአጭር ርቀት አትሌት ኖህ ላይልስና\nኖርዌያዊው የአጭር ርቀት ኮከብ አትሌት ካርልስተን ዋርሆልም የሽልማቱ ተፎካካሪ ነበሩ። በሴቶች\nመካከል የተደረገውን ሽልማት አሜሪካዊቷ ደሊላ ሙሃመድ አሸንፋዋለች። በዓመቱ በ400 ሜትር ያሳየችው አቋም ለሽልማቱ ያበቃት ሲሆን\nአትሌቷ በሃገር አቀፍ ቻምፒዮና 52ሰከንድ ከ20ማይክሮ ሰከንድ መበመግባት ቀዳሚ ናት። በ400 ሜትር መሰናክል በራሷ የተያዘውን\nክብረወሰን 52ሰከንድ ከ16ማይክሮ ሰከንድ በማሻሻል ብቃቷን አስመስክራለች። በ4በ 400 ሜትርም በተመሳሳይ የዓለም ቻምፒዮን ናት።\nበርዝመት ዝላይ ቬንዙዌላዊቷ ዩሊማር ሮጃስ ለመጨረሻው ዙር በመድረስ የተፎካከረች ሲሆን የአጭር ርቀት ተወዳዳሪዋ ጃማይካዊት አትሌት\nሼሊ- አን ፍራዘር-ፕረይሲ፣የማራቶን ክብረወሰንን ሰበረችው ኬንያዊት አትሌት ብርጊድ ኮስጊ፣በዶሃው የዓለም ቻምፒዮና በ1ሺ500\nእና10ሺ ሜትር አሸናፊ የሆነችው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ የኔዘርላንድስ አትልት ሲፋን ሃሰን ለመጨረሻ እጩነት ቀርበው ተፎካካሪ ሆነዋል።አዲስ ዘመን  ህዳር 16 ቀን 2012 ዓ.ምቦጋለ አበበ", "passage_id": "d94b6faf5448369e27cea8d63ea2e5df" }, { "passage": "ዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን በዓመቱ ከሚያካሂዳቸውና በጉጉት ከሚጠበቁ ትልልቅ ውድድሮች መካከል አንዱ የዓለም ሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና ነው። በተያዘው ወር መጨረሻ የሚካሄደው ውድድሩ ከወዲሁ ተጠባቂ ሲሆን፤ ማህበሩ በድረገጹ ላይ በርቀቱ ስኬታማ የሆኑና በውድድሩም ተጽእኖ ፈጣሪ እንደሚሆኑ የሚጠበቁትን ሀገራት ዘርዝሯል። ከአምስቱ ቀዳሚ ሀገራት መካከልም አንዷ ኢትዮጵያ ሆናለች። በረጅም ርቀት አትሌቲክስ ስኬታማ ከሆኑት የዓለም ሀገራት ተርታ የምትመደበው ኢትዮጵያ በዚህ ዝርዝር ባስመዘገበችው ውጤት ተጠቃሽ ስትሆን፤ የምትቀድማት ብቸኛዋ ሀገር ጎረቤቷ ኬንያ መሆኗም ነው በዘገባው የተጠቆመው። ዘገባው እአአ በ2004ዓ.ም በብራሰልስ አዘጋጅነት የተካሄደውን ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ከተሳትፎዎቿ መካከል እጅግ የደመቀችበት መሆኑን አንስቶ፤ በተለይ ስኬታማ የሆኑትን አትሌቶችን ስምም ጠቅሷል።43 ዓመታትን ያስቆጠረው የዓለም ሀገር አቋራጭ ውድድር እአአ በ1973 በቤልጂየም የተጀመረ ውድድር ነው። ውድድሩ እአአ እስከ 2011 ድረስ በየዓመቱ ሳይቆራረጥ ሲካሄድ ቢቆይም ከ2013 ጀምሮ ግን በየሁለት ዓመቱ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኢትዮጵያ በዚህ ውድድር ላይ ባላት ተሳትፎ ለመጀመሪያ ጊዜ ውጤት ያስመዘገበችው እአአ በ1981 ሲሆን፤ ሞሃመድ ከድር ባጠለቀው የብር ሜዳሊያ ነው።  በቀጣዩ ዓመትም አትሌቱ ሰዓቱን በማሻሻል ጭምር አሸናፊ በመሆን ኢትዮጵያን በመድረኩ ከወርቅ ሜዳሊያ ጋር ሊያወዳጃት ችሏል። አትሌት በቀለ ደበሌ እአአ በ1983 አሸናፊ ሲሆን፤ ከሁለት ዓመታት በኋላ ወዳጆ ቡልቲ የነሃስ ሜዳሊያ አጥልቋል። እአአ 1986 አበበ መኮንን የብር ሜዳሊያ ባለቤት ከሆነ በኋላ፤ ፊጣ ባይሳ የነሃስ ሜዳሊያ እስኪያገኝ፤ ለአምስት ዓመታት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሜዳሊያ ሰንጠረዡ አልታዩም ነበር።እአአ 1994 በሃንጋሪዋ ቡዳፔስት በተካሄደው ውድድርም ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ለመጀመሪያ ጊዜ የነሃስ ሜዳሊያ በማጥለቅ ስሙን በታሪክ አስጽፏል። ከዚያ በኋላ ባሉት ዓመታት ጥቂት አትሌቶች የብርና የነሃስ ሜዳሊያዎችን ቢያገኙም የወርቅ ሜዳሊያው በበላይነት የተያዘው በኬንያውያን አትሌቶች ነው። ኬንያዊው ፖል ቴርጋት ለአምስት ዓመታት በተከታታይ በማሸነፍም ታሪካዊ አትሌት ነው።እአአ ከ2012 ጀምሮ ግን የበላይነቱ ከኬንያዊው አትሌት ወደ ኢትዮጵያዊው ወጣት የተሸጋገረበት ነበር። እስካሁንም በመድረኩ አቻ ያልተገኘለት ቀነኒሳ በቀለ ለአምስት ጊዜያት በተከታታይ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት ሲሆን፤ ከአንድ ዓመት እረፍት በኋላ በድጋሚ ወርቅ በማጥለቅ በ12 ኪሎ ሜትር ውድድር የስድስት ጊዜ ሻምፒዮን በመሆን ወርቃማ ታሪኩን አስመዝግቧል። ቀነኒሳ በዚህ ውድድር አጭር ርቀትም ስኬታማ ሲሆን፤ አምስት የወርቅና አንድ የብር በአጠቃላይ ስድስት ሜዳሊያዎችን የግሉ በማድረግም ባለ ክብረወሰን ነው።    እአአ በ2004 በብራሰልስ በተካሄደው ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ቀነኒሳ በቀለ፣ ገብረእግዚአብር ገብረማርያም እና ስለሺ ስህን በሰከንዶች ልዩነት ተቀዳድመው ከአንድ እስከ ሶስት ያለውን ደረጃ የወሰዱበት ውድድር እስካሁንም እጅግ ስኬታማው ነው። አትሌት ገብረእግዚአብሄር ገብረማርያም አንድ የወርቅ ሁለት ብር ሜዳሊያዎችን ሲያስመዘግብ (በአዋቂዎች ዘርፍ)፤ ስለሺ ስህን አንድ የብርና የነሃስ ሜዳሊያ ከመድረኩ አግኝቷል። አትሌት ኢማና መርጋ እአአ በ2011 እና 2013 የወርቅ እና የብር ሜዳሊያ አሸናፊ ሲሆን፤ ሙክታር እድሪስና አባዲ ሃዲስ ደግሞ የነሃስ ሜዳሊያ ያስመዘገቡ አትሌቶች ናቸው። በሴቶች በኩል ኢትዮጵያ ከሜዳሊያ የተወዳጀችው በኮሎኔል ደራርቱ ቱሉ ሲሆን፤ ለሶስት ተከታታይ ዓመታትም ድሉ የኢትዮጵያውያን ነበር። እአአ በ1995 እና 1997 በደራርቱ በ1996 ደግሞ በጌጤ ዋሚ የወርቅ ሜዳሊያው ተወስዷል። ሁለቱ አትሌቶች በየዓመቱ እየተፈራረቁ የቆዩ ሲሆን፤ በተለይ አትሌት ጌጤ ዋሚ ሁለት የወርቅ፣ ሁለት የነሃስ እና ሁለት የብር ሜዳሊያዎችን በማግኘት ስኬታማ አትሌት ናት። ወርቅነሽ ኪዳኔ፣ መሪማ ደንቦባ፣ እጅጋየሁ ዲባባ፣ መሰለች መልካሙ እና መስታወት ቱፋም ሜዳሊያ ያስመዘገቡ አትሌቶች ሲሆኑ፤ ጥሩነሽ ዲባባ ደግሞ ሶስት ወርቅ እና አንድ ብር በማግኘት ከስኬታማ አትሌቶች መካከል ትመደባለች። ጥሩነሽ በአጭር ርቀትም አንድ የወርቅ እና የብር ሜዳሊያ ያገኘች አትሌት ናት። አትሌት ህይወት አለሙ፣ ሰንበሬ ተፈሪ፣ በላይነሽ ኦልጂራ እና ነጻነት ጉደታም በቅርብ ዓመታት የሀገራቸውን ስም ማስጠራት የቻሉ አትሌቶች ናቸው።በተመሳሳይ በአዋቂ ወንድና ሴት በቡድን ውጤትም ኢትዮጵያ የተሻለ ታሪክ ያላት ሲሆን፤ በወንዶች 10 የወርቅ፣ 13 የብር እና 7 የነሃስ ሜዳሊያዎችም ተመዝግበዋል። በሴቶች ደግሞ 11 የወርቅ፣ 12 የብር እና 1 የነሃስ ሜዳሊያዎች ተገኝተዋል። ከዚህ ባሻገር በርካታ አትሌቶች በወጣቶች፣ በአጭር ርቀት ሀገር አቋራጭ እንዲሁም በየርቀቱ በቡድን የሜዳሊያ ባለቤቶች ሆነዋል።ማህበሩ ከኢትዮጵያ ባሻገር በዘርፉ ስኬታማ የሆኑትን ሀገራት አንስቷል። ኬንያ ለሶስት አስርት ዓመታት በስኬታማነት የቆየች ሀገር ስትሆን፤ በተለይ ከ2010 ወዲህ በርካታ ሜዳሊያዎችን በማስመዝገብ ላይ ያለች ሀገር መሆኗም ተጠቁሟል። በወንዶች በኩል ኒውዝላንድ እና አሜሪካ ሲጠቀሱ በሴቶች ደግሞ ፖርቹጋል ትጠቀሳለች።አዲስ\nዘመን የካቲት 25/2011ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "b2f5f5f6a9d5972caf959e388b776e5b" }, { "passage": "የ2019 ውድድር ዓመት በማራቶን ወርቃማው ዘመን እንደነበር የዓለም አትሌቲክስ ተንታኞች የውድድር ዓመቱን መገባደድ ተከትሎ በርካታ ማሳያዎችን በማስቀመጥ ተጠምደዋል፡፡ ይህን የውድድር ዓመት ወርቃማ ካስባሉት ቁልፍ ማሳያዎች መካከል ግንባር ቀደሙ ኬንያዊው የርቀቱ የክብረወሰን ባለቤት ኢሉድ ኪፕቾጌ በቬና ማራቶን ርቀቱን በአርባ አንድ አሯሯጮችና በዘመናዊ ጫማ ታግዞ ከ2፡00 በታች ማጠናቀቁ ነው፡፡ ከኪፕቾጌ አስደናቂ ብቃት ባሻገር የ5ና 10 ሺ ሜትር የዓለም ክብረወሰን ባለቤቱ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ከረጅም ጊዜ ጉዳት በኋላ ወደ ውድድር ተመልሶ ባለፈው በርሊን ማራቶን 2፡01፡41 የሆነውን ሁለተኛ ፈጣን ሰዓት ማስመዝገቡ የውድድር ዓመቱን ወርቃማ ካሰኙት ምክኒያቶች አንዱ ነው፡፡ ከ5 ና 10ሺ ሜትር የመም(ትራክ) ውድድሮች ጀምሮ በኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮናን\nበመሳሰሉ ታላላቅ መድረኮች ባለፉት ሃያ ዓመታት በረጅም ርቀቶች ተፎካካሪ የሆኑት ቀነኒሳና ኪፕቾጌ አሁን ላይ በማራቶን የዓለማችን\nቁጥር አንድና ሁለት ናቸው፡፡ ኪፕቾጌ ከዓመት በፊት የርቀቱን ክብረወሰን በበርሊን ማራቶን 2፡01፡39 በሆነ ሰዓት ሲያስመዘግብ\nከእሱ ሌላ ይህን ክብረወሰን የሚደፍረው አትሌት እንደማይኖር የበርካቶች ግምት ነበር፡፡ በተቃራኒው ቀነኒሳ ባለፈው መስከረም ከረጅም\nጊዜ ጉዳት በኋላ ወደ ውድድር ተመልሶ በበርሊን ማራቶን ሲሳተፍ ፈጣን ሰዓት ያስመዘግባል ብሎ የገመተ አልነበረም፡፡ ያም ሆኖ ሦስት\nየኦሊምፒክ ወርቆችን መሰብሰብ የቻለው የሰላሳ ሰባት ዓመቱ ቀነኒሳ ከኪፕቾጌ የዓለም ክብረወሰን በሁለት ሰከንድ ብቻ የዘገየ ሰዓት\nበማስመዝገብ የዓለም ክብረወሰን የማሻሻል አቅም እንዳለው አስመስክሯል፡፡ ኪፕቾጌ በማራቶን የዓለምን አንደኛ ፈጣን ሰዓት በእጁ ይዞ ቀነኒሳም በሁለት ሰከንድ\nየዘገየ ሁለተኛውን ፈጣን ሰዓት ይዞ በዘንድሮው የውድድር ዓመት ብቻ በሁለት ታላላቅ የውድድር መድረኮች የሚፋለሙበት አጋጣሚ ሰፊ\nእንደሚሆን ሰሞኑን የወጡ መረጃዎችን ከግምት በማስገባት መገመት ይቻላል፡፡ ኪፕቾጌ ከትናንት በስቲያ በለንደን ማራቶን እንደሚሳተፍ\nማሳወቁን ተከትሎ ከቀነኒሳ ጋር የሚፋለምበት አጋጣሚ በመጪው ሚያዝያ እውን እንደሚሆን ታውቋል፡፡ ቀነኒሳ ከበርሊን ማራቶን አስደናቂ\nድሉ በኋላ በለንደን ማራቶን ለመሳተፍ ትልቅ ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ ይህም ሁለቱ አትሌቶች የጤና ወይም ሌላ የተለየ\nችግር ካልገጠማቸው ለንደን ላይ የዓለም ህዝብ በጉገት የሚጠብቀው ትልቅ ፉክክር እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡ ሁለቱ አትሌቶች\nበለንደን ማራቶን ከዚህ ቀደም እንደመፎካከራቸው የዘንድሮውን ምን ልዩ ያደርገዋል? የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችላል፡፡ ሁለቱ አትሌቶች\nከዚህ ቀደም የለንደን ማራቶንን ጨምሮ በሌሎች የጎዳና ላይ ውድድሮች የተገናኙባቸው አጋጣሚዎች ቢኖሩም ቀነኒሳ በጥሩ አቋም ላይ\nአልነበረም፡፡ ይህም የሁለቱን የረጅም ርቀት ፈርጦች ፉክክር በሚጠበቀው ደረጃ እንዳይገኝ አድርጎታል:: አሁን ላይ ሁለቱም ኮከቦች\nበድንቅ አቋማቸው ላይ እንደመገኘታቸው መጠን ዘንድሮ ሊያደርጉት የሚችሉት ፉክክር የተለየ እንደሚሆን ከወዲሁ መገመት አይከብድም፡፡\nኪፕቾጌ ቬና ላይ 1፡59፡41 በመሮጥ የሰው ልጅ የብቃት ጥግ ገደብ እንደሌለው ካሳየ በኋላ በጥሩ የስነ ልቦና ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡\nቀነኒሳ ደግሞ በሁለት ሰከንድ ምክኒያት ባመለጠው የዓለም ክብረወሰን ቁጭት ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ይህን ቁጭቱን ለመወጣት በከፍተኛ\nተነሳሽነት ጥሩ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል፡፡ኪፕቾጌ ባለፉት አራት ዓመታት በለንደን ማራቶን ነግሷል፡፡ የቦታው ክብረወሰንም በእጁ\nይገኛል፡፡ ቀነኒሳ በጥሩ አቋም ላይ ባልነበረበት ወቅት ለንደን ላይ ከአንዴም ሁለቴ የተራበውን ድል ማሳካት አልቻለም፡፡ ዘንድሮ\nግን ከበርሊን ማራቶን ጣፋጭ ድሉ በኋላ ይህን ውድድር የማሸነፍ ጉጉቱ አይሏል፡፡ ሁለቱ ፈርጦች በዚህ አይነት ደረጃ ላይ መገኘታቸው\nለስፖርት አፍቃሪው የምስራች ሲሆን ለስፖርቱም እድገት አንድ ርምጃ ነው፡፡ ምናልባትም በዚህ ፉክክር መካከል በቴክኖሎጂ በመታገዝ\nከ2፡00 በታች መጠናቀቅ የተቻለው አርባ ሁለት ኪሎ ሜትር በተፈጥሯዊ መንገድ እውን የሚሆንበት እድል ሊኖር ይችላል፡፡ ይህ ባይሆን\nእንኳን አዲስ የዓለም ክብረወሰን ሊመዘገብ የሚችልበት አጋጣሚ አይኖርም ለማለት አያስደፍርም፡፡ ከለንደን ማራቶን\nባሻገር ሁለቱን ኮከቦች በዘንድሮው የውድድር ዓመት የማየት ሌላ እድል ይኖራል፡፡ ይህም ዓለም በጉጉት የሚጠብቀው ታላቁ የስፖርት\nመድረክ ኦሊምፒክ ነው፡፡ 2020 ኦሊምፒክን ቶኪዮ ለማሰናዳት ዝግጅቷን እያጠናቀቀች ትገኛለች፡፡ ከለንደን ማራቶን በኋላ እዚህ\nኦሊምፒክ ላይ ለመሳተፍ ኪፕቾጌ ፍላጎት እንዳለው መግለፁ ይታወቃል፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በኦሊምፒክና በዓለም ቻምፒዮና\nየሚሳተፉ አትሌቶችን የሚመርጠው አትሌቶች በታላላቅ ውድድሮች ባስመዘገቡት ውጤትና ሰዓት መሰረት እንደመሆኑ መጠን ቀነኒሳ ለቶኪዮ\nኦሊምፒክ የመመረጥ እድሉ ሰፊ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል:: ይህም ሁለቱን ኮከቦች ዳግም በታላቅ የውድድር መድረክ የሚያፋጥጥ አጋጣሚ\nይሆናል፡፡ ሁለቱ አትሌቶች\nኦሊምፒክ ላይ ከተገናኙ የቶኪዮ ድግስ የበለጠ በማራቶን እንደሚደምቅ ግልፅ ነው፡፡ ኪፕቾጌ 2016 ሪዮ ኦሊምፒክ ላይ ቻምፒዮን\nመሆኑን ተከትሎ ለሁለተኛ ጊዜ በዚህ ታላቅ መድረክ ታሪክ ለመስራት ጉጉት ባይኖረው ይገርማል፡፡ ኪፕቾጌ ይህን ድል ካሳካ ከአበበ\nቢቂላ በኋላ በታሪክ ኦሊምፒክ ላይ ሁለት ጊዜ በማራቶን ያሸነፈ አትሌት የመሆን እድል አለው፡፡ ቀነኒሳ ባለፈው ሪዮ ኦሊምፒክ በማራቶን\nኢትዮጵያን ለመወከል ተመርጦ መጨረሻ ሰዓት ላይ ከቡድን ስብስቡ መውጣቱ ይታወሳል፡፡ ዘንድሮ ይህን እድል አግኝቶ መጠቀም ከቻለ\nግን ታሪካዊው አትሌት አበበ ቢቂላ ለሁለተኛ ጊዜ ታሪክ በሰራባት ቶኪዮ ስሙን በወርቅ ቀለም የሚፅፍበት ወርቃማ እድል ከፊቱ ይጠብቀዋል፡፡\nአዲስ ዘመን አርብ ታህሳስ 10/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "ddafc2a9f40caca7d7d01551f6d8b418" }, { "passage": "ኢትዮጵያዊቷ ወጣት አትሌት ለተሰንበት ግደይ የዓለም አስራ አምስት ኪሎ ሜትር ክብረወሰንን መጨበጥ ችላለች፡፡\nለተሰንበት ከትናንት በስቲያ በኔዘርላንድስ ‹ሰቨን ሂልስ ረን› በተባለ የጎዳና ላይ ውድድር ክብረወሰኑን ያሻሻለች ሲሆን ውድድሩን\nያጠናቀቀችበት ሰዓት 44፡20 ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ ከወር በፊት በዶሃው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በአስር ሺ ሜትር አስደናቂ ብቃት በማሳየት የብር ሜዳሊያ\nማሸነፍ የቻለችው ለተሰንበት በዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና በወጣቶች ምድብ ለሁለት ተከታታይ ዓመታት ቻምፒዮን እንደነበረች ይታወሳል፡፡\nለተሰንበት የዓለም የአስራ አምስት ኪሎ ሜትር ክብረወሰንን ከአንድ ደቂቃ በላይ ያሻሻለች ሲሆን ይህ ክብረወሰን\nከሁለት ዓመት በፊት በኬንያዊቷ ጆይስሊን ጂፕኮስጌ 45፡37 በሆነ ሰዓት በፓራጓይ ግማሽ ማራቶን ውድድር ላይ የተመዘገበ መሆኑን\nየዓለም አትሌቲክስ ድረ ገፅ ዘገባ አመልክቷል፡፡ የሃያ አንድ ዓመቷ አትሌት ለተሰንበት ከውድድሩ በኋላ ‹‹ገና ለውድድሩ ዝግጅት ሳደርግ በጥሩ አቋም ላይ እንዳለሁ\nአውቅ ነበር፣ በውድድሩም ላይ ምቾት ተሰምቶኛል፣ እውነቱን ለመናገር የቀድሞውን ክብረወሰን በምን ያህል ሰዓት እንዳሻሻልኩኝ ለማየት\nጓጉቼ ነበር›› በማለት የዓለም ክብረወሰን ስለመጨበጧ እርግጠኛ እንደነበረች ተናግራለች፡፡ ለተሰንበት ውድድሩን ከማሸነፏና የዓለም ክብረወሰን ከማሻሻሏ ባሻገር የመጨረሻዎቹን አስር ኪሎ ሜትሮች የሮጠችበት\nፍጥነት የአትሌቲክሱን ቤተሰብ ያስደነቀና ወደ ፊት ትልቅ ተስፋ እንዲጣልባት ያደረገ ነበር፡፡ ለተሰንበት የመጨረሻዎቹን አስር ኪሎ\nሜትሮች 29፡12 በሆነ ሰዓት ያገባደደች ሲሆን ይህም አልማዝ አያና በ2016 ሪዮ ኦሊምፒክ የአስር ሺ ሜርት የዓለም ክብረወሰንን\nስታሻሽል ካስመዘገበችው 29፡17፡45 ሰዓት የፈጠነ ነው፡፡ የአስራ አምስት ኪሎ ሜትር የዓለም ክብረወሰን ከዚህ ቀደም እ.ኤ.አ 2009 ላይ በተመሳሳይ ውድድር በጥሩነሽ\nዲባባ ተሻሽሎ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ጥሩነሽ በወቅቱ የርቀቱን ክብረወሰን 46፡28 በሆነ ሰዓት ስታሻሽል ከእሷ በፊት ክብረወሰኑ\n46፡55 በሆነ ሰዓት በጃፓናዊቷ ካዮኮ ፉኩሺ የተያዘ ነበር፡፡ ጥሩነሽ ይህን ክብረወሰን ባስመዘገበችበት ውድድር በወንዶች ባለቤቷ\nአትሌት ስለሺ ስህን ከዩጋንዳዊው ኒኮላስ ኪፕሮኖ ጋር እስከ መጨረሻ አንገት ለአንገት ተናንቆ በተመሳሳይ ሰዓት በመግባት አሸናፊ\nእንደነበር አይዘነጋም፡፡ ለተሰንበት በነገሠችበት የዘንድሮው ዓመት ውድድር በስቶች ኬንያዊቷ ኢቫሊን ቺርቺር 46፡32 በሆነ ሰዓት ሁለተኛ\nሆና ስታጠናቅቅ ሌላኛዋ ኬንያዊት ኢቫ ቺሮኖ 48፡14 በሆነ ሰዓት ሦስተኛ ደረጃን ይዛ ፈፅማለች፡፡ በወንዶች መካከል የተካሄደውን\nውድድር የሃያ ሦስት ዓመቱ ዩጋንዳዊ ስቲፈን ኪሳ 41፡49 በሆነ ሰዓት ማሸነፍ ችሏል፡፡ እሱን ተከትለው ኬንያውያኑ ኤድዊን ኪፕቶ\nበሁለት ሰከንድ ዘግይቶ ሁለተኛ፣ ሞሰስ ኮይች በ42፡05 ሰዓት ሦስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል፡፡አትሌት ለተሰንበት ግደይ ክብረወሰን ከማሻሻል ባለፈ ያሳየችው አስደናቂ አቋም ተስፋ እንዲጣልባት አድርጓል፣አዲስ ዘመን ህዳር\n9 ቀን 2012 ዓ.ምቦጋለ አበበ ", "passage_id": "9a8011dfb402f8a8d44870896ce6e824" } ]
f987ec66d457048433bca69cb0296099
1c88714479b8677ce89eed85faa70f55
ታላቁ ሩጫን በጥንቃቄ
 ቦጋለ አበበ የ20ኛው ቶታል ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጥር 2 ቀን ይካሄዳል። የውድድሩ ምዝገባ ባለፈው ታህሳስ 2 ቀን የጀመረ ሲሆን ፣ተሳታፊዎች በያሉበት የአሞሌን መተግበሪያ በመጠቀም ምዝገባውን እንዲያካሂዱ ተደርጓል ። የመጀመሪያዎቹ 200 ተሳታፊ ተመዝጋቢዎች ለውድድሩ መዘጋጃ የሚሆን የመለማመጃ ቲ-ሸርት በነጻ እንደሚሰጣቸውም የውድድሩ አዘጋጆች ከላኩት መግለጫ ታውቋል። 20ኛው ቶታል ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በዘንድሮ ውድድሩ ከወትሮው ለየት ባለ መልኩ 12ሺ500 ተሳታፊዎች ብቻ ይኖሩታል። በተጨማሪም የአለም አቀፍ ተሳታፊዎችን ለማካተት ውድድሩ በሚካሄድበት ተመሳሳይ ቀን በቨርቹዋል ውድድር በያሉበት ተሳታፊ እንዲሆኑና የ20ኛውን አመት ክብረ በዓል አብረው እንዲያከብሩ ቅድመ ሁኔታ ተጠናቋል። የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው መመሪያ መሰረት ከቀድሞ ተሳታፊ 25 በመቶ ብቻ አሳታፊ የሚያደርገው ታላቁ ሩጫ የሚከተሉትን የኮቪድ-19 ቅድመ ጥንቃቄዎች ተግባራዊ ያደርጋል። ውድድሩ የሚጀመረው በሶስት የተለያዩ ማዕበሎች(አረንጓዴ፤ ቢጫ፤ ቀይ) ይሆናል። ሶስቱ ማዕበሎች ወደ መስቀል አደባባይ የሚመጡበት አቅጣጫ በየቲሸርት ቀለሙ ተለያይቶ የተሰየመ ነው። እያንዳንዱ ማዕበልም ማህበራዊ ርቀትን ለማስጠበቅ ሲባል በ 3 እና በ4 ቡድን ይከፈላል። ሩጫው በሶስት የተለያዩ መነሻ ሰዓታት የሚደረግ ይሆናል፤ ተሳታፊዎች የሚጀምሩበትን ሰዓት እና አብረው የሚሮጡትን ቡድን ለመለየት ከሩጫ ቲ-ሸርታቸው ጋር አብረው የሚወስዱት የደረት የመሮጫ ፊደል ጠቋሚ ይሆናል። እያንዳንዱ ተሳታፊ ከሚመርጠው የቲ-ሸርት ቀለም ባሻገር የመወዳደሪያ የደረት ቁጥር በፊደል የሚወስዱ ይሆናል። ተሳታፊዎች የመሮጫ ቲ-ሸርታቸውን ሲወስዱ አብሮ የሚሰጣቸውን የአፍና አፍንጫ ጭንብል የውድድሩ መነሻ፤ የመሰበሰቢያ ቦታና ውድድሩን ከጨረሱ በኋላ ማድረግ ይኖርባቸዋል። ከዚያም በተጨማሪ ተሳታፊዎች መወዳደሪያ ቦታው ላይ እንደደረሱ እያንዳንዱ ተሳታፊ የሰውነት ሙቀት ልኬት ይደረግለታል።እንዲሁም በውድድሩ መነሻና መድረሻ የእጅ ማጽጃ ሳኒታይዘር ይቀርባል። ‹‹ወፎችን ታሳቢ ያደረገ የሀይል መሰረተ ልማት›› የ2013 የሩጫው መልዕክት ሲሆን፣ ‹‹በርድ ላይፍ አፍሪካ- የነጩ ጆፌ አሞራ ፕሮጀክት›› የዚህ መልዕክት አስተላላፊና አጋር ድርጅት ነው።የዚህን ዓመት ታላቁ ሩጫ ለየት የሚያደርገው የውድድሩ መነሻ መስቀል አደባባይ ሆኖ መድረሻው አትላስ አካባቢ መሆኑ ነው። ተሳታፊዎች ውድድሩ ሊካሄድ 10ቀናት ሲቀሩት የመወዳደሪያ ቲ-ሸርት፤ የመሮጫ የደረት ቁጥር ፊደል እና ጭምብል ምዝገባ ሲያደርጉ በመረጡዋቸው የዳሽን ባንክ ቅርንጫፎች በመሄድ መቀበል ይኖርባቸዋል።  አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 5/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=37370
[ { "passage": "አትሌቲክስ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ስፖርታዊ የውድድር መድረኮች በውጤታማነት ስሟን ለዓለም ያስተዋወቀችበትና ገናናነትን ያተረፈችበት መሆኑን ብዙዎችን የሚያስማማ ሀቅ ነው።ኢትዮጵያና አትሌቲክስ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች እንደመሆናቸውም ብርቅዬ አትሌቶቿ በዓለማችን ትልቁ የስፖርት መድረክ በኦሊምፒክና በሌሎችም ሻምፒዮናዎች ወርቅ ተለይቷቸው አያውቅም።\nከአትሌቲክስ ልዩ ልዩ ውድድሮች መካከል ደግሞ የረጅምና መካከለኛ ርቀት ሩጫ ውድድሮች ኢትዮጵያውያን በአህጉራዊና ዓለም አቀፍ ውድድሮች ተጠቃሽ ውጤት ያስመዘገቡባቸው የውድድር ፈርጆች ናቸው።በተለይም በረጅም ርቀት በዓለም ትኩረት ያገኘችበትና ኩራትን የተጎናጸፈችበት ስለመሆኑ የአትሌቶቻችን ድሎች ማሳያዎች ናቸው ።አትሌቶቻችን በዓለም አቀፍ ውድድሮች ከአንድ እስከ ሦስት ተከታትለው በመግባት ዓለምን ያስደመሙባቸው ወቅቶች በርካታ ናቸው።በዚህ ረገድ በሲድኒ ኦሊምፒክ የታየው ወርቃማ ታሪክ «አረንጓዴው ጎርፍ»ን (green flood ) ማስታወስ በቂ ምስክር ይሆናል።\nምንም እንኳን በዚህ ምልክ በተለይም ቀደም ባሉት ዓመታት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በአህጉራዊና ዓለም አቀፍ የረጅምና መካከለኛ ርቀት ሩጫ ውድድሮች ፈርጥ መሆን ቢችሉም አሁን ግን ይህ የቀደመ ውጤታማነታቸው አብሯቸው አለመሆኑን የሚያሳዩ ምልክቶች ይታያሉ።\nለዚህ የውጤት መራቅም በተለይ በአህጉርም ሆኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ዓመታትን ጠብቀው እስካልሆነ በአምስትና አስር ሺ ሜትር የሚካሄዱ ውድድሮች በእጅጉ መቀንስ፣ በምክንያትነት ይጠቀሳል። ይሁንና በአሁኑ ወቅት የጎዳና ውድድሮች መበራከታቸውን ተከትሎ በርካታ አትሌቶች ለአምስትና አስር ሺ ሜትር ውድድር የሚረዳ ልምምድ ከመስራት ይልቅ ለጎዳና ውድድሮች ትኩረት በመስጠት ወደዚያው መፍለሳቸው ዋነኛው ችግር ሆኖ ይጠቀሳል።አዲስ ዘመን ጋዜጣም በመም ውድድሮች በተለይ የአምስትና አስር ሺ ሜትር የኢትዮጵያን የቀድሞ ስምና ክብር በማስመለሱ ሂደት በአሁኑ ወቅት ዋነኛ ተግዳሮት የሆነውን የአትሌቶች ለጎዳና ውድድር ትኩረት መስጠት እና ወደ ጎዳና ውድድሮች መፍለስን እንዴት በመከላከል ውጤታማ መሆን ይቻላል ሲል የዘርፉ ባለሙያዎች አነጋግሯል።ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ አትሌቲክስ ክለብ ዋና አሰልጣኝ ንጉሴ ተፈራ፤ቀደም ባሉት ዓመታት በዓለም አቀፍ ደረጃ በአምስት እና አስር ሺ ሜትር ውድድሮች የዓለም ትኩረት ማረፊያ የነበረችው ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በርቀቱ ያላት ስምና ክብር በቀድሞው ልክ አለመሆኑን ይስማሙበታል።\nየዚህም ዋነኛ ምክንያት በሙሉ ለማለት በሚያስደፍር መልኩ አገሪቱ በርቀቱ የነበራትን ክብር ነገ ከነገ ወዲያ አስጥብቀው ይቀጥላሉ የተባሉ አትሌቶች ጭምር ወደ ጎዳና ውድድሮች ፈልሰዋል የሚሉት አሰልጣኙ፤አሁን ከአልማዝ አያና ውጪ በርካታ አትሌቶች በጎዳና በተለይ በማራቶን ውድድር መጠመዳቸውን ይጠቅሳሉ።ይህም ሁሉም ግላዊ ፍላጎቱን ወደ ማርካት ማድላቱና ገንዘብ ላይ በማተኮሩ የተፈጠረ መሆኑን የሚገልፁት አሰልጣኙ፤ ሁሉም ለማለት በሚያስደፍር መልኩ ማናጀሮች ትኩረት የሚሰጡት፣ አሰልጣኞችም የሚያሰለጥኑት አትሌቶችን ለጎዳና ውድድር ለማብቃት መሆኑን ይገልፃሉ።\nበተለይ ማናጀሮችና አሰልጣኞች አንድን አትሌት ነገ ስለሚካሄድ የጎዳና ውድድር እንጂ በቀጣይ ወራት ስለሚካሄድ ትላቅ አህጉር አቀፍ ሻምፒዮና ላዘጋጀው የሚል ሀሳብ የላቸውም» የሚሉት አሰልጣኙ፤አትሌቶቹ ወደ ጎዳና ውድድር እንዲያዘነብሉ በማድረጉ በኩል አብዛኛው ችግር ያለው አሰልጣኞቹ ዘንድ መሆኑን ያሰምሩበታል።‹‹የገንዘብ ጉዳይ ከሆነ ገንዘቡ በትራክ ውድድሮች ላይም አለ ›› የሚሉት አሰልጣኙ፤ በአግባቡ ከተሰራበት የትራክ ውድድርም ገንዘብ እንዳለውና ለዚህም ቀነኒሳ በቀለ፤ደራርቱ ቱሉ እነ ስለሺ ስህን የመሳሰሉ አትሌቶች በትራክ ውድድር ትልቅ ገንዘብ ሲያገኙ እንደነበር በማሳያነት በመጥቀስ ያብራራሉ።\nየአገሪቱን የቀደመ የረጅም ርቀት እውቅና እና ክብር መልሶ ለማስቀጠል የመም ውድድር አትሌቶችን በልዩነት መያዝ ይገባል የሚሉት ዋና አሰልጣኝ ንጉሴ፣ ለዚህም ራሱን የቻለ ህግ መውጣት እንዳለበት ነው የሚጠቁሙት፡፡ይህ እስካልሆነ ድረስ ነገም ከዚህ የከፋ አደጋ ውስጥ እንደምንወድቅ አልጠራጠርም»ይላሉ።እንደ ዋና አሰልጣኙ ገለፃ፤ በአሁኑ ወቅት ዓለም አቀፍ ውድድር በተቃረበ ቁጥር የጎዳና ተወዳዳሪ አትሌቶችን ወደ መም ለማምጣት ሲሞከር ይስተዋላል።ይሁንና በዚህ ዓይነት አካሄድ ውጤታማ ለመሆን መዳከር አግባብ አይደለም። እንደ የውድድሩ ባህሪም የሚገኘው ውጤትም ለየቅል የሆነውም ለዚሁ ነው።አንድ ሻምፒዮና ሲደርስ አትሌቶች ቢያንስ ከሦስት ወራት ቀድመው ማንኛውንም የጎዳና ውድድር ከማድረግ እንዲቆጠቡ ማድረግ እስካልተቻለ ድረስ አትሌቶች ከመም ውድድሮች ይልቅ ጉዳናን ምርጫቸው ከማድረግ እንደማይ ቆጠቡ ተናግረው፣ይህ አካሄድ የመም ውድድር አትሌቶችን እስከማሳጣት እንደሚደርስም ነው የሚያስገነዝቡት።ዋና አሰልጣኙ ይህን ችግር ለመፍታት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም አቅጣጫ ማስቀመጥ እንደሚኖርበት፣ለዚህም አዲስ አሰራር መተግበር የግድ እንደሚለው ይጠቁማሉ፡፡ ለአብነት ጎዳና ላይ የነበሩ አትሌቶች ከተወሰነ ወር በፊት ወደ ትራክ እንዳይመጡ፤የመም ተወዳዳሪ አትሌቶችም ከጎዳና ውድድር እንዳይመረጡ የሚገድብ ህግ መተግበር እንዳለበት ያስገንዝባሉ።አሰልጣኝ ሙልዬ እያዩም ኢትዮጵያ በተለይ በረጅም ርቀት የመም ውድድሮች የነበራት ዝና መደብዘዙን ይስማሙበታል።የዚህም ዋነኛ ምክንያት የጎዳና ውድድሮች በዓለም አቀፍ ደረጃ ትኩረት እየተሰጣቸው መምጣቱ መሆኑን ያሰምሩበታል።\nእንደ አሰልጣኝ ሙልዬ ገለፃ፤በአሁኑ ወቅት ከ27 ሺ 800 በላይ የጎዳና ውድድሮች በየዓመቱ ይካሄዳሉ። እነዚህ ውድድሮችም ከጊዜ ወደ ጊዜ አዝናኝነታቸው ተመራጭ እየሆነ በመምጣቱም አዘጋጅ አገራት የአትሌቶቹን ቀልብ በእጅጉ መቆጣጠር ከመቻላቸውም በተጨማሪ ፣በተለይ በቱሪዝም ዘርፉ ለገቢ ምንጭነት እየተጠቀሙት ይገኛሉ።ይህ እንደመሆኑ ኢትዮጵያን በርቀቱ የመወከል አቅም ያላቸው ወጣት አትሌቶች ጭምር ወደ ጎዳና እየፈለሱ መሆናቸውን የሚያረጋግጡት አሰልጣኝ ሙልዬ፤ይህ ማለት ግን የውድድሮቹ መብዛት አትሌቶቹን ወደ ጎዳና ስቧቸዋል አሊያም ማናጀሮቻቸው በሚያሳድሩባቸው ጫና ወደ ጎዳና ውድድር ሄደዋል ለማለት እንደማያስደፍር ያስቀምጣሉ።አትሌቶች ከትራክ ውድድር ይልቅ ለጎዳና ውድድሮች ቅድሚያ እንዲሰጡ በአሰልጣኝና ማናጀሮቻቸው በኩል ጫና ይደርስባቸዋል የሚለውን አስተያየት አሰልጣኙ አይስማሙበትም፡፡ይህ ማለት ለግል ጥቅማቸው ሲሉ አትሌቶችን ለጉዳት በሚዳርግ መልኩ ለረጅም ጊዜያት ከሳምንት እስከ ሳምንት በአስፋልት ውድድር ሙሉ ስልጠና የሚሰጡ አንዳንድ ማናጀሮች የሉም ማለት እንዳልሆነም ይጠቁማሉ።\nአትሌቶች ወደ ጎዳና ውድድሮች የሚፈልሱት በማናጀሮቻቸው ገፋፊነት ብቻም ሳይሆን በአብዛኛው በግል ውሳኔ ቀደም ሲል የነበሩ አትሌቶችን በመመልከት ነው የሚሉት አሰልጣኙ፤አትሌቶችም በውድድር በመካፈላቸው ብሎም ካሸነፉ የሚያገኙት ጥቅም ከፍተኛ በመሆኑም የጎዳና ውድድሮችን እንዲመርጡ እያስገደዳቸው መሆኑን ያስገነዝባሉ።አሰልጣኙ በዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ትላልቅ መድረኮች የአምስት እና አስር ሺ ሜትር ሩጫ የምስራቅ አፍሪካውያን መድመቂያ ነው፤ ኢትዮጵያውያንም የዚህ ድምቀት ፈጣሪዎች ናቸው፡፡ ይሁንና ይህ ትዕይንት አሁን ደብዝዟል ከማለት የቀደመውን ስምና ዝናችንን እንዴት መመላስ እንችላለን የሚለውን መመለስ ይገባል ሲሉ ያመለክታሉ።\nለዚህም በቀዳሚነት የመም ውድድር አትሌቶችን እንዴት በብቃት ማፍራት እንዲሁም ወደ ጎዳና የፈለሱትን በምን መልኩ ፊታቸውን እንዲያዞሩ ማድረግ ይቻላል የሚለውን የሚመለስ ተግባር መፈፀም እንደሚገባ ይጠቁማሉ።«ይህን ለማድረግ በቀዳሚነት በትራክ ውድድር የሚሳተፉ አትሌቶች የሚያገኙትን ጥቅም ከፍ ማድረግ ያስፈልጋል›› የሚሉት አሰልጣኙ፤አትሌቶች ወደ ጎዳና የመውጣታቸው ምክንያት ህይወታቸውን ለመደጎም መሆኑን ይገልጻሉ፡፡ይህን ችግር ለመፍታትም በመም ውድድር ለሚካፈሉት ከፍ ያለ ሽልማት ማዘጋጀት እንደሚያስፈልግ በመጠቆም፣ይህ ሲሆንም ተተኪ አትሌቶች ማግኘት እንደሚቻል ያመለክታሉ።ከዚህም ባሻገር በዚህ ዘርፍ ፍላጎት ያላቸውን ልጆች ማፍራት እንደሚገባ በመጠቆም፣ ለዚህም የተመረጡት ልጆች ቀጣይነት ባለው መልኩ ህይወታቸውን መምራት የሚያስችላቸው ራሱን የቻለ ፕሮጀክት መቅረጽ እንደሚያስፈልግም ይገልጻሉ።\nእንደ አሰልጣኙ ገለፃ፤ትራክ ላይ የሰራ አትሌት ውድድር ለማግኘት አንድና ሁለት ዓመት መጠበቅ ግድ ይለዋል።ከዚህ ባንፃሩ የጎዳና ውድድሮችን ቶሎ ቶሎ ማግኘት ይችላል።ይህ በሆነበት የጎዳና ውድድር መምረጡ አይቅሬ ነው።በመሆኑም መሰል ችግሮችን ለመፍታት የውድድር ተደራሽነት መስፋት ያስፈልጋል፡፡ በመም ውድድሮች በተለይ በአምስትና አስር ሺ ሜትር የኢትዮጵያን የበላይነት የውጤት ክብር ለማስቀጠል ውድድሮችን በውጭም ሆነ በአገር ውስጥ በማዘጋጀት ተደራሽነቱን ማስፋት ያስፈልጋል። ምንም እንኳን የጎዳና ላይ ሩጫዎች ተበራክተው የትራክ ውድድር ቢያንስ ሁለቱን ለማስታረቅ አትሌቶቹ ራሳቸውን ሳይጎዱ የሚካፈሉባቸው የልምምድ ዓይነቶችን ማዘጋጀትም የተሻለ ውጤት ማምጣት ይቻላል።\n«የጎዳና ላይ ውድድር የግል ህይወትን ማሻሻያ እንጂ ለክብር እና ለአገር ተብሎ የሚሮጥበት አይደለም» የሚሉት አሰልጣኝ ማሙዬ፤ከሁሉም በላይ አትሌቶች ለአገርና ለክብር ያላቸውን ስሜት በቃል ብቻ ሳይሆን በተግባር በድጋሚ እንዲያ ረጋግጡ ግንዛቤ የማስረፅ ተግባር ማከናወን እንደሚገባም ይገልጻሉ።የኢትዮጵያ አትሌቶች ማህበር ፕሬዚዳንትና ተወካይ አትሌት ስለሺ ስህን፤ በአሁኑ ወቅት የአስርና አምስት ሺ ሜትር የመም ውድድሮች ከቀደመው ጊዜ አንፃር ሲታይ በእጅጉ መቀነሳቸውን ጠቅሶ፣ ሙሉ በሙሉ ጠፍተዋል ለማለት እንደማያስደፍር አሁንም ትልልቅ ውድድሮች እንዳሉ ያብራራል።የግል ጥቅም አትሌቶቹ ወደ ጎዳና ለመውጣታቸው ምክንያት እንደማይሆን የሚናገረው አትሌት ስለሺ፣ በመም ውድድሮች ላይ ውጤታማ መሆን ከማራቶን ባልተናነሰ በስፖንሰር፤በዳይመንድ ሊግ የመመረጥ እና ሌሎችም ረብጣ ሽልማቶች የሚያስገኝበት ሁኔታ እንዳለም ያስረዳል።ለዚህም አሁንም በመም ውድድር አልማዝና እና ገንዘቤ እንዲሁም ሰለሞን ባረጋ እየሮጡ መሆናቸውን በአብነት ይጠቅሳል።\n‹‹እርግጥ ነው ማራቶን ጥቅም ሊኖረው ይችላል።ይሁንና ማራቶን በመጪዎቹ የአትሌቲክስ ዕድሜዎች የሚደረስበት ውድድር ነው›› የሚለው አትሌት ሰለሺ፤ ከጎዳና ውድድሮች በተለይም አንድ ጊዜ ማራቶን ላይ ገብቶ ሁለትና ሦስት ዓመታት ከቆዩ በኋላ ጨርሶኑ መጥፋት ጉዳት እንጂ ጥቅም እንደሌለውም ነው ያብራራው።በአሥርና አምስት ሺ ላይ የሚቆይ አትሌት ወደ ማራቶን ሲሄድ ውጤታማ መሆን እንደሚ ችልና በተለይ ወጣት አትሌቶች በልጅነት ዕድሜያቸው ወደ ማራቶን ከሚገቡ በመም ውድድሮች ላይ ብዙ ዓመታት መስራት ቢችሉ ውጤታማ ስለመሆናቸው ጥርጥር ሊገባቸው እንደማይገባም ይጠቁማል።\nእንደ አትሌት ስለሺ ገለፃ፤ይህን ችግር ለመፍታት በቀዳሚነት አትሌቶች ቸኩለው ወደ ጉዳና መውጣታቸው ስህተት እንደሆነና በቀጣይ የሩጫ ህይወታቸው ውጤታማነት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚያሳርፍ ጠንቅቀው እንዲረዱት ግንዛቤ ማስጨበጥ ያስፈልጋል፡፡ በዚህ ዓይነት ውድድር ውስጥ ለማለፍ እንደማይጠቅም በውድድሩ ቢያልፉም ውጤታማ እንደማይሆኑ ማስረዳት ይገባል፡፡ በመም ውድድሮች በስለው ወደ ጎዳና ውድድሮች ቢሄዱ የበለጠ ውጤታማ እንደሚሆኑ ማስገነዘብ የግድ ይላል።ከሁሉም በላይ የአገር ፍቅር ስሜት የሚባለው እንዲሰርፅባቸው ማድረግ ይገባል።አንድ አትሌት ወደ ጎዳና የሚወጣው በአሰልጣኝ አሊያም ማናጀሩ ከፍተኛ ጫና እያሳደረበት ከመሆኑ ጋር በተያያዘ መሆኑን የሚመሰክረው አትሌት ስለሺ፤እነዚህ ገንዘብ ተኮር የሆኑ አሰልጣኝና ማናጀሮችን መቆጣጠር እንደሚያስፈልግ ይናገራል፡፡ይህን ችግር መፍታትም የፌዴሬሽኑ ኃላፊነት መሆኑን ይናገራል።\nየኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቴክኒክ ዳይሬክተር አቶ ዱቤ ጅሎ፤በዓለም አቀፍ ደረጃ የመም በተለይ የአሥርና አምስት ሺ ሜትር ውድድሮች እየቀነሱ መምጣታቸውን ጠቅሶ፣ ፌዴሬሽኑም ራስ ምታት እንደሆነበት ይገልጻል፡፡ በተጠቀሱት ውድድሮች ሚኒማ ለማሟላት አትሌቶች ወደተለያዩ አገራት በመላክ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ እየከፈለ መሆኑንም ይገልፃሉ።ከመልክዓ ምድር ጋር በተያያዘ በአዲስ አበባ ስታዲየም ላይ ዓለም አቀፉ ፌዴሬሽን የሚያስቀም ጠውን ሚኒማ ማሟላት አይቻልም፤ይህ እንደመሆኑ ፌዴሬሽኑ አትሌቶችን በመምረጥ ወደ ተለያዩ አገራት በመውሰድ እያወዳደረ መሆኑንም ያስረዳሉ።\nየረጅም ርቀት ውድድሮች እያበቃላቸው፤ የጎዳና ላይ ውድድሮች እየተበራከቱ መምጣታቸውና ሽልማታቸውም እየገዘፈ በመሆኑ አሰልጣኞች፤ ማናጀሮች እንዲሁም አትሌቶች ወደ ጉዳና እየፈለሱ መሆናቸውን ፌዴሬሽኑንም እንደሚያሳስበው ያስረዳሉ።ይህ ችግር እያደር በመባባሱም ፌዴሬሽኑ በተለይ አጭር ርቀት ላይ እንዴት እንስራ የሚለውን አቅጣጫ እስከመከተል እንዳደረሰው የሚገልፁት አቶ ዱቤ፤ፌዴሬሽኑም ክልሎችና ክለቦችን በመደገፍ የትራክ አትሌት የማይጠፋበት ሁኔታ እንዲፈጠር የበኩሉን እያደረገ መሆኑንም ነው ያስረዱት።አሁን የመም ውድድሮችን የሚሳተፉ አትሌቶችን ለመለየትና ለማብቃት እንቅፋት ከሆኑት መካከል አንደኛው የመወዳደሪያ ቦታ እጥረት መሆኑንም የሚያስረዱት አቶ ዱቤ፤በቀጣይ የመም ውድድር ራጮችን ፍፅሞ ከማጣት ቀድሞ መሰል የመወዳደሪያ ቦታ እጥረቶች መስተካከል እንደሚገባ ይናገራሉ፡፡ለዚህም ሁሉም ባለድርሻ አካላት የየበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ ያቀርባሉ።\nየኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም ስፖንሰር አድራጊ ተቋማትን ፈልጎ እንዲሁም የአገር ውስጥ ውድድሮችን በማዘጋጀት ተወዳዳሪ አሸናፊዎች የተሻለ ጥቅማ ጥቅም የሚያገኙበትን አሰራር መዘርጋት እንዲሁም ለትራክ ተወዳዳሪዎች የሚሰጠውን ሽልማት ከፍ ለማድረግ መስራት እንደሚገባ ይጠቁማሉ።ታምራት ተስፋዬ", "passage_id": "29de9c359db0ea3019780eda698c1526" }, { "passage": "በ12/12/12 የሚደረገውን 5ኛው “የቡና ቤተሰባዊ ሩጫ”ን በተመለከተ ዛሬ ከሰዓት በክለቡ የፅህፈት ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ መግለጫ ተሰጥቷል።ይጀመራል ተብሎ ከነበረው ሰዓት 35 ደቂቃዎችን አርፍዶ የተጀመረውን ጋዜጣዊ መግለጫ የክለቡ ፕሬዝዳንት መቶ አለቃ ፈቃደ ፣ የክለቡ ስራ አስኪያጅ አቶ ገዛኧኝ፣ የደጋፊዎች ማህበር ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ሰለሞን እና ደጋፊዎች ማኅበር የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ክፍሌ ሰጥተዋል። በቅድሚያም የክለቡ ፕሬዝዳንት መቶ አለቃ ፈቃደ እና የክለቡ ስራ አስኪያጅ አቶ ገዛኸኝ ስለ ቤተሰባዊ ሩጫው መጠነኛ ገለፃ አድርገዋል።“ምንም እንኳን ኮቪድ-19 መጥቶ መደበኛ ሥራችንን ቢያስተጓጉለንም የክለባችን ደጋፊዎች ዓመታዊው ሩጫው ዘንድሮ እንዲደረግ ከፍታኛ ፍላጎት ነበራቸው። ምክንያቱም ደጋፊዎቻችን የክለቡ 12ኛ ተጫዋች ስለሆኑ በዚህ ዓመት የተከሰተውን አጋጣሚ(12/12/12) ማለፍ አልፈለጉም። እንደዚህ አይነት የቀን መገጣጠሞችም ከብዙ ዓመት አንድ ጊዜ ስለሆነ የሚከሰተው እኛም ነገሩን አጤነው። ግን ቀኑን አስበው ሩጫው ይደረግ የሚል ጥያቄ ያነሱት ደጋፊዎቻችን ናቸው። እኛም ይህንን በማሰብ አጋጣሚው እንዳያልፈን የተለያዩ ውይይቶችን ስናደርግ ነበር። በዚህም በስራ አስኪያጃችን አቶ ገዛኸኝ የሚመራ ኮሚቴ አዋቅረን ስራዎችን ስንሰራ ቆይተናል። በዋናነት ደግሞ ኮሚቴው ደጋፊዎቻችን በቨርቹዋል የሚወዳደሩበትን ነገር ሲሰራ ቆይቷል።” በማለት የዘንድሮ ውድድር ቀጣይነት እንዲኖረው እና በኮቪድ ምክንያት እንዳይቋረጥ የነበረውን የደጋፊዎች ፍላጎት አስረድተዋል።ከፕሬዝዳንቱ በመቀጠል የክለቡ ሥራ አስኪያጅ እና 5ኛውን የክለቡን የቤተሰብ ሩጫ ለማከናወን የተዋቀረውን ኮሚቴ ሲመራ የነበረው አቶ ገዛኸኝ መድረኩን በመረከብ በቦታው ለተገኙ የብዙሃን መገናኛዎች ማብራሪያ ሰጥቷል።“እንደሚታወቀው የኮቪድ ወረርሽኝ የዓለም ትላልቅ ውድድሮችን አሰርዟል። እኛም የዓለም አንዱ አካል ስለሆንን ውድድሩን እንደ ተለመደው ማድረግ አንችልም። ነገርግን ውድድሩ ቀን ተቆርጦለት ታስቦ እንዲውል ማድረግ እንችላለን በሚል ስራዎችን ስንሰራ ቆይተናል። የቡና ደጋፊ ደሞ ትክክለኛ 12ኛ ተጫዋች ስለሆነ ታሪካዊውን ቀን(12/12/12) ማሳለፍ አልፈለግንም። እንደሚታወቀው ውድድሮች ባለመኖራቸው ክለቡ በፋይናንስ ተጎድቷል። ስለዚህም ውድድሩ በተዘዋዋሪ ለክለቡ የገቢ ማሰባሰቢያም ነው። ይህ ቤተሰባዊ ሩጫ ከሌሎቹ የሚለየው በጋራ ሆነን የምንሮጥበት አደለም። ግን በሃገራችን የተደነገገውን አዋጅ ሳንጥስ የተለያዩ ፕሮግራሞችን በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች ለማድረግ አስበናል። በታሰበው እድቅድም መሰረት ታስቦ በሚውለው ይህ ታሪካዊ የክለቡ የሩጫ መርሃ ግብር ላይ 40 ሺ ደጋፊዎች እንዲሳተፉ እናደርጋለን። ሩጫው እንደ መደበኛ ሩጫ የሚሮጥበት ስላልሆነ ለ40 ሺ ደጋፊዎቻችን ሜዳልያ አናዘጋጅም። ግን በይዘቱ ለየት ያለ የምስክር ወረቀት(ሰርተፊኬት) ለደጋፊዎቻችን እንሰጣለን። በሰርተፊኬቱ ላይም የሚመዘገቡት የሩጫው ተሳታፊ ደጋፊዎቻችን ስማቸው በዳታ ቤዝ እንዲቀመጥ እናደርጋለን።”ብለዋል። አቶ ገዛኸኝ ጨምረውም ኮሚቴው ከተዋቀረበት ጊዜ ጀምሮ ሩጫው ታስቦ የሚውልበትን ቀን የመወሰን፣ የሚለበስ ማሊያ የማዘጋጀት፣ የሰርተፊኬት አዘገጃጀቶችን እና የአፍ ጭምብል የማዘጋጀት ሥራዎችን እንዳከናወነ ጠቁመዋል።ከሁለቱ አካላት ማብራሪያ በመቀጠል በስፍራው የተገኙ የብዙሃን መገናኛ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችን አንስተው መልሶች እና ገለፃዎች ተደርገዋል።“በ5ኛው የቡና የቤተሰብ ሩጫ ላይ ክለቡ ከወጪ ቀሪ 4 ሚሊዮን ብር ለማግኘት አቅዶ ነው እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው።” አቶ ገዛኸኝ“ከዚህ በፊት ያከናወናቸው 4 ዓመታዊ የቤተሰብ ሩጫዎች በሁለት መንገድ ጠቅመውናል። አንደኛው ክለቡን በፋይናንስ በማጠናከር ረገድ ነው። በተለይ የመጀመሪያዎቹ ሩጫዎች የክለባችንን ካምፕ ለመገምቢያ ረድቶናል። ሌሎቹም ለተለያዩ የክለቡ የመሰረተ ልማት ወጪዎች በሚገባ አገልግለዋል። ሁለተኛው ጠቀሜታ ደግሞ በደጋፊዎቻችን መካከል ቤተሰባዊ ስሜትን በመፍጠር ረገድ ነው። ስለዚህ በየአመቱ የምናደርጋቸው ሩጫዎች በሚገባ ጠቅመውናል” አቶ ገዛኸኝ“የኢትዮጵያ ቡና የገቢ ምንጮች በዋናነት አራት ናቸው። እነሱም ክለቡ ከቡና ሴክተሩ ፣ ከማሊያ ሽያጭ፣ ከስፓንሰር እና ከሜዳ ገቢ የሚገኙ ናቸው። በተለይ የሜዳ ገቢን በተመለከተ ዘንድሮ ጥሩ ጥቅሞችን እያገኘን ነበር። በተለይ የሜዳ ገቢያችንን እራሳችን መቆጣጠር ከጀመርን አንስቶ ጥሩ ገንዘብ እያገኘን ነበር። በሜዳችን ካደረግናቸው 8 ጨዋታዎች እንኳን 5.5 ሚሊዮን ብር በጠቅላላ አግኝተናል። እንደውም በትንሹ በየጨዋታው 7 እና 8 መቶ ሺ ብሮችን ስናገኝ ነበር። ነገር ግን ውድድሩ ተቋረጠ። መጀመሪያ ላይ እኛ እንደውም ከሜዳ ገቢ 12 ሚሊዮን ብር ለማግኘት አቅደን ነበር ስንቀሳቀስ የነበረው። ግን ውድደሩ ተቋረጠ። ከሜዳ ገቢ ውጪ ከቡና አቅራቢዎች እና ላኪዎች ከ12-14 ሚሊዮን ብር እናገኛለን። ከስፓንሰራችንም (ሀበሻ ቢራ) በዓመት ከ25-28 ሚሊዮን ብር እናገኛለን። ሀበሻ ቢራ እንደውም በተጨማሪነት በዓመት ውስጥ አራት ፕሮግራሞችን ካዘጋጀን 2 ሚሊዮን ብር(ለአንዱ ፕሮግራም 500 ሺ ብር) ሊሰጠን ተስማምተናል። ስፓንሰራችን ቀጣይም አብሮን እንዲሆን ውይይቶችን እያደረግን እንገኛለን። በጎ ነገሮችም ይኖራሉ ብለን እናስባለን። አሁን የሚደረገው ሩጫ ላይም ሀበሻ ቢራ አብሮን አለ። የወደፊቱን ግን እየተነጋገርን ነው። በቀጣይ የሚያሳስበን ገቢያችንን እንዴት ከስፖንሰር እናገኛለን የሚለው ነው። በተለይ ውድድር ይኑር አይኑር ሳይታወቅ አጋሮችን መፈለግ ከባድ ነው። ነገርግን በግሌ ከቡና ሴክተሩ የምናገኘው ገቢ የሚቀንስብን አይመስለኝም።” መቶ አለቃ ፍቃደ“የቡና ቤተሰቦች 12/12/12ን እንደ በዓል አይተን ነው የምናከብረው። የሚገርመው ሩጫው ታስቦ ይውላል ቢባልም የማሊያ ፍላጎቱ ግን በጣም ጨምሯል። እንደውም ከከዚህ ቀደሞቹ ዓመታዊ ሩጫዎች በበለጠ ደጋፊዎቻችን ማሊያውን ለመግዛት እየተሯሯጡ ነው። በጥቂት ቀናት ውስጥም ሽያጮችን እናጠናቅቃለን የሚል እምነት አለኝ። በዚህ አጋጣሚ ማሊያ ካለቀ በኋላ ፋላጎት እንደአዲስ እንዳይነሳ ደጋፊዎች ከአሁኑ ቢገዙ መልካም ነው።” አቶ ገዛኸኝ“እንዳልነው ሁሉም ደጋፊዎች ተሰብስበው ባይሮጡም የተለያዩ ስራዎችን በታሪካዊቷ ቀን ለማከናወን አቅደናል። በዚህም በእለቱ ደጋፊዎቻችን የአረንጓዴ አሻራቸውን እንዲያኖሩ እናደርጋለን። በዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር ቦታ እንዲፈቀድልን ንግግር እያደረግን ነው። በተጨማሪም ደጋፊዎቻችን በእለቱ የደም ልገሳ እንዲያደርጉ ከደም ባንክ ጋር ውይይት እያደረግን ነው። ከዚህ ውጪ በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ የምስኪኖቸን ቤት የማደስ እና አቅመ ደካሞቸን የማገዝ መርሃ ግብሮችን እናደርጋለን።” አቶ ገዛኸኝ“ክለቡ ከሚያከናውናቸው ፕሮግራሞች በተለየ ይህ ዓመታዊ ሩጫ ለእኛ በጣም ነው የተሳካልን። እቅዳችንም በአጭር ጊዜ ውስጥ የሩጫውን ተሳታፊዎች ወደ 100 ሺ ከፍ ማድረግ ነው። ዘንድሮ ይህንን ማድረግ ባንችልም በቅርብ ጊዜ የተሳታፊዎቹን ቁጥር አሳድገን ለማከናወን እናስባለን።” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ12/12/12 የሚውልበት ቀን ማክሰኞ ቢሆንም ደጋፊዎች በያሉበት ክለባቸውን እያሰቡ የበዓሉ አንድ አካል እንዲሆኑ እና የታሰቡትን በጎ ስራዎች እንዲሰሩ ጥሪ ቀርቧል። ከጥያቄ እና መልስ በኋላም ለደጋፊዎቹ የተዘጋጁት የመሮጫ ማሊያ፣ ማስክ እና ሰርተፍኬት በቦታው ለተገኙ ጋዜጠኞች ይፋ ሆኗል።*ከክለቡ የዝውውር ሁኔታ ጋር ተያይዞ በቦታው የተነሱ ማብራሪያዎችን ከቆይታ በኋላ ይዘን እንቀርባለን።", "passage_id": "aff37714ffb2b1fb6f3a9d8ab3b9994f" }, { "passage": " የታሪክ ድርሳናት እስከ 19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ድረስ የዓለም ስፖርት ካንቀላፋበት ፆታን እኩል ያለመመልከት ቅዠት እንዳልነቃ ይመሰክራሉ። ባልተሞከረና ባልተረጋገጠ ሁኔታ ‹‹አትችልም›› የሚል መላ ምት ሚዛን ደፍቶ ዘመናትን በመሻገሩ እጅግ ተወዳጁና ተመራጩ የመዝናኛ ዘርፍ ወደ አንድ ጎን ያዘነበለ ነበር። ሴት በስፖርት ትጥቅ ከሜዳ መገኘቷን ባለመቀበል አስተሳሰብ የተሸበቡትን ለማሳመንም በርካቶች ባልተፈቀደ መንገድ መገኘት ግድ ሆኖባቸዋል። ‹‹ነውር›› ለሚሏቸው ጆሯቸውን ሳይሆን ጀርባቸውን በሰጡ ደፋርና ቆራጥ ሴቶች መቻላቸውን በማስመስከር ዓለም የዛሬውን ቅርጽ እንዲይዝ አድርገዋል። የዛሬውን የሴቶች ቀን አስመልክቶም ‹‹ባልተፈቀደው›› መንገድ ከተጓዙ እንስቶች መካከል የአንዲትን ሴት ታሪክ ልናስታውስ ወደድን። በዓለም ላይ ዋና ዋና ከሚባሉት ስድስት ታላላቅ የማራቶን ውድድሮች መካከል አንዱ የቦስተን ማራቶን ነው። መነሻውን እኤአ 1897 ያደረገው አንጋፋው የጎዳና ላይ ሩጫ የ122 ዓመት እድሜ ባለጸጋም ነው። ታዲያ በዚህ ውድድር ተሳታፊ እንዲሆኑ ይፈቀድላቸው የነበሩት ወንድ አትሌቶች ብቻ ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ የሴቶች ተሳትፎ የሚጀምረው ዘግየት ብሎ ነው። በዓለም አትሌቲክስ ታላቅ ስፍራ ያለው ይህ ማራቶን የተለያዩ ክስተቶችን በተለያዩ ዓመታት ቢያስተናግድም ከሁሉም ይልቅ ሴቶች በሩጫው ላይ እንዲታዩ መሰረት የጣለው ድራማዊ ክስተት መቼም የሚዘነጋ አይደለም። እኤአ 1967 የቦስተን ማራቶን ተሳታፊ ለመሆን ከተመዘገቡት ወንድ ሯጮች መካከል ኬቪ ስዊዘር የሚል ስም ይገኝበታል። ስሙ በአጭሩ የተመዘገበ በመሆኑ ጾታው በትክክል የሚለይ ባይሆንም ለሩጫው ፈቃድ የሚያገኙት ወንዶች ብቻ በመሆናቸው ይህ ይከሰታል በሚል የጠረጠረ አልነበረም። የውድድሩ ዕለት ደርሶ የሩጫ ማስጀመሪያው ከተበሰረ በኃላ ግን ሯጮች ያዩትን ማመን አልቻሉም። ምክንያቱ ደግሞ በከባዱ የማራቶን ሩጫ ከእነዚያ ሁሉ ወንዶች መካከል አንዲት ሴት በመታየቷ ነው። ከቆይታ በኋላ ግን ክስተቱ ከሯጮችም አልፎ ከመንገዱ ዳር ቆመው ከሚያበረታቱና ለዘገባ በተሰየሙ የመገናኛ ብዙሃን እይታ ውስጥ ይገባል። ጉዳዩ ያስደነቃቸው የፎቶግራፍ ባለሙያዎችም ሩጫውን እየተከተሉ ካሜራቸውን ወደዚያው መደቀናቸውን ተያያዙት። ይህ ትዕይንት በዚህ ሁኔታ እንዳለ ግን በጎዳናው ግራና ቀኝ ካሉት ተመልካቾች መካከል ባልተለመደ መልኩ አንድ ሰው ሩጫውን ተቀላቀለ። የውድድሩን ክልል ጥሰው የገቡት አንጋፋ ሰውም እሳት ለብሰውና እሳት ጎርሰው ከሴቷ ሯጭ ጋር ግብግብ ጀመሩ፤ ነገር ግን ገላጋዮች በመሃል በመግባታቸው ከጀመረችው ሩጫ ሊገቷት አልቻሉም።ዕድሜ ሰጥቷት ዛሬን ለመመልከት የበቃችው የዚህ ታሪክ ባለቤት ካትሪን ስዊዘር ትባላለች። በጊዜው የሆነውን ስትተርክም ‹‹በረጅም ርቀት ሩጫዎች ላይ ሴቶች ለምን አይሳተፉም የሚለው የሁልጊዜም ጥያቄዬ ነበር። በሩጫው ላይ ለመሳተፍ ስነሳም እንዳይለዩኝ በሚል ስሜን አሳጥሬ ኬቪ ስዊዘር አደረኩት፤ በውድድሩ ዕለትም ከአሰልጣኜና የእግር ኳስ ተጫዋች ከሆነው ፍቅረኛዬ ጋር ተገኘሁ። ሩጫውን እንደጀመርንም ብዙዎች ሴት መሆኔን በመመልከት ተደንቀው ሲያዩኝ ‹‹አዎ እኔ ሴት ነኝ›› እላቸው ነበር፤ የካሜራ ባለሙያዎችም ፎቶ ሊያነሱኝ ሲከተሉኝ እንደነበር አስታውሳለሁ። ከቆይታ በኋላ ግን የውድድሩ ዳይሬክተር በንዴት ወደእኔ መጣ፤ የመሮጫ ቁጥሩን ስጪኝና ከዚህ ውድድር ውጪ እያለ ይጮህና ይጎትተኝም ነበር። በፊቱ ላይ ይታይ የነበረው ብስጭት የሚያስፈራ ቢሆንም አብሮኝ የነበረው ፍቅረኛዬ በመሃላችን በመግባት እኔን ወደፊት እንድሄድ ነገረኝ። አንዳንድ ሯጮች ግን ከኋላዬ እስኪቀሩ ድረስ ‘መቻልሽን ለማስመስከር ነው ምትሮጪው፣…?’ በማለት ሲያሾፉብኝ ነበር›› ትላለች በተንቀሳቃሽ ምስል የታገዘውን የዚያኔውን ሁኔታ ስታስታውስ።ካትሪን ከዚያ በኋላ የነበሩትን ኪሎ ሜትሮች የሸፈነቻቸው ያለማንም ጣልቃ ገብነት ነበር። ፍቅረኛዋ ሩጫውን ስለማጠናቀቅ በጠየቃት ጊዜም ‹‹በእጄና ጉልበቴ ድኼም ቢሆን እጨርሰዋለሁ አልኩት፤ ምክንያቱም ሩጫውን ካላጠናቀቅኩ ማንም የሴትን መቻል አይረዳም እያልኩ አስብ ነበር። እጨርሰዋለሁ እንዳልኩትም በ 4ሰዓት ከ20 ደቂቃ የመጨረሻውን መስመር ረገጥኩ፤ ምሽት ላይ ወደ ቤታችን ስንመለስም ክስተቱ ህይወቴን እንደቀየረው ተገነዘብኩ። ምክንያቱም በመንገዳችን ላይ ቡና ለመጠጣት ካረፍንበት ስፍራ ፎቶዬን የያዙና እኔን ዜና ያደረጉ በርካታ ጋዜጦችን በመመልከቴ ነው። በመጨረሻም ያደረኩት ነገር ሴቶች በስፖርት ያላቸውን ታሪክ ይቀይር ይሆናል በሚል ተስፋ አሳደረብኝ›› ትላለች ጠንካራዋ ካትሪን ስዊዘር። የ73 ዓመቷ ካትሪን ዛሬ ደራሲና የቴሌቪዥን አስተዋዋቂ ሆናለች። እርሷ የጀመረችው በቦስተን ማራቶን የሴቶች ተሳትፎም ከአምስት ዓመት በኋላ እኤአ በ1972 እውን ሲሆን፤ እኤአ በ1975 ለሁለተኛ ጊዜ ተሳትፋ የራሷን ምርጥ ሰዓት (2:51:37) በማስመዝገብ አሸናፊ ሆናበታለች። አሁን ዓመታዊው የቦስተን ማራቶን ሲካሄድ በክብር እንግድነት ትገኛለች፤ ሌሎች ሴቶች ሲመለከቷትም ለቅሶ እንደሚቀድማቸው ትናገራለች። የመጀመሪያ ሩጫዋን ባደረገችበት ዓመት የመሰረተችው የሴቶች ማህበርም እስከሁንም በአሜሪካ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል። አዲስ ዘመን\nየካቲት 29 /2012  ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "62db70ce50bc06bee8fd179408ba0e6e" }, { "passage": "በሩጫው ላይ 44 ሺህ ተወዳዳሪዎች ይሳተፋሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን 400 የሚሆኑት ከሌሎች ሀገራት የመጡ ሲሆን 5 አትሌቶች ደግሞ ኤርትራን በመወከል ይሳተፋሉ።\n\n• በሃሰተኛ ዜናዎች \"የሞቱ\" የኪነጥበብ ሰዎች\n\n• በካማሼ ዞን የመንግሥት ስራ ተቋርጧል\n\n• ኤርትራ ላይ የተጣለው ማዕቀብ ተነሳ \n\nበ10 ሺህ ሜትርና በግማሽ ማራቶን ዝነኛ የሆነው አትሌት ዘረሰናይ ታደሰ ውድድሩ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ተገኝቷል።\n\n\"ኢትዮጵያ በመምጣቴ በጣም ደስ ብሎኛል። የውድድሩ አዘጋጆችንም ስለጋበዙኝም አመሰግናለሁ\" ብሏል።\n\nእኤአ የ2012 ኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ የሆነው ዩጋንዳዊው ስቴፈን ኪፕሮቲች ውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ አትሌቶች መካከል አንዱ ነው።\n\nየኬኒያ፣ኡጋንዳ፣ ቦትስዋና ሀገራት የመጡ አትሌቶች በውድድሩ ላይ ይሳተፋሉ።\n\nየውድድሩ መነሻና መድረሻውን ያደረገው ስድስት ኪሎ መሆኑን በመግለጫው ላይ ተጠቅሷል።\n\nየታላቁ ሩጫ የቦርድ ሰብሳቢ የሆነው አትሌት ኃይሌ ገብረ ስላሴ ውድድሩ በሰላማዊ መንገድ ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ ጥሪ አቅርቧል። \n\n ", "passage_id": "54e5830f63b89a984fb12180ec7592ea" }, { "passage": "ሰላሳ አንደኛው ኦሎምፒያድ ብራዚል ሪዮ ዲጀኒሮ ላይ ሊጀመር ነው። ነገ አርብ የመክፈቻው ሥነ-ሥርአት ይካሄዳል። ኦሎምፒክስ ብዙ ጊዜ የደስታ የሆታ ጊዜ ነው በእርግጥ በየጊዜው ውዝግብም አያጣውም። የዘንድሮም ከዚህ የተለየ አይደለም።የኦሎምፒክስ ችቦ በጀልባ ሪዮ ገብቷል።የሪዮ ኦሎምፒክ ዝግጅትና በውድድሩ ዙርያ የተከሰቱ ውዝግቦችን ያጠናከረ ዘገባ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ። ", "passage_id": "23c29cd7a595bb132139b11e0fea0ed8" } ]
eb5aedce6adbdb0a4ed7ab8a22cb5329
5fde6f03d810d37932263bb6395869fa
የባዶ እግር ትሩፋቶች
ብርሃን ፈይሳየበጋማው ወቅት ሞቃታማ የአየር ሁኔታ ጎዳናውን ቢያግለውም፣ ባዶ እግሩን ሮጦ ከማሸነፍ አላገደውም። ጦር ያዘመተችባት ሃገር ሽንፈትን በተከናነበችበት ማግስት ብቻውን ዘምቶ እንደ አንድ ባታሊዮን ጦር አሸንፎ የኢትዮጵያዊያንን አንጀት አራሰ እንጂ፡፡ በእርሱ እግር የተተካውም፤ በቀናት ልዩነት በመም የተካፈለበትን ርቀት ከመጤፍ ሳይቆጥር በማራቶንም ዳግም ሃገሩን በክብር አስጠርቷል፡፡ሌላኛው ደግሞ እስርና ሌላ ኦሊምፒክን ማሳለፍ ተስፋ ሳያስቆርጠው በአንድ ኦሊምፒክ ሁለት የወርቅ ሜዳሊያዎችን በማጥለቅ ዓለምን ‹‹አጀብ›› አሰኝቷል፡፡ሴቶች በኋላ ቀሩ ሶስተኛው ዓለም በዚህ ደረጃ እንደሚገኙ በማይገመትበት ወቅት በአፍሪካ የመጀመሪያውን የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ የግሏ ያደረገች እንስት የተፈጠረችው በዚህችው ሀገር ነው፡፡በቀደሙት መንገድ የተጓዙ አይበገሬዎች፤ የዓለምን ክብረወሰኖች በመሰባበር ኢትዮጵያ የማትነጥፍ የድል አድራጊዎች እናት መሆኗን አስመስክረዋል፡፡በጉዳት ያልተበገሩ፣ ታላላቆቻቸውን ያከበሩ፣ ሃገራቸውን አስቀድመው፤ ላብ እንባና ደማቸውን ያፈሰሱ ኢትዮጵያዊያን ጀግኖች ጥቂት አይደሉም፡፡አንድን ውድድር መጨረስ ህልም የሆነባቸው ብዙ ሃገራት ባሉባት ዓለም አበበን የተከተሉ የባዶ እግር ትሩፋቶች፤ ህዝባቸውን በደስታ ጮቤ እያስረገጡና የሃሴት እንባ እያስነቡ ስድስት አስርት ዓመታትን ተሻግረዋል፡፡ሜዳሊያና ዲፕሎማ ከማስመዝገብም አልፈው ሃገራቸውን በተሳትፎ ያከበሩ አትሌቶች፣ በቡድን መሪነት፣ አሰልጣኝነት፣ የህክምና እና የቴክኒክ ባለሙያነት እንዲሁም በመገናኛ ብዙኃን ድሉን ለህዝብ በማድረስም ሚና የነበራቸው ጥቂቶች አይደሉም፡፡ይሁን እንጂ እነዚህ የሃገር ባለውለታዎች በሚገባቸው ልክ ሳይከበሩና ሳይመሰገኑ ቆይተዋል፡፡የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም ጀግናን ማክበር፤ ለመጪው ትውልድ ብርታት ነውና ከሜልቦርን እስከ ሪዮ ኦሊምፒኮች ሃገራቸውን ለወከሉ ምስጋናውን በልዩ ክብር አበርክቷል፡፡‹‹የባዶ እግር ትሩፋቶች›› በሚል በተካሄደው መርሃ ግብር ላይም ተሳትፎ ላስመዘገቡ አትሌቶችና ባለሙያዎች ከ25ሺ ብር ጀምሮ የሚጨምር የገንዘብና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡በህይወት0ቀዳሚዎቹ አትሌቶች፣ አሰልጣኝና ጋዜጠኛም እረፍታቸው በተደረገበት ስፍራ በመገኘት የአበባ ጉንጉን የማኖር ስነስርዓትም ተካሂዷል፡፡ በሽልማት መርሃ ግብሩ ላይም የታላቁ አትሌት ልጅ የትናየት አበበ ቢቂላ የሁለት ሚሊየን ብር ሽልማት ከኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ተቀብሏል፡፡ የሌላኛው ተአምረኛ አትሌት ልጅ ሳሙኤል ማሞ ወልዴ እና የልጅ ልጁ እንዲሁም የድርብ ድሉ ባለቤት ‹‹ማርሽ ለዋጩ›› ባለቤትና ልጃቸው ቢኒያም ምሩጽ ይፍጠር ደግሞ አንድ አንድ ሚሊየን ብር ተበርክቶላቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስንና ድልን ያወዳጃቸው ጀግናው አትሌት ሻምበል አበበ ቢቂላ ቢሆንም፤ የድሉን ቀጣይነት ያወጀው ሌላኛው ወርቃማ አትሌት ሻምበል ማሞ ወልዴ ነው፡፡ማሞ የአበበን ፈለግ ተከትሎ ሃገሩ የለመደችው እንዳይጎድልባት በላቡ ክብሯን ከማድመቅም አልፎ ለተተኪ አትሌቶችም መንገድ ጠራጊ ሆኗል፡፡ ይህ በድል የተንቆጠቆጠ አትሌት ዛሬ በህይወት ባይኖርም ከሃገሩ የቀረበለትን ምስጋና በልጁ ተረክቧል፡፡ ሳሙኤል ማሞ ወልዴ፤ አባቱን ወክሎ ለተገኘበት መድረክ ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማውም ገልጿል፡፡ለሃገሩ ብዙ ዋጋ የከፈለው አባቱ የሚገባውን ያህል ሳይደረግለት አልፏል፤ ቤተሰቦቹም ድጋፍ ይሹ ነበር፡፡ይባስ ብሎ ከ13 ዓመታት በፊት የመቃብር ሃውልቱ ፈረሰ፤ ይህንን ተከትሎም ልጁ በግሉ ብዙ ጥረቶችንም አድርጎ ሰሚ ባለማግኘቱ ትቶት ነበር፡፡አሁን ግን በአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ ጥረት ሃውልቱ በድጋሚ በመሰራቱና እውቅናው በመሰጠቱ እንዲሁም ሻምበል ማሞ ካረፈበት ጊዜ ጀምሮ ለቤተሰቦቹ ድጋፍ ላደረጉ ሁሉ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡ በኢትዮጵያ አትሌቲክስ የወንዶች ተሳትፎ ቀዳሚ ቢሆንም አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ግን የሴት ኦሊምፒያኖች ድል በእኩል ደረጃ የሚጠቀስ ሊሆን ችሏል፡፡ በስፖርቱ ከቀዳሚዎቹና ፈር ቀዳጆቹ መካከል አንዷ በምስጋና መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ለሃገራቸው ስላበረከቱት አስተዋጽኦ የዋንጫና የገንዘብ ሽልማታቸውን ወስደዋል፡፡ በአትሌትነትና አሰልጣኝነት ሃገራቸውን አገልግለው በጡረታ ላይ የሚገኙት ወይዘሮ ጽጌ ገብረመሲህ፤ እርሳቸውና መሰሎቻቸውን ተከትለው በየዘመኑ የወጡ አትሌቶች ሃገራቸውን በማስጠራታቸውና በዚሁ ምክንያትም የሽልማት ተካፋይ በመሆናቸው ክብር እንደተሰማቸው ገልጸዋል፡፡ አብዛኛዎቹ ተሸላሚዎች በጡረታ የተገለሉ፣ የተረሱ፣ ወደፊት ወጥተው ያልታዩ አንዳንዶች ደግሞ በሞት የተለዩ ቢሆኑም፤ ሁሉንም አስታውሶና አሰባስቦ ለሽልማት ማብቃት አስደሳች ነው፡፡ወደፊትም ይህን መሰል አትሌቶች አሰልጣኞችና አመራሮችም ጭምር በተመሳሳይ መልኩ እንዲታወሱ፤ በተለይ መገናኛ ብዙሃን የአትሌቲክስ ቤተሰቦች እንዲበረቱ ማስታወስ እንደሚገባቸውም ጠቁመዋል፡፡ በመድረኩ ተገኝተው እውቅናውን ያበረከቱት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፤ አበበ ቢቂላና እሱን የተከተሉ አትሌቶች ለሃገራቸው ያበረከቱት አስተዋጽኦ የሚለካ ባይሆንም፣ እንደሚገባቸው አለመከበራቸውን ጠቅሰዋል፡፡ይህ የምስጋና መድረክ መዘጋጀት በርካታ ጉዳዮችን ያስተምራል፤ ከምንም በላይ ኢትዮጵያን አስተዋውቀዋልና ጀግኖች ሊከበሩና ሊዘመርላቸውም ይገባል፡፡ ኢትዮጵያ ስትነሳ አብሯት የሚነሳው አበበ ቢቂላ፤ ዓለምን የማረከ፣ ባዶ እግሩን ሮጦ ኢትዮጵያን ያስተዋወቀ አትሌት ነው፡፡በተለይ ባንዲራዋን ከፍ ያደረገው በጣሊያን ሃገር መሆኑ ድሉን ከሩጫ በላይ ያደርገዋል።ይህም እጅግ የሚያኮራ በመሆኑ ጀግኖቻችንን ማክበር ከእነሱም መማር አለብን ብለዋል፡፡ጀግኖቹን የማያከብር ሃገር ወደፊት ሊሄድ እንደማይችልም ፕሬዚዳንቷ አመላክተዋል፡፡ የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሰው በበኩላቸው፤ የሃገር ባለውለታ የሆኑ አትሌቶችን ማመስገን አሁን ላሉት አትሌቶች ስንቅ መሆኑን ይገልጻሉ፡፡ ከዚህ ቀደም ቶኪዮ ላይ በተካሄደ የአበበ ቢቂላ ድል 60ኛ ዓመት መርሃ ግብር ላይ እንደተሳተፉ የጠቀሱት ሚኒስትሯ፤ የኢትዮጵያ በበቂ መልክ አለመዘጋጀት ያስረዳ እንደነበረ ያስታውሳሉ፡፡አበበን ከኢትዮጵያ ይልቅ የሚያከብሩት ጃፓናዊያን ህጻናትም ሳቀሩ ስለ እርሱ ይጠይቃሉ ብለዋል፡፡በወቅቱ በቦታው የተገኙ የፌዴሬሽኑ አመራሮች ስንቅ፣ ልምድና አሰራር ተምረው በመመለሳቸው መርሃ ግብሩን ለማዘጋጀት እንዳበቃቸውም አመላክተዋል፡፡ ስፖርት ኢትዮጵያን እንደ ሃገር የገነባት አንዱ ዘርፍ ነው፡፡በባዶ እግር ሮጦ ማሸነፍ ደግሞ ኢትዮጵያዊያን ውስጣዊና አካላዊ ጥንካሬ ያላቸው ህዝቦች መሆናቸውን ያሳየ ነው፡፡ይህም የይቻላል ስነልቦና ያለው ትውልድ ለመፍጠር የሚያስችል ነው ሲሉ አብራርተዋል፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ፤ በርካታ ስራዎችን ያከናወኑ የአትሌቲክስ ጀግኖቻችንን ክብር በመሰጠቱ ደስታዋን ገልጻለች፡፡ፈር ቀዳጆቹን አትሌቶች ተከትለው በ13 ኦሊምፒኮች ላይ ሃገራቸውን ያስጠሩ በርካታ አትሌቶችን ማፍራት ተችሏል ያለችው ፕሬዚዳንቷ፣ የአበበ ቢቂላ ከሮም መልስ በጃፓን ቶኪዮም የሜዳሊያ ድል ባለቤት መሆን የቆራጥነትና ጽናትን በማስተማር ድሉን ያስቀጠለ ሆኗል ብላለች፡፡በቶኪዮ 2021 ለሚካሄደው ኦሊምፒክም አትሌቶች በዝግጅት ላይ እንደሚገኙም ገልጻ፣ የባዶ እግር ትሩፋቶች በሚል የተካሄደው መርሃ ግብርም የኦሊምፒክ ባለውለታዎችን ከመዘከር ባሻገር የማይቋረጥ የሃገር ፍቅር ስሜትን ለመፍጠር በማሰብ መሆኑንም አብራርታለች፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 6/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=37432
[ { "passage": " ዳንኤል ዘነበ በዓለም ዙሪያ በማራኪነቱ፤ በአዝናኝነቱም ሆነ በልብ ሰቃይነቱ ወደር አልተገኘለትም፣ ዘመናዊው የእግር ኳስ ስፖርት። ለእግር ኳስ ፍቅር በከፍተኛ ደረጃ ባለቤት በመሆን ረገድ ብራዚላውያንን የሚስተካከል ስለመኖሩ እርግጠኛ መሆን እንደማይቻል ይነገራል፡፡ ብራዚል ብዙ ሚሊዮን የእግር ኳስ ስፖርት ፍቅር ያለው ሕዝብ ባለቤት ብቻም አይደለችም። ብራዚል የእግር ኳስ ክዋክብቶችን በማፍራት ተጠቃሽ ናት። በዓለም እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ተጽእኖ ፈጣሪ ተጫዋቾችን በማፍራት ነጥፋ አታውቅም። የብራዚላውያን የኳስ ጥበበኛነትን ዓለም አምኖ እንዲቀበል ካደረጉ የዘመናቸን ድንቅ ተጫዋቾች መካከል ሮናልዲንሆ ጎቾ ዲ አሲስ ሞሬራ!! ሮናልዲንሆ ጎቾ በተጫዋችነት ዘመኑ የሰራቸው ገድሎች «ዘመናዊ እግር ኳስ እንግሊዝ ውስጥ ተወልዶ ብራዚል አደገ» እስኪባል ድረስ ሀገሩን ብሎም ዓለምን በማስደመም ስሙን መትከል ችሏል። በዓለም ዋንጫ መድረክ ብቻም ሳይሆን ሌሎች መድረኮች ላይ በሜዳ ላይ በሚያሳያቸው እንቅስቃሴዎች፣ አብዶዎች ከስፖርት ቤተሰቡ ልብ ትዝታው ዛሬም የሚነሳለት ድንቅ ጥበበኛ፤ እኤአ በመጋቢት 1980 በብራዚል በደቡብ ብራዚል ፖርት ኤሌግሪ ተወለደ። እግር ኳስ ወዳድ ከሆነ ቤተሰብ የተገኘው ጎቾ ኳስን በ8 ዓመቱ ኳስ ከሰፈሩ ልጆች ጋር በፖርት አሌግሪ የባህር ዳርቻ በማንከባለል ነበር የጀመረው። ሜዳው ላይ በዕድሜው አነስተኛው ልጅ እሱ ሲሆን፤ በችሎታው የሰውን ዓይን በቀላሉ መማረክ የሚችልና ብዙዎች ከዓይን ያውጣህ ማስባል የጀመረው ያኔ ገና ነበር። ሮናልዲንሆ እስከ 13 ዓመቱ ከሰፈሩ በዘለለ ለትልልቅ ክለቦችም ሆነ ለታዳጊ መጫወት አልቻለም። ውሎው የባህርዳርቻ ነበር። በ13 ዓመቱ ግን አንድ ነገር ተከሰተ፣የወንድሙ ክለብ የሆነው የግሪሚዩ መልማዮች ጎበዝ ተጫዋቾችን ሊመለምሉ የነ ሮናልዲንሆ ሰፈር ደረሱ። ለምልመላው ይረዳቸው ዘንድም ተጫዋቾችን ለሁለት ከፍለው ግጥሚያ እንዲያደርጉ አዘዙ። ክፍፍሉም ፍትሃዊ እንዲሆን በሰፈር አደረጉት። የላይኛው ሰፈር ልጆችና የታችኛው ሰፈር ልጆች። ጨዋታው ተጀመረ። ልክ እንደተጀመረ ሮናልዲንሆ ተከላካዮችን አተራምሶ አስደናቂ ጎል አስቆጠረ። ከደቂቃዎች በኋላም የግል ብቃቱን ተጠቅሞ ሌላ ጎል ደገመ። ውጤቱም 23 ለ 0 ነበር። የሚገርመው 23ቱንም ጎሎች ያስቆጠረው ሮናልዲንሆ ጎቾ ዲ አሲስ ሞሬራ ነው። መልማዮቹ ወደ ካምፓቸው ሲመለሱ አንድ ሳቂታ ልጅ አስከትለው ተመለሱ። ሮናልዲንሆም ከወንድሙ ጋር አንድ ክለብ ውስጥ የመጫወት ዕድል አገኘ። ሮናልዲንሆ ለታዳጊዎቹ ሮቤርቶ ደግሞ ለዋናው ቡድን፡፡ ሆኖም ብዙም ሳይቆይ ወንድሙ ሮቤርቶ በደረሰበት ጉዳት ከኳስ ተሰናበተ። ሮናልዲንሆ ወንድሙ ባጋጠመው ነገር ቢያዝንም ኳስ ከመጫወት ግን ለደቂቃም አልቦዘነም። በግሪሚዩ የእግር ኳስ ካምፕ ውስጥ ኳስን ጓደኛው አደረጋት። ቀኑን ሙሉ ውሎው ከኳስ ጋር ሆነ። ከጓደኞቹ ቀድሞ ልምምድ ቦታ መገኘት እንዲሁም ከሁሉም በኋላ መውጣት ባህሪው ሆነ። ይህ ታታሪነቱ ወደ ታላላቅ የዓለማችን ክለቦች አምርቶ በአጭር ጊዜ ውስጥ በእግር ኳሱ ዓለም እስከዛሬም የማይዘነጉ ተዓምሮችን መፍጠር ቢያስችለውም ዝናና ገንዘብ ይዞት የሚመጣውን ጣጣ እንዲቋቋም አላደረገውም፡፡ ውሎና አዳሩ በየጭፈራ ቤቱ ሆነ፡፡ አብዝቶ መዝናናት ከድህነት ሕይወት ያስመለጠውን ኳስ አስረሳው፡፡ በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ ውስጥም ሆኖ ግን ዓለምን በእግር ኳስ ጥበቡ ማስደመም ለእሱ ቀላል ነበር፡፡ በታላቁ ኤልክላሲኮ ታሪክም ከማራዶና በኋላ በተቃራኒ ደጋፊዎች ሜዳ የተጨበጨበለት ተጫዋች እስከመሆን ደረሰ፡፡ በኳሱ ተዝናንቶበታል፣ ተመልካቹንም አዝናንቶበታል፡፡ ይህ ሁሉ ግን ከአምስት ዓመታት በላይ እንዲዘልቅ አብዝቶ መዝናናቱ አልፈቀደለትም:: ብራዚላውያን ለዚህ ዘመን ድንቅ ኮከባቸው ያላቸው ጥልቅ ስሜት ዛሬም እንደ አዲስ እየተቀሰቀሰ በትዝታው አብረው ሲደሰቱና ሲኮሩ ይሰተዋላሉ። ብዙዎች ጥበቡን ሳይጠግቡ የእግር ኳስ ሕይወቱ በአጭሩ ሊቀጭ ችሏል፡ ፡ እኤአ 2002 ከብራዚል ብሔራዊ ቡድን ጋር የዓለም ዋንጫን ማንሳት ችሏል። ሮናልዲንሆ የ2005 ባለንደኦር [የዓለም ኮከብ ተጫዋች ሽልማት] አሸናፊ ነበር። በኳስ ሕይወት ስኬትና ዝናንን በመጨበጥ አድናቆትን ማትረፍ የቻለው ሮናልዲንሆ በ800 ሺህ ዶላር ዋስ ሆቴል እንዲታሠር ታዘዘ ይላል የቢቢሲ ዘገባ። ሮናልዲንሆና ወንድሙ ፓራጓይ ውስጥ ሃሰተኛ ፓስፖርትና ሌሎች ሰነዶች ይዘው ተገኝተዋል በሚል በፖሊስ ሊያዙ ችለዋል። ወንድማማቾቹ በወቅቱ እንዲለቀቁ ይግባኝ አመልክተው የነበረ ቢሆንም ሰሚ ጠፍቶ ከአንድ ወር በላይ እሥር ቤት ውስጥ ለመሰንበት ተገደዋል። ብራዚላዊው የእግር ኳስ ጠቢብ ሮናልዲንሆ ጎቹ እና ወንድሙ ፓራጓይ ከሚገኘው እሥር ቤት ተለቀው ውሳኔ እስኪሰጣቸው ድረስ ሆቴል ታስረው እንዲቆይ ውሳኔ ተላልፏል። በተጨማሪ እያንዳንዳቸው 800 ሺህ ዶላር ዋስ ጠርተው የፓራጓይ ዋና ከተማ አሱንሲዮን የሚገኝ ባለ አራት ኮከብ ሆቴል ውስጥ እንዲቆዩ ትዕዛዝ ተላልፎባቸዋል ሲል ዘግቧል። በብራዚላዊው የእግር ኳስ ኮከብ ሮናልዲንሆ ጎቾና ወንድሙ ላይ ውሳኔውን ያስተላለፉት ዳኛ ገንዘቡ ጫን ያለ እንዲሆን የተደረገው ግለሰቦቹ ሀገር ጥለው እንዳይጠፉ በማሰብ መሆኑን አስገንዝበዋል። «የ40 ዓመቱ የእግር ኳስ ሰው ሮናልዲንሆና ወንድሙ አሲስ እኛ ሃሰተኛ ሰነድ መሆኑን አላወቅንም ነበር »ሲሉ ቢሟገቱም፤ ጠበቃቸውም «የወንድማማቾቹ እሥር ሕገ-ወጥ ነው» ሲል ቢከራከርም ውሳኔው ተፈጻሚ ከመሆን አላዳናቸውም ሲል ቢቢሲ ዘገባውን ቋጭቷል። አዲስ ዘመን ሚያዝያ 2/2012 ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "936cf6c1b06d1d1678fc4cc0fee04050" }, { "passage": "በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ደማቅ አሻራ ማሳረፍ ከቻሉ ጥቂት ክለቦች መካከል በዋነኛነት ይጠቀሳል። «ለኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውበትም ድምቀትም ነው» ይሉታል። ክለቡ የሚከተለው የኳስ አጨዋወት ውበትን፤ በኳስ ፍቅር የተደራጁት አስደማሚ ደጋፊዎቹ ያላበሱት ድምቀት እንዲህ አይነቱን ማንነት እንዳላበሱት ይነገራል። በ1975 ዓ.ም በቡና ቦርድ ሥር «ቡና ገበያ» ስፖርት ክለብ በሚል የተመሰረተውና፤ በቀጣይነት የቡና ላኪዎች ማህበር ከምርት ገበያ ጋር በመሆን በጀት እየመደቡለት በቦርድ በመመራት እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው፤ አንጋፋው ኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ።ኢትዮጵያ ቡና በአራት የአፍሪካ ውድድሮች የመሳተፍ ዕድል አግኝቷል። በአፍሪካ ሻምፒየንስ ሊግ በ1985\nየኢትየጵያ ሻምፒዮን መሆኑን ተከትሎ በ1990 ተሳትፏል፡፡ በተጨማሪም ሻምፒዮና ዋንጫ በተደጋጋሚ እንደማንሳቱ በአፍሪካ ኮንፌደሬሽን ዋንጫ ተደጋጋሚ ተሳትፎ አግኝቷል፡፡ በተለይ ከ1991-93 በተከታታይ ለሦስት ዓመታት ኢትዮጵያን በመወከል የተሳተፈ ክለብ ነው፡፡ ውድድሩ ያኔ የአፍሪካ የዋንጫ አሸናፊዎች ዋንጫ CAF cup winners cup ተብሎ ነበር የሚጠራው። በ1991 የብሩንዲው ኢንተርስታር ራሱን በማግለሉ ቅድመ ማጣሪያውን ካለፈ በኋላ በመጀመሪያው ዙር ለቀጣይ ዓመት 1992 የማላዊውን ቴልኮም ዎንደደርሰን 3ለ0 በማሸነፍ ወደ ሁለተኛው ዙር ካለፈ በኋላ በግብጽ ዛማሊክ ጋር ሦስት አቻ ከተለያየ በኋላ በመለያ ምት ተሸንፎ ወጥቷል፡፡ ለሦስተኛ ተከታታይ ጊዜ በቀረበበት 1983\nከሁለተኛ ዙር አላለፈም የሞዛምቢኩ ማጂጄ ራሱን ካገለለበት በኋላ በካሜሩኑ ኩምስ ስትራይከርስ ተሸንፏል፡፡ ቡና በከፍ ካራም ሁለት ጊዝ ተሳትፏል፡፡ በ1986 በሱዳን አልምሩዳ በ1996\nደግሞ በሊቢያው አልናስር ተሸንፎ ከአንደኛው ዙር አላለፈም፡፡ ኢትዮጵያ ቡና በአራት የአፍሪካ ውድድሮች የመሳተፍ መልካም የሚባል ታሪክ ባለቤት ከመሆን በተጓደኝ፤ በሀገር ውስጥ በጥሎ ማለፍና አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ ስኬቱን በጉልህ አሳይቷል። ክለቡ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በነበረው የ20 ዓመታት ጉዞ ውስጥ ከአንድ ጊዜ በላይ የሊጉን ዋንጫ ማንሳት አለመቻሉ ለብዙዎች እንቆቅልሽ መሆኑ አልቀረም፡፡ ኢትዮጵያ ቡና የታሪኩ፣ የገናናቱን በርካታ ደጋፊዎች ባለቤት የመሆኑን ያህል የሊጉን ዋንጫን ደጋግሞ አለማንሳቱ ስለምን ይሆን? የሚሉ በርካቶች ናቸው። የክለቡ ዋንጫ አለማንሳት በእጅጉ የሚያንገበግብና የሚያስቆጫቸው ደጋፊዎች ጥቂት አይደሉም፡፡ ይሁንና ይህ ውጤት ማጣቱ የደጋፊዎችን ቁጥር አልቀነሰበትም እንዲያውም በተቃራኒው የቡና ደጋፊዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ይገኛል፡፡ የክለቡ ደጋፊዎች በህብረት ተሰድረው ቆመው ተቃቅፈው እያዜሙ ሲንቀሳቀሱ ሲወዛወዙ ከሩቅ ለሚመለከት ቡናማ ወንዝ ላይ ማዕበል የሚንከባለል ነው የሚመስለው፡፡ በአዲስ አበባ ስታድየም ቀኝ ጥላ ፎቅ፣ ካታንጋ እና ሚስማር ተራ የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች ግዛቶች ናቸው፡፡ ለስታድየም ውበትና ድምቀት ትልቅ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱት ደጋፊዎቹ ‹የሊግ ዋንጫ ጥማችን አንድ ቀን ይሳካል ›እያሉ ተስፋ ሳይቆርጡ ክለቡን በመደገፍ ጉዟቸውን ዛሬም እንደ ትናንቱ በጽናት እንደቀጠሉ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ቡና ክለብ ደጋፊዎች ክለብ ከዋንጫ በላይ ስለመሆኑ ማሳያ ናቸው ቢባል ማጋነን አይሆንም። በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ደማቅ አሻራ ማሳረፍ ከቻሉ ጥቂት ክለቦች መካከል በዋነኛነት የሚጠቀሱት ቡናማዎቹ\n12/12/12 ላይ «የቡና ቤተሰብ ሩጫ» ለማካሄድ ሽር ጉድ እያደረጉ መሆኑ ተሰምቷል። በኢትዮጵያ ቡና ጥላ ሥር የተሰባሰቡት ቡናማዎቹ ደጋፊዎች በአዲስ አበባ ስታድየም ቀኝ ጥላ ፎቅ፣ ከታንጋ እና ሚስማር ተራ ከሚያሰሙት ማራኪ የድጋፍ ዜማ ተሻግሮ አንድነታቸውን የሚያጠናክሩበት ሁነት ሲፈልጉ ቆይተዋል። ቡናማዎቹ ‹ክለብ ከውጤት በላይ ነው፣ ቡና ደሜ ነው› የሚለውን መፈክር በተግባር ማሳየት የሚያስችለው ሁነት ለዓመታት ተጠንስሶ በ2007 ዓ.ም ነበር ሊወለድ ችሏል።የኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ ደጋፊዎች ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ ክፍሌ አማረ፤ የኢትዮጵያ ቡና የቤተሰብ ሩጫ የተጀመረው በ2007 ዓ.ም መሆኑን በመግለጽ ይሄንኑ መረጃ ያጠናክራሉ። በኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ አዘጋጅነት በየዓመቱ የሚካሄደው «የቡና ቤተሰባዊ ሩጫ» አላማ ያደረገው «በክለቡ ቤተሰባዊ ትስስርን መፍጠርና ማጠናከር እና የክለቡን የገቢ አቅም ለማጠናከር »መሆኑን በኢትዮጵያ ቡና ጥላ ሥር የተሰባሰቡትን ደጋፊዎች የሚያሳትፈው ሁነት ተጀመረ። ከአምስት ዓመት በፊት 8 ሺህ ቤተሰቦችን በማሳተፍ ተጀመረው ሁነቱ፤ በ2ኛው ዙር የቡና ቤተሰብ ሩጫ የተሳታፊውን ቁጥር ወደ 20 ሺህ በማሳደግ በታላቅ ድምቀት ለመካሄድ ተቻለ። የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ የድምቀቱ መጠን እያደር አብቦና ደምቆ በ30 ሺህ ተሳታፊዎች ሦስተኛው የቡና ቤተሰባዊ ሩጫ ለመካሄድ በቅቷል። የክለብን ጥቅም ለማጉላት «ቡና ደሜ ነው» የሚለው ሀቀኛ ደጋፊ ለክለቡ ያለውን ፍቅርና መጠንከር ተሳትፎው ወሳኝ መሆኑን እያደር በመገንዘብ ይመስላል በ4ኛው የኢትዮጵያ ቡና ቤተሰባዊ ሩጫ ላይ የተሳታፊው ቁጥር ከ40 ሺህ በላይ ሊያሻቅብ የቻለው። በኢትዮጵያ ቡና ጥላ ሥር የተሰባሰቡት ቡናማዎቹ ዘንድሮ እንዳምናው ደምቀው ለመታየት 12/12/2012 ዓ.ም ቡናን ከልብ በሚል ቀጠሮ እንደተያዘ አቶ ክፍሌ ገልጾልናል። የኢትዮጵያ ቡና ዓመታዊ የቤተሰብ ሩጫ መርሐ ግብር ዘንድሮ 5ኛው ዙር የሚካሄድ ይሆናል። የኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ ደጋፊዎች በድምቀት የሚያሰባስበውን ይህን ሁነት በተለያዩ ሁነቶች ለማካሄድ ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አስታወቋል።«የቤተሰብ ሩጫ ውድድሩን ለማካሄድ አሁን ያለንበት ወቅት እንደማያስችለን ይታወቃል። የዓለምን ሕዝብ ሥጋት የሆነው ኮቪድ 19 ወረርሽኝ የሩጫ ውድድሩን ለማከናወን የሚያግድ ቢሆንም፤ ዕለቱን በተለየ መልኩ ለማሰብ ዕቅድ ተይዟል። የኢትዮጵያ ቡና የቤተሰብ ሩጫ ውድድርን የክለቡ ደጋፊዎች ነሐሴ 12 ቀን 2012 ዓ.ም ቲሸርቱን ለብሰን ባለንበት ሆነን ከክለባችን ጋር በልብ በመገናኘት የምንሮጥ ይሆናል። የአረንጓዴ አሻራን ቀንን ምክንያት በማድረግ ደጋፊው በየአካባቢው ችግኝ ይተከላል። በተጨማሪም የደም ልገሳ መርሐ ግብር ሌላኛው የዕለቱ አብይ ጉዳይ ይሆናል »ሲል አብራርተዋል።የኢትዮጵያ ቡና የቤተሰብ\nሩጫን እንዲህ በመሰለ\nመልኩ ለማካሄድ የታሰበ\nመሆኑን የገለፀው አቶ\nክፍሌ፤ በዚህ መሠረትም\nየቲሸርት ሽያጭና ምዝገባ\nበመደረግ ላይ ሲሆን፤\nየአንዱ የመሮጫ ማልያ\nዋጋ ከአንድ የፊት\nማስክ ጋር ለአዋቂ\n350 ብር\nለህፃናት 300 ብር እየተሸጠ\nይገኛል። 12 ቁጥር\nየታተመበት የመሮጫ ቲሸርት\nሽያጩ በክለቡ ጽፈት\nቤት (ሜክሲኮ) እና\nበማህበሩ ጽህፈት ቤት\n(ቡልጋሪያ)፣ ከዚህ ቀደም\nእንደሚደረገው ሁሉ በየአካባቢው\nይሸጡ በሚገኙ የመሸጫ\nቅርንጫፍ ቦታዎች እንዲሁም\nበኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች\nበተቋቋሙ እድሮች እየተከናወኑ\nመሆኑን አመልክቷል። በ5ኛው\nየኢትዮጵያ ቡና የቤተሰብ\nሩጫ ሁነት ላይ\nከ40 እስከ 60 ሺህ\nቤተሰቦች ይካፈላሉ ተብሎ\nይጠበቃል። ከቲሸርት ሽያጩም\nእስከ 14 ሚሊዮን\nብር ገቢ ማግኘት\nእንደሚቻል ታሳቢ ተደርጓል።\nበመሆኑም ክለቡ በኮሮና\nምክንያት የደረሰበትን የፋይናንስ\nመንገራገጭ በተወሰነ ደረጃ\nለማስተካከል የሚረዳውና የሩብ\nዓመት የተጫዋቾች የደሞዝ\nክፍያን መሸፈን የሚያስችል\nገቢ ማግኘት ይቻላል\nየሚል እምነት እንዳላቸው\nአቶ ክፍሌ ነግሮናል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 28/2012  ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "bf90624962801de7a34ad5f3e316fa17" }, { "passage": "ኢትዮጵያ በዓለምና በአህጉር አቀፍ የአትሌቲክስ መድረክ በታሪክና በውጤት ስማቸው ጎልቶ ከሚነሱ አገሮች መካከል በቀዳሚነት ትጠቀሳለች። በየዘመኑ የሚፈጠሩ አትሌቶቿም በታሪክ ከከፍታው ላይ እንድትቀመጥ ያደረጓት ባለውለታዎቿ ናቸው። ጀግኖቿ በየዘመኑ የሚያስመዘግቡት ውጤት ኢትዮጵያ እና አትሌቲክስ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታ ተደርገው እንዲቆጠሩ አስችሏል።ይህ ስምና ዝና ምሉዕ ያልሆነ፤ የተገኙት ድሎችና የወለዱት ክብርና ዝና ግን ርቀት የገደባቸው ናቸው የሚሉ በርካቶች ናቸው። ኢትዮጵያውያን ከረዥም ርቀትና ከማራቶን ውጪ በአጭርና በመካከለኛ ርቀት ውጤታማ አለመሆናቸውን በአመክንዮዋቸው ውስጥ ይገልጻሉ፡፡ በኦሎምፒክ፣ በዓለም ሻምፒዮና እና በመሳሰሉት ውድድሮች የተገኙት ድሎች በሙሉ በረዥም ርቀት ነው። አጭር ርቀትን፤ ብሎም የሜዳ ተግባራትን ያማከለ አይደለም። ከአትሌቲክሱ ጋር ያለውን ታሪካዊና ጥብቅ ቁርኝት በርቀት የተገደቡ ለማለት ያስደፈረውም ይህ ምክንያት ነበር።በረጅም ርቀት የተገኘውን ድልና ውጤታማነት በተመሳሳይ በአጭር ርቀትና በሜዳ ተግባራት መድገም የሚቻል ቢሆንም፤ ባለመሠራቱ ግን ግንጥል ጌጥ የሆነ ታሪክ ተሸክመን ለመጓዝ ተገደናል ሲሉ ይሞግታሉ። የአጭር፣ የመካከለኛ፤ የእርምጃና የሜዳ ተግባራት መሥራት ቢቻል የሚመጣውን ውጤት ጎረቤት አገር ኬንያን እንደማነጻጸሪያነት በማንሳት ሀሳቡን ማጠናከር ይቻላል። ሞጋቾቹም የኢትዮጵያን የምንጊዜም የረጅም ርቀት የአትሌቲክስ ውድድር ብርቱ ተፎካካሪ የሆነችውን ኬንያን እንደማሳያ ያነሳሉ።ኬንያ በኦሎምፒክ፣ በዓለም ሻምፒዮና … ወዘተ. የመሳሰሉ ትልልቅ የውድድር መድረኮች ላይ በረጅም ርቀት ውጤታማ ናት። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ደግሞ፤ በአጭር ርቀት ላይም ጥሩ ጅምር በማሳየት ላይ ትገኛለች። የኬንያ ጅምር በተለይ ባለፉት የኦሊምፒክና የዓለም ሻምፒዮና የአጭርና የመካከለኛ ርቀት ውድድሮች ላይ ብቃቷን አሳይታለች። ይህ ጥረቷ በአጭርና በመካከለኛ ርቀቶች ብቻ ሳይገደብ በሜዳ ተግባሩም ሜዳሊያ ማግኘት ጀመራለች። ታዲያ እዚህ ላይ ኢትዮጵያና አትሌቲክስ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች የሚለው አባባል ለኬንያም ይሠራል። ግንጥል ጌጥነቱ ግን ለኬንያ የሚሠራ አይሆንም።የኬንያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በረጅም ርቀት በሚመዘገበውን ውጤት መወሰን ተገቢ አለመሆኑን በመገንዘብ ተንቀሳቅሷል። ይህም የተስፋ ብልጭታዎች ማሳየት ያስቻለም ጭምር ነው። ይህ የሆነውም ርቀት ሳይከልለው መጓዝ በመቻሉ ነው። በኬንያ ውጤት እያሳየ ያለውን የአጭር፣ የመካከለኛ እንዲሁም በሌሎች የሜዳ ተግባራት በኢትዮጵያም ማምጣት እንደሚቻል በርካታ ባለሙያዎች ያምናሉ። ሰሞኑን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለአምስት ቀናት በአዲስ አበባ ስታዲዮም በክለቦች መካከል ሲያከናውን በሰነበተው የአጭር፣ መካከለኛ፣ ዕርምጃና የሜዳ ተግባራት ውድድር ተሳታፊ ከነበሩት በዲስከስ ውርወራ ሲዳማ ቡናን በመወከል የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ ለማ ከተማ ይህንን ሀሳብ ይጋራል።\nአትሌት ለማ ኢትዮጵያ በየውድድር አይነቶቹ ላይ ከሌሎች አገሮች ጋር ለመፎካከር የሚያስችል አቅም እንዳላት ይስማማል። ይሁን እንጂ፤ «በአገሪቱ ያለውን እምቅ አቅም መሰረት ያደረገ የሥልጠናም ሆነ ሌሎች መሰረታዊ ተግባራት አልተከናወኑም። በመሆኑም መገኘት ያለበት ውጤት መምጣት አልቻለም» ሲል መሥራት ቢቻል ውጤታማ መሆን እንደሚቻል ሀሳቡን ያስቀምጣል። አትሌቲክስ ፌዴሬሽኑ በአጭር፣ በመካከለኛና ተመሳሳይ በሆኑ የውድድር አይነቶች ላይ የሰጠውን ትኩረት ካጠናከረ ውጤታማ መሆን እንደሚቻል ያምናል።እንደ አትሌት ለማ ሁሉ፤ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ውጤታማነት በረጅም ርቀት ብቻ ሳይገደብ ቢሠራ አመርቂ ምላሽ ማግኘት እንደሚቻል የበርካቶች እምነት ነው። ለዚህም እንደማሳያ እኤአ በ2017 በአልጄሪያ የተካሄደውን የአፍሪካ ከ20 ዓመት በታች ወጣቶች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተጠቃሽ ነው። በሻምፒዮናው ኢትዮጵያ በ38 ሜዳሊያዎች ቀዳሚ ሆና ፈጽማለች። ሜዳሊያዎቹ የተገኙት ደግሞ በተለመዱት የመካከለኛና የረጅም ርቀት ሩጫዎች ብቻ አልነበረም። ይልቁንም በአጭር ርቀትና ከሩጫ ውጪ ባሉ የአትሌቲክስ ውድድሮች ጭምር ነበር።ከነዚህም መካከል፤ በወንዶች 4በ400 ሜትር ዱላ ቅብብል ወርቅ፣ በወንዶች 5000 ሜትር ወርቅና ብር፣ በሴቶች 3000 ሜትር ወርቅና ብር፣ በሴቶች 10,000 ሜትር እርምጃ ወርቅና ብር እንዲሁም በሴቶች 4በ400 ሜትር ወርቅ አግኝታለች፡፡ በሴቶች ስሉስ ዝላይ የብር ሜዳሊያ ማግኘት ተችሏል። አዎን ሻምፒዮናው በኢትዮጵያ ከተሠራ እንደ ረጅም ርቀቶቹ ሁሉ በመካከለኛ፣ በአጭርም ሆነ በሌሎች የውድድር አይነቶች ታሪክ መሥራት እንደሚቻል ያመላከተ ነበር። በዚህ ውስጥ መመልከት የሚቻለውም በርቀቶቹ መሥራት ከተቻለ በርቀት የተገደበውን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ የድል ታሪክ ጉዞ በነዚህ የውድድር ዓይነቶችም ማስቀጠል እንደሚቻል ነው። ከዚሁ ጋር ተያይዞ አስተያየታቸውን የሰጡት ስፖርተኞች በርካቶች ሲሆኑ፤ እነርሱም፤ በአሠለጣጠን፣ በልምምድና በቴክኒክ ሥራዎች ላይ ያሉ ጉድለቶችን ለማስተካከል በተለየ መልኩ ትኩረት ቢሰጥ ውጤታማ መሆን እንደሚቻል ያመላክታሉ።በዓመታዊው ሻምፒዮና ላይ ተሳታፊ ከነበሩት ውስጥ በሴቶች የርዝመት ዝላይ አሸናፊ የሆነችው የኢትዮጵያ ንግድ ባንኳ አራያት ዲቦ አስተያየ ታቸውን ከሰጡት መካከል ትገኛለች። አትሌቷ እንደገለጸችው፤ ለስፖርቱ የሚያስፈልጉ ቁሳቁስ አለመሟላት እንደሳንካ የሚታይ መሆኑን ትገልጻለች። ለውድድርና ለልምምድ የሚያስፈልጉ የስፖርት ቁሳቁስ በበቂ ሁኔታ አይሟሉም፤ አልተሟሉምም። ኢትዮጵያ ለውድድር ዓይነቶቹ የሚሆን ተክለ ሰውነት፤ ጉልበትና ጥሩ አቅም ያላቸው አትሌቶች እንዳሉ ትናገራለች። ይህን አቅምና እምቅ ሀብት ሳይንሳዊ በሆነ ሥልጠና ማገዝ ቢቻል ፍሬያማ መሆን ይቻላልም ትላለች። በአገራችን እየሆነ ያለው ግን ከዚህ በተቃራኒ ነው። በተክለ ሰውነትና በጉልበት ጥሩ አቅም ያላቸው ስፖርተኞች ቢኖሩም፤ የቴክኒክ ችግር ይስተዋልባ ቸዋል። ምክንያቱም ሳይንሳዊ በሆነ ሥልጠና እየታገዙ አይደለም። ስለዚህ በስፖርተኞቹ ላይ የሚስተዋለውን የቴክኒክ ችግር በሳይንሳዊ ሥልጠና መቅረፍና አቅማቸውን መሙላት ያስፈልጋል ባይ ነች።የአሠልጣኞችንና የተወዳዳሪዎችን አቅም የሚያጎለብቱ ተከታታይ ሥልጠናዎች አለመስጠት የውድድር ዓይነቶቹ እንዳያድጉ ማድረጉን ነው ያመለከቱት የምትለዋ አትሌት፤ ሌሎች ጎረቤት አገሮች በአጭር፣ በመካከለኛ፣ በሜዳ ተግባራትና በእርምጃ ውድድር ችሎታ ያላቸውን አትሌቶች ብቃታቸውን ለማሳደግ ወደ ውጭ ሀገር ሁሉ ልከው ያሠለጥናሉ። በአገራችን ግን ይህ ነገር አይታይም። በመሆኑም አገራችንን በአጭርና በመካከለኛ ርቀቶች ውጤታማ ለማድረግ እነዚህን ክፍተቶች በሚገባ መሙላት ያስፈልጋል ስትል ሀሳቧን ቋጭታለች።የመከላከያ ስፖርት ክለብ የዝላይ አሠልጣኝ ሻምበል ኡጉላ ኡባንግ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በውድድር አይነቶቹ ላይ ከሌሎች አገሮች ጋር ለመፎካከር የሚያስችል አቅም የሌለን ለውድድሮች ትኩረት ባለመሰጠቱ ነው ሲሉ እንደምክንያት ያነሳሉ። ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ፣ አትሌቱ፣ አሰልጣኙም ሆነ ሌሎች ባለድርሻ አካላት አጠንክረው የሚሠሩት በረጅም ርቀት ላይ ነው። የውድድር መርሀ ግብሮችም ይህንኑ መንገድ ይዘው የሚፈሱ ናቸው። እንዲህ አይነቱ አሰራር ደግሞ፤ በቂ ውድድሮች በሌሉበት ሁኔታ አትሌቶች ራሳቸውን የሚፈትሹበትና የሚያዘጋጁበት እድል የሚያሳጣቸው ነው። በዓመት ውስጥ የሚደረጉ ውድድሮች ከሚገባው በታች አነስተኛ መሆናቸውን እንደ ሌላ ችግር ያነሱት አሠልጣኙ፤ በነዚህ ዘርፎች ላይ ይበልጥ ትኩረት ተሰጥቶ ቢሠራ ኢትዮጵያ ውጤታማ የማትሆንበት ምክንያት አይኖርም ባይ ናቸው። ሰሞኑን በአዲስ አበባ ስታዲየም ሲከናወን የሰነበተው ውድድርም ያሉበትን ችግሮች በሚገባ በማጤንና በማሳደግ፤ በተጨማሪም ሌሎች የውድድር መድረኮችን በመፍጠር በአጭር ርቀት እንደ ረጅም ርቀት ስኬታማ መሆን ያስችላል ሲሉ ሀሳባቸውን ይቋጫሉ።የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቢልልኝ መቆያ፤ ሻምፒዮናው ለአጭር፣ ለመካከለኛ፣ ለሜዳ ተግባራትና ለእርምጃ ተወዳዳሪ አትሌቶች የውድድር ዕድል ለመፍጠር ታሳቢ ያደረገ መሆኑን አስታውቀዋል። ሻምፒዮናው በውድድር ዓይነቶቹ ተወዳዳሪዎች ራሳቸውን የሚፈትሹበት የአቋም መለኪያ ውድድር ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል ጭምር ነው። በውድድር አይነቶቹ ኢትዮጵያ በአፍሪካና ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ ተሳትፎ አድርጋለች። የሚመዘገበው ውጤት ግን ከሌሎች አገሮች አኳያ ጠንካራ ሥራ መሥራት እንደሚያስፈልግ የቤት ሥራን ሰጥቶ አልፏል። ከአንድ ዓመት በፊት ናይጄሪያ አሳባ ከተማ የተካሄደውን 21ኛው የአፍሪካ የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ያስታወሱት አቶ ቢልልኝ ፤ ኢትዮጵያ በሁለቱም ጾታዎች ከ100 ሜትር ጀምሮ ተሳትፊ ነበረች። በሻምፒዮናው የተገኘው ውጤት መሰረታዊ ችግሮች እንዲለዩ አጋጣሚ የፈጠረ ነበር ።በውድድር አይነቶቹ ውጤታማ ለመሆን በአሠለጣጠን፣ በልምምድና ቴክኒክ ሥራዎች በመለወጥ ጊዜው በፈቀደውና ዓለም በደረሰበት ልክ መሥራት እንደሚያስፈልግ እርሳቸውም እንደሚያምኑ ይናገራሉ። በአሠለጣጠን በኩል ያለውን ክፍተት ለመሙላት በጋና፣ በኩባ፤ በደቡብ አፍሪካና በሌሎች አገሮች ከሚገኙ አሠልጣኞች ጋር በመነጋገር ወደኢትዮጵያ መጥተው እንዲያሠለጥኑ ጥረት መደረጉን ያነሳሉ። ነገር ግን አሠልጣኞቹ ያላቸው አቅም ያን ያህል አመርቂ እንዳልሆነ ይገልጻሉ። ከውጭ የሚመጡት አሠልጣኞች ከኢትዮጵያውያኖቹ መሻል አለባቸው። ከዚህ አኳያ ያለውን ጥረት ከመቀጠል ወደኋላ እንዳልተባለ ያመለክታሉ።በብሔራዊ ፌዴሬሽን በኩል በመቀጠል በአገራችን ውስጥ የተሻሉ አሠልጣኞች እስኪገኙ ድረስ የአገር ውስጥ አሠልጣኞች አቅማቸውን ማጎልበት የሚችሉበት ተከታታይ ሥልጠና ለመስጠት በእቅድ እንደተያዘ ይናገራሉ።«አሠልጣኞቹንም ወደ ውጭ አገር በመላክ ልምድ እንዲቀስሙ የማድረግና ታዋቂ አሠልጣኞች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ተሞክሯቸውን እንዲያካፍሉ ይደረጋል። የውድድር አማራጮችን ማስፋት፣ የስፖርት ቁሳቁስን ማሟላትና የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎች ፌዴሬሽኑ በቀጣይ ትኩረት ሰጥቶ የሚሠራባቸው ጉዳዮች ናቸው ብለዋል። በመጨረሻም፤ በአጭር፣ በመካከለኛ፣ በእርምጃና በሜዳ ተግባራት አትሌቲክስ ውድድሮች እድገት ክለቦች፣ አሠልጣኞችና ተወዳዳሪዎች የየበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።በአጠቃላይ በአጭር፣ በመካከለኛ፣ በእርምጃና በሜዳ ተግባራት ውድድሮች ኢትዮጵያ በዓለምም ሆነ በአህጉር አቀፍ መድረክ ከተወሰኑ አጋጣሚዎች ውጪ ውጤታማ አይደለችም። በውድድሮቹ ወቅት በተወዳዳሪዎች ላይ በአሠለጣጠን፣ በልምምድና ቴክኒክ ሥራዎች ላይ ጉድለት እንዳለ የተመላከተና በዘርፉ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንደሚገባ ተስተውሏል። በአሁኑ ወቅት በእነዚህ የውድድር ዓይነቶች ብቁ ተወዳዳሪዎችን ለማፍራትና ውጤታማ ለመሆን እንቅስቃሴዎች በመካሄድ ላይ ይገኛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ አትሌቱና ሀብቱ መኖሩ እሙን ነው ። በአግባቡ ጥቅም ላይ የሚውል ከሆነ፤ ይሄንን ወደ ውጤት ለመቀየር ደግሞ ባለድርሻ አካላት ከሚመለከታቸው ጋር ተግባብተው በቅንነት ከሠሩ ኅብረተሰቡ የሚፈልገውን ውጤት ለማስመዝገብ ብዙም አያዳግትም እንላለን።አዲስ ዘመን ታህሳስ 24/2011ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "53d61749024e89099cbd0f10dc5beb32" }, { "passage": "ለ\nስፖርቱ ዕድገት ሳይንሳዊ መሰረቱን በያዘ መልኩ ታዳጊዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ስልጠና መስጠት ዋነኛ መፍትሔ መሆኑ በዘርፍ ሊቃውንት ይነገራል። በተለይ በእግር ኳሱ ውጤታማ መሆን የቻሉ አገራት በዚሁ መስመር በመጓዝ የታዳጊና ወጣት ስፖርት ማዕከል ፕሮጀክቶችን እንደ ዋነኛ መፍትሔ በመጠቀም ሠርተውበታል። ፍሬያማ መሆንም ችለዋል። ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር ፊፋ እና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ይሄንን መሰረት በማድረግ ፤ «የአምቦ የእግር ኳስ ማሰልጠኛ ማዕከል ጎል ፊፋ» በሚል ስያሜ ለመገንባት በ1999 ዓ.ም የመሰረት ድንጋይ በአምቦ ከተማ አስቀምጠዋል። ማዕከሉ ለሀገሪቱ የእግር ኳስ መጻኢ ጉዞ ውጤታማነት ጉልህ ሚና እንደሚኖረውም ትልቅ ተስፋ ተጥሎበታል። ማዕከሉ እንደተባለው ተገንብቶ ለሀገሪቱ እግር ኳስ ግብዐት የሚሆኑ ታዳጊዎች መልምሎ የማሰልጠን ፕሮጀክቱ የት እንደገባ ሳይታወቅ ቀረ። የማዕከሉ\nግንባታ ከዛሬ ነገ ይጀመራል ቢባልም ሳይጀመር ቀረ፡፡ ለማዕከሉ ከፊፋ የተለገሰው ገንዘብ የት እንዳረፈ የሚናገር ጠፋ። ለማዕከሉ ግንባታ የተዘጋጀው 12 ሄክታር መሬት በተለያዩ የማሰልጠኛ ሜዳዎች ፣ ሳይንሳዊ ስልጠናን የሚሰጥባቸው ማዕከላት ፣ የሰልጣኞች ማደሪያ ፣ መማሪያ ፣ የመዋኛ ገንዳ፤ ለመገንባት የቀረበውን ንድፈ ሃሳብ ከወረቀት ወደ መሬት ለማውረድ ተዘጋጅቷል። ለዚህ ተግባር የተሰናዳው መሬት ሙጃና አረም እንጂ የተባለው ሳይሆን ቀረ። ለማዕከሉ ግንባታ ከፊፋ የተለገሰው ዶላርም ወዴት እንደዋለ አየሁም ሰማሁም የሚል ጠፍቶ «የውሾን ነገር…» በሚለው ተከድኖ ለመቆየት አስገደደ። ዓመታት ከተጓዘ በኋላ የአምቦ ከተማ ህዝብም ሆነ የኦሮሚያ ክልል መንግሥት የስልጠና ማዕከሉን “ወይ ገነቡልን አልያም እኛ እንገንባው” የሚል ጥያቄን በብርቱ ጠየቁ። ከብዙ ንትርክ በኋላም በክልሉ ሙሉ ወጪ ተገንብቶ በ2006 ዓ.ም ወደ ሥራ ገባ። የአምቦ ጎል ፊፋ የእግር ኳስ ማዕከል በምን መልኩ እየተጓዘ ይገኛል? በስልጠናው ሂደት ውስጥ ያሉት ተስፋ ሰጪ ነገሮች ፤ በማዕከሉ ሳንካዎችና በሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ስፖርት ዝግጅት ክፍል ከአምቦ ጎል ፊፋ እግር ኳስ ማሰልጠኛ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሊሳ ለሜሳ ጋር ቆይታ አድርጓል። መልካም ንባብ። አዲስ ዘመን ፦ የአምቦ ጎል ፊፋ እግር ኳስ ማሰልጠኛ ማዕከል መቼና እንዴት ነበር የተቋቋመው? አቶ ሙሊሳ፦ የአምቦ ጎል ፊፋ እግር ኳስ ማሰልጠኛ ማዕከል በሀገሪቱ ያለውን የእግር ኳስ ችግር ለመቅረፍ ለታዳጊዎች ሳይንሳዊና ዘመናዊ ስልጠና በመስጠት በብዛት በጥራት እና በዲሲፕሊን የታነጹ የእግር ኳስ ስፖርተኞችን ለማፍራት በማለም በ1999 ዓ.ም የተመሰረተ ነው። በዚሁ ጊዜም በፊፋና ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ትብብር በቀድሞ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕሬዚዳንት አቶ አባዱላ ገመዳ የመሰረት ድንጋይ ተጣለ። የማዕከሉን ግንባታ ወጪ ዓለም አቀፍ እግር ኳስ ማህበር በጀት መመደቡ ተገልጿል። የማሰልጠኛ ማዕከሉ ግንባታም ከአንድ ዓመት በኋላ ተጀመረ። ግንባታው ይጀመር እንጂ ካለበት ሳይነቃነቅ ሶስት ዓመታት ተቆጠሩ። ማዕከሉ ይጠናቀቃል ተብሎ በተያዘለት ጊዜ ለመጠናቀቅ ይቅርና ሊገነባ የተቀመጠው ንድፈ ሃሳብ መሰረት ተደርጎ የመተግበሩ ሁኔታ ራሱ ጥያቄ ውስጥ መግባት ጀመረ። የማዕከሉን ግንባታ በኃላፊነት የተረከበው አካል በአግባቡ መስራት ስላልቻለ ክልሉ ራሱ ለማሰራት ጥያቄ ለማቅረብ ተገደደ። የህዝቡም ጥያቄ በተመሳሳይ ሁኔታ እንዲንጸባረቅ ሆኗል። ይሄንኑ ተከትሎ ከብዙ ውዝግብ በኋላ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ተረከበው። ክልሉ በራሱ በጀት ግንባታውን ያከናወነ ሲሆን፤ ሰው ሰራሽ የማሰልጠኛ ሜዳውን ደግሞ ፊፋ በራሱ ወጪ በማሰራት ግንባታው በ2002 ዓ.ም ተጠናቀቀ። አዲስ ዘመን ፦የማዕከሉ ግንባታ ሂደት በዚህ መልክ ከተጠናቀቀ በኋላ ወደ ስራ የገባበት ሁኔታን እንዴት ያስታውሱታል ?አቶ\nሙሊሳ፦የስልጠና ማዕከሉ ግንባታው ከተጠናቀቀ በኋላ በፍጥነት አገልግሎት መስጠት አልጀመረም። ከጅምሩ የነበሩ ልክ ያልሆኑ አካሄዶች እንደነበሩ ሁሉ፤ ወደ አገልግሎት ለመግባትም ተመሳሳይ ችግሮች አጋጥመው ነበር። ይሁን እንጂ በ2005 ዓ.ም ክልሉ በመወሰኑ ስራ ጀመረ። ማዕከሉ ባለው መሰረተ ልማት፣ የማሰልጠን አቅም ስራ ሊጀምር ይገባል ተባለ። የሰራተኞች ቅጥር መፈጸም፣ ለሰልጣኞች የሚያስፈልገውን ቁሳቁስ ማሟላትና ሌሎች ተግባራትን ማከናወን ተቻለ። በተጨማሪም ወደማዕከሉ የሚገቡትን ሰልጣኞች ምልመላ አከናውኗል። በዚህም፤ በ2005 ዓ.ም በሀምሌ ወር በኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ አዘጋጅነት በሻሸመኔ ከተማ ለተካሄደው ውድድር ከ17 ዓመት በታች እድሜ ያላቸው ሰልጣኞች ተመለመሉ። የተመለመሉትም ልጆች 27 ወንዶች እና 22 ሴቶች ናቸው። በ2006ም ዓ.ም እነዚህኑ ታዳጊዎች በማዕከሉ በማቀፍ ስልጠና ጀምሯል። ሂደቱ ይሄን ይመስል ነበር። አዲስ ዘመን ፦ማዕከሉ ከተከፈተበት ግዙፍ አላማ አኳያ ያለፉት ዓመታት እንቅስቃሴው ምን መልክ አለው? አቶ ሙሊሳ፦ ማሰልጠኛ ማዕከሉ ሳይንሳዊና ዘመናዊ ስልጠና በመስጠት በብዛት፣ በጥራት እና በዲሲፕሊን የታነጹ የእግር ኳስ ስፖርተኞችን ማፍራት ዓላማው አድርጎ ነው የተነሳው፤ ከዚህ አኳያ ባለፉት አምስትና ስድስት ዓመታት ቆይታው ጅምሩ ተስፋ ሰጪ እንደሆነ ይታመናል። ለዚህ ደግሞ ማዕከሉ አቅሙን ባገናዘበ መልኩ ስልጠና ይሰጣል። ይሄንኑ ለማብራራት ያክል፤ ማዕከሉ ለሰልጣኞቹ ሳይንስን መሰረት ያደረገ የተግባርና የንድፈ ሃሳብ ስልጠና ይሰጣል። በሳምንት አራት ቀናት የሁለት ሰዓት የተግባር ስልጠና ይሰጣል። ሰልጣኞች በማዕከሉ በሚኖራቸው የአራት ዓመታት ቆይታ ይሄንኑ መንገድ በመከተል ያላቸውን ተፈጥሯዊ ችሎታ በሳይንሳዊ ስልጠና እንዲያጎለብቱት ይደረጋል። በዚህ ሂደት ውስጥ ከአመጋገብ፣ ከአካላዊ እንቅስቃሴ፣ ቴክኒካልና ታክቲካል በሆኑና ስፖርቱን በሚያግዙ ተያያዥ ጉዳዮች ላይ መሰረታዊ እገዛ መስጠትንም ታሳቢ በማድረግ ጭምር ነው። በተጨማሪም፤ በስልጠናው ምን ያህል ክህሎታቸውን አዳብረዋል? ምን ያህል ራሳቸውን ለውጠዋል? የሚለውም አብሮ በተግባር ይታያል። የወዳጅነት\nጨዋታዎችን በማድረግ፣ በክልልና በሱፐር ሊግ የውድድር መድረኮች በማሳተፍ ራሳቸውን በሚገባ እንዲፈትሹ ይደረጋል። ይህ ደግሞ የስልጠናው ሂደት በሚገባ እየተፈተሸና እየተመዘነ እንዲጓዝ ይረዳል። ይሄም ሰልጣኞቻችንን በሚገባ ረድቷቸውና አግዟቸው የተመለከትን ሲሆን፤ ሰልጣኝ የነበሩ ታዳጊዎቻችን ለዚህ ምስክር ይሆናሉ። ማዕከሉ ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ በመጀመሪያ ዙር ከ17 ዓመት በታች 27 ወንዶች እና 22 ሴቶችን ለሁለት ዓመት በማሰልጠን በድምሩ 49 ሰልጣኞችን በ2008 ዓ.ም. አስመርቋል። በዚህም የመጀመሪያ የውጤቱን ፍሬ ተመልክቷል። ከማዕከሉ የተመረቁት ሰልጣኞችም ተፈላጊ ናቸው። ሰልጣኞቹ በተለያዩ ክለቦች በመፈረም የመጫወታቸው ስኬት በቀጣይ ለሚሰራው ስራ ሞራል የገነባና ማሻሻል የሚገባውን ጉዳይም እንዲመለከት ያስቻለው ነበር። ማዕከሉ በዚህ ራሱን ተመልክቶና ማሻሻያዎች አድርጎ በአሁኑ ወቅት የወቅቱን ዘመናዊ የስፖርት ሳይንስ ያማከለ ካሪኩለም አስቀርጾ 15 እና 17 ዓመት የሆናቸውን 30 ወንዶች እና 24 ሴቶች በድምሩ 54 ልጆች እያሰለጠነ ይገኛሉ። ስልጠናቸውን ከአንድ ዓመት በኋላ የሚያጠናቅቁት እነዚህ ሰልጣኞችም ሲመረቁ በመጀመሪያ ዙር እንደነበረው ሁሉ በክለብ፣ ብሎም በብሄራዊ ቡድን ደረጃ እስከ መመረጥ ይደርሳሉ ተብሎ ይጠበቃል። ስለዚህ በቀጣይ የሚመረቁ ተጫዋቾች በዚህ ሂደት ውስጥ ያልፋሉ የሚል እምነት በመያዝ እየተሰራ ይገኛል። አዲስ\nዘመን ፦ በማዕከሉ የመጀመሪያ ዙር የተመረቁ ሰልጣኞች ውጤታማነት እንዴት ይገለጻል? አቶ\nሙሊሳ ፦ በማዕከሉ በመጀመሪያው ዙር ሰልጥነው የወጡ ታዳጊዎች በተለያዩ ክለቦች ይጫወታሉ፤ ብሎም በብሄራዊ ቡድን ደረጃ እስከ መመልመል ደርሰዋል። ከዚህ አኳያ ማዕከሉ ለክልልና ለሀገር ያበረከተው አስተዋጽኦ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከ17 ዓመት በታች 4 ሴቶች፣ በመላው ኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች ውድድር ኦሮሚያን የሚወክሉ ወንዶችና ሴቶች ማስመረጡ፤ ለመላው ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ኦሮሚያን የሚወክሉትን ወንዶችና ሴቶች ማስመረጡ ማሳያዎች ናቸው። ከሰልጣኞቹም መካከል ወደተለያዩ ክለቦች የተዘዋወሩ አሉ። ስለዚህ ማዕከሉ ያሉበትን ችግር ከቀረፈና የሚመለከተው አካል ተገቢውን ድጋፍ ማድረግ ከቻለ በሁለቱም ጾታ አሁን ከታየው በላይ ለሀገር ትልቅ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ተጫዋቾችን ማበርከት ይቻላል የሚል ሙሉ እምነት አለኝ ። አዲስ ዘመን ፦ማዕከሉ በጥሩ መስመር እንደተጓዘ ቢሆንም ችግሮች አሉ ብለዋልና ችግሮቹን ዘርዘር አድርገው ቢነግሩን ? አቶ\nሙሊሳ ፦ ማዕከሉ የተለያዩ ችግሮች አንቀው ይዘውታል። በመጀመሪያ ደረጃ ከመሰረተ ልማት ጋር ተያይዞ ያለው ችግር ነው። በማዕከሉ ንድፍ ላይ ሶስት አራት የመጫወቻ ሜዳዎች፤ የመዋኛ ገንዳ፣ ጂም፤… ወዘተ. እንዳሉት ያመለክታል። ነገር ግን፤ ማዕከሉ በአሁኑ ሰዓት አንድ ሜዳ ብቻ ነው ያለው፤ እሱም ሰው ሰራሽ (አርቴፊሻል) ሜዳ፤በዚህም ሰልጣኞቹ በውድድር ጊዜ በተፈጥሮ ሜዳ ላይ ሲጫወቱ ችግር ፈጥሮባቸዋል። የጂም፣ የመዋኛና ሌሎች ጉዳዮችም በተመሳሳይ ተጽእኖ ያሳደሩ ይገኛሉ። ከበጀት ጋር ተያይዞ ያለው ችግርም በሌላው ማዕዘን ይጠቀሳል። ለስልጠና ማዕከሉ የሚበጀተው በጀት እጅግ አነስተኛ ነው። በማዕከሉ በርካታ ሰልጣኞችን ለማሰልጠን የሚያስችል አይደለም። የሰል ጣኞችን ቁጥር ከፍ ለማድረግ እቅድ ቢኖረንም የበጀት ጉዳይ እንቅፋት ሆኖብናል። በማዕከሉ ያሉትን ሰልጣኞች በተስፋፋ መልኩ ይዞ ለመጓዝ የሚያስችል ራሱ በቂ አይደለም። ለሰልጣኞችም ሆነ ለአሰልጣኞች ትጥቅ በበቂ ሁኔታ ለማቅረብ ችግር ሆኗል። ምክንያቱም የትጥቁ በጀት በጣም ትንሽ ነውና፤ ሌላው የማዕከሉ ሳንካ የተሽከርካሪ ችግር ነው። ሰልጣኞች ከቦታ ቦታ ተጓጉዘው የአቋም መለኪያ ጨዋታዎችን ለማድረግ የመጓጓዣ አውቶቡስ ችግር ሆኖብናል። ሰልጣኞች ህመም ሲገጥማቸው ወደህክምና የሚወሰዱት በባጃጅ ነው። ምክንያቱም ማዕከሉ የራሱ የሆነ ሰርቪስም ሆነ ተሽከርካሪ የለውም። እነዚህ ችግሮች ማዕከሉ በሚያደርገው ግስጋሴ ላይ ሳንካ እየፈጠሩ ይገኛሉ። አዲስ ዘመን፦ ማዕከሉ ያለበትን የበጀትም ሆነ ተጓዳኝ ውስንነቶች እንዲ ቀረፉለት ለሚመለከተው አላሳወቀም? አቶ ሙሊሳ ፦ የማዕከሉን ችግሮች ለሚመለከተው አካል አቤት ብንልም ምላሽ ማግኘት ግን አልተቻለም። የኦሮሚያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ማዕከሉን በመጎብኘት፣ ትጥቅና ሌሎች ድጋፎችን በማድረግ አጋርነታቸውን አሳይተዋል። የማዕከሉ ጉዳይ በቀጥታ የሚመለከታቸው አካላት ግን ዘወር ብለው አልተመለከቱንም። በተለይ ደግሞ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ኃላፊነቱን ራሱ አልተወጣም። አዲስዘመን፦እነዚህ«የሚመለከታቸው አካላት የተባሉት» እነማን ናቸው ? አቶ\nሙሊሳ ፦ የስልጠና ማዕከሉ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስቴር እንዲያስተዳድረው ነበር የታሰበው፤ በግንባታው ሂደት ላይ ውዝግብ መፈጠሩን ተከትሎ አስተዳደሩን ለመቀየር አስገድዷል። በዚህም ማዕከሉ በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት እንዲተዳደር ውሳኔ የተቀመጠ ሲሆን፤ ለወጣቶችና ስፖርት፣ ለብሄራዊ ፌዴሬሽኑ፣ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የኦሮሚያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት የጋራ ኃላፊነት እንዲወስዱ ነበር የተደረገው፤ ይሄንኑ ተከትሎ ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ በቦርድ አባልነት ተካትቶና ኃላፊነት ወስዶ እንዲሰራ በመመሪያ ደረጃ የተቀመጠም ነበር። እነዚህ አካላት በተለይ ደግሞ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ኃላፊነቱን ለመወጣት ምንም አይነት ፍላጎት አላሳየም። በዚህም ምክንያት የስልጠና ማዕከሉ በእጅጉ ተጎድቷል። ከፊፋ ጋር ያለውን ግንኙነትም አሳጥቶታል። አዲስ ዘመን ፦ ይህ ሁሉ ችግር የብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ለመሆኑ ማስረጃው ምንድን ነው? አቶ\nሙሊሳ ፦በመመሪያው የተቀመጠው ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ በተለየ መልኩ ድልድይ በመሆን ማዕከሉንና ፊፋን የማገናኘት ስራ እንዲሰራ ነበር፤ ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፌዴሬሽን) በስሙ “ፊፋ አምቦ ጎል ፕሮጀክት የእግር ኳስ ስልጠና ማዕከል” በሚል መጠሪያ ማዕከሉን የከፈተው ያለምክንያት አይደለም። አንድ ማሳያ ለመጥቀስ፤ ማዕከሉ ሰው ሰራሽ (አርቴፊሻል) ሳር በመሆኑ በፊፋ አማካኝነት ሜዳውን በዓመት አንድ ጊዜ እድሳት እንዲደረግለት ቃል ተገብቷል። በማዕከሉ የስድስት ዓመት ቆይታ ግን ከአንድ ጊዜ በላይ ሜዳው እድሳት አልተደረገለትም። ፊፋ ለማዕከሉ ከሜዳ እድሳት በተጨማሪ ሌሎች መሰረታዊ ድጋፎችን ማድረግ ይገባው ነበር። ለማዕከሉ የገንዘብ፣ የትጥቅ፣ የሙያ ስልጠና በማድረግ ድጋፍ ለመስጠት ቃል መግባቱ ይታወቃል። ይህ እየሆነ አይደለም። ለዚህ ደግሞ ዋነኛው ሳንካ ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ነው። ፊፋ ማዕከሉን እንዲያግዝም ሆነ ማዕከሉ ከፊፋ ጋር እንዲገናኝ ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ እንደ ድልድይ ያገለግላል። ይሁንና፤ ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ከፊፋ ጋር ድልድይ መሆን ሲገባው ጭራሹኑ አቆራረጠን። ማዕከሉ ማንኛውንም ግንኙነት የሚያደርገው በብሄራዊ ፌዴሬሽኑ በኩል ብቻ ስለሆነ እኛ ለመገናኘት አልቻልንም። አዲስ\nዘመን ፦በመጨረሻም ማስተላለፍ የሚፈልጉት መልዕክት ካለ? አቶ\nሙሊሳ ፦ የስልጠና ማዕከሉ እያደረገ ያለው አበረታች እንቅስቃሴ እያደገ ነው። የማዕከሉን ፍሬያማነት ቀጣይነት እንዲኖረው የሚመለከታቸው አካላት የተጠቀሱት ችግሮች እንዲቀረፉ እገዛ ማድረግ ይገባቸዋል። በእኛ በኩል ለብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ተደጋጋሚ ጥያቄና ደብዳቤ ብንጽፍም ምላሽ ማግኘት ግን አልቻልንም። የስልጠና ማዕከሉ ከተነሳበት ሀገራዊ አላማ፤ እያደረገው ካለው በጎ እንቅስቃሴ አኳያ ይህ ችግር አንድ ቦታ መፍትሄ ሊበጅለት ይገባል። ብሄራዊ ፌዴሬሽኑም የተሰጠውን ኃላፊነት በሚገባ ሊወጣ ይገባል፤ እንላለን። አዲስ ዘመን ፦ ስለነበረን ቆይታ እናመሰግናለን። አቶ\nሙሊሳ ፦እኔም እዚህ ድረስ መጥታችሁ ሃሳቤን እንድናገር እድሉን ስለሰጣ ችሁኝ በማዕከሉ ስም በእጅጉ አመሰግናለሁ።አዲስ\nዘመን መጋቢት4/2011በዳንኤል\nዘነበ", "passage_id": "1b2fccd4aa267ede9fdea3eb6c8db1b1" }, { "passage": "1953 ዓ.ም ከአዲስ አበባ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው አቃቂ ከተማ ጋርዱባ 06 አካባቢ ነበር የተወለደው፤ በልጅነቱ ፈጣንና አስተዋይ እንደነበር ይነገራል። የታዳጊው ሁኔታ በቤተሰቦቹም ሆነ በአካባቢው ሰዎች ዘንድ ከፍተኛ ደረጃ እንደሚደርስ ተስፋ እንዲጣልበት አድርጎታል። የታዳጊው ብሩህ አዕምሮ በቀለም ትምህርት ቢታገዝ ደግሞ እኛንም አገሩንም ያኮራል ብለው አስበዋል።ተሻጋሪ ተስፋ ማድረግ ብቻም ሳይሆን በአካባቢው በሚገኘውና ፊት አውራሪ በሚባለው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት አስመዘገቡት። በአስኳላ ውሎው በጥሩ ተማሪነትና በፈጣን ሯጭነቱም ጭምር ለመታወቅ የቻለው የትናንቱ ታዳጊ የቀድሞ አትሌት ሸምሱ ሀሰን ነው። የትምህርት ቤት ቆይታውን እየወደደው ቢመጣም፤ የቤተሰቦቹ ሁኔታ ግን ሊያራምደው አልቻለም።የቤተሰቡን ችግር ለማቃለል እርሱ ቢያንስ ራሱን ማስተዳደር ቢችል ትልቅ ብርታት እንደሚሆናቸው ሃሳቡ ነበር። በቀለም ትምህርቱ ብዙ ርቀት መጓዝ ቢያልምም አልቻለም። ከቤተሰብ ጥገኝነት ለመላቀቅ ከስድስተኛ ክፍል አቋርጦ ወደ ውትድርና ለማቅናት ወሰነ። አደረገውም፤\nሸምሱ፤ በብሄራዊ ውትድርና ውስጥ ለስልጠና የተመደበለትን ጊዜ አጠናቀቀ። አዲስ አበባ ማዕከላዊ ዕዝ ተመድቦ የህይወቱን ሌላኛውን ምዕራፍ ማጣጣሙን ያዘ። ሸምሱ የልጅነት ህልሙ በዚህ መልኩ እንዲሆን ፍላጎት ባይኖረውም፤ የሆነውን ግን ተቀብሎ ቀጠለ። በትምህርት ቤት ውስጥ ፈጣንና ተስፈኛ እግሮቹ በጦሩ ቤት ያለውን ቆይታ ወደ ስፖርት እንዲገባ አስችለውታል። በማዕከላዊ ዕዝ ውስጥ የሚያደርገው የስፖርት እንቅስቃሴ በጦሩ ውስጥ ለእጩነት አበቃው።የእርሱን የዕጣ ጎዳና በአትሌቲክሱ ያደረገው አጋጣሚም በዚህ መልክ ተወለደ። የስፖርት አጀማመሩ በ1500 ሜትርና በ800 ሜትር ነበር። በእነዚህ ርቀቶች በተለያዩ ውድድሮች በመሳተፍ ሁለት ጊዜ ሦስተኛ ደረጃ ይዟል። አትሌቱ እግሮቹን ያሟሸው በእነዚህ ርቀቶች ይሁን እንጂ፤ እስከመጨረሻ የዘለቀው ግን በእርምጃ ውድድር ነበር። አጋጣሚው እንዲህ ነበር። አንድ ቀን በማዕከላዊ ዕዝ ስፖርት ውስጥ ብዙም ባልተለመደው የእርምጃ ሩጫ እንዲሳተፍ ይጠየቃል። ጥያቄው ለተሳትፎ ያህል የነበረ ቢሆንም፤ በውድድሩ ባለድል መሆን ቻለ። በ1974 ዓ.ም በአገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደ ውድድር ተሳትፎ አሸናፊ ሆነ። አትሌቱ በእርምጃ ውድድሩ አሸናፊነቱ በአሰልጣኞቹ የመመረጥ እድል አገኘ። አገሩን ለማስጠራት በብዙዎች ዘንድ ተስፋ እንዲጣልበት ያደረገም ነበር።በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ውስጥ ስማቸው ተጠቃሽ ከሆኑት መካከል ሻለቃ ባሻ ዋሚ ቢራቱ የሸምሱን ተስፈኝነት ከመሰከሩ ታላላቅ የስፖርት ሰዎች መካከል ተጠቃሽ ነበሩ። የእርሱ የእርምጃ ሩጫ የተለየ ክህሎት በመገንዘብና አርቀው በማስተዋል በደንብ እንዲሰራ ይመክሩት ነበር። ይህም በስፖርቱ ጉዞውን የጀመረበትን ርቀት በመተው ወደ እርምጃ ሩጫው ብቻ እንዲያዘነብልም ጭምር ሀሳብ እስከ መለገስ ደርሰዋል። እርሱም በእርምጃ ስፖርት ውድድር መጽናቱን ነው የሚናገረው፤ አገራችን በእርምጃ ውድድር ግን በማትታወቅበት ሁኔታ ገፍቶ ለመሄዱ የዋሚ ቢራቱ ምክር ለእርሱም ብቻም ሳይሆን በወቅቱ ለነበሩት ወንዴ ጦሬ፣ ተከስተ ዮሃንስ፣ ጥላሁን ሸገና በጽናት እንዲቆዩ ያደረገ ጭምር እንደነበር ሸምሱ ያስታውሳል።እርሱ እንደሚለው፤ «በአገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄዱ ውድድሮች እይታ ውስጥ ለመግባት የቻልኩበትን አጋጣሚ መፍጠር ቻልኩ። ይህ ሁኔታ ደግሞ የተሳትፎዬን ደረጃ ተሻጋሪ የሚያደርግልኝን አጋጣሚ ይዞ ብቅ አለ። በአገር ውስጥ የእርምጃ ውድድር ብቃቴ ተለክቶ በዓለም አቀፍ መድረክ ታጨሁ። በ1975 ዓ.ም በኬኒያ ናይሮቢ ላይ በተካሄደው የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ውድድር ላይ በእርምጃ ሩጫ ለአገሬ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ ማምጣት ቻልኩኝ። በዚህ ድል ለራሴም ሆነ ለእናት አገሬ አኩሪ ድል ያመጣሁበት ትልቅ የህይወት አጋጣሚዬ ነበር። ይህም አሸናፊነት ገና ጅምር እንጂ የሚያበቃ እንዳልሆነም ለራሴው ቃል የገባሁበት አጋጣሚም ነው»።የልጅነት ህልሙ መስመሩ በስፖርት ውስጥ ይሆናል የሚል ቅንጣት ያህል ፍላጎት ያልነበረው ወጣቱ ከስኬት ወደ ስኬት መሸጋገር ጀመረ። ከአንድ ዓመት ቆይታ በኋላ ግብጽ ውስጥ የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በመሳተፍና በአንደኝነት በማጠናቀቅ የወርቅ ሜዳሊያ እንዳሸነፈ ይናገራል። ከዚህ በኋላም፤ በተለይ በኬኒያ እና በግብጽ በተዘጋጁ ውድድሮች ላይ በተደጋጋሚ የመሳተፍ እድል እንደነበረው ያስታውሳል። «በኬኒያም ሆነ በግብጽ በተካሄዱ ውድድሮች አሸናፊ መሆን ችያለሁ። ኬኒያ ውስጥ በተካሄዱ ውድድሮች አራት ጊዜ ተሳትፌያለሁ። በሁሉም አንደኛ ሆኜ ነው ያሸነፍኩት፤ በግብጽ በተመሳሳይ የመሳተፍ አጋጣሚዎች ነበሩኝ። ከነበሩት አራት ውድድሮች በአንዱ ብቻ ሁለተኛ ስወጣ የተቀሩትን በአሸናፊነት ነበር ያጠናቀኩት» ይላል ሸምሱ።የወጣቱ የድል ጉዞ ከፍ በማለት በአራት ዓመት አንዴ በሚዘጋጀው ኦል አፍሪካ ጌምስ ላይ ሦስት ጊዜያት የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት ለመሆን በቅቷል። ፈጣኑና ትንታጉ አትሌት የድል አድማሱን ከፍታ ከአህጉር አፍሪካ ተሻግሮ ለኦሎምፒክ ውድድር ወደባርሴሎና መጓዙን የሚያስታውሰው ሸምሱ በውድደሩ አምስተኛ ደረጃ በመያዝ ነበር ያጠናቀቀው፤ ሩሲያ በመጓዝ ደግሞ ስምንተኛ ወጥቶ ማጠናቀቁን ያስታውሳል። «በጊዜው እኔ ትኩረት የማደርገው ሰዓቴን ማሻሻሌን ነው» ይበል እንጂ፤ አገራችን ብዙም ባልታወቀችበት የእርምጃ ውድድር በድሉ ከአገር ውስጥ እስከ አህጉር፤ ከዚያም እስከ ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች የተሻገረ ስኬት ያስመዘገበ የአገር ባለውለታ ነው። ሸምሱ በአትሌቲክሱ እያደገ የመጣው ውጤቱ በማዕረግ የታጀበም ሲሆን፤ ከአስር አለቅነት እስከ ሻለቃነት የደረሰ ነበር።የሸምሱ የስፖርት ጉዞው ብቻም ሳይሆን የህይወት ኡደቱ ከ1974 እስከ 1992 ወርቃማ ዓመታት ናቸው ለማለት ያስደፍራል። አትሌቱ በእነዚህ 18 ዓመታት በስፖርቱ እራሱንም ሆነ አገሩን አስጠርቷል። ቤተሰብ በማፍራትም ህይወቱን በደስታ አጣጥሟል። የዚህ ሁሉ ታሪክ ባለቤት የሆነውና የቀድሞው የእርምጃ ውድድር ባለድሉ ጎልማሳ የአዕምሮው ሁኔታ በመታወኩ ምክንያት እጅና እግሩን አጣጥፎ ከቤት ለመዋል ተገደደ። ከእርሱ በኋላም በመስኩ አሸናፊ ሆኖ የወጣ አትሌት አለመኖሩን ባገላበጥናቸው የተለያዩ መረጃዎች ለመገንዘብ ችለናል። በአሁኑ ወቅት ግን ለአገሩ የሰራው ገድል ተረስቶ፤ እርሱም አስታዋሽ አጥቶ በአዕምሮ ህመም እየተሰቃየ ይገኛል። ከኬኒያ እስከ ሩሲያ በእርምጃ ብቻ ሜዳሊያዎችን ያስገኙ እግሮች፤ የሚመራቸው ጤናማ አዕምሮ አጥተው ተሳስረው ቁጭ ለማለት ተገድደዋል። በከባድ ህመም ውስጥ ከመሰቃየት በቀር አማራጭ ያጣው ሸምሱ፤ በተለያዩ ውድድሮች አሸናፊ ቢሆንም ዘመኑ ስፖርተኞች እንዲህ እንደዛሬው የማይሸለሙበት ነበርና በስፖርቱ ተጠቃሚ መሆን እንዳልቻለ ይናገራል። «በአሁን ሰዓት አላውቅም እንጂ እኔ በነበርኩበት ጊዜ የገንዘብ ሽልማት ሳይሆን የአበባ ጉንጉን ነበረ ወደ አገራችን ስንመለስ የሚበረከትልን፤ መንግሥት በእርምጃ ውድድር አሸንፌ ስመጣ ይሰጠኝ የነበረው ከብር 1500 ያልበለጠ ገንዘብ ነበር» በማለት በጊዜው ከስፖርቱ ተጠቃሚ እንዳልነበር ያስታውሳል። የአገር ባለውለታ የሆነው የቀድሞው አትሌት ሸምሱ ሀሰን በስፖርቱ ያገኘው ጥቅም ያለመኖሩ ብቻም ሳይሆን ጤናው መታወኩ ደግሞ ቤተሰብ ይዞ በችግር ለመቆራመት እንደዳረገው ይናገራል።አትሌቱ ሲጀመር ስምንት መቶ፤ በአሁኑ ወቅት ደግሞ 1400 ብር በሚያገኛት የጡረታ ገንዘብ በችግር መኖር እጣው ሆኖበታል። የተገኘውን ሥራ ለመስራት እንዳይችል ህመሙ ጋሬጣ ሆኖበት የሚያገኛትን የጡረታ ገንዘብ አጠገቡ ከሚገኙት ባለቤቱና ሁለቱ ልጆቹ ጋር በመቋደስ የችግር ህይወት ለመግፋት ግድ እንደሆነበት ይገልጻል። የሥራ ፍላጎት ቢኖረውም የህመሙ ሁኔታ ሰርቼ እንኳን ለመብላት እንዳልችል አድርጎኛል ሲል ይናገራል። በአንድ ባንክ ውስጥ በጥበቃ ስራ ተቀጥሮ መስራት ቢጀምርም የጤናው ሁኔታ የሚያሰራ አይደለምና መቀጠል አልቻለም። የመንፈስ ከፍታው በዚህ ደረጃ የሆነው ሸምሱ ከአንዴም ሁለት ሦስቴ የተለያዩ ስራዎችን ለመስራት ጥሯል። የእርሱ ሁኔታ አላላውስ ያላት ባለቤቱም የህይወት አጋሯን በቤት ውስጥ ሆና ከማስታመም በስተቀር ወጥታና ሰርታ ተጨማሪ ገቢ ለማምጣት እንዳትችል ሳንካ እንደፈጠረባት ሲቃ እየተናነቀው ይናገራል።ሸምሱ፤ የጤናው መቃወስ ይሄንን ጠንካራ የመንፈስ ከፍታውን የናደበት ሲሆን፤ «አሁን ካለሁበት የችግር አረንቋ እንድወጣ እጃችሁን ዘርጉልኝ» ሲል ጥሪውን ለአገሩ ህዝብ ለማቅረብ ተገድዷል። ለርዳታ ጥያቄ የተዘረጋውን እጁን ተከትሎ የሁለት ኢትዮጵያዊያን ወገኖቹን ምላሽ እንዳገኘ አጫውቶናል።«እስካሁን የሁለት ኢትዮጵያዊያን ወገኖቼን መጎብኘት አስገኝቶልኛል። አንዷ ሁለት ሺ ብር አንደኛዋ ደግሞ አንድ ሺ ብር ሰጥተውኛል። ይሁን እንጂ፤ የእነዚህ ወገኖች ድጋፍ አሁን የደረሰበትን የጤና ችግርና ባዶውን ማጀት ለመሙላት አይችልም። አሁንም ጥያቄ የሆነብኝ ነገር አትሌቲክስ ፌዴሬሽኑ ስለምን በእኔ ላይ ጨከነ? ምን በድየው ይሆን!? ሊያስታውሰኝ እንዴት አቅም አጣ? ምን ላይ ወደክ እንኳን አላለኝም። እንዴት ነህ መባሉ የተሰበረን መንፈስ ያክማል። የገንዘብ ድጋፍ ይቅርና እስካሁን የት ወደክ አላለኝም። ይህ ሁሌም ጥያቄ የሚያጭርብኝና የዘወትር ብስጭቴ ነው» ሲል ሃሳቡን ይቋጫል።አገራችን ብዙም ስሟ በማይነሳበት በእርምጃ ውድድር በግሉ ጥረት ከፍ ብሎ የነበረውን የቀድሞ አትሌት ሸምሱ ሀሰን በአሁን ወቅት ካጋጠመው የጤና ቀውስና ከገባበት የችግር አረንቋ እንዲወጣ ድጋፍ ሊደረግለት ይገባል። በአሁን ወቅት በአዕምሮ ህመም መሰቃየት ብቻም ሳይሆን በጡረታ በሚያገኛት አንድ ሺህ አራት መቶ ብር ስድስት ቤተሰብ እያስተዳደሪ እንደሚገኝ ተናግሯል። ሸምሱ እንዲህ እንደዛሬው ህይወት ፊቷን ሳታዞርበት የጤናው ሁኔታም ባልተቃወሰበት ወቅት በአትሌቲክሱ በተወዳዳሪነት ብቻ ሳይሆን በአሰልጣኝነት አገልግሏል።የአገር መከላከያ ሰራዊት አባል በመሆንም ለአገሩ ለመድማትና ለመሞት እራሱን አሳልፎ ሰጥቷል። ሸምሱ አነሰም በዛም እናት አገሩን ለማገልገል የተቻለውን ያህል ርቀት እንደመሄዱ፤ ከዛሬው ሰቆቃው እንዲወጣ ሁሉም የበኩሉን ሊያግዘው ይገባል። በተለይ፤ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቀድሞውን አትሌት ማስታወስ ይጠበቅበታል። የአገር ባለውለታ የሆነውና የተረሳው የቀድሞው አትሌት የዚህ ባለታሪክ ሆኖ ይቅረብ እንጂ፤ አስታዋሽ የማጣት ቁጭት፤ የጤና መቃወስ፣ የወገን አይዞህ ባይነት ማጣት እንደ ሸምሱ ሁሉ በበርካታ የአገር ባለውለታዎች ላይ የደረሰ በደል ነው። በጉብዝናቸው ወቅት ለአገራቸው ታሪክ የሰሩትን በቁም እያሉ ለመርዳትና ለማዳን ርብርብ አለማድረግ ሲያልፉ ቁጭትን ሲያጭር በተደጋጋሚ ይስተዋላል። በተለያዩ ዘርፎች ተሰማርተው የነበሩ የአገር ባለውለታዎችን ተረባርቦ በህይወት ለማቆም ሳይሆን ከሞቱ በኋላ ኃውልት ለማቆም መሯሯጥ መገለጫችን ይመስለኛል።የአገር ባለውለታዎችን ማሰብ ጥቅሙ ለአገር ነው። በተለያዩ ዘርፎች ለአገር የአቅማቸውን የሚበረክቱ ጀግኖችን ማፍራት ብቻ ሳይሆን፤ ከከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ጀግኖችን የመርሳት አባዜም ባለቤት ነን። በተጨማሪም በቁም ሳለ ከችግሩ፣ ከበሽታው ለማዳን ርብርብ ከማድረግ ይልቅ ለመቅበር የሚደረገው ርብርብ «አጃኢብ»ያሰኛል። ለዚህም ትልቁ ማሳያ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ነው። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በአትሌቲክሱ ብዙ አስተዋጽኦ ያደረጉ ጀግኖችን ማስታወስና መዘከር የማይሆንለት እንደሆነ በተለያዩ አጋጣሚዎች ታዝበነዋል። በተለያዩ አለም ዓቀፍ ውድድሮች ላይ በእርምጃ ውድድር ሜዳሊያዎችን ያገኘው የቀድሞው አትሌት ሸምሱ፤«አትሌቲክስ ፌዴሬሽኑ ስለምን በእኔ ላይ ጨከነ? ምን በድየው ይሆን? ሊያስታውሰኝ እንዴት አቅም አጣ?» ሲል ቁጭቱን ሲገልጽ ታዝበናል።በኦሊምፒኮችና በዓለም ሻምፒዮናዎች ላይ ኢትዮጵያን ወርቅ በወርቅ ያደረጉ ጀግኖች አትሌቶች ዋና አሠልጣኝ የነበሩት ዶ/ር ወልደ መስቀል ኮስትሬን፣ ሻምበል ምሩፅ ይፍጠርን በህይወት ሳሉ በመርሳት፤ ህይወታቸው ካለፈ በኋላ ኃውልት ለማቆም ሲታትር ነበር። ይህም ፌዴሬሽኑ አንጋፋዎቹ የአገር ባለውለታዎች ህይወታቸው ሳይቃወስ ድጋፍ ከማድረግ ይልቅ፤ ሲሞቱ ለሙሾና ለሀውልት ከመሮጥ አባዜው ዛሬም እንዳልተላቀቀ ከተለያዩ ወገኖች የተሰነዘረ ትችት ነው።ፌዴሬሽኑ ትናንት ከሰራው ስህተት ከመማር ይልቅ፤ ሌላ ታሪካዊ ስህተት ለመፈጸም እደማይመለስም አብሮ የተነሳ ሃሳብ ነበር። በአትሌቲክስ ፌዴሬሽን በኩል የአገር ባለውለታዎችን እጀ ሰባራ የማድረጉ ስንኩሉ ልምድ በስፖርቱ ብቻም ሳይሆን፤ በተለያዩ የሙያ መስኮች የዜግነት ግዴታቸውን የተወጡ የአገር ባለውለታዎች የመደገፍ ልምዱ ኢምንት ነው። የአገር ባለውለታዎቹ ምናልባትም የሚታወሱት ወይ ታመው አልጋ ሲይዙ፣ ወይም ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ ነው፡፡ አንጋፋዎች ሲዘነጉ ተከታዩ ትውልድ ተስፋ ይቆርጣል፡፡ ለባለውለታዎች ዕውቅና ለመስጠት በሕግ ማዕቀፍ የሚመራ የሜዳሊያና የኒሻን፣ በአገልግሎት ዘመን መጠን የሚበረከት ሽልማትና የምሥጋና ሥነ ሥርዓት ሊኖር ይገባል፡፡ አገርን በፍቅር ማገልግል የውዴታ ግዴታ ቢሆንም፣ አስመስጋኝ ተግባር ላከናወኑ አኩሪ ዜጎች ዕውቅና መስጠት የአገር ባህል መሆን ይገባል ባይ ነን፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2011ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "7aa562443d19f2caff6421e1e336ad9b" } ]
d662787665fa6799e5cfc7a5b0f8e576
035e6da1ef177119d272c270d52a4dd9
የቀጣዩ አራት ዓመት የአትሌቲክስ መሪዎች
ቦጋለ አበበየኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከትናት በስቲያ ባደረገው 24ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ በቀጣይ አራት ዓመታት ፌዴሬሽኑን የሚመሩ ሰዎችን ለይቷል።ከአራት ዓመት በፊት ፌዴሬሽኑን በፕሬዚዳንትነት ለመምራት የተመረጠው ጀግናው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ሁለት ዓመት አገልግሎ በራሱ ፍቃድ ስልጣኑን ከለቀቀ በኋላ ሌላኛዋ ጀግና አትሌት ኮሎኔል ደራርቱ ቱሉ በተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንትነት ፌዴሬሽኑን ስትመራ ቆይታለች።ከትናንት በስቲያ ማታ በካፒታል ሆቴል በተደረገው ምርጫም ደራርቱ ለቀጣዩ አራት ዓመት ፌዴሬሽኑን በፕሬዚዳንትነት ለመምራት በጠቅላላ ጉባዔው ይሁንታ አግኝታለች።ምርጫው ከመከናወኑ ከሳምንት በፊት ለፕሬዚዳንትነት ለመወዳደር ዕጩ ሆነው በደቡብ ክልል የተወከሉት አቶ ተፈራ ሞላ፣ ለስፖርቱ ቅርበት ያላት ደራርቱ ከመሆኗ ባሻገር ባለፉት ሁለት ዓመታት በተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንትነት ፌዴሬሽኑን በመምራት ያደረገችውን ጥረት እንድትቀጥል ከእጩነት ራሳቸውን ማግለላቸው ይታወቃል።በዚህም ደራርቱ በፕሬዚዳንትነት ምርጫ ፉክክሩ ብቸኛ እጩ ሆና በመቅረብ አስቀድሞም ማሸነፏ የተረጋገጠ ነበር።በዚህም ጠቅላላ ጉባዔው በሃያ ሰባት ድምፅና በአንድ ተቃውሞ የደራርቱን ፕሬዚዳንትነት እንዳረጋገጠ በወቅቱ የተገለጸ ቢሆንም ፌዴሬሽኑ ደራርቱ ካለምንም ተቃውሞ በሙሉ ድምፅ ማሸነፍ እንደቻለች ትናንት ገልጿል።በምርጫው በተሰጠው ድምፅ በአንድ ተቃውሞ መመረጧ የተገለጸው በስህተት መሆኑን የጠቆመው ፌዴሬሽኑ በድምፅ አሰጣጥ ወቅት በምርጫ ወረቀት ላይ ድምፅ ሰጪው የራይት ምልክት ማድረግ ሲገባቸው የኤክስ ምልክት በማድረጋቸው መሆኑን አረጋግጧል። ከፕሬዚዳንታዊ ምርጫው ይልቅ ለሥራ አስፈፃሚነት በቀረቡት አስራ ስምንት እጩዎች መካከል የሚደረገው ፉክክር በጉጉት እንዲጠበቅ አድርጎታል።ከአራት ዓመት በፊት በሥራ አስፈፃሚነት ለመወዳደር እጩ ሆኖ ቀርቦ በአንድ ድምፅ ተበልጦ ያልተሳካለት የሲድኒ ኦሊምፒክ የማራቶን ባለድሉ አትሌት ገዛኸኝ አበራ ዘንድሮ በኦሮሚያ ክልል እጩ ሆኖ በመቅረብ ተሳክቶለታል።በተመሳሳይ ኦሮሚያ ክልል እጩ አድርጎ ያቀረባቸው ወይዘሮ ሰሃራ ሃሰን አዲስ የሥራ አስፈፃሚ አባል ሆነው ተመርጠዋል።አማራ ክልል እጩ አድርጎ ያቀረባቸው ወይዘሮ አበባ ዮሴፍም አዲስ የሥራ አስፈፃሚ አባል ሆነው ተመርጠዋል።ወይዘሮ አበባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሴቶች፣ወጣቶችና ሕፃናት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ መሆናቸው ይታወቃል።ባለፉት አራት ዓመታት የፌዴሬሽኑ ሥራ አስፈፃሚ አባል ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት ባለሀቱ አቶ በላይነህ ክንዴም ከአማራ ክልል ለሥራ አስፈፃሚነት ተወዳድረው በማሸነፍ የሚቀጥሉ ይሆናል።አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልነት ያቀረባቸው ሁለት እጩዎችም አሸናፊ መሆን ችለዋል።የስፖርት ሳይንስ መምህሩና በስፖርቱ ውስጥ ለረጅም ጊዜ በማገልገል የሚታወቁት ዶክተር በዛብህ ወልዴ ባለፉት ዓመታትም ሥራ አስፈፃሚ አባል የነበሩ ሲሆን፤ ለቀጣዩ አራት ዓመትም እንደሚቀጥሉ አረጋጠዋል።ሌላኛዋ  የአዲስ አበባ እጩ ወይዘሮ ትልቅሰው ገዳሙም አዲስ ሥራ አስፈፃሚ አባል ሆነዋል።ከፕሬዚዳንታዊ ምርጫው ራሳቸውን በማግለል በሥራ አስፈፃሚነት የተወዳደሩት አቶ ተፈራ ሞላም ከደቡብ ክልል ሥራ አስፈፃሚ ሆነው ተመርጠዋል።ባለፉት ዓመታት በሥራ አስፈፃሚነት ሲያገለግሉ የቆዩት የአፋር ክልል ተወካይ ወይዘሮ ፊዚያ ኢድሪስም የሚቀጥሉበት ዕድል አግኝተዋል።በጠቅላላ ጉባዔው ወቅት ስፖርቱን ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመምራት ምስጉን ሥራዎችን እንዳከናወነች በመግለጽ አድናቆት ሲቸራት የነበረችው ደራርቱ ከምርጫው በኋላ ፕሬዚዳንትነቷን በማረጋገጧ ባላት ልምድና እውቀት አገሯን በቅንነት ለማገልገል ቁርጠኝነቱ እንዳላት ተናግራለች።በእጩነት ያቀረባትን ኦሮሚያ ክልል እንዲሁም ከፕሬዚዳንታዊ ምርጫው ራሳቸውን በማግለል እድሉን እንድታገኝ ያደረጉትን አቶ ተፈራ ሞላን አመስግናለች።በቀጣይም ባለፉት ዓመታት ከነባሩ ሥራ አስፈፃሚ ጋር ስፖርቱ የሚፈልገውን ሁሉ ለማድረግ ያደረገችውን ጥረት ከአዲሱ ሥራ አስፈፃሚ ጋር እንደምትቀጥልበት ቃል ገብታለች።ፌዴሬሽኑ በቀጣይ ስምንት ዓመታት የሚመራበት ስትራቴጂክ እቅድ ለጠቅላላ ጉባዔው ቀርቦ የፀደቀ ሲሆን፤ የተለያዩ ሃሳቦች ቀርበውም ውይይት ተደርጎባቸዋል።ፌዴሬሽኑ የተለያዩ እቅዶችን ሲያቀርብ አትሌቶችን በዓለም አቀፍ ውድድሮች ወደተለያዩ አገራት በመላክ ለመወዳደር እንጂ በአገር ውስጥ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን የማዘጋጀት እቅድ ለምን አይኖረውም? የሚል ጥያቄ በመድረኩ ከተነሱ ሃሳቦች አንዱ ነው።ለዚህ ጥያቄ በተሰጠው ምላሽም ፌዴሬሽኑ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት ጥረት እንደሚያደርግ የተገለጸ ሲሆን፤ ዘንድሮ የአፍሪካ አገር አቋራጭ ቻምፒዮናን ለማስተናገድ እንደታሰበ ተጠቁሟል።ፌዴሬሽኑ በተለያዩ ዓመታዊ የውድድር መርሐግብሮቹ በሚያካሂዳቸው የጎዳና ላይ ውድድሮች የሕብረተሰብ ተሳትፎ አለመኖሩ ለብዙ ጊዜ ሲነሳ የነበረ ጥያቄ ሲሆን፤ ሕዝብ የሚሳተፍባቸው ውድድሮችን ለማካሄድ እቅድ እንዳለ ተጠቁሟል።ፌዴሬሽኑ በሌሎች ጉዳዮች ላይ ተወጥሮ ስልጠናን በመዘንጋት ውጤቶች በሚጠበቀው ደረጃ እየተገኙ እንዳልሆነም ትችቶች ተሰንዝረዋል።አዲሱ የሲዳማ ክልል አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የጉባዔው ተሳታፊ ከመሆኑ ባሻገር በሥራ አስፈፃሚ ምርጫ ላይ አንድ እጩ ባቀረበበት መድረክ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክኒያት ስፖርቱ አስቸጋሪ ጊዜ ማሳለፉ ተገልጿል።ይሁን እንጂ በነዚህ አስቸጋሪ ጊዜያት ፌዴሬሽኑ እቅዶቹን በታሰበው ልክ ማከናወን ባይችልም እጁን አጣጥፎ ሳይቀመጥ በጥንቃቄ የተለያዩ ሥራዎችን ሲያከናውን እንደቆየ ተጠቁሟል።ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በዓለም አቀፍ ውድድሮች ‹‹ይህን ያህል ሜዳሊያዎች እናስመዘግባለን›› ብሎ ማቀድ አዳጋች እየሆነ መምጣቱን የጠቆሙት የፌዴሬሽኑ ፅሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቢልልኝ መቆያ የስፖርቱ ባህሪ እየተቀየረ እንደሚገኝ አስረድተዋል።በተለይም ኢትዮጵያ በምትታወቅበት የረጅም ርቀት ውድድሮች ሌሎች አገራትም ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸው ለዚህ ፈተና አንዱ ምክኒያት እንደሆነ የገለጹ ሲሆን፤ የሌሎች አገራት የኢኮኖሚ ጥንካሬና የዓለም አቀፍ ውድድር አዘጋጆች የአትሌቶች አበረታች መድሃኒት ተጠቃሚነትን ሽፋን መስጠት ተፅዕኖው ቀላል እንዳልሆነ አብራተዋል።ፌዴሬሽኑ በጉባዔው ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ በፊት በነበረው የስፖርቱ እንቅስቃሴ ጥሩ ሥራ ሠርተዋል ያላቸውን ከክልልና ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም ከክለቦች ስምንት ስምንት ተሸላሚዎችን መርጦ እንደየደረጃቸው ገንዘብ አበርክቶላቸዋል።በዚህም የኦሮሚያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ቀዳሚ በመሆን 240ሺ ብር ተሸላሚ ሲሆን፤ የአማራ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን 180ሺ ብር ተሸላሚ ሆኗል።አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 140ሺ፣ ደቡብ ክልል 100ሺ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ 80ሺ፣ ሐረሪ 60ሺ፣ ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር 40ሺና ጋምቤላ 20ሺ ብር ተሸላሚ ሆነዋል።ከክለቦች መከላከያ ስፖርት ክለብ ቀዳሚ በመሆን ሦስት መቶ ሺ ብር ተሸላሚ ሲሆን፤ የፌዴራል ፖሊስ ስፖርት ክለብ 240ሺ ብር ሊሸለም ችሏል።ጥሩነሽ ዲባባ አካዳሚ 180ሺ፣ ኦሮሚያ ፖሊስ 140ሺ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 100ሺ፣ ደቡብ ፖሊስ 80ሺ፣ ሲዳማ ቡና 60ሺና ኦሮሚያ ውሃ ሥራዎች 40ሺ ብር ተሸላሚ ሆነዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 7/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=37493
[ { "passage": " ፡- እኔም አመሰግናለሁ።\n– ትልልቅ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የተጀመረ እና ታዋቂ አትሌቶችም የተሳተፉበት ውድድር እንደመሆኑ በጥሩ ጎኑ እመለከተዋለሁ። ከአትሌቶች ብዛት አኳያም የተሻለ ነገር መኖሩን ታዝቤያለሁ። የሜዳ ተግባራትን ጨምሮ በተለያዩ ውድድሮች ላይ በፊት ጥቂት አትሌቶች ብቻ ተሳታፊ የነበሩባቸው ውድድሮች አሁን በበርካቶች ተፎካካሪነት ተካሂዷል። ይህ እንደ ቀላል ሊታይ ይችል ይሆናል፤ ለእኔ ግን አጃኢብ ነው፤ ምክንያቱም 10ሺ ሜትርን አራትና አምስት አትሌቶች ብቻ ሲሮጡ አስታውሳለሁ። አሁን ግን 50 እና 60 አትሌት ሮጦ የተሻለ ሰዓት ማስመዝገብ መቻል ትልቅ ነገር ነው። አሰልጣኝ የሆንኩት ባልተለመደ መልኩ፤ በ25ዓመቴ ነው። በኢት ዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያው ወጣት አሰልጣኝም ነኝ። ላለፉት 27ዓመታት በነበረኝ የአሰልጣኝነት ቆይታም፤ ዛሬ ለሀገራቸው በኦሊምፒክ፣ ዓለም ሻምፒዮና፣ መላ አፍሪካ ጨዋታዎችና በሌሎች ውድድሮች በ70 ሀገራት ተካፋይ ሆኛለሁ። ረዳት በመሆን በጀመርኩት ስልጠናም ከበርካታ ውጤታማ አትሌቶች ጋር ሰርቻለሁ። ዛሬ አመራር፣ አሰልጣኝ እና ሌሎች ሥራዎች ላይ ያሉ አትሌቶችን የማሰልጠን ዕድሉ ገጥሞኛል። ከቀድሞዎቹ እነ ብርሃኔ አደሬ፣ ጌጤ ዋሚ፣ ደራርቱ ቱሉ፣ ፋጡማ ሮባ፣ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ ዱቤ ጂሎ፣…ን መጥቀስ ይቻላል። መሃል ላይ ካሉት ጀግኖችም፤ ጥሩነሽ ዲባባ፣ ስለሺ ስህን፣ መሠረት ደፋር፣ ቀነኒሳ በቀለ፣ እጅጋየሁ ዲባባ፣ ገንዘቤ ዲባባን አሰልጥኛለሁ። ከአዳዲሶቹ አትሌቶች ደግሞ ሰለሞን ባረጋ፣ አንዱአምላክ በልሁ፣ ደራ ዲዳ፣ ሰምበሬ ተፈሪ፣ …ን በማሰልጠን ላይ እገኛለሁ። በርካታ\nልዩነት አለ፤ በዚያን ጊዜ እንደ ባህል ተይዞ ይሰራ የነበረው የብሔራዊ ቡድን አትሌቶችን በማዕከል ይዞ ማሰልጠን ነው። አሁን ግን ስልጠናው በተበታተነ መልኩ፤ በክለብ፣ በግል እና በማናጀር ነው የሚሰጠው። በዚህ ወቅት አትሌቶች ካላቸው ብዛት አኳያ በተቀናጀ መልኩ ቢሰራ ውጤታማ መሆን ይቻል ነበር። ካጠቃላይ\nዝግጅት እስከ ውድድር መባቻ ድረስ አንድ አትሌት ከአሰልጣኝ ጋር ሊለማመድ ካልቻለ በመካከ ላቸው መግባባት ሊኖር አይችልም። አሁን እንደሚደረገው በሳምንታት አሊያም በአንድና ሁለት ወራት ቆይታም የአንድነት ስሜቱን ማምጣት አይቻልም። እንደ ድሮ በብሔራዊ ቡድን ይሰባሰቡ ለማለትም አዳጋች ነው። ድሮ አዲስ አበባ ውስጥ የነበሩት\nክለቦች ከስድስት አይበልጡም። አሁን የእነዚህ ክለቦች በተለይ በረጅም ርቀት ላይ ያላቸው ብቃት ወርዷል፤ በአንጻሩ ያሉት ደግሞ መቀመጫቸው በክልሎች ነው። ታዲያ እነዚህን አትሌቶች በብሔራዊ ቡድን አሰባስቦ ወደ ማዕከል እንዴት ማምጣት ይቻላል? ምክንያቱም የቤት ኪራይን ጨምሮ ሌሎች በርካታ ወጪዎችን ይጠይቃል። ስለዚህም አትሌቶቹ ባሉበት ቦታ ነው ድጋፍና ክትትል ማድረግ የሚያስፈልገው። ውድድሮች ሲቃረቡም ወደ ማዕከል በማምጣት ማዘጋጀቱ የተሻለ ነው። ወጥ ያልሆነ\nስልጠና የሚሰጥ ከሆነ ውጤቱ መዋዠቁ አይቀርም። የስልጠና ፕሪንሲፕሎችን ተከትለን መስራት ካልቻልን ውጤታማ መሆን አንችልም፤ ከአጠቃላይ ዝግጅት ጀምሮ እስከ ውድድር ወቅት ያለው ስልጠና ሳይንሳዊና ወጥ መሆን አለበት። ካልሆነ ግን ዛሬ ውጤታማ የነበረውን አትሌት ነገ በዚያ አቋሙ ልናገኘው አንችልም። እነ ኃይሌ በአንድ ሥርዓት በማለፋቸው ለ20ዓመታት መሮጥ ችለዋል። አሁን ግን አንድ አትሌት ከአንድ እና ሁለት ኦሊምፒክና ዓለም ሻምፒዮና በላይ አይታይም። አሁንም ወጥነት ያለው ስልጠና ከሌለ ብቅ ጥልቅ ማለቱ የሚቀጥል ነው የሚሆነው። ክለባችን\nከባርሴሎና እስከ ሪዮ በኦሊምፒክ ወርቅ በማምጣት አንደኛ ደረጃ ላይ ነው የሚገኘው። ቀድመውት ከተመሰረቱት ክለቦችም የተሻለ ታሪክ አለው፤ አሁን ግን ያንን እያሳየ አይደለም። ከዚህ ቀደም ከሠራዊቱ በሚገኘው መዋጮ የተሰራ ሆቴል ነበር፤ ነገር ግን ባልታወቀ መንገድ በጳውሎስ ሆስፒታል ተወስዶብን አትሌቶቻችንን የምንደጉምበት አጥተን ሞራላችን በከፍተኛ ደረጃ ተነክቷል። ይህንኑ ለመንግሥት አቤት ብንልም እልባት አላገኘንም፤ በዚህም የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ክለብ ቀጣይነት በጥያቄ ምልክት ውስጥ ይገኛል። በዚህ ወቅት ምንም ዓይነት የገቢ ምንጭ የለንም፤ ከሠራዊቱ የወር ደመወዝ የሚገኝ አንድ ብር ላይ ተመስርተን ነው ያለነው። በመንግሥት በኩልም እገዛ ሊደረግለት የሚችልበት መንገድ አለ፤ እኛም እንደ ክለብ ተቆርቋሪነታችን እልባት የሚገኝበትን መንገድ መፈለግ የግድ ነው። የፌዴራል ማረሚያ ቤት ክለብ ወደቀ ማለት ደግሞ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ግማሽ ክፍል ወደቀ እንደማለት ነው። የኢፌዴሪ\nስፖርት ኮሚሽን፣ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ፣ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እንዲሁም ሌሎች የስፖርት ማህበራትን (ቦክስ፣ እጅ ኳስ፣ ቮሊቦል) ይመለከታል። ነገር ግን አሁን ምንም እየተደረገልን አይደለም፤ እነ ደራርቱ ቱሉን፣ ፋጡማ ሮባን፣ ስለሺ ስህንን፣ ጥሩነሽ ዲባባን፣ ሰንበሬን ተፈሪን፣ ዱቤ ጂሎን፣ ቁጥሬ ዱለቻን፣ ገለቴ ቡርቃን፣ ንጉሴ ጌቻሞን፣ … ያፈራ ክለብ ዛሬ ሊቆም ነው። እነ አበበ ቢቂላን፣\nማሞ ወልዴ፣ ምሩጽ ይፍጠር፣ አዲስ አበበ፣ ቲኪ ገላና፣ ጸጋዬ ከበደ፣ ኢማና መርጋ፣ ሙክታር እድሪስ፣…ን ያፈራው መከላከያ አሁን ብዙም እየታየ አይደለም። እነ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በላይነህ ዴንሳሞ፣ ፊጣ ባዪሳ፣ ወርቁ ቢቂላ፣ ብርሃኔ አደሬ፣ ጌጤ ዋሚ፣ ከበደ ባልቻ፣ ሂርፓሳ ለሚ፣…ን ያፈራው ኦሜድላም ደብዛው ጠፍቷል። እንደ አንድ ባለሙያ በጣም ይቆጨኛል፤ መንግሥትም ለምን ዝም እንዳለ አልገባኝም። አሁን ስፖርትና\nስፖርተኛ የተገናኘበት ወቅት ነው። ፌዴሬሽኑ በባለሙያዎች ተደራጅቷል፤ ጠንክረው የሚሰሩ ከሆነም ትልቅ አጋጣሚ ነው የሚሆንላቸው። ፕሬዚዳንቷን ኮሎኔል ደራርቱ ቱሉን ጨምሮ እነ ገብረእግዚአብሔር ገብረማርያም፣ ዶ/ር በዛብህ ወልዴ፣ አቶ አድማሱ ሳጂ፣ ስለሺ ስህን እና መሠረት ደፋር በሥራ አስፈጻሚው ውስጥ መኖር ጥሩ አጋጣሚ ነው። ይህንንም መጠቀም ይገባል፤ በማንም ማሳበብ የማንችልበት ወቅት ላይ ነን። ደራርቱ በዴንማርኩ ውድድር ወቅት የአመራርና የማቀናጀት ሥራዋ አስደናቂ ነበር። ሁላችንም ተባብረን የምንሰራ ከሆነም የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ትንሳኤ አሁን ነው። ለአትሌቶች\nበርካታ የውድድር ዕድል እንዲያገኙ የሚያመቻችላቸው መሆኑን በበጎ ጎኑ እመለከተዋለሁ። ከ25 ዓመታት በፊት የነበረውን ብናስታውስ ደግሞ ቤትና መኪና ያላቸው አትሌቶች ሁለት ብቻ ነበሩ፤ አሁን ተቆጥረው አያልቁም። ከራሳቸውና ከቤተሰቦቻቸው አልፈው ተቋማ ትን በመክፈትም ለሌሎች ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ላይ ነው የሚገኙት። ይህንን ያመጣው ደግሞ ከአትሌቶችና አሰልጣኞች ጥረት ባሻገር የማናጀሮች ዕድሉን ማመቻቸት ነው። ይሁን እንጂ የሀገር ፍቅር እና የአንድነት ስሜት ቀንሷል። የአሁኖቹ አትሌቶች ሀገራቸውን አይወዱም ማለት ሳይሆን በተግባር የሚታይ ነገር ተቀዛቅዟል። በፊት እነ ኃይሌ፣\nቀነኒሳና ጥሩነሽ ካሉ ወርቅ አለ በሚል ነበር የሚጠበቀው። አሁን ግን እንደዛ ዓይን ውስጥ ሊገባ የሚችል አትሌት ስለመኖሩ የማንተማመንበት ደረጃ ላይ በመድረሳችን ይህንን መጠበቅ ይከብዳል። ቀድሞ የዓለም ክብረወሰኖች እና ፈጣን ሰዓቶች ይመዘገቡ የነበሩት በኢትዮጵያውያን በመሆኑ መተማመን ይቻል ነበር። አሁን ማረጋገጫ የለም፤ ውድድሮችም የሉም። አትሌቶችም ቢሆኑ 5ሺ እና 10ሺ ሜትርን ሳይሮጡ ወደ ማራቶን ይገባሉ፤ በያዙት ርቀትም ብዙ አይቆዩም። ለዓለም ሻምፒዮና የቀረን አራት ወር ብቻ ነው፤ አትሌቶች አሁኑኑ ካምፕ ገብተው ካልተዘጋጁ ተዓምር ካልተፈጠረ ድረስ ለመገመት አስቸጋሪ ነው። የአሰልጣኞችን\nመብት ከማስከበር ባሻገር በስልጠና፣ በውድድር እንዲሁም በምልመላ ላይ እገዛ እናደርጋለን። አሰልጣኞች በዘመናዊ ትምህርትም ራሳቸውን እንዲያበቁ ከክልሉ ፌዴሬሽን ጋር በመሆን አጫጭር ኮርሶች እንዲሰጥ እያደረግን ነው። በኢትዮጵያ ታሪክ ከአትሌቲክስ የሚወዳደር ስፖርት የለም። መላው የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት አትሌቲክሳችንን በእንክብካቤ መያዝ ይገባናል። ውድድር ሲደርስና ውጤት ሲጠፋ ብቻ መጮህ የለብንም። አትሌቶች የት ነው ያሉት፣ ክለቦችና አሰልጣኞችስ ምን እየሰሩ ነው በማለት ክትትል ማድረግ ተገቢ ነው። በመጨረሻም ለዓለም ሻምፒዮናው እና ቶኪዮ ኦሊምፒክ ጥሩ ዕድል እንዲገጥመን ከወዲሁ እመኛለሁ።አዲስ ዘመን ግንቦት 5/2011 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "a9bc37ab4354accd4c487ddad0e07096" }, { "passage": " ብስራቱን ለመንገር የመጀመሪያውን ማራቶን ከአቴንስ እስከ ስፓርታ የሮጠው ወታደሩ ፊዲፒደስ ከ30 ሰዓታት በላይ ፈጅቶበታል። ከዘመናት በኋላ ደግሞ 42 ኪሎ ሜትሩ በሁለት ሰዓት ውስጥ የሚጠናቀቅ ሆኗል፡፡ ነገር ግን በቅርቡ ከዚህም በታች በሆነ ሰዓት መግባት እንደሚቻል ኬንያዊው አትሌት አረጋግጧል። ይህንን ሃሳብ በመያዝ ሲንቀሳቀስ የቆየው ናይኪ የተባለው የስፖርት ትጥቅ አምራችም በጫማዎቹ አማካኝነት ርቀቱ እስካሁን በሰው ልጅ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅበት ሁኔታ ከሁለት ሰዓት በታች መግባት እንደሚቻል አሳይቷል። ነገር ግን የማራቶን ሰዓት እዚህ ከመድረሱ ናይኪም በዘመን አመጣሽ ጫማዎቹ ሳይራቀቅ በፊት ፊዲፒደስ ርቀቱን በምን ሸፈነው በማለት የታሪክ ማህደርን ማገላበጥ አስፈላጊ ይሆናል። ሩጫ መለያዋ የሆነው ኢትዮጵያም የተከበረውን የኦሊምፒክ መንደር አሃዱ ያለችው በምን መልኩ ነው ለሚለውም ታሪክን መለስ ብሎ ማስታወስ በቂ ነው። ባለሙያዎች «ተፈጥሮአዊ ሩጫ» ሲሉ የሚጠሩትና በተለምዶ በባዶ እግር መሮጥ ለማራቶን ስፖርት መሰረት ነው ለማለት ይቻላል። በዘመነው ዓለም የማይታሰበው የባዶ እግር ሩጫ በአፍሪካ እና በደቡባዊው አሜሪካ ግን እስካሁንም በስፋት ይስተዋላል። በኢትዮጵያም ይህ አሯሯጥ የተለመደ ቢሆንም ምርጫ በማጣት (ከድህነት ጋር በተያያዘ ምክንያት) አሊያም በአስገዳጅ ሁኔታ የሚከወን ስለመሆኑ ዋቢ መጥቀስ አያሻም። በአንጻሩ ከሃብት ማማ ላይ በሚገኙት ምዕራባዊያን ዘንድ ይህ ዓይነቱ ሩጫ ጥቅሙን በመረዳት ይዘወተራል። ከጊዜ ወደ ጊዜም እየታወቀና እየተስፋፋ የመጣ የአሯሯጥ ዓይነት ሆኗል። በተለይ በሃይቅና ውቅያኖስ ዳርቻዎች እንዲሁም በሳር በተሸፈኑ መስኮች ላይ ባዶ እግርን መሮጥ እያደገ ያለ ተግባር ነው። በዚህ የሩጫ ዓይነት ስሙ ጎልቶ የሚነሳው ኢትዮጵያዊው ታላቅ አትሌት አበበ ቢቂላ ቢሆንም ከእርሱ አስቀድመውም ሆነ በዚያው ዘመን በርካቶች ባዶ እግራቸውን በውድድሮች ላይ ይካፈሉ ነበር። ከታዋቂዎቹ መካከልም ደቡብ አፍሪካዊቷ የሁለት ጊዜ የሃገር አቋራጭ ሻምፒዮና ዞላ ቡድ፣ አውስትራሊያዊው የ1ሺ500 ሜትር እና 800 ሜትር አትሌት ኸርብ ኤሎት እንዲሁም እንግሊዛዊው የ3 ማይል ሻምፒዮን ብሩች ቱሎህ ጥቂቶቹ ናቸው። ጀግናውን አትሌት ከሌሎቹ ልዩ የሚያደርገውም በባዶ እግር ቀርቶ በጫማም የማይደፈረውንና እህል ውሃ የማያሰኘውን ማራቶንን በመሮጡ ነው። እርግጥ ነው ከረጅም ዓመታት በኋላም ሌላ ኢትዮጵያዊ አትሌት በዚህ መልክ 42 ኪሎ ሜትሮችን በማቋረጥ ዓለምን አጀብ ማሰኘት ችሏል። ከሰው ልጅ ስልጣኔ እና የአኗኗር ሁኔታ ጋር በተያያዘ የሰው ልጅ ሩጫን በባዶ እግሩ አሊያም ከድብ እና ከሌሎች እንስሳት ቆዳ በሚሰራ ጫማ ሲከውነው እንደነበረ ጥንታዊያን ታሪኮች ያስረዳሉ። ግሪካዊያንም በጥንታዊው ኦሊምፒክ ጭምር በሩጫ ብቻም ሳይሆን በተለያዩ ስፖርቶች የሚካፈሉ ተወዳዳሪዎች ባዶ እግራቸውን ነበር የሚቀርቡት። እንደሌላው ዘርፍ ሁሉ የስፖርት ቁሳቁሶችም ከዘመን ጋር እየዘመኑና በረቀቁ ቴክኖሎጂዎች ታግዘው እየተካሄዱ ይገኛሉ። ለዚህም በቅርቡ ኬንያዊው አትሌት ኢሉድ ኪፕቾጌ በ1ሰዓት ከ59 ደቂቃ ከ40ሰከንድ በሆነ ሰዓት ማራቶንን የሮጠበትን ጫማ ማንሳት ይቻላል። ናይኪ ቫፖርፍላይ የተባለው ይህ የመሮጫ ጫማ ከተፈጥሮአዊው አቅም ባሻገር አትሌቶችን ወደፊት በማፈናጠር ተጨማሪ ፍጥነት የሚሰጥ ነው። በርካቶች ግን 250 ዶላር ዋጋ የተተመነለት ናይኪ ቫፖርፍላይን በህግ ከሚያስቀጣው የአበረታች ቅመሞች ተጠቃሚነት ለይተው አያዩትም። ይህ ከዘመናዊው ዓለም ጋር ከመራመድ እና ከተፈጥሯዊው ልማድ ጋር የመቀጠል እሳቤም የአትሌቲክስ ቤተሰቡን ከሁለት የከፈለ አድርጎታል። በተፈጥሯዊ መንገድ በባዶ እግር መሮጥ ግን ላለንበት ወቅት የማይመጥን ተግባር ተደርጎ ይወሰድ እንጂ የጤና ባለሙያዎች እንዲተገበር የሚመክሩት የአሯሯጥ ዓይነት ነው። ሳይንስም በባዶ እግር መሮጥን ከጉዳት ማገገምን ጨምሮ በርካታ ጥቅሞችን እንደሚያስገኝ ያረጋግጣል። ነገር ግን ተግብሮት ለማያውቅ ሰው በመጀመሪያ ፈታኝ እንደሚሆን እና የሚሮጡበትን ስፍራ ደህንነትም አስቀድሞ ማረጋገጥ እንደሚገባም ያሳስባል። የመጫሚያዎች ምቾት ከሳምባ፣ ከአእምሮ፣ ከደም ዝውውር እንዲሁም ከነርቭ ጋር ይያያዛል። በመሆኑም ከባድ፣ ጠባብ፣ ከተረከዛቸው ከፍ ያሉ፣… ጫማዎች ያደረገውን ሰው ምቾት ከመንሳት ባሻገር ጤናም ላይ ተያያዥ እክሎችን ማድረሱ አይቀርም። በመሆኑም አልፎ አልፎም ቢሆን ባዶ እግርን መጓዝ እና መሮጥን መለማመድ ጠቃሚ ይሆናል። የደም ዝውውርን ለማስተካከል ተመራጭ መንገድ ሲሆን፤ በተለይ ለልብ ህመም እንዲሁም በደም ውስጥ የሚኖሩ መርዘኛ ንጥረ ነገሮችን ለማስወገድ እንደሚረዳ ተመራማሪዎች በሳይንስ ጆርናሎች ያሳተሟቸው ጽሁፎች ያስነብባሉ። በሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ዳንኤል ሊበርማን እንደሚገልጹት ከሆነ፤ (cushioned\nshoes) በመባል የሚታወቁትን የስፖርት ጫማዎች የሚያዘወትሩ አትሌቶች ተረከዛቸው በመዶሻ የመቀጥቀጥን ያህል ጉዳት ይደርስባቸዋል። በመሆኑም አሰልጣኞች አንዳንዴም አትሌቶቻቸውን ባዶ እግራቸውን በሳር ላይ እንዲሮጡ ቢያደርጉ፤ የእግራቸውን ጤንነት ከመንከባከብም በላይ ከደረሰባቸውም ጉዳት እንዲያገግሙ እንደሚረዳቸው ያስረዳሉ። በጫማ መሮጥ በባዶ እግር ከመሮጥ ይልቅ የኦክስጅን ፍጆታን በሁለት እጅ ይጨምራል፤ ይህም አትሌቱ (ሯጩ ግለሰብ) ከሚያወጣው ጉልበት የሚያያዝ በመሆኑ በሚሸፍነው ርቀት ላይ የራሱን ተጽእኖ ማሳረፉ አይቀርም። በእግር ጤንነት፣ ሚዛን፣ ነርቮችን በማነቃቃት፣ የእግር ቅርጽ እና እድገት ላይም በጫማ እና ያለጫማ እንቅስቃሴ ማድረግ ሚናው ይለያያል። በተለይ ደግሞ በሽንጥ፣ ባት፣ ተረከዝ፣ ቁርጭምጭሚት፣ ጅማት፣ አጥንት እና ጡንቻዎች ጤና ላይ የራሱን አሻራ ያሳርፋል። ከዚህ ባሻገር ሰው ከተፈጥሮ ጋር ያለውን ቁርኝትም በማስፋትና ተፈጥሮን በመንከባከብ ረገድ የራሱን ስነ-ልቦናዊ በረከት ያስገኛል።አዲስ ዘመን ጥቅምት24/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "721145480b76984363e8a73c5bcf2259" }, { "passage": "ቦጋለ አበበ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት የዓለም ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ገፅታ ዝብርቅርቁ በወጣበት የፈረንጆች 2020 ዓመት የዓለም ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችም ቀላል የማይባል አሉታዊ ተፅዕኖ አርፎባቸዋል። ኦሊምፒክን ጨምሮ ታላላቅ ዓለም አቀፋዊና የአገር ውስጥ ስፖርታዊ ውድድሮች በተሰረዙበትና በተራዘሙበት የውድድር ዓመት የአትሌቲክስ ስፖርት በርካታ ፈተናዎችን ማሳለፉ ይታወቃል። በዓለም ሕዝብ ዘንድ ጥሩ ትውስታን ጥሎ ያላለፈው\n2020 ተሸኝቶ ዛሬ በ2021 የውድድር ዓመት አንድ ብሎ የሚጀምርበት ቀን ነው። በአብዛኛው መጥፎ ትዝታውን ጥሎ ባለፈው ዓመት የአትሌቲክሱ ዓለም በርካታ አሉታዊ ተጽእኖዎች አርፈውበታል፤ በርካታ አዎንታዊ ክስተቶችንም አስተናግዷል። ከእነዚህ መካከልም አበይት ክስተት የሆኑት እንደሚከተለው ተዳሰዋል። ጥር የ2020 የውድድር ዓመት በጀመረበት ታህሳስ መጨረሻና ጥር ወር ላይ የአትሌቲክሱ ዓለም በርካታ የዓለም ክብረወሰኖችን አስተናግዷል።\nኬንያዊው አትሌት ሮኔክስ ኪፕሩቶ የአስር ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የዓለም ክብረወሰንን\nቫሌንሲያ ላይ 26፡24 በሆነ ሰዓት ያስመዘገበው በዚህ ወር ሲሆን፣ ሌላኛዋ ኬንያዊት\nሼላ ቺፕኪሩይ በተመሳሳይ\nውድድር የሴቶቹን የዓለም ከገጽ 46 የዞረክብረወሰን 29፡46 በሆነ ሰዓት በማሻሻል የውድድር ዓመቱን በስኬት ጀምራለች። በዚሁ ወር የማራቶን ቁጥር አንድና ቁጥር ሁለት የሆኑት ኢትዮጵያዊና ኬንያዊ አትሌቶች ቀነኒሳ በቀለና ኢሉድ ኪፕቾጌ በለንደን ማራቶን እንደሚፋለሙ ይፋ መደረጉም የውድድር ዓመቱ ትልቅ ክስተት ነበር። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በየዓመቱ የሚደምቁበት የዱባይ ማራቶን በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፈው ኦሊካ አዱኛ አሸናፊ ሲሆን፣ በሴቶች ወርቅነሽ ደገፋ የኢትዮጵያውያንን የተለመደ ድል ማስቀጠል ችላለች። በቻይና ናጂንግ ባለፈው መጋቢት ወር ሊካሄድ ቀጠሮ የተያዘለት የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ቻምፒዮና መራዘሙ የተሰማው በዚሁ ወር ነበር፤ ይህ ወድድር በኮቪድ-19 ስጋት የተራዘመ የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ ውድድርም ሆኗል። የካቲት ያለፈው የካቲት ወርም በዓለም አትሌቲከስ የተለያዩ የዓለም ክብረወሰኖች የተሻሻሉበት ሆኖ ይታወሳል። በተለይም ስዊድናዊው ምርኩዝ ዘላይ ሞንዶ ዱፕሌንቲስ 2014 ላይ በፈረንሳዊው ሪናውድ ላቪሌኒ ተይዞ የቆየውን የዓለም ክብረሰወን 6 ነጥብ 17 ሜትር በመዝለል በአንድ ሴንቲሜትር ያሻሻለበት አጋጣሚ ትልቁ ክስተት ነበር። ላቪሌኒ በተመሳሳይ ወር ግላስጎ ላይ 6 ነጥብ 18 ሜትር በመዝለልም ተጨማሪ የዓለም ክብረወሰን በአንድ ወር ውስጥ ያሻሻለበት አጋጣሚ የሚዘነጋ አይደለም። የውድድር ዓመቱን በበርካታ የዓለም ክብረወሰኖች ታጅቦ ያጠናቀቀው ዩጋንዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቺፕቴጌ የዓመቱን የስኬት ጉዞ ሞናኮ ላይ የአምስት ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የዓለም ክብረወሰንን 12፡51 በሆነ ሰዓት በማሻሻል የጀመረው በዚሁ የካቲት ወር ነበር። ኢትዮጵያዊቷ አትሌት አባብል የሻነህ የግማሽ ማራቶን የዓለም ክብረወሰንን በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ራስ አል ካይማህ 64፡31 በሆነ ሰዓት ያሻሻለችበትም አጋጣሚ በጉልህ የሚጠቀስ ነው። ቬንዙዌላዊቷ ስሉስ ዘላይ ዩሊማር ሮጃስ በማድሪድ በተካሄደው የቤት ውስጥ ውድድር ለአስራ ስድስት ዓመታት በታትያና ሌቢዴቫ ተይዞ የቆየውን የዓለም ክብረወሰን 15 ነጥብ 43 ሜትር በመዝለል ያሻሻለችበት አጋጣሚም ይታወሳል። መጋቢት የውድድር ዓመቱ ሦስተኛ ወር በሆነው መጋቢት ሕዝብ ባልተሳተፈበት የቶኪዮ ማራቶን ብርሃኑ ለገሰ ባለድል የሆነበት አጋጣሚ ሳይጠቀስ አይታለፍም። ቀነኒሳ በቀለም በለንደን ግማሽ ማራቶን አስደናቂ ብቃት አሳይቶያሸነፈበት ውድድርም አይዘነጋም። በዚህ ወር የኮቪድ-19 ስርጭት እየተስፋፋ መሄዱን ተከትሎ የዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮናም የመራዘም ዕድል ገጥሞታል። በተመሳሳይ ታላላቅ የሚባሉት የለንደንና የቦስተን ማራቶን ውድድሮችም በዚሁ የካቲት ወር እንደተራዘሙ ታውቋል። እንዲካሄድ በርካታ ጥረቶች ሲደረጉ ከቆዩ በኋላ የውድድር ዓመቱ ታላቅ የስፖርት መድረክ ቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ የተራዘመውም በዚሁ ወር ነበር። ሚያዝያ-ግንቦትበአሜሪካ ኦሪገን በሰኔ ወር ሊካሄድ የነበረው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ቻምፒዮና በ2022 እንዲካሄድ ውሳኔ ላይ የተደረሰው በሚያዝያ ወር ነበር። የሚያዝያ ወር ምናልባትም በአትሌቲክሱ ዓለም ውድድሮችና ክብረወሰኖች የተመዘገቡበት ሳይሆን በርካታ ተጠባቂ ውድድሮች የተራዘሙበትና የተሰረዙበት መጥፎ ትዝታ ጥሎ ያለፈ ነው ማለት ይቻላል። ከቤት ውስጥ ቻምፒዮናው በተጨማሪ በፓሪስ ሊካሄድ የነበረው የአውሮፓ አትሌቲክስ ቻምፒዮና በዚህ ወቅት ለመሰረዝ በቅቷል። ጥቁር አሜሪካዊው ጂዮርጅ ፍሎይድ ሜይዌዘር በፖሊስ በአሰቃቂ ሁኔታ መገደሉን ተከትሎ የዓለም አትሌቲክስ ‹‹የጥቁር ሕይወት ዋጋ አለው›› በሚል በዓለም አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን እንቅስቃሴ የተቀላቀለበት ወቅት ነው። የዓለም አትሌቲክስ አዲስ የኦሊምፒክ ተሳትፎ ማረጋገጫ ሂደትን ይፋ ያደረገውም በዚህ ወቅት ነበር። የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስፖርቱን እያዳከመው በመምጣቱም የዓለም አትሌቲክስ ስፖርቱን ለመደገፍ አዲስ ስትራቴጅክ ፕላን ይፋ አድርጓል። ተጠባቂው የኒውዮርክ ማራቶንም መሰረዙ የተሰማው በዚሁ ወቅት ነው። ሰኔ-ሐምሌ ውድድሮች ለወራት በዓለም ላይ አለመካሄዳቸውን ተከትሎ የስፖርቱ ዓለም በዘርፉ ፖለቲካ ተጠምዶ የቆየበት ጊዜ ነበር። በዚህም ከውድድርና ውጤቶች ይልቅ የተለያዩ ጉዳዮች የስፖርቱ ቤተሰብ መነጋገሪያ ሆነው ሰንብተዋል። በሰኔ ወር ትልቅ መነጋገሪያ ከሆኑ የአትሌቲክስ ጉዳዮች የቀድሞው የማራቶን ባለክብረወሰን ኬንያዊው ዊልሰን ኪፕሳንግ አበረታች ንጥረነገር ተጠቅሞ በመገኘቱ ለአራት ዓመታት ከስፖርቱ መታገዱ ትልቅ ትኩረት ስቦ ነበር። ተቋርጠው የቆዩ የዳይመንድ ሊግ ውድድሮች በወሩ መጨረሻ እየተመለሱ መምጣታቸው ግን በወረርሽኙ ሳቢያ ድብርት ውስጥ ለነበረው የስፖርቱ ቤተሰብ ተስፋ ሆነው ነበር። በዚህም በዙሪክ የተካሄደው የዳይመንድ ሊግ ውድድር ተጠቃሽ ነው። ያም ሆኖ እንደ ቺካጎ ያሉ ታላላቅ የማራቶን ውድድሮች በዚህ ወር ከመሰረዝ አልዳኑም። ወሩ ከመጠናቀቁ አስቀድሞም የዓለም አትሌቲክስ በመሮጫ ጫማዎች ላይ አዲስ ሕግ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። ውድድሮች ከወራት በኋላ በሂደት መመለሳቸውን ተከትሎ ለረጅም ዓመታት ያልተደፈሩ የዓለም ክብረወሰኖች ጭምር ሐምሌ ወር ላይ ተሰብረዋል። በተለይም ዩጋንዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቺፕቴጌ ሞናኮ ላይ በቀነኒሳ በቀለ ለአስራ አምስት ዓመታት ተይዞ የቆየውን የዓለም ክብረወሰን በ12፡35፡36 ማሻሻሉ ያልተጠበቀ የዓመቱ አበይት ክስተት ነበር። ነሐሴ ሐምሌ ወር ላይ የታየው ትልልቅ የዓለም ክብረወሰን የማሻሻል ሂደት በነሐሴም ተደግሟል። በተለይም በኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ኃይሌ ገብረስላሴና ድሬ ቱኔ ለረጅም ዓመታት ተይዘው የቆዩት የአንድ ሰዓት ውድድር የዓለም ክብረወሰኖች መሰበራቸው ያልተጠበቀ ነበር። ትውልደ ሶማሊያዊው የእንግሊዝ አትሌት ሞ ፋራህ የወንዶቹን ክብረወሰን ሲያሻሽል ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ የኔዘርላንድስ አትሌት ሲፈን ሃሰን የሴቶቹን ክብረወሰን መጨበጥ ችላለች። ኬንያዊቷ አትሌት ፒርስ ጂፕቺርቺር በፓራጓይ ግማሽ ማራቶን የርቀቱን የሴቶች ብቻ የዓለም ክብረወሰን ያሻሻለችበት አጋጣሚም አይዘነጋም። የቀድሞው የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ፕሬዚዳንት ሴኔጋላዊው ላሚን ዲያክ በሙስና ቅሌት በፓሪስ ለዓመታት በቁም እስር ቆይተው ፍርድ የተበየነባቸውም በዚሁ ወር ነው። የውድድር ዓመቱን በክብረወሰኖች ታጅቦ ያሳለፈው ስዊድናዊው ምርኩዝ ዘላይ ሞንዶ ዱፕሌንቲስ ከቤት ውጪ ባሉ ውድድሮች በዩክሬናዊው ታሪካዊ አትሌት ሰርጌ ቡካ ተይዞ የቆየውን የዓለም ክብረወሰን በ6 ነጥብ 15 ሜትር ያሻሻለበት አጋጣሚም ትልቅ ነው። የዓለም የማራቶን ክብረወሰን ባለቤት የሆነችው ኬንያዊት አትሌት ብሪጊድ ኮስጌ የለንደን ማራቶንን ለሁለተኛ ጊዜ አሸንፋለች። በዚህ ውድድር ለወራት ሊፋለሙ ቀጠሮ ይዘው ትልቅ ትኩረት የተሰጣቸው ቀነኒሳ በቀለና ኢሉድ ኪፕቾጌ ፍልሚያ አንድ ቀን ሲቀረው ቀነኒሳ በጉዳት ከውድድር ውጪ መሆኑ አሳዛኝ ነበር። ያም ሆኖ የርቀቱ የክብረወሰን ባለቤትና ባለፉት ዓመታት ሽንፈት ያልገጠመው ኪፕቾጌ ባልተጠበቀው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሹራ ቂጣታ ከመሸነፉ ባሻገር ሰባተኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ አስገራሚ ነበር።ዩጋዳዊው ቺፕቴግ ቀነኒሳ ለአስራ ስድስት ዓመታት ይዞት የቆየውን የአስር ሺ ሜትር የዓለም ክብረወሰን ቫሌንሲያ ላይ ሲያሻሽል ኢትዮጵያዊቷ ለተሰንበት ግደይ በጥሩነሽ ዲባባ ለአስራ ሁለት ዓመታት የተያዘውን የአምስት ሺ ሜትር የዓለም ክብረወሰን ማሻሻሏ የውድድር ዓመቱ ግንባር ቀደም አበይት ክስተት ሆኖ አልፏል። ኬንያዊቷ ፒርስ ጂፕቺርቺር በፖላንድ ጊዲኒያ የዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮና የርቀቱን የሴቶች ብቻ የዓለም ክብረወሰን መስበሯም ወሩን አስደናቂ አድርጎት አልፏል። መስከረም -ታህሳስ የ2023 የአውሮፓ አትሌቲከስ ቻምፒዮናን ቱርክ ኢስታንቡል ላይ እንድታዘጋጅ ዕድል ባገኘችበት መስከረም ወር በአየርላንድ ደብሊን ሊካሄድ የነበረው የ2020 የአውሮፓ አገር አቋራጭ ቻምፒዮና ከመሰረዙ በቀር በአትሌቲክሱ ዓለም ብዙም አነጋጋሪ ጉዳዮች ሳይፈጠሩ አልፈዋል። ከዚያ በኋላ ባሉት ሦስት ወራት ግን የዓለማችን ፈጣኑ አትሌት ጃማይካዊው ዩዜን ቦልት እንዲሁም የረጅም ርቀት ንግስቷ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ በእውቁ የእንግሊዝ የአትሌቲክስ መፅሔት የምን ጊዜም ምርጥ አትሌት ተብለው መሰየማቸው አብይ ጉዳይ ነበር። ቬንዙዌላዊቷ አትሌት ዩሊማር ሮጃስ እንዲሁም ስዊድናዊው ሞንዶ ዱፕሌንቲስ የዓመቱ ምርጥ አትሌቶች ተብለው ተሸልመዋል። ኬንያዊው ኪቢዎት ካንዲም በዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮና ሲያሸንፍአዲስ\nዘመን ታህሳስ 23/2013", "passage_id": "fa5997abb25501d92753abc953d0c38c" }, { "passage": " የዓለማችን ኮከብ አትሌቶች በዚህ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ (ኮቪድ 19) በተስፋፋበት ወቅት በምን ሁኔታ ቀናቸውን እያሳለፉ እንደሚገኙ የስፖርቱን ዓለም ሰዎችና ሌላውን ማህበረሰብ ከማስተማር አኳያ በተለያዩ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ሰፊ ሽፋን እያገኘ መሆኑ ይስተዋላል፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን የአትሌቲክስ የጀርባ አጥንት የሆኑትና አትሌቶችን ላሉበት ደረጃ ትልቅ ሚና የሚጫወቱት አሰልጣኞች ሥራቸውን በምን መልኩ እያከናወኑ እንደሚገኙ ከሥራቸውና ከቫይረሱ ባህሪ አኳያ ብዙዎች ጥያቄ ሲያነሱ ይስተዋላል፡፡ የዓለም አትሌቲክስም በድረ ገጹ በተለያዩ ዓለማት ቻምፒዮኖችን ያፈሩ አሰልጣኞች በዚህ ወቅት ሥራቸውን በምን መልኩ እየከወኑ እንደሚገኙ የተለያዩ ቅኝቶችን በማቅረብ ሌሎች እንዲማሩበት ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡ \nበዓለም አትሌቲክስ ተሞክሯቸውን እንዲያጋሩ ከተመረጡት አሰልጣኞች መካከል አንዱ ደግሞ የዓለም ሁለተኛው የማራቶን ፈጣን ሰዓት ባለቤቱ ቀነኒሳ በቀለ አሰልጣኝ መርሻ አስራት ናቸው፡፡ አትሌቱ በሦስት ኦሊምፒኮች ተሳትፎው ወርቃማ ታሪክ እንዲጽፍ ከጀርባ በመሆን ከፍተኛውን ድርሻ የተጫወቱት አሰልጣኝ፣ በዚህ የውድድር ዓመት ኮከቡ አትሌት በለንደን ማራቶን የርቀቱን ክብረወሰን እንዲሁም በጃፓኗ ቶኪዮ ለማካሄድ በታሰበው ኦሊምፒክ በማራቶን አራተኛውን ድል ለማስመዝገብ ትልቅ ዝግጅት አድርገው ነበር፡፡ \nየኦሊምፒኩንና የተጠባቂውን ለንደን ማራቶን መራዘም ተከትሎም ቀነኒሳ ከምንጊዜም ተቀናቃኙና የወቅቱ የማራቶን የዓለም ባለ ክብረወሰን ከሆነው ኬንያዊው ኢሉድ ኪፕቾጌ ጋር በተንቀሳሳሽ ምስል የታገዘ ውይይት ማድረጋቸውን ኤንኤን ትሬኒንግ የተባለው ድረገጽ አስመልክቷል፡፡ በዚህም አትሌቶቹ ከቤተሰቦቻቸው ጋር በቤታቸው በመሆን የግል እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አሰልጣኞች ዓለም ውጥረት ውስጥ በገባበት በዚህ ወቅት ሥራቸውን በምን መልኩ ይከውናሉ፣ ቀናቸውንስ እንዴት ያሳልፉታል፣ አትሌቶች ከልምምድ እንዳይርቁና ብቃታቸውን ጠብቀው እንዲቆዩ የአሰልጣኞቹ ሚና በምን መልኩ አትሌቶች ጋር እየደረሰ ይገኛል? ለሚለው የአምስትና አስር ሺ ሜትርን ክብረወሰን ለረጅም ዓመት ሳያስደፍር ይዞ የቆየው አትሌት ቀነኒሳ አሰልጣኝ ተሞክሯቸውን ያጋራሉ፡፡ \nአሰልጣኝ መርሻ የመጀመሪያው ቁም ነገር ዓለም የገጠማትን ይህንን ወጀብ በምን መልኩ ማለፍ ይቻላል? የሚለውን ማሰብ ቀዳሚ እንደሆነ እምነታቸው ነው፡፡ ወረርሽኙ በውድድሮች ላይ እንዲሁም በቡድን በሚሰጡ\n ስልጠናዎች ላይ የራሱን አሉታዊ አስተዋፅዖ እንዳሳደረ ይናገራሉ፡፡ ነገር ግን ጊዜውን በጥንካሬ ማሳለፍ የግድ ነው ይላሉ፡፡ ሰልጣኞቻቸውም በዚህ መልክ መቆየት እንዳለባቸው ይጠቁማሉ፡፡ በንግግራቸውም ‹‹ሁሉም አትሌቶቼ ጠንካራና በባህሪያቸውም ለሌሎች ምሳሌ መሆን ይገባቸዋል፤ እንደ አሰልጣኝ የምነግራቸውም ይህ ጊዜ ያልፋል ብዬ ነው›› ብለዋል፡፡ \nምንም እንኳን በዚህ ወቅት ሁሉም ውድድሮች ከተያዘላቸው መርሐ ግብር ሽግሽግ እንዲደረግባቸውና ሌሎቹም የተሰረዙ ቢሆንም አትሌቶች ልምምዳቸውን ማቆም እንደማይገባቸው አሰልጣኝ መርሻ ይመክራሉ፡፡ አትሌቶች የሚሠሩት እንቅስቃሴም ለጥንካሬ እና አቅምን ለማዳበር የሚረዱ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ ይህንንም ሲያብራሩ ‹‹ለተወሰኑ ጊዜያት ውድድሮች ስለሌሉ ጠንክሮ መሥራት ተገቢ የሆነበት ወቅት ነው፡፡ በመሆኑም በእኔ ስር ለሚሰለጥኑ ሁሉም አትሌቶቼ መሥራት የሚገባቸውን እየጠቆምኳቸው ነው፡፡ ወቅቱ ጥንካሬን የሚያዳብሩበት ነው፤ በደንብ እንዲሠሩም ዕድል ይሰጣቸዋል›› ብለዋል፡፡\n ከዓለም አትሌቲክስ ጋር ቆይታ ያደረጉት ሌሎች አሰልጣኞችም በተመሳሳይ ለአትሌቶቻቸው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ የማራቶንና ግማሽ ማራቶን የዓለም ክብረወሰን ባለቤቶቹ ኬንያዊን ኢሉድ ኪፕቾጌ እና ጆፈሪ ካምዎረር አሰልጣኝ ፓትሪክ ሳንግም ተሞክሯቸውን አጋርተዋል፡፡ በርካታ አትሌቶች በቡድን የሚያሰለጥኑት አትሌቱ ቡድናቸውን የበተኑት ከወር በፊትም ነበር፡፡ በተለያዩ የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ታግዘው አትሌቶቻቸውን ቢያገኙም ለውጣቸውን የመመልከት ዕድል አለማግኘታቸው ፈተና እንደሆነባቸው ጠቁመዋል፡፡ \nብራዚላዊው አሰልጣኝ ሞራ ኮት አትሌቶች ቀድሞ በነበራቸው መነቃቃት ማቆየት አዳጋች መሆኑን ይገልጻሉ፡፡ አሰልጣኞችና አትሌቶች መልካም መግባባት ያላቸው ከሆነም በሚያወጧቸው እቅድ መሰረት ባሉበት ሆነው በእንቅስቃሴ ላይ መቆየት ይችላሉ፡፡ ቢሆንም ይህ ጊዜ ሲያልፍ ምን ሊከሰት እንደሚችል ለመገመት አዳጋች መሆኑን አልሸሸጉም፡፡ ‹‹አዲስ ልምድ እንደምናገኝና ይህ\n ሁኔታ ለበጎ እንደሚሆንም ተስፋ አለኝ›› ይላሉ፡፡ \nየኒውዝላንድን አትሌቶች ሲያዘጋጁ የቆዩት አሰልጣኝ ዳሌ ስቴቨንሰን በበኩላቸው አትሌቶቻቸውን በስነልቦና እያገዙ እንደሚገኙና በቅርቡ ወደነበሩበት እንደሚመለሱ እየነገሯቸው መሆንኑን ገልጸዋል፡፡ ወቅቱ ወደኋላ የሚመለሱበት ሳይሆን በጥሩ ሞራል እንደ ሙሉ ጊዜ አትሌት ጊዜያቸውን መጠቀም እንዳለባቸውም ምክረሃሳብ ሰጥተዋል፡፡ አሰልጣኞችም አትሌቶቻቸው በምን መልኩ እንቅስቃሴ ማድረግ እንዳለባቸው ማሳየት ተገቢ ነው የሚሉት አሰልጣኙ፤ በአንዳንድ አትሌቶቻቸው መደነቃቸውንም ይናገራሉ፡፡ አትሌቶች በአካባቢያቸው በሚያገኟቸው ቁሳቁስ ስልጠናቸውን እያደረጉ እንደሚገኙና በዚህም እንዲቀጥሉ አሳስበዋል:: ሌላኛው አሰልጣኝ ብራም ሶም አትሌቶች ከሁኔታዎች ጋር ራሳቸውን በማስማማት በዝግጅት ላይ መቆየት እንዳለባቸውም ጠቁመዋል፡፡ ከአትሌቶች ጋር ፊት ለፊት በመተያየት ብቃታቸውን መገምገም ባይቻልም አዲስ ተሞክሮ እንዳስገኘላቸውም አክለዋል፡፡\nአዲስ ዘመን ሚያዝያ 28/2012ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "d72f0cca261bbd4f4d28a62fa25e7ecb" }, { "passage": "የኢትዮጵያ\nአትሌቲክስ ፌዴሬሽን በበላይነት ከሚመራቸው መርሐ ግብሮች መካከል በየዓመቱ የሚከናወነው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተጠቃሽ ነው፡፡ አንጋፋውና ያለምንም መቆራረጥ በየዓመቱ ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዘንድሮ ለ48ኛ ጊዜ እየተካሄደ ይገኛል። ክለቦችና\nክልሎች ከፍተኛ ፉክክር እንደሚያሳዩበት የሚጠበቀው ሻምፒዮናው በኦሊምፒክ ባህል መሰረት የውድድሩ የመክፈቻ ዝግጅት ትናንት አመሻሽ ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በይፋ ተጀምሯል። በዕለቱ በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ አንጋ ታዋቂና ስመ ጥር አትሌቶች፤ እንዲሁም የአትሌቲክሱ ባለድርሻ አካላት፤ የተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ታድመዋል። በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚካሄደው ሻምፒዮና በተሳካ ሁኔታ ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ ዝግጅት መደረጉም ተገልጿል። ለውድድር\nየሚሆኑ ቁሳቁሶችና ግብዓቶች ከማሟላታቸውም በላይ ውድድሩን የሚመሩ አደረጃጀቶችም ተፈጥረዋል። ለዚህም ከሁለት ነጥብ አንድ ሚሊዮን ብር በላይ በጀት በመመደብ ዓመታዊ ውድድሩን ከምንጊዜውም በተሻለ ሁኔታ ስኬታማ ለማድረግ ጥረት ማድረጉን ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ አስታውቋል። በፌዴሬሽኑ አዘጋጅነት የሚካሄደው ሻምፒዮናው ለአትሌቶች የሃገር ውስጥ የውድድር ዕድሎችን ከመፍጠሩ ባሻገር በክልሎች፤ በከተማ አስተዳደሮችና በክለቦች መካከል ፉክክር መፍጠርን፤ እንዲሁም ለብሄራዊ ቡድን የሚሆኑ አትሌቶችን የመምረጥ ዓላማ አንግቧል። በዓለም\nአትሌቲክስ ሻምፒዮና ሃገርን የሚወክሉና ሚኒማ ያሟሉትን አትሌቶች የሚመለመሉበት ትልቅ መድረክ ነው። ሻምፒዮናው በተጓዘባቸው ዓመታት ከያዘው ዓላማ አኳያ ስኬታማ እንደነበርና በኢትዮጵያ የአትሌቲክስ የስኬት ጉዞ ውስጥ ትልቅ ስም ያለው መሆኑ በመክፈቻው ዕለት ተነግሯል። ባለፉት ዓመታት ከዚህ ሻምፒዮና ውድድር በርካታ ብርቅዬ አትሌቶች ተገኝተዋል። ይሁን እንጂ፤ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ መቀዛቀዝ እየተስተዋለበት ነው። በተለይ በውጭ ሃገራት ውድድሮች ላይ ተሳታፊ የሆኑ ታዋቂ አትሌቶች በሃገር ውስጥ ውድድሮች አለመታየታቸው በብዙዎች ዘንድ ወቀሳ እንዲሰነዘርበት ያደርጋል። በመሆኑም\nበዚህ ዓመት በርካታ ታዋቂ አትሌቶች የተሳተፉ ሲሆን፤ አማን ወጤ፣ ጫላ በዮ፣ ዲኖ ስፍር፣ አንዷምላክ በልሁ፣ አባዲ ሃዲስ፣ የኔው አላምረው፣ ሰለሞን ባረጋ፣ አዲር ጉር፣… በወንዶች በኩል ተሳታፊ አትሌቶች ናቸው። በሴቶች በኩልም፤ ደራ ዲዳ፣ ነፃነት ጉደታ፣ በላይነሽ ጉደታ፣ ሱሌ ኡቱራ፣ ብርቱኳን ፈንቴ፣ ህይወት አያሌው፣ ፎቴን ተስፋይ፣ ሰንበሬ ተፈሪ፣ አራያት ዲቦ፣… ከተካፋዮቹ ጥቂቶቹ ይገኙበታል። ዘንድሮም እንደዚህ ቀደሙ ሃገራቸውን በዓለም አቀፍ ደረጃ ማስጠራት የሚችሉ አትሌቶች ተብሎ ይጠበቃል። ከውድድሩ\nአንጋፋነት አንጻር ብዙ የተነገረለት ሻምፒዮና ዘጠኝ ክልሎችና ሁለት ከተማ አስተዳደሮች፤ እንዲሁም 36 ክለቦችን ተሳታፊ አድርጓል። በዚህም በአጠቃላይ አንድ ሺህ 376 አትሌቶች ተሳታፊ ይሆናሉ። ከ47ኛው የኢትዮጵያ ሻምፒዮና የዘንድሮው በ122 ተሳታፊ አትሌቶች ብልጫ ያሳየም ሆኗል። ሻምፒዮናው ከዓመት ዓመት የፉክክር መንፈሱ እያየለ በመምጣቱ ዘንድሮም ጠንካራ አትሌቶችን በጥራትና በብዛት ለማግኘት የሚረዳ መሆኑ ተጠቁሟል። በአዲስ\nአበባ ስታዲየም በድምቀት እየተከናወነ የሚገኘውን በሻምፒዮናው የመጀመሪያ ቀን ውሎ የተለያዩ ውድድሮች የተካሄዱ ሲሆን፤ በእለቱ በተካሄዱት ውድድሮች በወንዶች የስሉስ ዝላይ ፍፃሜ ውድድር ፤አዲር ጉር ከመከላከያ 15 ነጥብ 88 ሜትር 1ኛ (ሪከርድ በመስበር) የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንኩ ቢኒኒ አንበሴ 15 ነጥብ 57 ሜትር በመዝለል 2ኛ በመሆን የብር ሜዳሊያ አጥልቋል። የሲዳማ ቡናው ጆሴፍ ኦባንግ 15 ነጥብ 35 ሜትር በመዝለል 3ኛ ደረጃን በመያዝ የነሃስ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል። ሌላው\nፍጻሜ ያገኘው ውድድር የሴቶች አሎሎ ውርወራ ሲሆን፤ በዚህም፣ 1ኛ ዙርጋ ኡስማን ከሲዳማ ቡና 13 ነጥብ 55 ሜትር (ሪከርድ በማስመዝገብ) ባለድል ሆናለች። ሌላዋ ተወዳዳሪ አመለ ይበልጣል ከመከላከያ 12 ነጥብ 63 ሜትር በመወርወር 2ኛ ስትሆን፤ ሰላማዊት ማሬ ከደቡብ ፖሊስ 12 ነጥብ 15 ሜትር በመወርወር 3ኛ በመሆን አጠናቅቃለች። ውድድሩ ዛሬን ጨምሮ ለቀጣዮቹ አምስት ቀናት በድምቀት እንደሚቀጥል ይጠበቃል። ውድድሩ\nዛሬን ጨምሮ ለቀጣዩቹ አምስት ቀናት በ80 የአትሌቲክስ ዳኞች፣በ45 የፌዴሬሽኑ አመራሮችና ባለሙያዎች፣ በ3 የህክምና ባለሙያዎችና አንድ አምቡላንስ ፣በ32 በጎፍቃድ አገልጋዮች እንዲሁም ሌሎች ሥራዎችን በሚያከናውኑ ሙያተኞች እየተመራበድምቀት እንደሚቀጥል ይጠበቃል። በ42ቱ ውድድሮች አሸናፊ ለሚሆኑ አትሌቶችም የ2,000.00 (ሁለት ሺህ)፣ 1,400.00 (አንድ ሺህ አራት መቶ) እና 1,000.00 (አንድ ሺህ) ብር ሽልማት እንደየደረጃቸው የሚያስገኝ ይሆናል። ክብረወሰን ለሚያሻሽሉ እና ከሦስት ወርቅ በላይ ለሚያስመዘግቡ አትሌቶችም 6,000.00 (ስድስት ሺህ) ብር ተጨማሪ ሽልማት የሚያገኙ ሲሆን፤ ሁለት ወርቅ ለሚያጠልቁ አትሌቶች ደግሞ 5,000.00 (አምስት ሺህ) ብር ይሰጣቸዋል። በአጠቃላይ\nበቡድን አሸናፊ ለሚሆኑት አትሌቶችም 20,000.00 (ሃያ ሺህ)፣ 16,000.00 እንዲሁም 10,000.00 ብር እንደሚበረከት ታውቋል። ዘንድሮ ለ48ኛ ጊዜ የሚካሄደው ውድድር በከፍተኛ ድምቀት በትናንትናው ዕለት የተጀመረ ሲሆን ለቀጣዮቹ ስድስት ቀናትም ይቆያል። በዓመት አንድ ጊዜ በሚካሄደው ይህ ውድድር በተመሳሳይ አምና ለ47ኛ ጊዜ ሲካሄድ ከፍተኛ ፋክክር የታየበት ነበር። በሻምፒዮናው በሴቶች አጠቃላይ አሸናፊዎች፣ 1ኛ. መከላከያ ስፖርት ክለብ በ158 ነጥብ ዋንጫ ተሸላሚ፣ 2ኛ. ኦሮሚያ ክልል በ148 ነጥብ፣ 3ኛ. ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ107 ነጥብ የደረጃ ሰንጠረዥ ውስጥ መካተት ችለዋል። በወንዶች\nአጠቃላይ አሸናፊዎች፣ 1ኛ. መከላከያ ስፖርት ክለብ በ180 ነጥብ ዋንጫ ተሸላሚ ሲሆን፣ 2ኛ. ኦሮሚያ ክልል በ177 ነጥብ፣ 3ኛ. ሲዳማ ቡና በ106 ነጥብ ባለድል ነበሩ። ከፍተኛ ፉክክር በታየበት ሻምፒዮና በሁለቱም ጾታ አጠቃላይ አሸናፊዎች መከላከያ ስፖርት ክለብ በ338 ነጥብ አንደኛ ሆኖ የዋንጫ ተሸላሚ ነበር። የኦሮሚያ\nክልል ደግሞ በ325 ነጥብ በሁለተኛ ደረጃ ሲያጠናቅቅ፤ ሲዳማ ቡና በ202 ነጥብ በሦስተኛ ደረጃ ነበር ያጠናቀቁት፡ ፡ ትናንት የተጀመረውና እስከ መጪው ግንቦት 04 ቀን 2011 ዓ.ም ለስድስት ተከታታይ ቀናት በሚካሄደው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና የአትሌቲክስ ስፖርት ወዳዱ ህብረተሰብ በአዲስ አበባ ስታዲየም ተገኝቶ ይደግፋል ተብሎ ይጠበቃል።አዲስ ዘመን ሚያዚያ 30/2011በዳንኤል\nዘነበ", "passage_id": "e29273145a5c9ccfcab2365cf0535e01" } ]
48c4f0258c9a44ac079b744402780a5c
0c246c95c710d21f1133b25ca0340f7b
ቡድኑ ዝግጅቱን አስቀድሞ መጀመሩ ለውጤታማነት ያግዘዋል
ብርሃን ፈይሳ የቶኪዮ 2021 ኦሊምፒክ ከመካሄዱ ወራትን አስቀድሞ ዝግጅት መጀመሩ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ የሚያደርግ መሆኑ ተገለጸ። በኦሊምፒክ መድረክ ሃገራቸውን ለወከሉ አትሌቶች የተካሄደው የምስጋና መርሃ ግብር፤ ለመጪው ኦሊምፒክ ተሳታፊዎች መነሳሳትን እንደሚፈጥርም ተጠቆመ፣ ከዚህ ቀደም ይደረግ ከነበረው በተለየ ሁኔታ ከወራት በፊት ካምፕ በመግባት የረጅም ጊዜ ዝግጅት ማድረግ በቶኪዮ ኦሊምፒክ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን የተሻለ ውጤት እንዲያመዘገብ ያስችላል ተብሏል። በ5ሺ ሜትር ሃገሩን ለመወከል በቡድኑ የተካተተው አትሌት ጫላ ከተማ፤ ብሄራዊ ቡድኑ ዝግጅቱን ከጀመረ አንድ ወር እንዳስቆጠረ ይገልጻል። ማረፊያውን በጥሩነሽ ዲባባ ሆቴል ያደረገው ቡድኑ በሰንዳፋ፣ አዲስ አበባ ስታዲየም እና በቃሊቲ ዝግጅት እያደረገ ሲሆን፤ በውድድሩ ወቅት በጃፓን የሚኖረው የአየር ሁኔታ ሞቃታማ ሊሆን ስለሚችል ከባድ ሊያደርገው ይችላል ከሚለው ግምት ባሻገር መልካም ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ያረጋግጣል።እንደ አትሌቱ ገለጻ፤ ከዚህ ቀደም ከወራት በፊት ካምፕ በመግባት ለረጅም ጊዜ ዝግጅት ተደርጎ አያውቅም። ኢትዮጵያ የምትታወቀው በቡድን ስራ ቢሆንም በዝግጅት ወቅት ተለያይቶ መስራት ውጤት እንዲጠፋ አድርጎት ቆይቷል። አሁን ግን ለረጅም ወራት አትሌቱ በአንድ ተሰባስቦ መስራቱ አትሌቶች እንዲግባቡና ለቡድን ስራም የሚያግዝ መሆኑን ያምናል። በአሰልጣኞችና በፌዴሬሽኑ ድጋፍና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑም የተሻለ ውጤት ይመጣል የሚል እምነቱንም አትሌቱ ያንጸባርቃል። ከዚህ ባሻገር ቡድኑ ኮቪድ 19ን በመከላከል ረገድም አስፈላጊውን ሂደት እየተከተሉ መሆኑን አትሌት ጫላ ይጠቅሳል። ያረፉበት ሆቴል ከአትሌቶች ውጪ ሌሎች ሰዎች የማይገለገሉበት ሲሆን፤ በልምምድና በሌሎች እንቅስቃሴዎች ውስጥም ንጽህናቸውንና ርቀታቸውን ከመጠበቅ ጎን ለጎን በጤና ባለሙያዎችም ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል ሲል ያብራራል። ‹‹የባዶ እግር ትሩፋቶች›› በሚል በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት በቅርቡ የተካሄደው የእውቅናና የሽልማት መርሃ ግብር፤ በቶኪዮ ኦሊምፒክ ተሳታፊ ለሚሆኑ አትሌቶች መነሳሳትን እንደሚፈጥርም በባለሙያዎች ታምኖበታል። በዓለም አቀፍ ደረጃ በተከሰተው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክንያት ኦሊምፒክ ለአንድ ዓመት መራዘሙ ይታወቃል። ይህንን ተከትሎም ለቶኪዮ 2021 ኦሊምፒክ አትሌቶችና አሰልጣኞች ከወዲሁ ዝግጅት መጀመራቸውን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ደራርቱ ቱሉ ጠቁማለች። ለብሄራዊ ቡድን የተመረጡት አትሌቶች ለሁለት ተከፍለው በአሰለፈች መርጋ እና በጥሩነሽ ዲባባ ሆቴል መቀመጫቸውን በማድረግ ዝግጅት እያደረጉ ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ ፌዴሬሽኑ ለቀደሙት የኦሊምፒክ ተሳታፊዎችና ባለድል አትሌቶች እንዲሁም ባለሙያዎች ማበረታቻ ማዘጋጀቱ፤ በቡድኑ ለታቀፉ አትሌቶች ሞራል እንደሚሆን ይጠበቃል። በምስጋና መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ለአትሌቶችና ቤተሰቦቻቸው ሽልማት ያበረከቱት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፤ ዘመኑ እንዳሁኑ ባልሰለጠነበትና መሰረተ ልማትም ባልተሟላበት ወቅት ኑሮ ከሩጫ ጋር የተያያዘ በመሆኑ አትሌቶች ስልጠናም ሳያስፈልጋቸው በኦሊምፒክ ሮጠው ማሸነፋቸውን ጠቅሰዋል። አሁን ግን ጊዜው እንደዚያ አለመሆኑን ጠቅሰው፣ አትሌቶች ለቶኪዮ ኦሊምፒክ በደንብ መዘጋጀት ይኖርባቸዋል ብለዋል። በኦሊምፒኩ የሚሳተፉ አትሌቶች ሆቴል ቢገቡም ጊዜው እጅግም ሩቅ ባለመሆኑ በደንብ መጠበቅ እንዳለባቸውም ነው ያሳሰቡት። መጪው ኦሊምፒክም በሽልማት መድረኩ ስማቸው የተነሳው አትሌቶች ገድል የሚታደስበት ሊሆን ይገባል ያሉት ፕሬዚዳንቷ፣ ለቶኪዮ በሁሉም መንገድ መዘጋጀት እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል። ኢትዮጵያንና አፍሪካን ከፍ ለማድረግና ቶኪዮ ላይ ያሸነፈውን የአበበ ቢቂላን ድል ለማደስ፤ የሚመለከታቸው ሁሉ አትሌቶችን በማዘጋጀትና በመደገፍ ጥረት ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አስታውቀዋል። በቶኪዮ 2021 በአሸናፊነት በተመሳሳይ መርሃ ግብር ለመገናኘት ፕሬዚዳንቷ ምኞታቸውን ገልጸዋል። የቶኪዮ ኦሊምፒክ መራዘም ለበጎ መሆኑን የሚያመላክቱት ደግሞ የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሰው ናቸው። የቶኪዮ 2021 ድል ከዚህ ቀደም ከነበረው እጥፍ ድርብ እንደሚሆን የጠቆሙት ሚኒስትሯ፤ ለአትሌቶች፣ አሰልጣኞች፣ አመራሮችና በስፖርቱ ላይ ለሚሰሩት ሁሉ የምስጋና መርሃ ግብሩ የብርታት ስንቅ እንደሚሆናቸው ነው የገለጹት። ከአንድ ዓመት በፊት በቶኪዮ በተካሄደ በሻምበል አበበ ቢቂላ ድል የ20 ኪሎ ሜትር የማስታወሻ ሩጫ ላይ የኢትዮጵያ ዝግጅት መልካም እንዳልነበር ለመታዘብ ተችሏል። በወቅቱ በጃፓን የተገኙ የፌዴሬሽኑ አመራሮች ልምድና አሰራር ተምረው መመለሳቸውን ተናግረው፣ በዚሁ መሰረት በመስራት የጀግና እና የይቻላል ስነልቦና የተላበሰ ህዝብ ያለባት ሃገር መሆኗ ዳግም እንደሚታይም ያላቸውን ተስፋ አንጸባርቀዋል።
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=37572
[ { "passage": "የወቅቱ የዓለማችን ራስ ምታት የሆነው የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ወረርሽኝ ምክንያት ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በግል እንዲከወኑ ሁኔታዎች አስገድደዋል። ወረርሽኙ በኢትዮጵያ መሰራጨት መጀመሩን ተከትሎም ውድድሮች፣ ስልጠናዎችና ሌሎች ስፖርት ነክ ክንዋኔዎች ተቋርጠዋል። ስፖርተኞችን የሚያሰለጥኑ ክለቦችና ማዕከላትም ስፖርተኞቻቸውን በትነዋል። ከእነዚህ መካከል አንዱ የሆነውና ታዳጊ ወጣቶችን የሚያሰለጥነው ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ሰልጣኞቹን ወደ የመጡበት ከመለሰ ወራትን አስቆጥሯል። በስመ ጥሯ አትሌት የተሰየመውና የኢትዮጵያን አትሌቲክስ ከነ ክብሩ እንዲቆይ ለማድረግ የሚጥረው ማዕከል፤ በሌሎች ስፖርቶችም ታዳጊዎችን ሲያሰለጥን ቆይቷል። በዚህ ወቅት ሰልጣኞቹ ወደየመጡበት ቢመለሱም ስልጠናውን ሳያቋርጥ ቀጥሏል። ይህ እንቅስቃሴውም ለሌሎች የማሰልጠኛ ማዕከላትና ክለቦች መልካም ተሞክሮ ሆኖ ይነሳል::ቅድመ ዝግጅት ወረርሽኙ ወደ ኢትዮጵያ መግባቱን ተከትሎ በመንግሥት መመሪያ ከተሰጠበት ጊዜ አንስቶ የማሰልጠኛ ማዕከሉ ቀዳሚ ሥራ ስልጠናውን በማቋረጥ ከ14-17 ለሚሆኑ ቀናት ሰልጣኞችን በየመኖሪያ ካምፓቸው እንዲቆዩ ማድረግ መሆኑን የማዕከሉ ዳይሬክተር ዶክተር አመንሲሳ ከበደ ይናገራሉ። የማዕከሉ ሰልጣኞች ባሉበት ሆነውም በእጅ ስልኮቻቸው በሚላክላቸው መልዕክት መሠረት በየግላቸው እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ቆይተዋል። ከዚህ ጎን ለጎን ስለ ወረርሽኙ ምንነት እንዲሁም በምን መልኩ ሊከላከሉ እንደሚችሉ በማዕከሉ የጤና ባለሙያዎች ለሰልጣኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጥቷል። በመንግሥት በኩል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲሁም የስፖርት ሰልጣኞች ወደየመጡበት እንዲመለሱ ውሳኔ ላይ መደረሱ ሲሰማም ተቋሙ ሰልጣኞችን ወደየቤታቸው ሊሸኝ ችሏል። ሰልጣኞች ወደየመጡበት እንዲመለሱም ማዕከሉ የራሱን አስር ተሽከርካሪዎች ያዘጋጀ ሲሆን፤ የጤና ባለሙያዎችን በመመደብ፣ የፊት መሸፈኛ ጭምብል፣ ጓንት እንዲሁም ሳኒታይዘር በማቅረብ ሙሉ ጥንቃቄ በማድረግ እንደነበር ዳይሬክተሩ ያስታውሳሉ። በጉዟቸውም ከሌሎች ሰዎች ጋር ሳይገናኙ ወደ ቤተሰቦቻቸው እንዲቀላቀሉ ጥረት ተደርጓል። ከዚህ ባሻገር ሰልጣኞች የትምህርት ማስረጃዎቻቸውን እንዲሁም የስልጠና ቁሳቁሶቻቸውን ይዘው በመሄድ ባሉበት ሆነው ከእንቅስቃሴ እንዳይርቁ የሚያደርግ ስልጠናም ወስደዋል። ወርሐዊው የኪስ ገንዘባቸውም በባንክ ቁጥራቸው በኩል እንዲደርሳቸው እየተደረገም ነው።ድጋፍና ክትትሉ በምን መልኩ ቀጠለ? ሰልጣኞች ወደየመጡበት ከተመለሱ በኋላም ስልጠናው መቆም ስለሌለበት ማዕከሉ በቴክኖሎጂ የታገዘ (ቨርቹዋል) ስልጠናን ቀዳሚ አማራጭ አድርጎ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። በተለያየ ደረጃ ያለው አፈፃፀም የተለያየ ቢሆንም በሁሉም የስልጠና ክፍሎች ስልጠናውን ማስቀጠል እንደተቻለም ዳይሬክተሩ ያስረዳሉ። ከአንድ ወር ቆይታ በኋላም ሰልጣኞች ያሉበትን ሁኔታ ለመገምገም የሚያስችል ቅኝት በሁሉም የአገሪቷ አቅጣጫዎች በባለሙያዎች እየተደረገ ይገኛል። ይህ ዘገባ በተዘጋጀበት ወቅትም ሶስተኛ ዙር ጉዞ የተደረገ ሲሆን፤ ወደ አርባ ምንጭ፣ ወላይታ ሶዶ እና ሃላባ እንዲሁም በባህርዳር መስመር የተጓዙ የአሰልጣኞች ቡድን መኖሩንም ዳይሬክተሩ ይጠቁማሉ። ማዕከሉ የሰልጣኞች ምልመላ የሚያደርገው በመላ አገሪቷ እንደመሆኑ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ውስጥ 280 ሰልጣኞች ይገኛሉ። በቅኝቱም 22 አሰልጣኞች፣ ስድስት የሚሆኑ የህክምና ባለሙያዎች እንዲሁም የህዝብ ግንኙነትና የትምህርት ክፍል ባለሙያዎች በቡድን እየተከፋፈሉ ወደየስፍራው ይዘው በመጓዝ ድጋፍ ሊደርጉላቸው ችለዋል። ከቁሳዊው ድጋፍ ባለፈ በቅኝቱ ወቅት የተለዩና መሰል ችግር ያሉባቸው 13 ሰልጣኞችን ከቤተሰቦቻቸው ድረስ በመሄድ ውይይት በማድረግ ችግራቸውን ለመፍታትም ተሞክሯል። ከሰልጣኞች ባለፈ በማዕከሉ የስልጠና፣ የህክምና፣ የአስተዳደር እንዲሁም ሌሎች በርካታ ሥራዎችን የሚያከናውኑ ባለሙያዎች ይገኛሉ። በመሆኑም ወረርሽኙን ሊስፋፉ የሚችሉ ምንያቶችን ለማስወገድ ጥረት ተደርጓል።የማዕከሉ የማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት ስፖርት ሁሉንም ማህበረሰብ የሚያሳትፍ እንደመሆኑ ከስፖርተኞችና ባለሙያዎቹ ባለፈ ማህበረሰቡንም ያቀፈ እንቅስቃሴ ላይ በስፋት ይሠራል። ማዕከሉም ከሰልጣኞቹና ከማዕከሉ ማህበረሰብ ባሻገር በአካባቢው ለሚገኙ ነዋሪዎች በእውቀት እንዲሁም በቁሳቁስ እገዛዎችን በማድረግ ላይ ይገኛል። የጥሩነሽ ዲባባ ትምህርትና ስልጠና ማዕከል በሚገኝበት አርሲ ዞን በሚገኙት ሁሉም ወረዳዎች በማዕከሉ የህክምና ባለሙያዎች የታገዘ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ በስፋት እየተሠራ እንደሚገኝ ዳይሬክተሩ ይናገራሉ። ግንዛቤ ማስጨበጫውም ወረርሽኙን ከመከላከል ባለፈ አካላዊ እንቅስቃሴ የማድረግ ጠቀሜታ፣ በሽታን የመከላከል አቅምን ለማጎልበት ስለሚያስችሉ የአመጋገብ ሥርዓት እንዲሁም የንጽህና አጠባበቅን አስመልክቶ ስልጠና ይሰጣል። ከትምህርት ሰጪው መርሃ ግብር ውጭ የማዕከሉ ሠራተኞች ከሚያገኙት ላይ በመቀነስ ግምቱ 287 ሺህ ብር የሚያወጣ ቁሳቁስ አቅመ ደካማ ለሆኑ ነዋሪዎች በማበርከት፣ ደም በመለገስ፣ ችግኞችን በመትከልና መሰል እገዛዎችን በማድረግ ላይም ይገኛል። ቀጣይ አቅጣጫ በዓለም ላይ የተሰራጨው ይህ ወረርሽኝ በቅርብ ጊዜ ይጠፋል የሚል ግምት እንደሌለ ይታወቃል። ነገር ግን ምልመላ፣ ምዘና እና ስልጠናው በቀድሞው፣ ሁኔታ ባይሆንም መቀጠሉ አይቀርም። በመሆኑም ወረርሽኙን ታሳቢ ባደረገ መልኩ ይህንን እንዴት ማከናወን ይቻላል የሚል ሰነድ በባለሙያዎች እየተዘጋጀ መሆኑን ዶክተር አመንሲሳ ይጠቁማሉ። አሰልጣኞች በዚህ ወቅት እያደረጉ ያሉት የሰልጣኞች ቅኝት ይህንንም ታሳቢ ያደረገና ግብዓት የሚገኝበትም ነው። ከወረርሽኙ ጋር በተያያዘም በቀጣይ አሁን ካለው በባሰ ሁኔታ የሚስፋፋ ከሆነ የተቋሙ ህክምና ባለሙያዎች ለማህበረሰቡ እገዛ ለማድረግ እንዲሁም ማዕከሉ ለማገገሚያነት እንዲውል ካስፈለገ ዝግጁ ሆኖ በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኝም ዳይሬክተሩ ያስረዳሉ። አዲስ ዘመን ሰኔ 8/2012ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "07b3ce4afce78621205c8033e6b869c0" }, { "passage": "ዋልያዎቹ ለአፍሪካ ዋንጫ አምስተኛ የምድብ ጨዋታ ቅድመ ዝግጅት ከወዲሁ ይጀምራሉ፡፡በ2021 አፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ አራት ጨዋታዎችን አድርጎ ስድስት ነጥቦች የሰበሰበው ብሔራዊ ቡድኑ ለቀጣዩ አምስተኛ የምድቡ ማጣሪያ መጋቢት ወር አጋማሽ ላይ ማዳጋስካርን በሜዳው የሚገጥም ሲሆን ለዚህም ጨዋታ ቅድመ ዝግጅት አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ለተጫዋቾች ጥሪ እንዳደረጉ ሰምተናል፡፡ ከሁለት ቀናት በኋላም ጥር 2 በጅማ ከተማ ዝግጅቱን እንደሚጀምር ታውቋል፡፡ አሰልጣኙ በኒጀሩ የማጣሪያ ጨዋታ ከጠሯቸው ተጫዋቾች በተጨማሪ አዳዲስ ዘጠኝ ተጫዋቾች በስብስቡ ማካተታቸውን ሰምተናል፡፡በጥር ወር የሚደረገው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ጅማ ላይ የሚከወን በመሆኑ ተጫዋቾቹ ባሉበት ጅማ ዝግጅት ለማድረግ እንደተመረጠ ሶከር ኢትዮጵያ ያገኘችው መረጃ ይጠቁማል። በጥር ወር መጨረሻ እና የካቲት መጀመርያ ባሉ የሊግ ጨዋታ በማይደረግባቸው ክፍት ቀናት ተጨማሪ ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚችልም ፍንጭ የሚሰጥ ነው፡፡", "passage_id": "7b0855d0116139c8066e1dc836164cf5" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በዚህ ዓመት የሚከናወነው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ቅድመ ዝግጅቱ ማጠናቀቁን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።የጉለሌ እፅዋት ማእከልም ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለተከላ ዝግጁ ማድረጉን ገልጿል።በ2011 ዓ.ም የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ”አረንጓዴ አሻራ ማሳረፍ” በሚል መሪ ሃሳብ በብሄራዊ ደረጃ ከ4 ቢሊዮን በላይ ችግኞች መተከላቸው የሚታወስ ነው።በዘንድሮው ዓመትም ይህንኑ በጎ ጅምር በማሳደግ 5 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተለያዩ ዝግጅቶች በመደረግ ላይ ናቸው።የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሳኒ ረዲ ÷ባለፈው ዓመት የነበረውን ተሞክሮ በመቀመር ዘንድሮ የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ እየተሰራ ነው ብለዋል።በአሁኑ ወቅት ችግኞቹ የሚተከሉባቸው ቦታዎች በዘመናዊ ዳታ ቤዝ እንዲገቡ እየተደረገ ሲሆን በየአካባቢው የሚተከሉባቸው የጊዜ ሰሌዳም  ተዘጋጅቷል  ነው ያሉት። ሚኒስትር ዴኤታው አያይዘውም በችግኝ ተከላ መርሃ ገብሩ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው የሚተከሉ ሲሆን ነባርና ሀገር በቀል  ችግኞትም እንደሚተከሉ ጠቁመዋል።እንደ አቶ ሳኒ ገለፃ ለችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ከችግኝ ማፍላት ጀምሮ ሌሎች አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅት ተጠናቀዋል።በተለይም እንደ ሀገር የአፈር ለምነትን የሚያሻሽሉ፣ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው፣ አግሮ ኢኮሎጅው ላይ ለውጥ የሚያመጡ ችግኞችን ለመትከል መታቀዱን ነው ያብራሩት።ለዚህ እቅድ ስኬትም ክልሎች አሁን ባለው የግንኙነት አማራጭ ተጠቅመው ሕብረተሰቡን የማዘጋጀት ስራ እያከናወኑ መሆኑን አስረድተዋል።በኢትዮጵያ ከ6 ሺህ 500 እስከ 7 ሺህ የሚደርሱ የእፅዋት ዝርያዎች ሲገኙ ከነዚህ መካከልም 10 በመቶው ብርቅዬዎች መሆናቸውን መረጃዎች ይጠቁማሉ።የጉለሌ እጽዋት ማእከል ምክትል ዳይሬክተር አቶ አበበ ተቀባ በበኩላቸው÷ በዘንድሮው ዓመት የሚተከሉ ችግኞች ሀገራዊ እንዲሆኑና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ እንዲኖራቸው ለማድረግ ማእከሉ አስቀድሞ ከተለያዩ አካላት ጋር እየሰራ ነው ብለዋል።ማእከሉ በፍጥነት ለተከላ የሚደርሱ 100 የእጽዋት ዝርያዎችን በማፍላት 550 ሺህ ችግኞችን ለተከላ ዝግጁ ማድረጉንም ገልጸዋል።“ችግኞችን መትከል ብቻ ለታለመለት አላማ አንዲውሉ አያደርግም” ያሉት አቶ አበበ አምና ከነበረው ልምድ በመነሳት ችግኞች ከተተከሉ በኋላ ተመልሶ ለመንከባከብ ያለው ተነሳሽነት ዝቅተኛ መሆኑን ጠቅሰዋል።በመሆኑም እንደ ሀገር የተዘጋጁት ችግኞች ለታለመለት አላማ እንዲውሉ ሁሉም የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግ ይገባዋል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል ።#FBCየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።", "passage_id": "76e172ff65c4fee65f23d97c4ef1945f" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለወትሮው ለትልልቅ ውድድሮች ቢያንስ አንድ ወር ዝግጀት የማድረግ ልማድ ቢኖረውም በ2014 መጀመርያ በሀገር ውስጥ ሊግ ውስጥ በሚጫወቱ ተጫዋቾች ብቻ በሚዋቀር ስብስብ ለሚደረገው ውድድር (ቻን) እስካሁን ዝግጅት አልጀመረም፡፡ውድድሩ ሊጀመር የ23 ቀናት እድሜ የቀሩት ቢሆንም ኢትዮጵያ እስካሁን ተጫዋቾቿን አላሳወቀችም (በምድባችን የምትገኘው ጋና ከወዲሁ 23 ተጫዋቿን አሳውቃለች)፡፡ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው በመጪው ሳምንት ሰኞ ዝግጅት ለመጀመር ጥያቄ ቢያቀርቡም የሊጉ ውድድር እንዳይቋረጥ በሚል በፌዴሬሽኑ ውድቅ ተደርጎባቸዋል፡፡ኢትዮጵያ በቻን ምድብ ሦስት ከኮንጎ ሪፐብሊክ (ብራዛቪል)፣ ሊቢያ እና ጋና ጋር መደልደሏ ይታወሳል፡፡", "passage_id": "6c5f8b58b6a6c92160461c73c4065dbf" }, { "passage": "ሰሜን\nአፍሪካዊቷ አገር ሞሮኮ በቅርቡ ለምታዘጋጀው መላ አፍሪካ ጨዋታዎች ለመሳተፍ ኢትዮጵያ በተለያዩ ብሔራዊ ስፖርት ፌዴሬሽኖቿ አማካኝነት ዝግጅት ከጀመረች ሰንብታለች በተለይም ዓመቱን ሙሉ በመርሐግብር መሰረት የሊግ ውድድሮችን የማያደርጉና የማጣሪያ ውድድር የማያስፈልጋቸው ብሔራዊ ፌዴሬሽኖች ባለፈው ወር የኢትዮጵያ ቻምፒዮናን በተናጠል በማካሄድ ወደ ሞሮኮ ይዘው የሚጓዟቸውን የብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች መርጠው በዝግጅት ላይ ናቸው በዓመታዊ መርሐግብር የተለያዩ ውድድሮችን የሚያካሂዱ ፌዴሬሽኖች የብሔራዊ ቡድን\nተጫዋቾችን ለመምረጥ ስለማይቸገሩ የውድድሮች ቀን ሲቃረብ ዝግጅት መጀመራቸው የተለመደ ነው ከእነዚህ ብሔራዊ ፌዴሬሽኖች መካከል የኢትዮጵያ ቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽን አንዱ ነው ፌዴሬሽኑ ለመላ አፍሪካ ጨዋታ ዝግጅቱን ለመጀመር የማጣሪያ ውድድር ማድረግ ይጠበቅበታል ለዚህም እቅድ አውጥቶ የሚያስፈልገውን በጀት እንዲፈቀድለት ለሚመለከታቸው የኢትዮ ጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴና የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን ያቀረበው ጥያቄ እስካሁን ምላሽ እንዳላገኘ የፌዴሬሽኑ የፅሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ይመር ሃይሌ ለአዲስ ዘመን አስታውቀዋል እንደ\nአቶ ይመር ገለፃ፣ የቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽን የመላ አፍሪካ ጨዋታን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴና ከፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን ጋር ስብሰባ ባደረገበት ወቅት ስፖርቱ በአገሪቱ ሰፊ እንቅስቃሴ እየተደረገበት የሚገኝ በመሆኑ ኢትዮጵያ በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች ከምትሳተፍባቸው ስፖርቶች አንዱ ሆኖ ተመርጧል በተመረጠበት ማግስትም የውድድሩ ቀን ባይደርስም የፌዴሬሽኑ የቴክኒክ ኮሚቴ አሰልጣኞችን መርጦ እንዲያሳውቅ በማድረግ ማስታወቂያ አውጥቶ አሰልጣኞች ተቀጥረዋል አሰልጣኞቹም ተጫዋቾች እንዲመርጡና እቅዳቸውን እንዲያቀርቡ ተደርጓል ፌዴሬሽኑ በዚህ ሂደት ውስጥ እያለ መላ አፍሪካ ጨዋታ ላይ ከመሳተፉ በፊት የአፍሪካ ዞን አምስት የቅርጫት ኳስ የማጣሪያ ውድድር መሳተፍ ስለሚኖርበት ከዞን አምስት በደብዳቤ ጥያቄ መጥቶለታል የዞን አምስት የማጣሪያ ውድድሩ ከአስር ቀናት በኋላ ተጀምሮ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ሲሆን በዚህ ውድድር ለመሳተፍ ፌዴሬሽኑ እቅዱን ከዞን አምስት ከመጣለት ደብዳቤ ጋር አያይዞ የሚያስፈልገውን ወጪ እንዲሸፍኑ የውድድሩ ባለቤቶች ለሆኑት የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴና የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን አቅርቧል ያም ሆኖ ከሚመለከታቸው አካላት እስካሁን ምንም አይነት ምላሽ እንዳላገኘና የተመረጡት አሰልጣኞችም ተጫዋቾች መልምለው ዝግጅት ለማድረግ እንዳልቻሉ አቶ ይመር ይናገራሉ የማጣሪያ ውድድሩ ሊጀመር ጥቂት ቀናት በቀሩበት በዚህ ወቅት የኦሊምፒክ ኮሚቴና የስፖርት ኮሚሽን አገርን ወክለው በማንኛውም ውድድር ላይ የሚሳተፉ ብሔራዊ ቡድኖችን ወጪ መሸፈን እንዳለባቸው አቶ ይመር ያብራራሉ ‹‹በፌዴሬሽኑ በኩል የምናደርገው ይሄ ነው፣አገራዊ ውድድሮች ላይ ስንሳተፍ ወጪውን መሸፈን ያለባቸው እነዚህ አካላት ናቸው፣ ተተኪ ወጣቶችን በስፖርቱ ለማግኘትም ሆነ አገር ለማስጠራት እንዲሁም ክለቦች የሚጠናከሩበትን መን ገድ ለመፍጠር እንደ መላ አፍሪካ አይነት ጨዋታዎች ላይ መሳተፍ አለብን፣ ካለበለዚያ ፌዴሬሽኑ መኖሩ ትርጉም የለውም›› ይላሉ ፌዴሬሽኑ ደብዳቤ አስገብቶ እስካሁን መልስ አላገኘም ማለት የሚያዘጋጃቸው ብሔራዊ ቡድኖች እንዳይወዳደሩ ማለት ነው ሲሉ ያስረዳሉ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር አቶ ታምራት በቀለ በበኩላቸው፤ ብሔራዊ ፌዴሬሽኖች አገርን ወክለው በዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ ለመወዳደር በቅድሚያ የማጣሪያ ውድድሮችን በራሳቸው ማድረግ እንዳለባቸው ይናገራሉ ማጣሪያውን ማለፍ ከቻሉ ግን ሙሉ ሃላፊነቱን ኦሎምፒክ ኮሚቴና ስፖርት ኮሚሽን ይረከባሉ እነዚህ ፌዴሬሽኖች የማጣሪያ ውድድሮችን በሚያደርጉበት ወቅት አቅም ካነሳቸው ድጋፍ የሚጠይቁበት ሁኔታ መኖሩን ያመለክታሉ ከቅርጫት ኳስ ጋር በተያያዘ መላ አፍሪካ ጨዋታዎች ላይ ሦስት በሦስት በሚባለው ውድድር ለመሳተፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እቅድ ውስጥ መካተቱትን ይጠቅሳሉ ቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽን የዞን አምስት ውድድርን በተመለከተ ያነሳው ነገር እንደሌለም ይጠቁማሉ ወደ ፊት ድጋፍ የሚጠይቁ ከሆነ ግን በኮሚቴው ሥራ አስፈፃሚ በኩል የሚታይ መሆኑን ያስገነዝባሉየፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን የኮሙ ኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ናስር ለገሰ እንደሚሉት፤ ብሔራዊ ፌዴሬሽኖች ለዓለም አቀፍ ውድድሮ በሚያደርጉት የማጣሪያ ጨዋታዎች ኦሎምፒክ ኮሚቴም ይሁን ስፖርት ኮሚሽን ወጪያቸውን ይሸፍናል ተብሎ የተቀመጠ ነገር የለም ፌዴሬሽኖች ከኮሚሽኑ የሚያገኙትን የድጎማ በጀት አብቃቅተው የሚጠቀሙበት ሁኔታ አለ እጥረት ሲገጥማቸው ግን ተጨማሪ ድጋፍ ይጠይቃሉ ጥያቄው አሳማኝና ውጤት ይመዘገብበታል ተብሎ ሲታመንም ተጨማሪ ድጎማ ይደረጋል ፌዴሬሽኖች ስፖርቱን እንዲመሩ እስከ ተቋቋሙ ድረስ በጀቱንም መምራት ይኖርባቸዋል አገርን ወክለው ሲወዳደሩ ሃላፊነቱን መውሰድ አለባቸው በሌላ በኩል ግን እግር ኳስ፣ አትሌቲክስና ሌሎችም አገርን ወክለው ሲወዳደሩ በራሳቸው በጀት ነው የሚንቀሳቀሱት ‹‹ስፖርት ኮሚሽን ሃያ ዘጠኙም ፌዴሬሽኖች ውጪ ሄደው የማጣሪያ ውድድር ሲያደርጉ ወጪ የቻልንበት አጋጣሚ የለም›› ያሉት አቶ ናስር፣ ማጣሪያውን ማለፋቸው ሲረጋገጥ ግን ከዝግጅት ጀምሮ ሙሉ ድጋፍ እንደሚ ደረግላቸው ይገልፃሉ የማጣሪያ ውድድር የማያስፈልጋቸው ነገር ግን ውጤት ይመጣባቸዋል ተብሎ የታመነባቸው እንደ አትሌቲክስ፣ ቦክስና ወርልድ ቴኳንዶ አይነት ስፖርቶች ለመላ አፍሪካ ጨዋታዎች ሆቴል ገብተው ዝግጅት እያደረጉ ይገኛሉ ኦሊምፒክ ኮሚቴና ስፖርት ኮሚሽን የማጣሪያ ውድድር ማድረግ የሚጠበቅባቸው የኳስ ስፖርቶች ማጣሪያውን ማለፋቸውን ካረጋገጡ በኋላ ወደ ሆቴል ገብተው ዝግጅት ያደርጋሉ የሚል እምነት አላቸው በጉዳዩ ላይ አንድ ወጥ የሆነ መተዳደሪያ ደንብ ባለመኖሩ ሦስቱ አካላት ማለትም ፌዴሬሽኑ፣ ኮሚቴውና ኮሚሽኑ የጋራ ስምምነት ላይ በቅርብ ቀን መድረስ ይችላሉ ማለት ከባድ ነው እነዚህ አካላት በቅርብ ቀን ተግባብተው መስራት ቢችሉ እንኳን በቅርጫት ኳስ የማጣሪያውን ጨዋታ ለማድረግ ከቀረው ቀን አንፃር የማይቻል ነው ቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽን ከኦሊምፒክ ኮሚቴና ስፖርት ኮሚሽን የበጀት ድጋፉን በቅርብ ቀን አግኝቶ፣ አሰልጣኞች በቀሪው አስር ቀን ውስጥ ተጫዋች መልምለውና ተዘጋጅተው በማጣሪያ ውድድሩ ምን አይነት ውጤት ሊያስመዘግቡ ይችላሉ? የሚለው የስፖርት ቤተሰቡ ጥያቄ ነው የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት\nዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ\nየኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ\nፕሬዚዳንት በመሆናቸው ጉዳዩን\nበቅርበት ያውቁት እንደሆነ\nበስልክ ለማነጋገር ብንሞክርም\nሊሳካልን አለመቻሉን መግለፅ\nእንወዳለንአዲስ ዘመን ቅዳሜ ሰኔ 8/2011", "passage_id": "38b1b6c715f12794fec8e2adb8be35e8" } ]
4f79f726b82aa9da10eea271f49f0917
24380bfbae78676c35a802682579d0f8
ኦሊምፒክ ኮሚቴ ባለድርሻ አካላትን አመሰገነ
ቦጋለ አበበ ባለፈው ህዳር 27/2013 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ሁለት አህጉራዊ ስኬቶችን በስፖርቱ ዘርፍ አስመዝግቧል። በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማህበር (አኖካ) ጠቅላላ ጉባዔን ማስተናገድ የመጀመሪያው ስኬት ነው። ከጉባዔው ጎን ለጎን ለመሪዎች የሚበረከተውን የአኖካ የስፖርት የክብር ኒሻን ሽልማት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በማሸነፋቸው የሽልማት ሥነሥርዓቱን ማስተናገድ ሌላው ስኬት ነው። ሁለቱን ታላላቅ የስፖርት ኩነቶች ኢትዮጵያ በአንድ ቀን በስኬት እንድታስተናግድ ከኦሊምፒክ ኮሚቴው ጋር በቅርበት በመስራት የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ትልቅ አስተዋፅኦ አበርክተዋል። ለዚህም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ‹‹ከስኬቴ ጀርባ ነበሩ›› ያላቸውን ባለድርሻ አካላት ከትናት በስቲያ ምሽት ያመሰገነበትን መርሃግብር አዘጋጅቷል። በብዙ የተመሰገኑት የስፖርት መገናኛ ብዙሃንን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ግለሰቦች በምስጋና መርሃግብሩ ተገኝተው የምስክር ወረቀት ተቀብለዋል። ለአኖካ ጠቅላላ ጉባዔና ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሽልማት ሥነሥርዓት ከተለያዩ አገራት የመጡ ከሁለት መቶ ሃምሳ በላይ እንግዶችን ለመቀበል በነበረው ሂደት ውስጥ ጉልህ ድርሻ የነበረው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ትልቅ ምስጋና የተቸረው ሲሆን፣ ቃል አቀባዩ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የምስክር ወረቀቱን ተቀብለዋል። ‹‹የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የአኖካ ሽልማት የተወሰኑ አገራትና መሪዎች ያገኙት እንደመሆኑ ትልቅ ስኬት ነው›› ያሉት አምባሳደር ዲና ለዚህ ስኬት እውን መሆን የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ትልቅ ስራ በመስራታቸው ሊመሰገኑ እንደሚገባ ገልጸዋል። የአኖካ ጠቅላላ ጉባዔ ካለ እንከን እንዲጠናቀቅም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጽሕፈት ቤት ሰራተኞች የተወጡት ትልቅ ሃላፊነት አድናቆት እንደሚገባው ተናግረዋል። ሁለቱ ስፖርታዊ ኩነቶች የአገር ገፅታ የተገነባባቸውና ትልቅ ዋጋ የሚገባቸው መሆኑንም አምባሳደሩ አስረድተዋል። ጉባዔውና የሽልማት ሥነሥርዓቱ የተሳካ እንዲሆን ከተዋቀሩት የመስተንግዶ ኮሚቴዎች መካከል አንዱ የሆነው የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጌታቸው ድንቁ በበኩላቸው፣ በወቅቱ ኢትዮጵያ በትግራይ ክልል የሕግ ማስከበር ዘመቻ ላይ እንደነበረች በማስታወስ ስፖርታዊ ኩነቶቹን በስኬት ለማስተናገድ ‹‹ከውጭ ሆኖ የሚመለከተው ብቻ ሳይሆን እኛም ጥርጣሬ ነበረን›› ብለዋል። ሆኖም ሁሉም ባድርሻ አካላት የቤት ስራቸውን በስኬት ተወጥተዋል። ይህም ጥሩ ልምድ፣ ትብብርና መልካም የስራ መንፈስ የታየበት እንደነበር አብራርተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ    የስፖርት ትልቅ ሽልማት በቀጣይ የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ዝግጅት ትልቅ መነሳሳትን እንደሚፈጥርም አክለዋል። የስፖርት መገናኛ ብዙሃን ከመነሻው አንስቶ ለጉዳዩ ሰፊ ሽፋን በመስጠት ያበረከቱት ትልቅ አስተዋጽኦም ብሮድካስት ባለስልጣንን እንዳስደሰተ ተናግረዋል። ‹‹በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን እንደዚህ ኮርቼ አላውቅም›› በማለት ምስጋናቸውን የጀመሩት የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር፣ በወቅቱ ከፖለቲካና ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት ጋር ተያይዞ ከነበረው አስቸጋሪ ሁኔታ አንፃር የአገር ገጽታ እንዲገነባና ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የሚገባቸውን ሽልማት እንዲያገኙ የስፖርት መገናኛ ብዙሃን ላበረከቱት ትልቅ አስተዋፅኦ ምስጋና እንደሚገባቸው ተናግረዋል። አገር አቀፍ የስፖርት ፌዴሬሽኖችና ማህበራት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን እንዲሁም የተለያዩ ግለሰቦችን በትልቁ ያመሰገኑት ዶክተር አሸብር፣ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ደመቀ መኮንን ስፖርታዊ ኩነቶቹ በስኬት እንዲጠናቀቁ የአንበሳውን ድርሻ የሚወስዱ በመሆናቸው ልዩ ምስጋና አቅርበዋል። የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን በተቋም ደረጃም ኮሚሽነሩ ኤልያስ ሽኩርና የተቋሙ ባለሙያዎች ከስኬቱ ጀርባ ለነበራቸው ትልቅ ሚና ተመስግነዋል። በርካታ አገራትና መሪዎች የገፉትን የአፍሪካ ፓራሊምፒክ ቻምፒዮና ኢትዮጵያ ለማዘጋጀት ፍቃደኝነቷን በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አማካኝነት ማረጋገጧን የጠቀሱት ዶክተር አሸብር፣ በተመሳሳይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ይሁንታ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ከኦሊምፒክ ስምንት ወራት አስቀድሞ ዝግጅት ሊጀመር እንደቻለ አስታውሰዋል። ይህም በቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ትልቅ ተነሳሽነትን መፍጠር እንደቻለ አብራርተዋል። ‹‹እንዲህ አይነት ልቡንም በሩንም ለስፖርት ክፍት አድርጎ የሚጠብቅ መሪ ባለበት ወቅት የስፖርቱን ትንሳዔ እውን ካላደረግን መቼም አናደርግም›› በማለትም ፕሬዚዳንቱ የምስጋና ንግግራቸውን ቋጭተዋል። የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ዳዊት አስፋው ጉባዔውና የሽልማት ሥነሥርዓቱ በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረጉ ባለድርሻ አካላት ምስጋና በማቅረብ ‹‹ሁለቱን ታላላቅ ስፖርታዊ ኩነቶች እኛ አመጣናቸው እንጂ ትልቁን ሃላፊነት የተወጣችሁት እናተ ናችሁ፣ በቀጣይም በርካታ እቅዶች አሉን፣ አብረን በመስራት እናሳካለን›› ብለዋል። የኢትዮጵያ ቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽንም ለዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ልዩ ሽልማት አበርክቷል።አዲስ ዘመን  ታህሳስ 10/ 2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=37676
[ { "passage": "ብርሃን ፈይሳየአፍሪካ ብሔራዊ\nኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማህበር\n(አኖካ) የዘንድሮ መዳረሻውን\nኢትዮጵያን ማድረጉ ይታወቃል፡፡\nበኮሚቴው ምስረታ ከፍተኛ\nአስተዋጽኦ በነበራትና የአፍሪካ\nመዲና በሆነችው አዲስ\nአበባ ከትናንት በስቲያ\nጠቅላላ ጉባኤውን ከማካሄዱም\nባሻገር ለኢ.ፌ.ዴ.ሪ.\nጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር\nአብይ አህመድም በአህጉሩ\nከፍተኛ የሆነውን የስፖርት\nየክብር ሽልማት አበርክቷል፡፡\nኮሚቴውና አባላቱ አጠቃላይ\nየነበራቸውን ቆይታ በተመለከተም\nየኢ.ፌ.ዴ.ሪ.\nስፖርት ኮሚሽነር ኤሊያስ\nሽኩር ለአዲስ ዘመን\nአብራርተዋል፡፡በመሪዎች ደረጃ\nይህንን ሽልማት ያገኙ\nጥቂት መሆናቸውን ኮሚሽነሩ\nጠቅሰው፤ ይህም ለኢትዮጵያ\nስፖርትና ለስፖርቱ ቤተሰቡ\nትልቅ የምስራች መሆኑንም\nይጠቁማሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩን\nለሽልማት ሊያበቋቸው የቻሉና\nአርአያ ሊያደርጓቸው የሚችሉ\nመነሻዎች መኖራቸውም ያብራራሉ፡፡\nእንደ ኮሚሽነሩ\nገለፃ፤ በሀገሪቷ እየተከናወኑ\nያሉ የልማት ሥራዎች\nአብዛኛዎቹ ከስፖርቱ ጋር\nየተሳሰሩ መሆናቸውን የእንጦጦ\nፓርክን በማሳያነት ማንሳት\nይቻላል፡፡ አረንጓዴ ልማት\nከስፖርት ጋር በእጅጉ\nየተቆራኘ እንደመሆኑ በየዓመቱ\nበቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን\nበመትከል ከዚህ ቀደም\nአስቸጋሪ የነበሩ አካባቢዎችን\nማልማትም ሌላኛው መነሻ\nነው፡፡ የጃፓን ኦሊምፒክ ኮሚቴ ዝግጅትን ተከትሎ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ባደረገው ውይይት ያገኘው ቀና ምላሽም ሌላው ምክንያት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ዝግጅቱን በተመለከተ ሁለት አቅጣጫዎችን ያስቀመጡ ሲሆን፤ የመጀመሪያው ዝግጅቱ ቀደም ብሎ እንዲጀመርና ውጤት እንዲመጣ ማመላከታቸው ነው፡፡ የተሻለ ውጤት የሚመዘገብ ከሆነም መንግሥት የሚሰጠውን ማበረታቻ በማስቀመጥ ተነሳሽነትን ሊፈጥሩ ችለዋል፡፡ ሁለተኛው አቅጣጫ ደግሞ ለአንድ ኦሊምፒክ ብቻም ሳይሆን ለቀጣይ ኦሊምፒኮችም መሰረት መጣል ስላለበት የኦሊምፒክ መንደር መገንባት አስፈላጊ ነው፡፡ በመሆኑም ሀብት ማሰባሰብ አስፈላጊ እንደመሆኑ፤ የራሳቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱ ቃል ገብተዋል፡፡ በሌላ በኩል በርካታ በየክልሉ የተጀመሩ የስፖርት መሰረተ ልማቶችና ግዙፍ ስታዲየሞች ተጠናቀው ሌሎች መጀመር አለባቸው የሚል አቅጣጫም አስቀምጠዋል፡፡ በመሆኑም ከስታዲየሞች ባሻገር የማሰልጠኛ ተቋማትም በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ በማስገባት ሁሉም አመራር ትኩረት እንዲሰጠው አድርገዋል፡፡ ለስልጠና፣ ለውድድርና ለሽልማት አስፈላጊው የገንዘብ ድጋፍ በመንግሥት እየተሰጠ በመሆኑ እንዲሁም ስፖርቱን የሚመሩት መንግሥታዊና ህዝባዊ አካላቱ በነፃነት ነገር ግን በመንግሥት መደገፍ ባለባቸው መልክ ማስኬድ መቻሉም ሌላኛው ምክንያት ነው፡፡ እነዚህ ጉዳዮችም ለስፖርቱ ትልቅ ትኩረት መስጠታቸውን የሚያሳይ መሆኑን በመመልከትም የአፍሪካ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ሽልማቱን ሊያበረክት ችሏል፡፡ ለረጅም\nጊዜ ዝግጅት ሲደረግበት\nየቆየውና በአጠቃላይ በአዲስ\nአበባ የተካሄዱት የአኖካ\nመርሐ ግብሮች ለኢትዮጵያ\nስፖርት ዕድገት እንዲሁም\nለአገር ገጽታ ግንባታ\nአስተዋጽኦ ያላቸው መሆኑንም\nኮሚሽነሩ ያመላክታሉ፡፡ ለቀናት ከአፍሪካና ከሌሎች አገራት የተገኙ የስፖርት አመራሮች ከጉባኤው ባሻገር፤ የኮሚቴው ሥራ አስፈፃሚ አባላት ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ እንዲሁም ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱም ወቅት ኢትዮጵያ በአህጉር አቀፍ ደረጃ ምን ሚና ነበራት ወደፊትስ የሚኖራት ሚና ምን ይመስላል በሚለው ላይ ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡ ሥራ አስፈፃሚውም ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ስፖርት ተምሳሌት መሆኗን እንዲሁም መንግሥት ለዘርፉ የሚሰጠው የጎላ ድርሻ፣ ህዝባዊና መንግሥታዊ አካሉ በቅንጅት ስፖርቱን የሚመራበት ሁኔታ እንዲሁም ለስፖርት የሚመድበው በጀት ለሌሎች አፍሪካዊያን አገራት ምሳሌ እንደሚሆን መግለፃቸውንም ኮሚሽነሩ አብራርተዋል፡፡ በአዲስ አበባ\nየተካሄደው ጠቅላላ ጉባኤም\nኢትዮጵያ የትኛውንም አህጉርም\nሆነ ዓለም አቀፍ\nጉባኤ የማስተናገድ አቅምና\nብቃት ያላት ሀገር\nመሆኗን በግልጽ ያሳየ\nነበር፡፡ ከዚህ ባሻገር\nበሀገሪቷ እየተከናወኑ ያሉ\nእንቅስቃሴዎችን በዘጋቢ ፊልምም\nጭምር በማዘጋጀት ለማስረዳት\nሙከራ መደረጉንም ኮሚሽነር\nኤሊያስ ሽኩር ጠቁመዋል፡፡አዲስ ዘመን ህዳር 29/2012", "passage_id": "1e4b5bcfc4318fb181c6d1baef25bc3a" }, { "passage": "የዓለምን ኢኮኖሚያዊ፣ማህበራዊና ፖለቲካዊ ነባራዊ ሁኔታ ወደተለየ አቅጣጫ ያዞረው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በስፖርቱ ዓለም ያሳደረው አሉታዊ ተፅዕኖ ተዘርዝሮ የሚልቅ አይደለም። አንዳች ውድድር በዓለም ላይ እንዳይኖር ከማስገደድ ባለፈ የስፖርቱን ዓለም ሽባ አድርጎታል። ብዙ ታቅዶባቸው፣ብዙም ተለፍቶባቸው ለዓመታት በዝግጅት ላይ የነበሩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች በትልቅ ኪሳራ የሚካሄዱበት ጊዜ እንዲራዘም ግድ ብላል። \nየኮሮና ቫይረስ ስርጭት በዓለም ዙሪያ ከተንሰራፋ ወዲህ በግለሰብ ደረጃ ካልሆነ በስተቀር የትኛውም የስፖርት እንቅስቃሴ ተገድቦ እንደቆየ ይታወቃል። የቫይረሱ ስርጭት በዓለም ዙሪያ እያሻቀበ መሄዱን ተከትሎም ታላላቅ ስፖርታዊ ውድድሮች በቅርቡ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው ይመለሳሉ የሚል ተስፋ የለም። ይሁን እንጂ የዓለማችን ታላላቅ የእግር ኳስ ሊጎች በዝግ ስታድየምም ቢሆን የውድድር ዓመቱን ቀሪ መርሐግብሮች ለማጠናቀቅ በቅርቡ ወደ ውድድር እንደሚመለሱ ተስፋ መስጠታቸው አልቀረም። የዓለም ጤና ድርጅት የሕክምና ባለሙያዎች ግን ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በትልቅ ደረጃ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው እንዳይመለሱ ምክራቸውን ለግሰዋል። \nበዓለማችን ብሎም በአገራችን በፍጥነት እየተስፋፋ የመጣውን የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ስርጭትን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት የስፖርት ቤተሰቡ መደበኛ እንቅስቃሴውን ገቶ የበኩሉን አስተዋፅኦ ማድረግ ከጀመረ ሰነባብቷ። የስፖርት ቤተሰቡ ወረርሽኙን ለመከላከል ግንዛቤ ከመፍጠር እስከ ደም ልገሳ፤ ከቁሳቁስ እስከ ገንዘብ ድጋፍ በማድረግ አጋርነቱን አሳይቷል ፤ በማሳየት ላይም ይገኛል። \nወረርሽኙ በዓለም ላይ ከተከሰተና ከተስፋፋ ወዲህ የስፖርቱን ዘርፍ ክፉኛ የጎዳው ሲሆን የአገራችንን ጨምሮ በዓለም ላይ በርካታ ታላላቅ ውድድሮች እንዲቆሙ አስገድዷቸዋል። በተለይም ወረርሽኙን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በተወሰዱ እርምጃዎች ስልጠናዎች፣ ውድድሮች ቁመዋል ፤ ስፖርተኛው እና የስፖርት ቤተሰቡ ከፍተኛ የሆነ የስነ ልቦና እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ አጋጥሟቸዋል ። \nበርካታ የስፖርት ክለቦች የመፍረስ አዳጋ ተደቅኖባ ቸዋል፤ አንዳንዶቹም ለስፖርተኞች ወርሃዊ ደመወዝ እስከ መከልከል ደርሰዋል። በመሆኑም የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ከባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በወረርሽኙ ወቅት እና ከወረርሽኙ በኋላ ስፖርቱ እንዴት ወደ ነበረበት መመለስ ያስችላል የሚለውን የሚያጠና እና ለመንግሥት የሚያቀርብ ጠንካራ ኮሚቴ መቋቋሙን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዱቤ ጅሎ መናገራቸውን የተቋሙ ይፋዊ የፌስ ቡክ ገፅ ላይ ተዘግቧል። \nየተቋቋመው ኮሚቴ አብይ እና ቴክኒካል ኮሚቴ ያለው ሲሆን አብይ ኮሚቴው በባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ዶክተር ሂሩት ጣሰው የሚመራ ይሆና። ቴክኒካል ኮሚቴው ደግሞ በአቶ ዱቤ ጅሎ እንደሚመራ ታውቋል። \nኮሚቴው አጠቃላይ የኮሮና ወረርሽኝ በአገራችን ስፖርት ላይ እያሳደረ ያለውን ጫና እና መፍትሔዎችን በማጥናት ሰነዱን ለመንግሥት የሚያቀርብ ይሆናል። በጥናቱም የሌሎች አገራት ተሞክሮ ምን እንደሚመስል ተካቶ እንደሚቀርብ አቶ ዱቤ አብራርተዋል። \nጥናቱን መሠረት በማድረግ መንግሥት ስፖርቱ ለአገራችን ማህበራዊ ፣ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ፋይዳ ግምት ውስጥ በማስገባት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ምክትል ኮሚሽነሩ ገልፀዋል ።አዲስ ዘመን ግንቦት 27/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "24c212eb0cbc2bfc4fa9a396312bd847" }, { "passage": "ስፖርት ሰላም፣ ፍቅር፣ የአብ ሮነትና የአንድነት፣ የመተሳ ሰብ፣ የወንድማማችነት ልዩ መገለጫ ነው። ስፖርት ዘር፣ ሃይማኖት፣ ፆታና ቀለምን አይለይም። በየት ኛውም ሁኔታ ውስጥ የስፖርታዊ እንቅስቃሴ አስኳል ሃሳብ ወዳጅነትና መተሳሰብ መሆኑ ይታወቃል። በታሪክ ገጾች እንደሰፈረውም በሰው ልጅ ታሪክ ባጋጠሙ በጎም ሆኑ መጥፎ ክስተቶች ስፖርት በአጋርነት ተሳትፏል። ስፖርታዊ ክንዋኔዎች ሰላምንና አንድነትን የሚሰብኩ እንደመሆናቸው በማህበራዊ፣ ፖለቲ ካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች በመግባት ሚናቸውን ሲወጡም ኖረዋል። ስፖርት ሰብዓዊነትን ያነገበ የልግስና ማዕድ መሆኑን ዘመነ ኮሮና በተጨባጭ አሳይቶናል። የቫይረሱ ስጋትነት በዓለም አቀፉ የጤና ተቋም ከተረጋገጠበት ጊዜ ጀምሮ፤ ውድድሮችን ከማቋረጥና ከመሰረዝ ባለፈ የስፖርቱ ተዋንያን በተናጠልም ሆነ በተቋማዊ ደረጃ አበርክቷቸውን ሲወጡ ታዝበናል።በስፖርቱ ዘርፍ ዓለም አቀፍ ዝናን ካተረፉ ግለሰቦች እስከ ዓለም አቀፍ ተቋማት ድረስ ወረርሽኙን ለመመከት እየተደረገ ባለው ርብርብ ከተሳትፎ አልጎደሉም።በተለያዩ ሀገራት ዓለም አቀፉን ወረርሽኝ ለመዋጋት በስፖርቱ ማኅበረሰብ ዘንድ የታየው ተሳትፎ በሀገራችንም ተመሳሳይ ሲሆን ታዝበናል። \nበኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት ይፋ ከተደረገበት ከወርሃ መጋቢት መጀመሪያ አንስቶ የስፖርቱ ማህበረሰብ ድርሻ ግዙፍ ነው።በስፖርት ዘርፍ የሚገኙ የመንግሥትና የግል ተቋማት፣ የስፖርት ማህበራት፣ ተጫዋቾች፣ አትሌቶች፣ የእግር ኳስ ክለቦችና ተጫዋቾች ወረርሽኙን ለመከላከል የሚደረገውን ርብርብ ተሳትፎ ሲያደርጉ ነበር።በስፖርት ማህበረሰቡ በኩል ሰብዓዊነትን መሰረት አድርጎ ህዝባዊነትን በመታጠቅ «ወገን ለወገን » ደራሽነቱን በገንዘብና በቁሳቁስ ድጋፍ ሲደረግ የታዘብንበት ሁኔታ ፤ስፖርት ሰላም፣ ፍቅር፣ የአብሮነትና የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የወንድማማችነት ልዩ መገለጫ የመሆኑን እውነታ በተግባር አስረድቷል።የኮሮና ወረርሽኝ በዓለም ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ መስተጋብር ላይ ያሳደረው ተጽእኖ መዘዙ ዓለም አቀፉን የስፖርት ቁመና የኪሳራ መልክ ያላበሰው ነበር ።በስፖርቱ ላይ የደረሰው ከፍተኛ የሆነ የፋይናንስ ቀውስ የተጽእኖው ሰንሰለት ዛሬ ላይ የሚቆም ሳይሆን እስከ ቀጣዮቹ አስር ዓመታት የሚጓዝ እዳን ያስከተለ መሆኑን ነው ጥናቶች ያመላከቱት።በወረርሽኙ ምክንያት ከፍተኛ መቃወስን ካስተናገዱ መካከል የስፖርት ዘርፍ ዋነኛ ነበር።ይህም በስፖርቱ ማህበረሰብ በኩል ወረርሽኙን ለመዋጋት እየተደረገ በሚገኘው ርብርብ እያደረገ ያለው ተሳትፎ ስፖርት ትልቅ ማህበራዊ ኃላፊነትን የተሸከመ ግዙፍ ተቋም መሆኑን ያመላክታል።\nበዓለም አቀፍ ደረጃ እንደታዘብነው ሁሉ በሀገራችን የስፖርት ማህበረሰቡ ከነጉዳቱ ትልቅ ተሳትፎ ሲያደርግ ነበር።በዘመነ ኮሮና የስፖርት ቤተሰቡ ሰብዓዊነትን ያነገበ ተግባር በይበልጥ ተጠናክሮ እንደቀጠለ የሚያሳይ መረጃ ከአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አካባቢ የወጣው መረጃ ያመላክታል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በኮሮና ቫይረስ ( ኮቪድ_19) ወረርሽኝ ምክንያት ለተቸገሩ 300 የሁለተኛ ዲቪዚዮን ክለብ አትሌቶች፣ ዳኞችና አሰልጣኞች የሰብዓዊ ድጋፍና ስለ ቫይረሱ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐ ግብር ማዘጋጀቱን አስታውቋል።«ለአትሌቶቻችን እንቁም» በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ ስታዲየም ዛሬ ማለዳ የሚደረገው የድጋፍና ግንዛቤ የማስጨበጫ መርሐ ግብር የስፖርቱ ቤተሰብና ማህበረሰብ ለሰብዓዊነት ተግባር የሚሰጠው ቦታ ምን ያህል ሰፊና ጥልቅ መሆኑን በዘመነ ኮሮና በይበልጥ የሚያሳይበት እንደሚሆን ተጠቁሟል።\nየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ቢኒያም ምሩፅ ይፍጠር እንደተናገሩት፤የኮቪድ -19 ወረርሽኝ ስጋት በአትሌቲክሱ ስፖርት እና ስፖርተኞችም ላይ ጥላውን ያጠላ መሆኑን ገልጸዋል ።በመሆኑ ከዚህ ችግር ተሻግረን ነገ የምንፈልገውን ውድድርና ውጤት ለማስመዝገብ ዛሬ መረዳዳት ይኖርብናል።ስለዚህ በሁለተኛ ዲቪዚዮን ክለብ የሚገኙ አትሌቶች፣ አሰልጣኞች፣ የታዳጊ ወጣቶች ፕሮጀክት አሰልጣኞች፣ እና ዳኞች ቁጥራቸው 300 ለሚሆኑ የስፖርቱ ቤተሰቦች በዛሬው እለት የሰብዓዊ ድጋፍ ሊደረግ መሆኑን አመልክተዋል። \nበኢትዮጵያ አትሌቲክስ የትልቅ ታሪክ ባለቤት ከሆኑት አትሌቶች አንዱ የሆነው ማርሽ ቀያሪው ምሩጽ ይፍጠር ልጅ የሆኑት አቶ ቢኒያም ፤«ነገን እንሻገራለን፣ የምንፈልገውንና የምንወደውን አትሌቲክስ ስፖርታችንን እናስቀጥላለን ዛሬ ላይ በህብረትና በአንድነት ቆመን ልንደጋገፍና ልንረዳዳ ይገባል» ሲሉም ሰብዓዊነትን የታጠቀውን መርሐ ግብር አስፈላጊነት የተናገሩት። የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለአትሌቲክስ የዘወትር አጋር ከሆነው ከሞሐ ለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማህበር ጋር በመተባበር የሰዋዊ ድጋፍና የግንዛቤ ማስጨበጫው የሚከናወን መሆኑንም ነው ያስታወቁት።\nአዲስ ዘመን ሰኔ 12/2012ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "94abbf8e37da82febbb057ee77459c41" }, { "passage": "የዓለም ሕዝብ ሁሉ ጭንቀትና ስጋት የሆነው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ከትንሽ እስከ ትልቅ፣ ከሀብታም እስከ ድሃ፣ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ዋነኛ ትኩረቱ እንዲሆን ካስገደደ ስድስት ወራት ተቆጠሩ፡፡ የቫይረሱ ስርጭት በእነዚህ ወራት እንደ ሰደድ እሳት ያላዳረሰው የዓለም ክፍል ስለመኖሩ አጠራጣሪ ሆኗል፡፡ ሀገራት ዓለም በጋራ የገጠማት ጦርነት በድል ለመወጣት የሚያስችል መፍትሄ ለማበጀት ጥረት ማድረጉን ተያይዘውታል። የቫይረሱ ማንነትና፣ ምንነት ፈጣን መፍትሄ ማበጀት የሚያስችል አልሆነም። በእርግጥም የኮሮና ወረርሽኝ በዓለም ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ መስተጋብር ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ብቻ ነውን? በእኔ እሳቤ አዎንታዊ እንዳለው መካድ ንፍግነት ይሆናል! የኮሮና ቫይረስ ዓለምን እንደጎዳት ባለበት ደረጃ ባይሆንም በጎ መልኮችን ይዞ መምጣቱን በድፍረት መናገር ይገባል። ዓለም ከገባችበት የጋራ ማዕጥ ለመውጣት ከሚደረግ ጉዞ የሚቀዳው «ሰውነትን» ያስቀደሙ ደጋግ እጆችን፤ ኅብረተሰቡ ከተጋረጠበት አደጋ ለመታደግ ሰብአዊነትን አርግዘው የሚወለዱ ድጋፎችን በዘመነ ኮሮና ሊበረክቱ ችለዋል። በዓለም አራቱም አቅጣጫዎች ሰብአዊነትን ባስቀደመ መልኩ ሲደረጉና እየተደረጉ ያሉ ድጋፎችን ብሶባቸው ታዝበናል። በተለያዩ መስኮች እንፋሎቱ ሳይበርድ የቀጠለው ልግስና ከስፖርቱ መስክ ያለውን ሁኔታ መመልከቱ ይበጃል።\nስፖርት ሰላም፣ ፍቅር፣ የአብሮነትና የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የወንድማማችነት ልዩ መገለጫ ነው። ስፖርት ዘር፣ ሃይማኖት፣ ፆታና ቀለምን አይለይም። በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ የስፖርታዊ እንቅስቃሴ አስኳል ሃሳብ ወዳጅነትና መተሳሰብ መሆኑ ይታወቃል። በታሪክ ገጾች እንደሰፈረውም በሰው ልጅ ታሪክ ባጋጠሙ በጎም ሆኑ መጥፎ ክስተቶች ስፖርት በአጋርነት ተሳትፏል። ስፖርታዊ ክንዋኔዎች ሰላምንና አንድነትን የሚሰብኩ እንደመሆናቸው በማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች በመግባት ሚናቸውን ሲወጡም ኖረዋል። ስፖርት ሰብአዊነትን ያነገበ የልግስና ማዕድ መሆኑን ዘመነ ኮሮና በተጨባጭ አሳይቶናል። የቫይረሱ ስጋትነት በዓለም አቀፉ የጤና ተቋም ከተረጋገጠበት ጊዜ ጀምሮ፤ ውድድሮችን ከማቋረጥና ከመሰረዝ ባለፈ የስፖርቱ ተዋንያን በተናጥልም ሆነ በተቋማዊ ደረጃ አበርክቷቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። በእግር ኳስ ጠቢብነታቸው ዓለም የመሰከረላቸው ተጫዋቾችና ስመ ጥር አሰልጣኞችም፤ ለደጋፊዎቻቸው መልእክት ከማስተላለፍና ገንዘብ ከመለገስ ባሻገር ሆቴሎቻቸውን ለህክምና አገልግሎት እንዲውሉም ጭምር መስጠታቸው ይታወሳል። በሀገራችን በተመሳሳይ የስፖርቱ ለጋስነትና ሰብአዊነት መገለጫ ያደረጉ ተግባራት ዛሬም እንደ ትናንቱ በዘመነ ኮሮና ከነበረው ብሶበት አለኝታነቱን እያሳየ ይገኛል። የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት ከታወቀበት ከመጋቢት መጀመሪያ አንስቶ በስፖርቱ ማህበረሰብ ጠንካራ እንቅስቃሴ በማድረግ አጋርነቱን በፈጠነና በቀደመ መልኩ ያሳየው። በስፖርት ቤተሰቡ በቡድንም ሆነ በተናጠል ለወረርሽኙ መከላከያ የሚውል የገንዘብ ድጋፍ በማሰባሰብ ከመንግስት ጎን በመቆም ወገን ላይ የተደቀነውን አደጋ በአንድነት ለመመከት ህዝባዊነቱን ማሳየት ችሏል፡፡\nበአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ የድጋፍ መሠባሰብ ጥሪ ተከትሎ የስፖርቱ ማህበረሰብ ተሳትፎ በተጠናከረ መልኩ መቀጠሉን ለመታዘብ ችለናል። ከመከላከያ ስፖርት ክለብ አካባቢ የተሰማው ዜና ይሄንኑ ያስረዳል። የመከላከያ ስፖርት ክለብ አዋቂ ወንዶች እና ሴቶች እግር ኳስ ቡድን እና ኮቺንግ አባላቱ 211 ሺህ ብር ድጋፍ አድርጓል። የስፖርት ክለቡ ለኮረና ቫይረስ መከላከልና መቆጣጠር እንዲውል በከተማ አስተዳደሩ ለተቋቋመ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ኮሚቴ ነበር ገንዘቡን ያስረከበው። «የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባቀረበው የድጋፍ ጥሪ መሠረት የኮቪድ -19 ለመግታት በሚደረገው ርብርብ የበኩላችንን ለመወጣት ነው» ሲሉ ነበር የስፖርት ክለቡ አባላት በስፖርቱን ማህበረሰብ ዘንድ ሰብአዊነትን ባስቀደመ መልኩ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት እየተደረገ ያለውን ተሳትፎ ያመላከቱት። የሀገር ዳር ድንበር ህልውና ከሆነው የስፖርቱ ክለብ በተመሳሳይ፤ በስፖርቱ የሰብአዊነት ልግስናው ተጠናክሮ የመቀጠሉን ሁኔታ የጠዋት ጎህ አትሌቶች የልማት መረዳጃ ተግባርም ይነሳል። በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ድል በማድረግ የሀገራችንን ሰንደቅ አላማ በማወለብለብ ስሟና ዝናዋን ከፍ ባደረጉት አትሌቶች የተቋቋመው ዕድሩ 200 ሺህ ብር ድጋፍ በማድረግ አጋርነታቸውን አስመስክረዋል፡፡\nየአትሌቶቹ የመረዳጃ ዕድር አባላት አስተባባሪዎች ኮማንደር አትሌት ጌጤ ዋሚ፣ አትሌት ተስፋዬ ቶላ፣ አሰልጣኝ ንጋቱ ወርቁ ፣ ዶክተር በዛብህ ወልዴ እና ወይዘሮ አይናዲስ ተስፋዬ ድጋፍ ለማድረግ የመሻታቸውን ሚስጥር በጋራ እንዲህ አጋርተዋል። «ዓለም ብሎም ሀገራችን በጭንቅ ተውጣለች። ህዝባችንም በሲቃ ተኮራምቷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለኮረና ቫይረስ መከላከል ጥሪ ማቅረቡን ተከትሎ እኛም የዜግነት ግዴታችን ለመወጣት የገንዘብ ድጋፍ ልናደርግ ወደናል። ኢትዮጵያዊነታችን የሚደምቀው በዚህ በጭለማና በጭንቅ ወቅት ስንረዳዳና ስንተጋገዝ በመንፈስና በፀሎት አብረን ከማህበረሰባቸን ጎን ስንቆም ነው» \nየኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ከሆኑ አትሌቶች ልግስና ወረድ በማለት እንደ መቋጫ አንድ ክስተት ስንጠቅስ፤ በኢትዮጵያ የወንዶችና የሴቶች ብሔራዊ ቡድኖች አሠልጣኞች እንዲሁም የስፖርቱ ሙያተኞች የተደረገ ልግስና የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ለመከላከል ከስፖርቱ ቤተሰብ በኩል እየተደረገ ያለውን ልግስና የሚያሳየው ሁነት ነው። እነዚህ አካላት ህዝብን ለመታደግ በሚደረገው ርብርብ በየአቅጣጫው 120 ሺህ ብር መሰብሰብ ችለዋል። ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ለኢንጂነር ታከለ ኡማ አስረክበዋል፡፡ ይህ ተግባር በአጠቃላይ ከስፖርት ማኅብረተሰቡ ዘንድ የተንፀባረቁትን ወገናዊ ድጋፎችንና ችግርን በአንድነት ለመመከት እየተደረገ ካለው ጥረት በመነሳት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ከፈጠረውና ካሳደረው አሉታዊ ተጽእኖ ጎን ለጎን የፈጠረው በጎ መልክ ስለመኖሩ የሚያስገነዝብ ይሆነናል። በስፖርት ማኅብረተሰቡ አካላዊ ርቀትን በጠበቀ መልኩ ማኅበራዊ ኃላፊነትን የመወጣት ጉዞ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እሙን ነው።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 9/2012 ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "e10eb64dc6d136aecb7fc5a3a35fdabe" }, { "passage": "በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰተው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል አቅመ ደካሞችን ለመርዳት ማኀበሩ ለስፖርት ቤተሰቡ የድጋፍ ጥሪ አቅርቧል።የጤና ባለሙያዎች የሚያስተላልፉትን መልዕክት እንጠብቅ የሚለው ማኅበሩ ጎን ለጎን የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች የሌላቸውን የጎዳና ተዳዳሪዎችን (አቅመ ደካማዎችን) ለመደገፍ የማኅበሩ ጠቅላላ ጉባኤ አባላት እና ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ማኀበራዊ ኃላፊነታችንን እንወጣ ሲሉ እያንዳንዳቸው በግል 300 ሳሙና ለመለገስ የወሰኑ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ይህን በጎ ተግባር ለማገዝ የሚፈልጉ ሌሎች አባላቶች እና የስፖርት ቤተሰቦች ከዛሬ ጀምሮ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሒሳብ ቁጥር ተጠቅመው መደገፍ እንደሚችሉ ተገልጿል፡-© ሶከር ኢትዮጵያ", "passage_id": "cd22c2e8e84fb0e429f787d1b8ff8b58" } ]
af07eaea6ac6599b1b9d41617fff1149
ae9bc8a3997d431210c2b66aee932e3c
በሀገሪቱ የሚስተዋሉ ግጭቶችን ለማስቆም ምክንያታዊ ትውልድ መፍጠር እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ
መርድ ክፍሉአዲስ አበባ፡- በሀገሪቱ የሚስተዋሉ ግጭቶችን ለዘለቄታው ለማስቆም በምክንያት የሚያምን ትውልድ መፍጠር እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ። በአገሪቱ የሚገኙ ወጣቶች በአገር ጉዳይ ምክንያታዊ የሆነ አስተሳሰብን መፍጠር የሚስችላቸው የሙግትና የንግግር መድረክ በአዲስ አበባ ተጀመረ። የብልጽግና ወጣት ሊግ ምክትል ፕሬዚዳንትና የጽህፈት ቤት ኃላፊ ወጣት አክሊሉ ታደሰ ትናንት መድረኩን በንግግር በከፈቱበት ወቅት እንዳስታወቁት ፤ በአገሪቱ በእምነት እና በፖለቲካ ልዩነት እንዲሁም በሌሎች ጉዳዮች ወደ ግጭት እየተገባ ነው። ይህን ለመቀነስና ለማስቆም ምክንያታዊ የሆነ ወጣት መፍጠርና በንግግር የሚያምን ትውልድ መቅረጽ ያስፈልጋል ፤ ለዚህም መድረኩ ተመቻችቷል። የጋራ ባህል፣ እሴት፣ ታሪክ እንዲሁም መተሳስሮች ባይኖሩ ባለፉት ጊዜያት የእርስበርስ ግጭት ለመፍጠር የተሰራጩት የታዘቡ መረጃዎች ሀገርና ህዝብን ከሆነው በላይ ሀገርና ህዝብን ዋጋ ያስከፍሉ እንደነበር አመልክተዋል። በቀጣይም ተመሳሳይነት ችግሮች እንዳይፈጠሩ ምክንታዊ የሆነ ወጣት ለመፍጠር የንግግር መድረኮች እየተዘጋጁ መሆናቸውን ጠቁሟል። የንግግር መድረኮቹ በአገርና በብሄር መንግስት ግንባታ ዙሪያ ያጠነጠኑ መሆናቸውን የጠቀሰው ወጣት አክሊሉ፤ በሰላማዊ መንገድ የትኛውም አስተሳሰብ ያለው ወጣት በመምጣት መነጋገርና መሟገት እንደሚችል አስረድቷል። በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚናፈሱ አገር የሚያፈርሱ ወሬዎችን ለማስቆም የንግግር መድረኮች ወሳኝ መሆናቸውን ገልጿል። የአዲስ አበባ ብልጽግና ወጣት ሊግ ፕሬዚዳንት ወጣት አዕምሮ አዱኛ በበኩሉ፤ በምክንታዊ ወጣት የንግግርና የሙግት መድረክ የአገርና የብሄረ መንግስት ምስረታ ሁኔታ መነሳቱ ወጣቱ በጉዳዮቹ ላይ ያለውን አመለካከት ለማስተካከል እንደሚረዳ አስታውቀዋል። በአገሪቱ የአገርና የብሄረ መንግስት ግንባታው ገና ያላለቀና ብዙ የሚቀረው መሆኑን የጠቀሰው ወጣት አዕምሮ፤ የአገርና የብሄረ መንግስት ግንባታውን ለማጠናቀቅ ወጣቱ ምንያታዊ ሆኖ መንቀሳቀስ እንዳለበት ጠቁሟል። ህብረ ብሄራዊ አስተሳሰብንም ለማምጣት በውይይት የሚያምን ወጣት ሊፈጠር እንደሚገባም አመልክቷል። በመድረኩ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና መምህር የሆኑት መምህር ዮናስ ዘውዴ ‹‹የአገርና ብሄረ መንግስት ግንባታ ምንነትና የወጣቱ ሚና›› በሚል መነሻ ጽሁፍ አቅርበዋል። በቀረበው መነሻ ጽሁፍ ላይም ውይይት ተደርጓል።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=39630
[ { "passage": "አዲስ አበባ፡- በትግራይና በአማራ ህዝቦች መካከል ለዘመናት የቆዩ የሃይማኖት፣ የባህልና ሌሎች እሴቶች እንዳይሸረሸሩ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ። አሁን ላለው አለመግባባት ያለፈውን ትውልድ ከመውቀስ በዘለለ በሰከነ መንፈስ ተነጋግሮ ለመጪው ትውልድ የተሻለ አገር ማስረከብ ያስፈልጋል ተብሏል። የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር\nዴኤታ አቶ አለማየሁ\nእጅጉ በካፒታል ሆቴል የአማራና የትግራይ\nክልሎችን ግንኙነት ለማጠናከር\nበተዘጋጀው የምሁራን የምክክር\nመድረክ ላይ እንደተናገሩት፤ በሀገር ግንባታ ዙሪያ የአማራና የትግራይ\nሕዝቦች ከፍተኛ ሚናን ተጫውተዋል፡፡ በተለይ ደግሞ ጠላትን ድል በማድረግ\nለሀገር ሉአላዊነት ዘመናቸውን\nሙሉ በጋራ አስጠብቀዋል፡፡ ሆኖም ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በፖለቲካ ልሂቃኖች\nመካከል የተፈጠረው  አለመግባባት ከሁለቱ ክልል ሕዝቦች አልፎ ለሀገር አለመረጋጋት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ የሁለቱ ህዝቦች ምሁራን የህዝቦችን አንድነት የሚያጠናክሩ ንግግሮችን ከማድረግና የእርስ በርስ ግንኙነቶችን ከማጠናከር ይልቅ ልዩነቶችን በማጉላት ሰላሟ የተጠበቀ ሀገር እንዳትኖር አድርገዋል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ እንደ ፖለቲከኞች ሀሳብ ቢሆን ሁለቱ ህዝቦች ወደ ጦርነት በገቡ ነበር ብለዋል። ነገር ግን ህዝቦቹ ምሁራኖቹን ባለመከተላቸው በደስታና በሀዘን አንድነታቸውን እንዳጠናከሩ መቀጠላቸውን ገልጸዋል፡፡ የሁለቱ ሕዝቦች ምሁራን አባቶቻቸው ደማቸውን አፍስሰው አጥንታቸውን ከስክሰው የመሰረቷት ሀገር እንደ ሀገር ጠንካራ እንድትሆን እንደምሁር ዓለም አቀፋዊ፣ አህጉራዊና ሀገራዊ ሀሳብን በማፍለቅ ለሀገር ግንባታና አንድነት መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል፡፡ ከራስ በላይ ለሀገር ቅድሚያ በመስጠት ሀገርን መታደግ እንደሚኖርባቸውም አሳስበው በተለይ ደግሞ እንደ ምሁር በሁለቱ ህዝቦች ባህላዊ የሰላም እሴቶች ላይ ጠንካራ ሥራ በመስራት የህዝቦችን ማህበራዊ ግንኙነት ማጠናከር እንዳለባቸው አመልክተዋል፡፡ የሕግ ባለሙያና የአማራ ምሁራን አባል አቶ ዮናስ ተስፋ በበኩላቸው፤ የምሁራን የምክክር መድረኩ ዋና ዓላማ በፖለቲካ አጀንዳዎችና በፖለቲካ ልሂቃኑ  የፖለቲካ ጥያቄዎች ላይ ለመወያየትና ያላቸውን ልዩነቶች በውይይት ለመፍታት እንዲችሉ ለማድረግ የታሰበ ነው ብለዋል። እንዲሁም በፖለቲከኞች መካከል ያሉ ልዩነቶች ላይ በመወያየት ለመፍታት ለፖለቲካ ልሂቃኖች ምቹ የሆነ የውይይት መድረክን ለመፍጠር የታሰበ ነው፡፡ ምሁራኑ ከውይይት ውጭ አዋጭ የሆነ መንገድ እንደሌለ አውቀው ተቃርኗቸውን በሰለጠነ መንገድ መፍታት እንዲችሉ ለማድረግ መሆኑንም አስረድተዋል። ፖለቲከኞች ባላቸው ተቃርኖ ሰላማዊ መንገድን ተከትሎ አሸናፊ መሆንን ከመምረጥ ይልቅ በጡንቻ አሸናፊ ለመሆን ሙከራዎችን የሚያደርጉ ከሆነ የሀገርን ሰላምና የሁለቱን ሕዝቦች አንድነት አደጋ ላይ እንደሚጥል በማወቅ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡ከመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የመጡት ዶክተር ገብረእየሱስ ተክሉ በበኩላቸው፤ የትግራይና አማራ ህዝቦች ከቋንቋ ውጪ የሚለያያቸው ጉዳይ አለመኖሩን ያነሳሉ። በእነዚህ ህዝቦች መካከል ያልነበረውን ልዩነት ለሥልጣንና ሌሎች ጥቅሞች ሲባል እንዲፈጠር ተደርጓል የሚል እምነትም አላቸው። በመሆኑም በአብሮነት እንጂ በልዩነት የሚመጣ ጥቅም ዘለቄታ ስለማይኖረው ችግሮችን በውይይት መፍታት ያስፈልጋል ብለዋል።አዲስ ዘመን ህዳር 7/2012ሞገስ ጸጋዬ", "passage_id": "14c54a29ef19bc887ed067761ad5e3df" }, { "passage": "ወጣቱ በተለያዩ ጊዜያት የሚነሱ ጥያቄዎችና ልዩነቶችን  ህጋዊና ሰላማዊ በሆነ መንገድ የመፍታት ባህል ማዳበር እንዳለበት የፌደራልና አርብቶ አደር ጉዳዮች ሚኒስትሩ አቶ ካሳ ተክለብርሃን  ገለፁ፡፡በአራተኛ አገር አቀፍ የወጣቶች ጉባኤ ላይ በፌዴራሊዝም ስርዓት ላይ ከወጣቶች ጋር ውይይት በተካሄደበት ወቅት ሚንስትሩ ሰላም፣ የህግ የበላይነትና ህገመንግስት በማክበር የጸረ ድህነት ትግሉን ማስቀጠል ይገባል፡፡በውይይቱም ወጣቶቹ አሁን ስላለው ወቅታዊ ሁኔታና የመልካም አስተዳደር ችግር ናቸው ያላቸውን በርካታ ጥያቄዎችን አንስተዋል፡፡ከሀገሪቱ ኢኮኖሚ ዕድገት ጋር ተያያዞ በርካታ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች አሉ፤ እነዚህን ጥያቄዎች  በሰላማዊ መንገድ በመታገል የተጀመረውን ልማት ማሳካት ይቻላል ብለዋል፡፡ ይህ ካሆነ ግን አንድ ትውልድ የማይፈታው ድህነት ውስጥ እየወረድን እንሄዳለን ነው ያሉት አቶ ካሳ፡፡ወጣቶች በደንብ መገንዘብ ያለባቸው፣ በኢትዮጵያ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እየተመዘገበ ነው፤ ይህ ደግሞ በህብረተሰብ ፈቃድ ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ ስልጣን በመመስረት የመጣ ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡“ኢህዴአግ በተለያዩ መድረኮች ላይ ችግሬ የመልካም አስተዳደር ነው ይላል ይህንን በዘላቂነት ለመፍታት ግን እያደረገ ያለው ምላሽ የዘገየ ነው ይህ ከምን መጣ?“” የሚሉ  ጥያቄዎች ከወጣቶች ቀርበዋል፡፡መንግስት ዘላቂ መፍትሄ ያመጣሉ ብሎ በዘረጋቸው አሰራሮች አማካኘነት ችግሮችን በብቃት ለመፍታት የሚያስችል እንቅስቃሴ መጀመሩንም ገልጸዋል፡፡በኢትዮጵያ ቅርብ ጊዜ ወዲህ በአንዳንድ አካባቢዎች እየተከሰቱ ያሉ ግጭቶች  የአክራሪነት አመለካከት ያላቸው ሃይሎችም ህዝቡን በተለይም ወጣቱን በተሳሰተ መንገድ ለመጠቀም እየተንቀሳሰቀሱ መሆናቸውን ያሳየ እንደሆነም አቶ ካሣ ገልጸዋል፡፡ህጋዊ ጥያቄዎችን መጠየቅና ሀገር ማፈራረስ ማለት የተለያዩ ናቸው ያሉት አቶ ካሳ አሁን ያሉ ግርግሮቹ ስንመለከታቸው ለወጣቱ የስራ ዕድል፣ ኑሮ ለመሻሻል ከማሰብ ይልቅ የኢንቨስትመንት ተቋማትን ማፍረስ አገሪቱ ወደ ብጥብጥና ለመውሰድ የመፈለግ ዝንባሌ ያላቸው ሃይሎች እንዳሉ የሚያሳይ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡ወጣቱም እያደገ የመጣውን የዴሞክራሲ መብቱን ተጠቅሞ ችግሮች በውይይት በመፍታት ሀገርን በዘላቂነት ከድህነት ለማወጣት በሚደረገው ጥረት ተሳትፎውን እንዲያጠናክር ጥሪ አቅርበዋል፡፡", "passage_id": "a6ca4708b61174afc2a9e0fb4c9c8efb" }, { "passage": "“ልዩነትን በማጥበብ የአንድነትን ድልድይ ለመገንባት ይሰራል” – አቶ አህመድ ሃሰን የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ዋና አስተዳዳሪከሚሴ፡-\nበሰሜን ሸዋና በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን አካባቢ የተፈጠረው ችግር ሁሉንም ያሳዘነ ነው:: ችግሩ ዳግም እንዳይደገም ራስን ለሰላምና ለፍቅር አሳልፎ መስጠት ትልቁ መፍትሄ ነው ሲሉ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት ዶክተር አምባቸው መኮንን ተናገሩ። ትናንት\nበከሚሴ አባገዳ አዳራሽ በተደረገው በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደርና በሰሜን ሸዋ አጎራባች ወረዳዎችና ህዝቦች የሰላምና የእህትማማችነት ጉባኤ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት ዶክተር አምባቸው መኮንን እንደተናገሩት፤ በአካባቢው የተፈጠረው ችግር የዜጎችን ህይወት የቀጠፈና በርካታ ንብረትን ያወደመ በመሆኑ ሁሉንም ያሳዘነ ነው። ይሁንና ችግሩን እያሰቡ ከመብሰልሰል ይልቅ ለፍቅርና ለሰላም እራሱን በመስጠት በይቅርታና ችግሩ እንዳይደገም መስራት ይጠበቃል ብለዋል። ‹‹ኢትዮጵያ\nበመቻቻልና በመተሳሰብ አቻ የሌላት ከሰማንያ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች ተቻችለው በሰላም የሚኖሩባት ቅድስትና ታላቅ ሀገር ነበረች። ሆኖም ባለፉት ዓመታት የተሰራውን መልካም የልማት ስራን ያህል የጎሰኝነት ትርክት በተለያየ መልኩ መሰራቱ ይህንን መልካም ገፅታ በሚያበላሽ መልኩ በህዝቦች መካከል መጠራጠርንና መከፋፈልን ፈጥሮ አልፏል። ለዚህም በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን አስተዳደርና በሰሜን ሸዋ ዞን አጎራባች አካባቢዎች የነበረው ችግር አንድ ማሳያ ነው። ዶክተር አምባቸው ይህን መሰል ችግር በመፈጠሩና በደረሰው ጉዳት ሁሉም ያዘነ መሆንኑ ገልጸዋል። ይሁን\nእንጅ ችግሩን እያሰቡ ከመብሰልሰል ይልቅ በይቅርታ ጉዳቱ ዳግም ችግር እንዳይፈጠር መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል። ዶክተር አምባቸው አክለውም ክረምት አንድ ጊዜ ቤትን በጎርፍ አንገላቶ ካለፈ በኋላ ቤት አይሰራለትም። ይልቁን በቀጣዩ ክረምት ድጋሚ ላለመጎዳት ዝግጅት ይደረጋል። በአካባቢው ለተፈጠረው ችግርም እንደዚሁ መስራት ያስፈልጋል። ምክንያቱም በችግሩ ወጥተው እስኪገቡ የሚናፈቁ ህፃናት እንደወጡ ቀርተ ዋል። እናቶች፣ አባቶችና አቅመ ደካሞች በማያውቁት ጉዳይ ተጎድተዋል። ስለዚህም\nሁሉም ብቻውን ይህንን እያሰበ ከመብሰልሰልና ከአቅም በላይ ለሆነ ችግር ከመጋለጥ ይልቅ እራስን ለፍቅር አሳልፎ በመስጠት በይቅርታ ችግሩ ድጋሚ እንዳይፈጠር መስራት ይገባል። ይህንን ማድረግ ለግል ሳይሆን ሀገርን፣ አረጋውያንን፣ እናቶችንና ህፃናትን የመታደግ ጉዳይ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል። የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ “ችግሮች እንዳይፈጠሩ… የሆኑት አቶ አህመድ ሃሰን በበኩላቸው የአማራና የኦሮሞ ህዝቦች አንድ የዘር ምንጭና የጋራ ስነልቦናና ታሪክ ያላቸው ናቸው። የኦሮሞ\nብሔረሰብ አስተዳደርዋ ከሚሴ የሁለቱ ህዝቦች የአብሮነት መገለጫ ናት። ህዝቦቿ ሀዘንና ደስታን አብረው ያሳለፉ ችግሮቻቸውንም በጋራ መክረው የተወጡ ናቸው። በቅርቡ በአካባቢው የተፈጠው ችግር መፈጠር የማይገባው ቢሆንም በቀጣይ እንዳይፈጠር መስራት እንደሚገባ ትምህርት ጥሎ ያለፈ ነው። አጥፊዎችንም ለህግ ለማቅረብ፣ የተዘረፉ ንብረቶችን ለማስመለስና የተጎዱ አካላትን ለመካስ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከርና ልዩነትን በማጥበብ የአንድነትን ድልድይ ለመገንባት ይሰራል ብለዋል።አዲስ\nዘመን ግንቦት 4/2011 በወንደሰን ሽመልስ", "passage_id": "6ee67fda3816f58ed1913d4a34026849" }, { "passage": "በኢትዮጵያ ዘላቂ ሠላም ለማስፈን አገር ተረካቢ ህጻናትን ስለ ሠላም መስበክና ማስተማር የሁሉም ድርሻ ሊሆን እንደሚገባ የሠላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል አሳሰቡ።በአገሪቱ ሠላም ለማስፈን የሚደረገውን አገራዊ እንቅስቃሴ የሚደግፍና በጉዳዩ ላይ የሚመክር የህጻናት ፓርላማዎች አገራዊ የሠላም ኮንፈረንስ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።ሚኒስትሯ ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት የሠላም መናጋት በአገር ህልውናና ሁለንተናዊ እድገት ላይ የሚያሳድረው ተጽዕኖ ከፍተኛ ነው።የህጻናትን ሰብዓዊ መብቶቻቸውን ከሚጥሱ፣ በትምህርታቸው፣ በጤናቸው፣ በስነ-ልቦናና አጠቃላይ እድገታቸው እንዲሁም ደህንነታቸውን ስጋት ላይ ከሚጥሉና መጻኢ ተስፋቸውን ከሚያጨልሙ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ችግሮች እንዲጠበቁ ማድረግም ግድ ይላል ነው ያሉት።ለዚህም የነገይቱ ኢትዮጵያ ተረካቢና አለኝታ የሆኑ ህጻናት ስለ ሠላም ፋይዳ እንዲረዱና የሠላሙ አንድ አካል እንዲሆኑ ማድረግ ቀዳሚ ተግባር ሊሆን ይገባል።ሠላምን በማስጠበቅና ለእሱም ዋስትና እንዲሰጡ ማድረግ ደግሞ የሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ሃላፊነት መሆን እንዳለበት ነው ሚኒስትሯ ያስገነዘቡት።የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ጉዳይ ሚኒስትሯ ወይዘሮ ያለምጸጋይ አስፋው በበኩላቸው የሠላም እጦት ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ተጎጂ እንደሚያደርግ ቢታመንም የመጀመሪያዎቹ ሰለባዎችና የችግሩ ገፈት ቀማሽ የሚሆኑት ህጻናትና ሴቶች ናቸው ብለዋል።ስለሆነም አገር ተረክበው ወደላቀ የስኬት ማማ የሚያደርሱ ህጻናት በዓለምና በአህጉር አቀፍ ደረጃ የተጎናጸፏቸውን መብቶች ‘ማረጋገጥ ይገባል’ ብለዋል።ሠላም የእድገትና ብልጽግና መሰረት በመሆኑ ሁሉም ህጻናትና የህጻናት ፓርላማዎች እንደ ዜጋ በየአካባቢያቸው ሠላም ለማስፈኑ ሂደት ትኩረት እንዲሰጡና ተሳትፏቸውን እንዲያጎለብቱ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑንም ገልጸዋል።ከተለያዩ ክልሎች የመጡ የህጻናት ፓርላማ ተወካዮችም ህጻናት በየአካባቢያቸው የሠላምን ፋይዳ እንዲገነዘቡ በማድረግና የአገራቸውን አንድነት በማስጠበቅ የድርሻቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።መሰል የሠላም ኮንፈረንሶች የነገ አገር ተረካቢ ህጻናትን አመለካከት የሚገነባና በመልካም ምግባር የሚቀርጹ በመሆናቸው ቀጣይነት እንዲኖራቸው ጠይቀዋል።“ሰላም ለህጻናት” በሚል መሪ ሃሳብ በተካሄደው አገራዊ የሠላም ኮንፈረንስ ከክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተወከሉ ከ1 ሺህ 200 በላይ የህጻናት ፓርላማዎች አመራሮችና አባላት ተሳትፈውበታል። (ኢዜአ)", "passage_id": "f779172f49d6fa355900526c1abf8c01" }, { "passage": "ከ43 በላይ የሚሆኑ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሳተፉበት የሀገራዊ መግባባት እና የእርቀ ሰላም ውይይት መድረክ ዛሬ ተካሂዷል፡፡ውይይቱ በወቅታዊ የሀገሪቱ የፖለቲካና የዴሞክራሲ እንቅስቃሴ በጋራ መምከርን ዓላማው ያደረገ ሲሆን በሀገሪቱ እየተስተዋሉ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ መሰራት እንደሚገባ በመድረኩ ተጠቁሟል፡፡አሁን የተገኘው የዴሞክራሲ እና የለውጥ ዕድል መጠቀም እንደሚገባ የተናገሩት የመድረኩ ተሳታፊዎች በሀገሪቱ እየተስተዋለ ያለውን ችግር ለመፍታት የተፎካካሪ ፓርቲዎች አስተዋጽኦ ጉልህ ድርሻ እንዳለው ገልጸዋል፡፡ለዚህም መፍትሔው የተፎካካሪ ፓርቲዎች ጠንካራ መሆንና ከብዛት ይልቅ ሶስት እና አራት በመሆን መደራጀት እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡አሁን ያለውን የብሔራዊ መግባባት እና ዕርቅ ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ መሰል መድረኮች በስፋት መዘጋጀት አለበት ተብሏል፡፡ይህንንም ለማድረግ በሚያስችል መልኩ እንደሚሰራ በውይይቱ ተነስቷል፡እንደ ሀገር የተጀመረውን ለውጥና በየአካባቢው የሚስተዋሉ ችግሮች ለመፍታት መንግስት ብቻውን መስራት እንደሌለበትና ችግሩን ለመፍታት የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ህዝቡ የተቀናጀ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለባቸው ተመልክቷል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ ምሁራን፣ የሀይማኖት ተቋማት ተወካዮች፣ የሲቪክ ማህበራትና ሌሎችም አካላት ተሳትፈዋል፡፡", "passage_id": "b4808e9aa12342339b37ebb926ebeb91" } ]
29d712cac4d423d41375aa922009ff02
d5376f65bc6405d807246889c3777dcb
በጎንደር የሚከበረውን የጥምቀት በዓል በደማቅ ሥነ- ሥርዓት ለማክበር የዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸው ተገለጸ
 መሃመድ ሁሴን አዲስ አበባ:- በጎንደር ከተማ የሚከበረውን የዘንድሮው የጥምቀት በዓል በደማቅ ሥነ ሥርዓት ለማክበር የዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን የጎንደር ከተማ አስተዳደር ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ አስታወቀ። በከተማዋ በሚደረገው ክብረ በዓልም የተለያዩ አዳዲስ አሰራሮችን ተግባራዊ ለማድረግ መዘጋጀቱን መምሪያው ገልጿል። በጎንደር ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ ኃላፊ አቶ አደባባይ ሙሉጌታ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ የዘንድሮውን የጥምቀት በዓል በታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ ባህላዊና ሐይማኖታዊ እሴቱን በጠበቀ መልኩ በደመቀ ሁኔታ ለማክበር አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉንና የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀዋል። የጥምቀት በዓል በሰላምና በደመቀ ሁኔታ እንዲከበር የተለያዩ ኮሚቴዎች ተቋቁመው እየሰሩ መሆናቸውን የገለጹት አቶ አደባባይ በጸጥታ፣ በእንግዳ አቀባበል፣ በባህልና ቅርስ ትውውቅ በቂ ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል። ከበዓሉ ዝግጅት ስራዎች ቀዳሚው ስራ የጥምቀተ ባህሩን ቦታ የማስተካከል ጉዳይ መሆኑን የጠቀሱት አቶ አደባባይ፤ ከዚህ አንጻር የቦታው የእድሳት ስራ መቶ በመቶ ተከናውኖ ውኃ የመሙላት ስራው ዛሬ እንደሚጠናቀቅና ለበዓሉ ዝግጁ እንደሚሆን አስታውቀዋል። እንደ አቶ አደባባይ ገለጻ፣ በበአሉ እለት የሚፈጠረውን መጨናነቅ ለመቀነስና ታዳሚው በጥምቀተ ባህሩ ዙሪያ ሳይጨናነቅ መስተናገድ እንዲችል የተለያዩ አዳዲስ አሰራሮች ተግባራዊ ተደርገዋል። ከእነዚህ መካከልም ታዳሚው ከአጥር ውጪ ሆኖ የበዓሉን ክዋኔ መከታተል እንዲችል በአራት አቅጣጫዎች ሰፋፊ ማሳያ ስክሪኖች ተዘጋጅተዋል። ከሀገር ውስጥም ሆነ ከተለያዩ የዓለም ሀገራት ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተው የሚታደሙ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ለእነዚህ እንግዶች ማስተናገጃ የሚሆንና ቅርሱን በማይጎዳ መልኩ ተነቃቅለው የሚሰበሰቡና መወገድ የሚችሉ ደህንነታቸው አስተማማኝ የሆኑ የብረት ማያዎች ተሰርተዋል። በመሆኑም የመጡት እንግዶች በቀጥታ ሐይማኖታዊ ክዋኔውን ያለስጋት መከታተል እንደሚያስችላቸውም ነው ያስረዱት። በዩኒስኮ በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበውን የጥምቀት በዓል ባህላዊ እሴቱን ጠብቆና እሴት በሚጨምር መንገድ ማክበር ያስፈልጋል ያሉት ኃላፊው፤ ይህን ታሳቢ በማድረግ ለጥምቀተ በዓሉ መዳረሻ ከጥር አንድ እስከ ዘጠኝ ድረስ የበዓል ሳምንት ተከብሯል። ለጎንደር ከተማ ሰላም ውሎ ማደርና ለመልካም አስተዳደሯ የሚሰሩና እየሰሩ የሚገኙ ታላላቅ ሰዎች፣ ወጣቶችና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችም የጥምቀት በዓል በሰላም ያለአንዳች ስጋት እንዲከናወን የተሰለፉ በመሆናቸው ምስጋና ይቸራቸዋል ነው ያሉት ሃላፊው። በክብረ በዓሉ ላይ ከ200 ሺህ በላይ ታዳሚዎች ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የጠቀሱት አቶ አደባባይ፤ ንግድና ባዛርን ጨምሮ በርካታ ትዕይንቶች የሚከወኑበት ሆኖ በዓለ ጥምቀቱ በደመቀ ሁኔታ መልካም ትዝታን ጥሎ እንዲያልፍ በትኩረት መሰራቱንም አክለው ተናግረዋል። በባለፈው አመት በጎንደር ከተማ በተከበረው የጥምቀት በአል በጥምቀተ ባህሩ አካባቢ ከእንጨት የተሰራ ማማ ተደርምሶ በታዳሚዎች ላይ ጉዳት ማድረሱ ይታወሳል።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=39628
[ { "passage": "11ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ቅድመ ዝግጅት በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ተመለከተ፡፡የበዓሉ አስተናጋጅ የሆነችው ሐረር ከተማ በዓሉን በድምቀት ለማክበር የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን እያከናወነች መሆኑን ፌዴሬሽን ምክር ቤት ገልጿል፡፡የሐረሪ ክልላዊ መንግስት ለበዓሉ ዝግጅት ተገቢውን ትኩረት በመስጠት አዳራሾችና የእንግዶች ማረፊያ የመሳሳሉ ቤቶችን የማዘጋጀት ሥራ እያከናወነ እንደሆነ የምክር ቤቱ አፈ ጉባዔ አቶ ያለው አባተ ለዋልታ ገልፀዋል፡፡በተለይም ከተማዋ ብዙ ሰው ማስተናገድ የሚችል አዳራሽ እንዳልነበራት አስታውሰው አሁን በዓሉን ምክንያት በማድረግ ትልቅ አዳራሽ እየተገነባ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡በከተማዋ የሚገኙ ሆቴሎች ውስን መሆናቸውን አፈ ጉባዔው ጠቁመው አሁን ላይ በርካታ ሆቴሎች መገንባታቸውን ጨምረው ገልፀዋል፡፡ የበዓሉ ሥነ ሥርዓት የሚከበርበት ስታዲየምም እየተዘጋጀ ነው፡፡የከተማዋ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ግንባታ፤ የፅዳትና የውበት ሥራዎችም በስፋት መከናወናቸውን አቶ ያለው ተናግረዋል፡፡ በዚህ በኩል ህብረተሰቡም በስፋት መሳተፉ ነው የተመለከተው፡፡ክልሉ በዓሉን በተለያዩ የልማት ሥራዎች ለማክበር የጀመራቸው ሥራዎችም በተያዘላቸው ዕቅድ መሰረት እየተከናወኑ ናቸው ብለዋል- አፈ ጉባዔው፡፡በ2010 ዓ.ም ግንባታውን ለማጠናቀቅ እየተገነባ የሚገኘው ትልቅ ሪፈራል ሆስፒታል ቀደም ብሎ በማጠናቀቅ ከተቻለም በበዓሉ ቀን ለማስመረቅ ግንባታው እየተፋጠነ ይገኛል፡፡የወጣት ማዕከላትና የፖሊስ ጣቢያዎችን የመሳሰሉ የተለያዩ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ግንባታም ተከናውኗል፡፡በክልሉ በዓሉን ምክንያት በማድረግ የተገነቡትና የተከናወኑት የልማት ሥራዎች ከ10 ዓመት በኋላ ሊከናወኑ የሚችሉ እንደነበር አቶ ያለው ይናገራሉ፡፡ በመሆኑም በዓሉ ልማትን ለማፋጠንም ጉልህ ሚና እንደሚያበረክት አስረድተዋል፡፡ቀደም ሲል በዓሉን ያስተናገዱ ክልሎችም ከፍተኛ የልማት ሥራዎችን በስፋት ማከናወናቸውን አስታውሰዋል፡፡የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔን ጨምሮ የተለያዩ አካላት የክልሉን የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በቅርቡ መጎብኘታቸው ይታወሳል፡፡", "passage_id": "2c13701337655bd36bfd507d83dbbaa3" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 14፣ 2013(ኤፍቢሲ) ዓመታዊው የቁልቢ ገብርኤል የንግስ በዓል በሠላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን የምስራቅ ኢትዮጵያ የፀጥታ አካላት አስታወቁ፡፡የሀረሪ ክልል፣ የድሬዳዋ አስተዳደር፣ የምስራቅና ምዕራብ ሐረርጌ ዞኖች የፖሊስ ኮሚሽኖችና የአስተዳደርና የፀጥታ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የፌደራል ፖሊስና የሃገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ታህሳስ 19 ቀን 2013 ዓ.ም በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ሜታ ወረዳ በቁልቢ ከተማ የሚከበረው የቁልቢ ገብርኤል ዓመታዊ የንግስ በዓል ያለምንም የፀጥታ ችግር በሠላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ የሚያስችል ውይይት አድርገዋል፡፡የፀጥታ አካላቱ በዓሉን ለማክበር ከሃገር ውስጥና ከውጭ ሃገራት የሚመጡ የእምነቱ ተከታዮችና ጎብኚዎች በዓሉን በሠላም አክብረው ወደ መጡበት እንዲመለሱ በጋራ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል፡፡ምዕመናኑ ወደ ንግስ በዓሉ ሲመጡ የሰዎች መጨናነቅ በሚበዛባቸው በደብሩ መግቢያና መውጫ በሮች፣ በክርስትና ቤትና በስለት ማስገቢያ እንዲሁም በቤተ መቅደሱ በሮችና በአጠቃላይ በዓሉ በሚከበርበት አካባቢ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ መጠቀምና አካላዊ ርቀትን መጠበቅ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡በዓሉ የሚከበርበት አካባቢም የመሬቱ አቀማመጥ ዳገታማ፣ ቁልቁለትና ጠመዝማዛ መንገዶች የሚበዙበትና የንግስ በዓሉን ለማክበር በርካታ ተሸከርካሪዎች ወደ ስፍራው የሚመጡ በመሆኑ አሽከርካሪዎች በከፍተኛ ጥንቃቄ ማሽከርከር እንደሚኖርባቸውና ከታህሳስ 18 ቀን 2013 እስከ ታህሳስ 19 ቀን ከሰዓት በኋላ ድረስ ከጨለንቆ ከተማ እስከ ቀርሳ ባለው ዋና መንገድ ላይ ከባድ ተሸከርካሪዎች ማለፍ እንደማይችሉና ሌሎች ተሸከርካሪዎችንም አቁሞ መሄድ የተከለከለ መሆኑ በውይይቱ ወቅት ተጠቅሷል፡፡በዓሉን ለማክበር የሚመጡ ምዕመናንና ጎብኚዎችም የኮሮና ቫይረስን ከመከላከል ጎን ለጎን የግል ንብረቶቻቸውን፣ ጌጣጌጥና ገንዘብ በጥንቃቄ ሊይዙ እንደሚገባ ጥሪ ተላልፏል፡፡የወንጀል ድርጊትቶች ተፈፅመው ሲገኙም አፋጣኝ ውሳኔ ለመስጠት በአካባቢው ጊዜያዊ ፍርድ ቤት እንደሚቋቋምና ፈጣን ውሳኔ እንዲሰጥ እንደሚደረግ ተጠቁሟል፡፡ፀረ ሠላም ኃይሎች በንግስ በዓሉ ወቅት ችግር እንዳያደርሱ የፀጥታ አካላት ከሚያደርጉት የተጠናከረ ጥበቃ ጎን ለጎን ህብረተሰቡ የአካባቢውን ደህንነት በንቃት እንዲጠብቅና አጠራጣሪ እንቅስቃሴዎችን ሲመለከት በአቅራቢያው ለሚገኙ ፀጥታ አካላት ጥቆማ እንዲሰጥም ጥሪ ቀርቧል፡፡የቁልቢ ገብርኤል ሃይማኖታዊ የንግስ በዓል በዓመት ሁለት ጊዜ ታህሳስ 19 እና ሐምሌ 19 ቀን በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የእምነቱ ተከታዮችና ጎብኚዎች የሚታደሙበት ሃይማኖታዊ ክብረ በዓል ነው፡፡በተሾመ ኃይሉከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!", "passage_id": "0a3260c9edc4a0ef9508b73781195474" }, { "passage": "ጎንደር:- በጎንደር ከተማ በጥምቀት በዓል ከ460 ሚሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ መታቀዱ የከተማ አስተዳደር አስታወቀ፡፡ ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት የጥምቀት በዓል ላይ ለመታደም ጎንደር ገብተዋል። የከተማ አስተዳድሩ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ሀላፊ አቶ አስቻለው ወርቁ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ በበዓሉ ምክንያት በከተማዋ ከሚገኙ ጎብኝዎች በአገልግሎት ሰጪዎች 450\nሚሊዮን ብርና ለመንግስት ከቲኬት ሽያጭና ሌሎች ገቢዎች 10 ሚሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል። በከተማው ከጥር 3 እስከ 9 ቀን 2012 ዓ.ም በተካሄደው የባህል ሳምንት፤ ሙዚቃና ቴያትርን ጨምሮ በርካታ የኪነጥበብ ስራዎች የቀረቡ ሲሆን የጎንደር አካባቢ ባህላዊ ምግብና መጠጥም ለእይታ ቀርቦ በበርካቶች መጎብኘቱንና በዚህም የቱሪስት ፍሰቱን ለመጨመር የራሱ ድርሻ እንዳበረከተ አቶ አስቻለው ተናግረዋል።በዘንድሮው የጥምቀት በዓል ቀደምት ነገስታት ለህዝባቸው ይከውኑት የነበረውን የግብር ማብላት ስነስርዓት ለማስታወስና የጎብኝውን ቁጥር ለማሳደግ በአፄ ፋሲል ቤተመንግስት ጥሪ ለተደረገላቸው እንግዶች የንጉስ እራት የተዘጋጀ ሲሆን፤ የነገስታትን ክዋኔ የሚያሳይ ህይወት በአብያተ መንግስት የሚል ትወናም ዛሬ በቦታው ለእይታ እንደሚቀርብ አቶ አስቻለው ተናግረዋል። በከተማዋ ቱሪስቶች ደረጃውን የጠበቀና የተሟላ አገልግሎት እንዲያገኙ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የተሰራ ሲሆን፤ የውጪ ጎብኝዎች አማካይ የቆይታ ጊዜ ከአንድ ቀን ወደሁለት ቀን፣ እንዲሁም የሀገር ውስጥ ጎብኝዎች ከሁለት ወደ ሶስት ቀን ከፍ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ሀላፊው ተናግረዋል።በያዝነው ጥር ወር\nብቻ ከ30 ሺህ\nበላይ የውጪ ሀገር\nጎብኝዎች የጥምቀት በዓልን\nምክንያት በማድረግ ጎንደርን\nእንደሚጎበኙ የተናገሩት ሀላፊው በኮንፈረንስ ቱሪዝም፤ በሀይማኖት፣ በስፖርት እና ሌሎች ዝግጅቶች የሚታደሙ የሀገር ውስጥ ጎብኝዎችም ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን ገልፀዋል።በጎንደር እየተከበረ ባለው\nየዘንድሮው የጥምቀት በዓል\nከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣\nየሀይማኖት አባቶች፣ የዲፕሎማቲክ\nማህበረሰብ አባላት፣ የዩኔስኮ ተወካዮች፣\nጥሪ የተደረገላቸው ኤርትራውያን\nእንግዶች፣ ጎብኝዎች እና\nየእምነቱ ተከታዮች ተገኝተዋል።\nበክብረ በዓሉ ላይ\nከ 2 ሚሊዮን በላይ\nእንግዶችና ምዕመናን በመታደም\nላይ ሲሆን ሁነቱን\nለመዘገብ ከአገር ውስጥና\nከውጪ የሚዲያ ተቋማት\nየተውጣጡ ከ90በ\nላይ ጋዜጠኞች በቦታው\nመገኘታቸው ተጠቁሟል፡፡ የጥምቀት በዓል በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት /ዩኔስኮ/ በማይዳሰስ የአለም ቅርስነት ከተመዘገበ በኋላ ዛሬ ለመጀመሪያ ጊዜ በመከበር ላይ ሲሆን ይህም ለበዓሉ የተለየ ድባብ አላብሶታል፡፡ዘንድሮ በልዩ ድምቀት እየተከበረ ባለው የጥምቀት በዓል ላይ ለመታደም የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ተመሥገን ጥሩነህ፣ የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ዑማ፣ ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ ዝናሽ ታያቸው እና ሌሎች የፌዴራልና የክልል የሥራ ኃላፊዎች ጎንደር መግባታቸው ተገልጿል፡፡ አዲስ\nዘመን ጥር 11/2012ድልነሳ ምንውየለት ", "passage_id": "44406d9b52fb69841f9b44e05a4fb711" }, { "passage": " ክፍለዮሐንስ አንበርብርጎንደር፡- የጥምቀት በዓል አከባበር፣ ከተራና አጠቃላይ ድባብ ውበት የተላበሰ እና ለቱሪስቶች ምቹ መስህብ መሆኑን ጥምቀትን በጎንደር የታደሙ የውጭ አገር ቱሪስቶች አስታወቁ።የጋዝጣው ዝግጅት ክፍሉ ካናገራቸው የውጭ አገሮች ዜጎች መካከል ከፈረንሳይ እውቅ ከሆኑ መፅሔቶች ሉፊጋ የሚሰራው ጋዜጠኛ ፓስካል ሜት እንዳስታወቀው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ባለው ነባራዊ ሁኔታ ጥምቀትን መታደም አደገኛ እንደነበር ቢነገረውም ጥምቀት በጎንደር ለማክበር መጥቷል፤ በሀገሪቱ ያለው እውነታ በውጭው ዓለም እና በመገናኛ ብዙኃን የተናፈሰውን ያክል እንዳልሆነ መታዘብ ችሏል።‹‹እኔ ጋዜጠኛ ነኝ። መረጃዎችን እጠይቃለሁ፤ አነባለሁ። በዚህም የተነሳ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ ተረድቻለሁ። እስካሁን በሠላም እየተንቀሳቀስኩ ነው፤ የተለየ ነገር አልተመለከትኩም›› ብሏል። የከተራ በዓልና ጥምቀት በዓል ትልቅ የቱሪስት መስብ እንደሆነም ጠቁሟል።ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ የሚሰራው ጋዜጠኛ ሮቢ ኮሪ በበኩሉ፤ ኢትዮጵያ የደማቅ ቅርስ ባለቤት ስለመሆኗ እና ከእነዚህም ውስጥ ጥምቀት አንዱ መሆኑን አመልክቷል። በጎንደር የተከበረው የከተራ እና ጥምቀት በዓል ከሥርዓተ ቅዳሴው እስከ ጥምቅተ ባህር ያለው ሁነት፣ ከባህረ ጥምቀቱ ዙሪያ የቀሳውስቱ ዝማሜ እና በበዓሉ ላይ የሚስተዋለው መንፈሳዊ ሥርዓትና የበዓሉ ታዳሚዎች ሁነት ለፀሐፊዎችና ተመራማሪዎች ብዙ ዕድል የሚሰጥ ነው። ለመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ዘገባም ድምቀት የተሞላበት በዓል መሆኑን መረዳት መቻሉን ጠቁሟል።ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አፍሪካ የመጣችውአሜሪካዊቷ አሽሊ ሄርናንዴዝ፣ የጥምቀት በዓልን በጎንደር መታደሟ ልዩ ስሜት እንደፈጠረባት ገልጻለች። የሕዝቡ በአንድነት መሰባሰብና በህብረ ቀለማት ያሸበረቁ አልባሳት ተውበው ወደ በዓሉ ስፍራ መትመማቸው በእጅጉ አስደናቂ መሆኑንና በሀገረ አሜሪካ ከሚከበሩ ሕዝባዊም ሆኑ ሃይማኖታዊ በዓላት የተለየ መሆኑን ጠቁማለች። ጥምቀት ጥሩ ለዛ ያለው በዓል ሲሆን የልጃገረዶቹ እና ወጣቶች አለባበስ፣ የሥርዓተ ጥምቀቱ ሂደትና አጠቃላይ የከተራ አከባበር የተለየ ስሜት እንደሚሰጥና በርካታ የውጭ አገር ቱሪስቶችን ለመሳብ የሚያግዝ ማራኪ በዓል መሆኑን አመልክታለች። በአሜሪካ በርካቶች ባተሌ ስለሆኑ በዓላትን ከቤተሰቦቻቸው ጋር የማክበር ልምድ እንደሌላቸውና የኢትዮጵያውያን ግን ማህበራዊ ሕይወታቸው የተጠናከረ መሆኑን ተናግራለች። ኢትዮጵያ ከመምጣቷ በፊት ስለ ሀገሪቱ የተሟላ መረጃ እንዳልነበራትና ከመጣች በኋላ ግን የተለየና ጉጉት የሚፈጥር ሕይወት ማየት እንደቻለች አሽሊ አብራርታለች። ፖላንዳዊ ቱሪስት ሚስተር ካሮል ኩስካ፤ ሥርዓተ ጥምቀቱ የሚከናወንበትና የፋሲለደስ ታሪካዊ ግንብና የጥምቀት በዓል መታደሙ ልዩ ስሜት እንደፈጠረበትና ቀጣይ የሰሜን ተራራችን የመጎብኘት እቅድ አለው። በቀጣይ አንድ ሣምንት የተለያዩ የኢትዮጵያ ታሪካዊ እና ባህላዊ እሴቶችን የመጎብኘት ውጥን እንዳለውም ጠቁሟል። በተንቀሳቀሰባቸው አካባቢዎች ፈገግታ የተሞላ ፊት ማየቱ ደግሞ የተለየ ስሜት እንደፈጠረለት አመልክቷል። በቀጣይም ኢትዮጵያን በድጋሜ የመጎብኘትና ጓደኞቹን የመጋበዝ ፍላጎት እንዳለው፤ ስለ ኢትዮጵያም የተቻለውን የማስተዋወቅ ፍላጎት እንዳደረበት ገልጿል።አዲስ ዘመን ጥር 13/2013", "passage_id": "8346729445f3cfd45414739c63bf16ee" }, { "passage": " ኮቪድ 19 እና የፀጥታ ሁኔታ ከፍተኛ ትኩረት ተደርጎባቸዋል በዘንድሮ የጥምቀት በዓል በጎንደር  ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የአገር ውስጥ ቱሪስቶች ይታደማሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የከተማዋ አስተዳደር መንግስት ኮሙሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሀላፊ አቶ ቻላቸው ዳኘው ተናገሩ፡፡በዓሉ ኮቪድ-19 በተሰራጨበት ወቅት እንደመከበሩና መንግስት ህግን ለማስከበር እየወሰደው ባለው እርምጃ ምክንያት፣ የፀጥታውና የጤናው ጉዳይ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ እንደሆነ አቶ ቻላቸው አስረድተዋል፡፡የጥምቀት በዓል የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴርና የጤና ሚኒስቴር ባወጡት የበዓል አከባበር ፕሮቶኮል መሰረት የሚከናወን ሲሆን የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስርጭት እየተከላከሉ በዓሉን በጥንቃቄ ለማክበር ከተማ አስተዳደሩ ከሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት ጋር  በቅንጅት እየሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ለበዓል አከባበሩ አንድ አብይ ኮሚቴና 8  ንዑሳን ኮሚቴዎች የተዋቀሩ ሲሆን፣ ኮሚቴዎቹ ከቤተ-ክህነት፣ከጤናው፣ከባህልና ቱሪዝም፣ ከፀጥታ አካላትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት ነውም ተብሏል፡፡ሀላፊው የፀጥታውን ጉዳይ በተመለከተ ሲያበራሩ፤ ጎንደር በህወሃት የጥፋት ሀይል ትኩረት የተደረገባት ከተማ የነበረች ቢሆንም ባለው ጠንካራ የፀጥታ መዋቅር ጉዳት ሳይደርስ መከላከል መቻሉንና በተላላኪነት እዚሁ ከተማ ሆነው ሲንቀሳቀሱ የነበሩትን በቁጥጥር ስር በማዋል መቻሉን ተናግረዋል።ለጥምቀት ህዝቡ ከተለያየ የአገሪቱ ክፍል በመምጣት በሰላም አክብሮ እንዲመለስ፣ ለፀጥታና ደህንነት ሁኔታ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ በመሆኑ ምንም የሚያሰጋ ነገር እንደሌለ ሃላፊው ገልፀዋል፡፡የኮቪድን ጉዳይ በተመለከተም በከተማ አስተዳደሩና በባለ ድርሻ አካላት ድጋፍ የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘርና የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል በተለይ ወደ ጥምቀተ ባህሩ ግቢ እንዲገቡ ለተፈቀደላቸው መዘጋጀቱንና ጠንካራ ወጣት አስተባባሪዎችን በመመደብ በዓሉን በሥርዓትና ያለ ስጋት ማክበር እንዲቻል ከፍተኛ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አቶ ቻላቸው ተናግረዋል፡፡ዘንድሮ በኮሮና ምክንያት የውጭ ቱሪስቶች ብዙ ባይጠበቁም፣ ከተለያዩ የአገሪቷ ክፍሎች ከ500 እስከ 600 ሺ ታዳሚ እንደሚመጣ ታሳቢ በማድረግ ለእንግዶቹ የሚመጥን ቅደመ ዝግጅት እየተደረገ በመሆኑ ሁሉም ጎንደር ላይ መጥቶ ደማቁን የጥምቀት በዓል በሰላምና በደስታ እንዲያከብረው ጥሪ አቅርበዋል አቶ ቻላቸው ዳኘው፡፡  ", "passage_id": "2651e427cb63cd6d4bbc4fb88a2e4a7c" } ]
793ba569bc9b868b09cf568104ef615d
0144761f9d48be2d7cb0bc3e1190105e
የሃገር ፍቅር ያጀገነው ወታደሩ ኦሊምፒያን
ብርሃን ፈይሳየኢትዮጵያ አትሌቲክስንና ድልን ያወዳጃቸው ጀግናው አትሌት ሻምበል አበበ ቢቂላ ይሁን እንጂ፤ የድሉን ቀጣይነት ያወጀው ሌላኛው ወርቃማ አትሌት ሻምበል ማሞ ወልዴ ነው። ማሞ የአበበን ፈለግ ተከትሎ ሃገሩ የለመደችው እንዳይጎድልባት በላቡ ክብሯን አድምቋል፤ ኢትዮጵያዊያን በቀላሉ የማይደፈሩ ጀግኖች መሆናቸውንም ለዓለም አረጋግጧል፡፡ የአሸናፊነት ወኔው ሳይሸረሸር ውጣ ውረዶችን ተሻግሮ የሃገሩን ክብር እንዳስጠበቀ ያለፈ፤ ገድሉም ከኢትዮጵያ የጀግኖች መዛግብት በወርቅ ቀለም የሰፈረ ነው፡፡ ይሁን እንጂ እስካሁንም የሚገባውን ያህል ክብርና ሙገሳ አላገኘምና አዲስ ዘመን በዛሬው የስፖርት ማህደር አምዱ ሊያስታውሰው ወደደ፡፡ ከሰነድ የተገኙ መረጃዎችና ልጁ ሳሙኤል ማሞ ወልዴ ከጋዜጣው ጋር በነበረው ቃለ ምልልስ ስለ ጀግናው አባቱ ያነሳቸው ሃሳቦች ተዋህደው እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡ የማሞ ትውልድ በ1924 ዓ.ም ቀድሞ ሸዋ ክፍለ ሃገር ተብሎ በሚጠራው አድአ ወረዳ ድሬድሌ በሚባል ቀበሌ መሆኑን የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ‹‹ኢትዮጵያ በኦሊምፒክ›› በሚል ርዕስ ባሳተመው መጽሄት የሰፈረው የህይወት ታሪኩ ያስነብባል፡፡ እድገቱ ከብት በመጠበቅ፣ እድሜው ሲገፋም እርሻ በማረስ፣ ቆቅ፣ ጅግራ እና ሚዳቋ አድኖ በመሸጥም ነበር፡፡ በአንድ ዕለት ግን ታዳጊው ማሞ እንደ አጎቱ የሚያያቸው ዘመዱ ሊጠይቋቸው መምጣታቸውን ተከትሎ የህይወቱ አቅጣጫ ተለወጠ፡፡ የክቡር ዘበኛ አባል የሆኑት ዘመዱ በለበሱት የደንብ ልብስ በመማረኩ ወደ አዲስ አበባ ወስደውት ውትድርና እንዲያስቀጥሩት ጥያቄ ያቀርብላቸዋል፡፡ እርሳቸው ለጥያቄው የሽንገላ መልስ ቢሰጡትም ልቡ የሸፈተው ማሞ ግን ቀን ጠብቆ በእግሩ ወደማያውቃት አዲስ አበባ ነጎደ፡፡ ያሰበው ተሳክቶም በ1943 ዓ.ም የክብር ዘበኛ አባል በመሆን በልጅነት ልቡ የተማረከለትን የደንብ ልብስ ለመልበስ በቃ፡፡ ለሁለት ዓመታት በኮሪያ የነበረውን ተልዕኮ ፈጽሞ ከተመለሰ በኋላም በአየር ኃይል ግቢ ውስጥ በሚዘጋጀው የሩጫ ውድድር ላይ በማራቶን ተሳትፎ፤ ሻምበል አበበ ቢቂላን ተከትሎ በሁለተኛነት ውድድሩን አጠናቀቀ፡፡ ውጤቱ ታላቅ ተስፋ በማሳደሩም የአትሌቲክስ ስልጠና እንዲከታተልና በሃገር ውስጥ ውድድሮችም እንዲካፈል መንገዶች ተከፈቱለት። በየወቅቱ የሚያስመዘግባቸው ውጤቶችም ለሜልቦርን ኦሊምፒክ ተሳታፊነት አሳጨው፡፡ ሻምበል ማሞ ወልዴ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በተሳተፈችበት የሜልቦርን ኦሊምፒክ (እአአ 1956) ተሳታፊ ከነበሩት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት መካከል አንዱ እንዲሆን አስቻለው። የተወዳደረውም በሶስት ርቀቶች ማለትም በ4 በ400ሜትር፣ 800 ሜትር እንዲሁም 1 ሺ 500 ሜትር ነበር፤ ሆኖም እንደሌሎች ተሳታፊዎች ሁሉ ውጤት ሊያስመዘግብ አልቻለም፡፡ የዚያን ጊዜ የአባቱን ሁኔታና ወቅቱን የሚያስታውሰው ሳሙኤል ማሞ ወልዴ፤ ለውጤት እጦት አንዱ ምክንያት የነበረው ወደ አውስትራሊያ ይደረግ የነበረው ጉዞ ስምንት ቀናትን ለመሄድና ለመመለስ ሌላ ስምንት ቀናትን የሚጠይቅ መሆኑን ነው። በጉዞ ላይ የነበረው ድካም ለውጤት ሊያበቃ የሚችል አልነበረምና፡፡ ከአራት ዓመታት በኋላም እስካሁንም በህያውነት የዘለቀ ታሪክ የተጻፈባት ተረኛዋ የኦሊምፒክ አዘጋጅ ሮም (እአአ 1960) መሰናዶዋን አጠናቀቀች፡፡ ኢትዮጵያ በሁለተኛው የኦሊምፒክ ተሳትፎዋ በማራቶን የመጀመሪያውን ሜዳሊያ ከማስመዝገቧም በላይ ውድድሩ ከተካሄደባት ሃገርና ከአበበ ቢቂላ የባዶ እግር ሩጫ ጋር ተያይዞ የዓለም መገናኛ ብዙሃን መነጋገሪያና የጋዜጦች አርዕስትም ሆና ነበር፡፡ የዚህ ታሪክ አካል ለመሆን በዝግጅት ላይ የቆየውና ሃገሩን ዳግም በሌላ ድል ሊያኮራ የተዘጋጀው የክቡር ዘበኛው ወታደር ማሞ ግን ተሳታፊ የመሆን እድሉን ሊያገኝ አልቻለም። ለሃገሩ ሜዳሊያ ለማስመዝገብ የነበረው ህልም እንዳይሰምር ምክንያት የሆነው ደግሞ በሰላም አስከባሪነት ወደ ኮንጎ ይዘምታል በሚል ከቡድኑ ጋር ባለመጓዙ እንደነበር የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሰሞኑን ‹‹የባዶ እግር ትሩፋቶች›› በሚል ርዕስ ባወጣው መጽሄቱ ያስነብባል፡፡ በቀጣዩ የቶኪዮ ኦሊምፒክ (እአአ 1964) ማሞ የቡድኑ አባል በመሆን በ10ሺ ሜትር ውድድሩን አድርጎ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ሩጫውን ሲመራ ቆይቶ ኩርባ ላይ ተገፍቶ ወድቆ ባቱ በመቁሰሉ ወርቃማው ድል ዳግም ሊያመልጠው ችሏል፡፡ የኦሊምፒክ ወርቅና ሃገሩን በክብር የማስጠራት መሻት እንዲሁም የኦሊምፒክ መንደር ናፍቆቱ ያልወጣለት ወታደሩ አትሌት ሌላ አራት ዓመት ጠብቆ የስፖርት አውድ ፍልሚያውን ከማድረግ ወደኋላ አላለም፡፡ ነፍሱ በማይዳፈን የሃገር ፍቅር ስሜት ነዷልና፤ የሃገሩን ዳር ድንበር ከመጠበቅና ሉዓላዊነቷን ከማስከበርም አልፎ ሃገሩን በክብር ማስጠራት ፍላጎቱ ነበር፡፡ ለዚህም ዝግጅቱን አጠናክሮ በመቀጠል በሜክሲኮ ኦሊምፒክ (እአአ 1968) ዳግም በሃገሩ መለያ ቀረበ፡፡ አስደናቂው ጉዳይ ደግሞ ተሳትፎውን በአምስት ቀናት ልዩነት በመም እና በጎዳና ላይ ርቀቶች ማድረጉ ነበር፡፡ በወቅቱ በአትሌቲክስ ስፖርት በተለይ በማራቶን ስሙ በዓለም ዙሪያ ከናኘው የሃገሩ ልጅ ሻምበል አበበ ቢቂላ ጋርም በአንድነት ተሰለፉ፡፡ ውድድሩም እንደተለመደው በአበበ አሸናፊነት እንደሚያልቅ ቅድመ ግምት አግኝቶ መካሄድ ቢጀምርም እንደተጠበቀው ሊቆይ የቻለው እስከ ርቀቱ አጋማሽ ነበር፡፡ ምክንያቱ ደግሞ እጅግ ተጠባቂውና የአትሌቲክስ ወዳጆችን ቀልብ የገዛው አበበ በጉዳት ምንያት 42 ኪሎ ሜትሩን መሸፈን ባለመቻሉ አቋርጦ መውጣቱ ስለተሰማ ነው፡፡ ይህ ለሌላው ዓለም ህዝብ አስደንጋጭ፤ ለተፎካካሪዎቹ ደግሞ ምናልባትም መልካም ዜና ሊሆን ይችላል፡፡ ጀግኖችን ማፍራት ለማይነጥፍባት ምስራቅ አፍሪካዊቷ ሃገር ኢትዮጵያ ግን ስጋት አልነበረም፡፡ ጥንትም ጀግናን በጀግና የመተካት ልማድ አላትና የአንደኛው ልጇ ጉዳት በሌላኛው ድል የሚተካ መሆኑን በማመንና በልበ ሙሉነት እንደጸናች ነበር፡፡ የተጠበቀው አልቀረም፤ ሌላኛው አትሌት ማሞ ወልዴ የሩጫውን የመጨረሻ መስመር ቀድሞ ረገጠ፡፡ ታሪክን ከስሩ ማወቅ መልካም ነውና በጊዜው የሆነውን የአባቱን ገድል ልጅ ሳሙኤል ወልዴ እንዲህ ይተርካል። ‹‹ማሞ በሩጫው ላይ ሳለ ለየት ያለ እንቅስቃሴ ይመለከታል፤ ይኸውም ከአበበ ውጪ የአሸናፊነት ግምት የተሰጣቸው የሌሎች ሃገራት ሯጮች ሲደሰቱ መመልከቱ አንዳች ጥርጣሬ አሳደረበት። የተፈጠረውን በውል ባለመረዳቱም ሩጫውን ይቀጥላል፤ በዚህ መሃል ግን ሰለሞን ተሰማ የተባለው እውቅ ጋዜጠኛ በጭነት መኪና ሆኖ ስሙን ይጠራዋል፡፡ እንዲህም ይለዋል ‹‹ማሞ ዛሬ ለሃገርህ ታሪክ ስራ፤ አበበ አቋርጦ ወጥቷል››፤ ይሄኔ ታዲያ ኢትዮጵያዊው የአልሸነፍ ባይነት ወኔው ተነሳስቶ በእልህ ለአሸናፊነት በቅቷል፡፡›› ሌላኛው ድል ሲደገምም በክብር የተውለበለበው ባንዲራ አልወረደም ነበር፡፡ ለሰሚ አስደናቂ የሆነው በአንድ ኦሊምፒክ ሁለት የረጃጅም ርቀት ድሎችን ማጣጣም የወሰደው የቀናት ልዩነት ብቻ ነበር፡፡ የስፖርቱ ዓለም አዲስ ክስተት የ10ሺ ሜትር ውድድር በተደረገበት ዕለት የሆነም ነበር፡፡ በዚህ ርቀት ከቀረቡት ተወዳዳሪዎች መካከል አንዱ ኢትዮጵያዊው የማራቶን ባለ ድል ሻምበል ማሞ ወልዴ ነበር፤ የውድድሩ ማስጀመሪያ ድምጽ እንደተሰማ አትሌቶቹ ወደፊት መትመም ጀመሩ፡፡ ጥቂት ሜትሮችን እንደሮጡም ወደፊት የሚገሰግሰው ማሞ ለጥቂት ተጠልፎ ከመውደቅ ተርፎ ሩጫውን ቀጠለ፤ አብዛኛውን ርቀት ከተሸፈነ በኋላ በመሪነት ሌላውን ሲያስከትልም ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ሩጫው ሊጠናቀቅ ጥቂት ሜትሮች ብቻ ሲቀሩት ኬንያዊው አትሌት ናፍታሊ ቴሙ ከየት መጣ ሳይባል እጅግ ተቀራራቢ በሆነ ሰዓት ቀድሞት ገባ፡፡ ይህም ማሞ በሁለተኛው ርቀት የብር ሜዳሊያ ሲያስገኝለት በሁለት የኦሊምፒክ ተሳትፎዎች በተለያዩ ርቀቶች ውጤት ማስመዝገቡ በዓለም ብቸኛው አትሌት ስላደረገው አድናቆትን አትርፎለታል፡፡ በኦሊምፒክ ውጤታማ ለመሆን ከፍተኛ ጥረት ማድረግን ይጠይቃል፡፡ በርካታ ሃገራትም ለተወዳዳሪነት ቡድናቸውን በተለያዩ ስፖርቶች በመድረኩ ያሳትፋሉ፤ ይሁን እንጂ ውጤት ማስመዝገብ ጉም እንደመዝገን ሆኖባቸዋል። በአንጻሩ ማሞ ብቻውን በአንድ ኦሊምፒክ ሁለት ሜዳሊያዎችን ቢያጠልቅም፤ በእነዚህ ድሎች ብቻ ሊረካ አልቻለም፡፡ እናም ዳግም ለሌላ ኦሊምፒክ ወደ ዝግጅት ገባ፤ እአአ በ1972 ሙኒክ ኦሊምፒክ ላይም ታየ፡፡ ውጤታማና ዝነኛ በመሆኑ የኢትዮጵያ ልኡክ በኦሊምፒኩ መክፈቻ በተመልካች ፊት ሲያልፍ የሃገሩን ባንዲራ በክብር ይዞ ታይቷል። በወቅቱ እድሜው አርባ ዓመታትን ቢሻገርም ጎልማሳነት ሳያግደው በማራቶን የነሃስ ሜዳሊያ ባለቤት በመሆን ጀግንነቱን በድጋሚ አረጋግጧል፡፡ ማሞ ከኦሊምፒክ ድሎቹ ባሻገር ከ500 በላይ በሚሆኑ በተለያዩ አህጉርና ዓለም አቀፍ ውድድሮች ተሳትፎው ካስመዘገባቸው በርካታ ሜዳሊያዎች ውጪ፤ ዋንጫዎችን፣ ኒሻኖችን፣ ሰዓቶችን፣ ሽጉጦችንና ወርቆችን ተሸልሟል፡፡ በስፔን በተካሄደ የሃገር አቋራጭ ውድድር ላይ በተከታታይ አሸናፊ በመሆኑም ሩጫው በሚካሄድበት ከተማ ሃውልት ቆሞለታል፡፡ ከእነዚህ ሽልማቶች መካከል ከፊሎቹ አሁንም ድረስ በልጁ ሳሙኤል ማሞ ወልዴ እጅ ይገኛሉ፡፡ የተቀሩት ግን ማሞ በህይወት ሳለ በአካባቢው ለሚካሄዱ የወረዳና ከፍተኛ ውድድሮች የራሱን ሽልማቶች አውጥቶ በመስጠቱ ምክንያት የሌሉ መሆኑን ያስታውሳል፡፡ ሳሙኤል አባቱን ሲገልጽ ‹‹ሃገሩን እጅግ የሚወድና መስዋዕትነትንም የከፈለ፤ ነገር ግን ውለታው የተዘነጋ እንዲያውም ጥቃቶችንም ያስተናገደ›› ነበር ይላል፡፡ ማሞ በ1983 ዓም ወደ ስልጣን የመጣውን መንግስት ተከትሎ በሁለተኛው ወር ‹‹የቀይ ሽብር ተጠርጣሪ›› በሚል ነበር ለእስር የተዳረገው፡፡ ሲታሰርና ሲፈታ ቢቆይም ከ1985 ዓ.ም ጀምሮ ግን እስሩ ጸንቶ በ1994 ዓ.ም ነበር የተፈታው፡፡ ሆኖም ከዚያ በኋላ ከአራት ወራት በላይ እድሜው ሊገፋ ባለመቻሉ በግንቦት ወር ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፡፡ በ1988 ዓ.ም ከቦክሰኛው መሃመድ አሊ ጋር የኦሊምፒክን ችቦ እንዲለኩስ በመመረጡ ከዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ልኡካን ከወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ዘንድ ቀርበው እንዲፈታ ቢጠይቁም ‹‹ማሞ ወልዴ ጀግና ነው፤ ሆኖም ወንጀል እንዲሰራ አንፈቅድለትም›› የሚል ምላሽ ተሰጥቷቸው እንደተመለሱ ሳሙኤል ያስታውሳል፡፡ የጀግናውን አትሌት ህልፈት ተከትሎም የስፖርቱ ወዳጅና ባለውለታ የሆኑት የቀስተደመና ስፖንጅ ፋብሪካ ባለቤት አቶ አቤሴሎም ይህደጎ ሃውልት አሰርተውለት ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ከ13 ዓመታት በፊት ማንነታቸው ባልታወቀ ግለሰቦች አጽማቸው ጎን ለጎን ያረፈው ጀግና አትሌቶች ሻምበል አበበ ቢቂላ እና ማሞ ወልዴ ሃውልት ሊፈርስ ችሏል፡፡ ይህንን ተከትሎም ሳሙኤል የተለያዩ አካላትን አስተባብሮ የማሞ ሃውልት ዳግም እንዲሰራ ያላደረገው ጥረት እንዳልነበረ ይገልጻል። ነገር ግን የአቅም ውስንነት ምላሽ ከማጣቱ ጋር ተዳምሮ ለዓመታት ጀግናው አትሌት ከመቃብር በላይ ለዋለው ስሙ ማስታወሻ የሚሆነውን ሃውልቱን አጥቶ ቆይቷል፡፡ ከረጅም ጊዜያት በኋላም ሌላኛዋ ጀግና አትሌትና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ደራርቱ ቱሉ ከሳምንት በፊት በራሷ ተነሳሽነት የማሞንና የአበበን ሐውልት እውን አድርጋዋለች፡፡ ለሃገሩ በከፈለው ውለታም ዛሬ በህይወት ኖሮ ባይቀበልም አንድ ሚሊየን ብር ለቤተሰቦቹ ተበርክቷል፡፡ በዚህ እጅግ የተደሰተው ሳሙኤልም ‹‹ትክክለኛው ሰው በትክክለኛ ቦታው ሲገኝ ምን ሊሰራ እንደሚችል ያመላከተ›› ሲል ደስታውን ያንጸባርቃል፡፡ ይህ የአባቱ ታሪክ በትውልዱ ሰርጾ እንዲኖርና በጽናት ያሳለፋቸው ውጣ ውረዶቹ መነሳሳትን እንዲፈጥርም በመጽሃፍ መልክ ለማሳተም ሃሳብ ቢኖረውም በአቅም ውስንነት ሊያሳካው አልቻለም። ስፖንሰር ቢያገኝ ግን የማሳተም ሃሳብ ያለው መሆኑን ይጠቁማል፡፡ ማሞ ጡረታውን ተከልክሎ እስር ቤት ከገባበት ጊዜ ጀምሮ ቤተሰቦቹ ከመበተን እንዲተርፉ ያደረጉትና አሁንም ለሳሙኤል ስራ ለልጁ ደግሞ የትምህርት እድል የሰጡትን የቀስተደመና ስፖንጅ ፋብሪካ ባለቤት አቤሴሎም ይህደጉ እንዲሁም ልጃቸውን ያመሰግናል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 11/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=37748
[ { "passage": "ከአዲስ አበባ በ110 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የምትገኘው ወንጂ ከተማ በእግር ኳሱ በርካታ ተጫዋቾችን ማፍራቷ ይነገርላታል። ይህም ከተማዋ ከምትታወቅበት ጣፋጭ የሸንኮራ አገዳ አምራችነቷ፣ የስኳር ፋብሪካ ማዕከልነቷ ትይዩ የእግር ኳስ ተጫዋቾች መፍለቂያ አሰኝቷታል። የወንጂን ከተማ በእግር ኳሱ ካስተዋወቁት ተጫዋቾች መካከል ደግሞ አንጋፋው ተጫዋች ተስፋዬ ኡርጌቾ ይጠቀሳል። በወንጂ ከተማ ተወልዶ ያደረገው ተስፋዬ፤ በእግር ኳሱ ትልቅ ቦታ መድረስን የልጅነት ህልሙ አድርጎ የተነሳ መሆኑን የቅርብ ወዳጆቹ ይናገሩለታል። ከልጅነቱ ጀምሮ ለእግር ኳስ ልዩ ፍቅር በመያዝ መነሻው ከሰፈር ሜዳ ነበር። በኳሱ የመጓዝ ህልሙ ሩቅ የሆነው የትናንቱ ታዳጊ ተስፋዬ፤ በስፖርቱ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ በማጎልበቱ ወደ ክለብ እንዲያድግ አጋጣሚን አገኘ። \nከከተማዋ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ መሠረት አንዱ የሆነው የወንጂ ስኳር ፋብሪካ ያቋቋመውን «የወንጂ ስኳር እግር ኳስ ክለብ» ነበር የተቀላቀለው። ተስፋዬ የወንጂ ስኳርን መቀላቀሉ በኳሱ ለሚያልመው ህልሙ፣ ለሰነቀው ተስፋ እውን መሆን መንደርደሪያውን የትውልድ ከተማው ሆነለት። ከክለቡ ጋር የተወሰኑ ጊዜያትን ቆይታ ካደረገ በኋላ የሕይወቱ አቅጣጫ ወደ ሌላ ምዕራፍ ተሸጋገረ። በወንጂ ስኳር እግር ኳስ ክለብ በፈጣንና ጥበብ የተሞላበት እንቅስቃሴ ባለቤትነቱ በአየር ኃይል እግር ኳስ ቡድን እይታ ውስጥ አስገባው። በወቅቱ የአየር ኃይል አሰልጣኝ የነበረው አንጋፋው አሰልጣኝ ሀጎስ ደስታ ልብ በማሸነፍ አሰልጣኙ አየር ኃይልን እንዲቀላቀል አስቻለው። በእግር ኳሱ ትልቅ ደረጃ የመድረስ ተስፋ በልቡ ሰንቆ ወደሜዳ ለሚመጣው ታዳጊ ትልቅ ዕድል ነበር። \nበአየር ኃይል ቤት ተስፋዬ ምኞቱን መኖር ለመጀመሩ መንደርደሪያው ነበር። በቡድኑ ውስጥ ያሳየው እንቅስቃሴ ክለቡ እንዲደሰትበት ከማድረግ አልፎ፤ ለብሔራዊ ቡድን እንዲጫወት ሀገራዊ ጥሪ እንዲቀርብለት አድርጎታል። በ1983 ዓ.ም ለኢትዮጵያ ወጣት ብሔራዊ ቡድን በመመረጥ በግብጽ አዘጋጅነት በተካሄደው 7ኛው የአፍሪካ ወጣቶች ዋንጫ ላይ ለመሳተፍ ችሏል። የወንጂው ፍሬው ተስፋዬ የስኬት ጀንበርን በአጭር ጊዜ ውስጥ መመልከት የቻለ ሲሆን፤ በሜዳ ላይ የሚያሳየው ብቃትና የተላበሰው መልካም ስብዕናው ተደምረው ጉዞው ያማረ እንዲሆን አደረጉት። የወጣት ብሔራዊ ቡድኑ በሻምፒዮናው ላይ ከተሳትፎ መልስ የተስፋዬ የክለብ መዳረሻ ከአየር ኃይል ተወርውሮ ወደ አንጋፋው ቅዱስጊዮርጊስ ላይ አረፈ። በ1983 ዓ.ም በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ አንፀባራቂ ታሪክ ባላቸው በኢንስትራክተር መንግሥቱ ወርቁ አማካኝነት ክለቡን ተቀላቀለ። የእግር ኳሱ ጥበበኛ ተስፋዬ ፈረሰኞቹን መቀላቀሉ በኳሱ የስኬትን ቁንጮ ለመቆናጠጥ ትልቅ ዕድል ፈጥሮለታል። በአማካይና የተመላላሽ ቦታዎች ላይ በመጫወት ክለቡን ለስኬት ማብቃት በመቻሉ የክለቡ ደጋፊዎች ዛሬም ድረስ ትልቅ ቦታ እንዲኖራቸው አድርጓል። \nከ1983 ዓ.ም እስከ 1992 ዓ.ም ፈረሰኞቹን ማገልገል የቻለው አመለሸጋው ተስፋዬ፤ በቆይታው ከፍተኛ ዝናና ተወዳጅነት አትርፏል። በፈረሰኞቹ ቤት በቆየባቸው የሰባት ዓመታት ቆይታ ውስጥ በ1986 ዓ.ም የአዲስ አበባ ሻምፒዮን ኮከብ ተጫዋችነትን ክብር አግኝቷል። ክለቡ ቅዱስጊዮርጊስ ከ1986 እስከ 88 ዓ.ም የአዲስ አበባ ሻምፒዮናነትን ክብር ሲቀዳጅ ግብ አስቆጣሪ ከሆኑት ተጫዋቾች ጀርባ የእርሱ ሚና ግዙፍ እንደነበር በወቅቱ የነበሩ ተጫዋቾች መስክረውለታል። ከክለቡ ስኬት ተሻግሮም ለሚወዳት ሀገሩ በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ተመርጦ በርካታ ጨዋታዎችን ተጫውቶ አሳልፏል። \nበ1985 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ላይ ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ኢትዮጵያ ናይጄሪያን 1ለ 0 ስታሸንፍ ብቸኛዋን ግብ በማስቆጠር ሀገሩን ለድል ያበቃበት አጋጣሚ በአብዛኛው የስፖርት ቤተሰብ ዘንድ ይታወሳል። በብሔራዊ ቡድን ብሎም በክለብ ደረጃ የነበረው እንቅስቃሴ ከክለቡ ተሻግሮ በስፖርት አፍቃሪው ዘንድ ከፍተኛ ተደናቂነት ማትረፍ የቻለ ተጫዋች ነበር። በሀገር ውስጥ የክለብ ፍልሚያዎች በፈረሰኞቹ ቤት በ4 ቁጥር ማሊያ መንገስ ችሏል። በሜዳ ላይ ፈጣንና ድንቅ እንቅስቃሴ የሚያሳይ መሆኑን ተከትሎ «ተምዘግዛጊው ሚሳኤል» የሚል ቅጽል ስም የተሰጠው ተስፋዬ፤ ከሀገር አልፎ ወደ አውሮፓም አምርቶ በፊንላንድ ሊግ መጫወት ችሏል። በኢትዮጵያውያን ተጫዋቾች ዛሬም ድረስ እንደ ብርቅ በሚታየው የአውሮፓ ሊግ የኳስ ጥበበኛው ተስፋዬ ባህር ተሻግሮ። \nእግር ኳስን በተጫወተባቸው ዓመታቶች በመሀል ሜዳ የጨዋታ ብቃቱ የብዙዎቹን የእግር ኳስ አፍቃሪዎች እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎችን ቀልብ ይስብ የነበረው፤ ተስፋዬ የተጫዋችነት ዘመኑን ቢያበቃም ከኳሱ አልተለየም ነበር። ከተጫዋችነት ወደ አሰልጣኝነት የሕይወቱ አቅጣጫ ተሸጋገረ። በአሰልጣኝነትም ሕይወት በመሰማራት የጌታ ዘሩን የታዳጊ ፕሮጀክት እና የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲንም ክለብን በመያዝ አሰልጥኗል። የሕይወቱን ፍጻሜ ከኳስና ከእናት ሀገሩ ለመነጠል ፍላጎት ያልነበረው ተስፋዬ፤ መኖር ግድ ነበርና በአሜሪካ በስደት በርካታ ዓመታትን አሳልፏል። «ተምዘግዛጊው ሚሳኤል» በገጠመው ህመም ከሚኖርበት አሜሪካ የመጣ ሲሆን፤ በሚወዳት ሀገሩ በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 05 ቀን 2012 ዓ.ም በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሕይወቱ አርፏል። በኢትዮጵያ የእግር ኳስ ታሪክ ውስጥ የራሱን አሻራ ማሳረፍ የቻለው ተስፋዬ የቀብር ሥርዓቱ በትውልድ ከተማው ወንጂ ሸዋ ኪዳነ ምህረት ከትናንት በስቲያ ተፈጽሟል። የተስፋዬ ሞት ብዙዎቹን ያሳዘነም ሲሆን የዝግጅት ክፍላችን በተስፋዬ ሞት የተሰማውን ጥልቅ ኀዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቹ ለወንድሙ ተከተል ኦርጌቾና ለመላው ስፖርት አፍቃሪ እና ለቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች መፅናናትን ይመኛል።\nአዲስ ዘመን ግንቦት 7/2012ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "ecca94964ee2573c01afae2acf372265" }, { "passage": " እርሱ ያንን መቼም አይረሳውም። ከኦሎምፒኩ ድሉ ማግስት የተዜመለትን። “ቀነኒሳ አንበሳ”። ይሄን ዜማ ሲሰማ በውስጡ ልዩ ሀሴት ይሰፍናል። ለውለታው የተዜመ ልዩ ስጦታው አድርጎ ይቆጥረዋል። አንዳች ልዩ ስሜትና ትዝታ ውስጥ የሚከተው ዜማ እንኳን ለተወዳደሪዎቹ ተመልካቹን በስሜት የናጠ ነው። “እልል በል ያገሬ ጎበዝ ለእምዬ ውለታ ወርቅ አመጣሁላት ልጇ ለክብሯ ስጦታ..” በረጅም ርቀት ውድድር የመጨረሻ ዙርን እንደ አጭር ርቀት የሚደመድም፤ በታላለቅ የውድድር መድረኮች በከፍታ የነገሰ ፤ እንደ አቦ ሸማኔ በፈጠኑ ጠንካራና ቀጫጭን እግሮቹ ተዓምር የሰራ ፤ የአገሩን ሰንደቅ አላማ በዓለም አደባባይ በክብር ከፍ አድርጎ ያወለበለበ፤ ህዝብ በእርሱ ድል እንዲፈነድቅ፣ ከያኒው ስለሱ አብዝቶ እንዲቀኝ ምክንያት የሆነ ኮከብ አትሌት ነው ቀነኒሳ በቀለ። ትጋት ጥንካሬና ፍጥነቱ “አንበሳው” የሚል ቅጥያ ያንሰዋል። ሀገር የሰጠውን ታላቅ አደራ አተልቆ የከፈለ ጀግና ነውና ። የዕረፍት ሰዓት ቆይታ ህይወትን ቀለል አድርጎ መኖር፤ የተካበዱ ጉዳዮችን ሳሳ አድርጎ ማየት የአትሌት ቀነኒሳ የኑሮ ፍልስፍናና ልምድ ነው። አዳዲስ ሞዴል ዘመናዊ አውቶሞቢሎችን የራሱ የማድረግ አቅም አለው፤ ነገር ግን ይህን ማድረግ አይወድም። የመረጠው ቦታ ላይ ቅንጡ ኑሮን መምራት ይችላል፤ ያን መሆን ግን አይፈልግም። ቀለል ያለ ህይወት ምቾት እንደሚፈጥርለት ይናገራል። የሚፈልገው በአኗኗሩ በዙሪያው ካሉ ሰዎች የተለየ አለመሆንን ነው። ያሻውን ከማድረግ ውጪ ለይሉኝታ ግድ የማይሰጠው ሰው መሆኑን ይናገራል። ለእርሱ ይህን ከማድረግ ነፍሱ በሀሴት የሚያጥለቀልቃት ከከተማ ርቀው ዓለም በቃኝ ብለው የመነኑ፤ የዓለምን ግሳንግስ ጠልተው የኮበለሉ፤ የምድርን ደስታ ንቀው ለነፍስ ያደሩ ባህታዊያንን አግኝቶ ከእርነሱ ጋር የእረፍት ጊዜውን ማሳለፍን ይመርጣል። ገዳማትና ራቅ ያሉ ተፈጥሯዊ ቦታዎች መገኘት እጅጉን ያስደስተዋል። ተፈጥሮ በራሱ የኳለውን አካባቢያዊ መልካም ምድር መመልከት ከምንም በላይ ያደንቃል። በእንዲህ ያለው ስፍራ መገኘትንም ሀሴት ያደርጋል። የዕረፍት ጊዜን ከቤተሰብ ጋር አብዛኛው የእረፍት ጊዜ ከቤተሰቡ ጋር ማሳለፍን የሚመርጠው አትሌት ቀነኒሳ ቤት ውስጥ ልዩ ቤተሰባዊ ድባብ በመፍጠር ከልጆቹ ጋር መጫወት፣ አዲስ የወጡ ፊልሞችን በጋራ መመልከት፣የተለያዩ የመናፈሻ ቦታዎች ላይ ቆይታን ማድረግ በእረፍት ቀኑ ያዘወትራል። ባለቤቱና ሶስቱ የአብራኩ ክፋይ ልጆቹ ‹‹ የደስታዬ ምንጭ ናቸው›› በማለት ለእነሱ ያለውን ጥልቅ ፍቅር ይገልፃል። ከቃላትም በላይ ገጽታው ይመሰክራል። በማህበራዊ ህይወት በኩል ንቁ ተሳታፊ ነው አትሌት ቀነኒሳ። ለቅሶ፣ ሰርግና ልዩ ልዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ አቅሙ በፈቀደው ሁሉ ይሳተፋል። በተጣበበ ጊዜውም ቢሆን ከጓደኞቹ ጋር የዕረፍት ሰዓት ቆይታ ያደርጋል። እዛ ደግሞ ቋንቋ ሁሉ ይቀየራል። አንድ አይነት ክንፍ ያላቸው አብረው ይበራሉም አይደል አባባሉ። የልብስ ምርጫ ለሚለብሰው ልብስ ምርጫ ግድ የሌለው ቀነኒሳ በተለይ በእርፍት ሰዓቱ ቀለል ያለ አለባባስን ያዘወትራል። በልብስ ፋሽን የመከተል ልምዱ አይደ ለም። ብቻ ከመልበሻ ሳጥኑ ውስጥ ያገኘውን ደስ የሚለውና ሲለብስ ይቀለኛል ብሎ የሚያስበውን ይመር ጣል። የባህል ምግብ በባለሙያ ክሽን ተደ ርጎ የተሰራ ዶሮ ወጥና ጨጨብሳ ከኢትዮጵያ ባህላዊ ምግቦች እጅጉን የሚወዳቸው ናቸው። ከገ በታው ላይ አትክልትና ፍራፍሬዎች አዘውትሮ ቢያገኝ ይመርጣል። ለሚያ ደርገው የአካል ብቃት እንቅስቃሴና ለጤናው ጠቃሚ የተባለ የአመጋገብ ልምድ ይከተላል። ከራሱ አልፎ የቤተሰቡን ጤናማ የሆነ አመጋገብ ክትትል ያደርጋል። የአትሌቱ መልዕክት “ተፈጥሮ ሳያጓድል ሁሉን ነገር የቸራት ኢትዮ ጵያ ለሁላችን በቂ ናት። አንድነታችን አጠንክረን ልዩነታችንን አስወግደን ለሁላችን ምቹ የሆነች ሀገር ለመፍጠር በቅን ልቦና እንትጋ።” ከአትሌቱ ጋር የነበረን አጭር መሳጭና አስተማሪ ቆይታችንን የማበ ቃው አትሌቱ ከሚወ ደው ሙዚቃ “..ይቺ ባንዲራ አንበሳ ናት እድለኛ ዛሬም አኮራት አንበሳ ቀነኒ ኬኛ አንበሳዬ አንበሳ”… የሚለውን ስንኝ በመው ሰድ ነው። ሰላም!አዲስ ዘመን ግንቦት 2/2012ተገኝ ብሩ", "passage_id": "204e529026bf08f31cfce08130dc75b7" }, { "passage": "የ123ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን በማክበር ላይ ነን። በጦርነቱ ድል ውስጥ ሁሌም አብሮ የሚነሳውን ታሪካዊ ስፍራና የእቴጌ ጣይቱ ወታደራዊ ጥበብ የታየባት እንዳየሱስን አለማስታወስ አይቻለንም። የጣሊያን ወታደሮች መቀሌ እንዳየሱስ ላይ ፎርቶ ዲ. ጋሊያኖ የሚባለው ቦታ መሽገው ለሁለት ሳምንት የኢትዮጵያን ጦር አላስጠጋም አሉ።በዚህ\nወቅት እቴጌ ጣይቱ አንድ ሃሳብ ብልጭ አለላቸው። እርሳቸው ባመጡት ብልሐትና በራሳቸው ከሚመራው ጦር ምርጥ ተዋጊዎች ተመረጡ። ጣሊያኖች የሚጠቀሙበትን ከምሽጋቸው በስተ ደቡብ ያለውን «ማይንሽቲ» የተባለውን ምንጭ በሌሊት ሂደው በኢትዮጵያውያን እጅ እንዲገባ አደረጉ፡፡ ይህ ወታደራዊ እርምጃ በጣሊያኖች ዘንድ ከፍተኛ የውኃ ችግር በመፍጠሩ ጣሊያኖች ምሽጋቸውን ለቅቀው እንዲሄዱ አስገድዷቸዋል፡፡", "passage_id": "90d8b3ce8e9eac35fbbfee204862654c" }, { "passage": "ኢትዮጵያ በተለይ በአትሌቲክስ ስፖርት በትውልድ ቅብብሎሽ የተጓዙ ጀግኖች ባለቤት ናት። እነዚህ ጀግኖች በኦሊምፒኮችና በዓለም ሻምፒዮናዎች ኢትዮጵያን ወርቅ በወርቅ በማድረግ ችሎታቸውን አስመስክረዋል። በአብሮነት ጉዞ የተገኘው ድል የ“ይቻላል”ን ታሪክ በማቀበል ዛሬ ትውልድ እንዲመሰክርና እንዲማር እያደረገ ይገኛል። ቀደምት አትሌቶች በጉብዝናቸው ወራት ለሀገራቸው ሮጠው ያኖሩትን የድል ታሪክ ትውልድ ሊያወሳው ይገባል። ይህን ድል የብርታትና የጽናት ምሳሌ አድርጎ የራሱን ታሪክ ለመስራት እንዲዘጋጅ ያግዘዋልና፤ ይህን እውነታ መነሻና መድረሻ በማድረግ የአዲስ ዘመን ጋዜጣም ከቀደምት ጀግኖች አንዱ የሆኑትን የቀድሞ አትሌት የ፶ አለቃ ኃይለ ሚካኤል ጃርሶን እንግዳ አድርጓል። የ፶ አለቃ ኃይለሚካኤል በ3 ሺህ ሜትር መሰናከል፣ በ5 ሺህ ሜትር፣ በ10 ሺህ ሜትር በመሮጥ ለሀገራቸው 54 ሜዳሊያዎች ያመጡ ባለውለታ ናቸው። እኛም በርቱዕ አንደበታቸው የተረኩልንንና ከተወዳዳሪነት እስከ አሰልጣኝነት የተሻገረውን የህይወት ገጻቸውን እንደሚከተለው አቅርበነዋል። መልካም ንባብ፤ትውልድና እድገት  ትውልድና\nእድገቴ በቀድሞ መጠሪያው ምዕራብ ሸዋ ጅባትና ሜጫ አካባቢ ነው። ዕድሜዬ ለትምህርት እንደደረሰም ወላጆቼ በአካባቢያችን በሚገኝ\nአንደኛ ደረጃ ትምህርት አስገቡኝ። ትምህርቴን ከአንድ እስከ አራተኛ ክፍል ተከታተልኩኝ። ከአራተኛ ክፍል በኋላ ያለውን ደግሞ አዲስ\nአበባ ነበር የተማርኩት፤ያው የህይወት አጋጣሚ ሆነና ወደ አዲስ አበባ መጣሁ። ትምህርቴንም እዚሁ አዲስ አበባ በሽመልስ ሀብቴ ትምህርት\nቤት መከታተል ጀመርኩ። ከአራተኛ እስከ አስራ ሁለተኛ ክፍል በዚሁ ትምህርት ቤት ተምሬያለሁ።  የትውልድና እድገቴ ሂደት ይህን ይመስላል።የስፖርት\nአጀማመር ስፖርት\nለእኔ ህይወቴ ነው። ገና ልጅ እያለሁ ጀምሮ ነበር የስፖርት ፍቅር ያደረብኝ፤ በትውልድ ስፍራዬም ሆነ አዲስ አበባ ከመጣሁ በኋላ\nበሰፈር ውስጥና በትምህርት ቤት በስፖርት እንቅስቃሴ አደርግ ነበር። በተለይ ደግሞ በትምህርት ቤት ውስጥ በልዩ ሁኔታ ስፖርት አዘወትር\nነበር። ሩጫውን፣ ጦር ውርወራውን፣ ዝላዩን፣ ቅርጫት ኳሱን እሞክራለሁ። ስፖርት በህይወቴ ውስጥ እስከ እለተ ሞቴ ተከትሎኝ እንደሚሄድ\nጭምር ይሰማኛል። ለስፖርቱ ጥልቅ የሆነ ፍቅር ያለኝ ቢሆንም የህይወቴ ጉዞ ከትምህርት ቤት ወደወታደር ቤት ነበር ያረፈው፤ ዘመናዊ\nትምህርቴን እስከ 12ኛ ከተከታተልኩ በኋላ የሀገር መከላከያ ሰራዊትን ተቀላቀልኩ። የሀገር ፍቅር ስሜቴና ወኔዬ ከልጅነቴ አብሮኝ\nያደገ ነውና ሀገሬን በምን ላገልግል ከሚል ጉጉት ነበር ጦሩን የተቀላቀልኩት።“ሁን ያለው ይሆናል” ነውና የልጅነት ህልሜን በጦሩ\nቤት ዳግም አገኘሁት። የስፖርት እንቅስቃሴ ለማድረግ ተመቸኝ። በጦሩ ቤት በሚደረጉ የውስጥ ውድድሮች ላይም በአትሌቲክስ የመሳተፍ\nአጋጣሚዎች ተፈጠሩ። የልጅነት ህልሜ ከተቀበረበት ተፈንቅሎ መውጣት ጀመረ። የህይወቴ ምዕራፍ ወደሌላ አቅጣጫ ተዛወረ።በሀይለስላሴም\nሆነ በደርግ ጊዜ በጦሩ ቤት ስፖርት በከፍተኛ ሁኔታ ይዘወተር ነበር። በየአካባቢው የነበሩት የጦሩ ክፍሎችም በሀገር አቀፍ ደረጃ\nበሚዘጋጁ የውድድር አውዶች ውጤታማ ቡድኖችን ይዘው በመቅረብ ይታወቃሉ። የውጤት ታሪክ በያዘው ቤት ውስጥ ዳግም የተወለደው የእኔ\nየስፖርት ህይወት ይሄንኑ መልክ የያዘ ነበር። ለመጥቀስ እንደሞከርኩት በጦሩ ቤት በተደረገ የውስጥ ውድድር እኔ የመታየት አጋጣሚው\nአግኝቻለሁ። ያኔ በሀገሪቱ ጠንካራ ተብለው ዛሬም ድረስ በታሪክ ከሚወሱት ቡድኖች አንዱ የሆነውን ክቡር ዘበኛን ለመቀላቀል በቃሁ።\nክቡር ዘበኛ ውስጥ ከገባሁ በኋላ ችሎታዬን በሚገባ የማውጣት እድል አግኝቻለሁ። በአጭር ጊዜ ውስጥ አይን ውስጥ ገባሁ። የመጀመሪያው\nየስኬት በርም ተከፈተ። በ1963 ዓ.ም በሸዋ ሻምፒዮና (ያኔ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት የሚባል አስተዳደር ነበር) ውስጥ መመረጤ ነበር\nይህንን ያበሰረኝ፤ በዚህ ውድድር በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል መድረክ ላይ የነበረኝ ውጤታማነት በሀገር አቀፍም ሆነ ከአገር ውጪ በሚደረጉ\nየስፖርት ውድድሮች በመሮጥ ሜዳሊያዎችን እንድሰበሰብ መንገድ ጠርጎልኛል።የአፍሪካ\nእና የዓለም አቀፍ መድረክ ተሳትፎና ውጤት በሀገራችን\nስፖርት እንቅስቃሴ  ውስጥ ትልቅ ታሪክ ባለበት በክቡር ዘበኛ ቤት\nውስጥ መቆየቴ በአጭር ጊዜ ከሀገር አቀፍ ወደ አህጉር አቀፍ ውድድር ለመሸጋገር ድልድይ ሆኖኛል። ዓመተ ምህረቱም 1964 ነበር።\nበሀገር አቀፍ ውድድር በማሸነፌ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተመረጥኩ። ይሁን እንጂ፤ ከብሄራዊ ቡድኑ ጋር በሙኒክ ኦሎምፒክ ለመሳተፍ\nከተመረጠው ቡድን ጋር ለመጓዝ እየተሰናዳሁ ባለሁበት ወቅት ከአሰልጣኝ ጋር በተፈጠረ ግጭት ከቡድኑ ውጪ ተደረግሁ። ወደትልቁ የውድድር\nመድረክ ለመጓዝ የቋመጠው ልቤ፤ በዚያም ለመሮጥ የተነሳው እግሬ በትንሽ አጋጣሚ “ነበር” ሆኖ ቀረ። ይህ መሆኑ ውስጤን ቢረብሸኝም\nተስፋ ሳልቆርጥ ልምምድ መስራቴን አላቋረጥኩም። ከአንድ ዓመት በኋላ፤ ማለትም በ1965 ዓ.ም በመላው አፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና\nላይ ለመወዳደር ለብሄራዊ ቡድን ተመረጥኩ። ናይጄሪያ ሌጎስ በተካሄደው በዚያ ሻምፒዮና ላይ በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ሀገሬን በመድረኩ\nወከልኩኝ። በውድድሩ አራተኛ በመውጣት ዲፕሎማ ተሸለምኩ። በሩጫው የገባሁበት ሰዓት ፈጣን የሚባል በመሆኑ ለፓን አፍሪካ ለመመረጥ\nያስቻለኝ ነበርና ከአንድ ዓመት በኋላ አልጀርስ ላይ ተወዳድሬ ሶስተኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቀኩ። በሻምፒዮናው የነበረኝ ተሳትፎና\nውጤት ደግሞ በአትሌቲክሱ የማደርገውን ጉዞ ቀጣይነት እንዲኖረው ያደረገ ነበር።በአህጉር\nደረጃ የነበረኝ የተወዳዳሪነት አድማስ ከፍ ያለና በተለያዩ የዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ የመሳተፍ እድሎችም ነበሩኝ። በአሜሪካ አዘጋጅነት\nበተካሄደውና ከተለያዩ አህጉራት የተውጣጡ ቡድኖች በሚተሳተፉበት ውድድር በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ተሳታፊ ሆኛለሁ። በውድድሩ ሶስተኛ\nበመውጣት ለአፍሪካም ሆነ ለኢትዮጵያ ታሪካዊ ሜዳሊያ ያጠለቅኩበት አጋጣሚ ከብዙዎቹ መካከል የሚጠቀስ ነው። በአህጉርም ሆነ በዓለም\nአቀፍ ደረጃ ያለኝ ተሳትፎና ውጤት ከዚህ አኳያ ታሪካዊ የሚባል እንደሆነ አስባለሁ። በተወዳዳሪነት ዘመኔ በተለየ መልኩ 3ሺህ መሰናክል\nእውቅና ላትርፍ እንጂ፤ በ5 ሺህ ና በ10 ሺህ ሜትር በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ ተወዳድሬያለሁ። በተለያዩ አገራት በመዞር በተወዳደርኩባቸው\nጊዜያት ባጠቃላይ 54 ሜዳሊያዎች አግኝቻለሁ።የአሰልጣኝነት\nህይወትበክቡር\nዘበኛ ቤት ውስጥ የጀመረው የተወዳዳሪነት ህይወቴ በተለያዩ የታሪክ ገጠመኞች ታጅቦ እዛው ተዘጋ። ለስፖርቱ የነበረኝ ጥልቅ ፍቅርና\nፍላጎት በዚያው እንድዘልቅ አደረገኝ። እናም የተወዳዳሪነት ቆይታዬ ካከተመ በኋላ፤ በዚያው ባሳደገኝ በክቡር ዘበኛ ቤት ውስጥ አሰልጣኝ\nሆኜ ቀጠልኩ። በሀገራችን የስፖርት ታሪክ ውስጥ ዛሬም ድረስ ስሙ በሚነሳው በጦሩ ቤት ከባልደረቦቼ ጋር በመሆን ታሪክ ለማስቀጠል\nተነሳን። በወቅቱም ማዕከላዊ ኮርን እንዳሰለጥን ተሰጠኝ። በዚያም ውርወራ፣ ዝላይና መሰናክል አሰለጥን ነበር። ከዚያም፤ እድሜዬ\nለጡረታ ሲደርስ በ1987 ዓ.ም ጡረታ ተገለልኩ። የአሰልጣኝነት ቆይታዬ ከተወዳዳሪነት ጊዜ ባልተናነሰ ስኬታማ እንደነበር አስባለሁ።\nለዚህም በአፍሪካ ሻምፒዮና የወርቅ ጫማ ተሸላሚ የሆነው አትሌት በቀለ ደበሌ የኔ ሰልጣኝ ነበርና እርሱ እንደማሳያ ይጠቀሳል። አትሌቱ\nወታደር ሆኖ የተቀጠረ ቢሆንም ለስፖርት የተመለመልኩት እኔ ነበርኩኝ። በቀለን በጊዜው እንዳየሁት በቂ ስልጠናና ክትትል ከተደረገለት\nውጤታማ እንደሚሆን እምነት አደረብኝ። እርሱም አላሳፈረኝም በአፍሪካ ሻምፒዮና ላይ የወርቅ ጫማ ተሸለመ። በአሰልጣኝነት ቆይታዬ\nሌሎች ውጤታማ አትሌቶችን አፍርቻለሁ። ሀገራችን ስሟና ታሪኳ ብዙም በማይጠቀሰው የእርምጃ ሩጫ ተወዳዳሪ የነበረው ሸምሱ ሀሰን የእኔ\nሰልጣኝ ነው። ሸምሱ በተለያዩ አገራት በመሳተፍ ውጤት ማስመዝገቡን ታሪክ ምስክር ነው። በአሁኑ ወቅት በአሜሪካን አገር የሚኖረውን\nአለማየሁ ሮባን ከትምህርት ቤት መልምዬ አምጥቼ ውጤታማ አድርጌዋለሁ። በዚህም የተነሳ፤ በክቡር ዘበኛ ተጠንስሶ በተወለደው የስፖርት\nህይወቴ በአትሌትነትም በአሰልጣኝነትም ስኬታማ ነበርኩ ብዬ በኩራት መናገር እችላለሁ። ከእኔም ሆነ ከሌሎች ቀደምት ስፖርተኞች ስኬት\nጀርባ ግን በጦሩ ቤት ውስጥ በመንግስትም ይህን በጦሩ መሪዎች ለስፖርት የሚሰጠው ትኩረት የአንበሳውን ድርሻ እንደሚይዝ ሳልናገር\nአላልፍም።ታሪካዊ  ድል፤ የጦሩ ጀብድበጦሩ\nቤት ለስፖርቱ ትኩረት ተደርጎ የተጠናከረ ስልጠና ይሰራል ነበር። ያኔ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚከናወኑ ውድድሮች ላይ የአትሌቲክስ\nዋንጫ ለአንድ ጊዜም ቢሆን ከክቡር ዘበኛ ወጥቶ አያወቅም። በቡድን ስራ ላይ ከፍተኛ ትኩረት ተደርጎ ይሰራል። በመሆኑም በአትሌቲክሱ\nበተለያዩ ርቀቶች ውጤታማ አትሌቶች በማፍራት ረገድ የክቡር ዘበኛን ያክል የነበረ ክለብ የለም ብሎ በድፍረት መናገር ይቻላል። ክቡር\nዘበኛ በርካታ ስፖርትኞችን አፍርቷል። ክለቡ ሀገራችንን በዓለም አቀፍ የውድድር አውዶች ላይ ውጤታማ እንድትሆን ያደረገ፤ ሰንደቋንም\nከፍ ብሎ እንዲውለበለብ ያሰቸለም ጭምር ነበር። ሻምበል ማሞ ወልዴ፣ ሰለሞን በላይ፣ ካሳ ባልቻ፣ ሀይሉ ወልደጻዲቅ  ፣የማራቶን ጀግናው ደረጄ ነዲ፣ ለማ ገዳ፣  እነዚህ ሁሉ አትሌቶች ከክቡር ዘበኛ የተገኙ የሀገር ባለውለታዎች ናቸው።\nለእነዚህ  አትሌቶች ስኬትና ውጤታማነት ደግሞ አሰልጣኞች የጀርባ አጥንት\nነበሩ። እንደትውስታም አሰልጣኝና ተቆጣጣሪ የነበሩት ተከስተ አባይ አብረው የሚነሱ ለክለቡ ብቻም ሳይሆን ለሀገር ባለ ውለታ ጭምር\nናቸው። እናም ክቡር ዘበኛ  የሀገሪቱ የስፖርት ማህጸን ነበር ማለት\nይቻላል። አሁን ባለው የሀገሪቱ ስፖርት ላይም አሻራው ይታያል። የአትሌቲክሱ\nጋሬጣዎች በአሁኑ\nወቅት በስፖርቱ ውስጥ የሚታየው  የመለማመጃና የመወዳደሪያ ሜዳ ችግር\nከፍተኛ ተጽእኖ እያሳደረ ይገኛል። በመንግስት በኩል ይህ ጉዳይ ትኩረት ተደርጎበት ሊሰራ  ይገባል። ስፖርቱን በሚፈለገው ደረጃና መልክ ለማከናወን የማዘውተሪያ ቦታ  እንደ ልብ ማግኘት አይቻልም። ለምሳሌ፤ የራሴን ተሞክሮ ባነሳ፤ የግል ክለብ\nአሰለጥን ነበር። ብዙም ሳልገፋበት ማሰልጠኑን በማቆም አቅጣጫዬን ቀየርኩኝ። ምክንያቱም የእኔ የማሰልጠን ፍላጎትና የአትሌቶች የመሰልጠን\nፍላጎት ብቻ በቂ አይሆንም።  ይልቁንም፤ የተሟላ የማሰልጠኛ ቦታ ያስፈልጋል።\nየስልጠና ሜዳ በሚፈለገው ደረጃና እንደ ልብ የሚገኝ ቢሆን ያካበትኩትን እውቀቴንና ልምዴን  ማጋራት እችል ነበር። ይህ ችግር ከራሴው ተሞክሮ መንሳቴ ነው እንጂ  በሌሎች ሙያተኞች በተደጋጋሚ ሲነሳ ይደመጣልና ብሄራዊ ፌዴሬሽኑም ሆነ መንግስት\nጉዳዩን በሚገባ ሊያጤኑት ይገባል። ኢትዮጵያ የአትሌቲክስ ሀገር ሆና አትሌቶች በበቂ ሁኔታ ስልጠና የሚሰሩበት ሜዳ አለመኖሩ ያሳፍራል።\nአዲስ አበባ ውስጥ አነሰ ቢባል ስምንት የስልጠና ሜዳ ሊኖር ይገባ ነበር። እውነታው ግን ይህ አይደለም። ሌላው ለሀገራችን አትሌቲክስ\nየቁልቁለት ጉዞ ምክንያት ተደርጎ  መወሰድ የሚገባው ልምድና እውቀት\nያካበቱ አንጋፋ ስፖርተኞችን መዘንጋት ነው።በብሄራዊ\nፌዴሬሽኑ አሁን የሚገኙት ወጣት አሰልጣኞችና አትሌቶች ልምድ ያካበቱ ሙያተኞችን ሲጠቀሙ/ሲያማክሩ አይስተዋልም። በኦሎምፒክ፣ በአለም\nሻምፒዮና ውድድሮች ላይ በመሳተፍ ሀገርን ያስጠሩ ትንታግ አትሌቶች ባለቤት መሆኗ ይታወቃል። እነዚህን የትናንት ጀግኖች ልምድና\nእውቀት ከዘመኑ ጋር አዋድዶ መጠቀም ያስፈልጋል። በእርግጥ በአሰልጣኝነቱ ባንመጥን እንኳን፤ ለወጣት አሰልጣኞች ረዳትና አማካሪ\nበመሆን የቀደመውን ልምድ ማካፈል እንችል ነበር። ያለፍንበትንና የሰራንበትን ማሳየቱ ለመጪው ትውልድ ጥሩ ነው ብዬ አስባለሁ። በሀገራችን\nአትሌቲክስ ውስጥ ይህ ባህል ብዙም የለም። አይስተዋልምም። በሌሎች ሀገራት ልምድ ያካበቱ ስፖርተኞችን ከማራቅ ይልቅ ቀርበው እንዲያግዙ፤\nልምዳቸውን እንዲያካፍሉ እንደሚያደርጉ በተለያዩ አጋሚዎች ታዝቤአለሁ። በእኛ ሀገርም ይሄን ልምድ ወስዶ ተግባራዊ ማድረጉ ጥቅሙ\nየጋራ ነው። በሀገራችን ነባራዊ ሀቅ የቀደሙ አትሌቶች አስታዋሽና እውቅና እያገኙ አይደለም።ይህ አይነቱ ውለታበል አካሄድ ስፖርቱን\nገድሎታል የሚል እምነት አለኝ።የሀገር\nባለውለታዎች የጊዜ ክፍያ በሀገራችን\nየቀድሞ አትሌቶችን ብዙን ጊዜ አስታውሶ እውቅና የመስጠቱ ዝንባሌ በእጅጉ ትንሽ ነው።  በዓለም አቀፍ መድረኮች የአትሌቲክስ ውድድሮች በመሳተፍና በማሸነፍ የሀገራችንን\nሰንደቅ አላማ በዓለም ህዝብ ፊት እንዲውለበለቡ ያደረጉ በርካታ የቀድሞ አትሌቶች አሉ። እነዚህ የቀድሞ አትሌቶች አሁንም በህይወት\nይገኛሉ።  በጉብዝናቸው ወራት የሀገራችንን ስም ያስጠሩትን እነዚህን\nባለውለታዎች ፈልጎ እውቅና መስጠትና ድጋፍ ማድረግ ትልቅ ቁም ነገር ነው። \nይሁን እንጂ፤ ይህ አይነቱ ሁኔታ በሀገራችን ብዙም ጠንካራ አይደለም። አስታውሶ እውቅና የመስጠት ባህሉ/ልምዱ እምብዛም\nነው። ይህ መሆን የለበትም። በእርግጥ በቅርቡ ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ (ምንም እንኳን ቢዘገይም) አስታውሶን ትጥቅና የተወሰነ ገንዘብ\nድጋፍ አድርጎልናል። ፌዴሬሽኑ ይሄን ሲያደርግ እኔ እውነቴን ነው ከእንቅልፌ የባነንኩኝ መስሎኛል። “ለካስ ያውቁናል” ነበር ያልኩት፤\nይህ ዓይነቱ ተግባር ሊቀጥል ይገባል።አዲስ\nዘመን የካቲት 202011በዳንኤል\nዘነበ", "passage_id": "3bb584c0ee64e26c05d6518b8ed575f6" }, { "passage": "ጥር\n\nኦሊቨር ምቱኩድዚ\n\nበጎርጎሳውያኑ አቆጣጠር 1970ዎቹ የዚምባብዌን የነጭ ጨቋኝ አገዛዝ በመቃወም የአብዮቱ ድምፅ የሆነው ኦሊቨር ምቱኩድዚ የዚምባብዌ ምሰሶ ተደርጎ ይታያል። በቅፅል ስሙ \"ቱኩ\" የሚታወቀው ስመ ጥሩው ዘፋኝ ከፖለቲካው በተጨማሪ ኤችአይቪ ኤድስ እንዲሁም ሌሎች ማህበራዊ ቀውሶችን በግጥሙ ውስጥ የሚያነሳ ሁለ ገብ አርቲስት ነበር። \n\nሁዋሪ ማናር\n\nየአልጀሪያን የሃገረሰብ የባህል ሙዚቃ ወደፊት ማምጣት የቻለ፤ እንዲሁም አነጋጋሪ ጉዳዮችንም በሙዚቃው በመድፈሩም አልጀሪያውያን ያወሱታል። ህይወቱ ያለፈው የፕላስቲክ ቀዶ ጥገና እያደረገ በነበረበት ወቅት ነው። ተችዎች በግጥሙ የሚያነሳቸው የማህበሩ ስስ ጉዳዮች መካከል የተመሳሳይ ፆታ አፍቃሪ መካተቱን ያወግዙታል።\n\nአህመድ ሁሴን ሱዋሌ\n\nበጋናዋ መዲና አክራ በሚገኘው የወላጆቹ ቤት በተተኮሰበት ጥይት የተገደለው ታይገር አይ (የነብር አይን) የሚል መጠሪያ ያለው የምርምር ጋዜጠኞች ቡድን አባል ነበር። በጋና በእግር ኳስ ሊጎች ላይ የተንሰራፋውን ሙስና ያጋለጠም የምርምር ዘገባም ሰርተዋል። ፖሊስ ከስራው ጋር በተያያዘ እንደተገደለ እምነት አለው።\n\nየካቲት \n\nቢሲ ሲልቫ\n\nኮንቴምፖራሪ ተብሎ በሚጠራው የአፍሪካ ጥበብ ትልቅ ስፍራ ያላት ቢሲ ሲልቫ በሌጎስ 'ኮንቴምፖራሪ አርት ኢን ሌጎስ' የሚባል ማዕከል እንዲሁም አሲኮ የተባለ ለመላው አፍሪካዊ ስነ ጥበብን የሚያስተምር የትምህርት ስርአት መስራች ናት። በመላው አለም የአፍሪካን ስነጥበብ ስራዎች የሚያንፀባርቁ አውደ ርዕዮችን አሰናድታለች። በጎርጎሳውያኑ 2014 ጄዲ ኦክሃይ ኦጄኬሬ የተባለው ፎቶግራፍ ስራዎችን የመሰነድን ጠቃሚነት አስመልክቶ ቢቢሲ ባናገራት ወቅት እየሞቱ ያሉ ባህሎችና ልምዶችን ልንጠብቃቸው ይገባል ብላለች። \n\nፍራንስ አልበርት ሬኔ\n\nሲሸልስ ከእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ነፃ መውጣቷን ተከትሎ በጎርጎሳውያኑ 1977 በመፈንቅለ መንግሥት ስልጣን ያዙ፤ ፍራንስ አልበርት ሬኔ ሲሸልስንም ለ27 አመታት ገዝተዋል።\n\nደጋፊዎቻቸው በሶሻሊስት ርእዮተ አለም የተቃኘ ልማት አምጥተዋል ቢሏቸውም ተችዎቻቸው ግን ጨቋኝ ነበሩ ይሏቸዋል። \n\nዶሮቲ ማሱካ\n\nበጎርጎሳውያኑ አቆጣጠር 1950ዎቹ በደቡብ አፍሪካ ዝቅተኛው ማህበረሰብ ውስጥ በሙዚቃው አለም እንደ ጀግኒት የምትታይ ነበረች። የፖለቲካ ግጥሞቿም በአፓርታይድ አገዛዝ ዘንድ አልተወደደም፤ ብዙ ነገርም አስከፍሏታል። ዳንኤል ማላን ስለተባለው የአፓርታይድ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የኮንጎ መሪ የነበሩት ፓትሪስ ሉምምባ አገዳደል ጋር የተያያዙ ሴራዎችን በግጥሟ ውስጥ ማካተቷም ለሰላሳ አመት ግዞት ዳርጓታል። \n\nካሮሊን ምዋታ\n\nፖሊስ የሚያከናውናቸውን ግድያዎች አፈንፍኖ በመሰነድ የምትታወቀው ካሮሊን ምዋታ ለአምስት ቀናት ከጠፋች በኋላ አስከሬኗ በሌላ ሰው ስም ተመዝግቦ ተገኝቷል። ባለስልጣናቱም ህጋዊ ካልሆነ ፅንስ ማቋረጥ ጋር ሞቷን አያይዘውታል። አለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቲ አምነስቲ ሞቷ ለሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ከፍተኛ ድንጋጤን የፈጠረ ነው ብሎታል። \n\nአለም አቀፍ ዝናን ያተረፉት ስመ ጥር ፀሃፊ ቻርለስ ሙንጎሺ ታላላቅ ሽልማቶችን ማሸነፍ የቻሉ ናቸው። 'ካሚንግ ኦፍ ዘ ድራይ ሲዝን' የተሰኘው የአጫጭር ታሪኮች ስብብ የሆነው መፅሃፋቸው እንደ ጎርጎሳውያኑ 1972 ዚምባብዌን ያስተዳድር በነበረው ቅኝ ገዥም ታግዶ ነበር። \n\nክሪስ ካንታይ\n\nካታንዳ በሚል ቅፅል ስሙ የሚታወቀው ራፐር በዘርፉ ፈር ቀዳጅ ከሆኑት ሙዚቀኞች አንዱ ነው። በግጥሞቹና በአዘፋፈኑም ስታይል በጎርጎሳውያኑ 2000ዎቹ መግነን ችሎ ነበር።\n\nየካቲት \n\nየአፍሪካ ሲኒማ መስራች የሚባሉት ሜድ ሆንዶ በጎርጎሳውያኑ 1967 የሰሩት' ሶሌሊ' የሚል ርዕስ የተሰጠው ፊልምም በዘርፉ... ", "passage_id": "3517512a64101fd2913729629b9e0b70" } ]
988b6a1a692b07ac3cb3a6cddd6bdcad
430c8d9066097f3359b2f48bb53a1754
አካል ጉዳተኞችን ተደራሽ ያላደረገው ስፖርት
 ስፖርት እድሜ ጾታና የሰውነት አቋም የማይለይ አካላዊ እንቅስቃሴና የሰው ልጆች መብት ምት ጭምር ነው፡፡ ይህም ማለት አካል ጉዳተኞችንም አካቶ የአካላዊና አእምሯዊ ጤናን ለመጠበቅ የሚያስችል ሚዛን ነው፡፡ ይሁን እንጂ በብዙ ሃገራት አካል ጉዳተኞችን በስፖርት ማሳተፍ አልተለመደም፡፡ በእርግጥ በዓለም አቀፍ ደረጃ አካል ጉደተኞችን በስፖርታዊ እንቅስቃሴና ውድድር ማካፈል እየተለመደ የመጣው ከ20ኛው ክፍለ ዘመን ወዲህ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ እንቅስቃሴ እንደሚጠበቀው ጎልቶ ባለመታየቱ አካል ጉዳተኞችን ለማሰብ ሁሌም በየዓመቱ ህዳር ወር ላይ ይከበራል፡፡ አካል ጉዳተኞች በሁሉም እንቅስቃሴዎች ለመሳተፍ የሚገድባቸው ነገር አለመኖሩን ለማስገንዘብም ከሚከናወኑ ነገሮች መካከል አንዱ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ነው፡፡ ስፖርት ህይወትን በመልካም መንገድ ለመምራት የሚያስችል፣ ጡንቻዎችን የሚያጠነክር፣ ከጉዳት የሚጠበቅና ፈጥኖ ለማገገም የሚረዳ እንዲሁም ድብርትና ተያያዥ የሆኑ ስነ-ልቦናዊ ችግሮችን የሚቀርፍ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህም በመሆኑ ዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ በየአራት ዓመቱ ጉዳት አልባ ስፖርተኞችን ካወዳደረ በኋላ አካል ጉዳተኞች የሚካፈሉበትን ‹‹ፓራሊምፒክ›› ያዘጋጃል፡፡ በመላው ዓለምም እንዲህ ዓይነት ውድድሮችና ቻምፒዮናዎች እየታዩ መጥተዋል፡፡ በኢትዮጵያም ይኸው እንቅስቃሴ አካል ጉዳተኞችን በስፋት ተደራሽ ባያደርግም አዲስ አበባን በመሳሰሉ ከተሞችና ሌሎች ክልሎች ላይ ውድድሮች ይካሄዳሉ፡፡ ነገር ግን ስፖርታዊ ውድድርና አካላዊ እንቅስቃሴ ለማድረግ የተዘጋጁ ምቹ ሁኔታዎች በምን ደረጃ ላይ ይገኛሉ የሚለውን መፈተሽ አስፈላጊ ነው፡፡አቶ ንጉሴ ግደይ የአዲስ አበባ አካል ጉዳተኞች ማህበር ፕሬዚዳንት ሲሆኑ፤ በየዓመቱ የአካል ጉዳተኞች ቀንን በማስመልከት ስፖርታዊ ውድድር እየተካሄደ ዘንድሮ አስረኛ ላይ መድረሱን ይጠቁማል። የዚህ መርሃ ግብር መካሄድ አንዱ ምክንያት በከተማዋ የሚኖሩ አካል ጉዳተኞች አካል ጉዳት ከሌለባቸው እኩል በማንኛውም የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች መሳተፍ እንደሚችሉ ግንዛቤ መፍጠርም ነው። ከእነዚህ ጉዳዮች መካከል አንዱ ስፖርት ሲሆን በዋናነት ለጤናና ለአካል ጥንካሬ ፋይዳው የጎላ በመሆኑ አካል ጉዳተኛ ስፖርተኞችን ለማፍራትም የውድድሩ መካሄድ ጠቀሜታ አለው። አካል ጉዳተኞች ከአካላቸው አንዱ ቢጎድልም ዘወትር አካላዊ እንቅስቃሴ ቢያደርጉ ለቀሪው አካላቸው ብርታት ይሆናቸዋል። አሁን በዓለም ደረጃ እነሱን ያማከሉ የስፖርት አይነቶችም በርካታ ናቸው። እነዚህ ስፖርቶች ላይ ቢሳተፉ ለአካል ጥንካሬ ስነ-ልቦናቸው እንዲገነባ እንዲሁም በራስ የመተማመን ብቃታቸው እያደገ እንዲሄድ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ስለዚህ አካል ጉዳተኞች በሕመም እንዳይጠቁ እንዲሁም ጉዳታቸው እንዳይባባስና ባለበት እንዲቆም እንደሚረዳቸውም ፕሬዚዳንቱ ያስረዳሉ። ከዚህም በተጨማሪ ጥሩ አካላዊ ቁመና እንዲኖራቸውም ይረዳል። በእለት ከእለት እንቅስቃሴያቸውና ከሰዎች ጋር በሚኖራቸው ግንኙነትም ደስተኛ እንዲሆኑ ይረዳቸዋል። አዲስ አበባ ከመቆርቆሯ አንስቶ በፕላንም ሆነ በተግባራዊ ስራው አካል ጉዳተኞችን መሰረት አለማድረጋቸውንም ፕሬዚዳንቱ ያስረዳሉ፡፡ ይህም አካል ጉዳተኞችን ከፍተኛ ዋጋ እየስከፈላቸው ሲሆን፤ በስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችም ይህንን ማካተት የተጀመረው በቅርቡ ነው፡፡ ከመግቢያ መውጫዎች ጀምሮ ውስጣዊ ይዞታቸውና ቁሳቁሶቻቸውም ጭምር አካል ጉዳተኞችን ከግምት ያስገቡ አልነበሩም፡፡ በተመሳሳይ ወጣት ማዕከላትም ወጣት አካል ጉዳተኞችን ታሳቢ ያደረጉ አይደሉም፡፡ በዚህም ምክንያት እንቅስቃሴያቸውን አስቸጋሪ አድርጎታል፡፡ በመሆኑም ማህበሩ የተለያዩ ግንባታዎች አካል ጉዳተኞችን ታሳቢ አድርገው እንዲካሄዱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተነጋገረ መሆኑን ፕሬዚዳንቱ ይጠቁማሉ፡፡ በከተማዋ በርካታ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እንደመኖራቸው በጥናት ተደግፎ ተሻሽለው ሁሉንም ማህበረሰብ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን እንዲሁም ተደራሽ የሚሆኑበትን መንገድ በማመቻቸት ላይ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 12/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=37833
[ { "passage": "ስፖርትን ከስፖርታዊ እንቅስቃሴው በተጨማሪ ለሌሎች መልካም ተግባራት የመጠቀሙ አዝማሚያ በሀገራችንም ሆነ በመላው ዓለም የተለመደ ነው፡፡ ለአብነትም በሀገራችን በስፖርት ዘርፍ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ግለሰቦች የሚታወሱባቸው የመታሰቢያ ውድድሮች እና የተለያዩ በሽታዎችን ለመከላከል ታሳቢ ተደርገው የሚዘጋጁ ውድድሮች ተጠቃሾች ናቸው፡፡ በቅርቡ አንድ ኢትዮጵዊ የአትሌቲክስ አሰልጣኝ ስፖርትን እንደ አይነተኛ መሳሪያ በመጠቀም የአየር ንብረት ብክለትን ችግር ለዓለም ማህበረሰብ ማስገንዘብ በሚል ተነሳሽነት ዓለም አቀፍ ይዘት ያለው የጎዳና ላይ ሩጫ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡የአትሌቲክስ አሰልጣኝ ሙሉየ ዕያዩ ይባላል፡፡ ተወልዶ ያደገው በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር በደንቢያ ወረዳ ውስጥ በምትገኝ ሰቀልት አምባጓሊት በምትባል ቀበሌ ውስጥ ነው፡፡ እንደብዙዎቹ የሀገራችን አትሌቶች ከቤት ወደ ትምህርት ቤት እንዲሁም ከትምህርት ቤት ወደ ቤት በሚጓጓዝበት ወቅት እስከ ሀምሳ ደቂቃ በሚወስድ የእግር መንገድ በሩጫ ይመላለስበት ስለነበር አጋጣሚው ለአትሌቲክስ ስፖርት መነሻ እንደሆነው ይናገራል፡፡ወጣቱ አሠልጣኝ ሙሉየ እያዩ በአሁኑ ወቅት የዓለም አንገብጋቢና ትልቅ የራስ ምታት የሆነውን የአየር ንብረት ብክለትና የሙቀት መጨመርን ለመከላከል ብሎም ለመቀነስ እንዲቻል ስፖርትን እንደ ግብዓት በመጠቀም የሚተገበር ዓለም አቀፋዊ የሆነ አዲስ የፈጠራ ሀሳብ አመንጭቶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ ይህ የፈጠራ ሥራው ደግሞ ስፖርትን እንደ ትልቅ መሳሪያ በመጠቀም በዓለም አቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ በአየር ፀባይ ለውጥ ላይ የሚሰራ ሲሆን፤ ይህንን ተግባራዊ ለማድረግም 17 ዓመታትን ፈጅቶበታል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ከኢትዮጵያ የአእምሯዊ ንብረት የፈጠራ ሥራ ባለቤትነት ማረጋገጫ አግኝቶ ‹‹ኢንተርናሽናል ክላይሜት ቼንጅ ኤንድ ስፖርት ኦክስጅንን ተጠቅመን ኃይላችንን እናድስ (ኦ.ተኃ)›› በሚል ተቋማዊ ሥም ተደራሽነቱን ለማስፋት የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡አሠልጣኙ እንደሚለው፤ ተቋሙ የአየር ንብረት ለውጥን ለመታደግ ካሰናዳቸው 306 የመፍትሄ ሀሳቦች ውስጥ ስፖርት አንዱ ሲሆን፣ ይህንኑ ግንዛቤ ለአጠቃላይ የዓለም ማኅበረሰብ ለመስጠት መነሻና መድረሻውን አዲስ አበባ ሰሚት አደባባይ ላይ ያደረገ የ15 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር የካቲት 10 ቀን 2011 ዓ.ም ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ የውድድሩ ስያሜ ‹‹ኢንተርና ሽናል ስፖርት ፎር ክላይሜት ቼንጅ – ኦተሃ›› (International Sport for Climate Change) ሲሆን፤ ስፖርትና ተፈጥሮ የማይለያዩ የሰው ልጅ የህይወቱ መድህን አለኝታውና እስትንፋሱ በመሆናቸው፤ ስፖርታዊ መድረኩን በመጠቀም የዓለማችን አሳሳቢ ችግር እየሆነ የመጣውን የአየር ንብረት ለውጥ ብክለትንና የሙቀት መጨመርን ለመከላከል የሚያስችል የመፍትሄ ሀሳቦችን ለማመላከት፤ ተሳታፊዎች የውድድሩ ተቋዳሽ በመሆን ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄ በጋራ እንዲሰሩ ለማስቻል የሚል ዓላማን ያነገበ የውድድር መድረክ መሆኑን አስታውቋል፡፡በውድድሩ ላይ የውጭ አገራት ተሳታፊዎችን ጨምሮ አንጋፋና ታዋቂ ስፖርተኞች፤ ዕድሜያቸው ከ11 ዓመት በላይ የሆናቸው በርካታ አትሌቶች ይሳተፋሉ፡፡ ከክልሎች፣ ከከተማ አስተዳደሮች፣ ከክለቦች፣ ከተቋማትና ዓላማውን ከሚደግፉ አካላት የተወጣጡ ግለሰቦች የሚሳተፉበት ውድድር በመሆኑ አጠቃላይ ተሳታፊዎችም እስከ 40ሺህ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ዋና ሳጂን አትሌት አሰፋ መዝገቡም የዚህ ውድድር አምባሳደር እንደሆነ አሠልጣኙ ጠቁሟል፡፡እንደ አሰልጣኙ ገለጻ፤ በውድድሩ ከአንደኛ እስከ 20ኛ ለሚወጡ ተሳታፊዎች ሜዳሊያን ጨምሮ ልዩ የሆነ ሽልማትና ከማግኘታቸውም በተጨማሪ የውጭ አገር እድሎችን ጥረት ይደረጋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ከአንደኛ እስከ አምስተኛ ለሚወጡ ተወዳደሪዎች በዓይነቱ የተለየና እስካሁን በአገር ውስጥ ውድድር ሲሰጥ ከነበረው የአትሌቲክስ ሽልማት በእጅጉ የተሻለ የገንዘብ ሽልማት እንዲያገኙና ‹‹International Climate Change and Sport- ኦተሃ››ን ወክለው አምባሳደር በመሆን በውጭ አገራት የስፖርት ሁነቶች ላይ እንዲሳተፉ ይደረጋል፡፡ በዕለቱ ከውድድር መልስ ሁሉም ተሳታፊዎች በመጪው ክረምት በስማቸው ችግኝ የተከሉበትን ቁስ የመረካከብ ሥነ-ስርዓት ይኖራል፡፡ በውድደሩ የታዋቂ ስፖርተኞችና የሌሎች ተሳታፊዎች የመነሻ ሰዓትም የተለያየ እንዲሆን ይደረጋል፡፡ጥር 24/2011አዲሱ ገረመው", "passage_id": "4128d53320d62d24fd8f6450e19dcf6c" }, { "passage": "ስፖርት የሰላም፣ ፍቅር፣ የአብ ሮነትና የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የወንድማማችነት ልዩ መገለጫ ነው። ስፖርት ዘር፣ ሃይማኖት፣ ፆታና ቀለምን አይለይም። በየት ኛውም ሁኔታ ውስጥ የስፖርታዊ እንቅስቃሴ አስኳል ሃሳብ ወዳጅነትና መተሳሰብ መሆኑ ይታወቃል። በታሪክ ገጾች እንደሰፈረውም በሰው ልጅ ታሪክ ባጋጠሙ በጎም ሆኑ መጥፎ ክስተቶች ስፖርት በአጋርነት ተሳትፏል። ስፖርታዊ ክንዋኔዎች ሰላምንና አንድነትን የሚሰብኩ እንደመሆናቸው በማህበራዊ፣ ፖለቲ ካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች በመግባት ሚናቸውን ሲወጡም ኖረዋል። ስፖርት ሰብዓዊነትን ያነገበ የልግስና ማዕድ መሆኑን የአለም ህዝብ እየፈተነ ባለው የኮሮና ወረርሽኝን ለመዋጋት ሲደረግና እየተደረገ ባለው ርብርብ ላይ በስፖርት ቤተሰቡ በኩል የታየው ተሳትፎ ትልቅ ማሳያ ይሆናል።የኮቪድ -19 ወረርሽኝ የአለም ህዝብን እንደ ቅጠል ከማርገፍ በተጨማሪ በተለያዩ መስኮች ላይ ይህ ቀረሽ የማይባል መቃወስን አስከትሏል።የስፖርት ኢንደስትሪው ደግሞ\nዋነኛ ሠለባ ከሆኑ\nመስኮች በግንባር ቀደምነት\nይጠቀሳል። የቫይረሱ ስጋትነት\nበዓለም አቀፉ የጤና\nተቋም ከተረጋገጠበት ጊዜ\nጀምሮ፤ ውድድሮች ተቋርጠዋል፤\nተሰርዘዋል። ይህን ተከትሎ\nየአለምን ኢኮኖሚ በማንቀሳቀስ\nረገድ ግንባር ቀደም\nተጠቃሽ የሆነው የስፖርት\nኢንደስትሪውን በአጭር ጊዜ\nለከፍተኛ የፋይናነስ ቀውስ\nዳርጎታል።በአለም ስፖርት ላይ\nየተፈጠረው ከፍተኛ መቃወስ\nግን የስፖርቱን ማኅበረሰብ\nየሰብዐዊነት ውሃ ልክ\nከመሆን አላደናቀፈውም ነበር።የስፖርት\nቤተሰብ በወረርሽኙ ጉዳት\nከመቆዘም ይልቅ ,፤\nየሰብዐዊነት ጋሻን በማንሳት\nአለምን ከጭንቅ ለማውጣት\nበሚደረገው ርብርብ ሰፊ\nተሳትፎ ሲያደርግ ነበር፤እያደረገም\nይገኛል። በስፖርቱ መስክ\nዓለም አቀፍ ዝናን\nካተረፉ ግለሰቦች እስከ\nዓለም አቀፍ ተቋማት\nድረስ ወረርሽኙን ለመመከት\nእየተደረገ ባለው ርብርብ\nሲያደርጉ የነበረው ተሳትፎ\nትልቅ ቦታ አጊንቷል።የስፖርቱ\nዘርፍ ባለድርሻ የሚባሉት\nአካላት በተናጠልና ተቋማዊ\nበሆነ መልኩ ድጋፍ\nለሚሹ ድጋፍ በማድረግ\nእንዲሁም ገንዘብ በማሰባሰብ\nወረርሽኙን የመዋጋት ሂደቱን\nበፊት አውራሪነት ሲመሩ\nታዝበናል።በተለያዩ ሀገራት ዓለም\nአቀፉን ወረርሽኝ ለመዋጋት\nበስፖርቱ ማኅበረሰብ ዘንድ\nየታየው ተሳትፎ በሀገራችንም\nተመሳሳይ ሲሆን ታዝበናል። በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት ይፋ ከተደረገበት ከወርሃ መጋቢት መጀመሪያ አንስቶ የስፖርቱ ማህበረሰብ ድርሻ ግዙፍ ነው። በስፖርት ዘርፍ የሚገኙ የመንግሥትና የግል ተቋማት፣ የስፖርት ማህበራት፣ ተጫዋቾች፣ አትሌቶች፣ የእግር ኳስ ክለቦችና ተጫዋቾች ወረርሽኙን ለመከላከል የሚደረገውን ርብርብ ተሳትፎ ሲያደርጉ ነበር።በዘመነ ኮሮና የስፖርቱ ማኅበረሰብ ሰብዐዊነትን መሰረት ያደረገው እንቅስቃሴ እንደቀጠለ ይገኛል። በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ስፖርት ኮሚሽን አስተባባሪነት ሚያዝያ 17 ቀን 2012 ዓ.ም የተጀመረውን «ማዕድ ማጋራት» መርሃ ግብር ሶስተኛው ዙር ከትናንት በስቲያ በአዲስ አበባ ትንሿ ስታዲየም ተጀምሯል።የስፖርቱ ማኅበረሰብ ህዝባዊነት\nየሚያረጋግጥ መሆኑ የተነገረለት\nሶስተኛው ዙር ማዕድ\nየማጋራት መርሃ ግብር\nሲጀመር ፤ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ\nስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር\nአቶ ኤሊያስ ሽኩር\nእንደተናገሩት፤ የኮሮና ቫይረስ\nወረርሽኝ መከሰት የመደጋገፍ\nእና የመረዳዳት የቀደመ\nባህላችንን የበለጠ እንዲጎለብት\nአድርጓል።የኮሮና ቫይረስ ወደ\nሀገራችን ከገባ ጀምሮ\nወረርሽኙን ለመከላከልና ለመቆጣጠር\nየስፖርቱ መንግስታዊ እና\nህዝባዊ አደረጃጀቶች፣ ታዋቂ\nአትሌቶች፣ የደጋፊ ማህበራት፣\nበአጠቃላይ የስፖርት ቤተሰቡ\nህብረተሰቡን በማንቃት እና\nኢኮኖሚያዊ ጫናውን ለመቋቋም\nየሚያግዝ የገንዘብ ድጋፍ\nበማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን\nበመጣት ላይ ያደረጉትን\nተሳትፎ ጠቅሰዋል። የስፖርቱ\nማኅበረሰብ ድጋፍ ተጠናክሮ\nየሚቀጥልና የምገባ መርሃ\nግብሩ መጀመር ለዚሁ\nማሳያ ይሆናል ብለዋል።\nየጎዳና ላይ የሚገኙ\nወገኖቻችንን በተወሰነ መልኩ\nለማገዝ አንድ ወር\nየሚቆይ የምገባ መርሃ\nግብሩ ይሄንኑ ሚና\nመሰረት ባደረገ መልኩ\nመጀመሩን የተናገሩት አቶ\nኤልያስ፤ በስታዲየም ዙሪያ\nመርሃ ግብሩ እንዲደረግ\nየተመረጠበትን ምክንያት መኖሩን\nአመልክተዋል። «በወቅታዊ የኮሮና\nወረርሽኝ ምክንያት ስርጭቱን\nለመቆጣጠር ሲባል በተለይ\nስታዲየም ዙሪያ የሚገኙ\nባር እና ሬስቶራንቶች\nመዘጋታቸው እና በአካባቢው\nያለው እንቅስቃሴ መቆሙ\nይታወቃል። ሬስቶራንቶች መዘጋታቸውን ተከትሎ\nከሬስቶራንቶች ተመላሽ የሚሆኑ\nምግቦችን ይጠቀሙ የነበሩ\nየጎዳና ተዳዳሪዎችም ሆነ\nበስታዲየም አካባቢ የተለያዩ\nነገሮችን በመሸጥ ይተዳደሩ\nየነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎች\nለከፋ ችግር ተጋልጠዋል።\nበመሆኑም ጊዜው የከፋ\nችግር ላጋጠማቸው የህብረተሰብ\nክፍሎች እጃችን የምንዘረጋበት፤\nየጋራ መከራችንን በመተጋገዝ የምናልፍበት መሆኑን በማመን እና ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ነው »ሲሉ አብራርተዋል። አቶ ኤልያስ በመጨረሻ የተጀመረው ተግባር የሚቋረጡ ሳይሆን በቀጣይም እነዚህ ወገኖቻችን በዘላቂነት ህይወታቸውን ሊመሩበት በሚችሉ ጉዳዮች ላይ የስፖርት ቤተሰቡ በሙሉ አቅሙ የሚደግፍ መሆኑን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና የቢጂ አይ ኢትዮጵያ አመራሮች በጋራ በመሆን ባስተላለፉት መልዕክት ደግሞ፤ የምገባ መርሃ ግብሩ በቀጣይ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።በስፖርት ኮሚሽን አስተባባሪነት የተጀመረው ማዕድ የማጋራት መርሃ ግብሩ 3ኛ መጀመሩን በዘመነ ኮሮና የስፖርቱ ማኅበረሰብ ሰብዐዊ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን ያመላክታል ተብሏል።ሰኔ 17 ቀን 2012 ዓ.ም የተጀመረው ሶስተኛው ዙር «ማዕድ ማጋራት» መርሃ ግብሩ 300 የጎዳና ተዳዳሪዎችን ለአንድ ወር ያህል እንደሚመገቡ ታውቋል።በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ስፖርት ኮሚሽን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና ከቢ. ጂ አይ ኢትዮጵያ በጋራ በመሆን የመጀመሪያው ዙር ሚያዝያ 17 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ወራት የዘለቀ ነበር።የስፖርት ተቋማቱ ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ያቀረቡትን «የማዕድ ማጋራት ብሄራዊ ጥሪን»ተከትሎ መርሃ ግብሩን የጀመሩት ሲሆን፤ 300 የጎዳና ተዳዳሪዎችን ለአንድ ወር ያህል በመመገብ ሀሳቡን ተግብረውታል።ሁለተኛ ዙር ግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ወር ያህል ተግባራዊ ተደርጎ በመጠናቀቁ ፤ሶስተኛው ዙር መርሃ ግብር ከሰኔ 17 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሐምሌ 16 ቀን 300 የጎዳና ተዳዳሪዎችን በምገባ መርሃ ግብሩ ተጠቃሚ እንደሚደረጉ ታወቋል።በ3ኛው ዙር የምገባ ፕሮግራም የኢትዮጵያ መድን ድርጅት 600 ሺ ብር ድጋፍ በማድረግ የወገን አጋርነቱን ማሳየቱ ተነግሯል። የምገባ መርሃ ግብሩን\nለሶስተኛው ዙር ማስቀጠል\nመቻሉ የስፖርቱ ማህበረሰብ\nበዘመነ ኮሮና ማህበራዊ\nኃላፊነትን በመወጣት እንደ\nከዚህ ቀደሙ ሁሉ\nየተጠናከረ ተሳትፎ እያደረገ\nመሆኑን አመላካች ሆኗል።\nየመርሃ ግብሩ ተግባራዊነት\nጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ\nአህመድ ያቀረቡትን «የማዕድ\nማጋራት ብሄራዊ ጥሪን»\nወደ መሬት ከማውረድ\nበተጨማሪ፤ ስፖርት -ሰብዐዊነትን\nጋሻ ያደረገ ማኅበራዊ\nክዋኔ መሆኑን በተግባር\nእንዲረጋገጥ ያረጋገጠ መሆኑን\nብዙዎች መስክረውለታል።አዲስ\nዘመን ሰኔ 19/2012ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "a05aeb114450545a22415d9f42e50c22" }, { "passage": "በዓለማችን ላይ\nተወዳጅነትን ያተረፉ ስፖርቶች እንደየ ባህሪያቸው እና እንደሚፈልጉት የማዘውተሪያ ስፍራ አይነት በቤት ውስጥና ከቤት ውጪ (indoor and outdoor) ይካሄዳሉ፡፡ አንዳንድ የውድድር አይነቶች ለምሳሌ የአትሌቲክስ በሁለቱም የመወዳደሪያ ስፍራዎች እንደሚደረጉት ሁሉ በጅምናዚየም ውስጥ ወይም ከቤት ውጪ ብቻ ሊዘወተሩ የሚችሉ የስፖርት አይነቶችም በርካታ ናቸው፡፡በቴክኖሎጂ ድጋፍ\nየሰው ልጅ ኑሮ እጅጉን በረቀቀበት በዚህ ጊዜ ተወዳጅነትን ያተረፉ የስፖርቶች አይነቶችም በተመሳሳይ እያደጉና እየዘመኑ ነው። ይህን ተከትሎ ደግሞ አገራት እንደ አካባቢያቸው ነባራዊ ሁኔታና እንዳላቸው እምቅ አቅም ውጤታማ ሊሆኑ የሚችሉባቸውን ስፖርቶች ለይተው ለስኬታማነት እና ድልን ለመጎናፀፍ ተግተው ይሰራሉ፡፡ አንዳንዶቹ ያላቸውን የአየር ፀባይ አሊያም ልዩ ችሎታ መሰረት አድርገው ይሰራሉ፡፡ ሌሎች\nደግሞ ለረጅም ዘመናት ሲከውኗቸው የቆዩትን ስፖርቶች ሳይበረዙ ዘመናዊ ቅርፅ እንዲኖራቸው በማድረግ ዓለም አቀፍ ይዘት ያላብሷቸዋል፡፡ እነዚህ ከላይ ለማንሳት የሞከርናቸው ስፖርቶች ደግሞ እንደየ ባህሪያቸው የመወዳደሪያ እና የማዘውተሪያ ስፍራቸው ቅርፃቸው የተለያየ ይሆናል፡፡ አንዳንዶቹ የቤት ውስጥ ስፖርት (indoor game) ሲሆኑ ቀሪዎቹ ደግሞ ከቤት ውጪ የሚዘወተሩ (outdoor game) ይሆናሉ፡፡ የረጅም ዓመታት ልምድ\nያካበቱ የስፖርቱ ዘርፍ ባለሙያዎች ቤት ውስጥም ከቤት ውጪም መዘውተር የሚችሉ ስፖርቶችን በማነጻጸር ከቤት ውጪ የሚደረጉት የተሻሉ እንደሆነ የተለያዩ የመከራከሪያ ነጥቦችን በመሰንዘር ይሞግታሉ፡፡ ስፖርትን ቤት ውስጥ ማዘውተር የተሻለ መሆኑን የሚያምኑ ደግሞ ከአየር ፀባይ ጋር በተያያዘ የሚያነሱት ሞጋች ሃሳብ አለ፡፡ እነዚህ ምሁራን ስፖርትን ቤት ውስጥ ማዘውተር ከአየር ፀባይ ጋር በተያያዘ ከሙቀት ወይም ከቅዝቃዜ ተፅዕኖ ማምለጥ እንደሚቻል ያስቀምጣሉ፡፡ውድድሮችና ልምምዶች በአየር ፀባይ መለዋወጥ የተነሳ የመሰረዛቸው እድል ጠባብ መሆኑን በመዘርዘር ቤት ውስጥ ስፖርትን ማዘውተር ለስፖርተኞች፣አሰልጣኞች ከዚያም ሲያልፍ ስፖርቱን ለሚታደሙ ተመልካቾች ምቹ መሆኑን ያብራራሉ፡፡ ከወጪ አኳያም የቤት ውስጥ ስፖርቶች መሰረተ ልማት አንዴ መገንባት ከተቻለ ለረጅም ጊዜ ተጨማሪ ወጪና ልፋት እንደማይጠይቅ ያምናሉ፡፡ ለዚህም ቤት ውስጥ ስፖርትን ማዘውተሪያ (ጅምናዚየም) አንድ ጊዜ መገንባት ከተቻለ መሰረተ ልማቱን ለመንከባከብ ግፋ ቢል ፅዳት መጠበቅ እንጂ ከቤት ውጪ የሚገነቡ ማዘውተሪያዎች በአየር ፀባይ መለዋወጥ በየጊዜው እንደሚፈልጉት ተጨማሪ የጥገና ወጪ እንደማይሹ ነው የሚያስረዱት፡፡ከቤት\nውጪ የሚገኙ የመወዳደሪያ ስፍራዎች የተሻሉ መሆናቸውን የሚያምኑት ወገኖች በበኩላቸው ስፖርትን ቤት ውስጥ ለማዘውተር በዋናነት ጅምናዚየም የመገንባት ወጪው በራሱ የተጋነነ መሆኑን በማስቀመጥ ሀሳቡን ይቃወማሉ፡፡ ከዚህ ባሻገር ስፖርትን ቤት ውስጥ ከማዘውተር ይልቅ ከቤት ውጪ መከወን የተሻለ ነፃነት እንደሚሰጥ በማንሳት ጠንካራ የመከራከሪያ ነጥብ ያስቀምጣሉ፡፡ ሁለቱም ወገኖች ግን በቂ የፋይናንስ አቅም ካለ የቤት ውስጥም ሆነ ከቤት ውጪም ያሉ የስፖርት መሰረተ ልማቶቹ መሟላታቸው ተገቢ መሆኑ ላይ ልዩነት የላቸውም፡፡ ይሁን እንጂ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ታዳጊና አቅም የሌላቸው አገራት አቅማቸውን አሳድገው ሁሉንም ማሟላት እስኪችሉ አዋጭ ለሆነው መንገድ ቅድሚያ መስጠት የግድ እንደሚላቸው ነው ባለሙያዎቹ ጎራ ለይተው ሃሳባቸውን የሚሰነዝሩት፡፡ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ለስፖርት መሰረተ ልማት ግንባታዎች ትኩረት በመስጠት በተለያዩ ክልሎች ግዙፍ ስቴድየሞችን ጨምሮ ሌሎች መሰረተ ልማቶችን በብዛት እየተገነባ ይገኛል። ከነዚህ መካከል በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍለ አገራት ጎልተው የወጡት ግዙፍ ስቴድየሞች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ከነዚህ መካከል አብዛኞቹ ሁለገብ ሲሆኑ የቤት ውስጥ ስፖርቶች የሚባሉትን ጭምር ከቤት ውጪ ማዘውተር እንዲያስችሉ ሆነው እየተገነቡ ይገኛሉ፡፡ ግንባታቸው የተጠናቀቀም በርካታ ናቸው፡፡ በመግቢያችን ላይ በስፋት ለመጥቀስ እንደሞከርነው እነዚህ ግንባታዎች ለቤት ውስጥ ስፖርቶች (indoor game) ትኩረት አለመስጠታቸውን ለመለየት ብዙ የሚከብድ ነገር የለውም፡፡ አብዛኞቹ የስፖርት መሰረተ ልማቶች እግር ኳስና አትሌቲክስ ስፖርቶች ብቻ ትኩረት የሰጡ ስለመሆናቸው በተለያዩ አጋጣሚዎች ተዘዋውሮ የማየት እድሉ የገጠመው ማንኛውም ሰው በቀላሉ እውነታውን መታዘብ ይችላል፡፡ እነዚህ ግንባታዎች አገሪቷ ካላት እምቅ አቅም አኳያ ‹‹ስፖርትን በቤት ውስጥ ወይም ከቤት ውጪ ማዘውተር የተሻለ ይሆናል›› የሚሉ ጥናቶች ተደርጎባቸው ይሰሩ አሊያም ደግሞ በዘፈቀደ በግብታዊነት ተግባራዊ ተደርገዋል የሚለው ጉዳይ እስካሁን በቂ ምላሽ አላገኘም፡፡ በተለይ ለየትኛው ስፖርት ትኩረት ሰጥተው ነው? በምንስ መስፈርት? የሚለው ጉዳይ አነጋጋሪ ይመስላል፡፡ባለፉት በርካታ ሳምንታት አዲስ ዘመን የተለያዩ ብሔራዊ የስፖርት ፌዴሬሽኖችን በተመለከተ በሰሯቸው ዘገባዎች የቤት ውስጥ ስፖርቶች ትልቁ እንቅፋታቸው የማዘውተሪያ ስፍራ ወይም ጅምናዚየም መሆኑን አስተውሏል፡፡ የቦክስ ፌዴሬሽን የፅሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጳውሎስ ማዳ የቦክስ መፋለሚያ ሪንግ የሚቀመጥበት ጅምናዚየም የስፖርቱ ትልቅ ችግር መሆኑን ነግረውናል። ፌዴሬሽኑ በዚህ ምክንያት ጥራት ያላቸው ውድድሮችን እንደ ልብ ማድረግ አለመቻሉ ስፖርቱን ወደ ኋላ እየጎተተው ሲሆን ከቤት ውጪ ምቹ ባልሆነ ሁኔታ ውድድሮችን ለማድረግም አማራጮቹ ትንሽ ናቸው፡፡ ወደ ፊትም ቢሆን አዲስ አበባ ላይ እየተገነባ ከሚገኘው ብሔራዊ ስቴድየም ጎን ለጎን ይገነባል የተባለው ጅምናዚየም እንጂ ሌላ ተስፋ እንደ ሌለ የፅሕፈት ቤት ሃላፊው መናገራቸውን ዘግበናል፡፡ የብሔራዊ ስቴድየም ግንባታው የእግር ኳስና አትሌቲክስ ስፖርቶችን ብቻ በሚያገለግል መልኩ ግንባታው እየተፋጠነ እንደሚገኝ ያስተዋሉ የስፖርት ቤተሰቦች የጅምናዚየሙ ግንባታ በቅርቡ እውን እንደማይሆን ጥርጣሬ አላቸው፡፡ ከብሔራዊ ስቴድየሙ ጎን ለጎን እንደሚሰራ እቅድ የተያዘለት ጅምናዚየም በአዲስ አበባ ደረጃ ለበርካታ የአገራችን የቤት ውስጥ ስፖርት ፌዴሬሽኖች ተስፋ ነው፡፡ ከቤት ውጪ ለማዘውተር የማይቻለው ‹‹የባድሚንተን›› ስፖርት ከብሔራዊ ስቴድየሙ ጎን ለጎን የሚገነባውንም ይሁን ሌላ ጅምናዚየም በተስፋ ከሚጠባበቁት ግንባር ቀደሙ ነው፡፡ አቶ ዮሴፍ ለታ የኢትዮጵያ ባድሚንተን ፌዴሬሽን የፅሕፈት ቤት ሃላፊ ናቸው፡፡ የባድሚንተን ስፖርት በባህሪው ከቤት ውስጥ ስፖርቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የተሟላ መሰረተ ልማት የሚጠይቅ መሆኑን ባለፈው ሳምንት ባስነበብነው ዘገባ መናገራቸው ይታወሳል። ይህን ስፖርት ለመጫወት አዳራሹ ወይንም ጅምናዚየሙ ቢያንስ ሰባት ሜትር ከፍታ ያለውና ሁለት ጨዋታዎችን በአንድ ጊዜ ማካሄድ የሚያስችል መሆን እንዳለበት ዓለም አቀፍ ህጉም ይደነግጋል። በእርግጥ የባድሚንተን ስፖርትን እንደ ቮሊቦልና ቅርጫት ኳስ አይነት ስፖርቶች ከቤት ውጪ ማዘውተር እንደሚቻል አቶ ዮሴፍ ያምናሉ፡፡ ይሁን እንጂ ባድሚንተንን ከቤት ውጪ ማዘውተር ስፖርቱን በፕሮፌሽናል ደረጃ ለማሳደግና ውጤታማ ለመሆን አያስችልም፡፡ እንደ ባድሚንተንና ቦክስ ስፖርቶች ሁሉ በብሔራዊ ፌዴሬሽን የሚመሩት በርካታ ስፖርቶች ጅምናዚየም የተራቡ ናቸው፡፡ እንደ ቴኳንዶ፣ ጁዶ፣ ካራቴና ጅምናስቲክ ያሉ የፍልሚያ ስፖርቶች የዚህ ችግር ተጋሪ ናቸው፡፡ ከእግር ኳስ በስተቀር ኳስን መሰረት ያደረጉ በርካታ ስፖርቶችም ጅምናዚየም የሚሹ ቢሆንም በአገራችን ካለው ችግር አኳያ ከቤት ውጪ መዘውተራቸው የተለመደ ነው። በእርግጥ ለጊዜውም ቢሆን አንዳንድ የቤት ውስጥ ስፖርቶች ከቤት ውጪ ቢዘወተሩ ችግር ላይኖረው ይችላል። የግዴታ በቤት ውስጥ መዘውተር ያለባቸው ስፖርቶች ችግርን ለመቅረፍ ከወዲሁ ካልታሰበ ግን የሚፈለገውን ውጤት ለማግኘት የማይታሰብ ከመሆኑ ባሻገር ኦሊምፒክን በመሳሰሉ ታላላቅ መድረኮች በአትሌቲክስ ላይ ብቻ ተስፋ አድርጎ መቆየቱን የግድ ያደርገዋል። አትሌቲክሱም ቢሆን ኦሊምፒክና ዋናው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ላይ እንጂ በራሱ የቤት ውስጥና ከቤት ውጪ ተብሎ የተከፈለ በመሆኑ ተጨማሪ የማዘውተሪያ ስፍራ የግድ አስፈላጊ የሚሆንበት ጊዜም መምጣቱ አይቀሬ ነው፡፡በፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን የስፖርት ፋሲሊቲ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኢንጂነር አስመራ ግዛው፣ ‹በኢትዮጵያ እየተገነቡ የሚገኙ የስፖርት መሰረተ ልማቶች በዋናነት ከቤት ውጪ ስፖርቶችን መሰረት ያደረጉ ናቸው› የሚለው ሃሳብ ከተሳሳተ ግንዛቤ የመነጨ መሆኑን ይናገራሉ። ግዙፍ ስቴዴየሞች በአገራችን ሲገነቡ ከቤት ውጪ ስፖርቶችን ብቻ መሰረት አድርገው እንዳልሆነም ያብራራሉ፡፡ የነዚህ ግንባታዎች ዲዛይን በትንሹ አምስት ወይም ስድስት ስፖርቶችን መሰረት ያደረገ ነው፡፡ ትናንሽና ትላልቅ አዳራሽና ጅምናዚየሞች አብረው እየተገነቡ መሆኑን በቀላሉ ማየት እንደሚቻል ያስረዳሉ፡፡ በአደይ አበባ ቅርፅ በሚገነባው ብሔራዊ ስቴድየም ውስጥ ሁለት ደረጃቸውን የጠበቁ ጅምናዚየሞችና ከ2500 ሰው በላይ ማስተናገድ የሚችሉ ሁለት አዳራሾች እየተገነቡ መሆኑንም በምሳሌነት ያስቀምጣሉ፡፡ ይህም የስፖርት መሰረተ ልማቶች ከቤት ውጪ ስፖርቶች ላይ ብቻ ትኩረት አድርገው እንደማይገነቡ ማሳያ አድርገው ያነሳሉ፡፡ በነዚህ ማዘውተሪያዎች ውስጥ ጅምናስቲክ፣ክብደት ማንሳትና ሰውነት መገንባት፣ ባድሚንተንና በርካታ የቤት ውስጥ ስፖርቶችን ማካሄድ እንደሚቻል ኢንጂነር አስመራ ያምናሉ፡፡ አገሪቷ ካላት አቅም፣የስፖርት ባህልና ነባራዊ ሁኔታ አኳያ ጥናት ተደርጎባቸው ነው የሚገነቡት ለማለት ግን ሌላ ጥናት ያስፈልጋል የሚል ሃሳብ ይሰነዝራሉ፡፡ ‹‹እያንዳንዱ ክልል የየራሱን አንድ ዘመናዊ ስቴድየም ለመገንባት ይነሳል፣ በዛም መሰረት ዲዛይን ያደርጋል፣ነገር ግን ያለውን እምቅ የስፖርት አቅም ለይቶ ለሚያስፈልገው ስፖርት ማዘውተሪያ ይሰራል የሚለው ጥናት ይፈልጋል፣እንደ ችግርም የታየው ይሄ ነው፣ የቅንጅት ስራም የሚጠይቅ በመሆኑ እኔ በግሌ እንደ ክፍተት ወስደዋለሁ›› የሚሉት ኢንጁነር አስመራ፤ በሁሉም ግንባታዎች ዲዛይን ለቤት ውስጥ ስፖርቶች የሚሆኑ ማዘውተሪያዎች መካተታቸውን ያነሳሉ፡፡ ነገር ግን በዲዛይናቸው መሰረት ግንባታዎቹ እየተጠናቀቁ አለመሆናቸውን ይቀበላሉ፡፡ በአንዳንድ ክልሎች ከእግር ኳስ እና አትሌቲክስ ማዘውተሪያዎች በተሻለ ጅምናዚየሞች ተጠናቀው ውድድሮችን እያስተናገዱ መሆናቸውን የጠቆሙት ኢንጂነር አስመራ፣የሐዋሳ ስቴድየም ኳስ ሜዳው እንደገና ፈርሶ እየተሰራ በመሆኑ ጎን ለጎን የተገነባው ጅምናዚየም በአንፃሩ በርካታ የቤት ውስጥ ስፖርቶችን እያስተናገደ እንደሚገኝ በምሳሌነት ያስቀምጣሉ፡፡ የቤት ውስጥ ስፖርቶች ትኩረት እንዳልተነፈገው፣ የጂም እቃዎች በዲዛይን መሰረት ተሟልቷል ከተባለ ግን ከበጀት ጋር የሚያያዝ ክፍተት መሆኑን፣ ችግሩ ከትኩረት ጋር የተያያዘ ሳይሆን ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ ስለማይጠናቀቁ እንደሆነ በዝርዝር አብራርተዋል፡፡ በተጨማሪም ከአብዛኞች ስቴድየሞች ጎን ለጎን ጅምናዚየሞች ከሩቅ ጎልተው ስለማይታዩ እንጂ እየተጠናቀቁ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን አስረድተዋል።‹‹ብሔራዊ ስቴድየም የሚገነባበት ዋና አላማ አንድ መገለጫ ስቴድየም እንዲኖር በማሰብ እንጂ የቤት ውስጥ ስፖርቶችን ለማካተት በማሰብ አይደለም›› የሚሉት ዳይሬክተሩ፤ መንግስት ብዙ ገንዘብ አውጥቶ ይሄን ሲያደርግ ደግሞ ግንባታው ለአንድ እግር ኳስ ብቻ እንዲውል እንደማይፈልግ ይናገራሉ። ስለዚህ ስቴድየሙ ገፅታውንና ነባራዊ ሁኔታውን ሳይቀይር ሌሎች ስፖርቶችን እንዲያስተናግድ እንደሚደረግ ይገልፃሉ። ብሔራዊ ስቴድየሙ የቤት ውስጥ ስፖርቶችን ማዘውተር የሚችሉ ነገር ግን ከቤት ውጪ የተገነቡ በርካታ መሰረተ ልማቶች አካቶ የያዘ ነው፡፡ ዳይሬክተሩ ከላይ ከጠቀሱት ሀሳብ በተቃራኒ የግዴታ በቤት ውስጥ መዘውተር ያለባቸው ስፖርቶች ችግር ጅምናዚየም መሆኑን ይናገራሉ፡፡ አሁን እየተገነቡ የሚገኙት ጅምናዚየሞችም በቂ አለመሆናቸውንም ያምናሉ፡፡ ይህን ክፍተት ለመቅረፍ ግን የግል ባለሃብቶች ተሳትፎ እያደረጉ መሆኑን አንስተው መንግስትም የቤት ውስጥ ስፖርቶች ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት አለበት የሚለው ቀጣይ የቤት ስራ እንደሆነ ያብራራሉ። መንግስት ትላልቅ የስፖርት መሰረተ ልማቶችን እየገነባ በሚገኝበት በዚህ ወቅት ግን ትላልቅ ጅምናዚየሞችን መገንባት ከበጀት እጥረት አኳያ ተገቢ ነው የሚል እምነት የላቸውም፡፡ በጊዜያዊነት ያሉትን በጋራ ተናቦና አብቃቅቶ መጠቀም አስፈላጊ መሆኑንም ነው በምክረ ሃሳብ ደረጃ የሚያነሱት፡፡ ለዚህም በቂ መሰረተ ልማት አለ ብለው ያምናሉ፡፡መንግስት በተለያዩ ክልሎች የስፖርት መሰረተ ልማቶች እየገነባ መሆኑ እሙን ነው፡፡ ለጊዜውም ቢሆን አስገዳጅ ሁኔታዎች በመኖራቸው የቤት ውስጥ ስፖርቶችም ከቤት ውጪ ባሉ ማዘውተሪያዎች እንዲከወኑ በማድረግ ግንባታዎችን እንደሚያከናውን መካድ አይቻልም፡፡ ከግዙፍ ስቴድየሞች ጎን ለጎን የጅምናዚየምና ሌሎች ስፖርቶች ማዘውተሪያ ግንባታዎች በዲዛይን መካተትም ግን ‹‹ለቤት ውስጥ ስፖርቶች ትኩረት ተሰጥቷል›› ማለትም አይደለም፡፡ ያሉትን መሰረተ ልማቶች አብቃቅቶና ተናቦ መጠቀም ሌላ ጉዳይ ነው፡፡ በቂ መሰረተ ልማት አለ ማለት ግን ወደ ፊት መንግስት ለቤት ውስጥ ስፖርቶች ትኩረት አድርጎ መስራት ይኖርበታል ከሚለው ሃሳብ ጋር አይጣጣምም፡፡ በቂ መሰረተ\nልማት ካለ መንግስት\nትኩረት ሰጥቶ የሚሰራበት\nምክንያት አይኖርምና፡፡ ስለዚህ\nየኢንጂነር አስመራ አስተያየት\nእርስበራሱ የሚጣረስ ነው።\nመንግስት ትላልቅ የስፖርት\nመሰረተ ልማቶችን እየገነባ\nበሚገኝበት በዚህ ወቅት\nትላልቅ ጅምናዚየሞችን መገንባት\nከበጀት አኳያ አያስኬድም\nማለትም በግልፅ የመንግስት\nትኩረት አሁን ላይ ወዴት\nእንዳዘነበለ ያሳያል፡፡ ኢትዮጵያ\nካላት አቅም አኳያ\nየጀመረቻቸውን የስቴድየም ግንባታዎች\nአጠናቃ በቀጣይ ለቤት\nውስጥ ስፖርት ማዘውተሪያዎች\nትኩረት መስጠት ይኖርባታል\nየሚለው ሃሳብ ግን በርካቶችን\nየሚያስማማ ይመስላል፡፡አዲስ ዘመን ቅዳሜ ሰኔ 1/2011", "passage_id": "d9804552fa4ad66c91b4fc59af7b2384" }, { "passage": "ስፖርት\nበስርዓት የሚመራ ውብ ክዋኔ መሆኑ ለተወዳጅነቱ በምክንያትነት ይጠቀሳል። ከአደረጃጀቱ ጀምሮ የትኛውም ዓይነት ስፖርታዊ እንቅስቃሴ የራሱ የሆነ ሂደትና ስርዓት አለው። ይህ ስርዓት ተጥሶ በዘፈቀደ ሲከወን ደግሞ የተወዳጅነቱን ያህል በአደገኛ አካሄድ ላይ ሊገኝ ይችላል። በኢትዮጵያ ስፖርት አደረጃጀት የሚስተዋለውም ይኸው ነው። የተቀመጠለትን አቅጣጫ በመሳቱም፤ ስልጠናው፣ ሰልጣኞች፣ ሃብት፣ ጉልበት፣ ጊዜ፣ … ለብክነትና ለአሰራር ድርርቦሽ ተዳርገዋል። ለውጤት ማጣትም የራሱን ሚና ሲጫወት ቆይቷል። በአገሪቷ ስፖርቱን በበላይነት የሚመራው የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን፤ የታዳጊ ማሰልጠኛ ፕሮጀክት፣ የስፖርት ማሰልጠኛ ማዕከላት፣ አካዳሚዎች፣ ክለቦች እንዲሁም ብሄራዊ ቡድን የሚል መስመር በመዘርጋት እየሰራ መሆኑ ይታወ ቃል። ነገር ግን ይህ አሰራር በቅብብሎሽ ከመከናወን ይልቅ ሁሉም በራሱ መንገድና አካሄድ ሲመራው ቆይቷል። ይህም ለብክነት ምክንያት ሲሆን፤ ማሰልጠኛ ማዕከላቱ ሚናቸው ተመሳሳይ በመሆኑ የሰልጣኞች ሽሚያ እና የእርስ በርስ ቅሬታ ውስጥ እንዲገቡ ሲያደርጋቸው ቆይቷል። ይህንን የተመለከተው ኮሚሽኑ አገር አቀፍ ስፖርት ስልጠና ጣቢያዎች፣ ማዕከላትና አካዳ ሚዎች አደረጃጀትና ስርዓት መተግበሪያ ረቂቅ ሰነድ በማዘጋጀት፤ ግብዓት የሚሆኑ ሃሳቦችን በመሰብሰብ ላይ ይገኛል። ረቂቁ አምስት ክፍ ሎች ያሉት ሲሆን፤ የመጀመሪያው ክፍል በማዕከ ላትና ፕሮጀክቶች መዋቅራዊ አደረጃጀት ላይ ትኩረቱን ያደርጋል። ቀጣዩ ክፍል ምዘና እና ውድድርን የሚመለከት ሲሆን፤ ሦስተኛው የሰል ጣኞችን የቅብብሎሽና ዝውውር፣ አራተኛው የባለቤትና ባለድርሻ አካላትን ተግባርና ኃላፊነት እንዲሁም በመጨረሻው ክፍል የክትትል፣ ድጋፍና ግምገማ ስርዓትን የሚያጠቃልል ነው። የሰነዱ አስፈ ላጊነትም፤ በየደረጃው በሚገኙ ፕሮጀክቶች፣ ማሰል ጠኛ ማዕከላት፣ አካዳሚዎችና ክለቦች መካከል ወጥ እና ቅንጅታዊ አሰራርን መዘርጋት ነው። በዚህም መሰረት ለሁሉም የየራሳቸው የሆነ የአሰራር ስርዓት ተበጅቶላቸዋል። በየአካባቢውና ትምህርት ቤቶች ከ13ዓመት በታች (11እና12) በሆነ ዕድሜ ስልጠናው የሚጀመር ሲሆን፤ በዚህም በርካታ ፍላጎት ያላቸው ታዳጊዎችን በተመሳሳይ ዕድሜ ማግኘት ይቻላል። ሁለት ዓመታትን በሚሸፍነው በዚህ ስልጠናም በዋናነት ሥራው የተሰጥኦ ፍለጋ ይሆናል። በቀጣይም ታዳጊዎቹ በ15 ዓመት በታች (13እና14) የስልጠና ጣቢያዎችን በመቀላቀል ለሁለት ዓመታት ይሰለጥናሉ። በዚህ የተሰጥኦ ልየታ ወቅትም ከአሰልጣኞቻቸው እገዛ ባሻገር በምዘና ያላቸውን ተሰጥኦ ለመለየት ይቻላል። በ17\nዓመት በታች (15እና16) ወደ ስልጠና ማዕከላት በመግባት የተለየውን ተሰጥኦአቸውን ማልማት የሦስት ዓመታት ሥራ ይሆናል። በዚህ ወቅት የስልጠና ጫናን የመሸከም ብቃታቸው የሚ መዘን ሲሆን፣ በማዕከላት መካከል የሚደረገውን ውድድር ጨምሮ በአገር አቀፍ ሻምፒዮናዎች እንዲሁም በዕድሜ በሚካሄዱ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይም ተሳታፊ ይሆናሉ። ይህንን ሲያጠናቅቁ ወደ አካዳሚዎች የሚገቡ ሲሆን፤ ከ3- 4ዓመታት በሚዘልቀው ቆይታቸው ለኦሊምፒክ ብቁ እንደሚሆኑ ስለሚታመን ክለቦችን እንዲሁም ብሄራዊ ቡድኖችን ይቀላቀላሉ። የዚህ\nሂደት ባለቤቶችም የተለዩ ሲሆን፤ ከ13-17ዓመት በሚዘልቀው የስልጠና ወረዳ እና ዞኖች ኃላፊነት አለባቸው። የስፖርት ማሰልጠኛ ማዕከላትን በባለቤትነት ክልሎች ሲያስተዳድሩ፤ አካዳሚዎች ደግሞ በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ስር ይገኛሉ። የትምህርት ሚኒስትር፣ የጤና ሚኒስትር፣ ኦሊምፒክ ኮሚቴ፣ ወላጅ፣ አሰልጣኝ፣ ክለብ፣… ደግሞ ባለድርሻ አካላት እንደመሆናቸው ሥራውን በቅንጅት ያከናውናሉ። በዚህ ሂደትም ለዓመት ለሦስት ጊዜያት የመስክ ምልከታ፣ የብቃት ምዘና፣ ዓውደ ጥናት፣ ወቅታዊ ሪፖርት እና የዳሰሳ ጥናቶች እንደሚካሄድም ሰነዱ ይጠቁማል። ሰነዱ ገለጻ ከተደረገበት በኋላም ከተሳታፊዎች በርካታ አስተያየት ተሰጥቷል። የስልጠና ቁሳቁስ፣ የምግብ አቅርቦትና የላብ መተኪያ ላይ ቢታሰብበት፣ ሰልጣኞች ከክለቦች ብቻም ሳይሆን ከማናጀሮች ጋር በምን መልኩ ይሰራሉ፣ ወደ ውጭ አገራት ክለቦች የሚኖራቸው ዝውውር እንዴት ይሆናል፣ ስልጠናው ሳይጠናቀቅ ወደ ክለቦች የሚያደርጉት ዝውውር፣ በምልመላ ላይ መስፈርት ቢቀመጥ፣ እንደየ ስፖርት ዓይነቱ የምልመላ ዕድሜው ቢቀነስ፣ የስልጠናውን ጊዜ በዕድሜ ከመገደብ ይልቅ በሰዓት ማድረግ ቢቻል፣ ማስተግበሪያውን ወደ ሥራ ለማስገባት መመሪያ ማዘጋጀት አስፈላጊ መሆኑ፣ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የስፖርት ማሰልጠኛ ሥፍራዎች አጠቃቀምን በተመለከተ፣ ማዕከላት ትኩረታቸውን በአትሌቲክስ ላይ ያደረጉ እንደመሆኑ የሌሎች እጣፋንታ ምን ይሆናል፣ እንደየ ደረጃው የአሰልጣኞች ደረጃ ቢወሰን፣… የሚሉ ሃሳቦች ተንጸባርቀዋል። በኢፌዴሪ\nስፖርት ኮሚሽን የትምህርትና ስልጠና ዳይሬክተር ሲሳይ ሳሙኤል፤ ለሰነዱ ግብዓት የሚሆኑ አስተያየቶችን ማሰባሰቡ ቀጣይነት ያለው መሆኑን ይጠቁማሉ። ክልሎች፣ ፌዴሬሽኖች እን ዲሁም የሚመለከታቸው አካላት በአጠቃላይ አስተያየታቸውን በመስጠት ረቂቁ ዳብሮ ወደ ተግባር ይገባል። ይህ ሰነድ በትክክል ወደ ሥራ የሚለወጥ ከሆነም በስልጠናውና በአገሪቷ ውጤት ላይ ትልቅ ድርሻ እንደሚኖረውም እምነታቸው ነው። ሰነዱ ሲዘጋጅ በአገሪቷ ያሉትን የማሰልጠኛ ማዕከላትና አካዳሚዎች ልምድ እንዲሁም ጠን ካራና ደካማ ጎኖች በመያዝ ነው። ከዚህም ባሻገር በዘርፉ የተሻለ ተሞክሮ ካላቸው አገራት እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ማዕከል እና አካዳሚ ለመባል መስፈርቶች በመነሻነት ተይዘዋል። አሰራሩ በወጥ አደረጃጀት፣ ደረጃ እና በተመሳሳይ አቅርቦት የሚካሄድ እንደመሆኑም በአንድ ቀን አዳር ይሳካል ለማለት እንደማያስደርም ዳይሬክተሩ ይጠቁማሉ። ነገር ግን ማዕከላቱ በምን መልኩ መስራት እንደ ሚገባቸው ራሳቸውን ይመለከቱበታል፤ እንዲሁም ከዚህ በኋላ የሚከፈቱ የማሰልጠኛ ማዕከላት እንደ መስፈርት በመሆን የሚያግዛቸው መሆኑን አስረድተዋል። የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚ ሽነር ጌታቸው ባልቻ፤ ሰነዱ በዘርፉ በምን መልኩ ውጤታማ መሆን ይቻላል የሚለውን ለማመላከት የተዘጋጀ መሆኑን ይገልጻሉ። ከሰነዱ\nየሚጠበቀውም፤ ማዕከላት ተሳስረው ውጤታማ ሥራ በማከናወን በዓለም አቀፍ ደረጃ ውጤት ማግኘት ነው። በስፖርት ላይ በሚሰሩ አካላት 50ሺ እና ከዚያ በላይ የሆኑ ስፖርተኞች ሰልጥነዋል ይባላል፤ የሚታየው ግን ለአብነት ያህል በእግር ኳስ ስፖርት11 ተጫዋቾችን ማፍራት አለመቻሉን ነው። በርካታ የማሰልጠኛ ጣቢያዎችና ማዕከላት ኖሮን ሰልጥነው የሚወጡት ውጤት ማስመዝገብ ካልቻሉ አሰራሩንና አደረጃጀቱን ቆም ብሎ መመልከት አስፈላጊ ይሆናል። ይህ ሰነድ ዳብሮ ወደ ተግባራዊነት እንዲገባም ህግና መመሪያ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች እንደሚኖሩም ምክትል ኮሚሽነሩ ይጠቁማሉ።አዲስ\nዘመን መጋቢት 16/2011ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "47b43da4d0a7ec84c955c2256ff82e36" }, { "passage": "በአትሌቲክስ ስፖርት ዝና እና ክብሯን የገነባችው ኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞችንም አግኝታበታለች። ስፖርቱ አንድ የስራ ዘርፍ በመሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣት አትሌቶችን ያቅፋል። አትሌቶችም በዓለም አቀፍ ውድድሮች ሲሳተፉ ከውጤት ባሻገር የውጭ ምንዛሪን በማስገኘት የሀገሪቷን ኢኮኖሚ ያግዛሉ። በሚያፈሱት መዋዕለ ነዋይም ለበርካቶች የስራ እድል ፈጥረዋል። \nእንደሚታወቀው በዚህ ወቅት ይህ ዘርፍ እንደሌሎች ስፖርቶች ሁሉ ለውድድር ዝግ ሆኗል። ማልዶ ለልምምድ ይወጣ የነበረውና በዓመት ውስጥ ተደጋጋሚ ውድድሮች ላይ ተሳታፊ የነበረው እረፍት የለሽ አትሌትም ከተላላፊው ቫይረስ ጋር ተያይዞ ከቤት ውሏል። በብሄራዊ ቡድን የተያዙ፣ በተለያዩ ክለቦች የተካተቱ እንዲሁም የአትሌቲክስ ማሰልጠኛ ተቋማት ሰልጣኝ የሆኑ አትሌቶችም እንዲበተኑ ተደርጓል። በግላቸው የሚሰለጥኑትም ቢሆን እንደ ቀድሞው ከመኖሪያቸው ርቀው የማይጓዙበት ሁኔታ ተጋርጦባቸዋል። \nለአንድ ዓመት የተራዘመውን ኦሊምፒክ ጨምሮ በሌሎች ዓለም አቀፍ ቻምፒዮናዎች ላይ ተሳታፊ ለመሆን በብሄራዊ ቡድን የተካተቱ አትሌቶች ደግሞ ከሌሎች በተለየ ሁለት አማራጮችን ያስተናግዳሉ። \nየመጀመሪያው ለተላላፊው የኮሮና ቫይረስ ተጋላጭ ላለመሆን በሚደረገው የቤት ውስጥ ቆይታ ከልምምድ በመራቃቸው የአቋም መውረድን ማስተናገድ ነው። ሌላኛው ደግሞ የውድድሮችን መራዘም እንደ መልካም እድል በመጠቀም በተደጋጋሚ ውድድር ላይ ያሳለፉ አትሌቶች እንደ ማገገሚያ ጊዜ በመመልከት በተሻለ ብቃት ለመመለስ የራሳቸውን ጥረት ማድረግ ነው። \nበእነዚህ ሁኔታዎች ውስጥ ስፖርተኞች ከስፖርቱ ላለመራቅ ምን ማድረግ አለባቸው፣ ፌዴሬሽኑስ ሚናውን በምን መልኩ እየተወጣ ነው ለሚለው በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የአትሌቲክስ ህክምና ከፍተኛ ባለሙያና እና የጸረ አበረታች ቅመሞች ተጠሪዋ ቅድስት ታደሰ ከአዲስ ዘመን ጋር ቆይታ አድርገዋል። \nየመጀመሪያው ነገር ስነ-ልቦና መሆኑን ባለሙያዋ ይገልጻሉ።በዓለምና በሃገር በመጣው በዚህ ቫይረስ ምክንያት በቤታቸው እስኪቆዩ ድረስ ኦሊምፒክን ጨምሮ ለዚህ የውድድር ወቅት በዝግጅት ላይ የነበሩ አትሌቶች በጥሩ አቋም ላይ ነበሩ። በዚህም ምክንያት አቋማቸው እንዳይወርድና ጂምናዚየሞችም በመዘጋታቸው በቤት ውስጥ የተለያዩ የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችን ለማድረግ ይገደዳሉ። ከትንፋሽ ጋር በተያያዘ ያለውን ደግሞ የሰዎች ንክኪ በሌለበት በግላቸው ጫካ አካባቢ መስራት ይችላሉ። ይህም ወቅታዊ ብቃታቸው እንዳይወርድ እንጂ ለውድድር በሚደረግ ልክ አይሆንም። \nይህ እንዲሆን ደግሞ አስቀድሞ እንደተገለጸው ዋናው ነገር በመልካም ስነ-ልቦና ላይ መገኘት መሆኑን ይጠቁማሉ። በማብራሪያቸውም ‹‹የሰው ልጅ በተፈጥሮው በጭንቀት ወቅት ሰውነቱ በሚሰጠው ግብረመልስ የተለያዩ ቅመሞችን ስለሚያመነጭ ለውጥረትና ለመደበት ስሜት ይጋለጣል። አትሌትሌቲክስ የሙሉ ጊዜ ስራው የሆነው አትሌትም ውድድሮች ከሌሉ በእንዲህ ዓይነቱ ሁኔታ ውስጥ ሊገባ ይችላል። ይህ እንዳይከሰትም አትሌቶች ራሳቸውን በስነ-ልቦና ማዘጋጀት ይገባቸዋል›› ሲሉ ያስረዳሉ ባለሙያዋ። ሁኔታዎችን አእምሮ ሲቀበል ሌሎች አካላትን ማዘዝ ስለሚቻል ስነ-ልቦና የመጀመሪያውና ዋነኛው ጉዳይ ነው።\nከዚህ ባሻገር በአትሌቲክስ ስፖርት የሚፈራው ነገር ክብደት መጨመር ነው። በክብደት ተወስነው እንደሚካሄዱት የቦክስና የማርሻል አርት ስፖርቶች ሁሉ የረጅም ርቀት በአትሌቲክስም ክብደት መጨመር የራሱ አደጋ ይኖረዋል። በመሆኑም የቡድን እና ጫና ያላቸውን ልምምዶችን በማስቀረት ሰውነትን ባለበት እንዲቆይና የብቃት መዋዠቅ እንዳይከተል የሚያደርግ መሆን እንዳለበት ባለሙያዋ ያስገነዝባሉ። \nአመጋገብ ላይም አትሌቶች የራሳቸውን ጥንቃቄ ማድረግ ይገባቸዋል፤ አመጋገብ ከሚወጣው ኃይል ጋር ተመጣጣኝ መሆን ይኖርበታል። በዚህ ወቅት ቀለል ያሉ ልምምዶችን እየሰሩ እንደ ወትሯቸው የሚመገቡ ከሆነ ግን ሰውነት ያንን ለማስተናገድ ስለሚከብደው የክብደት መጨመር ይከሰታል። በመሆኑም ይህንን መከታተልና ከቻሉ በየዕለቱ ያሉበትን ሁኔታ በመመዝገብ ማስታወሻ እንዲይዙ ይመከራል። የዓለም አትሌቲክስም በየወቅቱ የሚያወጣውን መረጃ መከታተልም አስፈላጊ ነው። \nበዚህ ሂደት ሊዘነጋ የማይገባው ዋናው ነገር በቤት ውስጥ የሚሰሩ ማሳሳቢያዎችና ሌሎች የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎች ንጹህ አየር ባለበት ስፍራ መሆኑን ማረጋገጥ ነው። \nሰው የማይበዛበትና ነፋሻማ አየር ባለበት ስፍራ ቢንቀሳቀሱ ደግሞ የተሻለ ይሆናል። እንደ ዓለም አትሌቲክስ መረጃ ከሆነ አትሌቶች በተለይም የረጅም ርቀት ሯጮች ትንፋሻቸው የዳበረ በመሆኑ ከሌላው በተለየ ተጋላጭነታቸው የሰፋ ይሆናል። \nበመሆኑም ራሳቸውን ለየት ባለመልኩ መጠበቅ ይኖርባቸዋል። ፈሳሽ በብዛት መውሰድና በሽታን ሊቋቋሙ የሚችሉ ምግቦችንም ከዚህ ቀደሙ በተሻለ ሁኔታ ማዘውተርና በዓለም የጤና ድርጅት እንዲሁም ጤና ጥበቃ ሚኒስቴርን ከመሳሰሉ ተቋማት የሚወጡ መረጃዎችን መከታተል ለአትሌቱ ጠቃሚም ነው። ምክንያቱም አብዛኛው የማህበራዊ ትስስር ገጾችን የሚጠቀም እንደመሆኑ መረጃዎችን የሚያገኙበት መንገድ በራሱ ጎጂ ሊሆን ይችላል። \nይህንንና መሰል ግንዛቤዎችን ከማስጨበጥ አንጻር ባለሙያዎች አትሌቱን በአካል ለማግኘት አዳጋች በመሆኑ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የተለያዩ ስራዎችን እንደጀመረም ባለሙያዋ ይጠቁማሉ። የፌዴሬሽኑ አመራሮች ባደረጉት ውይይት አትሌቱ ከአዲስ አበባ ውጪ ባሉ ክልሎችም የሚገኝ እንደመሆኑ ሁሉንም ተደራሽ ለማድረግ በቴሌቪዥንና በሬዲዮኖች መልዕክቶችን ማስተላለፍ የተሻለ አማራጭ ሆኖ አግኝቶታል። በመሆኑም ሰፊ ሽፋን ካላቸውና ከክልል የመገናኛ ብዙሃን ጋር በመተባበር፤ አትሌቱ ልምምዱን እንዴትና በምን ሁኔታ መስራት እንዳለበት በባለሙያዎች ግንዛቤ የሚሰጥ ይሆናል። \nከዚህ ባሻገር ከወቅታዊው ሁኔታና ከቫይረሱ ጋር የተያያዙ መረጃዎችን፣ ስነ- ምግብ፣ ስፖርታዊ ስነ-ልቦና፣ የስፖርት ህክምና፣ የመረጃ ክትትል ምን መምሰል አለበት የሚሉና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ነባራዊ ሁኔታውን ባገናዘበ መልኩ ለአትሌቱ እንዲደርስ ይደረጋል። በዚህ ሁሉ ሁኔታ ውስጥ ግን መዘንጋት የሌለበት ዋነኛ ጉዳይ አበረታች ቅመም መሆኑን ያሳስባሉ። \nይህንን ግንዛቤ የሚሰጡትም በስፖርቱ ላይ ለረጅም ጊዜ ያሳለፉ ባለሙያዎች እና ኦሊምፒክን ጨምሮ በተለያዩ መድረኮች ላይ ስኬታማ የሆኑ አንጋፋና ተምሳሌት አትሌቶች ሲሆኑ፤ መልእክቶችን፣ ምክሮችንና በተግባር የታገዙ እንቅስቃሴዎችንም ለአትሌቶች የሚያስተላልፉ ይሆናል። ከፌዴሬሽኑ የህዝብ ግንኙነት እንዲሁም ከስልጠና ጥናትና ምርምር ክፍል ጋር በመሆንም በተለያዩ የማህበራዊ ገጾች መልእክቶችን ለማስተላለፍም በእንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኙ ባለሙያዋ ጨምረው ገልጸዋል።\nአዲስ ዘመን ሚያዝያ 5/ 2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "1dee20ef7f798a5f4f9393c780beb163" } ]
566eb44a3ff177a71729515f017b86c0
4f5d1647ca86aca61fd41ca40bcd7120
በሲሚንቶ አቅርቦት ሰንሰለቱ ላይ አሁንም ችግሮች እንደሚታዩ ሚኒስቴሩ አስታወቀ
አስናቀ ፀጋዬ አዲስ አበባ፡- በሲሚንቶ አቅርቦት ሰንሰለቱ ላይ አሁንም ችግሮች እንደሚታዩ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ። በሀገሪቱ የሚታየውን የሲሚንቶ እጥረት በዘላቂነት ለመቅረፍ የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝም አመለከተ። በንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የብረታ ብረትና ኬሚካል ሚኒስትር ዴኤታ አማካሪ አቶ ዱጋሳ ዶንሳ ለአዲስ ዘመን እንደገለፁት ፣ሚኒስቴሩ ከስድስት ወር በፊት በምርትና በአቅርቦት በኩል የተፈጠረውን የሲሚንቶ እጥረት መንስኤ ለማጥናት በሀገር አቀፍ ደረጃ ኮሚቴ አቋቁሞ ሲሰራ ቆይቷል። በዚህም በሀገሪቱ ያሉ ፋብሪካዎች ለረጅም ጊዜ የሚቆሙ፣ ገሚሶቹም ያረጁና መለዋወጫ የሚፈልጉ፣ የገበያ ፍላጎታቸውም በሶስት ኢንዱስትሪዎች ላይ መሰረት ያደረጉ መሆናቸውንና አብዛኛዎቹ ግንባታዎችም በተመሳሳይ ወቅት መከናወናቸው ችግሩ እንዲጎላ ማድረጉን ለማረጋገጥ መቻሉን ገልጸዋል። የሲሚንቶ ምርት ፍላጎትና አቅርቦት ልዩነት እንደነበር መረጋገጡን አመልክተዋል። የሲሚንቶ ምርት አቅርቦትና ፍላጎት በኩል ያለውን ልዩነት ለማጥበብ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተወሰነ ሲሚንቶ ከውጭ ሀገር እንዲገባ መፍቀዱን ጠቁመው ፣ ከዚህ በፊት ተይዞ የነበረው የሲሚንቶ ኢንቨስትመንትም እንዲለቀቅ መደረጉንም አስታውቀዋል። በአማራ ብሄራዊ ክልል ደጀን አካባቢ የሚገኘው አባይ የሲሚንቶ ፋብሪካ ግንባታ እንዲፋጠንም የ20 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ተፈቅዶለት ግንባታው እየተከናወነ እንደሚገኝም ገልፀዋል። ቀደም ሲል የነበረውን የሲሚንቶ የማምረት አቅም ለመጨመርም የመለዋወጫ እቃዎች ከውጭ ሀገር እንዲገቡ 85 ሚሊዮን ብር መመደቡንም ጠቁመዋል። የክረምቱን ወቅት ተከትሎ በሲሚንቶ ፋብሪካዎች ላይ ያጋጠሙ የተፈጥሮ አደጋዎችና በዘርፉ የሰለጠኑ ባለሙያዎች እጥረቶች እንዳሉ ሆነው እነዚህን ስራዎች በመስራት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከሲሚንቶ አምራቾች ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሞ በበጀት ዓመቱ የሀገሪቱን አጠቃላይ ሲሚንቶ የማምረት አቅም ለማሳደግ ከያዘው 85 በመቶ እቅድ ውስጥ 79 ያህሉን ማሳካት እንደቻለም ገልጸዋል። በነሃሴ ወር መጨረሻ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሲሚንቶ የመሸጫ መቁረጫ ዋጋ መመሪያ አውጥቶ እንደነበርም አማካሪው አስታውሰው፤ ዋጋው እንደገበያው መሆን እንዳለበት ታምኖ መመሪያው እንዲነሳ መደረጉንም ጠቁመዋል። የዋጋ መመሪያው ከተነሳ በኋላም የሲሚንቶ ዋጋው እንዳልወረደ ነገር ግን መመሪያው እንዳያሻቅብ ማድረጉን የተደረጉ ጥናቶች እንደሚያሳዩ አመልክተዋል። አምና የተመረተውን 8 ነጥብ 5 ሜትሪክ ቶን ሲሚንቶ ወደ 11 ሜትሪክ ቶን በማሳደግ በአቅርቦቱና በፍላጎቱ መካከል ያለውን ክፍተት ለመማጥብ እየተሰራ እንደሚገኝም አማካሪው አስታውቀው፣ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ባስቀመጠው እቅድ መሰረት ባደረገው ጥረት ከዚህ ቀደም በሃይል መቆራረጥ ምክንያት ሲቆም የነበረውን የሲሚንቶ የማምርት አቅም ችግር ሙሉ በሙሉ መፍታቱን አመልክተዋል። ፋብሪካዎች ከውጭ የሚያስገቧቸውን የድንጋይ ከሰል የመሰሉ የኢነርጂ ምንጮችን በሀገር ውስጥ እንዲጠቀሙ ከመአድን ነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስቴር ጋር በመሆን ጥረት መደረጉንም አማካሪው ጠቁመዋል። በዚህም የመሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካን ሳይጨምር በቀን በአማካይ 240 ሺ ኩንታል ማምረት እንደተቻለም ጠቁመዋል። ሆኖም ምርቱ ከወጣ በኋላ የአቅርቦት ሰንሰለቱ ላይ አሁንም ችግሮች እንደሚታዩ አስታውቀዋል
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=39629
[ { "passage": "አዲስ አበባ፡- በኢትዮጵያ ውስጥ ከነዳጅ አቅርቦቱና ፍላጎቱ ጋር ተመጣጣኝ የሆነ ተርሚናልና የነዳጅ ማደያዎች አለመኖራቸው በነዳጅ ስርጭቱ ላይ ችግር እየፈጠረ መሆኑን የኢትዮጵያ ነዳጅ ኩባንያዎች ማህበር አስታወቀ።\nየማህበሩ ፕሬዚዳንትና የኖክ ኩባንያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ታደሰ ጥላሁን በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ የማደያዎች ተደራሽነት ከአገሪቷ ፍላጎት ጋር ሲነጻጸር በቂ ባለመሆኑ እንዲሁም በጅቡቲ የሚገኙት የነዳጅ ማከማቻ ታንከሮች ነዳጅ የመያዝ አቅማቸው ውስን በመሆኑ እያደገ የመጣውን የነዳጅ ፍላጎት ማሟላት አልተቻለም። ይህን ተከትሎ በነዳጅ ጭነት በሚያጋጥም መስተጓጎልና በማደያዎች ቁጥር ውስንነት ምክንያት በማደያዎች ረጃጅም ሰልፍ ይታያል። \nየነዳጅ ኩባንያዎች በአገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች ማደያዎችን በብዛት ሠርተው ነዳጅ ለህብረተሰቡ እንዳያቀርቡ ተነሳሽነት በሚፈጥር መልኩ ዘርፉ እየተመራ አይደለም ያሉት አቶ ታደሰ፤ ለነዳጅ ኩባንያዎች፣ ለትራንስፖርት አቅራቢዎች፤ ለማደያዎች በቂ የሆነ የትርፍ ህዳግ አልመወሰኑ የነዳጅ ኩባንያዎች ማደያዎችን በብዛት ገንብተው ለህብረተሰቡ ነዳጅ በሚፈለገው መልኩ ማቅረብ እንዳይችሉና በየማደያዎቹ ነዳጅ ቢኖርም እንኳን ረጃጅም ሰልፎች እንዲፈጠሩ ማድረጉን ገልጸዋል። \nበአሁኑ ጊዜ በአዲስ አበባም ሆነ በአገሪቱ በተለያዩ\n አካባቢዎች ማደያዎች እየተሠሩ ቢሆንም በቂ አለመሆናቸውን የጠቀሱት አቶ ታደሰ፤ ለአብነትም በህዝብ ብዛትም ሆነ በቆዳ ስፋት ከኢትዮጵያ የምታነሰው ኬንያ ከሁለት ሺህ 500 በላይ ማደያዎች እንዳላትና በአንጻሩ ብዙ ህዝብና ሰፊ የቆዳ ስፋት ያላት ኢትዮጵያ አንድ ሺህ የማይሞሉ ማደያዎች ብቻ እንዳሏት ተናግረዋል። ይህም ዘርፉ ገና ሰፊ ኢንቨስትመንት የሚጠይቅ መሆኑን ያመላክታል ብለዋል።\nማህበሩ የትርፍ ህዳጉ እንዲስተካከል ለመንግሥት ጥያቄ መቅርቡን አውስተው፤ በመንግሥት በኩል የትርፍ ህዳጉ ከተሻሻለና የመሬት አቅርቦቱ ከተመቻቸ አገሪቱ ከምትፈልገው የነዳጅ አቅርቦት ጋር የሚመጣጠኑ ብዛት ያላቸው የነዳጅ ማደያዎች ስርጭት ይኖራል የሚል እምነት እንዳላቸው አመልክተዋል።\nሌላው እየጨመረ የመጣውን የኢትዮጵያ ነዳጅ ፍላጎት ለማሟላት መሰረታዊ ከሆኑ የመሰረተ ልማት ችግሮች አንዱ በጅቡቲ ወደብ በቂ የነዳጅ ማከማቻ ታንከሮች አለመኖራቸውና የጭነት ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ የሚያስችል ተርሚናል አለመኖሩ መሆኑን ተናግረዋል።\nከ15 ዓመት በፊት የተሠሩ የነዳጅ ማከማቻ ታንከሮች አሁን ያለውን የነዳጅ ፍላጎት ሊያሟሉ ባለመቻላቸው ተጨማሪ ታንከሮችን መገንባትና ነዳጅን ከወደብ ለማጓጓዝ የተለያዩ አማራጭ የትንስፖርትና ወደቦችን መጠቀም እንደሚገባም ጠቁመዋል።\nእስከአሁን የነዳጅ ኢንዱስትሪውን የሚመራ ፣የሚያስተዳድርና የሚቆጣጠር አንድ ወጥ ተቋም\n እንዳልነበረ የገለጹት አቶ ታደሰ፤ችግሩን ለመፍታት ብዙ ጥናቶች ቀርበው መንግሥት የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢዎችና አስመጪዎችን የሚቆጣጠር፣የሚመራና ችግሮችን የሚፈታ ተቋም እንዲቋቋም የወሰነ መሆኑንና ይህ ተቋም ሥራውን ተርክቦ፤ ራሱን አደራጅቶ ለመምራት ጊዜ የሚወስድ ቢሆንም በመንግሥት የተሰጠው ምላሽ ዘርፉን የሚያበረታታ መሆኑን ተናግረዋል።\nበኢትዮጵያ እየተፋጠነ የመጣውን ልማትና የህብረተሰቡን ኑሮ ለማሻሻል የተለያዩ አማራጭ የኃይል ምንጮች እንደሚያስፈልጉ አውስተው፤ ከውሃ፣ከንፋስ፣ከፀሐይ፣ ከእንፋሎትና ከተፈጥሮ ጋዝ የሚገኙ የኃይል አማራጮችን በስብጥር ማልማት መጠቀምና ለነዳጅ የሚወጣውን ከፍተኛ ወጪ መቀነስ እንደሚገባ አመልክተዋል። \nበሌላ በኩል በዓለም ላይ የኮሮና ቫይረስ መቀስቀስን ተከትሎ የዓለም ኢኮኖሚ እየተዳከመ መምጣቱን ተከትሎ የነዳጅ ዋጋ መቀነሱን ገልጸው፤ ይህን አጋጣሚ ለመጠቀም ኢትዮጵያም ስትራቴጂክ ዲፖዎችን እየሞላችና የነዳጅ ኩባንያዎቹም ዲፖዎቻቸውንና ማደያዎቻቻውን እየሞሉ እንደሚገኙ ነግረውናል። ለምሳሌም ኖክ አዲስ አበባ አየር ማረፊያ ግቢ ውስጥ የሚገኘውን 600 ሚሊዮን ሊትር የሚይዘውን ታንከርና አራት ሚሊዮን ሊትር የሚይዘውን የዱከም ታንከር እየሞላ መሆኑን ጠቅሰዋል። በዚህም አገሪቱ ከ500 ሚሊዮን ዶላር በላይ ማዳን እንደምትችል ገልጸዋል።\nኢትዮጵያ የዓመት የነዳጅ ፍጆታዋ አራት ቢሊዮን ሊትር ሲሆን፤ ለዚህ ነዳጅ አቅርቦትም ሦስት ቢሊዮን\n ዶላር ወጪ ይደረጋል። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙት 30 የነዳጅ ኩባንያዎች አራት ቢሊዮን ሊትሩን እንደየገበያ ድርሻቸው ወስደው እንደሚያሰራጩም ታውቋል።\nአዲስ ዘመን ሰኔ 12/2012ጌትነት ምህረቴ", "passage_id": "04617acaf73e596d3a6bd80b0bcf9324" }, { "passage": " – ሲሚንቶን በዘመናዊ የአመራረት ዘዴ ተጠቅሞ በማምረት ዋጋው አሁን ካለበት የሚቀንስበት አሰራርን ለመቀየስ እየተሰራ ነው። በኢትዮጵያ የተለያዩ የግንባታ ፕሮጀክቶች ተቀርፀው እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል።ይሁን እንጅ ከህብረተሰቡ የግንባታ ፍላጎት አንፃር የሲሚንቶ ዋጋው ተመጣጣኝ አለመሆኑ ይነገራል። ለዚህ ደግሞ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የአመራረት ዘዴ ዋነኛ ምክንያት መሆኑን ነው የኬሚካልና የኮንስትራክሽን ግብአት አቅርቦት ልማት ኢንስቲቲዩት የሚናገረው።የኢንስቲቲዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳሙኤል ሃላላ እንደሚሉት፤  ፋብሪካዎች ሲሚንቶን ለማቃጠል የሚጠቀሙበት የማዙት ሃይል ዋጋው እንዲንር ያደርገዋል።ከማዙት የተሻለና ወጪ ቆጣቢ የሆነው የሃይል ምንጭ የድንጋይ ከሰል መሆኑንም ነው የሚናገሩት።  የመሶቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ ማዙትና የድንጋይ ከሰል ቴክኖሎጂን ለመሻገር የባዮ ጋዝ ቴክኖሎጂን ለመጠቀም ጥናት እያደረገ መሆኑን ዋና ስራ አስኪያጁ አቶ ጌታቸው እቁባይ ይናገራሉ።ከአንድ ወር በኋላ ስራ ላይ የሚውለው ቴክኖሎጂ አሁን ያለውን የሲሚንቶ ዋጋ እንዲወርድ እንደሚያደርገው ተናግረዋል። ኢንስቲቲዩቱም በሀገሪቱ ላሉ 18 ፋብሪካዎች ወደዚህ አይነት አሰራር እንዲገቡ የሚያስችል የሲሚንቶ ልማት ስትራቴጂ ለመቅረፅ እየተንቀሳቀሰ ነው።ስትራቴጂው ፋብሪዎች የአመራረት ቴክኖሎጅያቸውን እንዲያሻሽሉ ቁጥጥር በማድረግ ድጋፍ እንደሚሰጥ ነው ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ሳሙኤል የተናገሩት።ፋብሪካዎቹ አሁን ያላቸውን 11 ሚሊየን ቶን አመታዊ የማምረት አቅማቸውን አሳድገው ወደ ጅቡቲ፣ ኬንያና ሶማሊላንድ ብሎም የሌሎች አካባቢዎችን ገበያ ማሸነፍ እንዲችሉም ያደርጋቸዋል።በተያዘው አመትም ቢሆን ወደ እነዚህ ሀገራት ሲሚንቶን በመላክ 10 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ለማግኘት እየተሰራ መሆኑንም ሃላፊው መናገራቸውን ኤፍ ቢ ሲ ዘገባ ያስረዳል።", "passage_id": "276a57fda468bb591edd7c9e51b22706" }, { "passage": "በሥራ ተቋራጮችና በአማካሪ ድርጅቶች ላይ የሚስተዋለው የአቅም ክፍተት የኮንስትራክሽን ዘርፉ እንዳያድግ እያደረገ መሆኑን ባለሙያዎች ተናገሩ። የኮንስትራክሽን ሚኒስቴር በበኩሉ የዘርፉ ባለሙያዎቹ \"ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል የአቅም ግንባታ ሥራዎች እየሰራሁ ነው\" ብሏል።የኮንስትራክሽን  ባለሙያዎችና የማህበራት ወኪሎች የተቋራጮችና የአማካሪዎች አቅም ማነስ ከሌሎች የዘርፉ ችግሮች በበለጠ በኮንሰተራክሽን እድገት ላይ ጫና ማሳደሩን ይገልጻሉ።የአመሃ ሥሜ የህንጻ ሥራ ተቋራጭ ድርጅት ባለቤትና የኢትዮጵያ ሥራ ተቋራጮች ማኅበር ፀሀፊ አቶ አመሃ ሥሜ እንደተናገሩት፤ የግንባታ ባለሙያዎች አቅም ማነስ ይስተዋልባቸዋል። በመሆኑም ተቋራጮች ግንባታዎችን በታቀደላቸው ጊዜ ያለማጠናቀቅና በግንባታዎቹም ላይ ጥራት እያጓደሉ መሆኑን ነው የገለጹት።የኢትዮጵያ የውኃ ነክ ሥራዎች ግንባታ ተቋራጮች ማኅበር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታሁን ታገሰም ባለሙያዎች የአቅም ክፍተት ችግር እንዳለባቸው የሚነገረውን ሀሳብ ይጋራሉ።  በተለይም ግንባታ ከመጀመራቸው በፊት የሚካሄዱ አዋጭነትን የመሳሰሉ ጥናቶች ክፍተቶች አጠቃላይ የሥራ ሂደቱ ላይ ችግር እየፈጠሩ መሆኑንም ነው የተናገሩት።   ባለሙያዎቹ፤ የአቅም ክፍተት መኖሩ ግንባታዎች በእቅድ እንዳይመሩና በሙያው ሥነ – ምግባር እንዳይፈጸሙ ማድረጉንም ተናግረዋል።አግባብ ባልሆነ መልኩ እየተሠጠ ያለው የግንባታ ሥራ ፈቃድና የተቋራጮች ደረጃ ዘርፉን እየጎዳው መሆኑንም ጠቁመዋል።በሌላ በኩል በመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ግልጽ የሆነ የግዥ ሥርዓት አለመኖሩ ተቋራጮች እኩል ተወዳዳሪ እንዳይሆኑ ጫና ማሳደሩንም ይናገራሉ።በኮንስትራክሽን ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሲሳይ ደርቤ፤ በተለይም በሥራ ተቋራጮችና በአማካሪዎች ላይ የአቅም ክፍተት መኖሩን መሥሪያ ቤታቸው እንደደረሰበት ተናግረዋል። በመሆኑም የፕሮጀክቶች መዘግየት፣ የግንባታ ሥራዎች ጥራት መጓደልና ከአቅም ክፍተት ጋር በተያያዘ የሥነ-ምግባር ግድፈቶችም በዘርፉ እንደሚስተዋሉ ነው የገለጹት።አቶ ሲሳይ፤ ክፍተቱን ለመሙላት የሚቻልበት የሥልጠናና የልምድ ልውውጥ መድረኮችን በማዘጋጀት \"የባለሙያዎቹን አቅም ለማጎልበት እየሰራን ነው\" ብለዋል።ከውጭ አገሮች ባለሙያዎች ጋር በመሆንም ለአገር ውስጥ ሥራ ተቋራጮችና አማካሪዎች የቴክኖለጂ ሽግግር እንደሚሰሩም ተናግረዋል።በሌላ በኩል አሁንም በዘርፉ ያሉ ባለሙያዎች ከሙያው ሥነ-ምግባር ጋር በማይጣጣም መልኩ ድርጊቶችን እንዳይፈጽሙ ክትትል እንደሚደረግ ገልጸዋል።ዘርፉ በአሁኑ ወቅት በአገር አቀፍ ደረጃ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ እድል መፍጠሩን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያሳያል።( ኢዜአ) ", "passage_id": "1ff305bed1e0da78f7fe3bf432746868" }, { "passage": "አንጋፋው የሲሚንቶ አምራች የሆነውና በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ሥር የሚተዳደረው የሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ፣ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ችግር በምርታማነቱ ላይ ትልቅ ሳንካ እንደፈጠረበት አስታወቀ፡፡በተደጋጋሚ የሚገጥመው የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ሲሚንቶ በማምረት ላይ ተፅዕኖ መፍጠሩንና ማሽኖች ለብልሽት እንደሚዳረጉበት፣ ይህም ለምርት መቋረጥና ለከፍተኛ ወጪ እንደዳረገው ፋብሪካው አስታውቋል፡፡ የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የኮርፖሬት ጥናትና ልማት ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ተባባል ውድነህ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ለገጠር ኤሌክትሪክ አቅርቦት ተብሎ ከሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ ከተተከለ ትራንስፎርመር የተቀጠለ የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር በመኖሩ በገጠር ቀበሌዎች መስመር ላይ የቴክኒክ ችግር በተፈጠረ ቁጥር ችግሩ ወደ ፋብሪካውም መስመር ይመጣል፡፡‹‹የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ በፋብሪካው ምርታማነት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ አሳድሯል፤›› ያሉት አቶ ተባባል፣ ከፋብሪካው ትራንስፎርመር ላይ ለገጠር ቀበሌዎች ተብሎ የተዘረጋው መስመር የሚነጣጠልበት ሁኔታ እንዲመቻች፣ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ማመልከታቸውንና በኮሚቴም ደረጃ በተደጋጋሚ መነጋገራቸውን ገልጸዋል፡፡የአገሪቱ የኮንስትራክሽን ዘርፍ እመርታ ባሳየበት ወቅት የተፈጠረውን የሲሚንቶ እጥረት በመመልከት የሙገር ሲሚንቶ በ138 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ሰፊ የማስፋፊያ ፕሮጀክት በማካሄድ የማምረት አቅሙን 150 በመቶ በማድረስ በዓመት ወደ 2.2 ሚሊዮን ቶን ሲሚንቶ አሳድጓል፡፡ ይሁን እንጂ ባለበት የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ችግር ምክንያት በማስፋፊያ ፕሮጀክቱ የተተከለውን አዲስ ፋብሪካ ሙሉ በሙሉ መጠቀም እንዳልተቻለ የኩባንያው ኃላፊዎች ገልጸዋል፡፡የሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ ከአዲስ አበባ ሰሜን ምዕራብ 90 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ቢሆንም፣ ለገበያ ቅርበት ሲባል የፋብሪካው ሁለተኛ ክፍል የሆነው ወፍጮና ሲሚንቶ ማሸጊያ በታጠቅ አካባቢ ተገንብቷል፡፡ አቶ ተባባል እንዳሉት በታጠቅ ሁለት ትልልቅ እያንዳንዳቸው በሰዓት 105 ቶን የመፍጨት አቅም ያላቸው ማሽኖች የተተከሉ ቢሆንም፣ በኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ችግር ምክንያት በግማሽ አቅም ብቻ እየሠሩ ነው፡፡ ‹‹በታጠቅ እየሠራን ያለነው በ50 በመቶ አቅም ብቻ ነው፡፡ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ከኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር ተደጋጋሚ ጥረት እያደረግን ነው፤›› ብለዋል፡፡ታጠቅ ላይ የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረት ፋብሪካውን እንደጎዳው የሚናገሩት አቶ ተባባል፣ ሙገር ዋና ፋብሪካው ላይ የክሊንከር ምርት በሙሉ አቅም ማምረት እንዳልተቻለ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ይህ ሊሆን የቻለው በጥሬ ዕቃ አቅርቦት በኩል በኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ምክንያት ከኳሪ የጥሬ ዕቃዎች ዝግጅት በአግባቡ ማካሄድ ባለመቻሉ ነው፤›› ብለዋል፡፡አክለውም በኃይል መቆራረጥ ምክንያት ውድ የሆኑ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ክፍሎች እንደሚቃጠሉ፣ መሣሪያዎቹን ከውጭ በትዕዛዝ ለማስመጣት ረዥም ጊዜ እንደሚወስድ ገልጸዋል፡፡በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሰሜን አዲስ አበባ ዲስትሪክት ኃላፊ አቶ አንድነት ደጉ ለሪፖርተር በሰጡት ምላሽ፣ የሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ትራንስፎርመር ለብቻው የተተከለ በመሆኑ ከገጠር መስመር ጋር አይገናኝም ብለዋል፡፡ ‹‹ብሬከር የመለየት ሥራ በቅርቡ ሠርተናል፡፡ የገጠር መስመሩ ለብቻ ተለይቶ የሚያስወጣ ተሠርቷል፤›› ያሉት አቶ አንድነት፣ የሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካን አልፎ የሚሄድ 120 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር የእንጨት ምሰሶዎች በኮንክሪት ምሰሶ የመለወጥ ሥራ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ታጠቅ ፋብሪካ ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እጥረት በተመለከተ አቶ አንድነት የሰብስቴሽን አቅም ውስንነት መኖሩን አምነዋል፡፡ ‹‹የፋብሪካው ማስፋፊያ ከስምንት ዓመት በፊት ሲሰሠራ ከነበረው የሲሚንቶ እጥረት አኳያ፣ አዲሱ ፋብሪካ በአፋጣኝ ወደ ሥራ እንዲገባ ከመንግሥት በተሰጠ መመርያ አማካይነት ሰብስቴሽን ሳይገነባ ነው የኤሌክትሪክ መስመር በቀጥታ የተሰጠው፤›› ያሉት አቶ አንድነት፣ በአሁኑ ወቅት ገፈርሳ ያለው ሰብስቴሽን ከፍተኛ የአቅም ውስንነት እንዳለበት ገልጸው፣ ይህን ችግር ለመቅረፍ የሰብስቴሽን ማሻሻያ ሥራ እየተከናወነ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡‹‹ችግሩን ለመፍታት ሁላችንም እየተረባረብን ነው፡፡ የሰብስቴሽኑ ግንባታ ሥራ በመጠናቀቅ ላይ በመሆኑ መስመር የማገናኘት ሥራ በቅርቡ ይሠራል፡፡ ለፋብሪካው ብቻ ሳይሆን ለኅብረተሰቡም ስለምንፈልገው በጉጉት እየጠበቅን ነው፤›› ብለዋል፡፡በዓመት 2.2 ሚሊዮን ቶን ሲሚንቶ የማምረት አቅም ያለው ሙገር ሲሚንቶ የአቅሙን ከ55 እስከ 60 በመቶ ያህል እየተጠቀመ እንደሆነ ታውቋል፡፡ በቀድሞ ወታደራዊ መንግሥት በ1976 ዓ.ም. የተቋቋሙ ሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ በምሥራቅ ጀርመን ባለሙያዎች የተተከለ የጀርመን ቴክኖሎጂ ነው፡፡ በ1990 ዓ.ም. የሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካንና የአዲስ አበባ ሲሚንቶ ፋብሪካን በማዋሀድ እንደ አዲስ በ334.7 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል እንዲቋቋም ተደርጓል፡፡ የሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ ሦስት የምርት መስመሮች ሲኖሩት የመጀመሪያው እ.ኤ.አ. በ1984፣ ሁለተኛው በ1990 እና በ2011 ሥራ ጀምረዋል፡፡በአሁኑ ወቅት ሙገር ሲሚንቶ የሚተዳደረው በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ሥር ነው፡፡ ኮርፖሬሽኑ የአገሪቱን የኬሚካል አምራች ንዑስ ዘርፍ ልማት እንዲያስተባብርና እንዲመራ በሚኒስትሮች ምክር ቤት እ.ኤ.እ. በ2012 በ21.7 ቢሊዮን ብር ካፒታል የተቋቋመ ሲሆን፣ ከሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ በተጨማሪ በማጂ ዞን የሚገኘውን የተፈጥሮ ጎማ ዛፍ ልማት ምርትና የዩሪያ ልማት ፕሮጀክቶችን ያስተዳድራል፡፡ሙገር ሲሚንቶ ባለፉት ዓመታት ትርፋማ ሊሆን አልቻለም፡፡ ለዚህም አንደ ዋነኛ ምክንያት የሚጠቀሰው ፋብሪካው ሲጠቀም የነበረው የፈርነስ ነዳጅ ለከፍተኛ ወጪ ስለዳረገው እንደሆነ አቶ ተባባል አስረድተዋል፡፡ ባለፈው ዓመት የፈርነስ ነዳጅ መጠቀሙን አቁሞ ወደ ድንጋይ ከሰል በመዞሩ፣ በአሁኑ ወቅት በወደ ትርፋማነት በመሸጋገር ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ፋብሪካው በብር ምንዛሪ ማሽቆልቆል ከቻይናው ኤግዚም ባንክ ለማስፋፊያው ፕሮጀክት የተበደረውን ብድር ክፍያ ፈታኝ እንዳደረገበት ተገልጿል፡፡ በተጨማሪም ፋብሪካው የጎማ ዛፍ ፕሮጀክቱንና ዋና መሥሪያ ቤቱን (የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን) በገንዘብ የሚደግፍ በመሆኑ፣ ከፍተኛ ኃላፊነቶች የተጣሉበት እንደሆነ አቶ ተባባል ገልጸዋል፡፡ ‹‹ይሁን እንጂ ይህን ሁሉ ተቋቁሞ የድንጋይ ከሰል መጠቀም ከጀመረ በኋላ ወደ ትርፍ በመምጣት ላይ ይገኛል፤›› ብለዋል፡፡ ", "passage_id": "c8c92271b7af41dc58629e8698a3eb26" }, { "passage": "በአዲስ አበባ ከተማ የሲሚንቶ ገበያ በደላላ እጅ ላይ በመውደቁ ዋጋው እየናረ መምጣቱን፣ አሁንም እንዳልተረጋጋና በወር ውስጥ እስከ 30 ብር ጭማሪ በማሳየት ከ520 እስከ 550 ብር ድረስ በኩንታል እየተሸጠ እንደሚገኝ፣ ነጋዴዎችና የግንባታ ባለሙያዎች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡ የግብይት ሰንሰለት ችግር ለዋጋ ንረቱ ምክንያት ነው ተብሏል፡፡ ይህ ዓይነቱ የዋጋ ጭማሪ ከመከሰቱ በፊት አንድ ኩንታል ሲሚንቶ ከ390 እስከ 450 ብር ይሸጥ እንደነበር ይናገራሉ፡፡የብሎኬት አምራች የሆኑት አቶ ሙከረም ሀቢብ እንደሚሉት፣ የሲሚንቶ ዋጋ ይረጋጋል የሚል ወሬ በተደጋጋሚ ቢሰማም፣ ነገር ግን ከጊዜ ወደ ጊዜ ጭማሪ እያሳየ ይገኛል፡፡‹‹ብሎኬት ለማምረት ሲሚንቶ ወሳኝ ግብዓት ነው›› የሚሉት ብሎኬት አምራቹ፣ በመስከረም ወር አካባቢ መንግሥት የሲሚንቶ ዋጋን እንደሚያረጋጋ የሰጠውን ተስፋ በመጠበቅ የግዥ እንቅስቃሴያቸውን ገታ አድርገውት እንደነበረ ገልጸው፣ ሆኖም ምንም የታየ ለውጥ ባለመኖሩ አሁን ኩንታሉን ከ500 ብር በላይ እየገዙ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡አቶ እንድሪስ ከድር በጎተራ አካባቢ በሲሚንቶ ንግድ ላይ የተሠማሩ ነጋዴ ሲሆኑ፣ የዳንጎቴና መሰል ሲሚንቶዎች መሸጫ ዋጋቸው ከ500 ብር በላይ ከገባ ሦስት ወራት ማስቆጠሩን፣ ሆኖም በወር ውስጥ ከ15 እስከ 20 ብር ጭማሪ እየታየባቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ‹‹ከፋብሪካ ሲሚንቶ እያገኘን አይደለም›› የሚሉት ነጋዴው፣ ከመንግሥት የልማት ድርጅቶች ሲሚንቶ አግኝቶ ለመሸጥ ረጅም ወራት እንደሚጠይቅ ገልጸው፣ ይኼም ለዋጋ አለመረጋጋት መንስዔ መሆኑን ሲሉ አስረድተዋል፡፡ፋብሪካዎች በአቅማቸው መጠን አለማምረታቸው የሲሚንቶ ዋጋ እንዳይረጋጋ ማድረጉን የሚናገሩት አቶ እንድሪስ፣ ሁሉም የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ምርቱን በበቂ መጠን ለገበያ ቢያቀርቡ ዋጋው በአንድ ጊዜ ወደ ታች እንደሚወርድ ገልጸዋል፡፡ከመንግሥት የልማት ድርጅቶች ሲሚንቶ ማግኘት ባለመቻሉ ምክንያት ከወኪል አከፋፋዮች ላይ ከ100 ብርና ከዚያም በላይ ጭማሪ በማድረግ እየገዙ እንደሚገኙ የገለጹት ወ/ሪት ማህሌት ፈለቀ የተባሉ የሲሚንቶ ችርቻሮ ነጋዴ፣ ወኪል አከፋፋዮች በሚያቀርቡት ዋጋ ላይ የትራንስፖርትና ሌሎች ወጪዎች ተዳምረው በመጨረሻ ሲሚንቶ ከቸርቻሪው እጅ ሲወጣ በኩንታል አሁን ያለበት 520 ብር አካባቢ ደርሷል ብለዋል፡፡በፋብሪካዎች በሚያጋጥም የጥሬ ዕቃና የውጭ ምንዛሪ እጥረት መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ ቢኖርም፣ በሥራው ላይ ያለው የደላሎች ጣልቃ ገብነት ገበያውን ረብሾታል የሚሉት ብሎኬት አምራቹ አቶ ሙከረም፣ ፋብሪካዎች በቀጥታ ለተጠቃሚው ከማድረስ ይልቅ ምርቱ ደላላው እጅ ላይ በመውደቁ በግብይቱ ላይ ለውጥ እንዳይመጣ አድርጎታል ሲሉ አስረድተዋል፡፡የናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ ተወካይ አቶ ፍጹም ንጉሤ በአሁኑ ጊዜ ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ እያመረተ እንደሚገኝ አስታውቀው፣ ሆኖም ከሲሚንቶ ፍላጎት አንፃር በሁሉም የሲሚንቶ ፋብሪካዎች አቅርቦቱ ስለማይጣጣም የዋጋ ጭማሪ እየተስተዋለ ነው ብለዋል፡፡ ከሁሉም የሲሚንቶ ፋብሪካዎች በአቅርቦት አሁን ናሽናል ሲሚንቶ ቀዳሚ ነው ያሉት ተወካዩ፣ ፋብሪካው የሲሚንቶ ፍላጎት በከፍተኛ ሁኔታ ካለበት አዲስ አበባ በብዙ ርቀት እንደመገኘቱ ምርቱን እያዳረሰ ያለው ለምሥራቅ ኢትዮጵያ፣ ለደቡብና ኦሮሚያ ስለሆነ ሌሎች ፋብሪካዎች እዚህ ላይ ብዙ ሊሠሩ ይገባል ብለዋል፡፡ የናሽናል ሲሚንቶን ጨምሮ የ12ቱ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የመሸጫ ዋጋ በኩንታል ከ280 እስከ 290 ብር ነው የሚሉት አቶ ፍጹም፣ ታየ የተባለው ጭማሪ ከፋብሪካዎቹ ጋር የተያያዘ እንዳልሆነ ገልጸዋል፡፡ አቶ ፍጹም አገሪቱ የገጠማትን የሲሚንቶ ተግዳሮት ለመፍታት የመጀመርያው ነገር የምርት አቅምን ማሳደግ ነው ብለው፣ ከዚህ ጎን ለጎን የተንዛዛውና አንዳንድ ተዋናዮች የሚሳተፉበት የግብይት ሥርዓቱ ሰንሰለት ማጠር አለበት ይላሉ፡፡ የአከፋፋዮችና የቸርቻሪዎችም ሚና በግልጽ ተለይቶ እንደ እነዚህ ዓይነት ቀውስ ሲከሰት የሚያባብሱበት ሳይሆን፣ የሚያረጋጉበትን መንገድ ማመቻቸት የሁሉም ኃላፊነት ይገባል ሲሉ አቶ ፍጹም አስረድተዋል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የሲሚንቶ አከፋፋዮች እንደ ደርባና ዳንጎቴ ያሉ የሲሚንቶ ምርቶችን ከ260 እስከ 273 ብር፣ እንዲሁም ቸርቻሪዎች ከ280 እስከ 293 ብር እንዲሸጡ የሚያዝ የዋጋ ዝርዝር ቢወጣም፣ ሪፖርተር ባደረገው ቅኝት ሲሚንቶ በአዲስ አበባ በኩንታል ከ500 እስከ 550 ብር እየተሸጠ እንደሚገኝ ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡በኢትዮጵያ ውስጥ 20 የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የሚገኙ ሲሆን፣ ካሉት ፋብሪካዎች 12 የሚሆኑት 14.1 ሚሊዮን ቶን ሲሚንቶ በዓመት የማምረት አቅም አላቸው፡፡ ሆኖም በጥሬ ዕቃ ችግርና ለመለዋወጫ ግዥ በሚውል የውጭ ምንዛሪ እጥረት ሳቢያ ፋብሪካዎቹ በቂ ምርት ባለማምረታቸው፣ የሲሚንቶ እጥረት በተደጋጋሚ እንደሚከሰት ይታወቃል፡፡", "passage_id": "766b7ce1c16d7727ef91bb1314e57444" } ]
c884aa80e5ae2e6ce836f84ffb7c3e45
6695d2a28da370b035b3aaac016b2d35
“የኢትዮ-ሱዳን የድንበር ጉዳይ በሁለትዮሽ ስምምነቶች እና በጋራ የድንበር መድረኮች አማካኝነት መፈታት አለበት” – ይበልጣል አዕምሮ በሱዳን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ አምባሳደር
በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ፦ በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል ያለው የድንበር ጉዳይ ባሉ የሁለትዮሽ ስምምነቶች እና የጋራ የድንበር መድረኮች አማካኝነት በሰላማዊ መንገድ መፈታት እንዳለበት በሱዳን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ አሳሰቡ። ከሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የብሔራዊ ድንበር ኮሚሽን ተቀማጭነታቸው በሱዳን ለሆኑ ዲፕሎማቲክ ሚሽኖች፣ ቆንስላዎች እና የዓለምአቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች ገለጻ አድርጓል። በዚህም ወቅት፣ አምባሳደር ይበልጣል ከዳግልሽ ተራራ በስተሰሜን ከሰፈራ እና ከእርሻ መሬት ጋር  በተያያዘ የተፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት ሁለቱን ሀገራት የሚያስማማ የመፍትሔ ሃሳብ እንዲመጣ የሚደነግገው እና በሁለቱ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እ.ኤ.አ. ሐምሌ 18 ቀን 1972 የተደረገው የማስታወሻ ልውውጥ ከፍ ያለ ፋይዳ እንዳለው አስታውቀዋል።በ1972ቱ የማስታወሻ ልውውጥ በተቀመጠው መሰረት የጉዊን መስመርን ዳግም ማካለል ከመጀመሩ በፊት ከዳግልሽ ተራራ በስተሰሜን ከእርሻ መሬት እና ሰፈራ ጋር በተያያዘ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት የጋራ ልዩ ኮሚቴው ሁለቱን ሀገራት የሚያስማማ የመፍትሔ ሃሳብ ያካተተ ሪፖርት ለጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ማቅረብ እንደሚኖርበት አመልክተዋል።የጋራ ልዩ ኮሚቴው ሁለቱን ሀገሮች የሚያስማማ የመፍትሔ ሃሳብ ለማቅረብ ስምንት ዙር ስብሰባዎችን ቢያካሂድም ኃላፊነቱን ገና እንዳላጠናቀቀ ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ-ሱዳን ድንበር የጋራ ልዩ ኮሚቴ ስራ ባልተጠናቀቀበት ሁኔታ እና የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በጥቅምት ወር መጨረሻ ህግ ለማስከበር ወደ ትግራይ ክልል ያደረገውን ስምሪት እንደ መልካም አጋጣሚ መጠቀሙን አምባሳደር ይበልጣል አመልክተዋል። በዚህም የሱዳን ሰራዊት ወደ ኢትዮጵያ ግዛት ዘልቆ በመግባት ንብረት ከመዝረፉ፣ ወታደራዊ እና የእርሻ ካምፖችን ከማቃጠሉ ባሻገር በኢትዮጵያውያን ላይ እስራት፣ ጥቃት እና ግድያ መፈጸሙ እንዲሁም በሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ማፈናቀሉን አስታውቀዋል ፤ ይህ የ1972 የማስታወሻ ልውውጥን በግልጽ የጣሰ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።በሁለቱ እህትማማች ሀገራት ጸንቶ ከቆየው አጋርነት እና ትብብር መንፈስ በተቃረነ መልኩ የሱዳን ሰራዊት አጋጣሚውን በመጠቀም  የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ   ሰራዊት ለቋቸው የወጣ ካምፖችን መቆጣጠሩን ጠቁመዋል።ሱዳን በችግር ውስጥ በነበረችበት ጊዜ ሁሉ ኢትዮጵያ ከሱዳን ህዝብ ጎን መቆሟን ያስታወሱት አምባሳደር ይበልጣል፤ ኢትዮጵያ በውስጥ ጉዳይዋ በተጠመደችበት ወቅት ከሱዳን ሰራዊት የደረሰባት ጥቃት የሚገባት እንዳልሆነ አመልክተዋል።የማስተካከያ እርምጃ በፍጥነት ካልተወሰደ፣ ታይቶ የማይታወቀው የሱዳን ሰራዊት ተግባር የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ብሎም የጋራ ድንበሩን ዳግም የማካለሉን ስራ የሚያወሳስብ እና ለሁለቱ ሀገራት ህዝቦች እንዲሁም ለቀጠናው ከፍ ያለ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚኖረው አስታውቀዋል።የኢትዮጵያ እና ሱዳን የድንበር ልዩነቱን ሁለቱ ሀገራት በገቧቸው ስምምነቶች እና ባሉ የጋራ የድንበር መድረኮች መሰረት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ኢትዮጵያ ቁርጠኛ መሆኗንም አረጋግጠዋል። ለችግሩ ዘላቂ እልባት ለመስጠት ፣ የሱዳን ሰራዊት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፈጸመውን ወረራ በመቀልበስ በ1972ቱ የማስታወሻ ልውውጥ በተቀመጠው መሰረት ወደ ቅድመ-ኖቬምበር 2020 (እ.ኤ.አ.) መመለስ እንዳለበት አስታውቀዋል።ከዚህም በተጨማሪ ወደ ድንበር ዳግም ማካለል ከመገባቱ በፊት የጋራ ልዩ ኮሚቴው በ1972 የማስታወሻ ልውውጥ መሰረት ከዳግሊሽ ተራራ በስተሰሜን ከሰፈራ እና እርሻ መሬት ጋር በተያያዘ የተፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት ሁለቱን ሀገራት የሚያስማማ የመፍትሔ ሃሳብ የማቅረብ ስራውን ማጠናቀቅ እንዳለበት አመልክተዋል ።የጋራ ድንበሩን ዳግም ለማካለል ሁለቱ ሀገራት ያቋቋሟቸው የጋራ የድንበር ኮሚሽን፣ የጋራ የቴክኒክ የድንበር ኮሚቴ፣ እና የጋራ ልዩ ኮሚቴ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እና ስራቸውን እንዲያጠናቅቁ ማድረግ ተገቢ እንደሆነ ጠቁመዋል ።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=39551
[ { "passage": "ፕሬዚዳንት ኪር የሱዳን ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት አባል የሆኑትን ቼምስ አል ዲን ካባሽ እና ተጠባባቂ የሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦመር ጋማር ኢልዲንን በጁባ አነጋግረዋል፡፡ ተጠባባቂ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በኢትዮ ሱዳን ድንበር ከሰሞኑ የተፈጠረውን ሁኔታ ለፕሬዚዳንት ኪር ገልጸዋል፡፡\nፕሬዚዳንት ኪር ካርቱምና አዲስ አበባ የድንበር እሰጥ አገባውን በድርድርና በሰላማዊ መንገድ ብቻ መፍታት እንዳለባቸው ጁባ ለተገኙት የሱዳን ባለሥልጣናት መግለጻቸውን ሱዳን ትሪቡን ዘግቧል፡፡\nኢትዮጵያና ሱዳን የሚጋሩትን ድንበር በተመለከተ በዲፕማሲያዊ መንገድ ብቻ መፍታት ይገባል ያሉት ፕሬዚዳንት ኪር በቀጠናው ከዚህ በኋላ ጦርነት መኖር እንደሌለበት አሳስበዋል፡፡\nሱዳን ባለፈው ኅዳር ከኢትዮጵያ ጋር በምትዋሰንበት ድንበር አቅራቢያ ወታደሮችን ማስጠጋቷና የኢትዮጵያን ሚሊሻዎችና አርሶ አደሮችን ማፈናቀሏ የተዘገበ ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስት ልዑክም ይህንኑ ጉዳይ ካርቱም ተገኝቶ መገለጹ ይታወሳል፡፡\nበዚህ ጉዳይ ዙሪያ የኤርትራና ግብጽ ባለሥልጣናት ከሱዳን ሹሞች ጋር በካርቱም ውይይት አድርገዋል፡፡\nከ15 ቀናት በፊት የኢትዮጵያ እና የሱዳን ድንበር የጋራ ከፍተኛ የፖለቲካ ኮሚቴ በካርቱም ያደረገው ውይይት ያለስምምነት መጠናቀቁን የሱዳን የሽግግር መንግስት ምንጮች በወቅቱ መግለጻቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ በወቅቱ ውይይቱ የተመራው በኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን እና በሱዳን ካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር አምባሳደር ኦማር በሽር ማኒስ ነበር፡፡\nሱዳን በድንበር አካባቢ የምታደርገውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ በአስቸኳይ እንድታቆም ኢትዮጵያ ማሳሰቧ የሚታወስ ሲሆን በድንበር ላይ ያለው ችግር በውይይትና በንግግር እንዲፈታም በተደጋጋሚ ጠይቃለች፡፡\nየኢትዮጵያና ሱዳን ድንበር የጋራ ከፍተኛ የፖለቲካ ኮሚቴው ውይይቱ በሌላ ጊዜ ለማድረግ ተለዋጭ ቀጠሮ ተይዟል፡፡\nየኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ከአል ዐይን ኒውስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ኢትዮጵያ ከሱዳንጋር ያላትን ግንኙነት እንደምትንከባከብ ገልጸው በድንበር ላይ የተፈጠረው ችግር ግን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ብቻ እንዲፈታ ትፈልጋለች ብለዋል፡፡\nበአውሮፓውያኑ 2014 የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ እና የወቅቱ ሱዳን መሪ ኦማር ሐሰን አልበሽር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቻቸውን ድንበሩ መሬት ላይ የሚመላከትበትን የመጨረሻ ቀን እንዲያሳውቁ መመርያ አስተላልፈውላቸው እንደነበር ይታወሳል።\n", "passage_id": "334746f100235a527cc812404e07fc96" }, { "passage": "“ሰሞኑን የሱዳን ኀይሎች ኀላፊነት በጎደለው መልኩ የኢትዮጵያን መሬት መያዛቸው ስህተት እንደሆነ፤ አንዳንድ የሱዳን ሚዲዎችና ባለስልጣናትም መሬታቸውን እንዳስመለሱ አድረገው በመግለጫ የሚያሰራጩት መረጃ ተቀባይነት የለውም” የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲባሕር ዳር፡ ታኅሣሥ 25/2013 ዓ.ም (አብመድ) የኢትዮ ሱዳን ድንበር ግጭት ሱዳን መንግሥትና ሰፊው የሱዳን ሕዝብ ፍላጎት እንዳልሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ አስታወቁ። ግጭቱ ለማንም እንደማይበጅ የኢትዮጵያ አቋም መሆኑንም አመላክተዋል።አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በግጭቱ ዙሪያ እንዳስታወቁት፣ የኢትዮጵያና የሱዳን ድንበር 100 ዓመት ያስቆጠረ ቢሆንም በሌሎችም የአፍሪካ አገራት እንደሚታየው ከቅኝ ገዥዎች የተወረሱ ችግሮች መኖራቸውን ጠቁመዋል።ኢትዮጵያ በቅኝ ገዥዎች ባትገዛም ሱዳን በቅኝ ግዥዎች ስር ስለነበረች፣ ድንበሩ ምንም እንኳ ምልክቶች ቢኖሩትም በዘመናዊ ዘዴ በትክክል ባለመካለሉ አንዳንዴ በሁለቱም ሀገራት የድንበር አካባቢዎች መገፋፋቶች ይፈጠራሉ ብለዋል፡፡አሁን ያለው ድንበር ባህላዊ መሆኑን ጠቁመው፣ ሰሞኑን የሱዳን ኀይሎች ኀላፊነት በጎደለው መልኩ የኢትዮጵያን መሬት መያዛቸው ስህተት መሆኑ እንዳለ ሆኖ አንዳንድ የሱዳን ሚዲዎችና ባለስልጣናት መሬታቸውን እንዳስመለሱ አድረገው በመግለጫ የሚያሰራጩት መረጃ ተቀባይነት የሌለውና ህገ ወጥ መሆኑ አስታውቀዋል።አንዳንድ የሱዳን ባለስልጣናት ከኋላ ሆነዉ ጉዳዩን ለሚያቀጣጥሉ የኢትዮጵያ ጠላቶች መጠቀሚያ ሆነው ቢያገለግሉም፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ግን ግጭቱ የሱዳን ሕዝብና መንግሥት ፍላጎት ነው የሚል መደምደሚያ ላይ እንዳልደረሰ ገልጸዋል።ይልቁንስ መጠቀሚያ እየሆኑ ያሉ የሱዳን ባለስልጣናት ድርጊታቸው ሱዳንንም ሆነ ኢትዮጵያን በፍጹም ስለማይጠቅም ያሉትን ችግሮች በሰላማዊና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንዲፈታ የኢትዮጵያ መንግሥት እያሳሰበ መሆኑን ገልጸዋል። ድንበሩም በድንበር ኮሚሽን መርሆዎች ብቻ እንዲፈታም የኢትዮጵያ አቋም እንደሆነም አስታውቀዋል።ግጭቱ የሱዳን መንግሥትና የሱዳን ሕዝብ ፍላጎት እንዳልሆነ የሚገልጹ “እኛ ከኢትዮጵያ ጋር ፈጽሞ ወደ ግጭት አንገባም” የሚሉ ድምፆች እየጨሩ መምጣታቸውን የጠቆሙት አምባሳደር ዲና፣ ከበስተጀረባው ግን የተለያዩ ኃይሎች እንዳሉ ጠቁመዋል።እነዚህ ኃይሎች ለዘመናት ያልጠቀሟትን ሱዳን ወዳጅ በማስመሰል የጥፋት አጀንዳቸውን ለማሳካት እየታተሩ እንደሚገኙ ጠቁመው ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ለሠላም ወዳዱ የሱዳን ሕዝብ እና ባለስልጣናት፣ እንዲሁም ለሰላም ወዳዱ የአረቡ ማህበረሰብ ፣ ግጭቱ ለማንም እንደማይበጅ በተጨባጭ እያሳወቀች መሆኑን አመልክተዋል።", "passage_id": "be99bcf89c480355ca3b169bb470f7ac" }, { "passage": "ኢትዮጵያና ሱዳን በድንበር ጉዳይ የጋራ መፍትሄ ለማበጀት የተፈራረሙትን ስምምነት ሱዳን መጣሷን የኢትዮ-ሱዳን ድንበር ኮሚሽን አባላት ገለጹ።\nበኢትዮጵያ በኩል የተወከሉት የኢትዮ-ሱዳን የድንበር ኮሚሽን አባላት በዛሬው እለት መግለጫ ሰጥተዋል።\nየኮሚሽኑ አባል አምባሳደር ኢብራሂም ኢድሪስ በመግለጫቸው ፣ ሁለቱ ሀገራት እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣጠር በ 1972 በድንበር ጉዳይ የጋራ መፍትሄ ለማበጀት የተፈራረሙትን ስምምነት ሱዳን መጣሷን አብራርተዋል።\nስምምነቱ ፣ ሁለቱ ሀገራት በድንበር ጉዳይ የጋራ መፍትሄ እስኪያስቀምጡ ድረስ መሬት ላይ ያለው ነባራዊ ሁኔታ እንዲቀጥል ያስገድዳል።\nሆኖም ሱዳን የኢትዮጵያን ድንበር ጥሳ በመግባት የያዘችው መሬት ይህንን ስምምነት የሚጥስ መሆኑን አምባሳደር ኢብራሂም ኢድሪስ አብራርተዋል።\nየድንበር ጥሰቱ በግብርና ምርትና በንብረት ላይ ጉዳት በማድረስ ዜጎችን ለመፈናቀል ዳርጓል ብለዋል።\nበመሆኑም ሁለቱ ሀገራት አለመግባባቱን ዓለም አቀፍ ህግንና የድንበር ስምምነትን በማክበር በሰላማዊ መንገድ በውይይት መፍታት ይኖርባቸዋል ብለዋል።\nሱዳን በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ ገብታ መሬት መያዟ በሕግ የሚያስጠይቃት በመሆኑ በአስቸኳይ ለቃ የቀድሞው ነባራዊ ሁኔታ መመለስ እንዳለበት እና በ1972 የተደረሰውን ስምምነት እንድታከብር ጠይቀዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።\nሱዳን በአል ፋሻቃ ድንበር አካባቢ “በኢትዮጵያ ተይዞብኝ ቆይቷል” ያለችውን መሬት “በኃይል አስመልሻለሁ” ማለቷ ይታወሳል፡፡ “እስከ 70 በመቶ የሚሆነውን መሬቴን አስመልሻለሁ” ያለችው ሀገሪቱ “ገና የሚቀራት ይዞታ መኖሩንም” የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አስታውቀዋል፡፡\nበቅርቡ በካርቱም በተካሔደው የሁለቱ ሀገራት የከፍተኛ ፖለቲከኞች ስብሰባ ላይ ከተሳተፉ በኋላ የኢትዮጵያ ም/ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ደመቀ መኮንን ፣ ሱዳን በትግራይ ክልል የሕግ ማስከበር ዘመቻ ከተጀመረ ከ6 ቀናት በኋላ ወረራ መጀመሯን አስታውቀዋል፡፡ በዚህም የሰዎችን ሞት ጨምሮ ሌሎች ጉዳቶችም መድረሳቸውን ነው የገለጹት፡፡\nየውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲም ትናንት በሰጡት ሳምንታዊ መግለጫ ሱዳን ወደ ቀድሞ ይዞታዋ እንድትመለስ እና ድርድሩ እንዲቀጥል ኢትዮጵያ ለሀገሪቱ መግለጿን ይፋ አድርገዋል፡፡\n", "passage_id": "ac885267a0c4f70d63392334a046a165" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ህዳር 9፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በካርቱም የኢፌዴሪ ልዩ መልዕከተኛና ባለመሉ ስልጣን አምባሳዳር ይበልጣል አእምሮ ከካርቱም ስቴት ገዥ አይማን ካሊድ መሀመድ ካልድ ጋር ተወያዩ፡፡አምባሳደሩ ስለ ወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳይና ህግ ማስከበር ስራ ላይ ገለፃ አድርገዋል፡፡ከዚህ በተጨማሪ በሱዳን ለሚኖሩ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ አባላት ክለብ የሚያገለግል ተጨማሪ ቦታ እንዲሰጥ ለአስተዳዳሪው ጥያቄ ማቅረባቸውን በሱዳን የኢትዮጵያ ኢምባሲ አሳውቋል፡፡", "passage_id": "c3fdd2a7a64dcfc26f821e0a4f2ef1f9" }, { "passage": "18ኛው የኢትዮ ሱዳን የድንበር ልማት ስብሰባ መቀሌ ከተማ ውስጥ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ከኢትዮጵያ መሬት ተቆርሶ ለሱዳን ተሰጥቷል ለሚለው ከተቃዋሚ ድርጅቶች የሚቀርበውን ተደጋጋሚ ክስ ልብ ወለድ ነው ይላል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፡፡በኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የጎረቤት አገሮች ጉዳይ ሃላፊ አቶ መለስ አለም ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት መግለጫ የስብሰባው ዋና ዓላማ በሁለቱም አገራት ጥቅም ዙርያ የሚነጋገር መሆኑን አስረድተዋል፡፡በኢኮኖሚና ማሕበራዊ፣ በፖለቲካና ፀጥታ፣ በጤና፣ በሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ዙርያ ዝርዝር ውይይት መካሄዱን አቶ መለስ ይናገራሉ፡፡ከኢትዮጵያ ለሱዳን ተቆርሶ የተሰጠ መሬት ስለመኖሩ ተቃዋሚ ድርጅቶች በተደጋጋሚ የሚያቀርቡትን ክስ፣ በሁለቱም አገሮች ድንበር ላይ የሚኖሩ ገበሬዎች በመሬት የባለቤትነት ጉዳይ ላይ እንደሚጋጩ ሱዳን ቱሪቡን ላቀረበው ዘገባ፣ እንዲሁም በማሕበረሰባዊ ድረ ገፅ ውይይቱ በድንበር አከላለል ዙርያ የሚደረግ ስለመሆኑ የተጻፈው በጎበዝ ፀሐፊ የተፃፈ ልብወለድ ነው ሲሉ አቶ መለስ አለም መልስ ሰጥተዋል፡፡ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ። ", "passage_id": "b245923fe7869ae15d82b1500543bc3a" } ]
075b8875b71f3bbde24f0f56eda9afc0
b9b17c39bdd2fcfcf7b3bdaf958ba6ee
የጎዳና ላይ ሩጫ በቢሾፍቱ
ቢሸፍቱ ፦የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከወራት መቋረጥ በኋላ የመጀመሪያውን አገር አቀፍ የ30 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ አካሂዷል፡፡ ለ7ኛ ጊዜ በቢሾፍቱ ከተማ በተካሄደው በዚህ ውድድር ላይም በአጠቃላይ ነጥብ በሴቶች ኦሮሚያ ፖሊስ በሴቶች ደግሞ መከላከያ ስፖርት ክለብ ቀዳሚ በመሆን አጠናቀዋል፡፡ የመከላከያዋ አትሌት ገበያነሽ አየለ በሴቶች ቀዳሚ ሆና ስታጠናቅቅ፤ የገባችበት ሰዓት ደግሞ 1:47.03 ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ የግል ተወዳዳሪዎቹ ብርሃን ምህረቱ እና ንግስት ሙሉነህ ደግሞ ሁለተኛና ሶስተኛ በመሆን ውድድራቸውን ፈጽመዋል፡፡ በወንዶች በኩል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ክለብ አትሌቱ ኃይለማርያም ኪሮስ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል፡፡ አትሌቱ 30 ኪሎ ሜትሩን ለመሸፈን የፈጀበት ጊዜም 1:31.18 ሆኗል፡፡ 1:31.23 የሆነ ሰዓት ያስመዘገበው ፌዴራል ማረሚያ አትሌት ዴሬሳ ገለታ እና 1:32.08 በሆነ ሰዓት የገባው የመከላከያው ሙስጠፋ ከድር ደግሞ ሁለተኛና ሶስተኛ ሆነው በማጠናቀቅ የብርና ነሐስ ሜዳሊያ ተሸላሚዎች ሆነዋል፡፡ በ7ኛው የኢትዮጵያ 30 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ አጠቃላይ ነጥብም በሴቶች ኦሮሚያ ፖሊስ ስፖርት ክለብ እንዲሁም በወንዶች የመከላከያ ስፖርት ክለብ የዋንጫ ተሸላሚዎች ሆነዋል፡፡አዲስ ዘመን ህዳር 28/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=36908
[ { "passage": "ከባድ በሆነውና ታላቅ ጽናትን በሚጠይቀው የአትሌቲክስ ዘርፍ ማራቶን ዓለም አቀፍ ተሳትፎዋን የጀመረችው ኢትዮጵያ፤ በበርካታ ገድሎች የአትሌቲክስ ታሪኳን አድምቃለች። ከኦሊምፒክ ቀጥሎ ታላቅ ስፍራ ባለው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናም የመጀመሪያውን ሜዳሊያ ያስመዘገበችው በማራቶን ነው። ሃገሪቷ ካስመዘገበቻቸው 77 ሜዳሊያዎች መካከልም 10 የሚሆኑት በማራቶን የተገኙ ሲሆን፤ ከእነዚህም መካከል ሁለቱ ወርቅ ሲሆኑ፤ አራት ብር እና አራት ነሃስ ናቸው። የኢትዮጵያ ተሳትፎ መነሻውን እአአ\nበ1983 በፊንላንዷ ሄልሲንኪ ካደረገው የዓለም ሻምፒዮና ሲጀመር በማራቶን የብር ሜዳሊያ ነው ሰንጠረዡ የተሟሸው። በወቅቱ ኢትዮጵያዊው አትሌት ከበደ ባልቻ በአውስትራሊያዊው ሮበርት ዴ ካስቴሌ ቢቀደምም ጀርመናዊውን ዋልዴማር ሴርፒኒስኪን በማስከተል የብር\nሜዳሊያ ተሸላሚ በመሆን ነበር ውድድሩን ያጠናቀቀው። ይህ ሜዳሊያም ኢትዮጵያን በሻምፒዮናው በብቸኝነት ያስጠራ ሆኖ ነው የተጠናቀቀው። ከዚያ\nበኋላ በተካሄዱት ዓለም ሻምፒዮናዎች በዚህ ርቀት ተሳትፎ እንጂ ውጤት ሳታስመዘግብ ነበር የቆየችው። ድሉ ወደ ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች እስከተመለሰበት እአአ 2001 የኤድመንተን ሻምፒዮና ድረስም ለረጅም ጊዜ ተቋርጦ ቆይቷል። ኤድመንተን ላይ የ23 ዓመቱ\nወጣት አትሌት ገዛኸኝ አበራ ባልተጠበቀ መልኩ ሌሎቹን አስከትሎ በመግባት ለመጀመሪያ ጊዜ የወርቅ ሜዳሊያውን ለሃገሩ ማስመዝገብም ችሏል። በወቅቱ የአትሌት ገዛኸኝ አበራ\nየማራቶን እና የአትሌት ደራርቱ ቱሉ የ10ሺ\nሜትር የወርቅ ሜዳሊያዎች ከሌሎቹ ጋር ተደምረው ኢትዮጵያን ከአፍሪካ ሁለተኛ ከዓለም ደግሞ ስድስተኛ ደረጃን እንድትይዝ አድርገዋት ነበር። ገዛኸኝ በዚህ ውድድር የወንዶች ተሳትፎ እስካሁንም ያልተደገመ ድል ሲያስመዘግብ፤ በዓለም ሻምፒዮና ታሪክ ከገዛኸኝ ባነሰ እድሜ ማራቶንን ያሸነፈ አትሌት ባለመታየቱ ባለ ድርብ ክብር አትሌት ያደርገዋል። እአአ\nበ2009 በበርሊን በተካሄደው ሻምፒዮና የበላይነቱ በኬንያዊያን አትሌቶች ቢያዝም ኢትዮጵያዊው አትሌት ጸጋዬ ከበደ ግን የነሃስ ሜዳሊያውን በማጥለቅ ለሃገሩ የርቀቱን ሦስተኛ ሜዳሊያ አጥልቋል። ይህ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በማራቶን ሁለት ሜዳሊያ ያገኘችበት ሲሆን፤ በሻምፒዮናው ተሳትፎ ሴቶች የሜዳሊያ ሰንጠረዡን የተቀላቀሉበት የመጀመሪያው ዓለም ሻምፒዮናም ነው። በውድድሩ የቻይናና የጃፓን አትሌቶችን ተከትላ በመግባት የነሃስ ሜዳሊያውን ያጠለቀችው አትሌትም አሰለፈች መርጊያ ናት። በቀጣዩ የዴጉ\nየአትሌቲክስ ዓለም ሻምፒዮና ላይም ሌላኛው አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ በማራቶን የሜዳሊያ ሰንጠረዡን መቀላቀል ችሏል። አትሌቱ ሁለቱን ኬንያዊያን አትሌቶች ተከትሎ በመግባቱም ነበር የነሃስ ሜዳሊያ ባለቤት የሆነው። በ13ኛው\nየሞስኮ ዓለም ሻምፒዮና አትሌት ሌሊሳ ዴሲሳ እና ታደሰ ቶላ ዩጋንዳዊውን አትሌት ተከትለው የብርና የነሃስ ሜዳሊያዎችን አስመዝግበዋል። በሴቶች የታየው ውጤታማነት ግን ለሁለት ሻምፒዮናዎች ሳይደገም ነበር የቆየው። በቤጂንጉ ሻምፒዮና አትሌት የማነ ጸጋዬ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ የብር ሜዳሊያውን ሲያገኝ፤ በሴቶች በኩል ሁለተኛው ሜዳሊያ የወርቅ ሆኖ ሊመዘገብ ችሏል። የጎዳና ላይ ሯጭ አትሌት ማሬ ዲባባ በሻምፒዮናው የኬንያ እና ባህሬን አትሌቶችን በማስከተልም ነው አሸናፊ ልትሆን የቻለችው። ከሁለት ዓመታት በፊት በለንደን በተካሄደው የዓለም ሻምፒዮናም በአትሌት ታምራት ቶላ የብር ሜዳሊያ ተመዝግቧል። ኢትዮጵያ በማራቶን ካስመዘገበቻቸው 10 ሜዳሊያዎች መካከል ስምንቱ ሜዳሊያዎች በወንዶች የተመዘገቡ ናቸው። በዓለም ዓቀፍ ደረጃም ባስመዘገቧቸው ሜዳሊያዎች 4ኛ ደረጃ\nላይ ሊቀመጡ ችለዋል። ከሦስት ወራት በኋላ በኳታሯ ዶሃ አስተናጋጅነት ትልቁ የአትሌቲክስ ውድድር የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለ17ኛ\nጊዜ ይካሄዳል። በዚህ ሻምፒዮና ላይም ኢትዮጵያን አትሌቶች እንደተለመደው በርቀቱ የሚሳተፉ ሲሆን፤ ቡድኑን የሚወክሉት አትሌቶችም ታውቀዋል። በሻምፒዮናው ላይ በርካታ ሃገራትን ጨምሮ ማህበሩን የወከሉት የስደተኞችና በተለያዩ ምክንያቶች ለሃገራቸው የማይሮጡ በሺዎች የሚቆጠሩ አትሌቶችም ተሳታፊዎች ይሆናሉ። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም በሁለቱም ጾታዎች የማራቶን ቡድኑን ከእነ ተጠባባቂዎቻቸው አስታውቋል። ምርጫውም አትሌቶቹ ባስመዘገቡት የተሻለ ሰዓት እንዲሁም በዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ዋና ዋና ውድድሮችና የወርቅ ደረጃ በተሰጣቸው ማራቶኖች ተሳትፏቸው የተመረጡ ናቸው። በውድድሮቹ ላይ እአአ ከሴፕቴምበር 2018- ኤፕሪል 2019 ድረስ ተወዳድረው ያስመዘገቡት የተሻለ ሰዓትም በሻምፒዮናው ሃገራቸውን እንዲወክሉ ያደርጋቸዋል። በወንዶች በኩል ስድስት አትሌቶች ቡድኑን ሲቀላቀሉ፤ በቅርቡ በተካሄደው የለንደን ማራቶን ተሳትፎው የኢትዮጵያን ክብረወሰን የሰበረው እና በዓለም ሦስተኛውን ፈጣን ሰዓት ያስመዘገበው አትሌት ሞስነት ገረመው በቅድሚያ የተመረጠ አትሌት ሊሆን ችሏል። ሞስነት ቀዳሚ ለመባል የቻለው ደግሞ ባስመዘገበው 2 ሰዓት ከ02 ደቂቃ\nከ55 ሰከንድ የሆነ ምርጥ ሰዓት ነው። ባለፈው ዓመት በቺካጎ ማራቶን ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ያጠናቀቀው ሞስነት፤ እአአ በ2015ቱ\nየቤጂንግ ዓለም ሻምፒዮና 10ሺ ሜትር\nሃገሩን እንደወከለ የሚታወስ ነው። በለንደኑ ማራቶን ከሞስነት ጋር በአንድ ደቂቃ ልዩነት የግሉን ፈጣን ሰዓት ማስመዘግብ የቻለው አትሌት ሙሌ ዋሲሁን ለቡድኑ በሁለተኛነት ተመርጧል። አትሌቱ ያለው ሰዓት 2 ሰዓት ከ03 ደቂቃ\nከ16 ሰከንድ ሲሆን፤ እአአ በ2016 የካርዲፍ ግማሽ\nማራቶን ሻምፒዮና፤ ስምንተኛ ደረጃን በመያዝ ነበር ያጠናቀቀው። ሌላኛው አትሌት ሌሊሳ ዴሲሳም ባስመዘገበው ሰዓት ቡድኑን የተቀላቀለ ሦስተኛው አትሌት ነው። እአአ በ2013ቱ\nየሞስኮ ዓለም ሻምፒዮና የብር ሜዳሊያ ለሃገሩ ያስመዘገበው አትሌቱ፤ ባለፈው ዓመት በተካሄደው የኒውዮርክ ማራቶን የገባበት 2 ሰዓት ከ05 ደቂቃ\nከ59 ሰከንድ የሆነ ሰዓት ተመራጭ አድርጎታል። በማራቶን ዝነኛ ከሆኑ የዓለም አትሌቶች መካከል ተጠቃሽ የሆነው ሌሊሳ፤ ከኒውዮርክ ጎዳናዎች ባሻገር በቦስተን ማራቶንም ተደጋጋሚ ድሎችን አጣጥሟል። ዘንድሮ ባደረገው አራተኛ ተሳትፎውም ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ነበር ያጠናቀቀው አትሌቱ። በሴቶች በኩልም በተመሳሳይ ሦስት አትሌቶች የተመረጡ ሲሆን፤ አትሌት ሩቲ አጋ ባላት ሰዓት ቡድኑን ትመራለች። አትሌቷ ቀዳሚ ምርጫ ልትሆን የቻለችው ባለፈው ዓመት በተካሄደውና የወርቅ ደረጃ ባለው የበርሊን ማራቶን ባስመዘገበችው 2 ሰዓት ከ18ደቂቃ\nከ34 ሰከንድ የሆነ ምርጥ ሰዓቷ ነው። አትሌቷ ከወራት በፊት በተካሄደው የቶኪዮ ማራቶን 2:20:40 በሆነ ሰዓት አሸናፊ ነበረች። በዚህ ዓመቱ የዱባይ ማራቶን 2 ሰዓት 17ደቂቃ ከ41 ሰከንድ የገባችው አትሌት ወርቅነሽ ደገፉም በቡድኑ የተካተተች ሁለተኛዋ አትሌት ናት።\nበማራቶን ውድድሮች የተሻለ ውጤት ያላት አትሌቷ፤ ከዱባይ በኋላ በተካሄደው የቦስተን ማራቶን አሸንፋለች። በባለፈው ዓመቱ የዱባይ ማራቶን 2 ሰዓት ከ19ደቂቃ\nከ17ሰከንድ ያስመዘገበችው ሌላኛዋ አትሌት ሮዛ ደረጀም በሻምፒዮናው ሃገሯን እንደምትወክል አረጋግጣለች። በወንዶች በኩል በተጠባባቂነት ሦስት አትሌቶች የተያዙ ሲሆን፤ በቅርቡ በለንደኑ ማራቶን ተሳታፊ የነበረው ሹራ ኪጣታ ባለው ሰዓት ቀዳሚው ተጠባባቂ ሆኗል። ሹራ በዚህ ማራቶን 2ሰዓት ከ05ደቂቃ\nከ01ሰከንድ የሆነ ሰዓት አስመዝግቧል። በተመሳሳይ በዚህ ዓመት በተካሄደው የቶኪዮ ማራቶን ተሳትፎው 2ሰዓት ከ04 ደቂቃ\nከ48ሰከንድ በመግባት ያሸነፈው አትሌት ብርሃኑ ለገሰ ሁለተኛው ተጠባባቂ ነው። ባለፈው ዓመት የዱባይ ማራቶንን 2ሰዓት ከ04ደቂቃ\nከ06 ሰከንድ የሮጠውና በለንደኑ የዓለም ሻምፒዮና በማራቶን ብቸኛውን ሜዳሊያ ያስመዘገበው አትሌት ታምራት ቶላም በተጠባባቂነት ከተያዙ አትሌቶች መካከል ይገኛል። በቶኪዮ ማራቶን በሰከንዶች ተበላልጠው ውድድራቸውን የፈጸሙት አትሌት ሹሬ ደምሴ እና ሄለን ቶላ ደግሞ በሴቶች በኩል በተጠባባቂነት የተያዙ አትሌቶች ናቸው። ከሄልሲንኪ የጀመረው\nየኢትዮጵያ የማራቶን ድል እስከ\nዶሃ እንዲዘልቅም ዝግጅቱ\nከወዲሁ ተጀምሯል። በውድድሩ\nህግ መሰረት ለሻምፒዮናው\nየተመረጠ አትሌት ለሦስት\nወራት የማገገሚያ ጊዜ የግድ\nያስፈልገዋል። በዚህም መሰረት\nአሁን አትሌቶቹ ከውድድር\nርቀው በአሰልጣኞቻቸው ልምምድ\nበማድረግ ላይ ይገኛሉ።\nበመጪው ሐምሌ ወር በሻምፒዮናው ተሳታፊ የሚሆኑ\nአትሌቶችን ለመምረጥ በኔዘርላንድ\nሄንግሎ ከሚካሄደው የሟሟያ\nውድድር በኋላም ብሄራዊ\nቡድኑ ወደ ካምፕ\nገብቶ ልምምዱን እንደሚጀምር\nየኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን\nመረጃ ያመላክታል።አዲስ ዘመን ሀምሌ 8/2011 ", "passage_id": "e1b7442d800b9ee7d781bdfcb6823f6e" }, { "passage": "በእስያ አህጉር ትልቁ የጎዳና ላይ ሩጫ የፈረንጆቹ ዓመት በገባ የመጀመሪያው ወር ሦስተኛው እሁድ ይካሄዳል። በአህጉሪቷ በርካታ ሯጮችን አሳትፎ የሚካሄደው ውድድር 45ሺ የአሜሪካ ዶላር ሽልማትን በማሳፈስም ቀዳሚው ነው። በለንደን ማራቶን በመነሳሳት እአአ 2004 ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው የሙምባይ ማራቶን በቀጣዩ ዓመት ከዓለም ታላላቅ የጎዳና ላይ ውድድሮች ተርታ ለመሰለፍ በቅቷል። በአጭር ጊዜ እድገት በማሳየቱም እአአ 2009 የብር ደረጃ ሲያገኝ፤ በቀጣዮቹ ዓመታት በወርቅ እና ብር ደረጃዎች ውድድሮችን ሲያካሂድ ቆይቶ ያለፈው ዓመት በድጋሚ የወርቅ ደረጃውን ተረክቧል። ሕንድ ስሟን በምታስጠራበት ዓመታዊው የማራቶን ውድድር ላይም ታላላቅ የቦሊውድ ተዋናዮች፣ የንግድ ሰዎች፣ ጎብኚዎችና የሀገሬው ዜጋ ሲሳተፉ፤ ታዋቂና ዝነኛ አትሌቶችም ይፋለሙበታል።በዚህ ዓመቱ ውድድር ላይም እንደተለመደው ተሳታፊነታቸውን ያረጋገጡት ኬንያውያንና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የአሸናፊነት ቅድመ ግምቱን አግኝተዋል። በሴቶች በኩል በሚካሄደው ውድድር የአምናዋ አሸናፊ ወርቅነሽ አለሙ በድጋሚ የቦታውን ክብር ትቀዳጃለች በሚል ይገመታል። ከ2:28:00 በታች የሆነ ፈጣን ሰዓት ካላቸው ስምንት አትሌቶች መካከል አንዷ የሆነችው አትሌቷ ባለፈው ዓመት የገባችበት\n2:25:25 የሆነ ሰዓት በሙምባይ ማራቶን ሁለተኛው ፈጣን ሰዓት ነው። በዚሁ ዓመት በአምስተርዳም ማራቶን የተሳተፈችው አትሌቷ ስድስተኛ ደረጃን በመያዝ ታጠናቅ እንጂ ያስመዘገበችው 2:24:42 የሆነ ፈጣን ሰዓት ነው። በወንዶች ምድብ ደግሞ ኬንያዊው ኮስማስ ላጋት የሙምባይ ማራቶንን ለሁለተኛ ጊዜ አሸናፊ እንደሚሆን ይጠበቃል። ባለፈው ዓመት በዚህ ውድድር ላይ የተካፈለው ላጋት ከ29ኪሎ ሜትር በኋላ ያሉትን ርቀቶች ከሌሎች ተነጥሎ ብቻውን በመሮጥ ነበር ለአሸናፊነት የበቃው፤ የርቀቱን የመጨረሻ መስመር ለመርገጥ የፈጀበት ጊዜም 2:09:15 ነበር። አትሌቱ በዚህ ውድድር ላይ ከአሸናፊነት ባለፈ እአአ 2016 በሀገሩ ልጅ የተመዘገበውን ክብረወሰን በማሻሻልም ጭምር 15ሺ የአሜሪካ ዶላር ማበረታቻውንም ለመውሰድ አቅዷል። አትሌቱ በሰጠው አስተያየትም፤ አምና የዚህ ውድድር አሸናፊ መሆኑ ለዚህ ዓመት ሊረዳው የሚችል ልምድ እንዳስገኘለትና የመጀመሪያውን ግማሽ በፍጥነት በመሮጥ ሰዓት ለማሻሻል ማቀዱን ነው የገለጸው።አዲስ ዘመን\nጥር\n2/2012 ዓ.ም ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "a13550c94ac8c2abddd3ebc9ec5ed107" }, { "passage": "በመክፈቻው\nዕለት በመም እና በሜዳ ላይ ተግባራት ሀገር አቀፍ ክብረወሰን በመስበር የተጀመረው፤ 48ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ሶስተኛ ቀኑን ይዟል። ከሰዓት በኋላ በሚኖረው መርሃ ግብርም ስድስት የፍጻሜ ውድድሮች ይካሄዳሉ። ከትናንት በስቲያ በተጀመረው በዚህ ሻምፒዮና ላይ ጠዋት እና አመሻሽ ላይ የተለያዩ የማጣሪያ እና የፍጻሜ ውድድሮች ተካሂደዋል። ጠዋት በተካሄደው የወንዶች ሱሉስ ዝላይ የፍጻሜ ውድድር የመከላከያው አትሌት አዲር ጉር፤ 15 ነጥብ 88 ሜ በመዝለል በራሱ ተይዞ የቆየውን ክብረወሰን አሻሽሏል። የኢትዮጵያ\nንግድ ባንኩ ቡኒኒ አንበሴ እና የሲዳማ ቡናው ጆሴፍ ኦባንግ ደግሞ እርሱን ተከትለው የሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን የያዙ አትሌቶች ሆነዋል። በዕለቱ የተካሄደው ሌላኛው የፍጻሜ ውድድር ደግሞ የሴቶች አሎሎ ውርወራ ነው። በዚህ ውድድር ላይም ዙርጋ ኡስማን ከሲዳማ ቡና፣ አመለ ይበልጣል ከመከላከያ እንዲሁም ሰላማዊት ማሬ ደቡብ ፖሊስ ቀዳሚውን ደረጃ በመያዝ አጠናቀዋል። አመሻሽ ላይም በወንዶች እና ሴቶች የ10ሺ ሜትር ውድድሮች ተካሂደዋል። አስቀድሞ\nበተደረገው የወንዶች ውድድር ላይም በ87 አትሌቶች መካከል ከፍተኛ ፉክክር የተካሄደ ሲሆን፤ ወጣቱ አትሌት ሰለሞን ባረጋ አሸናፊ ሆኗል። አንዱዓለም በልሁ እና አባዲ ሀዲስ ደግሞ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ የብር እና ነሃስ ሜዳሊያ ተሸላሚዎች ሆነዋል። ሌላኛው ከፍተኛ ፉክክር የተካሄደበትና ሀገር አቀፍ ክብረወሰንም የተሻሻለበት ውድድር በሴቶች መካከል የተካሄደው ነው። ታዋቂ አትሌቶችን ጨምሮ ከ54 በላይ አትሌቶች የተሳተፉበትን ውድድርም የትራንስ ክለብ አትሌት የሆነችው ለተሰንበት ግደይ 32 ደቂቃ ከ10 ሰከንድ ከ13 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ሰዓት ሸፍናለች። አትሌት\nፀሐይ ገመቹ እና ነፃነት ጉደታ ደግሞ በማይክሮ ሰከንዶች (32:17.20 እና 32:17.82 በሆነ) ተቀዳድመው ውድድራቸውን አጠናቀዋል። ትናንት በሁለተኛው ቀንም የተለያዩ ውድድሮች ፍጻሜያቸውን አግኝተዋል። በሱሉስ ዝላይ የሴቶች ፍፃሜ ውድድርም፤ የመከላከያዋ አጁዳ ኡመድ፣ የንግድ ባንኮቹ አራያት ዲቦ እና አማር ኡባንግ አሸናፊዎች ሆነዋል። በወንዶች 400 ሜትር ደግሞ አብዱራህማን አብዱ ኦሮሚያ ክልል፣ ኤፍሬም መኮንን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ፣ ሙስጠፋ ኢደኦ ከኦሮሚያ ክልል ከአንድ እስከ ሶስት ያለውን ደረጃ ይዘዋል። በ100\nሜትር የወንድ እና የሴት ውድድሮችም በትናንትናው ዕለት የተፈጸሙ ሲሆን፤ የትኛው አትሌት እንደቀደመ መለየት እስኪያዳግት ድረስ እጅግ ከፍተኛ ፉክክር የታየበትም ነበር። በሴቶች በተካሄደው ውድድርም ወርቄ ኩማሎ ከንግድ ባንክ፣ ሰዓዳ ሲራጅ ከመከላከያ እንዲሁም አቤቤ ከበደ ከኦሮሚያ ክልል በማይክሮ ሰከንዶች ልዩነት ገብተዋል። በወንዶች\nበተካሄደው ውድድር ደግሞ የኤሌክትሪኩ ናታን አበበ፣ የሲዳማ ቡናው ቴዎድሮስ አጥናፉ እንዲሁም የኦሮሚያ ክልሉ አብዱልሰታር ከማል አሸናፊዎች ሆነዋል። ዛሬ 9 ሰዓት ላይ በሚጀምረው የሶስተኛ ቀን መርሃ ግብር ላይም የወንዶች ዲስከስ ውርወራ፣ የሴቶች የርዝመት ዝላይ፣ የሴትና ወንድ 400 ሜትር መሰናክል እንዲሁም በሁለቱም ጾታ የ800 ሜትር ውድድር የሚካሄድ ይሆናል።አዲስ\nዘመን  ግንቦት 1/2011በብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "0eed3a41c94875c78c0733c3fb33851b" }, { "passage": "“ለፋሲል እንሩጥ” በሚል መርህ በደጋፊዎች ማኅበር የተዘጋጀዉ የገቢ ማሰባሰብያ ታላቁ ሩጫ ዛሬ ከ 6000 እስከ 6500 የሚገመቱ የዐፄዎቹ ደጋፊዎች ተሳትፈውበት በጎንደር ከተማ ተከናውኗል።ጎንደር ከተማ ከነበረው ወቅታዊ ሁኔታ እና የመሮጫ ማልያ ሽያጭ የታሰባውን ያህል ገቢ ባለማስገኝቱ በተደጋጋሚ ለማራዘም የተገደደው ይህ ሩጫ በዛሬው ዕለት በተሳካ ሁኔታ ታካሂዷል። ከጠዋቱ 2:00 ላይ የህፃናቶች ሩጫ ተካሂዶ ከ1-10 ለወጡ ህፃናት የቦርሳዎች ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን በአዋቂዎች ቀድመው ሩጫውን ለጨረሱ 1000 ሜዳልያዎች በሽልማትነት ተበርክቶላቸዋል።ከዛሬው ውድድር የሚገኝውን 70 በመቶ ገቢ ለቡድኑ እንደሚያስረክብ የቀረውን 30 በመቶ ደግሞ ለሰራተኛ ደሞዝ እና ለስራ ማስኬጃ እንደሚውል ከቅናት በፊት በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ተገልጿል።በዘንድሮው የውድድር ዓመት በርካታ የገቢ ማሰባሰቢያዎችን ያደረጉት የዐፄዎቹ የደጋፊዎች ማኅበር ከዛሬው ታላቁ ሩጫ በተጨማሪ የንግድ ትርዒት እና የሙዚቃ ኮንሰርት አዘጋጅተዉ እንደነበር ይታወሳል ።", "passage_id": "419955c29558fabc96dd73ebc53522ed" }, { "passage": " በጀግናው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ መስራችነት የተቋቋመው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ባለፉት አስራ ስምንት ዓመታት አስር ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር በአዲስ አበባ በማካሄድ ተወዳጅነትን ማትረፉ ይታወቃል፡፡ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የተሳታፊዎቹን ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳደገም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ እውቅናን አትርፏል፡ ፡ አሁን ደግሞ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለታላቅ ሽልማት ለመብቃት እጩ መሆን እንደቻለ ኢትዮ ስፖርት በድረ ገፁ አስነብቧል፡፡ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በዓለም ላይ ከሚካሄዱ ሃያ ምርጥ የጎዳና ላይ ውድድሮች አንዱ በመሆን ‹‹ሌትስ ዱ ዚስ›› በተባለ ድረ ገፅ እጩ ተደርጓል፡፡ ሽልማቱን የሚያዘጋጀው ድረ ገፅ በዓለም ላይ ትልቅ እውቅና ያለው ሲሆን ከአስራ ስምንት ሺህ በላይ የጎዳና ላይ ውድድሮችን በዝርዝሩ የያዘ ነው፡፡ በአንድ ወር ውስጥም ከአንድ ሚሊየን በላይ ተመልካቾች አሉት፡፡ ሽልማቱ የሚካሄደው ብስክሌትን ጨምሮ በተለያዩ ስፖርቶች በአስራ ሦስት የሽልማት ዘርፎች ተከፍሎ ሲሆን ታላቁ ሩጫ የታጨበት የሽልማት ዘርፍ ዓለም አቀፍ የጎዳና ላይ ውድድር መሆኑ ታውቋል፡፡ ሽልማቱ በመጪው ጥቅምት ለንደን ከተማ ላይ ሲከናወን የቀድሞው የማንቸስተር ዩናይትድ የተከላካይ አማካይ ተጫዋችና በአሁኑ ወቅት የቴሌቪዥን ተንታኝ ሪዮ ፈርዲናንድ እንዲሁም ሌሎች ዝነኛ የስፖርቱ ዓለም ሰዎች እንደሚታደሙ ዘገባው ያመለክታል፡፡ ታላቁ ሩጫ እጩ በሆነበት የሽልማት ዘርፍ ዝነኞቹ የማራቶን ውድድሮች ኒውዮርክ ማራቶንና ቦስተን ማራቶን ተካተዋል፡፡ የሽልማቱ አሸናፊዎች በየዘርፉ የሚወሰኑት ውድድሮቹ ላይ የተሳተፉ የሕብረተሰብ አካላት በድረ ገፅ አማካኝነት በሚሰጡት ድምፅ ቁጥር መሰረት ይሆናል፡፡ ታላቁ ሩጫ ባለፉት 18 ዓመታት እንደስሙ ታላላቅ ስኬቶችን ማስመዝገብ የቻለ ውድድር መሆኑን በርካቶች ይመሰክራሉ፡፡ በተለይ ተተኪ አትሌቶችን በማፍራት በኩል ረጅም ርቀት መጓዙን የሚገልጸው የውድድሩ ድረ ገጽ የበጎ አድራጎት ሥራዎችን በማከናወንም ስኬታማ መሆኑ ተገልጿል። ከበጎ አድራጎትና ተተኪ አትሌቶችን ከማፍራቱ በተጨማሪ ታላቁ ሩጫ ኢትዮጵያን በሌላ መንገድ በማስተዋወቅ ስኬታማ ጉዞ ማድረጉ ይታወቃል።አዲስ ዘመን  ነሐሴ 30/2011 ቦጋለ\nአበበ", "passage_id": "838e6edc9d7b1e17580350674e044123" } ]
b36f04eab06336c0a8ecfc1fd411ebc1
310b702c671cc8e10f98729a26736d74
አትሌት ገንዘቤ ዲባባ የቫሌንሺያን የግማሽ ማራቶን አሸነፈች
አዲስ አበባ፡- አትሌት ገንዘቤ ዲባባ በስፔን በቫሌንሺያ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር አሸነፈች። በመካከለኛ እና የአጭር ርቀት ሩጫ የምትታወቀው አትሌት ገንዘቤ ዲባባ ግማሽ ማራቶን ለመጀመሪያ ጊዜ ተወዳድራ አሸናፊ መሆን ችላለች። ጀግናዋ አትሌት ገንዘቤ ዲባባ ውድድሩን ለማጠናቀቅ 1 ሰዓት ከ05 ደቂቃ ከ18 ሴኮንድ ፈጅቶባታል።የገባችበት ሰዓት የቦታው አዲስ ክብረወሰን በመሆንም ተመዝግቧል። ውድድሩን በሁለተኛነት ያጠናቀቀችው ኬንያዊቷ ሼይላ ቼፕኪሩይ ስትሆን፤ ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት ሰንበሬ ተፈሪ ደግሞ ሶስተኛ ሆናለች። የነሐስ ሜዳሊያ ባለቤቷ ሰንበሬ ርቀቱን ለመሸፈን የወሰደባት ሰዓትም 1፡05፡51 ነው። በእለቱ በተካሄደው የሴቶች ማራቶን ደግሞ ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ከ4-7 ባለው ደረጃ ተከታትለው ገብተዋል። በተመሳሳይ በእለቱ በተካሄደው የወንዶች ማራቶን ኢትዮጵያዊው ብርሃኑ ለገሰ 2፡03፡16 በሆነ ሰዓት ሶስተኛ ደረጃን ወጥቷል።አዲስ ዘመን ህዳር 28/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=36915
[ { "passage": "በመጪው ጥቅምት በፖላንድ ጊዲኒያ በሚደረገው የ2020ቱ ግማሽ ማራቶን ውድድር የሚሳተፉ አትሌቶች ለመለዬት ዛሬ የማጣሪያ ሩጫ በሰንዳፋ ተካሂዷል።በማጣሪያው ላይ አስር ወንድና አስር ሴት አትሌቶች መሳተፋቸውን የኢትዮጵያ አትሌቲከስ ፌዴሬሽን በማኅበራዊ ገጹ አስታውቋል፡፡በዚህ ውድድር የተካፈሉ አትሌቶች አምና በሀገር ውስጥ ከተደረገ ግማሽ ማራቶንና በኢንተርናሽናል ደረጃ ባላቸው ውጤት የተመረጡ መሆኑንም ፌዴሬሽኑ አስታውቋል፡፡መነሻውን ከበኬ ከተማ ወጣ ብሎ ፍፃሜውን ሰንዳፋ ከተማ ባደረገው የ15 ኪሜ የማጣሪያ ውድድር በሴቶች➊ኛ የለም ዘርፍ የኋላ 50:14.87❷ኛ ነፃነት ጉደታ 50:17.45❸ኛ ዘይነባ ይመር 50:29.80❹ኛ አባ በል የሻነህ 50:38.10❺ኛ መሰረት ጎላ 50:59.13❻ኛ መድህን ገ/ስላሴ 51:14.10በወንዶች➊ኛ ሀይለማርያም ኪሮስ 42:58.55❷ኛ አንዱዓምላክ በልሁ 43:02.36", "passage_id": "253e131424e02e688a0dd22ba0f4b624" }, { "passage": "በትናንት እለት በቻይና በተደረገው የዢያሜን ዓለም አቀፍ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች ማሸነፋቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡\n\nበሴቶች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከአንድ እስከ ሶስት ያለውን ደረጃ በመያዝ ነው ያሸነፉት።\n\nአትሌት መዲና ደሜ 2 ሰአት ከ26 ደቂቃ ከ12 ሴኮንድ አሸናፊ ስትሆን በባለፈው ዓመት ውድድር በርቀቱ ያስመዘገበችውን የግል ምርጥ ሰአት በ1 ደቂቃ ከ13 ሴኮንድ አሻሽላለች።\n\nአትሌት መዲና የዢያሜን ዓለም አቀፍ ማራቶንን ለሁለተኛ ቀን ተከታታይ ዓመት ማሸነፍ የቻለች ሲሆን ውድድሩን ለሁለት ጊዜ ያሸነፈች አራተኛዋ አትሌት ሆናለች።\n\nአትሌት ፋቱማ ሳዶ፣አትሌት ማሬ ዲባባና ቻይናዊቷ አትሌት ዙ ቹንዢዩ የዢያሜን ዓለም አቀፍ ማራቶንን ሁለት ጊዜ ማሸነፍ የቻሉ አትሌቶች ናቸው።\n\nአትሌት መሰራ ሁሴን 2 ሰአት ከ26 ደቂቃ ከ28 ሴኮንድ ሁለተኛ፤ አትሌት አፈራ ጎድፋይ 2 ሰአት ከ26 ደቂቃ ከ42 ሴኮንድ ሶስተኛ ወጥታለች።\n\nየትናንትናው ውጤት በሴቶች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በዢያሜን ዓለም አቀፍ ማራቶን ለ11ኛ ተከታታይ ዓመት ያሸነፉበት ነው።\n\nበወንዶች ባለፈው ዓመት በዢያሜን ዓለም አቀፍ ማራቶን ሶስተኛ ደረጃ ወጥቶ የነበረው አትሌት ብርሃን ነበበው 2 ሰአት ከ8 ደቂቃ ከ16 ሴኮንድ የዘንድሮው ውድድር አሸናፊ ሆኗል።\n\nኬንያዊው አትሌት ሩበን ኬሪዮ 2 ሰአት ከ8 ደቂቃ ከ46 ሴኮንድ ሁለተኛ የወጣ ሲሆን አትሌት ግርማይ ብርሃኑ 2 ሰአት ከ8 ደቂቃ ከ52 ሴኮንድ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል።\n\nበውጤቱ መሰረት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች ለአራተኛ ተከታታይ ዓመት በዢያሜን ዓለም አቀፍ ማራቶን በማሸነፍ የበላይነት መያዛቸውን የዓለም አትሌቲክስ ዘገባ ያመለክታል።\n\nለ18ኛ ጊዜ የተካሄደው የዢያሜን ዓለም አቀፍ ማራቶን በዓለም አትሌቲክስ የወርቅ ደረጃ የተሰጠው ውድድር ነው።\n\nበሌላ በኩል ዛሬ በጣልያን በሚካሄደው የካምቺዮ አገር አቋራጭ ውድድር በ10 ኪሎ ሜትር ወንዶች አትሌት ለሜቻ ግርማ የማሸነፍ የቅድሚያ ግምት አግኝቷል።\n\nአትሌት ለሜቻ በመስከረም ወር 2012 ዓ.ም በኳታር በተካሄደው 17ኛው ዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ሻምፒዮና በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል በኬንያዊው አትሌት ኮንሰስሉስ ኪፕሩቶ በ0 ነጥብ 01 ማይክሮ ሴኮንድ ተቀድሞ የወርቅ ሜዳሊያውን ማጣቱ የሚታወስ ነው።\n\nአትሌት ታደሰ ወርቁ በውድድሩ ላይ የሚሳተፍ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ነው።\n\nየኬንያ፣ጣልያንና ስዊድን አትሌቶች የኢትዮጵያውያን አትሌቶች ዋንኛ ተፎካካሪ እንደሚሆኑ ይጠበቃል።\n\nበሴቶች የ6 ኪሎ ሜትር ውድድር አትሌት አለሚቱ ታሪኩና አትሌት ፎተን ተስፋይ ይሳተፋሉ።\n", "passage_id": "563c5b12bae9c2596ce6ca39b2c1dc5b" }, { "passage": "አትሌት ኦሊቃ አዱኛ ውድድሩን በአንደኝነት አጠናቋል።\n\nበወንዶች አትሌት ኦሊቃ አዱኛ ቢቂላ ሲያሸንፍ በሴቶች ደግሞ ወርቅነሽ ደገፋ የመጀመሪያ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። \n\nአትሌት ኦሊቃ ውድድሩን በአንደኝነት ለማጠናቀቅ 02፡06፡15 የፈጀበት ሲሆን፤ ሌሎች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከሦስተኛ እስከ 10 ያለውን ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል። \n\nሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው ኬኒያዊው ኤሪክ ኪፕታኑ ነው። \n\nበሴቶች በተካሄደው ውድድር አትሌት ወርቅነሽ ደገፋ 02፡19፡37 በመግባት በአንደኝነት ስትጨርስ፤ ሌሎች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከሁለተኛ እስከ ዘጠነኛ ያለውን ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል። \n\nአትሌት ጉተኒ ሾኔ ሁለተኛ ስትሆን አትሌት በዳቱ ሂርጳ ደግሞ ሦስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። \n\nአትሌት ወርቅነሽ ደገፋ የ2017ቱን የዱባይ ማራቶንን ማሸነፏ ይታወሳል።\n\nአትሌት ወርቅነሽ ትናንት ከውድድሩ በፊት ለቢቢሲ ለዚህ ውድድር ከፍተኛ ዝግጅት ማድረጓን ተናግራለች። አትሌት ወርቅነሽ \"የዱባይ አቀማመጥ ለኔ በጣም ምቹ ነው አሸንፋሁ\" ብላ ነበር።\n\nአትሌት ወርቅነሽ ደገፋ የ2017ቱን የዱባይ ማራቶን ማሸነፏ ይታወሳል።\n\nሁለተኛ ደረጃን የያዘችው አትሌት ጉተኒ ሾሜ 02፡20፡11 የገባች ሲሆን አትሌት በዳቱ ደግሞ 02፡21፡54 በሆነ ሰዓት አጠናቃለች።\n\nየዱባይ ማራቶን መዘጋጀት ከጀመረ ወዲህ ኢትዮጵያውያን ሴት አትሌቶች 15 ጊዜ በወንዶች ደግሞ 14 ጊዜ አሸንፈዋል። \n\n ", "passage_id": "45b2b8dc94f9da5cd609169b87471321" }, { "passage": "በመካከለኛና\nረጅም ርቀት የሩጫ ውድድሮች የምትታወቀው አትሌት መሰረት ደፋር በሳምንቱ መጨረሻ በጃፓን ናጎያ በተካሄደው የሴቶች ማራቶን ውድድር አራተኛ ወጣች። በውድድሩ የኢትዮጵያና የኬንያ አትሌቶች ከፍተኛ የማሸነፍ ቅድሚያ ግምት ቢሰጣቸውም ናሚቢያዊቷ አትሌት ሂሊያ ጆሃንስ ሳትጠበቅ ቀዳሚ መሆን ችላለች። 2 ሰዓት ከ22 ደቂቃ ከ25 ሰከንድ የገባችበት ሰዓት ሆኖ ተመዝገቧል። ኬንያውያኑ አትሌት ቪሲሊን ጆፕኪሾ ከ22 ደቂቃ ከ58 ሰከንድ በማስመዝገብ ሁለተኛ ስትሆን፣ ሌላኛዋ የአገሯ ልጅ ቫለሪ ጄምሊ 2 ሰዓት ከ23 ደቂቃ ከ01 ሰከንድ በመግባት ሦስተኛ ደረጃን መያዝ ችላለች። ኢትዮጵያዊቷ መሰረት ደፋር 2 ሰዓት ከ23 ደቂቃ ከ33 ሰከንድ በመግባት አራተኛ ሆና ውድድሩን አጠናቃለች። አትሌቷ በሁለተኛ የማራቶን ወድድሯ የገባችበት ሰዓትም በቀጣይ ውድድሮች ውጤታማ መሆን እንደሚያስቻላት አመላክቷል። የ35 ዓመቷ አትሌት መሰረት ባሳለፍነው ዓመት ለ12ኛ ጊዜ በተካሄደው የጃፓን ቶኪዮ ማራቶን ለመጀመሪያ ጊዜ ለመሳተፍ ወስና የነበረ ቢሆንም፤ ይህ ሳይሆን ቀርቶ በአምስተርዳም ማራቶን 2 ሰዓት ከ27 ደቂቃ ከ25 ሰከንድ በሆነ ሰዓት ስምንተኛ መውጣቷ ይታወሳል። ከዓመት በፊት በአሜሪካ ሳንዲያጎ ግዛት በተካሄደ የግማሽ ማራቶን ውድድር 1 ሰዓት ከ8 ደቂቃ ከ27 ሰከንድ በሆነ ሰዓት ማሸነፏም ይታወሳል። አትሌት መሰረት ደፋር በ1999 ዓ.ም በፖላንድ የ3 ሺ ሜትር ዓለም አቀፍ ውድድር አድርጋ ሁለተኛ ከወጣችበት ጊዜ ጀምሮ በ1 ሺ 500፣ በ5 ሺ እና በ10 ሺ ሜትር ውድድሮች ኢትዮጵያን በመወከል የተለያዩ ስኬቶችን ተጎናጽፋለች። በ5ሺ ሜትር ሁለት ጊዜ የኦሎምፒክ የዓለም ሻምፒዮና መሆን ችላለች። በ3,000 ሜ በዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና አራት ጊዜ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት ሆናለች። መረጃው የዓለም አቀፍ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ማህበር ነው፡፡አዲስ\nዘመን መጋቢት 3/2011", "passage_id": "057c9aecd912b5321562a679f45f7550" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ መስከረም 29፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በስፔን ቫሌንሺያ የሴቶችን የ5 ሺህ ሜትር ክብረወሰን የሰበረችው አትሌት ለተሰንበት ግደይ አቀባበል ተደረገላት፡፡ለተሰንበት ከዋና አሰልጣኟ ኃይሌ እያሱ ጋር ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ስትደርስ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ደራርቱ ቱሉ፣ አትሌት ማርቆስ ገነቴ የኢትዮጵያ አትሌቶች ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ ቢልልኝ መቆያ የፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት ኃላፊ በስፍራው ተገኝተው አቀባባል አድርገውላታል፡፡የ22 ዓመቷ ለተሰንበት ከትናንት በስቲያ ሌሊት የተካሄደውን ሩጫ ውድድር 14 ደቂቃ ከ6 ሰከንድ ከ62 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ጊዜ በመግባት ማሸነፏ ይታወሳል፡፡ይህን ተከትሎም በሌላኛው ኢትዮጵያዊት አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ ተይዞ የነበረውን የሴቶች የ5 ሺህ ሜትር ክብረ ወሰን አሻሽላለች፡፡ከዚህ ቀደም ከ12 ዓመታት በፊት በ14 ደቂቃ ከ11 ሰከንድ ከ15 ማይክሮሰከንድ በሆነ ጊዜ ጥሩነሽ ዲባባ የርቀቱ ክብረ ወሰን ባለቤት እንደነበረች የሚታወስ ነው፡፡ለተሰንበት በወቅቱ ማሸነፏን ተከትሎ በሰጠችው አስተያየት የረጅም ጊዜ ህልሟ እንደነበር ጠቅሳ በማሸነፏ መደሰቷን ገልጻለች፡፡ፌዴሬሽኑ የለተሰንበት ድል ለአመራሮቹና ሠራተኞቹ ተጨማሪ መነሳሳትን እንደፈጠረ ገልጿል፡፡", "passage_id": "99676df6b1c3f9a9578403883913a7e1" } ]
4e288290a19ea18a81a6bcca3d227c76
e637ae7ddadabed4d44b390722c63ad5
ከተፋቀርን አባይ ይገደባል ፤ እኛም እንጠግባለን
ተሰልፈን ቆመናል አምባሳደር አካባቢ ታክሲ ተራ።ታክሲዎች ተሳፋሪውን ተራ በተራ እየጫኑ ወደ መድረሻቸው ይጓዛሉ።ተሳፋሪው ሌላ ታክሲ እስኪመጣ ይጠብቃል።አንድ ከፍ የለ ድምፅ በሰልፍ የቆመውን ተሳፋሪ ትኩረት ስቧል።ሁሉም ወደ ተሰማው ድምፅ አማተረ።አንድ ወጣት አንዲት ህፃን ልጅ አቅፎ ተሳፋሪውን ቀረበና በእጁ የያዘውን በፕላስቲክ ማሸጊያ የተለበጠ ወረቀት ላይ የተፃፈ ጽሁፍ ድምፁን ከፍ አድርጎ ያነባል፡፡የተለያዩ ጎዳናዎች ላይ በተደጋጋሚ የሚሰማ ምልዕክት አይነት የመሰለው አይንና ጆሮው መለሰ። ልጁ ቀጥሏል፤ ወረቀቶችን ይዞ ድመፁን ከፍ አድርጎ ያነባል። “ከተፋቀርን አባይ ይገደባል እኛም እንጠግባለን። እባካችሁ ተዋደዱ፤ እርስ በርስ ተፋቀሩ ያኔ ኢትዮጵያ ከፍ ትላለች፡፡” ሰውየው ከፍ ባለ ድምፅ ይናገራል። ይሄን እዚያ ለመሳፈር የቆመው ሁሉ ጆሮ ሰጥቶ ይሰማው ጀምር፡፡ከሰውየው አንደበት የሚፈልቁ ቃላት የተመጠኑና ሁሉም ሰው ሊያዳምጣቸው የሚገቡ በመሆናቸው እንዲቀጥሉ ተመኘሁ።ታክሲ ለመያዝ ተጣድፌ የነበርኩትን ያህል፤ ታክሲ እንዲዘገይ ተመኘሁ።ሰውየው በፈገግታ ተሞልቶ ስለ ፍቅር ታላቅነት ይሰብካል።“እባካችሁ ተዋደዱ ያኔ ለውጥ ይመጣል ተከባበሩ ያኔ ድል ይመጣል….” ስለ ፍቅርና መዋደድ ስለ አብሮነትና ፍቅር በማይጠገብ አንደበቱ ያስረዳል። እናንተዬ ፍቅርን የሚሰብክ አንደበት፣ እድገት የሚያፀና ምክር፣ ህብረትን የሚሰብክ ንግግር ምንኛ ይጥማል።ታክሲ መጣና ተሳፈርኩ። ስራ ረፍዶብኝ ነበረና ቦታውን ሳልወድ ለቀኩ።ሰውየው ግን ከአይምሮዬ አልጠፋም ደጋግሞ ይታሰበኛል።ይህ ሰው ስለዚህ ጉዳይ እንዲናገር ምን አነሳስቶት ይሆን? የጎደለን ፍቅር መሆኑ ከኛ ከፍ ባለ ሁኔታ ገብቶት መንገርስ ላይ ያደረሰው ምን ይሆን? ብዙ አሰብኩ፤ እዚያው ቦታ ሆኜ የጎደለን ፍቅርና መተሳሰብ እንጂ እውነትም አባይ አይደለም ችግርና መከራችንም መገደብ እንችላለን የምር!!።ስለ ፍቅር ብለን እርስ በርስ ብንተጋገዝ ስለ ሀገር ፍቅር ብለን ለሀገራችን በጎ ካበረከትን ምን ሊጎለን ይችላል?ምንም! ለራሴ መልስ ሰጠሁ፡፡ታክሲ ውስጥ ረዳቱ ሒሳብ ሲለኝ ከሄድኩበት ሰመመን ተመለስኩ።አውጥቼ ሁለት ብር ሰጠሁት።“አምስት ብር ነው፡፡” እ…ከሁለት ወደ አምስት ብር ያደገው ከመቼ ጀምሮ ነው? አትነጫነጭ ሁሉም ከፍሏል። “በአቋራጭ ነው የምሄደው ጨምር።” ሹፌሩ በመሀል ረዳቱን ለማገዝ ቃላት መወርወር ጀመረ። “አንተ ሰው ስራ አይደል እንዴ ምን እያልክ ነው ለምን ገባህ እየተናገርን አይደል የጫንክ” ተሳፋሪውን ዞር ብዬ አየሁ ፊቱን ሁሉም ቅጭም ሲያደርግብኝ መኪናው ሙሉ በኔ ያኩረፈ መሰለኝ፤ አውጥቼ ሰጠሁ።እስክሰጠው ድረስ በስድብ እያጥረገረገኝ ነበር። ኦህ! አምላኬ ትግስቱን ስጠኝ ትርፍ ከፍዬም ተሰድቤም ከባድ ነው።ሰልፉ ቦታ ወደነበረው ሰው በሀሳብ ተመለስኩ።“ እርስ በርስ እንከባበር እንዋደድ፣ ፍቅር አተን ነው የተቸገርነው እባካችሁ እንፋቀር፡፡” ንዴቴ ረገበ።ስለፍቅር ብዬ ዝም አልኩ።እኛ ግን ምን ነካን።ፍቅራችን የት ገባ።ረዳቱና ሹፌሩ ግን ያንን ሰው ሰምተውት ይሆን ሲጭኑ እዚያ ቦታ ነበሩና ሳይሰሙት አይቀሩም።ችግሩ አያደምጡትም…። ወዳጄ ስላለን ብቻ የፈለግነው አንበላም እኮ አረ እንዋደድ ተዉ…። አብዝቶ መስገብገብ ምንድነው እንዴ? ሆድ ልክ አልባ ይመስል ሰውን መበደል፣ ሰውን መግፋት የሰውን መሰብሰብ አስጭኖና ቋጥሮ መቃብር ይዞ ላይሄዱት ነገር ኧረ ነውር ነው…!!።ሰው ከተዋደደ በደህነቱ ንፁህ ህሊናውን ይዞ ሊሰፈር የማይችል ደስታን ይጎናፀፋል።ህሊና ቢስ ከሆነ ግን ሰው ከሚለው ስብዕና የራቀ ክፉ አውሬ ከመሆን አይድንም። በክፉ ስራው ሰዎችን ክፉኛ ያቆስላል፣ ከሚታሰበው በላይ ክፋትን ይለምድና ለሰዎች ሴራን ይጎነጉናል ስለሌላው አይጨንቀውም ስለማንም አይገደውም።ይህ ሰው እያደረ ‹‹ሰው ጤፉ›› ነው።ሰውየው ግን አይቶናል ፍቅር በማጣታችን መቸገራችን ከኛ በላይ ገብቶት ጎዳና ላይ መስበክ ተያይዞታል… እንደው በዚህ በጎ ተግባሩ እስከ መቼ ይቀጥል ይሆን? ታድሎ።ውስጡ የሚሰማው ሰላምስ ምን ያህል ይሆን? እኔ ምለው ሰላም ግን ይሰፈራል። ምን ያህል ነው ክብደቱ? ኦህ! ይከብዳል አቻ የሌለው ነገር በምን ሊሰፈር ይችላል።ሰውየው ውስጡ ያ ሰላም ሳስበው ቀናው። ወዳጄ ደስታህ ከእጅህ እንዳይወጣ ባንተ ሰው እንዲደሰት ትፈልጋለህን? ውስጥህ ሰላም ከሆነ ባትበላ ረሀቡ አይቀፈድድህም፣ ባትለብስ የሰው ፍቅር ትሞቃለህ፣ በሰው ክብር ምቾት ይሰማሀል።የትም ጋደም ብትል ለሽ… ብለህ የሚያስቀና እንቅልፍ ትተኛለህ።ሰዎች ብዙ ጊዜ ስግብግብ የሚሆኑት ፈፅሞ ቢያገኙም በማይጠቀሙበት አግኝተውም በማይደሰቱበት መሻታቸው ላይ ነው። ይሰበስባል፣ ላይ በላይ ደራርቦ ከምሮም ከልክ በላይ ያደልባል እድሜውን ሙሉ ያለ እረፍት የሱ ያልሆነን የማይገባውን የሌሎችን እየነጠቀ ባለው ላይ እየጨመረ ቀዶ እንኳን የማይጨርሰው ሀብት ያከማችና ሰላሙን ያጣል።ሰውየው ግን ከየት ተልኮልን ይሆን “ተፋቀሩ ተዋደዱ” ያለው ፍቅር ከኛ መንጠፉ ምን ያህል ቢገባው ነው።ፍቅር አተን እንጂ ምን ይጎለን ነበር።በተጓዘበት በደረሰበት ሁሉ የሚሰብከው መልካም ነገር ስንቶቻችን ይሆን ጆሮ ሰጥነት የምንሰማው ምን ያህሎቻችንስ ነን ከልብ የምናዳምጠው።ዛሬ ላይ የምነሰማው መልካም ነገር ጎሎ ሳንፈልግ የሚቀርበን መጥፎ ዜና በተበራከተበት ለሁሉ ጉዳት መፍትሄ የሚሆነው ፍቅር ማጣታችን ዋንኛው ምክንያ ነው።ፍቅር ውስጥ የማይፈታ ችግር የማይታለፍ ፈተና የለም።መከባበር ውስጥ የማያስችል ጉዳይ የማያግባባ ሀሳብ አይኖርም ግን በተቃራኒው ከኛ ፍቀር ከራቀ ጥላቻ ቦታውን ይወርስና የማያርቅብን ጉዳይ አይኖርም፡፡አዲስ ዘመን የካቲት 30/2012ተገኝ ብሩ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=28753
[ { "passage": "የዓባይ ውሃ አጠቃቀምን በተመለከተ አጀንዳ ሲፈጠር ከግብጻውያን ዘንድ ደጋግመን የምንሰማው ዓይናችሁን ጨፍኑ ላሞኛችሁ ዓይነት ዜማ አለ። ኢትዮጵያ ብዙ ወንዞች ስላሏት ዓይኗን ከዓባይ ታንሳ የሚል። ይህንን ዘመን ያለፈበትን የውሸት ህሳቤ ከተጨባጩ የኢትዮጵያ ሁኔታ ጋር ስናስተያየው ግን እውነታው እንደ ሰማይና ምድር ተቃራኒ ሆኖ እናገኘዋለን። ኢትዮጵያ ካሏት ተፋሰሶች ውስጥ ከሚመነጨው ውሃ 92 በመቶው ወደውጭ የሚፈስ ነው። ስለዚህም ኢትዮጵያ ብዙ ወንዝ እንጂ ብዙ ውሃ የሌላት አገር ናት ማለት ነው። በአካባቢ እንክብካቤ ሥራዎች ዙሪያ በነበሩ ጉድለቶችና ከደኖች መመናመን ጋር ተያይዞም ታገኘው የነበረው የዝናብ ውሃ መጠንም በየጊዜው እየቀነሰ እንደመጣ ጸሐይ የሞቀው ሀቅ ነው። \nኃይል ከማመንጨት አኳያ ስንመለከት፤ ግብፅ የተለያዩ የኃይል ማመንጫ ዘዴዎች በመጠቀም 45‚000 ሜጋ ዋት ኃይል እያመነጨች ለሕዝቧ 100% ኤሌክትሪክ ተደራሽ አድርጋለች። ከ 45‚000 ሜጋ ዋት ውስጥ 2‚100 ሜጋ ዋቱ ምንጩን ዓባይ ካደረገው የአስዋን ግድብ የሚገኝ ነው። የኢትዮጵያን ያየን እንደሆነ ከተለያዩ የኃይል ማመንጫ ዘዴዎች በመጠቀም 4‚400 ሜጋ ዋት ብቻ እያመረተች ሲሆን ከዚህም የአንበሳውን ድርሻ የሚወስደው ከውሃ ኃይል የሚመረተው ነው። በዚህም ስሌት የኤሌክትሪክ ተደራሽ የሆነው ሕዝብ ከ 44% አይበልጥም። እዚህ ላይ መታወቅ ያለበት ግብፅ የአባይ ውሃን 85 በመቶ ከምታመነጨዋ ኢትዮጵያ በኃይል ማመንጨት በ10 እጥፍ ልቃ መገኘቷ ነው። በተለይ ከ 80% የሚበልጠው የገጠር ሕዝብ የኢነርጂ ምንጩ ማገዶ በመሆኑ በጭስና በኩራዝ ህይወቱን እየገፋ ይገኛል። \nግብፅ በመስኖ ልታለማው ከምትችለው 4.42 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ውስጥ 3.6 ሚሊዮን ሄክታሩን (81.4%) በላይ የሚሆነውን አልምታለች። ኢትዮጵያ ከሦስቱ ለናይል ከሚያበረክቱት ተፋሰስ ወንዞች ውስጥ 1.5 ሚሊዮን ሄክታር በመስኖ ልማት ሊለማ የሚችለው መሬት ውስጥ ከ20‚000 ሄክታር በላይ በመስኖ አላለማችም። በአጠቃላይ በሀገር አቀፍ ደረጃ በመስኖ የለማው መሬት ከ 6 – 7 % አይበልጥም።\n ኢትዮጵያ በዝናብ ከሚገኝ ውሃ ጥገኛ ሆና በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ እያመረተች ህዝቦቿን መመገብ ተስኗት በየዓመቱ ዜጎቿን ለመመገብ የለጋሾችን እጅ እንደምትጠብቅ ዓለም የሚያውቀው እውነታ ነው። \nከላይ የተገለጹትን እውነታዎች ላየ በዓባይ ወንዝ ዙሪያ የሰፈነው ኢፍትሃዊነትና በዚህም የተነሳ ኢትዮጵያ እየተጎዳች ያለችው ጉዳት እጅግ ያንገበግበዋል። ይህንኑ ጉዳይ አስመልክቶ ከሰሞኑ ለአዲስ ዘመን መረጃ የሰጡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና የዓባይ ውሃ ጉዳይ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ “እንደናይል የታችኞቹ ተፋሰስ ሀገራት በበላይነት ተቆጣጥረው የሚጠቀሙበት ወንዝ በዓለም የለም” ሲሉ ገልጸዋል። \nክብርና ምስጋና ለኢትዮጵያ ህዝብ ይድረሰውና ይህ ሁኔታ ግን መጋቢት 24/2003 ዓ/ም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ተቀልብሶ ዓባይን እየረገሙና እያወገዙ መኖሩ አብቅቷል። በዓባይ ዙሪያ የዘመናት ቁጭት የነበረባቸው ኢትዮጵያውያን ከህጻን እስከአዋቂ ያለምንም ልዩነት ግድባቸውን በመደገፍ ከጅማሬ ወደፍሬ አቃርበውታልና። መላ ኢትዮጵያውያን ከትርፋቸው ሳይሆን ከጉድለታቸው በመቆጠብ በቦንድ ግዥ፣ በ8100 ኤ የገቢ ማስገኛና በአካባቢ ጥበቃ ዙሪያ በታሪክ ውስጥ ተመዝግቦ የሚኖር ደማቅ ገድል ፈጽመዋል። \nየኢትዮጵያን የኃይል አቅርቦት 115 በመቶ የማሳደግ አቅም ያለው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለ24 ሰዓታት ያለምንም መቋረጥ ተገንብቶ አሁን ላይ ውሃ ወደሚይዝበት ምዕራፍ ተቃርቧል። ይህ ሁነት የግድቡን የመሰረት ድንጋይ ከማስቀመጥና ለግድቡ ሥራ ሲባል የዓባይን ወንዝ አቅጣጫ የማስቀየር ሥራዎች ከተሰሩባቸው ሁነቶች በመቀጠል ሶስተኛውና ወሳኙ ምዕራፍ ነው። \nኢትዮጵያ ማንንም ሳትጎዳና የራሷንም ጥቅም አሳልፋ ሳትሰጥ የግድቡን ሂደት ለዚህ ደረጃ ማብቃቷ ትልቅ ደስታን የሚፈጥር ነው። ግድቡ እውን ሆኖ ከጅማሬ ወደፍሬ እንዲቃረብ መላ ኢትዮጵያውያን ያበረከቱት አስተዋጽኦም ታላቅ ነውና እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እንወዳለን!\nአዲስ ዘመን ሰኔ 9/2012", "passage_id": "6fde11c73e281fb97003960b7e921fdf" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፦ እኔ\nያየሁትን\nየአዲስ\nአበባን\nአውድ\nላስቃኛችሁ\nእንጂ\nበድፍን\nኢትዮጵያ\n፤\nብሎም\nበድፍን\nዓለም\nባሉ\nኢትዮጵያውያን\nዘንድ\nተመሳሳይ\nስሜት  ስለመኖሩ\nአልጠራጠርም። ጉዳዩ የታላቁ\nህዳሴ ግድባችን ጉዳይ\nነውና። አሁድ ሃምሌ 26 /2012 ዓ.ም ለወትሮው በክረምቱ ጭጋግና ዝናብ ጨለምለም የምትለው አዲስ አበባ ትናንት ያለወትሮ ባህሪዋ ፈክታለች። የአዲስ አበባ ጎዳናዎች በሰንደቅ ዓላማ ተሞሽረው መብራት በሚያበሩና የጡርንባ ድምጽ በሚያሰሙ ተሸካርካሪዎች ተጨናንቀዋል። እግረኞች ግራና ቀኝ ሆነው ፤ ሌሎችም በየበራፋቸው ላይ ቆመው የሀገርን ፍቅርና አንድነት በሚገልጹ ዘፈኖች ደስታቸውን ይገልጻሉ። አንዳንዶች ይጨፍራሉ። አንዳንዶችም ያለቅሳሉ። ብዙዎች ስሜታቸውን መቆጣጠር የቻሉ አይመስልም። ብቻ የተደበላለቁ ሰዎች ፤ የተደበላለቁ ስሜቶች ይታያሉ። እኚህ ሰዎች የጋራ ጉዳያቸው አንድ ነው። የህዳሴው ግድብ የመጀመሪያ ዙር የውሃ ሙሌት ይፋዊ የብስራት ቀን ፤ እና የመጨረሻን ምዕራፍ የማጠናቀቅ የቃል ኪዳን ቀን ። ይህ የዘመናት ቁጭት መልስ ያገኘበት የመጀመሪያው ምዕራፍ ብዙዎችን በደስታ አስክሯል፤ አስፈንጥዟል ፤ ቀልብ ነስቷል። መኪኖቻቸውን በባንዲራ አሸብርቀው የተለያዩ ዜማዎችን አያዜሙ ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ያላቸውን አጋርነት የሚገልጹ የከተማዋ ነዋሪዎች ስሜት በቋንቋ ለመተረክ የሚመች አይደለም። ዕልልታው ፣ፌሻታው በያንዳንዱ ሰው ላይ የሚታየው ፈገግታ ፤ ፈገግታ ውስጥ ያለው ተስፋ ውብ ነው። የግንባታው አሁን ያለበት ደረጃና እውነታ ለከተማዋ ነዋሪ ከደስታ በላይ ሆኖ አምሽቷል። አብዛኛው የከተማዋ ነዋሪ ስሜቱን ለመግለጽ ቋንቋ ያገኘ አይመስልም ። ስሜቱ ተደበላልቆበታል ፤ በአንዳንዶች አይን ስር የሚታይ የእምባ እንክብል እና ሲቃ የያዘው ድምጽ ብዙ ይናገራል። በርግጥም የታላቁ የህዳሴ ግድብ ጉዳይ በያንዳንዱ ዜጋ ስጋና ደም ውስጥ ስለመግባቱ ትይንቱን በማስተዋል ለሚመለከት ተጨማሪ ትርክት አያስፈልገውም ። ለኢትዮጵያውያን የአባይ ጉዳይ ሌላው ዓለም ከሚረዳው በላይ ስለመሆኑ ተጨባጭ ማሳያ ነው።ግድቡን ከኑሮው ላይ ቆጥቦ የገነባው ከመሆኑ በላይ የዘመናት የአይቻልምን ተግዳሮት ሰብሮ ይቻላል በሚል መንፈስና ቁርጠኝነት እየገነባው መሆኑ ፣ ከዛም በላይ ከብዙ አሉባልታ ቦኋላ እዚህ ደረጃ ላይ መድረሱ ታላቅ እልልታው ነው። አደባባይ ወጥቶ እልል ፤ ቋንቋ አውጥቶ ኡኡ ቢል ለተመልካች እና ለሰሚ ግር የሚል አይደለም። አቶ ተመስገን ዝናቡ በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስድስት ነዋሪ ናቸው። ዕድሜያቸው ከ60 እስከ 70 ዓመት ይሆናል። ሙሉ ልብስና ከረባት አስረዋል። በላዩ ላይ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ተጎናጽፈው ከፒያሳ ወደ አራት ኪሎ በሚወስደው ጎዳና ላይ በእግራቸው እየተጓዙ ድምጻቸውን ጮክ አድርገው ደስታቸውን ይገልጻሉ። አዲስ ዘመን ስለደስታቸው\nምንጭ ሲጠይቃቸው ሲቃ በተናቀቀውና\nበተቆራረጠ ድምጽ እንዲህ\nአሉ ‹‹መጀመሪያ ይችን\nቀን እንዳይ ያደረገኝ\nእግዚአብሔር ይመስገን ፤\nበእኔ ዘመን አባይ\nመገደቡና የአባቶቻችንን ቁጭት\nበእኛ በልጆቻቸው መልስ\nማግኘቱ እጅግ ደስታ\nፈጥሮብኛል፤ ዛሬ ውስጤ\nየሚንቀለቀለው የድል አድራጊነት\nስሜት ነው። የመጪው ትውልድ ተስፋና የኢትዮጵያ ትንሳኤ ያየሁት ዛሬ ነው። ከምንም በላይ በዚህ በፈተና ወቅት ሀገሬ እንዲህ ዓይነት ድል ማግኘቷ ክብርና ኩራት ነው። ይህ ክስተት በቀሪው የህዳሴው ግድብ ግንባታ ላይ አዲስ ተነሳሽነት የሚፈጥር ነው። ግብጽም ግድቡ ለእኛ ምን ማለት እንደሆነ የምትረዳው ዛሬ ነው። የኢትዮጵያ ልጆች አሁንም ከመንግስት ጎን ቆመን ግድባችንን አንጨርሰዋለን። ብልጽግናችንንም እናረጋግጣለን ሲሉ ነበር ስሜታቸውን የገለጹት አቶ ተመስገን። አሁንም ክንዳችንን አጠናክረን ግድቡን ከመጨረስ የሚከለክለን አንዳችም ነገር ሊኖር አይችልም፤ ከተባበርንና ከተደማመጥንና በሀገራችን ጉዳይ ለማንም ቀዳዳ ካልከፈትን አንሸንፋለን። ቀጣዩንም በድል እናጠናቅቃለን። ለዚህ ደግሞ ኢትዮጵያዊነት ስሜት እና ወኔያችንን አጠናክረን መቀጠል ይጠበቅብናል። ይላል ወታደር ፍቃዱ በስሜትና በተጋጋለ ወኔ ተሞልቶ። ወጣት ሄኖክ ወርቁ መኪናቸውን የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ አልብሰው ደስታቸውን ሲገልጹ ከነበሩ የጨርቆስ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች አንዱ ነው ። ህዳሴው ግድብ ወደ ቀደመው ማንነታችን እና ክብራችን የመለሰን የስራችን ውጤት ነው ይላል። ተባብረን ከሰራን ድህነትን ታሪክ ማድረግ እንደምንችል ያሳየንበትና ተቀናቀኞቻችንን ተስፋ ያስቆረጥንበት ልዩ ክስተት ነው ። ይህ ግድብ የዚህ ትውል አሻራ ያረፈበት እንደመሆኑ አሁንም አንድነትን በማጠናከር ሌሎች ድሎችን ማስመዝገብ ይኖርብናል። አንድነታችን የህዳሴውን ግድብ ከዳር ለማድረስ እንደረዳን ሁሉ አሁንም ያሉብንን ችግሮች በድል መወጣት የምንችለው ትልቁ አቅማችን እንደሆነም ስሜት አውርቶናል። አሁንም እስከ መጨረሻው ለማድረስ በእውቀታችን፣ በጉልበታችን ፣ በገንዘባችን ድጋፍ ማድረግ ይኖርብናል። እኔ ዛሬ ቃል ገብቻለሁ ለዚህም ነው በአደባባ ደስታዬን እየገለጽኩ ያለሁት ብሎናል። የህዳሴውን ግድብ በአንድነት አምረንና ደምቀን እንደጀመር ነው እንዲሁ እንዳማረብንና እንደደመቅን እንጨርሰዋለን ያሉት ደግሞ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ናቸው፤ ቀኑን አስመልክቶ በሸራተን አዲስ በተዘጋጀ መድረክ ላይ ባስተላለፉት መልእክት። ለዚህ የመጀመሪያው ዙር የውሃ ሙሌት እንኳን ደስ ያላችሁ በማለትም ቀሪውን የግድቡን ስራ አጠናቀን ወደ ናፈቅነው ስራ ለመግባት ሁሉም የተለመደው ድጋፉን ማድረግ እንደሚገባውም አመልክተዋል። ገና የቤት ስራችን\nአላለቀም ፤ አብረን\nየምንዘምትባቸው ሌሎችም ጉዳዮች አሉን\n፤ ኮቪድ 19ኝን\nመዋጋት፣ ኢኮኖሚን እንዲያገግም\nበጋራ መስራት ፣\nውስጣዊ ችግሮቻችንንና ሰላማችንን\nማስጠበቅ ሲሉም ለመላው\nህዝብ ለቀጣይ ስራና\nድል እንዲዘጋጅ ጠይቀዋል።\nየታላቁ ህዳሴ ግድብ\nግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ\nአስተባባሪ ብሄራዊ ምክር\nቤት ጽህፈት ቤት\nዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ\nሮማን ገብረስላሴ እንዲሁ\nእለቱን አስመልክተው ባስተላለፉት\nመልእክት ፣ ሁሉንም\nኢትዮጵያ ውያን ሀገር\nውስጥ ያለነውና በውጭ\nየምንኖር ያለምንም ልዩነት\nአንድ ሆነን በሞራል፣\nበጉልበት፣ በእውቀት የዚህ\nድል ባለቤት ሆነናል\nብለዋል። በዲፕሎማሲ በተለይም በተለያዩ ሀገራት ያሉ ምሁራንና የአረብኛ ቋንቋ ተናጋሪ ዜጎች እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን አረቡን ዓለም በመሞገትና በማስረዳት ፤ ባለፉት ዓመታት ከልጅ እስከ አዋቂ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ይህንን ውጤት አግኝተናል ሲሉም ተናግረዋል። አይጀምሩትም ተብለን ጀምረናል፤\nአይችሉትም ተብለን ችለናል፤\nአይቀጥሉም ተብለን ቀጥለናል\n፤ ውሃ አትሞሉም\nተብለንም ሞልተን አሳይተናል\nበዚህም እንደምንችል ለዓለም\nእያሳየን ያለን ህዞቦች\nነን ብለዋል። መላው\nህዝብ ድጋፉን አጠናክሮ\nመቀጠል እንዳለበት ጥሪ\nአስተላልፈዋል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 27/2012 እያሱ መሰለ", "passage_id": "28597447ad734e5e6c7272abb08aa28c" }, { "passage": "የኦለንጪቲ ከተማ ነዋሪዋ ወይዘሮ ማሜ ነጋሽ ለበርካታ ዓመታት በሌሊት ተነስተው ከጅብና ከሌሎች\nየዱር አራዊቶች ጋር በመጋፋት ስድስት ሰዓት የሚሸፍን የእግር መንገድ ተጉዘው ውሃ ሲቀዱ ቆይተዋል፡፡ ምንም እንኳን ውሃውን ለመቅዳት\nሌሊት ጉዟቸውን ቢጀምሩም ረጅም ርቀት መሄዳቸው ስለማይቀር ለቀኑ የጸሐይ ሀሩር መጋለጣቸውም ግዴታ ነበር፡፡ ይህ የሆነው በከተማዋ\nከፍተኛ የመጠጥ ውሃ ችግር በመኖሩ ነው፡፡ ታዲያ እንዲህ ያለውን ድካም ለዘመናት ሲያስተናግዱ ቢቆዩም፤ ንጹህ የመጠጥ ውሃ ይገባልን\nይሆናል የሚል ተስፋ ነበራቸው፡፡ ከሶስት ዓመት በፊት በ2008ዓ.ም በአካባቢያቸው የንጹህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ሲጀመር፤ ተስፋቸው\nለመለመ፡፡ አሁን ላይ ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ሥራ መጀመሩ ውሃን በማንኛውም ጊዜ ከበራፋቸው ላይ ቀድተው ለመጠቀም\nእንዳስቻላቸው የሚገልጹት ወይዘሮ\nማሜ፤ ፕሮጀክቱ የውሃ ጥምን ለማርካት ብቻ ሳይሆን ለከተማዋ እድገት መሰረት በመሆኑም ድርብ ደስታን እንዳጎናጸፋቸው ይናገራሉ፡፡\nእንደ ወይዘሮ ማሜ ሁሉ ከንጹህ የመጠጥ ውሃ እጥረት የተነሣ ረጅም መንገድ በመጓዝ ለጤና ተስማሚ\nያልሆነ ውሃ ለረጅም ጊዜ  ሲጠቀሙ መቆየታቸውን የሚገልጹት ሌላው ነዋሪ\nአቶ በላይ ገዛኸኝ ናቸው፡፡ በአካባቢያቸው በነበረው የውሃ እጦት \nእንስሳት የሚጠጡትን ውሃ ፍለጋ ከረዥም ርቀት ውሃ ለማምጣት ስለሚከብዳቸው እንስሳቱም በውሃ ጥም ይሰቃዩ እንደነበር\nእና ከእንስሳቱም ተገቢውን ጥቅም ማግኘት ባለመቻላቸው በኑሯቸው ላይ የውሃ ችግሩ አሉታዊ ጫና አሳድሮ መሰንበቱን ይናገራሉ፡፡ በአሁኑ\nወቅት በየቤታቸው የቧንቧ ውሃ ተጠቃሚ በመሆናቸው፤ የከብት ማጠጫና የልብስ ማጠቢያ ገንዳ በመስራት ያገኙትን ውሃ ያለምንም ብክነት\nእየተገለገሉበት እንደሆነ ሰዎች ብቻ ሳይሆኑ እንስሳት ሳይቀሩ ውሃ ጥማቸው እየተቆረጠ መሆኑን ነው የሚገልጹት፡፡ የሰው ልጅ ሕይወቱን ለማቆየት ከእስትንፋሱ ጋር የተቆራኙና አማራጭ ከማይገኝላቸው መሰረታዊ ጉዳዮች\nመካከል ውሃ አንዱ ነው ያሉት አቶ በላይ፤ አብስሎ ለመብላት፣ ጠጥቶ ለመርካት እና ታጥቦ ለመጽዳት አገልግሎት የጀመረው የውሃ ፕሮጀክት ፋይዳው ቀላል እንዳልሆነም\nተናግረዋል፡፡ በኦለንጪቲ ዳንጉሬ ጢዮ ቀበሌ  ነዋሪ\nየሆኑት ወይዘሮ የውብዳርተግን ሀይሌ በበኩላቸው፤ ቦታው ሞቃታማ በመሆኑ በአካባቢያቸው የውሃ አማራጭ አለመኖሩን ጠቁመዋል፡፡ ረዥም\nርቀት ተጉዘው ውሃ ለመቅዳት ጊዜና ጉልበታቸውን ሲያፈሱ እንደነበር ያስታውሳሉ፡፡ ረጅም ርቀት በመጓዝ የሚቀዱበት ቦታ ሲደርሱ ረጅም\nሰልፍ ይጠብቃቸው እንደነበር ጠቅሰው፤ በአሁኑ ወቅት በክልሉ መንግስትና፣ ሌሎች ዓለም አቀፍ  ድርጅቶች ተሳትፎ በተገነባው የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግራቸው ተቃሎ  እንስሳት ጭምር ያለ ችግር ውሃ በማግኘታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡የኦሮሚያ ክልል የውሃና ኢነርጂ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰይፈዲን መሃዲ እንደሚሉት፤ ፕሮጀክቱ\nበኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት፣ በተባበሩት መንግስታት የህፃናት ነፍስ አድን ድርጅት ‹‹ዩኒሴፍ›› እና በ‹‹ዲ.ኤፍ.አይ.ዲ››\nበብሪታኒያ መንግስት የዓለም ዓቀፍ ልማት እና እርዳታ ክፍል ድጋፍ በኦለንጪቲ ከተማና አካባቢዋ በ120 ሚሊዮን ብር የተሰራ ነው፡፡  የአካባቢውን ማኅበረሰብ ተጠቃሚ ከማድረጉም ባሻገር ሌሎች አካባቢዎች ላይ\nተመሳሳይ ስራዎችን ለማከናወን እንደተሞክሮ ይወሰዳል፡፡  አጠቃላይ የፕሮጀክቱ ሥራ ለማጠናቀቅ ሶስት\nዓመታትን ፈጅቷል፡፡ አገልግሎቱ ኦለንጪቲ ከተማና አካባቢዋ ላሉት ሶስት የገጠር ቀበሌዎች ተደራሽ ይሆናል፡፡ አካባቢዋ ከዚህ ቀደም\nንጹህ የመጠጥ ውሃ ያላገኘች በመሆኑ የፕሮጀክቱ መጠናቀቅ ችግሩን በማቃለል 48ሺ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡የዩኒሴፍ ተወካይ በኢትዮጵያ ሚስ ጊላን ሚልሶፕ በበኩላቸው፤ የኦለንጪቲ መጠጥ ውሃ አስተዳደር ፕሮጀክት\nእና ሌሎች መሰል ፕሮጀክቶች መኖራቸው በኢትዮጵያ ሴቶችና ልጃገረዶች ውሃ ለመቅዳት ረጅም ርቀት በመጓዝ ያጠፉት የነበረውን ጊዜና\nያባክኑ የነበረውን ጉልበት ይቆጥባል፡፡ በመሆኑም ልጃገረዶቹ ትምህርት ቤት ለመሄድና ለመማር፤ እናቶችም ከልጆቻቸው ጋር ጊዜያቸውን ለማሳለፍና ሌላ ጠቃሚ ተግባር ለመከወን\nያስችላቸዋል ብለዋል፡፡ ለህብረተሰቡም\nንጽህናው የተጠበቀ አካባቢ እንደሚፈጥር አመልክተዋል፡፡በውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ነጋሽ ዋጌሾ\nበበኩላቸው፤ ለምርቃት የበቃው የውሃ ፕሮጀክት ዕድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች የሆኑ 22 ሺህ ሕጻናትን ጨምሮ ለበርካታ የህብረተሰብ\nክፍሎች አገልግሎት ይሰጣል በማለት፤ ፕሮጀክቱ የከተማውን የውሃ ሽፋን 100 በመቶ እንደሚያደርስና በተጨማሪም በኦለንጪቲ ከተማ ዙሪያ የሚገኙ ሦስት የአርሶ\nአደር ቀበሌዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አስታውቀዋል፡፡ የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር በቂና አስተማማኝ የመጠጥ ውሃ አገልግሎት\nለሁሉም ዜጎች ተደራሽ በማድረግ ለኢኮኖሚ እድገቱ ጉልህ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ጤናማና ምርታማ ዜጋ ለመፍጠር ዋነኛው ዓላማ አድርጎ\nእየሰራ  መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ የኦለንጪቲ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት የደረቅ ቆሻሻ ማጣሪያ፣ የፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ\nሥርዓት፣ በትምህርት ቤቶችና በገበያ ቦታ መጸዳጃ እና መታጠቢያ ቤቶች የተካተቱበት ሞዴል ፕሮጀክት ሲሆን፤ ፕሮጀክቱ በታቀደው መሠረት\nበ2008 ዓ.ም መጨረሻ ተጀምሮ በያዝነው ዓመት ተጠናቋል፡፡ አዲስ ዘመን የካቲት22/2011", "passage_id": "33269d0c2f083c607a3d251df30c642b" }, { "passage": "– 21ሚሊዮን ብር ወጥቶበታል፤\n– በ9ሚሊዮን ብር ሁለት ጎታች ጀልባዎች ተሠርተውለታል፤\n– አሁን ሥራ ለማስጀመር ከ5ሚሊዮን ብር በላይ ያስፈልጋል፤በጣና ሐይቅ ጎርጎራ ወደብ ላይ ነን። ወደቡ የጀልባ መስሪያና መጠገኛ ክፍሎች እንዲሁም የሆቴል አገልግሎት ይሰጣል። ከወደቡ ተጠግቶ ግማሽ አካሉን ውሃ ውስጥ ዘፍዝፎ ግማሹ ለፀሐይ ተጋልጦ የባለቤት ያለህ እያለ ለዓመታት የኖረ አንድ ትልቅ የደለል ማውጫ ማሽን ይገኛል።\n«ድሬጂንግ ወይም ድሬጀር ማሽን» ይሉታል ባለሙያዎቹ፤ የጣና ሐይቅን ደለል ለማውጣት ታስቦ ነበር በውጭ ምንዛሬ የተገዛው። ካለምንም ፋይዳ ለዓመታት በእንቦጭ በሚታመሰው ጣና ሐይቅ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።ትልቋ የዕቃና የሰው ማመላለሻ ጀልባ «ጣናነሽ»ን በወደቡ ሲያድሱ ያገኘኋቸው የጀልባዋ ካፒቴን አቶ ስጦታው አላምረው፤ የደለል ማውጫ ማሽኑን «የተረሳ ንብረት ሆኗል» ይላሉ። ከስድስት ዓመት በፊት ሲመጣ ጣሊያኖች ከኢትዮጵያውያን ጋር ገጣጥመው እና ሞክረው ነበር ያስረከቡት። አሁን ግን ባለቤት አልባ ሆኗል። ዘጠኝ ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ጎታች ጀልባ ለማሽኑ ተሠርቶለት ያለሥራ ሐይቁ ላይ ከማሽኑ ጎን አብሮ ታስሮ ተቀምጧል። አብሮ የተገጠመው ጀኔሬተርም ማሽኑ ላይ እንዳለ ካለሥራ በመቀመጡ የመበላሸት እጣፋንታ እንደሚገጥመው መስጋታቸውን ይናገራሉ።ማሽኑ ለዓመታት ውሃ ውስጥ መቀመጡን የሚናገሩት ካፒቴኑ፤ ባለቤት ነኝ የሚል አካል አለመምጣቱ አሳዝኗቸዋል። ከአስር ዓመት በፊት በተደረገ ጥናት ጣና ሐይቅ ከፍተኛ የደለል ስጋት ስላለበት እንደቻድ ሐይቅ ሊጠፋ ይችላል የሚል ስጋት ስለነበረ ነው። ይህንን ታሳቢ ተደርጎ ቢገዛም እስከአሁን አገልግሎት ለመስጠት አልተቻለም። ማሽኑ ወደ ሥራ ቢገባ ኖሮ ደለሉን በመጥረግ ለአካባቢ ጥበቃ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ይሆን ነበር። ያለአገልግሎት ረጅም ጊዜ በመቀመጡ በየጊዜው በሐይቁ በሚነሳው ማዕበል ምክንያት ወደቡን እያፈራረሰው መሆኑ አቶ ስጦታውን አሳስቧቸዋል።ጉዳዩን ይዤ ወደቡን ወደሚያስተዳድረው የጣና ሐይቅ ትራንስፖርት ድርጅት ዋና መስሪያቤት ባህርዳር አቀናሁ። የድርጅቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙላት ፀጋው እንደሚገልጹት፤ ማሽኑ ወደ ወደቡ የመጣው በ2005 ዓ.ም መጨረሻ ነው። ድርጅቱ በባለቤትነት ቢረከበውም ለጣና በለስ የተቀናጀ ውሃ ሀብት ልማት ፕሮጀክት ድጋፍ በሚል በውጭ ፈንድ አማካኝነት የፌዴራል ውሃ፤ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ነው የገዛው። ማሽኑ ለረጅም ጊዜ ያለሥራ የተቀመጠው የመለዋወጫ ጉድለት ስለነበረበት ሲሆን፤በተጨማሪ ለማሽኑ ማንቀሳቀሻ የሚሆኑ ሁለት ጀልባዎች ተሠርተውለታል። ደለል ማውጫው ቱቦ ተገጥሞለት እስከ አምስት መቶ ሜትር ርቀት የሚገኝ አሸዋና አፈር ያወጣል ተብሎ ታሳቢ ተደርጎ ነው። ለማሽኑ የሚያገለግሉ ስድስት ሜትር ርዝመት ያላቸው 200 የብረት ቱቦዎች በተጨማሪ ወጪ ቢገዙም አሁንም በድርጅቱ ግቢ ቦታ ይዘው ያለአገልግሎት ተቀምጠዋል። አንዱ ሁለት ነጥብ ስድስት ኪሎ የሚመዝን ብረት በመሆኑ ውሃ ላይ የመንሳፈፉ ጉዳይም አጠራጣሪ መሆኑን ይናገራሉ።እንደ አቶ ሙላት ገለጻ፤ የጣና ሐይቅ ውሃ በደለል ምክንያት እየቀነሰ ነው። ለአብነት ደልጊ ወደብ በደለል የተጠቃ በመሆኑ ጀልባዎች ወደቡን ለመጠጋት ባለመቻላቸው እስከ ሦስት መቶ ሜትር ድረስ እየራቁ ለመቆም ተገደዋል። በሌላ በኩል ለእምቦጭ አረም ምቹ ነው የሚባለው ደለሉ ከጠፋ የእንቦጭ አረም ይቀንሳል። ምክንያቱም አረሙ ደለል በበዛባቸው አካባቢዎች ላይ ስር ሰዶ ይቆያልና። በውሃ ላይ ሲበቅል ግን ከሳምንት በኋላ ይደርቃል። በመሆኑም መሳሪያው ደለል ማውጣት ብቻ ሳይሆን በተዘዋዋሪ የእንቦጭ አረምን ችግር ሊቀርፍ ስለሚችል የማሽኑ አስፈላጊነት እንደማያጠያይቅ ያስረዳሉ።ማሽኑን ያመጣው የጣልያን ኩባንያ ድጋሚ ስልጠና ሰጥቶ አገልግሎት እንዲጀምር ካልተደረገ ደለል ማውጫው አገልግሎት ሊሰጥ አይችልም። ወደ ሥራ እንዴት ይግባ? የሚለውም ጉዳይ አሳሳቢ ነው። ማሽኑን ወደሥራ ለማስገባት በማሰብ አባይ ተፋሰስ ባለስልጣን ተረክቦ እንዲሠራበት በመወሰኑ በቅርቡ የሰነድ ልውውጥ መደረጉንም ይናገራሉ።የአባይ ተፋሰስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ የወንድወሰን መንግሥቱ በበኩላቸው ማሽኑ የተገዛው በቀድሞው ውሃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር አማካኝነት ከዓለም ባንክ በተገኘ ገንዘብ መሆኑን ያስታውሳሉ። ወጪውም 21 ሚሊዮን ብር አካባቢ ነበር። «ማሽኑ ከውጭ ሲመጣ ተሟልቶ እንዲቀርብ መደረግ የነበረባቸው ያልተሟሉ ክፍሎች ስለነበሩበት የሚፈለገውን አገልግሎት አልሰጠም። ቴክኖሎጂው ለኢትዮጵያውያን አዲስ ስለነበርና መለዋወጫዎች ተሟልተው እንዲገቡ አልተደረገም። ነገርግን ያለሥራ ሐይቁ ውስጥ ያለሥራ በመቀመጡ ወደሥራ ለማስገባት ጥረት እየተደረገ ነበር» ይላሉ።እንደ አቶ የወንድወሰን ማብራሪያ፤ አሁን ላይ ማሽኑ ጥገና አግኝቶ ሥራ እንዲጀምር ማሽኑን ያስገባው ድርጅት ባለሙያዎች እንዲመጡ ጥረት እየተደረገ ይገኛል። ማሽኑን ለማስነሳትና ስልጠና ለመስጠት ባለፈው ዓመት 160 ሺ ዩሮ(ከ6ሚሊዮን ብር በላይ) ክፍያ ተጠይቆ ነበር። አሁን ጊዜው በመሄዱ ክፍያው ሊጨምር ይችላል። ስልጠናው ከተሰጠና የጎደሉ ዕቃዎች ከተሟሉ ማሽኑ ባፋጣኝ ሥራ ይጀምራል። መቼ ይጀምራል? የሚለውን ግን እርሳቸውም በውል አያውቁትም። በደፈናው «ቀኑ ይሄ ነው ማለት ባይቻልም፤ በጀት ከተገኘ እና ስልጠናው ከተሰጠ በኋላ ይጀመራል» ይላሉ።የቀድሞው የጎርጎራ ወደብ ኃላፊ የነበሩትና አሁን የአማራ ብረታብረት ኢንዱስትሪና ማሽን ቴክኖሎጂ ልማት ኢንተርፕራይዝ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ዳንኤል ጌራ፤ ማሽኑ ሲገዛ ስፔሲፊኬሽን ያዘጋጀው ኮሚቴ ውስጥ ሠርተዋል። በዓለም ባንክ ድጋፍ የተገዛው ማሽን በሰዓት አንድ ሺ ሜትር ኪዩብ ውሃ እያጣራ ከደለል ነፃ እንደሚያደርግ ይናገራሉ። መሳሪያው ሲመጣ ግን ደለል ማስወገጃ ቱቦዎቹ ባለመኖራቸው ሥራ ላይ አልዋለም። ቱቦዎቹ በአገር ውስጥ ከተመረቱ በኋላ ደግሞ ብረት በመሆናቸው ውሃ ላይ መንሳፈፍ የሚችሉበት መንገድ ያስፈልግ ነበር። እነዚህ ችግሮች ተደማምረው ማሽኑ እንዲቆም ምክንያት መሆኑን ያስረዳሉ።እርሳቸው በሰጡኝ ሰነድ መሰረት የማሽኑ ግዢ ጨረታ ሰነድ ሲዘጋጅ «Technical Evaluation» በሚል መስፈርት ተዘርዝሯል። በመስፈርቱም ስር ማሽን አቅራቢው ድርጅት ያስረከበው መሳሪያ በሥራ ላይ ከዋለ በኋላ ቢያንስ እስከ ሦስት ሺ የሥራ ሰዓታት ድረስ አስፈላጊው መለዋወጫ ዕቃዎች ቢኖሩ የማቅረብ ግዴታ እንዳለበት ሰፍሯል።አቶ ዳንኤል አስራት በቀድሞ የፌዴራል ውሃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር የጣና በለስ የተቀናጀ ውሃ ሀብት ልማት ፕሮጀክት የቁጥጥር እና ምዘና ባለሙያ እንዲሁም የፕሮጀክት አስተባባሪ ተወካይ ሆነው አገልግለዋል። አሁን በሚኒስቴሩ የብሔራዊ ባዮጋዝ ፕሮግራም የቁጥጥር እና ምዘና ባለሙያ ናቸው። ማሽኑ ሲገዛ በፕሮጀክቱ ስር ነበሩ። ማሽኑ ዋና ሥራው እንደርብ እና ጉመራ ያሉ ትልልቅ ወንዞች ወደሐይቁ በሚገቡበት ቦታ ላይ ያለውን ደለል ለማውጣት መሆኑን ያስታውሳሉ።እንደ አቶ ዳንኤል ማብራሪያ ፤ ማሽኑ ከመጣ በኋላ ያለውን የመለዋወጫ ችግር ለመቅረፍ የገንዘብ ችግር አጋጥሞ ነበር። በዚህ ምክንያት ውሃ ውስጥ ያለሥራ ለዓመታት ተቀምጧል። አሁን ግን የአባይ ተፋሰስ ባለስልጣን ስለተረከበው ችግሮቹን በጋራ በመቅረፍ በቀጣይ ወደ አገልግሎት ይገባል ተብሎ ይጠበቃል። ቀሪው ተግባር የውጭ ምንዛሬ በማፈላለግ ባለሙያዎች አስመጥቶ መሳሪያው እንዲሠራ የሚያስችል ሥራ ማከናወን እንደሚገባ ያስረዳሉ።ማሽኑ በዓለም አቀፍ ደረጃ ካሉት ተመሳሳይ ማሽኖች መካከለኛ የሚባል አቅም ያለው ነው። በመሆኑም በፍጥነት ወደሥራ የማስገባቱ ጉዳይ እንዳለ ሆኖ፤ ይህን ያህል ዓመት ያለሥራ ለመቆየቱ ተጠያቂው ማን ነው? የሚለው ጉዳይ ሊጣራ ይገባል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 7/2011ጌትነት ተስፋማርያም", "passage_id": "7abb0da89e6d630686400f31ccfeab18" }, { "passage": "በኢትዮጵያ የትኛውም አካባቢ የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎች ንጹህ ውሃን የማግኘት ጉዳይ የማያልፉት ፈተና ሆኖ ዘልቋል። በገጠሩ የሀገሪቱ ክፍል ውሃን ብዙ ኪሎ ሜትር ተጉዘው በመቅዳት ለሚፈልጉት ፋይዳ የማዋል ሀላፊነት ከትከሻቸው ለተጫነባቸው ሴቶች ደግሞ ችግሩን የማይገላገሉት ምጥ አድርጎባቸዋል። የሀገሪቱ መለያ አርማ የውሃ ማማ መሆኑ ሳይካድ በሌላኛው ጫፍ ደግሞ ቀላል የማይባለው ማህበረሰባችን ውሃ የተጠማ መሆኑ እስከመቼ? መፍትሄውስ ምን ይሆን? የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ እንዳሉት ፤በኢትዮጵያ 25 ሚሊዮን ሕዝብ አሁንም ንጹህ የውሃ አቅርቦት የለውም። በገጠር የሚኖረው ማህበረሰብ በቀን 25 ሊትር ውሃ በነፍስወከፍ እንዲያገኝ በከተማ የሚኖረው ደግሞ ከ40 እስከ 100 ሊትር ውሃ በቀን ማግኘት እንዲችል እየተሰራ እንደሆነ ገልጸው በዚህ ስሌት መሰረትም የከተማው ነዋሪ 68 በመቶ እና የገጠሩ ደግሞ 78 በመቶ የንጹህ መጠጥ ውሃ ማድረስ መቻሉን ይገልጻሉ።አቶ አስራት ካሳዬ በአማራ ክልል ውሃ መስኖና ኢነርጂ ቢሮ የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ዳይሬክተር ናቸው። እርሳቸው እንደሚሉት፤ የክልሉን ሕዝብ የውሃ አቅርቦት ለማሟላት አነስተኛ የውሃ ተቋማትን መገንባት፣የገጠር ባለ መስመር ውሃ ዝርጋታ እና የከተማ ውሃ አቅርቦት እየተሰራ ነው ይላሉ። በዚህም በ2011 ዓ.ም ከ15 በላይ የከተማ የውሃ ተቋማትና ከ5 ሺህ በላይ አነስተኛ የውሃ ተቋማት ተገንብተው አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኙ የሚናገሩት ዳይሬክተሩ፤ ከአለም ባንክና ከሌሎች አጋር ድርጅቶች ጋር በትብብር በከተማ 24፣በገጠር 31 የውሃ ተቋማት ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ እንደሆነ ይጠቅሳሉ።ዳይሬክተሩ እንደገለጹት ከሆነ በአማራ ክልል በከተማ 75 በመቶ በገጠር ደግሞ 88 በመቶ የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ማድረስ ተችሏል። ከዚህ በፊት በገጠር አካባቢዎች ይሰሩ የነበሩት አነስተኛ የውሃ ተቋማት የእጅ ጉድጓድና ምንጭ ማጎልበት ሲሆኑ አሁን ላይ ግን ባለመስመር የሆኑ እስከ 15 ቀበሌዎችን የሚያገናኙ ትላልቅና ብዙ ሰዎች የሚይዙ በመሆናቸውና በቀን 25 ሊትር በሰው በመሆኑ ሽፋኑን ባልተለመደ ሁኔታ አሳድጎታል። በከተሞች በቀን 20 ሊትር በሰው የነበረው ስሌት አሁን ላይ ዝቅተኛው 40 ከፍተኛው ደግሞ 80 ሊትር አድጓል። በዚህ የተነሳ ሽፋኑ ከገጠሩ ማነሱን በምክንያትነት አስረድተዋል። በክልሉ ከተሰሩ የውሃ ተቋማት ከ20 በመቶ በላይ አገልግሎት መስጠት ማቆማቸው በቆጠራ እንደተረጋገጠ የተናገሩት አቶ አስራት፤ ይሄ ሁኔታ የተደራሽነት ሽፋኑን አሁን ከሚገኝበት ደረጃ ሊያሳንሰው እንደሚችል ግምታቸውን ተናግረዋል። የከርሰምድር ውሃ መቀነስና መድረቅ እንዲሁም የአየር ለውጥ መከሰትን በምክንያትነት አንስተዋል። በክልሉ ውሃ ተደራሽ ያልሆነባቸው ወረዳዎችና ቀበሌዎች ምን ያህል እንደሆኑና የት አካባቢዎች እንደሚገኙ አዲስ ዘመን ላነሳላቸው ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡ እንዳሉት፤‹‹ ውሃ ተደራሽ ያልሆነባቸው ወረዳዎች ባይኖሩም ቀበሌዎች ግን አሉ። ለድርቅ ተጋላጭ የሆኑት እንደ ምስራቅ በለሳ ያሉ ቀበሌዎች ሙሉ በሙሉ ውሃ የላቸውም። እስከ 60 ሜትር ተቆፍሮ ውሃ ማግኘት አልተቻለም። በዋግኽምራ አካባቢዎች ደግሞ እስከ 450 ሜትር ተቆፍሮ ውሃ ያልተገኘባቸው አካባቢዎች አሉ።በሰቆጣ ከተማ የተቆፈረውም ቢሆን ከታሰበው በታች በግማሽ ያነሰ ውሃ ነው በመስጠት ላይ የሚገኘው።ምክንያቱ ደግሞ የከርሰ ምድር ውሃ መጠን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ በመምጣቱ የተፈጠረ ነው። በመፍትሄነት የተወሰዱት ርምጃዎችም ከከርሰ ምድር ውሃ ጥገኝነት በመላቀቅ የገጸ ምድር ውሃን መጠቀም ሲሆን በሰቆጣ አካባቢዎች ያሉ 16 ቀበሌዎች ጥናት ተጠናቅቋል።ስራውን በማፋጠን በሚቀጥለው አመት ውሃ ማግኘት እንዲችሉ እየተሰራ ነው። በምስራቅ በለሳ አካባቢዎች ደግሞ አሙሲትን ጨምሮ 17 ቀበሌዎችን የሚያገናኝ ዲዛይን ተጠናቅቋል በመሆኑም የከርሰ ምድር ውሃ ተጠቃሚ ይሆናሉ›› ሲሉ አቶ አስራት ካሳዬ አብራርተዋል።በቀጣዮቹ አምስት አመታትም የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦቱ በከተማም ሆነ በገጠር ተደራሽ ይሆናል። ለድርቅ ተጋላጭ በሆኑ ቆላማ አካባቢዎች ደግሞ ከማህበረሰቡ ባለፈ ለእንስሳትም ጭምር የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦቱ የሚሟላ ይሆናል። ለዚህ ማስፈጸሚያም የሳውዲ መንግስትን ጨምሮ ከሌሎች ሀገራትና ድርጅቶች ከ600 ሚሊዮን ዶላር(USD) መገኘቱን ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ጥር 29/2012ሙሐመድ ሁሴን", "passage_id": "268877f30f210993de150c64de6273ff" } ]
32b6162afa720ddaa24903b80441e2c7
0634a8d957187a25e09eacba777eaf5e
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን 12ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔን አካሄደ
አዲስ አበባ፦ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን 12ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን ትናንት አካሂዷል፡፡ ያለፈው ዓመት ባጋጠሙ በርካታ ውጣ ውረዶች ስፖርቱ አሉታዊ ተጽእኖ ቢደርስበትም የተሻለ አፈጻጸም የተመዘገበበት መሆኑ ተመላክቷል፡፡ በተለይም በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኘውን የካፍ አካዳሚን በማስጠገን ለአገልግሎት መብቃቱ፤ ፌዴሬሽኑ ለብሔራዊ ቡድን ዝግጅት የሚያወጣውን ከፍተኛ ወጪ ታድጓል። የአህጉርና ዓለም አቀፍ ግንኙነትን በማጠናከር ረገድም ጠንካራ ሥራ በመከናወኑ ኢትዮጵያ በሴካፋ የመሪነት ቦታ ማግኘቷም በጉባኤው ላይ መነሳቱን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን በድረ-ገጹ አስነብቧል፡፡ በጉባኤው በቀረበው የ2012 በጀት ዓመት የአፈጻጸም ሪፖርት ላይም ፌዴሬሽኑ የገንዘብ አቅሙን ማሳደጉ ተገልጧል፡፡ ለዓመታት የክለቦች ጥያቄ የነበረውን የሊግ ካምፓኒ ምስረታ እውን ማድረጉንም እንደ ስኬት ተነስቷል፡፡ በቀረበው ሪፖርት እና የ2013 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይም በጉባኤው አባላት ውይይት ተደርጓል፡፡ በመጨረሻም የሲዳማ ክልል የጉባኤው አባልነት ጥያቄን ተቀብሎ በማፅደቅ እና በአጭር ጊዜ ውስጥ በተሻሻለው መተዳደሪያ ደንብ ላይ ለመወያየት እና ለማጽደቅ በሀዋሳ ከተማ አስቸኳይ ጉባኤ እንደሚካሄድ በመወሰን ጉባኤው መጠናቀቁን በዘገባው ተመላክቷል።አዲስ ዘመን ህዳር 28/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=36914
[ { "passage": "የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳይያስ ጂራ ትላንት በአዳማ በተደረገው የስፖርታዊ ጨዋነት ጉባዔ ላይ በዘር እና ብሔር ስያሜ የተቋቋሙ ክለቦችን አንመዘግብም ሲሉ ተደምጠዋል፡፡የክለብ ፕሬዝዳንቶች፣ የስፖርቱ መሪዎች፣ የደጋፊ ተወካዮች፣ ዳኞችና ኮሚሽነሮች እና ሌሎች በርካታ ባለድርሻ አካላትን አሳታፊ ባደረገውና በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን አዘጋጅነት በተሰናዳው የስፖርታዊ ጨዋነት የውይይት መድረክ ላይ የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳይያስ ጂራ ለእግርኳሱ ዕድገት ማነቆ ከሆነው የፖለቲካ ሽኩቻ በተጨማሪ በዘር እና ብሔር ስያሜ የተደራጁ ክለቦች ችግር እየፈጠሩ እንደሆነ ገልፀዋል። “ሁላችንም ለእግርኳሱ ከዛሬዋ ቀን ጀምሮ በመቆርቆር ለሰላማዊ ተግባር ብቻ ልናውል ይገባል። ሁላችንም ከተረባረብን የማይለወጥ የለም። በኛ በኩል ብሔርን ማዕከል በማድረግ እና በዘር ስያሜ የተቋቋሙ መጠሪያ ስያሜዎችን የያዙ ክለቦችን አንመዘግብም። ተለዋጭ መጠሪያ ስያሜን እስከ ቅርብ ቀን አሳውቁን” በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡", "passage_id": "1399455216b4ca743f3fdb726eccbcd1" }, { "passage": "የኢትዮዽያ ቡና ስፖርት ክለብ የደጋፊዎች ማኀበር መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ እና የ2 አመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ዛሬ ከ04:00 ጀምሮ በአምባሳደር አዳራሽ ተካሂዷል፡፡\nየክለቡ የቦርድ ተወካይ ፣ የደጋፊዎች ማህበር ሰብሳቢዎች እንዲሁም ደጋፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙበት ጉባኤ የተጀመረው በ2009 ከዚህ አለም በሞት ለተለዩ የክለቡ የልብ ደጋፊዎች የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት በማሰብ ነበር፡፡ጉባኤውን በንግግር የጀመሩት አቶ ክፍሌ አማረ ካለው የጊዜ እጥረት አንፃር ጠቅለል ያለ የ2 አመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ሲያቀርቡ ‹‹ በስፖርታዊ ጨዋነት ዙርያ ያለፉት ሁለት አመታት ለደጋፊዎቻችን ጥሩ ጊዜ አልነበረም፡፡ በዚህም ምክንያት ያለፉትን ሁለት አመታት የልማት ስራዎችን ሰርተናል ማለት አይቻልም፡፡ ያም ቢሆን በተወሰነ መልኩ ባለን ውስን የሰው ሀይል የተወሰኑ ስራዎች ሰርተናል›› ብለዋል፡፡ አቶ ክፍሌ በማህበሩ የተሰሩ ስራዎችንም ጠቅሰዋል፡፡ ለአብነት ያህል፡--ከተለያዩ ክልሎች እና አቻ ክለቦች ጋር ሰፊው ከስፖርታዊ ጨዋነት ዙርያ ውይይት አድርገናል፡፡ በዚህም ባለፈው አመት የተሻለ ስፖርታዊ ጨዋነት በየሜዳዎቹ ማሳየት ችለናል፡፡-427 ብቻ የነበረውን የተመዘገቡ የአባላት ቁጥር ወደ 14 ሺህ ከፍ በማድረግ የደጋፊውን ቁጥር አብዝተናል፡፡ በገቢ ደረጃ 2 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰብስቧል፡፡ ይህም የገንዘብ መጠን የተገኘው በተለያዩ የአአ አካባቢ ቅርንጫፍ በመክፈት ነው፡፡-ክለቡ በ40 አመት ምስረታ ውስጥ በተለያዩ ምክንያቶች የራቁ ቀደምት ደጋፊዎች ተከታታይነት ያለው ስብሰባዎችን በማድረግ ወደ ክለቡ እንዲመለሱ ተደርጓል፡፡-ከ10 ሺህ በላይ ደጋፊዎች የተሳተፉበት ቤተሰባዊ ሩጫ ባመረ ፣ በደመቀ ሁኔታ እንዲካሄድ አድርገናል፡፡ በደጋፊው መሀል የእርስ በእርስ ቤተሰበዊ ግኑኝነት እንዲፈጠርም ተደርጓል።-የክለቡ መገለጫ የሆነ ቋሚ ሎጎ እንዲኖረው እና ከጊዜያዊ ስራ ከመጠመድ ይልቅ ዘላቂ የሆኑ ሰራዎችን ለመስራት የሚያስችል በአምስት አመት የሚፈፀም እስትራቴጂ ፕላን ተዘጋጅቷል፡፡-የደጋፊዎች ማህበሩ የሚመራበት መተዳደርያ ደንብ የሌለው በመሆኑ ከተለያዩ ደጋፊ ማህበሮች ጋር የአሰራር ልምድ በመውሰድ ስራ አስፈፃሚው እና ደጋፊው የሚመራበት ደንብ እያዘጋጀን እንገኛለን፡፡-የማህበራዊ ተሳትፎ ላይ ደጋፊው ይበልጥ በግል ተነሳሽነት የተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎች ተሰርተዋል።-ከሀገር ውስጥ ድሬዳዋ እና ቢሾፍቱ ፣ ከኢትዮዽያ ውጨ በተለያዩ ሀገሮች ቅርንጫፍ ቢሮዎችን በመክፈት የደጋፊውን ቁጥር ለማብዛት እየተንቀሳቀን እንገኛለን፡፡በሁለት አመት ውስጥ ያጋጠሙ ችግሮች-የስራ አስፈፃሚ አባላት በራሳቸው ፍቃድ በመልቀቃቸው ተጓድለናል፡፡-የመዋቅርና የአሰራር ስርአት ያልተዘረጋ በመሆኑ ስራ አስፈፃሚ አባላት ሁሉም ስራ ላይ እንዲገቡ መደረጉ ሌሎች ስራዎችን ለመስራት እንዳይችል አድርጎታል፡፡-በተለያዩ ባለሙያዎች የቀረቡ ገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮፖዛሎች እንደ ዋዛ በተለያዩ ምክንያቶች  ተግባራዊ ሳይሆኑ ቀርተዋል፡፡-በደጋፊዎች መካከል የነበረው መከፋፈል ለቡድኑ ውጤትም ሆነ ደጋፊ ማህበሩ ስኬታማ እንዳይሆን ቢያደርገውም አሁን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ተቀርፎ አሁን በጥሩ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡-የክለቡ ደጋፊውን የሚመጥን ቡድን አለመሰራት እና ውጤት አለመምጣቱ ሰፊ ስራ አቅደን ላለመስራት እንቅፍት ሆኖብናል።\nበቀጣይ የአደረጃጀት ሁኔታውን የማሻሻል ጠንካራ ስራ እንዲሰራ ማድረግ ፣ በጎደሉ ምትክ ስራ አስፈፃሚ መተካት እና ከላይ የገለፅናቸውን ስራዎች ለመስራት አቅደናልም ተብሏል።\nየኦዲት ሪፖርት በአቶ ታምራት ጠንክር የቀረበ ሲሆን በ2008 ዓም 400ሺ ብር በላይ ገቢ ሲገኝ 2009 በሦስት እጥፍ ጨምሮ 1 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል፡፡ አጠቃላይ በሁለት አመት ውስጥ ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ እንደተገኘ ተገልፃል፡፡በወጪ ደረጃ ከ1ሚሊዮን ብር በላይ እንደወጣ ሲገለፅ ከፍተኛውን ወጪ የሚወስደው ለክልል ጉዞዎች ፣ በስፖርታዊ ጨዋነት ዙርያ ለተሰሩ ስራዎች ፣ የህትመት ስራ ወጪ ፣ ለፅህፈት ቤት ሰራተኞች ደሞዝ እና ማህበራዊ ጉዳይ ላይ የዋሉ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡ ከወጪ ቀሪም 7 መቶ ሺህ ብር በላይ እንዳለ ተገልፃል፡፡\nከተሳታፊ ደጋፊዎች የቀረቡ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች-በክለቡ ወቅታዊ ጉዳይ ለምናነሳው ጥያቄ መልስ እንዲሰጡን ለምን የክለቡ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ወይም ሌላ የቦርድ አባል አልተገኙም?ጠቅላላ ጉባኤው ዘግይቷል ፣ የክ/ከተማ የደጋፊ ማህበር እየተቋቋመ ይገኛል ማነው የሚቆጣጠራቸው ምን ያህልስ ግኑኝነት አላችሁ?በጄቲቪ እየቀረበ ያለው ፕሮግራም ደጋፊዎችን እያሳተፈ አይደለም፡፡ በጣም መሻሻል እና ደጋፊውንም የሚያሳትፍ መሆን ይገባል።ለክለቡ እየቀረበ ያለው የደጋፊ ማልያ በጣም አነስተኛ ነው፡፡ ሁሌ ይመጣል ትሉናላችሁ፡፡ ሆኖም እስካሁን መጥቶ አላየንም፡፡ ምድነው ችግሩ? መቼ ነው የማልያ ጥያቄዎችን የሚመለሰው?ከክለቡ አመራር ጋር ያላቹ ግኑኝነት ምን ይመስላል?  የምናቀርባቸው ጥያቄዎችን አቅርቡልን፡፡ ክለቡ ጋር በጣም ተራርቀናል፡፡ ስለ ክለቡ ምንም አናውቅም፡፡ በቦርዱ ያለን ድምፅ ሆኗል፡፡ ስለዚህ በአጭር ጊዜ ውስጥ የምንገናኝበት እድል ፍጠሩልን፡፡የደጋፊ ማህበሩ የገቢ ምንጭ ለማግኘት ከፍተኛ እቅድ አውጥቷል፡፡ ታዲያ ይህ ከክለቡ የገቢ ምንጭ ጋር እንዳይጋጭ ምን እያሰባቹ ነው?ከደጋፊ ማህበሩ አመራር የተሰጡ ምላሾችአቶ ክፍሌ አማረ ሰብሳቢ‹‹የውክልና ጉዳይ ላይ እኛም ያሳስበናል፡፡ በቦርዱ አንድ ውክልና አለን፡፡ ሆኖም ድምፃችንን እየተጠቀምንበት አይደለም፡፡ ይህ ካልሆነ የደጋፊው ማህበር ምንም ጥቅም የለውም። ስለሆነም ቦርዱ ደጋፊውን ድምፅ እንዲሰማ ውክልናችን ትርጉም እንዲኖረው ጥረት እናደርጋለን።››\nክፍሌ ወልዴ  ህዝብ ግንኙነት‹‹ በየሰፈሩ የሚቋቋሙ ደጋፊዎችን ጥሩ ጎን አለው፡፡ ብዙ ነገሮችንም ያቃልላሉ፡፡ በስፖርታዊ ጨዋነት ላይ በርካታ ስራዎችን በአካባቢያቸው እየሰሩ ነው፡፡ ይህ መልካም ጎን ነው።‹‹ ማልያን በተመለከተ ክለቡ ከሀበሻ ቢራ ጋር የተዋዋላቸው ውሎች አሉ፡፡ ትጥቅ ፣ ቁሳቁስ የማቅረብ ፣ የደጋፊ ማልያዎችን ጨምሮ ሀበሻ ቢራ 20 ሺህ ጥራት ያለው ማልያ እንደሚመጣ ተገልፆ እስካሁን አልመጣም፡፡ በቅርብ እንዲመጣ እየጣርን ነው። ካልሆነ እኛ ከክለቡ ጋር ተነጋግረን ችግሩን ለመቅረፍ ከፍተኛ ስራ እንሰራለን፡፡\n‹‹ የደጋፊ ማህበር መታወቂያ ጥቅም እንዲኖረው እየሰራን ነው፡፡ ፌዴሬሽኑ ድረስ በመሄድ መታወቂያው ዋጋ እንዲኖረውና አስፈላጊውን ነገር ቅድሚያ እንድታገኙ እየሞከርን ነው፡፡‹‹ በስፖርታዊ ጨዋነት ዙርያ ከሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት ፣ ከፌዴሬሽን እና ከሌሎች ደጋፊዎች ማህበር ጋር እየሰራን እንገኛለን፡፡ ቋሚ ኮሚቴም አዋቅረናል፡፡ በተጨማሪም በየበሩ የሚያስተባብሩ 100 አባላትን መርጠን በየቦታው አሰማርተናል፡፡ ለእነርሱ ተገዢ እንሁን፡፡ የስፖርታዊ ጨዋነት ጉዳይ ለኢትዮዽያ ቡና የህልውና ጉዳይ ነው፡፡ ››\nከምላሾች በኋላ በጎደሉ የስራ አስፈፃሚ አባላት ምትክ ከመድረኩ በቀረበው ጥቆማ መሰረት አቶ በፍቃዱ አባይ እና ናትናኤል ተክሉ በጉባኤው ሙሉ ድምፅ ተመርጠዋል።  አቶ ዳንኤል የቦርድ አባላትን መልዕክት አስተላልፈው እንዲሁም የክለቡ የቦርድ ሰብሳቢ እና ሌሎች አባላት የቀሩበትን ምክንያት ለተሳታፊው በመግለፅ ጠቅላላ ጉባኤው ፍፃሜውን አግኝቷል።በመጨረሻም በጣም ቀልብን የሚገዙ፣ አትክሮትን የሚስቡ፣ የኢትዮዽያ ቡና ደረጃ ከፍ የሚያደርጉ፣ በደጋፊው መካከል መተማማን የሚያመጡ ፣ ራስን የማረም እና የመገሰፅ ፣ የስፖርት ነውጠኝነት ለመቀየር የሚያስችሉ ጠቃሚ መልክቶች ከመድረኩ ተሳታፊዎች በጥሩ መንገድ ሲገለፁ ተመልክተናል።", "passage_id": "7919ec8a36abc3842526f31d83c0d259" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ሕዳር 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የስፖርት ምክር ቤት የምሥረታ ጉባዔ ተካሄደ።በጉባዔው ላይ የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች፣ የወረዳና ከተማ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪዎች እንዲሁም የተለያዩ ስፖርት ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንቶችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።የምክር ቤቱ የመመሥረቻ ደንብና የ2013 በጀት ዓመት ዕቅድ ቀርቦ በምክር ቤቱ አባላት ውይይት ተደርጎ ውሳኔ እንደሚተላለፍ ከክልሉ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።", "passage_id": "5f0e2df14717880e4016209973ade2eb" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ታህሣሥ 1/2006/ዋኢማ/ – የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር አስቸኳይ የአባላት ጠቅላላ ጉባዔውን ባለፈው ቅዳሜ ሕዳር 28 ቀን 2006 ዓ.ም አካሄደ። ማህበሩ ከተቋቋመበት ከ1931 ዓ.ም ጀምሮ የገጠሙትን በርካታ ውጣውረዶችና ችግሮችን ጉባዔው በመፈተሽ መፍትሔ የሰጠ ሲሆን የአቋም መግለጫም አውጥቷል። የጉባኤው ሙሉ የአቋም መግለጫ የሚከተለው ነው።በጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር አስቸዃይ የአባላት ጠቅላላ ጉባዔ የወጣ የአቋም መግለጫ ሕዳር 28 ቀን 2006 ዓ.ም.ፋሽስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በቅኝ ገዥነት ለመያዝ ልዩ ፍላጐት ስለነበራት ቀደም ሲል የነበራትን የትብብር ውልና እንዲሁም በመንግሥታቱ ማህበር የገባችውን አለም አቀፍ ግዴታዎች በጠመንጃ አፈሙዝ ናደችው። በጊዜው የነበሩትም ኃያላን መንግሥታት የኢትዮጵያን ህዝብ አቤቱታና ሰቆቃ ከምንም ባለመቁጠር ኢትዮጵያን ለጣልያን ፋሺዝም ለእጅ መንሻነት አቀርቧት።በዚህ ፈታኝ ወቅት ነበር እኛ በዘር፣ በሃይማኖት፣ በፆታ ሳንከፋፈል “የጋራን ጠላት በጋራ ክንድ” የሚል መፈክር በማንገብ ወራሪውን ጠላት በጦርና በጐራዴ በመረፍረፍ ሥጋውን የአማራና የአውሬ ቀለብ እንዲሆን በማድረግ ከፍተኛ ድል ተቀድጅተን አገራችንንና ሕዝባችንን ከወረራ ነፃ ያወጣነው። በትግል ወቅት የመሰባሰብ ጥቅም የተገነዘቡ አርበኞች ሸዋ ተጉለት ልዩ ሥሙ አንቀላፊኝ ላይ በ1931 ዓ.ም. የተቋቋመው ማህበራችን ዛሬ የ75 ዓመት አዛውንት እንደሆነው ጉባዓ በኩራት አስቦታል።ማህበሩ በ75 ዓመቱ በርካታ ውጣውረድ እንዳሳለፈ በተለይም የመረጥናቸው የማህበራችን ሹማምንትም በማህበራችን ደንብ ክፍል ስድስት የተደነገገውን አምስት ዓመት የምርጫ ዘመን በመጣስ ለ11 ተከታታይ ዓመታት በማህበሩ ብልሹ የሆነ አመራርና አሰራር በማስፈናቸውና ጉዳት በማድረሳቸው በማህበራችን ታሪክ ላይ ጥላሸት ጥለዋል። በዚህ ምክንያትም ይህ አስቸኳይ ጉባዔ ተጠርቶ ጉዳዩን አይቷል። ጉባዔው ማህበራችንን የደረሰበትን ችግር በማየት፣ የሚያስፈልገውን መፍትሔ በመስጠት እና ሌሎች ተግባራት በመመርመር እልባት ከመስጠቱም በላይ ይህንን የአቋም መግለጫ አውጥቷል።1.    የፌዴራል የበጎ አደራጎት ድርጅቶችና ማህበራት ኤጀንሲ በአዋጅ ቁጥር 621/2001 አንቀጽ 91 እና 70 በተሰጠው አስተዳደራዊ ሥልጣን በመጠቀም ሐምሌ 30 ቀን 2006 ዓ.ም. የቀድሞ የማህበሩን ፕሬዝዳንት፣ ም/ፕሬዝዳንት፣ ፀሐፊ ከደሞዝና ከሥራ በማገድ፤ የማህበሩ የሥራ አመራርና የአስተዳደር ምክር ቤት እና በየካቲት ወር 2005 የተሰየመው ጊዜያዊ አጣሪ ኮሚቴ በማፍረስ፤ ማህበራችንን ከተከታታይ ብልሹ ከሆነ አመራርና አሰራር መታደጉና “የጠቅላላ ጉባዔ አዘጋጅና ጊዚያዊ አስተዳደራዊ ኮሚቴ” ከውስን ሥልጣን ጋር ማቋቋሙ ከመዘግየቱ በስተቀር በእጅጉ የምንደግፈው ነው። ጉባዔው የኤጀንሲውን ውሳኔ የራሱ ውሳኔ አድርጐ ተቀብሎታል።2.    የጠቅላላ ጉባዔ ተዘጋጅና ጊዜያዊ አስተዳደራዊ ኮሚቴም በተሰጡት አራት ሥራዎች ላለፉት አራት ወራት የተሰሩ ሥራዎች ክንውን፣ ለገጠሙት ችግሮች የተወሰዱ መፍትሔዎችና ጉባዔው መመሪያ ሊሰጥባቸው የሚገቡትን ነጥቦች በማካተት በኮሚቴው ሰብሳቢ የቀረበው የአስተዳደር ሪፖርት በአድናቆት ተመልክቶ፣ ተወያይቶ ተቀብሎታል። አፅድቆታልም።3.    ጉባዔው ብልሹ ለሆነ አመራርና አሰራር ለመፈጸም የቀድሞ የማህበሩ መሪዎች በመሳሪያነት የተጠቀሙት ድክመት የነበረባቸውን የማህበራችንን ደንቦች በመጠቀም እንደሆነ ኤጀንሲው በመረዳት ደንቡን ማሻሻል የጠቅላላ ጉባዔ አዘጋጅና ጊዜያዊ አስተዳደራዊ ኮሚቴ ቀዳማይ ሥራ ማድረጉ ጉባዔው ትክክለኛ አካሄድ መሆኑን አረጋግጧል። የጠቅላላ ጉባዔ አዘጋጅና ጊዜያዊ አስተዳደራዊ ኮሚቴውም ሥራው ሙያ የሚጠይቅ መሆኑን በመገንዘብ የ1990 ደንባችንን ለማሻሻል አርቃቂ ኮሚቴ በማቋቋም ሥራውን ማሰራቱ አድንቋል። ከሁሉም በላይ የጠቅላላ ጉባዔ አዘጋጅና ጊዚያዊ አስተዳደራዊ ኮሚቴው አርቃቂ ኮሚቴ ያቀረበው ረቂቅ በቀጥታ ለጉባዔ አባላት በቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች በኩል ቀደም ብሎ ለጉባዔተኞች እንዲደርስ መደረጉ የግልፅነት አሰራር ብልጭታ መታየቱ ተስፋ ሰጭ ነው። ጉባዔው ያለጊዜ እጥረት ቃላትን ጨምሮ በመፈተሽ፣ አስተያየቱን በጽሑፍ በማቅረብ ሰፊ የጉባዔ ጊዜውን በመጠቀም የሚቀበለውን ተቀብሎ፣ የሚጥለውን ጥሎ ደንቡን አሻሽሏል፡ አፅድቋል። ከህዳር 29 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ ደንቡ ሥራ ላይ እንዲውል ወስኗል።4.    ህዳር 28 ቀን 2006 ዓ.ም. በፀደቀው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት የምርጫ ዝግጅት ኮሚቴ በመመረጥ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ የማህበሩን አመራር ለመምረጥ ቀጠሮ የሰጠ ሲሆን የተመረጡት አስመራጭ ኮሚቴ አባላት ማህበራችንን ለማዘመን በትምህርት ዝግጅታቸው፣ በልምዳቸውና በክህሎታቸው ላይ ትኩረት ሰጥቶ ብቃት ያላቸው እጭዎች እንዲያቀርብ መመሪያ ሰጥቷል።5.    የማህበሩ የ2004 እና 2005 ዓ.ም. የሂሳብ ሪፖርት ሒሳቡን የመረመረ የውጭ ኦዲተር በሚቀጥለው የምርጫ ጉባዔ ለሥራ አመራር ከሚቀርበው መግለጫ (management qualification report) ጭምር እንዲያቀርብ ከወዲሁ በጽሁፍ እንዲገለጽለት፤6.    ኤጀንሲው የሰየመው የጠቅላላ ጉባዔ አዘጋጅና ጊዜያዊ አስተዳደራዊ ኮሚቴ ተልዕኮ ህዳር 28 ቀን 2006 ዓ.ም. ቢያጠናቅቅም ጉባዔው ኮሚቴውን እስከ ምርጫና ተመራጮች ማህበሩን ተረክበው እስኪ መሩ ድረስ እንዲቀጥል ወስኗል።7.    የጠቅላላ ጉባዔ አዘጋጅና ጊዜያዊ አስተዳደራዊ ኮሚቴው የታዘባቸው ጉዳዮች ተመልክተን በጥልቀት በመመርመር፣ በማጠናከርና አዲስ በመጨመር የጠቅላላ ጉባዔ አዘጋጅና ጊዜያዊ አስተዳደራዊ ኮሚቴም ሆነ ወደፊት ማህበሩን ለሚመራ የሚያገለግል መመሪያ ሰጥቷል። የጉዳዮቹን አፈፃፀም የማህበሩ ጠቅላላ ጉባዔ ማይጠብቅ በየጊዜው ለማህበሩ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች በጽሁፍ እንዲያውቁት እንዲደረግ በማስገንዘብ ጉባዔው የሰጣቸው መመሪያዎች ቀጥለው ቀርበዋል።7.1    የአባላት ማኅደር ምርመራ ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል፤7.2    የማህበሩ ቅርስ አቀማመጥና ጥበቃ ተጠናክሮ እንዲቀጥል፤7.3    የቅጥር ሠራተኞች የአስተዳደር መመሪያ /ማኑል/ በባለሙያ ተሰርቶና በማህበሩ የሥራ አመራርና የአስተዳደር ምክር ቤት ሲፀድቅ ሥራ ላይ እንዲውል፤7.4    ቀደም ሲል በብልሹ አመራርና አሰራር የወረዱት ተመራጮች የምርጫ ዘመናቸው /አምስት ዓመት/ ካለቀ በኋላ የበሉት ደመወዝ በፍርድ ቤት ክስ ተዘጋጅቶ እንዲመልሱ እንዲደረግ፤7.5    በብልሹ አመራርና አሰራር በወንጀል በተከሰሱትም ሆነ ባልተከሰሱት ላይ ማስረጃ ተጠናክሮ በፍትሐ ብሔር ከነወለድና ወጭው ጭምር ተከሰው የማህበሩ ገንዘብ የሚመለስበት የሕግ አካሄድ እንዲጀመር፤7.6    በብልሹ አመራርና አሰራር አማካኝነት አባል ሣይሆኑ እስከ ምክትል ፕሬዝዳንት ደረጃ በተሳሳተ ማስረጃ ማህበሩን አሳስተው ሰርገው በመግባት ለተከታታይ ጥፋት በመፈፀም እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል እንዳለችው እንሰሳ ከወደቁም በኋላ ሥራ አላሰራ ብለው ከትግሥት በላይ በመሆን በሚበጠብጡት በአቶ ወርቅነህ ተገኝ ላይ በወንጀል፣ በፍትሐ ብሔር በአስተዳደር እንደአግባቡ እንዲከሰሱ ማስረጃ ተጠናክሮ ከህዳር 30 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ የድርጊት ሥራ እንዲጀመር፤7.7    በየሁኔታው ለሚነሱት ክሶች ወይም ለምንመሰርታቸው ክሶች ማህበሩ የሕጉን ሒደት በብቃት የሚከታተል ብቁ የሕግ እውቀት ያለው አርበኛ ወይም የአርበኛው ተተኪ ተቀጥሮ በክፍያ እንዲሰጥ፤7.8    የአርበኞች ሕንፃ ግንባታ፣ ጥገናና የኪራይ አስተዳደር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ከብልሹ አመራርና አሰራር የፀዳ ሥራ እንዲሰራ፣ ከዚህም የሚገኘው የማህበሩ ገቢ በግልፅና በአስተማማኝ ሁኔታ ወደ ማህበሩ ካዝና እንዲገባ፤7.9    በኮንዶሚኒየም ቤቶች የተፈፀመው በደል ክትትል ተደርጐ፣ በሰከነና ማህበሩን ባማከለ ሁኔታ ከብልሹ አመራርና አሰራር በፀዳ አግባብ ባለው ሁኔታ እንዲስተካከል፤7.10    የሥላሴ መካነ መቃብር እንደ አዋጁ እንዲፈፀም፣ ብልሹ አሰራር እንዲወገድ ከቤተክርስቲያንዋና ከመንግስት አካላት ጋር ክትትል ተደርጎ በፍርድቤትም ቢሆን መብታችን እንዲከበር እንዲደረግ፤7.11    የተወሰኑ አዲስ አበባ ነዋሪ የሆኑ አርበኞች በድጎማ የተሰጣቸውን ገንዘብ አንድ ላይ በማድረግ በገዙት ቤት ላይ ማህበሩ እነሱ በሚጠቀሙበት መልክ ከብልሹ አመራርና አሰራር የፀዳ የአመራር ድጋፍና እገዛ እንዲደረግላቸው ተጠቃሚነታቸው እንዲረጋገጥ፤7.12    ማህበራችን በወከልናቸውም ሆነ ባልወከልናቸው በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር በማህበሩ ወይም በአርበኛ ሥራ የተሰበሰበ ወይም የሚሰበሰብ ሀብት በአግባቡ ግልፅ በሆነ አሰራር ወደማህበሩ ካዝና /የባንክ ሂሳብ/ ክትትል፣ ጥረትና ድጋፍ ተደርጎ እንዲገባ ብቁ የሆነ ሰው እንዲመደብ፤7.13    በመንግሥት ወይም በሌላ 3ኛ ወገኖች እጅ የሚገኝ ሕንፃ፣ ገንዘብ፣ ንብረት፣ ቅርስ ድጋፍ ተደርጎ እንዲገባ ብቁ የሆነ ሰው እንዲመደብ፤7.14    ማህበራችን ገቢ የሚያገኝበትና አርበኞች ቀሪ ዘመናቸውን ሳይራቡ የሚያኖር ድጎማ ለመስጠት የሚያስችል የገቢ ማስገኛ ጥረት እንዲደረግ፤7.15    ፋስት ኢታሊያ በእኛ በአርበኞች አካል፣ ሕይወትና ንብረት ባደረሰችው ጉዳት ካሳ የምትከፍልበትን መንገድ ልማታዊ መንግሥታችንን በመያዝ ጥረት እንዲደረግ፤7.16    ሌሎች ተመሳሳይ ጉዳዮች የስራ አመራር ምክር ቤት እየተመለከተ ማህበሩ በታሪኩ አይቶት የማያውቁን ለውጥ ማምጣት የሚያስችል ሥራ እንዲሰራ።8.    በብልሹ አመራርና አሰራር ቀውስ ደርሶበት የነበረውን ማህበራችን ቀውሱን ያስወገድንለት መሆኑን አመነው በሀገራችንም ሆነ በውጭ አገር የሚገኙ የግልም ሆኑ የመንግሥት የመገናኛ ብዙሐን የማህበራችንን መልካም ተግባርና ዝና እንዲዘግቡ ጉባዔው ጥሪውን እያቀረበ፣ ሆኖም አፍራሽ ዘገባ በማህበራችን ላይ ለማቅረብ ከአስተማማኝ ወገን የቀረበ ማስረጃ ማግኘትን፣ የሚዲያን ሕግ ያከበረና ሚዛናዊ እንዲሆን ያሳስባል።የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበርሕዳር 28 ቀን 2006 ዓ.ምአዲስ አበባ", "passage_id": "e0f752031c63b352aeafd4eeaf64429b" }, { "passage": "ጥቅምት 1 ቀን ይካሄዳል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን 11ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ በኅዳር ወር ሊካሄድ ይችላል።መካሄድ ከነበረበት ጊዜ ዘግይቶ ጥቅምት 1 ቀን በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ፌዴሬሽኑ አስቀድሞ ቢያሳውቅም በሀገር አቀፍ ደረጃ ጥቅምት ወር በሚካሄደው የስፖርት ምክር ቤት ጉባዔ ምክንያት የሚደረግበት ቀን ወደ ጥቅምት 29 ተገፍቶ ለማደረግ ታስቦ የነበረ ቢሆንም የሚለወጥ ነገር ከሌለ በቀር አሁን እየወጡ ባሉ መረጃዎች ኀዳር 6 ቀን ጠቅላላ ጉባዔውን ለማካሄድ መታሰቡን ሰምተናል።ለወትሮም መነጋገርያ ጉዳዮች የማያጡት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባዔ የተለመደው የ2010 ዕቅድ አፈፃፀም፣ የኦዲት ሪፖርት ማዳመጥ መወያየት ማፅደቅ እና በተጓደሉ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ማሟላት እንዳለ ሆኖ ከወዲሁ ብዙ ክርክሮች ያስነሳል ተብለው የሚጠበቁ በርከት ያሉ አዳዲስ አጀንዳዎች በዕለቱ ይነሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።", "passage_id": "50ff87b6f463b61d89afe07b05d36d8e" } ]
dc0014c798abfb279f5043c197e6519a
b53b76d935ddc0241d056dbf9e648942
የብስክሌት ኮርቻ ቀበኛው
ሌባ ላመሉ ዳቦ ይልሳል እንዲሉ አመለኛ ሌባ ያገኘውን ከመስረቅ ወደኋላ አይልም። ታዲያ ሌብነት ሁሌም አይቀናምና አንድም በሰዎች መደብደብን ባስ ሲልም በፖሊስ መያዝና ለአስር መዳረግን ያስከትላል። ሌባ ከትንንሽ እቃዎች አንስቶ አስከ ከፍተኛ ውድ እቃዎች ድረስ ፤ ከትንሽ አስከ ከፍተኛ ገንዘብ ድረስ ይሰርቃል። አንዳንድ ሌባዎች የሚሰርቋቸው እቃዎች ግን እንግዳና ያልተለመዱ ሆነው ‹‹ምን ሊያደርግላቸው ነው?›› የሰረቁት ያሰኛሉ። ከሰሞኑ ኦዲቲ ሴንትራል ይዞት የወጣው መረጃም ይህንኑ ያመለክታል። ነገሩ እንዲህ ነው፤ የ57 ዓመቱ ጃፓናዊ የከባድ መኪና አሽከርካሪ ሂሮዋኪ ሱዳ ከወራት በፊት በአንድ የባቡር ጣቢያ በርካታ ብስክሌቶች በሚቆሙበት ቦታ ግምታቸው 8 ሺ የጃፓን የን ወይም 75 የአሜሪካ ዶላር የሚያወጡ የሁለት ብስክሌቶች ኮርቻ ወይም መቀመጫ ሲሰርቅ በቅኝት ካሜራ በመታየቱ በፖሊስ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል። ሱዳ ድርጊቱን መፈ ፀሙን ያመነ ሲሆን ባል ተለመደ ሁኔታ የብስ ክሌት ኮርቻዎችን ወይም መቀመጫዎችን ያውም ለሃያ አምስት ዓመታት ሲሰርቅ መቆየቱን ለፖሊስ አስታውቋል። የሚገርመው ደግሞ የሰረቃቸውን እቃዎች በሙሉ በአንድ ላይ በመሰብሰብ በሚ ማርክ መልኩ እንዳስቀ መጣቸውም ለፖሊስ መና ገሩ ግርምትን ፈጥ ሯል። ‹‹የብስክሌት ኮርቻ ዎችን መስረቅ የጀመርኩት ከዛሬ ሃያ አምስት ዓመት በፊት በቶኪዮና ኦሳካ ነው። ስርቆቱን የጀመርኩትም በሥራ የሚገጥመኝን ውጥረት ለመቀነስ በሚል ሲሆን፣ በኋላ ላይ ግን ኮርቻዎቹን ሰርቄ መሰብሰብ ስጀምር ደስታን አጎናፅፎኛል›› ሲል ሶዳ ለፖሊስ ቃሉን ሰጥቷል። የ57 ዓመቱ የከባድ መኪና አሽከርካሪ የሚሰርቃቸውን የብስክሌት ኮርቻዎች ተከራይቶ ወደሚያስቀምጥበት ቦታ ፖሊሶችን መርቶ አሳይቷል። በቦታው 5 ሺ 800 የሚሆኑና ላለፉት ሃያ አምስት ዓመታት የተሰረቁ ኮርቻዎች መገኘታቸው ተረጋግጧል። የአሽርካሪነት ሞያውን በመጠቀም በጃፓን የተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የብስክሌት ኮርቻዎችን ሲስርቅ መቆየቱንም ለፖሊሶች አስረድቷል። ከዚህ በፊትም ሌላ ጃፓናዊ በተመሳሳይ በአንድ ዓመት ውስጥ 159 የሚሆኑ የብስክሌት ኮርቻዎችን በመስረቅ መነጋገሪያ ሆኖ እንደነበርም መረጃው አስታውሷል። አዲስ ዘመን መጋቢት 1/2012አስናቀ ፀጋዬ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=28828
[ { "passage": "ክስተቱ በደቡብ አፍሪካ፣ ፖርት ኤልዛቤት በምትባል ከተማ ዛሬ የሆነ ነው።\n\nተጎታች ከባድ መኪና አሽከርካሪው ልጆቹን ከፓርሰንስ ሂል ትምህርት ቤት ሊያወጣ መኪናውን እንደነገሩ አቁሞት ነበር። \n\nሾፌሩ ከባዱን ተሽከርካሪ የቆመበት ቦታ አቀበታማ የሚባል ነበር ይላል ፖሊስ።\n\nልጆቹን ከትምህርት ቤት ሊያወጣ የሄደው ሾፌር እነሱን ይዞ ሲመለስ ከባዱ መኪናው ከቆመበት ቦታ የለም። \n\nእንዴት ከባድ ተሽከርካሪ ከዐይን ይሰወራል ብሎ መገረሙን ሳይጨርስ ሾፌሩ የሆነውን ይረዳል።\n\nከባድ ተሽከርካሪው ፍሬኑን በጥሶ፣ ሌላ መኪና ላይ ወጥቶ፣ ሰው ላይ ከባድ ጉዳት ማድረሱን የተረዳው ኋላ ነበር። \n\nከባድ ተሽከርካሪው የተጫነው የቤት መኪና እጅግ በመጨፍለቁ ማንም ከዚያች የቤት መኪና ውስጥ በሕይወት ይወጣል አልተባለም ነበር።\n\nአራት ሰዓታት በፈጀ እልህ አስጨራሽ ሂደት ግን ሕይወት ተርፏል።\n\nፖሊስ እንደሚለው ከባዱ ተሽከርካሪ ፍሬን በጥሶ ከአቀበት እየተንደረደረ ነው ኦፔል አዳም ሞዴል የቤት መኪና ላይ የወጣው ።\n\nድንገተኛ መአት የተጫናት የቤት መኪና ከአስፋልት ተመሳሰለች በሚባል ደረጃ መጨፍለቋ ነበር የብዙዎችን ተስፋ ያጨለመው።\n\nየእርዳታ ሰጪዎች 40 ደቂቃ የፈጀ ጥረት አድርገው ልጅቱን አትርፈዋታል።\n\n•በየቤቱ እና በየጎዳናው የሚደፈሩ ሴት የአእምሮ ህሙማን\n\n•''እግሬን ባጣም ትልቁን ነገር አትርፌ ለትንሹ አልጨነቅም''\n\nልጅቱ ትትረፍ እንጂ ከባድ የሚባል የአካል ጉዳቶች እንዳጋጠሟት ተነግሯል። \n\nእሷን ከዚያ ለማውጣት መኪናውን መቁረጥ አስፈላጊ ነበር።\n\nፖሊስ የከባድ መኪናውን ሾፌር በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያደረገበት ይገኛል።\n\n ", "passage_id": "2c2ff302980370f5e25166b1f174d403" }, { "passage": "ከፒያሳ አቡነ ጴጥሮስ አደባባይ ወደ ጄነራል ውንጌት የሚወስደውን ዋናውን የአስፓልት መንገድ ይዘው ሲጓዙ በስተቀኝ የራስ ደስታ ሆስፒታልን የግንብ አጥር እንደጨረሱ የሚገኘው ወደ ቀጨኔ የሚወስደው መንገድ አይሆኑ ሆኗል። ቀጭን የነበረው አስፓልት መልኩን ቀይሮ በተቆለለ አፈርና በተፈረካከሰ መሬት ተተክቷል። በመንገዱ ላይ የሚፈሰው ውሃ፤ የቀጠነውና የጓጎለው ጭቃ፤ መንገደኛ እንዳያልፍ ሆነ ተብለው የተሠሩ እንቅፋቶች ይመስላሉ። ሰዎች ወደ በዚህ መንገድ በመኪና መሄድ አይችሉም። መኪና ሆስፒታሉ አጠገብ አቁመው የሚፈሰውን ውሃ እና የቦካውን ጭቃ ተጠንቅቀው ቢያልፉም ቤታቸው በር ላይ ሲደርሱ የተቆፈረውን ትልቅ የቱቦ ጉድጓድ ለማለፍ ከባድ ፈተና ይጠብቃቸዋል። በተለይ አቅመ ደካማ አረጋውያንና ነፍሰጡር ሴቶች፤ እንዲሁም ሕፃናት የያዙ ሰዎች ከግቢያቸው በር እስከ መንገዱ የተዘረጋችውን የእንጨት ድልድይ ለማለፍ እጅግ ይሰጋሉ። ይጠነቀቃሉ። ከአካባቢው ነዋሪ መካከል አቶ አላዶር መኩሪያ አንዱ ናቸው። ሁለት ሕፃናት ልጆች ያሏቸው ሲሆን፤ ባለቤታቸውም ነፍሰጡር በመሆናቸው አቶ አላዶር ሁለቱን ልጆቻቸውን በሁለት እጆቻቸው ግራና ቀኝ ታቅፈው ከግቢያቸው ወጥተው መኪና ወደሚያቆሙበት የሆስፒታሉ አጥር ድረስ እስኪደርሱ ይሳቀቃሉ። እንደ አቶ አላዶር ገለጻ፤ መንገዱን ለማስፋትና ደረጃውን ለማሻሻል መሠራቱ መልካም ነው። ሆኖም የመንገዱ ሥራ ቀደም ሲል ሌትና ቀን ያለማቋረጥ ይካሄድ ነበር። ከሁለት ወር ወዲህ ግን ሥራው የቆመ ይመስላል። ክረምቱ እየባሰ ሰው እየተሰቃየ ነው። አሁን ጥያቄ ውስጥ ገብተዋል። ስቃያችን እስከመች ይቀጥላል? ይህ መንገድ መቼ ተጠናቅቆ እንደልባችን እንገባ እንወጣ ይሆን? በሚል በጭንቀት ተወጥረዋል። ሌላው የአካባቢው ነዋሪ ወጣት ሄኖክ ነጋሽ ነው። ወጣት ሄኖክ እንደሚናገረው፤ የመንገዱ መሠራት የአካባቢውን ዕድገት ያሻሽለዋል። የበለጠ ምቹ እንዲሆንም ያግዛል የሚል ተስፋን በማጫሩ መንገዱን ለማስፋት የግቢ አጥሮች፤ ሱቆችን ጨምሮ የተለያዩ የንግድ እና የመኖሪያ ቤቶች ሲፈርሱ የአካባቢው ህዝብ ለመንገዱ መሠራት ከፍተኛ ጉጉት ስላለው ብዙም ጫጫታ አልነበረም። የመንገዱ ግንባታ ደግሞ ቀንና ሌሊት ሲካሄድ ብዙ ሰው ደስ ብሎት ቶሎ ይጠናቀቃል ብሎ በተስፋ አድርጎ ነበር።ነገር ግን፤ ከሦስትና ከሁለት ወር ወዲህ ሥራው የቆመ ይመስላል። አንዳንድ የቀን ሠራተኞች ትንንሽ ሥራ ሲሠሩ ይታያሉ። ለመንገድ ግንባታ የሚያገለግሉ ማሽኖችና መቆፈሪያዎች ደግሞ ሁለት ቀን ታይተው ይሄዳሉ። ይህ በነዋሪዎቹ ላይ ስጋት ፈጥሯል። መንገዱን ለማስፋት በሚል ሰበብ በፊት የነበረው ቀጭን አስፓልት ተበለሻሽቶ ዘመናትን እንዳያስቆጥር የሚል ፍራቻ እንዳሳደረም ነው ወጣት ሄኖክ የሚናገረው፤ “በአዲስ አበባ እየተካሄዱ ካሉ የመንገድ ፕሮጀክቶች መካከል በተሻለ ፍጥነት እየተሠራ ያለው መንገድ የራስ ደስታ ቀጨኔ፤ ስምንት ቁጥር ማዞሪያ የመንገድ ፕሮጀክት ነው። ይህ መንገድ ከተጀመረ በጥቂት ወራት ውስጥ 30 በመቶ የሚሆነውን መሰረታዊ ለአስፓልት የማዘጋጀት ሥራው ተሠርቷል።” በማለት ስጋቱ ተገቢ አለመሆኑን የሚገልጹት ደግሞ የመንገድ ፕሮጀክቱ ተቋራጭ የማርካን ትሬዲንግ የኮንስትራክሽን ኃላፊ አቶ ዘነበ ምሩፅ ናቸው። አቶ ዘነበ፤ አስፓልት ለመሥራት የሚያስችሉ ግብአቶች የተዘጋጁ ሲሆን፤ ግንባታውን የያዘው ወይም ያዘገየው ዝናቡ ብቻ መሆኑን ያመለክታሉ። እንደ አቶ ዘነበ ገለጻ፤ ሥራው አልቆመም። ለአስፓልት ሥራው ከሁለት ሺህ በላይ በርሜል ሬንጅ ተዘጋጅቷል። ነገር ግን አስፓልት ለማንጠፍ ዝናቡ አያመችም፤ አስፓልቱ ይበላሻል። የአፈሩ ሥራ እንዳይሠራ ይቦካል የሚል ስጋት አለ። ያም ሆኖ ግን ሥራው አልቆመም። ሰዎች እንዳይንገላቱም ሌሎች ተጨማሪ ሥራዎች እየተሠሩ ናቸው። የመንገድ ግንባታው ቀጨኔን፤ ችሎትን፤ ዘበኛ ሰፈርን እና ራስ ደስታን የያዘ ነው። የዘበኛ ሰፈር ነዋሪዎች ከተራራ ስር በመሆናቸውና ኃይለኛ ጎርፍ ስለሚያጥለቀልቃቸው ከአሁን በፊት ለክረምት አካባቢውን ለቅቀው ይሄዱ ነበር። አሁን ግን ስካቫተር እና 50 የቀን ሠራተኞችን በመመደብ ጊዜያዊ መፍትሔ ለመስጠት ታስቦ በመሥራቱ አደገኛውን ቦታ በማስተካከል፤ ውሃው በቱቦ እንዲሄድ ተደርጓል። ይህ በብዙ ወጪ ከፍተኛ ዋጋ ተከፍሎበት የተሠራ ሥራ ነው። በችሎት አካባቢም የውሃና የኤሌክትሪክ፤ እንዲሁም የቴሌ መስመር ችግሮች ቢኖሩም የጋራ ሥራ እየተካሄደ ይገኛል። እነርሱን በመዝለልም ቱቦ እየተቀበረ ነው። የአካባቢዎቹ ነዋሪዎች በፕሮጀክቱ መጀመሪያ ወቅት መሬት በሚቆፈርበትና አፈር በሚሞላበት ጊዜ ለ24 ሰዓት ሲሠራ ነበር። አሁን ማታ ማታ ብቻ ስለሚሠራ እና በፊት የነበረው እንቅስቃሴ ስላልቀጠለ ይጓተታል ብለው ፈርተዋል። ነገር ግን አሁንም በተወሰነ መልኩ እየተሠራ ነው። አሁን በቱቦ ሥራ ላይ ትኩረት ተደርጓል። ዝናቡ ሲያልፍ ከመስከረም በኋላ የ24 ሰዓት ሥራው ስለሚቀጥል መስጋት አይኖርባቸውም። ምክንያቱም ፕሮጀክቱ ከተያዘለት የሁለት ዓመት ተኩል ጊዜ በፊት ቀድሞ መጠናቀቁ አይቀርምና፤ ይላሉ። የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን የሥራ ክፍል ኃላፊው አቶ ጡዑማይ ወልደገብርኤል በበኩላቸው፤ ከፒያሳ ወደ ውንጌት የሚወስደውን ዋና መንገድ ከሽሮ ሜዳ ከሚመጣው መንገድ ጋር የሚያገናኘው ይህ ሁለት ነጥብ አምስት ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን ትልቅ የመንገድ ፕሮጀክት በተቋማቸው ግምገማ መሰረት አሁን ካሉት የመንገድ ፕሮጀክቶች በሙሉ አፈፃፀሙ እጅግ የተሻለ የተባለለት ነው ይላሉ። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በታኅሣሥ ወር በምክትል ከንቲባው አቶ ታከለ የተጀመረው ይህ ፕሮጀክት፤ ከስምንት ፕሮጀክቶች ውስጥ ምሳሌ ይሆናል ተብሎ ተስፋ ተጥሎበታል። የአካባቢው ሰዎች፤ የልማት ኮሚቴዎች ባለስልጣኑ ከሥራ ተቋራጩ ጋር ሲፈራረም ጀምሮ በአካል ተገኝተው እየተከታተሉ ነው። ሥራው እንዲቀላጠፍም ጥረት በማድረግ ላይ ናቸው። ተቋራጩ በኃላፊነት ስሜት እየሠራ ነው። አካባቢው የጉልት ገበያን ጨምሮ የተለያዩ የንግድ ቦታዎችን ያካተተ ቢሆንም፤ ነዋሪው በማይመች ሁኔታ ውስጥ ሳይማረር ለመሥራት ጥረት እየተደረገ ነው። ሰዎች የሚገቡበት እና የሚወጡበት እንዳያጡ፤ አደጋ እንዳያጋጥም አፈር በማንጠፍ በተወሰነ መልኩ አሽከርካሪዎችን በሚያንቀሳቅስ መልኩ እንዲሠራ ለኮንትራክተሩ በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት ተቋራጩም አስተካክሎ እየሠራ ነው ይላሉ። “የከተማ መንገዶች ሲሠሩ ጭቃ ሆነብን የሚል ቅሬታ መሰማቱ የተለመደ ነው።” የሚሉት አቶ ጡዑማይ፤ ነገር ግን ፕሮጀክቱ ዘንድሮ የተጀመረ ሆኖ እያለ ይዘገያል ብሎ መስጋት ተገቢ አለመሆኑን ይገልጻሉ። እንደርሳቸው ገለጻ፤ ጊዜው ክረምት በመሆኑ የግንባታ ስካቫተሮችም ሆኑ ሌሎች ትልልቅ ማሽኖች ሲንቀሳቀሱ የባሰ መንገድ ይበላሻል። ስለዚህ ወቅቱ ለአስፓልት መንገድ ግንባታ አይመችም። በዚህ ሳቢያ ብዙ የመንገድ ግንባታዎች ቆመዋል። የሚሠሩት በሰው ጉልበት ብቻ የሚከናወኑ ትንንሽ ሥራዎች ናቸው። በአናፂና በግንበኛ የሚሠሩ የውሃ መተላለፊያ ቦዮች፤ የድጋፍ ግንቦች እንጂ ሌሎች ሥራዎች አይሠሩም። ይህ መሆኑ እየታወቀ ይጓተት ይሆናል ብሎ መስጋቱ ተገቢ አይደለም። የከተማ የመንገድ ግንባታ በወሰን ማስከበር እና በሌሎችም ምክንያቶች ይጓተታል። ይኸኛው ፕሮጀክት ግን ከመጀመሪያ ጀምሮ ክፍለ ከተማውም ዝግጅት አድርጎ ኮንትራክተሩ ከመግባቱ በፊት ቤቶች ፈርሰው ለግንባታው ነፃ ተደርጓል። ተቋራጩ ልክ እንደፈረመ ሥራ ጀምሮ ምንም ሳያቋርጥ እየሠራ ቀጥሏል። አፈፃፀሙም ጥሩ ነው። መንገድ አካባቢን ይቀይራል፤ ልማቱና ዕድገቱም ተያያዥ ይሆናል። ስለዚህ ለጊዜው መንገዱ እስከሚጠናቀቅ የአካባቢዎቹ ነዋሪዎች ከመስጋት ይልቅ መታገስ ይኖርባቸዋል ብለዋል። ይህ የመንገድ ግንባታ ጠባቡን የአስፓልት መንገድ በማሻሻል ከ20 እስከ 30 ሜትር ስፋት ባለው መንገድ ለመተካት የታቀደ ሲሆን፤ ወጪውም ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ይፈጃል ተብሎ ተገምቷል። ከተያዘለት ጊዜ ቀደም ብሎ በ2013 ዓ.ም አጋማሽ ያልቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። አዲስ ዘመን\nነሃሴ 10/2011ምህረት ሞገስ ", "passage_id": "1dcf93aba34442ff7f663b277816db70" }, { "passage": "ከቤቴ ለጉዳዬ ፈጥኜ ለመድረስ ተቻኩዬ ወጥቻለሁ፡፡ ምርጫዬ  ከስቴዲየም  አራት ኪሎ፣ ሥድስት ኪሎ ከዚያም ማሳረጊያው ሽሮ ሜዳ የሆነ የሕዝብ መገልገያ ታክሲ መያዝ ነበር፡፡ እስከ 1፡20 ደቂቃ ባለው ጊዜ ውስጥ ለመድረስ አቅጄ ብወጣም ረጃጅም ሰልፎቹ ተስፋ የሚሠጡ አልነበሩም፡፡ ተደርድረው የቆሙት ሰዎች ከአሁን አሁን ታክሲ ይመጣል በሚል ሥሜት አይናቸው ላፍታ አይቦዝንም፤ያማትራል፤ይቃኛል፤አሻግሮ በመምጫው በኩል ይወረወራል፡፡ ግን አልመ ጣም፡፡ ደቂቃዎች ተቆጠሩ፡፡ በሰልፉ ከተኮለኮሉት ውስጥ አብዛኛውን ቁጥር የሚይዙት የትምህርት ቤት የደንብ ልብስ የለበሱ ተማሪዎች ናቸው፡፡ የሌሎችም ቁጥር ቀላል አይደለም፡፡ከቆይታ በኋላ ተራ አስከባሪ የነበረው ወጣት የኮንትራት አገልግሎት ከሚሠጡት ትናንሽ ታክሲዎች አንዱን ጠራ፡፡ ሹፌሩም እርሱም በላዳ ካልሄዳችሁ በሚል ተሳፋሪውን ይወተውቱት ጀመር፡፡ በሕዝብ ታክሲ ሦስት ብር የሚከፈልበትን በሀምሳ እና በመቶ ብር ካልሄዳችሁ በሚል፡፡ ከኋላ ከተሰለፉት አንዱ ‹‹ለዚህ ሲሉ እኮ ነው የህዝብ ታክሲዎችን እንዲዘገዩ የሚያደርጉት›› አለ በንዴት፡፡ በአብዛኛው ሰው ምንም ምላሽ ሣይሰጥ መጠበቁን ቀጠለ፡፡እየዘገዩ የሚመጡ ታክሲዎችን ተሣፋሪው ተንሰፍስፎ ይቀበላል፡፡ ጢም እስኪሉ ድረስ ይሞላል፡፡ ልክ እንደ እቃ ሰው በሰው ላይ ይደረባል፡፡አሥራ ሁለት አካባቢ ሰው የጭነት ልካቸው የሆኑ ታክሲዎች እስከ አስራ ሰባት ሰው ድረስ ይጭናሉ፡፡ በጫኝም በተሣፋሪም ዘንድ ሕጋዊ እውቅናና ፈቃድ ያለው ሊሆን ተቃርቧል፡፡ ሽርፍራፊ የሣንቲም መልስ ለተሣፋሪ መመለስም እንዲሁ፡፡ ጉዞውን ጨርሶ ሲወርድ ‹‹ሃምሣ ሣንቲም መልስ ሥጠኝ?›› በሚል የጠየቀ ሰው በታክሲ ረዳቱ ብቻ ሣይሆን በተሣፋሪም ጭምር ሊመናጨቅ  ይችላል፡፡ወጣት አለማየሁ ቢተው ወደ ሽሮ ሜዳ ለመሄድ ተሰልፈው የታክሲ መምጣትን  ከሚጠባበቁ ሰዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ በታክሲ አገልግሎቶች አካባቢ የሚስተዋሉ ችግሮች በዋናነት ምን ይሆኑ? ሥንል ትዝብቱን እንዲያካፍለን ጠየቅነው፡፡ እርሱ እንደሚለው፤ የታክሲዎች የረጅም ጊዜ ተጠቃሚ መሆኑን ገልጾ፤ በሕዝብ ትራንስፖርት አካባቢ የሚስተዋለው ችግር በአንድ አካል የሚፈጠርም የሚፈታም አይደለም፡፡ በቅርቡ የተፈጠረም አይደለም፡፡ የቆየ ነው፡፡ አሁንም አለ፡፡ ለመቅረፍም ረጅም ጊዜ ይወስዳል፡፡ወጣት ዓለማየሁ እንደተናገረው፤ በትራንስፖርት ዘርፉ በዋናነት የሚታየውና ኅብረተሰቡን የሚያማርረው ችግር አሰልቺው ወረፋ ነው፡፡ የታክሲ ሥራ በተሰማሩት አካላት ላይም ያለ ታሪፍ መቀበል፣ከልክ በላይ መጫን፣ አቆራርጦ መጫን፣ለተሳፋሪ መብት አለማሰብ ጥቂቶቹ ችግሮች  ናቸው፡፡ በተሳፋሪዎች በኩል እንዲከፍሉ የተጠየቁት ታሪፍ ተገቢ እንዳልሆነ እያወቁ መክፈልና መብትን አውቆ አለማስከበር መሰረታዊ ችግሮች ናቸው፡፡ በመንግሥት በኩል ተራ ለማስጠበቅ ያደራጃቸው፣ መንገድ ሥምሪት ተቆጣጣሪዎችና የትራፊክ ፖሊሶች አካባቢ ሰፊ ችግሮች ይስተዋላሉ፡፡ በጥቅም መጋራት ተሳስረዋል፡፡ ብዙዎቹ የሕዝብ አገልጋይ አይመስሉም፡፡በትራንስፖርት ዘርፉ የተሰማሩ አንዳንድ አካላት ያልተገባ ጥቅም የሚያገኙበትን መንገድ ብቻ የሚያሰሉ ይመስለኛል ሲል ይገልጻል፡፡ መፍትሔውን ከአንድ አካል መጠበቅ አይቻልም፡፡ እንደውም ዋናው ሥርዓት ማስያዝ የሚገባው ተሳፋሪው ራሱ ነው፡፡ ወቅታዊ መረጃ ሊኖረው ይገባል፡፡ ይህ ሲሆን በተገቢው መብቱን ያስጠብቃል ግዴታውንም ይወጣል ብሏል፡፡ከቦሌ እስከ ሜክሲኮ በሚጭን ሚኒባስ የሕዝብ መጠቀሚያ ታክሲ በሾፌርነት በመስራት ላይ ያገኘነው አቶ ታደሰ ወንድሙ እንዳሉት፤ ችግሩ በመጠን ይለያይ ይሆናል እንጂ በሁሉም የሕዝብ መገልገያ የከተማ ትራንስፖርት አካባቢዎች ያለ ነው፡፡ በአንድ ሥራ ውስጥ በርካታው ሕግ የማያከብር ከሆነ ሕግን የሚያከብር በልቶ መኖር፣ ሰርቶ ልጅ ማሳደግና ቤተሰቡን ማስተዳደር ይሳነዋል ሥለዚህ ለሕገ ወጥ ሥራ ይዳረጋል፡፡ ሕግን አክብሮና ፈርቶ ከሚኖርና ከሚሰራው ይልቅ በድብብቆሽ የሚሆነው ይበልጣል፡፡ተገልጋዩም ወዶና ፈቅዶ አይደለም በትርፍ የሚጫነው፡፡ መንገድ ይጨናነቃል፡፡ ካሰበው ላይደርስ ይችላል፡፡ ያለው አማራጭ ሕገ ወጥም ቢሆን የተሻለውን ለመምረጥ ይገደዳል፡፡ እውነተኛ ለውጥ የሕዝቡ ወይም የተገልጋዩ አስተሳሰብ ሲለወጥና ትራፊክ ፖሊስ፣ ሾፌሩ፣የመንግሥት አካላትና ሌላውም የሕዝብ አገልጋይነት ሥሜቱ ከዕለታዊ ጥቅሙ በልጦ ራሱን ለሕዝብ እስከመስጠት ካላሰበ ችግሩ የሚቀረፍ አይመስለኝም ሲል ተናግሯል፡፡የትራንስፖርት ሚኒስቴር በበኩሉ የዚህ አይነት ችግሮች መኖራቸውን አውቆ በተደጋጋሚና በየጊዜው የማሻሻያ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑን ይገልጻል፡፡ ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ በቅርቡ የተቋሙ የመቶ ቀን ዕቅድ አስመልክተው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደተናገሩት፤ በየደረጃው በማስተማርና ግንዛቤ በመፍጠር፣መመሪያና የአሰራር ደንቦቹን በማሻሻል፣ በአዲስ አበባ የሚስተዋለውን የትራንስፖርት ችግር በተለይም በመንገድ ግንባታና ጥገና፣ በመንገድ ትራንስፖርት ዙሪያ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን ጭምር ለመቅረፍ መቶ ቀን ተቆርጦ እየተሰራ ነው፡፡ችግሮቹ ከኅብረተሰቡ የእለት ከእለት ተግባር ጋር የተቆራኙ በመሆናቸው የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆነዋል፡፡የሕዝቡን እሮሮ ጆሮ ሰጥቶ በማድመጥና በመቅረፍ፤ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማታችን እንዲፋጠን ያለመ ተግባር በመቶ ቀናቱ ይከወናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡በትራንስፖርቱ ዘርፍ በተለይም የሕዝብ ምሬትና እሮሮ በሚበረክትባቸው አካባቢዎች ያሉትን ችግሮች የመቶ ቀናቱ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እቅድ መፍትሄ ያስገኝ ይሆን ? ስንል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የትራንስፖርትና ኮንስትራክሽን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑትን አቶ አሸናፊ ጋዕሚ ጠይቀናቸዋል፡፡  እርሳቸውም በበኩላቸው፤ቋሚ ኮሚቴው የተግባር እቅዱን አንድ በአንድ የገመገመው መሆኑን ገልጸው ክፍተቱንና መካተት የሚገባቸውን ጉዳዮች በተገቢው አመላክቷል ብለዋል፡፡በመሰረተ ልማት ማስፋፋት፣ በመንገድ መዘጋት በተለይም በመግቢያና በመውጫ ሰዓት፣ ከቀላል ባቡሩ ጋር በተያያዘ የሚነሱ ችግሮችን ቋሚ ኮሚቴው በእቅዱ ላይ የተመለከታቸው ጉዳዮች ናቸው፡፡ ነገር ግን የተቀመጠው እቅድ እንደ ትራንስፖርት አቅርቦትና ሥምሪት ያሉ ችግሮችን በተገቢው የሚፈታ አለመሆኑ ተገምግሟል፡፡ በመሆኑም ከቀላል ባቡሩ የመለዋወጫ አቅርቦት ጋር ያጋጠመውን ችግር ጨምሮ ሌሎቹም በዚህ በጀት ዓመት መፍትሔ እንዲያገኙ ቋሚ ኮሚቴው አቋም ይዟል ብለዋል፡፡ከዚህ ጋር አያይዘውም በምክር ቤቱ የታመነባቸውን መመዘኛዎች ተከትለው በዘርፉ  ክትትልና ድጋፍ የሚያደርጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ መመዘኛዎቹ ምንድን ናቸው? በምንስ ላይ ያተኩራሉ? ብለን ላነሳንላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፤ውጤትን መሰረት ያደረገ ምዘና ይካሄዳል፡፡ በዋናነትም በባለብዙ ዘርፍ ተግባራት፣በመንግሥት የፋይናንስ በጀት አጠቃቀምና  በኦዲት በተሰጡ አስተያየቶች ተፈጻሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ የተሰሩና ያልተሰሩ ተግባራትን ለይቶ ይፈትሻል፡፡ በመመዘኛዎቹም መሰረት እንደየጥረታቸው ከፍተኛ ፣መካከለኛና ዝቅተኛ በሚል ይለያል፡፡ ለእያንዳንዱ  እንደየጥረቱ እውቅናም ይሰጣል፡፡ ይህ ሲሆን የህዝብን ብሶት አዳምጦ የሚሰራውና የማይሰራው ይበልጥ ይለያል፤አድሏዊ አሰራሩም ይቀረፋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 18/2011በሙሐመድ ሁሴን", "passage_id": "721325a4f2fd65333115994dc090e4c9" }, { "passage": "1953 ዓ.ም ከአዲስ አበባ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው አቃቂ ከተማ ጋርዱባ 06 አካባቢ ነበር የተወለደው፤ በልጅነቱ ፈጣንና አስተዋይ እንደነበር ይነገራል። የታዳጊው ሁኔታ በቤተሰቦቹም ሆነ በአካባቢው ሰዎች ዘንድ ከፍተኛ ደረጃ እንደሚደርስ ተስፋ እንዲጣልበት አድርጎታል። የታዳጊው ብሩህ አዕምሮ በቀለም ትምህርት ቢታገዝ ደግሞ እኛንም አገሩንም ያኮራል ብለው አስበዋል።ተሻጋሪ ተስፋ ማድረግ ብቻም ሳይሆን በአካባቢው በሚገኘውና ፊት አውራሪ በሚባለው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት አስመዘገቡት። በአስኳላ ውሎው በጥሩ ተማሪነትና በፈጣን ሯጭነቱም ጭምር ለመታወቅ የቻለው የትናንቱ ታዳጊ የቀድሞ አትሌት ሸምሱ ሀሰን ነው። የትምህርት ቤት ቆይታውን እየወደደው ቢመጣም፤ የቤተሰቦቹ ሁኔታ ግን ሊያራምደው አልቻለም።የቤተሰቡን ችግር ለማቃለል እርሱ ቢያንስ ራሱን ማስተዳደር ቢችል ትልቅ ብርታት እንደሚሆናቸው ሃሳቡ ነበር። በቀለም ትምህርቱ ብዙ ርቀት መጓዝ ቢያልምም አልቻለም። ከቤተሰብ ጥገኝነት ለመላቀቅ ከስድስተኛ ክፍል አቋርጦ ወደ ውትድርና ለማቅናት ወሰነ። አደረገውም፤\nሸምሱ፤ በብሄራዊ ውትድርና ውስጥ ለስልጠና የተመደበለትን ጊዜ አጠናቀቀ። አዲስ አበባ ማዕከላዊ ዕዝ ተመድቦ የህይወቱን ሌላኛውን ምዕራፍ ማጣጣሙን ያዘ። ሸምሱ የልጅነት ህልሙ በዚህ መልኩ እንዲሆን ፍላጎት ባይኖረውም፤ የሆነውን ግን ተቀብሎ ቀጠለ። በትምህርት ቤት ውስጥ ፈጣንና ተስፈኛ እግሮቹ በጦሩ ቤት ያለውን ቆይታ ወደ ስፖርት እንዲገባ አስችለውታል። በማዕከላዊ ዕዝ ውስጥ የሚያደርገው የስፖርት እንቅስቃሴ በጦሩ ውስጥ ለእጩነት አበቃው።የእርሱን የዕጣ ጎዳና በአትሌቲክሱ ያደረገው አጋጣሚም በዚህ መልክ ተወለደ። የስፖርት አጀማመሩ በ1500 ሜትርና በ800 ሜትር ነበር። በእነዚህ ርቀቶች በተለያዩ ውድድሮች በመሳተፍ ሁለት ጊዜ ሦስተኛ ደረጃ ይዟል። አትሌቱ እግሮቹን ያሟሸው በእነዚህ ርቀቶች ይሁን እንጂ፤ እስከመጨረሻ የዘለቀው ግን በእርምጃ ውድድር ነበር። አጋጣሚው እንዲህ ነበር። አንድ ቀን በማዕከላዊ ዕዝ ስፖርት ውስጥ ብዙም ባልተለመደው የእርምጃ ሩጫ እንዲሳተፍ ይጠየቃል። ጥያቄው ለተሳትፎ ያህል የነበረ ቢሆንም፤ በውድድሩ ባለድል መሆን ቻለ። በ1974 ዓ.ም በአገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደ ውድድር ተሳትፎ አሸናፊ ሆነ። አትሌቱ በእርምጃ ውድድሩ አሸናፊነቱ በአሰልጣኞቹ የመመረጥ እድል አገኘ። አገሩን ለማስጠራት በብዙዎች ዘንድ ተስፋ እንዲጣልበት ያደረገም ነበር።በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ውስጥ ስማቸው ተጠቃሽ ከሆኑት መካከል ሻለቃ ባሻ ዋሚ ቢራቱ የሸምሱን ተስፈኝነት ከመሰከሩ ታላላቅ የስፖርት ሰዎች መካከል ተጠቃሽ ነበሩ። የእርሱ የእርምጃ ሩጫ የተለየ ክህሎት በመገንዘብና አርቀው በማስተዋል በደንብ እንዲሰራ ይመክሩት ነበር። ይህም በስፖርቱ ጉዞውን የጀመረበትን ርቀት በመተው ወደ እርምጃ ሩጫው ብቻ እንዲያዘነብልም ጭምር ሀሳብ እስከ መለገስ ደርሰዋል። እርሱም በእርምጃ ስፖርት ውድድር መጽናቱን ነው የሚናገረው፤ አገራችን በእርምጃ ውድድር ግን በማትታወቅበት ሁኔታ ገፍቶ ለመሄዱ የዋሚ ቢራቱ ምክር ለእርሱም ብቻም ሳይሆን በወቅቱ ለነበሩት ወንዴ ጦሬ፣ ተከስተ ዮሃንስ፣ ጥላሁን ሸገና በጽናት እንዲቆዩ ያደረገ ጭምር እንደነበር ሸምሱ ያስታውሳል።እርሱ እንደሚለው፤ «በአገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄዱ ውድድሮች እይታ ውስጥ ለመግባት የቻልኩበትን አጋጣሚ መፍጠር ቻልኩ። ይህ ሁኔታ ደግሞ የተሳትፎዬን ደረጃ ተሻጋሪ የሚያደርግልኝን አጋጣሚ ይዞ ብቅ አለ። በአገር ውስጥ የእርምጃ ውድድር ብቃቴ ተለክቶ በዓለም አቀፍ መድረክ ታጨሁ። በ1975 ዓ.ም በኬኒያ ናይሮቢ ላይ በተካሄደው የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ውድድር ላይ በእርምጃ ሩጫ ለአገሬ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ ማምጣት ቻልኩኝ። በዚህ ድል ለራሴም ሆነ ለእናት አገሬ አኩሪ ድል ያመጣሁበት ትልቅ የህይወት አጋጣሚዬ ነበር። ይህም አሸናፊነት ገና ጅምር እንጂ የሚያበቃ እንዳልሆነም ለራሴው ቃል የገባሁበት አጋጣሚም ነው»።የልጅነት ህልሙ መስመሩ በስፖርት ውስጥ ይሆናል የሚል ቅንጣት ያህል ፍላጎት ያልነበረው ወጣቱ ከስኬት ወደ ስኬት መሸጋገር ጀመረ። ከአንድ ዓመት ቆይታ በኋላ ግብጽ ውስጥ የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በመሳተፍና በአንደኝነት በማጠናቀቅ የወርቅ ሜዳሊያ እንዳሸነፈ ይናገራል። ከዚህ በኋላም፤ በተለይ በኬኒያ እና በግብጽ በተዘጋጁ ውድድሮች ላይ በተደጋጋሚ የመሳተፍ እድል እንደነበረው ያስታውሳል። «በኬኒያም ሆነ በግብጽ በተካሄዱ ውድድሮች አሸናፊ መሆን ችያለሁ። ኬኒያ ውስጥ በተካሄዱ ውድድሮች አራት ጊዜ ተሳትፌያለሁ። በሁሉም አንደኛ ሆኜ ነው ያሸነፍኩት፤ በግብጽ በተመሳሳይ የመሳተፍ አጋጣሚዎች ነበሩኝ። ከነበሩት አራት ውድድሮች በአንዱ ብቻ ሁለተኛ ስወጣ የተቀሩትን በአሸናፊነት ነበር ያጠናቀኩት» ይላል ሸምሱ።የወጣቱ የድል ጉዞ ከፍ በማለት በአራት ዓመት አንዴ በሚዘጋጀው ኦል አፍሪካ ጌምስ ላይ ሦስት ጊዜያት የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት ለመሆን በቅቷል። ፈጣኑና ትንታጉ አትሌት የድል አድማሱን ከፍታ ከአህጉር አፍሪካ ተሻግሮ ለኦሎምፒክ ውድድር ወደባርሴሎና መጓዙን የሚያስታውሰው ሸምሱ በውድደሩ አምስተኛ ደረጃ በመያዝ ነበር ያጠናቀቀው፤ ሩሲያ በመጓዝ ደግሞ ስምንተኛ ወጥቶ ማጠናቀቁን ያስታውሳል። «በጊዜው እኔ ትኩረት የማደርገው ሰዓቴን ማሻሻሌን ነው» ይበል እንጂ፤ አገራችን ብዙም ባልታወቀችበት የእርምጃ ውድድር በድሉ ከአገር ውስጥ እስከ አህጉር፤ ከዚያም እስከ ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች የተሻገረ ስኬት ያስመዘገበ የአገር ባለውለታ ነው። ሸምሱ በአትሌቲክሱ እያደገ የመጣው ውጤቱ በማዕረግ የታጀበም ሲሆን፤ ከአስር አለቅነት እስከ ሻለቃነት የደረሰ ነበር።የሸምሱ የስፖርት ጉዞው ብቻም ሳይሆን የህይወት ኡደቱ ከ1974 እስከ 1992 ወርቃማ ዓመታት ናቸው ለማለት ያስደፍራል። አትሌቱ በእነዚህ 18 ዓመታት በስፖርቱ እራሱንም ሆነ አገሩን አስጠርቷል። ቤተሰብ በማፍራትም ህይወቱን በደስታ አጣጥሟል። የዚህ ሁሉ ታሪክ ባለቤት የሆነውና የቀድሞው የእርምጃ ውድድር ባለድሉ ጎልማሳ የአዕምሮው ሁኔታ በመታወኩ ምክንያት እጅና እግሩን አጣጥፎ ከቤት ለመዋል ተገደደ። ከእርሱ በኋላም በመስኩ አሸናፊ ሆኖ የወጣ አትሌት አለመኖሩን ባገላበጥናቸው የተለያዩ መረጃዎች ለመገንዘብ ችለናል። በአሁኑ ወቅት ግን ለአገሩ የሰራው ገድል ተረስቶ፤ እርሱም አስታዋሽ አጥቶ በአዕምሮ ህመም እየተሰቃየ ይገኛል። ከኬኒያ እስከ ሩሲያ በእርምጃ ብቻ ሜዳሊያዎችን ያስገኙ እግሮች፤ የሚመራቸው ጤናማ አዕምሮ አጥተው ተሳስረው ቁጭ ለማለት ተገድደዋል። በከባድ ህመም ውስጥ ከመሰቃየት በቀር አማራጭ ያጣው ሸምሱ፤ በተለያዩ ውድድሮች አሸናፊ ቢሆንም ዘመኑ ስፖርተኞች እንዲህ እንደዛሬው የማይሸለሙበት ነበርና በስፖርቱ ተጠቃሚ መሆን እንዳልቻለ ይናገራል። «በአሁን ሰዓት አላውቅም እንጂ እኔ በነበርኩበት ጊዜ የገንዘብ ሽልማት ሳይሆን የአበባ ጉንጉን ነበረ ወደ አገራችን ስንመለስ የሚበረከትልን፤ መንግሥት በእርምጃ ውድድር አሸንፌ ስመጣ ይሰጠኝ የነበረው ከብር 1500 ያልበለጠ ገንዘብ ነበር» በማለት በጊዜው ከስፖርቱ ተጠቃሚ እንዳልነበር ያስታውሳል። የአገር ባለውለታ የሆነው የቀድሞው አትሌት ሸምሱ ሀሰን በስፖርቱ ያገኘው ጥቅም ያለመኖሩ ብቻም ሳይሆን ጤናው መታወኩ ደግሞ ቤተሰብ ይዞ በችግር ለመቆራመት እንደዳረገው ይናገራል።አትሌቱ ሲጀመር ስምንት መቶ፤ በአሁኑ ወቅት ደግሞ 1400 ብር በሚያገኛት የጡረታ ገንዘብ በችግር መኖር እጣው ሆኖበታል። የተገኘውን ሥራ ለመስራት እንዳይችል ህመሙ ጋሬጣ ሆኖበት የሚያገኛትን የጡረታ ገንዘብ አጠገቡ ከሚገኙት ባለቤቱና ሁለቱ ልጆቹ ጋር በመቋደስ የችግር ህይወት ለመግፋት ግድ እንደሆነበት ይገልጻል። የሥራ ፍላጎት ቢኖረውም የህመሙ ሁኔታ ሰርቼ እንኳን ለመብላት እንዳልችል አድርጎኛል ሲል ይናገራል። በአንድ ባንክ ውስጥ በጥበቃ ስራ ተቀጥሮ መስራት ቢጀምርም የጤናው ሁኔታ የሚያሰራ አይደለምና መቀጠል አልቻለም። የመንፈስ ከፍታው በዚህ ደረጃ የሆነው ሸምሱ ከአንዴም ሁለት ሦስቴ የተለያዩ ስራዎችን ለመስራት ጥሯል። የእርሱ ሁኔታ አላላውስ ያላት ባለቤቱም የህይወት አጋሯን በቤት ውስጥ ሆና ከማስታመም በስተቀር ወጥታና ሰርታ ተጨማሪ ገቢ ለማምጣት እንዳትችል ሳንካ እንደፈጠረባት ሲቃ እየተናነቀው ይናገራል።ሸምሱ፤ የጤናው መቃወስ ይሄንን ጠንካራ የመንፈስ ከፍታውን የናደበት ሲሆን፤ «አሁን ካለሁበት የችግር አረንቋ እንድወጣ እጃችሁን ዘርጉልኝ» ሲል ጥሪውን ለአገሩ ህዝብ ለማቅረብ ተገድዷል። ለርዳታ ጥያቄ የተዘረጋውን እጁን ተከትሎ የሁለት ኢትዮጵያዊያን ወገኖቹን ምላሽ እንዳገኘ አጫውቶናል።«እስካሁን የሁለት ኢትዮጵያዊያን ወገኖቼን መጎብኘት አስገኝቶልኛል። አንዷ ሁለት ሺ ብር አንደኛዋ ደግሞ አንድ ሺ ብር ሰጥተውኛል። ይሁን እንጂ፤ የእነዚህ ወገኖች ድጋፍ አሁን የደረሰበትን የጤና ችግርና ባዶውን ማጀት ለመሙላት አይችልም። አሁንም ጥያቄ የሆነብኝ ነገር አትሌቲክስ ፌዴሬሽኑ ስለምን በእኔ ላይ ጨከነ? ምን በድየው ይሆን!? ሊያስታውሰኝ እንዴት አቅም አጣ? ምን ላይ ወደክ እንኳን አላለኝም። እንዴት ነህ መባሉ የተሰበረን መንፈስ ያክማል። የገንዘብ ድጋፍ ይቅርና እስካሁን የት ወደክ አላለኝም። ይህ ሁሌም ጥያቄ የሚያጭርብኝና የዘወትር ብስጭቴ ነው» ሲል ሃሳቡን ይቋጫል።አገራችን ብዙም ስሟ በማይነሳበት በእርምጃ ውድድር በግሉ ጥረት ከፍ ብሎ የነበረውን የቀድሞ አትሌት ሸምሱ ሀሰን በአሁን ወቅት ካጋጠመው የጤና ቀውስና ከገባበት የችግር አረንቋ እንዲወጣ ድጋፍ ሊደረግለት ይገባል። በአሁን ወቅት በአዕምሮ ህመም መሰቃየት ብቻም ሳይሆን በጡረታ በሚያገኛት አንድ ሺህ አራት መቶ ብር ስድስት ቤተሰብ እያስተዳደሪ እንደሚገኝ ተናግሯል። ሸምሱ እንዲህ እንደዛሬው ህይወት ፊቷን ሳታዞርበት የጤናው ሁኔታም ባልተቃወሰበት ወቅት በአትሌቲክሱ በተወዳዳሪነት ብቻ ሳይሆን በአሰልጣኝነት አገልግሏል።የአገር መከላከያ ሰራዊት አባል በመሆንም ለአገሩ ለመድማትና ለመሞት እራሱን አሳልፎ ሰጥቷል። ሸምሱ አነሰም በዛም እናት አገሩን ለማገልገል የተቻለውን ያህል ርቀት እንደመሄዱ፤ ከዛሬው ሰቆቃው እንዲወጣ ሁሉም የበኩሉን ሊያግዘው ይገባል። በተለይ፤ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቀድሞውን አትሌት ማስታወስ ይጠበቅበታል። የአገር ባለውለታ የሆነውና የተረሳው የቀድሞው አትሌት የዚህ ባለታሪክ ሆኖ ይቅረብ እንጂ፤ አስታዋሽ የማጣት ቁጭት፤ የጤና መቃወስ፣ የወገን አይዞህ ባይነት ማጣት እንደ ሸምሱ ሁሉ በበርካታ የአገር ባለውለታዎች ላይ የደረሰ በደል ነው። በጉብዝናቸው ወቅት ለአገራቸው ታሪክ የሰሩትን በቁም እያሉ ለመርዳትና ለማዳን ርብርብ አለማድረግ ሲያልፉ ቁጭትን ሲያጭር በተደጋጋሚ ይስተዋላል። በተለያዩ ዘርፎች ተሰማርተው የነበሩ የአገር ባለውለታዎችን ተረባርቦ በህይወት ለማቆም ሳይሆን ከሞቱ በኋላ ኃውልት ለማቆም መሯሯጥ መገለጫችን ይመስለኛል።የአገር ባለውለታዎችን ማሰብ ጥቅሙ ለአገር ነው። በተለያዩ ዘርፎች ለአገር የአቅማቸውን የሚበረክቱ ጀግኖችን ማፍራት ብቻ ሳይሆን፤ ከከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ጀግኖችን የመርሳት አባዜም ባለቤት ነን። በተጨማሪም በቁም ሳለ ከችግሩ፣ ከበሽታው ለማዳን ርብርብ ከማድረግ ይልቅ ለመቅበር የሚደረገው ርብርብ «አጃኢብ»ያሰኛል። ለዚህም ትልቁ ማሳያ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ነው። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በአትሌቲክሱ ብዙ አስተዋጽኦ ያደረጉ ጀግኖችን ማስታወስና መዘከር የማይሆንለት እንደሆነ በተለያዩ አጋጣሚዎች ታዝበነዋል። በተለያዩ አለም ዓቀፍ ውድድሮች ላይ በእርምጃ ውድድር ሜዳሊያዎችን ያገኘው የቀድሞው አትሌት ሸምሱ፤«አትሌቲክስ ፌዴሬሽኑ ስለምን በእኔ ላይ ጨከነ? ምን በድየው ይሆን? ሊያስታውሰኝ እንዴት አቅም አጣ?» ሲል ቁጭቱን ሲገልጽ ታዝበናል።በኦሊምፒኮችና በዓለም ሻምፒዮናዎች ላይ ኢትዮጵያን ወርቅ በወርቅ ያደረጉ ጀግኖች አትሌቶች ዋና አሠልጣኝ የነበሩት ዶ/ር ወልደ መስቀል ኮስትሬን፣ ሻምበል ምሩፅ ይፍጠርን በህይወት ሳሉ በመርሳት፤ ህይወታቸው ካለፈ በኋላ ኃውልት ለማቆም ሲታትር ነበር። ይህም ፌዴሬሽኑ አንጋፋዎቹ የአገር ባለውለታዎች ህይወታቸው ሳይቃወስ ድጋፍ ከማድረግ ይልቅ፤ ሲሞቱ ለሙሾና ለሀውልት ከመሮጥ አባዜው ዛሬም እንዳልተላቀቀ ከተለያዩ ወገኖች የተሰነዘረ ትችት ነው።ፌዴሬሽኑ ትናንት ከሰራው ስህተት ከመማር ይልቅ፤ ሌላ ታሪካዊ ስህተት ለመፈጸም እደማይመለስም አብሮ የተነሳ ሃሳብ ነበር። በአትሌቲክስ ፌዴሬሽን በኩል የአገር ባለውለታዎችን እጀ ሰባራ የማድረጉ ስንኩሉ ልምድ በስፖርቱ ብቻም ሳይሆን፤ በተለያዩ የሙያ መስኮች የዜግነት ግዴታቸውን የተወጡ የአገር ባለውለታዎች የመደገፍ ልምዱ ኢምንት ነው። የአገር ባለውለታዎቹ ምናልባትም የሚታወሱት ወይ ታመው አልጋ ሲይዙ፣ ወይም ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ ነው፡፡ አንጋፋዎች ሲዘነጉ ተከታዩ ትውልድ ተስፋ ይቆርጣል፡፡ ለባለውለታዎች ዕውቅና ለመስጠት በሕግ ማዕቀፍ የሚመራ የሜዳሊያና የኒሻን፣ በአገልግሎት ዘመን መጠን የሚበረከት ሽልማትና የምሥጋና ሥነ ሥርዓት ሊኖር ይገባል፡፡ አገርን በፍቅር ማገልግል የውዴታ ግዴታ ቢሆንም፣ አስመስጋኝ ተግባር ላከናወኑ አኩሪ ዜጎች ዕውቅና መስጠት የአገር ባህል መሆን ይገባል ባይ ነን፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2011ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "7aa562443d19f2caff6421e1e336ad9b" }, { "passage": "ለሥራ በተለያዩ አገሮች የሚጓዙት ቤተልሔም ነጋሽ፥ ገላጭ በሆነው ጽሁፋቸው የቱሪስቶች መናኸሪያ የሆነችውን የኬንያዋን የባሕር ዳርቻ ከተማ ሞምባሳን ያስቃኙናል፤ በጎ በጎውን ብቻ ሳይሆን ሥጋት ናቸው ያሏቸውንም ጉዳዮች ከትበዋል።የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ ሞምባሳ ቀጥታ በረራ ያደርጋል። ኢቲ 322 ከዚህ ተነስቶ ወደ ሞምባሳ የሚሔደው ሲሆን ኢቲ 323 ወደ አዲስ አበባ የሚመላለሰው ነው። የሔድኩት እሁድ ቀን ቢሆንም ከመንገድ ላይ ትራፊኩ ጀምሮ የኤርፖርቱ ውስጥ ባልተለመደ መልኩ ተጨናንቆ ነበር። ሻንጣ ከሚረከቡበትና የመሳፈሪያ ቅጽ ከሚሰጡበት ጀምሮ እስከ ኢሚግሬሽኑ ያለወትሮ ረጅም ሰልፍ ሆኖ በመከራ ዘለቅን። የኢሚግሬሽን ኦፊሰሩ ከሳምንታት በፊት ወደ ጆሃንስበርግ ስሔድ እንደተጠየቅኩት ደከም ባለ የድምጽ ቅላፄ እስቲ የቤተሰብሽን ሥልክ አላለኝም። በወቅቱ ያንን ጥያቄ መጠየቄ የፈጠረብኝን ድንጋጤ አስታውሳለሁ። ለካ እንደወጡ መቅረትም አለ! አልፎ አልፎ አስታዋሽ ቢያስፈልግም ድንገት ሲጠየቁ ብዙ ያሳስባል።ከአዲስ አበባ ሞምባሳ ያለው የ2፡20 ደቂቃ አካባቢ በረራ ብዙም ሳይቆይ ነበር የተጠናቀው። በነገራችሁ ላይ በኋላ ከሌሎች አገራት የመጡ የሔድኩበት ሥልጠና ተሳታፊዎች ሲነግሩኝ ሞምባሳ ለመምጣት ከየአገሮቻቸው ከተሞች ሌሎች ቦታዎች ሔዶ ከዚያ በናይሮቢ በኩል ማለፍን ይጠይቃል። ከባማኮ ሞምባሳ ለመምጣት በፓሪስ በኩል ማለፍ አልታያችሁም። በቀጥታ እዚህ ነው የመጣነው ስንል አላመኑም። እንዴት ይላሉ ግማሾቹ። አየር መንገዳችን! ነው መልሳችን።\nሥሜን ከነአባቴ የያዘ ‘ፕላካርድ’ ይዞ እየጠበቀኝ ቀጥ ብዬ ወደ እሱ ሔድኩና እኔ ነኝ ካልኩት በኋላ አንቺ ነሽ? ብሎ አረጋግጦ ፣ የምገፋውን ጋሪ ተቀብሎ ወደ መኪና ማቆሚያው እየመራ ወስዶ መኪናው ጋር ሲያደርሰኝ\n“ራሷ የኔ መኪና” አልኩ ወሬ ለመጀመር – ‘አይስ ብሬከር’ ይላል ፈረንጅ\nየመጀመሪው ጥያቄ ሁሌም ሊያጋጥም የሚችለው የሥም ጉዳይ ነበር\n“ሥምሽ ይገርማል፣ የየት አገር ሰው ሥም ነው ይሔ – ወንድ ነው ሴት? እያልኩ እያሰብኩ ነበር” አለኝ።\n“እንዴ ኢትዮጵያዊ መሆኔን አላወቀወክም?” አልኩ በማዳነቅ\n“ኢትዮጵያዊ ነሽ – በፍፁም አላወኩም” አለ\nአገሬ ሥሜም የአባቴም ሥም የተለመደ ነው አልኩት\nጆሴፍ ከኬንያዋ የወደብ፣ የሕንድ ውቅያኖስ ዳርቻ ሞቃታማ ከተማ አውሮፕላን ማረፊያ ለሳምንት በተከራየሁት የቢች ዳር ‘አፓርትመንት’ የተዘጋጀልኝ ሾፌር ነበር።ከኤርፖርቱ ሳንወጣ የተከራየሁት ስቱዲዩ አፓርትመንት ባለቤት ደወለና ሊያናግረኝ እንደሚፈልግ ነግሮት ሥልኩን አቀበለኝ\n“እንዴት ነሽ? ደህና ገባሽ ወይ፣ እንኳን ደህና መጣሽ” አለ የሳምንት አከራዬ\nአመስግኜ ደህና መግባቴን ገልጬ እሱም ገብቼ ተረጋግቼ ቀስ ብዬ ክፍያ መፈፀም እንደምችል ነግሮኝ ተለያየን።የደንበኛ መስተንግዷቸው ሁሌም ይደንቀኛል። ምነው የኛዎቹ ይህቺን ቢኮርጁ ብዬ ሳስብ ባለፈው ወር ጎንደር ለሥራ ስንሔድ የሆነውን አስታወሰኝ።\nታዬ በላይ የተባለ ሆቴል በሥራ ባልደረባዬ በኩል ተደውሎ ክፍል ሲያዝልን፥ ከአውሮፕላን ማረፊያው ትራንስፖርት እንደሚዘጋጅልን ጭምር ተነግሮን ነበር። ገና ከአዲስ አበባ ሳንነሳ ቀኑን ስንሠራ ውለን አመሻሸ ላይ ለመሔድ ያሰብነው ቀርቶ በረራችን ከ12፡40 ወደ 10፡25 መቀየሩ ሲነገረን እኛም ይህንኑ ለሆቴሉ አሳውቀን ነበር። ወደ አውሮፕላናችን ስንገባ ቀጥታ ጎንደር ሳይሆን በአክሱም በኩል እንደምንሔድ ሲነገረንም እንዲሁ የሰዓት ለውጡን ተናግረን ሳለ ኤርፖርት ስንደርስ የተባለው ትራንስፖርት አልነበረም። ብንደውልም ስንደውልበት የነበረው ሥልክ አልተነሳም። በታክሲ ደርሰን ለምን ስንልም ማንም ከቁብ አልቆጠረን። በዚያ ላይ ወደ አዲስ አበባ ለመመለስ የኤርፖርት ትራንስፖርት ጥያቄ ሳቀርብ እንዲሁ ችላ ተብዬ አንድ ፈረንጅ መጥቶ ገላገለኝ። መሔዴን ብቻ ስለፈለኩ እኔን አባ ከና ሳይሉ ለእሱ ማሽቃበጣቸውን ብዙም ጉዳዬ አላልኩት።ወደ ሞምባሳ ስንመለስ በመንገድ ያንንም ይሔንንም ስናወራ ወሬያችንን ያቋርጠን የነበረው የሚኒ ባስ ታክሲዎች እብደት ነበር። አዲስ አበባ ምን እብድ ታክሲ ነጂ አለ ጎበዝ! የባሰ አለ አገርክን አትልቀቅ ይሔኔ ነው።በዛች አንድ መኪና የማታስኬድ ጠባብ መንገድ ጥግ ጥጉን ደርበው ይመጡና ድንገት አፍጫውን ጥልቅ ለማድረግ ሲሞክሩ አንዴማ ገጩን ብዬ ልቤ ስንጥቅ!\nመንገድ ብትሉ ከኤርፖርቱ ወደ ከተማው የሚወስደው መንገድ ሁኔታ ትንሽ ያሳስባል። ሹፌሬ የፍጥነት መንገድ እየተሠራ ነው ቢልም በየቦታው ያለው ግማሹ በጎርፍ ተወስዶ የተቦዳደሰ መንገድ ሌላው በጅምር የቀረ ነው።ሚኒባሶቹ ተረጋግቼ እንዳልቀመጥ ሲያደርጉት የኔውም አገር ታክሲዎች እንዲህ ናቸው አልኩት ጆሴፍን። ተገረመ!\nየሚኒባስ እብደት ጉዳይ አፍሪቃዊ ነው ብለን ደመደምን።ሌላ አፍሪቃዊ ነገር ያየሁት ለሾፌሬ ባላወራውም – አንዱ ወጣት ድልድይ ሥር ቆሞ ሽንቱን ሲያንፎለፉለው ማየቴ!\nየሞምባሳን የውቅያኖስ ዳርቻ በጽሁፍ መግለጽ መሞከር ድካም ነው። መጨረሻው የማይታየው ሰማያዊው የሕንድ ውቅያኖስ፣ በተለይ ወደ ማታ ላይ፣ ቀኑን ሙሉ ደርቆ በእግር መንሸራሸሪያ ሰፊ አሸዋ የነበረው መሬት መሔጃ እስኪታጣ ውሃው ሲናወጥ፣ አረፋ ደፍቆ የሚመጣው ሞገድ\nባለኅብረ ቀለሟ፣ ደማቋ ሞምባሳ የአገሪቱ የኢኮኖሚና የባሕል ማዕከል ናት ይሏታል። ከተመሰረተች ክፍለ ዘመናት በማስቆጠርም ከኬንያ ግዛቶች ቀዳሚዋ እንደሆነች መረጃዎች ይጠቅሳሉ። ከክርስቶስ ልደት በፊት በ900 ዓመተ ዓለም እንደተመሰረተች ሲነገር ቅኝ ገዥዎች የመጡት ግን ከ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በኋላ ነው። በቅድሚያ ፖርቱጋል (1593- 1698 እ.ኤ.አ) ቀጥሎ የኦማን ኢማማቶች (1698–1728) ከዚያም በድጋሚ የፖርቹጊዝ ኢምፓየር (1728–1729) የኦማን ኢማማቶች (1729–1824) ተፈራርቀውበታል። የብሪታኒያ ኢምፓየር (1824–1826) ገዝቷል የመስካትና ኦማን ሱልጣኔቶች (1826–1887) በመካከል ገብተው ብሪታኒያ በድጋሚ “ብሪቲሽ ምሥራቅ አፍሪካ” ግዛት (የአሁኗ ኬንያ አካል ሆና) ነፃ እስከ ወጣችበት 1887–1963 ቆይታለች። ሞምባሳ ከናይሮቢ ቀጥላ የኬንያ ኹለተኛዋ ትልቅ ከተማ ስትሆን የከተማው ነዋሪ 1.5 ሚሊዮን ይገመታል። በኬንያ ግዛት አጠራር መሠረት የሞምባሳ አውራጃ (ካውንቲ) መቀመጫ ስትሆን ከናይሮቢ ሌላ የመንግሥት መቀመጫ (ቤተ መንግሥት – ስቴት ሃውስ) ያለባት ከተማም ናት።የከተማዋ ዋነኛ የመገበያያ ማዕከላትና ከላይ የጠቀስኩትን ቤተ መንግሥት ጨምሮ ጥሩ የሚባሉ የመኖሪያ ሥፍራዎችን፣ የመንግሥት ቢሮዎችንና ሆቴሎችን የሚይዘው የሞምባሳ ክፍል (ደሴት) ኪዚነጎ በመባል የሚጠራ ሲሆን ዙሪያውን የከበቧትና የባሕር ዳርቻዎቿን ይዞ ሰሜናዊ፣ ደቡባዊ የባሕር ዳርቻዎች ዋናው የሞምባሳ መሬት (Mombassa Mainland) በሚል ተከፋፍላለች።ሞምባሳ ለመድረስ በሞይ ዓለም ዐቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ በኩል በአየር መግባት ዋነኛው ሲሆን በአውቶብስ ከዋና ከተማዋ ናይሮቢ የስምንት ሰዓት ጉዞ እንደሚጠይቅ (አምስት መቶ ሃያ ኪሎ ሜትሮች አካባቢ) ተነግሮኛል። በቅርቡ እድሳት የተደረገለት የናይሮቢ ሞምባሳ የባቡር ትራንስፖርትም ሌላው አማራጭ ነው። ከአካባቢው አገሮችም በጀልባና በየብስ በጥሩ ሁኔታ የሚገናኝ ሲሆን ቅርቡ ከመቶ ምናምን ኪሎ ሜትሮች በኋላ የሚገኘው ታንዛንያ ነው። በተጨማሪ ከዩጋንዳና ከሌሎች የአካባቢው አገራት ጋር የሕዝብ ትራስፖርት ስምሪት አለ። ከኢትዮጵያ በስተቀር እነኝህ አገራት የምሥራቅ አፍሪካ ማኅበረሰብ የሚባል ማኅበር ስላላቸው ከአንዳቸው ወደ ሌላኛቸው አገር ለማቋረጥ ዜጎቻቸው ቪዛ አይጠየቁም።ሞምባሳ ወደብ በምሥራቅ አፍሪቃ ከሚገኙት ትልቁ ሲሆን ኬንያ በርካታ ሸቀጦችን ውጪ የምታስመጣበትና የምትልክበት ነው። ሌላው በሞምባሳ ያስደነቀኝ ጉዳይ ከቦብባሳ ደሴት ወደ ደቡባዊው ዳርቻ ለመሔድ ውቅያኖሱ ጥልቅ በመሆኑና በሌሎችም ምክንያቶች ድልድይ ከመገንባት ይልቅ ሰፊ ጀልባ (Ferry ይሉታል) ከላይ ለሰዎች መቀመጫ የተሠሩ ብዙ ወንበሮች ያሉበት ከታች ባዶውን ሜዳ ሆኖ መኪኖች የሚጫኑበትን ተጠቅሞ በየ5 ደቂቃው ሲያሻግር ይውላል። ለመንገደኞች ነፃ ሲሆን ቀላል መኪኖች 1 ሺሕ 600 የኬንያ ሽልንግ (16 ዶላር) የጭነት መኪኖች 2 ሺሕ 400 (24 ዶላር) እንደሚከፍሉ ተነግሮናል። ከሥልጠናው ጋር ተያያዞ ለመስክ ጉብኝት ወደ ደቡብ ስንጓዝ ሚኒባሳችን በጀልባ ተጭና እኛ ከላይ ወንበር ላይ ሆነን ስናይ በየጉዞው የሚመላለሰውን ሕዝብ ብዛት ዓይተን ስንጠይቅ ኬንያዊ ባልደረባችን እንደነገረን በየቀኑ እስከ 400 ሺሕ ሰው (ተማሪዎችን ጨምሮ) ከደቡብ ወደ ደሴቲቷ እየመጣ ሥራ ሠርቶ ተምሮ ይመላለሳል። ደቡብ ዳርቻ ቤት ኪራይም ኑሮም ረከስ ስለሚል የቱሪስት ብዛት ከሚያደምቃት ሞምባሳ የተሻለ በመሆኑ ለብዙኀኑ ለኑሮ እንደሚመረጥ ተነግሮናል።የሴኩሪቲ ወይም ደኅንነት ጉዳይ በቆይታችን ከዐሥራ አምስት የአፍሪቃ አገራት የመጣን የሥልጠናው ተሳታፊዎች ምንም ያክል ባያጋጥመንም፣ ማስጠንቀቂያና ይህን አድርጉ አታድርጉ መባል የተለመደ ነው። ወደዚህ ጉዞ ከማድረጌ በፊት የተሰጠኝ የሴኩሪቲ ሥልጠና በሌሎች ከተሞች እንደልቤ የምጠቀመውን ኡበርን ሳይቀር አይመከርም ስለተባለ ውድ የሆነውን የሆቴል ታክሲ መጠቀም የግድ ነበር። እየቆየን ግን ከሌሎች አገራት ከመጡ የሥራ ባልደረቦቼ ጋር ስንሆን ኡበር መጠቀም ብቻ ሳይሆን ከታክሲዎቹ ጋር ሲነፃፀር ዋጋው ርካሽ መሆኑንም ደርሰንበት፣ አዘውትረነው ነበር።በኋላ ላይ ከተማ መሔድ ካልፈለግን ለሥልጠና ከቆየንበት ሆቴል እስከማረፊያችን በባሕር ዳርቻው በኩል በእግራችን የውቅያኖሱን የሚገርም ውበት እያደነቅን መጓዝ የዕለት ተግባራችን ነበር። ከባሕር ዳርቻው ውበት ቀጥሎ በሞምባሳ ያስደሰተኝ የአንድ የከተማ ፓርክ ቆይታችን ነበር። ሃለር ፓርክ ሲሰኝ በአካባቢውና በኬንያ ታዋቂ የሆነው ባብቡሪ ሲሚንቶ ፋብሪካ ለሲሚንቶ የሚሆን ድንጋይ ሲያወጣ የሠራውን ሰፊ ቦታ የሚሸፍን ጉድጓድ መልሶ ለማልማት ባደረገው ጥረት ፓርኩን መሥራቱን ሰምተናል። የዚህንም ውበት፣ ፀጥታ፣ የረጃጅም ዛፎቹን ግርማ፣ የአረንጓዴውን መስክ ድምቀትና ፀጥታ ለመግለጽ መሞከር ድካም ነው። በፓርኩ ቀጭኔ፣ ጉማሬ፣ አዞ የተለያዩ ዝርያ ያላቸው እባቦች፣ ወፎች ይገኛሉ። የሔዱበት ሰዓት ከቀና ጉማሬና ቀጭኔ ሲመገቡ ያያሉ። በተለይ ቀጭኔዎቹን ከጧቱ አምስት ሰዓት ደርሰን ከባልደለቦቼ ጋር ፓርኩ የሸጠልንን የተቀመመ ምግብ ከእጃችን ለማብላት፣ ውበትና ግርማቸውን ለማድነቅ ዕድል አግኝተን የነበረ ሲሆን ጥቂት ቱሪስቶችና በርካታ ተማሪዎች በሳይንስ ስለተማሩት ስለአዞና ሌሎችን እንሰሳት በአካል እያዩ ገለፃ እየተደረገላቸው ለማየት ችለናል።ስለውቢቷ ሞምባሳ እውነታም ያየሁትንም ይህቺን ካልኩ እንደማጠቃለያ የከተማዋ ሥጋት የሚባሉትን ትንሽ ምቾት የማይሰጡ ነገሮች ላንሳ።\nእንደምታውቁት ሌላ አገር ስትሔዱ አገሬው በተለይ ሌሎች የአፍሪካ አገራት እንደ ኢትዮጵያውያን (ዛሬ ጊዜ እንኳን ኤርትራ ነሽ ኢትዮጵያ ተብሎ መጠየቀ አልፎ አልፎም ቢሆን ተለምዷል) ለየት ያለ መልክ ባለበት ከእናንተ ጋር የሚያዛምደው ወይም የሚያግባባው ፍለጋ አንዳንድ ነገር መጠቃቀሱን አይተውም። እንደመግባቢያም ነው። ሰላምታውን አፀፋ መልሳችሁ መንገዳችሁን ለመቀጠል ስትፈልጉ ግን አንዳንድ ጊዜ “የያዝኩትን ሸቀጥ ግዙኝ ወይም የት ነው ያረፍሽው? መቼ መጣሽ? መቼ ትሔጃለሽ? እዛኛው ደሴት ለመሔድ ጀልባ አለ፥ ለምን አልወስድሽም? ብዙ ተደጋጋሚ ጥያቄ ሰልችቶ አልፈልግም ሲባልም ትንሽ የማስጨነቅ ነገር አስተውያለሁ። እኛጋ ምናልባት የቋንቋዋም ጉዳይ ስላለች (ከሌላ አገር በሚመጡ ባልደረቦቼ ልምድ እንደታዘብኩት) ከአንዳንድ የታክሲና የሆቴሎች ትራንስፖርት ሾፌር ውጪ ተራው መንገድ የሚገኘው ዜጋ ብዙ የሚሰለች አይደለም።ሌላው ሞምባሳ የተለያዩ ዓይነት በሽታዎች እንዳሉ (ወባ ፣ የደንጊ ትኩሳት፣ ታይፎይድ ዲዘንትሪ) ተነግሮን ውሃ ከቧንቧ እንዳንጠጣ ስንመከር ከፀሐይ መጥለቅ በኋላ ባሕር ዳርቻው ላይ እንዳንቆይ፣ የሴክስ ቱሪዝም በቤተሰብ በሚደረግ ድጋፍና ማበረታቻ ጭምር ዕድሜያቸው ያልደረሱት ሳይቀር እንደሚሰማሩበት፣ ከዚህ ጋር ተያይዞ ወንዶች ባልደረቦቻችን ችግር ውስጥ እንዳይገቡም ተነግሮን ነበር። የሄሮይንና ኮኬይን ሕገወጥ ሽያጭ እንደተስፋፋ እዚህም ውስጥ መሳተፍ አደጋ እንደሆነም ጭምር።ለእኔ በግሌ ሞምባሳና አካባቢዋ ላይ ያጠላ ጥላ ብዬ ያሰብኩት ግን የሃይማኖት ጽንፈኝነትና አክራሪነት ጉዳይ ነው። በከተማዋ ይንቀሳቀስ የነበረ ሞምባሳ ሪፐብሊካን ካውንስል ብሎ የሚጠራ መሰል ቡድን እንደነበር እንቅስቃሴው ተዳክሞ ቆይቶ ካለፈው ሚያዝያ ጀምሮ ማንሠራራት መጀመሩም ከሴኩሪቲ ኦፊሠራችን ተነግሮናል። ከሶማሊያ ጋር የቅርብ ጎረቤት መሆኗ ብቻ ሳይሆን ከሌላው የኬንያ አካል ገንጠል ብላ ያለች፣ በንጽጽር በአብላጫው የእስልምና እምነት ተከታዩች ያሉባት መሆኗ ከኬንያ ለመገንጠል እስከመፈለግ የደረሰ ለየት ያለ የፖለቲካ አዝማሚያ ያላት ከመሆኑ ጋር ተደምሮ አልሸባብ ወታደር ይመለምልባት የነበረች መሆኗም አንድ የከተማዋ እውነት ነው። ከሴኩሪቲ አንፃር በተለይ ከደሴቲቷ ባሉት ዳርቻዎች መውጣት የአደጋ ሥጋት ያለው በዚሁ ምክንያት ነው።የምደመድመው ከሥልጠናው ጋር በተያያዘ የትምህርት ቤት ጉብኝት ወቅት ያጋጠመኝን በመግለጽ ነው። ከሥራ ባልደረቦቼ ጋር በመሆን ከተማሪቹ ጋር ለመወያየት ስንቀመጥ አስተማሪያቸው ሥማችንን፣ ሥራችንንና የመጣንበትን አገር እንድናስተዋውቅ ሲጠይቀን እነሱ በምላሹ ስለመጣንበት አገር የሚያውቁትን እንዲናገሩ ሲጋብዝ ሞዛምቢክ ሲባል “ደቡባዊ አፍሪካ ያለች፣ በፖርቹጊዝ ቅኝ የተገዛች” ብለው መለሱ። ዩጋንዳ ሲባል “ምሥራቅ አፍሪካ በእንግሊዝ ቅኝ የተገዛች” ተባለ። ተራዬ ደርሶ አገሬ ስትጠራ “ምሥራቅ አፍሪካ፣ ኢትዮጵያን ማንም በቅኝ አልገዛትም” አሉ በአንድነት፤ ልክ ነው፣ እሷ ናት አገሬ አልኩ በምላሹ።ቅጽ 1 ቁጥር 36 ሐምሌ 6 2011", "passage_id": "d61ce9cea832ebbf61eb622a4cc4a3f4" } ]
3b713cf2c1de620f7585535e8a7032f0
03fa5a413657297766e83ca6df1155e0
ትራምብ
የአድዋን ድል ለማክበር የትውልዱ ተረኛ ወጣት በነቂስ ወጥቷል:: ያስገመግማል:: ያጉተመትማል:: ሆ በል ይላል:: በባህላዊ አልባሳትና በጥንት አባቶች የጦር ሜዳ አለባበስ ተውቦ ደምቋል:: አባት አርበኞች ጋሻና ጦር ጎራዴ ይዘው ቁጭ ብድግ እያሉ በወኔ ተሞልተው ይሸልላሉ:: ያቅራራሉ:: ይፎክራሉ:: ‹‹በለው ሲል ገዳይ…ያንን ጥልያን ከተረተሩ ከጉድባው ላይ›› እያሉ:: እናቶች ወጣት ሴቶችና ወንዶች የአባቶችን ወኔና ጀግንነት በማወደስ እልልታውን ያቀልጡታል:: እልልል እንደገና:: እልልል እንደገና:: እንደገና:: የዘንድሮው የአድዋ ድል በምኒሊክ አደባባይ ሲከበር ከሰሞኑ የአሜሪካም መንግስት ለግብጽ በማድላት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውሀ መሙላት ስራ አሜሪካ የጀመረችው ማደራደር ሳይቋጭ ኢትዮጵያ እንዳታካሂድ የሚል ቀጭን የድፍረት ትእዛዝ ለኢትዮጵያ ማስተላለፉን ሁሉም ኢትዮጵያዊ በነቂስ ሰምቷል:: ክፉኛ አዝኗል:: ተበሳጭቷል:: ቁጣው ገንፍሎ ይታያል:: ይህን የሰሙ አንድ አባት አርበኛ እዛው ጊዮርጊስ ምኒሊክ አደባባይ ላይ ዙሪያቸውን ለነበሩት አባት አርበኞች ከፍ ባለ ድምጽ የአድዋን ድል በኩራት ስናከብር ሌላ ግራዚያኒ ትራምብ የሚባል ደግሞ መጣብን አይደለም ያሉ ግዜ ዙሪያ ገባው በአባት አርበኞች ሽለላና ቀረርቶ አስተጋባ:: እምቢ ለሀገሬ…እምቢ …እምቢ ለጠላት እምቢ…ኢትዮጵያ ሀገሬ …የነብሮች እናት…የአምበሶች እናት …እልፍ ጀግና አለ የሚሞትላት…ማንአባቱ ነው ችሎ ሚደፍራት…እያሉ አባት አርበኞች በፈላ ወኔ በሚፋጅ ቁጣ ወዲያና ወዲህ እየተንቆራጠጡ ወደፊት እየሄዱ ደሞ ወደኋላ እየተመለሱ ይይዙትን ይጨብጡትን አጡ:: ደሞ የማናባቱ ወሮበላ ነው ትራምብ የሚባለው አሉና አንዱ አርበኛ ጠየቁ:: እንጃለቱ አሉና ቆፍጣናዋ የሴት አርበኛ መለሱ:: ምንድነው ደሞ ትራምብ ብሎ ስም ለጠቁ ሌላው አርበኛ:: ይሄ የሰው ሳይሆን የአጋንንት ስም መሆን አለበት አሉ ከአርበኞቹ ጋር የተሰለፉት ባለነጭ ጥምጣሙ መምሬ:: ሁሉም በአንድ ግዜ የተማከሩ ያህል ልክ ነው፤ ልክ ነው ሲሉ በአደባባዩ አስተጋቡ:: እዚህም እዚያም ጭፈራው ሆታው ሽለላው ፉከራው ቀልጧል:: አራዳ ጊዮርጊስ አደባባዩ ያለወትሮው ደምቋል:: ፈክቷል:: አንዳች ግርማ ሞገስ የተደፋበት መስሏል::ይሄ ትራምብ የምትሉት ጨፈረር ኢትዮጵያን ሲጣላ፤ ለመሆኑ ማንን እንደነካ ያውቃል፤ መጥፊያው ደርሶ ነው:: የኢትዮጵያ መሪ አሳዳሪ ጠባቂ ሰው ሳይሆን እግዚአብሄር ነው:: ኢትዮጵያን በመዳፈሩ የአምላክ ፍርድና ታላቅ ቁጣ በእሱም በሀገሩም ላይ ይወርዳል አሉ፤ የቄሱ ጓደኛ መሪጌታ ገብረአምላክ:: የተመካበት መሳሪያ፣ ቴክኒዮሎጂ፣ ሳተላይት፣ መንኮራኩር፣ የስለላ ድሮን በሰማይ በውቅያኖስ በምድር በባህር ያሰማራውና የታበየበት ሰራዊት ኃያልነት ሁሉ በአምላክ ፊት ምንም ናቸው:: እንደ ጉም በኖ ይጠፋል:: ይፈራርሳል:: ሀገሩ ምድረበዳ ትሆናለች:: ሰውም አእዋፍም አይኖርበትም:: ታላላቅ ነን የሚሉት ሀገራት መሪዎችና አለምን ያንቀጠቀጠው ወራሪና እብሪተኛ ሠራዊታቸው ሁሉ በአምላክ ክንድ ይደረመሳል አሉና ዝም አሉ:: መምሬ ቀጠሉና የኢትዮጵያ አምላክ ከነኩት ቁጡ ነው:: ሲያሻው በመሬት መንቀጥቀጥ፤ በመብረቅ፤ በአውሎ ንፋስ፤ በክፉ ማእበል፤ በውሀ ሙላት ይመታቸዋል:: ያጠፋቸዋልም:: እነሱ ከፈጣሪ በላይ ነን ብለው አለምና ምድሪቱን ሁሉ ገዢዎቹ መሪዎቹ አስተዳዳሪዎቹ እኛ ብቻ ነን ብለዋል:: ይሄኔ ነው መፍራት አሉ መምሬ:: እንግዲህ ነገር ሁሉ ለበጎ ነው እንዲሉ መጪውን ሁሉ በጥሞና በማስተዋልና በአርምሞ መጠበቅ ነው አሉ:: በበአሉ ላይ ከአርበኞቹ ጋር የታደሙት ሙሉ ቢጫ ከላይ እስከታች የለበሱ ጸጉራቸው ከአናታቸው ወርዶ መታጠቂያቸው ድረስ የተንዠረገገው በሰንሰለት ወገባቸውን የታጠቁት አባ አለም በቃኝ የተባሉ ባሕታዊ:: አባታችን በህልምዎ ነው በምናብ ነው አርምሞውን ያዩት ሲሉ አርበኞቹ ጠየቋቸው:: ሁለቱንም አይቻለሁ አሉ ባህታዊው ረዥሙን ጫፉ ጦር ያለበትን መቋሚያቸውን ተደግፈው:: አባት አርበኞቹ ለአፍታ በዝምታ ተዋጡ:: ወዲያው የበአሉ ጭፈራና እምቢ ለሀገሬ የሚለው ሆታና መዝሙር አነቃቸው:: ተከብረሽ የኖርሽው በአባቶቻችን ደም…እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውድም…የደፈረሽ ይውደም የሚለው የወጣቶች መዝሙር ጎልቶ ይሰማል:: ይሄኔ አባትና እናት አርበኞች እየፎከሩ ተንጫጩ:: እሳት ቢያንቀላፋ…ገለባ ጎበኘው…ባያውቀው ነው እንጂ ባይጠራጠረው…ዘራፍ የኢትዮጵያ ልጅ…ለነጻነቱ በደም የሚዋጅ… ትራምብ የሚባል ሆዳም አውደልዳይ…የግብጾች አሽከር ከርከሮ መሳይ…ሲያናፋ ቢውል እንደ አህያ…ወግድ ክላ አለው ጀግናው ኢትዮጵያ ብለው ፈከሩ ሸበቶውና ደረታቸው በሜዳሊያ የተንቆጠቆጠው አባት አርበኛ:: በእልልታና በጭብጨባ በሆታ በፉከራ አካባቢው ተደበላለቀ:: ሌላው አርበኛ ተቀበሉና ቀጠሉ:: ለዚያ ሰላቶ ትራምብ ለሚሉት …ለነጫጭባው…ንገር ሂድና…ጦር ልማዱ ነው የኢትዮጵያ ጀግና…ለሀገሩ ይሞታል ደግሞ እንደገና…የታመነ ነው በቃሉ የጸና…ብለህ ንገረው…እስከሚገርመው…ዘራፍ የአምዮ ልጅ የኢትዮጵያ…ከእናቱ በፊት ጥሎ ሚወድቀው …የወኔው ግለት…የሚጋረፈው…ዘራፍ የአባቶቹ ልጅ ….ነበልባል ቋያ… ሰደድ እሳቱ…መጠቃት ሞቱ…መደፈር… ሞቱ …የማይሳሳ ለአንድ ሕይወቱ…ብለህ ንገረው ትራምብ ለሚሉት…ለግብጾች ፈረስ ለሚጋልቡት…ዘራፍ የመይሳው ልጅ የነዮሀንስ የነአባ ዳኘው…የነጎበና የነአባ ዳጨው የነጃገማ የእነ ባልቻ መድፍ አገላባጭ ብቻ ለብቻ…ብለህ ንገረው ለዚያ ለትራምብ እስከሚገርመው እያሉ አርበኛው በቁጣና በጋለ ወኔ እየሸለሉ ሲንደቀደቁ አካባቢው አረገደ:: የአድዋ ድሉን 124ኛ አመት ለማክበር የተሰበሰበው ሕዝብ በሆታ አስተጋባ እምቢ ለሀገሬ እያለ:: የአሜሪካንን መግለጫ ከ2 ቀን በፊት ሕዝቡ ሰምቶ ስለነበር ቁጣውን በባህሉ መሰረት በተለያየ መንገድ ሲገልጽ ውሎ ከአባቶቹ ጋር ወደ ቤቱ ተመለሰ:: ለሀገራቸው ክብር የሚቆሙ ጀግና ወጣቶች ስለተካን ክበር ተመስገን አሉ- አዛውንቶቹ አባትና እናት አርበኞች:: ኢትዮጵያ የታላቁን ህዳሴ ግድብ ውሀ እንዳትሞላ የሚለው የአሜሪካ ድፍረትና ንቀት የተሞላበት ሉአላዊነታችንን የደፈረ አቋም እጅግ ከፍተኛ የማይበርድ ሕዝባዊ ቁጣን ቀሰቀሰና አረፈው አለ አንዱ የበአሉ ታዳሚ ወጣት:: እብሪትና ድፍረት መዘዙ ብዙ ነው አሉ አባት አርበኛ ደጋጋ ሁንዴ:: ኢትዮጵያን መናቅ መድፈር ታላቅ ዋጋ ያስከፍላል ብላችሁ ለትራምብ ንገሩት አሉ ደገሙና ወደ ወጣቶቹ ዞረው:: ወጣቶቹ ይህን ግዜ እንደ መሳቅ ብለው – አባባ አባባ ትራምብ እኮ አማርኛም ኦሮሚኛም አይሰማም አሏቸው:: የት አባቱ አሉና በዛው በሱ ትብታብ ቋንቋው ንገሩት:: ከእኛ ላይ ይውረድ:: ትራምብ ለግብጽ አሽከርም ገረድም መሆን መብትህ ነው በሉት:: ከኢትዮጵያ ትከሻ ግን ይውረድ አሉ መለሱና:: እምቢ ካለ የኢትዮጵያ ታላቅ አምላክ ሳይውል ሳያድር የሚሰጠውን ፍርድ ይጠብቅ እንዲያውም ተውት አሉ- አርበኛ ደጋጋ ሁንዴ:: አዲስ ዘመን የካቲት 26/2012ወንድወሰን መኮንን
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=28551
[ { "passage": "ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ ጀምሮ በቤተሰብ ዕቅድ እና በስነ-ተዋልዶ ጤና ላይ ለዓመታት በሰራቸው ስራዎች የሚታወቀው ዲኬቲ ኢትዮጵያ ለየት ያለ የበይነ -መረብ ላይ ትርኢት እያሳየ ይገኛል። ትርኢቱ ደግሞ በዕውቅ የፋሽን ንድፍ ባለሙያዎች የተዘጋጁ የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛዎች የሚታዩበት ነው። ሀብታሙ ስዩም ያናገራቸው የድርጅቱ የገበያ ዘርፍ ሃላፊ ወ/ሮ እመቤት አቡ የትርኢቱ ዓላማ ወጣቶች ጤናቸውን እየጠበቁ ሊደምቁባቸው ከሚችሉባቸው መላዎች ጋር ማስተዋወቅ እንደሆነ ጠቁመዋል። ሙሉ ቃለ-ምልልሱን ያዳምጡ፦\n\n ", "passage_id": "b37236be7418f1c68f15ac9ed964f724" }, { "passage": " የወጣት አፍሪቃዊያን መሪዎች ተነሳሽነት መርሃ፡ግብር በእንግሊዝኛው ምህፃር YALI ፣ በቀድሞው የደቡብ አፍሪቃ የነጻነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ ስም የሰየመው የቀለም ትምህርትና፣የአመራር ስልጠና ከሰሞኑ ተጠናቋል፡፡ ቁጥራቸው ከ30 በላይ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን በዚህ መርሃ ግብር ላይ ተሳትፈዋል፡፡\n\nከታሳታፊዎቹ መካከል ከአራቱ ጋር ቆይታ አድርገናል፡፡ስለቀሰሙት ቁምነገር፣ስለ መጪው ዘመን ህልማቸውም አውግተውናል፡፡ ", "passage_id": "5949d6f3f8f13a54bc4bfeb03e700d67" }, { "passage": "ሙኒት መስፍን የሶስት ዘመን ኢትዮጵያዊን ጆሯቸውን ከሚሰጧቸው ባለ ልዩ ቃና ሙዚቀኞች መካከል አንዷ ናት ። “ኖሮ ኖሮ “ የሚለውን ሙዚቃዋን በመሰሉ ብርታትን ቀስቃሽ ሙዚቃዎቿ በወጣቶች ዘንድ ንቃትን ፈጥራለች። የኮ/ል ለማ ደምሰውን “ አስታውሳለሁ” ፣የሰይፉ ዮሃንስን “ የከረሞ ሰው” እና የመሳሰሉትን ዳግም ባቀነቀነችነት አፍታ የአረጋዊያንን ትዝታ ቀሰቅሳለች።ህጻናትን እና ህጻንነትን በሚዘክሩ ስረወቿ ደግሞ ከመጪውን ትውልድ ጋር ተዋወቃለች።የዛሬ ጋቢና መዝናኛ እንግዳ ሙኒት መስፍን አበበ፣ሙዚቃ ለማህበረሳባዊ ለውጥ ለማዋል በተቀረጹ መርሀ ግብሮች ውስጥ ዐቢይ ተሳታፊም ናት።ከሙያዊ ህይወቷ ጋር የተገናኙ ሀሳቦች የሚደመጡበትን መሰናዶ ይዘን ቀርበናል ። መልካም ቆይታ። ", "passage_id": "3889e794d8d76b122082a5d46d1ab513" }, { "passage": "የወባ የሕይወት ዑደት የሚጀምረው አንዲት በወባ ቫይረስ የተመረዘች ቢምቢ ጤነኛን ሰው ስትነድፍ ነው። ከዚያም ቫይረሱ ወደ ጤነኛው ሰው ደም ይገባና መራባት ይጀምራል። ከዚያ በኋላ ቀድሞ ጥገኛው ሕዋስ የሌላት ቢምቢ አሁን የተነደፈውን ሰው ደም ስትመጥጥ እንደገና እንዲራባ መንገድ ትከፍትና የዝግጁው የወባ ተውሣክ ተሸካሚ ትሆናለች።የለንደኑ ኢምፔርያል ኮሌጅ ሳይንቲስትና የደቂቅ ሕዋስ ሥነ-ሕይወት ፕሮፌሰር ጄክ ባውምና ሌሎችም ተመራማሪ ባልደረቦቻቸው እየሠሩ ያሉት ያንን እንደገና ለመራባት ዝግጁ የመሆን ደረጃን ለማቋረጥ ወይም ለማቆም ነው። በንድፈ ሃገሣብ ደረጃ ይቻላል... ", "passage_id": "15d25526f6cdb0a4e02719d87a53a489" }, { "passage": " ወረህ አቡል፡ በገነቴ ዘዬ የምርቃት መክፈቻ ነው። ብዙውን ጊዜ አክስቴ ቤት ስሄድ ቡና ሲፈላ እደርሳለሁ። ታድያ ይሄ በሂና የቀላ ጢማቸው የእሳት ፏፏቴ መስሎ ከአገጫቸው የሚወርደው፤ ዘወትር መፋቂያ ሰክተው የማያቸው ሰውዬ፤ በቡና ጠጪ ጎረቤቶቻቸውና በሚጣፍጥ የቆላ እጣን መካከል ሆነው ‹‹ ውረህ አቡል!›› ብለው ይጀምሩና ወደ አስቂኝነት የተጠጋ ግጥም የመሰለ ረጅም ምርቃት ይቀጥላሉ። ‹‹ አሜን በል፤ ተቀበል /የማታውቅ ፈቀቅ በል/ ከጎረቤት ምቀኛ/ ከአሮጊት ነገረኛ/ ከጅል ግልምጫ/ ከአህያ እርግጫ/ … ይሰውርህ ‹‹አቦ›› ታድያ ‹‹አቦ›› ሲሉ ‹‹ቦ›› ን ጠበቅ አድርገው ነው። አንዴ ጨብ የሚያደርጓት ደማቅ ጭብጨባቸው የምታጅበው ይህቺ ‹‹አቦ›› ሲናገሯት የምታረካ፤ እገጭ አድርጋ የምትዘጋ ቤት መምቻ ነበረች። ‹‹አቦ››ን ማንም እንደሳቸው ሲላት ሰምቼ አላውቅም። ############# ኤህ! የእርግማን መክፈቻ። ልክ ‹‹ወረህ አቡል›› የምርቃት መጀመሪያ እንደሆነው ሁሉ። ‹‹ኤህ›› አንዳንዴም በራሷ እርግማን ልትሆን ትችላለች። ብዙ ጊዜ ሁለተኛዋ ድምፅ ‹‹ህ›› ላላ ስለምትል ቃሉ ‹‹ኤ›› ብቻ ይመስላል። ታድያ የጓደኛዬ የመሰረት ወንድም፤ ተረጋሚው ሀብታሙ ‹‹ኤህ!›› ሲሉት አንቱታቸውንም ትቶ ጭራሽ ያሾፍባቸው ጀመረ፡ ‹‹ አይሻልሽም ቢ?›› አሮጊቷ ወደ ሰማይ አንጋጠው፤ የእንባ ግት በቋጠሩ ትናንሽ ዐይኖቻቸው ወደ አርአያም እያዩ፤ አመልካች አውራ ጣታቸውን አጋጥመው በሌሎቹ ሶስት ጣቶቻቸው ወደ ሰባተኛው ሰማይ እየጠቆሙ፤ ብቸኝነት በቀጠነው የተራጋሚ አሮጊት ድምፅ፡ ‹‹የእናት አባቴ ውቃቢ በአጭር ያስቀርህ፤ በአጭር ቅር እቴ!›› እርግማናቸው መሬት ጠብ አትልም የሚባሉትና በዚህም ብዙው የመንደር ሴት የሚፈራቸው ይህቺ መካን ሴት በሌላም ጊዜ ይህቺን እታለም ሉሉ የተባለች ታታሪ ወላድ ሲረግሟት የሰማሁት ከዚህ ይብሳል፡ ‹‹እመቤቴ በሽፍን ትውሰድሽ፤ ማህፀነ ጃርት ያድርግሽ››። እታለም ያኔ ስድስተኛ ልጇን አርግዛ ነበር። በሽፍን አልወሰደቻትም፤ ማህፀነ ጃርት አለመሆንዋን ግን አላውቅም። ምንጭ፡- ( በደራሲ ሙሉጌታ አለባቸው ከተፃፈው ማህረቤን ያያችሁ መፅሀፍ ከገፅ 118 እና 122 የተወሰደ)አዲስ ዘመን  መስከረም 19/2012", "passage_id": "376a80f310d2e2a933192e5a063a3254" } ]
fa0f716b47584c419d2e18151765ee74
9be60c81f6d9b633b7259fa832d0c1cd
የእብድ ገላጋይ ያቀብላል ድንጋይ
 በአሁኑ ወቅት ዓለማችን በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ እየተፈተነች ትገኛለች፡፡ በቫይረሱም ምክንያት ሰው እንደ ቅጠል በእያንዳንዱ ሰከንድ ይረግፋል። በሽታው በትንፋሽና በንክኪ በቀላሉ የሚዛመት መሆኑ ደግሞ ስርጭቱን በቀላሉ ለመቆጣጠር አዳጋች አድርጎታል፡፡ ታዲያ በዚህ የዓለማችን ስጋት በሆነው በሽታ ስጋት የገባው አባወራ ራሱንና ልጆቹን ለማዳን ያደረገው ድርጊት የሰሞኑ የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን መነጋገሪያ ሆኖ ነበር፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው ግለሰቡ የሊትዌንያ ነዋሪ ሲሆን በኮኖራ ቫይረስ ተይዛለች በሚል ስጋት ባለቤቱን መታጠቢያ ቤት በማስገባት ቆልፎባት፤ እንዳትወጣም የከለከላት ሲሆን ይህ ድርጊቱም ዓለምን ጉድ አሰኝቷል፡፡ ባሳለፍነው የካቲት ወር አጋማሽ በሊትዌንያን ቪሊኒዩስ የሚገኝ ፖሊስ በአካባቢው ከሚገኝ አንድ ስፍራ አስጨናቂ የስልክ ጥሪ ይደርሳቸዋል፡፡ ለፖሊስ የደረሰው ጥሪም በመኖሪያ ቤቷ መታጠቢያ ቤት በባልዋና በሁለት ልጆቿ የተቆለፈባት አንድ እንስት ጥሪ ነበር፡፡ ወደ ጥሪው ቦታ ያመራው የፖሊስ ቡድን ወደ ትዕይንቱ ቦታ ሲደረስ ድርጊቱን የፈፀመው አባወራ ያለአንዳች ፍርሐት የመኖሪያ ቤቱን በር በመክፈት ሚስቱን በመታጠቢያ ቤት እንደቆለፈባት በመግለጽ ይህንንም ያደረገው ከኮሮና ቫይረስ ጥቃት ራሱንና ልጆቹን ለመከላከል አስቦ ያደረገው መሆኑን ተናግሯል፡፡ የአካባቢው ብሄራዊ ፖሊስ ቃል አቀባይ ራሙናስ ማቶኒስ ለጋዜጠኞች እንደገለጹት “አባወራውና ሁለቱ ጎረምሳ ልጆቹ እማወራዋን ከመታጠቢያ ቤት እንዳትወጣ የከለከሏት በኮሮና ቫይረስ ተጠቅታ ሊሆን እንደሚችል እንደምትጠረጥር ስለነገረቻቸው ነው፡፡ ሴትየዋ ወደ ጣሊያን ሄዳ በነበረበት ወቅት ከወደ ቻይና ከመጡ ሰዎችም ጋር ተገናኝታ ስለነበር በዚህም ምክንያት በኮሮና ቫይረስ ተጠቅታ ሊሆን እንደሚችል ስጋት እንደገባት ለባለቤቷ ታጫውተዋለች፤ታዲያ በጉዳዩ ላይ ቀልድ የማያውቀው አባወራም ነገሩን በቸልታ አልተመለከተውም አባወራው በአስቸኳይ አንድ የህክምና ዶክተር ጠርቶ በኮሮና ቫይረስ ተጠቅታ ሊሆን እንደሚችል ስጋቱን ነገረው። ሀኪሙም “የእብድ ገላጋይ ድንጋይ ያቀብላል” እንደሚባለው ሙያውን ዘንግቶ ለሰውየው ሴትየዋን ገለል እንዲያደርጋት ይመክረዋል፡፡ አባወራውም የሀኪሙን ምክር በመስማት ከሁለት ልጆቹ ጋር በመሆን እማወራዋን በመታጠቢያ ቤት በማስገባት ቆለፉባት፡፡ ሰውየው እንደተናገረው በሚስቱ ላይ አንዳች ጉዳት ለማድረስ ወጥኖ የሠራው እንዳልሆነና እንዲያው ዝም ብሎ የዶክተሩን ምክር ተከትሎ ሚስቱ በሽታውን እንዳታሰራጭ ለመከላከል ያደረገው መሆኑን ገልጿል፡፡ በድርጊቱ የተከሰተ ምንም ጥቃት የሌለ ሲሆን በሴትየዋም በኩል የቀረበ ቅሬታ የለም፤ስለዚህ ፖሊስ አምቡላንስ በመጥራ ሴትየዋ በሽታዋን እንድትመረመር ወስዷታል፡፡ በመጨረሻ የባልየው ጭንቀትና ፍራቻ መሠረት የለሽ መሆኑንና ሴትየዋም ተመርምራ ከኮሮና ቫይረስ ነፃ መሆኗ ተረጋግጧል፡፡ ቢሆንም ግን ይህ ክስተት ኮቪድ 19 ምን ያህል ሰዎች ላይ ተፅዕኖ እያደረሰ መሆኑን ያስረዳል፡፡ ሰዎች ራሳቸውን ከበሽታው ነፃ ለማድረግ የትዳር አጋራቸውን መታጠቢያ ቤት ውስጥ ቆልፈው መውጣት ከጀመሩ ጉዳዩ ምን ያህል አሳሳቢ መሆኑን ያሳያናል፡፡ አዲስ ዘመን መጋቢት 1/2012 ኃይለማርያም ወንድሙ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=28831
[ { "passage": "ስትገነባ ሲፈርስባት ደግማ ስትክበው መልሶ ሲናድ … እኔ አንድ ጫማ ሰፍቼ ጨረስኩ። ከመደቧ ላይ ትንንሽ ቋጥኞች አስመስላ እንደየ ዓይነታቸው ማሰናዳት ከጀመረች ቆይታለች፤ ግን አልሆነላትም። አንዱን ደርድራ ስታበቃ ሌላኛው ይፈርስባታል። ድንቹን ያስተካከለች መስሏት ዘወር\nከማለቷ ተደርምሶ ከሽንኩርቱ ይቀላቀላል። እርሱን ለማስተካከል ስትጥር ደግሞ ከወዲያ የከመረቻቸው ሎሚዎች ተዘረጋግፈው ስራዋን ያበዙባታል። ነገሯ «ውሃ ቅዳ፤ ውሃ መልስ» ስለሆነባት አሳዝናኝ እርሷኑ መከታተል ያዝኩ። ይህቺ ሴት ከጎረቤት መደቦች በላይ ስራ እንደሚበዛባት ከኔ በላይ ምስክር አያሻም። በጉሊታችን ከበዛው ወጪ ወራጅ ይልቅ ዓይኔ አዘውትሮ የሚያርፈው እርሷ ላይ ነው። እርግጥ ነው፤ የእኔ ቆጥ ከእርሷ ፊት ለፊት መገኘቱ ሳልፈልግም ጭምር እንዳያት ያደርገኛል። የማያት ግን በምክንያት ነው፤ ነገረ ስራዋ ሁሉ ታሪክ ስላለው። አንገቷን አቃንታ አይኖቿን ስመለከት በስሱ ጭል ጭል ከሚል ዓይነ ውሃዋ ተቀድቶ የማያልቅ ታሪክ አነባለሁ። ከአጥንቷ ከተጣበቀው የጉንጯ ቆዳ ላይ የበለዘው ስፍራም አንዳች የህይወት ካርታ የተሳለበት ይመስለኛል። አሁንም አሁንም በድንችና ሽንኩርት ቁልል መሃል ወዲያ ወዲህ ከሚል የእጇ አይበሉባ የተዘረጉት የደም ስሮቿም መድረሻ የሌለውን አቅጣጫ የሚጠቁሙ ይመስለኛል።ካጠረው ቁመቷ ላይ የከሳው ሰውነቷ ተዳምሮ ወገቧ ሰበር ማለቱን ላስተዋለ፤ አንድ ሃሙስ የቀራት በሽተኛ ትመስላለች። ከመደቧ ስትቀመጥ ኮስሟና ሰውነቷ ከቁልሎቹ አይጎላም፤ በዚያ ላይ ጃንጥላ ስትደርብበት ደግሞ ከነመኖሯም አትታይም። እንዲያም ሆኖ ቀኑን ሙሉ እየካበች የሚፈርስባትን አትክልት በሸክም የማጓጓዝ ብርታት አላት።መኖሯ የሚታወቀው ሁሌም ከእርሷ አቅጣጫ ግርግር ስለማይጠፋ ነው። ብቻዋን የምታሳ ድጋቸው ልጆቿ ቢደርሱላትም እናታቸውን የሚያሳርፉ አልሆኑም፤ ሁሌም የገበያተኛውንና ነጋዴዎችን ቀልብ የሚይዝ ሰቀቀን ይጭሩባታል። እረፍት የሚነሷት ጎረምሳ ልጆቿ ድንገት ደርሰው አንዳች ረብሻ ይፈጥሩባታል። ብዙ ጊዜ የተለያዩ ሰዎች ስሞታ ሲያነሱላት እመለከታለሁ። «ልጆችሽ እንዲህ አድርገው፤ እንዲህ አጥፍተው» እያሉ ይከሱላታል። ይህን ሲሏት በሰቀቀን ከሳሾቹን አሻቅባ ከመመልከት በቀር የምትፈጥረው ነገር ባይኖርም፤ በልጆቿ ፋንታ ይቅርታ ትጠይቃለች። እንደምት ገስጻቸውና እንደሚታረሙም ታስረዳለች። እን ዲህ ሆና ሳያት እንደ ድንቾቿ ሁሉ ከቀለሰችው ጎጆ አንድ ማገር፤ ከገነባችው ህይወቷም ቅንጣት ተስፋ ሲናድ ይታየኛል።ወዲያው ሃሳብ ይይዛታል፤ እንደ ሌሎች ነጋዴዎች ገበያዋን በንቃት አትጠብቅም። ከሳሾቹ ከሄዱም በኋላ አገጯን ከእጇ ላይ አስደግፋ በሃሳብ ጭልጥ ትላለች። እንዲህ ስትሆን ታሳዝነኛለች፤ የእኔም ሃሳብ በእርሷ ላይ ይደረባል። ከትካዜዋ መለስ የምትለው ገበያተኛ ሲመጣ ነው። አፍታም ሳትቆይ ሁለመናዋ እርሷን የማይመስል ሴቷ ልጇ ትመጣለች። ከልብሷም ከመልኳም እንዳማረች እናቷን ትጠጋለች፤ አይናማዋን ልጅ ስመለከት ልቤን ይሞቀዋል። ግን ብዙም አይቆይም፤ ከእናቷ ጋር ከምታደርገው ጥቂት የቃላት መመላለስ በኋላ ስሜቴ በበረዶ ይተካል። እናት አንገቷ ላይ ከምታንጠለጥለው ከረጢት መሰል ቦርሳዋ ከሸጠችው ቆንጥራ ትሰጣታለች። ልጅት ግን ተጨማሪ ካልተሰጣት አትንቀሳቀስም። እርሷን ከመሸኘቷ በዱቤ የቤት ዕቃ የሚሸጠው ነጋዴ ደርሶ ያፈጥባታል። በችርቻሮ የምትለቃቅመው ገንዘብ ከቤቷ ሳታደርስ እዛው ትጨርሰዋለች። እርሷን መከታተል ከጀመርኩ እንስቶ የደሃ መጫሚያዎችን እየጠገንኩ በምገፋው ኑሮዬ ማዘንና ማማረር አቁሜያለሁ። በጊዜ ብዛት ጠረን የፈጠሩት ጫማዎችም ቢሆኑ ለአፍንጫዬ ቤተሰብ ሆነዋል። ቀልቤ ከዚያች ሴት ስለሚሆን፤ ውሎዬን እንድትጋራ የምከፍታትን ሬዲዮንም አድምጫት አላውቅም። ዓይኔን ከወዲያ ጥዬ ቆዳውን ከሶሉ ለማያያዝ ስታገልም ወስፌ ከእጄ ቢሰካም የሚሰማኝ ነገር የለም።አንድ ረፋድ ላይ አንድ ሁለት መደብ እንደ ሸጠች በሚሯሯጡ ሰዎች ትንሿ ጉሊታችን ትረበሽ ጀመር። ከፊት የቀደመው ተባራሪ የመከረኛዋ ሴት ልጅ ነው፤ አባራሪዎቹ ከኋላው ድንጋይና ዱላ ይዘው ሊደበድቡት ይከተሉታል። እናት ለማስጣል ተነሳች፤ እርሱ እንደ ልጅነቱ ከእናቱ ጉያ ሊደበቅ፤ እርሷም ልትሸሽገው ነበር። ግን አልደረሰችበትም ዓይኗ እያየ ደብድበውት ሄዱ። ሰዎች ከአንድ ጥግ አስቀምጠው ሊያረጋግጉት ሞከሩ፤ ለቅሶዋ ግን የሞተ ያህል ነበር። እኔ ብቻ የምመለከተው ምሬቷ አፍ አውጥቶ መናገር ጀመረ። ውስጧ ያለው ብሶት አንድም በእንባ አንድም ሳግ በሚቆራርጠው ሳጓ ሲፈስ ይበልጥ አዘንኩላት። ለምን እንደሆን እንጃ እያንዳንዱ እንቅስቃሴዋ መንፈስን የሚይዝ ታሪክ አለው። አጋሮቿ ከበው ሊያባብሏት ሲሞክሩ፤ ልቤ አብሯት እያነባ ነበር። ከሰው ፊት እንዳላነባ ስለሰጋሁ ወትሮውንም ብከፍት እንጂ የማልሰማውን ሬዲዮ ድምጽ ጨመርኩበት። በአስገምጋሚ ድምጹ ዜና የሚያነበው ጋዜጠኛ «… በተባለ ስፍራ በተቀሰቀሰ ግጭት፤ … ያህል ሰዎች ሲሞቱ … የሚሆኑት ደግሞ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቀሉ» ይላል። ጋዜጠኛው ሃተታውን ሲቀጥል የእኔ ቀልብ መልሶ ከዚያች ደሃ ሴት አርፈዋል። እንባ ያቀረሩት\nአይኖቼ እንባዋን ሲመለከቱ\nአእምሮዬ ጥያቄውን ማዝነብ\nጀመረ። ቀልቧ ከቀልቤ\nለምን እንደተሳሰረ፣ ሳያት\nለምን እንደምፈዝ፣ እያንዳንዱ\nየአካል ክፍሏ ለምን\nታሪክ እንደሚሆብኝ፣ ሁኔታዋ\nሁሉ ለምን አንጀቴን\nእንደሚያላውሰው፣ …።\nየገባኝ ቆይቶ ነው፤\nለካስ በእርሷ ውስጥ\nስመለከት የቆየሁት ስትክብ\nየሚናድባትን፤ ልጆቿ ሁሉ ጎርምሰው\nበግልፍተኝነት ችግር የሆኑባትን\nሃገሬን ነበር።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 14/2011", "passage_id": "488890826ed8f2f69f2c6648b8d0c7a5" }, { "passage": "አያ ቢተው ይባላሉ፤ለፍተው ለሥራ ካበቋ ቸውና እያስተማሯቸው ካሉት ልጆቻቸውና የልጅ ልጆቻቸው ጋር በአዘቦት ቀን በአንድ ላይ ሰብሰብ ብለው እየተ ጨዋወቱ ነው። የሚያዩትና የሚሰሙት ትዝብትም፣ ግርምትም፣ቁጭትም ፈጥሮባቸ ዋል፡፡ የአገራቸው ጉዳይ ከልባቸው ተሰንቅሮ እረፍት ቢነሳቸው በቤተሰብ ጨዋታቸው መካከል አንስተውታል፡፡ መምህር ታለጌታ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዋ አለሚቱ እንደ ቅደም ተከተላቸው የእድሜ ጠገቡ አያ ቢተው ልጅና የልጅ ልጅ ናቸው። ውይይቱን አድምቀው ታል፡፡ የስም መመሳሰል ከተፈጠረ ታስቦበት እንዳልሆነ ይያዝልኝ እያልኩ ጭውውታቸውን እንደወረደ ጋበዝኳችሁ፡፡ መኮምኮም የእናንተ ፋንታ ነው፡፡ አያ ቢተው፡- ‹‹ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው›› ብለው አበው የተረቱት መሬት ጠብ አላለም፡፡ ጉብል እስከ አዋቂ በወሬ የሰከረ፣ በወሬ የተምታታ ይሁን? ወሬን በወሬነቱ አድምጦ ከማን ሰማኸው? የትስ አገኘኸው? ብሎ መጠየቅ ነውር ነው እንዴ? እንዲህ ሆኖ አረፈ ወጉ? ንፋስ ሲያመጣው መቀበል፤ንፋስ ሲነሳ መሸኘት። በፌስቡክ ጉሊት ከሚነፍሰው ጋር ገለባ ሆኖ አብሮ መንፈስ። አይጣል እቴ! መምህር ታለጌታ፡- ምነው? ምን ገጥሞህ ነው? አያያ። (አባቱን የሚጠራበት ስም ነው) እንዲህ ሆድ ያስባሰህ። አያ ቢተው፡-ሰማህ ልጄ አገር መስታወት ነው። ተጠንቅቃችሁ፣ ወልውላችሁ ያዙኝ ይላል። እንደ ቀልድ ባረባ ቦታ አስቀምጠህ፤ አለያም በአቧራ ሲለወስ እያየህ ያልሰተርከው መስታወት እንደፈለከው ትክክለኛ መልክህን ሊያሳይህ ይሳነዋል፡፡ አገርህም እንደዚያው ነች። እንደቀላል ሥሟን ማጉደፍ ለመወልወል ያስቸግራል፡፡ አገርህንና አይንህን በዋዛ አታስነካ፡፡ መተኪያቸው ይቸግርሃል፡፡ በአገር መስታወት ውስጥ ማን የሚታይ መስሎሃል? መምህር ታለጌታ፡- ድሮ ልጅ እያለሁ ‹አብወ ለድ› ብስኩት ልገዛ ሳላስፈቅድ ከኪስህ ገንዘብ አሹልኬ ስወስድ ተቆጥተህ የምታሳየኝን ፊት ነው ዛሬ ያየሁብሀ። እንዲህ ለብሶት የዳረገህን ጉዳይ ለምን አትነግረኝም፡፡ አያ ቢተው፡- አየህ አገር ሲከፋት ብሶቷ የሚታየው በእኛ ፊት መጥቆር ነው፡፡ አገር በውሸት ስትታመስና ሠላሟ ሲናጋ የሚናጋው የእኛ ኑሮ፣ የእኛ ሰላም ነው፡፡ አለመታደሌ ሆኖ እነሱ በዋሉበት ሳልውል ቀርቼ ይሁን እንጃ ጆሮዬ በየቀኑ የሚሰማውና የሚያደምጠው ሟርት ብቻ ሆነ፡፡ እንዴት ሰው ካላጣው ማሟረቻ በአገሩ ያሟርታል፡፡ ‹‹አንድ አይና በአፈር አይጫወትም›› አሉ፡፡ ሌላ መጠለያ ያለን ይመስል እንዴት አንሳሳላትም፡፡ መረን ትቶ ከአሳሩ መራቅ፣ መሸሽ አይቻል፡፡ በአገር የሚመጣ እንዴት ዘራፍ አያስብልም፡፡ በጠላሸት በተጥሞረሞረና በጠቆረ ነጠላ ማጌጥ የለም፡፡ ወተት መስሎ መታየት ይናፍቃል፡፡ መከበርም አይታሰብ፡፡ በአገርም ያው ነው፤ ያውም ይብሳል፤ ቀና ብሎ እኩል ማያ አይን ያሳጣል፤ ምላስ እንዳልፈታ ሕጻን አንደበት ጉልበት አጥቶ ይንተፋተፋል፡፡ አገር መስታወት የጨበጠች ዕለት ከፊት ለፊቷ የሚታዩት የእናንተ የትውልዶቿ የሰከሩ ፊቶች ናቸው፡፡ እንጂማ ምን አብሰከሰከኝ፡፡ መምህር ታለጌታ፡- እንደ እናንተ ዘመን አገርን የሚወድ ትውልድ የለ ሆኖ ይሆን እንዴ? ተማሪዎቻችን ዘመን አመጣሽ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚዎች ናቸው፡፡ ብዙ ነገር ያወቁ አድርገው ራሳቸውን ያስባሉ፡፡ በዚህ የተነሳ አሻግረው የሚመለከቱት ውጪ አገር ነው፡፡ ያ ይሆን? ተማሪ አለሚቱ፡- ተማሪዎች የሚማሩት እኮ ዲቪ ለመሙላት ነው፡፡ ደግሞ እዚህ አገር ማን ተምሮ የተለወጠ አለ? ጋሼ ይሙት(በአያቷ ስትምል)፡፡ ፊዚክስ መምህራችንን ብታዩት ፈላጭ ነው‹(ጎበዝ ነው ለማለት ነው) በዚያ ላይ ጨዋ ነው፡፡ አምስተኛ ክፍል እያለሁ የለበሳትን ስኩዌር ሸሚዝ እስካሁን ድረስ አልቀየራትም። እና መማር ቢለውጥ እሱን አይለውጥም ነበር። አያ ቢተው፡- አይምሰላችሁ ልጆቼ። አገሩን የሚወድ ትውልድ በየዘመኑ ይበቅላል፡፡ ዋናው ነገር አስተዳደጉ ነው። እየሰማችሁኝ ነው? መምህር ታለጌታ፡- አዎ፡፡ በደንብ እንጂ። እያዳመጥን ነው። አያ ቢተው፡- በዚች ምድር ላይ ያልዘሩት አይበቅልም። ያልዘሩትን የሚያጭዱም አይኖሩም። ካሉም ደግሞ ርባና ቢስ ናቸው፡፡ እናም ‹‹ተማሪው ማንን ይመስላል ቢሏችሁ አስተማሪውን፤ አገር ማንን ይመስላል ከተባላችሁም መሪውን›› ነው መልሱ፡፡ ተማሪዎቻችሁ የእናት አገራቸውን ሰንደቅ ዓላማ ክብር ያውቁታል? ሲወጣና ሲወርድ ያለውን ክብርስ? መዝሙሩ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ በሚያስረቀርቅ ድምጽ ያዜሙ ታል? ተማሪ አለሚቱ፡- ጋሼ አንተ የምትለው የድሮውን ነው? እሱኮ አሁን የለም ቀርቷል፡፡ ሰንደቅ ዓላማ ሲወጣና ሲወርድ እኛ ትምህርት ቤት ቀስ ተብሎ ነው የሚኬድ። አስተማሪዎቻችንም፣ርዕሰ መምህራችንም እንደኛ ቀስ ብለው ነው የሚራመዱት፡፡ እኔ እስካሁን ሳይንቀሳቀስ ቀጥ ብሎ የሚያከብር አላየሁም፡፡ በሰልፍ ላይም የዜግነት ክብር መዝሙር መዘመር ግዴታ አይደለም፡፡ የፈለገ ይዘምራል፤ ያልፈለገ ዝም ቢልም ችግር የለውም፡፡ አንድ ቀን የሥነ ዜጋና ሥነምግባር አስተማ ሪያችንን በጣም ረበሽነው፡፡ ከዚያ‹‹ የኢትዮጵያ ሕዝብ መዝሙር ቆሞ በደንብ የዘመረ 10 ማርክ እጨምርለታለሁ›› አለ፡፡ 56 ታችንም ጸጥ ነው ያልነው፡፡ 38 ተማሪዎች ሞክረው አንዳቸውም አልቻሉትም፡፡ ቲቸርየ ለነገ ተለማምደነው እንድንመጣ አስጽፈን አልነው፡፡ ብዙ ሳያስብበት ‹‹እሺ›› ብሎ ጀመረልንና መካከል ላይ አራት መስመር ብቻ ጽፎ ጠፍቶት ቀጥ አለ፡፡ ከዚያም ነቄ አልንበት፤እንዴት እንፋታው፡፡ አዘናግቶ ላሽ ሊል ነበር፡፡ ማቲስ (ሒሳብ) ክፍለጊዜ ገብቶ አስተማሪያችን ቆርቁሮ አስወጣው፤ ገላገለው፡፡ መምህር ታለጌታ፡- እሱስ እውነት ነው፡፡ እኛም አናደርግም፡፡ተማሪዎቹም እንዲያደርጉ የሚመክር አስተማሪ እስካሁን አላየሁም። ራሳችን አስተማሪዎችም ከልባችን አድርገን ማሳየት ነበረብን፡፡ እንደውም መምህር የሆንበትን እድል እየረገምን ከመዋል ባለፈ መቼ ወደነውስ እየሰራነው። መብላት ስላለብን ብቻ እኮ ነው የምናስተምረው እንጂ ተማሪው ሲቀልድ ነው የሚውለው፡፡ በቀደም እለት አንድ ተንኮለኛ ጋዜጠኛ የወራቱን እና የእለቱን ግጥምጥሞሽ እያሰላ ‹‹የካቲት 12፣ አርበኞች፣ድል ፍሬ…ወዘተ ተብለው በሚጠሩ ትምህርት ቤቶች ከች እያለ ጉድ ሰራቸው። ተማሪዎቹ የትም ህርት ቤታቸው ስም(መጠሪያ) መሆኑን እንጂ ከዚያ የዘለለ አንዳች ነገር የሚያውቁት እንደሌለ ገለጹ። የታሪክ አስተማሪዎችንም ለትዝብት እንደዳረጋቸው ሰምቻለሁ፡፡ እንደውም አንዱስ ‹‹ጥሩ ስትከፍሉኝ ጥሩ አስተምራለሁ›› ብሏል አሉ፡፡ አያ ቢተው፡- አያችሁ ታዲያ ተማሪዎቹ ከየትና ከማን ያዩ የሰሙትን ነው አገራቸውን፣ ሰንደቃ ቸውን፣ የኢትዮጵያን ሕዝብ መዝሙር ሊያውቁ የሚችሉት፡፡ የአገር ፍቅር ከልጅነት ጀምሮ አብሮ የሚያድግና ሲነካ የሚቆጠቁጥ የአካላችን አንድ ክፍል እንጂ ዘሎ መጥቶ የሚሳፈር ውቃቤ ወይም ዛር አይደል። ልጆቻችን የአገር ፍቅር ስሜትን ከቤተሰቦቻቸው በተግባር አይተው መቅሰም ካልታደሉ በትምህርት ቤት ብቻ ሙሉ ሊያደርጉት አይችሉም፡፡ ልጆቻችን የእኛ ውጤቶች ናቸው፡፡ ከእኛ ከወላጆች በተግባር ያዩትን ከእኛ በላይ ሁነውት ያድጋሉ፡፡ ልጆች ሲያድጉ እናቴን፣አባቴን ያስቀይምብኛል ወይም ነውር ነው ብለው የማያደርጉት ወይም የተከለከሉት ተግባር እንዳለ ሁሉ አገርህን(አገርሽን) ያስከፋል፡፡አገራችሁ ትቆጣባችኋለች በሌላ በኩል ይሄን ብታደርጉ አገራችሁ ታመሰግናችኋለች ተብለው ያደጉት ተግባር ሊኖር ይገባል፡፡ በትምህርት ቤት ደግሞ ይበልጥ መጎልበት ይኖርበታል፡፡ ሕጻናት እኛ ቤተሰቦቻቸው በሰራናቸው ልክ የሚያድጉ ችግኞች ናቸው፡፡ በረጅም ጊዜ ስኬት ፍሬያቸው ሊታይ የሚችል፡፡ መምህር ታለጌታ፡- እናንተ ስታድጉ ሀሜት፣ስድብ፣ አሽሙር፣ጥላቻ ፍጹም ነውር የሆኑት እና የተወገዙት በምን መንገድ ነበር፡፡ አሁን እኮ ተማሪዎቻችን መክረናቸው እየሰሙን አይደለም፡፡ አያ ቢተው፡- አልቀበላችሁ አሉ? መጀመሪያ እናንተ ሁናችሁ ተግብራችሁ አርአያ ሁኑላቸው፡፡ ከዚያ ተማሪዎቻችሁ በራሳቸው ጊዜ እንዲሆኑ የምትፈልጉትን ሆነው ታገኟቸዋላችሁ፡፡ እንደው ይሄ መከረኛ ዘመን እያላችሁ ትደልቁበ ታላችሁ እንጂ ኮ ከዚህ በላይ ወርቅ የሆነ ዘመን ታይቶም ተሰምቶም አይታወቅም፡፡ ማሰልጠኛ ፍዳ ሳይከፈል፣መሳሪያ በየዕለቱ እየፈቱ በመወልወል ሳይሞሽሩ፣ መሳሪያ ከነዘሩ አብሪ ታጣፊ እያሉ ሳይዋትቱ፣ከሞቀ ቤቱ የሞቀ ጭን እንደታቀፉ ተንደላቀው ሹም ሽር ታይቶ ያውቃል? አሜኬላ ሳይለ ብሱ ቋጥኝ ሳይንተራሱ የአገርን አሜኬላ ለመንቀል ታስቦ ያውቃል፡፡ አይታሰብም ። ችግሩ ለዘመናት ሲገረፍ የለመደ ሕዝብ ሆነና ቢያንስ ቆንጥጡኝ፣ስደቡኝ አለበለዚያ አደብ አልገዛም ማለቱ ነው። ቆዳው ነጻነትን መሸከም አይችልም፡፡አለመደም የሚሉም አሉ።‹‹የለመደ ልማድ ያሰርቃል ከማዕድ›› እንዳሉት አበው ሀሜትን፣ሽርደዳን፣ቂምን፣ጥላቻን በቡና ጠጡ የሰፈር ፕሮግራም መዝራትና ማቃቃር ሥራ ሆኖ ደመወዝ አስከፍሏል ይባላል፡፡ ዛሬ ከሥራ ገበታ ዝርዝር ሲሰረዝ በርካቶች ለአደገኛ ሥራአጥነት መዳረጋቸው ይነገራል፡፡ ፍጹም ለእኛ ለኢትዮጵያውያን አሳፋሪና አስነዋሪ የሆኑ ተግባራትን ጭምር የተፈቀዱ ያህል መላመድ አልቸገረንም፡፡አላሳፈረንም፡፡ ማታለል ፣መዋሸት፣መስረቅ (ያውም የሚልሰው ካጣ) ከፖለቲከኛ እስከ ቤተ እምነት ጓዳ ዘልቀው ከተጣቡ ሩብ ክፍለ ዘመን አስቆጥረዋል፡፡ ጥሮ ግሮ ከመክበር በአቋራጭ ከደሃ ጎሮሮ መንትፎ ፎቅ መደርደር፣ መንደላቀቅ በአደባባይ ወግ ሆኗል፡፡ እነዚህን በእውን ማድረግ የቻልን ሰዎች ከድህነት የሚያላቅቅ ወኔን መላበስ ተስኖናል፡፡ ነገሩማ አያድርስ ነው፡፡ ክፉ አመል አመለኛውን ሳያጠፋ አይጠፋም፡፡ የሚባለው ሐሰት አይም ሰላችሁ። አሁን በጥሩንባ ከመለፈፍ ላልተላቀቅን ሕዝቦች ዘመን አመጣሽ ቴክኖሎጂዎችን እንደ እድል ልንጠቀምባቸው በተገባ ነበር፡፡ እኛ ግን አሁንም የንትርክ አፈሙዝ መማዘዣ፣የሐሜት እና የጥላቻ መንዣ አድርገናቸዋል፡፡ መምህር ታለጌታ፡- ወሬን ወሬ ያነሳዋልና እዚህ ላይስ የሰማሁትን እኔም ላክልበት፡፡እነፌስ ቡክ ለእኛ አገር ከእድልነታቸው ይልቅ ጦሳቸውን አልቻልነውም። ሌሎቹ ምርታቸውን እና አገልግሎቶቻቸውን ያስተዋ ውቁባቸዋል። እኛ ደግሞ ክፋቶቻችንን፣መርዛማ ንግግሮ ቻችንን እንረጭ ባቸዋለን።ከክፋታችንና ከምቀኝነታችን የአስተሳሰብ የእድገት ደረጃ ሳንላቀቅ ፈጥነው መጥተውብን ነው፡፡ እኛ እኮ ገና ‹‹ኩብኩባ›› ደረጃ ላይ ነን ብሎ ከትከት አድርጎ ያሳቀንን የሥነ ሕይወት አስተማሪ አልረሳውም፡፡ በፖለቲካው መስክ ተከራክረህና ተወዳድረህ ልትደር ስባቸው ያልቻልካቸውን እንደ ዶክተር አብይ አይነት የልጅ አዋቂ ትንታግ መሪዎች ተግባር ከአፍ እና ከእጅ እየለቀምክ ጥላሸት በመቀባት ለፌስቡክ ጉሊት ቀርበው ይቸረችራሉ ይባላል፡፡ በአካባቢው በሚገኝ ትጉህ ነጋዴ ላይ ምቀኝነት ያደረበት ሙትቻ ነጋዴ አለያም የእሱ ቅጥረኛ ተከፋይ ሁለት ዘዴን በማጥመጃነት ይጠቀማል አሉ። የመጀ መሪያው የሐሰት ክስ መስርቶ ፍርድ ቤት እያመላለሱ ሥራ ማስፈታት ከተቻለም ንብረቱን ማሳገድ። ሁለተኛው ደግሞ የምርቶቹን ዝርዝር ከመርዛማ ቃላት ጋር ለፌስ ቡክ ጉሊት አቅርቦ ለሐሜት ንፋስ ማጋለጥ። በቀደዱለት ቦይ የሚፈሰው የፌስቡክ ጉሊት ተሰላፊ የጫኑትን ተሸክሞ ከመንጎድ በዘለለ ማላመጫም ማዳመጫም የላቸውም ይባላል፡፡ ተማሪ አለሚቱ፡- ይሄን ያህል ቀውስ ፈጥሯል እንዴ? ሁሉም ሰው ተለክፏል? አያ ቢተው፡- ሰማችሁ ልጆቼ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ጥሬ እንዳየች ጅግራ ትውልዱ ወጥመድ ውስጥ ገብቷል፡፡ ‹‹ትዝብትህን ንገረን ካላችሁ ከሕጻናት እስከ አዋቂ ምሁር ነኝ ባይ ድረስ ‹‹መርዞ›› መርዛለች፡፡ በአይኑ ከሚያየው፣ በእጁ ከሚዳስሰው እውነታ በላይ የማህበራዊ ሚዲያ አማኝ፣ሰጋጅ፣ተከታይና ዘማች ትውልድ በርክቷል፡፡ ከእምነት ቦታዎቻችን በር እኮ አንድያችንን ጠቅልለን ስንሄድ ካልሆነ በስተቀር እግራችን ድርሽ አልልም ብሎናል፡፡ እናንተም እኔም ሁላችንም የፌስ ቡክ ጋሪዎች መሆናችንን እረሳችሁት? አሁን የእኛ መሪ ማን እንደሆነ ጠፍቶን ነው? ሆሆ…ሆሆ.. ‹‹ወደው አይስቁ›› ነበር ተረቱስ፡፡ ከየት አባቴ ሣቅ ላምጣ እንጂ፡፡ እንደውም ‹‹ወደው አያብዱ›› ብየዋለሁ፡፡ አዎ ንገረን ካላችሁ ‹‹አሁን እንደው ጆሯችን ቀጥ ብሎ ቆሞ ወሬ የሚያዳምጠውና የሚጠብቀው ከቤተ መንግስት ነው ወይስ ከፌስ ቡክ? መልሱን ከራሳችሁ ኪስ ፈትሹ፡፡ መሪዎቻችን እንዲህ አሉ ብለን ከምናጣቅስ ይልቅ ሺ ጊዜ ፌስቡክን አናነሳምን? ስለዚህ እስኪ ንገሩኝ? የእኛ መሪ ማን ነው? ሕዝብ መሪውን ይሰማል፣ ያዳምጣል፣ ይከተላል፣ አብሮ ይተማል፡፡ ስለዚህ እኛ እንዲህ ነን ወይ፡፡ እየተመምን ያለነው ከየትኛው መሪያችን ጋር ነው? የየትኛውን መሪያችንን ቃል በመፈጸም ላይ ነን? ራሳችሁን ጠይቁ፡፡ ሁላችንም የፌስቡክ ነጋዴ ነን፡፡አዲስ ዘመን ሚያዝያ 3/2011በ", "passage_id": "03c862633d1b8c0c85900cb3bc4f72db" }, { "passage": "እንደተለመደው በሥራ መውጫ ሰዓት ሰርቪስ ለመያዝ ተሰልፈናል። የአጋጣሚ ጉዳይ ሆኖ ወደእኛ ሰፈር የሚሄደው መኪና ሁሌም በተሳፋሪዎች ይጨናነቃል። ብዙዎች የሾፌሩ ፍጥነትና የመንገድ ቆረጣ ስለሚመቻቸው ምርጫቸውን ለይተዋል። የባስ ካፒቴኑ ፈጣንና ቀልጣፋ ነው። መንገድ መርጦ መጓዝ ያውቅበታል።ከረጅሙ ሰልፍ መሀል ወንበር ለማግኘት የታደልነው ጎን ለጎን ተቀምጠን ጨዋታ ይዘናል። ተራው ያልደረሳቸው ደግሞ ከውጭ ወደውስጥ እያንጋጠጡ ነው። እንደእውነቱ ከሆነ ራቅ ያለ መንገድ ቆሞ መሄድ ከባድ ነው። እንደታክሲ ሦስት ሆኖ መቀመጥ ደግሞ አይሞከርም። እናም ከደጅ ያሉት ተንጠራርተው ቢያንጋጥጡ አይፈረድም።መቼም የመንገድ ላይ ወግ አይነቱ ብዙ ነው። አንዳንዴ ስለቤት ጣጣ ይወራል። አንዳንዴ ደግሞ ወቅታዊና አገራዊ ጉዳይ ሰፊ ሽፋን ያገኛል። ብዙ ጊዜ ግን አስራሁለት ሰዓት ላይ የሚደመጠውን ዜና መነሻ አድርጎ የሚከተለው አስተያየት ይበረክታል። ጥግ ይዘው የሚያንጎላጁት መንገደኞችም ከዕንቅልፋቸው በባነኑ ጊዜ የሚጨዋወቱት አያጡም።እሰይ! አሁን መንገዱን ገፋ አድርገነዋል። ፈጣኑ ካፒቴን እንደተለመደው በአጭር ጊዜ ረጅሙን ጎዳና አጋምሶታል። ሜክሲኮ አደባባይን ከመሻገራችን መጨናነቅ መጀመሩ ግን እንዳያስመሸን እየሰጋን ነው። ከኋላችን ደርሶ «እሪ» የሚለው አምቡላንስ ማለፊያ በማጣቱ ጨኸቱ ቀጥሏል። አንዳንድ መኪኖች ችግሩን ተረድተው ሊያሳልፉት እየሞከሩ ነው። ይህ መሆኑ ብቻ ግን እምብዛም መፍትሄ አልሆነም።\nየአምቡላንሱን ጨኸት ተከትሎ አዲስ ጨዋታ ተነሳ። አንደኛው የሚናገረው ከሌሎች በተለየ ነው። እርሱ አካባቢውን ስላወከው ድምጽ እምብዛም የተጨነቀ አይመስልም። መኪናው የታመመ ሰው ይዟል የሚለው እውነታም አልተዋጠለትም። እንደውም በስፍራው እንደተገኘ ሆኖ አሳማኝ የሚመስሉ ማሳያዎችን መምዘዝ ይዟል። የእርሱን ሀሳብ ተከትሎም ብዙዎች የራሳቸውን ግምት ማከል ጀምረዋል። በየወንበሩ ጨዋታው ደርቷል። አስተያየትና የግምት ሀሳብም እንዲሁ፤የእኔን ጆሮ የሳበው ግን ይህ አይነቱ ክርክር አልነበረም። ከጎኔ የተቀመጠችው ወይዘሮ በስልኳ በያዘችው ፎቶግራፍና ተያያዥ ታሪክ ልቤ ተማርኳል። ጉዳዩን በጥልቀት ስሰማው ደግሞ አእምሮዬ ርቆ ተጓዘ። በዚህ መሀል የብዘዎችን የተሳሳተ ግምት አሰብኩ። ራሴንም ገመገምኩ። እውነት ግን ስንቶቻችን በተሳሳተ እሳቤ እንመራለን? ስንቶቻችንስ ይህን በጎ ያልሆነ አመለካከት እንደያዝን እንገኛለን?ነገሩ እንዲህ ነው። አንድ ማለዳ ወደቤ ተክርስቲያን የሄዱት አባወራ ጸሎታቸውን አድርሰው ዞር ከማለታቸው ከአንድ ጎስቋላ አዛውንት ጋር ዓይን ለዓይን ይጋጫሉ። ሰውዬው ጥሩ ቁመና ቢኖራቸውም ኑሮ እንደጎዳቸው ያስታውቃል። ከላይ የደረቡት ልብስ አርጅቷል። ጫማቸው አልቋል። ችግር ያንገላታው መልካቸው ድካም ተጭኖታል።ከእርሳቸው አለፍ ብሎ ከተቀመጡት ባልንጀራቸው ጋር በልመና የሚያገኙትን ቁራሽ ይካፈላሉ። ለነፍስ ብሎ ሳንቲም የሚጥል ሲገኝም የተሰጣቸውን ተቀብለው ለሌላ ምጽዋዕት እጃቸውን ይዘረጋሉ። ልመና ለአዛውንቶቹ መተዳደሪያ ከሆነ ዓመታት ተቆጥረዋል።\nከሁለቱ ግን የአንደኛው ታሪክ ይለያል። ባገራቸው ቤት ንብረት አላጡም። ጥማድ በሬና የሚታረስ መሬትም አላቸው። እንደዋዛ አዲስ አበባን የለመደው እግራቸው ግን በቀላሉ አልመለሳቸውም። የልጆቻቸው ከተማ መዝለቅ ምክንያት ሆኗቸው ዋል አደር ማለት ለመዱ። ልጆችና እርሳቸው በአንድ ቤት አይኖሩም። ገሚሶቹ በቀን ሥራ ራሳቸውን ይደጉማሉ። የተቀሩትም በተመሳሳይ ሙያ ተሰማርተው ገንዘብ ያገኛሉ።አሁን አባትና ልጆች በአንድ ቤት ስለማይኖሩ አዋዋላቸውም ለየቅል ሆኗል። አባት በልመና ከሚያገኙት ገንዘብ የራሳቸውን ቤት ኪራይ ይከፍላሉ። ባገኟት ቁራሽ ሆዳቸውን ይችላሉ። በልመና ውሎ ህይወታቸውን ይመራሉ። ከማለዳ እስከምሽት በሚዘልቁበት አጸድ ብርድና ፀሐይ ብርቃቸው ሆኖ አያውቅም። ሁሉንም እንደአመጣጡ ተቀብለው የሰው ፊት ማየትን ከተለማመዱት ቆይተዋል።በቅርበት ሆነው ሁኔታቸውን ሲያስተውሉ የቆዩት አባወራ በአዛውንቱ ጉስቁልና ልባቸው በኀዘን ተነክቷል። ይህ ስሜት ብቻ ግን የበቃቸው አይመስልም። እርሳቸውን እያሰቡ ከቤት የተቀመጡትን ልብሶች ያስታውሳሉ። ካስታወሷቸው መሀልም ለእርሳቸው የሚበጀውን ይለያሉ። ይህን ሀሳባቸውንም ለአዛውንቱ ሲነግሯቸው ምስኪኑ ሰውየ ከልብ ተደሰቱ። እንዲህ አይነት ቅን አሳቢ ስላገኙም ፈጣሪያቸውን አመሰገኑ።አዛውንቱና አባወራው ወደቤት ከመሄዳቸው በፊት ጉዳዩን የሰሙት ባልንጀራቸው ጥያቄ አነሱ። እርሳቸውም እንደጓደኛቸው ቢለብሱ እንደሚወዱ ተናገሩ። አባወራው በጥያቄአቸው አልተከፉም። ሁለቱንም ሊያለብሷቸው ቃል ገብተው እንዲከተሏ ቸው አደረጉ።\nእኔና ወይዘሮዋ ጨዋታችንን ቀጥለናል። በግሌ የሰዎቹ ታሪክና የአባወራው ቅንነት እያስገረመኝ ነው። እግረመንገዴን በርካቶችን አሰብኳቸው። ቤት ንበረታቸውን ትተው፤ የሞቀ ትዳራቸውን ፈትተው ለልመና የተዳረጉ ቁጥር አልባ ወገኖች ትውስ አሉኝ ። ቤት ይቁጠራቸው እንጂ ብዙዎቹ ተመሳሳይ ህይወት ይጋራሉ። እያላቸው የሌላቸው ሳያጡ ያጡ ጎስቋሎች ጥቂት አይደሉም።ሦስቱ ሰዎች ጀሞ አንድ ከሚገኙ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በአንደኛው ተገኝተዋል። አባወራው ከፊት ቀድመው ሁለቱ እየተከተሉ ነው። በቁምሳጥኑ ከተሰደሩት ሙሉ ልብሶች መሀል ያሰቧቸውን አውርደው ለአዛውንቶቹ መስጠት የጀመሩት ሰው ምስጋና እየደረሳቸው ነው። እነርሱም የተራበን ያበላ፣ የታረዘን ያለበሰ በሚለው ቃል መሰረት ቅን ላደረጉት አባወራ ምርቃት እያወረዱ ነው።አሁን ሁሉም ተጠናቅቆ ተሰነባብተዋል። ይህ ከመሆኑ በፊት ግን ዳግም ለመገናኘት ቀነ ቀጠሮ ወስደዋል። ከቀናት በኋላ አባወራው በቤታቸው የሚያደርጉትን ጠበል ጠዲቅ ምክንያት አድርገው እንዲመጡ ጠርተዋቸዋል። ሁለቱም ተጋባዞች ዕለቱን አልዘነጉም። እንዲህ አይነቱ ጥሪ ለእነሱ ከስንት አንድ ነው። አክብረው የሚጠሯቸውና እንደሌሎች በእኩል የሚጋብዟችውም ጥቂቶች ናቸው።ቀናት ተቆጥረዋል። በአባወራው መኖሪያ ለጠበል ጸዲቁ የሚሆነው ዝግጅት ተጀምሯል። የሚጠሩ ሰዎች ተለይተው የጎደለው ሁሉ ተሟልቷል። ሁሌም ዕለቱን አስበው የሚዘክሩት ባልና ሚስት በጥሪው የሚገኙ እንግዶች እንዳይረሱ ያስባሉ።አሁን ቀኑ ደርሷል። እንደተለመደው መላው ቤተሰብ በመስተንግዶው ተዋክቧል። እንግዶች ይገባሉ፣ ይወጣሉ። አባወራውና ወይዘሮዋ ቆመው ያስተናግዳሉ፤ ሰዎችን ይቀበላሉ፣ ይሸኛሉ። ከተጠሩት መሀል ቀኑን ያልዘነጉት አዛውንት በሰዓቱ ተገኝተዋል። እርሳቸው ከሌሎች ቀደም ብለው ቢገኙም እንደአመጣጣቸው ፈጥነው መውጣት አልፈለጉም። ወጪ ገቢውን እያስተዋሉ በዝምታ ተቀምጠዋል።ቀኑ ተጋምሶ ምሽቱ እንደተቃረበ የተጠሩት እንግዶች ቁጥርም ጋብ ማለት ጀመረ። ጥቂት ቆይቶም ቤቱ ጭር አለ። ይህኔ አዛውንቱ እንግዳ ከመቀመጫቸው ተነሱ። ተነስተውም መላው ቤተሰብ ወደ እርሳቸው እንዲመጣ ጠየቁ። ይህን የሰሙ ሁሉ ቃላቸውን አክብረው በአንድ ተሰባሰቡ። ቀኑ እየመሸ በመሆኑ አባወራውና ባለቤታቸው ማሰብ ጀምረዋል። የእርሳቸው ቤት ከአካባቢው የራቀ በመሆኑ እያስጨነቃቸው ነው ። እርሳቸው ግን ይህ ሁሉ ስሜት ምናቸውም አልነበረም።ንግግራቸውን በተለየ ምስጋና የጀመሩት እንግዳ እንባ እየተናነቃቸው እጃቸውን ወደጉያቸው ሰደዱ። ወዲያው ዳጎስ ያለ እስር በጣቶቻቸው መሀል ታየ። አዛውንቱ ያወጡትን ከማስረከባቸው በፊት ስለሆነው ሁሉ ተናገሩ። የዛን ዕለት አባራው ስለእርሳቸው አዝነው ሙሉውን ልብስ በሰጧቸው ጊዜ ቤታቸው ገብተው ልብሱን ሲለኩት በኮቱ የውስጠኛው ኪስ የታሰረ የብር ኖት ያገኛሉ።ብሩ ከለመዱት መጠን የበዛ በመሆኑ በድንጋጤ ክው ብለው ይቆያሉ። አዎን! አባወራው በተለገሳቸው ሙሉ ልብስ ውስጥ አስር ሺ ብር እንደታሰረ ተቀምጧል። ይህን ሲመለከቱ አዕምሯቸው ክፋት አላሰበም። ቅን አስቦ መልካም ላደረገ ማንነት ውለታው በበጎነት መመለስ እንደሚኖርበት ወስነው ብሩን እንደነበረ አስቀመጡት። ይህን እውነት ያጫወተችኝ ወይዘሮ ይህ ታሪክ በባለቤቷና በመኖሪያ ቤቷ ስለመፈጸሙ ሳውቅ ግርምታዬ ላቀ ።ሰውዬው ያስረከቡትን የአስር ሺ ብር ጥቅል ባለቤቷ ቆጥረው ሲረከቡም በፎቶግራፍ የቀረውን ምስል ተመልክቼ አረጋገጥኩ። ወዳጆቼ! እውነት እንነጋገር ከተባለ ምን ያህሎቻችን እንሆን ይህን መሰሉን ታሪክ የምንጋራው? ማንኛችንስ ነን ሰውን በልቡ ሳይሆን በልብሱ ብቻ የማንመዝነው? እኚህ ገንዘብና እንጀራ ናፋቂ አዛውንት ግን ይህን እውነት ፈጽመዋል። ሰዎችን በልብስ ብቻ ሳይሆን በንጹህ ልቦና ብቻ እንድንመዝንም አስተምረውናል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 24/2011መልካምስራ አፈወርቅ", "passage_id": "53d642158a8f272c4658dbff4dcacaaa" }, { "passage": "በውንሽፍሩና በዝናቡ መሀል አልፎ አልፎ ንፋስ ያፏጫል፡፡ መጣሁ ቀረሁ ሲል የነበረው ዝናብ በሰማዩ አዥጎድጓጅ የመብረቅ ድምፅ እየታጀበ ማስገምገሙን ቀጥሏል፡፡ ሰዓቱ ከትምህርት ቤት፤ ከሥራ መውጪያ ወደቤት መመለሻም በመሆኑ ከዝናቡና ከጎርፉ ለመሸሽ የሚደረገው የሕዝቡ ሩጫ የክረምቱን መግባት ያበስራል።እነሆ ክረምቱ ገባ፡፡ እንግዲህ ዝናቡን ውሽንፍሩን የመብረቁን ጩኸት የወንዞችን ሙላትና ግሳት እያዩ መክረም ነው፡፡ የክረምቱ ዝናብ አዛዥ የለውም፡፡ አያ እንደልቡ፡፡ ያሻውን ያፈርሳል፡፡ ያሻውን ይንዳል። በል ሲለውም ይደረምሳል፡፡ ክረምቱ ጠፍተው ተደብቀው የነበሩ እፅዋትንም ያሳድጋል። ክረምት ገብቶ ዝናብ ከነጠፈ ችግር ይገባል፡፡ ውሃ የለም፤ሕይወት የለም፡፡ ክረምት ለዘለዓለም ይኑር እንበል እንዴ? አባ ሙላት ክረምት፤አባ አደፍርስ ክረምት ባሻው አዳሪ ባሻው ፈሳሽና ተንጎማላይ ነው። ሰማዩ ጨለማ መስሎ ሲዳምን በሙሉ ግርማ ሞገስ በመብረቅ እየታገዘ ሲያስገመግም ሁሉም በያለበት ይመሽጋል።ክረምቱ ሲወድቅ (ሲገባ) ትርው ዝርው የለም ይሉ ነበር በጎጆ ቤታቸው ውስጥ የወይራ ፍልጦችን ማግደው የተጋጋመን እሳት እየሞቁ ዙሪያቸውን የመንደሩን ውሪ ሰብስበው እየተጫወቱ ይሞቁ የነበሩት እማማ ዲንጎ፡፡ እማማ ዲንጎ ባላቸው በኢጣሊያን ጦርነት ከመዝመታቸው በፊት ስድስት ልጆች ነበራቸው። የደረሱት ጎረምሶች ከአባታቸው ጋር ዘምተው ሁሉም ሳይመለሱ በዚያው ቀርተዋል፡፡ የተቀሩት ሴቶች ደግሞ አግብተው ወልደው ይኖሩ ነበር። ዛሬ ማንም አጠገባቸው የለም፡፡ ልጆቻቸው የመንደሩ ልጆች ናቸው፡፡ ይላላኳቸዋል፡፡ የሚረዷቸውና ከእሳቸው ጋር የሚኖሩም አሉ፡፡ ታዲያ አንዳንዴ በሃሳብ ይቆዝማሉ፡፡ ‹‹ምነው እማማ›› ሲሉ ልጆቹ እሳቸው ደግሞ ‹‹ምንም ልጆቼ ምንም›› ይሉና ያንጎራጉራሉ። ከቤታቸው የአበሻ አረቄ አይጠፋም፡፡ ከሌለም ያስገዛሉ። ይሄ እኮ ዋናው የብርድ መድሀኒት ነው ይላሉ። ስለሚያሞቃቸው ይሆናል፡፡ እማማ ዲንጎ ጨዋታና ቀልድ አዋቂ በመሆናቸው በመንደሩ ነዋሪ በትንሹም በትልቁም የተወደዱ፤በሰፈሩ የተከበሩ አንቱ የተባሉ አዛውንት ናቸው፡፡ የባሕል ሕክምና አዋቂ በመሆናቸው የታመመ ሰው ሁሉ ሀገር አቋርጦ ቦታቸውን ጠይቆ እሳቸው ጋር ይመጣል፡፡ በባሕላዊው ኬሚስትሪ እሳቸው የሚያውቁትን ሥራ ሥሩን ቅጠላ ቅጠሉን ቀጣጥፈው ቀምመው ለታመመው ይሰጡታል፡፡ የሩቅ ሀገር ሰው ከሆነ ለሕክምና የመጣው እዚያው ጎጆ ቤታቸው መደብ ላይ ተኝቶ ቤት ያፈራውን መግበውት ድኖ ይሄዳል፡፡ ዙሪያ ገባውን በቅርብና በሩቅ ያለው ሕዝብ ‹‹እማማ ዲንጎ እጃቸው መድሀኒት ነው›› ብሎ ስለሚያምን የታመመ ሁሉ ወደሳቸው መሮጡ አዲስ አይደለም፡፡ በኢጣሊያ ወረራ ጊዜ የነበሩ አንዳንድ ሰዎች የሀኪም ስም ‹ዶክቶራ› ነው የሚባለው ብለው ለሕዝቡ ወሬ ስለነዙ እማማ ዲንጎን ዶክቶራ ብለው የሚጠሯቸውም ነበሩ፡፡ ‹‹ምነው እኔ በፈረንጅኛ ጥሩኝ መቼ አልኩ›› ብለው ይቆጣሉ፡፡ ጥሎባቸው ፈረንጅ የሚባል አይወዱም፡፡ ምናልባት በጦርነቱ ለሀገራቸው ክብር ሲዋደቁ የሞቱትን ልጆቻቸውንና ባላቸውን እያስታወሱ ይሆናል፡፡ አይፈረድባቸውም፡፡ ‹‹ፈረንጆች ሰላቢዎች፤ መተተኞች ናቸው›› ይላሉ እማማ ዲንጎ፡፡ ‹አረ ተው እማማ ዲንጎ አይባልም›› ቢሏቸውም በጄ አይሉም፡፡ ‹‹ሰላቢ፣ መተተኛ ፈረንጅ ነው›› ሲሉ አባ ሻቃ የተባሉ አዛውንት ለጠቅ አድርገው ‹‹አይ ዲንጎ፤ አሁን ከእኛ ደብተራዎች በላይ መተተኛ አለ ብለው ነው›› ቢሏቸው ‹‹እሱማ እውነት ነው የእኛንማ ማን ያህል መተተኛ ደብተራ ሁላ›› በማለታቸውም ይጠቀሳሉ። ፈረንጅ ደግሞ ምን ያውቃል ከእኛው እውቀትና ጥበብ እየወሰዱ አይደለም እንዴ የሚኩራሩት ይላሉ።የውጭው ስልጣኔ እምብዛም ባልታወቀበት ዘመን በራሳችን የቀደመ ስልጣኔ ኩሩዎች ነበሩ አባቶች፤ እናቶችና አያቶቻችን።እነ እማማ ዲንጎ፡፡ እንደዚህ እንደ አሁኑ ዘመን ከማንነታቸው ተፋተው ነጭ አምላኪ አልነበሩም፡፡ የእኛን የባሕል መድሀኒት ጠይቆ እየወሰደ አይደለም እንዴ ፈረንጅ በሌብነት የከበረው ብለው ይቆጣሉ። እማማ ዲንጎ አንዳንዴ የበዛ ነጭ አምላኪ ሰው ሲገጥማቸው፡፡ እናንተ ልጆች እስቲ በቅጡ ሁኑ፡፡ ወደ ቀልባችሁ ተመለሱ፡፡ ኢትዮጵያ ብዙ ሊቃውንት የእውቀት አውራ የሆኑ አባቶች የነበሯት ያሏት ሀገር ነች፡፡ ጠጋ ብላችሁ አክብራችሁ ብትይዟቸው ብትጠይቋቸው ብዙ መላ ታገኙ እውቀትም ትጨብጡ ነበር። ይላሉ እማማ ዲንጎ፡፡ ሰሚ ቢገኝ፡፡ የራሳችሁን ባህል እውቀት ጠብቃችሁ ብትይዙት ትከበሩበት ነበር፡፡ ዳሩ ምን ያደርጋል፡፡ ‹‹መቼ ሰሚ አለና›› በማለት ከልባቸው ይጸጸታሉ፡፡ እንደው ደርሶ የራስን ባሕልና እውቀት እያጣጣሉ፤ ኋላ ቀር ነው እያሉ ፤የነበረውን እያጠፉ፤ ታሪክና ባህል እንደሌለው ነጭ አምላኪ መሆን ያሳፍራል እናንተ ልጆች ይላሉ ድምፃቸውን ዘለግ አድርገው፡፡ እማማ ዲንጎ በትንሹ እስቲ ይሄን እውቀት አስተምሩኝ ግለጡልኝ የሚል ልጅ እንኳን የለም፡፡ ይዤው አልሄድ፡፡ ይልቅስ ለእናንተ ይበጃችሁ ይላሉ ዙሪያቸውን ወደከበቧቸው ልጆች ዞር ዞር እያሉ፡፡ እንግዲህ ክረምቱ ተግ አድርጎ ያበቀለውን ለሀገር ባሕል መድሀኒት የሚሆኑ የተለያዩ እፅዋት በከተማ ዳርቻና በገጠር በየገዳሙ በየበረሀው ጭምር እየዞሩ ለእነ እማማ ዲንጎ ፈልፍለው የሚያመጡ አዋቂዎች በብዛት ነበሩ፡፡ ዛሬ የሉም፡፡ ‹‹የሀገራችን ሰው መቼም ሲያጣጥል አያድርስ ነውና ቅጠል በጣሽ፤ስር ማሽ ይላቸዋል። የመድሀኒቱን ቅጠል ለይቶ ለመቁረጥ ስሩንም ምሶ ለማውጣት እኮ ባሕላዊ እውቀት ይጠይቃል። አለበለዚያ መድሀኒቱ ከየት ይገኛል›› ብለው ይገረማሉ እማማ ዲንጎ፡፡ እነዛ ሰዎች አብዛኞቹ ወደ ሰማይ ቤት ተጉዘዋል፡፡ ‹‹ሆሆይ— እንዴ በእግራቸው የሚተካ ልጅ እንኳን ይጥፋ›› ብለው ከመገረም አልፈው ይተክዛሉ፡፡ ‹‹ለአወቀውማ ይሄ እውቀት የሀገር ሀብት ነበር፡፡ የሀገር መድሀኒት፡፡ ፈረንጁም እኮ ዘመናዊ መድሀኒት የሚሠራው በሀገሩ ከኖረው የቆየ የባሕል ሕክምና እውቀት ተነስቶ ነው፡፡ ‹ከሞኝ ደጃፍ ሞፈር ይቆረጣል››› አሉ አባ ይልቃል፡ ፡ ደገሙና እውነት ብለዋል አሉ ዲንጎ፡፡ እሳቸው ነበሩ በየገዳሙ በየታቦቱ፤በየገበሬው መንደር በረሀ ጭምር ሳይቀር እየዞሩ የማይገኙ የቅጠላ ቅጠል መድሀኒቶችን ስለሚያውቋቸው ሰብስበው የሚያመጡልኝ፡፡ ዛሬማ ምን አለ ብላችሁ ነው፡፡ የአባቶቻችሁ እውቀት ከጣሪያ በላይ የዘለለ ነበር፡፡ የትኛው ልጅ በእግራቸው ተተክቶ ያግኘው የማይሆነውን መመኘት ብለው ተከዙ፡፡ በጥንት ጊዜ ከተማ የሚባሉትም ሆነ የገጠር መንደሮች ሁሉም በሳር ክዳን የተሠሩ ጎጆ ቤቶች ነበሩ፡፡ በዚያ ዘመን ክሊኒክ፣ ሀኪም ቤት የሚባል አልነበረም፡፡ ሁሉን ሸፍነው ሕዝቡን ያክሙ ያድኑ የነበሩት የእራሳችን የባህል ሕክምና አዋቂዎች ነበሩ፡፡ እነ እማማ ዲንጎ። ስንቱ ጀግና፤ ስንቱ አድጎ ለትልቅ ደራጃ የበቃ ጎበዝና ቆነጃጅት የተወለደው ሀኪም ቤት አልነበረም፡፡ በባሕላዊ ሐኪሞቻችን እንጂ። ወድቆ የተሰበረው ስሩ የዞረው ሮጦ መሄጃው እነሱው ጋ ነበር፤አሽተው ልክ ያስገቡለታል። እውቅ ወጌሻም አዋላጅም ነበሩ፡፡ በእጃቸው ለደባበሱበትም ሆነ ላከሙበት የሚያስከፍሉት እንደዛሬው ሙላ የሚያላቅቅ ዓይን ያወጣ ገፈፋና ዘረፋ የሞላበት አልነበረም፡፡ በልኩ ነበር፡፡ የዛሬው ዘመን ሲታይ የጥንቶቹን ያስታውሳል። ኸረ እናንተ ብሩካን ሆይ ወደስተየት አላችሁ ብሎ ትውልዱ ቢናፍቃቸው ነውርም የለው፡፡ የካርድ\nማውጫ፤\nሀኪምጋ\nመቅረቢያ፤\nለምንትሴ\nለቅብጥርሴ፤\nለምርመራ\nወዘተ በሚባል ስመ ብዙ ገቢ ማሰባሰቢያ የሕዝቡን ወገብና አንጀት የሚበጥስ የሂሳብ ክፍያ አልነበረም፡፡ ድሀ ሆይ አትታመም፡፡ አምላክህ ይጠብቅህ፤ አምላክህ ይቁምልህ፤ ከማለት በዘለለ በዚህ ዘመን ሰው ታሞ በሕክምና ይድናል ለማለት ድፍረት አነሰን፡፡ አነሰን እንጂ፡፡አዲስ ዘመን ግንቦት 29/2011", "passage_id": "61dd4857b19c7fe519f7cad5dc2e4dd0" }, { "passage": "ንድ ወጣት ሶስት ጉልቻ ሊያቆም አስቦ ከህይወቱ ረጅሙን ዘመን በምርጫ ያሳልፋል። የሚያማልለውን መልክ ሲያስስ የባህሪ ነገር ያሳስበዋል፤ መልኳም ባህሪዋም የተስተካከለውን ሲያገኝ ደግሞ የሙያዋ ነገር አልሳካ ይለዋል። እነዚህን ሁሉ አሟልታለች ብሎ ያገኘ ግዜ ደግሞ ቤተሰቦቿ እሱ እንደሚፈልገው የተመረጡ ፣ የከበሩና የተከበሩ አይሆኑም። እንዲህ ግራ በመጋባት በሰፊ የምኞት ጀልባ የሚቀዝፈው ውቅያኖስ አልገፋ ሲለው የቤተሰቡ የንሰሀ አባት ወደ ሆኑት አንድ መነኩሴ ጥያቄውን፣ የጨነቀውን ሊያካፍልና መንፈሳዊ ከሆኑት ግራ ቀኙን አይተው ምክር ይለግሱኛል ብሎ ወደተማመነባቸው አባት ያመራል። የተለመደውን ሰላምታ ሰጥቶ ቡራኬ ያቸውን ከተቀበለ በኋላ ከጎናቸው አረፍ ብሎ አይን አይናቸውን ተመለከተ። አባ ? “አቤት ልጄ ምን እግር ጣለህ”? ጥያቄያቸው አስቀደሙ ከአፉ የሚወጣውን ለመስማት አንገታቸውን ጎንበስ አድርገው እየጠበቁ። እሱም ምን ብሎ እንደሚጀምር ግራ ገብቶት ትንሽ መሰላሉን ቀጠለ። ወጣቱ ቀጠለ”ሚስት ላገባ ፈልጌ ነበር ?” አባት ፈጠን ብለው” እንዴ ይሄማ ጥሩ ነው፤ የፈጣሪን ትእዛዝ መፈፀም እኮ ነው።” ወጣቱ “አይ አባ ግን ሊሳካልኝ አልቻ ለም። አባ” “ለምን ?” ወጣቱ”እኔ የምፈልጋት አይነት ሴት ማግኘት አልቻልኩም።” አባ”አንተ ምን አይነት ሴት ነው የምትፈልገው?” ወጣቱ ”ቆንጆ ፣ደግ ፣ የተማረች፣ ስነምግባር ያላት\n፣ሀብት ያላት…” ቀጠለ ከልቡ ያለውን ፍላጎት ሁሉ ዘረዘረላቸው። አባ ከአጎነበሱበት ቀና ብለው ”አይ ልጄ እንዲህ አይነት ሴት ብትኖር ኖሮ እኛም ባልመነኮስን ነበር”። አሉ።\nይሄውልህ ሰው ሁሉ በተፈጥሮ በሁሉ ነገር ሙሉ አይደለም። በአንዱ ስታመሰግነው በአንዱ ይጎልብሃል፤ በዛ ላይ ሰዎች እኛ እንደምንፈልገው እንዲሆኑ በተመኘን ቁጥር የበለጠ ጎዶሎ ሆነው ይታዩናል። ስለዚህ አንተ በሁሉም ነገር ወደመረጥካት ለመቅረብ ራስህን አስተካክል እንጂ የተስተካከለ ለማምጣት አትሞክር። ፍፁማዊ ሰው ፍፁማዊ ህይወት የለምና ይሄን አትመኝ። አንተም በሌሎች ሰዎች ብዙ ጉድለቶች አሉብህ። ሆኖም ከሰው ጋር ለመኖር የጎደለው እየሞሉ እየተቻቻሉና እየተደጋገፉ ነው ብለው ምክር ለገሱና ሸኙት። ይህን የቆየ ትርክት ያቀርብኩላችሁ አታውቁትም ብዬ ሳይሆን ለሀሳቤ መንደርደሪያ ቢሆ ነኝ ብዬ ነው እንጂ የኔ ነገር ወዲህ ነው። ከቀናት በፊት ነው የመሬት ካርታ ጉዳይ ለማስፈፀም በአዲስ አበባ ከሚገኝ ክፍለ ከተሞች በጠዋት የተገኘሁት። በክፍለ ከተማው መሬት አስተዳደር ቢሮ የተገኘሁት ለአምስተኛ ግዜ ቢሆንም የነበረው አካሄድ ያለጥርጥር ደጋግሜ እንደምመላለስ የሚያሳብቅ ነበር። እናም ምሬትም ተስፋ መቁረጥም መበሳጨ ትም የታከለበትን ውይይት አብረውኝ ካሉት ተገልጋዮች ጋር ጀመርን። ሁላችንም በሚሰጠው አገልግሎት ደስተኞች አልነበርንም። የየራሳችንን ችግር ውጣ ውረድ እያነሳን አሰራሩ እንዴት መስተካከል እንዳለበትም የግል አስተያየታችንን ሰነዘርን። ትንሽ ቆይተው የተቀላቀሉን አንድ አዛውንት ግን ችግሩ ዛሬ ባሰበት እንጂ እዚህ ሀገር ሁሌም መጉላላት እንዳለ ማብራራት ጀመሩ። በንጉሱ ዘመን ከየትምና የእከሌ ልጅ ነው ካልተባለ የሚሰማህ የለም። ለእነሱ የሆነ እንደሁ የባላምባራስ ልጅ ነው፤ የነጋድራስ ልጅነው አንዳንዴም የእከሌ ዘመድ ነው ካልተባለ ጉዳይህን የሚሰማ የለም። እጅ መንሻም አቅርበህ እንኳ የምትገፋበት ግዜ ነበር። ደርጉም ያው ነው የጄነራል እከሌ፤ የኮሎኔል እከሌ እየተባለ ማእረግ ስልጣን ካልተጠራ ከመስከረም እስከ መስከረም ብትመላለስ ዞር ብሎ የሚያይህ የለም። አቤት ለማለት እንኳ የሚፈራበት ግዜ ነበር። ይቆጡሃል፤ ትገለመጣለህ ፤ትሰደባለህ። አሁንም ያው ነው ለስሙ ዲሞክራሲ መብት ምናምን ይባላል እንጂ ለደሀው የተረፈው ስብሰባና ወሬ ብቻ ነው። ድሮ ተቆጥተው፣ ገላምጠው፣ አገጫብረው አመት ሁለት አመት ያመላልሱ ነበር። አሁን ደግሞ ፈገግ ብለው እየሳቁ አመት ሁለት አመት ያመላልሱናል። ደግሞ እኮ እንደአህያ መልክ ሁሉም መስሪያ ቤት ያሉት ሰራተኞች በክፋት አንድ ናቸው። ሀኪም ቤት ሂድ፤ ውሃ ፍሳሽ ሂድ…. ምን አለፋህ ህዝብን በደሉ፣ አንገላቱ፣… ተብለው የተቀመጡ ነው የሚመስሉት። አዛውንቱ ቀጠሉ፤ እስካሁን ያለችውን ኢትዮጵያን ያለበሷት ማቅ አልበቃ ብሏቸው ወደ ፊቷም ጀመሩ። እናንተ ልጆች ናችሁ ብቻ ፈጣሪ እድሜ ሰጥቶ ያሳያችሁ እንጂ የዛሬ አርባ አመትም እዚች ሀገር ምንም የሚቀየር ነገር የለም። አያያዙ ሁሉ ያስታውቃል። አንዱ ወጣት ጣልቃ ገብቶ ከሞቀ ወሬያቸው አናጠፋቸው እርስዎ ምንድ ነው የሚሰሩት ? አሁንማ ምን እሰራለሁ ጡረታ ከወጣሁ አስር አመት ሊሞላኝ ነው። ድሮማ ምን ያልሰራሁበት ቦታ አለ አለ መዘጋጃ ቤት ብትል፤ መብራት ሀይል ብትል፤ ውሃና ፍሳሽ ብትል ምን አለፋህ በቀዳማዊ ሀይለ ስላሴ ዘመን ከንግድ ስራ ኮሌጅ በዲፕሎማ ከተመረቅኩበት ግዜ አንስቶ ጡረታ እስክወጣ ድረስ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ስር ያልነካሁት ቦታ ያላየሁት ጉድ የለም እያሉ በጣፋጭ አንደበታቸው ትረካውን ምሬቱን እያቀ ላቀሉ ያቀርቡልን ጀመር። እኛም ለማድ መጡ ጆሮ ሰጥተናል። ማንም ያጥፋ ማን ተወቃሹ ትውልድ እኛ አይደለን? ወጣቱ በስጨት ብሎ አዛውንቱን አስከፍቶ ውይይቱን ለመበተን ያበቃውን ንግግር ድምፁን ከፍ አድርጎ ተናገረ። ከተረት ውጪ ያለ ድካም ማርና ወተት የምታቀርብ ሀገር የለችም። እኔ እርሶዎን ብሆን ዲፕሎማዬን እንደያዝኩ ሀገሪቱን እለቅ ነበር። አሁንም ግን እንደማትቀየር እርግጠኛ ከሆኑ የሚሄዱበት ሌላ ሀገር ፈልገው ቢሄዱ ጥሩ ይመስለኛል። ተስፋ መቁረጥ አንድ ነገር ነው ሰውን ተስፋ ማስቆረጥ ግን ለማንም አይበጅ። ስለዚህ እያንዳንዳችን እየሰራን ብንጠይቅ ለኛም ለሀገርም ለህዝብ ይበጃል አለ። ሁላችንም በዚህ ሀሳብ ተስማማን። በያለንበት በየደረስንበት ያለፈን ታሪክ ከመተረክ አሁን በተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት መስራት፤ ወጣቱን ተስፋ ከማስቆረጥ ወጣቱን በተስፋ መሰነቅ፤ ስነልቦናውን ማነሳሳት፣ ሰርቶ ማሰራት… ያኔ የጎደለው ይሞላል። የሰነፈው ይንቀሳቀሳል፤ ሙሰኛው ያፍራል፤ ለዚህ ግን ሰጪም ተቀባይም እጁን መሰብሰብ አለበት ባይ ነኝ።አዲስ ዘመን ሰኔ 23/2011 ", "passage_id": "92495d7076d8d72f84f3365280b6e405" } ]
91277392701320c5cb323ac1d8563c95
b77c8ba81f69726e50f4a3aff664e0ec
ለአዳኞች እጅ የሰጠው ግዙፉ ተኩላ
በሩሲያ በረዷማ አካባቢዎች ላይ በሚገኙ ደኖች ውስጥ ተኩላዎች በብዛት ይኖራሉ። እነዚህ ተኩላዎች ታዲያ በጫካ ውስጥ የሚኖሩ ሌሎች እንስሳትን ይመገባሉ እንጂ ለአካባቢው ነዋሪዎች ብዙም ስጋት አይሆኑም። በሩሲያ አንዲት አነስተኛ መንደር ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ግን በአንድ ግዙፍ ተኩላ ስጋት ገብቷቸው ሲቸገሩ ቆይተው ሰሞኑን እፎይ ብለዋል ሲል ኦዲቲ ሴንትራል ፅፏል። ነገሩ እንዲህ ነው፤ በሩሲያ አሌክሳንደሮቭካ በተሰኘች አንዲት አነስተኛ መንደር ውስጥ የሚኖሩት እነዚህ ሰዎች በተደጋጋሚ ሲያስጭንቃቸው የቆየው አንድ ተኩላ በአዳኞች መመታቱ ሪፖርት ይደረጋል። እንዲህ መንደሪቷን ሲያምሳት የቆየው ተኩላ በአዳኞች መመታቱ ነዋሪዎችን እፎይ ያሰኘ ቢሆንም፣ ተኩላው ባለፉት አርባ አመታት በአካባቢው ውስጥ ያልታየ መሆኑና በዚህ የክረምት ወቅት ሰዎች በሰፈሩባቸው አካባቢዎች ላይ መግባት መጀመሩ አነጋጋሪ ሆኗል። ተኩላው ወደዚች መንደር መግባት ከጀመረ ወዲህ ብዙ ውሾች ቅርጥፍ ጥፍ ተደረገው ተብልተዋል። ከሃያ በላይ የሚሆኑ ላሞች፣ በጎችና ፈረሶችም የዚሁ ተኩላ ሲሳይ ሆነዋል። ተኩላዎች፣ መምጣታቸውን ለማንቃት በየቤቱ በጠባቂነት የተያዙ ውሾችም ይህንኑ ተኩላ በመፍራት ድምፃቸውን አጥፍተዋል። ከዚህ ሁሉ ውድመት በኋላም ተኩላው በአካባቢው አዳኞች በመከራ የተገደለ ሲሆን፣ አዳኞች ተኩላውን ከበው ለማንሳት ሲታገሉ የሚያሳይ ምስል በማህበራዊ ትስስር መለቀቁን ተከትሎ ተኩላው በግዙፉነቱ ወደር ያልተገኘለት መሆኑ ብዙዎችን አስደንቋል። ‹‹ውሾች እንኳን ሊጮሁ ራሳቸውን ነው የደበቁት፤ ምንም አይነት የውሾች ጩኸትም አይሰማም። ለምን እንደሆነ ባላውቅም ምን አልባት ውሾቹ ተኩላውን ፈርተው ሊሆን ይችላል›› ሲል አንድ የመንደሪቷ ነዋሪ ተኩላው ከመገደሉ በፊት የነበረውን ሁኔታ ገልጿዋል። የአካባቢው አዳኞች በኋላ እግሩ ሲቆም መካከለኛ ቁመት ካለው ሰው ጋር እኩል የሚሆነውን ይህን ግዙፍ ተኩላ ለመግደል ሲዘጋጁ የመንደሪቷ ነዋሪዎች ፍርሃት ነግሶባቸው እንደነበር በዘገባው ተመላክቷል። ጉዳዩ በማህበራዊ ትስስር ገፅ መለቀቁን ተከትሎ ደግሞ በርካቶችን አስገርሟል። የዚህ ግዙፍ ተኩላ መገደል በኢንተርኔት የብዙሃንን ትኩረት ያገኘ ጉዳይ ቢሆንም፣የመንደሪቷ ነዋሪዎች ቤታቸውን በከበበው ደን ውስጥ አሁንም የዚሁ አይነት ግዙፍ ተኩላ ሊኖር ይችላል የሚል ስጋት እንዳደረባቸው በዘገባው ተመላክቷል። አዲስ ዘመን መጋቢት 15/ 2012 አስናቀ ፀጋዬ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=29010
[ { "passage": "ቦጋለ አበበእግር ኳስን በመሳሰሉ ተወዳጅና ንክኪ በሚበዛባቸው ስፖርቶች ተጫዋቾች በእንቅስቃሴ ውስጥ እያሉ አውቀውም ይሁን ሳያውቁ በተቃራኒ ቡድን ተጫዋቾች ላይ ጥፋት(ፋውል) ይሰራሉ። እነዚህ ጥፋቶች ከቀላል እስከ ከባድ የአካል ጉዳት ሊያስከትሉ የሚችሉና ያስከተሉበት አጋጣሚም በርካታ እንደነበር መመልከት ይቻላል። በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ወቅት ስፖርተኞች መሰል ጥፋት ሲሰሩ ውድድሩን በሚመሩ ዳኞች ከቢጫ የማስጠንቀቂያ ካርድ አስከ በርካታ ጨዋታዎች መታገድ ሊያደርሱ የሚችሉ ቅጣቶች ይከተሏቸዋል። ዳኞች አውቀውም ይሁን ሳያውቁ ከትንሽ እስከ ትልቅ ጥፋቶች በዝምታ ሲያልፉ የሚታይበት አጋጣሚም ጥቂት አይደለም። በዛሬው የስፖርት ማህደር አምዳችንም እኤአ በ1982 የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ ጨዋታ ወቅት የተከሰተውን ከባድና ታሪካዊ ጥፋት ከቅጣት የዳነበትን አጋጣሚ እንደሚከተለው እንዳስሳለን።ታሪካዊው ፈረንሳዊ ተጫዋች ሚሼል ፕላቲኒ ያሻገራት ኳስ ፓትሪክ ባቲስቶን ከጀርመኑ ግብ ጠባቂ ጋር አገናኘችው። በአጠገቡ ተከላካዮች የሉም፣ ከጨዋታ ውጭ አይደለም። የተከላካይን መስመር ሰንጥቆ ያለፈ ለጎል የተመቻቸ ያለቀለት ዕድል ነበር። ሄራርድ ሹማኸር ኳሷን ማዳን አለበት። አለበለዚያ ጀርመን ለዓለም ዋንጫው ፍፃሜ ላትደርስ ትችላለች። ከባቲስቶ ጋር ፊት ለፊት ተጋፈጠ። በረኛው እየተንደረደረ ኳሷን ተከትሎ ወደ ፈረንሳዊው መጣ። ሁለቱም ወደ አንድ አቅጣጫ ፈጠኑ። ሁለቱም የሀገሮቻቸው ጀግና ለመሆን በየፊናቸው እየሮጡ ነው…።የ1982ቱ የዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ነበር፣ ፈረንሳይ ከምዕራብ ጀርመን። ውጤቱ 1-1 እያለ ባቲስቶ ተቀይሮ ገባ። ከመግባቱ በፊት በተጠባባቂዎች ወንበር ላይ የምዕራብ ጀርመኑ በረኛ ባህሪይ አልተመቸውም ነበር። ከፈረንሳይ ተጫዋቾች ጋር ሲናቆር ታዝቦታል። የበዛ ግልፍተኛነት ይታይበታል። ከደቂቃዎች በኋላ አሰልጣኙ ወደ ጨዋታው አስገቡት። ከሰባት ደቂቃ በኋላም ከሹማኸር ጋር ተፋጠጠ። ፈረንሳዊያን ጎል ሲጠብቁ ሹማኸር ባለ በሌለ ጉልበቱ እንደ ፊጋ በሬ ተንደርድሮ በትከሻውና ዳሌው ተላተመው። ባቲስቶ ከሹማኸር ጉልበት ጋር አልተመጣጠነም። ከወገቡ በላይ ወደኋላው ተገፍትሮ አካሉን ሊቆጣጠር በማይችልበት ኃይል በጀርባው ከመሬት ተደባለቀ። በክርኑ መሬቱን የተደገፈው የቀኝ እጁ፣ ጣቶቹ እንደታጠፉ ቀና ብሎ ቀስ እያለ መሬቱ ላይ አረፈ። ከዚያም ተጫዋቹ በወደቀበት ሳይነቃነቅ በድን ሆነ። ግጭቱ እጅግ ከባድ ስለነበር ባቲስቶ ራሱን ሳተ። ሁለት ጥርሶቹ ወለቁ፣ ሶስት የጎድን አጥንቶቹ ተሰበሩ። በሜዳ ላይ የህክምና እርዳታ ሲደረግለት በተጫዋቹ ዙሪያ ሆነው አሰቃቂውን ጉዳት በቅርበት የሚከታተሉ የፈረንሳይ ተጫዋቾች ፊታቸውን ወደ ሹማኸር መለስ ቀለስ እያደረጉ ቁጣቸውን ይገልፃሉ። በረኛው ግን ከቁብም አልቆጠራቸው። በመጀመሪያ ወገቡን በእጆቹ ይዞ ባለበት ቆሞ ቆየ። ከዚያም ከሌላ የቡድን ጓደኛው ጋር ኳስ እየተቀባበለ ሰውነቱ እንዳይቀዘቅዝ ማድረጉን ቀጠለ። በኦክስጅን ጭምብል ከሜዳ እንዲወጣ ያስገደደ ከባድ ጥፋት ቢፈጽምም አርቢትር ቻርልስ ኮርበር ለሹማኸር ቀይ ካርድ ቀርቶ የማስጠንቀቂያ ካርድ እንኳን አልመዘዙበትም። ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ በረኛው በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የባቲስቶ ጥርሶች መውለቃቸውን ሲነግሩት ‹‹እኔ ወጪውን እሸፍናለሁ›› በሚል ስላቅ እብሪተኛነቱን ጨምሮ አሳየ። በወቅቱ አንድ ቡድን መቀየር የሚችለው ሁለት ተጫዋቾችን ብቻ በመሆኑ ሁለተኛው ተቀያሪ በጉዳት ከሜዳ የወጣበት የፈረንሳይ ቡድን አጋጣሚው ለፍፃሜ የመድረስ አቅሙን ክፉኛ አዳከመበት። በጭማሪ ሰዓት ፈረንሳይ አከታትላ ባስቆጠረቻቸው ሁለት ጎሎች 3-1 መምራት ብትችልም፣ አልሞት ባዮቹ ጀርመናዊያን ሁለት ጎሎች አግኝተው በ3-3 የመጨረሻ ውጤት ወደ መለያ ምት ሄዱ። ከዚያም የሹማኸር ምዕራብ ጀርመን ለፍፃሜው በቃች። አጋጣሚው በፈረንሳይ ህዝብ ዘንድ ፀረ-ጀርመን ጥላቻን ፈጠረ። ሹማኸር የፈረንሳይ ቁጥር አንድ ጠላት ሆነ። አንድ የሀገሪቱ ጋዜጣ በሰበሰበው የህዝብ መጠይቅ ሹማኸር ከናዚው አዶልፍ ሂትለር በላይ በዚያች ሀገር እንደተጠላ ተረጋገጠ። የጀርመኑ መራሔ መንግስት ሄልሙት ሽሚድት ቁጣውን ለማቀዝቀዝ ለፈረንሳዩ አቻቸው ፍራንሷ ሚቴሯ የቴሌግራም መልዕክት ላኩ። የጋራ መግለጫ ሊያወጡም ተገደዱ። ተጫዋቾቹም እንዲገናኙ ለማድረግ ሞከሩ። በሰዎች ግፊትም ይሁን ዘግይቶ በመጸጸቱ፣ ሹማኸር ተጎጂው ባለበት ሄዶ ይቅርታ ሊጠይቀው ቢሞክርም በጋዜጠኞች መገኘት ምክንያት ያሰበውን ያህል ሳይሳካለት ቀረ። አሁን ባቲስቶ ከስልሳ ዓመት ያለፈው ጎልማሳ ሆኗል። ጉዳቱ በጀርባ አጥንቱ ላይ የፈጠረው አደጋ እስካሁንም የህመም ስሜት እንዳለው ይናገራል። ራስ ምታት ልማዱ ነው። በቃሬዛ ከወጣ በኋላ የተከናወነውን ቀሪ የጨዋታ ፊልም ላለማየት ወስኖ ቢቆይም በመጨረሻ ከሰላሳ ዓመታት በኋላ ተመልክቶታል። ወደ እርጅናው የተጠጋው ሹማኸርም አሁን ደርሶ በአጋጣሚው መጸጸቱን ይናገራል። ከጨዋታው ሁለት ዓመት\nበኋላ፣ በ1984፣\nፈረንሳይና ምዕራብ ጀርመን\nበወዳጅነት መርሃ ግብር\nተገናኙ። ከጉዳቱ በኋላ\nወደ ጨዋታ የተመለሰው\nባቲስቶ በድጋሚ በብሔራዊው\nማሊያ ከሹማኸር ጋር\nበተቃራኒ ቆመ። በመጨረሻ\nሁለቱ ሰዎች ማሊያ\nተቀያየሩ። ቅይይሩ ግን\nበህዝብና በሚድያው ፊት\nሳይሆን በተጫዋቾች መልበሻ\nቤት ውስጥ፣ ብቻቸውን\nያደርጉት ነበር።አዲስ ዘመን\nታህሳስ 4/2013", "passage_id": "3407396a6333f1b62dae159ed6064b4b" }, { "passage": " ውሻ ታማኝ እንስሳ ነው፡፡ጌቶቻቸው ሞቶውባቸው የተቀበረበት አካባቢ ለብዙ አመታት የቆዩ ውሾች ስለመኖራቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ በቅርቡ አሜሪካ የአይኤስኤስን መሪን በገደለችበት አውድ ላይ አነፍናፊ ውሾች ሰፊ ስፍራ መያዛቸው ይታወቃል፡፡ ይሁንና በአብዛኛው አካባቢ የውሻ ውለታ የቱንም ያህል ቢሆን ከመጣል አይድንም፡፡በአዲስ አበባ የምንመለከታቸው ቁጥር ስፍር የሌላቸው ውሾችን ብንመለከት በአንድ ወቅት ጌታ የነበራቸው ናቸው፡፡በኑሮ ሁኔታም ይሁን ለውሻ ያለን ግንዛቤ አነሳ በመሆኑ ሳቢያ የውሻ የመጨረሻ እጣ ፈንታ ወደ ጎዳና መውጣት ነው፡፡ ሰሞኑን ኦዲቲ ሴንትራል በድረ ገፁ ባወጣው ዘገባ በሰርቢያ 750 ውሻ ስለሚንከባከብ ልበ ሩህሩህ ሰው አስነብቧል፡፡ ሳሻ ፔሲክ የሚባለው ሰርቢያዊ በ2008 በቆሻሻ ሥፍራ የተተዉ ውሾችን የታደገ ሲሆን በዚህ መልኩ 1ሺ200 ውሾችን በ10 ዓመታት ታድጓል፤ አሁን ደግሞ 750 ውሾችን እየተንከባከበ ነው፡፡ ሳሻ ፔሲክ በዓለም ዕውቅና ያገኘው ከፈረንጆች አቆጣጠር ከ2015 ጀምሮ ሲሆን በተለይም ከድልድይ እግር ሥር በአክሮባት ተገላብጦ ወርዶ የታሰረች ቡችላ ለማዳን ያደረገው ጥረት በማኅበራዊ መገናኛዎች በተለይም በፌስ ቡክ ብቻ 63 ሚሊየን ተመልካቾች ባዩት ጊዜ ነው፡፡ ሳሻ ፔሲክ ህይወቱን መስዋዕት በማድረግ በኒስ ጎዳናዎች 1ሺ200 ውሾችን ሰብስቦ ከ400 በላይ ውሾችን ለሰዎች ሰጥቷል፤750ዎቹ በእንክብካቤው ሥር ናቸው፡፡ ‹‹በየቦታው ተጥለው ሲንገላቱ ሳይ አዝናለሁ፤ እራራለሁ፤ ለዚህም ነው ሰብስቤ ማኖር የጀመርኩት›› ይላል፡፡ ለውሾች ምግብ ብቻ ወደ 11ሺ 150 የሚጠጋ ዶላር በየወሩ ያወጣል፤ወደ ሀገራችን ሲመነዘር ከ278ሺ750 ብር በላይ ማለት ነው፡፡ ይህም መጠለያዎችን ለመጠገንና ለማፅዳት እና ለውሾቹ ህክምናን ጨምሮ ለተንከባካቢ ሠራተኞች የሚወጣውን ወጪ ሳያካትት ነው፡፡ “ሰዎች ባብዛኛው የማይፈልጉዋቸውን ውሾች በጎዳና መጣል ያስባሉ፤ አንዳንዶቹ ውሻቸውን ይዘው ወደ መጠለያ ይመጣሉ። እንዳይታዩ ብለውም ውሻቸውን በጨለማ መጠለያው አቅራቢያ ጥለው የሚሄዱም አሉ። ውሾች ህይወት ያላቸው እንደ መሆናቸው ጥሩ እንክብካቤ ሊደረግላቸው ይገባል ብዬ እገምታለሁ፡፡እዚህ እየሆነ ያለው ይህ ነው፡፡” ሲል ሳሻ ፔሲክ ይናገራል። በዓለም ዙሪያ ብዙ ቅን አእምሮ ያላቸው ሰዎች የእንስሳ ወዳጆች በየወሩ ገንዘብ እየረዱት መሆናቸውን ጠቅሶ፣ውሾቹ ዘላቂ ቤቶች እንዲያገኝ እየረዱት መሆናቸውንም ይገልጻል፡፡ለብዙ ሰዎች 750 ውሻ ይቅርና አንድ ውሻ መንከባከብ ያዳግታል፤ የሚገርመው ሳሻ ፔሲክ ግን ይህን ሁሉ ውሻ እየተንከባከበ እና እያኖረ ሁሉንም በየስማቸው ማወቁ ነው፡፡ ‹‹ውሾቹ እንደመጡ በፍጥነት ያገግማሉ ፤ትንሽ ፍቅር ምግብና ክብካቤ ከተሰጣቸው በፍጥነት አጋርና ደስተኛ ይሆናሉ፣ የተሻለ ነገር እንዲኖራቸው እመኛለሁ። ጥሩ ምግብ እና መጠለያ ሳጥኖች ትልቅ መጠለያዎችን ከገነባን እና የሚጠበቅብንን ደረጃ እስካሟላን ድረስ መጨረሻ ላይ ህጋዊ እንሆናለን፡፡”ይላል፡፡ ለዚህ ሥራው ህንዶች አባ ውሻ (የውሾች አባት) ሜክሲኮዋዊያን የውሻ ሰው ሲሉት ቻይናውያን ደግሞ የውሾች እረኛ በሚል ፅፈውበታል፡፡አዲስ ዘመን ጥቅምት25/2012 ሀይለማርያም ወንድሙ", "passage_id": "55c076e83ab8e6b2a3868c0b789e7f19" }, { "passage": "ማኒኒ በኦሎምፒክ እና ዓለም ሻምፒዮን ሜዳሊያዎችን ማሸነፍ ችሏል\n\nድንገት ሃይቁ ላይ ሲንሳፈፍበት የነበረው ፕላስቲክ ከእጁ አምልጦ ቤዴንቶ መስመጥ ጀመረ። እድለኛ ሆኖ በኦሎምፒክ ውድድር ላይ ጣሊያንን ወክሎ የተወዳደረው ፊሊፖ ማኒኒ በቅርብ እርቀት ይገኝ ነበር። የቀድሞ የዓለም ሻምፒዮን ዋናተኛም እየሰጠመ የነበረውን ቤዴንቶን ህይወት ማትረፍ ችሏል። \n\nየህይወት አድን ዋናተኞች እስኪደርሱለት ድረስ ዋናተኛው ሊሰጥም የነበረውን ቤዴንቶን ጭንቅላት ከውሃ በላይ አድርጎ ቆይቷል።\n\n• \"እባካቹን ለቤተሰቦቼ ንገሩልኝ! መዋኘት አልችልም፤ ለቤተሰቦቼ ብቸኛ ነኝ\"\n\n• ስደተኞችን ያሳፈረች መርከብ ተገልብጣ 65 ሰዎች ሞቱ \n\n• በቱኒዚያ የ48 ስደተኞች ሕይወት አለፈ\n\n''ማድረግ የሚጠበቅብኝን ነው ያደረኩት'' ብሏል የቀድሞ የዓለም ሻምፒዮን ዋናተኛ።\n\nቤዴንቶ ከሁለት ቀናት በፊት ያገባ ሲሆን፤ ከትዳር አጋሩ ጋር በአየር የተሞላ ፕላስቲክ መንሳፈፊያ ላይ ተመርኩዘው በሃይቁ ዳርቻ ሲዝናኑ ነበር። ከዚያ ቤዴንቶ ከፕላስቲኩ መንሳፈፊያ ላይ ወደቀ። ወዲያው ኃይለኛ ንፋስ የፕላስቲክ መንሳፈፊያውን እንደወሰደው አብረውት የነበሩት ጓደኞቹ ይናገራሉ። \n\nበህመም ምክያት እግሮቹን ማንቀሳቀስ የማይችለው የ45 ዓመቱ ቤደንቶ ህይቱን ለማትረፍ ቢጥርም እየሰጠመ ነበር። \n\nበህመም ምክያት እግሮቹን ማንቀሳቀስ የማይችለው የ45 ዓመቱ ቤደንቶ ህይቱን ለማትረፍ ቢጥርም እየሰጠመ ነበር።\n\nበሁነቱ የተደናገጡት የቤዴንቶ ጓደኞች መጯጯህ ጀመሩ። ህይወት አድን ሰራተኞችም ቤዴንቶን ለማዳን ወደ ሃይቁ ቢገቡም ዋናተኛው ቀድሞ ደርሶ ህይወቱን አትርፏል። \n\n''አጠገቡ ሲደርስ መናገር እንኳን አቅቶት ነበር፤ የባህር ውሃ ጠጥቶ ነበር'' ሲል ዋናተኛው ለጣሊያን መገናኛ ብዙሃን ተናግሯል።\n\nየመስጠም አደጋ ያጋጠመው ቤዴንቶ ራሱን ስቶ የነበረ ሲሆን ከሰዓታት ቆይታ በኋላ ራሱን ያወቀው ሆስፒታል ከደረሰ በኋላ ነበር። ''ህይወቴን ያዳነው ፊሊፖ መሆኑን ሆስፒታል ከደረስኩ በኋላ ነው ያወኩት። እሱን የማመሰግንበት አጋጣሚ እንኳን አላገኘሁም። በአካል አግኝቼው እንደማመሰግነው ተስፋ አለኝ።'' ሲል ተናግሯል።\n\nዋናተኛው በባህር ዳርቻው ላይ ከታዋቂ ፍቅረኛው ጋር እየተዝናና ነበር። \n\n ", "passage_id": "b6bfadc071693702c518469a203efff0" }, { "passage": "የተፈጥሮ ውበታቸውን በጠበቀ መልኩ ስራ ላይ የምታውላቸው የዛፍ አይነቶችን ከየት ታገኛለህ?ሰዎች ዛፎችን ከመኖሪያ ቤትና ከመስሪያ ቤቶች ቆርጠው ይጥሏቸዋል፡፡ ያጫርቱታል፡፡ የእንጨቶችን ባህሪና ውበት ለይቼ ስለማውቅ በየመንገዱና በየአካባቢው አይኔ እንጨቶችን ፍለጋ ይባዝናል፡፡ የተጣሉ የእንጨት ዝርያዎችን የመበስበስና ያለ አግባብ ወድቀው ከመቅረት የማዳን ስራ ነው የምሰራው፡፡ በእግሬ ስጓዝ እንኳን የወደቀና የሚያምር እንጨት ካየሁ አነሳለሁ፡፡ በተፈጥሮዋቸው ውስጥ የራሳቸውን ባህሪ እፈልጋለሁ፡፡ ሶፋ፣ የመስታወት ፍሬም፣ የወንበር እግሮች፣ ጠረጴዛ የመሳሰሉትን ይገኝበታል፡፡ እንዴት ነው ወደዚህ ሙያ የገባኸው?ውስጤ ያለውን ሞያ አውጥቼ እንድጠቀም የረዳኝ እግዚአብሔር ነው፡፡ ከዚህ ስራ ጋር የምተዋወቅበት ምክንያት አልነበረም፡፡ በችግር ምክንያት ቤተሰቦቼን ለመርዳት ብዬ የቀን ስራ ተቀጥሬ በመስራት ነው ነገሮች እዚህ ደረጃ የደረሱት፡፡ ለቤተሰቤ ሁለተኛ ልጅ ነኝ፡፡ ገና 8ኛ ክፍል እያለሁ በ14 ዓመቴ ነው እየተማርኩ ቤተሰቤን ለመርዳት ወደ ቀን ስራ ገባሁት፡፡ በቀን 3 ብር ከ50 ሳንቲም አገኝ ነበረ፡፡ እኔ እና የአሁን ሞያዬ በዚህ ሁኔታ ተጣጥመን እዚህ ደረሰን እንጂ የእኔ ፍላጐት ቦክሰኛ መሆን ነበር፡፡ ኑሮው ግን አልተመቸም… እንኳን ተደባድቤበት… እናም ኑሮ ግራ ሲያጋባኝ ከጓደኞቼ ተደብቄ የ3 ብር ከ50 ሳንቲም ስራዬን ጀመርኩ፡፡ መቼም ይደርስብኝ የነበረው ጫና የሚገርም ነው፡፡ ጓደኞቼ “አንተ ኩሊ፣ ከእኛ ጋር እየተማርክ እንዴት የቀን ስራ ትሠራለህ” እያሉ ያሸማቅቁኝ ነበር፡፡ ግን ለዛሬ ስኬት ያበቃኝ ትናንት ያገኘሁትን ሥራ መስራቴ ነው፡፡ የቀን ስራ ስትል… ምን አይነት ነው?የሰው ቤት አጥር እሰራ ነበር - በቆርቆሮ በእንጨት፡፡ ሲሚንቶ እሸከም ነበር፡፡ ድንጋይ ከመኪና አወርዳለሁ፡፡ ይህን እየሠራሁ ትምህርቴን ጨረስኩ፡፡ ከዛም ተግባረድ ገባሁ፡፡ ከተግባረዕድ በኋላ ነው ወደ እንጨት ስራ የገባኸው?አዎ! ለእንጨት ውበት ያለኝ ፍቅርና አድናቆት የተለየ ነው፡፡ እንጨት ሲማገድ፣ ያለ አግባብ ሲጐሳቆል ደስ አይለኝም፡፡ በጣም አዝናለሁ፡፡ የማይረሳኝ ገጠመኝ አለ፡፡ አንዲት እናት እንጀራ ይጋግራሉ፤ በእንጨት፡፡ ቆሜ ስመለከታቸው በጣም የሚያምረውን እንጨት አንስተው ይማግዱታል፡፡ የእንጨቱ ቅርጽ አፉን ይከፍትና መንታ ምላስ ያለው እባብ ይመስል ነበር፡፡ ስጡኝ ብላቸው ‹‹እየጋገርኩት ያለው ሊጥ ይበላሽ? እንጀራ እየጋገርኩ መሰለኝ›› ብለው ተቆጡ፡፡ ልክፈል ብላቸውም እንኳን እምቢ አሉኝ፡፡ ‹‹ምን ትፈላሰፍብኛለህ!›› ሲሉኝ ዞር አልኩ፡፡ ያንን የመሰለ የእንጨት ውበት ከየትም ላመጣ እንደማልችል ስለማውቅ እንባ ነው የተናነቀኝ፡፡ ውበት ያላቸው የእንጨት ዝርያዎች በተለይ ከየት ታገኛለህ? ከአዲስ አበባ ነው ወይስ…አዲስ አበባ አዲስ አበባ ደግሞ ምን የሚታይ እንጨት አለ፡፡ አርሲ ነገሌ ብትሄጂ የዛፎቹ ተፈጥሮ ያስደንቅሻል፡፡ ጉብጥብጥ ያሉና የተለያዩ አይነት ቅርፆች ያላቸው ዛፎች አሉ፡፡ የሰው ቅርጽ የሚመስሉ አሉ፡፡ ወንድና ሴት፣ ትናንሽ ልጆች፣ የወንድና የሴት ብልት የሚመሳስሉ ሁሉ አሉ፡፡ እዛ አካባቢ ዝግባ፣ ቀረሮ፣ ባህር ዛፍ፣ ግራር የመሳሰሉ ዛፎች አሉ፡፡ አቤት ሲያሳዝንሽ… ደን ልማት ብትይ የአካባቢው ማህበረሰብ እንደ ጉድ ነው አልኩሽ የሚጨፈጭፋቸው፡፡ እንጨቶቹ እንዲሁ ወድቀው ስታያቸው እምባሽ ይመጣል፡፡ ባክነው እንዳይቀሩ እኔ ወደ ህዝብ እይታ አመጣቸዋለሁ፡፡ ደብረብርሃን፣ አክሱም፣ ዝዋይ፣ ጅማ፣ አካባቢ ያሉ እንጨቶችም ድንቅ ጥበብና አፈጣጠር ያላቸው ናቸው፡፡ እኔ በእንጨት ፍቅር ወድቄያለሁ፡፡ የአገር ባህል ቤቶችንም ትሰራለህ?ሌላው ህይወቴ የተመሠረተው በጐጆ ቤቶች ጥበብና ውበት ነው፡፡ በሳር፣ በፊላ፣ በቀርከሃ ጐጆ ቤቶች እሰራለሁ፡፡ በመዝናኛ ቦታዎችና በተለይ በአዲስ አበባ ጥሩ ገቢና መኖሪያ ያላቸው ሰዎች ግቢ ውስጥ ምርጥ ጐጆዎችን ሰርቻለሁ፡፡ እስቲ ከሰራሃቸው መዝናኛ ስፍራዎች ጥቀስልኝ? ያንተ ጐጆዎች የት የት ይገኛሉ?የአፍሪካ ቫኬሽን ክለብ፣ ቦራቲ ሎጂ፣ የሳቫና ሎጅ፣ በአዋሳ የሌዊ ሪዞርት የሚጠቀሱ ሲሆን በላንጋኖ ዙሪያ የሚገኙ ባለሀብቶች ገዝተው የሚያከራይዋቸውና ከነቤተሰቦቻቸው የሚዝናኑበትን ጐጆዎች ዲዛይኑን ከማውጣት ጀምሮ እስከመገንባት ድረስ ሰርቻለሁ፡፡ በአዲስ አበባ ሃያት፣ ሲኤምሲ፣ ቦሌ፣ ፒያሳ እና ሌሎች አካባቢዎች በግለሰቦች መኖሪያ ቤት ውስጥ ጐጆዎችን እንዲሁም ባንኮኒና ባንኮኒ ዙሪያ የሚቀመጡ ወንበሮችን በእንጨት አሳምሬ ሰርቻለሁ፡፡ ሰዎች በአሁኑ ጊዜ ጊቢያቸው ውስጥ ወይንም በሳሎናቸው ውስጥ ጐጆ ቤት እንዲሰራላቸው ይፈልጋሉ፡፡ ለምን መሰለሽ ጐጆ ቤት ሙቀት ሆነ ቅዝቃዜ የአየር ንብረቱን ከመቆጣጠሩ በተጨማሪ የአገር ቤት ስሜት ይፈጥራል፡፡ ከሚያብረቀርቅርና ከተፈጥሮ ውጭ ከሆነ ጌጣጌጥ የበለጠ ያምራል፡፡ ብቻ ደስታ ይሰጥሻል፡፡ የገጠር ድባብ ይፈጥርልሻል፡፡ ይሄው እንግዲህ 18 ዓመት ሙሉ ህይወቴ ሆኗል፡፡ ጐጆ ቤት ለመስራት ወጪው ውድ ነው ይባላል?ተመጣጣኝ ነው፡፡ ውድም ቢሆን እኮ እድሜ ይቀጥላል፡፡ እንዴት መሰለሽ… ጐጆ ቤት ውስጥ ዘና ብሎ መጽሐፉ ማንበብ፣ እረፍት ማድረግ፣ ቡና መጠጣት… በጐጆ ቤቶች ውስጥ የምትተነፍሽው አየር ሁሉ ደስ የሚልና የሚያነቃቃ ነው… የተረጋጋ መንፈስ ይሰጥሻል፡፡ አይንሽን አይሰለቸውም፡፡ በእርግጥ ሳሩና ቀርከሃው ውድ ነው፡፡ እኔ የማስበው እንዴት ተውቦ ይሰራል የሚለውን እንጂ የሚያስወጣኝንና የማተርፈውን አይደለም፡፡ ደግሞ ከየት ነው የምታመጣው ብለሽ ገበያዬን እንዳትዘጊብኝ… ከሩቅ አካባቢ ነው (ሳቅ)አንዱ ጎጆ በምን ያህል ብር ይሠራል?በርግጥ እንደ ሁኔታው ቢለያይም በአማካይ ልነግርሽ እችላለሁ፡፡ ሶስት በአራት የሆነ ጎጆ ስልሳ ሺህ ብር ይሠራል፡፡የጐጆ ቤት ዲዛይኑ የራስህ ነው ወይስ ሰዎች እንዲህ ሥራልን ይሉሃል?ሰዎች ፍላጐታቸውን ይነግሩኛል፡፡ እኔ ደግሞ የዲዛይኑን ውበት በአዕምሮዬ ስዬ እንደዚህ ይሁን እላቸዋለሁ፡፡ እነሱም ይሰሙኛል፡፡ ቦታውን አያለሁ… የሚያመቸውን ዲዛይን መርጬ በሚያምር መልኩ አስውበዋለሁ፡፡እንዴት ነው… ሰው ጐጆ ቤት ይፈልጋል?ዛሬ ዛሬ በጣም ብዙ ጥያቄዎች አሉ፡፡ ሰው መኖሪያ ቤቱን በጐጆዎችና በተፈጥሮ እንጨቶች ማስጌጥ ይፈልጋል፡፡ ግን ያን ያህል ጥቅሙ የገባው አለ ማለቱም ይቸግራል፡፡ ባለሃብቶች አካባቢ ግን ፍላጐት አለ፡፡ ከውጭ የሚመጡ ሰዎች መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ጐጆ ቤትና የእንጨት ስራ ውጤቶች እንዲኖራቸው ይፈልጋሉ፤ ያሠራሉም፡፡ የውጭ ዜጐችም የመኖርያ ቤታቸውን በር፣ መቀመጫ፣ ጠረጴዛ… የተለያዩ የቤት ቁሳቁሶችን ወዘተ… በእንጨት ውጤቶች ያሰራሉ፡፡ጎጆዎች ስያሜ አላቸው?አዎ! የሲዳሞ ባህላዊ ጐጆ የሚሰራው በቀርከሃ ሲሆን ውስጣዊ ክፍሉ ግርግዳው ዙሪያውን በወፊጮ (በሰኔል) ይሠራል፡፡የወላይታና የጎጃም በሳር ይሠራል፡፡ የኦሮሚያ አካባቢ በፊላ ይሠራል፡፡ በስርህ ስንት ሰራተኞች ይተዳደራሉ?እንደ ስራው ሁኔታ በየጊዜው ቢለያይም እስከ 50 ጊዜያዊ ሠራተኞችን እቀጥራለሁ፡፡ በስሬ እስከ 15 ባለሞያዎች አሉኝ፡፡የአንተ መኖሪያ ቤትስ… በዚህ መልኩ የተሰራ ነው? ቤቴን በዚህ መልኩ ለመስራት ዲዛይኑን ነድፌ አስቀምጫለሁ፡፡ ግን ሃዘን ላይ ስለነበርኩ እስካሁን አልተሰራም፡፡ አሁን ተረጋግቻለሁ፡፡ በቅርቡ ቤቴን በጐጆና በእንጨት ስራ ውጤቶች አስውቤ በአጭር ጊዜ ውስጥ እጋብዝሻለሁ፡፡ ቤተሰብ መስርተሃል?አዎ ሁለት ልጆች አሉኝ፡፡ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ናቸው፡፡ ባለቤቴ የዛሬ ሦስት ዓመት አካባቢ በካንሰር በሽታ አርፋለች፡፡ ራሴ ያስተማርኳቸው እህትና ወንድሞቼ ከእኔ ጋር ይኖራሉ፡፡ በባለቤቴ ሀዘን ምክንያት አንዳንድ ያሰብኳቸውንም ስራዎች አጓትቻቸው ነበር፡፡ እንግዲህ በቅርቡ የራሴን ቤት በባህላዊ መልኩ ከመገንባት በተጨማሪ በዝዋይ የራሴን የእንጨት ቤት እየከፈትኩ ነው፡፡ ስራዬ ተንቀሳቃሽ በመሆኑ እዚህ አዲስ አበባም የእንጨት ቤት አለኝ፡፡ በዚህ ሁኔታ ነው ያለሁት፡፡ ገቢህ ምን ያህል ነው?ገንዘቡን ተይው ግን እግዚአብሔር ይመስገን ገቢዬ ከፍተኛ ነው፡፡ ጥሩ ገንዘብ ሰርቻለሁ፤ የተሻለ ጊዜ ላይ ነኝ ብልሽ ይበቃል፡፡ ዛሬም እንግዲህ ቀን ከሌሊት እየሰራሁ ነው፡፡ በኮንስትራክሽን ስራም እድገት እያሳየሁ ነው፡፡ እግዚአብሔር ይመስገን ሁሉም መልካም ነው፡፡", "passage_id": "26ca38c9433c1803f569c129b139dcc2" }, { "passage": " ስለቁንጅናቸው በእጅጉ ይጨነቃሉ፤ ሴቶች። በዚህ የተነሳ ቁንጅናቸውን ለመጠበቅ፣ ቁንጅና ለመጨመር ወይም እንደ አዲስ ቆንጆ ለመሆን የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም፤ ይባላል። ጥቂቶች ካልሆኑ በቀር የተማሩትም ቢሆኑ «ዞሮ ዞሮ ሴት ነኝ» በሚል እሳቤ ነው መሰል፤ ብዙ ጊዜያቸውን ለመቆነጃጀት ባያውሉም፤ ብቻ በሆነ መልኩ ቁንጅናቸውን ለመጠበቅ ይጥራሉ። ቁንጅናን የመጠበቅ\nአልፎም የመጨመር ሥራ\nበታዳጊነት የእድሜ ክልል\nየሚጀመር ይመስላል። በዚህ\nበኩል ቤተሰብ የራሱን\nድርሻ ሲወጣ ታዳጊዎቹም\nያዩትን ሁሉ በራሳቸው\nላይ ለመተግበር ሲጣጣሩ\nይስተዋላል። ይህ ደግሞ\nየተለመደና ተፈጥሯዊ ሊባል\nየሚችል ሂደት ነው።\nከዚህ በመለስ\nግን ቁንጅናን የመጠበቅን\nእና የመጨመርን ተግባር\nየእንጀራ ያህል የሚያከናውኑ ጥቂት የሚባሉ\nአይደሉም። እንደውም የቁንጅና\nውድድርስ ማን ዘንድ\nነው ያለው? ሴቶች\nዘንድ አይደል? ይህ ቁንጅናን የመጠበቅና የመጨመር ተግባር ታዲያ ብዙ ዋጋም ያስከፍላል። የቀደሙትስ «ሲያጌጡ ይመላለጡ» ማለታቸው ለዚህ አይደለ? ያኔስ ሹሩባውም ጠበቅ ተደርጎ የተሠራ እንደሆነ፣  የጆሮ\nጌጥ ለማድረግ ጆሮ\nላይ ቀዳዳ ማበጀቱ\nህመም ያለው በመሆኑ፣\nጥርስን መነቀስም ቀላል\nየማይባል ህመም ስላለው\nነው። አሁን ደግሞ\nለቁንጅና መጠበቂያና መጨመሪያ\nበሚል ኮስሞቲክ ቅባቶችን\nበእጅጉ መጠቀም አለ።\nበነገራችን ላይ በእነዚህ\nለውበት ተብለው በተዘጋጁ\nቅባቶች ውበትን መጠበቅም\nሆነ መጨመር፤ «ሲያጌጡ\nይመላለጡ» ብቻ ሳይሆን\n«…መዋዕለ ነዋይዎትን\nያውጡ» የተባለ ያህል\nከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅም\nነው። ዋናው ግን\nጤና ነውና፤ የጤና\nጉዳይ ላይ ስናተኩር\nበቀዶ ህክምናና በተለያዩ\nቅባቶች ሳቢያ ሊመጣ\nየሚችል ጉዳት በፊታቸውና\nበመሳሰሉት የአካል ክፍሎቻቸው\nላይ እያጋጠማቸው ፊታቸው\nየተገለበጠ የሚመስል ሰዎች\nየሚያጋጥሙበት ሁኔታ ጥቂት\nየሚባል አይደለም። ኦዲቲ ሴንትራል በድረ\nገጽ ላይ ሰሞኑን\nከዚህ ጋር የተያያዘ\nዜና አስነብቧል። አንዲት\nጃፓናዊት ናት አለ፤\nበሥራዋ የአውሮፕላን አስተናጋጅ\n(ሆስተስ) እና\nሞዴሊስት ናት። ይህቺ\nሴት ላለፉት 21 ዓመታት ለመቆነጃጀት ስትል\n30 ሚሊዮን የጃፓን\nገንዘብ (የን) ወይም\n280 ሺ ዶላር አፍስሳለች፤ ወጪ አድርጋለች። ይህ ሁሉ ተደርጎም\nታዲያ የዚህች የጃፓናዊት\nሴት እናት ልጃቸው\nእርሳቸው የሚያስቡትን ያህል\nልትቆነጅላቸው አልቻለችም። ጹባኪ\nቶሞሚ የተባለችው ይህች\nሞዴሊስት የእናቷን ፍላጎት\nለማሟላት ብላ በ18\nዓመቷ ልክ የሁለተኛ\nደረጃ ትምህርቷን እንዳጠናቀቀች ነው የመጀመሪያ\nየፕላስቲክ ቀዶ ህክምና\nያደረገችው። በ20 ዓመቷ ጥርሶቿን እና\nየአይኗን ቅርጽ በፕላስቲክ\nቀዶ ህክምና አቃንታለች፤ የጡት ንቅለ\nተከላም አድርጋለች። ቅርጽዋን በማስተካከል በኩል\nለአፍታም አርፋ የማታውቀው\nጹባኪ ቶሞሚ፤ ይህንንም\nእስከ ህይወቷ ፍጻሜ\nድረስ እንደምትቀጥልበት ትገልጻለች። ጹባኪ ወጣት\nለመምሰል በሚል የፕላስቲክ\nቀዶ ህክምና የምታደርግ\nሲሆን፣ ቁንጅናን ብላ\nበምታከናውናቸው ተግባሮች\nክፉኛ የተለከፈችው ገና\nበጨቅላነቷ መሆኑንም ነው\nየምትናገረው። ኦዲቲ ሴንትራል በዘገባው\nላይ የጹባኪ እናት\nሁሌም ስለ ልጃቸው\nመልከጥፉነት ሁልጊዜ ይናገሩ\nነበር ብሏል። እንደውም\nለልጃቸው አንዳች ርህራሄ\nባለማሳየት ሰው ፊት\nሳይቀር ቆንጆ አለመሆኗን\nበግልጽ ይነግሯት ነበር።\nእንግዲህ ይህ በልጅቷ\nአእምሮ ውስጥ ክፉኛ\nዘልቆ ኖሮ፤ ጹባኪ\nየእናቷን ፍላጎት ለማሟላት\nበሚል ያላደረገችው እንደሌለ\nራሷ ትናገራለች። መቼም ሰው እድሜው\nመገስገሱ ያሳስበው ይሆናል\nእንጂ ጊዜ አይቆምም።\nእናም ጹባኪም የእድሜዋ\nእየጨመረ መምጣት የፕላስቲክ\nቀዶ ህክምና ለማድረግ\nእንደማያስችላት ትረዳለች።\nእናም ሞዴሊስቷ ለቁንጅናዋ\nስትል 30 ሚሊዮን የን\nማውጣቷንም ትናገራለች። ጹባኪ ቶሞሚ ከጃፓኑ\nየሆስቴሶች መጽሔት «ካባ»\nጋር ባደረገችው ቆይታ\nየአንደኛ ደረጃ ተማሪ\nከሆነችበት ጊዜ አንስታ\nመለስተኛ ሁለተኛ ደረጃን\nጨምሮ እናቷ ሁሌም\nቁንጅናዋ ሙሉ እንዳልሆነ\nስታስብበት መኖሯን ገልጻለች።\nበየአዲስ ዓመቱ ዋዜማና\nቦን የተሰኘው ፌስቲቫል\nበመጣ ቁጥርም እንዲሁም\nዘመድ አዝማድና ጓደኞቻቸው\nወደ ጹባኪ እናት\nቀረብ ብለው «ወይ\nጊዜ! ልጅሽ እንዴት\nትልቅ ሆነች?!» ሲሏቸው፤ እናቷ ግን\nከማደጓ የልጃቸው መልክ\nአለማማር ነበር የሚያሳስባቸውና የሚናገሩትም። ጹባኪ እናቷን አክብራ\nዝም ትበል እንጂ፤\nይህን ከማድረግ እንዲቆጠቡ\nነግራቸዋለች። እናቷ ግን\nከሚሰጡት አስተያየት ለመቆጠብ\nፈቃደኛ እንዳልሆኑ ታስታውሳለች፡፡ በዚህ የተነሳ\nእናቷ የሚሏትን በአእምሮዋ\nይዛ ማደጓን እና\nራሷን ለፕላስቲክ ቀዶ\nህክምና አሳልፋ መስጠቷን\nአስታውሳለች። በእርግጥ ነገሩ ለወጪ\nየዳረጋት ቢሆንም ያገኘችው\nገቢም ቀላል አይደለም።\nለምሳሌ ለመጀመሪያ ቀዶ\nጥገና ሥራ ከቁጠበዋ\nአንስታ የከፈለች ሲሆን፣\nከዛ በኋላ በሃያዎቹ\nእድሜ ታዋቂ ሆስቴስ\nለመባል ከመብቃትም ባሻገር\nበርካታ መጠን ያለው\nገንዘብ አግኝታበታለች። ምን\nዋጋ አለው! በምታገኘው\nገንዘብ «ኑሮዬን ልለውጥ!\nቤት ልሥራ!…» አላለችማ! ከምታገኘው ገቢ ውስጥ\nአብዛኛውን ገንዘብ ከአገጭ\nእንስታ አፏን፣ አፍንጫዋን፣ ፊትዋን ለማስተካከል ለተደረጉ የፕላስቲክ\nቀዶ ህክምናዎች ነው\nያዋለችው። ባለፉት 21 ዓመታትም 300 ጊዜ የአካል\nማስተካከያ ሥራዎች ተደርገውላታል። በቅርቡም ኢንቲማ\nየተሰኘ እና 160 ሺ የን ወይም\nአንድ ሺ 500 ዶላር ወጪ የተደረገበት ሌሰር ዘመናዊ\nየቀዶ ህክምና ተደርጎላታል። ፕላስቲክ ቀዶ ህክምና\nበጃፓን በዚህ ዘመን\nእየተለመደ መምጣቱንም ጠቅሳ፤\nእሷ ቀዶ ህክምናውን\nበጀመረችበት ዓመት ግን\nህዝቡ በእጅጉ ያወግዘው\nእንደነበር ታስታውሳለች። እርሷ\nግን ይበልጥ መቆንጀትን\nበመምረጥ ለህብረተሰቡ አስተያየት\nስፍራ ሳትሰጠው ቆይታለች።\nጹባኪ አሁንም ሞዴሊስት በመሆን ተጽእኖ ፈጣሪ እስከ መሆን መድረሷን ዘገባው አመልክቶ፣ በኢንስታ ግራም፣ ፌስ ቡክና ትዊተር ገጾች ሁሉ የማትጠፋ በጃፓን የተለያዩ ድረ ገጾች በመጻፍም እንደምትታወቅ ይጠቁማል።አዲስ ዘመን ሰኔ\n25/2011 ", "passage_id": "9eb3f57bfa0a8394207e572889a2396e" } ]
21e86a8e2275084826169e59b140db12
336e37b4196b0d6f32aab1da2478c1ce
ባይሆን ጥሩ ነበር፤ ግን ሆነ
ሳንፈልግ የሚያስፈግጉን፤ ሳንወድ የሚያስቁን ብዙ ሁነቶች በሰሞኑ በውዝግብ ውስጥ አሳልፈናል። እርግጥ ነው እንደ ማህበረሰብ ለጉዳዮች ያለን ግንዛቤ እጅግ ያነሰ ነው። የኛ ያልሆኑ ነገሮች ደግሞ አዳዲስ ለሚፈጠሩ ጉዳዮች ማለቴ ነው። እንጂማ ስለኛ ከኛ በላይ የሚያውቅ እንደሌለ ዘንግቼው አይደለም። እናም ከሳምንት በፊት ወደ ሀገራች ገባ የተባለው የኮሮና ቫይረስ ብዙዎቻችንን በሀሳብ ኮርኩሮናል። እጅግ ደጋጎችን አይተን “እናንተማ በርክቱልን፤ ስለኛ ህይወት ጣዕም ቅመሞች ናችሁና ጤናችሁ ይብዛልን” እንዳልነው ሁሉ፤ አንዳንድ ጉደኞች “ጉድ!” የሚያስብል ተግባር ውስጥ ገብተው መክረማቸውም ተሰምቷል። እርግጥ ተቆንጥጠዋል አሉ። ቁንጥጫው ተገቢ ነው ግን አይበቃቸውም። የምር በወገን ላይ ለጨከነ ቁንጥጫ ያረካል? በፍፁም። አቤት አቤት ጭካኔ! በወገን ላይ የምር ይደረጋል? ወይ ዘንድሮ! ባይሆን ጥሩ ነበር ወገን፤ መሆን የሌለበት ግን ሆኗል። ባንሰማ ጥሩ ነበር፤ ግን ደግሞ ባንወድም ሰማን። ባይደረግ መልካም ነበር፤ ግን ደግሞ ተደረገ። ስናሳዝን ግን! መተዛዘንናችንንና መተሳሰባችንን ማን ቀምቶን ይሆን? ማንስ ለውጦብን ይሆን? ግን የእኛ የምንለውን እኛነታችንን በ“እኔ” ቀየረብን። “እኔ ከሞትኩ…..ን” ከኛ ጋር ያጋባው ግን ማን ነው? ከዚህ ጋርማ መፋታት አለብን። ጉድ ነው! ይሄ ለማመን ይከብዳል። ወገን ስለወገን ሳይሆን ስለራስህ ብለህ ሰው ሰው ሽተት፤ ካልሆነ ኑሮህ ጣዕም ያጣል። በሰዎች ችግር ለመክበር መጣር ከባድ ነው። በሰዎች ስጋት ነግደህ፤ ለሽሮ የሚጋፋን ረግጠህ ቁርጥ ስጋ ለመብላት መስገብገብ የምር በጣም ያስተዛዝባል። ሰሞኑን የሆነው ይህ ነው። ምስኪኑ፤ የማያውቀው “መዓት መጣብህ” ተብሎ ወደአንተ ዘንድ ለመሸመት ደጅህ የመጣን አቅመ ቢስ ገፈተርክ አሉ። በደህናው ጊዜ ለአንተ መለወጥ የተጋውን ሚስኪን በክፉ ቀኑ ክፉ ሆንክበት ሲባል ለሰሚው ግራ ሆኗል። ኧረ በፍጹም በዚህ ሰዎች በፍቅር በኖሩበት ሀገር ነጋዴ ህዝቡን በክፉ ቀን አይገፋም፤ ሰዎች በአንድነት ጠብቀው ባቆዩት ፍቅር እንዳይበጠስ ሆኖ በተጋመደበት ምድር ነጋዴ በህዝብ ላይ አይጨክንም፤ መነጠል በሚከብድበት፤ መነጠል በማይቻልበት ማህበረሰብ እንዲህ አይደረግም ተብሎ ሙግት ቢገጥሙም እውነቱ የተገላቢጦሽ መሆኑ አስፈርቷል። አንዳንዴ ሳይፈልጉት የሚውጡት ሂስ አለ። ነጋዴ ሆይ “ዋጥ!” ተብለሀል ዋጠው። ይህን አድርገኸው ከሆነ ከባድ ነው። በወገንህ ላይ ጨክነህ ከነበር አጉል ነው። ይህ እውነት ሳይፈልጉትም የመረረ ነው። ወዳጄ! እሰኪ አስበው ምንአልባት የዚህ ህዝብ ቀና መሆን አንተን ጠብቆሀል። የዚህ ህዝብ እያንዳንዱ ጥረት አንተን ጠቅሞሀል። አይንህን አስፍተህ ከተመለከትክ በምንም መልኩ በራስህ የያዝከው አንዳች ነገር እንኳን የለም። ስለራስህ ብታስብ ይህንን ለማድረግ ባላሰብክ፤ ሌላውን ተወው። ስለራስህ ምቾት፤ ስለራስህ ደስታና የተቃና ኑሮ ሌላውን ማኖር ግድ ይልሀል። ወዳጄ ደሀው እኮ ላንተ ውበት ነው። ከመሀሉ ስትቆም አንተን የሚያስጌጥ፤ ደፋ ቀና ብሎ፤ ብዙ አምርቶልህ ትንሽ ጎርሶ የሚያድር፤ ብሎኬት ተቀባብሎ ቤትህን የሚያንፅ፤ ቀለም አስቀስሞ ልጆችህን በእውቀት የሚያበለፅግ፤ ጠዋት ቤትህን አንኳኩቶ ቆሻሻህን የሚያፀዳ፤ የእርሱ መኖር ነው አንተን የሚያኖርህ! እንዲያው ሌላው ይቅር፤ “ማነህ… “ እያልክ የፈለከውን የምታዝዘው፤ “እዚያ ጋ አምጣልኝ እንጂ!” እያልክ የምትጣራው “ሎሌ” ላንተ እንዴት ጠቃሚ መሆኑን ዘነጋህ? ያለ መስተንግዶ መኖር አይከብድህም፤ እንዲያው “ጌታው ምን ልታዘዝህ? ምን ጎደለህ?” የሚልህን አትወድድም? እና እንዴት ብለህ በዚህ ሰው ጨከንክ ታዲያ? ግን ካንተ ጋር በገቢው አነስ የሚል ከጎንህ ከሌለ በምን ትኮፈሳለህ? እንዲያው በሞቴ ወዳጄ ለአንተ ዛሬ እዚህ ላይ መቆም መሰረት ከእስርህ ያለው ያ ወገንህ መሆኑን እንዴት ዘነጋኸው? ኮሮና የሚባል ጉድ መጣልህ ፤እራስህን ጠብቅ፤ መጠበቂያውም እኛውልህ ተብሎ የተነገረውና እራሱን ለማዳን ለሸመታ ወዳንተ የመጣን ምስኪን “አምጣ” እያልክ ስትነጥቀው የዋልከው ገንዘብ እኮ እረፍት አይሰጥህም። ጥረው ግረው የበሉት ነው የሚጣፍጠው፤ በእርግጥ ጣዕም የሚገባህ ከሆነ ያ ነው ትክክለኛ ጣዕም የሚፈጥር፤ ያ ነው የራስ ከሆነ ልፋት ተገኝቶ ሲበሉት የሚጥም፤ ከወገንህ መንጭቀህ የሰበሰብከውን ገንዘብ መሽቶ ጣትህን ከምላስህ ምራቅ እያስነካህ ስትቆጥረው ቫይረሱን ወደ ውስጥህ ብታዘልቀውስ? ከባድ ነው! የተያዝክበት መንገድ እንኳን አጉል ነው። ወዳጄ ትላንት የጨከንክበት ወገንህ መታመምህን ሰምቶ የሚጠይቅህ ይመስልሀል? በፍፁም! ሰው የእጁን ፍሬ ነው የሚበላ፤ ስለ መልካም ውለታህ መልካም ምላሽ ጠብቅ፤ ካልሆነ ግን በተቃራኒው ነው። ሁሉም የተሰፈረ ልኬት አለው። ከዚያ ውልፍች አይልም። ስላግበሰበሰ ከተፈቀደልት አምልጦ ትርፍ አያሻምድም፤ ስለተወው የርሱ የሆነ ድርሻ በሌላ አይቀማም። ወገን ስለራስህ ምቾት ለሌሎችን ምቹ ሁን። ስለራሰህ መልካም ፍፃሜ ስትል መልካምነት ላይ አዘውትር! ሰው በቁርጥ ቀን ይለያል፤ ሳንፈልግ የለየናችሁ እነአጅሬ፤ ያደረጋችሁትን ባናውቅ መልካም ነበር። እናንተም ይሄንን ባታደርጉ ምንኛ በወደድን፤ ተግባር እኮ ጥላ ነው በሄዱበት ሁሉ የሚከተል፤ ሲበርድ ፀሀይ ሆኖ የሚያሞቅ፤ ሲሞቅ ምቾትን የሚፈጥር በጭለማ የፋኖስን ያህል ብርሀን የሚፈነጥቅ፤ የምር መንገድ የሚገራው በበጎነት ነው። ዛሬ ነገ ላይ ታሪክ ነው። ያ ታሪክ፤ ያ ትውስታ ነገ ላይ ሲገለፅ ሁለት መልክ አለው። አንዱ በተወሳ ቁጥር የሚያስፈግግ፤ ሌላኛው ደግሞ ምነው ባልተነሳ፤ አሁን የምር ይህንን የሰው ልጅ ያደርገዋል የሚያስብል፤ ከመጀመሪያው ማህደር ውስጥ እራስን ማስገኘት ነው። ቸር ያሰማን! አዲስ ዘመን መጋቢት 14 /2012 ተገኝ ብሩ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=28957
[ { "passage": "በልጅነቴ ያስተዋልኩትን ሐቅ ልንገራችሁ። ነገሩ እንዲህ ነው። ሰዎች ተሰባስበው፣ እንዲቀናቸው ተመርቀው አደን ይሸኛሉ፡፡ኑሯቸውን በዱርና በገደል ያደርጋሉ፡፡በዚህ ሁኔታ ለወራት በመቆየት በለስ የቀናው አንበሳ በመግደል ጀግና ይሰኛል፡፡በለስ ያልቀናው በርሃብ ሲናውዝ ከርሞ ይመለሳል። ገዳዩም ጀግንነቱን በገበያ ያስመርቃል፤ ያውጃል፡፡የገደለውን የአንበሳ ቆዳ በትከሻው ላይ ይደርባል፤ ፀጉሩንም ቅቤ ይቀባል፡፡ከዚያም ሌሎች ጥቂት የሥጋ ዘመዶቹን አስከትሎ በገበያው መሐል እየተንጎማለለ ስለመፈጠሩ እንኳን በውል የማያውቁት በርካታ ሰዎችን በመንጋ ያስጨፍራል፤ ሲዘፍኑለት ይውላሉ፡፡እርሱም እንደሙሽራ ሲሳምና ሲሸለም የሞራል ግለቱ ጣራ ይነካል፡፡እግር የጣለው ሁሉ እያጨበጨበ አብሮ ይተማል፡፡የእንስሳት መብት ተሟጋች በማያውቃት አገራችን በቀደሙት ጊዜያት የአንበሳ ነፍስ ማጥፋት በመንጋ ያስከብርና በመንጋ ያዘፍን ነበር፡፡አሁን ላይ ይባስ ብሎ የሰው ልጅ ሕይወትን በመንጋ ማጥፋት እና በመንጋ አስክሬን መጎተት በመንጋ ያስከብር ይዟል፡፡በመንጋም ሲያስጨፍር አስተውለናል፡፡ እርግጥ ነው በዚህ የመንጋ እንቅስቃሴ ውስጥ የሀብት ጥሪት የመቋጠር ዕድል ያጋጠማቸው እንዳሉም ሹክሹክታ ይሰማል፡፡በመንጋው በአባልነት ተቀላቅለው የዘመቱ በቀን እስከ 500 ብር ሲቋደሱ፤ በመንጋው ዘመቻ በርካታ ሰው በመውረር ‹‹አራስ ነብር›› ሆነው ለዋሉ ደግሞ እንደዘመቻ አውዱ በበቃኝ ሳንቲም እንዲዘግኑ ይደረጋል መባሉን ከመከራ ቀማሿ ድሬ ሹክ ብለውናል፡፡አጃኢብ ያሰኛል፤ ጆሮ አይሰማው የለ፡፡ይሄ ገንዘብ የሚበቅልበትን ዛፍ አምላክ ይወቀው፡፡ተሠርቶ ያልተገኘ በጂኒ የሚመጣ ገንዘብ ሕዝቡን በመንጋ የጂኒ አመል እንዲኖረው አደረገ፡፡ለመልካም ተግባር ሲሆን የመሰባሰቡና የመደመሩ ጉዳይ ዳገት ይሆንብናል፡፡የእኛ ትውልድ እንዲህ ነው፡፡ቅን መሪዎችን ሳይሆን ቅንቅኖችን የሚሻ፡፡ከአብዮች ሳይሆን ከአባዮች የሚወዳጅ፣ ከሚወዱት ሳይሆን ከሚንቁት ጉልበት ሥር የሚወሸቅ፤ ተራማጅ አስተሳሰብን ያልፀነሰ ጮርቃ ሆኗል፡፡ ቢቆነጠጥና አደብ ቢይዝ አይሻልም ትላላችሁ? ‹‹አገር ሲያረጅ ጃርት ያፈራል›› ነበር ብሂሉ፡፡ታዲያ አገሬ ተባይ ማፍራቷ አርጅታ ይሆን እንዴ? እንጃ አይመስለኝም፡፡ትውልዳችንን ልንፈትሽና ልንመረምር ይገባል፡፡ወቅቱን ጠንቅቆ የሚረዳ ብልጥ ትውልድ ያስፈልግ ይመስለኛል፡፡ዋሽቶ ማስታረቅ እንጂ ዋሽቶ ማጋደል በክብር ሲያስጠራ ከታሪካችን አልሰማንም፤ አልተማርንም፤ ለማንም አይበጅም፡፡ዘመኑን የተነጠቀና ቀልቡ የተገፈፈ ባካኝ በአንዳንዶች አጠራር ‹‹የተረገመ›› ትውልድ እንዲበቅል ቆላ ከደጋ እየባከኑ ደም ሲያራጩ መዋልን ሥራዬ ብለው የተያያዙት በርክተዋል፡፡አዎ አገሪቱ እንዲህ አይነት አዳዲስ የሥራ መስኮች የሚፈጥሩ ሰዎች እንዳሻቸው የሚኖሩባት አገር ሆናለች፡፡የተራ ዜጋውም ጉዳይ ‹‹በሬ ካራጁ ….›› አይነት ሆኗል ወዳጄ፡፡‹‹ከደሙ ንፁህ ነን›› ባይ አፈቀላጤዎችም ወንድም ወንድሙን መግደልና ሲያሸብሩ መዋል እንደ ሥራ ስለመቆጠሩ እየነገሩን ነው፡፡እንደው ማን ይሙት በእኔ ልጅ ደም የእሱን ልጅ እንጀራ የሚያበስል የዋህ ኢትዮጵያዊ ስለመፈጠሩ እንደመስማት የሚያንገሸግሽ ሕመም ምን አለ?፡፡ በእምነት ቅንብብ አጥር ውስጥ በቅሎ እዚህ የደረሰ ኢትዮጵያዊ ‹‹ያልዘራውን የሚያጭድ›› አለመኖሩን መረዳት አያዳግተውም፡፡ የሰው ልጅ በሥራው ልክ ተመዝኖ የሚከፈለው በአንድ ወቅት በዓለም ላይ የበቀለ አረም ተደርጎ ሊታይ ይገባል፡፡ራሱን ዘላለማዊ በማስመሰል የአልማዝ፣ የወርቅና የብር ደረጃዎች እየሰጡ እያንዳንዱን ነገር ‹‹ለእኔ›› እያሉ መስገብገብ የኢትዮጵያውያን ስብዕናም አይደለም፡፡የሰው ልጅ ሕይወት መጥፋት የሚያስጨፍረው አካል መታየት ሲጀምር መላ ሊበጅለት ይገባል፤ ሕመም መለከፉን መረዳት ያስፈልጋል። ነገ ራሱ ተራ ጠባቂ ሟችነቱን ረስቶታል ማለት ነው፡፡‹‹ሆሆይ›› ለካ ነገረ ሥራው ከተቀየረ ዋል አደር ብሏል። የምኑ እንዳትሉኝ፤ ከመኖሪያ ቀያችሁ እስከ ፌስቡክ ሰፈራችሁ የምታዩትንና የምትሰሙትን ወሬና ድርጊት አብጠርጥራችሁ ፈትሹ፡፡‹‹ከሞኝ ደጃፍ ሞፈር…›› ነው ነገሩ፡፡ከእነ እንትና ሰፈር ዕሳት እየጫሩ በእነ እንትና ሰፈር በ‹‹ቪ ኤይት›› ቄንጠኛ መኪና መንፈላሰስ ዋ! ካላስባለ፣ ነገ ጨዋ ልጅ ከሰፈርህ ቀርቶ ከአብራክህ ሊወጣ አይችልም፡፡የሰውነት ሚዛናችን እያነሰ የእንስሳነት አመላችን እየጎለመሰ ይሄድ ይዟል፡፡ እኔ ለአቅመ ማስተዋል ከደረስኩበት ጊዜ አንስቶ ያስተዋልኩት የሰው ልጅ ሞራል የማጣት ልክ እንደዚህ ጊዜ ሲዘቅጥ አስተውዬ አላውቅም፡፡ምን አልባት የእኔ የማስተዋል ልክ ከሆነ አላውቅም፡፡ኧረ እንደውም ባደግንበት ወግና ባህልማ የሰው ልጅ በሕይወት ሲኖር ከሚያገኘው ክብር የላቀ አስክሬኑ ይከበር ነበር፡፡አብሮን ባደገው የመበቃቀል ክፉ ልማዳችንም ውስጥ ቢሆን እንጥፍጣፊ መከባበር ነበረበት፡፡እንኳንስ ሰውን ያህል ነገር ቀርቶ የእንስሳትም ቢሆን አስክሬን የተመለከተ ሰው ያዝናል፤ ባስ ሲልም በዓይኑ በብረቱ የሰው አስክሬን ወድቆ በድንገት የተመለከተ ሰው ራሱን ለከፍተኛ ፀፀት ይዳርጋል፡፡ምን የሠራሁት ሐጢያት (ክፉ ሥራ ) ቢኖር ይሆን ፈጣሪ ይሄን ያሳየኝ፤ በሚል ነፍሱን እሱ ያጠፋ ያህል ፈጣሪውን በፀፀት ይለምናል፡፡ነፍሱ በፈጣሪው ፊት ትጠየቅ እስከሚመስለው ድረስ ይፀፀታል፡፡‹‹ማረኝ›› ይላል፡፡አሁን አሁን የሚስተዋለው\nድርጊት ግን ለየቅል\nሆኗል፡፡እመኑኝ ታሪክ ዋሽቷል\nወይም ትውልዱ ላሽቋል\nየሚያሰኝ ደረጃ ላይ\nእንገኛለን፡፡በመንጋ ተነስቶ በመዝመት\nየሰው ልጅ ሕይወትን\nማጥፋት በየትኛውም እምነት\nየተወገዘ ብቻ ሳይሆን\nአውሬነት ተደርጎ የሚቆጠር\nተግባር ነው፡፡እንዲህ አይነት\nየአውሬነት ተግባር የመፈፀም\nድፍረት እንዲሁ በአጭር\nጊዜ የሚለመድ ባህሪ\nአይምሰላችሁ፡፡ይህ ትውልድ ጤንነቱ\nሊፈተሽ የሚገባ ይመስለኛል፡፡በማንኛውም\nመመዘኛ ሊያሳምን የሚችል\nአመክንዮ የሚቀርብበት ጉዳይ\nአይደለም፡፡አዲስ\nዘመን\nኅዳር 11/2012 ሙሐመድ ሁሴን", "passage_id": "5185dadf64d68adb195255824800fbd0" }, { "passage": "መሰለፍ በዝቷል፡፡ ለዳቦ፣ ለታክሲ፣ ለዘይትና ስኳር ኧረ ለምግብ ብፌም ጭምር መሰለፍ ግድ ሆኗል፡፡ ጊዜ የተረፈን ይመስል ሰዓታትን በሰልፍ ማሳለፍ ሳንወድ በግድ ለኛ የቀረበልን የየዕለት ገጠመኛችን ብሎም ተግባራችን ሆኗል፡፡ ዛሬ ስለ ዳቦና ዘይት ሸመታ ሰልፍ አይደለም የማውራው ወዳጆቼ፡፡ እሱማ ተብሎ ተሰለቸ ፤ ጭራሽ ተላምደነው ረስተንዋል እኮ፡፡ ይልቅ መንገድ ዘግተው መኪኖችን የሚያሰልፉ ምን አገባኝ ብለው ሰውን ብዙ ጉዳይ ውስጥ የሚያስገቡ መንገድ ዘጊዎች ላወራችሁ ነው፡፡ በእነርሱ ምክንያት መንገድ መድረሻችን ርቆን በእነርሱ ሰበብ ወደምንፈልገው መድረስ ያልቻልንና ስራችን ተበላሽቶብን ውስጣችን የደበነ ስንቶቻችን እንሆን? ታክሲ ውስጥ ነኝ፡፡ አጠገቤ የተቀመጠው ሰው እጅጉን መቸኮሉ ከሚለዋወጠው የስልክ ምልልስ ተረዳሁ፡፡ “እየደረስኩ ነው 10 ደቂቃ ብቻ፡፡” ይህን አረፍተ ነገር እሱን በመጠበቅ ላይ ላለና ለሚደውልልት ሰው እየደጋገመ ይመል ሳል። የታክሲው ተሳፋሪዎች አብዛኛዎቻችን መነሻችን አራት ኪሎ መዳረሻችን ደግሞ ሜክሲኮ ነው ፡፡ ታክሲው ከአራት ኪሎ ትምህርት ሚኒስቴር ህንፃ አለፍ እንዳለ ከፊት ለፊቱ አላነቃንቅ ያሉት የተሰለፉ መኪኖች ተከትሎ ይንፏቀቃል፡፡ አጠገቤ የተቀመጠው ደዋይ አሁንም ቃሉን ሳይለውጥ “አስር ደቂቃ ብቻ ታገሰኝ መጣሁ ማለቱን አላቋረጠም፡፡ የሰውዬው አስሬ ከኪሱ የሚጣራውን ስልክ እያወጣ በጣም ይቅርታ አሁን እየደረስኩ ነው አስር ደቂቃ ብቻ ማለት ማብዛቱ ካለው ሁኔታ ጋር አነጻጽሬ ግራ ገብቶኝ ይሄ አስር ደቂቃ ለውጥ ተደርጎበት ተሻሽሎ ይሆን እንዴ ብዬ ማሰብ ጀመርኩ፡፡ በነገራችን ላይ ምንም ማደስ መለውጥ እና መቀየር ሲቻል የማይታደስ የማይለወጠው አንዴ ከመረሸ መመለስ የማይቻለው ጊዜ ብቻ መሆኑን ስንቶቻችን አስበነው ይሆን፡፡ ወደ ኋላ የለም በቃ፡፡ ካለው ላይ መቀነስ የነበረውን ትቶ ያልነበረ ላይ ማድረስ የጊዜ ተፈጥሮአዊ ኡደት ነው፡፡ ሰውዬው ቀጥሏል መጣሁ ደረስኩ አስር ደቂቃ…ወይ አስር ደቂቃ! እኮ ሜክሲኮ አይደለም ፍልውሀ ሳንደርስ ብዙ አስር ደቂቃዎች አለፉ፤ ተደምረው ሰዓት የሚሞሉ አስር አስር ብዙ ደቂቃዎች፡፡ ከወዲያኛው የስልክ ደዋይ ወይም ባለ ጉዳይ ደውሎ በማርፈዱ ምክንያት ትቶ በሆዱ ነገረው፡፡ ሰውዬው ተበሳጭቷል ያመለጠው ወሳኝ ጉዳይ መሆኑ ሁኔታው ያሳብቅበታል፡፡ ከታክሲው ወርዶ በእግር አይሮጥ አይደርስ ነገር፤ ታክሲውን አይታገስ ነገር ቆሟል፡፡ ወዳጄ ከወዳጁ ጋር ተቀያይሞ መቅረቱ አልያም ደግሞ ጉዳዩ ሳይሰምር መቅረቱ አናዶታል ። የሚጠብቀው ሰው\nቁጣ በተቀላቀለ ግሳፄ ሲናረውና ያሰበው ባለማሳካቱ ቆጨው፡፡ ያለመው ያለመስመሩ አበሳጨው፡፡ እዚያ መድረስ ያልቻለበትን ምክንያት ቢያቀርብ፣ ይቅርታ ቢጠይቅ፣ ቢያስረዳው ወይ ፍንክች፡፡ ከወዲያኛው ስልክ የሚሰማው የቁጣ ድምፅ የሰውዬውን ታጋሽነት እንዳውቀው አደረገኝ፡፡ ሰውዬው በስልክ የሚያወራውን ንግግር ለማስረዳት አልተቸገርኩም፡፡ የደዋዩ ድምፅ አጠገቤ ከተቀመጠው ሰው አልፎ በደንብ ይሰማኛል። ስልኩ የሚልከው ብቻ ሳይሆን የሚቀበለውም እንዳይመጥን የተደረገ ነው፡፡ እና ሰውየው ተሳድቦ ተሳድቦ ዘጋው፡፡ አጠገቤ ያለው ሰው የምር አሳዘነኝ፡፡ እሱም አለመታመኑም ያሰበው አለመሳካቱም አናዶታል፡፡ ወዶጆቼ ስንት ተመሳሳይ ገጠመኝ ገጥሞን በሁኔታውም ተማረን ይሆን፡፡ ከተማዋ ያልዋት መንገዶች በስርዓት መጠቀም አለመቻላችን ለትራፊክ መጨናነቁ አንድ ምክንያት ነው፡፡ አዲስ ያሏት መንገዶች ከሚርመሰመሱባት መኪኖች ጋር አለመግጠሙ ብቻ አይደለም ወዳጆቼ የተሳፈርንባቸው መኪኖች ተሰልፈው እያየን የማሳለፋችን ምስጢሩ፡፡ ይልቁንም መንገዶቹ በአግባቡ መምራት በሥርዓት የትራፊክ ፍሰቱን እንዲያሳልጡ ባለመድረጋቸው ነው፡፡ እርግጥ የመኪናው ቁጥር መጨመር የመንገዱ ውስን መሆን ለዚህ ችግር ማባባሻ ትልቅ ምክንያት መሆኑ አይቀሬ ነው፡፡ አንዱ ጓደኛዬ ደጋግሞ ሲቀልድ እሰማ ዋለሁ ። እንዲሁ እንቶ\nፈንቶ አይደለም ቀልዱ ቁም ነገር የበዛው ለዛን የተላበሰ ቀልድ የሚቀልድ ነው። አንዳንዴ ቢያወሩ የማንሰለቻቸው ጥዑም ንግግሮችን የተካኑ ቢነገሩ የማይጠገቡ ወጎችን አዋዝተው የሚያቀርቡ አንደበተ ርቱዕ የሆኑ ሰዎች ይገጥሙናል፡፡ እንደዚያ ያለ ሰው ነው ወዳጄ፡፡ በሚከብዱ ነገሮች ላይ መቀለድ የሚወድ በዚያም ከባድ ነገሮችን አቅሎ የሚያይ፡፡ ቀላጁ ጓደኛዬ መኪና መግዛት አይደለም በቀን በታክሲ ብዙ ተመላልሶ ኑሮን መግፋት የከበደው ነው፡፡ ኑሮ አንዳይቀልድበት ቀድሞ ኑሮ ላይ ይቀልዳል፡፡ እንዲህ ነው መዳፈር ምን አባቱ የቀለዱበት ጉዳይ መቅለሉ አይቀር፡፡ ሰሞኑ የሆነ ስብሰባ ላይ አርፍዶ ተገኝቶ ለምን እንደዘገየ ተጠየቀ፡፡ “ያው አዲስ አበባ መኪና መንዳት ይከብዳል፤ መኪናዬ መንገድ ዳር ጥዬው አልመጣ ነገር መንገድ ተዘጋግቶብኝ በየት ልንዳ፡፡” የሱ ምላሽ ነበር፡፡ ከኔ በቀር ሁሉም የእሱን ምላሽና አሁን ያለው ሁኔታ አገናዝቦ ያላንዳች ምክንያት ጥርጣሬ ተቀበለው፡፡ አዲስ አበባ መንገዶችዋ ጠበው መሄጃ አጥሮ ብቻ እኮ አይደለም ይሄ ሁሉ የትራፊክ መጨናነቅ ውስጥ የገባችው፡፡ እነዚያን የበዙ ምክንያቶች ደግሞ መኪናው በሚፈለገው መልክ እንዳይጓዝ ሰራተኛውን የፈለገበት በሰዓቱ እንዳይደርስ አድርገውታል፡፡ አስራ አንድ ሰዓት ተኩል ከስራ የወጣን በትራፊክ መጨናነቁ እቤት የምንገባው አምሽተን የናፈቁን ልጆቻችን ጋር ሳንጨወት ደክመው ተኝተው ሆኗል፡፡ ውዶቼ አንዳንዴ መድረስ የፈለጋችሁበት ሳትደርሱ መገኘት ያለባችሁ ቦታ ሳትገኙ ታክሲ ውስጥ ቁጭ ብላችሁ ሰዓታት ያሰለፋችሁበት ጊዜ ትዝ ይላችኋል? ትዝ ይላችኋል ነው ያልኩት የኔ ነገር ያለንበትና የምንኖርበት እኮ ነው ምን ነካህ ካላችሁኝ ልክ ናችሁ፡፡ አንዳንድ ልክ ያልሆኑ ነገሮች ልክ እንዳንሆን ያደርጉናል፡፡ እናም ልክ ባልሆኑ መንገድ ብዙ ልክ የሆኑ ነገሮች ይናዳሉ፡፡ በተለይ የመንገድ መዘጋጋቱን ለማቅለል የሚሰራው የአዲስ አበባ መንገድ ትራፊክ ማኔጅመንት በትራፊክ መጨናነቅ የታወቁና ለጉዞ አስቸጋሪ የተባሉ መንገድና ቦታዎች ለይቶ ማሳለጥ እንዴት ከበደው፡፡ በየመሸታ ቤቱ በራፍ ላይ ተሰልፈው መንገዱ በመዝጋት ሌላን አላሳልፍ ያሉ እነርሱ ደግሞ በአንፃሩ እርፍ ብለው አልኮል በየአይነቱ የሚኮሞክሙ ግድ የለሾች ለምን መግራት አቃተው፡፡ አሁን አሁንማ አንዳንድ ሰፈሮች ላይ ቀን ሲያንቀላፉ ውለው ማታ የሚያብዱ ጉዳኛ የውስኪና መጠጥ ቤቶች ተበራክተዋል ። የመጠጥ ቤቶቹ\nደንበኞችም መኪናቸውን አሰልፈው መንገድ ዘግተው በማን አለብኝነት በካካታ ያመሻሉ፡፡ ለመንገድ ስርዓቱ አለመከበር ለትራፊክ ፍሰቱ አለመሳለጥ ትልቅ እንቅፋት የሚሆኑና ያልታወቁ በምክንያት ያልተለዩ ችግሮች እንደነዚህ በርክተዋል፡፡ ይህቺ ከአቅምዋ በላይ ብዙ ነገሮችን የተሸከመችው ከተማ የከተማነት ጥግ ላይ ማድረስ ከብዶን እኛን ጥግ ጥግ ማስያዝ ጀምራለች፡፡ ከፈለግነው ጋር ተገናኝተን በፈለግነው ሰዓት ጉዳያችን ላይ እንዳናወራ ካሻን ቦታ ተገኝተን የሚጠበቅብን እንዳንወጣ ያላትን አቅም ባለመጠቀማችን አቅም አሳጥታናለች፡፡ አዲስ እንደ ባህሪያችን አውላ እንደ አመላችን አሳድራ በሰፊው ሆድዋ ችላን ዛሬ ድረስ ደርሳለች፡ ፡ እኛው\nበሰራናት ልክ ገጽታዋ የምንመለከት ሰሪዎቿ ነን፡፡ ይህች የብዙኋን መዲና የስምዋን ያህል ባትዋብም የሚበቃንን ባይሆን የአቅምዋን ችራ ታኖረናለች፡፡ እኛ የምንሰጣት ነገር አንሶ ከእርሷ የምንጠብቀው በዝቶ እንጂ ለውጧንማ ማቅረብ እጅጉን በቀለለን ነበር፡፡ ይህቺ የኛ የሆነች ከተማ እንደራሳችን በኃላፊነት የምንይዛት እንደ ግል ጉዳያችን ማደግዋን የምንመኝና ለዚያም የምንታትር ቢሆን ከፍታ ላይ ባስገኘናትና እኛም በዚያ ውስጥ በዋኘን ነበር፡፡ ያላት ውስን ነገር በአግባቡ ባለመጠቀማችን እንቅስቃሴያችን ውስን እንዲሆን አድርጎብናል፡፡ ያሉትን መንገዶች ከኃላፊነት በራቀ ሁኔታ እየዘጋን ለኛ ስራ ስምሪት የሌላውን መዳረሻ ያራቅን ብዙዎች ነን፡፡ ዛሬ ላይ የመንገዱ መጨናነቅ ቀጠሮ እንዳ ናከብር ስራችንን በወጉ እንዳንወጣ አድር ጎናል ። መዳረሻው ርቆን\nበእግር አንሄደው ነገር ርቀቱ የማይሞከር ሆኖብን የቀጠርነው ሲቀር እየታዘብን ቀጥረውን ስንዘገይ እየታዘቡንም ቅያሜ ውስጥ ገብተናል፡፡ ስለራሳችን ምቾት ስንል የሌላን መንገድ መዝጋቱ ስለራሳችን ስምሪት ስንል ሌላውን መስመር ማሳጠቱ እስከመቼ ይቀጥል ይሆን፡፡ ለእያንዳንዱ ችግር\nመነሻ ተብሎ የሚጠቀስ\nቀጥተኛ የሆነ መነሻ\nከማሳየትና ከማየት ባለፈ\nትልቁን ችግር የፈጠሩ\nትንንሽ ችግሮች ላይ ትኩረት\nማድረግ ቢለምድብን የትልልቆቹ\nችግሮች መቆሚያ የሆኑ\nትንንሽ ችግሮች መቅረፍ\nየምንችል አይመስላችሁም፡፡ ውዶቼ\nመንገድ እንሁን ለዚያውም\nምቹ መንገድ፤ ሰዎች\nበተቃና መልኩ ተጉዘው\nወዳሰቡበት የሚደርሱበት ቅን መንገድ፡፡\nቸር እንሰንብት፡፡አዲስ ዘመን ነሃሴ 3/2011", "passage_id": "3385261c274ec26df56c4c3ca45d3faa" }, { "passage": "አብርሃም ተወልደ የአንዳንድ ሰዎች ጽሞና ማን ወሰደው? ምን ዋጣው? ሰው እንዴት የጽሞና ጊዜ ያጣል።በሁሉም ሁኔታዎች ውስጥ ትችት፣ ስድብ ፣ማጉረምረም … የለመደባቸው ጥቂት አይደሉም።ትዕግስት የሚባል ነገር አጥተናል፤ ሲሆንልም ሲሆንብንም አንድ አይነት ሆነናል።ባለፈው ሳምንት ከብዙ ጊዜ መለያየት በኋላ ከአንድ ወዳጄ ጋር ተቀጣጥረን በአንድ ምግብ ቤት ተገናኘን፤ የዚያ ቤት ምግብ ጉዞ ፍታት/ረጅም ጊዜ የሚወሰድ የፍታት አይነት ነው/ የሚሉት አይነት ስለሆነ መጨዋወት ጀመርን፤ ባለመገናኘታችን የተነሳ ብዙ ያልተወያየንባቸው ርዕሰ ጉዳዮች ነበሩና መወያየት ጀመርን።እንዳው ለወጉ ተወያየን አልኩ እንጂ አንዱን ስናነሳ ሌላውን ስንጥል እና ስንተች ነው የቆየነው።በእርግጥ አንዱን ማንሳት ሌላውን መጣል ተፈጥሯዋዊ ናቸው።ግን ያዢያቸውን ይመስላሉ።ውይይት ካደረግንባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ በትግራይ ሲካሄድ የቆየው ህግን የማስከበር ዘመቻ ነው፤ በዚህም ላይ ወዳጄ በአብዛኛው የሚችለውን ያህል ነቀፈ፤ አቃቂር አወጣ፤ ትንሿን ችግር ዘርፍ አበጃጅቶና አግዝፎ ገለጻት፤ ተቸ።በቃላት መተቸት ያልሆነለትን ደግሞ ቀኝ እጁን በማወናጨፍ ፣ ፊቱም በማንጠልጠል ጭምር ልክ አለመሆኑን ገለጸ፤ ለተነሳው ጉዳይ ድምቀት ለመስጠት ሞከረ።የተናገረው አስፈርቶት ይሁን አላውቅም ደግሞ በረድ አለ።የህዝቡና የመንግስት አይንና ጆሮ እኮ እኛ ነን አለኝ፤ አየህ አንከኖችን እና ችግሮችን ነቅሶ በመውጣት የሚተች ባይኖር፣ ሁሉም ልክ ነው ቢል አንደኛ መንግስታትን አምባገነን እናደርጋቸዋለን ሲል አብራራልኝ።የፈለገውን ያህል ብናገር አስፈልጋለሁ ማለቱ ነው።በጨወታችን መሐል ምግቡ ቀረበ፤ ቀመስኩት፤ ሸጋ ነበር፤ የገበታ ስነ ስርአት ባይሆንም አሁንም ጨዋታችንን ቀጠልን።እኔ የምልህ፤ የምትሰራበት አካባቢ የመመገቢያ ቦታ እና የምግብ አማራጮች ብዙም ያሉበት አይደለም።የት ትመገባለህ ስል ጠየኩት? ምን እባክህ! በሚል ሃሳቡን ጀመረ።የትስ ቢሆን ያው ነው፤ ምን ደህና ነገር አለ፤ ሌላ ዘንድ አትሂድ፤ አሁን እየባለነው ያለውን እንጀራ ብቻ ተመልከት፤ ከእንጀራው ስንት በመቶው ጤፍ እንደሆነ አናውቅም፤ በቅርቡ ከባልደረቦቼ ጋር ምግብ እየበላን ስንጨዋወት አንዱ ጓደኛችን አያችሁ ይህን እንጀራ ሲል አመለከተን፤ ምን ሆነ አለነው፤ ዛሬ ገና ጤፍ ያለበት እንጀራ አየሁ ሲል አስተያየቱን ሰጠ።አሁንስ ተሳክቶልሃል አልኩት በልቤ፤ መቶ በመቶ የጤፍ እንጀራ የሚበላው መኖሪያ ቤት ሲዘጋጅ ብቻ ነው።ሆቱል ቤቱም፣ አንጀራ ሻጩም ጥራጥሬ የተቀየጠበት የጤፍ እንጀራ ነው የሚያቀርቡት።መኖሪያ ቤትም የሆነው እጁ ጤፍ ይሆንና የተቀረው ጥራጥሬ ሊሆን የሚችልበት ሁኔታ አለ፤ ይሄ ምን ችግር አለው፤ እህል ነው፤ ችግሩ የሚከፋው የጄሶ እንጀራ መሆኑ ላይ ነው አልኩት።ወደ ገበታው ተመለሰን፤ ወጡን እየው፤ እየው! በበርበሬ ይሰራ በሸክላ … አለኝ፤ ያነሳቸው ሀሳቦች ምግቡን ይበልጥ እንዳጣጣም አረጉኝ።ስጀመር ያገኘሁትን ጥፍጥና ከወዳጄ አስተያየት በኋላ እያጣሁ መጣሁ።ሁሉም ነገሩ የሰው ልጆችን ሆን ተብሎ ለመጉዳት ታስቦ የሚደረግ አርጎ እየወሰደ መሆኑ አሳሰበኝ፤ የወዳጄ ትችት እኔን ፍርሃት ውስጥ ከተተኝ።ቃላት እና ሃሳቦች እንደ አጥንት እና መቅኒ ናቸው፤ አንድ አምሳል አንድ አካል የሆኑ፤ ልንለያያቸው እጅጉን የሚያዳግቱ።ሀሳቦቻችን ማለትም እኛ ብቻ የምንሰማቸው ደምጽ አልባ ቃላት በውስጣዊ ማንነታችን፣ በጤናችን፣ ደስታ እና አመለካከታችን ላይ ተጽእኖ ይፈጥራሉ።እኔም የሆንኩት እንዲሁ ነው፤ ለካ ወዳጄ በአነሳው የነቀፌታ ሀሳብ ተወስጄ ነበር።እውነት እኮ ነው፤ አንድም ደህና ነገር የለም ማለት ጀምሬ ነበር።ጸሐፍት ከአፋችን የምናወጣው ያሰብነውን ነው ይላሉ።አንደበታችን እኛን እንደሞኝ የሚያስቆጥርበት አጋጣሚ አለ፤ በመረጃ ላይ ሳይመሰረቱ መፍረድ፣ መተቸትና መላምት መስጠት ከማዋረድ እና ከማጥፋት ባሻገር መቼም ቢሆን ደስታ እና ሰላም አይሰጥም።የወዳጄ አንዳንድ ሀሳቦቹ መልካም ናቸው፤ ነገር ግን ሁሉም ነገር መንቀፍ እየጉረመረሙ መግለጽ ለምን? ሁሉንም ነገር አለሚዛኑ መተቸትስ ተገቢ ነውን ስል ራሴን ጠየቅኩ፤ አእምሮዬ ይሆናል ያለውን የመፍትሔ ሀሳብ ለገሰኝ።እውነት እኮ ነው፤ የሚጨበጨብላቸው የአዋቂነት እና የንባባቸው ስፋት ልኬቱ ከፍ ያለ ነው የሚባልላቸው “ምሁራን” ጀግኖች ጎበዞች የሚባሉት ትችት ሲያቀርቡ ብቻ ነው፤ ለዚያም ነው በጨለማ የሚታያቸው፤ በሄዱበት ሁሉ መልካም ከመናገር እና ከመዝራት ይልቅ ሁሌም ጨለማውን ሲያዩ ሲያትቱ እና ሲናገሩ የሚታዩት ከዚህ በፊት ባቀረቡት ሃሳብ ባገኙት ሙገሳ ተገፍተው እንደሆነ እገምታለሁ።ከዚህ ቀደም ከተለያዩ ማዕዘናት ስለአገሪቱ የፖለቲካ ጉዳይ የትምህርት ዝግጁቱም ሆነ ለነገሩ መረጃው የሌለው ነገር ግን በሆነ አንድ የትምህርት መስክ ሶስተኛ ዲግሪውን የተማረ ይመጣና ዶክተር እገሌ እባላለሁ፤ ለአገሬ ይህንንና ያንን አድርጌያለሁ፤ የቀድሞ መንግስት… መከራ ሲያደርስብኝ ነበር ሲሉ ያመለክታሉ።እነዚህን ለማረም ፣ ለማስተካከል እንዲሁም አንዳንዱን ወደ ቀድሞ ቦታው ለመመለስ አሁን ያለውም መንግስት አቅም ያለው አይመስለኝም።አሁን አገሪቱን እያስተዳደረ ያለው መንግስት “ሰባኪ” ነው፤ አገርን ለመምራት ሳይሆን በእምነት ተቋም ነው መገኘት ያለበት ሲል ይቆይና፤ መንግስት ህግ ማስከበር አለብኝ ብሎ ሲነሳ ደግሞ ይሄው ግለሰብ /“ዶክተሩ”ተብዬው/ ወንድም ወንድሙን ገድሎ አሁን ይህ ምን የሚሉት ጉዳይ ነው ይልሃል፤ ብቻ የምንም ነገር ሱስ አይያዝህ፤ በተለይ አለሚዛኑ የመተቸት እንዲሁም የመንቀፍ ሱስ፤ በጎ አይታይህማ!ችግሮችን ነቅሶ በማውጣት መወያየት፤ ለመፍትሄውም መምከር የሚበረታታም የሚፈለግም ጉዳይ ነው፤ ከብዙ መልካም ነገሮች ይልቅ ጥቂት ስህተቶችን እየለቃቀሙ አንድም መፍትሄ ሃሳብ ሳይዙ ነቀፌታ ላይ ማተኮር ግን የበሽታ ነው።የህይወት ገጠመኜ (life evenet) የተባለ አንድ የማህበራዊ ትስስር ገጽ ሶቅራጦስ አለ ብሎ ያነበብነውን እስቲ እንመለክት።አንድ ሰውዬ ወደ ታዋቂው ፈላስፋ ሶቅራጦስ ይቀርባል፤ “ስለ ጓደኛህ አንድ ወሬ ልነግርህ ነበር…” ይለዋል።ሶቅራጦስም “ቆይ አንዴ! ምንም ነገር ሳትነግረኝ በፊት ሶስቱ ወንፊቶች ወይም ማጥለያዎች ብዬ የምጠራቸውን ጥያቄዎቼን ላንሳልህ…”ሲል ይጠይቀዋል። “ሶስቱ ወንፊቶች?”ሲል ሰውዬው ራሱን ጠየቀ።“አዎ!” ሲል ሶቅራጦስ መለሰ።የመጀመሪያው ወንፊት እውነታ ነው፤ አሁን የምትነግረኝ ነገር እውነት መሆኑን እርግጠኛ ነህ?” ሲል ሶቅራጦስ ሰውዬውን ይጠይቀዋል።ሰውዬውም “እርግጠኛ አይደለሁም! እኔ እንጃ! ሰው ነው የነገረኝ…”ሲል ይመልሳል።ሶቅራጦስ “ስለዚህ… እውነት ይሁን አይሁን አታውቅም!” ብሎ በሁለተኛው ወንፊት ላይ ተመስርቶ ጥያቄውን ያስከትላል።ሁለተኛው ወንፊት መልካም ዜና ወይም ወሬ ነው? የሚል ነበር፤ አይደለም ሲል ሰውየው ይመልሳል፤ እንደውም በተቃራኒው ነው አለው።ሶቅራጦስ “በአጭሩ… ልትነግረኝ የመጣኸው… ስለ ጓደኛዬ እውነት መሆኑን ያላረጋገጥከውን መጥፎ ነገር ነው ማለት ነው›› ሲል መለሰለት።አንድ ወንፊት ይቀራል! በሱ ወንፊት ካለፍህ ወሬውን ልሰማህ እችላለሁ…” ሲል ሶቅራጦስ ይገልጻል።በ“ሶስተኛው ወንፊት የምትነግረኝ ለኔ ይጠቅመኛል?” ሲል ሰውዬውን ይጠይቀዋል።ሰውዬውም “ይጠቅምሃል ለማለት አልደፍርም! ግን…” ይላል።ሶቅራጦስም “የምትነግረኝ ነገር እውነት ካልሆነ እንዲሁም የማይጠቅመኝ ከሆነ ለምን ልትነገርኝ መጣህ?” ሲል ሰውዬውን ይጠይቀዋል።ሰውዬው ምላሽ አልነበረውም።ቀደም ሲል ለተጠቀሰው\nአይነት በሽታ አንዱ\nመፍትሄ የሶቅራጦስ አይነት\nማንጠሪያ ማዘጋጀት ነው፤\nሌላኛው ደግሞ ማንኛውም\nሰው ችግር አየሁ\nብሎ አንዳች ነቀፌታን\nበሚሰነዝርበት ቅጽበት የመፍትሄ\nአካልም እንዲሆን መጋበዝ\nነው፤ በዚህም አይነት\nመንገድ ክፉ ብቻ\nየሚታያቸውን በመተቸት የተካኑ\nግለሰቦች ላመጡት ነቀፌታ\nመፍትሄ እንዲያቀርቡ ሲጠየቁ\nበጎንም ለማየት ይሞክራሉ፤\nአሊያም ለአንደበታቸው ልጓም\nያበጃሉ።አዲስ\nዘመን ታህሳስ 6/2013", "passage_id": "7be77c866579923455090f2ee63a843d" }, { "passage": "የትኛውም\nነገር የሚለካበት የራሱ ሚዛን አለው። ዘመናችን መሬት ላይ ተገጥመው ግዙፍ ነገሮችን ከሚመዝኑት አንስቶ ጥቃቅን ነገሮችን እስከሚለኩት ሚዛኖች አሳይቶናል (ያውም ከጣሳና ቁና እስከ ዲጅታል)። ቢሆንም ግን የተፈጥሮን ያህል ሚዛን ማግኘት የማይታሰብ ነው፤ ምክንያቱም የተፈጥሮ ስራ ሁሉን ያመጣጠነ ነዋ።ይህ\nያልገባው አንድ ተላላ ሰው ታዲያ፤ ከጠዋት እስከ ማታ ካልተኛ በቀር ያለ እረፍት ወዲህ ወዲያ እያለ የሚቦርቅን ህጻን «እስተካከላለሁ» ብሎ ከባልንጀሮቹ ጋር ይወራረዳል። በውርርዱ መሰረትም ህጻኑ ጠዋት ሲነሳ ተከትሎት፤ የሚያደርገውን፣ የሚሰራውን፣ የሚሄድበትን፣ … ሁሉ እንደ እርሱ ሲከውን ዋለ። የማታ ማታ ግን መቋቋም ተስኖት እጅ ሰጠ።  እህሳ፤\nተፈጥሮ የራሷ ሚዛን አላት ብያችሁ አልነበር? ህጻኑ ለትንሿ አካሉ ፍጥነት ሲሰጠው ለትልቁ ሰው ደግሞ ትልቅ አካል ከኃይል ጋር እንጂ ከዚያን ያህል ፍጥነት ጋር አልነበረም። የተሰመረልንን ምህዋር የመከተል ያህል ትክክለኝነት ላይኖር አጉል መንፈራገጥ ዋጋ ቢስ መሆኑንም ያሳያል ገጠመኙ።  አበው\nሲተርቱ «…ነገርን በምሳሌ» ስለሚሉ ነው ምሳሌውን አስቀድሜ ነገሬን ማስከተሌ። ጉዳዬ ግን ከመታዘብ ነው፤ እኛኑ ከመታዘብ። አስተውላችሁ ከሆነ እኛ የአሁኖቹ፤ የምንነጋገርበትና የምንግባበት አጀንዳ ጠፍቶብናል። ውሏችን ከማህበራዊ ድረገጾች ጋር ነውና አንዱ «….» ብሎ ከመለጠፉ፤ ሌላው ተከትሎት«.. .. ..» በሚል ይለጥፋል (ያው መልስ መሆኑ ነው)።ከዚያማ\nእኔ፣ አንተ፣ አንቺ፣ ሁላችን፤ ነገሩን ነገራችን አድርገነው ቁጭ ነው። አንድና ሁለት ሳምንት ሙሉ አንዲቷን ጉዳይ ላይ ሰፍረን፤ ስንተማማ፣ ስንካሰስ፣ ስንሰዳደብና ስንጣላ እንቆያለን። በዚያኛው ሳምንት ደግሞ አንዲት ነገር ኮሽ ትልልናለች፤ እርሷንም ጉዳያችን አድርገን ወደ ጭቅጭቃችን እንገባለን።ማሳያ\nአንሺ የሚለኝ ካለ ልቀጥል። አቶ እከሌ የተባሉ ባለስልጣን፣ ምሁር፣ ከበርቴ፣ የጥበብ ሰው፣… (ያሻችሁን በሉት) የሸሚዛቸውን ቁልፍ አዛንፈው በመገናኛ ብዙሃን ቀረቡ እንበል። የእኛ ምላሽ ታዲያ የሸሚዝ ቁልፍን ከማዛነፍ ታሪካዊ አመጣጥ አቶ እከሌ ሊያዛነፉ እስከ ቻሉበት ሁኔታ መዘርዘርን ያካትታል (አሁን ይሄን ምን ይሉታል?)። ብዙ\nተከታዮች ያሉት ሌላ ሰው ደግሞ «እከሌ የተባሉት የ… ባለስልጣን መንገድ ሲሄዱ ተደናቅፈው ወደቁ» ብሎ የጭቅጭቅ መነሻ ይጠናል። እኛም የጫማውን ዓይነት፣ የመንገዱ ምቾት፣ የጫማቸው መስፋት፣ የጫማ ክራቸው መፈታት፣ የአካሄዳቸው መንሻፈፍ፣ … የማያልቅ ትንታኔያችንን ስላላየነው ጉዳይ እንሰጣለን።  አሁን አሁንማ የ«እንሞካከር» የትግል አውድማችን ፌስ ቡክ ሆኗል። ያም የመሰለውን ያነሳል ሌላውም የጣመውን ያንጸባርቃል (ለሚቃረኑትም ስድብ ይደርሰዋል)። ሃሳብን በግልጽ ማንጸባረቅ ስህተት ባይሆንም ቅሉ ስራ ፈትቶ በተራ ሃሳብና ንፋስ አመጣሽ ወሬ ላይ መራኮት ግን ከእኛ አይጠበቅም። የሚገርመው\nደግሞ እኛ በምንራኮትበት ሃሳብ ላይ፤ ባለስልጣናቱ፣ ምሁራኑ፣ የምናከብራቸው ታላላቅ ሰዎችም ምላሽ መስጠታቸው ነው (አሁንማ ተቋማቱም ለግለሰቦች ምላሽ መስጠት ጀምረዋል)። እነርሱን ተከትለን ደግሞ እኛ ሌሎች ገባሮቻችንን ፈጥረን ለሁለት ሳምንት እንከራከርበታለን።  ሃቀኛ\nስራ የሚሰራ ሰው «ሌሎች እንዲህ አሉኝ» ብሎ ለምን መልስ ሊሰጥ ይፈጥናል? አንዳንዶች ይህንን ዓይነት አጀንዳ የሚፈጥሩት አንድም ከሩጫ ገታ ሊያደርጓቸው አንድም የመተቸት አባዜ ተጠናውቷቸው ነው። የተለመደም ቢሆን አንድ አባባል አለ፤ «ውሾቹ ይጮሃሉ፤ ግመሎቹም ይጓዛሉ» የሚለውን መከተል ተገቢ ይመስለኛል።  ከላይ\nእንዳነሳሁት ታሪክ ከዚህ ጋር ይሄዳል፤ በደረጃችንና መሆን ባለብን ልክ መሆን ሳንችል መልሶ ራሳችንን መጉዳቱ አይቀሬ ነው (ትልቅ ሰው እንዴት ከህጻን ጋር ይፎካከራል?)። ሁሉም የሚለካበት የራሱ ሚዛን አለው ብለንም አልነበር?ሆኖልን\nስለ ሚጠቅመን ነገር ብናወራ እሰየው፤ አብዛኛው ግን ጉንጭ አልፊና መቋጫ የሌላቸው አሉባልታዎች ናቸው። ሚዛን የማይደፋ አንድ ጉዳይ ላይ ጊዜያችንን መግደላችንም ዘመናችንን አይመጥንም።ምክንያቱም\nህይወቱን ከድህነት ያላላቀቀ ህዝብ አጀንዳ አጥቶ በትርፍ ጉዳዮች መራኮቱ ግራ አጋቢ ነዋ። ኑሯችንና ኢኮኖሚው፣ የጤና እና የትምህርት ጉዳይ፣  የወጣቱና ታዳጊዎች\nስነ-ምግባር፣ በእጅጉ እየተስፋፋ የሚገኘው የመጤ ባህል፣ … ማለቂያ የሌላቸው በርካታ ጉዳዮች አጀንዳችን ሊሆኑ አይችሉም ነበር?«ስራ\nከምፈታ ልጄን ላፋታ» እንደሚለው ተረቱ ስራ ሲፈቱ «ምን ብለን ህዝቡን እናወዛግብ?» በሚል የቤት ስራ የሚሰጡን እኮ በርካቶች ናቸው። በዚሁ ከቀጠልን እነሱ ሲነዱን እኛ ስንነዳ ተያይዘን ገደል መግባታችን ነው። ከሁሉ\nይልቅ እኔን የሚገርመኝ ግን፤ መቼ እንዲህ እንደሆንን ነው። ከማህበራዊ ገጾች ጋርስ ውል ያሰርነው መቼ ነው? የመገናኛ ብዙሃን ዘገባዎችን ቢያዘጋጁ በፌስቡክ የሚሰራጩትን የወሬ ጫፎች ይዘው፣ ባለስልጣናቱ መግለጫ ቢያዘጋጁ «በፌስቡክ ምን ተባልኩ?» ብለው፣ እኛ ብንወያይ አሊያም ብንከራከር ፌስ ቡክ ላይ ከተባለው ተነስተን፣…። መነሻና መድረሻችን ከዚህ አቅጣጫ መሆን ከጀመርን ስንት ጊዜ ሆነን?    አልታወቀንም\nእንጂ የአጀንዳ ያለህ እያልን እኮ ነው። ወገን ጉዳያችን በምን ሚዛን ይለካል፤ ተግባራችንስ? አድራጎታችን ከሚዛን ሲቀመጥ ከሁሉ የቀለለ እንዳይሆን ማሰብና መጠንቀቅ እኮ አለብን። አጀንዳችንን በእጃችን ከምናሽከረክራት ትንሿ ስልካችን ላይ ከማድረግ ወደ ሚጠቅመን ነገር ብናዞረው አይሻልም?አዲስ\nዘመን የካቲት 18/2011ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "93eef5a8efcf4ad8027f3605739ec870" }, { "passage": "በአንድ ወቅት ከወደሀገረ አሜሪካ የተሰማው ታሪክ ልብን በሀሴት የሚሞላ ነው። ወጣቱ በችግር ምክንያት ከቤቱ ርቆ እየተጓዘ ሳለ አንድ መንደር ይደርሳል። እጅጉን ከመድከሙ የተነሳ አንድ ቤት አንኳኩቶ ጉሮሮውን የሚያረጥብበት ውሃ እንዲሰጡትም ይጠይቃል። በሩን ከፍተው ያናገሩት አዛውንት እናት ግን በልጁ መድከም እና የፊት መገርጣት የተነሳ አዝነው በጠየቀው ውሃ ምትክ በትልቅ ኩባያ ትኩስ ወተት ያቀርቡለታል። በሴትየዋ መልካምነት የተደነቀው ወጣትም የፊታቸውን ገጽታ እየተመለከተ ከልቡ አመስግኖ ይለያቸዋል። ከዓመታት በኋላ\nሴትየዋ በጠና ታመው ሆስፒታል ይወሰዳሉ፤ ለህክምና የሚሆናቸው ገንዘብ ግን አልነበራቸውም፤ ወደሆስፒታል ሲገቡ ግን አንድ ሀኪም\nይመለከታቸዋል። ሀኪሙም አስታወሳቸው፤ ወዲያውም በእርሱ አማካኝነት ሙሉ ወጪያቸው ተሸፍኖ እንዲታከሙ ያደርጋል። ታካሚዋ ሀኪሙን\nባያስታውሱትም እርሱ ግን ፈጽሞ ሊረሳቸው የማይችል፤ በችግሩ ጊዜ ወተት ያቀረቡለት መልካም ሴት ናቸውና በጉብዝናው ወራት አስታውሶ\nውለታውን እጥፍ እድርጎ ከፈለ። በኋላም እናት በጎነታቸው መልሶ እንደሚከፍላቸው አስበው እንዳላደረጉት ተናግረው ህይወታቸውን ያዳነውን\nሀኪም አመሰገኑ። በጎነታቸው\nመልሶ የሚከፍላቸው በርካቶች ቢሆኑም፤ በጎነት መልሶ ባይከፍል እንኳን መልካም ማድረግ ደግሞ ተመራጭ መሆኑን ደራሲና ጋዜጠኛው ክቡር\nዶክተር ከበደ ሚካኤል “ፅድቅና ኩነኔ ቢኖርም ባይኖርም፤ ከክፋት ደግነት ሳይሻል አይቀርም “ ብሎ ገልጾታል። ይህን ሁሉ ማለታችን\nያለምክንያት አይደለም። ትላንት በፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አዳራሽ <<በጎነት ለአብሮነት>> በተሰኘ መድረክ\nላይ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ የተሰማሩ ሰዎች በኢትዮጵያ ዘላቂነት ያለው አገልግሎት እንዲኖር የሚያግዙ ምክረ ሃሳቦችን በተመለከተ\nካነሷቸው ነጥቦች ጥቂት ለማካፈል ነው።የጋሞ እና\nኦሮሚያ የወጣቶች ህዝብ ለህዝብ ግንኙነት አስተባባሪ ኮሚቴ አቶ አብርሃም ይርዳ እንደሚናገረው፤ በኢትዮጵያ የቆየ የበጎፈቃድ አገልግሎት\nልምድ አለ። በኮርያም ሆነ በኮንጎ የዘመቱ አባቶች ደግሞ የዚህ ተግባር ምሳሌ ናቸው። በጋሞ ህዝብ ዘንድም አያቶችና ቅደመአያቶች\nየተገበሩት የመተጋገዝ ልምድ አለ። በጋሞ <<ዲሪ>> የሚባሉ 44 የአካባቢው አስተዳደር ህግጋት አሉ። ዲሪዎቹ\nበደቦ ሥራ፣ በሠርግ እና ኀዘን፣ ከብት ማገድ እና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ እንዴት በጎፈቃደኝነትን ተጠቅሞ መተጋገዝ ይቻላል የሚለው\nተግባራዊ ይደረጋል። ይህ ልምድ ተጠናክሮ ነው የጋሞ አባቶች እርጥብ ሳር ይዘው ለሰላም በመቆማቸው የተወደሱት፤ ይህ ሁሉ ተግባር\nግን በበጎፈቃድ እና በእርስ በርስ አነሳሽነት የሚካሄድ ባህላዊ መዋቅር ነው። እንደ አቶ አብርሃም ከሆነ፤ እንደጋሞው ሁሉ በሀገር ደረጃ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ወጣት ማስተባበር ከተቻለ ሰፊ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ተግባራትን በልማት እና ሰላም ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ማድረግ ይቻላል። በጎፈቃደኞችን የሚያስተባብሩ አካላት በቅንጅት ሀገራዊ ሥራ እንዲከውኑ ተቋማዊ አሠራር ያስፈልጋል። ማንም ሰው ተነስቶ በጎ ማድረግ ቢችልም ከአንድ ብርቱ እንዲሉ ነውና በጎፈቃድ ተግባራት በተደራጀ እና ዘላቂነት ባለው መልኩ ሲከወን ውጤታማነቱም ይጨምራል። የሰርዶ በጎ ፈቃድ ማህበር መስራች አቶ\nአክሊሉ ስመኝ በበኩላቸው፤ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ውስጥ ያለውን የበጎነት ስሜት አውጥቶ እንዲጠቀምበት መርዳት ያስፈልጋል። ወጣቶች ሊሰማሩበት\nየሚፈልጉት የበጎፈቃድ ፍላጎት ቢኖራቸውም እንዴት እና የት? የሚለውን መልስ ግን ሊመልስ የሚገባ አሠራር ሊቀርብላቸው ይገባል።\nበተለይ በሁለተኛ ደረጃ እና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ወጣቶች በምን መልኩ በጎፈቃደኝነትን መተግበር ይችላሉ የሚል ስልጠና\nያስፈልጋቸዋል። በሀገር ደረጃ የበጎፈቃደኝነት ማኔጅመንት ስርዓት ማዘጋጀት ያስፈልጋል የሚሉት አቶ አክሊሉ፤ በተጨማሪነት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ፖሊሲ በማጽደግ መልካምነትን ተቋማዊ አድርጎ ማስቀጠል እንደሚያስፈልግ ይናገራሉ። በዚህም አማካኝነት ከሰብዓዊ ድጋፍ ባለፈ በልማት እና የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ላይ የሚተገበሩ የበጎፈቃደኝነት ልምዶችን ማጠናከር እንደሚገባ ያስረዳሉ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወጣቶችና በጎፈቃድ ማስተባበሪያ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ነፃነት ዳባ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እየተዳከመ ይገኛል። በክረምት የሚሠራው የበጎፈቃድ ተግባር በበጋ ወቅትም ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል። ለዚህም እንዲረዳ ቢሮው በየጊዜው የሚከናወኑ የበጎፈቃድ ሥራዎችን ለማስተባበር ውጥን ይዟል። በቀጣይም በፋሲካ ወቅት ጧሪ ያጡ ደካማ ሰዎችን 500 ቤቶችን ለማደስ እና አረጋውያንን በትንሳኤ በዓል ለማገዝ በጎፈቃደኞችን እያቀናጀ ይገኛል። በተመሳሳይ በደም ልገሳ እና የልማት ሥራዎች ላይ ወጣቶች ያላቸውን ውስጣዊ ፍላጎት አውጥተው ህብረተሰባቸውን ለመርዳት እንዲችሉ የተቀናጁ አሠራሮች ተግባራዊ እንዲሆኑ ጥረት ይደረጋል።አዲስ ዘመን ቅዳሜ የካቲት 21/2012ጌትነት ተስፋማርያም", "passage_id": "98b7f3c61893ddbdc34a59f210a53a4b" } ]
00d26359f62ba5cfd4e52e17efa83cb6
b3d84f41241974feeae15d9a25cca6a3
ስዕልን በሁለት እጅ
አለማችን ከሊዮናርዶ ዳቪንቺ እስከ ፓብሎ ፒካሶ ድንቅ ሰአሊያንን አፍርታለች። አሁንም በየሃገራቱ በተለያዩ የስነ ስዕል ዘርፎች የስዕል ጥበባቸውን ለዓለም የሚያሳዩ ዝነኛ አርቲስቶች አልጠፉም። ሃገራችንም ብትሆን ሰዓሊና ባለቅኔ ገብረ ክርስቶስ ደስታን ጨምሮ በርካታ አንጋፋና ወጣት የስነ ስዕል ጥበበኞችን አፍርታለች። ሰዓሊያን በተለያየ የስነ ስዕል ዘርፍ የየራሳቸውን የአሳሳል ዘይቤ በመከተል የስዕል ስራቸውን የሚሰሩ ቢሆንም፣ አብዛኞቹ ቀለም ነክረው በዘረጉት ሸራ ላይ የሚቀቡት በአንድ እጃቸው ብቻ ነው። ይሁንና አንዳንድ በተፈጥሮም ሆነ በአደጋ ሁለት እጃቸውን ያጡ ሰአሊያን በአንድ እጃቸው ብቻ ብሩሽ ወይም እርሳስ መጨበጥ ስለማይችሉ ስዕል ለመሳል ሁለቱንም እጆቻቸውን ይገለገላሉ። ኦዲቲ ሴንትራል ሰሞኑን ከወደ አሜሪካ ይዞት ብቅ ያለው መረጃ ደግሞ ሁለት ጤነኛ እጆችን በአንድ ጊዜ በመጠቀም ስዕል መሳል እንደሚቻል ያረጋግጣል። መክሊት ካልሆነና ከላይ ካልተሰጠ በቀር ስዕልን እንዲሁ በቀላሉ በአንድ እጅ እንኳን ለመሳል ያስቸግራል። በሁለት እጅ በአንድ ጊዜ ሲሆን ደግሞ ጭራሽ የማይታሰብ ይሆናል። ለአሜሪካዊው አማተር ሰአሊ ግን ይህ እጅግ የቀለለ ጉዳይ ነው ይላል የኦዲቲ ሴንትራል ዘገባ። እንደ ዘገባው፤ በአሜሪካ ዴትሮይት ግዛት ጠበቃና አማተር ሰአሊው ኮሊን ዳርክ የተለያዩ ቀለሞችን በመጠቀም ጠለቅ ያሉ የስዕል ጥበብ ስራዎችን በሁለት እጆቹ በአንድ ጊዜ የመስራት ችሎታው ረፍዶም ቢሆን፣ የብዙሃንን ትኩረት ለመሳብ በቅቷል። የ42 አመቱ ይህ ጎልማሳ ከታዋቂ የፊልም አክተሮችና ታዋቂ ሰዎች ጀምሮ የተለያዩ እንስሳትንና ተፈጥሮን የሚያሳዩ ስዕሎችን ጨምሮ ልዩ ልዩ የስዕል ስራዎችን ሁለቱን እጆቹን በአንድ ጊዜ በመጠቀም ለማሳል ብዙ አልከበደውም። ኮሊን ይህን በሁለት እጅ በአንድ ጊዜ የመሳል ጥበቡን ሚስጥር ለረጅም ጊዜ ደብቆ ካቆየው በኋላ በአነቃቂ ንግግር ተነሳስቶ የሚሰራቸውን ስዕሎች የሚያሳዩ ፎቶዎችና የቪዲዮ ክሊፖች በኢንስታግራም መልቀቅ ከጀመረ ወዲህ የብዙሃንን ትኩረት ለመሳብ ችሏል። ‹‹የተደረገልኝ ቀና ድጋፍ የስዕል ስራዎቼን ይበልጥ እንድሰራና ችሎታየን እንድጠቀምበት አነሳስቶኛል››ሲልም ተደምጧል። ‹‹በርግጥ የቀኝ እጄ ሲደክም ስዕል ለመስራት የግራ እጄን እጠቀማለሁም›› ብሏል። በአምስት አመቱ ስዕል መሳል የጀመረው ኮሊን ይህን ችሎታውን በመጠቀም በሆሊውድ ፊልም የሚታወቀውን የሃሪ ፖተር ገፀባህሪ፣ ሊዮናርዶ ዳቪንቺን፣ ኮቤ ብሪያንትንና ሩድ ባድረ የተሰኙ ዝነኞችን ከሰራቸው የስዕል ስራዎቹ ውስጥ ይጠቀሳሉ። በእንዲህ አይነቱ ስዕል የመሳል ጥበብ ኮሊን የመጀመሪያው ሰው እንዳልሆነ ዘገባው ገልጾ፣ከዚህ በፊትም ራጃሴና የተሰኘች ኔዘርላዳዊት በሁለት እጆቿ በአንድ ጊዜ ስዕል እንደምትሰራ መዘገቡን አስታውሷል። የስዕል ስራዎቿ በአንዳንድ ወገኖች የውሸት ናቸው በሚል የተፈረጁ ቢሆንም፣ይህን የሚያረጋግጥ ትክለኛ ማስረጃ ግን እስካሁን እንዳልተገኘ ዘገባው አመልክቷል። አዲስ ዘመን መጋቢት 15/ 2012 አስናቀ ፀጋዬ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=29017
[ { "passage": "ሥዕሉ ለበርካታ ዓመታት በኩሽና ውስጥ ከማብሰያ ምድጃ በላይ ግድግዳ ላይ ተንጠልጥሎ ቆይቷል።\n\nበእውቅ ጣሊያናዊ ሰዓሊ ተስሎ የነበረው እና ለረዥም ዓመታት ጠፍቶ የቆየው ይህ ሥዕል በአንዲት አዛውንት ፈረንሳዊት ሴት ኩሽና ውስጥ ከተገኘ በኋላ ሪከርድ በሆነ በ24 ሚሊዮን ዩሮ ዋጋ በጨረታ መሸጡ ይታወሳል። \n\nይህ የሥዕል ሥራ ከሁለት ወራት በፊት ነበር በሰሜናዊ ፈረንሳይ ነበር የተገኘው።\n\n24 ሚሊዮን ዩሮ ከፍሎ የገዛው አካል ማን እንደሆነ በአጫራቾቹ በይፋ ባይነገርም፤ የፈረንሳይ መገናኛ ብዙሃን ግን ሥዕሉን የገዙት የጣሊያን የጥንት የሥዕል ሥራዎችን በመሰበሰብ የሚታወቁ ነዋሪነታቸው በአሜሪካ የሆኑ ሁለት የቺሊ ዜጎች መሆናቸውን ዘግበዋል።\n\nየፈረንሳይ መንግሥት ይህን የሥዕል ሥራ መልሶ ከግለሰቦች እጅ ለመግዛት የሚያስፈልገውን ገንዘብ ምንጭ እስኪያገኝ ድረስ ለ30 ወራት ሥዕሉ ከሃገር እንዳይወጣ ወስኗል።\n\nሥዕሉ ለበርካታ ዓመታት በኩሽና ውስጥ ከማብሰያ ምድጃ በላይ ግድግዳ ላይ ተንጠልጥሎ ቆይቷል። አንድ የሥዕል ባለሙያ እና አጫራች ሥዕሉን ከተመለከተ በኋላ ባለቤቶቹ የሥዕሉን ዋጋ ለማስተመን ባለሙያዎችን እንዲያማክሩ ሲወተውት ነበር ተብሏል። \n\nባለቤቶቹ ግን ሥዕሉ እድሜ ጠገብ ሃይማኖታዊ ምልክት ያለው ሥዕል ከመሆን ባለፈ ብዙ ዋጋ ያለው የጥበብ ሥራ መስሎ አልታያቸውም። \n\nበሥዕሉ ላይ የተደረጉ ጥልቅ ምርምሮች ሥዕሉ የጣሊያናዊው ሰዓሊ ሶኒ ዲ ፔፖ መሆኑን አረጋግጠዋል። \n\nበጣሊያን ፍሎረንስ የተወለደው ሶኒ ዲ ፔፖ በ13ኛው ክፈለ ዘመን መጨረሻ ላይ እና በ14ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ የሥዕል ሥራዎችን ሰርቷል። \n\nይህ የጥበብ ሥራ በመጠን አነስተኛ ሲሆን 20 ሲ.ሜትር በ26 ሴንቲ ሜትር ያክላል። ሥዕሉ የአንድ የሥዕል ሥራ አካል ሲሆን የተቀሩት ሥዕሎች ሎንደን እና ኒው ዮርክ በሚገኙ የሥዕል ማሳያ ማዕከል ውስጥ ይገኛሉ። \n\n ", "passage_id": "4aca079f207bc1822c2167492e532096" }, { "passage": "የሰው ልጅ ኑሮ ዛሬን አሳልፎ ትላንት በማድረግ ጉጉትና፣ ትላንትን ሰንዶ አስቀምጦ ለነገ በማቆየት መጠመድ ውስጥ የተቋጠረ ይመስላል። ለዚህም ነው ወደኋላ ታሪክ እና ትዝታ ወደ ፊት ደግሞ ተስፋ በጉልህ የሚታዩት። በዚህ መልኩ የአዲስ አበባን ገጽታ በፎቶ አስቀርቶ የዛሬን ዐይን የሚገልጥ ለነገም ሰነድ የሚያስቀምጥ መድረክ ከኹለት ሳምንት ቀደም ብሎ በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ጊቢ ሲካሔድ ነበር።‹‹አዲስን እናንሳ›› (Capture Addis) የተሰኘው ይህ አውደ ርዕይ ከመከፈቱ ቀድሞ ማንኛውም ሰው ፎቶ በማንሳትና በመላክ እንዲሳተፍ ጥሩ ቀርቦ እድሉ ተከፍቷል። ይህንን ተከትሎ ከባለሙያው የተረፈውን ባለሞባይሉ፣ ባለሞባይሉ ያለፈውን ደግሞ ባለሞያው ይዘው ያቆዩትን፣ አቅርበው አዲስ አበባን በፎቶ የሚያስቃኝን አውደ ርዕይ እውን ሊያደርጉ ችለዋል። በማዘጋጃ ጊቢ በተካሔደው ይህ አውደ ርዕይ በቆየባቸው ቀናት ማምሻውን በተከናወኑ የውይይት መድረኮች ደግሞ አዲስ አበባ ከተለያዩ ጥበባት አንጻር ተቃኝታለች።\nአዲስ አበባ ለበርካታ የልብ ወለድ መጻሕፍት መቼት ሆና አገልግላለች። ታድያ ግን ሰፈሮቿ በስም ይጠሩ እንጂ መልካቸውና ገጽታቸው በጉልህ ተቀምጦ አይታይም። ይህን ያነሱት የሥነ ጽሑፍ መምህርና ሃያሲ መሠረት አበጀ፤ አንድ አንባቢ ቀድሞ ወደ ሐሳቡ የሚመጡ ልብ ወለድ መጻሕፍትን ጥራ ቢባል የአብዛኞቹ መቼት አዲስ አበባ ስለመሆኗ ይገልጻሉ።በዓሉ ግርማ፣ ዓለማየሁ ገላጋይ፣ ዘነበ ወላ፣ ስብሐት ገብረእግዚአብሔር፣ አውግቸው ተረፈ እና ሌሎችም ደራስያን በዚህ ይጠቀሳሉ። ‹‹የደራሲ ግብ አንባቢን በመንፈስ መንጠቅ ነው›› የሚሉት መሠረት፤ መጻሕፍት ተደራሲ ሊያውቀው ከሚችለው በታች መስጠት የለባቸውም ሲሉ ይከራከራሉ። እናም መቼትን በተመለከተ ያለውን አሳድጎ ማቅረብና ፈጠራን ማከል እንዲሁም ገለጻን መጨመር ያሻል ይላሉ።የመሠረት ሌላው ነጥብ፤ ደራስያን ገጸ ባህርያቱን ኳኩለውና አሳምረው፣ ተደራሲ የሚያወቃቸው ያህል እንዲሰማውና በዐይነ ሕሊናው እንዲስላቸው አድርገው ሳለ፣ ለመቼት ግን የዛን ያህል ሲጨነቁ አይታይም። እናም ለመቼት በተለይም ‹‹የት›› ለሚለው፣ ለስፍራው ትልቅ ዋጋ እየተሰጠ እንዳልሆነ ትዝብታቸውን ያስቀምጣሉ።\nየአዲስ አበባ የድህነት፣ የመከራና የሰቆቃ ገጾች እየታዩ የመሻሻሉ ተስፋስ ወዴት አለ ሲሉም ይጠይቃሉ፤ መሠረት። ይህንንም ያሉት ከመቼት አንጻር ብቻ ነው። ‹‹ድርሰት ኃልና ጉልበት ነው። አዲስ ነገር መጨመርና ማነቃቃት ላይ ልንጠቀምበት እንችላለን፤ በዛ መልኩ የሆነ የመቼት ምልከታ ሊኖር ይገባል።›› ብለዋል፤ የሥነ ጽሑፍ መምህርና ሃያሲ መሠረት አበጀ።\n‹‹ሙዚቃ ማህበረሰብን ለማቀራረብና አንድ ለማድረግ ያግዛል።›› ያለው አዲስ አበባን ከሙዚቃ ስፍራነት አንጻር የቃኛት ሙዚቀኛና ፒያኒስት ሳሙኤል ይርጋ ነው። ሙዚቃ በከተማ እድገት ውስጥ የራሱ የሆነ ማህበራዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ አለው ያለው ሳሙኤል፤ ይህም እንደ አገር የሚኖረውን አስተዋጽኦ ለማየት ይረዳል ባይ ነው።አዲስ አበባን በተመለከተ እስከ አሁን ሙዚቃ የነበረውን ድርሻ ለማየት የተደረገ ጥናት አለመኖሩን ሳሙኤል ያወሳል። ከተማዋ ለሙዚቃ፣ ሙዚቃው ደግሞ ለከተማዋ ያበረከቱት ነገር ባለመታወቁም፤ ሙዚቀኛውም ሆነ ከተማዋ ሳይናበቡ በየራሳቸው መስመር እንዲሔዱ አድርጓቸዋል።ይህም ሆኖ ታድያ አዲስ አበባ የሙዚቃ ከተማ እንደሚባሉት ሁሉ በዛ ደረጃ ልትጠራ ትችላለች። የተለያዩ ፌስቲቫሎች የሚከናወንባት መሆኗ፣ መገናኛ ብዙኀንን ጨምሮ ከሙዚቃ ጋር የተገናኙ ጉዳዮች ማረፊያም ስለሆነች ነው። በሌላ አገላለጽ አዲስ አበባ የሙዚቃ ማዕከል ነች፤ የሳሙኤል ምልከታ ነው።ነገር ግን ከሌሎች የሙዚቃ ከተሞች የምትለይበት ጉልህ መገለጫ አላት። ይህም ምንም ዓይነት የሙዚቃ ስልት ይዞ ለመጣ ሁሉ ክፍት የሆነችና ብቸኛዋ እድል ያለባት ከተማ ሆና መገኘቷ ነው። ከተለያዩ ከተሞች ሙዚቃን የሚሠሩ ሙዚቀኞች ሳይቀሩ አዲስ አበባ መጥተው ነው ተመልሰው ወደ መጡበት ከተማ ሥራቸውን ይዘው የሚያቀኑት። የሙዚቃ ገበያው በአዲስ አበባ ላይ ማዕከል አድርጓል።ነገር ግን በዛ ልክ አውድ አልተፈጠረባትም፤ ሳሙኤል ይርጋ የሚቆጭበት ነጥብ ነው። የሙዚቃ ስፍራዎች፣ ስቱድዮዎችና ቀን ቀን ሙዚቃ የሚቀርብባቸው መድረኮች የሏትም። ‹‹ሙዚቃውን ለማሳደግ የሚያግዝና ለዛ ታስቦ የተዘጋጀ ስፍራ አይገኝባትም።›› ይላል።በድምሩ ግን ለሙዚቃ ባልተሰጠ ትኩረት የተነሳ ሙዚቃውን ‹‹ዘርፍ›› ብሎ ለመጥራት አስቸጋሪ አድርጎታል። አዲስ አበባም ልታገኝ የሚገባውን ጥቅም ልታገኝ ያልቻለችው በዚህ ምክንያት መሆኑን ሳሙኤል ይገልጻል። ከገቢ አንጻር ሌሎች አገራት ጥቅሙን አይተው ምን ያህል ትኩረት እንደሰጡትና እንደተጠቀሙበት በማንሳት ለአዲስ አበባም በተመሳሳይ እንድትጠቀም፤ እንደ አገር ሙዚቃውንም እንድትጠቅም ከባለሙያዎች ጀምሮ ሁሉም የድርሻውን መወጣጥ አለበት ብሏል።\nበ‹‹አዲስን እናንሳ›› የፎቶ አውደ ርዕይ ክዋኔ ላይ ከቀናት በአንዱ የአዲስ አበባን ትዝታዎች ከኪነ ህንጻ (Architecture) ጋር የሚያያይዝ ውይይት ተደርጓል። በጉዳዩ ላይ ሐሳባቸውን ያጋሩት የኪነ ህንጻ ባለሙያ ማህደር ገብረመድኅን፤ ኪነ ህንጻ የትላንት ትዝታን የሚያቆይ፣ የዛሬን በራሱ መንገድ የሚቀርጽ፣ የነገም ትዝታ ላይ ተጽእኖ ማሳረፍ የሚችል ዐቢይ የኪነጥበብ ዘርፍ ነው ሲሉ ገልጸዋል።የኪነ ህንጻ ለውጥም ከማህበራዊና ፖለቲካዊ ፍልስፍና ጋር ይያያዛልአ አሉ። ፖለቲካዊ እንቅስቃሴውን በተመለከተ ክስተቶች እንዴት ነገሮችን እንዳይመለሱ አድርገው እንደሚቀይሩ ማህደር በማሳያ አስቀምጠዋል። ይህም ለምሳሌ ከ1966 ቀደም ብሎ ታቅዶ የነበረው የከተማ ፕላን ነው። በዚህም ከዓድዋ አደባባይ በቸርችል ጎዳና እስከ ፒያሳ ሊሠራ የታሰበ ሥራ ነበር። ነገር ግን በ1966 የፈነዳው አብዩት እቅዱን አስቀርቶት አካባቢው አሁን ያለውን ገጽ እንዲይዝ አድርጓል። ማህደርም ‹‹በአንድ አብዩት አርክቴክቸሩም ተቀይሯል፤ ትዝታችንንም አብሮ ቀይሮታል።›› ሲሉ ይገልጹታል።ማህበራዊ ኑሮም ተጽዕኖ እንደሚፈጥር ሳይጠቅሱ አላለፉም፤ ይህም በአዲስ አበባ በጉልህ ይታያል። ማህደር እዚህ ላይ በአሁኑ ጊዜ የአዲስ አበባ ኪነ ህንጻ መገለጫ እየሆነ ያለውን ኮንዶሚንየም ቤት ጠቅሰዋል። ኪነ ህንጻ የማህበረሰቡን አኗኗር ከግንዛቤ ያላስገባ ሲሆን ችግሮች እንደሚፈጠሩም ጠቅሰዋል።‹‹ኪነ ህንጻው ለምንፈልገው የኑሮ ሒደት ቦታ ካልሰጠ ማህበረሰቡ የራሱን እርምጃ ይወስድና ግንባታው የታሰበለትን ዓላማ ይቀይሩበታል።›› ይላሉ። እናም ኪነ ህንጻ ለተሠራለት ዓላማ ማገልገል እንዲችል ትውልድና አስተሳሰብን ማግኘት መቻል አለበት። ካልሆነ አገልግሎት ላይ አይውልም፤ የማህደር ገለጻ ነው።ታድያ በዚሁ አንድ ስጋታቸውን አጋርተዋል፤ ይህም ወደፊቱ እንደ ከተማ አዲስ አበባውያን የሚጋሩት ትዝታ ሊቀንስ ይችላል የሚል ነው። በቀደመው ጊዜ የተወሰነ ጋዜጣ፣ ከአንድ ያልዘለለ የቴሌቪዥን ጣቢያ እና ራድዮ እየሰማ የኖረና ያደገው የማህበረሰብ ክፍል፣ የኑሮ ደረጃው ቢለያይ እንኳ ተመሳሳይ ትዝታን የመጋራት እድል ነበረው። አሁን ግን ዲጂታል ቴክኖሎጂ ብዙ አማራጭ በሰጠበት ወቅት ይህ ነገር እንደሚቀንስ ነው ያነሱት።\nአዲስ አበባን የሚወዱ፣ የሚሳሱላትና የሚኖሩባት እንዲሁም በተለያየ ሙያ ውስጥ ያሉ ሰዎች፤ ታዳሚ በሆኑበት በዚህ መድረክ፤ የሚሰጠው አስተያየትም ብዙና ሰፊ ነበር። በውይይት ሰዓት በኪነጥበቡ ዘርፍ ፊልም ለብቻው ከአዲስ አበባ ጋር በተገናኘ በውይይት ርዕስነት አልተጠቀሰም። ሆኖም አስተያየት ከሰጡ የተለያዩ ባለሙያዎች መካከል የመቅረጸ ምስልን ነገር ከአዲስ አበባ ጋር አቆራኝተው ያነሱ አልጠፉም።የፊልም ባለሙያው ሰውመሆን ይስማው (ሶሚክ) አዲስ አባባ ለፊልም ሥራ ምን ያህል አስቸጋሪና ከባድ እንደሆነች ጠቅሷል። አሁን ላይ ይሄ ነው የሚባል የራሷ የሆነ ቀለም የሌላት በመሆኑም የፊልም ባለሙያዎች በመቼት ደረጃ የአሁኗን ሳይሆን የቀደመችውን አዲስ አበባን ከምናብ ጓዳ ፈልፍሎ አውጥቶ በካሜራ ዐይን ማሳየትን ለመምረጥ ይገደዳሉ/ እንገደዳለን ይላል።አንዳች ባህሪ ያለው የከተማ ቀለም፣ አዲስ የሆነ እይታን ማውጣት ይስበኛል የሚለው ሰውመሆን፣ አዲስ አበባ ላይ ያተኮሩ ሥራዎችን ብዙ እንዳላዘጋጀ ይጠቅሳል። ካሜራውን ዝግጁ አድርጎ ለቀረጻ ሲነሳና ‹‹ምን የተለየ ነገር አለ?›› ብሎ ሲጠይቅ፤ አዲስ አበባ ለዚህ አጥጋቢ ምላሽ ሰጥታው እንደማታውቅና መልስ ማግኘት አዳጋች ሆኖበት እንደሚያውቅ ከልምዱ ያለውን ጠቅሷል። ‹‹ስለዚህ አዲስ አበባን በተመለከተ መጻፍ ካለብኝ 1960ዎቹ ነው የምለው። በዛ ዘመን ላይ ሊሆን የሚችለውን በምስል እያሰብኩ ነው የምሠራው።›› ሲል ያክላል።ከዚህ በተጨማሪ ለእይታ አዲስ ነገርን ያመጣሉ የተባሉ አካባቢዎችንና ህንጻዎችን ፈልጎ ማግኘትም አስቸጋሪ ነው። ለዚህም ነው በርከት ያሉ ፊልሞች ትዕይንቶቻቸው ከቤት ውስጥ የሚሆኑት። እንደ ሰው መሆን ገለጻ እንደውም ውጪው ተበላሽቷል፤ ለቀረጻ አስቸጋሪና ምቹ ያልሆነ ነው። ጉራማይሌ መሆኑም ለዚህ ዳርጎታል ባይ ነው።በተመሳሳይ የፊልም ባለሙያ የሆነችው መዓዛ ወርቁ ሐሳቧን ያካፈለችው ከአንድ ገጠመኟ በመነሳት ነው። አንዲት ኡጋንዳዊት ደራሲ አዲስ አበባ ተገኝታ ዙሪያ ገባውን ማየት ፈለገች፤ አንዳች አዲስ ነገር ለማየት በመጓጓት። መዓዛም አዲስ አበባን አስጎበኘቻት፤ ነገር ግን እንግዳዋ ኡጋንዳዊት አልተደነቀችም፤ አዲስ ነገር እንዳላየች ሆነች።\n‹‹ለእኔ አዲስ አበባ ትልቅ ከተማ ናት፤ ለምን አላየቻትም/አልታየቻትም ብዬ አሰብኩ።›› ትላለች መዓዛ። እናም ያቺ ኡጋንዳዊት እንድታይላት የምትፈልጋቸውን ስፍራዎች አሁን ላይ የፊልሞቿ መቼት አንድ አካል አድርጋ ታስቀራቸው ጀመረች። ‹‹በዚህ ትንሽ እርካታ ላገኝ እሞክራለሁ።›› ስትል በአስተያየቷ መካከል ተናግራለች።በተጓዳኝ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሚታዩ ፊልሞቸ ላይ አዲስ አበባን በምስል ሰንዶ የማስቀመጥ ሩጫ እንደሚታይ ነው የጠቀሰችው። የአዲስ አበባ መልክ እያደር እየተቀየረና እየተለወጠ ስለሚሔድ።\nየሥነ ጥበብ ባለሙያና በሥነ ጥበብ ተባባሪ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን ‹‹አዲስ አበባ፤ ምናብና ምስል›› በሚል ርዕስ መወያያ ሐሳብ አቅርበው ታዳሚን አነጋግረዋል። ባቀረቡት ሐሳብ ከሚታየው ይልቅ ስፍራን ለመረዳት የምናብን ጥንካሬ አንስተዋል። ለማሳያነት ከአዲስ አበባ ሰፈሮች መካከል የተወሰኑትን እያነጻጸሩ ጠቀሱ።\n‹‹ጨርቆስን በቦሌ ፊት ደረቷን ነፍታ እንድትቆም ያደረጋት ምናብ ነው›› የሚለው ካነሱት ማሳያ መካከል ነው። ለምን ሲባል ስለ ጨርቆስ የሚያነሱ ሰዎች ጨርቆስን በቁሟ (በሚታይ መልኳ) አያይዋትም። ይልቁንም በነዋሪዎቿና በውስጧ ባለ ሙቀትና የሕይወት መስተጋብር ነው የሚመለከቷት። ይህም ስፍራንና አካባቢን በቁሙ እንደማንፈርጅና ይልቁንም ምናብ የላቀውን ስፍራ እንደሚይዝ ያሳዩበት ነጥብ ነው።ይህ ታድያ በጎ ጎን አለውም ብለዋል። ‹‹ድህነታችንን ከወንጀል አርቆ ያቆየው ይህ ምናብ ይመስለኛል።›› ያሉት በቀለ፤ እነዚህ ምናቦች በማህበራዊ ጉዳይም ማህበረሰቡን አቻችለው ያቆዩ ናቸው ሲሉ ምልከታቸውን ገልጸዋል። ይህም ምናባዊነት የሚሰጠው ጠቀሜታ ሆኖ ሊመዘገብ ይችላል።\nበፎቶና በምስል ሲታይ ግን ስፍራን በቁም ማየት ግድ እንደሚል ያነሳሉ። ታድያ አካባቢን በመረዳት ምናባዊነት የጠቀመው ነገር መኖሩ እንዳለ ሆኖ፣ በአንጻሩ ግን ሊሞላ የሚገባ ክፍተት እንዳለና አካባቢን በቁሙ አይቶ ማሻሻል ላይም ትኩረት እንደሚያስፈልግ ጠቅሰዋል።\nከተከናወነ ከአንድ ሳምንት የዘለለው ይህን የፎቶ አውደ ርዕይ ስናነሳ አንዴ ታይቶ የሚጠፋ ክዋኔ እንደማይሆን በማመን የተነሱ ሐሳቦችም ለብዙዎች ቢደርሱ እይታን ሊያሰፉ ይችላሉ ከሚል እይታ አንጻር ነው። ታድያ የ‹‹አዲስን እናንሳ›› የፎቶ አውደ ርዕይ አዘጋጆች መካከል ሐሳቡን ለአዲስ ማለዳ ያካፈለው አክሊሉ ገብረመድኅን፤ በቀጣይም ይህ ክዋኔ እንደሚኖርና ዓመታዊ ሆኖ እንደሚቀጥል ገልጿል።በዚህ የመጀመሪያ በሆነው ክዋኔ ጥሩ ግብረ መልስ ማግኘታቸውን ያነሳው አክሊሉ፤ በቀጣይ ፎቶ ግራፍ በማንሳት የሚሳተፈውን ባለሙያ እና ባለሙያ ያልሆኑም ሆነው ፍላጎት ያላቸውን ተሳታፊዎች፣ የዳኞች ቁጥር ከፍ እንዲል እቅድ እንደተያዘ፤ እንዲሁም የተሰጠውን የወርክሾፕ ጊዜ ለማፋት እንደታሰበም ጠቅሷል።\nየአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር ለአውደ ርዕዩ ቦታ ከመስጠት ጀምሮ በተለያየ መንገድ ዝግጅቱን ደግፏል። ‹‹ቃል የተገባልን ነገር ተፈጽሞ አይተናል›› ያለው አክሊሉ በቀጣይም የከተማ መስተዳደሩ ድግፍ እንደሚኖር ተስፋ እንዳለ ጠቅሷል። በተያያዘም በዚህ ክዋኔ ላይ አስተዋጽኦ ማድረግና አዲስ አበባን ሰንዶ በማቆየትና በማክበር በኩል መሳተፍ ለሚፈልጉ ሁሉ በራችን ክፍት ነው ሲል ጥሪውን አስተላልፏል።ቅጽ 2 ቁጥር 54 ህዳር 6 2012", "passage_id": "796e9dfbc251d17196b9c47aacb12efc" }, { "passage": "ዳግም ከበደ ውበት እንደ ተመልካቹ ነው ይባላል ።አንዱ አካባቢ ለውበት የሚሰጠው ትርጓሜ ለሌላው አካባቢ ሊዋጥለት አይችልም ።አፍንጫ ስንደዶ፣ ጥርሰ በረዶ፣አይናማ፣ ስስ ከንፈር፣ ዞማ ጸጉር ብሎ ውበትን መግለጽ እንደማይቻል የዘመኑ የውበት ጠበብት ይገለጻሉ ።ምክንያቱም የአንዱን አካባቢ ከሌላው አካባቢ ውበት ለመለየት በአንድ መስፈርት ውስጥ ማስቀመጥ ፈጽሞ አይቻልምና ።ለዚህም ነው ውበት እንደ ተመልካቹ ነው የሚባለው፡፡ከመብላትና ከመጠጣት ባሻገር የሰው ልጅ እርካታን ከሚጎናጸፍባቸው መንገዶች አንዱ ውበት ነው ።በየትኛውም ባህል ውስጥ የሚኖሩ ህዝቦች ውበትን በተቀበሉት ልክ ይስማሙበታል ፤በተስማሙት ልክ ደግሞ ይደነቁበታል ።በመረጡትና በተሰማሙበት ልክም ቆንጆ ሆነው መታየትን ይፈልጋሉ ።አምረውና ተውበው ለመታየት ደግሞ ማህበረሰቡ ያመነበትን ወይም የተቀበላቸውን የመዋቢያ አይነቶች ይጠቀማሉ፡፡የዓለማችን የውበት ጠበብም ስለውበት ብዙ ብላለች፤ በየዕለቱ ቀላል የማይባል ገንዘብ ውበትን ለመጠበቂያ ታወጣለች ።በየወቅቱ ቆነጃጅቱን እያወዳደረች ትሸልማለች…ሌላም ሌላም ።ለመሆኑ ውበት ምንድን ነው? ውበት በምን መስፈርት ይለካል? በምን ቋንቋ ይገለጻል? ውበት ከሥነ-ምግባር ምን ዝምድና፤ ከሃብት ጋርስ ምን ግንኙነት አለው? ሥነ-ውበት (Aesthetics) የውበትን ጽንሰ ሃሳብ ምንነት፣ እሴቶች፣ አተያዮች እንዲሁም የመገምገሚያ መስፈርቶችን የሚያጠና ዐቢይ የፍልስፍና ዘርፍ ሲሆን የዛሬው ጸሁፌ ዋና ዓላማም ስለ ውበት አጭር ሐተታ ማቅረብ ይሆናል ።የሥነ-ውበት ፈላስፎች ውበት የሚለው ጽንሰ ሃሳብ በአጠቃላይ የሰው ልጅን፣ ኪነ-ህንጻን፣ ስዕልን፣ ሙዚቃን፣ ቅርጻ-ቅርጽን፣ ቲያትርን፣ ስነጽሁፍን፣ ፊልምንና የመሳሰሉትን የሰው ልጆች የጥበብ ስራዎች እንዲሁም የተፈጥሮን መስህቦች አካቶ የሚያጠና ዘርፍ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ውበት ማለት የአንድ ነገር የሚስብ፤ የሚያረካ ወይም የሚያስደስት ገጽታ ወይም ሁኔታ ማለት ነው። ውበት ውጫዊ ቅርጽን፣ ቀለምን፣ መጠንን፣ መልክን ወይም ደምግባትን አልያም ውስጣዊ ማንነትንና ሥነ-ምግባርንየሚመለከት ጉዳይ ሊሆን ይችላል ።ነገር ግን አስቸጋሪው ጥያቄ ማንን የሚስብ፣ ማንን የሚያስደስት ወይም የሚያረካ ነው የሚለው ነው – የውበቱን ባለቤት? ማህበረሰቡን? ማንን? የሚለውን ማለት ነው፡፡የዓለማችን ሊቃውንት እነዚህን መሰረታዊ የሥነ-ውበት ጥያቄዎች ለመመለስ በሁለት ታላላቅ ጎራ ተሰልፈው ለበርካታ ዘመናት ተሟግተዋል፤ መጻህፍትን ጽፈዋል፤ የሰው ልጆችን የአስተሳሰብ አድማስም አስፍተዋል። በመጀመሪያ የምናገኘው የሁሉን አቀፎች ወይም የፍጹማውያኑን ርዕዮተ ዓለም ነው፤ ይህም ውበት መለካት ያለበት ነገሮቹ በራሳቸው ባላቸው ማንነት እንጂ ከእነርሱ ውጪ በሚገኝ ማንኛውም ነገር ላይ ማለትም በማህበረሰቡ ወግ፣ አመለካከት ወይም እምነት ላይ ተመስርቶ መሆን የለበትም የሚል አቋም የሚያራምድ ነው፡፡በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በታተመ «ባህል ወቱሪዝም» የተሰኘ መጽሔት ላይ «ሴቶችና የውበት ማድመቂያቸው ድሮና ዘንድሮ» በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሑፍ ስለቁንጅና እንዲህ ይላል….«ለቁንጅና በዓለም ላይ ያልተደረገና ያልተሞከረ ጥረት የለም። የፈረንሳይ ንግስት ኢውጀኒ ገላዋን በታጠበች ቁጥር ለሰውነቷ ቆዳ ማሳመሪያና ማለስለሻ አንድ ቅርጫት ኢንጆሪ ያስፈልጋት ነበር። ቤድፎርድ የተባለች የሆላንድ ወይዘሮ ደግሞ ገላዋን ስትታጠብ አንድ ደርዘን ጠርሙስ ወተት አዘጋጅታ ከውሃ ጋር በመቀየጥ ለሰውነቷ የተለየ ውበት ለመስጠት ትጥር እንደነበር ይነገርላታል።»ሁሉም የሰው ልጅ ለውበቱ የሚጨነቅ ቢሆንም ሴቶች የበለጠ ለውበታቸው ስሱ ናቸው። በአንጻሩ ደግሞ ወንዶች በሴቷ ፊት የሚታይ ጀግንነታቸው ብቻውን ውበታቸው እንደሆነ ተደርጎ ሲቆጠር እናያለን። በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ በጦር ጀግንነት ፊትአውራሪዎች በበዙባት አገር። ሥነጽሑፋዊ ሥራዎቻችንም የወንዶችን ሳይሆን የሴቶችን ውበት ነው በብዛት አድምቀውና አድነቀው የሚጽፉት። ቆንጆ መባልና ውብ ሆኖ መታየት ለራስ ያለን ግምት ከፍ ለማድረግ ይረዳል። በራስ መተማመን ይጨምራል። በሌሎች ዐይን ውስጥ ውብ ሆኖ መታየት ደስ ይላል። ለዚህ ታዲያ የውበት መጠበቂያና መዋቢያዎችን መጠቀም በየትኛውም ማህበረሰብ ዘንድ የተለመደና ማህበረሰቡ የሚቀበለው እውነታ ነው። ይህን ያህል ስለውበት\nለመንደርደሪያነት ከጠቃቀስን ወደ\nስለ አፋር ወንዶች\nየጸጉር አሰራር በጥቂቱ\nላስቃኛችሁ፡፡የአፋር ወንዶች ከሴቶቹ\nይልቅ ለውበታቸው ይጨናቃሉ\n።መጨነቅም ብቻ ሳይሆን\nብዙ ጊዜያቸውን ለሸጉራቸው\nውበት ያጠፋሉ፡፡ ይኖርበታል። በየጊዜው ንጽኅናውን መጠበቅና ቅባት መቀባትም ይጠበቃል፡፡ጸጉሩ በሚፈለገው መጠን እንዲያድግ ማድረግ ያለበት ሁሉ አድርጎ በቂነው ብሎ ሲያስብ ወደ መጠቅለሉ ይገባሉ፡፡ለመጠቅለያነት የሚጠቀሙበትን ደግሞ የሰሊጥ እንጨት ያዘጋጃሉ ።የአፋር ወጣትን ጸጉር ለመስራት ሌሎች ሁለት ሰዎች ያስፈልጉታል ።በሰሊጥ እንጨት ወይም በእስኪርቢቶ ቀፎ ለሁለት ይጠቀልሉለታል ።ከመጠቅለሉ በፊት ሞራ፣ና ቅቤ ወይም ቅባት ይቀባል፡፡ሞራው ነጭ እንደሆነ የሚያቆይ ሲሆን፣ ቶሎ እንዳይበታተንም ያደርገዋል፡፡ቅባቱ ከሌለ ቶሎ ይበላሻል ነጭ እንደሆነ አንድ ሳምንቴ ይቆያል ። መጨረሻ ላይም ሞራው ቀልጦ ይፈሳል፡፡ዲረካሞ በወጣቶች ዘንድ እጂግ የሚወደድ ሲሆን ጥሩ የውበት መግለጫም ነው ።ወጣትነት ካለፈ ይህን አይነት መዋቢያ ስለማይጠቀም ጸጉሩን ይቆረጣል፡፡ከ30 አመት በላይ የሆነው ወንድ በኮልኮሎ እንዲዋብ ማህበረሰቡ አይፈቅድለትም ።በኮልኮሎ ስለሚያምር የአፋር ኮረዶች በጣም ይወዱታል ። ኢትዮጵያውያን ወጣቶች አሁን ላይ ለፋሽን ልዩ ቦታ የሚሰጡ ናቸው። ይህን ጉዳይ ከዚህ ቀደም በእንግድነት የጋበዝናቸው ሜካፕ አርቲስት አትክልት፣ ዲዛይነር ዮርዳኖስ እንዲሁም ኢንተርናሽናል ሞዴል ፈቲያ ገልፀውልን ነበር። ባጠቃላይ ኢትዮጵያዊ (ሃበሻ) መዘነጥ፣ ውበቱን መጠበቅ፣ መልበስን የሚወድ ማህበረሰብ መሆኑን መረዳት እንችላለን።ቀደም ባሉት ጊዜያት ኢትዮጵያውያን በባህላቸውና ባላቸው የራሳቸው የፋሽን ስልት ተውቦ ለመታየት ይጥሩ ነበር። የአፋር ወንዶችን እንደ ምሳሌ ማንሳት ይቻላል። አሁን ላይ ደግሞ በተለየ መንገድ በማህበራዊ ድረ ገፅና በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ይህን ልምድ በማስፋት የፋሽን ኢንዱስትሪው እንዲያድግ እየሰሩ መሆኑን ምልክቶችን አይተናል። ኢትዮጵያውያን ለዓለም ልናስተዋውቀው የምንችለው ቋንቋ፣ ውበት አጠባበቅ፣ አለባበስ፣ አመጋገብና ሌሎች በርካታ ነገር እንዳለን ማሳየት ስንችል ነው። ይህን በፋሽን ኢንዱስትሪው አማካኝነት ለማስተዋወቅ ደግሞ ባለሙያዎቻቸን ተግተው ሊሰሩ ይገባል እያልን ሃሳባችንን እዚህ ላይ እንቋጫለን።የአፋር ኮበሌዎች በብዛት ከሚጠቀሙበት የጸጉር አሰራር መካከል ቀዳሚው “ አይዲ ዲሪካሞ” ይሰኛል በአማርኛ “ኮልኮሎ” ይባላል ።የአፋር ኮበሌ (ጎረምሳ) በኮልኮሌ ለመዋብ ጸጉሩን ንጹህ አድርጎ ማሳደግ \n", "passage_id": "29bd6412a07a6d27f4f059764652c54b" }, { "passage": " የዘንድሮው እንቁጣጣሽ በጣም አስደሳች ነበር። አበቦቼን ሁሉ ሰጥቼ ጨረስኩ። ጎረቤቶቻችን ብዙ ሽልንጎች፣ ከርኮች፣ ዲናሬዎች ሰጥተውኛል። የፍራንኩ ብዛት ቁጥሩን አሳሳተኝ። ያም ሆነ ይህ ብዙ ገንዘብ አግኝቻለሁ። ያሰብኩትን ሁሉ እንደምገዛ እርግጠኛ ሆንኩኝ። በድንቡሎ አራት ከገዛሁት ደስታ ከረሜላ አንዷን ከመጠቅለያዋ ፈትቼ እየመጠጥኩ እማዬን ሂሳብ እንድናደርግ ጠየቅኳት። «መለዮህንና ማሊያህን እሚገዛልህ አምስት ሽልንግ አለህ» አለችኝ። ተደሰትኩ። (ዳቦ ብላ ብለው እማማ ሸጊቱ ባያስቀምጡኝ ኖሮ ብዙ እሸቅል ነበር) እቤት ቁጭ ብዬ እማዬ ጠብሳ የሰጠችኝን ስጋ እየበላሁ የአንዳንዶቹ ጎረቤቶቻችን ሁኔታ ትውስ አለኝ። አንድ ዓይናው አባባ አጋፋሪ ዓይናቸውን አፍጥጠው አበባዎቹን አንድ በአንድ «ይሄ ማን መሆኑ ነው?» «እመቤታችን ከጌታችን ጋር ነች!» አልኳቸው። መለዮአቸውን ሲያወልቁት ጸሃይ አርፎበት የማያውቀው መላጣ አናታቸው ነጭ ሆኖ ያብለጨልጫል። «ይሄ ጌታችን መሆኑ ነው? ኧረ ልጅ ሳይሆን ትልቅ ሰው ነው እሚመስለው! አስተያየቱስ ቢሆን? ኤድያ! ይሄ አላማረኝም ይቀየርልኝ። ቅዱስ ሚካኤል ጎራዴውን መዞ ሳጥናኤልን ሲቀጣ የሚያሳየውን አበባ ሰጠኋቸው። «ምነው ሰይፉን ጎራዴ አስመሰልከው?» «ጎራዴና ሰይፍ አንድ አይደለም?» «ዝም በል! ጎራዴና ሰይፍ አንድ ነው ይለኛል? ‘ልጅ ለእናቷ ምጥ አስተማረች’ እሺ ይሁንልህ፣ ደግሞስ ሺ በክንፉ ሺ ባክናፉ የመላዕክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል አንድ ብቻውን በሳጥናኤል ላይ ዘምቶ ሳልከው? አይ የልጅ ነገር! እስኪ ሌላውን አሳየኝ።» የቅዱስ ገብርኤልን ስሰጣቸው አፍጥጠው ሲያዩት ዓይናቸው እንደዓሳ ዓይን ቅንድብ አልባ ሆነ። ትንሽ ፈገግ ብለው የምስራች ነጋሪው ኃያሉ ቅዱስ ገብርኤል ምነው በእሳት ላይ መራመዱን፣ በሚንተገተግ እቶን ላይ ማዝገሙን ገደፍከው?» ብለው ሁሉም ስዕሎች ላይ አቃቂር አውጥተው በገንቦ አበባ የተደረደረበትን ስዕል መረጡ። ራስጌያቸው ካስቀመጡ ዝርዝር ፍራንክ ከርክ አንስተው ሰጡኝ «እድግ በል ልጄ! የሰለሞንን ጥበብ፣ የማቱሳላን እድሜ፣ የኢዮብን ትዕግስት እርሱ አንድዬ ይስጥህ! እናትና አባትህን ጧሪና ቀባሪ ያድርግህ» ብለው መርቀውኝ «ያ አባትህ እንዴት አደረ?» «አንበሳው ሲያገሳ እርሱ ነው የነገረኝ።» «መናገር ጀመረ?\nለእርሱ ለአንድዬ ምን\nይሳነዋል?አይዞህ እየተሻለው ነው» ብለውኝ ወጣሁ። ለከርሞው ለአበባ አጋፋሪ አበባ እምሰጣቸው መጨረሻ ላይ ነው ብዬ እየዛትኩ ወደ ቤቴ ተመለስኩ። እቤቴ ስገባ የስጋ ጥብስ ሽታ አወደኝ። «ስጋ ከየት አመጣሽ?» «እድሜ ላንተ! አንተ ነህ የገዛህልን» «አበባ ሰጥቼ ባመጣሁት ፍራንክ?» «ታዲያ! እግዚአብሄር ውለታህን ይክፈልህ። በአምስት ሽልንግ ግማሽ መደብ ከማርገጃ ገዝቼ መጣሁ። አሁን ደግሞ ቡና አፈላና ቤታችን ዓመት በዓል ዓመት በዓል ይሸታል።» ኩራት ተሰማኝ። «ግን ከማሊያዬና መለዮዬ መግዣ ፍራንክ ላይ ወሰድሽ?» «በፍጹም! ከእርሱማ አልነካብህም።» ተደሰትኩ። ብር ከስሙኒን ሰጥታኝ ከጉልት ሄጄ መለዮዬን ከእነመነጽሩ እንድገዛ ጠየቅኳት። «ያታልሉሃል» ብላ እምቢ አለችኝ። በዚህ ስንጨቃጨቅ የክርስትና እናቴ እማማ ቦጋለች አንድ በዳንቴል የተሸፈነ ሳህን ይዘው ገቡና «ምንድነው?» ኮስተር ብለው ጠየቁኝ። ነገርኳቸው\n«ስጪው፣ ጓደኞቹ ውጪ አሉ ያጋዙታል» ሲሉ ፈጥኜ ወጥቼ እኔ ያሰብኳትን ባለመነጽሩን ባርኔጣ ያደረገውን ሲሳይ ጎቢጥን ጠራሁት። አንድ ዓይና መነጽሩን ዛሬ ቀይሮታል።«ና! ባለመነጽሩን ኮፍያህን ለእማዬ ግባና አሳያት!» «እሺ» አለና እየዘነጠ ከፊት ለፊቴ ተራመደ። እናቴን በዚያ ፈጣን ምላሱ አሳመናትና ብር ከስሙኒውን ተቀብለን ወደ ጉልት ሄድን። «የበግ ቆዳ ያለው?!» እየጮኸ ይለፈልፋል ነጋዴው። «የዶሮ ቆዳ ያለው!» አብረውት ይጮኻሉ የሰፈሩ ልጆች። ነጋዴው ጸጥ ብሏቸው ስራውን እየለፈፈ አለፈ። ከገበያ ስንመለስ የሰፈር ልጆች እኛ ቤት አበባየሆይ ይጨፍራሉ። አስናቀች በድርብ ጥርሷ እየሳቀች ከበሮ ትመታለች። መሰረት፣ ሰብለ፣ ፋንቲሽ፣ ጸሃይ፣ አሰገደች፣ ሃዋ፣… እያጨበጨቡ ይቀበሏታል። የካፊያው ጭቃ ከቤት ቤት ሲዞሩ ጫማቸው ላይ ክፈፍ ሰርቷል። ሸራ ጫማ፣ ኮንጎ ጫማ፣ ባዶ እግር ይታየኛል። የሃገር ባህል ልብስ፣ ሻማ፣ ሽንሽን ለብሰው ዘንጠዋል። እማዬ ስሙኒ ሰጠቻቸው። ከብረው ይቆዩን ከብረው በዓመት ወንድ ልጅ ወልደው ሰላሳ ጥጆች አስረው … ከብረው ይቆዩን ከብረው በመነፅሬ ሳያቸው አረንጓዴ ይመስላሉ። ጎረቤታችን እማማ በለጡ ቤት እየጨፈሩ ሲሄዱ እኔ ወደ ጓደኞቼ ሄድኩኝ። ቀጢሳው ፊኛ ይነፋል፣ ተረፈ ገልጆ ሆዱን እያባበሰ ስለበላው ምግብ ደስ እያለው ያወራል፣ ጎቢጥ መነጽሩን አስሬ እያስተካከለ ሲያድግ ስፖርተኛ እንደሚሆን ያወራል፣ ሴምላል ከረሜላውን ቆርጥሞ ያከፋፍለዋል፣ ሻቃ ስለሚገዛው ባለ ብር ኳስ ያወራል፣ ይጥና ትምህርት ቤት ሲጋባ ስለሚገዛቸው ደብተሮች፣ እርሳስና ላጲስ ላውራ እያለ ይወተውታል፣… … አለሚቱ አንጎሏ አበባዬን ተቀብለው ፍራንኬን ሳይሰጡኝ ብዙ አመላለሱኝ። እንደዋዛ ጎራ እያልኩ በሌላ ጉዳይ በበራቸው የማልፍ እየመሰልኩ ታየኋቸው። እርሳቸው ግን ከእነመፈጠሬም የረሱኝ መሰሉ። በመጨረሻም እኔም የማላውቃቸው፣ እነርሱም የማይሰጡን ሆነን እንደተፋጠጥን፣ እንቁጣጣሽ አለፈ። በማግስቱ በራቸው አጠገብ ከጓደኞቼ ጋር ስንጫወት ጠሩኝና ስሙኒ ሰጡኝ። ድካሜን ቋንቋ አልባ ውትወታዬን ሁሉ ረሳሁት። ለነገ «ሙቪ» መግቢያ ቼላ ኖረኛ!!! (ዘነበ ወላ፥ ልጅነት)አዲስ ዘመን መስከረም\n5/2012", "passage_id": "7a1582433eb029d6859854d300b9a4f9" }, { "passage": "የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር፣ እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ ያረፉት ከዛሬ ሰባት ዓመታት በፊት፣ በዚህ ሳምንት (ሚያዝያ 2 ቀን 2004 ዓ.ም) ነበር። እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ ከአባታቸው አቶ ተክሌ ማሞ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ጥቅምት 13/1925 ዓ.ም በቀድሞው ሸዋ\nጠቅላይ ግዛት፣ አንኮበር ከተማ ተወለዱ። ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በግፍ ስለወረረች፣ የልጅነት ትዝታቸውም ይሄው የግፍ ወረራ እና ጦርነት ያስከተለው የሰው፣ የንብረት እና የባህል ጥፋት ነበር። ከነፃነት በኋላም ዐቢይ ሥራቸው በወረራ የተበላሸችውን ሀገራቸውን እንደገና መገንባት ነበር። ለዚህም የሀገር ግንባታ አስፈላጊውን እውቀት መሸመት የፈለጉት በማዕድን ምሕንድስና ዘርፍ ነበር። ወላጆቻቸውና ዘመዶቻቸው ግን የኪነ-ጥበብ ስጦታቸውን በቤታቸውና በከተማው ዙሪያ በሚስሏቸው ስዕሎች ተገንዝበውት ነበር። ገና በአሥራ አምስት ዓመታቸው በ1940 ዓ.ም ለከፍተኛ ትምህርት ተመርጠው የምሕንድስና ትምህርታቸውን ለመከታተል ወደ እንግሊዝ አገር ተላኩ። በትምህርት ቤት ቆይታቸውም፣ የባዕድ ባህላት፣ የአየር ለውጥ እና የተለመደው የተማሪ ቤት ዝንጠላ ቢያስቸግራቸውም ትምህርታቸውን በትጋት ሲከታተሉ ቆይተው በተለይም በሒሣብ፣ በኬሚስትሪ እና በታሪክ ትምህርቶች ጥሩ ውጤት በማምጣት ሰለጠኑ። ነገር ግን አስተማሪዎቻቸው የተፈጥሮ ስጦ ታቸው ኪነ-ጥበብ እንደሆነ ለመገንዘብ ብዙም ጊዜ አልወሰደባቸውም። በእነርሱ አበረታችነትም በዚህ ስጦታቸው ላይ የበለጠ ለማተኮር ወስነው በለንደን (Central School of Arts & Crafts) ተመዝግበው መማር ጀመሩ። ከዚህ ትምህርት ቤት ትምህርታቸውን ሲያጠናቅቁም፣ ለከፍተኛ ጥናት ወደ ስመ ጥሩው የለንደን ዩኒቨርሲቲ የስሌድ ኪነ ጥበብ ትምህርት ቤት (Faculty of Fine Arts at Slade) የመጀመሪያው አፍሪቃዊ ተማሪ በመሆን ገቡ። በዚህ ትምህርት ቤት ውስጥም በስዕል፣ ቅርጽ እና በአርክቴክቸር ጥናቶች ላይ አተኩረው ተመረቁ። ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ፣ በየጠቅላይ ግዛቶቹ እየተዘዋወሩ (በየቦታው እስከ ሦስት ወራት በመቀመጥ) የኢትዮጵያን ታሪክና የብሔረሰቦቿን ባህልና ወግ ሲያጠኑ ቆዩ። ከውጭ ሲመለሱ የተመደበላቸውን ሚኒስቴራዊ ሥራ ትተው የኪነ-ጥበብ ሥራቸው ላይ በማተኮር ስዕሎቻቸውን በአገር ውስጥና በውጭ እያሳዩ ለማገልገል ቆረጡ። በሃያ ሁለት ዓመታቸውም በ1946 ዓ.ም ሥራቸውን የሚያሳይ የመጀመሪያውን የኪነ-ጥበብ ትርዒት በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት አቀረቡ። ወዲያውም ከዚህ ትርዒት ባገኙት ገቢ ተመልሰው ወደ አውሮፓ በመሄድ ለሁለት ዓመታት በኢጣልያ፣ በፈረንሳይ፣ በስፔን፣ በፖርቹጋል፣ በብሪታንያና በግሪክ የጠለቀ የኪነ- ጥበብ ጥናት አከናወኑ። በተለይም በነዚህ አገሮች ውስጥ በስደት የሚገኙትን የኢትዮጵያ ጥንታዊ ሃይማኖታዊ የብራና መጻሕፍት በጥልቅ አጠኑ። በተጨማሪም፣ የመስታወት ስዕል (Stained Glass Art) እና የሞዛይክ አሠራርን ጥበብ ተምረው ወደአገራቸው ተመለሱ። ከዚያም ንጉሠ ነገሥቱ የመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያንን በሃይማኖታዊ የግድግዳና የጣሪያ ስዕሎች፣ የሞዛይክ ሥራዎች፣ መስኮቶቹንም በመስታወት ስዕሎች እንዲያሳምሩት ነግረዋቸው አሁን የምናያቸውን እንደ “የዳግማዊ ምጽአት ፍርድ”፣ የእመቤታችንን ንግሰት የሚያሳየው “ኪዳነ ምሕረት”፣ እና የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን የዘውድ ሥርዓት የሚያሳዩ ሥራዎቻቸው ይገኙበታል። አከታትለውም አሁን በሐረር ከተማ የሚገኘውን የልዑል ራስ መኮንንን ሐውልት ሠሩ። የስዕል እና ሌሎች የኪነ ጥበብ ሥራዎቻቸውም በቴምብሮች፣ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር የኪነ ጥበባት ትርዒቶች ላይ እጅግ በጣም እየታወቁና እየገነኑ መጡ። እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ በውጭ አገር የተማሩ ቢሆኑም፣ እሳቸው ‹‹ዋጋ ቢስ›› የሚሉትን፣ እንደሌሎች (ምዕራባውያንም ሆኑ ሌሎች) የሚጠቀሙበትን ‹‹ኩረጃ›› ላለመከተል በትጋት ጥረዋል። ከአያሌ ድንቅ ሥራዎቻቸው መካከል አዲስ አበባ፣ በአፍሪቃ አዳራሽ መግቢያ የሚታየው በመቶ ሃምሳ ካሬ ሜትር ላይ የተሳለው ትልቅ የመስታወት ስዕል፣ በአዲስ አበባ በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሚገኙ ስዕሎች፣ በአዲስ አበባ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል የሚገኘው የመጀመሪያው የ‹‹ዳግመኛ ምጽዓት ፍርድ››\nስዕል፣ በሐረር የልዑል ራስ መኮንን ሐውልት፣ ‹‹እናት ኢትዮጵያ››፣ በለንደን ‹‹ታወር\nኦፍ ለንደን›› የቅዱስ ጊዮርጊስ ጸሎት ቤት ከብርና ከእንጨት የተሠራ የመንበር መስቀል እንዲሁም በሩሲያ፣ በአሜሪካ እና በሴኔጋል ትርዒቶች የታየው ‹‹የመስቀል አበባ›› ተጠቃሽ ናቸው። እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ ዓለም አቀፍ ዝናን ባስገኙላቸው ሥራዎቻቸው ምክንያት በርካታ ሽልማቶችን ያገኙ ሲሆን ለአብነት ያህል በ1958 ዓ.ም የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ የሽልማት ድርጅት ተሸላሚም ናቸው። በ1958 ዓ.ም በሩስያ ሞስኮ ታላቅ የስዕል ኤግዚቢሽን አሳዩ፤ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በመገኘት አስደናቂ ንግግሮችን አደረጉ። በ1959 ዓ.ም በአሜሪካ መንግሥት ግብዣ በዋሽንግተን እና ኒው ዮርክ ከተሞች የአንድ ሰው የስዕል አውደ ርዕይ ለሕዝብ አቀረቡ። በታወቁና ከ22 በላይ\nበሆኑ ዩኒቨርሲቲዎችና ተቋማት በመገኘት ንግግር አደረጉ፤ በ1964 ዓ.ም የሰው ልጆችን ወንድማማችነትና የሰላም ልዕልናን የሚመሰክረውን ሥራቸውን በተለያዩ አገሮች አቀረቡ። በዚህ ሥራቸው በ1971 ዓ.ም በአልጀርስ የጥበብ ፌስቲቫል የወርቅ ሽልማት ክብርን አገኙ። በፈረንሳይ አገር ባቀረቡት የሥዕል ሥራ የጃፓን፣ የፈረንሳይና የሜክሲኮ ተወዳዳሪዎችን በልጠው አንደኛ ወጥተው ከመሸለማቸውም በላይ፣ የቤናል የሎሬት ማዕረግን ክብር አገኙ። እ.ኤ.አ በ2000\nዓ.ም በዋሽንግተን ዲሲ በተጠራው 27ኛው የአሜሪካ ባዮግራፊካል ኢንስቲትዩት ዓለም አቀፍ ጉባዔ ላይ የዓለም ሎሬትነት ክብርን ተቀዳጁ። እ.ኤ.አ በ2004\nበአየርላንድ ደብሊን ላይ በተጠራው የሳይንስ፣ ባህልና ጥበብ ጉባኤ ለሰው ልጆች ትምህርትና ለጥበብ ዕድገት ለዓለም ባበረከቱት መልካም ተግባር ‹‹የዳቪንቺ አልማዝ ሽልማት››ን ሲቀበሉ፣ በዚሁ\nጉባኤ በአሜሪካ ዩናይትድ ካልቸራል ኮንቬንሽን (United Cultural Convention) የተባለው ተቋም ለዓለም ጥበብ ዕድገት ላበረከቱት መልካም ሥራ የጀግና ክብር ኒሻን ሸልሟቸዋል። እጅግ የተከበሩ\nየዓለም ሎሬት ሜትር\nአርቲስት አፈወርቅ ተክሌ\nባደረባቸው ጽኑ ሕመም\nበሕክምና እየተረዱ ሳለ፣\nማክሰኞ፣ ሚያዝያ 2 ቀን\n2004 ዓ.ም በተወለዱ በ79 ዓመታቸው\nበአዲስ አበባ ካዲስኮ\nሆስፒታል አርፈዋል። የቀብር\nሥርዓታቸውም በመንበረ ጸባኦት\nቅድስት ሥላሴ ካቴድራል\nተፈጽሟል፡፡አዲስ ዘመን ሚያዝያ 4/2011በ", "passage_id": "d3ed571714dd4f25605cbea791ac18cf" } ]
7896cf55f1fedc0bd71063c4e7058eb6
1e4b5bcfc4318fb181c6d1baef25bc3a
ለአፍሪካ አገራትም ተምሳሌት የሆነው የኢትዮጵያ ስፖርት
ብርሃን ፈይሳየአፍሪካ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማህበር (አኖካ) የዘንድሮ መዳረሻውን ኢትዮጵያን ማድረጉ ይታወቃል፡፡ በኮሚቴው ምስረታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በነበራትና የአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ ከትናንት በስቲያ ጠቅላላ ጉባኤውን ከማካሄዱም ባሻገር ለኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድም በአህጉሩ ከፍተኛ የሆነውን የስፖርት የክብር ሽልማት አበርክቷል፡፡ ኮሚቴውና አባላቱ አጠቃላይ የነበራቸውን ቆይታ በተመለከተም የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ስፖርት ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር ለአዲስ ዘመን አብራርተዋል፡፡በመሪዎች ደረጃ ይህንን ሽልማት ያገኙ ጥቂት መሆናቸውን ኮሚሽነሩ ጠቅሰው፤ ይህም ለኢትዮጵያ ስፖርትና ለስፖርቱ ቤተሰቡ ትልቅ የምስራች መሆኑንም ይጠቁማሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ለሽልማት ሊያበቋቸው የቻሉና አርአያ ሊያደርጓቸው የሚችሉ መነሻዎች መኖራቸውም ያብራራሉ፡፡ እንደ ኮሚሽነሩ ገለፃ፤ በሀገሪቷ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች አብዛኛዎቹ ከስፖርቱ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን የእንጦጦ ፓርክን በማሳያነት ማንሳት ይቻላል፡፡ አረንጓዴ ልማት ከስፖርት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንደመሆኑ በየዓመቱ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል ከዚህ ቀደም አስቸጋሪ የነበሩ አካባቢዎችን ማልማትም ሌላኛው መነሻ ነው፡፡ የጃፓን ኦሊምፒክ ኮሚቴ ዝግጅትን ተከትሎ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ባደረገው ውይይት ያገኘው ቀና ምላሽም ሌላው ምክንያት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ዝግጅቱን በተመለከተ ሁለት አቅጣጫዎችን ያስቀመጡ ሲሆን፤ የመጀመሪያው ዝግጅቱ ቀደም ብሎ እንዲጀመርና ውጤት እንዲመጣ ማመላከታቸው ነው፡፡ የተሻለ ውጤት የሚመዘገብ ከሆነም መንግሥት የሚሰጠውን ማበረታቻ በማስቀመጥ ተነሳሽነትን ሊፈጥሩ ችለዋል፡፡ ሁለተኛው አቅጣጫ ደግሞ ለአንድ ኦሊምፒክ ብቻም ሳይሆን ለቀጣይ ኦሊምፒኮችም መሰረት መጣል ስላለበት የኦሊምፒክ መንደር መገንባት አስፈላጊ ነው፡፡ በመሆኑም ሀብት ማሰባሰብ አስፈላጊ እንደመሆኑ፤ የራሳቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱ ቃል ገብተዋል፡፡ በሌላ በኩል በርካታ በየክልሉ የተጀመሩ የስፖርት መሰረተ ልማቶችና ግዙፍ ስታዲየሞች ተጠናቀው ሌሎች መጀመር አለባቸው የሚል አቅጣጫም አስቀምጠዋል፡፡ በመሆኑም ከስታዲየሞች ባሻገር የማሰልጠኛ ተቋማትም በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ በማስገባት ሁሉም አመራር ትኩረት እንዲሰጠው አድርገዋል፡፡ ለስልጠና፣ ለውድድርና ለሽልማት አስፈላጊው የገንዘብ ድጋፍ በመንግሥት እየተሰጠ በመሆኑ እንዲሁም ስፖርቱን የሚመሩት መንግሥታዊና ህዝባዊ አካላቱ በነፃነት ነገር ግን በመንግሥት መደገፍ ባለባቸው መልክ ማስኬድ መቻሉም ሌላኛው ምክንያት ነው፡፡ እነዚህ ጉዳዮችም ለስፖርቱ ትልቅ ትኩረት መስጠታቸውን የሚያሳይ መሆኑን በመመልከትም የአፍሪካ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ሽልማቱን ሊያበረክት ችሏል፡፡ ለረጅም ጊዜ ዝግጅት ሲደረግበት የቆየውና በአጠቃላይ በአዲስ አበባ የተካሄዱት የአኖካ መርሐ ግብሮች ለኢትዮጵያ ስፖርት ዕድገት እንዲሁም ለአገር ገጽታ ግንባታ አስተዋጽኦ ያላቸው መሆኑንም ኮሚሽነሩ ያመላክታሉ፡፡ ለቀናት ከአፍሪካና ከሌሎች አገራት የተገኙ የስፖርት አመራሮች ከጉባኤው ባሻገር፤ የኮሚቴው ሥራ አስፈፃሚ አባላት ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ እንዲሁም ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱም ወቅት ኢትዮጵያ በአህጉር አቀፍ ደረጃ ምን ሚና ነበራት ወደፊትስ የሚኖራት ሚና ምን ይመስላል በሚለው ላይ ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡ ሥራ አስፈፃሚውም ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ስፖርት ተምሳሌት መሆኗን እንዲሁም መንግሥት ለዘርፉ የሚሰጠው የጎላ ድርሻ፣ ህዝባዊና መንግሥታዊ አካሉ በቅንጅት ስፖርቱን የሚመራበት ሁኔታ እንዲሁም ለስፖርት የሚመድበው በጀት ለሌሎች አፍሪካዊያን አገራት ምሳሌ እንደሚሆን መግለፃቸውንም ኮሚሽነሩ አብራርተዋል፡፡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ጠቅላላ ጉባኤም ኢትዮጵያ የትኛውንም አህጉርም ሆነ ዓለም አቀፍ ጉባኤ የማስተናገድ አቅምና ብቃት ያላት ሀገር መሆኗን በግልጽ ያሳየ ነበር፡፡ ከዚህ ባሻገር በሀገሪቷ እየተከናወኑ ያሉ እንቅስቃሴዎችን በዘጋቢ ፊልምም ጭምር በማዘጋጀት ለማስረዳት ሙከራ መደረጉንም ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር ጠቁመዋል፡፡አዲስ ዘመን ህዳር 29/2012
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=36968
[ { "passage": "የዓለም\nታሪክ ሴቶችን በስፖርት ዓውድ መመዝገብ የጀመረው ዘግይቶ ነው ። በ19ኛው ክፍለ ዘመን ጥቂት ሴቶች በስፖርቱ ተሳትፎ ከማድረጋቸው በፊት ሴት ልጅ በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች የመሳተፍ አካላዊ ብቃት የላትም የሚል አመለካከት ነበር። በዚህ የተነሳም ሴቶችን ስፖርት ሜዳ ውስጥ መመልከት እንደ ነውር ይቆጠር ነበር። ይሁንና በጥቂቶች እንዲሁም የተሻለ እሳቤ በነበራቸው ሰዎች ጥረት የሴቶች የስፖርት ተሳትፎ እውን ሆኖ ዛሬ ካለው ነባራዊ ሁኔታ መድረሱን ታሪክ ያወሳል። የኢትዮጵያ ልምድም ከሌላው ዓለም የተለየ አልነበረም። ሴት ልጅን ከጓዳ ብቻ ያዛመደውን ልማድ ለመቅረፍ በርካታ ዓመታት ተቆጥረዋል። ተሳትፎው በሂደት እየጎለበተም በሺዎች የሚቆጠሩ ሴቶች ስፖርቱን ቋሚ ሥራቸው በማድረግ ከራሳቸው አልፈው ለሌሎችም የሥራ ዕድል እስከ መፍጠር ደርሰዋል። ብቃታቸውም ቢሆን ከኢትዮጵያም ባለፈ በኦሊምፒክም ጭምር ባስመዘገቡት ድል ተመስክሮላቸዋል። በ1990ዓ.ም በወጣው የኢፌዴሪ ስፖርት ፖሊሲ ላይ «ሴቶች በስፖርት እንቅስቃሴ ቀጥተኛ ተሳታፊና በእኩል ደረጃ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ይደረጋል» በሚል ሰፍሯል። በዚህም\nመሰረት ከወንዶች እኩል በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችም ሆነ ሙያዊ ሥራዎች ላይ እንዲሳተፉ ተደርጓል። ይህ ብቻውን በቂ ባለመሆኑም በሴቶች እየተመራ ሴቶች ብቻ የሚፎካከሩበት መድረክም ተዘጋጅቶላቸዋል። ሴቶች በስፖርት ተሳታፊ በመሆናቸው በቅድሚያ ጤናቸውን ለመጠበቅ፣ የአካል ብቃታቸውን ለማዳበር እንዲሁም ተፈጥሯአዊና ሰው ሰራሽ ችግሮችን ለመቋቋም ያስችላቸዋል። ከዚህ ባ ሻገር በራስ የመተማመን ብቃታቸውእንዲያድግ፣ በስፖርት ምክንያት እርስ በርስ ያላቸው ግንኙነት እንዲዳብር እና የስፖርት ስነ- ምግባርንና ባህልን እንዲያውቁ የሚረዳቸው መሆኑን በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ናስር ለገሰ ይገልጻሉ። በዚህም\nከ2007ዓ.ም ጀምሮ «የመላ ኢትዮጵያ ሴቶች ጨዋታ» በሚል በየሁለት ዓመቱ ውድድር ይካሄዳል። ውድድሩ ክልሎች የየራሳቸውን የውስጥ ውድድር ካጠናቀቁ በኋላ በአገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄድ ነው። የመጀ መሪያው ውድድር በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር አስተናጋጅነት ሲካሄድ፤ ሁለተኛው ደግሞ በሃረር ከተማ ተደርጓል። ሦስተኛው የመላ ኢትዮጵያ ሴቶች ጨዋታም ትናንት በጅግጅጋ ከተማ አስተናጋጅነት መካሄዱን ጀምሯል። ውድድሩ\nበሌሎች ውድድሮች የመሳተፍ ዕድል ያላገኙ ሴት ስፖርተኞች አጋጣሚውን እንዲጠቀሙበት እንዲሁም በመምራት በኩል ያላቸውን የራስ መተማመንም እንዲያሳዩ ይረዳቸዋል። የተሻሉና አገራቸውን መወከል የሚችሉ ስፖርተኞችን ማፍራት የሚቻልበት ነው። የመገናኛ ብዙሃንን ሽፋን ማግኘታቸውም ውጤታማ ስፖርተኞች የሚበረታቱበት እንዲሁም ለክለቦችና ብሄራዊ ቡድኖች የሚታጩበት ዕድልም ያስገኝላቸዋል። ከዚህ ባሻገር ጥቂት ሴት የስፖርት ባለሙያዎች ከአገርም አልፈው በዓለም አቀፍ ደረጃም በመስራት ላይ እንደሚገኙ የሚጠቅሱት ዳይሬክተሩ፤ ከመሰረቱ መስራት ከተቻለ የተሻለ ተሳትፎ እንደሚኖርም ይጠቁማሉ። ነገር\nግን በርካታ ሴት ባለሙያዎች በሌሉ ባቸው ስፖርቶች ላይ ወንዶች እንዲገቡ የተደረገ ሲሆን፤ በሂደት ሴቶችን በማብቃት ወንዶቹ እንደሚቀነሱም አቶ ናስር ይጠቁማሉ። በመጀመሪያው ውድድር የነበረው የባለሙያዎች ተሳትፎ አናሳ ቢሆንም፤ በሁለተኛው ግን የተሻለ ቁጥር ለመመልከትም ተችሏል። በየውድድሩ መሻሻል እየታየ ሲሆን፤ ይህም በተለያዩ መንገዶች ይረጋገጣል። በክልሎች በኩል የእኔነት ስሜት በማሳደር ላይ እንደሚገኝ ክልሎች ከሚሰጡት ግብረ መልስ ለመረዳትም ይቻላል። ከባለሙያዎች ባሻገር ውድድሩ በየዓመቱ የተሳታፊዎቹን ቁጥር እንዲሁም ውድድር የሚካሄድባቸውን ስፖርቶች እያሳደገ ሲሆን፤ የባህል ስፖርት እንዲሁም መስማት የተሳናቸው በውድድሩ ተሳታፊ እንዲሆኑም ተደርጓል። የተሳታፊዎች ብዛትም እየጨመረ ይገኛል። በመጀመሪያው\n500 ስፖርተኞች ተካፋይ ቢሆኑም በሁለተኛው 700መድረስ ችለዋል። አሁን ደግሞ ከ 2ሺ በላይ ሴት ስፖርተኞች ተሳታፊ ሆነዋል። ሴቶች በስፖርቱ ያላቸው ተሳታፊነት ሲጎለብትም በማህበራዊ ህይወታቸው እንዲሁም በኢኮኖሚው ውስጥ ያላቸው ተሳትፎ ከፍተኛ ይሆናል። ይህንን የሚደግፍም መሪ ቃል የተዘጋጀ ሲሆን፤ «ስፖርት ለሁለንተናዊ ለውጥ» የሚል ነው። ስፖርቱ ላይ ትኩረት ተደርጎ ሲሰራ ለስፖርቱ ዕድገት እንዲሁም ስፖርታዊ ጨዋነትን ለማንገስ ሚናቸው ከፍተኛ ይሆናል። ህግ ማክበርን እንደሚያስተምሩ የሚጠቁሙት ዳይሬክተሩ፤ ለስህተቶች ላለመጋለጥ በጥንቃቄ እንደሚሰሩም ያረጋግጣሉ። ይህንንም ደግሞ ከዚህ ቀደም በተካሄዱት ውድድሮች ላይ በትክክል ለመገንዘብ ተችሏል። በርካታ የሚያስተምሩት ነገር እንደመኖሩም በስፖርቱ ዕድገት ላይ ከሚያደርጉት አስተዋጽኦ ባሻገር ለውጥ ማምጣት ይችላሉ። ጤንነታቸው ሲጠበቅም በኢኮኖሚው ላይ የራሳቸው የሆነ አስተዋጽኦ ማበርከት ይችላሉ።አዲስ\nዘመን የካቲት 29/2011በብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "2afeac9ed262f305c821f105c1fdf6e6" }, { "passage": "በዘንባባ\nያሸበረቀው የውቧ ባህርዳር ጎዳናዎች ባላለፉት ቀናት ከመኪና ይልቅ ብስክሌቶች ነበሩ የሚታዩባት። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ብስክሌት መጠቀም እየቀነሰ የመጣባት ባህርዳርም በርካታ አፍሪካዊያን የብስክሌት ጋላቢዎችን ስታስተናግድ ቆይታ ለማጠናቀቅ አንድ ቀን ብቻ ቀርቷታል። ኢትዮጵያ ያላት የመልከዓምድር አቀማመጥ እንዲሁም ከአየሩ ጋር በተያያዘ ለብስክሌት ስፖርት ምቹ መሆኗ ይነገራል።በተለይ በትግራይ እና በአማራ ክልሎች ደግሞ ተዘውታሪነቱ የላቀ ነው። አብዛኛውን ጊዜ ኢትዮጵያን ወክለው እስከ ኦሊምፒክ መሳተፍ የቻሉ ጋላቢዎች ከትግራይ ክልል የተገኙ ናቸው። ክልሉ በርካታ ክለቦችን በመያዝ ወጣቶችን የሚያሰለጥን ሲሆን፤ ያፈራቸው ስፖርተኞችም በውጭ ሃገራት ክለቦች እስከ መጫወት ደርሰዋል። በአማራ ክልልም በተመሳሳይ በርካታ የብስክሌት ስፖርተኞች የሚወጡ ሲሆን፤ ጥረት ኮርፖሬሽንን እና አምባሰልን የመሳሰሉ ክለቦችን ማንሳት ይቻላል። በአፍሪካ አህጉር ትልቅ የሆነውን ብስክሌት ሻምፒዮናም ክልሉ (ባህርዳር ከተማ) በማካሄድ ላይ ትገኛለች።በአፍሪካ\nብስክሌት ኮንፌዴሬሽን የሚመራው የአፍሪካ ብስክሌት ሻምፒዮና በየዓመቱ የሚካሄድ ውድድር ሲሆን፤ የዘንድሮው ለ14ኛ ጊዜ ነው። ያለፈው ዓመት መጨረሻ የኮንፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ከኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ጋር በመወያየትም ከመግባባት ደርሰዋል። በዚህም መሰርት ለአዘጋጅነቱ ፍላጎት ካሳዩት ከተሞች መካከል ባህርዳር የፌዴሬሽኑን መስፈርት በማሟላት ተመራጭ ሆናለች። በዚህም መሰረት ላለፉት ስድስት ወራት ዝግጅት ሲካሄድ ቆይቶ፤ ውድድሩ በደማቅ ሁኔታ በመካሄድ ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ ነገ ይጠናቀቃል። ይህንን\nውድድሩን ከሌላው ጊዜ ለየት የሚያደርገው የ2020 የቶኪዮ ኦሊምፒክ ማጣሪያ በመሆኑ ነው፤ በመሆኑም በርካታ ሃገራት ተሳታፊ እንደሚሆኑ ይጠበቅ ነበር። ይሁን እንጂ ከ46ቱ የኮንፌዴሬሽኑ አባል ሃገራት የተመዘገቡት 17 ሲሆኑ፤ በውድድሩ ላይ እየተካፈሉ ያሉት ግን 13 ቡድኖች፤ 180 ልዑካን ናቸው። በውድድሩ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙትም አዘጋጇን ኢትዮጵያ ጨምሮ፤ ቡርኪናፋሶ፣ ሩዋንዳ፣ ኤርትራ፣ ቤኒን፣ ኮትዲቯር፣ ግብፅ፣ ናሚቢያ፣ ሞሪሽየስ፣ ሲሼልስ፣ አልጄሪያ፣ ዴሞክራቲክ ኮንጎ እና ደቡብ አፍሪካ ናቸው። ባለፈው\nሳምንት መጨረሻ በተካሄደው የመክፈቻ መርሐ ግብር ላይም፤ የክልሉ ፕሬዚዳንት ዶክተር አምባቸው መኮንን፣ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳውና ሚኒስትር ዴኤታው ሀብታሙ ሲሳይ፣ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ርስቱ ይርዳ፣ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ፣ የአፍሪካ ብስክሌት ማህበር ፕሬዚዳንት ዶክተር መሃመድ ወጋይ፣ የኢትዮጵያ ብስክሌት ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ወርቁ ገዳ እንዲሁም የክልል እና የሃገራት ፌዴሬሽን ሥራ አስፈጻሚ አባላት ተገኝተዋል። ባለፈው\nሳምንት መጨረሻ በተጀመረው በዚህ ሻምፒዮና በመጀመሪያው ዕለት ኢትዮጵያ ሦስት ወርቅ እና አንድ ነሐስ በማስመዝገብ ነበር መምራት የጀመረችው። በወጣት ሴቶች 15 ኪሎ ሜትር የቡድን ክሮኖ ኢትዮጵያዊያኑ ብስክሌተኞች ተፎካካሪያቸውን ኤርትራዊያንን በመብለጥ የወርቅ ሜዳሊያውን ወስደዋል። በአዋቂ ሴቶች 30 ኪሎ ሜትር የቡድን ክሮኖም በተመሳሳይ የወርቅ ሜዳሊያውን ወስደዋል። በወጣት ወንዶች የ30 ኪሎ ሜትር የቡድን ክሮኖም የበላይነቱ በኢትዮጵያዊያን ሲያዝ በአዋቂ ወንዶች 46 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የነሐስ ሜዳሊያውን ወስደዋል።ኢትዮጵያ ከአዘጋጅነቷ ባሻገር በውድድሩ ተሳታፊ እንደመሆኗ ዝግጅቷን ቀድማ ነው የጀመረችው። ባለፈው ታኅሣሥ ወር የብሄራዊ ቡድን ምልመላ የተካሄደ ሲሆን፤ በተደረገው ማጣራት 35 የብስክሌት ጋላቢዎችን በብሄራዊ ቡድኑ በማካተት አንድ ወር ያህል ልምምድ ሲደረግ ቆይቷል። ኢትዮጵያ በዚህ ሻምፒዮና እንደ ኤርትራ እና ደቡብ አፍሪካ የተሻለ ስም ያላት ሃገር ስትሆን፤ ከረጅም ዓመታተ በኋላ በሪዮ ኦሊምፒክ በስፖርቱ መሳተፏም ይታወሳል። በአምናው ሻምፒዮና ቡድኑ ሁለተኛ በመውጣት አመርቂ ውጤት አስመዝግቧል።አሁን ደግሞ በራሳቸው አየር ላይ በሚያደርጉት ውድድር የተሻለ ውጤት እንደሚመዘገብ የሚጠበቅ ሲሆን፤ በዚህም በቶኪዮ ኦሊምፒክ ኢትዮጵያ የምትወከልበት አንድ ስፖርት ይሆናል። ውድድሩ አራት ተግባራትን የሚያጠቃልል ሲሆን፤ እነርሱም በቡድን የሰዓት ሙከራ፣ በግል የሰዓት ሙከራ፣ የጎዳና ውድድር እንዲሁም ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደው የቅልቅል ውድድር ናቸው። ይህ ውድድር 50 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን፤ ሦስት ሴት እና ሦስት ወንዶች ርቀቱን እኩል ተካፍለው በቅብብል ይወዳደራሉ።አዲስ ዘመን መጋቢት 9/2011በብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "0f38a4328cffe674cc29747974f523cc" }, { "passage": "በተለያዩ ዓለም አቀፋዊ የስፖርት ውድድሮች ላይ በብሄራዊ ደረጃም ይሁን በሌላ መንገድ ተሳታፊ የሚሆኑ አካላት ውጤታማነታቸውን አስመስክረው ይመለሳሉ። ነገር ግን ስፖርተኞቹ ለአንድ ወቅት የዜና ማማሟቂያ ከመሆን በዘለለ ቀጣይነት ሲኖራቸው አይታይም። አብዛኞቹ ለጥቂት ጊዜ ብቅ ብለው ይጠፋሉ። ምክንያቱም ከሚመለከታቸውና ባለ ድርሻ ከሆኑ አካላት የክትትል እና እገዛ ስለሚያንስ ነው። በቅርቡ በቻይና ጂንጃንግ ከተማ ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የዓለም ዩኒቨርሲቲዎች ውድድር ላይ አፍሪካን በመወከል በእግር ኳስ ስፖርት ተሳታፊ የነበረው የኮተቤ ሜትሮ ፖሊታን ዩኒቨርሲቲ ቡድን እንደነበር ይታወሳል።የዚህ ቡድን ተስፋ እንደ ሌሎቹ እንዳይደበዝዝና\nውጤታማነቱም ቀጣይነት እንዲኖረው ምን መደረግ ይኖርበታል በሚለው ሃሳብ ላይ የሚመለከታቸው ሊረባረቡ ይገባል። በኮተቤ ሜትሮፖሊታን\nዩኒቨርሲቲ የስፖርት ሳይንስ አካዳሚ ዳይሬክተር ዶክተር ሃብታሙ ደመላሽ፤ ውድድሩ በዓለም ደረጃ ተወዳዳሪ የሆኑ ስፖርተኛ ተማሪዎችን\nለማፍራት ምን እንደሚያስፈልግ ልምድ የተገኘበት መድረክ እንደነበር ይገልጻሉ። ተጫዋቾቹ ራሳቸውን ማሳየት የሚችሉበት መድረክም ተፈጥሮላቸዋል፤\nአንዳንዶቹም በሊግ ደረጃ መጫወት ችለዋል። ተቋሙ የራሱ ክለብ እስኪኖረው የሊግ ክለቦች ተጫዋቾቹን እንዲጠቀሙባቸው ሁኔታዎችን አመቻችቷል።\nስፖርት መሰረተ ልማት የሚፈልግ እንደመሆኑ ዩኒቨርሲቲው የጀመረውን እንቅስቃሴ አጠናክሮ ይቀጥላል። የራሱ ሜዳዎችና ማዘውተሪያዎች\nሲኖሩት ደግሞ ክለቦችን በመመስረት ስፖርቱን ማሳደግ እንደሚችሉም ተስፋ ያደርጋሉ። ኮተቤ በስፖርት ፈር ቀዳጅ ዩኒቨርሲቲ ሲሆን በሃገሪቷ ካሉት የስፖርት ባለሙያዎች አብዛኛዎቹ ከተቋሙ\nየወጡ ናቸው። አካዳሚው በአሁኑ ወቅት በተለየ አደረጃጀት ከመማር ማስተማር ስራዎች ባሻገር ማህበረሰቡ ድረስ በመውረድ በርካታ ስራዎችን\nበማከናወን ላይ ይገኛል። እንደሚታወቀው ስፖርት ያለ ውድድር ሊያድግ አይችልም፤ ነገር ግን በሃገሪቷ የታየው አለመረጋጋት የዩኒቨርሲቲዎች\nውድድር እንዳይካሄድ አድርጎታል። በርካቶች ከዚህ ውድድር ወጥተው አሁን በፕሪሚየር ደረጃ በመጫወት ላይ ይገኛሉ። ይህ ውድድርም\nበዚህ ምክንያት አለመካሄዱ የራሱን ተጽእኖ እንደሚያሳድር ዶክተር ሃብታሙ ይጠቁማሉ። በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስፖርት\nማህበር ፕሬዚዳንት አቶ አባይ በላይሁን ቡድኑ በቻይና በነበረው ቆይታ በርካታ ልምዶችን ያገኘበትና በተጫዋቾቹ በኩልም ብዙም ብልጫ\nያልታየበት እንደነበር ያስታውሳሉ። ይልቁንም የሌሎች ሀገራት ተጫዋቾች የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችም ሆነው ለክለቦች የሚጫወቱ እንደነበሩም\nለማወቅ ተችሏል። ከዚህ ባሻገር በምልመላ እንዲሁም በዝግጅት ረገድ በርካታ ቀሪ ስራዎች እንዳሉ ያሳየ መድረክም ነው። በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ስፖርት ማህበር ፕሬዚዳንት አባይ በላይሁን በበኩላቸው በውድድሩ\nበርካታ ልምዶች መገኘታቸውን ያስታውሳሉ። በዩኒቨርሲቲ ውድድር ላይ አንድ ቡድን የተሻለ ነገር ቢያስመዘግብም በነበረበት ላይቀጥል\nይችላል፤ ምክንያቱም ተማሪዎች ተመርቀው ተቋሙን ይለቃሉ። የተሻለ አቅም ያላቸው ስፖርተኞም በአብዛኛው ከስፖርቱ ሲርቁ ይስተዋላል።\nበመሆኑም ዩኒቨርሲቲዎች የስፖርት ክለቦችን ማቋቋም ለዚህ መፍትሄ እንደሚሆን ፕሬዚዳንቱ ይጠቁማሉ። ኮተቤ ሜትሮ ፖሊታን ዩኒቨርሲቲም\nአሁን ያሳየው ስኬት ታሪክ ሆኖ እንዳይቀር ባሉት አትሌቶችም ይሁን ሌሎች ተጨማሪ ስፖርተኞችን በመያዝ ጠንካራ የእግር ኳስ ቡድን\nለመመስረት የሚያስችል መነሳሳት አሳይቷል። ተጫዋቾቹ ያሳዩት እንቅስቃሴ በሃገሪቷ ባሉት የሊግ ክለቦች ለመጫወት የሚያስችላቸው በመሆኑም\nክለቦች ወደ ተቋሙ ማማተር ቢችሉ መልካም ነው። በቀደምትነት ከሚነሱት መካከል አንዱ የሆነው ኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ በስፖርት\nስልጠና ላይ ትኩረቱን እንደማድረጉ መጠን የስፖርት አካዳሚውን በዓለም አቀፋዊ ደረጃ ማጠናከር ተገቢ መሆኑንም አስገንዝበዋል።የኢፌዴሪ\nስፖርት ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር፤ የተቋሙን ስኬት ስፖርት ወደ ተፈጥሯዊ ቦታው መመለስ እንደሚገባ ያሳየ መሆኑን ጠቁመዋል። ውጤታማ\nስፖርተኞች ከትምህርት ተቋማት የተውጣጡ እንደመሆናቸው አሁንም ቢሆን በሁሉም የትምህርት ደረጃዎች በስፖርት ላይ ትኩረት ማድረግ\nአስፈላጊ ነው። መልካም ጅምር ያሳየው ቡድኑም እንደ ጋራም ሆነ በግል ተጫዋቾቹ ራሳቸውን በመጠበቅ ለብሄራዊ ቡድን ተምሳሌት መሆን\nይገባቸዋል። እንደ ስፖርት ኮሚሽንም በትምህርት ተቋማት ላይ ርብርብ በማድረግ ስፖርቱ በቀጣይ የሃገሪቷ የውጤት ምንጭ ለማድረግ\nእንደሚሰራም ገልጸዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2012ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "e25b6527a3ddb4d7d00c8abed4c66ccc" }, { "passage": " ብዙዎች ጥቂቶችን ተከትለው ሃገራቸውን ለማስጠራት ታትረዋል። ሰንደቅ ዓላማ አስታቅፎ በምርቃት የሸኛቸውን ህዝብ አሳፍረው አያውቁም። ከጉዳት መልስ፣ ከወሊድ በኃላ እንዲሁም በጤና መታወክ ተበግረው ከውድድር ማፈግፈግንም አልሞከሩም። የቀንና ሌሊት መፈራረቅ የማያሳስበው የሩጫ ወዳጅም በድጋፉ አብሯቸው ዘመናትን ተሻግሯል። ጥረታቸው ሰምሮ የሃገራቸው ሰንደቅ ኣላማ በድል ከፍ ሲል በደስታ አንብተዋል። ህዝባቸውን በጀግንነት ስለሚያኮሩም በአበባ ጉንጉን ይቀበላቸዋል። ከሽልማትና ስፖንሰር የሚያገኙትን ገንዘብ ሃገራቸው ላይ ፈሰስ በማድረግም ለበርካቶች የስራ ዕድል ፈጥረዋል። እነርሱም ተምሳሌት ያደረጉ ታዳጊዎችም እንደምንጭ ከስር ከስር እየፈለቁ ረጅም ዓመታትን አስቆጥረዋል። ለምስራቅ አፍሪካ ሃገራት በተለይም ለኢትዮጵያ እና ኬንያ የ10ሺህ እና 5ሺህ ሜትር ሩጫ ታላቅ ትርጉም ያለው ነው። ያሉበት የመልካምድር አቀማመጥና የአየር ሁኔታ ለስኬታማነታቸው እንዳገዛቸው በባለሙያዎች ይነሳል። በግልጽ እንደሚታየው ባለፉት ዓመታት በርቀቶቹ በተካሄዱ ውድድሮች የበላይነቱን የያዙት የሁለቱ ሃገራት አትሌቶች እየተፈራረቁ ነው። በዚህም ምክንያት በአካባቢው እንደ ባህል ስፖርት እንዲታይ ምክንያት ሆኗል። ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን በእነዚህ ርቀቶች የሚካሄዱ ውድድሮች በዓለም ላይ እየተመናመኑ ነው የሚገኙት። የ10ሺህ\nሜትር ሩጫ በብቸኝነት የሚታየው በዓለም ሻምፒዮና እና ኦሊምፒክ ላይ ብቻ ነው። በዳይመንድ ሊግ ይካሄድ የነበረው የ5ሺህ ሜትር ሩጫም ከቀጣዩ ዓመት ጀምሮ እንደማይካሄድ ዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር አስታውቋል። ይህም ሃገራቱን ያስቆጣ ሲሆን፤ ቅሬታዎቻቸውን በማንሳት ውሳኔውን ለማስቀልበስ የተለያዩ እርምጃዎችን በመወሰድ ላይ ይገኛሉ። ከሳምንት በፊት በዴንማርክ የተካሄደው የዓለም ሃገር አቋራጭ ሻምፒዮና ላይ ጉዳዩን የተቃወሙት ኢትዮጵያ እና ኬንያ በተናጥል የዓለም አቀፉን ማህበር ፕሬዚዳንት ሰባስቲያን ኮን አናግረዋል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮሎኔል ደራርቱ ቱሉም ከፕሬዚዳንቱ ጋር ቆይታ አድርጋለች። በውይይቱ ላይ ካነሷቸው ነጥቦች መካከል አንዱም የ5ሺህ ሜትር ውድድር ጉዳይ አንዱ ነበር። በኦሊምፒክ 10ሺህ ሜትር የመጀመሪያዋ ጥቁር ሴት አትሌት በመሆን አፍሪካን ያስጠራችው ደራርቱ፤ «እኔን እና ሌሎች አትሌቶችን ያሳወቀን 5ሺህ እና 10ሺህ ሜትር ሩጫዎች ናቸው። ኢትዮጵያም የታወቀችበትና የተከበረችበት ይኸው ርቀት ነው። በመሆኑም እንዲህ መሆን የለበትም፤ እኛንም እንደ ህዝብ እና እንደ ምስራቅ አፍሪካ ያስከፋ በመሆኑ በድጋሚ ሊታይ ይገባል» ትላለች። ከማህበሩ ፕሬዚዳንት ጋር በነበራቸው ንግግር ላይም፤ አትሌቶች ወደ ሩጫ ሲገቡ ከ3ሺህ ሜትር በታች ባለው አጭር ርቀት ነው። ከዚያ በኃላ ነው ወደ ማራቶን የሚሄደው። አሁን ግን በቀጥታ ወደ ረጅም ርቀት ለመግባት ይገደዳሉ። ስለዚህም ውሳኔው በድጋሚ ሊታይ ይገባል የሚል ሃሳብ ማንሳቷን ትገልጻለች። በቅርቡ አቢጃን ላይ በሚኖረው ስብሰባ ጉዳዩ የሚነሳ በመሆኑም፤ የሚሆነውን በጋራ እንደምታይም ጠቁማለች። ከዚህ ባሻገር የአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን የቦርድ አባል እንዲሁም የምስራቅ አፍሪካ አትሌቲክስ ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆኗ፤ የተለያዩ ስራዎችን በማከናወን ላይ እንደምትገኝ ታስረዳለች። «ከኬንያው የኮንፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ጋር በቅንጅት ምን መሰራትና እንዴት መሰራት እንዳለበት በመነጋገር ላይ እንገኛለን። የአፍሪካ ተወካይ እንደመሆናቸው ጉዳዩ ሲወሰን ለምን ዝምታን እንደመረጡ ጥያቄ እናቀርባለን። እነርሱን መተካት ካለብንም ሌሎች ጠንካራና መሞገት የሚችሉ ሰዎችን ከኢትዮጵያም ቢሆን መተካት እንዳለብን እዚያ የምንነጋገር ይሆናል»ም ብላለች። የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴም፤ ዓለም አቀፉ ማህበር ከዚህ ቀደም በዳይመንድ ሊግ ይካሄድ የነበረውን የ10ሺህ\nሜትር ሩጫ ማስቀረቱን አስታውሶ፤ እ.አ.አ ከ2020 ጀምሮ\nየኢትዮጵያ አና የአፍሪካ ባህላዊ ሩጫ የሆነውንና በርካታ አትሌቶችም ለራሳቸውና ለሃገራቸው አኩሪ ድል ያስመዘገቡበትን የ5ሺህ ሜትር ሩጫ ከውድድሩ እንደሚቀንስ ማስታወቁን እንደማይደግፍ በመግለጫው ማስታወቁ ይታወሳል። ይህንን በተመለከተም ኮሚቴ በማቋቋም ውሳኔ የማስቀልበስ ስራውን ጀምሯል። በርቀቱ  ታዋቂና ዝነኛ የሆኑ አንጋፋ አትሌቶች በተካተቱበት ኮሚቴ ውስጥም የፌዴሬሽኑ ምክትል ፕሬዚዳንት ገብረእግዚአብሄር ገብረማርያም አንዱ ነው። ፌዴሬሽኑ እና ኦሊምፒክ ኮሚቴው ከዓለም አቀፎቹ ማህበራት ጋር የሚያደርጉት ግንኙነት እንዳለ ሆኖ የዚህ ኮሚቴ ስራ ድጋፍ መስጠት መሆኑን ይጠቁማል። የኮሚቴው ተግባር ሃሳብ መስጠት ሲሆን፤ ሃገር አቀፎቹ ማህበራትም በዓለም አቀፍ ደረጃ ሃሳቡን የሚያንጸባርቁ ይሆናል። ገብረእግዚአብሄር ሲያብራራም «5ሺህ ሜትርን ከዳይመንድ ሊግ ማስወጣት ስፖርቱን በጣም የሚጎዳና ለመረሳትም የሚያበቃ ነው። በርቀቶቹ ለዓለም ሻምፒዮና እና ለኦሊምፒክ ብቻ መዘጋጀቱም አስቸጋሪ ይሆናል። ይህንን ተያያዥነት ያለው ስፖርት ማስቀጠል ካስፈለገም 5ሺህ ሜትር መመለስ አለበት የሚለው የፌዴሬሽኑ አቋም ነው። ይህንንም በደብዳቤ ለማህበሩ አሳውቀናል፤ እስካሁን የተባለ ነገር ባይኖርም ወደፊት ግን ምላሽ ይሰጣሉ በሚል ይጠበቃል» ብሏል። የውሳኔ ዜናው እንደተሰማ ከኢትዮጵያም ቀድማ ተቃውሞዋን ይፋ ያደረገችው ጎረቤት ሃገር ኬንያ ነበረች። ነገር ግን በዴንማርክ በተካሄደው የዓለም ሃገር አቋራጭ ሻምፒዮና በኋላ ሃገሪቷ የአቋም ለውጥ ማድረጓን የሚያሳይ ዜና ተሰምቷል። የሀገሪቷ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ከዓለም አቀፉ ማህበር ፕሬዚዳንት ጋር ቆይታ ካደረጉ በኋላ ውሳኔው የተደረሰበት ምክንያት እንዳሳመናቸው ገልጸዋል። ይህ የኬንያዊያን የአቋም መወላወል ኢትዮጵያ የምታቀርበው ተቃውሞ ላይ ተጽእኖ ያሳድር ይሆን የሚለው የብዙዎች ስጋት ነው። አንጋፋው አትሌት ገብረእግዚአብሄር ግን «ተቃውሞው አንድ እና ሁለት መሆኑ ሳይሆን የሚያሸንፈው እውነታው ነው» የሚል\nእምነት አለው። «ወጣቶች\nከአጭር ርቀት በአንዴ ዘለው ማራቶንን መቀላቀል የለባቸውም። በመሆኑም እኛ ደጋፊ ኖረም አልኖረም እውነታውን ይዘን ነው የምንቃወመው። በእነርሱ በኩል የተቃውሞ መቀዛቀዝ ቢኖርም ትክክለኛውን ሃሳብ ይዞ መጓዙ ይሻላል» በማለትም የተቃውሞውን ቀጣይነት ያረጋግጣል።አዲስ ዘመን መጋቢት 30 /2011 ", "passage_id": "3250a503d75327e78d92b138d9603d50" }, { "passage": "ኢትዮጵያ ከዘመናዊ ስፖርት ጋር ከተዋወቀች ከድፍን ምዕተዓመት በላይ\nየተቆጠረ ቢሆንም ዘርፉ አሁንም ድረስ በውስብስብ ችግሮች ውስጥ ተዘፍቆ ወደ ፊት መራመድ እንዳቃተው ባለሙያዎች ይናገራሉ።ስፖርቱን\nከነዚህ ውስብስብ ችግሮች ለማውጣት ከሃያ ዓመት በፊት ተግባራዊ የሆነውን አገር አቀፍ የስፖርት ፖሊሲ ከመከለስ አንስቶ የስፖርት\nሪፎርም በማካሄድ ከቀጣዩ ዓመት ጀምሮ ለአስር ዓመታት ተግባራዊ የሚሆን ስትራቴጂክ እቅድ ተዘጋጅቷል።የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን በአገራዊ የስፖርት ሪፎርም ዙሪያ ከተለያዩ\nባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶችን ሲያደርግ እንደሰነበተ የሚታወስ ሲሆን ባለፈው አርብ በዚሁ በሪፎርም ዙሪያ ለስፖርት ጋዜጠኞች\nበቢሾፍቱ ከተማ የአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጅቶ ነበር።በዚህ መድረክ ላይም የስፖርት ሪፎርሙንና የአስር ዓመት\nስትራቴጂክ እቅዱን ለመተግበር ጥናት የተደረገበት ሰነድ ቀርቧል።ጥናቱ ከዚህ ቀደም ሲቀርብ ከነበሩት ተመሳሳይ ጥናቶች ብዙ ልዩነት\nያለው ባይሆንም በአገሪቱ ስፖርት ዙሪያ ያሉ ውስብስብ ችግሮችን በስፋት ለመዳሰስ ሞክሯል። በጥናቱ ከተዳሰሱ የአገሪቱ የስፖርት ችግሮች መካከል አደረጃጀት\nዋነኛው ሲሆን በስፖርታዊ ተቋማት፣ በኢሊት ስፖርትና በማስ ስፖርት አገሪቱ ያለችበት ደረጃ እዚህ ግባ የማይባል መሆኑን አመላክቷል።ይህም\nየአገሪቱ ስፖርት የቱ ጋር ነው? ብሎ ለመጠየቅ ትክክለኛ መነሻ መሆኑን ጠቁሟል።በውድድርና ተሳትፎ መካከል ያለው ልዩነት ጠባብ መሆኑን የጠቆመው ጥናቱ በክለብና ከዚያ በታች ባሉ አደረጃጀቶች\nበሚካሄዱ ውድድሮች መካከል ልዩነቶች አለመኖራቸው የአገሪቱ ስፖርት ውድቀት አንዱ ማሳያ መሆኑን አመላክቷል።በአገሪቱ ከመጀመሪያ\nደረጃ አንስቶ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዙሪያ ከአርባ እስከ ሃምሳ ሚሊየን ህዝብ እንዳለ የጠቀሰው ጥናቱ፤ ከአገሪቱ ህዝብ\nግማሽ ያህሉ በሚገኝበት አካባቢ ስፖርቱ እንዳልተሰራበትና የአገሪቱን ስፖርት ለማሳደግ ትምህርት ቤቶች ላይ መስራት አማራጭ የሌለው\nግዴታ መሆኑን ያስቀምጣል።ትምህርት ቤቶች የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች የሚገኝባቸው እንደመሆኑ ከማህበረሰብ አቀፍ የስፖርት እንቅስቃሴ(ማስ\nስፖርት) አኳያ ለህብረተሰቡ ጥቅም እየሰጡ እንዳልሆነ ያስቀመጠው ጥናቱ ፤በእረፍት ቀናትና ከትምህርት በኋላ የማዘውተሪያ ስፍራዎች\nነፃ ቢሆኑም ማህበረ ሰቡ እንዲጠቀምባቸው እየተደረገ እንዳልሆነ ይጠቁማል። ለዚህም ህብረተሰቡ መንገድ ዘግቶ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን\nለማድረግ እንደተገደደ ተቀምጧል።የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ግዙፍ ስቴድየሞችን ጨምሮ በርካታ የማዘውተሪያ ስፍራዎችን በህዝብ ገንዘብ\nየገነቡ ቢሆንም ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ውጪ እንዲጠቀማቸው ባለመደረጉ የማስ ስፖርትን ማሳደግ እንዳልተቻለም ተጠቁሟል።አገር አቀፍ ስፖርቶችን የሚመሩ ፌዴሬሽኖችን በተመለከተ ጥናቱ የጠቆመው አንድ ነጥብም የሚያ ነጋግር ነበር።ፌዴሬሽኖች\nአገር አቀፍ ስፖርቶችን ሲመሩ ዋነኛ ስራቸው ስፖርቶችን ለህብረተሰቡ በማስተዋወቅ በስፋት እንዲዘወተሩ ማድረግ ቢሆንም የአገራችን\nፌዴሬሽኖች ተጠምደው የሚ ታዩት ስፖርተኞችን ለዓለም አቀፍ ውድድሮች ማዘጋጀትና ይዞ መጓዝ ላይ ብቻ መሆኑን ጥናቱ አመልክቷል።\nየስትራቴጂክ እቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ በጥናት ከተጠቀሱት በርካታ ውስብስብ ችግሮች ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ተሞከረ\nእንጂ የአገሪቱ ስፖርት የገባበት አዘቅጥ ተቆጥሮ የሚያልቅ አይደለም።ይሁን እንጂ የስትራቴጂክ እቅዱም ይሁን የስፖርት ሪፎርሙ እነዚህን\nችግሮች ቀርፎ በቀጣዩ አስር ዓመት የስፖርት ዘርፍ ልማትን በማስፋፋት ንቁ ማህበረሰብ በመፍጠር በዓለም አቀፍ መድረኮች ተፎካካሪና\nአሸናፊ አገርን እውን በማድረግ ስፖርቱ ለአገር ብልፅግና ያለውን ሚና ለማሳደግ እንደሚጥር ታምኖበታል።የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን 22 ዓመታትን ያስቆጠርውን የኢትዮጵያ ስፖርት ፖሊሲ እንዳሻሻለውና በቀጣይ 10 ዓመታት\nተግባራዊ ሊያደርግ ዝግጅት ማጠናቀቁን በገለፀበት መድረክ በ1990 የወጣው ፖሊሲ ጠንካራ እና ደካማ ጎን ምን ይመስላል በሚለው\nሃሳብ ዙሪያ በጥናት አቅራቢው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህራኖች በአቶ ሳሙኤል ስለሺ እና በዶክተር ዘሩ በቀለ ቀርቧል።ጥናቱ\nያስቀመጠውን የመፍትሄ ሃሳብ አካቶ ለቀጣይ አስር አመት ኢትዮጵያ የምትጠቀምበትን እቅድ በኮሚሽኑ የእቅድና ዝግጅት ክትትልና አፈፃፀም\nዳይሬክተር አቶ እንድሪስ አብዱ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።ጋዜጠኞች ቢካተቱትና ትኩረት ቢሰ ጠው ያሉትን ሃሳብ በአስተያየታቸው\nአካተዋል። ኢትዮጵያ የፖሊሲ ችግር የለባትም አፈፃፀሙ ላይ ነው ችግሩ\nያሉት አስተያየት ሰጪዎቹ፤ አሁንም አስፈፃሚው አካል በእውቀትና በትጋት ቢሰራ ውጤት የማምጣት አቅም ያለው ፖሊሲ መሆኑን ተናግረዋል።አዲሱ\nፖሊሲ ዘጠኝ ፒላሮች (ምሰሶዎች) ያሉት ሲሆን ስፖርቱን ህዝባዊ ለማድረግ ፣ ስፖርቱ ኢንቨስትመንት መሆኑ ታውቆ ባለሃብቱ የሚሳተፍበት\nመድረክ እንዲሆን እና ትምህርት ቤቶች የስፖርተኛ ማመንጫ ለማድረግ የሚያስችሉ አንቀፆች ተካተውበታል፡፡አዲስ ዘመን የካቲት 3/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "5539e5d03fd2bfcd678fee505baa2546" } ]
3421e9cf1ff00e433878c4297756bc80
df4d4d14e7f3613c8a3c56d0fc184f47
እግራችንን እንሰብስብ፤ ቤታችን እንዝጋ!
 የአለም አቀፍ ስጋት የሆነው የኮሮና ቫይረስ ለመከላከል ለሚደረገው ጥንቃቄ እያሳየነው ያለነው ዝግጁነት እንደ ጣሊያን ዋጋ እንዳያስከፍለን እሰጋለሁ። ብዙዎችም ሊመጣ የሚችለውን ችግር ቀድመው በመተንበይ እያስጠነቀቁን ነው። ነገር ግን አፍንጫው ላይ ነጭ ሽንኩርት፣ ሎሚና ጤናዳምን እስከነቅጠሉ አስሮ ከመሳለቅ በዘለለ ንክኪን ለማቆም የደፈረ የለም። ብዙዎቻችን ኮሮና ኢትዮጵያ አይገባም፤ ቢገባም አይጎዳንም የሚል ፌዝ ይዘን እራሳችን እያታለልን ነው። ማታለል ብቻም ሳይሆን ለሚመጣው ሰደድ እሳት ብዙዎችን አሳልፈን እየሰጠን ነው። ኋላ በኮሮና የተያዝኩት በማንነቴነው ምናምን አይሰራም። በሚገርም ሁኔታ ኮሮና የሚባል ነገር እንኳ በኢትዮጵያ በተቀረው የዓለማችን ክፍልም አለ ብሎ የማያምን ብዙ ሰው አለ። አብዛኛው ሕዝብ ደግሞ ኮሮናን ለማስደሰት እስኪመስል ድረስ እስከ አንድ ኪሎ ሜትር ድረስ የሚጮህ የእጅ ሰላምታ ሲለዋወጡ እየተመለከትን ነው። ሌላው ደግሞ ኮሮናን ለመከላከል ከሥራ ቀርቶ ካፌ ሲያሞቅ ይውላል። አንዳንዱ ሥራ አይገባም ነገር ግን በሠራተኞች ማመላለሻ ሰርቪስ ነጠላውን አጣጥፎ ይገባና ቤተክርስቲያን ያሳልፋል። የተቀረው ከመገናኛ እስከ ሜክሲኮ፤ ከአውቶቡስ ተራ እስከ ቃሊቲ ሰው በብዛት የሚሰበሰብበትን እየመረጠ ሲዘዋወር ይውላል። በሽታው ከሚሰራ ሰው ጋር ነው እንዴ ጥሉ? ይህ እኮ አግባብ አይደለም ስትላቸው መልሳቸውና ራሳቸውን የማታለያ መንገዳቸው «ፈጣሪ አለ» የሚል ነው። «ኢትዮጵያ ትፈተናለች እንጂ አትፈርስም። ይህ የአውሮፓውያን ሴራ ነው» ብለው ይመልሳሉ። እኔም አምናለሁ ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይጠብቃል። ግን ደግሞ «አትፈታተኑኝ» ብሏል። ክፉ ቀንንና ጥምዝምዝን ማሳለፍ ጎንበስ ብሎ ነው ይባል የለም? ምን ችግር አለው ፈጣሪያችንን እያመንን ቤታችንን ብንዘጋ? ችግሩ ከየትም ይሁን ከየት ማንም ያምጣው ማን የሚጎዳን ከሆነ በመጠንቀቅ ፈንታ ሌሎችን መኮነን አግባብ አይደለም። ቤትን መዝጋት ብዙ ጥቅሞች ይኖሩታል። መጥፎ ከማየትና ክፉ ከመስማት በጥቂቱም ቢሆን ይቆጥበናል። ፈጣሪን መማፀኛ ሰፊ ጊዜም ይኖረናል። ፈጣሪ ሁሌም አለ። ግን ሰዎች በራሳቸው ስህተትና በማያውቁት ነገር ይሞታሉ። እና የሚሞቱ ኢትዮጵያውያን ፈጣሪ አያውቃቸውም ማለት ነው? ብዙ አታስወሩኝ ከፈጣሪዬ ጋር ታጣሉኛላችሁ። አንዳንድ ሰዎችማ ኮሮናን ደስ ለማሰኘት ካላቸው ከፍተኛ ፍላጎት የተነሳ ከተጣሉት ሰው ጋርም ሳይቀር ሰላምታ ሳይለዋወጡ አይቀሩም። እናም እላለሁ እባካችሁ መመሪያ እናክብር። የኤሲያ ሀገራት ለቻይና ቅርብ እንደመሆናቸው በከፍተኛ ሁኔታ የመጠቃት ዕድል ነበራቸው፤ እነሱ ግን የበላይ አካላትንና ሕግን የማክበር ጠንካራ ባህል አላቸው። ይህም ጠቅሟቸዋል። መንግሥት ያወጣውን ሕግ ተግባራዊ ማድረግ በመቻላቸው በሽታው ሳይስፋፋ ብዙም ሳይጎዱ ማለፍ ችለዋል። አያችሁ ቤታቸውን ዘግተው ፈጣሪያቸውን የሚለምኑ እንዲህ ናቸው። እውነት እናውራ ካልን ብልህነት ይህ ነው! ‹‹በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ›› በቤት ውስጥ ቁጭ ብሎ ከፈጣሪ ጋር መቀራረብ እንዲሁም ከበሽታው መትረፍ። ‹‹ስንቱን አስታወስኩት ስንቱን አሰብኩት ልቤን በትዝታ ወዲያ እየላኩት አንዴ በመከራው አንዴ በደስታየ ስንቱን ያሳየኛል ይሄ ትዝታየ›› አይደል ያለው መሀሙድ አህመድ ። መሀሙድን ትዝታው ብዙ ነገርን እንዳሳየው ሁሉ እኔንም ኮሮና ብዙ ፀባይ ያላቸው ሰዎችን አሳይቶኛል። አንዳንድ ሰዎችማ ግርም እኮ ነው የሚደርጉት በግድ ስለ ኮሮና ብዙ እንድታስብ ያደፋፍሩሃል። ጣሊያን በቫይረሱ በጣም ብዙ ሰዎች ሞቱ ሲባል «ኢትዮጵያ ስለወረረች ነው» ይላሉ። ግብፅ ሦስት ጀነራሎቿንና በርካታ ዜጎቿን በበሽታው መነጠቋ ታውቋል ሲል ዜናው ሰው ቀበል ይልና ማን ኢትዮጵያን ተንኩሽ አላት። የማይገባትን የአባይን ውሃ ለምን ለእኔ ብቻ ልጠቀም አለች?…ሲል ይጠይቅና ቀጠል አድርጎም አያችሁ አይደል ኢትዮጵያን ፈጣሪ ይወዳታል ይላል። በአንድ የቴሌቪዥን መስኮት ደግሞ በአሜሪካ የሟች ቁጥር ከአንድ ሺ በላይ ደረሰ። በቫይረሱም ከ60 ሺ በላይ ሰዎች ተይዘዋል ሲል ወንድሜ ምን ቢል ጥሩ ነው «አይ ትራምፕ በማያገባህ ገብተህ ሕዝብህን አስጨረስክ አይደል» አለ። ዞር አልኩና ምን ማለት ነው ስለው? «ለምን በግድቡ ዙሪያ ከግብጽ በኩል ወገነ። » ሲል ሳልወድ ፈገግ አልኩ። ስለእውነት ከሆነ ይህ የዋህነት ነው። ፈጣሪ የሁሉም እንጂ ጥቂቶች እንደምናስበው አንዱን ደግፎ ሌላውን የሚበቀል አይደለም። ይህ ሁሉ ምክንያት ድርደራ እራስን ማዘናጊያ ነው። ግን ሁሉንም ትተን እንጠንቀቅ፤ መመሪያዎችን እንተግብር። አሁን ራስን መደለል አቁመን ወደ መጠንቀቁ ካልገባን ተያይዘን ማለቃችን ነው። በቦሊቪያ ከአንድ ቤተሰብ ከቤት እንዲወጣ የሚፈቀድለት አንድ ሰው ነው። ይህ የሆነው ወረርሽኙ እንዳይስፋፋ ታስቦ ነው። ደግሞም ሰዎች የሚያስፈልጋቸውን በእዛ ሰው አማካኝነት እንዲያገኙ ነው። በእኛ ሀገርስ ይህ ሕግ ቢተገበር የሚቀበለው ስንቱ ነው? ከእንትና ብሔር ከአንድ ቤተሰብ ሁለት ሰዎች እንዲወጡ ተፈቅዶላቸዋል። የእንትና ሃይማኖት ተከታዮች እንደልባቸው እየተንቀሳቀሱ ነው። እኛ ተከለከልን መብታችን ተነፈገ ብሎ አቤቱታ የሚያቀርብ አይጠፋም። ግን ሁሉም አይሆንም ከሳሽም ተከሳሽም የማይሰማው ኮሮና ቫይረስ ለወሬ ነጋሬ ሳያስቀር እንዳይጨርሰን መጠንቀቁ ይበጃል። በማንነቴና የእንትን ብሔር ተወላጅ በመሆኔ ማለት ኮሮና ላይ ዋጋ የለውም፤ ዋጋ ያስከፍላል እንጂ። እራስን ፃዲቅ ሌላውን ሀጢአተኛ በማድረግ ኮሮናን ማምለጥ አይቻልም። ኮሮና ቫይረስን ማምለጫው ዋና መንገድ የሚሰጡ መመሪያዎችን በትክክል መተግበር መቻል ነው። ከሁሉም በላይ እግራችንን ሰብስበን ደጃፋችንን ዘግተን የኮሮናን ማህበራዊ ተጽዕኖ እንቋቋም።አዲስ ዘመን መጋቢት 20 ቀን 2012 ዓ.ምሞገስ ጸጋዬ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=29384
[ { "passage": "ባሕር ዳር፡ መስከረም 18/213ዓ.ም (አብመድ) ያሁኑ ይባስ ! ከጽሕፈት ቤቶች አጥር በር ላይ እኔና የሥራ ባልደረባዬ ለመግባት ሁለት የወረዳው አመራሮች ደግሞ ለመውጣት መግቢያው ላይ ተገናኝተናል። አንደኛው አመራር ግን “ባክህ ኮሮና የለም ምናባቱ” በማለት የሥራ ባልደረባዬን አንገት አቅፎ ይስመው ጀመር። ጓደኛየም እየተገላበጠ ተሳመ የሚገርመው ደግሞ ኮሮና የለም እያለ የሚስመው የወረዳው ጤና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ መሆኑ ነው።በእርግጥ ኃላፊነት አልባ የሆኑ ኃላፊዎች የሀገርን ምሰሶ ይንዳሉ የሚባለው እውነት ነው። “ኮሮና ገዳይ ነውና መሸፋፈን፣ መራራቅንና መታጠብን አትርሱ” እያለ የሚያላዝን አስተማሪ እንዲህ በአደባባይ ሲተቃቀፍ ልብ ብሎ ያየ ተመልካች ምን እንደሚማር ለእናንተ ማውጋት ለቀባሪ ማርዳት ይሆናል።በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ስር ከሚገኙ ወረዳዎች መካከል አንዷ በሆነችው ጃዊ ወረዳ ተገኝተናል። ሰዓቱ ከቀኑ ስምንት ሰዓት መሆኑ ከአካባቢው በርሃ ጋር ተዳምሮ ሙቀቱ እጅግ አይሏል! ሰውነትን ይወብቅም ይዟል።ከቀኑ ሰባት ሰዓት አካባቢ ነው እንደ ወፍ ስትከንፍ በነበረችው ሀይሩፍ መኪና ታግዤ ጃዊ ወረዳ የደረስኩት። የተገኘውን እንደ ነገሩ ቀማምሼ ለሌላ ተልኮ እዚህ በሥራ ላይ ከነበረው የሥራ ባልደረባዬ ጋር ለሥራ የሚያግዙንን ቁሶች ይዘን ወደ ጽሕፈት ቤቶች ዘልቀናል። በዚህ ወቅት ነበር ያስደነገጠኝንም ያስገረመኝንም ክስተት ከምክትል ጤና ጽሕፈት ቤት ኃላፊው ድርጊት የታዘብኩት።ከፊት ሆኖ ዕራዩን እየተከተለ የሚሄድ መሪ ከጠፋ የሕዝቡ መዘናጋትና መረንነት ብዙ ላይደንቅ ይችላል። ግን በእጅጉ ሊታሰብበትና ሊታረም የሚገባው ይመስለኛል።በማለዳ ነው ባሕር ዳር አውቶብስ መናኸሪያ የተገኘሁት፤ በመናኸሪያው ከአስተናጋጆች ጀምሮ አብዛኛው ሰው የአፍና የፍንጫ መሸፈኛ አድርጓል። ተሳፋሪው ግን እምብዛም አለበሰም፤ መኪናው ሞልቶ መንቀሳቀስ ስንጀምር የመኪናው ረዳት ለሁሉም መመሪያ በሚመስል መልኩ የፊት መሸፈኛችንን እንድናደርግ ማሳሰብ ጀመረ ልብ ብሎ ትኩረት የሰጠው ግን አልነበረም።ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ባሕር ዳር መውጫ ኬላ ላይ ልዩ ኃይሎች አካባቢ ስንደርስ ረዳቱ ልመና በሚመስል መንገድ ‘‘እባካችሁ ፖሊሶች መጥተዋል ልበሱ’’ ብሎ ወደ ፖሊሶች ተጠግቶ መኪናው ቆመ። በዚህ ቅፅበት ወንዶች ከኪሳቸው ሴቶችም ከቦርሳቸውና ከጉያቸው እያወጡ የፊት ማስካቸውን ለበሱ። ወዲያውም የክልሉን የልዩ ኃይል ልብስ የለበሱ የእጅ ጎንት ያጠለቁ የፊት መሸፈኛ ግን ያላደረጉ የፀጥታ ኃይሎች ሁሉም እንዲወጡ አዝዘው መኪናውንና ከውስጥ ያሉትን ሻንጣዎች ፈትሸው በመቀጠል ሰውንም እየፈተሹ አስገብተው መኪናው ጉዞውን እንዲቀጥል ፍቃድ ሰጥተውታል።የዚህ ዓይነት ተደጋጋሚ ክስተት በየቅርብ ርቀት ይደጋገማል ተሳፍሪውም “ማስክህን አድርግ አላደርግም” ድብብቆሽ ዓይነት ጨዋታ ነፍሱንና ጤናውን አስይዞ የሚጫወት ይመስላል። ፈታሽ ሲመጣ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛውን ከመቅፅበት ያደርገዋል፤ ፈታሽ ሳይኖር እንደ ዱምቡሎ ሳንቲም ወደ ኪሱ ይወረውረዋል። በርግጥ ፈታሽ የፀጥታ ኃይሎችም ልበሱ እንጅ ለብሰው አይታዩም አመራሩም እንደዛው ታዲያ አርአያ ሆኖ የሚመራ በሌለበት መዘናጋቱን እንዴት በሕዝቡ መፍረድ ይቻላል?በዚህ ዓይነት ሁኔታ ብዙ እየተጓዝን እንደየሁኔታው የደንብ ልብስ የለበሱ ወጣቶችም መኪናውን አስቁመው ለግንባታ የዕርዳታ መዋጮ ይጠይቃሉ። በመሀሉም የተቀቀለ ሽንብራ ‘‘በረከቱ ይድረሳችሁ!’’ እያሉ በየፊታችን ያዞራሉ። ብዙ ነገር ሲነካካ በነበረው ባልታጠቡ እጆች ከጥሬው እያነሱ ይቋደሳሉ፤ “ኧረ አልታጠብኩም ብዙ ነገር ነክቻለሁ “የሚል የለም በዚህ መሀል ግን የኮሮናቫይረስ መተላለፊያ መንገዱን ድንገት ያለመረዳት ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል ገመትኩ።ከባሕር ዳር ተነስቼ በጃግኒ ዙሬ ጃዊ እስክገባ በሁሉም ከተሞች ኮሮና ያለ አይመስልም መዘናጋቱ እጅግ በዝቷል። የፊት መሸፈኛ የሚጠቀም የለም፤ ማኅበራዊ ርቀት የሚታሰብ አይደለም፤ ምን አለፋችሁ ሰው ተቃቅፎና ተዛዝሎ ነው የሚውለው ማለት ይቻላል።ጃዊ ወረዳም ለምሳሌ የሚሆን ማስክ ያደረገ ሰው በዓይኔ ሳማትርም አላገኘሁም፤ ማስክ የሚያደርግ ሰውን የሚፈልገው ዓይኔ ያሻውን ሳያገኝ ባንድ ሰብሰብ ብለው ወደ ሚገኙት ጽሕፈት ቤቶች ዘለቅሁ፤ ማስክ ያደረገ የለም።ግን ለምን ይሆን የተማረው የመንግሥት ሠራተኛውም ሆነ ኅብረተሰቡን የሚመራው አመራር የኮሮናቫይረስን በመከላከል አርአያ ሆኖ ፊት በመቆም መምራት የተሳነው? መልስ ያላገኘሁለት ጥያቄ ነው።በነገታው ወደ ገጠር ቀበሌ ወጣ ለማለት መናኸሪያ መኪና ይዘናል፤ መኪናዋ ሚኒባስ ናት፤ የመያዝ ልኳ እርግጠኛ ባልሆንም ከአሥራ አራት አይበልጥም፤ ነገር ግን በሰው ላይ ሰው ደርባ 22 ሰው ይዛ ጉዞዋን ጀምራለች። በመኪናው ውስጥ ካለነው የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ያደረግነው እኔና የኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ባለሙያ ብቻ ነን። ሌላው ሌጣውን ሆኖ ነው አፍ ለአፍ ገጥሞ የሚያወጋው። በመኪናው ውስጥ በተደጋጋሚ የሚስሉትንም ታዝቢያለሁ።\nኮሮናን የተመለከተ የግንዛቤ እጥረት አለ ብየ ስላሰብኩ ከአርሶ አደሮች ጋር ጥቂት ሐሳብ ተለዋዋወጥኩ። አርሶ አደር አለነ ስሜ ይባላሉ፤ ስለኮሮና ቫይረስ በቂ ግንዛቤ አላቸው፡፡ ስለመከላከያውም አፍና አፍንጫን መሸፈን መታጠብ እና አለመቀራረብ መሆኑን ጠንቅቀው ያውቃሉ፡፡ ታዲያ አሁን ለምን ባንድ ተሰበሰባችሁ? ስል ጥያቄ አነሳሁ፤ እሳቸውም “ሥራ ላይ ስለሆንን ነው፤ ደሞ እኛ በአንድ ቀየ ያለነው እንተማመናለን፤ ለዛ ነው፡፡ እንግዳ ሰው ሲመጣ አንቀርብም” በማለት ገለፁልኝ። ደሞም በርሃው ላይ በሽታው ያው አቅም የለውም ስለሚባል ኅብረተሰብ አልፈራውም በማለትም አስረዱኝ፤ እርሳቸው ግን ይህንን አያምኑበትም።", "passage_id": "51228b51e92524a52f6abdb874477701" }, { "passage": "የዛሬ ሳምንት የሸኘነው ሰኞ ዛሬም ተመልሷል፤ የሳምንቱ ማክሰኞም ነገ ሊመለስ ቀጠሮ ይዟል። ከአስር ወራት በፊት የሸኘው ክረምትም ወራቱን ሲያካልል ቆይቶ እነሆ በሰኔ «ግም» ብሏል። ማታ የተረከብነውን ጽልመት ንጋት ላይ ለጸሃይ ብናስረክብም ደግሞ ሰዓታትን ቆይቶ ዳግም ከተፍ ይላል። እድሜም እንዲሁ ነው፤\nበደካማ አካላት ህይወት ይጀመራል። ጉርምስናና ጥንካሬውም ጥቂት ዓመታትን ቢያስቆጥር ነው። ጉልምስናው እርጅናውን እየጎተተ አምጥቶ በድካም ያሳርፈዋል። ህይወት ዙረት ናት ይባላል፤ ዳሩ መሬቷም ክብ አይደለች? አዙሪቱ ሞት ከወሰደው በቀር የሄደውን መልሶ ማምጣት ሃቁ ነው። «ዞሮ ዞሮ ከቤት፤ ኖሮ ኖሮ ከመሬት» ያሉት አበውም ይህንኑ ተገንዝበው ነው። እኔ\nየምለው ግን ሳይንስ የነገረን የዓለማችን መሽከርከር በጸባያችን ላይም ተጽእኖ ያሳድር ይሆን እንዴ? «ተውነው» ያልነውን እየመላለስን፤ «ተግባባን» ያልነውን እያፈረስን፣ የረሳነውን እያስታወስን፣ የተረዳነውን እየዘነጋን፣… እንዴት እንዘልቀው ይሆን? በልጅነቴ የሰማሁትን አንድ\nቀልድ ላካፍላችሁ፤ በአንድ የአእምሮ ህሙማን ማእከል የሚገኙ የጤና ባለሙያዎች ህመምተኞቹ ተሽሏቸው እንደሁ ለማጣራት ይነሳሉ። ከዚያም ቴሌቪዥን ከሚመለከቱበት ክፍል አቧራ ያለባቸውን ወንበሮች ደርድረው ሲያበቁ፤ ህሙማኑን አንዳንድ ወረቀት እየሰጡ እንዲታደሙ ይጋብዟቸዋል። የጤና\nባለሙያዎቹ ሲመለሱም ሁሉም አቧራማው ወንበር ላይ ተቀምጠው ቴሌቪዥን ሲመለከቱ ያገኟቸዋል። ከመካከላቸው አንዱ ግን ወረቀቱን ከአቧራው ላይ አንጥፎ ነበር የተቀመጠው። ባዩት ነገርም በመደሰትና ለውጥ እንዳለው በማመን፤ «ለምን ወረቀቱን ከወንበሩ ላይ አነጠፍክ?» ሲሉ ይጠይቁታል። እርሱም «ከፊት ለፊቴ የተቀመጠው ሰው ስለከለለኝ ከፍ እንዲያደርገኝ ነው» ሲል ነበር የመለሰላቸው። ከሁሉ ይበልጥ ተስፋ ቢጣልበትም የታየው ግን ተቃራኒውን ነው። እኛም ያው ሆነናል፤ የገነባነውን መልሰን እናፈርሳለን፣ ያስተካከልነውን እናበላሻለን፣ ብንሄድም እንመለሳለን፣ ያወገዝነውን እናከብራለን፣ የሰቀልነውን ደግሞ እናወርዳለን፣ አልፈን አናልፍም፤ መልሰን ከዚያው ነን። እንዲህ ለማለት ምን አነሳሳሽ አትሉኝም? ተግባራችን ነው። ከሰሞኑ ከአዲስ አበባ አንዱ ስፍራ በእግር ጉዞ ላይ ሳለሁ፤ አንድ ወጣት ተጠግቶኝ «ዶላር ነው፤ ምንዛሬ?» እያለ ይከተለኝ ጀመር። ከወራት በፊት በዘመቻ ይህ የጥቁር ገበያ የገንዘብ ምንዛሬ እንዲቀር መደረጉን አስታውሳለሁ። እንዲያውም ይህንን ህገወጥ ተግባር የሚያከናውኑ ሱቆችም መታሸጋቸው የአንድ ወቅት ዜና ነበር። ከቆይታ በኋላ ግን ዳግም አንሰራርቷል ለማለት ይቻላል፤ ምክንያቱም ወጣቱን ጥቂት አለፍ እንዳልኩ ሌላኛውም በተመሳሳይ «ምንዛሬ?» ብሎኛላ። ስደትም ሌላኛው አዙሪት ነው። «ስደት ይብቃ» የሚል መፈክር ይዘን ነበር ቅርብ ጊዜ፤ ስለ ስደት መጥፎነትም ብዙ ተሰብከን በብዙ ኮንነናል። አሁን ደግሞ ዳግም ማሻሻያ ተደርጎበት በጋዜጣ እና ሌሎች መንገዶች በገንዘብ እያስተዋወቁና እየደለሉ ወደ ስደት ለማጋዝ በአዲስ መልክ እንቅስቃሴ ተጀምሯል። ምን ይሄ ብቻ፤ ሌላም አለ። ከወራት በፊት ከአዲስ አበባ ምድር የጎዳና ተዳዳሪነትን ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እናስወግዳለን ተብሎ በከተማዋ ሲደረግ የነበረው ሽር ጉድ የጉድ ነበር። ከተመረጡ ክፍለ ከተሞችም የጎዳና ተዳዳሪዎችን ወደ ማሰልጠኛና ማገገሚያ የመውሰዱ ተግባር ተጀመረ። ለጊዜው የተመረጡት ክፍለ ከተሞች ፀዱ። አሁንስ? ያው የአዙሪታችን ጉዳይ ሆነና “ፀዱ” የተባሉት ክፍለ-ከተሞች ተመልሰው እዛው ገብተዋል። ለአንድ ሰሞን ታትረን ብንሰራም ድካማችን ቅርብ ነው። ላንደግመው ምለን ተገዝተን የተውነውን ስንፍና፣ መጥፎ እሳቤ፣ መከፋፈል፣ መጠላለፍ እና መሰል ነገሮች ውለን ስናድር እርግፍ አድርገን እንተዋቸዋለን። ግለታችን ንፋስ ሲነካው ወዲያው ቀዝቅዞ ወደ ነበርንበት ይመልሰናል። ሌሎችም አሉ፤ ትናንት ጥያቄ አንስተው እንደተመለሰላቸው ዘንግተው ዳግም መሰል ጥያቄ ያነሱ። ከአንድ የሙያ ዘርፍ ለተነሳ ጥያቄ የተሰጠ ምላሽ፤ መሰል ጥያቄ ላለው ሌላ ሙያም እንደሚያገለግል እየታወቀ መልሶ ለጥየቃ መነሳትን ምን ይሏል? ከስፖርቱ መድረክም አንድ ምሳሌ ላንሳላችሁ፤ እግር ኳሳችንና ደጋፊዎቹን። ከስታዲየሞቻችን እስከ ጨዋታ ሜዳዎች፤ መሰዳደቡ፣ ለጠብ መፈላለጉ አልፎም ተርፎ ድብድብና ሁከቱ ጠንክሮ ነበር በአንድ ወቅት። በመንግስታዊ አካላትም ምክክር፣ ተግሳጽ እና ቅጣት ሲተገበሩም ጥቂት መሻሻል ታየ። ኧረ እንዲያውም «ስፖርታዊ ጨዋነት ቀንሷል» ተብሎ ነበር። ግን አፍታም አልቆየም፤ መልሶ አገረሸና ጭራሽ «ጨዋታውም ይቅር» ተባለ። የህይወትን አዙሪት\nመጋፋት አይቻል ይሆናል፤\nይኼኛው አዙሪት ግን\nከድክመታችን ይመነጫል። በየደረስንበት\nእየተማማልን መልሰን እዚያው\nከሆንን እርምጃችን ሁሉ\n«ባለህበት እርገጥ» ኑሯችንም\nውል አልባ መሆኑን\nእያየን ነው። ግን\nአዙሪቱ ነው መሰል፤\nከጥፋታችን አልተማርንም።አዲስ ዘመን ሰኔ3/2011 ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "6e08b001336110c76c332700f30de5a0" }, { "passage": "በሰፈራችን ያገኙትን መመረቅ የሚወዱ አንድ አባት ነበሩ። «ደግሞ ይስመርላችሁ…አምላክም ይስማኝ እንጂ ልጆቼን እናንተን ለመመረቅ ለምን ብዬ እሰስታለሁ?» ይላሉ። ፈገግ ካሉላቸው መመረቅ ነው፣ ዞር ካሉላቸው መመረቅ ነው፣ አቤት ካሏቸው መመረቅ ነው። ነጋዴ አይደሉም፤ ሽበት የተጎናጸፉ፤ እድሜ ያስከበራቸው ደግ አባት ናቸው። እኛ ደግሞ ሲመርቁ እንዳያመልጠን፤ ቶሎ አሜን አሜን ማለት።አንድ ወዳጃችን ታዲያ አብዝቶ ይወዳቸዋል። ምርቃታቸው የሠራለት ነገር ኖሮ እንደሆነ አላውቅም፤ ብቻ እኛ ጓደኞቹ ከምንወዳቸው በላይ ነው እርሱ የሚወዳቸው። እናም ይህን ፍቅሩን ለመግለጽ በዓል አስታክኮ፣ የእኛን ቦርሳና ኪስ በመዋጮ ስም ፈትሾ፤ ነጣ ያለ ጋቢ ገዝቶ አበረከተላቸው። መረቁት! መቼም የእኛ ነገር! ጥቅም ሲያገኙ አብዝተው የመረቁት ይመስለን ይሆናል? ግን አይደለም። እንደወትሮው ሳያደሉ፤ ሳይጨምሩ ወይም ሳይቀንሱ መረቁት። «አትጣ! አግኝ!» አሉት።ምርቃታቸው እያንዳንዱ ፍሬ እንዳያመልጠው ከስር ከስር በ«አሜን» እየለቀመ ቆየና፤ «አባብዬ… እንደው ይሄ አትጣ አግኝ ብለው የመረቁኝ ነገር ምኑን ነው?» አላቸው። እርሳቸውም ነገሩ ጨዋታ መስሏቸው ፈገግ ብለው፤ «ምንስ ቢሆን የኔ ልጅ? ሰላምም ቢሆን ጤና፤ ፍቅርም ቢሆን አንድነት፤ በጎውን የልብህን መሻት ሁሉ እንድታገኝ ነው ምርቃቴ» አሉት።እርሱ ግን ፊቱን ቅጭም አድርጎ፤ «እንደው ወደላይ አስፈጻሚዎች ጋር ሲደርስ ለመምረጥ እንዳይቸግራቸው፤ «ትራንስፖርት አግኝ…ታክሲ አትጣ!» ብለው ለይተው ቢጠቅሱልኝ ብዬ ነው» አላቸው። ነገሩ ቀልድ ነው ተብሎ በዛን ሰሞን በሰፈራችን እንደ ጉድ ተሳቀ። እርሱ ግን ከልቡ ነበር፤ ተማሯላ!\nባለፉት ቀናት የነዳጅ መጥፋት ድፍን አዲስ አበባ እንዴት የገበያ ማዕከሏን መርካቶን እንደመሰለች አላያችሁም? ግን እኔ የምለው፤ ለነዳጅ እንዲህ ከሆንን…ሰላም ጨርሶ የጠፋች ቀን ምን ሊውጠን ነው። ነዳጅና ሰላም ምን አገናኛቸው እንዳትሉኝ። ሰዎች! ሁሉም ነገር ፖለቲካ መሆን የለበትም። ግን አንዳንዴ አርቆ ማሰብ ያስፈልጋል ብዬ ነው። አርቀሽ አስበሽ ልብሽ ውልቅ ብሏል! በሉኛ! ይሁን እተወዋለሁ።\nግን እውነቴን ነው፤ አትጡ! አግኙ። ለምን? በትራንስፖርት ማጣትና ማግኘት መካከል ያለውን ሰፊ ልዩነት ስትመለከቱ ራሳችሁን ታያላችሁ። ባለመኪና ከሆናችሁ ደግሞ እኛን መኪና አልባዎቹን ታዩናላችሁ። ለምሳሌ አሁን በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ቀን ረዥም ዘንዶ የሚያስንቅ ሰልፍ ይዘን አውቶብስ ጥበቃ ላይ ታድመናል።ከስንት አንዴ የሚመጣውን ባስ «ሰለፉ ከእኔ ነው የሚጀምረው» በሚል ንትርክ ጥቂት አቆየነው። ከዚህ ቆይታ በኋላ ሰላማዊና ሰልፋዊ ግፊያ ተደርጎ ተሳፈርን። ማን እንደመረቀኝ ባላውቅም ወንበር አገኘሁ። እማማ አፍሪካ! በየክፍሏ ለወንበር የሚራኮትባት መቼስ ብዙ ነው። ብቻ እድሜው ገፋ ያለ፤ «ኧረ እርስዎ ይቀመጡ» የሚባል ዓይነት ሰው በአካባቢዬ ስላልነበር ተደላድዬ ሃሳቤን ጥዬ ተቀመጥኩ።\nታዲያ ከገባን በኋላ፤ «እዛጋ ተጠጉ…እዚህ ጋር አለፍ በሉ» ልመና ጀመረ፤ ውጪ ያለው ተሰላፊ። «ከዚህ በላይ ወዴት ልጠጋ?» ንጭንጭ ያሰማል ተሳፋሪ። «ቆይ ሰው ሌላ ባስ አይጠብቅም እንዴ? ሞልቶ እያዩት እዚህ ተፋፍኖ ለመሄድ መጋፋት ምንድን ነው?» ይላል፤ ለባሱ መጨረሻኛ ሆኖ የገባው ሰው። ሁሉም ብቻ የየራሱ የሆነ አስተያየት ይሰጣል።ብቻ መሙላት አይቀርም ባሱ ሞልቶ ተንቀሳቀሰ። ልክ ሲንቀሳቀስ ባሱን የተሳፈረ ሁሉ በመስኮቱ አሻግሮ የተሰለፈውን ሰው እያየ ከንፈሩን መምጠጥ ይጀምራል። «በስመ አብ ሰልፍ! አሁን ስንት ሰዓት ነው ይህ ሁሉ ሰው ቤቱ የሚገባው?» ይላል። ተጋፍቶና ተጣልቶ በባሱ የተሳፈረው ሰው፤ ለገፋውና ለታገለው ለጣለውም ሰው መልሶ ያዝናል።እናላችሁ! መቼም ሀብታም ሰው ነው ለምስኪን ደሃ ሲያዝን የሚያምርበት፤ እኛ ቀንቶን የተሳፈርን ሰዎችም ገና ሰልፍ ላይ ላሉት ሀዘን ገባን። እኔም ራሴ አዘንኩ፤ እውነት እላችኋለሁ ሰልፉ ላይ እኔ የነበርኩ እስከማይመስለኝ ድረስ ነው የተሰለፉት ሰዎች ያሳዘኑኝ። አሃ! እኔ አገኘሁኛ! ይሄኔ ይህ ተከታዩ ሃሳብ ብልጭ አለልኝ፤ ለካ መተሳሰባችንን የሰረቀው ድህነት ነው። ብዙ አውቶብስ ቢኖረን ኖሮ፤ መንገዱ ቦርቀቅ ቢልልን ኖሮ፤ ከየምንሠራበትና ከየምንማርበት አፈስ አድርጎ ካሰብነው የሚያደርሰን ባለመኪና ዘመድ ቢሰጠን ኖሮ፤ መንገዱን እንጃ እንጂ ራሱ መኪና ቢኖረን ኖሮ፤ ይሄ ሁሉ ይኖር ነበር? አይኖርም።አትጡ አግኙ…አንጣ እናግኝ ያልኩት ለዚህ ነው። በየትራንስፖርቱ ማንነታችን እየታየ ይመስላል። በዛ ቦታ መታገስ የቻለ ትዕግስቱ፣ በዛ ቦታ መሳደብ የቻለ ድፍረቱ፣ በዛ ቦታ መጋፋት የቻለ ጥንካሬው…ሁሉም ቁልጭ ብሎ ይታያል። በቃ! ሰውን የምታውቀው አብረኸው ረጅም ጉዞ ስትሄድ ነው ምናምን የሚሉት ነገር ተለዋጭና አማራጭ አግኝቷል። ወይም «ጓደኛህን ንገረኝና አንተነትህን ልንገርህ» እንደሚባለው፤ «ረጅም የታክሲ ሰልፍ አብሬአቸው ልሰለፍና ስለሀበሾች እነግርሃለሁ» የሚል ብሂል አያይዞ መናገር ይቻላል።«ሰላምም ቢሆን ፍቅርና አንድነት፤ ሊፍት የሚሰጥ ክፉ ያልገጠመው ደግ ባለመኪና፣ ባዶ ታክሲና አውቶብስ፣ ቅድሚያ ለሴት የሚሉ የታክሲ ተራ አስከባሪዎች፣ ስታረፍዱ የማይቆጣ…በጊዜ ስትወጡ የማይከፋው አለቃ፣ መኪና ገዝቶ የሚሰጥ ዘመድ፣ በምትንቀሳቀሱበት መስመር የሚሠራ የምታውቁት የሚያውቃችሁ ሹፌር ወይ ረዳት…የመሳሰሉትን ሁሉ አግኙ፤ ይስጣችሁ። እንዲሁም ጠላት አንዳንዴ ያስፈልጋልና እርሱንም ጠራርጎ አያሳጣችሁ።» የሰፈራችን መራቂ አባት፤ አባባ፤ የጓደኛችን ጥያቄ ቀልድ እንዳልነበረ ከተረዱ በኋላ ነው እንዲህ መመረቅ የጀመሩት። ሰላም!አዲስ ዘመን ጥር 12/2011ሊድያ ተስፋዬ", "passage_id": "09fbcd487380c53fa976508cb2074e7c" }, { "passage": "የተጠራንበት\nሰዓት እየደረሰ ቢሆንም እስካሁን አልጨረሰችም። ፀጉሯን ስትሰራ፣ ስትለባብስ ከዚያም ስትኳኳል ሰዓቱ ነጉዶ የሙሽሮች መምጫ ደርሷል። መርፈዱን ላሳውቃት ከበር ቆሜ «ኧረ ውጪ» ማለት ከጀመርኩ ደቂቃዎች ተቆጥረዋል። ልጅት ግን የምትጨርስ አልሆነችም፤ አንዱን ለብሳ ጨረሰች ስል «ይሄስ አላማረብኝም» እያለች ሌላውን ታነሳለች። በዚህኛውም ልቧ አይረካም «… ይህ አይሆንም» በሚል ሌላ ፍለጋ ትጀምራለች። ቆሜ መጠበቁ ስላደከመኝ ከአንድ ጥግ ተቀመጥኩ፤ እየቆየች «ጨርሻለሁ …» ትለኛለች። ጥቂትም ሳትቆይ መልሳ «አላማረብኝም» ትላለች፤ በእኔ ዓይን ግን ሁሉም የሚያምርባት ቅንብብ ያለች ቆንጆ ናት። እርሷ ውስጥ ልጅነቴን እመለከታለሁ፣ ለዛ እና ወዘናዬን ወደ እርሷ ያጋባሁ ይመስለኛል። ሰዎች «ቁርጥ አንቺን የመሰለች…» ይሉኛል፤ እኔም ከአባቷ ስሙን ብቻ ከመጋራት በቀር፤ ሁለመናዋ የእኔ ወጣትነት እንዳለበት ነው የሚታየኝ። አሁን አንጋፋነቴ ማርፈዴን አስታወሰኝ እንጂ፤ እኔም በእርሷ እድሜ የሚያሳስበኝ ማማሬ ብቻ ነበር። ቁንጅት ብሎ መታየቱን፣ የሰዎችን ቀልብ መሳቡን፣ ከእኩዮች ጋር የስርቆሽ መተያየቱን፣ መጠቃቀስና መጎነታተሉን፣ መግደርደርና መሽኮርመሙን … ከየትኛውም ጉዳይ በላይ ቦታ የምሰጣቸው ነገሮች ነበሩ። ዕድሜ እያሳሳቀ እንደ ደራሽ ይዞኝ ሳይፈተለክ በፊት፤ ለእኔ የጊዜ ትርጉሙ ከውበት ጋር የተያያዘ ነበር። ከቤት ለመውጣት የሚፈጅብኝ ጊዜም አንድ ሰው ጉዳዩን የሚያጠናቅቅበት ነው። እናቴ ከአንድ ቦታ ይዛኝ ለመሄድ ስታስብ ማርፈዴ ስለማይቀር ቀድማ ታስነሳኝ እንደነበር አስታውሳለሁ። እኔም ደርሶብኛልና የዛሬዋ የልጄ መዘግየት ምክንያቱ አልጠፋኝም፤ ያው በትልልቅ ሰርግ መሃል ትንንሽ ሰርግ አይጠፋም የሚለውን ብሂል ተከትሎ መሆኑ አይቀርም። በየአጋጣሚው እንዲህ መሆኑበእድሜዋ የሚጠበቅ ነው። ታሪክ\nራሱን ይደግማል ይባል የለ፤ እኔም ወደ ትዳር ከመግባቴ በፊት የሆንኩት ትዝ አለኝ። የተዋደደ ሁሉ አብሮ ባይኖር እንኳ ጊዜያዊ ስሜቱ ግን አንዳች ደስታን ይሰጣል። እንዲህ እንደዛሬው እድሜ ቀዝቀዝ ማለት ሲጀምርም ለልባችን ሙቀት መፍጠሩ አይቀሬ ነው። ነገሩ የሆነው እኩያዬ የሆነች አንዲት ዘመዴ መዳሯን ተከትሎ ነው። ሰፈራችን ከሙሽሪት መንደር ብዙም ያልራቀ በመሆኑ፤ ወዲህም ሥራ ለማገዝ፣ ሰርጉን ለማድመቅ፣ ሙሽሪትን እንሶስላ ለመቀባትም፣… መመላለሴ አልቀረም። አመሻሹ ላይም እኛ ሴቶቹ ተሰባስበን «… ሙሽርዬ አይበልሽ ከፋ ሁሉም ያገባል በየወረፋ» እያልን እንጨፍራለን። ከእኛ አንጻር ደግሞ ሰብሰብ ብለው «ሃይሎጋ» ከሚሉት ጎረምሶች አንዱ በዓይን ጎብኘት ሲያደርገኝ ይታወቀኛል። አሁን ከትዝታዬ ማህደር በቀር ወዴት እንዳለ የማላውቀው ወጣት፤ ደማም በመሆኑ ሰርቆ ሲያየኝ ከመከፋት ይልቅ ደስታ ተሰምቶኝም ነበር። የሙሽሪት\nጎረቤት በመሆኑም ሲወጣ እና ሲገባ ቃል ሳናወጣ በዓይን መነጋገሩ እና መጠቃቀሱን ቀጠልን። ታዲያ በሰርጉ ቀን ኃፍረታችን ለቆን ለራሳችን ጥንስስ እንነሳ ይሆናል በሚል ዝግጅቴንየጀመርኩት ከቀናት በፊት ነበር። የምሰራው ሹሩባ፣ የምዋብበት አምባር፣ የምደምቅበት ኩል፣ የምለብሰው ሸማ፣ የምቀባው ሽቶ፣ … ሁሉ ሃሳብ ሆኖብኝ ቆየ። እንዳይደርስ የለም በዕለቱ፤ አሁን ልጄ እንደምታደርገው ሁሉ እናቴን «ጨርሻለሁ…» እያልኩ ሳስጠብቃት ቆይቼ «ያምርብኛል» ባልኩት ራሴን አሰማምሬ ወጣሁ። እናቴ በማርፈዴ እየተቆጣችኝ መንገዳችንን ቀጠልን። እንደ\nዛሬው ድንጋይ ያልተነጠፈበት መንገድ በበልግ ዝናብ መሬቱ የረሰረሰ በመሆኑ ጸዓዳው ልብሴ እንዳይቆሽሽ በጥንቃቄ ነበር የምጓዘው። ግን ምን ዋጋ አለው፤ ከሰርጉ ቤት ለመድረስ ጥቂት ሲቀረን አንድ መኪና፤ መሬቱ ላይ የታቆረውን ውሃ እንደጸበል አጠመቀን። እንዲያ ያለ እንከን የተዘጋጀሁበት ልብስ፣ ያደመቀኝ ጸጉሬ፣ የተኳኳለው ገጼ፣ … ሁሉ በጭቃማው ውሃ ተሸፈነ። ጥፋት አድራሹ መኪናም አለፍ ብሎን ከቆመ በኋላ የሾፌሩ በር ተከፈተ፤ እናቴም ለቁጣ ወገቧን ይዛ አንገቷን ትሰብቅ ጀመር። ለካስ እንዲያ አምሬ እንዲያየኝ ስኳኳልለት የቆየሁት ወጣት፤ ሾፌር ኖሮ ከመኪናው ሲወርድ አንድ ሆነ።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 28/2011ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "c6690e44c3b00939dcb35d30d4515b88" }, { "passage": " ኧሯ! እንዴት ሆኖ እንዴት ሆኖ እኛንማ አይደፍርም! ብለን ነበር ደፈረን። በሩቅ ሆኖ የሰማነው ዜና ገስግሶ መጥቶ አጠገባችን ከደረሰ የወራት እድሜን አስቆጠረ። በሰው ሀገር ሲነገር፤ ሲወራ እኛ ዘንድ የማይደርስ መስሎን ተዘናግተንማል። እኛ ሀገር አይገባም ፤ ጥቁሮችን አይነካም በማለት እራሳችንን በማይሆን ተስፋ እያታለልን ቆይተናል። ቁርጡ ቀን ደርሶ በሀገራችን የቫይረሱን መገኘት እውነታ ሲነገር ሰምተን ላለማመን ያመነታነው ስንቶቻችን እንሆን? ታዲያ አስፈሪ ዝናውን አስቀድሞ በርካቶቻችንን ኮርኩሮ ሃሳብ በማሰንዘር ፤ ከሃሳባችን መደምደሚያ ሳንደርስ ከች ብሎ ጉድ ያደረገን እሱም አይደል ወይ ኮሮና። ስለ ቫይረሱ ያለን እውቀት እንደ ግንዛቤ የሚለያይ ነው። አንዳንዱ ህይወቱ ግድ ሰጥቶ ለራሱ ኖሮ ሌላውን ለማትረፍ የሚጥረው ነው። ሌላው ደግሞ ለራሱም ሆነ ለሌላው ግድ የሌለው ቢነገረው ቢዘከር ሰምቶ እንዳልሰማ አይቶ እንዳላየ የሚሆን ነው። ራሱን በመኖርና ባለመኖር መካከል ከቶ በደመነፍስ እንደሚኖር ሰው ቫይረሱ ምንም እንደሚያመጣ የሚናገርም ዛሬ ድረስ አልጠፋም። ሰውን ለማዳን ራሱን ያልሰሰተውን ተመልክተን እሰየው በርታልን ጓድ እንዳላልን ሁላ ፤ በግዴለሽነት የሚኖረውን ደግሞ በትዝብት እያየን ከማለፍ ለመምከር የሞከርን እንኖራለን። የሚጠነቀቀውም ሆነ ግዴለሹ፤ የአንዱ ጤንነት የሌላው መኖር ዋስትና ነው ። የሰው ልጅ በምድር ላይ የሚኖረው ለራሱ ብቻ አይደለም፤ ለሌሎችም ነው። አንዱ ከሌለ የሌላው መኖር ትርጉም አልባ ነውና ። ህይወት ጣዕም የሚኖራት በመኖር ነው። መኖር ትርጉሟ ሙሉ የሚሆነው አንዳችን ለአንዳችን በሚኖረን አብሮነት ፤ መረዳዳትና መደጋገፍ ነው። ለዚህ ዋንኛው ደግም የኔ ጤንነት ሲጠበቅ የጎረቤት፤ የአካባቢዬ ፤ የሀገር፤ የሁሉም ጤና መሆን ግድ ይላል ። ታዲያ አለመታዘዛችን ከምን የመነጨ ይሆን? ለመኖር ራሳችን ከመጠበቅ ሌላው አማራጭ ይኖር ይሆን። ታላላቆቻችን፤ አባቶቻችን ማድመጥ፤ መደማመጣችንን እሴቶቻችንን ማን ነጠቀን? ለምን ረሳነው? በራሳችን ፈርደን በሌሎችም የመጨከን አባዜን ከየት አመጣነው? የሰውን ልጅ ሳይመርጥ ከምድረ ገጽ እያጠፋ ያለው ይህ ጨካኝ ቫይረስን እንዴት ልባችንን ሊያደነድን ቻለ። ሰው የሚችለውን ነውና የሚታዘዘው እራሳችንን እንመርምር ለመለወጥ መትጋት አለብን። የማንችለውን ትተን የምንችለውን መምረጥ ፤ ዛሬን መኖር ለነገ ተስፋ ነው። የእኛ ጥንቃቄ ለወገን መሆኑ ማመን አለብን። ነጭ፤ ጥቁር፤ ዘመድ፤ ባዕድ እያልን ራሳችንን ሳንከፋፈል ከስጋት ራስን ጠብቆ በማስመለጥ አብሮ ማምለጥ ይቻላልና ነው። ካለበለዚያ ግን “ከኑግ ጋር ያለህ ሰሊጥ አብረህ ተወቀጥ” ከሆነ ጉዳይ የታሪክ ተወቃሽ መሆናችን አይቀርም። መቼም ቫይረስ በሀገራችን ከተከሰተ ማግስት ጀምሮ ብዙ ለውጦችን፣ አዳዲስ ነገሮችን ታዝበናል። ለመከላከል የሚረዱን እጅን በሳሙና ቶሎ ቶሎ በደንብ መታጠብን ፤ ፊት በእጅ አለመንካት፤ አካላዊ ርቀትን መጠበቅ በዋናነት ከህክምና ባለሙያዎች የሚሰጡትን ምክሮች ተግባራዊ ለማድረግ ተሞክሯል። ለራሱ ያለ ራሱ ተጠንቅቆ ሌላውን ለማዳን እየጣረ እየተጋ ታይቷል። ይገርማችኋል! ለዛሬ ትዝብቴ መነሻ የሆኑት ይህንን የሰሙ የማይመስሉ የሰፈሬ ወጣቶች ናቸው። በከተማችን የሚገኙ በርካታ ወጣቶች በጎ ተግባራት ላይ በመሳተፍ ከወገናቸው ጎን የቆሙበትን አይተናል፤ ሰምተናልም። የነገ የሀገሪቱ ተስፋዎች መሆናቸውንም አስመስክረዋል። የኔ ሰፈር ወጣቶች ግን ቫይረስ መኖሩን አልሰሙም!! በአንድ ላይ በጋራ በመሆን መጠጥ ይጠጣሉ ፤ ጫት ይቅማሉ፤ መንገድ ዳር ተዛዝለው በሚባል ሁኔታ ሆነው ያወጋሉ። የቫይረሱ የተከሰተ ሰሞን አልነበሩም፤ ጠፍተው ነበር ። እሰየው አልኩኝ፤ ራሳቸውን ለመከላከል ወስነው ቤት ለመቀመጥ የከተሙ መስሎኝ። አልሰሜን ግባ በለው አሉ። ለካ የቦታ ለውጥ በማድረግ ከሰው አይን ዞር ብለው ነበር። ታዲያ እኔም የግዴታዬን ለመወጣት ወደእነሱ አመራሁ። በእግዜር ስላምታ ተቀላቀልኳቸው። ስለቫይረሱ አስከፊነት የነሱ መጠንቀቅ ለሚወዷቸው ሁሉ ፤ ለወላጆቻቸው፤ ለሰፈራችን ሁሉም እንደሆነ አስረዳኋቸው። ለማዳመጥ ፈቃደኛ ባልሆነ ጆሮ ሰሙኝ ። መልስ አልሰጡኝም። አንደኛው እሺ አለኝ ቀልድ በተሞላበት ፌዝ ። በእውነት አመመኝ። ለምን አትተሳሰቡም እርስ በርሳችሁ እንኳን አትዋደዱም አልኳቸው። እሺ ሌላው ቢቀርስ ለምን አትታዘዙም አልኩት? አቀርቀረው ስልካቸውን መጎርጎር ተያያዙት ። ትቻቸው ስሄድ መታዘዝ ከመሰዋዕትነት ይበልጣል አልኩ ሰምተውኛል፤ ግን ዝምታን መርጠዋል። ለብቻዬ እንዳስብበት የቤት ስራ የሰጡኝ ወጣቶች ዞር ብዬ በማየት ጉዞዬን በሃሳብ ቀጠልኩ። “ለምን ይሆን የተከለከለ ነገር የሚያምረን?” አልኩኝ ለራሴ ። ወደ አፈጣጣራችን ተመለስኩ ለካ አዳምን ከገነት ያስባረረው አታድርግ የተባለው በማድረጉ ነው። እኛም ዛሬ ለመቅጽበት ለሚያልፍ ቀን ብለን አታደርጉ የተባልነውን በማድረግ በጎ ተግባር እንደፈጸመ ጀግና በየአደባባዩ እንታያለን። ማንንም መስማት አንፈልገም፤ እራሳችንን ብቻ ካልሆነ በስተቀር ፤ ራሳችንን በቅጡ አውቀን ብናዳምጥ ጥሩ ነው። በዓለም ያሉ ሀገራት እንደኛ አይነት ተው ተብለው የማይሰሙ ዜጎች በመያዛቸው ነው። ዛሬ ለመስማት የሚቀፍ ዜና እየሰማን የምንገኘው። እነሱ ቢጸጸቱም ወደ ኋላ ሊመልሱት የማይችሉት ነገር ሆኖባቸዋል። ለኛ ትምህርት መሆን አለባቸው። እኛ ላይ በቅድሚያ ያልተፈጸመብን መሆኑን እያመሰገን ከሰማነው፣ ካየነው ቀድሞ መገኘት የግድ ይለናል። ጊዜው ፈጣን ነው ፤ ዛሬ ላይ እንኳን ቆመን ነገን ለማየት በተሰጠን መልካም እድል መጠቀም አለብን። ያለመታዘዛችን ዋጋ እንዳያስከፍል መበርታት ያስፈልገናል። ለዚህም ቀኑ ዛሬ እንጂ ነገ አይደለም። የቤት ስራን ከወዲሁ በመፈጸም ለወገን አለኝታነታችን በመግለጽ እራስን ሆኖ መገኘት፤ ታዝዞ መታዘብ ማስተማር ፤ቀዳሚ ሆኖ ለሌሎች አርአያ በመሆን መስመሩን በመጥረግ ከመስመሩ ያፈነገጡትን መመለስ ይገባል። የዛሬ ሁላችንም አብሮነትና ትብብርን አንዱ ለአንዱ መኖር ግድ ይሆናል። ታላላቆቻችንን በማስቀደም እነሱን አድምጠን ከዚህ አስከፊ አደጋ ማምለጥ ይኖርብናል። አብረን ስንሆን፣ ስንተባበር፣ ስንደማምጥ፤ ስንረዳዳ ያምርብናል። ባህሩን አቋርጠን መሻገር እንችላለን። የሰው ልጆችን እየጠረገ ያለውን አስከፊ ወረርሽን ለመከላከል ወኔ አቅም ጉልበት ይኖረናልና ። መጪው ጊዜ መልካም ዜና የምንሰማበት ጊዜ ይሁንልን ። አዲስ ዘመን ሚያዝያ 19/2012 ወርቅነሽ ደምሰው", "passage_id": "d7ff0b5545f060e154c21078eb959f90" } ]
444c85a42ceb886c3d1ff7e5bfb4d6a4
a7908648a8118009f4808a922feb8dbb
ዶክተር ካትሪን ሀምሊን
   • “የኢትዮጵያ እናቶች እናት” በመባል የሚታወቁና የረጅም አመት የማህጸን ሀኪም በመሆን ያገለገሉ ናቸው። •እ.አ.አ በ1924 ሲድኒ አውስትራሊያ ውስጥ ተወለዱ።•እ.አ.አ በ1959 ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ እቅዳቸው ሦስት ሳምንት የመቆየት ብቻ ቢሆንም በርካታ ሴቶች ህክምና እንደሚያስፈልጋቸው በመገንዘብ ከመሄድ ይልቅ መቆየትን መረጡ።•እ.አ.አ በ1974 አዲስ አበባ ውስጥ የመጀመሪያ የሆነውን የፌስቱላ ሆስፒታል አሰሩ።•ይህ ሆስፒታል ከ45 ሺ በላይ ለሆኑ ኢትዮጵያውያን ሴቶችን ከህመም ፈውሶ መደበኛ ህይወታቸውን እንዲመሩ አድርጓል።•ዶክተር ካትሪን ሴቶችን የመርዳት ተግባራቸው ሴቶችን በማከም ብቻ የተገደበ አልነበረም። አዋላጅ ነርሶችን የማሰልጠን ሕልማቸውን ለማሳካት በ2000 ዓ.ም የሐምሊን አዋላጅ ነርሶች ማሰልጠኛ ኮሌጅ እንዲቋቋም በማድረግ በርካታ ባለሙያዎች በየገጠሩ እንዲሰማሩ ማድረግ ችለዋል።•ለ60 አመት በኢትዮጵያ የፌስቱላ ህሙማንን በማከም ሰርተዋል።•ዶክተር ካትሪን ሃምሊን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያለ እድሜ ጋብቻንና የተራዘመ ምጥን ተከትሎ በሚከሰት ሽንትንና ሰገራን መቆጣጠር ያለመቻል ችግር ይሰቃዩ የነበሩ በርካታ ሺህ ኢትዮጵያዊያንን ሲታደጉ ኖረዋል።•ዶክተር ካትሪን የአዲስ አበባውን ጨምሮ በሃገሪቱ ስድስት የሃምሊን ፌስቱላ ሆስፒታሎችን በማቋቋም ሴቶች ከሚገጥማቸው የፌስቱላ በሽታ በነጻ ታክመው እንዲወጡ ከማድረግ ባሻገር ይደርስባቸው ከነበረ የመገለልና የስነ ልቦና ስብራት መታደግ ላይ ሰርተዋል።• በበጎ ተግባር ላይ ተሰማርተው የበርካታ ኢትዮጵያውያን ሴቶች ችግርን የቀረፉት ዶክተር ካትሪን ሐምሊን የኢትዮጵያ የክብር ዜግነትና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ የክብር ዶክትሬት ተበርክቶላቸዋል።• ዶክተር ካትሪን ሐምሊን በዋጋ ለማይተመነው አበርክቷቸው በርካታ ሽልማቶችንና ክብሮችን ተቀዳጅተዋል። ከነዚህም መካከል• የቀዳማዊ ኃይለስለሴ የሰብአዊነት ሽልማት • የኦርደር ኦፍ አውስትራሊያ ሽልማት• የቀዶ ጥገና ሀኪሞች ኮሌጅ የክብር ወርቅ ሜዳሊያ ሽልማት• የአውስትራሊያ ከፍተኛ ብሄራዊ ሽልማት • አለም አቀፍ የጤና ምክር ቤት የላቀ አፈፃፀም ሽልማት• የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስነ ህዝብ ሽልማት• የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአውስትራሊያ ማኅበር ሽልማት• የሮተሪ ኢንተርናሽናል አለም አቀፍ የሰላም ሽልማት• የእንግሊዝ ህክምና ማህበር ሽልማት• የሲዲኒ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ሽልማት• የአውስትራሊያና ኒው ዚላንድ ጦር ዘማቾች የሰላም ሽልማት• የታላቁ የቅድስ ጊዮርጊስ የላቀ የወርቅ ሜዳሊያ ሽልማት• የዞንታ አለም አቀፍ ሽልማት• የኤደንብራ የቀዶ ጥገና ሐኪሞች ኮሌጅ የክብር ሽልማት• የሰዎች ለሰዎች ድርጅት የህይወት ዘመን ሽልማት• የ2009 ዓ.ም የበጎ ሰው ሽልማት ከብዙ በጥቂቱ ተጠቃሾች ናቸው።• ከነዚህ ሽልማቶች በተጨማሪ ካትሪን ሐምሊን እ.አ.አ የ1999ና የ2004 የኖቤል ሽልማት እጩ ሆነው ቀርበው ነበር።• እ.አ.አ በ2009 ‹‹ተለዋጭ ኖቤል›› በመባል የሚታወቀውና አስቸኳይ ምላሽ ለሚሹ አለም አቀፍ ፈተናዎች ተግባራዊና ተምሳሌታዊ የሆኑ መፍትሔዎችን ላፈለቁ አካላት የሚሰጠው የ‹‹ራይት ላይብሊሁድ ሽልማት ›› ተበርክቶላቸዋል።• ባለፈው ዓመትም ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ አህመድ ለሀገራችን በተለይም በፊስቱላ የተጠቁ ሴቶችን ከችግራቸው በመፈወስ ለሰሩት ስራ ሽልማት አበርክተውላቸዋል።• ዶክተር ካትሪን ሀምሊን በ96 አመታቸው መጋቢት 14 ቀን 2012 ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል። ስርዓተ ቀብራቸውም በጳውሎስ ወጴጥሮስ ቤተክርስቲያን ተፈፅሟል።አዲስ ዘመን መጋቢት 20 ቀን 2012 ዓ.ም
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=29379
[ { "passage": "አፍሪካዊያን ዓለም በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ የተጨነቀችበትን ይህን ጊዜ በማሰብ፤ ሌሎችን ለመርዳት አስገራሚ በጎ ተግባራት እያከናወኑ ነው። ከእነዚህ ጀግኖች መካከል ስድስቱን እናስተዋውቃችሁ።መኖሪያ ቤቷን ለለይቶ ማቆያነት የሰጠችው ኢትዮጵያዊት ድምጻዊትከፋሽን ዲዛነርነት የህክምና ገዋን ወደ መስፋት የተሻገሩት ሊቢያዊያንየአረጋዊያን ቤትን በአበባ ያስጌጡት አበባ አምራቾችየቤት ኪራይ ነጻ ያደረጉ ኬንያዊ ቤት አከራይበኦንላይን የዳንስ ትርኢት የምታቀርበዋ ቱኒዚያዊትለአድናቂዎቹ የምግብ የከፈለው ናይጀሪያዊው እግር ኳስ ተጫዋችአንጋፋዋ ድምጻዊት ሐመልማል አባተ መኖሪያ ቤቷን ለለይቶ ማቆያነት እንዲውል አበርክታለች። ባለፈው ወር መንግሥት ማንኛውም ወደ አገር ውስጥ የሚገባ ሰው በራሱ ወጪ ራሱን ለ14 ቀናት ያህል በሆቴል ውስጥ ለይቶ እንዲያቆይ ውሳኔ አስተላልፎ ነበር።• ይህም ድምጻዊቷን ያሳሰበ ጉዳይ ነበር፤ ውሳኔው ገንዘብ ላላቸው የውጭ ዜጎች ይሁን፤ ገንዘብ ለሌላቸውስ በሚል ሀሳብ ገብቷት ነበር። በመሆኑም በአዲስ አበባ የሚገኘውን መኖሪያ ቤቷ ለለይቶ ማቆያ እንዲሆን አበረክታለች።ሐመልማል ቤታቸውንና የንግድ ቦታቸውን ለለይቶ ማቆያነት ከሰጡ ኢትዮጵያዊያን መካከል አንዷ ናት።ሊቢያዊያኑ የፋሽን ዲዛይነር የፋሽን ልብስ ከመስራት ወደ የህክምና ገዋን ማምረት ተሸጋግረዋል።በሊቢያ መዲና ትሪፖሊ በሚገኘው የፋሽን ልብስ ማምረቻ፤ ስድስቱ ሴቶች ለህክምና ባለሙያዎች የሚሆን ራስን መጠበቂያ አልባሳት መስፋቱን ተያይዘውታል።ሁሉም ሴቶች በጎ ፈቃደኞች ሲሆኑ አንዳንዴ በሥራ መብዛት ምክንያት እዚያው ፋብሪካው ውስጥ ይተኛሉ።በጎ ፈቃደኞቹ እስካሁን 50 የሚሆኑ የህክምና አልባሳት የሰሩ ሲሆን ሁለተኛ ዙር ተጨማሪ ለማምረት እየሰሩ ነው።ወረርሽኙ በርካታ ሠርጎችና ሌሎች ክንውኖች እንዲሰረዙ ምክንያት ሆኗል። በዚህም ምክንያት የአበባ ምርቶች ከጥቅም ውጪ እንዲሆኑ በማድረግ መጥፎ አሻራ አሳርፏል።ይሁን እንጅ በደቡብ አፍሪካ ፓርል የሚገኙ አበባ ሻጮች በመሰባሰብ ይህንን ጨፍጋጋ ጊዜ ትንሽም ቢሆን ብርሃን ለመስጠት እየሰሩ ነው።ከአንድ የአበባ እርሻ የተበረከተላቸውን 600 አበቦች የአዛውንቶችን ቤት የውጪ ግድግዳ እያስጌጡበት ነው።የደቡብ አፍሪካ ነዋሪዎች ወረርሽኙን ለመከላከል በተጣለው የእንቅስቃሴ ገደብ ቤታቸው ከከተቱ ሁለት ሳምንታት አልፏቸዋል።በኬንያ 34 ተከራዮች ያሉት የቤት ባለቤት ተከራዮች መጋቢትና ሚያዚያ ወርን ተከራዮች ኪራይ እንዳይከፍሉ ወስነዋል። ይህን ውሳኔ ያሳለፉት የኮሮናቫረስ ወረርሽኝ በርካቶችን ለገንዘብ ችግር ስለዳረጋቸው ነው ብለዋል።ማይክል ሙኔኔ የተባሉት እኝህ ባለሃብት በኬንያ ምዕራባዊ ግዛት እያንዳንዳቸው 3 ሺህ የኬንያ ሽልንግ [ከ250 ዶላር በላይ] የሚከፈልባቸው 28 አፓርትመንቶች አሏቸው።• ከዚህም በተጨማሪ በወር 5 ሺህ ሽልንግ የሚከፈልባቸው ስድስት የንግድ ቤቶችም ባለቤት ናቸው። ተከራዮች ይህንን ካልከፈሉ በወር ከ2 ሺህ ዶላር በላይ ገንዘብ ያጣሉ። ይህንን ነው በነጻ የሰጡት።\"በዚህ ጊዜ ከእነርሱ ጋር መስራትና መረዳዳት ያስፈልጋል\" ብለዋል።ቱኒዚያዊቷ ዳንሰኛ ኔርሚን ስፋር በእንቅስቃሴ ገደብ ቤት ውስጥ ተዘግተው ለሚገኙ የሰሜን አፍሪካ ሕዝቦች ዳንስ በማቅረብ ታዝናናቸዋለች።ከቤቷ ሆና የምታስተላልፈውን የዳንስ ትርኢትን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች በፌስቡክ ተከታትለውታል።• ዳንሰኛዋ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ \"እናንተ ቤታችሁ ቆዩ፤ እኔ እደንስላችኋለሁ\" የሚል ዘመቻ ከፍታ ነበር።የናይጄሪያ ፕሪሚየር ዲቪዥን እግር ኳስ ተጨዋች ለአራት አድናቂዎቹ በወረርሽኙ ጊዜ ምግብ መመገብ የሚያስችላቸውን ገንዘብ ሰጥቷቸዋል።የፕላቶ ዩናይትድ ግብ ጠባቂ ቺኔዱ አኖዜ፤ ለአራቱ አድናቂዎቹ ለእያንዳንዳቸው 5 ሺህ የናይጄሪያ ናይራ (14 ዶላር) ለግሷል።ይህም በጣም ትንሽ ልገሳ ነው ብሏል።", "passage_id": "aa1fc074967d7b20cd42c00fc954093b" }, { "passage": " ልክ እንደሰዎች ሁሉ እምባ አውጥተው አያልቅሱ እንጂ እንስሳትም የሚወዱትን ሲያጡ ሀዘን ይሰማቸዋል። ልጇን በሞት ያጣች እናት በሃዘን እንደምትንገበገብ ሁሉ እንስሳትም የአብራካቸውን ክፋይ በሞት ሲነጠቁ ያዝናሉ። በእንዲህ አይነቱ አጋጣሚ ታዲያ የቤት እንስሳት በተለይም ውሻና ድመት መሰሎቻቸውን እንጂ ሌላ አያስጠጉም። ይሁን እንጂ በደቡብ አፍሪካ አንዲት ሙጭሊቶቿን በሞት የተነጠቀች ድመት አራት የውሻ ቡችሎችን በማስጠጋት ከደረሰባት ሀዘን ለጊዜውም ቢሆን አገግማለች ሲል ሚረር ኦንላይን ከሰሞኑ ዘግቧል። እንደዘገባው ከሆነ፤ ካትሪን የተሰኘቸው ድመት ለመወለድ በተቃረበች ወቅት በቆሻሻ ውስጥ ተጥላ ነበር። በዚያም ትወልድና ሙጭሊቶቿ በደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ወደ ሚገኝ አንድ የእንስሳት መንከባከቢያ ማእከል ይወሰዳሉ። ይሁንና ሙጭሊቶቹን ከሞት ማትረፍ አልተቻለም። ታዲያ በዚህ ሀዘን የገባት ድመት ብቸኛ ትሆናለች፤\nአብዛኛውን ጊዜዋንም በማልቀስ\nማሳለፍ ትጀምራለች። ይሁን እንጂ አራት ቡችሎች የእንስሳት\nመጠለያ ማእከሉን ድምበር ተሻግረው በመግባታቸው\nነገሮች ይቀየራሉ፤ ካትሪን ሶስት ሳምንት የሆናቸውን ቡችሎች እንደ ልጆቿ በማየት እየላሰቻቸው\nማጥባት ጀምራለች፤ በነዚህ ቡችሎች ምክንያት\nለጊዜውም ቢሆን ሀዘኗንም\nመሻር ችላለች ይለናል ዘገባው። አዲስ ዘመን  ታኅሣሥ 28 / 2012 ዓ.ም አስናቀ ፀጋዬ", "passage_id": "2151da1fb26552bcad664a04949745d8" }, { "passage": "የወ/ሮ ዳፌን ሻህ ከልጃቸው ዌስሊ ሻህ ጋር\n\nአሮጊቷ እናቴ ወደ ሆስፒታል በተወሰደች ጊዜ፣ በተለይም በኮሮናቫይረስ መያዟን ስሰማ አልዋሻችሁም ለመጥፎ ዜና ራሴን እያዘጋጀሁ ነበር።\n\nአምቡላንሱ መጥቶ ሲወስዳት እውነት ለመናገር በድጋሚ አያታለሁ ሁሉ አላልኩም ነበር።\n\nሐኪሞቹም ቢሆኑ 99 ዓመት ሊደፍን ወራት የቀሩት ሰው ቫይረሱን ድል ሲመታ አይተው የሚያውቁ አይመስለኝም።\n\nእናቴ ዳፌን መጀመርያ ወደ ናይንዌልስ ሆስፒታል ነበር የተወሰደችው። እዚያም አንድ ሳምንት ለሚሆን ጊዜ የሆስፒታል አልጋ ይዛ ቆይታለች። ከትናንት ወዲያ ሰኞ ለታ ነው ከሆስፒታሉ የወጣችው።\n\nበዚያ ሆስፒታል ምን ተአምር ተፈጥሮ እንደዳነች ለኔም ትንግርት ነው። \n\nየትንፋሽ መርጃ ቬንትሌተር እንኳ አላስፈለጋትም ነው ያሉኝ ሐኪሞቹ። ከሆስፒታሉ ስትወጣ ግን አተነፋፈሷ ትክክል ነበር ማለት አልችልም።\n\nየስኮትላንድ የብሔራዊ ጤና አገልግሎት መኮንኖች ሁልጊዜም ምስጉን ናቸው። አሁን ግን የማይታመኑ ነው የሆኑብኝ።\n\nእናቴን ላለፉት 20 ዓመታት ተንከባክቢያታለሁ። ያም ማለት አባቴ ከሞተ ጀምሮ እንደማለት ነው፡፡ ለዚህን ሁሉ ጊዜ ጤናዋ እክል አልነበረበትም አልልም። ሆኖም የከፋ ነገር ገጥሟት አያውቅም።\n\nበቅርቡ ግን ደረቅ ሳል ስትስልና ትኩሳቷ ሲጨምር ይሄ ነገር ምነድነው ብዬ ሐኪሞች ዘንድ ደወልኩኝ።\n\nየጠረጠርኩት አንዳች የባክቴሪያ ኢንፌክሽን አግኝቷት ይሆናል ብዬ ነው፤ በቃ አንቲባዮቲክ ሰጥተዋት ትድናለች ስል አሰብኩ።\n\nሆኖም አንቲባዮቲክ ወስዳ ሳይሻላት ሲቀር ይሄ ነገር ምንድነው ብዬ ወደ ሆስፒታል ወሰድኳት።\n\nከደረቅ ሳሉ በተጨማሪ የምግብ ፍላጎቷ እልም ብሎ ጠፍቶ ነበር። በዚያ ላይ ድካም ይሰማታል።\n\nእናቴ በመጪው ሐምሌ ወር ላይ 99 ዓመቷን ትደፍናለች። እንደምንም 100 ዓመት ሞልቷት ከግርማዊነታቸው ንግሥት ኤልዛቤጥ 2ኛ የቴሌግራም የደስታ መግለጫ እንዲላክላት ከልቤ እመኛለሁ።\n\nኮቪድ ሕይወቷን ቢያሳጣት ኖሮ ሐዘኔ ቅጥ ያጣ ይሆን ነበር፤ ምክንያቱም እርሷ ጠንካራ ሴት እንደሆነች አውቃለሁ፡፡ ጤንነቷም ለክፉ የሚሰጥም አልነበረም፡፡ በዚህ ሁኔታ ብትሞት ትልቅ ሐዘን ላይ ነበር የምወድቀው።\n\nእርሷ አልጋ በያዘችበት ሆስፒታል አንድም ሰው እንዲጠይቃት አይፈቀድም ነበር። መጀመርያ አካባቢ እናቴ ምን እየሆነ እንዳለ የገባትም አይመስለኝም። \n\n\"ልጄ ምነው ቸል አለኝ፤ እንዴት ታምሜ አይጠይቀኝም\" ስትል ተገርማ ነበር። በናይንዌልስ ሆስፒታል ነርሶቹ እንደነገሩኝ \"እናትህ ደጋግማ ልጄ የታለ? ልጄን ጥሩልኝ!\" ትል ነበር።\n\nየጤና ረዳቶቹ ነገሩን ሊያስረዷት ቢሞክሩም ልትሰማቸው የፈቀደች አይመስለኝም።\n\nበቀን ቢያንስ አራት ጊዜ ወደ ሆስፒታሉ እደውላለሁ። በእውነት የጤና ባለሞያዎቹን እንዴት ማመስገን እንዳለብኝ አላውቅም።\n\nአሁን ይህንን የእናቴን ታሪክ ለሚያነቡ ታማሚዎችም ሆኑ አስታማሚዎች የምለው ነገር አለኝ። \n\n\"ኮሮና ቫይረስ ክፉ ደዌ ነው፤ ይህ ምንም ጥያቄ የለውም፤ ነገር ግን የ98 ዓመት አሮጊቷ እናቴ ድል ነስታዋለች፤ የምን ተስፋ መቁረጥ ነው ታዲያ!\"\n\n ", "passage_id": "f817b206dd44204069a730e75cf1b1b9" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 14 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ የፌስቱላ ሆስፒታል መስራች ዶክተር ካትሪን ሐምሊን የቀብር ስነ ስርዓት ተፈፀመ።የዶክተር ካትሪን ሐምሊን አስከሬን የሽኝት ፕሮግራም በመኖሪያ ቤታቸው ከተደረገ በኋላ የቀብር ስነ ስርዓታቸው በጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን ተፈፅሟል።በስነ ስርዓቱ ላይም የዶክተር ካትሪን ሐምሊን ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች ተገኝተዋል። ዶክተር ካትሪን ሐምሊን በ96 ዓመታቸው መጋቢት 9 ቀን 2012 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ይታወሳል።ዶክተር ካትሪን ሀምሊን ፌስቱላ ኢትዮጵያ የተባለ ግብረሰናይ ድርጅት በማቋቋም ከ60 ዓመታት በላይ የፌስቱላ ህክምናን ሰጥተዋል።በበጎ ተግባር ላይ ተሰማርተው የበርካታ ኢትዮጵያውያን ሴቶች ችግርን የቀረፉት ዶክተር ካትሪን ሐምሊን የኢትዮጵያ የክብር ዜግነት እና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ የክብር ዶክትሬት ተበርክቶላቸዋል።በሳራ መኮንንትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!\nhttps://t.me/fanatelevision", "passage_id": "e3b963ee1cd36c503e4f17804db3f4b9" }, { "passage": "\"ቁጭ ብዬ ነበር የማድረው\" ትላለች። ስትወልድ ከዚህ ሁሉ ችግር እንደምትላቀቅ ብታስብም፣ እንደፍላጎቷ ግን አልሆነላትም ነበር።\n\nመንታ ልጆቿን በየሁለት ሰዓት ልዩነት ማጥባት እና እንደልብ መንቀሳቀስ አለመቻል ችግር ሆነውባት ነበር።\n\nበዚህ አላበቃም ማሕደር \"እኔ በምክንያት እና በውጤት የማምን ነበርኩ፤ በትንሽ ነገር ስሜታዊ አልሆንም ነበር፣ ከወልድኩ በኋላ ግን ማልቀስ እና ሰዎች ለምን አይረዱኝም በማለት ማኩረፍ ጀመርኩ። በተለይም በእናቴ እና በባለቤቴ እናደድ ነበር\" ትላለች።\n\nማህደር አንዲት ሴት ስትወልድ፣ አዲስ የሕይወት ምዕራፍ ስለምትጀምር የተለየ ልምድ ውስጥ ነው የምትገባው በማለት የነበረውን ሁኔታ ትገልፀዋለች።\n\nለዚህ ደግሞ ቤተሰብም ሆነ ሐኪሞች ቀድመው አያዘጋጁንም ስትል የራሰወን ልምድ በመጥቅ ታስረዳለች።\n\nእንቅልፍ ማጣት፣ ስራ ሳይሰሩ ለረዥም ጊዜ መቆየት፣ ከራስ በላይ ለጨቅላዎቹ ትኩረት መስጠት፣ ውጥረቱን ያብሰዋል ትላለች። ማሕደር ያሳለፈችውን ከባድ ጊዜ ስትገልጽም፣ \"ራሴን እጠላ ነበር። በሕይወቴ ተስፋ እቆርጥ ነበር፣ እንዲሁም ልጆቼ ሲያለቅሱ በጣም ስለምናደድ እናቴን 'ነይ ውሰጃቸው' ስል እጠራት ነበር።\"\n\n ይኹን እንጂ እንዲህ ባሕሪዋን የቀየረው ነገር ሴቶች ከወሊድ በኋላ ሊገጥማቸው የሚችል የአእምሮ ድባቴ እንደሆነ ያወቀችው ከሶስት ወር በኋላ ነው።\n\n\"ይህ ነገር ምንድን ነው ብዬ ጉግል ሳደርግ ፖስት ማርተም ዲፕረሺን የሚባል ሕመም እንደሆነ ተረዳሁ። እኔም የዚያ ተጠቂ መሆኔን አወቅሁ\" ስትል ታብራራለች።\n\nይህ ጉዳይ የባህሪ መቀየር ጉዳይ እንዳልሆነ እና እንደ ማንኛውም ዓይነት በሽታ መሆኑን ስታውቅ መጀመሪያ የወሰደችው እርምጃ ራሷን መቀበል እና ከራሷ ጋር ለመታረቅ መሞከር ነበር።\n\nከዚያ በመቀጠል ደግሞ በአካበባቢዋ ለሚገኙ ሰዎች ማስረዳት ነበር። \n\nእንደ ማህደር ገለጻ ይህ ቀላል አልነበረም። ምክንያቱም ትላለች \"በከፍተኛ የስሜት መለዋወጥ ውስጥ ስለነበርኩኝ ችግሬን በአግባቡ ማስረዳት እንኳ አልቻልኩም ነበር።\"\n\nኋላ ላይ ወደ መደበኛ ስራዋ ስትመለስ ከሰዎች ጋር መገናኛት ስትጀምር እና ችግሯን መግለጽ ስትጀምር እየቀለላት መጣ። \n\nከዚህ በኋላ ለትምህርት ከአገር ርቃ ሄደች።\n\n\"ለትምህርት ወደ ውጪ አገር እስከ ምሄድበት ለብቻዬ ጊዜ እስካገኝ ድረስ ተስፋ የመቁረጥ እና ስሜታዊ የመሆን ነገር ቢቀንስም አልጠፋም ነበር።\"\n\nቤተሰቦቿ በአራስነት ጊዜዋ በጣም ተጎድታ ስለነበር ትልቁ ትኩረታቸው እርሷን በምግብ መጠገን ነበር።\n\n\"ስለዚህ ያመጣሁት የባህሪ ለውጥ ብዙም አልታያቸውም። ብዙ ጊዚያቸውን ልጆቹን በመንከባከብ ነበር የሚያሳልፉት።\" ስትል ሁኔታውን ታስታውሳለች።\n\nበተጨማሪ \" ብቻዬን ሆኜ አለቅሳለሁ። ወይ ደግሞ አመመኝ የሚል ምክንያት እሰጣለሁ።\" ያለምክንያት ስታለቅስ ማንም ሊረዳ ት እንደማይቸል የምትናገረው ማሕደር ከባድ ወቅት ማሳለፈን ለቢቢሲ አካፍላለች።\n\nከራስ አልፎ ለሌላ መትረፍ\n\nማሕደር ይህን ያሳለፈችውን ጊዜ የማህበራዊ ሚዲያ ላይ ካሉ ጓደኞቿ ጋር ቡድን በመፍጠር ማካፈል ጀመረች።\n\nያኔ ሰዎች ስልክሽን ስጪን። ስለዚህ ጉዳይ ልናዋራሽ እንፈልጋለን በማለት አጭር መልዕክት ይሉኩላት ጀመር።\n\nከእነዚህ ጓደኞቿ ጋር በማህበራዊ ሚዲያ በምታደርገው ውይይት ብዙዎቸ ወንዶች ይህንን ጉዳይ ከእነ አካቴው ሰምተውት እንደማያውቁት፣ ገሚሶቹ ሴቶችም እውቀቱ እንደሌላቸው፣ ሌሎቹ ደግሞ ጉዳዩ ቢገጥማቸው እንኳ የችግሩ ምንነት እንደማይረዱት ግንዛቤውን አገኘች።\n\n\"በአጭር መልዕክት ካዋሩኝ ሰዎች አንዷ 'ባለቤቴን ላየው አልፈልግም።' ሌላዋ ደግሞ 'ልጄን እጠላዋለሁ' ስትለኝ ከወለድሽ ስንት ጊዜሽ ነው ብዬ ጠየኳት። ከዚያም 'ሰላይ ነሽ እንዴ? ልጄን እጠላዋለሁ ስልሽ እብድ... ", "passage_id": "b90be238352d5e0ed9f5bd6ebd328832" } ]
9832322f36df1939ef60fb23bd9a64e0
fc1c402f9da6b05e36015b0cb49c27bd
አንዳንድ እውነታዎች ስለ ታላቁ ህዳሴ ግድብ
 የኢትዮጵያ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ በ2003 ዓ.ም ተጀመረ።• ግድቡ ሲጠናቀቅ ከ 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ በላይ ቦታ ይይዛል።• የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለመሙላት የሚወስድባት ጊዜ እስከ ሰባት አመት ነው።• በሚመጣው ክረምት የውሃ ሙሌት ይጀ መራል። •ታህሳስ 2013 ዓ.ም የመጀመሪያዎቹ ሁለት ተርባይኖች ኃይል ማመንጨት ይጀምራሉ። እያንዳንዳቸው የኃይል ማመንጫ ተርባይን 375 ሜጋዋት በጠቅላላው 750 ሜጋ ዋት ኃይል ለማመንጨ ይችላሉ።• በእያንዳንዱ ኢትዮጵያውያን የገንዘብ መዋጮ የሚገነባና የሁሉም ዜጋ አሻራ ያረፈበት ነው። • ግድቡ ሲጠናቀቅ 6ሺህ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም ይኖረዋል።• በርካታ ሕዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደልብ በማያገኝባት ኢትዮጵያ ግድቡ ሲጠናቀቅ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞችን ይሰጣል። • ከዚህ ባለፈም እያደገ ለመጣው የማኑፋ ክቸሪንግ ዘርፍ ትልቅ እፎይታን የሚሰጥ ይሆናል።• ኢትዮጵያ ግድቡ ሙሉ በሙሉ ኃይል ማመንጨት ሲጀምርላት ለጎረቤት ሀገራት ኮረንቲ መሸጥ ትችላለች። በተለይ ደግሞ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኤርትራና ጂቡቲ ከሕዳሴው ግድብ ጥቅም የሚገኙ ሀገሮች ናቸው።• ታላቁ ህዳሴ ግድብ አጠቃላይ የግንባታ ሒደት 72 በመቶ ደርሷል።• በአሁኑ ወቅት የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎቹ ከ42.3 በመቶ በላይ ተጠናቀዋል።•የሲቪል ስትራክቸር የግንባታ ሒደትም ከ20 በመቶ በላይ አፈጻጸም አስመዝግቧል።•መጋቢት 24 ቀን 2012 ዓ.ም ዘጠነኛ አመት የምስረታ በዓሉን ያከብራል።አዲስ ዘመን መጋቢት 20 ቀን 2012 ዓ.ም
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=29376
[ { "passage": " አዲስ አበባ(ኢዚአ)፡-«የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ፍሬ ለመቅመስ የተጓዝነው ብዙ፤ የቀረው ትንሽ ነው» ሲሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የቦርድ ሰብሳቢና የኢኖቬሽንና የቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር አብርሃም በላይ ገለጹ። «ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የብሔራዊ ቁጭታችን እልባት የሚያገኝበት የመጨረሻ ምዕራፍ ነው» ሲሉም ተናግረዋል። ዶክተር አብርሃም ግድቡ የተጀመረበትን ዘጠነኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ባስተላለፉት መልዕክት «የሕዳሴው ግድብ በዚህ ዘመን ላሉ ኢትዮጵያውያንና ለቀጣዩ ትውልድ የተፈጥሮ ሀብትን ያለምንም ክልከላ በማልማት ድህነትን ለመቀነስ የሚያስችል ሁነኛ መንገድ መሆኑን፤ ግድቡ የዘላቂ ልማት መርሃ ግብሮችን ለማሳካት፣ እንደ ትውልድ ደግሞ ሕዝባዊ ቁርጠኝነትን ለማስመስከር የተጀመረ ብሔራዊ ፕሮጀክት ነው» ብለዋል። ዶክተር አብርሃም የዛሬ ዘጠኝ ዓመት የተጀመረው ግድቡ በአስተዳደር ቅብብሎሽ የተጠነሰሰ፣ በላቀ ሕዝባዊ ስሜትና ተነሳሽነት ተጀምሮ እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ “ግድቡ ድህነትን ለማስወገድ በሚደረገውጥረት ከሚኖረው ፋይዳ ጎን ለጎን ለተፈጥሮ ሚዛን ጥበቃና ለአረንጓዴ ልማት ትልቅ ዳይዳ ያለው ነው“ ሲሉ ተናግረዋል። ግድቡ ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ሕግጋትና መርሆዎች ተገዥነቷን፣ መተባበርና መተማመንን የምታስቀድም እንዲሁም የጋራ ተጠቃሚነትና የጋራ መበልጸግ የማሳያ አገር መሆኗን እንደሚያመለክት አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ ለዘመናት በወንዙ አጠቃቀም ላይ ሰፍኖ የቆየውን ኢ-ፍትሃዊነት የሚንጸባረቅበትን ሀቅ እንደማትቀበል ሊታወቅ እንደሚገባም ዶክተር አብርሀም አስገንዝበዋል። «የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት በሌሎቹ የተፋሰስ አገሮች ዘንድ ምክንያታዊ፣ ፍትሃዊና ጉዳት አልባ የውሃ አጠቃቀምን እንደሚያበረታቱም ይታወቃል» ያሉት ዶክተር አብርሃም፤ ይህ የሚታወቅ ቢሆንም የግድቡ ግንባታ ከተጀመረ አንስቶ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች በተለመደው ኢትዮጵያዊ ጨዋነትና የሰከነ ዲፕሎማሲያዊ እርምጃዎች ለመፍታት እንቅስቃሴ በመደረጉ የግድቡ ፕሮጀክት መቀጠሉን አመልክተዋል። በቅርቡ በአሜሪካን መንግሥትና በዓለም ባንክ ታዛቢነት ሲካሄድ በቆየው ውይይት ዙሪያ ያጋጠሙ ችግሮችን የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ አንድ ሆነው መመከታቸውን የጠቀሱት ዶክተር አብርሃም፤በሕግ፣ በርትዕና በፍትሃዊ ተጠቃሚነት ያልተቃኙ ውይይቶችን እንደማይቀበሉ በማያሻማ መልኩ ለሚመለከታቸው አካላትና ለዓለም ሕዝብ በግልጽ ማሳየታቸውንና ድምጻቸውን ማሰማታቸውን አስረድተዋል።ኢትዮጵያም በዓለም አቀፍ ሕግ መርሆዎች መሠረት በቀጣይ ውይይቶች ላይ ለመሳተፍ ፈቃደኛ መሆኗን የጠቆሙት ዶክተር አብርሃም፤«ችግሩን ያስከተለው ፕሮጀክቱ በወቅቱ ባለመጠናቀቁ ነው» ሲሉ ተናግረዋል:: «በቀጣይም የተጓዝነው ብዙ፤ የቀረው ትንሽ መሆኑን በመገንዘብ ግድቡን በማጠናቀቅ ፍሬውን ለመቅመስ ሁላችንም በጋራ መቆሙን መቀጠል ይገባናል፤ የኮቪድ19 ወረርሽኝን ከመከላከል ጎን ለጎን ፕሮጀክቱን በጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርቡ ይቀጥላል» ብለዋል። በግድቡ ግንባታ ሥራ 24 ሰዓት እየተሳተፉ የሚገኙ ሙያተኞች፣ የፌዴራል ፖሊስ፣ የመከላከያ ሠራዊት አባላትና የአካባቢው ነዋሪዎችንም አመስግነዋል።ምንጭ ኢዜአ አዲስ ዘመን መጋቢት 30/2012", "passage_id": "3d317dd3e6dab8f47cc916d71a1cabf5" }, { "passage": "ከሰሞኑ የወጡ የሳተላይት ምስሎች በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ውስጥ ያለው የውሃ መጠን መጨመሩን ማመልከታቸውን ተከትሎ የግድቡ የመጀመሪያ ምዕራፍ የውሃ ሙሌት ተጀምሯል የሚሉ መረጃዎች መውጣት ጀምረዋል።የህዳሴው ግድብ ግንባታ ባህሪይተፈጥሯዊ የውሃ ሙሌት የህዳሴ ግድብ ቀጣይ ደረጃ ያልተቋጨው ውዝግብየግድቡ ሙሌት በይፋ አለመጀመሩን የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ስለሺ በቀለ የገለፁ ቢሆንም እየጣለ ባለው ከፍተኛ ዝናብ ግድቡ ውሃ መያዝ መጀመሩን አስረድተዋል።የሳተላይት ምስሎቹ ወደ ግድቡ የሚገባው ውሃ መጨመሩን የሚያሳዩ መሆናቸውን ገልፀው፤ ባለፈው ዓመት ውሃው ያልፍ የነበረው በ520 ሜትር ከፍታ ላይ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት 560 ከፍታ ላይ መድረሱን ተናግረዋል።ከ560 ሜትር ከፍታ በታች ያለው ውሃ ግድቡ ውስጥ የሚቀር እንደሆነም አስረድተዋል። ከዚህም ጋር ተያይዞ በግድቡ ዲዛይንና ባለው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት የውሃ ሙሌቱ በይፋ መንግሥት ጀምሬዋለሁ ባይልም ግድቡ ውሃ መያዙንም ሚኒስትሩ አሳውቀዋል።ሚኒስትሩም ለፋይናንሻል ታይምስ በሰጡት ቃለ መጠይቅም \"የዝናብ ወቅት እንደመሆኑ መጠን ግድቡ ውሃ ይዟል። ይሄ በሁሉም አካላት ዘንድ የሚታወቅ ነው፤ ግብጾችም ያውቁታል። ለሕዝባቸው መንገር አለባቸው\" ብለዋል። የታላቁ ህዳሴ ግድብ ውሃ ያዘ ሲባል ምን ማለት ነው? የውሃ ሙሌት በይፋ ተጀረ ሲባል እንዴት ይገለፃል? የሚለውን ለማብራራት ቢቢሲ በውሃ ምህንድስናና በግድብ ግንባታ ዘርፍ የበርካታ ዓመታት ልምድ ያላቸውን ባለሙያዎች አነጋግሯል።የግንባታውን ሂደት ከመነሻው አንስቶ በቅርበት የሚያውቁና ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ኢትዮጵያዊ የዘርፉ ባለሙያ ሲያስረዱ ግድቡ ውሃ ያዘ ወይም ሙሌት ተጀመረ የሚለውን ፅንሰ ሃሳብ ለመረዳት የህዳሴው ግድብ አገነባብን መረዳት እንደሚያስፈልግ ይገልጻሉ።እርሳቸው እንደሚሉት ግድቡ የተሰራው ሸለቆ ውስጥ በመሆኑ ኢትዮጵያ ግድቡን ለመሙላት የምትዘጋውም ሆነ የምትከፍተው ነገር እንደሌለ በቀዳሚነት በማስረዳት የተፈጥሮ አካበቢው ለዚሁ ተብሎ የተመረጠ መሆኑን ይጠቅሳሉ።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይም ሆኑ ሚኒስትሩ ዶ/ር ስለሺ በተደጋጋሚ ሲናገሩት እንደነበረው በዚህ ዓመት ግድቡ 25 ሜትር የነበረው ከፍታው ወደ 60 አድጓል። በዚህም የተነሳ ከዚህ ቀደም በግድቡ አናት ላይ ይፈስ የነበረውን የክረምት ውሃ ማጠራቀም ጀምሯል ሲሉ ተደምጠዋል።እንደ እኚህ ባለሙያ ማብራሪያ ከሆነም በክረምት ዝናብ ምክንያት ወደ ውሃ ማጠራቀሚያው የገባው ውሃ የሚወጣበት እድልም የለውም።ለዚህ የግድቡ ማዕከላዊ ክፍል ከላይ የክረምት ውሃ ማሳለፍ እንዲችል በበጋ ደግሞ በዚሁ ማዕከላዊ ክፍል ያለምንም ችግር ማሳለፍ እንዲችል ተደርገው የተሰሩ መዋቅሮች ( ስትራክቸሮች) እንዳለውም ይጠቅሳሉ።ይህ በበጋ ውሃውን ለማሳለፍ የሚያስችለው ክፍል በህዳሴው ግድብ ላይ አንድ ብቻ ሳይሆን ሁለት መሆኑንም ከተመለከቷቸው የግድቡ ዲዛይንና ምስሎች እንደሚረዱ ባለሙያው ያብራራሉ።በክረምት ወቅት ወደ ግድቡ የሚገባው ውሃ እና የሚወጣው ስለማይመጣጠን በክረምት እንዲጠራቀምም ተደርጎ ዲዛይን መደረጉንም በማመልከት ውሃው ግድቡ ላይ እንዳይፈስ ማዕከላዊው የግድቡ ክፍል ዝቅ ተደርጎ ነው የተሰራው።ክረምት ሲመጣ ከስር ለማሳለፍ ተብለው በተሰሩት መዋቅሮች እየፈሰሰ ይሄድና ከማስተንፈሻው አቅም በላይ ሲሆን ደግሞ በዚህ በ25 ሜትር ከፍታ ላይ ይፈሳል። ኢትዮጵያ በዚህኛው የበጋ ወራት ይኸኛውን 25 ሜትር የነበረውን ከፍታ ወደ 60 ሜትር ከፍ እንዳደረገችው ያስረዳሉ።በቀላል አገላለጽ በበጋው ወቅት በማስተንፈሻው በኩል ያልፍ የነበረው ውሃ በክረምት ወቅት መጠኑ ከፍተኛ ስለሚሆን ማለፍ አይችልም። ስለዚህ ተወደደም ተጠላ ውሃ እየተጠራቀመ 60 ሜትር ከፍታ ላይ ሲደርስ በግድቡ ላይ ይፈሳል። እስከዚያ ድረስ ግን የትም መሄጃ ስለሌለው ውሃው ይጠራቀማል።የግድቡን ግንባታ ካላቸው ሙያና ከተለያዩ ምንጮች በቅርበት የሚከታተሉት የውሃ ምህንድስና ባለሙያው እንደሚሉት አሁን ባለው ሁኔታ የሚከፈት ወይም የሚዘጋ ነገር አለመኖሩን ደግመው ያረጋግጣሉ። በአተጠቃላይ የታላቁ የህዳሴ ግድብ አገነባብ ውሃው እንዲጠራቀምም እንደሚያስገድደው በመሆኑ አሁን እታየ ያለው የውሃ ክምችት ከፍተኛ ዝናብ እጣለ በመሆኑ በዚህ ምክንያት የተፈጠረ መሆኑን ይናገራሉ። ባለሙያው ሲያጠቃልሉ \"ይህ ማንም የሚቆጣጠረው አይደለም፤ ስለዚህ በጋ ሲሆንና የውሃው መጠን ሲቀንስ የግድቡ ማዕከላዊ ክፍል በግንባታ ምክንያት ውሃ እንደ ቀድሞው በማስተንፈሻው በኩል ያልፋል ማለት ነው\" ብለዋል።በግድቡ በስተጀርባ ባለው የውሃ ማጠራቀሚያ ሰፊ ስፍራ ላይ ከሰኔ ጀምሮ እስከ መስከረም ድረስ በሚቆየው የዝናብ ወቅት ላይ በተፈጥሯዊ ሁኔታ ውሃ መጠራቀም ይጀምራል። የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከተጀመረ በኋላ አንስቶ በቅርብ ሲከታተሉ የቆዩት ዶክትር ኬቭን ዊለር እንደሚሉት አሁን ግድቡ ከደረሰበት የግንባታ ደረጃ አንጻር \"የግድቡን ዝቅተኛ የውሃ መያዣ ክፍልን ውሃ እንዳይዝ የሚያደርግ አንዳችም ነገር የለም\" ሲሉ የግንባታው ሂደት ውሃ ለማቀብ መድረሱን ይገልጻሉ።የግድቡ ግንባታ ከተጀመረበት ከዘጠኝ ዓመት በፊት አንስቶ ግዙፍ የግንባታ ሥራ እየተከናወኑ የአባይ ወንዝ ውሃ ያለችግር ሲከናወን የቆየ ሲሆን፤ በበጋ ወቅት ደግሞ የውሃው መስመር በሌላ በኩል እንዲያልፍ ተደርጎ ቀሪው ክፍል እንዲገነባ ተደርጓል። በአሁኑ ጊዜ የግድቡ ማዕከላዊ ክፍል የታችኛው አካል ተገንብቶ በማለቁ ውሃው በግድቡ ግድግዳ ላይ ባሉ የውሃ ማስተላለፊያዎች በኩል እንዲፈስ እየተደረገ ነው።ከፍተኛ ዝናብ የሚጥልበት በአሁኑ የክረምት ወቅት ላይ ከፍተኛ መጠን ያለው ውሃ ወደ ግድቡ ስለሚገባ ውሃው በግዙፎቹ የግድቡ የማስተላለፊያ ቦዮች በኩል መፍሰስ ከሚችለው አቅም በላይ ይሆናል።ይህም ማለት በግድቡ በኩል አልፎ ከሚፈሰው ውሃ በተጨማሪ ከፍተኛ መጠን ያከለው ከግድቡ ጀርባ ባለው ውሃ እንዲያርፍበት በተዘጋጀው ሰፊ ቦታ ላይ በመጠራቀም ሐይቅ መፍጠር ይጀምራል ሰሉ ዶክተር ዊለር ለቢቢሲ ተናግረዋል። ጨምረውም ኢትዮጵያ በውሃ ማጠራቀሚው ቦታ ላይ የሚያርፈውን የውሃ መጠን መጨመር ከፈለገች በግድቡ ላይ ያሉትን የውሃ ማፍሰሻ መተላለፊያዎችን መዝጋት ትችላልች። ነገር ግን ይህ አስፈላጊ ላይሆን ይችላል ሲሉ ተናግረዋል። የአባይ ወንዝ ዓመታዊ አማካይ የውሃ ፍሰት 49 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ሲሆን ከዚህ ውስጥ በመጀመሪያው ዓመት የውሃ ሙሌት ታላቁ የህዳሴ ግድብ 4.9 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር በመያዝ የግድቡ ዝቅተኛው ውሃ መያዝ ደረጃ ድረስ ውሃ ለማቀብ ይችላል። ይህም ኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹን የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ተርባይኖችን እንድትሞከር ያስችላታል። በቀጣዩ የበጋ ወቅት ከግድቡ ጀርባ የተጠራቀመው ውሃ ስለሚቀንስ የግድቡን ቁመት መጠን ለመጨመር የሚደረገው ግንባታ እንዲቀጥል ዕድል ስለሚሰጥ ሥራውን በማከናወን በሁለተኛው ዓመት ደግሞ 13 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ እንዲይዝ ይደረጋል ይላሉ ባለሙያው። በዚህ ጊዜም በግድቡ አማካይነት የሚታቀበው የውሃ መጠን በሁለተኛ ደረጃ ላይ የተገነቡትን የኤሌክትሪክ ማመንጫ ተርባይኖች ጋር ይደርሳል። ይህ ደግሞ የውሃውን ፍሰት በበለጠ ለመቆጠጠር ያስችላል። ኢትዮጵያ እንዳለችው የግድቡ ከፍተኛ አቅም የሆነውንና አስፈላጊውን የ74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ በግድቡ ውስጥ ለመያዝ ከአምስት እስከ ሰባት ዓመታት ያስፈልጋል። ግድቡ በሚጠበቀው መጠን በውሃ ተሞልቶ ሲያበቃ በተጠራቀመው ውሃ የሚፈጠረው ሐይቅ 250 ኪሎ ሜትሮችን የሚያካልል ቦታን በውሃ ይሸፍናል። ግድቡ ተጠናቆ ሥራ ሲጀመር በአፍሪካ ትልቁ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ግድብ ሲሆን በዓለም ካሉ 10 ግዙፍ ተመሳሳይ ግድቦች መካከልም ይመደባል። ለአስር ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ ከአምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ ወጪ ተደርጎበት እተገነባ ያለው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታው ከሦስት አራተኛው በላይ ጠተናቋል።ቢሆንም ግን በግድቡ ዙሪያ በተነሱ ሕጋዊና ቴክኒካዊ ጉዳዮች ዙሪያ ኢትዮጵያ ከሱዳንና ከግብጽ ጋር ለዓመታት ስታካሂዳቸው የነበሩት ድርድሮች እስካሁን መቋጫ አላኙም።ኢትዮጵያ ከአገራቱ ጋር ከስምምነት ለመድረስ ፍላጎት እንዳላት በተደጋጋሚ የገለጸች ሲሆን፤ ቢሆንም ግን በድርድሮቹ የሚገኘው ውጤት ግድቡን ውሃ ከመያዝና ሥራውን ከማስጀመር እንደማያግዳት በተደጋጋሚ አሳውቃለች። ሱዳንና ግብጽ በበኩላቸው ግድቡ ከሚያገኙት ዓመታዊ የውሃ መጠን ላይ መቀነስን ስለሚያስከትል ከስምምነት ከመደረሱ በፊት የውሃ ሙሌቱ እንዳይጀመር ሲወተወቱ ቆይተዋል።ኢትዯጵያ የግድሙን ሙሌት ገና እንዳልጀመረች ያሳወቀች ሲሆን ከሰኔ ወር ጀምሮ በአገሪቱ እጣለ ባለው ከባድ ዝናብ ምክንያት የግድቡ የውሃ ማተራቀሚያ ክፍል ላይ መጠኑ እጨመረ የሚሄድ የውሃ መጠን መታቱ ሱዳንና ግብጽን ሳያሳስባቸው አልቀረም። ይህንን በተመለከተም ግብጽ ኢትዮጵያ መንግሥት በግድቡ የውሃ አያያዝ ዙሪያ ማብራሪያ እንዲሰጣት ጠይቃለች። ", "passage_id": "7a63c4558033e39b3760c84d316274c2" }, { "passage": "እየተመናመነ የመጣውን ውሃ ለመጠቀም የሚደረገው ፉክክር በአካባቢው ሃገራት መካከል ግጭት ሊፈጥር ይችላል\n\nክፍል 2 ፡የህዝብ ብዛት መጨመርና የአካባቢ ብክለት ሌሎቹ የዓባይ ስጋቶች \n\nክፍል 3 ፡የዓለማችን ረጅሙ ወንዝ መፃኢ ዕጣ ፈንታ ምን ይሆን?\n\nየህዝብ ቁጥር መጨመር ውሃውን እያቆሸሸው እና እያደረቀው ሲሆን የአየር ንብረት ለውጥ ደግሞ መጠኑን እየቀነሰው ይገኛል። \n\nአንዳንዶች ደግሞ እየተመናመነ የመጣውን ውሃ ለመጠቀም የሚደረገው ፉክክር በአካባቢው ሃገራት መካከል ግጭት ሊፈጥር ይችላል የሚል ስጋት አላቸው።\n\nበዓባይ ዙሪያ በሦስት ክፍሎች ከምናቀርበው ዘገባ፤ በመጀመሪያው ክፍል ወንዙ ስለገጠመውን ፈተና፣ ስለተፈጥሮ ሃብቱ እና ስለአካባቢው ህዝቦችን ዕጣ ፈንታ እንመለከታለን።\n\nዝናብ\n\nችግሩ የሚጀመረው ከወንዙ መነሻ ነው።\n\nየዓባይ ወንዝ ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነውን የውሃ መጠን በኢትዮጵያ ከሚጥለው ዝናብ ያገኛል። \n\nከጣና ሐይቅ በስተደቡብ ከሚገኘው ጫካ ውስጥ የሚነሳው ጥቁር ዓባይ በመጠኑ እያደገ ይሄዳል።\n\nከቪክቶሪያ ሃይቅ የሚነሳው ነጭ ዓባይ በበኩሉ አነስተኛ መጠን ያለው ውሃ ይዞ ካርቱም ላይ ከኢትዮጵያው ጥቁር ዓባይ ጋር ይቀላለቀላል። \n\nበኢትዮጵያ ዝናብ እንደዚህ ቀደሙ እየዘነበ አይደለም። ይህ ደግሞ ዓባይ ሙሉ ለሙሉ እንዲሞት ሊያደርገው ይችላል። \n\nከረዥም የበጋ ወቅት በኋላ በየዓመቱ የሚኖረው አጭር የዝናብ ወቅት አንዳንዴ አነስተኛ ዝናብ ብቻ ይዞ ይመጣል።\n\n\"ዝናቡ አሁን ይበልጥ የማይገመት ሆኗል። አንዳንዴ ጠንካራ ሌላ ጊዜ ደግሞ አነስተኛ መጠን ያለው የዝናብ ወቅት ይሆናል። መጠኑ ሁሌም የተለያየ ነው\" ይላል የአርባ ምንጭ ዩንቨርሲቲ መምህሩና የአየር ንብረት ለውጥ ተመራማሪው ላዕከማርያም ዮሃንስ።\n\nየዓባይ ወንዝ ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነውን የውሃ መጠን በኢትዮጵያ ከሚጥለው ዝናብ ያገኛል\n\nከባድ የሆነ የክረምት ወቅት ሲኖር ወንዙ በቢሊዮን ቶኖች የሚቆጠር ለም አፈርን ከኢትዮጵያ በየዓመቱ ይዞ ይሄዳል። ይህ ደግሞ ግድቦችን የሚገድልና አርሶ አደሮች የሚያስፈልጋቸውን ለም አፈር የሚያሳጣ ነው። \n\nይህ ችግር በህዝብ ቁጥር በፍጥነት ማደግ ምክንያት ተባብሷል። የቤተሰብ መስፋፋትን ተከትሎ ሰዎች መኖሪያቸውን ለመቀለስ የሚረዳቸውን ቦታ እና ቁሳቁስ ለማግኝት ዛፎችን እየቆረጡ ነው።\n\nከፍተኛ አደጋ የሚያስከትሉ ጎርፎችም በተደጋጋሚ መከሰት ጀምረዋል። \n\nየሰብሎች ምርታማነት እየቀነሰ እና የምግብ ዋጋ ደግሞ እየጨመረ ይገኛል። በዚህም ወንዞችን በመስኖ ከመጠቀም ይልቅ ዝናብ ላይ የተመሰረተ ግብርና ላይ የሚተዳደሩ የገጠር መንደሮች ወደ ድህነት እየተሸጋገሩ ይገኛሉ።\n\nአንዳንድ የገጠር ነዋሪዎች የግብርና ሥራቸውን እርግፍ አድርገው በመተው ወደ ክልሉ ርዕሰ መዲና ባህር ዳር ወይንም በማደግ ላይ ወደምትገኘው የአገሪቱ መቀመጫ አዲስ አበባ ማቅናትን መርጠዋል። \n\nአብዛኛዎቹ ሰዎች ዝናቡ እንደቀድሞው ይሆናል በሚል ተስፋ ያገኙትን ውሃ በመጠቀም ህይወታቸውን ለመግፋት ተገደዋል።\n\nለአንዳንድ ታዳጊዎች ግን ተስፋ አስቆራጭ ሆኗል። \n\nቤተሰቦቹን በእርሻ ሥራቸው ለመደገፍ ትምህርቱን አቋርጦ ያለችውን ብስክሌት በመሸጥ አዲስ ምርጥ ዘር የገዛው የ17 ዓመቱ ጌትሽ አዳሙ በስደት ሜድትራኒያንን ስለማቋረጥ እያሰበ ይገኛል።\n\n\"ቆም ብዬ ሳስበው ከቤተሰቤ ጋር መኖር እፈልጋለሁ። ነገር ግን ዝናቡ እንዲህ ሆኖ የሚቀጥል ከሆነ እዚህ ስፍራ መቆየት አልችልም\" ይላል። \n\nአንዳንድ የመንደሩ ነዋሪዎች የግብርና ስራቸውን እርግፍ አድርገው ትተዋል\n\nየግድብ ውዝግብ\n\nዓባይ ብዙ በተጓዘ ቁጥር ያለበትም ችግር እየጨመረ ይሄዳል። \n\n30 ማይሎችን ያህል ከጣና ሃይቅ ከራቀ በኋላ አስደማሚውን የዓባይ ፋፏቴን አልፎ... ", "passage_id": "39df378a54710608f5a2192cd12c17da" }, { "passage": "የማያረጅ ውበት የማያልቅ ቁንጅናየማይደርቅ የማይነጥፍ ለዘመን የፀናከጥንት ከፅንሰ አዳም ገና ከፍጥረትየፈሰሰ ውሃ ፈልቆ ከገነት።ነበር ያለችው እጅጋየው ሽባባው አባይ በሚለው ዜማዋ። እውነት አባይን በቅርበት ለተመለከተው የሆነ ውስጥ የሚነካ የተለየ ስሜት እንዲሰማን የሚያደርግ ውብ የተፈጥሮ ፀጋ ነው። አባይ ጣና ላይ ሲፈስ ጥቁር ቀለሙን ፅፎ ውሃው ሳይቀላቀል ሲያልፍ፤ ከጣናም ከወጣ በኋላ በዝምታ የባህር ዳር ከተማን አቋርጦ ሲወርድ ለተመለከተው እንደልብ ወዳጅ ሆድ እያባባ የሚሰናበት ያህል ልብ ይነካል። ከዚህ ቀጥሎ ጢስ አባይ ሲደርስ ደግሞ ከላይ ተወርውሮ ሲወርድ፤ ከዛ ተመልሶ ደግሞ ጭስ የመሰሉ ትናንሽ የውሃ ነጠብጣቦችን ይዞ ሲመለስ ለተመለከተው ልብን በሃሴት ጮቤ የሚያስረግጥ ውበት ያሳያል።እንኳን ከተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች ሀገራችንን ሊጎበኙ ለመጡ ቱሪስቶች ይቅርና ከማህፀኗ ለፈለቅኩት ለኔ እንኳን ሳይቀር ሀገሬ ድንቅ ምድር እንደሆነች የፈጣሪ ውብ ስራ አንደሆነች ማመልከቻ ነው። ስለአባይ ማንሳት ከጀመርኩ ማቆሚያ የለኝም። አሁን ደግሞ ከሁሉ የሚልቀው ጉባ ላይ የከተመው ታላቁ የህዳሴ ግድብ የሀገር ኩራት እውነተኛ የኢትዮጵያዊነት ወኔን የሚቀሰቅስ ነው።የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ̋እንኳን ደስ አላችሁ የመጀመሪያው ዙር የግድቡ የውሃ ሙሌት ስራ በስኬት ተጠናቋል” ብለው ለህዝቡ ሲያበስሩ ልቤን ፈንቅሎ የወጣው ስሜት ከልቤ የምወደውን አባይ ሳሞጋግስ አንድውል አድርጎኛል።ከቢሮዬ ወጣ ብዬ የህዝቡን ሁኔታ መመልከት ጀመርኩ። በእግሬ ትንሽ እርምጃዎችን ከተራመድኩኝ በኋላ ሰብሰብ ብለው የሚጨዋወቱ የእድሜ ባለፀጎች አጠገብ ደረስኩ። ፈቃዳቸውን ጠይቄ መቅረፀ ድምፄን ወደእነርሱ ጠጋ አደረግኩ።አቶ ታደሰ ሲሳይ ይባላሉ፤ የ63\nዓመት እድሜ ባለፀጋ ናቸው። ጡረተኛ መሆናቸውን የሚናገሩት አባት የአንድ ወር የጡረታ አበላቸውን አዋጥተው የግድቡን እድገት እንደ ህፃን ልጅ ከስር ከስር ሲከታተሉ መቆየታቸውን ይናገራሉ። “ከባልንጀሮቼ ጋር በተገናኘን ቁጥር ግድቡ እንዴት ሆነ? ምን ሰማችሁ? እንባባል ነበር” የሚሉት አቶ ታደሰ” ዛሬ ቀኑ ደርሶ የመጀመሪያውን ውሃ ለመያዝ መቻሉ ከአድዋ የማይተናነስ ድል ነው ብለዋል። እኔ እንኳን ባልደርስበት ለልጅ ልጆቼ የሚተላለፍ ግድብ ላይ አሻራዬን ስላኖርኩ ኩራት ይሰማኛል” ብለዋል። አቶ ጌታነህ አበባው በአንድ የግል ኮሌጅ ውስጥ በጥበቃ ስራ የሚተዳደሩ አባት ናቸው “ፈጣሪ እድሜ ሰጥቶኝ ይሄን ለማየት በመቻሌ እራሴን እንደ እድለኛ እቆጥረዋለሁ” ብለዋል። “ከኛ እኩል ካላቸው ላይ ቆጥበው ይሄን ቀን ለማየት ሲጓጉ የነበሩ ጓደኞቻችን ዛሬ በህይወት የሉም። እነርሱን ከጎናችን ብናጣቸውም ግን በነበራቸው አቅም ታሪክ ፅፈው እንዳለፉ እያሰብን እንጽናናለን ሲሉ ተናግረዋል። በውትድርና ሙያ ሀገራቸውን ሲያገለግሉ የኖሩት አቶ ይደርሳል ብርሃኔ የሀገር ዳር ድንበርን በማስከበር ስራ ላይ ከኖሩበት ጊዜ በላይ የልማት አርበኛ ሆነው የቻሉትን ያህል ገንዘብ አዋጥተው የግድቡን መጠናቀቅ የድል ብስራት የሚጠባበቁበት ጊዜ እንደሚበልጥባቸው ገልፀው፤ በድሉም ወደር የሌለው ደስታ እንደተሰማቸው ይናገራሉ። ሌላዋ እናት ወይዘሮ ምህረት ልመንህ ይባላሉ፤ የ72 ዓመት የእድሜ ባለፀጋ ናቸው፤ በመንግስት ስራ ላይ ለበርካታ ዓመታት ሲያገለግሉ ከቆዩ በኋላ በጡረታ ጊዜያቸው ሀገርን በአንድ ድምፅ የሚያነጋግር ድል መገኘቱ የማይቆጣጠሩት ደስታ እንደሰጣቸው ተናግረዋል። ወይዘሮዋ እንደሚሉት ከሚመሩት እድር አባላቶቹን በማስተባበር የአስር ሺ ብር ቦንድ እንደገዙ አስረድተው፤ ህብረተሰቡ ከእለት ጉርሱ ቀንሶ ያዋጣው ገንዘብ ወደ ስራ ተቀይሮ ውጤት ላይ ሲደርስ ከማየት የበለጠ ደስታ የለም ብለዋል።የእድሜ ባለፀጎቹ በአንድ አይነት ሃሳብ ግድቡ የኛም የአረጋውያኑ መጦሪያ የልጆቻችን ሀብት ማፍሪያ በመሆኑ “ አዎ ግድቡ የኛም ነው” ብለን አስተዋጽኦችንን በህይወት እስካለን እንቀጥላለን ብለዋል።“አዎ ግድቡ የኔም ያንችም የእነሱም የሁላችንም ነው”።አዲስ ዘመን ሐምሌ 20/2012አስመረት ብስራት", "passage_id": "48e84f4f2b42e9e1cc0d21726bd83ef8" }, { "passage": "– የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫ ግድብ ስራ ለሌሎች ፕሮጀክቶች ምሳሌ ሊሆን እንደሚችል በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የተፈጥሮ ሀብት ልማትና አካባቢ ጥበቃ ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡ቋሚ ኮሚቴው ግድቡ አሁን ያለበትን ደረጃ ገምግሟል፡፡ ግድቡን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ የ24 የፈረቃ ስራን ተግባር ላይ በማዋል የሚደረገው ርብርብ አርአያነቱ ጎልቶ እንደሚታይ አባላቱ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡በፕሮጀክቱ የግንባታው ቀኝ ክንፍ፣ የግድቡ አካል እያረፈበት ያለው ቦታ፣ የግድቡ መካከለኛው ክፍል፣ የግራ ክንፉ የቁፋሮ ስራውና የአርማታ ሙሌት በተጓዳኝ እየተከናወነ መሆኑንም የፕሮጀክቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ስመኘው በቀለ ለኮሚቴው ገለፃ አድርገዋል፡፡ ምንጭ ኢሬቴድ", "passage_id": "4b4fdd9295a6b0b32521dbea3aab225f" } ]
4502db2292cadf26351accd71b9a4dfe
b7ab928b164395002a477f98c03bdeec
የብሔራዊ ስታዲየም ሁለተኛ ምዕራፍ ግንባታ ተጀመረ
 አዲስ አበባ ቀደምት ከሚባሉ የኢትዮጵያ ከተሞች ተርታ ብትመደበም፣ መጠሪያዋን ስያሜው ያደረገ ብሔራዊ ስታዲየም ሳይኖራት ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ ዘመናዊ ስታዲየምም መመልከት ብርቅ ሆኖባት ዘመናት አልፈዋል:: አንድ ለእናቱ የሆነው የአዲስ አበባ ስታዲየም የዓለም አቀፍ እግር ኳስ ማኅበር (ፊፋ) ለዚህ ወቅት የሚመጥን አይደለም በሚል ማንኛውንም አኅጉራዊም ይሁን ዓለም አቀፋዊ ውድድሮችን እንዳያስተናግድ ክልከላ ጥሎበታል:: በ2008 ዓ.ም. ታህሣሥ ወር ላይ «ሀ»ብሎ የግንባታውን መሠረት የተጣለለት የአደይ አበባ ስታዲየም አንድ ለናቱ የነበረውን የአዲስ አበባ ስታዲየም ን ያሳርፋል የሚል ተስፋ እንዲሰነቅ ያደረገ ነበር። ለአዲስ አበባ ተጨማሪ ውበትና ኩራት ይሆናል ተብሎ የታሰበውና በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ገርጂ አካባቢ እየተገነባ ያለው ብሄራዊ ስታዲየሙ፤ የሁለተኛ ምዕራፍ ግንባታ አካል የሆነው የስታዲየሙን ጣራ እና የማጠቃለያ ግንባታ የተለያዩ እንግዶች በተገኙበት ከትናንት በስቲያ በይፋ ተጀምሯል።የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ኤልያስ ሽኩር በሥነ ስርዓቱ ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት ፤ በሁሉም የሀገራችን ክልልሎች ከ 12 በላይ ስታዲየሞች በመገንባት ላይ ይገኛሉ ። በአዲስ አበባ እየተገነባ ያለው ግዙፍ አደይ አበባ ስታዲየም ከዚህ ውስጥ አንዱና ዋነኛው ሲሆን ፤ስታዲየሙ ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ ለኢትዮጵያ የእግር ኳስ ተመልካች ትልቅ ብስራት እንደሚሆን ገልጸዋል። የብሔራዊ ስታዲየም ሁለተኛው ምዕራፍ ግንባታ ስፖርት ኮሚሽን ከተቋራጩ የቻይና ስቴት ኮንስትራክሽን ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ጋር ከወራቶች በፊት በተደረገው ስምምነት መሠረት በታቀደለት ጊዜ ጥራቱን ጠብቆ መጠናቀቅ ይችል ዘንድ አስፈላጊው ክትትልና ቁጥጥር እንደሚደረግ ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡የቻይና ስቴት ኮንስትራክሽን ኢንጂነሪንግ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ሚስተር ሚንግ ቾ በበኩላቸው ፤ኩባንያው ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በመስራት ከፍተኛ ልምድ ያለው መሆኑን ጠቅሰው የዓለም አቀፍ ስጋት የሆነው የኮሮና ቫይረስ በመቋቋም ስታዲየሙን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እንደሚሰሩ አመልክተዋል።«በአሁን ሰዓት የካፍ እና የፊፋን መስፈርት ያሟላ ኢንተርናሽናል ጨዋታዎችን ማስተናገድ የሚያስችል ስታዲየም የለም»ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ እግር ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ፤ የአደይ አበባ ስታዲየም የዓለም ዋንጫ ፍፃሜን ማስተናገድ የሚያስችል ስታዲየም እየተገነባ መሆኑን ትልቅ ደስታ እንደፈጠረላቸው ገልጸዋል። የአደይ አበባ ስታዲየም የሁለተኛው ምዕራፍ ግንባታ 900 ቀናት እንደሚፈጅ ተነግሯል ። ለስታዲየሙ መዋቅራዊ ይዘት (የመጀመርያ ምዕራፍ) ግንባታ 2.7 ቢሊዮን ብር ወጪ ተደርጎበታል፣ ለቀሪው ግንባታ ደግሞ 5 ነጥብ 57 ቢሊዮን ብር ያስፈልገዋል ተብሏል:: በስምምነቱ መሠረት ተቋራጩ የተረከባቸው ዝርዝር ሳይቶች ስታዲየሙን ሳር የማልበስ ሥራና የመሮጪያ ትራክ፣ የመገናኛ ብዙኃን ቦታና የጋዜጣዊ መግለጫ ክፍሎች፣ የተለያዩ መሰብሰቢያ አዳራሾችና የቪአይቪ ማረፊያ ክፍሎችና መቀመጫ ወንበሮች፣ አሳንሳሮች፣ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የካፌና የሬስቶራንቶች ክፍሎች፣ ለሁለቱም ፆታ አገልግሎት የሚሰጡ መፀዳጃ ክፍሎች፣ የፍሳሽ ማስወገጃና የኤሌክትሪክ መስመሮች፣ የተለያዩ ሰው ሠራሽ ሐይቆች፣ ለአደጋ ጊዜ የሔሊኮፕተር ማረፊያና ዘመናዊ የደኅንነት ካሜራዎች እንዲሁም የሳውድ ሲስተም ገጠማ፣ ቡድኖች ከጨዋታ የሚለማመዱባቸው የተለያዩ ሜዳዎችና የፓርኪንግ አገልግሎት መስጫ የሚውሉ ቦታዎች እንዲሁም ብሔራዊ ስታዲየሙ ከጨዋታ በኋላ ተመልካቾችን ጨምሮ ተሽከርካሪዎች ከአሥር እስከ አሥራ አምስት ባለው ደቂቃ ውስጥ አካባቢውን ለቀው መንቀሳቀስ የሚችሉባቸው መንገዶች ተከተዋል፡፡ ዓለም አቀፍ ደረጃውን ጠብቆ እየተገነባ የሚገኘው የአደይ አበባ ስታዲየም አራት ዋና ዋና በሮች ሲኖሩት፣ በወንበር 62 ሺህ ተመልካቾችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል፡፡ ለክብር እንግዶች (ቪአይፒ) እና ለሚዲያ አባላት 2 ሺህ ወንበሮችን መያዙን ታውቋል። በቻይና ስቴት ኮንስትራክሽን ኢንጂነሪን ኮርፖሬሽን እየተገነባ የሚገኘውና በውጭ ምንዛሪና መሰል ችግሮች የፕሮጀክቱ የመጠናቀቂያ ጊዜ መጓተቱ ይታወሳል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 24/2012 ዳንኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=36398
[ { "passage": "የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ እና የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ለማ መገርሳ 196 ሚሊየን ብር ወጪ የተደረገበትን የወለጋ ስታዲየም መርቀው ከፍተዋል።በዛሬው እለት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት የተደረገውና በነቀምቴ ከተማ የተገነባው የወለጋ ስታዲየም ግንባታ በመንግስት እና በህብረተሰቡ ድጋፍ የተከናወነ ነው።ለግንባታው እስካሁን 196 ሚሊየን ብር ወጪ የተደረገ ሲሆን፥ ከዚህም ውስጥ 181 ነጥብ 7 ሚሊየን ብሩ በመንግስት የተሸፈነ መሆኑ ተነግሯል።ስቴድየሙ  30 ሺህ ሰው የማስተናገድ ዐቅም ያለው ሲሆን ለከተማዋ ነዋሪዎች የስፖርት ማዘውተሪያና የመዝናኛ ስፍራ በመሆን ያገለግላል ተብሏል፡፡።በፊፋ መመዘኛ መሰረት ዓለም አቀፍ ደረጃውን ጠብቆ የተሰራ ሲሆን፥ የእግር ኳስ፣ የቮሊቦልና የቅርጫት ኳስ ሜዳዎች፣ የመሮጫ መምና ሌሎች የመወዳደሪያ ሥፍራዎችን ያካተተ ነው።", "passage_id": "9cadbbb8f40bdc8f85f7c7dcb195b259" }, { "passage": "አንጋፋው የድሬዳዋ ስታዲየም ከአንድ ዓመት በላይ ሲደረግለት የነበረው የማስፋፊያ እና የማሻሻያ ግንባታ የማጠናቀቂያ ሥራ ወደ መጨረሻው ምዕራፍ እየደረሰ ይገኛል።ኢትዮጵያ ባስተናገደችው የ1968 የአፍሪካ ዋንጫ ላይ አገልግሎት መስጠት የጀመረው የድሬዳዋ ስታድየም ለወራት የማስፋፊያ እና እድሳት ሲደረግለት በመቆየቱ እና ግንባታው በፍጥነት ባለመጠናቀቁ ድሬዳዋ የ2012 የውድድር ዘመንን ጨዋታዎቹን በሁለተኝነት ባስመዘገበው ሐረር ስታድየም እንዲጫወት አስቀድሞ ውሳኔ መሰጠቱ ይታወቃል።\nየሜዳውን ጥራት እና ጨዋታ ለማጫወት ያለውን ዝግጁነት አወዳዳሪው አካል ከገመገመ በኃላ ድሬደዋ በሜዳው የሚያደርገውን ጨዋታ እንዲጫወት ማረጋገጫ ሰጥቶታል። በዚህም መሠረት ድሬደዋ የ2012 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተከታታይ ሁለት ጨዋታዎች እንዳጋጣሚ ሆኖ ከሜዳው ውጭ ከሀዋሳ ከተማ እና ከፋሲል ከነማ ጋር ከተጫወተ በኃላ የመጀመርያ የሜዳ ላይ ጨዋታውን ከሀዲያ ሆሳዕና ጋር ታኀሳስ ወር ላይ እንደሚያደርግ ታውቋል።", "passage_id": "fcf776909c8daa5c85f7cdabeb7fd2a6" }, { "passage": "የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲዬም ጣሪያ፣ ወንበር እና ሌሎች ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ለማሟላት እንቅስቃሴ መጀመሩን የአማራ ክልል ስፖርት ኮሚሽን ለአብመድ ገልጿል፡፡የተጫዋቾች፣ የዳኞች፣ የአሠልጣኞች ክፍል እና ሌሎች የውስጥ ለውስጥ መሠረተ ልማቶችን በመዘርጋት ስታዲየሙን የማዘመን ሥራ እየተሠራ እንደሆነ የአማራ ክልል ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ አዱኛ ይግዛው አስረድተዋል፡፡ወንበር፣ ጣሪያ እና የድምጽ አገልግሎት ሳይኖሩት ግልጋሎት እየሰጠ የሚገኘው የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ደረጃ በደረጃ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የማሟላት ሥራ መሥራት እንደተጀመረ ነው አቶ አዱኛ የተናገሩት፡፡ምክትል ኮሚሽነሩ እንዳብራሩት የስታዲዬሙን ጣሪያ ለመሸፈን ‹ሲሲሲ› የተባለ የቻይና ኩባንያ በ5 ዓመታት የሚመለስ የብድር ስምምነት ሐሳብ አቅርቧል፡፡ ይህም ሐሳብ ለክልሉ የርእሰ መሥተዳድር ምክር ቤት መመራቱን ምክትል ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል፡፡ሥራውን ለመሥራትም ኩባንያው ወደ 560 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ ገልፆ ሥራውን በብድር ለመሥራት ፍላጎት እንዳለው ሐሳብ ማቅረቡን አስታውቀዋል፡፡ ኩባንያው ሊሠራ ያሰበውን ጣሪያ እና ዲዛይ እንዲሁም በኩባንያው የቀረበውን የመነሻ ሐሳብ ሰነድ የርእሰ መሥተዳድር ምክር ቤቱ ያጸድቀዋል ተብሎ እየተጠበቀ መሆኑን ነው የጠቆሙት፡፡ኩባንያው በርካታ ዓለም አቀፍ ስታዲዬሞችን ጣራ በመሸፈን ልምድ ያለው መሆኑንም አቶ አዱኛ ገልጸዋል፡፡ምክትል ኮሚሽነሩ ኩባንያው ሥራውን በአንድ ዓመት ውስጥ እንደሚያጠናቅቅም ተናግረዋል፡፡ የስታዲየሙን ጣሪያ ወጭ የሚሸፍነው የክልሉ መንግሥት መሆኑን የጠቆሙት ምክትል ኮሚሽነሩ የወንበር ዝርጋታውን ወጪ ኮሚሽኑ ባካሄደው የገቢ ማስገኛ በሰበሰበው 60 ሚሊዮን ብር የሚከናወን ይሆናል፤ ይህም ገንዘብ  በዝግ ‹አካውንት› መቀመጡን ተናግረዋል፡፡", "passage_id": "a542e65c5e1776e485d80799d3b74811" }, { "passage": "በአሜሪካና በቻይና መንግሥታት እንዲሁም በሞሮኮና የኢትዮጵያ መንግሥታት መካከል ውዝግብ ፈጥሮ የቆየው፣ የአፍሪካ በሽታ አጠባበቅና መከላከል ማዕከል (ሲዲሲ)፣ በአዲስ አበባ በ100 ሚሊዮን ዶላር ወጪ እንዲገነባ ሰኞ ታኅሳስ 5 ቀን 2013 ዓ.ም. የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ፡፡ የአፍሪካ ኅብረት አዳራሽን እ.ኤ.አ. በ2012 ዓ.ም. የገነባችው ቻይና የአፍሪካ ሲዲሲን ለመገንባት እ.ኤ.አ. ጁን 2019 ከአፍሪካ ኅብረት የማኅበራዊ ጉዳዮች ኮሚሽነር አሚራ ኢልፋዲል መሐመድ ጋር ስምምነት ከተደረገ በኋላ፣ አሜሪካ ሥጋቷን ስትገልጽ ቆይታለች፡፡ እንደ ሞሮኮ ያሉ አገሮች ደግሞ ከኢትዮጵያ የተሻልን በመሆናችን ተቋሙ እኛ ዘንድ ቢገነባ የተሻለ አገልግሎትና ድጋፍ እንዲያገኝ ማድረግ እንችላለን ሲሉ ነበር፡፡በተለይ በዓለም አቀፍ ደረጃ የኮሮና ወረርሽኝ ከተከሰተ በኋላ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ የቻይና መንግሥትና የዓለም ጤና ድርጅትን ቫይረሱን ደብቀዋልለ በማለት በመውቀሳቸው፣ ለዓለም የጤና ድርጅት አገራቸው ታደርግ የነበረውን ድጋፍ ያቋረጠች ሲሆን፣ ይኼንን ተከትሎም በአሜሪካና በቻይና መካከል የሚደረገው የቃላት ጦርነት ተካርሮ እንደነበር ይታወሳል፡፡ከዚህ በኋላ ቻይና የአፍሪካ ሲዲሲን ለመገንባት ዕቅድ እንዳላት፣ ከአፍሪካ አኅጉር ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ይረዳኛል ያለችውን ፕሮጀክት ለመገንባት በጀት መድባ ስትንቀሳቀስ ነበር፡፡ይሁንና የአፍሪካ ኅብረት የመሰብሰቢያ አዳራሽና የኅብረቱን ኮምፒዩተሮች መጥለፍና መረጃዎችን ወደ ቻይና መላክ የሚችሉ ቴክኖሎጂዎች ተጠምዳ እንደነበር፣ ይህም እ.ኤ.አ. በ2017 በመታወቁ ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ትኩረትን ስቦ እንደነበር በማውሳት፣ የአሜሪካ ቅሬታ ‹‹አሁንም ቢሆን ቻይና የአፍሪካ ሲዲሲ ማዕከልን ለመገንባት የምትሻው ለአፍሪካ አስባ ሳይሆን፣ የአፍሪካን ሲዲሲን በመሰለል፣ በአፍሪካ የሚገኙ በሽታዎችን ዘረመላዊ መረጃ በመሰብሰብ ለወደፊት የሚሆኑ መድኃኒቶችን ለማምረት የበላይነትን ለማግኘት በማለም የገባችበት ተግባር ነው፤›› በማለት ተችታለች፡፡ስለዚህም ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገነባውን የሲዲሲ ዋና መሥሪያ ቤት ሕንፃ ቻይና የምትገነባው ከሆነ፣ ለተቋሙ አሜሪካ የምታደርገውን ድጋፍ እንደምታውቆም ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዝተው ነበር፡፡ ስለዚህም የኢቦላን ወረርሽኝ መከሰት ተከትሎ እ.ኤ.አ. በ2017 የተመሠረተው የአፍሪካ ሲዲሲ መሥሪያ ቤት ግንባታ በቻይና እጅ እንዳይገባ የሚቻላቸውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ፕሬዚዳንቱ ተናግረው ነበር፡፡አሁን በቻይናው ሲሲኢሲሲ የግንባታ ተቋራጭ ኩባንያ የሚገነባውና ከአጠቃላዩ 9,000 ካሬ ሜትር መሬት ቅጥር ግቢ ውስጥ በ4,000 ካሬ ሜትር ላይ የሚያርፈው የዚህ ተቋም ዋና መሥሪያ ቤት የመሠረት ድንጋይ፣ የአፍሪካ ኅብረት የማኅበራዊ ጉዳዮች ኮሚሽነር አሚራ ኢልፋዲል መሐመድ፣ በአፍሪካ ኅብረት የቻይና አምባሳደር ሊዩ ዩሺ፣ የጤና ሚኒስትሯ ሊያ ታደሰ (ዶ/ር)፣ እንዲሁም የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በተገኙበት ኃይሌ ጋርመንት አካባቢ ተቀምጧል፡፡የአፍሪካና የቻይና ወዳጅነትን ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግረዋል የተባለለት ይኼ ፕሮጀክት በ25 ወራት ውስጥ የሚጠናቀቅ ሲሆን፣ በሥነ ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የማኅበራዊ ጉዳይ ኮሚሽነሯ አሚራ ኢልፋዲል ‹‹አፍሪካ እንተባበር ከሚላት ማንኛውም አካል ጋር ለመተባበርና አብሮ ለመሥራት ዝግጁ ናት›› ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ከዋና መሥሪያ ቤቱ በተጨማሪ በአምስት የአፍሪካ አገሮች ቀጣናዊ ጣቢያዎች እንደሚኖሩት የተነገረው የአፍሪካ ሲዲሲ በኬንያ፣ በናይጄሪያ በዛምቢያ፣ በጋቦንና በግብፅ የተለያዩ ቀጣናዎችን የሚያስተባብሩ ቢሮዎች ይኖሩታል ተብሏል፡፡ይሁንና ኢትዮጵያ የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ በመሆኗ እንዲህ ያለ ትልቅና ተጨማሪ አኅጉራዊ ቀጣና በአዲስ አበባ ሊገነባ አይገባውም የሚሉ እንደ ሞሮኮና  ደቡብ አፍሪካ ያሉ ተፅዕኖ ፈጣሪ አገሮችን በመጫን ውሳኔውን ለማስቀየር ጥረቶች የተደረጉ ቢሆንም፣ የአፍሪካ ሲዲሲ ማቋቋሚያ ሕግ ላይ የተቋሙ ዋና መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ኅብረት ዋና መሥሪያ ቤት የሚገኝበት አገር እንደሚሆን መጠቀሱ ጥረቱ እንዳይሳካ ካደረጉ ምክንያቶች አንዱ ነው፡፡ ይሁንና የኅብረቱ የመሪዎች ጉባዔ ሌላ አገር ከመረጠ የዋና መሥሪያ ቤቱ መቀመጫ ሊለወጥ እንደሚችልም ተደንግጓል፡፡የዋና መሥሪያ ቤቱ ግንባታ እ.ኤ.አ. በ2015 እንዲጀመር ታቅዶ እነዚህን በመሳሰሉ ምክንያቶች የዘገየ ቢሆንም፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬቱን አዘጋጅቶ ‹‹የአፍሪካ መንደር›› ተብሎ በሚጠራው ኃይሌ ጋርመንት አካባቢ ለተቋሙ ማስረከቡም ለዚህ ፍላጎት አለመሳካት የራሱን ሚና ተጫውቷል፡፡ይኼ የዋና መሥሪያ ቤት ግንባታ የቫይረሶችና ባክቴሪያዎች ላቦራቶሪ፣ ቢሮዎችና አፓርትመንቶችን የሚይዝ ሲሆን፣ የሕንፃዎቹ ንድፎች የተሠሩት ከዘረመል ማጉያ መነጽር (ማይክሮስኮፕ) ምሥልና የአፍሪካ የዕንጨት ቅርፃ ቅርፅ ጥበብ በመቅዳት እንደሆነ ተነግሯል፡፡", "passage_id": "b5db927dd907d4ffece617539b0bee32" }, { "passage": "ግንባታው ከተጀመረ ዘጠኝ ዓመታትን ያስቆጠረው የሀዋሳ ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተለያዩ ምክንያቶች እየተጓተተ ለምን እስካሁን መጠናቀቅ አልቻለም?በ2004 ግንባታው የተጀመረውና ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ ከ45-50 ሺህ ተመልካቾችን በወንበር እንደሚያስተናግድ የተነገረለት ስታዲየሙ በአራት ዓመታት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ቢጠበቅም በተለያዩ ምክንያቶች እየተጓተተ ዓመታት ተቆጥረው እስካሁን መጠናቀቅ አልቻለም፡፡ በ2008 ለመላው ኢትዮጵያ ውድድሮች ሲባል አፋጣኝ ሥራዎችን ሲከወን የነበረው የዚህ ስታዲየም ፕሮጀክት ከውድድሩ በኋላ ግን ያዘገመ ሥራዎች እየተሰሩበት አሁን ላይ “ቆሟል” የሚባልበት ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ሳትኮም በተባለ የኮንስትራክሽን ተቋራጭ ሲሰራ የቆየው ስታዲየሙ ባልተጠናቀቀበት ሁኔታ ከሀገር አቀፍ ስፖርታዊ ጨዋታዎች አንስቶ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ወላይታ ድቻ ክለቦች አህጉራዊ ውድድሮች ግልጋሎት ሰጥቷል። ስታዲየሙ በውድድር ወቅት በተለይ እንደ ችግር የሚነሳበት የመጫወቻ ሳሩን የመቀየር ሥራ በስድስት ወራት ውስጥ ተፈፃሚ ይሆናል ተብሎ ቢጠበቅም ወቅቱን መጠበቅ ሳይችል ይኸው ድፍን ሁለት ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ የመብራት (ፓውዛ)፣ ስክሪን ገጠማ፣ የሚዲያ ክፍል፣ የመልበሻ፣ የውስጥ ማማሟቂያ እና መፀዳጃ ቤቶች የተሰሩለት ቢሆንም የወንበር፣ የተጠባባቂ ተጫዋቾች መቀመጫ፣ ጥላ፣ መጠነኛ ማሻሻያን የሚሹ የዲዛይን ሥራዎች እንዲሁም የፊኒሺንግ ሥራዎች ይጠብቁታል። ከዚህም በተጨማሪ ከሜዳው ውጪ የሚገኙ ሁለት የእግር ኳስ መለማመጃ ሜዳዎች እና በዲዛይኑ ላይ የተካተቱ የሌሎች ስፖርቶች ማከናወኛ ግንባታዎች ከዚህ ቀደም በጥንድፊያ የተሰሩ በመሆናቸው በዲዛይኑ መሠረት መጠናቀቅ ይጠበቅባቸዋል።የደቡብ ክልል ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ የሺዋስ ዓለሙ ከሶከር ኢትዮጵያ ጋር ባደረጉት ቆይታ ስታዲየሙ አሁን ያለበት ሁኔታ እና እየተሰሩ ያሉ ሥራዎችን በዚህ መልኩ አስረድተዋል።“በመጀመሪያው ዙር ግንባታ በአመዛኙ ትልቁ ስታዲየም መሠረታዊ ሥራዎች እያለቁ ነው። ችግር የነበረበት የሳር ንጣፉ አሁን እየተስተካከለ ነው። ከዛ ውጪ ያለው የቴክኖሎጂ ገጠማው ነው፤ እሱ የኮንስትራክሽን ድርጅቱ ሳትኮም ያመጣው የውጪ ድርጅት ጋር በመሆን አብዛኛዎቹን የቴክኖሎጂ ሥራዎችን ጨርሷቸዋል፡፡ ባለፈው ህዳር እና ታኅሣሥ ላይ የቴክኖሎጂ ገጠማ ሥራው ተሰርቷል፡፡ በሁለተኛ ምዕራፍ የተያዘው የጣራ እና የወንበር ሥራ ነው የሚቀረው። እሱ በኮንትራክተሩ እና በክልላችን ኮንስትራክሽን ቢሮ አማካኝነት አዲስ የተሰራ ዲዛይን ስላለ ዲዛይኑ ላይ ማሻሻያ እንዲደረግ ተብሎ የማሻሻያ ሥራው እየተሰራ ነው። ይህ የዋናውን የስታዲየም ገፅታ የተመለከተ ጉዳይ ነው።“ከዚህ ጋር ተያይዞ ካፍ በተደጋጋሚ የሰጣቸው ኮመንቶች አሉ። በተሰጡን ኮመንቶች መሠረት ከማስተካከል አኳያ አንዳንዶቹ ከመጡት ገምጋሚ ቡድን ጋር ካለ የመረጃ ልውውጥ ችግር ጋር የተያያዘ ነው። ያ ደግሞ ሰነዶች ከታዩ በኃላ ለማስተካከል ተሞክሯል፡፡ የሚቀሩ ክፍሎችን የማደስ መሠረታዊ የሆኑ ሀሳቦች ቀርበዋል። የመጫወቻ ሜዳ፣ የመልበሻ ክፍል፣ የውስጥ ማማሟቂያን በተመለከተ በአመዛኙ በተሰጡት አስተያየቶች መሠረት ለማስተካከል ተችሏል፡፡ ከዋናው ስታዲየም ጋር በተጓዳኝ የማስፋፊያ ሥራዎች ደግሞ አሉ። የመለማመጃ ሜዳ፣ ትንንሽ ሜዳዎች (እንደ ቅርጫት ኳስ ሜዳ እና መሰሎች)፣ ውሀ መዋኛ እና ሌሎች ቀሪ ሥራዎች አሉ። ”ኮሚሽነሩ ሥለ ግንባታው በጊዜው አለመጓዝ ላነሳንላቸው ጥያቄ ማብራሪያቸውን በመቀጠል የበጀት፣ የኮሚቴ መቀያየር፣ ከተቋራጮች ጋር አለመግባባት፣ የፀጥታ ሁኔታ እና ኮሮና ወረርሺኝ ለፕሮጀክቱ መጓተት ምክንያት መሆናቸውን ገልፀዋል።“ሥራውን ከያዘው የኮንስትራክሽን ድርጅት ጋር አለመግባባት እየተፈጠረ በመሆኑ በአማካሪው እና በአሰሪ ቢሮው በኩልም ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶት ነበር፤ ነገር ግን ውጤታማ ባለመሆኑ እያነሳ ያለውም ጥያቄ በአሰራር ደረጃ የማይመለስ በመሆኑ ውሉን ለማቋረጥ እንቅስቃሴ ላይ ነን። የማስፋፊያ ሥራውን የሚሰራው ‘በረከት እንደሻው’ የሚባል ድርጅት ጋር ከ2008 ጀምሮ (የመላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ጀምሮ) ሲሰራ የነበረ ድርጅት ነው። የሚጠይቃቸው ጥያቄዎችን ከተገባው ውል አንፃር ሊመለሱ የማይችሉ ከመሆኑ ባለፈ ያለፉትን 18 ወራት ሥራ ላይም ስላልነበረ ተገምግሞ የመጨረሻ ውሳኔ ላይ እየተደረሰ ነው ያለው፡፡” ከተቋራጩ በተጨማሪ ፕሮጀክቱን የሚከታተለው ኮሚቴ በየጊዜው መለዋወጥ ሥራውን አስቸጋሪ አድርጎታል። ‘የሀዋሳ ስታዲየም የህዝብ ተሳትፎ እና አስተዳደር’ የሚባል ኮሚቴ አለ። እዚህ ክልል በነበረው የአመራር መለዋወጥ እና ሽግሽግ በአብዛኛውም ሥራ አስፈፃሚ ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩም በአጠቃላይ አሁን ስለሌሉ ያን የመተካት ጉዳይ ከክልሉ ባህልና ቱሪዝም እና ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጋር ተነጋግሮ የፈረሰውን ቦርድ መልሶ ለመሰየም እና ለማቋቋም እንቅስቃሴ ላይ ነው ያለነው።” ከዚህ ጎን ለጎን በሁለተኛው ምዕራፍ የሚካተቱ የፊኒሽንግ እና ብዙ ወጪ የሚያስወጣው የጣሪያ፣ የወንበር እንዲሁም ዙሪያ አጥር ግንባታ ለመስራት ባለፈው ክረምት ጨረታ ወጥቶ ነበር። ሆኖም የወጣውን የሚያሟላ አካል ስላልነበር፣ ለዛ የሚረዳ በቂ በጀትም ስላልነበረ በቴክኒክ ውድቅ ተደርጎ ተጨማሪ በጀት ወጥቶ በድጋሚ ጨረታ ለማውጣት ከ200 እስከ 250 ሚሊዮን ያስፈልጋል የሚል መመሪያ ስላለ ያን ለማድረግ በሒደት ላይ ነው ያለነው። ትልቅ ሀገር አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ውድድሮች ሲያስተናግድ የነበረ ሜዳ ቢሆንም በተጠበቀው ልክ ባለፉት ሁለት ዓመታት ሥራ አልተሰራም። ለሥራው የክልሉ መንግሥት በጀት በአግባቡ ሲበጅት ቢቆይም በነበረው የፀጥታ ችግር ጥቅም ላይ ማዋል አልተቻለም። በዚህ ዓመት ለመከናወን ሲታሰብ ደግሞ ለግንባታው የተያዙ አብዛኛው ወጪዎች ወደ ኮሮና ስለዞሩ የበጀት እጥረት አጋጥሟል።“የሳር መቀየር ሥራው እንደተባለው መከናወን ከነበረበት ጊዜ አንፃር በጣም ቆይቷል። ወደ መቀየሩ ሒደት ዘንድሮ ነው የተገባው። ግን ችግሩን በጥልቀት ገምግሞ ከማቅረብ አንፃር መዘግየቶች ነበሩ፡፡ አብዛኛው የሜዳውን ስራ የሚይዘው ይሄን ሳር የመቀየር ነው፡፡ ሳሩን ለመቀየርም በዝርዝር ነው እየተገመገመ የሄደው ለዚህ የሚመች ደረጃው የጠበቀ ኮረት የማስተካከል አፈሩን የማጠብ የፍሳሽ ሥርዓቱን የማስተካከል ጉዳይ አሁን በሚገባ እየሄደ ነው ያለው። ከኮንትራክተሩ ጋር የነበረን ውል በዚህ ሚያዚያ ወር ላይ የሚያልቅ የነበረ በመሆኑ በፍጥነት ነው ሲሰራ የነበረው። አሁን ላይ ያለበት ሁኔታ ጥሩ ነው። ያው የዘገየበት ሁኔታ የአስፈፃሚ አካላት መጓተት አመራሩ በፍጥነት መመሪያ ያለመስጠት ያመጣው ችግር ቢሆንም ዘንድሮ ያን ለማስተካከል ተሞክሯል፡፡ የሳር ንጣፉ በአምስት ወር ለመጨረስ ነው ስምምነት ላይ የተደረሰው። ጥሩ እየሄደ ከኮሮና መምጣት ጋር በተያያዘ ግን ዘግይቷል፡፡ አሁን ግን በፍጥነት ተመልሶ ወደ ስራ እንዲገባ መግባባት ላይ ስለተደረሰ በሁለት ወር የመጨረስ ስራ ላይ እንገኛለን። ችግሩ ተከስቷል፤ ለማስተካከልም ተዘግይቷል። ያም ቢሆን በአጭር ጊዜ ይጠናቀቃል፡፡ ”ስታዲየሙ መቼ እንደሚናቀቅ እና ቀጣይ ሥራዎች በምን መልኩ እንደሚካሄዱ ግልፅ መረጃ ማግኘት አዳጋች ሲሆን ካለው የሀገሪቱ ተጨባጭ ሁኔታ አንፃር በቂ የማጠናቀቂያ በጀት የማግኘቱ ጉዳይ አጠያያቂ ሆኖበታል። በጉዳዩ ላይም ለስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነሩ ጥያቄውን አንስተን ስታዲየሙን ለማጠናቀቅ እየሄዱ ስላሉበት መንገድ እና እቅድ የሚከተለውን ብለውናል።” ከዋናው ስታዲየም ጋር በምዕራፍ ሁለት መካተት ያለበት የጣሪያ እና የወንበር ሥራ የራሱ የሆነ በጀት ስለሚፈልግ ከመስተዳድር ምክር ቤት እና ከክልሉ ምክር ቤት ጋር ተነጋግሮ ማስመደብ፤ በመቀጠል ባለፉት ሁለት ዓመታት የዘገየውን ስታዲየም በምን አይነት መልኩ እናፋጥነው የሚለው ጉዳይ ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተነጋግረን አዲስ ቦርድም ተቋቁሞ ይሄን በበላይነት የሚመራውን ዳግም ለመመለስ በሒደት ላይ ነን።“እንደ ኮሚሽን የመጀመሪያው ምዕራፍ ዘንድሮ መጠናቀቅ አለበት የሚል አቋም ነው የያዝነው። በመጀመሪያው ዙር ቅድም ያልኩት የመጫወቻ ሳሩ ያልቃል፣ የቴክኖሎጂ ገጠማው ያልቃል፣ በዚህ ዙር ተጨማሪ ኮንትራት የተሰጡ የውጪ የማስፋፊያ በአመዛኙ ብዙዎቹ አልቀው የተወሰኑት በኮንትራክተሩ በተፈጠረው ችግሮች የተቋረጡ ቢኖሩም የተሰሩ ሥራዎች ግን አሉ፡፡ ከማስፋፊያ ስራዎች አንፃር 86% ተሰርቷል፡፡ በትልቁ ስታዲየምም ላይ መሰራት ካለበት መሀከል 96% ተሰርቷል፡፡ የማስተካከል እና የለቀማ ስራዎች ሲቀሩ ይሄን ዘንድሮ ለመጨረስም ነው ያሰብነው። የአጥር ግንባታ እና የላንድ ስኬፒንግ ስራ በሚቀጥለው በጀት ዓመት አጋማሽ ላይ እንጨርሳለን የሚል ነው የኮሚሽኑ እቅድ። ”እስከ አሁን 750 ሚሊዮን ብር ፈሰስ እንደተደረገበት የተነገረለት ስታዲየሙን ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ለአዲስ የኮንስትራክሽን ተቋራጭ ጨረታ አውጥቶ በቀጣይ ሥራ የሚጠብቀው ሲሆን ዘንድሮ ወደ ሥራ ለመመለስ 20 ሚሊዮን ብር በጀት ቢመደብለትም በተለያዩ ምክንያቶች መንግስት ከዚህ በጀት ላይ 16 ሚሊዮን ብሩን ለሌላ ስራ አውሎታል ተብሏል፡፡ በቀጣይ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅም ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብን እንደሚጠይቅ ታውቋል።", "passage_id": "e6e7e64ab165afacb36b0ee524cf2e98" } ]
d12fe24d1751afad52129fe75ad42bad
ba0430a10d73ea907fb452f93e417c2b
መልስ ያላገኘው የአፍሪካውያን የአገር አቋራጭ ሩጫ ጥያቄ
አትሌቲክስን ፈታኝ ስፖርት ከሚያደርጉት ውድድሮች አንዱና ዋነኛው የአገር አቋራጭ ሩጫ ነው። የአገር አቋራጭ ውድድር አትሌቲክስን ፈታኝ ብቻም ሳይሆን ተወዳጅና ቀልብ ሳቢ ካደረጉት ምክኒያቶች አንዱ ነው ቢባል ስህተት አይሆንም። በገባ ወጣ መልክዓምድር፤ ኮረብታና ቁልቁለት እንዲሁም በጭቃና አልፎ አልፎም በበረዶ ክምር መሰናክሎች የታጀበው ይህ ውድድር አትሌቶች ከመምና ከጎዳና ላይ ውድድሮች ወጥተው ራሳቸውን በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚፈትኑበት ነው።የአገር አቋራጭ ሩጫ የምስራቅ አፍሪካውያን የበላይነት እየገዘፈበት ከመጣ ጀምሮ ግን ተወዳጅነቱ እየቀነሰ የሚሰጠውም ትኩረት እያነሰ መጥቷል። ይህም ከአውራው የስፖርት መድረክ ኦሊምፒክ እንዲወጣ ከማድረጉ ባሻገር በአፍሪካውያን ላይ የፈጠረው ተጽዕኖ በቀላል የሚታይ አይደለም። የዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና በየሁለት ዓመቱ ራሱን ችሎ የሚካሄድ ቢሆንም በዋናው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮናም ውጪ ነው። የቀድሞው የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የአሁኑ የዓለም አትሌቲክስ በእንግሊዛዊው የቀድሞ የአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር ኮከብ አትሌት ሴባስቲያን ኮ ፕሬዚዳንትነት መመራት ከጀመረ ወዲህ ውድድሩን ወደ ኦሊምፒክ ለመመለስ እንቅስቃሴ መጀመሩ ይታወቃል።የአገር አቋራጭ ሩጫን ወደ ኦሊምፒክ የመመለስ እንቅስቃሴ አሁን የተጀመረ ባይሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ጠንከር ያሉ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ። ከዓመት በፊት በአርጀንቲና ቦነ ሳይረስ በተካሄደው የወጣቶች ኦሊምፒክ ጨዋታ ላይ እንዲካተት መደረጉ አንድ ርምጃ እንደነበር ቢታወስም የአፍሪካውያን ጥያቄ አሁንም ድረስ መልስ አላገኘም።የአገር አቋራጭ ሩጫ ለመጨረሻ ጊዜ በኦሊምፒክ መድረክ የተካሄደው እኤአ በ1924 የፓሪስ ኦሊምፒክ ነበር። ቦነ ሳይረስ በወጣቶች የኦሊምፒክ ጨዋታም ቢሆን ይህን ውድድር ከዘመናት በኋላ በአዲስ መልኩ የማዘጋጀቱን እድል አግኝታለች። በዚህ የወጣቶች ኦሊምፒክ የመካከለኛ ርቀት አትሌቶች በተለይም አንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር፤ ሦስት ሺ ሜትርና ሁለት ሺ ሜትር መሰናክል ተወዳዳሪዎች የማጣሪያ ውድድር በማድረግ በሁለቱም ፆታ አርባ ስምንት አርባ ስምንት አትሌቶች ተፎካክረውበታል፡፡ ይህም ጅምር አገር አቋራጭ ሩጫ በዋናው የኦሊምፒክ ውድድር እንዲካተት ትልቅ መሰረት ይሆናል ተብሎ ታምኖበታል። የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንት ሴባስቲያን ኮ« የአገር አቋራጭ ሩጫን በኦሊምፒክ መድረክ ማየት የረጅም ጊዜ ፍላጎታችን ነው፤ በቦነ ሳይረስ የወጣቶች ኦሊምፒክ መካተቱም በዋናው ኦሊምፒክ ለማካተት የሚደረገውን ጥረት ያጠናክራል» በማለት ከዓመት በፊት አስተያየት መስጠታቸውን ተከትሎም ትልቅ ተስፋ ታይቶ ነበር። ሴባስቲያን ኮ አገር አቋራጭ ሩጫ በተለይም የመካከለኛ ርቀት አትሌቶች አካል ብቃት የሚታይበት በመሆኑ በኦሊምፒክ መድረክ መካተት እንደሚገባው ፅኑ እምነት አላቸው። በዚህ አቋማቸው መፅናታቸውን ግን እርግጠኛ መሆን አይቻልም፡፡የአገር አቋራጭ ሩጫ በዋናው ኦሊምፒክ መድረክ እኤአ ከ1912 እስከ 1924 በወንዶች መካከል ብቻ ተካሂዶ ነው የተቋረጠው። ከዚህ በኋላ ግን የኦሊምፒክ መርሐግብር መሆኑ ቀርቶ የአትሌቲክስ ጉዳይ ብቻ ሆኖ ቀርቷል። ለዚህ ብዙ ምክኒያቶች በተለያዩ ጊዜዎች የሚቀርቡ ሲሆን ለመጨረሻ ጊዜ በተካሄደው የፓሪስ ኦሊምፒክ ላይ በርካታ አትሌቶች ውድድሩ ከብዷቸው ሲፍረከረኩና ራሳቸውን ሲስቱ ጭምር ነበር። ይሁን እንጂ አገር አቋራጭ ሩጫ በተካሄዱባቸው ሦስት ኦሊምፒኮች የፊንላንድ አትሌቶች የበላይነት እንደነበር በታሪክ ተጽፎ ይገኛል። ከዚህ በኋላ የተፈጠረው የአትሌቲክስ ትውልድ በተለይም በረጅምና መካከለኛ ርቀቶች የአፍሪካውያን የበላይነት እየጎላ የመጣበት እንደመሆኑ በአገር አቋራጭ የዓለም ቻምፒዮናዎችም ይሁን በግል አፍሪካውያን የበላይነቱን ተቆጣጥረውታል። ይህም አገር አቋራጭ ሩጫ ወደ ኦሊምፒክ እንዲመለስ የሚደረገውን ሂደት እንዳዘገየው የሚያምኑ በርካቶች ናቸው። አፍሪካውያን ይህ ውድድር ወደ ኦሊምፒክ እንዲመለስ ብዙ ጊዜ ታግለዋል። ጀግናው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ፤ የመም ውድድሮችና የአገር አቋራጭ ውድድሮች ንጉሱ አትሌት ቀነኒሳ በቀለና የኬንያው ታሪካዊ አትሌት ፖል ቴርጋት አገር አቋራጭ ውድድር ወደ ኦሊምፒክ እንዲመለስ ትግል ካደረጉት መካከል ይጠቀሳሉ። በተለይም እነዚህ ሦስት ድንቅ የምስራቅ አፍሪካ የምን ጊዜም ኮከብ አትሌቶች እኤአ 2008 ላይ ለወቅቱ የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ጃኩዌስ ሮግ በአንድ ላይ ጥያቄ አቅርበው እንደነበር ይታወሳል። ይህን ሃሳብ የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበርና በርካታ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን የደገፉት ቢሆንም ተግባራዊ ሳይሆን ዘመናትን ተሻግሯል።አገር አቋራጭ በኦሊምፒክ መካተት አይኖርበትም የሚሉ ሃሳቦች በብዛት ከምዕራባውያን ዘንድ ሲነሳ ይሰማል። ለዚህም የተለያዩ መላ ምቶችን ያስቀምጣሉ። በዋናነት አገር አቋራጭ ሩጫ የክረምት ኦሊምፒክ ስፖርት እንጂ የበጋ ኦሊምፒክ ስፖርት አይደለም የሚሉ በርካታ ናቸው። አገር አቋራጭ ሩጫ በተለምዶ ከአስር እስከ አስራ ሁለት ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን በበጋ ኦሊምፒክ ወቅት መካሄዱ እኤአ በ1924 ላይ አትሌቶች እንደተፍረከረኩት አይነት ችግር ይፈጠራል ወይንም የአየር ብክለት ሊኖር ይችላል የሚል ሃሳብም በስፋት ይነሳል። በሌላ በኩል የመም ውድድሮችና ማራቶን በኦሊምፒክ ስለ ተካተተ አገር አቋራጭ ሩጫ አያስፈልግም ወይንም የሚፈጀው ጊዜ ረጅም ስለሆነ አያስፈልግም የሚሉ ሃሳቦች ሲንፀባረቁ ይስተዋላል። አገር አቋራጭ ሩጫ በኦሊምፒክ መካተት የለበትም የሚሉት ወገኖች ከነዚህ የበለጠ ጠንካራ የመከራከሪያ ሃሳብ ይዘው ሲቀርቡ አይታዩም። እነዚህ የመከራከሪያ ነጥቦች ቢሆኑም በራሳቸው ምክኒያታዊና አሳማኝ ናቸው ተብሎ አይታሰብም። ለምሳሌ ያህል ዋነኛ ምክኒያት የሆነው አገር አቋራጭ ሩጫ የክረምት ኦሊምፒክ ውድድር ነው መሆን ያለበት የሚለው ሃሳብ ከምዕራባውያን ጥቅም ጋር የተያያዘ ስለመሆኑ ማመላከት ይቻላል። አገር አቋራጭ ሩጫ በበጋ ኦሊምፒክ መካሄዱ የአየር ብክለት ሊኖር ይችላል ወይንም ከፍተኛ ሙቀት ይኖራል የሚለው ስጋት በራሱ የኦሊምፒክ አዘጋጅነት ከምዕራባውያን አይወጣም የሚል አንድምታ አለው። በእርግጥ ኦሊምፒክን ከዚህ ቀደም የሚያዘጋጁት አቅም ያላቸው አገራት አብዛኞቹ ምዕራባውያን ቢሆኑም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወደ ደቡብ አሜሪካና ሌሎች የኤሽያ አገራት እየሄደ ነው። ለዚህም ያለፈውን የሪዮ ኦሊምፒክና መጪውን የቶኪዮ ኦሊምፒክ መጥቀስ በቂ ነው። ከዚህ በኋላም ቢሆን የዓለም ዋንጫን የማስተናገድ አቅም እንዳላቸው ያሳዩ አፍሪካ አገራት እድሉን ያገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል። ከዚህ በተጨማሪ ምዕራባውያን በጋ ብለው በሚጠሩት ወቅት የክረምት ወራትን የሚያስተናግዱ አገሮች ኦሊምፒክን ሊያዘጋጁ እንደሚችሉ ልብ መባል አለበት። ከዚህ ጎን ለጎን ውድድሩ ረጅምና አድካሚ በመሆኑ በበጋ ወራት አይመችም የሚለው ሃሳብ በራሱ አርባ ሁለት ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የማራቶን ውድድር በበጋ ኢሊምፒክ መኖሩን ልብ ያለው አይመስልም።ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ይህ ሃሳብ ሰፊ እንቅስቃሴ እየተደረገበት የሚገኝ ቢሆንም አሁንም ጠንከር ያለ ግፊት ያስፈልገዋል። አዲስ ዘመን ከሁለት ዓመት በፊት በዚሁ ጉዳይ ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮችን አነጋግሮ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተሉ በተገኘው አጋጣሚ ጥያቄ እያቀረቡ እንደሚገኙ ምላሽ መስጠታቸው ይታወሳል። ይህን ሃሳብ አሁንም አጠናክረው ይቀጥላሉ ተብሎ ይጠበቃል። ይህ ጉዳይ የበለጠ አፍሪካውያንን ተጠቃሚ የሚያደርግ በመሆኑ የአፍሪካ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር (ሲ ኤኤ)፤ የአፍሪካ ኦሊምፒክ ኮሚቴ(አኖካ)፤ የአፍሪካ ተጽዕኖ ፈጣሪ መገናኛ ብዙሃንና ጋዜጠኞች ግፊት ማድረግ አለባቸው ተብሎ ይታመናል። የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንት ሴባስቲያን ኮ ምዕራባዊ ቢሆኑም በአትሌቲክሱ ያሳለፉ በመሆናቸው አገር አቋራጭ ሩጫ ወደ ኦሊምፒክ እንዲመለስ ጥረት እያደረጉ ነው። ይሁን እንጂ በዚህ ውድድር የአፍሪካውያን ብቻ የበላይነት የሚጎላ በመሆኑ ምዕባራውያን ወደ ኦሊምፒክ እንዲመጣ ፍላጎት አላቸው ማለት ይከብዳል።በኦሊምፒክ መድረክ አሜሪካና ምዕራባውያን በርካታ ሜዳሊያ በመሰብሰብ የበላይነት ይዘው የሚያጠናቅቁት በአንድ ስፖርት አይነት ብቻ ከአስር በላይ ሜዳሊያ መሰብሰብ የሚያስችላቸው እድል ስላላቸው ነው። ለዚህም በውሃ ዋና ውድድር አንድ አትሌት ብቻ ከአስር በላይ የወርቅ ሜዳሊያ የሚያፍስበት አጋጣሚ እንዳለ ማስቀመጥ ይቻላል። ምዕራባውያኑ እንዲህ አይነቱ አጋጣሚ በኦሊምፒክ እንዲስፋፋና የበላይነታቸውን ይዘው እንዲዘልቁ ያገኙትን እድል ይጠቀማሉ። አሁንም በቀጣዩ የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ እንኳን የነሱ ፍላጎት ያለባቸው በርካታ ስፖርቶች እንዲካተቱ ማድረግ ችለዋል። አፍሪካውያንም ከምዕራባውያን ጋር በኦሊምፒክ ተፎካካሪ ሆነው ለመገኘት እንደ አገር አቋራጭ ሩጫ አይነቶችን ሊጠቀሙ ይገባል። አገር አቋራጭ ሩጫ በኦሊምፒክ ቢካተት በውድድሩ አፍሪካውያን የበላይነት ስላላቸው በኦሊምፒክ የሚያገኙት የሜዳሊያ ቁጥርም ከፍ ሊል እንደሚችል ግልፅ ነው።አዲስ ዘመን ሐምሌ 23/2012ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=36334
[ { "passage": "ባለፉት አስር ዓመታት በአትሌቲክስ ስፖርት ውስጥ በርካታ ክስተቶች ተስተናግደው አልፈዋል። ለቁጥር የሚታክቱ ክብረወሰኖች ከመሻሻላቸውም ባለፈ በሰው ልጅ ሊደፈሩ ይችላሉ በሚል የማይጠበቁና የማይገመቱ ታሪካዊ ክንውኖችም ታይተዋል። ከእነዚህ መካከል በተለይ በስፖርቱ አጭር ርቀት ውድድር (100ሜትር) እና በረጅሙ ርቀት (ማራቶን) የተመዘገቡት ስኬቶች የሰውን ልጅ አቅም በትክክልም ማሳየት የሚያስችሉ ሆነዋል። ታዲያ በአስሩ ዓመታት ከታዩና ክብረወሰንም ካስመዘገቡ አትሌቶች መካከል የተሻለው ማን ነው? በዚህ ጥያቄ ላይ ተንተርሶ ምርጫውን\nያካሄደው ደግሞ እአአ በ1940 መሰረቱን በአሜሪካ በማድረግ የተቋቋመውና ትኩረቱን በመምና ሜዳ ተግባራት ስፖርቶች ላይ ያደረገው\nመጽሄት ነው። መጽሄቱ እአአ ከ2010-2019 ድረስ ባሉት ዓመታት ከጎዳና ላይ ውድድሮች ባሻገር ባሉት ውድድሮች አስር አትሌቶችን\nበእጩነት በማቅረብ ምርጫውን በአዲሱ የፈረንጆች ዓመት መጀመሪያ ነበር የጀመረው። በተሰጠው ድምጽ መሰረትም ኬንያዊው የ800 ሜትር\nአትሌት ዴቪድ ሩዲሽያ ተመራጭ ሊሆን ችሏል። በእጩነት ከቀረቡት አትሌቶች መካከል\nአንዱ በአጭር ርቀት የአትሌቲክስ ተጽእኖ ማሳደር የቻለው ጃማይካዊ አትሌት ዩሲያን ቦልት ነው። አሁን ራሱን ከተወዳዳሪነት ያገለለው\nቁመተ መለሎ አትሌት በ100 ሜትር የሸፈነበት 9ሰከንድ ከ63 ማይክሮ ሰከንድ የምንጊዜም የርቀቱ ምርጥ አትሌት ያደርገዋል። በውድድር\nተሳትፎው ከደረጃ ወርዶ የማያውቀው አትሌት አራት የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያዎችን ከማጥለቅ ባሻገር የዓለም ቻምፒዮን በመሆንም ክብረወሰኑን\nአርቆ የሰቀለ አትሌት መሆኑ ምርጫውን በአሸናፊነት ያጠናቅቃል በሚል ይጠበቅ ነበር። በረጅም ርቀት የመም ላይ ውድድሮች በኢትዮጵያዊያኑ ጀግና አትሌቶች እግር የተተካው እንግሊዛዊ አትሌት\nሞሃመድ ፋራም በእጩነት ከቀረቡት መካከል ነበር። የዓለም ቻምፒዮናው በኦሊምፒክ አራት የወርቅ ሜዳሊያዎችን ያሳካ ሲሆን፤ በ5ሺ\nእና 10ሺ ርቀቶች ሃገሩን በተደጋጋሚ ለማስጠራት ችሏል። አትሌቱ ምንም እንኳን ከመም ወደ ጎዳና ላይ ውድድሮች ባደረገው ሽግግር\nእንደሚጠበቀው ውጤታማ ባይሆንም ያለፉት አስር ዓመታት ግን ለእርሱ አስደሳች ነበሩ። ከመም ይልቅ በማራቶን ስሙ የገነነውና የዚህ ወቅት የርቀቱ ቁጥር አንድ አትሌት የሆነው ኬንያዊ ኢሉድ\nኪፕቾጌም ቀዳሚ ተመራጭ ይሆናል በሚል ከሚጠበቁት እጩዎች መካከል ነበር። የዓለም ክብረወሰን ባለቤቱ እንዲሁም ማራቶንን ከ2 ሰዓት\nበታች የመግባት ሙከራውን ያሳካው አትሌት በሮጠበት ጫማ ምክንያት ውዝግቦችን ያስተናግድ እንጂ የጎዳና ላይ ሩጫዎች ንጉስነቱን ማንም\nሊቀማው እንደማይችል ነው አዘጋ ጆቹ ያረጋገጡት። አሜሪካዊያኑ ክርስ ቲያን ቴይለርና አሽተን ኢትን፣ ደቡብ አፍሪካዊው ዋይዴ ቫን ኔኬርክ፣ ፈረንሳ\nዊው ሬናውድ ላቪሌኔ፣ የኳታሩ ሙታዝ ባርሺም እንዲሁም ጀርመናዊው ሮበርት ሃርቲንግም ከአስሩ እጩዎች መካከል ይገኙበታል። ከእጩዎቹ መካከል በተለይ ‹‹የዓለም ፈጣኑ ሰው›› በሚል የሚታወቀው ጃማይካዊ አትሌት አብላጫውን\nድምጽ ያገኛል የሚል ግምት ያግኝ እንጂ አሸናፊ የሆነው ግን ዴቪድ ሩዲሽያ ነው። የለንደንና ሪዮ ኦሊምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤቱ\nእንዲሁም የዴጉና ቤጂንግ የዓለም ቻምፒዮናው አትሌት፣ በተለይ እአአ በ2012ቱ የለንደን ኦሊምፒክ ርቀቱን ያጠናቀቀበት ሁኔታ በአስር\nዓመታት ከማይዘነጉ ትዝታዎች መካከል ቀዳሚው በሚል በዓለም አትሌቲክስ መመረጡ የሚታወስ ነው። አትሌቱን አስደናቂ ከሚያደርጉት ምክንያቶች\nመካከል አንዱ፣ በርቀቱ የዓለም ክብረወሰንን ለሶስት ጊዜያት(1:41.09፣ 1:41.01፣ 1:40.91) መስበር መቻሉ ነው። መጽሄቱ መሰል ምርጫዎችን ማካሄድ የጀመረው እአአ በ1960ዎቹ ሲሆን፣ የመጀመሪያው አሸናፊም ኒውዝላንዳዊው\nፒተር ስኔል ነበር። እአአ የ1970ዎቹን ክብር ደግሞ የሶቬት ህብረት አትሌት የሆነው ቪክቶር ሳኔይቭ ነበር የወሰደው። በ1980ዎቹ\nአሜሪካዊው ካርል ሉዊስ ምርጥ ሲሰኝ፤ የ90ዎቹንም ሌላኛው የሃገሩ ልጅ ሚካኤል ጆሃንሰን አሸናፊ ሆኗል። እአአ ከ2000-2009\nባሉት ዓመታት ምርጥ አትሌትነት ምርጫ ወደ ኢትዮጵያ የመጣ ሲሆን፤ አንበሳው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ቀዳሚ ሊሆን ችሏል። አዲስ ዘመን የካቲት 2/2012ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "c1a3934ef128e2c24bafaf397641a09b" }, { "passage": " በፊንላንድ ሄልሲንኪ ከተማ እኤአ በ1983 የተጀመረው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና የዓለማችን ትልቁ የአትሌቲክስ መድረክ በመሆን ያለፉትን አርባ ዓመታት አሳልፏል። እኤአ በ1987ና 1991 በአራት ዓመት ልዩነት የጣሊያኗ መዲና ሮምና የጃፓኗ ቶኪዮ ይህን ታላቅ ውድድር ያዘጋጁ አገሮች ናቸው። ከቶኪዮ ወዲህ ግን ውድድሩ በሁለት ዓመት ልዩነት ነው እየተካሄደ የሚገኘው። የጀርመኗ ስቱትጋርት፤ የስዊድኗ ጉተንበርግ፤ የግሪኳ አቴንስ፤ የስፔኗ ሴቪሊ፤ የካናዳዋ ኤድመንተን፤ የፈረንሳይ መዲና ፓሪስ፤ የፊንላንዷ ሄልሲንኪ (ለሁለተኛ ጊዜ) የጃፓኗ ኦሳካ፤ የጀርመኗ በርሊን፤ የደቡብ ኮሪያዋ ዴጉ፤ የሩሲያዋ ሞስኮና የቻይናዋ ቤጂንግና የእንግሊዟ ለንደን ቻምፒዮናውን በሁለት ዓመት ልዩነት በቅደም ተከተል መድረኩን አዘጋጅተውታል። የዘንድሮ ተረኛዋ የካታሯ ዶሃ ስትሆን የምዕራባውያን መገናኛ ብዙኃን ትኩረት ቢነፍጓትም ከአምስት ወራት በኋላ ለሚጠብቃት ታላቅ የስፖርት ድግስ ሽርጉድ ማለት ጀመራለች። የአሜሪካዋ ዩጂንም ቀጣዮን ቻምፒዮና ለማዘጋጀት ወረፋ ይዛለች። ኢትዮጵያም ቻምፒዮናው ከተጀመረ አንስቶ በመሳተፍ ላይ ትገኛለች። የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና አሁን ያለውን መልክ ይዞ መካሄድ ከመጀመሩ በፊት እኤአ በ1913 የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ማህበር ኦሊምፒክ እንደ ዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ያገለግላል ብሎ አምኖበት ነበር። ይህም ለሃምሳ ዓመታት ያህል አገልግሎ 1960ዎቹ ውስጥ በርካቶቹ የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ማህበር አባል አገሮች «የራሳችን የሆነ ውድድር ይኑረን» ብለው ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት እኤአ በ1976 ፑርቶሪኮ ላይ በተደረገ ዓመታዊ የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ማህበር ስብሰባ ላይ የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ከኦሊምፒክ ተለይቶ ራሱን የቻለ ውድድር እንዲያካሂድ ተወሰነ። በእዚህን ወቅት የመጀመሪያውን ውድድር ለማስተናገድ የምዕራብ ጀርመኗ ስቱትጋርትና የፊንላንዷ ሄልሲንኪ ጥያቄ አቀረቡ። እኤአ በ1952 ኦሊምፒክን ያስተናገደችው ሄልሲንኪ እድሉን አገኘች። የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በውድድር አይነትና በተሳታፊዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ በርካታ ለውጦችን አስተናግዷል። እኤአ በ1983 ከመቶ 54 አገራት የተውጣጡ1 ሺ 300 አትሌቶች ተሳታፊ ነበሩ። ይህ ቁጥር እኤአ 2003 ፓሪስ ላይ ተካሂዶ በነበብቻ ሳይሆን በተለያዩ የውድድር አይነቶችም በርካታ ለውጦች ታይተዋል። በተለይም ወንዶች በሚወዳደሩባቸው የውድድር አይነቶች ሴቶችም ተካፋይ እንዲሆኑ መደረጉ የቻምፒዮናው ትልቅ ለውጥ ነው። አሁን ላይ በዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ወንዶች የሚወዳደሩበት ለሴቶች ያልተፈቀደ የሃምሳ ኪሎ ሜትር የርምጃ ውድድር ብቻ ነው። እኤአ በ1987 የሴቶች አስር ሺ ሜትር ሩጫና አስር ኪሎ ሜትር ርምጃ ውድድር የዓለም ቻምፒዮናን የተቀላቀለ አዲስ የውድድር አይነት ነው። ከስድስት ዓመት በኋላም የሴቶች ስሉስ ዝላይ የውድድሩ አካል ሆኗል። እኤአ በ1995 የሴቶች አምስት ሺ ሜትር ሩጫ የሦስት ሺ ሜትርን ወክሎ የውድድር አካል ሆነ። እኤአ በ1999 ደግሞ የሴቶች ምርኩዝ ዝላይና መዶሻ ውርወራ የውድድር አካል ከመሆናቸው በተጨማሪ የሴቶች አስር ኪሎ ሜትር ርምጃ ውድድር በሃያ ኪሎ ሜትር ርምጃ ውድድር ተተካ። እኤአ በ2005 የሴቶች ሦስት ሺ ሜትር መሰናክል ውድድር ተጨመረ። የለንደኑን ቻምፒዮኗ ሳይጨምር ባለፉት 15 ረው ቻምፒዮና ከሁለት መቶ ሦስት አገሮች የተውጣጡ 1 ሺ 907 አትሌቶች አሻቅቧል። በዓለም ቻምፒዮና የተሳታፊዎች ቁጥር የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮናዎች 98 አገራት የሜዳሊያ ሰንጠረዥ ውስጥ የገቡ ሲሆን፣ 2036 ሜዳሊያዎች (670 የወርቅኸ 685 የብርና 681 የነሐስ) ለአሸናፊዎች ተበርክተዋል፡፡ ከ16ኛው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በፊት የምንጊዜም የሜዳሊያ ስብስብ ደረጃን በድምሩ 323 ሜዳሊያዎች (143 የወርቅ፤ 96 የብርና 84 የነሐስ) በመሰብሰብ አሜሪካ አንደኛነቷን አስጠብቃለች፡፡ ሩሲያ 172 ሜዳሊያዎች (55 የወርቅ ፤ 60 የብርና 57 የነሐስ)፤ ኬንያ 128 ሜዳሊያዎች (50 የወርቅ፤ 43 የብርና 35 የነሐስ) ፤ ጀርመን 108 ሜዳሊያዎች (33 የወርቅ፤ 35 የብርና 40 የነሐስ)፤ ጃማይካ 110 ሜዳሊያዎች (31 የወርቅ፤ 44 የብርና 35 የነሐስ)፤ ታላቋ ብሪታኒያ 89 ሜዳሊያዎች (25 የወርቅ፤ 30 የብርና 34 የነሐስ)፤ ሶቭዬት ህብረት 77 ሜዳሊያዎች (22 የወርቅ፤ 27 የብርና 28 የነሐስ) እንዲሁም ኢትዮጵያ 72 ሜዳሊያዎች (25 የወርቅ፤ ቦልትን ያክል በዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በርካታ ሜዳሊያዎችን የሰበሰበ አትሌት የለም። ቦልት አስራ አንድ የወርቅና ሁለት የብር በማጥለቅ ቀዳሚ ነው። አሜሪካዊው ካርል ሌዊስ ስምንት የወርቅ፤ አንድ የብርና አንድ የነሐስ ሜዳሊያዎች በማጥለቅ ተከታይ ነው። በተመሳሳይ አሜሪካዊው ሚካኤል ጆንሰን ስምንት የወርቅ ሜዳሊያ በማጥለቅ ሦስተኛ ነው። ሌላኛው አሜሪካዊ ላሻውን ሜሪት ስድስት የወርቅና ሁለት የብር ሜዳሊያ በመውሰድ አራተኛ ነው። የረጅም ርቀት ነጉሱ ኃይሌ ገብረስላሴ አራት የወርቅ ሁለት የብርና አንድ የነሐስ ሜዳሊያ በማጠለቅ አምስተኛ ደረጃ ላይ ይቀመጣል። የቀድሞ የምርኩዝ ዝላይ ባለ ክብረወሰኑ ዩክሬናዊው ሰርጌ ቡካ ስድስት የወርቅ ሜዳሊያዎችን በዓለም ቻምፒዮና መድረክ በማጥለቅ ኃይሌን ይከተላል። አሜሪካዊው ጃርሚ ዋሪነር አምስት የወርቅና አንድ የብር ሜዳሊያ ይዞ ሰባተኛ ነው። የአስርና አምስት ሺ ሜትር ባለ ክብረወሰኑ ቀነኒሳ በቀለ በአምስት የወርቅና አንድ የነሐስ ሜዳሊያ ይከተላል። በሴቶች የረጅም ርቀት ንግስቷና የአምስትና22 የብርና 25 የነሐስ) በማስመዝገብ እስከ 7 ያለውን ደረጃ አከታትለው ይዘዋል፡፡ ጃማይካዊው የአጭር ርቀት ንጉስ ዩሴን አስር ሺ ሜትር የዓለም ክበረወሰን ባለቤቷ ጥሩነሽ ዲባባ በዓለም ቻምፒዮና መድረክ አምስት የወርቅ ሜዳሊያ ብታጠልቅም፣ ከአንድ እስከ አስር ባለው ደረጃ ውስጥ አትካተትም። ጃማይካዊቷ ማርሌን ኦቴይ ሦስት የወርቅ፤ አራት የብርና ሰባት የነሐስ ሜዳሊያ በመሰብሰብ በአስራ አራት ሜዳሊያዎች ቀዳሚ ነች። አሜሪካዊቷ አሊሰን ፌሊክስ ስምንት የወርቅ፤ አንድ የብርና አንድ የነሐስ በማጥለቅ በአስር ሜዳሊያዎች ሁለተኛ ነች። ሌላኛዋ አሜሪካዊት ጄርል ሚልስ ክላርክ በአራት ወርቅ፤ ሦስት ብርና ሁለት ነሐስ ትከተላለች። ጃማይካዊቷ ቬሮኒካ ካምቤም ብሮውን ቀጣዩ ደረጃ ላይ ትገኛለች። በዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ታሪክ በበርካታ ቻምፒዮናዎች ላይ በመካፈል ፖርቹጋላዊቷ የአስርና የሃያ ኪሎ ሜትር ርምጃ ተወዳዳሪ ሰሳን ፌተር እኤአ ከ1991 እስከ 2011 ድረስ በአስራ አንድ ቻምፒዮናዎች በመሳተፍ ትልቅ ታሪክ አላት። ስፔናዊው የሃምሳ ኪሎ ሜትር ርምጃ ተወዳዳሪ ጂሰስ ኤንጅል ጋርሺያም እኤአ ከ1993 እስከ 2013 ድረስ በአስራ አንድ ቻምፒዮናዎች በመካፈል ተመሳሳይ ታሪክ አለው።አዲስ ዘመን የካቲት 7/2011ቦጋለ አበበ", "passage_id": "06685c2154b650e4de54c7efb313a9b9" }, { "passage": "የዓለም አትሌቲክስ ከሚያዘጋጃቸው ዓመታዊ የዙር ውድድሮ መካከል አንዱ የዓለም ቤት ውስጥ የዙር ውድድር ነው። እኤአ በ2016 መካሄድ የጀመረው ይህ ውድድር በትራክና በሜዳ ተግባራት የውድድር ዓይነቶችን ማሳደግ ዓላማው ሲሆን፤ የዳይመንድ ሊግን አካሄድ የሚከተልም ነው። በዳይመንድ ሊግ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ በዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ተሳታፊ ለመሆን መስፈርት እንደሚሆነው ሁሉ፤ በዚህ የዙር ውድድር ውጤታማ መሆንም በዓለም የቤት ውስጥ ቻምፒዮና መሸጋገሪያ በመሆን ያገለግላል። ሲጀመር በአራት ዙር የሚካሄደው ይህ\nውድድር ሁለት አህጉራትን በማካለል ሶስቱን በአውሮፓ አንዱን ደግሞ በአሜሪካዋ ፖርትላንድ በማድረግ ይከናወን ነበር። ከቀናት በኋላ\nበሚጀመረው በዘንድሮው የቤት ውስጥ የዙር ውድድርም ሁለት መዳረሻዎችን በመጨመር ስድስት ዙሮችን የሚያካልል ይሆናል። በዚህ ውድድር\nላይ የሚካፈሉ አትሌቶችም በዚህ ዓመት በናንጂንግ በሚካሄደው የዓለም የቤት ውስጥ ቻምፒዮና ለመካፈል ከማስቻሉም በላይ የ20 ሺ\nየአሜሪካ ዶላር ተሸላሚ ያደርጋቸዋል። ከሶስት ቀናት በኋላ በሚጀመረው በዚህ\nውድድር ላይም እጅግ ተጠባቂ ከሆኑ ጉዳዮች መካከል አስር የሚሆኑትን የዓለም አትሌቲክስ በድረ ገጹ አስፍሯል። ከተጠባቂዎቹም ውስጥ\nኢትዮጵያዊው የ1 ሺ 500 ሜትር አትሌት ሳሙኤል ተፈራ ይገኝበታል። የ22 ዓመቱ ወጣት አትሌት በባለፈው ዓመት ተሳትፎው የራሱን\nምርጥ ሰዓት በሶስት ሰከንዶች ካሻሻለ ከቀናት በኋላ በበርሚንግሃም የዓለም የቤት ውስጥ ክብረወሰንን ማሻሻሉ የሚታወስ ነው። ሳሙኤል\nበሞሮኳዊው ሂቻም ኤል ጉሩዥ ለረጅም ዓመታት ተይዞ የቆየው ሰዓት 3 ደቂቃ ከ32 ሰከንድ ከ01 ማይክሮ ሰከንድ ነበር። ኢትዮጵያዊው\nአትሌት ግን ርቀቱን በ3 ደቂቃ ከ31 ከ04 ማይክሮ ሰከንዶች ክብረወሰኑን ሲረከብ የርቀቱ ፈጣን አትሌትም ተሰኝቷል። ይህም አትሌቱን\nበዚህ ዓመት በስፖርት ቤተሰቡ ዘንድ ተጠባቂ አትሌት አድርጎታል።አዲስ ዘመን ረቡዕ ጥር 13/2012 ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "e834183865a7804e5ed3f1df0eb0a449" }, { "passage": " ከሦስት ዓመት በፊት ይሆናል። ወደ ሀዋሳ ለሥራ ጉዳይ ከባልደረቦቼ ጋር ተጉዘን በውቧ የደቡብብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ዋና ከተማ መሽገናል። ከተማዋ እንደዛሬው ጭር ሳትል፤ ፍርሀት ሳይነግስባት፤ የአገር ውስጥም ሆነ የውጭ አገር ጎብኚዎች የሚጎርፉባት፤ ሁሉም የነፃነት ክንፉን ዘርግቶ የሚንሳፈፍባት ነበረች:: ነዋሪዎቿም ቢሆኑ ኢትዮጵያን የሚመስሉ ውብ ድብልቅ ናቸው። አሁንም ጭርሱኑ እንቅስቃሴ የለም ብዬ ባልታበልም። መንፈሷ መታወኩን ሳልናገር ማለፍ ግን ይከብደኛል። ከያዛት ቆፈን ለመውጣት ዳር ዳር የምትል ይመስለኛል። ነገሩ ግን ወዲህ ነው ንትርኩን ሳላበዛ ወደ ጉዳዬ ልግባ መሰለኝ።በወቅቱ በደቡባዊቷ ፈርጥ የከተምኩት በአትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ ባለቤትነት የሚዘጋጀውን «የታላቁ ሩጫ በሀዋሳ» የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ውድድርን ለመዘገብ ነበር። ታዲያ በዚያን ጊዜ ነው ለዓመታት ከአእምሮዬ ሊወጣ ያልቻለ አስተማሪ ነገር ያጋጠመኝ። በጊዜው ማረፊያችንን ያደረግነው በከተማዋ በሚገኘው በኃይሌ ሪዞርት ነበር። ኃይሌ ሮጦ ብቻ ሳይሆን አልምቶ አንጀት የሚያርስ መሆኑን ያወኩትም ያኔ ሳይሆን አይቀርም። ገጠመኜም ከዚሁ ጀግና ጋር የሚያያዝ ነው። ቀኑ ቅዳሜ ነው። የጎዳና ላይ ሩጫው የሚካሄደው ደግሞ እሁድ ጠዋት ነበር። ቅዳሜ ምሽት ደግሞ ኢትዮጵያውያንንና የውጭ አገር ዜጎችን ያሳተፈ ከፓስታ ብቻ የሚዘጋጅ ጣፋጭ ምግቦች የሚወራረዱበት ‹‹ፓስታ ፓርቲ›› የመክፈቻ መዝናኛ ዝግጅት ነበር። በምሽቱ ከጣፋጭ ምግቦቹ ውጪ ታዳሚዎች የሚሳተፉበት የተለያዩ ጨዋታዎች ነበሩ:: ከዚህ መካከል የኢትዮጵያ ጀግና ኃይሌ ገብረሥላሴ ተመልካችን እንዲያዝናና ከሌሎች ተሳታፊዎች ጋር ውድድር ማድረግ ነበረበት።ጨዋታው እንዲህ ነው። የተወዳዳሪዎቹን ቁጥር የሚስተካከል እንቁላል እና ማንኪያ ተዘጋጅቷል:: ኃይሌን ጨምሮ ተፎካካሪዎቹ ይሄን እንቁላል በማንኪያው ላይ አድርገው በአፋቸው ይይዛሉ። መነሻው እና መድረሻው በተዘጋጀው ስፍራ እንቁላሉን በማንኪያው ይዘው ቀድመው መድረስ ይኖርባቸዋል:: ኃይሌ እንቁላሉን ይዞ ቀድሞ ገብቶ ውድድሩን አሸንፎ ይሆን? የሚለው የእናንተ ጥያቄ እንደሚሆን አልጠራጠርም። ነገሩ ግን ወዲህ ነው።ኃይሌ ውድድሩ ምን እንደሆነ ሲነገረው። ተሳታፊ እንደማይሆን ተናግሮ የተወዳዳሪዎቹንና የታዳሚውን ወሽመጥ ቆረጠው። ለምን አትሉኝም። የሱ መልስ እጅግ በጣም ቀላል ነበር። ‹‹አንድ ጊዜ በልቶ የማያድር ሕዝብ ባለበት መሀል ተፈጥሬ በእንቁላል አልጫወትም›› በማለት በምግብ መጫወት የኑሮውም፣ የባህሉም ሆነ የእምነቱም ሁኔታ እንደማይፈቅድለት ተናግሮ ታዳሚውንም እጅግ አስደንቆና አስተምሮ ከመድረክ ወረደ።በወቅቱ የተከሰተው ሁኔታ አብዛኛዎቻችንን ያስገረመ ነበር። ከድህነት ውስጥ በበቂ ሁኔታ ባንወጣም፤ የኛን ባህል በማያውቁ የውጭ አገር ዜጎች መሀል በመከበባችን እና ፓስታ ፓርቲ ላይ በመሆናችን አዘጋጆቹም እኛን ሊያዝናኑ፤ እኛም በእንቁላል ልንዝናና ቃንጥቶን ፍፁም አቅላችንን ስተን ነበር። በገጠሩ አካባቢ አድጎ የገጠሯን እናት ልፋት፤ የአርሶ አደሩን አባት ድካም የሚያውቀው ብርቱው ጀግናችን ግን ያለው ሀብት እና ዝና ሳያስተው፤ ብልፅግና ልቡን ሳይሰውረው አሁን ደረቱን ነፍቶ ‹‹እኔ በእንቁላል አልጫወትም›› ሲል አዲስ መንገድ አሳየን።ይሄ ክስተት ላለፉት ሦስት ዓመታት የተለያዩ አጋጣሚዎች በተፈጠሩ ቁጥር በህሊናዬ ሲመላለስ ቆይቷል። ዛሬ ደግሞ በምን አጋጣሚ አስታወስከው ካላችሁ ሌላ አንድ ልብ የሚሰብር አሳዛኝ አጋጣሚን እነግራችኋለሁ። ከሦስት ዓመት በፊት ይህ እውቅ እና አስተዋይ ሰው በእንቁላል መጫወት ትክክል አለመሆኑን በአስገራሚ እይታው እና አንደበቱ ቢነግረኝም ይበልጥ እንዳከብረው ያደረገኝ ገፊ ምክንያት ሰሞኑን ያጋጠመኝ ጉዳይ ነው። ነገሩ እንዲህ ነው…የሥራ ባህሪዬ ሆነና በሁሉም የአገሪቷ ክፍል (ከገጠር እስከ ከተማ) የመዘዋወር እና ከሰዎች ጋር የመገናኘት አጋጣሚዬ ሰፊ ነው። ባሳለፍነው ሳምንትም ወደ ሰሜን ሸዋ ምድር የመጓዝ ዕድሉን አግኝቼ ነበር:: ሸዋ ከሥርዓተ መንግሥት ምስረታ ገድሏ ባሻገር በአሁኑ ወቅት እስከ ሦስተኛ ዲግሪ መመረቂያ ጽሑፍ ለማቅረብ የሚጠቅሙ የምርምር የታሪክ እና ሥነ ጽሑፍ ለኢትዮጵያ፣ ለአፍሪካ እንዲሁም ለዓለም የተረፉ የጥበብና የሥልጣኔ ፊትአውራሪ ሰዎች የፈለቁባት ነች። በተለይ ከግእዝ ወደ አማርኛ በርካታ መጽሐፍትን በመተርጎም፤ ከፊደል ገበታ እስከ ታላላቅ መጽሐፍት በመድረስ ለኢትዮጵያውያን ያበረከቱት ተስፋ ገብረሥላሴ፣ንጉስ ሳህለሥላሴ፣አፄ ምኒልክ እና የታሪክ ተመራማሪው እና ምሁሩ ተክለፃዲቅ መኩሪያ የሚጠቀሱ ናቸው።ታዲያ በሸዋ ምድር ቆይታዬ ለማየት ከቻልኳቸው ቦታዎች መካከል የምኒልክ እና የበርካታ ነገስታት መቀመጫ የነበረው የሚገኝበትን ‹‹አንኮበር ቤተ መንግሥት›› አንዱ ነበር። ግዘፍ እንደነሳው ታሪኩ እና ባለውለታነቱ የተረሳ እና እጅግ የሚያሳዝን ማህበረሰብ ያለበት መሆኑን በስፍራው የተገኘ ብቻ ነው የሚረዳው። ሕዝቡንና አካባቢውን አይቶ አይን ባያነባ እንኳን ልብ ማልቀሱ አይቀሬ ነው። ይህን ጉዳይ የሚያስረዳልኝ ደግሞ ቅዳሜ ቀን ገበያ ወጥታ ያገኘኋት የምስኪኗ እናት መከራ ነበር።ይህቺን እናት በገበያ ውስጥ ስዘዋወር ነው ያገኘኋት። የሥራ ባልደረቦቼ አብረውኝ ነበሩ። ግርግር በበዛበት ስፍራ ከፊት ለፊቷ ብጫቂ ጨርቅ ዘርግታ ከአንዲት ትንሽ ድንጋይ ላይ ቁጢጥ አለች:: ነገረ ሥራዋ ትኩረታችንን ስለሳበው ድርጊቷን መከታተል ጀመርን:: ልትለምን አልነበረም። ከያዘችው ቀረጢት ውስጥ በጥንቃቄ ሁለት ትናንሽ ነገሮችን አውጥታ ከዘረጋችው ጨርቅ ላይ አስቀመጠቻቸው። እንቁላሎች ነበሩ። ሁለት እንቁላሎች። ለዚያውም የሚሸጡ እንቁላሎች:: ይቺ እናት አይኗን ወደ ገበያተኛው እያማተረች ገዢዎችን እየተጠባበቀች ነው።ጠጋ ብዬ ስለሁኔታው አነጋገርኳት። የሚያስ ገርመው ደግሞ እዚህ የገበያ ቦታ ለመድረስ ከ10 ኪሎ ሜትር በላይ ተጉዛለች። ሁለት እንቁላል ለመሸጥ!! በምታገኘው ገንዘብ ደግሞ ጨው ገዝታ ወደ ልጆቿ ትበራለች። ሌላ አስር ኪሎ ሜትር ተጨማሪ:: ትራንስፖርት የማይታሰብ ነው። ጉዞ በእግር ነው። አዛኙ ጓደኛዬ ኪሱ ያለውን አውጥቶ እጁን ዘረጋላት:: ፊቷ በብርሃን ፈካ። ቢያንስ ለሦስት ሳምንት ገበያ መውጣት አይጠበቅባትም። ኑሮዋ እጅጉን ያሳዝናላ።እኔ ደግሞ በሀሳብ ነጎድኩ። ወደ ሃዋሳ። ኃይሌ ሪዞርት። ኃይሌ እንዲህ ይላል ‹‹እኔ በእንቁላል አልጫወትም!!››      አዲስ ዘመን ጥቅምት 16/2012 ዳግም ከበደ", "passage_id": "1b470bbcfe41888b22972dc4823e2ac7" }, { "passage": "በታሪክ አጋጣሚ ቀደም ባሉት ዓመታት በተለያዩ የአትሌቲክስ ውድድሮች ወንድና ሴት አትሌቶች በተለያዩ ርቀቶች በተመሳሳይ ውድድር ላይ ሲሮጡ መመልከት የተለመደ ነው። ‹‹ወንዶች የሚሮጡትን ርቀት ሴቶች መሮጥ አይችሉም›› የሚል አስተሳሰብ በነበረበት ዘመን በተመሳሳይ ውድድር ላይ ሴቶች ከወንዶች ያነሰ ርቀት ለመሮጥ ይገደዱ ነበር። እንዲያውም በአንዳንድ ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች ላይ ወንዶች በሚሮጡበት ርቀት ሴቶች እንደማይወዳደሩ ከታሪክ መረዳት ይቻላል። ለምሳሌ ያህል በታላቁ የዓለማችን የስፖርት መድረክ ኦሊምፒክ ማራቶን አንጋፋና ምናልባትም ከመጀመሪያ አንስቶ የሚካሄድ የውድድር አይነት ቢሆንም ሴቶች በርቀቱ መወዳደር የጀመሩት ዘግይተው ነው።በኦሊምፒክ መድረክ ብቸኛው የጎዳና ላይ ውድድር በሆነው ማራቶን ወንዶች መሳተፍ የጀመሩት እኤአ 1896 ላይ ነው። የሴቶች ማራቶን የኦሊምፒክ ውድድር ውስጥ የተካተተው ግን ዘጠና ዓመታትን ዘግይቶ በ1984 ኦሊምፒክ ነበር። ከማራቶን በተጨማሪም በርካታ በተለይም ረጅም ርቀት ውድድሮች በኦሊምፒክም ይሁን በዓለም ቻምፒዮና ሴቶችን ማካተት የጀመሩት ዘግይተው ነው። ይሁን እንጂ በዘመናዊው የአትሌቲክስ ዓለም ሴቶች ወንዶች በሚወዳደሩበት ርቀት ሙሉ በሙሉ ለማለት በሚያስችል ደረጃ ተወዳዳሪ ናቸው።ከአታካቹ ማራቶን አንስቶ እስከ ተለያዩ የጎዳና ላይ ውድድሮች ሴቶች ወንዶች የሚሮጡትን ርቀት በመሮጥ ብቃታቸውን አስመስክረዋል። ርቀቶቹን ሮጠው  ለማጠናቀቅ የሚፈጅባቸው ሰዓት ከተፈጥሮ ጋር በተያያዘ ከወንዶች የዘገየ ቢሆንም የትኛውንም ርቀት ሴቶች አይሮጡም ብሎ የሚያምን ሰው ፈልጎ ማግኘትም ከባድ የሚመስልበት ዘመን ላይ ተደርሷል። ይሁንና ሴቶች በአገር አቋራጭ ውድድሮች ላይ ከወንዶች ያነሰ ርቀት እንዲሮጡ መደረጉ በአትሌቲክሱ ቤተሰቦች መከራከሪያ አጀንዳ ከሆነ ዓመታት ተቆጥረዋል።እንግሊዛዊቷ የቀድሞ የአገር አቋራጭ ቻምፒዮና የሜዳሊያ ባለቤት አትሌት ጆ ፓቬይ «በአገር አቋራጭ ውድድሮች ሴቶች ከወንዶች ባነሰ ርቀት መወዳደራቸው የፆታ እኩልነትን አያሳይም» የሚል አስተያየት ከሁለት ዓመት በፊት ለስካይ ኒውስ መስጠቷን ተከትሎም የአገር አቋራጭ ውድድር አዘጋጆች ከአትሌቲክስ ቤተሰቡ ጋር ሙግት ገጥመው እንደነበር ይታወሳል። በርካታ የስፖርቱ ባለሙያዎችና የውድድር አዘጋጆችም በጉዳዩ ላይ ሲሟገቱ ይስተዋላል። አገር አቋራጭ ውድድሮች በየዓመቱ በተለያዩ ከተሞች በተለይም በአውሮፓ ይካሄዳሉ። የዓለም አትሌቲክስም በየሁለት ዓመቱ የዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና ያዘጋጃል። በእነዚህ ውድድሮች ሴትና ወንድ አትሌቶች በእኩል ርቀት ሲወዳደሩ አይታይም። እኤአ ከ2017 በፊት በዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና የሚካሄደው ፉክክር በአራት አይነት መንገድ ተከፍሎ ነው። የመጀመሪያው አዋቂ ወንዶች የሚወዳደሩበት የአስራ ሁለት ኪሎ ሜትር ውድድር ሲሆን አዋቂ ሴቶች ስምንት ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ርቀት ላይ ብቻ ተፎካካሪ ነበሩ። በወጣት ወንዶች መካከል የሚካሄደው ውድድር ደግሞ ስምንት ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን ወጣት ሴቶች ስድስት ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ፉክክር ያደርጋሉ። እነዚህ ርቀቶች በዓለም ቻምፒዮናም ይሁን በግል አገር አቋራጭ ውድድሮች በብዛት የተለመዱ ናቸው። አልፎ አልፎ ግን በዓለም ቻምፒዮናም ይሁን በግል ውድድሮች እንደየሁኔታው ወንዶች ከሴቶች እኩል ርቀቶችን የሚሮጡበት አጋጣሚ ሲፈጠር ይታያል። ለአብነት ያህልም በ2017 በዩጋንዳ ካምፓላ ተካሂዶ የነበረው የዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮናን ማንሳት ይቻላል። በዚህ ቻምፒዮና ለመጀመሪያ ጊዜ አዋቂ ሴቶችና ወንዶች እኩል አስር ኪሎ ሜትር የሸፈነ ውድድር ማድረጋቸው ይታወሳል። «ታዲያ ሴቶች በዚህ ውድድር ከወንዶች እኩል መሮጥ እየቻሉ አነስተኛ ርቀት እንዲሮጡ መደረጋቸው ለመጪው ትውልድ ምን አይነት መልዕክት ያስተላልፋል?» የሚል ከጾታ እኩልነት አኳያ ጥያቄ የሚያነሱ ቁጥራቸው ብዙ ነው።በምስራቅ ለንደን የአትሌቶች ማህበር አባል የሆነችው ማዑድ ሆድሰን በዚህ ውድድር የጾታ እኩልነት መረጋገጥ ካለበት ሴትም ወንድም እኩል ርቀት መሮጥ አለባቸው የሚል አቋም ይዛ ባለፉት ዓመታት ስትከራከር ቆይታለች። ይህን ሃሳቧንም በርካቶች ደግፈውታል። ሆድሰን በጉዳዩ ላይ ለራነርስ ዌብ ከዓመታት በፊት እንደገለፀችው፣ በአገር አቋራጭ ውድድሮች ሴትና ወንድ እኩል ርቀት እስካልሮጡ ድረስ መጪው የአትሌቲክስ ትውልድ በሩጫው ዓለም ሴትም ወንድም እኩል መሆናቸውን ሊረዳ አይችልም። ወንዶች ከፍ ያለውን ርቀት መሮጣቸው በአገር አቋራጭ ውድድሮች የሴቶቹ ፉክክር ከወንዶቹ ያነሰ የሚመስል ትርጉም ይሰጠዋልም ትላለች። ሆድሰን በዚህም ሳታበቃ በጉዳዩ ላይ አንድ መፍትሄ ለማምጣት በኤሌክትሮኒክስ መንገድ ፊርማ አሰባስባ በቀናት ውስጥ ከአንድ ሺ በላይ ተከታዮችን አግኝታለች። ይህ ሃሳብ በፌስ ቡክ ገፅም«አይ ወዝ ኦር አም ራነር» በሚል በተፈጠረ የቡድን ገፅም በርካታ ወንዶች የደገፉት ሲሆን ብዙ ተከታዮች አግኝቶ መነጋገሪያነቱ እየጨመረ መጥቷል።አዳጋች በሆነው የአገር አቋራጭ ውድድር አትሌቶች በጭቃ፤ በዳገትና ቁልቁለት አልፎ አልፎም በበረዶ ይፈተናሉ። ይህን ከግምት የሚያስገቡ በርካታ ሰዎች ሴቶች በውድድሩ እንደ ወንዶች ረጅም ኪሎ ሜትር መሮጥ አይችሉም የሚል አስተሳሰብ እንዲይዙ ያደርጋቸዋል። አንዳንድ ጥናቶች እንደሚያመላክቱት ግን ሴቶች በሌሎች ፈታኝ በሚባሉ ማራቶንና ግማሽ ማራቶን ውድድሮች ላይ ከወንዶች እኩል ርቀት ሮጠው ከሚያስመዘግቡት የሰዓት ልዩነት የተጋነነ አያስመዘግቡም። በቢኬት ዩኒቨርሲቲ የስፖርት ሳይንስና ባዮሜካኒክስ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ብሬን ሃንሌይ ጥናታዊ ፅሁፍ ግን በአገር አቋራጭ ውድድር ሴቶች ከወንዶቹ ባልተናነሰ ተመሳሳይ ርቀት መወዳደር እንደሚችሉ ይጠቁማል። ጥናቱ ልክ እንደ ወንዶቹ የሴቶቹም ውድድር መጀመሪያ ላይ ቀዝቃዛ ፉክክር የሚታይበት ቢሆንም መጨረሻው በፉክክር የታጀበ እንደሚሆን አረጋግጧል። አብዛኞቹ የውድድር አዘጋጆች ግን ሴቶች በዚህ ውድድር ከወንዶች እኩል ርቀት ቢሮጡ መጨረሻው በፉክክር እንደማይታጀብና አሰልቺ እንደሚሆን ስለሚያምኑ ሴቶች አነስተኛ ርቀት እንዲወዳደሩ ያደርጋሉ የሚል ክርክር ይነሳል። ይህ ግን ዞሮ ዞሮ ከፆታ እኩልነት ጋር ባይያያዝ እንኳን በርካታ ወጣት አትሌቶችን ወደ ውድድሩ እንዳይመጡ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል መላ ምቶች ይቀመጣሉ። ይህም ርቀቱ በረዘመ ቁጥር በርካታ አትሌቶች እንደ ጎዳና ላይ ረጅም ርቀት ውድድሮች ሁሉ የመወዳደራቸው አጋጣሚ ሰፊ ይሆናል የሚል ነው።የአርባ ስድስት ዓመቷ ጆ ፓቬይ አትሌቲክስን ካቆመች በርካታ ዓመታት ቢቆጠሩም ሴቶች በአትሌቲክሱ ዓለም አስደናቂ ታሪኮችን ከወንዶች እኩል መስራታቸውን በማስታወስ በአገር አቋራጭ ውድድሮችም ከወንዶች እኩል ርቀት መሮጥ እንዳለባቸው ከስካይ ኒውስ ጋር በነበራት ቆይታ ገልፃለች። «ለበርካታ ዓመታት በአስቸጋሪው የማራቶን ውድድር ሴቶች ከወንዶች እኩል ርቀት ሲወዳደሩ ቆይተዋል፤ በአገር አቋራጭ ውድድሮች እኩል ርቀት ያለመሮጣቸው ሴቶች ከወንዶች እኩል አቅም የላቸውም የሚል አመለካከትን ይፈጥራል» በማለትም ፓቬይ አቋም ይዛለች።የማራቶን ባለክብረወሰኗና የቀድሞ የዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮኗ አትሌት ፓውላ ራድክሊፍ ሰሞኑን በጉዳዩ ላይ በማህበራዊ ሚዲያው የሚደረገውን ክርክር ተቀላቅላ ‹‹ርቀቶች መመሪያ ናቸው፣ የአገር አቋራጭ መወዳደሪያ ቦታዎች ጥሩ ከሆኑ በሁለቱም ፆታ ተመሳሳይ ርቀት ቢሮጥ ችግር የለውም፣ የውድድሩ ተፈጥሯዊ ባህሪ ሆኖ አንዳዶች አጭር ርቀት መሮጥ ሲፈልጉ ሌሎች ረጅም መሮጥ ሊፈልጉ ይችላሉ፣ ወንድም ሴትም ተመሳሳይ ርቀት መሮጥ እንደሚችሉ ግን አምናለሁ›› በማለት ፅፋለች። የአገር አቋራጭ ውድድር አዘጋጆች ይህ ልዩነት ለምን እንደተፈጠረ አሳማኝ ምክንያት ማቅረብ ባይችሉም በተለምዶ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ በመሆኑ ብቻ አሁን ላይ እየተገበሩት እንደሚገኙ ይታመናል። ይህ ግን በአንዳንድ የስፖርት ቤተሰቦች የፆታ ልዩነት እንዳለ ለማሳየት ሆን ተብሎ የተደረገ ሳይሆን የሴቶቹን ፉክክር ረዘም ላለ ሰዓት መመልከት ስለማይፈለግ ነው የሚል ትችት ይቀርባል። የእንግሊዝ አገር አቋራጭ ውድድር ማህበርም ይህ ልዩነት በተለምዶ አሰራር የመጣ መሆኑን በማመን በአገር አቀፍ ውድድር ላይ ሴቶች ከወንዶች እኩል ርቀት መሮጥ እንዳለባቸው ሲከራከርና ተፅዕኖ ሲያሳድር ቆይቷል። በዚህም የእንግሊዝ አትሌቲክስ ማህበርን ድጋፍ ማግኘት ችሏል። የእንግሊዝ አትሌቲክስ ማህበርም ጥያቄውን ወደ ፊት በማምጣት የተለያዩ ሙግቶችን ሲያደርግ ቆይቷል። ለረጅም ጊዜ ጉዳዩ የተዘነጋና ተድበስብሶ ያለፈ ቢመስልም የእንግሊዝ አትሌቲክስ ማህበር ከቀናት በፊት ዳግም ጉዳዩን በማንሳት በጥናት ጭምር አስደግፎ እየተሟገተ ይገኛል። አትሌቲክስ ማህበሩ በፈጠረው ተፅዕኖ በአገሪቱ በሚደረጉ የአገር አቋራጭ ውድድሮች ላይ ለውጦች ማምጣት ቢችልም በዓለም አቀፍ ደረጃ የተለያዩ የውድድር አዘጋጆችን ለማሳመን ተጨማሪ ስራዎች ይቀሩታል። ለዚህም የአውሮፓ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ላይ የሰራውን ጥናት ሰሞኑን ይፋ አድርጓል። 2016 ላይ ከሃምሳ አንድ የአውሮፓ አገራት አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ሰላሳ ሰባቱ ለጥናቱ ምላሽ የሰጡ ሲሆን ከሰላሳ ሰባቱ ሃያ አንዱ ሴቶችና ወንዶች በአገር አቋራጭ ውድድሮች እኩል ርቀት መሮጥ አለባቸው የሚል እምነት እንዳላቸው ጠቁሟል። አገር አቋራጭ ውድድር እንደ ረጅም ርቀት ውድድሮች ሁሉ በስፋት የሚታወቁት ምስራቅ አፍሪካውያኑ ኢትዮጵያና ኬንያ ቢሆኑም በጉዳዩ ላይ የተነሳው ሙግት ከወደ ምዕራባውያኑ መሆኑ አስገራሚ ነው። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቴክኒክ ዳይሬክተር የነበሩትና አሁን የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር የሆኑት አቶ ዱቤ ጂሎ በአንድ ወቅት ከአዲስ ዘመን ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስ በዚህ ጉዳይ ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያለውን አቋም አሳውቀው ነበር። አቶ ዱቤ ይህ በሴቶችና በወንዶች አገር አቋራጭ ውድድሮች ላይ ያለው የመወዳደሪያ ርቀት በተለምዶ ሲሰራበት ስለመጣ እንጂ ሴቶች ወንዶች የሚሮጡትን ርቀት መሮጥ ስለማይችሉ የተፈጠረ እንዳልሆነ ያብራራሉ። የርቀቱ ልዩነት የመጣው ቀደም ሲል በውድድሩ ደንብ ላይ የተቀመጠ በመሆኑ እንጂ ከጤናም አኳያ ይሁን ከሌሎች ነገሮች ሴቶች በአገር አቋራጭ ውድድር ከወንዶች ያነሰ ርቀት እንዲሮጡ የሚያደርጋቸው ምንም አይነት አሳማኝ ምክንያት እንደሌለ ገልፀው ነበር። «ሴቶች ከወንዶች እኩል በአገር አቋራጭ ውድድር መሮጥ አለባቸው፤ ማራቶንም ይሁን ግማሽ ማራቶን እኩል እስከ ሮጡ ድረስ በአገር አቋራጭም እኩል ርቀት መሮጥ አለባቸው፤ ይህ ካልሆነ ማራቶንም እኩል ኪሎ ሜትር መሮጥ የለባቸውም» በማለትም አቶ ዱቤ ሃሳባቸውን ሰንዝረው ነበር። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በየዓመቱ ጃን ሜዳ ኢንተርናሽናል አገር አቋራጭ ውድድሮችን በክልሎችና በክለቦች መካከል እንደሚያካሂድ ይታወቃል። በነዚህ ውድድሮች ወንዶቹም ሴቶቹም እኩል ርቀት የሚሸፍን ውድድር እንዲያካሂዱ ማድረግ ይቻላል ያሉት አቶ ዱቤ፣ ይህን ጥያቄ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለዓለምአቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ሊያቀርብ እንደሚችልም ጠቁመዋል። ከዚያም ዓለምአቀፍ ማህበሩ አሁን ያለውን ህግ አሻሽሎ በተመሳሳይ ርቀት እንዲወዳደሩ ከፈቀደ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም በእኩል ርቀት ውድድሮቹን ለማካሄድ የሚያግደው ነገር እንደሌለ አብራርተዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 17/2013 ዓ.ም ", "passage_id": "45eada520b80135f2da51e6ad708b565" } ]
cf089f8abbbea5947b0b0f02322953ac
cfdb45e3039b64b45e3682ea59b31759
የግመሎቹን ቅስም እስከ ወዲያኛው የሰበረው የዓለም ዋንጫ ክስተት
የ1982 የዓለም ዋንጫ ለኤሽያዊቷ አገር ኩዌት የእግር ኳሷ ወርቃማ ዘመን ሆኖ ይታወሳል። የዓለም ዋንጫ በመጣ ቁጥር ግን ይህ የኩዌት ወርቃማ የእግር ኳስ ዘመን ሲታወስ አይታይም። እግር ኳስ በተለያዩ ቴክኖሎጂዎች እየረቀቀ ሲመጣ፤ በይነ መረብ ዓለምን ሲያቀራርብና ቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭቶች እንደ ልብ እየሆኑ ሲመጡ እኤአ ከ199oዎቹ ጀምሮ በዓለም ዋንጫ የታዩ ወርቃማ ብሔራዊ ቡድኖች፤ በርካታ ከዋክብቶችና አይረሴ አጋጣሚዎች አሁንም ድረስ በእግር ኳስ አፍቃሪው ዘንድ ይታወሳሉ። ያም ሆኖ ከ1978 የዓለም ዋንጫ አስቀድሞ ከጣሊያንና አርጀንቲና ውጪ ያሉ የእግር ኳስ አፍቃሪዎች ዘንድ ፓውሎ ሮሲና ማሪዮ ኮምፐስን የመሳሰሉ ተጫዋቾች ትልቅ እውቅና ነበራቸው። ከዚህ የዓለም ዋንጫ በኋላም መረጃዎች እንደ ልብ በሌሉበት ዘመን የዲያጎ አርማንዶ ማራዶና ለመጀመሪያ ጊዜ ለአርጀንቲና ተሰልፎ ቤልጂየምን እስከ ገጠመበት ጨዋታ በበርካታ የዓለማችን እግር ኳስ አፍቃሪዎች በቴሌቪዥን መስኮት የመመልከት እድላቸው ጠባብ ቢሆንም ስምና ዝናው ይታወቅ ነበር።የዓለም ዋንጫ አይረሴዎቹ ኮከቦች ሚካዔል ላውድሩፕ፤ ህሪስቶ ስቶቺኮቭ፤ ጂዮርጅ ሃጂና ሌሎችም የጀገኑበት ዘመን ሩቅ ቢሆንም የዓለም ዋንጫ በመጣ ቁጥር ሳይታወሱ የማይታለፉበት ታሪክ አኑረዋል። በተመሳሳይ በብሔራዊ ቡድን ደረጃም የ1966 የሰሜን ኮሪያ፤ በ1982 የአልጄሪያና በ199o የካሜሩን ብሔራዊ ቡድኖች የሚዘነጉ አይደሉም። የኩዌት የ1982 ብሔራዊ ቡድንም ከነዚህ ብሔራዊ ቡድኖች እኩል የሚታወስ ነው። በዛሬው የስፖርት ማህደር አምዳችንም ይህን ብሔራዊ ቡድን ለማስታወስ ወደድን፡፡የ1982 የስፔን የዓለም ዋንጫ የኤሽያን እግር ኳስ አንገት ቀና ያደረገ ድንቅ የብሔራዊ ቡድን ስብስብ ከኤሽያ አልፎ በመካከለኛው ምስራቅና የገልፍ አገራት እግር ኳስ ላይ ትልቅ መነቃቃትን ፈጥሮ ነበር። ይህ ከ197o መጀመሪያ እስከ 198oዎቹ መጀመሪያ ላይ ትልቅ የእግር ኳስ አብዮት የፈጠረ የኩዌት ወርቃማ የእግር ኳስ ትውልድ ኤሽያ እስካሁንም መልሳ ያላየችው ስብስብ ይዞ ነበር። ከ1976 እስከ 1978 በታሪካዊው ብራዚላዊ ማሪዮ ዛጋሎ እንዲሁም ከ1978 እስከ 1982 በሌላኛው ብራዚላዊ ካርሎስ አልቤርቶ ፔሬራ እየሰለጠነ ዓለምን ጉድ ያሰኘ የብሔራዊ ቡድን ስብስብ በድንቅ ባለ ተሰጥኦ ተጫዋቾች የተሞላም ነበር። ከግብ ጠባቂው አህመድ ታራቡልሲ አንስቶ እስከ አብዱላዚዝ አል አንባሪ፤ አህመድ አቡ ሐማድና ግብ አፈንፋኙ ጃሴም ያቆብ እንዲሁም አምበሉ ሳድ አል ሆቲና ፋሳል አል ዳክሂል ድረስ በከዋክብት የተሞላው የኩዌት ብሔራዊ ቡድን ስብስብ ከእግር ኳስ በላይም ትልቅ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ተጽዕኖዎች ነበሩት። ይህ ስብስብ በዓለም እግር ኳስ ላይም በትልቅ ደረጃ ተፅዕኖ መፍጠር የቻለ የመጀመሪያው የገልፍ አገራት ብሔራዊ ቡድን ሆኖ ይታወሳል።የኩዌት ወርቃማ የእግር ኳስ ትውልድ በአንድ ጊዜ ተፈጥሮ በዓለም እግር ኳስ ላይ ድንገት ተፅዕኖ የፈጠረ ሳይሆን በሂደት እየተገነባ የመጣ ነው። ለዚህም በኤሽያና በገልፍ አገራት የእግር ኳስ ቻምፒዮና ሃያል የሆኑትን እንደ ኢራን አይነት አስደናቂ የቡድን ስብስብ ያላቸውን አገራት በሂደት አሸንፎ ዋንጫ በማንሳት ነው። ከዚህ በዘለለም ለ198o የሞስኮ ኦሊምፒክ አልፎ እስከ ሩብ ፍፃሜ ድረስ በመጓዝ በርካቶችን አሳምኖ ነው ወደ ዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጣው።በኤስያ አገራት የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች ኩዌት ኒውዘላንድ፤ ቻይናና ሳውዲ ዓረቢያ ከሚገኙበት ምድብ በፔሬራ አሰልጣኝነት እየተመራች በቀላሉ ወደ 1982 የዓለም ዋንጫ ማምራት ችላለች። እንደ አጋጣሚ ሆኖ ግን ኩዌት በዓለም ዋንጫው ጠንካራ በሚባል ምድብ ውስጥ ተደለደለች። ይሁን እንጂ በቡድኑ ውስጥ የነበረው ጠንካራ ስነ ልቦና ጠንካራውን ምድብ አልፈው ወደ ጥሎ ማለፍ እንደሚገቡ ትልቅ ተስፋ የሰጠ ነበር።«ግመሎቹ» በሚል ቅጽል ስም የሚታወቀው የኩዌት ብሔራዊ ቡድን የመጀመሪያቸው በሆነው የዓለም ዋንጫ በምድብ ድልድሉ ከሦስቱ አውሮፓውያን አገራት ቺኮስላቫኪያ፤ ፈረንሳይና እንግሊዝ ጋር ነበር የተደለደሉት። ይህ ምድብ ከቺኮስላቫኪያ በስተቀር ፈረንሳይና እንግሊዝ ያላቸው ትልቅ ስም ለግመሎቹ ስጋት ቢሆንም የፔሬራ ልጆች ወደ ቀጣዩ ዙር የማለፍ ትልቅ ተስፋን ሰንቀው ነበር። በተለይም በመጀመሪያው የቺኮስላቫኪያ ጨዋታ ሙሉ ሦስት ነጥብ ይዘው ለመውጣት ግምት የተሰጣቸው ቢሆንም ጨዋታው አንድ ለአንድ በሆነ አቻ ውጤት መጠናቀቁ ያልተጠበቀ ነበር። ይሁን እንጂ ጠንካራዋ ፈረንሳይ በእንግሊዝ ሦስት ለአንድ መሸነፏን ተከትሎ ግመሎቹ ወደ ቀጣዩ ዙር የማለፍ ተስፋቸው እንደገና ነብስ ዘራበት። ያም ሆኖ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታ ሚሼል ፕላቲኒ፤ አሊያን ጊረስና ጄን ቲጋና ለፈረንሳይ ግቦችን አስቆጥረው ፈረንሳይ በቀላሉ መምራት ቢችሉም ግመሎቹ ወደ ጨዋታው ተመልሰው ወይ ለማሸነፍ ወይንም የአቻ ውጤት ይዘው ለመውጣት ተስፋ አልቆረጡም። በዚህም ፈረንሳይን ተጭነው በመጫወት በአብዱላህ አል ቦኑሺ የግንባር ኳስ ሦስት ለአንድ መሆን ቻሉ። ይህም ተነሳሽነታቸውን ጨምሮ ሌላ ግብ ለማስቆጠር ጥረት በሚያደርጉበት ሰዓት አንድ ተስፋ አስቆራጭ ክስተት ተፈጠረ። ይህም አለን ጊረስ ከጨዋታ ውጪ የሆነ ግብ ኩዌት ላይ አስቆጥሮ ዳኛው ይሽሩታል ተብሎ ሲጠበቅ ማፅደቃቸው ነበር።ይህች ቅፅበት ግመሎቹን ተስፋ ከማስቆረጧም በላይ በወቅቱም የኩዌት ተጫዋቾች ውሳኔውን በመቃወም ጨዋታውን ሳይጨርሱ ሜዳውን ለቀው ወጥተዋል። በወቅቱ የኩዌቱ ኤሚር ወንድምና የአገሪቱ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት የነበሩት ሼክ ፋሃድ አል አህመድ አል ጃበር አል ሳባህ ከክብር ወንበራቸው ተነስተው ወደ ሜዳ በመግባት በዳኛው ውሳኔ ላይ ያላቸውን ቅሬታ ከተጫዋቾቹ ጋር የገለፁበት አጋጣሚ አይረሳም። በዚህም ዳኛው አሁንም ድረስ የዓለም ዋንጫ አስገራሚ ክስተት ተብሎ እንዲታወስ ያደረገውን አጋጣሚ ያፀደቁትን ግብ በመሻር ጨዋታው እንደገና እንዲጀመር ማድረጋቸው ነበር። ያም ሆኖ ግን ግመሎቹ ወደ ጨዋታው ቢመለሱም ወደ ቀድሞው ተነሳሽነታቸው ሳይመለሱ ቀርተው ፈረንሳይ በመጨረሻ ሰዓት ሌላ ግብ አስቆጥራ አራት ለአንድ ማሸነፍ ቻለች። ከዚህም ቅፅበት በኋላ የኩዌት እግር ኳስ የተሰበረ ቅስም አሁንም ድረስ ሳይጠገን ደብዛው ሊጠፋ ችሏል።የ1982 የስፔን የዓለም ዋንጫ ለኩዌት እግር ኳስ ወርቃማ ዘመን እንደመሆኑ መጠን ደብዛው የጠፋበት አጋጣሚም ሆኖ ይታወሳል። አብዛኞቹ የኩዌት ተጫዋቾች እድሜያቸው የገፋ እንደመሆኑ ከዚያ የዓለም ዋንጫ በኋላ ሌላ ተዓምር ሳያሳዩ ጫማቸውን ለመስቀል ተገደዋል። በእርግጥ የተወሰኑ ተጫዋቾች ከዚያም ወዲያ የተወሰኑ ዓመታትን ተጫውተዋል። እነዚህ ተጫዋቾች ከዓለም ዋንጫው በኋላ በገልፍ አገራት ቻምፒዮና እኤአ 1986ና 1990 ላይ ዋንጫ ማንሳት ቢችሉም ኩዌት የዓለም ዋንጫ ማጣሪያን ለማለፍ የተቃረበችበት ወቅት እንኳን አልተከሰተም። ከዚህም በኋላ እኤአ በ1990 ኩዌት በኢራቅ የተወረረችበትና ቀጥሎም የገልፍ አገራት ጦርነት የተከሰተበት አጋጣሚ የአገሪቱን እግር ኳስ ከተነቃቃበት ወደ ገደል ገፍትሮታል። በፖለቲካ ጣልቃ ገብነት ብሔራዊ ቡድኑ በተደጋጋሚ በፊፋ እገዳ እየተጣለበትም ከድጡ ወደ ማጡ ሲገባ ታይቷል። የኩዌት እግር ኳስ አፍቃሪዎችም የወርቃማ ትውልዳቸው ከዋክብቶችን አል ዳክሂል፤ ያቆብ እንዲሁም አል አንባሪን በማስታወስ የዓለም ዋንጫ በመጣ ቁጥር ይደሰታሉ።አዲስ ዘመን ሐምሌ 26/2012  ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=36497
[ { "passage": "ያልተጠበቁ አስደናቂ አሸናፊዎች፣ ለአሸናፊነት ጥቂት የቀራቸው የሚያስቆጩ ሽንፈቶች፣ አሳዛኝና አስደንጋጭ አጋጣሚዎች፣ በስፖርታዊ ጨዋነት የታጀቡ ክስተቶች፣ ለቀጣዩ ትውልድ ለታሪክ የሚዘልቁ ሁነቶች ባለፉት አስር ቀናት ተስተናግደውበታል። ሁለት ዓመታትን የጠበቀው 17ኛው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ከ10 ቀናት ቆይታ በኃላ ለቀጣይ ሁለት ዓመታት በቀጠሮ ተሰናብቷል። ከጅማሬውም በእስያ መካከለኛው ምስራቅ አቅጣጫ የምትገኘው አገር ከስፔኗ ባርሴሎና እና ከአሜሪካዋ ኦሪጎን ግዛት በልጣ ለዚህ ውድድር መታጨቷ አነጋጋሪ ነበር። በርካታ አስደናቂ ጉዳዮች እና ጥቂት ጉድለቶች ከአስቸጋሪው የአየር ሁኔታ ጋር አጣምሮ ሲካሄድ የቆየው የዶሃው ዓለም ቻምፒዮናም ከትናንት በስቲያ መቋጫውን አግኝቷል። 200 አገራት በሺዎች የሚቆጠሩ አትሌቶቻቸውን ባሳተፉበት ቻምፒዮና፤ 43 አገራት የሜዳሊያ ሰንጠረዡ ውስጥ ሲገቡ 68 የሚሆኑት ደግሞ እስከ 10ኛ ደረጃ ባለው ውጤት ውድድራቸውን አጠናቀዋል። ይህም እ.ኤ.አ በ2017 ለንደን ላይ ከተመዘገቡ ክብረወሰኖች እጥፍ የሚሆኑትም በዶሃ ሊሰበሩ መቻላቸውን ማህበሩ በድረገፁ አስነብቧል። በከሊፋ ስታዲየም በተካሄደው የመዝጊያ መርሀ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ፕሬዚዳንት ሰባስቲያን ኮ የዶሃውን ዓለም ቻምፒዮና በታሪክ ምርጡ እንደነበር መስክረዋል። ኮ በንግግራቸው «ስፖርታችንን ለምትከታተሉና ለስፖርቱ ቅርብ ለሆናችሁ ሁሉ የአትሌቶቻችንን እና አሰልጣኞቻችንን ስኬት በቻምፒዮናው መመዘን ችለናል። በዓለም ላይ ያሉ አትሌቶች ሁሉ በቻምፒዮናው ታሪክ የሚልቀውን አቋማቸውን አሳይተዋል፤ ይህም አስደናቂ ነበር። ለውድድሩ የሚሆነውን ሁሉ ያሟላችው አዘጋጇ አገርም በዚህ መመስገን ይገባታል» ብለዋል። የኳታር ዓለም ቻምፒዮና\nአዘጋጅ ኮሚቴ ምክትል ፕሬዚዳንት ዳሃላን አል ሃማድ በበኩላቸው፤ የቻምፒዮናው አዘጋጅ በመሆናቸው የኳታራዊያን ህልም እንደሰመረ ነው የገለፁት። በአስተያየታቸውም «ለአዘጋጅነት ፍላጎት ያሳየነው ከ1997 ጀምሮ ነበር፤ ለዓመታት ፍላጎታችንን ስናቀርብ ቆይተንም በ2010 የዓለም የቤት ውስጥ ቻምፒዮናን ለማሰናዳት እንዲሁም የዳይመንድ ሊግ አንድ መዳረሻ ለመሆን በቃን። ይህ ጥሩ ቢሆንም መሰል ውድድርን በአገራቸው ሲካሄድ ለመመልከት የሚፈልጉ ትውልድ ላይ በመድረሳችን ለማዘጋጀት በቅተናል» ማለታቸውን ዘገባው ጠቁሟል። በዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር እስካሁን ከተደረጉት የዓለም ቻምፒዮናዎች በተሰጠው ደረጃ መሰረትም ዶሃ ቀዳሚውን ስፍራ መቆጣጠር ችላለች። ለንደን ሁለተኛ ስትሆን፤ የሴቪላ፣ የቤጂንግ እና የበርሊን ቻምፒዮናዎች ከአንድ እስከ አምስት ያለውን ደረጃ ይዘዋል። በዚህ ቻምፒዮና ላይ በርካታ ወጣት አትሌቶች የታዩ ሲሆን የሜዳሊያ ባለቤቶችም ሆነዋል። ከእነዚህ ስኬታማ አትሌቶች መካከል ደግሞ ኢትዮጵያዊያኑ ሰለሞን ባረጋ እና ለሜቻ ግርማ ተጠቃሽ ሆነዋል።አዲስ ዘመን  መስከረም 27/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "e89e3596cf846fe32929f8ef7b64ad76" }, { "passage": "ሮናልዲንሆን ከሌሎች ብራዚላውያን ተጫዋቾች ልቆ ልዩ የሚያደርገው ነገር አለ። ይሄም በብሄራዊ ቡድን ውስጥ በሁሉም የእድሜ ክለል ላይ የሚደረጉ ለዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ መሳተፉ ነበር። በ1997 የፊፋ በግብፅ ባካሄደው ከ17 አመት በታች የዓለም ዋንጫ፣ በ1999 የደቡብ አሜሪካ ወጣቶች የእግር ኳስ ሻምፒዮና ከ20 ዓመት በታች እንዲሁም በዚያው ዓመት በተመሳሳይ ናይጄሪያ ውስጥ በተሰናዳው የዓለም ወጣቶች ዋንጫ ውድድሮች ላይ ተካፋይ ሆኗል። በዚህም የሚከተሉትን ስኬቶች አግኝቷል። ሮናልዲንሆ በብራዚል ብሄራዊ ቡድን በተለያዩ የእድሜ ደረጃዎች የጫወተ ሲሆን በ1999 ኮፓ አሜሪካን ውድድር ላይ ላቲቪያን 3ለ0 በሆነ ውጤት ብራዚል ስታሸንፍ የመጀመሪያውን ዋንጫ ማንሳት ችሏል። በዚያው አመት በተመሳሳይ ወር ላይ በተካሄደው የፊፋ ኮንፌዴሬሽን ካፕ ላይ በተደረጉት እያንዳንዱ ጨዋታዎች ላይ ከዋንጫ ጨዋታው በስተቀር ለብሄራዊ ቡድኑ ግብ ማስቆጠር ችሏል። በዋንጫ ጨዋታው ላይ ብራዚል በሜክሲኮ የ4ለ3 ሽንፈት ደርሶባት ዋንጫውን ማግኘት ባትችልም ኮንፌዴሬሽን ካፕ ጎቾ የ«ጎልደን ግሎብ» የምርጥ ተጫዋችነት ሽልማት እና የወርቅ ጫማን በግሉ አሳክቷል። በ2000 ላይ ደግሞ ሲድኒ ላይ በተካሄደው ኦሎምፒክ ከብሄራዊ ቡድኑ ጋር በመጓዝ ተጫውቷል። በቅድመ ኦሎምፒክ ውድድሮች ላይም በሰባት ጨዋታዎች 9 ጎሎችን ማስቆጠር ችሏል። ጎቾ በዓለም ዋንጫ ታሪኩ ከብራዚል ጋር የማይረሳ ትዝታን ያስተናገደው በኮሪያና ጃፓን አስተናጋጅነት በ2002 ዓ.ም ነው። በዚህ ውድድር ላይ በስሙ ሁለት ግቦች እና በርካታ ለግብ የሚሆኑ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር ችሏል። በተለይ በግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ላይ ከእንግሊዝ ጋር የተገናኘችውን ብራዚል ጨዋታውን በድል እንድትወጣ ያስቻላትን አስደናቂ ቅጣት ምት አስቆጥሯል። በተለይ ጎሏን ልዩ የሚያደርጋት ከ40 ሜትር ርቀት ላይ የተቆጠረች እና ዴቨድ ሴማንን በእጅጉ የፈተነች በመሆኗ ነበር። በ2005 ሮናልዲንሆ የብራዚል ብሄራዊ ቡድንን በአንበልነት እየመራ የፊፋ ኮንፌደሬሽን ካፕን አንስቷል። በተለይ በውድድሩ በሜክሲኳዊው ኩቲሞክ ብላንኮ የተያዘውን የ9 ጎል ክብረ ወሰን መጋራት ችሏል። በ1999 አሜሪካን ካፕ እንዲሁም በ1997 በፊፋ 17 ዓመት በታች የዓለም ሻምፒዮን ዋንጫን አንስቷል። በዋናው የብራዚል ብሄራዊ ቡድን በ97 ጨዋታዎች ተሰልፎ ያስመዘገባቸው 33 ጎሎች ናቸው። ከ1996 ጀምሮ በብራዚል ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በ6 ጨዋታዎች 2 ግብ አስቆጥሯል። ከ1999 ጀምሮ በብራዚል 20 ብሄራዊ ቡድን በ5 ጨዋታዎች 3 ጎሎችን፤ ከ1999 እስከ 2008 በብራዚል 23 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በ27 ጨዋታዎች 18 ጎሎች፤ ከ1999 እስከ 2013 በብራዚል ብሄራዊ ቡድን በ97 ጨዋታዎች 33 ጎሎች አስመዝግቧል። 2006 ለጎቾ ጥሩ ጊዜ አልነበረም። ምክንያቱ ደግሞ አንድ ነው። የዓለም ዋንጫ። እርሱን፣ አድሪያኖን እና ካካን የያዘው ብሄራዊ ቡድን ዋንጫውን ያነሳል የሚል ከፍተኛ ግምት ተሰጥቶት ነበር። ነገር ግን በግልባጩ ያልታሰበ ነገር ተከሰተ። ስምንት ውስጥ ቢደርሱም በፈረንሳይ የ1ለ0 ሽንፈት ስለገጠማቸው ከውድድሩ ውጪ ለመሆን ተገደዱ። ጎቾ በዚህ ውድድር ላይ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ አቋሙ ወርዶ ነበር። ዓለምን ያስደነቀው ምርጥ ተጫዋች በዚያን ዓመት ለአገሩ ሊደርስላት አልቻለም። በዚህ የተናደዱት ደጋፊዎችም 7 ነጥብ 5 ሜትር የሚደርሰውን ለክብሩ የተተከለለት ሀውልት ጥቃት አድርሰውበት ነበር።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 6/2011", "passage_id": "ffcf974a46604a52afff06cd614b8c2e" }, { "passage": "አውሮፓ ውስጥ ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆነው የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ የዓለማችን ልጥጥ ክለቦች የሚገኙበት ቢሆንም አደጋ የተጋረጠበት ይመስላል። አደጋው ደግሞ የባለፈው ውድድር ዘመን ቻምፒዮና - ማንቸስተር ሲቲ፤ ይላል የቢቢሲ ስፖርት ተንታኙ ቤን ሱዘርላንድ። \n\n•ጊነስ ዎርልድ ሪከርድስ፡ «ስለተተከሉት ዛፎች ከኢትዮጵያ የደረሰን መረጃ የለም»\n\n•\"የት ይቀርልሃል!? አፈር ድሜ ትበላለህ...!\" ጋሽ አበራ ሞላ\n\nየእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ተወዳጅ እንዲሆን ካደረጉት ጉዳዮች መካከል ዋነኛው ልብ-አንጠልጣይ ፉክክር የሚታይበት መሆኑ ነው። ፈጣን፣ ፈታኝ እና የማይጠበቁ ውጤቶች የሚመዘገቡበት ሊግ ነው። ቢሆንም ይህ ምስል አደጋ ላይ ይመስላል። \n\nበዓመታት ሂደት ሊጉ ስድስት ኃያላን ክለቦች ተብለው የሚታወቁትን አምርቷል። ዩናይትድና ሲቲ፣ ሊቨርፑል፣ አርሴናል እና የከተማ ተቀናቃኙ ቶተንሃም እንዲሁም የምዕራብ ለንደኖቹ ቼልሲ።\n\nአደጋው እዚህ ጋ ነው። በሂደት ስድስቱ ኃያላን ቀርቶ አንድ ኃያል እንዳይሆን የሚል ስጋት። \n\n'እግር ኳስ ከስማለች'\n\nያለፈው ውድድር ዘመን እጅግ ተወዳጅ ያደረገው ሊቨርፑል የሲቲን እግር እየተከተለ ዋንጫ ለማግኘት ያደረገው ጥረት ነበር። \n\nነገር ግን ሁለቱም ክለቦች የቋመጡለትን ዋንጫ ተቀያይረው አግኝተዋል። ፕሪሚዬር ሊግን የቋመጠው ሊቨርፑል ቻምፒዮንስ ሊግ ሲያነሳ፤ ቻምፒዮንስ ሊግን ለማንሳት የሻተው ሲቲ የሊጉን ዋንጫ ወስዷል።\n\n•ታዳጊዎችን በወሲብ ንግድ በማሰማራት ተከሶ የነበረው ቱጃር አሟሟት ጥያቄን ፈጥሯል \n\nሊቨርፑል የሊጉን ዋንጫ ካነሳ ሶስት አስርት ዓመታት ተቆጥረዋል፤ በአቡ ዳቢ ቱጃሮች የተያዘው ሲቲ ደግሞ ቻምፒዮንስ ሊግ አንስቶ አያውቅም። \n\nሲቲ ዘንድሮ የሊጉን ዋንጫ ማንሳት ከቻለ ሌላ ታሪክ ይፅፋል። በአንድ ውድድር ዘመን በርካታ ጎሎች በማስቆጠር እና በርካታ ነጥቦች በማምጣት ሲቲ ሪከርዱን ይዟል። \n\nበኤፍ ኤ ዋንጫ ዋትፈርድን 6-0 በመርታት ተመልካችን አጀብ አሰኝተዋል። ይህን ያዩ የኳስ ተንታኞች 'እግር ኳስ ከስማለች' እስከማለት ደርሰዋል። \n\nየፈርናንዲሆ ምትክ ያስፈልጋቸዋል እየተባሉ ሲታሙ የነበሩት ሲቲዎች ባለተሰጥዖው ሮድሪን አስፈርመዋል። በዘመናዊ እግር ኳስ ምርጡ አሰልጣኝ የሚል ስያሜ የተሰጠው ፔፕ ጉዋርዲዮላን የያዙት ሲቲዎች ወደፊትም ተፅዕኖዋቸው እንደሚቀጥል ይገመታል። \n\nየተሻለ የእረፍት ጊዜ ያሳለፉት ሲቲዎች በኮሚኒቲ ሺልድ ጨዋታ ሊቨርፑልን መርታት ችለዋል። በአቋምም ሆነ በስነልቡና ጥንካሬ ከሊቨርፑል የተሻሉ ሆነው ነበር የታዩት። \n\nበሌላ በኩል ሌሎች ኃያላን ሲቲን ተቋቁመው የሊጉን ዋንጫ ያነሳሉ ማለት ከባድ ነው። \n\nአርሴናሎች ፔፔን ቢያስፈርሙም፤ ተከላካይ መስመሩ አሁንም ጥገና የሚያሻው ይመስላል። ኪዬራን ቲየርኒን ከሴልቲክ፣ ዴቪድ ልዊዝን ደግሞ ከቼልሲ ማስፈረማቸው ሳይዘነጋ። \n\nአዲስ አሰልጣኝ የቀጠሩት ቼልሲዎች ኤደን ሃዛርድን ለቼልሲ ቢሸጡም በተጣለባቸው ቅጣት ምክንያት ተጫዋች መግዛት አልቻሉም። ይህ ደግሞ ለአዲሱ አሰልጣኝ ፍራንክ ላምፓርድ ሁኔታዎችን የሚያከብድበት ይመስላል። \n\nየዩናይትዱ ኦሌ ጉናር ሶልሻዬር ቡድኑን የተቀበለ ሰሞን ድንቅ አቋም ቢያሳይም ወደ መጨረሻ ከበድ ያለ ጊዜ አይቷል። ዩናይትዶች ሊጉን ያሸንፋሉ ተብሎ የተሰጣቸው ግምት ከእስከዛሬው እጅግ ዝቅ ያለ ነው። \n\n•ዘሩባቤል ሞላና በአነቃቂ መንፈስ የታሸው 'እንፋሎት' አልበሙ\n\nታድያ የእነዚህ ኃያላን ቡድኖች እንደ ሲቲ ዝግጁ አለመሆን ለሊጉ አደጋ መሆኑ አይቀርም። እንደ ጣልያን [ጁቬንቱስ ለ8 ተከታታይ ዓመታት ዋንጫ ያነሳበት]፤ እንዲሁም ጀርመን [ባየርንሚዩኒክ ለሰባት ተከታታይ ዓመታት] ሊጎች አጓጊነቱ የወረደ እንዳይሆን ነው ዋነኛው ስጋት። \n\nበየወሩ... ", "passage_id": "ac4b84f42beba8c28a273aa8d4c8757f" }, { "passage": "አራት የምዕራብ አፍሪካ ሃገራት የያዘው የመጨረሻው ምድብ ከሞት ምድብ ቀጥሎ አጓጊ ምድብ ነው። ቻምፒዮኗ ካሜሩን፣  ጋና፣ ቤኒን እና ጊኒ ቢሳዋን የሚያገናኘው ይህ ምድብ ጠንካራ እና እልህ አስጨራህ ፉክክር ይታይበታል ተብሎ ይጠበቃል።🇨🇲 ካሜሩን የተሳትፎ ብዛት – 19ምርጥ ውጤት – 5 ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ (1984, 1988, 2000, 2002, 2017)በቀድሞ የኤስሚላን ጀግና ክላረንስ ሲዶርፍ የሚመሩት የባለፈው ውድድር አሸናፊ ካሜሩን ይሄ ውድድር እንደባለፈው ፉክክር አልባ አፍሪካ ዋንጫ አልጋ በአልጋ እንደማይሆንላቸው የታወቀ ነው።በማጣርያው በምድብ ‘B’ ከሞሮኮ፣ ኮሞሮስና ማላዊ ተደልድለው በደካማው ምድብ ሳይፈተኑ ወደ ውድድር ያለፉት ካሜሩኖች የፓሪ ሰን ጀርመው አጥቂ ቾፓ ሞቲንግን ይዘው ወደ ግብፅ ሲያመሩ ቡድኑ ቻምፒዮን በሆነበት ዓመት በፍፃሜው ጨዋታ የቡድኑ የነብስ አዳኝ የነበረው ቪንሰንት አቡበከር እና ባለፈው የውድድር ዓመት ከሊቨርፑል ጋር ድንቅ ዓመት ያሳለፈውና የሃገሩን ጥሪ አልቀበልም በማለቱ በሃገሩ ልጆች እንደ ከሃዲ የታየው ቀውላላው ተከላካይ ዮኤል ማቲፕ በክላረንስ ሲዶርፍ ጥሪ አልደረሳቸውም።የቅድመ ዝግጅታቸው በስፔን እና ኳታር ያደረጉት ካሜሩኖች በአቋም መለኪያ ጨዋታ ዛምቢያ እና ኤዲ ኮርኮን የተባለ የስፔን ክለብ ሲያሸንፉ ከማሊ ጋር አቻ ተለያይተዋል።የማይበገሩት አናብስት ከአያክስ ጋር ድንቅ ዓመት ያሳለፈው ግብጠባቂው አንድሬ ኦናና እና በሃገሩ ማልያ ጥሩ የጎል ክብረወሰን ያለው ማክሰም ቾፓሞቲንግ ላይ ተስፋ ጥለዋል።🇬🇭 ጋና የተሳትፎ ብዛት – 22\n\nምርጥ ውጤት – 4 ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ (1963 ,1965 ,)ሃገራችን ኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ሴራሊዮን ከነበሩበት ምድብ ‘F’ ምድቡን በበላይነት በማጠናቀቅ በቀላሉ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፉት ጥቋቁር ከዋክብቶች በውድድሩ በተከታታይ አምስት ጊዜ ለፍፃሜ በመድረስ ባለ ታሪክ ናቸው። አንድሬ አየው አምበልነት ወደ ግብፅ የሚያቀኑት ጥቋቁር ከዋክብቶች በዱባይ በቆዩባቸው የዝግጅት ቀናት ሶስት የአቋም መለኪያ ጨዋታዎች አድርገው አንድ ድል ፣ አንድ አቻ እና አንድ ሽንፈት ቀምሰዋል።ሁሌም በውድድሩ ተጠባቂ ከሆኑት ሀገራት ተርታ ብትሰለፍም 37 ዓመት ያስቆጠረችው ሀገር ታሪኳን ለማደስ አስር ለውድድሩ እንግዳ የሆኑ ተጫዋቾችን ከማካተት ባሻገር እንደ አትሌቲኮ ማድሪዱ ቶማስ ፓርተይ፣ ባለልምዶቹ ክዋዱ አሳሙሃ፣ አንድሬ አዬው እና አሳሞሃ ጅያን ባሉ ተጫዋቾች ላይ ተስፋ ጥለዋል።ሳይጠበቅ አዳዲስ ፊቶች ይዞ ወደ ውድድሩ ለማቅናት የወሰነው ክዌሲ አፒያ እነ ባባ ኣህማን ፣ ጆናታን ሜንሳህ ፣ ጆሴፍ አይዶ እና ዓብዱልመጅድ ዋሪስ ወደ መጨረሻው ስብስቤ ሳያካትት ወደ ግብፅ ያመራል።🇧🇯 ቤኒን የተሳትፎ ብዛት – 3ምርጥ ውጤት – የምድብ ጨዋታዎችአልጀርያ ፣ ቶጎ እና ኮሞሮስ ከነበሩበት ምድብ ‘ D’ ከምድቡ መሪ አልጀርያ በአንድ ነጥብ ዝቅ ብላ በሁለተኛነት በማጠናቀቅ ከዘጠኝ ዓመት በኃላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው የተመለሰችው ቤኒን የማጣርያ ጉዞዋን መሰረት በማድረግ ቀላል ተጋጣሚ እንደማትሆን መገመት አያዳግትም።በማጣርያው ጨዋታዎች ላይ አምስት ግቦች ብቻ ያስቆጠሩት ቤኒኖች እንደ አብዛኞቹ የአፍሪካ ሃገራት ግብ የማስቆጠር እና ንፁህ የግብ ዕድል በመፍጠር ረገድ ቀላል የማይባል ክፍተት አለባቸው።ለቅድመ ዝግጅት ሞሮኮ የቆዩት ቤኒኖች ሶስት ጨዋታዎች አድርገው ሶስቱም በድል ተወጥተዋል።በርከት ያሉ ተጫዋቾች ከፈረንሳይ የመረጡት ቤኒኖች በአንጋፋው ስቴፈን ሴሴኞ እና በሃደርስፊልዱ ስቲቭ ሞውኔ ላይ ተስፋ ጥለዋል።🇬🇼 ጊኒ ቢሳው የተሳትፎ ብዛት – 2ምርጥ ውጤት – የምድብ ጨዋታዎችዛምቢያ ፣ ናሚቢያ እና ሞዛምቢክ ከነበሩበት ምድብ ‘ k ‘ ሳትጠበቅ ምድቡን በበላይነት ያጠናቀቀችው ጊኒ ቢሳው ትላቋን ዛምቢያ ጨምሮ ሌሎቹን ሁለት ሃገራት ረምርማ ወደ ውድድሩ ታልፋለች ብሎ የገመታት አልነበረም። ከሞዛምቢክ ጋር በነበረው ድራማዊ ክስተት በተሞላበት ጨዋታ በአስደናቂ ብቃት አቻ ከተለያየች በኃላ የብዙዎች ትኩረት ስባ የነበረችው ጊኒ ቢሳው ሽንፈት ሳትቀምስ ነበር ወደ ውድድሩ ያለፈችው።በአሰልጣኝ ካንዴ እየተመራች ለሁለተኛ ጊዜ በውድድሩ የምትሳተፈው ጊኒ ቢሳው በማጣርያው ሶስት ግብ ያስቆጠረላት ፍሬድሪክ ሜንዲ ኮከብ ተጫዋቿ ነው።የምድቡ ተጠባቂ ጨዋታ፡ ካሜሩን ከ ጋናሁለቱ በውድድሩ ትልቅ ታሪክ ያላቸው የምንግዜም ተቃናቃኞች የሚያገናኘው ይህ ጨዋታ በታሪክም በወቅታዊ አቋም ረገድም ተጠባቂ ጨዋታ ነው።ተመሳሳይ አጨዋወት የሚከተሉት ሁለቱ ቡድኖች የሚያገናኘው ይህ መርሐ ግብር የምድቡ ሁለተኛ ጨዋታ ነው።ከምድቡ የሚጠበቅ ኮከብ ተጫዋች: ቶማስ ፓርቲይከምድብ ስድስት የሚጠበቀው ተጫዋች ጋናዊው የአትሌቲኮ ማድሪዱ ወሳኝ አማካይ ቶማስ ፓርተይ ነው። በምድቡ በርካታ የማጥቃት ባህሪ ያላቸው እና ከዚ በፊት በውድድሩ ልምድ ያላቸው እንደነ አሳሞሃ ጅያን የመሳሰሉ ተጫዋቾች ቢኖሩም እንደ የሃያ ስድስት ዓመቱ ውጤታማ አማካይ የሚያክል ግን አይጠበቁም። በአትሌቲኮ በበርካታ ሚናዎች ላይ የሚጫወተው አይደክሜው ተጫዋች በጋናም ተመሳሳዩ ሚና ከተሰጠው እንደሚያንፀባርቅ ይጠበቃል።የምድቡ ጨዋታዎችማክሰኞ ሰኔ 18 ቀን 2011ካሜሩን 2:00 ጊኒ ቢሳውጋና 5:00 ቤኒንቅዳሜ ሰኔ 22 ቀን 2011ካሜሩን 2:00 ጋናቤኒን 5:00 ኢኳቶርያል ጊኒማክሰኞ ሰኔ 25 ቀን 2011ቤኒን 1:00 ካሜሩንጊኒ ቢሳው 1:00 ጋና*ይፋዊ የተጫዋቾች ስብስብ እንደደረሰን እናካትታለን", "passage_id": "61b18c41140d8d708b3603bdddfe2c94" }, { "passage": "በአሜሪካ ፉትቦል የኒው ኢንግላንድ ፔትሪየትስ፣ በሱፐርቦል ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደ የጭማሪ ሰዓት አሽንፈው ዋንጫ አነሱ። ዋና አከፋፋዩ ቶም ብሬዲ ከቻርልስ ሄሊ ቀጥሎ 5 የሱፐርቦል ቀለበት በማግኘት ሁለተኛው ተጫዋች ሆኗል።የኢትዮጵያን ፕሪምየር ሊግና የአትሌቲክስ ስፖርት ዘገባ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡ ", "passage_id": "88b1798f68dd4315fb5dc5474e268c18" } ]
3539bc3430f924ef143aed3b8ec081b6
6d433d0150840ea67e532f9662178373
የስፖርት ማህበራትን ለመከለስ መመሪያ እየተዘጋጀ ነው
ዘመናዊ ስፖርት ወደ ኢትዮጵያ ከገባ አንድ ምዕተ ዓመት ሊያስቆጥር መቃረቡን ሰነዶች ያሳያሉ። ይሁን እንጂ ስፖርት በኢትዮጵያ በዕድሜው ልክ እንዲሁም ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ አንጻር መድረስ ካለበት ስፍራ እንዳልደረሰ አፍን ሞልቶ መናገር ይቻላል። ስፖርት የአንድ ሀገር እድገት መለኪያ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ቢሆንም፤ በኢትዮጵያ የህዝቡን ጥቅምና ፍላጎት አስጠብቋል ለማለት አያስደፍርም። ለስፖርቱ እድገትም ሆነ መዳከም ድርሻ ያላቸው የተለያዩ ምክንያቶች ቢኖሩም ስፖርቱን የሚመሩ አካላት ጥንካሬና ብቃት ግን ወሳኝነት እንዳለው ይታመናል። ይሁን እንጂ እስካሁንም ድረስ በዚህ አቅጣጫ ሳይሆን በራሳቸው ጥረት የተሻለ ብቃት ያሳዩትን ስፖርተኞች በውድድር ላይ ማሳተፍ ላይ ያተኮረ አካሄድ እየተተገበረ ይገኛል። ስፖርትን ለልማት ከማዋል ይልቅ ውድድሮችን ብቻ ኢላማ ያደረገ አካሄድም ስፖርቱ በሚፈለገው ልክ እንዳያድግ ያደረገ ገፊ ምክንያት ሆኖ በተደጋጋሚ ይነሳል። የአገራችን ስፖርት ከየት ተነስቶ ወደ የት ማምራት እንዳለበት የሚያሳይ የስፖርት ፖሊሲ አቅጣጫ በ1990 ዓ.ም ተቀርጿል። ነገር ግን በፖሊሲው በተቀመጠው ልክ በተጨባጭ ስኬታማ የሆነ ሂደት ባለማሳየቱ በአሰራሩ ላይ ፍተሻ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል። በዚህም መሰረት በጥናት ላይ የተመረኮዘ ብሄራዊ የስፖርት ሪፎርም በቅርቡ በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን መዘጋጀቱ ይታወቃል። በሪፎርሙ ምክረ ሃሳብ መሰረትም መመሪያዎች በመከለስና በመሻሻል ላይ ይገኛሉ። ሪፎርሙ ካመላከታቸው ነጥቦች መካከል አንዱ የሆነው አደረጃጀቱን የሚመለከት ሲሆን፤ በተለይ መንግስታዊው አካል ላይ ክፍተት መኖሩን አመላክቷል። በኢትዮጵያ 30 የሚሆኑ የስፖርት ፌዴሬሽኖችና አሶሴሽኖች ይገኛሉ። ከፌዴራል እስከ ቀበሌ ባለው አደረጃጀትም በጥቅሉ 397 ፌዴሬሽኖችና የስፖርት ማህበራት እንዳሉ ይታመናል። ከእነዚህ ማህበራት መካከል ራሳቸውን ችለው ከመንግስት ድጎማና ድጋፍ የተላቀቁት ግን ሁለቱ ብቻ ሲሆኑ፤ አትሌቲክስና እግር ኳስ ፌዴሬሽኖች በዋናነት ይጠቀሳሉ። የተቀሩት እስካሁንም የመንግስትን ድጎማ የሚጠብቁ በሁለት እግራቸው ያልቆሙ ሲሆኑ፤ በግላቸው የሚያደርጉት እንቅስቃሴም አነስተኛና የተገደበ ነው። ለዚህና ለስፖርቱ አለማደግ በዋናነት እንደ ምክንያት የሚያነሱትም በመንግስት በኩል የሚመደብላቸውን አነስተኛ የበጀት ድጎማ ነው። ነገር ግን የየስፖርት ዓይነቱን በኃላፊነት የሚመሩትና በየደረጃው የሚገኙ የስፖርት ማህበራት (ፌዴሬሽኖች) ካሉባቸው ችግሮች ባሻገር ከራሳቸው ድክመት የተነሳ ስፖርቱ እንዲዳከም ምክንያት እንደሆነ ይታመናል። አሁን ባለው ሁኔታ ፌዴሬሽኖቹ ራሳቸውን ከተረጂነት ነጻ ለማውጣት ያላቸውን እድል ተጠቅመው ለውጥ ለማምጣት የሚፍጨረጨሩት ጥቂቶች ናቸው። መልካም ተሞክሮ ካላቸው ሌሎች ፌዴሬሽኖች ልምድ ለማግኘት የሚችሉበት መንገድም ዝግ መሆኑ ይስተዋላል። አንዳንድ ስፖርቶች በህዝቡ ዘንድ በቅጡ ያልታወቁና ተደራሽነታቸውም በአሳሳቢ ደረጃ ላይ የሚገኙ ሲሆን በማህበር ታቅፈው የመንግስትን በጀት ለብክነት የሚዳርጉም አሉ። በአንጻሩ መልካም ድልና የተሻለ ውጤት ሊመዘገብባቸው የሚችሉ ስፖርቶች ደግሞ እንቅስቃሴያቸው የተገደቡ ሆነዋል። ሌሎች ደግሞ በተወሰኑ አካላት ተሸብበው እድገታቸው ቀጭጮ እንዲቀር ሆነዋል። ስፖርቱ በህዝቡ ዘንድ ተስፋፍቶ ጥቅም የሚገኝበት እንዲሁም በሀገር ደረጃ ውጤት እንዲመዘገብበት ካስፈለገም እነዚህ ችግሮች በቅድሚያ ሊቀረፉ እንደሚገባ ብዙዎች ይስማማሉ። በመሆኑም ሀገር አቀፉን የስፖርት ማህበራት ማቋቋሚያ መመሪያ ማሻሻል አስፈልጓል። ባለፈው ሳምንት ኮሚሽኑ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የተሻሻለው መመሪያ ረቂቅ በኮሚሽኑ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን አልዩ ለተሳታፊዎቹ የቀረበ ሲሆን አስተያየትም ተሰጥቶበታል። በገለጻው ላይ እንደተመላከተው ከሆነም ለመመሪያው መሻሻል አስፈላጊ የሆኑት ምክንያቶች፤ በሪፎርሙ የተሰጠው ምክረ ሃሳብ፣ የማህበራዊ ወቅታዊ አቋም፣ ያሉባቸውን ችግሮች ለመፍታት እንዲሁም የስፖርት ምክር ቤቱ የውሳኔ አቅጣጫ ናቸው። የማህበራቱን አሰራሮችና አደረጃጀቱን በመፈተሽ ተገቢውን መስፈርት አሟልተው እንዲሄዱ ማድረግም አላማው ነው። አብዛኛዎቹ ማህበራት ተገቢውን መስፈርት ሳያሟሉ የማህበር ስያሜ ብቻ በመያዝ እውቅና አግኝተው የሚንቀሳቀሱ በመሆናቸው ውጤታማ መሆን አልቻሉም፤ በመሆኑም ዳግም ዕውቅና ማግኘት አስፈልጓቸዋል። መሆኑም ማሻሻያው የተለያዩ ሂደቶችን ተከትሎ ሊዘጋጅ ችሏል። ይኸውም ነባሩን መመሪያ መሰረት በማድረግ፣ የሌሎች ሀገራትን ተሞክሮ በመዳሰስ፣ ዓለም አቀፍ አሰራሮችን በመመልከት እንዲሁም ያጋጠሙ ተጨባጭ ሁኔታዎችን በመውሰድ መሆኑንም በመድረኩ ተጠቁሟል። በስራውም የኮሚሽኑ፣ የተለያዩ ፌዴሬሽኖች እንዲሁም የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ባለሙያዎች ተሳታፊዎች ነበሩ። መመሪያው ከያዛቸው ሃሳቦች መካከል አደረጃጀትና ስያሜን የሚመለከት ሲሆን፤ በክልል ያሉ ፌዴሬሽኖች ‹‹አሶሴሽን›› ከዚያ በታች ያሉት ደግሞ ‹‹ኮሚቴ›› በሚል ቢጠሩ ለአሰራር አመቺ እንደሚሆኑ ተመልክቷል። የፌዴሬሽን ማቋቋሚያ መስፈርትን በተመለከተም የቡድንና የግል ስፖርቶችን በራሳቸው አሰራር መሰረት እውቅና የሚያገኙበት ሁኔታም ተካቷል። በዚህም የቡድን ስፖርቶች የሚያወዳድሯቸው ቢያንስ ስድስት ክለቦች ሊኖሯቸው እንደሚገባ፤ በአርት ስፖርቶች 10 ማዕከላት እንዲሁም በግል ስፖርቶች 250 የተመዘገቡ ስፖርተኞች ሊኖሩ ይገባል። ደረጃውን የጠበቀ የውድድርና የስልጠና ቁሳቁስ መኖሩ ሲረጋገጥ፣ የሀብት ምንጭ ሲኖራቸው እና የሂሳብ አያያዝ ሥርዓት የዘረጉ ሊሆኑም ይገባቸዋል። የሀገር አቀፍ ስፖርት ፌዴሬሽኖች የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት እጩ አቀራረብ፣ የመምረጫ መስፈርት እንዲሁም ተግባርና ኃላፊነትም በመመሪያው ተካቷል። በዚህም የኮሚቴዎቹ የስራ ዘመን አራት ዓመት ብቻ ሲሆን፣ በድጋሚ የሚመረጡትም ለአንድ የስራ ዘመን ብቻ ይሆናል። ይህም ቀድሞ በተለያየና በተበታተነ ሁኔታ ይከናወን የነበረው ምርጫ አንድ የኦሊምፒክ ጨዋታ በተጠናቀቀ ሶስትና አራት ወራት ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤ በመጥራት ምርጫ እንዲከናወን የሚያስገድድ ነው። ከዚህ ጋር የተካተተው መመሪያም የትኛውም የስራ አስፈጻሚ ሊያገለግል የሚችለው በአንድ ስፖርት ላይ ብቻ መሆኑን የሚያመለክት ነው። የማህበራት ፈቃድ አሰጣጥ፣ እድሳትና መፍረስን በተመለከተም በምን መልኩ ይከናወናል የሚለውን የተሻሻለው የመመሪያ ረቂቅ በዝርዝር አስቀምጧል። የኦሊምፒክና ፖራሊምፒክ ኮሚቴዎች፣ የከፍተኛ ትምህርት ስፖርት ማህበር እንዲሁም የጤና ስፖርት ማህበር በበኩላቸው የተለያዩ ስፖርቶችን አቅፈው የሚያካሂዱ ማህበራት እንደመሆናቸው ከሌላው የተለዩ መሆናቸውም ተገልጿል። በመመሪያው ዝግጅት ላይ ተሳታፊ የነበሩትና ገለጻውን ያደረጉት የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ሰለሞን አልዩ ምላሽ የተነሱ ሃሳቦች ላይ ምላሽ ሰጥተዋል። መድረኩ የተዘጋጀው ግብዓት ለመሰብሰብ እንደመሆኑ በተለያዩ አካላት ዘንድ የተለያዩ እይታዎች ይፈጠራሉ። በመሆኑም ጠቃሚ የሆኑትን ለማካተት ያስችላል፤ የስፖርቱ አደረጃጀት በምን መልክ ሊቃኝ ይገባል በሚለው ላይ ጠቃሚ ሃሳቦች እንጂ ፍላጎቶችን ለማስተናገድ እንደማይቻልም አሳስበዋል። አደረጃጀቶቹ ያሉባቸውን ክፍተቶች በመሙላት አደረጃጀቱን ለማጠናከር ይቻላል፤ ስለዚህም የተሰጡት ግብረ መልሶች በሰነዱ የሚካተቱ ይሆናል። በተጨማሪም መድረኩ የተዘጋጀው በምክር ቤት በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በመሆኑ መንግስት ወደፊትም ለማህበራቱ እገዛና ድጋፍ ከማድረግ ወደኃላ እንደማይልም አመላክተዋል። በኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ዱቤ ጂሎ በበኩላቸው ይህ የቀረበው ረቂቅ መመሪያ ወደ ክልሎች ወርዶ የራሳቸውን ደንብና መመሪያ እንዲያወጡ የሚደረግ መሆኑን ገልጸዋል። ማህበራቱ የየራሳቸውን መመሪያና ደንብ ካዘጋጁ በኋላም በዚህ ላይ ተመስርተው ክልሎች በስታንዳርዱ መሰረት የሚተዳደሩ ይሆናል፤ በመሆኑም በመድረኩ የተንጸባረቁ ሃሳቦች ጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል። አዲስ ዘመን ሐምሌ 25 ቀን 2012 ዓ.ምብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=36457
[ { "passage": "የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌደሬሽን በእግር ኳስ ሊጎቻችን አደረጃጀት ላይ ያተኮረ የጥናት ውጤት ነገ ይፋ ያደርጋል፣ ከጥናቱ መቅረብ በኋላም ለሚዲያ መግለጫ ይሰጣል።\nበኃይለየሱስ ፍስሃ (ኢ/ር) ፕሬዝዳንትነት የሚመራው የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌደሬሽን በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የእግር ኳስ ሊጎችን አደራረጅት እና አካሄድ የሚመለከት ጥናት እያስጠና መሆኑን መግለፁ ይታወሳል። በዚህም መሰረት ባሳለፍነው ሳምንት ፌደሬሽኑ በቀጥተኛ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት (ክለቦች) ጋር ውይይት በማድረግ ለጥናቱ ተጨማሪ ግብዓት ሰብስቦ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።የዚህ የጥናት ውጤት ነገ 8 ሰዓት በጁፒተር ሆቴል ለሚመለከታቸው አካላት እንደሚቀርብ ታውቋል። ፌደሬሽኑ እንዳስታወቀው ከሆነ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን እና የስፖርት ኮሚሽን ተወካዮችን ጨምሮ በእግር ኳሱ አካባቢ ያሉ አካላት ነገ በቦታው ይገኛሉ። በሥነስርዓቱም ጥናቱ በአቶ ገዛኸኝ (የአዲስ አበባ ከተማ ክለብ ስራ አስኪያጅ) አማካኝነት ከቀረበ በኋላ ለብዙሃን መገናኛዎች መግለጫ እንደሚሰጥ ታውቋል።", "passage_id": "06d5d9afe996c8bb88249ad377064fef" }, { "passage": " ቦጋለ አበበ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ባለፈው ዓመት በቢሾፍቱ ባካሄደው አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔ ወቅት ኮሚቴው የሚተዳደርበትን አዲስ መተዳደሪያ ደንብ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። ይህ መተዳደሪያ ደንብ ገና ከመጀመሪያው ውዝግብ ያስነሳና በስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት መካከል አለመግባባትን እንደፈጠረ አይዘነጋም። ኮሚቴው ከትንናት በስቲያ በሲዳማ ክልል ሐዋሳ ከተማ ባካሄደው አርባ አምስተኛው መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ላይም መተዳደሪያ ደንቡን በተመለከተ ከጉባዔው አባላት ጥያቄ አስነስቷል። በተለይም ደንቡ ይፋ ከተደረገ ጀምሮ ተቃውሞ እንዳላት ስትገልፅ የነበረችው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ በጉባዔው ላይ ጥያቄዋን ዳግም አንስታለች። በቢሾፍቱው አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔ ይፋ የተደረገው መተዳደሪያ ደንብ የጠቅላላ ጉባዔው አባላትና ስራ አስፈፃሚው እንዲወያይበት በይደር ላይ እንደነበር ያስታወሰችው ደራርቱ፣ ኮሚቴው ከትናንት በስቲያ ባደረገው ጉባዔ ላይ ባቀረበው የ2012 ዓ.ም የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ መተዳደሪያ ደንቡ እንደፀደቀ አድርጎ ማስቀመጡ ተገቢ እንዳልሆነ በመግለፅ ጥያቄ አንስታለች። ‹‹ስራ አስፈፃሚው ባላመነበትና ባልተወያየበት ሁኔታ መተዳደሪያ ሕጉ ፀድቋል፣ መተዳደሪያ ሕጉን በተመለከተ በኮሚቴ እንዲታይ በይደር ተውነው እንጂ አላፀደቅነውም›› ያለችው ደራርቱ በኮሚቴው ውስጥ የተለያዩ ሰዎች በተለይም የፅሕፈት ቤቱ ኃላፊ ተነስተው ሌላ ሰው ሲተካ በተለይም እሷ እንደ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል እንዳልተሳተፈች ተናግራለች። የኮሚቴው መተዳደሪያ ደንብ ጉዳይ ባለፈው ሳምንት በሸራተን አዲስ በተካሄደው የብሔራዊ ስፖርት ምክር ቤት ጉባዔ ላይ ለሰብሳቢው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ቀርቦም ባለድርሻ አካላት ከስፖርት ኮሚሽን ጋር ተወያይተውበት ውዝግቡን እንዲፈቱ አቅጣጫ ማስቀመጣቸው ይታወሳል። የብሔራዊ ስፖርት ምክር ቤት ሰብሳቢው ይህን አቅጣጫ ባስቀመጡበት ሁኔታ ኮሚቴው በእቅድ አፈፃፀሙ ሪፖርት ላይ መተዳደሪያ ደንቡ በዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ሕግና ደንብ መሰረት እንደፀደቀ አድርጎ ማቅረቡ ከብሔራዊ ስፖርት ምክር ቤቱ ሕግና ደንብ ጋር እንደሚጣረስ ከደራርቱ በተጨማሪ ሌሎች የጉባዔው አባላትም ጥያቄ አንስተውበታል። በጠቅላላ ጉባዔው በቀረበው ሪፖርት መሰረት የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴን አደረጃጀት፣ አሰራርና የሰው ሃይል አመራር ለማሻሻል የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስራዎችን እንዳከናወነ የገለፀ ሲሆን፣ በዋናነት በአሰራር ሊሻሻሉ ከሚገባቸው ስራዎች ቀዳሚዎቹ ደንቦችንና መመሪያዎችን በማዘጋጀት ማሻሻል መሆኑን በማመን ኮሚቴው ከዚህ በፊት በጠቅላላ ጉባዔ የፀደቀ ደንብ እንዳልነበረው አስቀምጧል። ሲሰራበት የነበረው ‹‹የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ መቋቋሚያና መተዳደሪያ መመሪያ›› በሚል በጠቅላላ ጉባዔ ያልፀደቀና በርካታ ክፍተቶች የነበሩበት መሆኑን በመጥቀስ፣ ኮሚቴው የሕግ ባለሙያዎችን አደራጅቶ የዓለም አቀፉን ኦሊምፒክ ኮሚቴ ቻርተርና የተለያዩ አገራት ተሞክሮዎችን በማካተት አዲስ መተዳደሪያ ደንብ በስራ አስፈፃሚ ቦርድ ተወያይቶና ግብዓት አክሎበት ለጠቅላላ ጉባዔ በማቅረብ መስተካከል አለባቸው የተባሉትን አስተካክሎ እንዲፀድቅ ማድረጉን ያስቀምጣል። በዚህም ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ መተዳደሪያ ደንብ ቀርፆ ለዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በመላክ ግብዓት እየጠበቀ እንደሚገኝ ተብራርቷል። የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ\nፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር\nወልደጊዮርጊስ በጉዳዩ ላይ\nለተነሱ ጥያቄዎች በሰጡት\nማብራሪያ፣ ጠቅላላ ጉባዔው\nመረዳት ያለበት የስፖርት\nምክር ቤቱ ያቀረበው\nየስፖርት ማህበራት ማቋቋሚያ\nመመሪያ ረቂቅና ውይይት\nየሚደረግበት ሃሳብ እንጂ\nፀድቆ መተዳደሪያ የሆነ\nደንብ እንዳልሆነ አስረድተዋል።\nከኦሊምፒክ ጋር ተያይዞ\nእያንዳንዱ የሚተላለፍ ውሳኔ\nየዓለም አቀፉን ኦሊምፒክ\nኮሚቴ ሕግና ደንብ\nመሰረት ባደረገ መልኩ\nእንደሆነ የገለፁት ፕሬዚዳንቱ፣\n‹‹እኛ እዚህ የተቀመጥነው\nየዓለም አቀፉን ኦሊምፒክ\nኮሚቴ ሕግና ደንብ\nለማስፈፀም ነው፣ የኢትዮጵያ\nኦሊምፒክ ኮሚቴ ቀዳሚ\nተግባርም ይህንኑ ማስከበር\nነው፣ ከዚህ የተለየ\nነገር ካለ ለዓለም\nአቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ\nአቅርበን ተቀባይነት ካገኘ\nእኛም እንቀበላለን›› ብለዋል።\nብሔራዊ ስፖርት ምክር\nቤቱ ባቀረበው ረቂቅ\nደንብ ላይ ኦሊምፒክ\nኮሚቴ ሳይሆን ክልሎች፣ፌዴሬሽኖች፣የታወቁ\nየስፖርት ድርጅትና ተቋማት መልስ መስጠት እንዳለባቸው የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ፣ እነዚህ የተጠቀሱ ባለድርሻ አካላት በብሔራዊ ስፖርት ምክር ቤቱ ረቂቅ ደንብ ላይ ድምፅ እንዳይኖራቸው መቀመጡን አስረድተዋል። ይህን መቀበል አለመቀበል ደግሞ የእነሱ ድርሻ ነው ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል። የስፖርት ማህበራትና ፌዴሬሽኖች፣ ክልሎችና የታወቁ የስፖርት ተቋማትን ከኦሊምፒክ ኮሚቴ አባልነት ያስወጣው ረቂቅ ደንብ መሆኑን ገልፀውም፣ እሳቸው እንደ ኮሚቴው አባልና ፕሬዚዳንት በረቂቅ ደንቡ ላይ እንደማይስማሙበት ተናግረዋል። ‹‹ይሄ እንዲሆን አልፈቅድም፣ ያለክልሎች የኢትዮጵያ ስፖርት ስፖርት አይደለም፣ ያለሕዝብ ተሳትፎ ስፖርቱ ስፖርት ሊሆን አይችልም፣ እነዚህ ትልልቅ ባለድርሻ አካላት የበዪ ተመልካች ሊሆኑ አይገባም›› ሲሉም አብራርተዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 27/2013", "passage_id": "82a04f598fe58ad5c12b91808119f124" }, { "passage": "ብርሃን ፈይሳ በኢትዮጵያ ስፖርት፤ ማህበራትና ክለቦች ከመንግስት እገዛ አለመላቀቃቸውና ሃብት በማመንጨት ተግባር ላይ ተሳታፊ አለመሆናቸው እንደ ድክመት ይነሳል።የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በአጭር ጊዜ ውስጥ ፕሪሚየር ሊጉ በአክሲዮን ማህበር እንዲተዳደር በማድረግና ከጥገኝነት እንዲላቀቅ የማድረጉ ጅማሬም መልካም የሚባል ነው።ስፖርቱን በበላይነት በሚመራው ብሄራዊ የስፖርት ምክር ቤትም የፌዴሬሽኑ ተግባር ለሌሎች ስፖርት ማህበራትም አርአያነት ያለው መሆኑ በሪፖርት ቀርቧል።ይሁን እንጂ ስፖርቱ በገቢ ረገድ ችግር እየደረሰበት መሆኑ ነው ፌዴሬሽኑ የጠቆመው። የኢትዮጵያ እግር ኳስ\nፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኢሳያስ\nጂራ በመድረኩ ላይ\n፤ እግር ኳሱ\nበስፖንሰር ምክንያት እየደረሰበት\nያለውን ችግርና ችግሩ\nየተፈጠረበትን ምክንያት መንግስት\nማጤን ይኖርበታል ሲሉ\nገልጸዋል።ይኸውም በህዝብ ተወካዮች\nምክር ቤት የወጣውን\nየአልኮል መጠጦች ማስታወቂያ\nበህዝብ መገናኛ ብዙሃን\nእንዳይተላለፍና በስታዲየሞች \n ውስጥ እንዳይሰቀል የሚከለክለው አዋጅን በቀጥታ እግር ኳሱን የጎዳ መሆኑን ይጠቁማሉ።በእርግጥ መንግስት ዜጎቹን የመጠበቅ ኃላፊነት ይኑርበት እንጂ መታየት ያለባቸው ጉዳዮች ሳይመዘኑ ታልፈዋል የሚሉት አቶ ኢሳያስ፣ ‹‹ጉዳት አድርሶብናልና ቢፈተሽ›› ሲሉ ጥያቄያቸውን ለብሄራዊ ስፖርት ምክር ቤቱ ጥያቄያቸውን አቅርበዋል። ለዚህም ማሳያ የሚሆነው ፌዴሬሽኑ ባለፈው ዓመት ከዋሊያ ቢራ ጋር 56 ሚሊየን ብር የስፖንሰር ስምምነት አድርጎ ነበር፤ ነገር ግን ይህ አዋጅ በወጣ ማግስት ስምምነቱ ተቋርጧል።በዓለም ላይ በሃብቱ ቀዳሚ የሆነው የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ በሃይንከን ቢራ ስፖንሰር እንደሚደረግ ያነሱት ፕሬዚዳንቱ፤ ሌሎች ሊጎችም በመጠጥ አምራች ተቋማት ስፖንሰር የሚደረጉበት አሰራር በዓለም ላይ የተለመደ መሆኑን ጠቁመዋል።ፌዴሬሽኑ በዚህ ረገድ ያለውን ሃሳብ በጽሁፍ ለመንግስት ማቅረቡንና አዋጁ በፌዴሬሽኑ ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረሱ በድጋሚ እንዲፈተሽ ካልሆነም መንግስት ብሄራዊ ቡድኖችን እንዲደግፍ ጠይቀዋል። እንደ ፕሬዚዳንቱ ማብራሪያ፤\nችግር ሲያጋጥም እርዳታ\nከማድረግ ባለፈ በኢፌዴሪ\nስፖርት ኮሚሽን ስር\nካሉ የስፖርት ማህበራት\nመካከል ምንም ዓይነት\nድጋፍ ከማይደረግላቸው መካከል\nአንዱ የኢትዮጵያ እግር\nኳስ ፌዴሬሽን ነው።ፌዴሬሽኑ\nበስሩ ያሉትን ሰባት\nብሄራዊ ቡድኖችን (በሁለቱም\nጾታ በተለያየ የዕድሜ ክልል እና ዋናውን ቡድን ጨምሮ) በራሱ ነው የሚያስተዳድራቸው።ካሜሩን ለምታዘጋጀው የአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታዎች የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን(ዋሊያዎቹ) ከማዳጋስካር፣ ኒጀር እና ኮት ዲቭዋር ጋር ተደልድሏል።በመሆኑም ቡድኑ የጉዞ፣ የሆቴልና ሌሎች በርካታ ወጪዎችን ማድረጉ የግድ ነው።በተመሳሳይ ለዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ከደቡብ አፍሪካ፣ ከዚምቧቡዌ እና ከጋና ጋር ባላት ድልድል ሌሎች ወጪዎችን ማድረግም ይጠይቃል።ሌሎቹ ብሄራዊ ቡድኖችም ለሚኖሯቸው አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ጨዋታዎች ተጨማሪ ወጪዎች ይጠበቃሉ።መንግስት ይህንን በባለቤትነት ወስዶ ብሄራዊ ቡድኖችን ሊያግዝ ይገባዋል። ብሄራዊ ቡድን ሃገር የምትወከልበት መሆኑ መንግስት ሊደግፈው ይገባሉ ያሉት ፕሬዚዳንቱ፣ በቶኪዮ ኦሊምፒክ የሚካፈለው የአትሌቲክስ ቡድን በመንግስት እገዛ እየተደረገለት መሆኑን በማሳያነት ይጠቅሳሉ።ይህ የስፖርት ማህበራት ድክመት ደግሞ ብሄራዊ ቡድኑንም ደካማ አድርጎታል፤ በመሆኑም መንግስት ድጋፍ ሊያደርግለት ይገባል ሲሉ ጠይቀዋል። አብዛኛዎቹ የእግር ኳስ ክለቦች የሚተዳደሩት በመንግስት እንደመሆኑ፤ ፌዴሬሽኑ ደግሞ ይህ መንግስት የሚመድበው ከፍተኛ ገንዘብ በዚህ መቀጠል የለበትም የሚል ሃሳብ እንደሌለው ገልጸዋል።ክለቦችን ወደ ግል ተቋም ለመመለስ በማቀድ ለሶስት ዓመታት ፕሮጀክት በመያዝ እየተንቀሳቀሱ ሲሆን፤ የመጀመሪያዎቹን ስድስት ወራት ከአንድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ጋር በመሆን በትምህርት ቀጣዮቹን ጊዜያት ደግሞ 30 ከመቶ የሚሆኑትን ክለቦች 30 በመቶ መንግስት 40 በመቶ ህብረተሰቡ እንዲይዛቸው የግል ባለሃብት ተሳትፎ በማከል ሙሉ ለሙሉ ከመንግስት ለማላቀቅ ታቅዷል።በመሆኑም ምክር ቤቱ አንድ አቅጣጫ መስጠት እንደሚገባው አሳስበዋል፤ ይህ ካልሆነ ግን መንግስት ድጋፉን ቢያቋርጥ አስቸጋሪ ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚችል ጠቁመዋል። ክልሎችም በስራቸው የሚያስተዳድሯቸው ክለቦች እንደመኖራቸው ለዚህ ስራ ተባባሪና በሚወጣው ደንብም ለመመራት እገዛ እንዲያደርጉም ፕሬዚዳንቱ ጠይቀዋል። በመድረኩ ላይ ሃሳባቸውን ያንጸባረቁት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሼር ካምፓኒ የቦርድ ሰብሳቢ መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ፤ ባለፉት ዓመታት በሁለቱም ጾታዎች በዋናው ብሄራዊ ቡድንም ሆነ በእድሜ በተቀመጡት ቡድኖች የተደረጉት እንቅስቃሴዎች ደካማና አንገት የሚያስደፉ እንደሆኑ መታየታቸውን ይጠቁማሉ።ብሄራዊ ቡድኖች ሲያሸንፉ በተለያዩ የሃገሪቷ ከተሞች ላይ በህዝቡ ዘንድ የሚፈጠረው ተነሳሽነት ታይቷል። ሰብሳቢው አንድ ያልታተመ ጥናትን ዋቢ በማድረግ በ2011/12 ዓ.ም በስፖርቱ ወደ 2ነጥብ2 ቢሊየን ብር ወጥቷል፤ ነገር ግን ውጤት አልመጣም ይላሉ።በመሆኑም እግር ኳስ በሚቀጥሉት 10 ዓመታት በዚህ መንገድ ይቀጥላል ወይስ ክለቦች ወደ ግል እንዲዘዋወሩና በገንዘብ ራሳቸውን እንዲችሉ ለማድረግ ታቅዷል የሚለው መመልከት አስፈላጊ መሆኑንም ነው ሰብሳቢው ያመላከቱት። በእቅዱ ላይ ክለቦች ከመንግስት ተረጂነት ሊወጡ ይገባል በሚለው ላይ ፖሊሲ አውጥቶ ወደ ግል ይዞታነት የሚዘዋወሩበትን ስትራቴጂ መንደፍ አስፈላጊ ሲሆን፤ ተግባራዊነቱም ሊመዘን ይገባል። በዚህ ወቅት ከመንግስት ጥቂት መቋቋሚያ ቢያገኙ በአጭር ጊዜ ውስጥ ራሳቸውን የሚችሉና ከፍተኛ ደጋፊ ያላቸው ክለቦች መኖራቸውንም ሰብሳቢው ይጠቁማሉ።በመሆኑም ይህ ሊታሰብበትና በብሄራዊ የስፖርት ምክር ቤቱ አቅጣጫ ሊሰጠው የሚገባ ነው ይላሉ። የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር፤ በ1990 ዓ.ም የወጣው የስፖርት ፖሊሲ ከስፖርት ማህበራትና ክለቦች አደረጃጀት ጋር በተያያዘ ቀስ በቀስ ከመንግስት ድጎማ መውጣት እንዳለባቸው የሚያመላክት መሆኑን ይጠቅሳሉ።ይህንን ተከትሎ የተከናወኑ ስራዎች ቢኖሩም አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ከጥቂቶቹ በቀር የተቀሩት በመንግስት የሚተዳደሩ ናቸው። ዓለም አቀፍ ደረጃቸው ሲፈተሽም፤ ከስያሜ፣ ከመዝሙር፣ ከአርማ፣… ጋር የተያያዙ ጉዳዮች መስተካከል ይገባቸዋል። ብሄራዊ ምክር ቤቱም ከዚህ ቀደም አቅጣጫ ቢያስቀምጥም ብዙም አልተሄደበትም።ክለቦቹም ከመንግስት ድጎማ በመውጣት ራሳቸውን እንዲችሉ ስልቶችን መቀየስ ይገባቸዋል።ለአብነት ያህልም የቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ ደጋፊዎቹን ወደ አክሲዮን የቀየረበት መንገድ ገቢውን ከማሳደግ ጎን ለጎን የታዳጊ ቡድኖችን የያዘበት ጅማሮ የሚበረታታ ነው፡፡ ፌዴሬሽኖች በገቢ ራሳቸውን እንዲችሉ ከማድረግ ባሻገር መንግስት በስሩ ያሉትን ከ30 በላይ ማህበራት ድጋፍ የማድረግ አቅሙ ውስን ነው።በመሆኑም ክለቦችና ስፖርት ማህበራት በራሳቸው ከሚያደርጉት ባሻገር ኮሚሽኑም ጥናት ላይ ተመስርቶ በቀጣይ የሚሄድበት መሆኑን ጠቁመዋል።  ", "passage_id": "36f13b967202258e302af2bc40e2da9c" }, { "passage": "የኢፌዲሪ ባህልና ወጣቶች ሚኒስቴር ሂሩት ካሳ (ዶ/ር)፣ የኢፌዲሪ ስፖርት ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር፣ አሸብር ወ/ጊዮርጊስ (ዶ/ር)፣ የኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝደንት፣ የዘጠኙ የክልልና የ2ቱ ከተማ መስተዳድር የስፖርት ኮሚሽን አመራሮች እና እግርኳስ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንቶች እንዲሁም የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝደንት አቶ ኢሳይያስ ጅራ እና ስድስት የሥራ አስፈፃሚ አባላት በውይይቱ ላይ ተካፍለዋል።በዶ/ር ሂሩት ሰብሳቢነት በተመራው በዚህ የውይይት መድረክ አቶ ኢሳይያስ ጂራ በ2011 በእግርኳስ የተፈጠሩ ያሉ ችግሮች ምን እንደሆኑ በዝርዝር በማስረዳት እየተፈጠሩ ያሉ አለመግባባቶችን ለመቀነስ እንደመፍትሄ በጊዜያዊነት በሁለት ምድብ የተከፈለ 24 ቡድኖች የሚካፈሉበት ውድድር ማዘጋጀት እንዳስፈለገ ለተሰብሳቢው ገልፀዋል።” ይህ ውሳኔ የተወሰነው ክለቦች ሳይማከሩበት እና ጥናትን መሠረት ያላደረገ መሆኑን በቅወቱም በሥራ አስፈፃሚ ስብሰባ ወቅት አፅኖት ሰጥተን ተናግረን ነበር። ሆኖም እኛ በማናቀው መልኩ የተወሰነ ውሳኔ ነው።” በማለት አንዳንድ የፌዴሬሽኑ የሥራ አስፈፃሚ አባላት መናገራቸውን ተከትሎ በፌዴሬሽኑ አመራሮች መካከል አለመግባባት ተፈጥሮ እንደነበረ ሰምተናል።የክልል እግርኳስ ፌዴሬሽን አመራሮች በተለይ የአማራና የትግራይ እግርኳስ ፌዴሬሽን አመራሮች በበኩላቸው 24 ቡድኖች ሆነው አማራና ትግራይ ክለቦች እንዳይገናኙ በማለት የተወሰነው ውሳኔን እንደማይቀበሉት፤ እግርኳስ የሠላም እና የማቀራረቢያ መድረክ መሆኑን ተናግረዋል። አዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን ጥናት በማስጠናት በውስጥ ውድድር ተካሂዶ በኃላም በኢትዮጵያ ሻምፒዮና ውድድሩ ይጠናቀቅ በማለት ያቀረበው ሀሳብ የሚያስመሰግን ሆኖ ሳለ ፌዴሬሽኑ እንደ መፍትሄ ከመቀበል ይልቅ የራሱን መንገድ መከተሉ ስህተት መሆኑን እና የክልል እግርኳስ ፌዴሬሽኖች ጋር ተቀራርቦ የመስራት ችግሮች እንዳለበት ተናግረዋል። የኦሊምፒክ ፕሬዝደንቱ በበኩላቸው 24 ቡድኖች መሳተፋቸውን እንደማይደግፉ እና ከኦሊምፒክ መርህ አንፃር ክልሎች እና ህዝቦች እንዳይገናኙ ማድረግ ተገቢ አለመሆኑን ገልፀዋል።የመድረኩ ሰብሳቢ በበኩላቸው “ፊፋ ላስቀመጠው ደንብ እና ህግ ተገዢ በመሆን፤ አባል ሀገራቱም ለተቀመጠው መመርያ ተገዢ እንዲሆኑ በማድረግ እያስተዳደረ በመገኘቱ ነው ተፈሪና ተቀባይነት ያለው ተቋም የሆነው። እናተም ላወጣችሁት ደንብ እና መመረያ ተገዢ በመሆን እግርኳሱን መምራት ይገባችኋል።” የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል።በመጨረሻም በፌዴሬሽኑ አመራሮች መካከል የተፈጠረውን የሀሳብ ልዩነት በውስጥ እንዲፈቱ፤ በ24 ቡድኖች ለሁለት የተከፈለው ውድድር ለጊዜው እንዲቆም እና ባለ ድርሻ አካላት ክለቦች በተገኙበት ውይይት በማድረግ ዘላቂ መፍትሄ እንዲቀርብ ተወስኗል። ስፖርት ኮሚሽንም ጉዳዩን በጥንቃቄ እንደሚከታተለው ሰምተናል።", "passage_id": "e964f1fbf044458a55ebdf2193bc3446" }, { "passage": "በ1990 ዓ.ም. በአገር አቀፍ ደረጃ የወጣው የስፖርት ፖሊሲ ሕዝቡ በሚኖርበት፣ በሚማርበትና በሚሰራበት አካባቢ ስፖርት እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚገባው ይደነግጋል። ህብረተሰቡ በሚኖርበት፣ በሚማርበትና በሚሠራበት አካባቢ በስፖርት እንቅስቃሴ ተሳታፊ የሚሆንበት መንገድ መመቻቸት እንዳለበት ያስቀምጣል። ከመንግሥት ተቋማት እስከ ታችኛው የኅብረተሰብ ክፍል በየደረጃው ኅብረተሰቡ ለሚሳተፍባቸው መድረኮች ትኩረት በማድረግ ልሂቃን (ኤሊቶች) የሚፈጠሩበት ዕድል እንዳለም ፖሊስው ያመለክታል። በሌላ በኩል አምራች ዜጋ ለመፍጠር፣ የኅብረተሰቡ ማኅበራዊ ግንኙነት የሚዳብርበት፣ ከዚያም ሲያልፍ ዜጎች ጤንነታቸውን ለመጠበቅና ለመዝናናት እንዲሁም አካላቸውን ለማጎልበትና አዕምሯዋቸውን ለማበልጸግ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ታምኖበታል። የስፖርት ፖሊሲውን መሰረት በማድረግ የሕብረተሰቡን ተሳትፎ በማስፋት ረገድ እየተሄደበት ያለው መንገድ አጥጋቢ አለመሆኑ ተደጋግሞ ይነሳል። በመንግስትም ሆነ በህብረተሰቡ በኩል እንደሚነሳው «ሕዝቡ በሚኖርበት፣ በሚማርበትና በሚሰራበት አካባቢ የስፖርት እንቅስቃሴ ማድረግ አለበት»በሚል በፖሊሲ ደረጃ ቢቀመጥም ወደ ተግባር ከመለወጥ አንጻር ከፍተኛ ክፍተት መኖሩ ይታመናል። በተለይ በመንግስትና በግል ተቋማት ህብረተሰቡ በሚሰራበት ቦታ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ እንዲያደርግ እድል በመፍጠር ረገድ የፍላጎትም ሆነ የግንዛቤ ክፍተቶች እንዳሉ በስፖርቱ አዋቂዎች በኩል ይነገራል። በተቋማት የስፖርቱን ማህበራዊም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳን በመረዳት ስፖርታዊ ክንውኖችን የማዘጋጀት ባህሉ በእጅጉ አናሳ መሆኑም አብሮ ይነሳል። መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት በኩል የስፖርቱን ዘርፈ ብዙ ፋይዳ በመረዳት የስፖርት ፌስቲቫል የማዘጋጀት ልምድ ባለቤት የሆኑ ተቋማት በጣት የሚቆጠሩ ናቸው። ከእነዚህ ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳል። የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫሉ ዘንድሮ ለ5ኛ ጊዜ ከመስከረም 26 ጀምሮ ለአስር ቀናት ያክል «የኋላውን እያደስን የወደፊቱን ለመገንባት እንተጋለን »በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ይገኛል። የኮርፖሬሽኑ የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫል በ2002 ዓ.ም እንደተጀመረ መረጃዎች ያመላከታሉ ። ኮርፖሬሽኑ በሚያከናውነው የስፖርት ፌስቲቫል፤ አገር አቀፍ የስፖርት ፖሊሲውን ተግባራዊ ከማድረግ ባሻገር በሰራተኞች መካከል መቀራረብን እንደሚፈጥር ታምኖበታል። የስፖርት ፌስቲቫሉ ጤናው የተጠበቀና አምራች ዜጋን በማፍራት ውጤታማ መሆን እንደሚቻል ማሳያ መሆኑም ተጠቁሟል። የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫል አስተባባሪ አብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጥንፉ ሙጬ፤ የስፖርት ፌስቲቫሉ በአገር አቀፍ ደረጃ የወጣውን የስፖርት ፖሊሲ መሰረት በማድረግ የተጀመረ መሆኑን ይናገራሉ። ህዝቡ በሚኖርበትና በሚሰራበት አካባቢ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በማድረግ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን ማጉላት እንደሚችል መሰረት ባደረገ መልኩ ተቋሙ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑንም ይገልጻሉ። እንደ አቶ ጥንፍ ገለጻ፣ ስፖርት በተለይ ደግሞ በሰራተኞች መካከል እርስ በእርስ እንዲተዋወቁ፣ ጤናው የተጠበቀና አምራች ዜጋን ለማፍራት እንዲቻል፣ የሰራተኞችን አንድነት ለማጠናከር ፋይዳው ግዙፍ መሆኑን ያብራራሉ። በመሆኑም ኮርፖሬሽኑ የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫሉን እነዚህን ውጤቶች መሰረት በማድረግ ትኩረት ሰጥቶ እንደጀመረ ይናገራሉ። «ፌስቲቫሉ በየሁለት ዓመቱ ቢደረግ የበለጠ ዝግጅት ተደርጎ በጠንካራና ባማረ ሁኔታ ማከናወን ይቻላል »በሚል አስተዳደሩ ወስኖ በየሁለት ዓመቱ ሊካሄድ እንደቻለም ያስታውሳሉ። የኮርፖሬሽኑ የቤተሰብ ስፖርት በዚህ መልኩ በመቋቋም ባለፉት አስር ዓመታትን መጓዝ ችሏል። በስፖርት ክንውኑ ተቋሙ ውጤታማ መሆን ችሏል? ስንል ጥያቄ ሰንዝረናል። አቶ ጥንፍ ባለፉት አስር ዓመታት በነበረው ስፖርታዊ ክንዋኔ ተቋሙ ውጤታማ መሆኑን ይገልጻሉ። በመጀመሪያ ደረጃ አመራሩና ሰራተኛው መልካም የሆነ ግንኙነት እንዲፈጥሩ አድርጓል። እያደረገም ይገኛል። በአካልም፣ በአዕምሮም የበለፀገ ሰራተኛና አመራር እንዲኖር አስችሏል። ጤናማ ሰራተኛ በመፍጠር ረገድ ውጤት ማምጣት ተችሏል። መታወቅ ያለበት ያለ ጤናማ ሰራተኛ የኮንስትራክሽን ስራ የሚታሰብ እንዳልሆነም ያብራራሉ። የስፖርት ፌስቲቫሉ ሠራተኛውም ሆነ አመራሩን የበለጠ የሚያቀራርብ፣ ሠራተኛው ትርፍ ጊዜውን አዕምሮውንና አካላዊ ብቃቱን የሚያዳብርበት፣ ለተቋሙ ያለውን ወገናዊነት የሚያሳይበት፣ በሌሎች ፕሮጀክቶች ከሚገኙ ሠራተኞች ጋር ለመቀራረብና ለመተዋወቅ መንገድ እየከፈተ እንደሚገኝ ይገልጻሉ። እንደ አቶ ጥንፍ ማብራሪያ፤ የዘንድሮ መድረክ ከእስከ ዛሬው ለየት የሚያደርገው የተሳታፊነቱን ኮታ ለአመራሩ አንድ ሶስተኛውን በመስጠት ዋና ሥራ አስፈጻሚውን ሳይቀር ተሳታፊ ማድረጉ ነው። ስፖርት ፌስቲቫሉ ለአመራሩና ለሰራተኛው እኩል እድል ከመስጠት ባሻገር፤ በሁለቱ አካላት መካከል መቀራረብ እንዲፈጠርና የበለጠ ቀረቤታን መፍጠር እንዲያስችል ነው። ይህን በተግባርም ለመመልከት ተችሏል። የዘንድሮው ውድድር ሴቶችን የበለጠ ተሳታፊ እንዲሆኑ አድርጓል። በመድረኩ ያለፉት ዓመታት ጉዞ ሴቶች ቡድን አልነበራቸውም፤ ዘንድሮ ሁለት ቡድኖች ተቋቁመው በመረብ ኳስና በጠረጴዛ ቴኒስ ስፖርቶች ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ተደርጓል። «የዘንድሮው ፌስቲቫል ልዩ ገጽታው የለውጥ አስተሳሰቦችን ለማስረጽ ጥረት መደረጉ ነው። በውድድሩ ያሉትን ቡድኖች ስያሜን በዚህ ሁኔታ እንዲቃኙ የተደረገ ሲሆን ስያሜዎቹም አሸናፊ፣ ብቁ፣ ታዋቂ፣ ድንቅ፣ ባለራዕይ እና ተስፋ በሚል እንዲሰየሙ ተደርጓል›› ያሉት አስተባባሪው ከዚህ በተጨማሪም ቀደም ሲል ዘርፎች በቡድን ተደራጅተው እርስ በዕርስ የሚያደርጉት ውድድር እንደነበር ተናግረዋል። አደረጃጀቱ እንደ ኮርፖሬሽን ውህደት ባለማምጣቱ አዲስ አደረጃጀት በመፍጠር ወድድሩ እየተካሄደ ሲሆን፤ በመድረኩ የበለጠ መቀራረብና ተቋማዊ ስሜት መፍጠር እንደተቻለ በውድድሩ የአምስትና ስድስት ቀናት ቆይታ ወቅት ለመታዘብ ተችሏል። የስፖርት ፌስቲቫሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ ተቋማዊ ፋይዳውን እያሳደገ መምጣቱን የ5ኛው የቤተሰብ ስፖርት ውድድር እያሳየም ይገኛል። አቶ ጥንፍ ኮርፖሬሽኑ ግዙፍና በርካታ ፕሮጀክቶች ያቀፈ እንደመሆኑ በስፖርት ፌስቲቫሉ ሁሉም ፕሮጀክቶች ተሳታፊ እንዲሆኑ በመስራት የስፖርቱን ግዙፍ ፋይዳ በተቋሙ ምሉእ እንዲሆን ለማድረግ በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም አስቀምጠዋል። በ5ኛው የኮርፖሬሽኑ የቤተሰብ ስፖርት ሲሳተፍ ያገኘናቸው በኮርፖሬሽኑ የፋሲሊቲ ሰራተኛ የሆኑት አቶ ዜናው ደነቀው በበኩላቸው፤ የስፖርት ክንውኑን እንደ ኮርፖሬሽኑ ሁሉ ሌሎች ተቋማት ተግባራዊ ማድረግ ቢችሉ ያለውን ፋይዳ ይናገራሉ። «በእኛ ተቋም ያለውን ተሞክሮ በሌሎች የመንግስትና የግል መስሪያ ቤቶች ተግባራዊ ማድረግ ቢቻል፤ በአገር አቀፍ ደረጃ ተጠቃሚ መሆን ይቻላል። ከስፖርቱ የሚገኘውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ማግኘት ይቻላል። በተጨማሪም ኢሊት ስፖርተኞች የሚፈሩበትን አጋጣሚ በማስፋት ረገድ የራሱ የሆነ ድርሻ ይኖረዋል። የአገራችንን ስፖርት በማሳደግ ረገድም የመንግስት ተቋማት ድርሻቸውን እንዲወጡ አጋጣሚውን መፍጠር ይቻላል» ሲል ያብራራል። በኮርፖሬሽኑ የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫል ላይ ከአሰልጣኝነት እስከ ዳኝነት የተሻገረ ተሳትፎን ከመጀመሪያው ጀምሮ ሲያደርጉ እንደነበረ የገለፁልን የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ሰራተኛ የሆኑት አቶ አለማየሁ ገብሬ፤ የኮርፖሬሽኑ ተሞክሮን ሌሎች ተቋማት መውሰድ ቢችሉ ያለውን ነጥብ በማሳት ተመሳሳይ ሃሳብ ይጋራሉ። የቤተሰብ ስፖርቱን ከመጠንሰስ እና ቀጣይነት እንዲኖረው ከማድረግ አካያ በተቋሙ የነበሩና ያሉ አመራሮች ትልቅ ድርሻ እንደነበራቸውም ይናገራሉ። የኮርፖሬሽኑ አመራሮች የስፖርት ፌስቲቫሉ ሳይቋረጥ እንዲቀጥል ከማደርግ አኳያ ያሳዩት ቁርጠኝነት በተለይ ደግሞ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ዮናስ አያሌው ትልቅ ስራን መስራታቸውን ያስረዳሉ። አቶ አለማየሁ ዋና ስራ አስፈፃሚው ስፖርታዊ ክንውኑ ቀጣይነት ኖሮት በጠንካራ መስመር እንዲጓዝ ከመስራት ባሻገር፤ በውድድሩ ተጫዋች በመሆን የስፖርቱ ተሳታፊ መሆናቸው የሚያስመሰግናቸው መሆኑን ይገለጻሉ። ስፖርቱ ትኩረት እንዲያገኝ ከማድረግ አኳያም አመራሩ ያሳየው ቁርጠኝነት በሌሎች ተቋማት እንደ አርዓያ ሊወስዱት ይገባል ባይናቸው። ኮርፖሬሽኑም በየሁለት ዓመቱ ይህ የስፖርት ባህል ተጠናክሮ እንዲቀጥል ማድረግ እንደሚገባው ያስቀምጣሉ። በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የቤተሰብ ስፖርት ፌስቲቫል ተሞክሮ በሌሎች መንግስታዊና መንግስታዊ ባልሆኑ ተቋማት መውሰድ ቢቻል ዘርፈ ብዙ ውጤቶች እንደ አገር ማትረፍ እንደሚቻል መመስከር ይቻላል። ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በህብረተሰቡ ዘንድ ትኩረት እንዲሰጠው ፖሊሲ ከመቅረጽ ባሻገር ተግባራዊ እንዲሆን እንደ ኮርፖሬሽኑ ሌሎች ተቋማት መስራት አለባቸው።አዲስ ዘመን  ረቡዕ ጥቅምት 5/2012ዳንኤል ዘነበ ", "passage_id": "6d84cfd7c86d1084995b22e46a54eca8" } ]
a9b9e975b6eb0f146a7545ffe248be6a
1d1a1ad6453ac1b9d55f82607753f4f5
አይጦችን ከአገልግሎት ክፍያ ለማምለጫ
 በተለያዩ ሀገራት የሚገኙ ሆቴሎች እንደ የደረጃቸው ለደምበኞቻቸው አገልግሎቶችን ያቀርባሉ።ለአገልግሎቶቻቸውም ደምበኞቻቸውን ያስከፍላሉ።ደምበኞችም በሆቴሎቹ ቆይታቸው ከያዙት አልጋ ጀምሮ እስከተጠቀሟቸው ምግቦችና መጠጦች ድረስ ክፍያ መፈፀም ይጠበቅባቸዋል። ይሁን እንጂ አንዳንዴ ደንበኞች በሆቴሎች ውስጥ ያሻቸውን ተጠቅመው ሲያበቁ ሂሳብ ሲጠየቁ ድንጋጤ ውስጥ የሚገቡ፤ ለመክፈልም የሚያንገራግሩ አይጠፉም።ለተጠቀሙበት አልጋ፣ ምግብ፣ መጠጥና ሌላም የአገልግሎት ክፍያ ሳይፈፅሙ እንዲሁ በነፃ ከሆቴሉ ውልቅ ብለው ለመውጣት የሚዳዱም አልፎ አልፎ አይታጡም።ኦዲቲ ሴንትራል ከሰሞኑ ይዞት የወጣው መረጃም የሆቴል አገልግሎቶችን በሚገባ ተጠቅሞ ክፍያ ሳይፈጽም ስለተገኘ አንድ ግለሰብ አስነብቧል። የሰላሳ ሰባት አመቱ አሜሪካዊው የኡታ ግዛት ጎልማሳ ሪያን ቀልቡ ባረፈባቸው ሆቴሎች ሁሉ በመግባት ከአልጋ ጀምሮ የሚፈልገውን አገልግሎት በሙሉ ተጠቅሞ ምንም አይነት ክፍያ ሳይከፍል በተደጋጋሚ ውልቅ ብሎ ይወጣል።ሂሳብ ሳይከፍል የሚወጣው ግን ተደብቆ ወይም በስፖንሰር ተከፍሎለት አይደለም፤ በአይጦች እንጂ።እዚህ ላይ የእርሱ ከሆቴሎች በነፃ ተስተናግዶ መውጣት ከአይጦች ጋር ምን አያያዘው ሊሉ ይችላሉ።እውነታው ግን አይጦቹ ሪያንን ከከባድ ወጪ ያዳኑት መሆኑ ነው። ነገሩ ወዲህ ነው፤ ሪያን በቅድሚያ ወደ ሆቴሎች ሰተት ብሎ ይገባል። ከዛም አልጋ ይይዛል።ጥቂት ቆይቶም ከውጭ ወደሆቴሉ በሳጥን ደብቆ የሚያስገባቸውን አይጦች በያዘው ክፍል ውስጥ ይለቃቸዋል። በመቀጠልም ከሆቴሉ ስታፍ ለአንዱ ስልክ በመደወል በሆቴሉ የንፅህና አያያዝ ዙሪያ ቅሬታውን ያቀርባል፤ ይጮሃል። ታዲያ በዚህ ጊዜ የሆቴሉ ስራ አስኪያጆች የሆቴላቸው ስም እንዳይጠፋ ‹‹የአልጋ ሂሳብ አናስከፍልህም፤ የምግብና የመጠጥ ወጪህንም እኛ እንሸፍንልሃለን›› ይሉታል።እንዲህ አይነቱን የማታለያ ድርጊት በተደጋጋሚ በመፈፀምም ሪያን በተለያዩ ሆቴሎች በሚገኙ አልጋዎች ላይ በነፃ ተኝቷል፤ ሌሎች የምግብና የመጠጥ አገልግሎቶችን እንዳሻው ተጠቅሟል። መቼም እንዲህ አይነቱ የማታለያ ተግባር ሁሌም አያዋ ጣምና በዚህ ድርጊት በሶስት ሆቴሎች ላይ የጠረጠረው ፖሊስ ሪያንን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያደረገበት ይገኛል። ሪያን እንዴት በፖሊስ ሊያዝ እንደቻለ በግልፅ የተነገረ ባይኖርም በሁለት ሆቴሎች የመኝታ ክፍሎች ወስጥ አይጦቹን ስለመልቀቁ ግን ራሱ አምኗል።ሌብነትና ማጭበርበርን ጨምሮ አምስት ክሶች እንደሚጠብቁትም ተነግሯል። አዲስ ዘመን የካቲት 10/2012 አስናቀ ፀጋዬ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=27458
[ { "passage": "ባለፈው ወር መጨረሻ በኒው ኦርሊንስ ፍሬንች ኳርተር አካባቢ በርካታ ጎብኚዎች ይታዩ ነበር። ልክ ኮሮናቫይረስ አዋጅ ክተት ሲያስብል እነዚያ የፍሬንች ኳርተር ዝነኛ ጎዳናዎች ጭርታ ሞላቸው።\n\nቡና ቤቶችም ሆኑ ምግብ ቤቶች ተዘጉ። አይጦች የሊዊዚያና ከተማ አካባቢዎችን ለመውረር ብዙ ጊዜ አልወሰደባቸውም።\n\nየአይጦችና ሌሎች ትንንሽ እንሰሳት አጥኚ የሆነው ሮበርት ካሪጋን ይህ አስገራሚ ነገር አይደለም።\n\n\"የአይጥ መንጋዎች በአንድ ከተማ ሲኖሩና የዕለት ጉርሳቸውን እዚያም እዚም በቱሪስቶችና በነዋሪዎች ከሚጣል ትራፊ የሚለቃቅሙ ሆነው ቆይተው ድንገት ይህንን ሲያጡ ግር ብለው ወደ ጎዳና መውጣታቸው የሚጠበቅ ነው። ይህ በዲሲም፣ በኒው ዮርክም ሊሆን የሚችል ነው።\"\n\nበኒው ኦርሊንስ የተባይ መድኃኒት አዋቂ ክላውዲያ ሬግል ለጋዜጠኞች እንደተናገረችው \"አይጦች ረሀብ ጊዜ የሚሰጣቸው አይደሉም\" ትላለች። \n\nሰዎች በመላው ዓለም በኮሮናቫይረስ ምክንያት የአኗኗር ዘይቤያቸውን ለውጠዋል። ይህም ነገር አይጦችን ግራ አጋብቷቸዋል። የለመዱትን በፈለጉት ቦታ እያገኙ አይደለም።\n\nዶ/ር ኮሪጋን በሎወር ማንሃታን ቢሮ አላቸው። ከጓደኞቼ የስልክ ጥሪዎች ይደርሱኛል፤ አይጦች ባልተለመደ ቦታና ወቅት በየጎዳናው ማየታቸው አስገርሟቸዋል ይላል።\n\nበዩናይትድ ኪንግደም የጸረ ተባይ ባለሙያዎች ብሔራዊ ማኅበር በዚህ ወቅት አንዳንድ ያልተለመዱ ክስተቶች ሊኖሩ እንደሚችል አስጠንቅቆ ነበር።\n\nየትምህርት ቤቶች፣ ምግብ ቤቶችና የሆቴቶች መዘጋት እንዲሁም የጎብኚዎች መዳረሻዎች ክፍት አለመሆን እንዲህ ያሉ ያልታሰቡ ነገሮችን ሊያመጣ እንደሚችል ቀደም ብሎ አስጠንቀቆ ነበር ማኅበሩ።\n\nአይጦቹ ምግብ ቢያገኙ እንኳ ወደ ባዶ ሕንጻዎች መሽሎክሎካቸው አይቀርም ነበር፤ ምክንያቱም አብዛኛዎቹ ሕንጻዎች ወና ሆነዋልና ነው።\n\nአሁን ግን የለመዱትን ትርፍራፊ ምግብ በለመዱት ቦታ አለማግኘታቸው አይጦቹ የሚላስ የሚቀመስ ፍለጋ ወዲያ ወዲህ እንዲሉ አድርጓቸዋል።\n\nዶ/ር ኮረጎን ለቢቢሲ ሲናገሩ \"አይጦች ከተራቡ ረዥም ርቀት ሊጓዙ ይችላሉ፤ በጭራሽ ሄደው የማያውቁበት ቦታ ሄደው ሊላመዱ ይችላሉ\" ብለዋል።\n\nበጭራሽ እጅ የማይሰጡና የምግብ ሽታን ከብዙ ርቀት አነፍንፈው ይደርሱበታል። በዚያ ላይ ጠንካራ ጥርስ ስላላቸው ከምግብ የሚያግዳቸውን ማናቸውንም ነገር ከመቦርቦሩ አይመለሱም።\n\nዶ/ር ኮረጎን \"አይጦችን ዓለም አቀፋዊ ያደረጋቸው ይኸው ባህሪያቸው እንደሆነ ይናገራል። የትም የምናገኛቸው ራሳቸውን በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ማኖር የሚችሉ እንሰሶች ስለሆኑ ነው\" ይላል።\n\nነገር ግን አይጦች በብዛት ወደ ደጅ ወጡ ማለት ከተማው እየወረሩት ነው ማለት አይደለም።\n\nእንዲያውም ዶ/ር ኮሪጎን እንደሚለው ይህ ጊዜ አይጦቹን ለመቆጣጠር እጅግ የተመቸው ወቅት ነው። የኒው ኦርሊንስ አስተዳዳሪዎችም አይጦቹን ለመቆጣጠር ተጨማሪ እርምጃ ለመውሰድ እያሰቡ ነው።\n\nበዚህ ጊዜ ሆዳቸው ባዶ የሆኑ አይጦች ምግብ ከተሸሸገበት ከየትኛውም ቦታ ለመንጠቅ ዝግጁ ናቸው።\n\nዶ/ር ኮሪጎን የሚመክረው ንጽህናን መጠበቅን ነው። ወሳኙ የአይጥ መርዝ ማለት አካባቢን ንጹህ ማድረግ ነው ይላል። \n\nምግብ ያጡ አይጦች አንዳቸው በአንዳቸው ላይ የዘምታሉ። የእርስበርስ እልቂት ይከተላል። በዚህ ሁኔታ ቁጥራቸው እየቀነሰ ይመጣል።\n\nአይጦችን ለምንድነው የምናገላቸው?\n\nየተራቡ አይጦች አደጋ ሊያደርሱ ይችላሉ። አደጋው ደግሞ በሽታን ማስፋፋት ሊሆን ይችላል።\n\nአይጦችን ካልተቆጣጠራችኋቸው ወደ ቤት ዘልቀው መኝታ ቤት ሰተት ብለው ልጆች ላይ ጭምር በሽታን ሊያስተላልፉ ይችላሉ።\n\nአይጦች በዋናነት 55 ለሚሆኑ በሽታዎች ዋንኛ አስተላላፊዎች እንደሆኑ ተረጋግጧል።\n\nለጊዜው ግን አይጦች ኮሮናቫይረስን ከሰው ወደ ሰው... ", "passage_id": "c9881720792dd38e7bdd9cc7019a55e4" }, { "passage": "እንደተለመደው በሥራ መውጫ ሰዓት ሰርቪስ ለመያዝ ተሰልፈናል። የአጋጣሚ ጉዳይ ሆኖ ወደእኛ ሰፈር የሚሄደው መኪና ሁሌም በተሳፋሪዎች ይጨናነቃል። ብዙዎች የሾፌሩ ፍጥነትና የመንገድ ቆረጣ ስለሚመቻቸው ምርጫቸውን ለይተዋል። የባስ ካፒቴኑ ፈጣንና ቀልጣፋ ነው። መንገድ መርጦ መጓዝ ያውቅበታል።ከረጅሙ ሰልፍ መሀል ወንበር ለማግኘት የታደልነው ጎን ለጎን ተቀምጠን ጨዋታ ይዘናል። ተራው ያልደረሳቸው ደግሞ ከውጭ ወደውስጥ እያንጋጠጡ ነው። እንደእውነቱ ከሆነ ራቅ ያለ መንገድ ቆሞ መሄድ ከባድ ነው። እንደታክሲ ሦስት ሆኖ መቀመጥ ደግሞ አይሞከርም። እናም ከደጅ ያሉት ተንጠራርተው ቢያንጋጥጡ አይፈረድም።መቼም የመንገድ ላይ ወግ አይነቱ ብዙ ነው። አንዳንዴ ስለቤት ጣጣ ይወራል። አንዳንዴ ደግሞ ወቅታዊና አገራዊ ጉዳይ ሰፊ ሽፋን ያገኛል። ብዙ ጊዜ ግን አስራሁለት ሰዓት ላይ የሚደመጠውን ዜና መነሻ አድርጎ የሚከተለው አስተያየት ይበረክታል። ጥግ ይዘው የሚያንጎላጁት መንገደኞችም ከዕንቅልፋቸው በባነኑ ጊዜ የሚጨዋወቱት አያጡም።እሰይ! አሁን መንገዱን ገፋ አድርገነዋል። ፈጣኑ ካፒቴን እንደተለመደው በአጭር ጊዜ ረጅሙን ጎዳና አጋምሶታል። ሜክሲኮ አደባባይን ከመሻገራችን መጨናነቅ መጀመሩ ግን እንዳያስመሸን እየሰጋን ነው። ከኋላችን ደርሶ «እሪ» የሚለው አምቡላንስ ማለፊያ በማጣቱ ጨኸቱ ቀጥሏል። አንዳንድ መኪኖች ችግሩን ተረድተው ሊያሳልፉት እየሞከሩ ነው። ይህ መሆኑ ብቻ ግን እምብዛም መፍትሄ አልሆነም።\nየአምቡላንሱን ጨኸት ተከትሎ አዲስ ጨዋታ ተነሳ። አንደኛው የሚናገረው ከሌሎች በተለየ ነው። እርሱ አካባቢውን ስላወከው ድምጽ እምብዛም የተጨነቀ አይመስልም። መኪናው የታመመ ሰው ይዟል የሚለው እውነታም አልተዋጠለትም። እንደውም በስፍራው እንደተገኘ ሆኖ አሳማኝ የሚመስሉ ማሳያዎችን መምዘዝ ይዟል። የእርሱን ሀሳብ ተከትሎም ብዙዎች የራሳቸውን ግምት ማከል ጀምረዋል። በየወንበሩ ጨዋታው ደርቷል። አስተያየትና የግምት ሀሳብም እንዲሁ፤የእኔን ጆሮ የሳበው ግን ይህ አይነቱ ክርክር አልነበረም። ከጎኔ የተቀመጠችው ወይዘሮ በስልኳ በያዘችው ፎቶግራፍና ተያያዥ ታሪክ ልቤ ተማርኳል። ጉዳዩን በጥልቀት ስሰማው ደግሞ አእምሮዬ ርቆ ተጓዘ። በዚህ መሀል የብዘዎችን የተሳሳተ ግምት አሰብኩ። ራሴንም ገመገምኩ። እውነት ግን ስንቶቻችን በተሳሳተ እሳቤ እንመራለን? ስንቶቻችንስ ይህን በጎ ያልሆነ አመለካከት እንደያዝን እንገኛለን?ነገሩ እንዲህ ነው። አንድ ማለዳ ወደቤ ተክርስቲያን የሄዱት አባወራ ጸሎታቸውን አድርሰው ዞር ከማለታቸው ከአንድ ጎስቋላ አዛውንት ጋር ዓይን ለዓይን ይጋጫሉ። ሰውዬው ጥሩ ቁመና ቢኖራቸውም ኑሮ እንደጎዳቸው ያስታውቃል። ከላይ የደረቡት ልብስ አርጅቷል። ጫማቸው አልቋል። ችግር ያንገላታው መልካቸው ድካም ተጭኖታል።ከእርሳቸው አለፍ ብሎ ከተቀመጡት ባልንጀራቸው ጋር በልመና የሚያገኙትን ቁራሽ ይካፈላሉ። ለነፍስ ብሎ ሳንቲም የሚጥል ሲገኝም የተሰጣቸውን ተቀብለው ለሌላ ምጽዋዕት እጃቸውን ይዘረጋሉ። ልመና ለአዛውንቶቹ መተዳደሪያ ከሆነ ዓመታት ተቆጥረዋል።\nከሁለቱ ግን የአንደኛው ታሪክ ይለያል። ባገራቸው ቤት ንብረት አላጡም። ጥማድ በሬና የሚታረስ መሬትም አላቸው። እንደዋዛ አዲስ አበባን የለመደው እግራቸው ግን በቀላሉ አልመለሳቸውም። የልጆቻቸው ከተማ መዝለቅ ምክንያት ሆኗቸው ዋል አደር ማለት ለመዱ። ልጆችና እርሳቸው በአንድ ቤት አይኖሩም። ገሚሶቹ በቀን ሥራ ራሳቸውን ይደጉማሉ። የተቀሩትም በተመሳሳይ ሙያ ተሰማርተው ገንዘብ ያገኛሉ።አሁን አባትና ልጆች በአንድ ቤት ስለማይኖሩ አዋዋላቸውም ለየቅል ሆኗል። አባት በልመና ከሚያገኙት ገንዘብ የራሳቸውን ቤት ኪራይ ይከፍላሉ። ባገኟት ቁራሽ ሆዳቸውን ይችላሉ። በልመና ውሎ ህይወታቸውን ይመራሉ። ከማለዳ እስከምሽት በሚዘልቁበት አጸድ ብርድና ፀሐይ ብርቃቸው ሆኖ አያውቅም። ሁሉንም እንደአመጣጡ ተቀብለው የሰው ፊት ማየትን ከተለማመዱት ቆይተዋል።በቅርበት ሆነው ሁኔታቸውን ሲያስተውሉ የቆዩት አባወራ በአዛውንቱ ጉስቁልና ልባቸው በኀዘን ተነክቷል። ይህ ስሜት ብቻ ግን የበቃቸው አይመስልም። እርሳቸውን እያሰቡ ከቤት የተቀመጡትን ልብሶች ያስታውሳሉ። ካስታወሷቸው መሀልም ለእርሳቸው የሚበጀውን ይለያሉ። ይህን ሀሳባቸውንም ለአዛውንቱ ሲነግሯቸው ምስኪኑ ሰውየ ከልብ ተደሰቱ። እንዲህ አይነት ቅን አሳቢ ስላገኙም ፈጣሪያቸውን አመሰገኑ።አዛውንቱና አባወራው ወደቤት ከመሄዳቸው በፊት ጉዳዩን የሰሙት ባልንጀራቸው ጥያቄ አነሱ። እርሳቸውም እንደጓደኛቸው ቢለብሱ እንደሚወዱ ተናገሩ። አባወራው በጥያቄአቸው አልተከፉም። ሁለቱንም ሊያለብሷቸው ቃል ገብተው እንዲከተሏ ቸው አደረጉ።\nእኔና ወይዘሮዋ ጨዋታችንን ቀጥለናል። በግሌ የሰዎቹ ታሪክና የአባወራው ቅንነት እያስገረመኝ ነው። እግረመንገዴን በርካቶችን አሰብኳቸው። ቤት ንበረታቸውን ትተው፤ የሞቀ ትዳራቸውን ፈትተው ለልመና የተዳረጉ ቁጥር አልባ ወገኖች ትውስ አሉኝ ። ቤት ይቁጠራቸው እንጂ ብዙዎቹ ተመሳሳይ ህይወት ይጋራሉ። እያላቸው የሌላቸው ሳያጡ ያጡ ጎስቋሎች ጥቂት አይደሉም።ሦስቱ ሰዎች ጀሞ አንድ ከሚገኙ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በአንደኛው ተገኝተዋል። አባወራው ከፊት ቀድመው ሁለቱ እየተከተሉ ነው። በቁምሳጥኑ ከተሰደሩት ሙሉ ልብሶች መሀል ያሰቧቸውን አውርደው ለአዛውንቶቹ መስጠት የጀመሩት ሰው ምስጋና እየደረሳቸው ነው። እነርሱም የተራበን ያበላ፣ የታረዘን ያለበሰ በሚለው ቃል መሰረት ቅን ላደረጉት አባወራ ምርቃት እያወረዱ ነው።አሁን ሁሉም ተጠናቅቆ ተሰነባብተዋል። ይህ ከመሆኑ በፊት ግን ዳግም ለመገናኘት ቀነ ቀጠሮ ወስደዋል። ከቀናት በኋላ አባወራው በቤታቸው የሚያደርጉትን ጠበል ጠዲቅ ምክንያት አድርገው እንዲመጡ ጠርተዋቸዋል። ሁለቱም ተጋባዞች ዕለቱን አልዘነጉም። እንዲህ አይነቱ ጥሪ ለእነሱ ከስንት አንድ ነው። አክብረው የሚጠሯቸውና እንደሌሎች በእኩል የሚጋብዟችውም ጥቂቶች ናቸው።ቀናት ተቆጥረዋል። በአባወራው መኖሪያ ለጠበል ጸዲቁ የሚሆነው ዝግጅት ተጀምሯል። የሚጠሩ ሰዎች ተለይተው የጎደለው ሁሉ ተሟልቷል። ሁሌም ዕለቱን አስበው የሚዘክሩት ባልና ሚስት በጥሪው የሚገኙ እንግዶች እንዳይረሱ ያስባሉ።አሁን ቀኑ ደርሷል። እንደተለመደው መላው ቤተሰብ በመስተንግዶው ተዋክቧል። እንግዶች ይገባሉ፣ ይወጣሉ። አባወራውና ወይዘሮዋ ቆመው ያስተናግዳሉ፤ ሰዎችን ይቀበላሉ፣ ይሸኛሉ። ከተጠሩት መሀል ቀኑን ያልዘነጉት አዛውንት በሰዓቱ ተገኝተዋል። እርሳቸው ከሌሎች ቀደም ብለው ቢገኙም እንደአመጣጣቸው ፈጥነው መውጣት አልፈለጉም። ወጪ ገቢውን እያስተዋሉ በዝምታ ተቀምጠዋል።ቀኑ ተጋምሶ ምሽቱ እንደተቃረበ የተጠሩት እንግዶች ቁጥርም ጋብ ማለት ጀመረ። ጥቂት ቆይቶም ቤቱ ጭር አለ። ይህኔ አዛውንቱ እንግዳ ከመቀመጫቸው ተነሱ። ተነስተውም መላው ቤተሰብ ወደ እርሳቸው እንዲመጣ ጠየቁ። ይህን የሰሙ ሁሉ ቃላቸውን አክብረው በአንድ ተሰባሰቡ። ቀኑ እየመሸ በመሆኑ አባወራውና ባለቤታቸው ማሰብ ጀምረዋል። የእርሳቸው ቤት ከአካባቢው የራቀ በመሆኑ እያስጨነቃቸው ነው ። እርሳቸው ግን ይህ ሁሉ ስሜት ምናቸውም አልነበረም።ንግግራቸውን በተለየ ምስጋና የጀመሩት እንግዳ እንባ እየተናነቃቸው እጃቸውን ወደጉያቸው ሰደዱ። ወዲያው ዳጎስ ያለ እስር በጣቶቻቸው መሀል ታየ። አዛውንቱ ያወጡትን ከማስረከባቸው በፊት ስለሆነው ሁሉ ተናገሩ። የዛን ዕለት አባራው ስለእርሳቸው አዝነው ሙሉውን ልብስ በሰጧቸው ጊዜ ቤታቸው ገብተው ልብሱን ሲለኩት በኮቱ የውስጠኛው ኪስ የታሰረ የብር ኖት ያገኛሉ።ብሩ ከለመዱት መጠን የበዛ በመሆኑ በድንጋጤ ክው ብለው ይቆያሉ። አዎን! አባወራው በተለገሳቸው ሙሉ ልብስ ውስጥ አስር ሺ ብር እንደታሰረ ተቀምጧል። ይህን ሲመለከቱ አዕምሯቸው ክፋት አላሰበም። ቅን አስቦ መልካም ላደረገ ማንነት ውለታው በበጎነት መመለስ እንደሚኖርበት ወስነው ብሩን እንደነበረ አስቀመጡት። ይህን እውነት ያጫወተችኝ ወይዘሮ ይህ ታሪክ በባለቤቷና በመኖሪያ ቤቷ ስለመፈጸሙ ሳውቅ ግርምታዬ ላቀ ።ሰውዬው ያስረከቡትን የአስር ሺ ብር ጥቅል ባለቤቷ ቆጥረው ሲረከቡም በፎቶግራፍ የቀረውን ምስል ተመልክቼ አረጋገጥኩ። ወዳጆቼ! እውነት እንነጋገር ከተባለ ምን ያህሎቻችን እንሆን ይህን መሰሉን ታሪክ የምንጋራው? ማንኛችንስ ነን ሰውን በልቡ ሳይሆን በልብሱ ብቻ የማንመዝነው? እኚህ ገንዘብና እንጀራ ናፋቂ አዛውንት ግን ይህን እውነት ፈጽመዋል። ሰዎችን በልብስ ብቻ ሳይሆን በንጹህ ልቦና ብቻ እንድንመዝንም አስተምረውናል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 24/2011መልካምስራ አፈወርቅ", "passage_id": "53d642158a8f272c4658dbff4dcacaaa" }, { "passage": "በመዲናችን\nአዲስ አበባ ተመሳስሎ ያልተሰራ፣ከጎኑ ማታለያ ያልተቀመጠለት፣አለያም ባዕድ ነገር ያልተቀየጠበት አገልግሎት ማግኘት ላሳር ነው። አሁን አሁንማ ቆመው የሚሄዱት ሰዎችም ተመሳስለው የተሰሩ እየመሰሉኝ መጥተዋል። የሚሸመቱ እቃዎችን ተዋቸው። ከአይን እይታ የዘለሉ ማታለያዎችን ጭምር መጠቀም ተክነውበታል። ምነው በዚህ ደረጃ ለማታለያነት የሚያውሉትን (የሚያስቡበትን) አዕምሮ ህብረተሰቡን ቢጠቅሙበት፣ ቢመረቁበት እና የሚለወጡበት ተግባር ቢፈጽሙ ያሰኛል። የሚገርመው በዘላቂነት የሚጠቅም ነገርን መኮረጅ አለመቻላቸው ነው። እንደ ቴክኖሎጂ አይነት እውቀትን ምነው በኩረጃም ማስፋት በተቻለ። ተጠቅመውበት እልፍ ሲልም ተሸልመውበት መንገስ ይችሉ ነበር። ተፈላጊነታቸውም በገበያ ላይ ይጨምራል፡ ምክንያቱም የሀገሪቱ የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ በአዲስ መልክ መፍጠር ያልተቻሉ ቴክኖሎጂዎችን ለራስ በሚሆን (በሚጠቅም) መንገድ መኮረጅን ይመክራል። ለካ በነካ እጃቸው ነው ሟች ነፍሳቸውን ይማረውና ‹‹መስረቅ ካልተያዙ ሥራ ነው፣ ከተያዙ ግን ወንጀል ነው›› አሉ ተብለው የሚታሙት። ልብ በሉ ሃሜት ነው። አሁን ላይ በእነሱ የማታለያ ማሽኖች ተፈብርኮ ከእኛ የማየት አቅም በላይ ተሸፍኖ ያልቀረበ ቁስ ያለ አይመስለኝም። ህብረተሰባችን በጫንቃው ተሸክሟቸው የሚኖሩ እልፍ አታላዮች ከጓዳ እስከ አደባባይ ሞልተዋል። ምን ህብረተሰቡ ብቻ መንግስት ጭምር እንጂ ተሸካሚው። ከእለት ጉርስ ፈላጊው እስከ አገር ኢኮኖሚ ሾፋሪው ቱጃር ድረስ ማታለል፣ መዋሸት፣ ማጭበርበር በሙያነት ተመርቀውበታል። ከታች እስከ ላይ ያደግንበትን ወግ፣ ባህልና እምነታችንን አስክዶ ትውልዱን የወረረ አደገኛ ተዛማች በሽታ ሆኗል። የሰው ልጅ በዘመን ዥረት መሃል ሲፈስ በአዎንታም ሆነ በአሉታ ለውጦች ማሳየት ተፈጥሯዊ ግዴታ ነው። የሚጠቅሙትን\nበእጁ ጨብጦ የማይጠቅሙትን ከመዳፉ እያራገፈ ሰዋዊ ባህሪን ተላብሶ መገስገስ የእሱ ፋንታ ነው። አሁን ላይ አውሬነት ባህሪያችን ይመራን ይዟል። ሰሞኑን አንዲት ጎረቤቴ ያጫወተችኝን ልንገራችሁ፤ መቼም ሚስጥር ብዬ የነገርኩህን በአደባባይ ለምን አወራኸው እንደማትለኝ ተስፋ አደርጋለሁ። ምክንያቱም የእሷ ልብ ያልቻለውን ሚስጥር እንዴት የእኔ ልብ ይችላልና። ለሁላችንም መቻያውን ይስጠን። ምነው? አሜን፣ አሜን… አይባልም!? እንዴ? ሲሆን ሲሆን ቆሞ ከወገብ ጎንበስ ተብሎ እጅ ተዘርግቶ የሁለት እጅ መዳፍን እስከ መሳም ነበር። ለነገሩ ይሄስ ቢሆን ተመሳስሎ ሳይሰራ ይቀር ብላችሁ ነው?ድሮ ለምርቃት ተብሎ እግር እስኪነቃ ይኬዳል፤ አገልግሎት ይሰጣል። ለሚከወን መልካም ተግባር ምርቃት በሂሳብነት ይከፈላል። በዚያኛው ጫፍ ደግሞ እርግማንም የመብረቅ ያህል ይፈራል፤ ይከበራል፤ ያለ ቦታው አይወረወርም። እርግማን ከማደህየት አልፎ እድሜን ይቀጫል፤ያሣጥራል። እነዚህ ህግጋት ሰጥ ለጥ አድርገው ሀገር ሙሉ ሕዝብ ያስተዳድሩ ነበር። የሰው ልጆች ወንጀል የሚፈሩ እጆች እና ኩነኔ የሚፈሩ አንደበቶች ባለቤት ሆኖ ለእልፍ ዘመናት እንዲኖር አስችለውታል። ዛሬ እርግማንም፣ ምርቃትም፣ እምነትም ረክሰዋል፤ ዋጋ አጥተዋል፤ የአውሬነት ድርጊታችንን የመመከት አቅማቸው ሞቷል። ማን ከቁብ ቆጥሮ ጆሮ ይሰጣቸዋል። ታዲያ እነዚህ ፎርጂድ አልሆኑም ትላላችሁ? እንደ ‹‹ሥድ አደግ›› በሄድኩበት ቀረሁ እኮ። ጨዋታየን አስረሳችሁኝ። እናም እኚሁ ጎረቤቴ ቀጠሉ ‹‹የጤፍ እብቅ ከማበጠር፣ከወፍጮ ሥር ዱቄት ከማቡነን ተገላገልኩ እያልኩ ዘወትር እመርቃለሁ። ዘወትር ሥል በየወሩ ማለቴ ነው። ዱቄትና ደመወዝ ከእኛ ቤት አብረው ይመጣሉ፤አብረው ይሸኛሉ። እንዲህ ነው ኡደታቸው›› ብለው በረዥሙ ተነፈሱ። ቀጥለውም ‹‹ዱቄት ሲቀርለት አይኔም ብርታት ያገኘ መስሎ ይሰማኛል›› ወፍጮ ቤት ድረስ የምሄደው በአይኔ አይቼ ነጭ፣ቀይ፣ማኛ ጤፍ ለመምረጥ ነበር። አሁንስ ሂጀ አላውቅም። እኔም ቀረሁ፣ሥሙም ቀረ፣ጣዕሙም የለ›› አሉኝ። ምነው ሥል ጠየቅኳቸው። እሳቸውም ‹‹ አሁን ላይ ከቤቴ ሁኜ ይሄን ያህል ኪሎ በሚል ነው የማዘው። ጤፍ የበፊት ሥሟንም ቀይራለች። የአሁን መጠሪያዋ ነጭ፣ቀይ ማኛ ሳይሆን አንደኛ ደረጃ፣ሁለተኛ ደረጃ በሚል ሆኗል። የበፊቱን ወዛምና በምጣድ ላይ የሚዘናፈል፣ ለምለሙን እጥፍ አድርገህ ቆርሰህ ሥመህ የምትጎርሰው የጤፍ እንጀራ እግርህ እስኪ ነቃ ድረስ ብትሄድ ለመድሃኒት አታገኝም። ጣዕሟንም ቀይራለች ያልኩህ ለዚህ ነው›› አሉኝ። ጤፍና የወፍጮ ቤት ውሎዋን ተርከህመቋጨት አትችልም። እናም ወተት የመሰለ ነጭ ጤፍ ወይም በዘመኑ አጠራር አንደኛ ደረጃ ጤፍ ብታዝም፣ባታዝም እንጀራው እንደሆነ መናገር አቁሟል። ከምጣዱ የተሰፋውን እንጀራ ለማውጣትም በሠፌድ ያለሰለሰ መማጸንን ይጠይቃል። ወዶ አይምሰልህ። ከወፍጮ ቤት እስከ ምጣድ ድረስ በየደረጃው ለቁጥር የሚታክቱ ሥመ ጤፍ አረሞች ያለፍላጎታቸው ተዋህደው እንዲኖሩ ይደረጋል። በዚህ የተነሳ ጤፍ ማንነቷን ትነጠቃለች። በሀገር ደረጃ የሚስተዋለው የለውጥ እስትንፋስም በወፍጮ ቤቶቻችን አካባቢ ደርሶ የጠፋችውን የጤፍ ጣዕም ለአፍቃሪዎቿ ሊያስመልስ ይገባል። በተመሳሳይ በወፍጮ ቤት ሰፈር ደርሰው የተመለሱ እህሎችን ጤንነት እና ደህንነት በማረጋገጥና በማስጠበቅ መስራት የሚያስችል ጠንካራ አሰራርን መዘርጋት ቢችል ለዜጎች የማይተካ ሚና ያበረክታል። ዜጎች ለዚህ ተግባር ምቹ መደላድል በመፍጠር አጋርነታቸውን እንደሚያሳዩ ጥርጥር የለውም። የሱቅና የመጋዘን ባዕድ ቁስ ማብላያዎች ሥፍር ቁጥር የላቸውም ይባላል። በየወፍጮ ቤቶችም በርካታ ትርክቶች ትሰማላችሁ። ‹‹ደንበኛ ንጉስ ነው›› የሚሉት የግድግዳ ጌጥ ጽሁፎች ከነጋዴዎች አንደበት የተተነፈሱ አይምሰሏቹህ። እንደውም የሚተያዩት እንደ ባላንጣ ነው። በተመሳሳይ ‹‹ደረሰኝ ሳይቀበሉ ሒሳብ አይክፈሉ›› የሚሉትም በነጋዴዎች የተጠሉ ናቸው። በእነዚህ ህግጋቶች ልመራ ሞክሬ የገጠመኝን ላጫውታችሁ። ቀኑን ሙሉ አንዲት እቃ ሸምቼ መመለስ ተስኖኛል። ይልቁንስ ዱላ አትርፋችሁ ልትመለሱም ትችላላችሁ። እነዚህ ትዕዛዛት የገቢዎች ሚኒስቴር ሥሜት እንጂ የነጋዴው ሥሜት አያነባቸውም። አልተዋሃዱትም። አንተ አስተገብራቸዋለሁ፤እኔ መጀመርም እችላለሁ ካልክ አንተ የብርቱዎች ብርቱ ነህ። ክንድህም ኪስህም ብርቱ መሆንአለበት። ሩቅ ማሻገር የሚያስችል። በእርግጥ ይህ እሳቤ እና ድርጊት ከለውጡ በፊትና በኋላ በሚሉ ሁለት ብልቶች ተክፍሎ ሊታይ የሚችል እንደሆነ ከዕለት ኑሯችን በላይ መስካሪ አያሻም። የለውጡን መሪ በሁለት እጇ የጨበጠችው የገቢዎች ሚኒስቴር እንስት በቀላሉ ክንዷ የሚዝል አይመስልም። ይልቁንስ የእኛም ጠጠር መወርወር ዋጋ እንዳለው ተገንዝበን ድርሻችንን ልንወጣ ይገባል። በአገራችን ከሰው ልጆች ክብር በላቀ ደረጃ የገንዘብ ክብር ልቋል። የሰው\nልጅ የሚዛን የልኬት ደረጃው የት እንደነበረ መመርመር ይኖርብናል። መዋደዳችንን፣መከባበራችንን፣መተዛዘናችንን\nፈልገን መልበስ አለብን።ለዚህም በየቀየው የሚገኙ ሽማግሌዎች ትምህርት ቤቶቻችን ናቸው። አትጠራጠሩ የኋላውን ዘንግቶ ወደ ፊት መራመድ የቻለ የትውልድ ሰንሰለት የለም። ለተወሰነ ደቂቃም ቢሆን ጊዜያችሁን ሰጥታችሁ በርከክ ብላችሁ የአገራችሁን ወግና ባህል ከአዛውንቶች ጋር ተጨዋወቱ። ህይወታችሁም ይታደሳል። የሰውን ልጅ በዋጋ የማይተመን የክብር ልክ ማጤን የምትችሉበት ልቦና ይነቃቃል። ሳይበረዝ፣ሳይደለዝ እና ሳይጋነን ተፈጥሯዊ እውነታው ከእነርሱ ጋር ነው። የሰውን\nእምነት የለሽነት ልክ፣ ቅጣባሩ የጠፋውን የነጋዴውን ሥግብግብ ባህሪና አመል፣ የንግግርንና የቃልን ዋጋ ማጣት እንዲሁም የሰው ልጅ ሚዛን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀለለ መምጣት በአይናችን ከምናየው ሀቅ በተጨማሪ በንጽጽር አስረጂዎች ናቸው። ‹‹የተናገሩት ከሚጠፋ የወለዱት ይጥፋ›› የሚሉት አባቶች አስገዳጅ ህግ ፈርተው አይደለም። መዋሸት፣ መቅጠፍ፣ መካካድ ከነውርነቱም በላይ የተወገዘ ነበር። እንደ ርካሽ ያስቆጥራል። የዘመድ አዝማድን ሥምና ክብር ያሳጣል። የእገሌ ቤተሰብ የሆነው አቶ እገሌ ዋሾ ነው፣ ቃል አያከብርም።‹‹እሱን ያመነና ጉም የዘገነ አንድ ነው›› ከተባለ በዝምድናቸው ቤተሰቡ ያፍራል። በመሆኑም እርምጃ የሚወስድበት ሕግ ሳይሆን ቤተሰብ ነበር። ያውም የማያዳግም ቆራጥ ርምጃ። እነዚህ ሁሉ የአብሮነት ውብ መስተጋብሮች አሁን ላይ አርገዋል አለያም ሰርገዋል። በአጭር ጊዜ መመለስ ካልቻልን የእኛም እጣፋንታ ይሄው ነው። መ…ክ…..ሠ……ም።አዲስ\nዘመን መጋቢት 5/2011በሙሀመድ\nሁሴን", "passage_id": "db3ab666ec0c5f28eea98abca97b6a6d" }, { "passage": "«ጉዳይዎን እንደ እርስዎ በመሆን ላይ ታች ብለን እናስፈጽማለን። ለስራዎ አጋርና አማካሪ የሚያስፈልግዎ ከሆነም ቀን ከሌት ሰርተን የስኬትን ቁልፍ እናስጨብጥዎታለን»፤ እንዲህ ዓይነት ማስታወቂያዎች አዲስ አይደሉም። ገንዘብ በመክፈል ብቻም በተለያዩ ምክንያቶች እኛ መፈጸም ያልቻልናቸውን ጉዳዮች ያለሃሳብ መከወን የሚቻልበት ጊዜ ላይ ቆመናል። በየዕለቱ ፍጥነቷ እየጨመረ በመጣው ምድራችን ኑሮን ለመግፋት ፉክክር ከመግጠም ባሻገር አማራጭ የለም። ለስራ የሚሰጠው\nሰዓት ከፍተኛ በመሆኑም፤ ቤተሰብን ለመምራት፣ የአገልግሎት ሂሳብ ለመክፈል፣ ፍጆታን ለማሟላት፣ ለማህበራዊ ጉዳይ እና ሌሎች ስራዎችን ለመከወን ግብ ግብ ውስጥ መግባታችንንም እያንዳንዳችን ራሳችንን መታዘብ በቂ ነው። ታዲያ ጊዜን ለመቆጠብና እጅግ አስፈላጊ ለሆነው ጉዳይ ቅድሚያ ለመስጠት ሌሎቹን ስራዎች በአደራ ለሌሎች መስጠት አስፈላጊ ነው። የሰው ልጅ በምድር ሲኖር ከሚያስተናግዳቸው ተፍጥሯዊ ባህሪያት መካከል አንዱ ፍቅር ነው። ፍቅር እንደየ አፍቃሪው በተለያየ ሁኔታ ሊከሰት ይችላል፤ እንደ አመጣጡ ለመመለስም የአፍቃሪው ወይም ተፈቃሪው ባህሪው ወሳኝ ነው። አንዳንዱ ደፋር በግልጽ ተናግሮና አሳምኖ አሊያም በተለያየ ሁኔታ ስሜቱን ገልጦ የሚወደውን ሰው ከእጁ ያስገባል። ሌላው ደግሞ በአይናፋርነት መናገር ባለመቻሉ ሲማቅቅና እንደሚመኘው ፍቅሩን በጊዜ ለማጣጣም አይችልም። መቼም እዚያ ስለ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እዚህ ደግሞ ስለ ፍቅር የምታወሪው ምን አገናኝቷቸው ነው ሳትሉኝ አልቀራችሁም። ሁለቱን ጉዳዮች ያገናኛቸው የሰሞኑ የኦዲቲ ሴንትራል ዘገባ ነው። ነገሩ ግራ አጋቢ ቢሆንም ለአንዳንዶች ግን እፎይታን የሚሰጥ አገልጋይ ተቋም በጃፓን በስራ ላይ ውሏል(ለግልጋሎቱ ግን ገንዘብዎን ሆጨጭ ማድረግዎ የግድ ነው)። «ኮኩናቪ» ሁለት የጃፓን ቃላት በጥምረት የፈጠሩት ቃል ሲሆን፤ «በፍቅር ግራ መጋባት» የሚለውን ፍቺ ይሰጣል። ይህንን ትርጓሜ ይዞ የተመሰረተው ኮኩናቪ የተሰኘው ተቋምም፤ አፍቃሪን ከተፈቃሪ የማገናኘት (የተቀደሰ ተግባር ነው መቼም) አገልግሎት ይሰጣል። ጃፓናዊያኑ አፍቃሪዎች በፍቅር የተንበረከኩለት ተፈቃሪ ፊት ደርሰው ስሜታቸውን መግለጥ ከተሳናቸው፤ የሚጠበቅባቸው 260 ዶላር ብቻ መክፈል ነው። ኮኩናቪም እሳት በላሱት ሰራተኞቹ የፍቅር መልዕክቶችን በመላክ፣ ደብዳቤዎችን በመጻፍ እንዲሁም የተፈቃሪዋን/ውን ልብ ለማሸነፍ የሚችሉ ነገሮችን ይከውናል፤ ከተፈቃሪ ለሚሰጥ ምላሽም አፍቃሪውን ወክሎ መልስ ይሰጣል። ገንዘቡን ወደ 530 ዶላር ማሳደግ ከቻሉም ከመልዕክት ልውውጡ በተጓዳኝ አፍቃሪው አይነጥላውን ገፎ ደፋር እንዲሆን የሚረዳው ምክር በባለሙያዎች ይሰጠዋል። እንዲህ ዓይነቱ ስራ ሲከናወንም መረጃዎችን በመመልከት ያሉት ለውጦች ይመዘናሉ፤ በዚህም ስራው ስኬታማ መሆኑ ታይቷል። አገልግሎቱን ያገኙ አፍቃሪዎችም በተቋሙ ይፋዊ ማህበራዊ ድረ ገጾች ላይ ጭምር በድፍረት ስኬታቸውን በመመስከርም አረጋግጠዋል። «እርዳታቸውን ፈልጌ ወደ ኮኩናቪ በማምራቴ ደስተኛ ነኝ፤ ምክንያቱም በፍቅር ግራ መጋባቴ በስኬት አልፏል። በስራቸውም እጅግ ተደንቄያለሁ» ስትል አስተያየቷን የሰጠችው የ23 ዓመቷ ወጣት ናት። በዚህ ወቅትም አገልግሎቱን ለማግኘት ወደ ተቋሙ የሚያመሩ ሰዎች ቁጥር እያደገም ነው ተብሏል። በጃፓን መሰል አገልግሎት ሰጪዎች እየተስፋፉ ሲሆን፤ ከዚህ ቀደም የስራ መልቀቂያ ለማስገባት የአለቃቸውን ዓይን ለማየት ለሚፈሩ ሰዎች አገልግሎት የሚሰጥ ተቋም መኖሩን ድረ ገጹ ዘግቦ ነበር። ኮኩናቪ ግን በመገናኛ ብዙሃን ራሱን ሲያስተዋውቅ «ጭንቀትዎ ጭንቀታችን፤ ፍቅርዎም ፍቅራችን ነው» የሚል አይመስላችሁም?አዲስ ዘመን የካቲት 11/2011ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "65463c851141f31667ae147bceed438e" }, { "passage": " ክረምቱ ጨክኗል ጠዋት ማታ የሚጥለው ዶፍ ለመንገደኞች፣ በተለይ ትራንስፖርት ለሚጠቀሙ ወገኖች አዳጋች መሆን ጀምሯል፤ ወቅታዊው የኮቪድ 19 ስጋት ደግሞ እንደቀድሞው አማራጭ የሚሰጥ አልሆነም። በርካቶች ማልደው በሚቆሙበት ጎዳና ብቅ የሚል ታክሲና አውቶቡስን እየናፈቁ ያንጋጥጣሉ፤ መጨረሻቸውን ለማግኘት በሚያታክቱ ረጃጅም ሰልፎች የተደረደሩ ተሳፋሪዎች ያለመታከት ሰዓታትን ቆመው ይገፋሉ በሰልፉ መሀል ነፍሰጡሮች፣ ህፃናት የያዙ እናቶች ፣ አቅመ ደካማዎችና ሌሎችም ይታያሉ። ተራ ጠብቀው የሚደርሱ አንዳንድ ታክሲዎች እልፍ ሆነው ከተደረደሩት ጥቂት ያህሉን ብቻ ዘግነው እብስ ይላሉ፤ ቀጣዩን የሚጠብቁ ሌሎች ደግሞ በቀደሟቸው ተሳፋሪዎች ዕድለኝነት እየጎመጁ የራሳቸውን ዕጣ ፈንታ ይናፍቃሉ፡፡ ታክሲዎች እንደታሰበው በጊዜው አይደርሱም ይሄኔ በዳመናው መክበድ የሰጉ ሰልፈኞቹ ተስፋ ይቆር ጣሉ፣ ከፊት ያለው ሳይሸኝ ከኋላ በኩል ያለው ሰልፍ በእጥፍ ይጨምራል። አቶ አሰፋ ቢተው የግል ድርጅት ተቀጣሪ ናቸው። በርካቶች ቤት በዋሉበት በዚህ ዘመን እሳቸው ይህን ማድረግ አልተቻላቸውም፤ የሥራ ባህሪያቸው ከቤት የሚያውል አይደለም። ይህ እንኳን ባይሆን እጃቸውን ናፍቀው ለሚያድሩ ልጆቻቸው የዕለት ዳቦ ሊያጎርሱ ግድ ይላል። በሚኖሩበት የቱሉዲምቱ አካባቢ በርካታ አውቶቡስና ታክሲዎች አገልግሎት ይሰጣሉ። እሳቸው አብዛኛውን ጊዜ በሚጠቀሙበት የታክሲ ትራንስፖርትም በረጃጅም ሰልፎች ላይ መቆምን ልምድ አድርገዋል። አሰፋ ይህ እንዳይሆን ማልደው ይወጣሉ እንዳሰቡት ሆኖ ግን ከችግሩ ማምለጥ አይቻላቸውም፤ ጠዋት ማታ በረጃጅም ሰልፎች ታድመው ከቤት ወደ ሥራ፣ ከሥራም ወደ ቤት ለመመላለሰ ተገደ ዋል። የኮሮና ቫይረስ ከተከሰተ በኋላ ሁሉም ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል። በርካታ ሠራተኞችም ቤት ሆነው ሥራዎቻቸውን እንዲከውኑ ተወስኗል። እንዲህ መደረጉ የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት ታሰቦ ነበር። ዛሬም ግን ‹‹ቤትህ ተቀመጥ›› የተባለ ነዋሪ ኑሮ አስገድዶት ወደውጪ በመውጣቱ ትራንስፖርቱና የሰው ቁጥር ሊመጣጠን አልቻለም፤ እንዲህ መሆኑ ደግሞ እንደ አቶ አሰፋ በመሰሉ ለፍቶ አዳሪዎች ላይ እያሳደረ ያለው ተጽዕኖ ላቅ እንዲል አድርጎታል። እሳቸውን ጨምሮ ሌሎች ተጠቃሚዎች እንደሚሉት የትራንስፖርት ዋጋውና የተጠቃሚዎች ቁጥር በእጥፍ ጨምሯል። መፍትሔ የለሹ የከተማችን የትራንስፖርት ጉዳይም እልባት ካልተበጀለት የችግሩ ስፋት በአሳሳቢነቱ ይቀጥላል። ከጀሞ አየር ጤና፣ ወደ ጦር ኃይሎች በየቀኑ የሚመላለሱት ወይዘሮ ወርቅነሽ በርካቶች የሚያነሱትን ችግር ይጋራሉ። ከጡረታ በኋላ በጥቂት ክፍያ ተቀጥረው የሚሠሩበት የግል ድርጅት ከኮቪድ መከሰት በኋላ ተዘግቶ ቢቆይም በቅርቡ ሥራ ጀምሯል፤ ይህ መሆኑ እሳቸውን ጨምሮ ሌሎች ሠራተኞች በትራንስፖርት እጦት እንዲንገላቱ አስገድዷቸዋል። ወይዘሮዋ ቀደም ሲል ለታክሲ በቀን ይከፍሉት የነበረው ሰባት ብር አሁን ላይ በእጥፍ ጨምሮ ሃያ ስምንት ብር እያስወጣቸው መሆኑን ይናገራሉ፤ በሰዓቱ ለመድረስና ተመልሶ ለመምጣትም የሚገጥማቸው ውጣውረድ በእጅጉ እየፈተናቸው ነው። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራንስፖርት ባለስልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ ኮማንደር አህመድ መሐመድ ከኮቪድ መከሰት በኋላ ህብረተሰቡ ቤቱ እንዲቀመጥ መወሰኑን ያስታውሳሉ፡፡ ይሁን እንጂ በአሁኑ ጊዜ በርካታው የከተማ ነዋሪ ያለማቋረጥ በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛል፡፡ ይህ መሆኑም በትራንስፖርት አቅርቦቱና አጠቃቀሙ ላይ ከፍተኛ ችግር እያስከተለ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡እንደ ኮማንደር አህመድ ገለጻ ከወረርሽኙ መከሰት በኋላ የታክሲዎች የመጫን አቅም በሃምሳ ፐርሰንት መቀነሱ ለረጃጅም ሰልፎች መፈጠር ምክንያት ሆኗል፡፡ ከክረምቱ ጋር ተያይዞ የሚኖረው የመንገድ መዘጋጋትም የታክሲዎች ምልልስ እንዲቀንስና በተጠቃሚው ላይ ተጽዕኖ እንዲፈጠር አድርጓልቀደም ሲል ህብረተሰቡ ቤት የመዋል ልምድን አዳብሮ እንደነበር ያስታወሱት ኃላፊው፣ በአሁኑ ጊዜ አብዛኞቹ መስሪያቤቶች ሥራ ከመጀመራቸው ጋር ተያይዞ በርካታ ሠራተኞች ትራንስፖርት ፈላጊዎች ሆነዋል፡፡ ይህ እውነታም ቀደም ሲል በነበረው ልክ እንቅስቃሴው እንዳይ ቀጥልና የሚስተዋለው ችግር እንዲባባስ አስገድዷል። በአሁኑ ጊዜ ከተለያዩ ቦታዎች ወደ መሀል ከተማ የሚገቡ ሰዎች መበራከታቸውን የገለጹት ኮማንደሩ እነሱን ጨምሮ ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ከወትሮው በባሰ የትራንስፖርት ተጠቃሚዎች መሆናቸው ለችግሩ መባባስ በምክንያትነት የሚጠቀስ ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየጨመረ ያለውን የትራንስፖርት ተጠቃሚዎች ቁጥር መፍትሔ ለመስጠት ጥናት በመደረግ ላይ መሆኑን የተናገሩት ኮማንደር አህመድ፣ በቅርበት በመቀመጥ ካለው ስጋት ይልቅ ተጠጋግቶ በመቆም የሚመጣው ችግር እንደሚብስ በመታመኑ በጉዳዩ ላይ ውይይት መደረጉን ገልጸዋል፡፡በሃምሳ ፐርሰንት መሆኑ ቀርቶ በወንበር ልክ ይጫን የሚለው ሃሳብ የህብረተሰቡ ጥያቄ መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው ጉዳዩ አሳማኝ በመሆኑ ቢሮው ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተወያበት መሆኑን ተናግረዋል። በቅርብ ጊዜ ተጨማሪ አስር የከተማ አውቶቡሶች ርክክብ መካሄዱን የተናገሩት ኮማንደር አህመድ ይህ መሆኑ የትራንስፖርቱን ችግር ለማቃለል በቂ እንደማይሆንና ቀደምሲል የተጀመረውን የሦስት ሺህ አውቶቡሶች ግዢን የማጠናቀቅ ሂደት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። በአሁኑ ጊዜ በተወሰኑ አካባቢዎች ለአውቶቡስ መጓጓዣነት ብቻ የተለዩ መንገዶችን በመጠቀም የሚስተ ዋለውን መጨናነቅ ለመፍታት ጥረት እየተደረገ ነው። ችግሩ በዘላቂነት እስኪፈታ ሕብረተሰቡ ሊተባበር ይገባል ያሉት ኮማንደር አህመድ በተለይ አሽከርካሪዎች በእነዚህ መንገዶች ላይ መኪና ባለማቆም፣ የተበላሹትን ፈጥኖ በማንሳትና በተመሳሳይ ሰዓት ባለመውጣት የመንገዱን መጨናነቅ ሊቀንሱ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡አዲስ ዘመን ሐምሌ 20/2012መልካምስራ አፈወርቅ", "passage_id": "8664eeb073fe58019f706a462bd08ec1" } ]
dd42826ee9de53d2601d4cd9e0038d6c
4c64656042e6ddb504d280c730f6b584
ባድሚንተን-ትኩረት የተነፈገ ተወዳጅ ስፖርት
 በስፖርቱ ዓለም ጥሩ የአካል ብቃት፣ሰውነትን እንደ ልብ የማዘዝ ችሎታ፣ፅናት፣ጥንካሬና ፍጥነትን ከሚሹ ጨዋታዎች መካከል ባድሚንተን ዋነኛው ነው። ከሜዳ ቴኒስ ወይንም ከጠረጴዛ ቴኒስ ጋር ተመሳሳይ አጨዋወትን የሚጋራው የባድሚንተን ስፖርት በብሪታኒያና ህንድ እንደጎለበተ የሚነገር ቢሆንም በአውሮፓዊቷ አገር ዴንማርክ ትልቅ ዝና አለው። ይህ ስፖርት ተወዳጅነቱን እያሰፋ በኤሽያ አገራት በስፋት መዘውተሩን ተከትሎም ባለፉት ጥቂት የማይባሉ ዓመታት የቻይና የበላይነት የሚንፀባረቅበት ሆኗል። እኤአ 1992 በባርሴሎና የበጋ ወራት ኦሊምፒክ ተካቶም በአራት የውድድር ዘርፎች አገራት ተፎካካሪ ሆነውበታል። በነጠላ ወንዶች፣ ነጠላ ሴቶች፣ በቡድን ሴቶችና በቡድን ወንዶች ኦሊምፒክ ላይ የነበረው ፉክክር አድጎም በድብልቅ ፆታ አምስተኛ የመወዳደሪያ ዘርፍ ለመሆን ጊዜ አልፈጀበትም። የባድሚንተን ስፖርት በኢትዮጵያ በይፋ መቼ እንደተጀመረ ሰነዶችን ማግኘት አይቻልም። ይሁን እንጂ ይህ ስፖርት በ1940ዎቹ መጨረሻ አካባቢ በታወቁ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች፣ የሚሲዮን ተቋማትና በወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማህበር (ወክማ) አካባቢ በውጭ አገር ዜጎችና መምህራን አማካኝነት እንቅስቃሴው እንደተጀመረ ከፌዴሬሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። በተለይም የባድሚ ንተን ስፖርት በ1970 ዎቹ ገደማ ከወክማ ባሻገር በህንድ ኤምባሲ ውስጥ በስፋት መዘውተር እንደ ጀመረ ይነገራል። በህዳር ወር 1978 ዓ.ም ስፖርቱ በአደራጅ ኮሚቴነት ተዋቅሮ በሂደት 1982 ዓ.ም ላይ አደረጃጀቱ ወደ ፌዴሬሽን አድጓል። ከዚህም በኋላ ከ1986 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ የኢትዮጵያ ቻምፒዮናን በውድድር ደረጃ ማከናወን ችሏል። ባለፉት ዓመታትም በአገራችን በሚካሄዱ እንደ መላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች፣የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስፖርት ፌስቲቫል፣የታዳጊ ወጣቶች የምዘና ውድድሮችና ሌሎችም ፉክክሮች ላይ የምንመለከተው ስፖርት መሆን ችሏል። ከኦሊምፒክ ስፖርቶች መካከል አንዱ የሆነው የባድሚንተን ስፖርት በተለይም በኤሽያ አገራት በስፋት የሚዘወተር ብቻ ሳይሆን እነዚህ አገራት በብዛት ኦሊምፒክ ላይ ተሳትፈው በሜዳሊያ ሰንጠረዥ የአገራት ፉክክር ውስጥ የሚገቡበት የስፖርት አይነት ነው። የባድሚንተን ስፖርት አሁን ላይ በአገራችን ብዙ እውቅና ከሌላቸው የስፖርት አይነቶች አንዱ ሆኖ እናገኘዋለን። የአገራችን መገናኛ ብዙሃንም አብዛኞቹ ለዚህ ስፖርት ትኩረት ሲሰጡት አይታይም። ስፖርቱን በቅርበት ከሚያውቁት ባሻገ ርም አብዛኛው ህዝብ ባድሚንተን ምን እንደሆነ ግን ዛቤ አለው ለማለት ይቸግራል። በአጠቃላይ የባድሚንተን ስፖርት በአገራችን ካለመስፋፋቱ ባሻገር ሌሎች የኦሊምፒክ ስፖርቶች በሚጓዙበት የእድገት ደረጃ ላይ የሚገኝ ነው ለማለት አይቻልም። ለመሆኑ ይህ ስፖርት እንደ እግር ኳስና አትሌቲክስ ባይሆን እንኳን ሌሎች ደካማ የሚባሉት ስፖርቶች በሚንቀሳቀሱበት ደረጃ ለመንቀሳቀስ ለምን ተሳነው?፣ ክለቦችን መስርተው የሊግ ውድድሮችን በቀጣይነት ለማስኬድ ዳዴ ከሚሉት አንዳንድ ፌዴሬሽኖችስ በምን ይለያል? የሚሉ ጥያቄዎች በስፖርት ቤተሰቡ ዘንድ ይነሳሉ። የስፖርቱ አፍቃሪዎች ከስፖርቱ ባህሪ ተነስተው ለነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ ሲሰጡ የባድሚንተን ትልቁ ችግር መሰረተ ልማት እንደሆነ ያብራራሉ። የባድሚንተን ስፖርት በባህሪው ከቤት ውስጥ ስፖርቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የተሟላ መሰረተ ልማት የሚጠይቅ ነው። ስለዚህ ስፖርቱን ለማስፋፋትና ለማዘውተር ቢያንስ መሰረታዊ የሆነ አዳራሽ ወይም ጅምናዚየም ያስፈልጋል። የባድሚንተን መጫወቻዋ ላባ(በተለምዶ እፉየ ገላ የምትመስል መጫወቻ) በጨዋታ ወቅት በንፋስ ምክንያት አቅጣጫ የመለዋወጥ ባህሪ ስላላት ስፖርቱን ከቤት ውጭ ማድረግ አስቸጋሪ ነው። ይህን ስፖርት ለመጫወት አዳራሹ ወይንም ጅምናዚየሙ ቢያንስ ሰባት ሜትር ከፍታ ያለውና ሁለት ጨዋታዎችን በአንድ ጊዜ ማካሄድ የሚያስችል መሆን እንዳለበት ዓለም አቀፍ ህጉ ይደነግጋል። በአገራችን አብዛኞቹ ስፖርቶች ከቤት ውጭ ሊዘወተሩ ይችላሉ። ባድሚንተን ግን ቤት ውስጥ ብቻ የሚደረግ ውድድር በመሆኑ በቀላሉ እንዳይዘወተርና እንዳይስፋፋ እንቅፋት መሆኑን የስፖርቱ ቅርብ ሰዎች ይናገራሉ። ከአዲስ አበባና ድሬዳዋ ከተሞች በስተቀር ስፖርቱን ሌሎች ክልሎች ላይ እንደልብ ማካሄድና ማስፋፋት የሚያስችል መሰረተ ልማት የለም። በአዲስ አበባ ወክማ ውስጥ ባድሚንተን በስፋት እንደሚዘወተር ይታወቃል። ነፃ የሆኑ አዳራሾች ወይም ጅምናዚየሞች ቢኖሩ ስፖርቱ የሚፈልጋቸው ሌሎች ቁሶችን በቀላሉ ማግኘት እንደሚቻል ይታመናል። በእርግጥ የባድሚንተን ስፖርትን እንደ ቮሊቦልና ቅርጫት ኳስ አይነት ስፖርቶች ከቤት ውጪ ማዘውተር የሚቻልበት እድል ዝግ አይደለም። ይሁን እንጂ ባድሚንተንን ከቤት ውጭ ማዘውተር ስፖርቱን በፕሮፌሽናል ደረጃ ለማሳደግና ውጤታማ ለመሆን እንደማይቻል እውን ነው። አገር አቀፍ ፌዴሬሽኑ ስልጠናዎችን ለመስጠት አይደለም አገር አቀፍ ውድድሮችን ለማካሄድ እንቅፋት ከሆኑበት ነገሮች ዋነኛውም ይሄው ማዘውተሪያ ስፍራው መሆኑም ይታመናል። ስፖርቱ እጅግ የሚወደድና የብዙዎችን ቀልብ ሊስብ የሚችል ነው። በአገራችን በተለያዩ ውድድሮች ላይ እንደሚታየውም ወጣቱ ስፖርቱ ላይ ትልቅ ፍላጎት አለው። በተለይም በለጋ እድሜ ላይ የሚገኙ እድሜያቸው አሥራ አንድና አሥራ ሁለት አካባቢ የሚገኙ ታዳጊዎች ለባድሚንተን ስፖርት ከፍተኛ ፍላጎት አላቸው። ሁኔታዎች ተመቻችተው እንደ ስፖርት ለሁሉም እድሜያቸው የገፋ ሰዎች ቢያዘወትሩትም ይመከራል። የባድሚንተን ስፖርት በደንብ ትኩረት ተሰጥቶት ተከታታይ ስልጠናና በርካታ ውድድሮች ቢደረጉ ቢያንስ በአፍሪካ ደረጃ በሚካሄዱ ውድድሮች ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ይታመናል። አሁን ባለው ሁኔታ ስፖርቱ ከነችግሮቹ እንኳን ውጤቱ ብዙ ባይሆንም በመላ አፍሪካና ሌሎች ዓለም አቀፉ ጨዋታዎች መሳተፍ እየተቻለ ይገኛል። መንግሥት ስፖርቱን በተመለከተ ሥራው በዋናነት ስፖርቱን ማስፋፋት ነው። የልማት ሥራዎችን መስራት ደግሞ ያለበት ፌዴሬሽኑ ነው። ፌዴሬሽኑን ሊመሩ የሚችሉ ደግሞ ሥራ አስፈፃሚዎች ተቀምጠዋል። እነዚህ ሥራ አስፈፃሚዎች ሃብት አሰባስበው ስፖርቱን በደንብ በማህበረሰቡ ውስጥ እንዲያስፋፉ ትልቅ ድርሻ ያላቸው ህዝባዊ አካል ናቸው። መንግሥት እንደማንኛውም የስፖርት ፌዴሬሽን ለባድሚንተንም ድጋፍ ያደርጋል። እንዲያውም መንግሥት አሁን የሚያደርገው ድጋፍ ከስፖርቱ እንቅስቃሴ አንፃር ጥሩ የሚባል እንደሆነ ማስቀመጥ ይቻላል። ባድሚንተን የኦሊምፒክ ስፖርት እንደመሆኑ እንደሌሎች መሰል ስፖርቶች በታዳጊ ወጣቶች የተለያዩ ፕሮጀክቶችና በአካዳሚ ደረጃ ሰፊ እንቅ ስቃሴ ሲደረግበት አይታይም። ባድሚንተን በሁሉም ክልሎች በታዳጊ ወጣቶች ፕሮጀክት ከሚሰራባቸው ስፖርቶች አንዱ ሆኖ እየተሰራ ይገ ኛል። ፌዴሬሽኑም በየዓመቱ የሚደረጉ የፕሮጀክቶች የምዘና ውድድሮችም ተሳታፊ ነው። በታዳጊ ፕሮጀክት ደረጃ የሚሰራባቸው በአካዳሚ ደረጃ ግን ስልጠና የማይሰጥባቸው ሌሎች ስፖርቶችም አሉ። በባድሚንተን ስፖርት በግለሰቦች የሚመሰረቱ ቡድኖች አሉ፣ እንደ ክለብ ግን ተደራጅተው የሚንቀሳቀሱ አይደሉም። በዚህ ሁኔታ በባድሚንተን ስፖርት በተለያዩ ክልሎች የታዳጊ ወጣቶች ፕሮጀ ክቶችን ቀርፆ መንቀሳቀስ እንደ አገር ስፖርቱን ከመጥፋት ሊታደግ ይችላል። ይሁን እንጂ ከነዚህ ፕሮጀክቶች የሚወጡ ታዳጊዎች ወደ አካዳሚ ገብተው ከዚያም ወደ ክለብ መሸጋገር ካልቻሉ ከስፖርቱ ጋር ያላቸው እህል ውሃ የሚዘልቀው እስከ ምዘና ውድድር ድረስ ነው። ይህ ደግሞ ብዙ ወጣቶች ወደ ስፖርቱ እንዳይመጡ እንቅፋት መሆኑ አይቀርም። ክለቦች ከሌሉ ከፕሮጀክት የሚወጡ ታዳጊዎች ተጎጂ ሊሆኑ እንደሚችሉ ቢታመንም ከፕሮጀክት ከወጡ በኋላ ሌላ ማረፊያ የላቸውም። በአገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄዱ ውድድሮች ክልላቸውን ወክለው መሳተፍ አንዱ አማራጫቸው መሆኑ ግን ይታመናል። ከባድሚንተን ጋር በተመሳሳይ በጀት ይንቀሳቀሱ የነበሩ በርካታ ፌዴሬሽኖች ክለቦችን በማቋቋምና ውድድሮችን በብዛት በማድረግ ራሳቸውን እያሳደጉ እንደሚገኙ ብዙ ማስረጃዎችን ማቅረብ ይቻላል። በአገራችን ከታሪካቸውም አንፃር የኳስ ስፖርቶች ላይ ትኩረት የማድረግ ልምድ ስላለ የኳስ ስፖርቶችና ባድሚንተን እኩል ማየት ተገቢ አይደለም። የኳስ ስፖርቶች የሚባሉት እግር ኳስ፣እጅ ኳስ፣ቅርጫት ኳስ ወዘተ በሚሊተሪ አካባቢ ሰፊ መሰረት ስላላቸው እነሱን ለማሳደግ ከባድሚንተን አይነት ስፖርቶች አኳያ ብዙ ልፋት እንደማይጠይቅ የሚሞግቱ የስፖርት ቤተሰቦች ጥቂት አይደሉም። የባድሚንተን ስፖርት በርካታ ችግሮች ቢኖ ሩበትም በአንዳንድ ክልሎች መሰረታዊ ነገር ሳይሟ ላላቸው ጭምር እየሰሩ ነው። ስፖርቱ የመሰረተ ልማት እጥረት ቢኖርበትም ፌዴሬሽኑ በተቻለው አቅም ከዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኑ ከሚያገኛቸው የቁሳቁስ ድጋፍ ተነስቶ ለክልሎች ድጋፍ እየሰጠ ነው። ይህ ስፖርቱ እንዲያንሰራራ ትልቅ እድል ነው። የመሰረተ ልማት ጉዳይ የባድሚንተን ስፖርት ብቻም ሳይሆን የበርካታ ስፖርቶች እንቅፋት እንደመሆኑና ከአገር አቅም ጋር የተያያዘ መሆኑ ችግሮች በአንድ ጀምበር ሊፈቱ አይችሉም። ያም ሆኖ ኢትዮጵያ በስፖርቱ መሰረተ ልማት ግንባታ ረገድ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ለመሆኗ በተለያዩ ክልሎች ግዙፍ ስቴድየሞችን ጨምሮ ጅምናዚየምና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን ማስተዋል ይቻላል። ባድሚንተንን ለመሳሰሉትና በመሰረተ ልማት ችግር በአገራችን መራመድ ያልቻሉት ስፖርቶችም የነዚህን መሰረተ ልማት ግንባታዎች መጠናቀቅ በተስፋ የሚጠበቁ ይሆናል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 27/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=36543
[ { "passage": " በስፖርት የመጨረሻውን ደረጃ ክብር የሚያስገኘው ውድድር ኦሊምፒክ መሆኑ ይታወቃል። በዓለም ትልልቅ ስም ያላቸው ዝነኛ አትሌቶች ሃገራቸውን ወክለው የሚሳተፉበት እንዲሁም በርካታ ክብረወሰኖች የሚሰባበሩበትም ነው። በመሆኑም በአትሌቶች ዘንድ በመድረኩ የሜዳሊያ ባለቤት መሆን ብቻም ሳይሆን ተሳትፎውም ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ነው።ኦሊምፒክ በየአራት ዓመቱ ስለሚካሄድ ከፍተኛ ዝግጅት የሚደረግበት ሲሆን፤ ወጥ አቋም የሌላቸው አትሌቶች በተደጋጋሚ ኦሊምፒክ ላይ ሊታዩ አይችሉም። በመሆኑም በርካታ ተሳትፎ ያላቸው አትሌቶችን ለማግኘት አዳጋች ነው። እንግሊዛዊቷ አትሌት ግን በመጪው ዓመት ስድስተኛ የኦሊምፒክ ተሳትፎዋን ለማድረግ በዝግጅት ላይ መሆኗን ነው ያሳወቀችው። በተለይ ለወጣት አትሌቶች አስተማሪ የሆነ ተሞክሮዋንም ለቢቢሲ አጋርታለች።ጆ ፓቬ አምስት አሊምፒኮች ላይ የተሳተፈች አንጋፋ አትሌት ስትሆን በሚቀጥለው ዓመት በሚካሄደው የቶኪዮ ኦሊምፒክ ስድስተኛ ተሳትፎዋን በማድረግ የክብረወሰን ባለቤት ለመሆን ፍላጎት አላት። ከዚህ ቀደም የሃገሯ ልጅ የሆነችው ጦር ወርዋሪ ቴሳ ሳንደርሰን ስድስት ኦሊምፒኮች ላይ ሀገሯን የወከለች አትሌት በመባል ተመዝግባለች። ፓቬ ስድስተኛዋን ተሳትፎ የምታደርግ ከሆነ ደግሞ በመም አትሌት የመጀመሪያዋ ትሆናለች።\nፓቬ እአአ በ2014 ከወሊድ በኋላ በአውሮፓ ሻምፒዮና በ10ሺ ሜትር ስትሳተፍ በአንጋፋነቷ የመነጋገሪያ ርዕስ ሆና ነበር። ይሁን እንጂ በ40ዓመቷ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት በመሆን ብቃቷን ማስመስከር ችላለች። በቶኪዮው ኦሊምፒክ ስትሳተፍም ዕድሜዋ 46 ስለሚሆን ምናልባትም በኦሊምፒኩ አንጋፋዋ አትሌት ልትሆን ትችላለች። ፓቬ ለቢቢሲ በሰጠችው አስተያየት ላይም «ዕድሜዬን ረስቼ ስድስተኛውን የኦሊምፒክ ተሳትፎዬን አደርጋለሁ» ብላለች።አትሌቷ ሃገሯን ወክላ በኦሊምፒክ የመጀመሪያ ተሳትፎዋን ያደረገችው እአአ በ2ሺ በተካሄደው የሲድኒ ኦሊምፒክ ላይ ነበር። «በቶኪዮ የሚካፈለው ብሄራዊ ቡድን ጥሩ ተፎካካሪ እንዲሆን እፈል ጋለሁ። በመሆኑም ዝግጅታችንን ቀድመን መጀመር ይገባናል፤ ፉክክሩ ደግሞ ይበልጥ ደስ የሚያሰኝ ነው» ብላለች። የሁለት ልጆች እናት የሆነችው አትሌቷ ከኦሊምፒኩ አስቀድሞ በዘንድሮው የዶሃ ዓለም ሻምፒዮና አቅሟን የመፈተሽ ፍላጎት እንዳላትም ጨምራ ገልጻለች። እአአ በ2017 በለንደን በተካሄዱት ሁለት ትልልቅ የአትሌቲክስ ውድድሮች ላይ ተሳታፊ ብትሆንም አልተሳካላትም ነበር። በለንደን ማራቶን ውድድሯን ሳታጠናቅቅ አጋማሽ ላይ ስታቋርጥ፤ በ10ሺ ሜትር በተካፈለችበት ሻምፒዮና ደግሞ በጉዳት ምክንያት ውድድሯን ለማጠናቀቅ አልቻለችም ነበር።ያለፈው ዓመት በተካሄደ ሌላ ውድድር ግን በረጅም ርቀት የመም ላይ ውድድር ሶስተኛ በመሆን የነሃስ ሜዳሊያውን ወስዳለች። በባለቤቷ የምትሰለጥነው አትሌቷ በልምምድ ቦታዎች ላይም ነፍስ ያላወቁ ልጆቿን ይዛ ትሄዳለች «ሩጫ እወዳለሁ፤ የአእምሮ እና ሰውነት ጤናን ለማግኘት ያግዛል። ከቤተሰብህ ጋር ሆነህ ስትከውን ደግሞ ይበልጥ መነሳሳትን ይፈጥራል። ባለቤቴ ያግዘኛል፤ ሥራችንን የምንሰራውም እንደ ቡድን ነው። ሯጭ ስትሆን መጨናነቅን ማስወገድ የግድ ነው ይህም የአእምሮን ጤና ይሰጣል። እድሜህንም እንደ ልምድ መጠቀም ትጀምራለህ» ስትልም የህይወት ልምዷን ታጋራለች።የአትሌቷ የኦሊምፒክ ተሳትፎ በተለያዩ ችግሮች የታጀበ ይሁን እንጂ ተስፋ አለመቁረጧ ግን ለብዙዎች ተሞክሮ የሚሆን ነው። እአአ 1997 ከባድ የሆነና ውስብስብ ቀዶ ጥገና የሚያስፈልገው የጉልበት ጉዳት የደረሰባት ቢሆንም፤ ከዚያ አገግማ በሲድኒ ኦሊምፒክ 12ኛ ደረጃን በመያዝ ነበር ያጠናቀቀችው። እአአ በ2004ቱ የአቴንስ ኦሊምፒክ ከመሳተፏ ሶስት ወራት በፊት የጡንቻ ጉዳት ቢደርስባትም አምስተኛ ደረጃ በመያዝ የዲፕሎማ ተሸላሚ ነበረች።በ2008ቱ የቤጂንግ ኦሊምፒክ 12ኛ ደረጃ በመያዝ ውድድሯን ያጠናቀቀችው ደግሞ በውድድሩ ዋዜማ በምግብ መበከል የጤና መታወክ ስለደረሰባት ነበር። በሀገሯ በተዘጋጀው የ2012 ኦሊምፒክ በ5 እና 10ሺ ሜትር ውድድሮች ተሳትፎዋ ሰባተኛ ደረጃ በመያዝም የመጀመሪያዋ አውሮፓዊት አትሌት ተሰኝታለች። በሪዮ በተካሄደው የ2016ቱ ኦሊምፒክ ደግሞ ዘግይታ ውድድሩን በመጀመሯ በ10ሺ ሜትር 15ኛ ደረጃን ነበር የያዘችው። «የሪዮ ኦሊምፒክ ተሳትፎዬ በጣም አስደሳች ነበር፤ አብረውኝ የሮጡት አትሌቶችም ከእኔ በ20ዓመት የሚያንሱ ነበሩ። ቢሆንም ሁሌም ሃገሬን መወከል ለእኔ ኩራት ነው» ስትልም ትገልጻለች።አዲስ ዘመን ጥር 13/2011ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "121a3477a1e1f36d985d4b50ab4afece" }, { "passage": " በፊንላንድ ሄልሲንኪ ከተማ እኤአ በ1983 የተጀመረው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና የዓለማችን ትልቁ የአትሌቲክስ መድረክ በመሆን ያለፉትን አርባ ዓመታት አሳልፏል። እኤአ በ1987ና 1991 በአራት ዓመት ልዩነት የጣሊያኗ መዲና ሮምና የጃፓኗ ቶኪዮ ይህን ታላቅ ውድድር ያዘጋጁ አገሮች ናቸው። ከቶኪዮ ወዲህ ግን ውድድሩ በሁለት ዓመት ልዩነት ነው እየተካሄደ የሚገኘው። የጀርመኗ ስቱትጋርት፤ የስዊድኗ ጉተንበርግ፤ የግሪኳ አቴንስ፤ የስፔኗ ሴቪሊ፤ የካናዳዋ ኤድመንተን፤ የፈረንሳይ መዲና ፓሪስ፤ የፊንላንዷ ሄልሲንኪ (ለሁለተኛ ጊዜ) የጃፓኗ ኦሳካ፤ የጀርመኗ በርሊን፤ የደቡብ ኮሪያዋ ዴጉ፤ የሩሲያዋ ሞስኮና የቻይናዋ ቤጂንግና የእንግሊዟ ለንደን ቻምፒዮናውን በሁለት ዓመት ልዩነት በቅደም ተከተል መድረኩን አዘጋጅተውታል። የዘንድሮ ተረኛዋ የካታሯ ዶሃ ስትሆን የምዕራባውያን መገናኛ ብዙኃን ትኩረት ቢነፍጓትም ከአምስት ወራት በኋላ ለሚጠብቃት ታላቅ የስፖርት ድግስ ሽርጉድ ማለት ጀመራለች። የአሜሪካዋ ዩጂንም ቀጣዮን ቻምፒዮና ለማዘጋጀት ወረፋ ይዛለች። ኢትዮጵያም ቻምፒዮናው ከተጀመረ አንስቶ በመሳተፍ ላይ ትገኛለች። የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና አሁን ያለውን መልክ ይዞ መካሄድ ከመጀመሩ በፊት እኤአ በ1913 የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ማህበር ኦሊምፒክ እንደ ዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ያገለግላል ብሎ አምኖበት ነበር። ይህም ለሃምሳ ዓመታት ያህል አገልግሎ 1960ዎቹ ውስጥ በርካቶቹ የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ማህበር አባል አገሮች «የራሳችን የሆነ ውድድር ይኑረን» ብለው ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት እኤአ በ1976 ፑርቶሪኮ ላይ በተደረገ ዓመታዊ የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ማህበር ስብሰባ ላይ የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ከኦሊምፒክ ተለይቶ ራሱን የቻለ ውድድር እንዲያካሂድ ተወሰነ። በእዚህን ወቅት የመጀመሪያውን ውድድር ለማስተናገድ የምዕራብ ጀርመኗ ስቱትጋርትና የፊንላንዷ ሄልሲንኪ ጥያቄ አቀረቡ። እኤአ በ1952 ኦሊምፒክን ያስተናገደችው ሄልሲንኪ እድሉን አገኘች። የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በውድድር አይነትና በተሳታፊዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ በርካታ ለውጦችን አስተናግዷል። እኤአ በ1983 ከመቶ 54 አገራት የተውጣጡ1 ሺ 300 አትሌቶች ተሳታፊ ነበሩ። ይህ ቁጥር እኤአ 2003 ፓሪስ ላይ ተካሂዶ በነበብቻ ሳይሆን በተለያዩ የውድድር አይነቶችም በርካታ ለውጦች ታይተዋል። በተለይም ወንዶች በሚወዳደሩባቸው የውድድር አይነቶች ሴቶችም ተካፋይ እንዲሆኑ መደረጉ የቻምፒዮናው ትልቅ ለውጥ ነው። አሁን ላይ በዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ወንዶች የሚወዳደሩበት ለሴቶች ያልተፈቀደ የሃምሳ ኪሎ ሜትር የርምጃ ውድድር ብቻ ነው። እኤአ በ1987 የሴቶች አስር ሺ ሜትር ሩጫና አስር ኪሎ ሜትር ርምጃ ውድድር የዓለም ቻምፒዮናን የተቀላቀለ አዲስ የውድድር አይነት ነው። ከስድስት ዓመት በኋላም የሴቶች ስሉስ ዝላይ የውድድሩ አካል ሆኗል። እኤአ በ1995 የሴቶች አምስት ሺ ሜትር ሩጫ የሦስት ሺ ሜትርን ወክሎ የውድድር አካል ሆነ። እኤአ በ1999 ደግሞ የሴቶች ምርኩዝ ዝላይና መዶሻ ውርወራ የውድድር አካል ከመሆናቸው በተጨማሪ የሴቶች አስር ኪሎ ሜትር ርምጃ ውድድር በሃያ ኪሎ ሜትር ርምጃ ውድድር ተተካ። እኤአ በ2005 የሴቶች ሦስት ሺ ሜትር መሰናክል ውድድር ተጨመረ። የለንደኑን ቻምፒዮኗ ሳይጨምር ባለፉት 15 ረው ቻምፒዮና ከሁለት መቶ ሦስት አገሮች የተውጣጡ 1 ሺ 907 አትሌቶች አሻቅቧል። በዓለም ቻምፒዮና የተሳታፊዎች ቁጥር የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮናዎች 98 አገራት የሜዳሊያ ሰንጠረዥ ውስጥ የገቡ ሲሆን፣ 2036 ሜዳሊያዎች (670 የወርቅኸ 685 የብርና 681 የነሐስ) ለአሸናፊዎች ተበርክተዋል፡፡ ከ16ኛው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በፊት የምንጊዜም የሜዳሊያ ስብስብ ደረጃን በድምሩ 323 ሜዳሊያዎች (143 የወርቅ፤ 96 የብርና 84 የነሐስ) በመሰብሰብ አሜሪካ አንደኛነቷን አስጠብቃለች፡፡ ሩሲያ 172 ሜዳሊያዎች (55 የወርቅ ፤ 60 የብርና 57 የነሐስ)፤ ኬንያ 128 ሜዳሊያዎች (50 የወርቅ፤ 43 የብርና 35 የነሐስ) ፤ ጀርመን 108 ሜዳሊያዎች (33 የወርቅ፤ 35 የብርና 40 የነሐስ)፤ ጃማይካ 110 ሜዳሊያዎች (31 የወርቅ፤ 44 የብርና 35 የነሐስ)፤ ታላቋ ብሪታኒያ 89 ሜዳሊያዎች (25 የወርቅ፤ 30 የብርና 34 የነሐስ)፤ ሶቭዬት ህብረት 77 ሜዳሊያዎች (22 የወርቅ፤ 27 የብርና 28 የነሐስ) እንዲሁም ኢትዮጵያ 72 ሜዳሊያዎች (25 የወርቅ፤ ቦልትን ያክል በዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በርካታ ሜዳሊያዎችን የሰበሰበ አትሌት የለም። ቦልት አስራ አንድ የወርቅና ሁለት የብር በማጥለቅ ቀዳሚ ነው። አሜሪካዊው ካርል ሌዊስ ስምንት የወርቅ፤ አንድ የብርና አንድ የነሐስ ሜዳሊያዎች በማጥለቅ ተከታይ ነው። በተመሳሳይ አሜሪካዊው ሚካኤል ጆንሰን ስምንት የወርቅ ሜዳሊያ በማጥለቅ ሦስተኛ ነው። ሌላኛው አሜሪካዊ ላሻውን ሜሪት ስድስት የወርቅና ሁለት የብር ሜዳሊያ በመውሰድ አራተኛ ነው። የረጅም ርቀት ነጉሱ ኃይሌ ገብረስላሴ አራት የወርቅ ሁለት የብርና አንድ የነሐስ ሜዳሊያ በማጠለቅ አምስተኛ ደረጃ ላይ ይቀመጣል። የቀድሞ የምርኩዝ ዝላይ ባለ ክብረወሰኑ ዩክሬናዊው ሰርጌ ቡካ ስድስት የወርቅ ሜዳሊያዎችን በዓለም ቻምፒዮና መድረክ በማጥለቅ ኃይሌን ይከተላል። አሜሪካዊው ጃርሚ ዋሪነር አምስት የወርቅና አንድ የብር ሜዳሊያ ይዞ ሰባተኛ ነው። የአስርና አምስት ሺ ሜትር ባለ ክብረወሰኑ ቀነኒሳ በቀለ በአምስት የወርቅና አንድ የነሐስ ሜዳሊያ ይከተላል። በሴቶች የረጅም ርቀት ንግስቷና የአምስትና22 የብርና 25 የነሐስ) በማስመዝገብ እስከ 7 ያለውን ደረጃ አከታትለው ይዘዋል፡፡ ጃማይካዊው የአጭር ርቀት ንጉስ ዩሴን አስር ሺ ሜትር የዓለም ክበረወሰን ባለቤቷ ጥሩነሽ ዲባባ በዓለም ቻምፒዮና መድረክ አምስት የወርቅ ሜዳሊያ ብታጠልቅም፣ ከአንድ እስከ አስር ባለው ደረጃ ውስጥ አትካተትም። ጃማይካዊቷ ማርሌን ኦቴይ ሦስት የወርቅ፤ አራት የብርና ሰባት የነሐስ ሜዳሊያ በመሰብሰብ በአስራ አራት ሜዳሊያዎች ቀዳሚ ነች። አሜሪካዊቷ አሊሰን ፌሊክስ ስምንት የወርቅ፤ አንድ የብርና አንድ የነሐስ በማጥለቅ በአስር ሜዳሊያዎች ሁለተኛ ነች። ሌላኛዋ አሜሪካዊት ጄርል ሚልስ ክላርክ በአራት ወርቅ፤ ሦስት ብርና ሁለት ነሐስ ትከተላለች። ጃማይካዊቷ ቬሮኒካ ካምቤም ብሮውን ቀጣዩ ደረጃ ላይ ትገኛለች። በዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ታሪክ በበርካታ ቻምፒዮናዎች ላይ በመካፈል ፖርቹጋላዊቷ የአስርና የሃያ ኪሎ ሜትር ርምጃ ተወዳዳሪ ሰሳን ፌተር እኤአ ከ1991 እስከ 2011 ድረስ በአስራ አንድ ቻምፒዮናዎች በመሳተፍ ትልቅ ታሪክ አላት። ስፔናዊው የሃምሳ ኪሎ ሜትር ርምጃ ተወዳዳሪ ጂሰስ ኤንጅል ጋርሺያም እኤአ ከ1993 እስከ 2013 ድረስ በአስራ አንድ ቻምፒዮናዎች በመካፈል ተመሳሳይ ታሪክ አለው።አዲስ ዘመን የካቲት 7/2011ቦጋለ አበበ", "passage_id": "06685c2154b650e4de54c7efb313a9b9" }, { "passage": "ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የስፖርት መድረኮች አንገቷን ቀና አድርጋ የምትሄደው በአትሌቲክስ ነው:: ለዚህ ደግሞ የኢትዮጵያዊነት መገለጫ የሆነውን ህብረትና መተሳሰብን ዘመን የማይሽራቸው ጀግኖች አትሌቶች ለተተኪው ጀግና አውርሰው አሳይተውናል:: ድል ድል ነው:: በመደጋገፍና በመረዳዳት ከራስ ጥቅም በላይ አገርን አስቀድሞ የሚመጣ ድል ደግሞ የበለጠ ጣፋጭ ነው:: ጀግኖች አገርን አስቀድመው ለባንዲራ ክብር በሕብረት የሚፅፉት ታሪክ አገርን አንድ ያደርጋል:: ለቀጣዩ ትውልድ አንድነትም ትምህርት ይሆናል:: ይህ የአያሌ አትሌቶቻችን መገለጫ ቢሆንም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ከአገር በላይ ራስን የማስቀደም፣ በሕብረት ታግሎ ጣፋጭ ድል ከማስመዝገብ ይልቅ በግል ታሪክ ለማስመዝገብ የሚደረግ ጥረት በአትሌቶቻችን መካከል እንደሰፈነ የተመለከትንበት አጋጣሚ ብዙ ነው:: የአሁኑ ትውልድ የአትሌቲክስ ጀግኖቻችን በግለኝነት መወቀሳቸው የተደበቀ ነገር አይደለም:: ተደጋግፎ መሮጥና የአረንጓዴ ጎርፍ ታሪክ መፃፍ ከእነ ኃይሌና ቀነኒሳ የአትሌቲክስ ትውልድ ወዲህ እየደበዘዘ የመጣ ይመስላል:: ያም ሆኖ በአሁኑ ትውልድ አትሌቶቻችን መካከል ጠፍቶ እንዳልጠፋ ከትናንት በስቲያ ምሽት ከከፍተኛ ሙቀትና ወበቅ ጋር ታግለው ጣፋጭ ድል በአምስት ሺ ሜትር ያስመዘገቡ የዘመኑ ጀግኖች አስመስክረዋል:: ድላቸውም ሕብረትና መደጋገፍ የታየበት ኢትዮጵያዊ ድል ሆኖ ያለፉትን ጀግኖች ለማስታወስ የሚያስገድድ ሆኗል:: እአአ 2009 በርሊን ላይ ቀነኒሳ የወርቅ ሜዳሊያ ካጠለቀ በኋላ ወደ አገሩ መመለስ ያልቻለው የ5ሺ ሜትር ድል፤ እነሆ ጊዜውን ጠብቆ ለንደንና ዶሃን ለማከታተልም በቃ። በርቀቱ የኢትዮጵያዊያን ታሪክም ብርቱው አትሌት ሙክታር እድሪስ በተከታታይ ለሁለት ዓመታት ያሸነፈ የመጀመሪያው አትሌት አድርጎታል። ረጅም ጊዜ በቆየው ጉዳቱ ምክንያት ተሳታፊነቱ ያጠራጥራል ሲባል የቆየው አትሌቱ የትላንት በስቲያውን ምሽት ያደመቀ ኢትዮጵያዊ ኮከብ ነበር። ከውድድሩ በኋላ ሙክታር በሰጠው አስተያየትም «ለዓመታት ከገጠሙኝ ተደጋጋሚ ጉዳቶች ለማገገም ጥረት ሳደርግ ቆይቻለሁ። እግሬ ላይ ከአንድ ዓመት በፊት ነው ጉዳት ያስተናገድኩት፤ የሆድ ውስጥ ህመምም ነበረብኝ። በዚህም በደንብ አልተንቀሳቀስኩም፤ ነገር ግን ወደዚህ ከመምጣቴ በፊት የህመም ስሜት ስላልተሰማኝ ለድል መፋለም እንዳለብኝ ለራሴ ነገርኩት። በዚህም ደስተኛ ነኝ፤ እንዲህ ዓይነት ደጋፊዎች ሲኖሩ ደግሞ ታሸንፋለህ» በማለት በአረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ ባንዲራ አጊጠው የከሊፋን ስቴድየም በልዩ ድባብ ስላደመቁት ኢትዮጵያውያን ደጋፊዎች አድናቆትና ምስጋናውን ተናግሯል:: በመሰል ድሎች መኩራት ለኢትዮጵያውያኑ አዲስ ባይሆንም የስታዲየሙ ድባብ ተቀዛቅዟል በሚል እየተወቀሰ ያለውን የከሊፋ ስታዲየምንም ወደ ተለመደ ሞቅታው የመለሱት ኢትዮጵያውያን ደጋፊዎች ለመደነቅ አብቅቷቸዋል። አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ባንዲራ የያዙ እና በእነዚሁ ቀለማት የደመቁት የኳታር ነዋሪ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም የብሔራዊ ቡድኑ ልኡክ በስታዲየሙ ተገኝተው ያደረጉት ማበረታቻ ለውጤቱ መገኘት የራሱን ሚና ተጫውቷል። ይህንንም ዓለም አቀፉን ማህበር ጨምሮ ሌሎችንም ያነጋገረ ነው። ውድድሩን ከመነሻው ለተመለከተ የመጨረሻውን የወርቅ እና የብር ሜዳሊያ ብቻም ሳይሆን የኢትዮጵያውያኑ መታወቂያ የመመለሱንም ፍንጭ ያመላከተ ሆኗል። ለ«አረንጓዴው ጎርፍ» ምክንያት የሆነው የቡድን ስራ እንዲሁም የአገር ክብርን በማስቀደም ድልን ለጓደኛ አሳልፎ መስጠት የታየበትም ነበር፤ የወንዶች 5ሺ ሜትር። የኃይሌ ገብረስላሴ እና ገብረእግዚአብሄር ገብረማርያም እንዲሁም የቀነኒሳ በቀለ እና ስለሺ ስህን ጥምረትም ታይቶበታል ለማለት ያስችላል። ሙክታር እድሪስ፣ ሰለሞን ባረጋ እና ጥላሁን ኃይሌ በመፈራረቅ ሲያሳዩ የነበረው እንቅስቃሴ ለሜዳሊያው መገኘት ከፍተኛ ሚና የተጫወተም ሆኗል። በተለይ የመጨረሻው ዙር ላይ ሰለሞን የሌላ አገር ተፎካካሪ አትሌቶችን በመፋለም ቻምፒዮኑ ሙክታር ወደፊት እንዲወጣ ያደረገበት መንገድ ምስጋና አዝንቦለታል:: በቻምፒዮናው ለአገራቸው የመጀመሪያውን የወርቅ፣ ሁለተኛውን የብር እንዲሁም ዲፕሎማ ደረጃ እንዲገኝ ምክንያት ሆነዋል። ይህንን ቻምፒዮና ልዩ የሚያደርገው ካለፈው ቻምፒዮና በአንድ ደቂቃ የፈጠነ ሰዓት የተመዘገበበት መሆኑ ነው። የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤቱ ሙክታር 12:58.85 የሆነ ሰዓት ሲያስመዘግብ፣ ሰለሞን ባረጋ በአንድ ሰከንድ ዘግይቶ 12:59.70 የሆነ ሁለተኛውን ፈጣን ሰዓት አስጽፏል። በኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች መካከል በመግባት የነሃስ ሜዳሊያውን የወሰደው ካናዳዊ አትሌት ሞሃመድ አህመድ የነሃስ ደግሞ13:01.11 ርቀቱን ለማጠናቀቅ የፈጀበት ሰዓት ነው።አዲስ ዘመን መስከረም 21/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "715f41bfa0826ed07aefad2947b8a5c6" }, { "passage": "ስፖርት ጤንነትን ከመጠበቅና ከመዝናኛነት ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለው ክንዋኔ መሆኑ ይታወቃል። በተለይ አሁን አሁን እያደገና እየሰፋ የመጣው ስፖርትን ለማህበራዊ ኃላፊነትና በጎ ተግባራት ማዋል ዋናውና ተጠቃሽ ዘርፍ ሲሆን፤ በህብረተሰቡ ዘንድ ያለው ተቀባይነት ከፍተኛ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በቀላሉ የህዝብ ንቅናቄን ለመፍጠር እንዲሁም ዓላማን ለማሳካት መቻሉም ውጤታማነቱ በተለያዩ መድረኮች እየታየ ነው። የኮትዲቯራውያን ኩራትና መለያ የሆነው ተወዳጁ የእግር ኳስ ተጫዋች ዲድየር ድሮግባ «የእርዳታው ንጉስ» የሚል ተጨማሪ መጠሪያ ተሰጥቶታል። ይህ ስም የተበረከተለት ደግሞ የበጎ አድራጎት ድርጅት በማቋቋም በሚያደርገው መጠነ ሰፊ እርዳታ ነው። ድሮግባን የመሳሰሉ ሌሎች ስፖርተኞችም ተመሳሳይ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን በመክፈት እንዲሁም ተጽዕኖ አሳዳሪነታቸውን በመጠቀም በዓለም አቀፍ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ይሳተፋሉ። በዚህም በተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ለተጎዱ፣ በበሽታ ለሚሰቃዩ፣ መሰረተ ልማት ለሚያስፈልጋቸው እንዲሁም ወላጅ አልባ ህጻናትን በመደገፍ ምስጉን ለመባል ያስቻላቸውን ተግባራት ያከናውናሉ። ስፖርት የገቢ ምንጭ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ፤ የውድድር አዘጋጆች፣ ክለቦችና ተጫዋቾች ከሚያገኙት ረብጣ ገንዘብ ለበጎ አድራጎት ሥራዎች ማካፈልን ባህል እያደረጉት ይገኛሉ። ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ ዓለማት የበጎ አድራጎት ሥራን ለማከናወን የወጠኑ ውድድር አዘጋጆች የተለያዩ ውድድሮችን ማዘጋጀታቸው እየተለመደ መጥቷል። የውድድር አዘጋጆቹ የተለያዩ ታዋቂ አትሌቶችን በመጋበዝና በማሳተፍ ህዝቡን የማነቃቃትና ገንዘብ የማሰባሰብ እንዲሁም መልዕክት የማስተላለፍ ሥራ ያከናውናሉ። በቅርቡ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በሃዋሳ ከተማ ያከናወነውም ይኸው በጎ አስተሳሰብ ነው። የኢትዮጵያ አንድ መገለጫ እየሆነ ያለው ተቋም ዓመታዊ ውድድሮችን በማዘጋጀት ይታወቃል። ከእነዚህ መርሃ ግብሮቹ መካከል አንዱ በሃዋሳ ከተማ የሚካሄደው የግማሽ ማራቶን የሩጫ ውድድር ሲሆን፤ በዘንድሮው የሩጫ ውድድር ላይም 200 አትሌቶች፣ 200 ጤናቸውን ለመጠበቅ የሚሮጡና የውጭ ሀገር ዜጎች፣ 700 ህጻናት በጥቅሉ 4ሺ የሚሆኑ የከተማዋ ነዋሪዎች ተሳታፊዎች ነበሩ። ከውድድሩ በተጓዳኝም የተለያዩ መልዕክቶች የተላለፉበት እንዲሁም በጎ ተግባራት የተከናወኑበት መርሃ ግብሮች ተካትተዋል። በተለይ በዚህ ወቅት በሀገሪቱ ባሉ ውሃማ ስፍራዎች ላይ የተጋረጠው አደጋ የህልውናም ጭምር መሆኑ ይታወቃል። በደለል መሞላትና በቆሻሻዎች መበከል የሃዋሳ ሐይቅ እየተጋፈጠው ያለው አንዱ ችግር በመሆኑ «የሃዋሳ ሐይቅን እንጠብቅ» የሚል መልዕክት ተላልፎበታል፤ የሩጫው ተሳታፊዎችም ከውድድሩ መካሄድ አስቀድሞ የጽዳት ዘመቻ አካሂደዋል። የውጭ ሀገራት ዜጎች እንዲሁም የከተማ ነዋሪዎች በተሳተፉበት እንቅስቃሴ በርካታ ኪሎ ግራሞችን የሚመዝን ቆሻሻ ተወግዷል። ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከሃዋሳ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር የከተማዋን የቱሪስት መስህብ የመጨመር ሥራ ሌላኛው የውድድሩ ዓላማ ነበር። በዚህም በርካታ የውጭ ሀገር ዜጎችን በሩጫ ውድድሩ ላይ ለማሳተፍ ተችሏል። የቀድሞው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አንጋፋው አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ፤ በርካታ መልዕክቶችን ይዞ በደመቀ ሁኔታ የተካሄደ ውድድር መሆኑን ይገልጻል። ከሃዋሳ ሐይቅና ከግብር መክፈል ጋር በተያያዘ መልዕክቶች የተላለፉበት ነበር። ሃዋሳ ያለ ሐይቁ አሁን ባለችበት ሁኔታ ልትገኝ እንደማትችል የሚጠቁመው ኃይሌ፤ ለማንም ሰው የማይተውና ሁሉም ተባብሮ ሊጠብቀው የሚገባ መሆኑንም ይጠቁማል። ከከተማው ወደ ሐይቁ የሚገቡትን ቆሻሻዎች ህዝቡ እየተከታተለ ሊያስወግድ እንደሚገባ፤ ካልሆነ ግን ሌሎች ሐይቆች ላይ የተከሰተው ሁኔታ እጣ ፋንታው እንደሚሆንም አሳስቧል። ከዚህ በተጨማሪ በውድድሩ ላይ በርካታ የውጭ ዜጎች መሳተፋቸው በቱሪዝም በኩል የራሱን አስተዋጽኦ የሚያበረክት ሲሆን፤ ከተማዋን ምቹ በማድረግ የቱሪስቶች ቁጥር እንዲበራከትና ከዚህም ተጠቃሚ ለመሆን እንደሚቻል አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ይጠቁማል። የበርካታ ብርቅዬ አትሌቶች ማፍሪያ ከሆነችው በቆጂ በርካታ ስመጥር አትሌቶችን በመመልመል አሁን ላሉበት ያደረሱትና የበቆጂ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል አሰልጣኝ ስንታየሁ እሸቱ በውድድሩ ላይ በተጋባዥ እንግድነት ተገኝተው ዕውቅና ከተሰጣቸው በኋላ በውድድሩ ላይ በመሳተፋቸው የተሰማቸውን ደስታ ሲገልፁ« ከሀገር ውስጥ አልፎ በርካታ የውጭ ሀገራት ዜጎችን ያሳተፈው ውድድር፤ ስፖርቱ የሚያድግበት እንዲሁም የውጭ ሀገራት ዜጎች ስለ ኢትዮጵያዊያን የሚያውቁበትና በትክክል የሚገነዘቡበት ነው። በመሆኑም ይህ ዓይነቱ እንቅስቃሴ ለኢትዮጵያ ወሳኝ ነው» ብለዋል፡፡አዲስ ዘመን የካቲት 7/2011ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "015ad8c3835eb7e3e2b1cc91b937a4e2" }, { "passage": "የኦሎምፒክ ችቦ ዘንድሮ ውድድሮቹን ወደ ምታስተናግደው ወደ ሪዮ ዲ ጃኔሮ (Rio De Janero) የብራዚል ከተማ ጉዞ ጀምሯል። ችብው ትናንት አጠር ያላ የማብራት ሥነ ሥርዓት ተደርጎለት ጉዞውን የጀመረው የኦሎምፒክ ውድድሮች ከተጀመሩባት ከግሪክ ከተማ ከኦሎምፒያ (Olympia) ነው። ችቦውን በርካታ የግሪክ ከተሞችን ለስድስት ቀናት አቋርጦ በሚያልፍበት ወቅት አንድ የዚያችን ሃገር ጥገኝነት የጠየቀውን ሦሪያዊ ስደተኛ ጨምሮ፥ 450 ሰዎች ይቀባበሉታል። በግንቦት ወር መጀመሪያ ላይ አስተናጋጇ ብራዚል ከገባ በሁዋላም፥ በ 83 ትላልቅና በ 500 አነስተኛ ከተሞቿ ሲያልፍ 12 ሺህ ሰዎች ይቀባበሉታል። የመጨረሻው ሰው በኦሎምፒክ መክፈቻው እለት በሚደረገው ሥነ ሥርዓት ላይ ችቦውን ማራካና (Maracana) ስታዲየም በተዘጋጀለት ልዩ ሥፍራ ላይ ያኖራል።በነገራችን ላይ ኦሊምፒክ በአንድ የላቲን አሜሪካ ሃገር ውስጥ ሲዘጋጅ የ 2016ቱ በታሪክ የመጀመሪያው ነው። ", "passage_id": "3899ca19ab42c77d93f35d142ca79538" } ]
e067a1ecc1a9d04b55d040cdb3f806bd
f2c16530eff05967a886de0081dad5f7
የሚወዱት -ሲወደድ” ደስ ይላል!
እነ ኒያላና ጓደኞቹ በመወደዳቸው፤ ዋልያና ቤተሰቦቹ አልቀመስ በማለታቸው አኮረፉ አሉ። ሰው የሚወደው ነገር ሲወደድ ደስ ሊለው ነው የሚገባው፤ አይደል? ምን ነካቸው? ሰሞኑን በፀደቀው አዋጅ ምክንያት አኩራፊዎች በዝተዋል ሲሉ ተገረምኩ። የእነ ሀበሻ አድናቂዎች የእነ ግስላ ቲፎዞዎች እንዲያው ምን ነካችሁ? ሰው ወዳጁ ወደላይ ከፍ እንዲልለት በብርቱ ሲመኝ እንዴት የወደዳችሁት ነገር መወደዱን ጠላችሁት ግን? አኮረፉ ‘ለምን? አሉ’ ሲሉኝ እኔ አላመንኩም ነበር። ግን አመንኩ፤ በቢራ መወደድ ማዘናችሁ፤ በሲጃራ ዋጋ ማሻቀብ ማኩረፋችሁ በገጠመኜ እኔም ታዘብኩ። አቤት ግን ግፋችሁ! ቆይ ስንት ሀገራዊ የሆኑ ውድ ውድ ስሞችን ተሸክመው እንዴት እስከ ዛሬ እንደረከሱ ይገርመኛል። ዋልያ የተሰኘ ብርቅዬ እንስሳችን መጠሪያው አድርጎ፣ ኒያላ የተባለው ተወዳጅ ልዩ ብርቅዬ እንስሳን የፓኮው ስያሜ አድርጎ አራክሶ ሲቸበችም ዝም ያልነው እኮ ስያሜያቸውን አይተን እንጂ ውስጡ ያሉትን ጤናን አቃዋሽ ጉዶችን አክብረን አልነበረም። ስለጤፍ መወደድ፤ ስለ ኑሮ ጣራ መንካት ግድ ሰጥቶት የማያውቅ ሰው እንዴት ሲርበው በልቶ፤ ጠግቦ ለሚጠጣው ኦክስጂን ሰልችቶኛል ሲጃራ ነው አምሮቴ ብለው ያኮርፋል? በነገራችን ላይ፤ ሱሰኞቹ “እኛን ብቻ ለምን?” በማለት ሲሞግቱ ነበር አሉ። በጫትና ሌሎች ነገሮች ላይም ታክስ ይጨመር፤ ካልሆነ ከሌላው በተለየ የእኛ መብት ተገፋ፤ በደል ተፈጸመብን” በማለት ሲሟገቱ ከረሙ የሚል ጭምጭምታ ሰምተናል። ስለትውልድ ሲታሰብ፤ የትውልዱን መለወጥ ሀገራዊ ለውጥ መሆኑ ይታመንበታልና ትውልድ ገዳይ፤ ሀገር አጠልሺ የሆኑ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚፈጥሩ ጉዳዮችን ማስቆም፤ አሊያም የሚቀንሱበትን መንገድ ማበጀት ከሀገሬው የሚጠበቅ ነውና ጠቃሚው ተተገበረ። እርግጥ ይህ ሲታሰብ መልካምነቱ የማይካድ፤ ውጤቱም አመርቂነቱ የማይታበይ ሀቅ ነው። ታዲያ ጠጪዎች ይሄንን ማን ጋረደባቸው? ስለ ሀገሩ የሚያስብ፤ ስለ ትውልዱ የሚጨንቀው እንዴት “እኔ ፍላጎቴን ላስታግስ እንጂ ስለሌላው ምን ገዶኝ” ይላል? ሰው ሀገሩንና ህዝቡን ሊወድድ ለውጡንም ሊመኝ ይገባል። ሀገራዊ ለውጥንና እድገትን የወደደ ደግሞ ስለ ሀገሩ መልካም ያስባልና እንዴት መልካም የሆነ ሀገራዊ ነገር ይጠላል? እናም ውዶቼ ሀገራዊ ራዕይ ያለው የትውልድን መልካም ፍሬ ማየት የሚወድድ ጥሩ ያልሆኑ ነገሮችን የሚያርቅ አዋጅ አይደለም ሊያሳድድ ሊደግፍ ይገባል። ትልቅ ሀገራዊ አላማ ያለው ስለ ለውጥና እድገት በእጅጉ የሚመኝ ሲጃራን “እምቢ” አልኮልን “አይ” ማለት ነው ያለበት፤አንድ ታወቂና በዓለም አቀፍ ደረጃ ቁንጮ የሆነ አየር መንገድ በደንበኞች አያያዝና በመስተንግዶው ተወዳጅ ስለሆነ ብዙ መንገደኞች ይመርጡት ነበር። አንድ ሰው ከመኖሪያ አካባቢው ወደ ሌላ አገር መሄድ ይፈልግና ይህን አየር መንገድ ይጠቀማል። በአውሮፕላን ውስጥ አስተናጋጆች ደንበኞችን በልዩ ትህትና እያስተናገዱ ወደአንደኛው ሰው ይጠጋሉ። ቀድሞ የጠቀስነው ተጓዥ አጠገብ የደረሰች አንዲት መልከ መልካም አስተናጋጅ፤ ወደሰውዬው ቀርባ በእጇ የያዘችውን መጠጥና ብርጭቆ ታቀርባለች።የአስተናጋጇ ፍላጎት የደንበኛዋ ጉዞ በፍስሀ እንዲሞላና ሳይሰላች እንዲያሳልፍ ነውና ፈገግታ ተላብሳ አንድ ውድ የአልኮል መጠጥ ከብርጭቆ ጋር አቀረበች። ሰውዬውም እጅግ ትህትና በተሞላበት ሁኔታ ይቅርታ ጠይቆ እንደማይጠጣ ይገልፅላታል። አስተናጋጇ ከዚያ በፊት ይህንን ውድ መጠጥ በፍቅር ይጠጡት የነበሩ ደንበኞቿን እያሰበች በማነፃፀር እየተገረመች ሰውዬውን ትመለከተውና በድጋሚ ጠጋ በማለት “ሌላ አይነት መጠጥ ይሁንልዎ” ብላ ትጠይቀዋልች። ሰውዬው ግን ከአቋሙ ሳነቃነቅ በድጋሚ አለመፈለጉን ይነግራታል።አስተናጋጇ ደንበኛው በሆነ ጉዳይ ተከፍቶ እንጂ ይህንንማ አያልፈውም ነበር በማለት ለአለቃዋ ሄዳ ስለ ጉዳዩ ትነግረዋለች። አለቃዋም ከርስዋ ይበልጥ በመገረም “በሌላ በሚምያር ብርጭቆና ማራኪ በሆነ መልኩ በድጋሚ አቅርቢለት” በማለት ያዝዛታል አስተናጋጅዋን፤ አደረገችው። ግን የተለወጠ ነገር የለም። ይሄኔ አለቅየው እራሱ ቀርቦ ሰውዬውን ማናገር ይጀምራል።“ጌታዬ ችግር አለ? መስተንግዶዋችን አልተመ ቸዎትም? ምን እናስተካክል?” እያለ ትህትና የተላበሱ ተከታታይ ጥያቄዎችን ያቀርባል። ሰውዬው ፈገግታ በተሞላበት መንገድ ምላሹን ሰጠ። “አይ መስተንግዶዋችሁም በጣም ጥሩ ነው፤ ነገር ግን እኔ መጠጥ አልጠጣም” ይለዋል። ይሄኔ ኃላፊው ተገርሞ “እንዴ ለምን?” ብሎ ጠየቀው። ለዚህ ምላሽ ግን የሰጠው መልሶ እራሱን በመጠየቅ ነበር። “እስኪ ለኔ ልትሰጠኝ ካሰብከው ፊት ለፊት ባለው በር ከፍተህ ግባና ለፓይለቱ ስጠው በኔ ፋንታ ይጠጣ” ብሎ ጠቆመው።ይሄኔ ኃላፊው “እንዴ! እሱማ እንዴት ይጠጣል? ይሄን ማደረግማ አይችልም የስንት ሰዎችን ህይወት አደጋ ላይ ሊጥል ይችላል። ስለዚህ እሱ የመጠጥ ሽታም ሊደርስበት አይገባም።” በማለት ፓይለቱ በመጠጣቱ ሊደርስ የሚችለው አደጋ ዘረዘረ። ተጓዡም የሚፈልገው እንዲህ እንዲለው ነበርና በመልሱ ላይ የራሱን አስተያየት በማከል የማይጠጣበት ምክንያት ተናገረ። “ወዳጄ እኔ የራሴ የሆነ ልዩ ዓላማ አለኝ አላማዬን ከስኬቱ እንዳደርስ ጥንቁቅ መሆን አለብኝና “ፈፅሞ አልጠጣም” ያልኩት ለዚህ ነው። በማለት መለሰለት።እናም ዓላማ ያለው፤ እሩቅ መጓዝ ያሰበ እርግጥም እራሱን ሆኖ የትኛውም ቦታ ይደርሳል። ሰሞኑን የወጣውን የኤክሳይዝ ታክስ ተከትሎ በመጠጥና በዘር ማንዘሮቹ፤ በሲጃራና በግብረ አበሮቹ ላይ የተደረገውን የታክስ ጭማሪ ጥቅም በትክክል ከተረዳን ጠጪዎችንና አጫሾችን ቢያስከፋም እነሱኑ የሚያድን መራራ መርፌ ነው። እናም በደንብ መውጋት/መወጋት ነው። ኧረ እንዲያውም ከፍ አድርጎ። ቸር ይግጠመን! አዲስ ዘመን የካቲት 16/2012ተገኝ ብሩ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=27764
[ { "passage": "የዕድሜውን አብላጫ ጊዜ በራዲዮ ፕሮግራም አቀናባሪነት ነው የሰራው። ከሰላሳ ዓመታት በላይ የአሜሪካ ድምጽ አገልግሎቱ በኋላ በጡረታ ዕድሜው ሙሉ ቀልቡን የሰጠው ሙዚቃ ጥሩ አድርጎ የተቀበለው ይመስላል።ስለ ሙዚቃ ሥራዎቹ .. ስለ አዲሱ የሕይወት መንገዱ ሊያወጋን ቀጠሮ አክብሮ ብቅ ብሏል።", "passage_id": "495a7d390642d0968760a0c33c96849f" }, { "passage": "በሰፈራችን ያገኙትን መመረቅ የሚወዱ አንድ አባት ነበሩ። «ደግሞ ይስመርላችሁ…አምላክም ይስማኝ እንጂ ልጆቼን እናንተን ለመመረቅ ለምን ብዬ እሰስታለሁ?» ይላሉ። ፈገግ ካሉላቸው መመረቅ ነው፣ ዞር ካሉላቸው መመረቅ ነው፣ አቤት ካሏቸው መመረቅ ነው። ነጋዴ አይደሉም፤ ሽበት የተጎናጸፉ፤ እድሜ ያስከበራቸው ደግ አባት ናቸው። እኛ ደግሞ ሲመርቁ እንዳያመልጠን፤ ቶሎ አሜን አሜን ማለት።አንድ ወዳጃችን ታዲያ አብዝቶ ይወዳቸዋል። ምርቃታቸው የሠራለት ነገር ኖሮ እንደሆነ አላውቅም፤ ብቻ እኛ ጓደኞቹ ከምንወዳቸው በላይ ነው እርሱ የሚወዳቸው። እናም ይህን ፍቅሩን ለመግለጽ በዓል አስታክኮ፣ የእኛን ቦርሳና ኪስ በመዋጮ ስም ፈትሾ፤ ነጣ ያለ ጋቢ ገዝቶ አበረከተላቸው። መረቁት! መቼም የእኛ ነገር! ጥቅም ሲያገኙ አብዝተው የመረቁት ይመስለን ይሆናል? ግን አይደለም። እንደወትሮው ሳያደሉ፤ ሳይጨምሩ ወይም ሳይቀንሱ መረቁት። «አትጣ! አግኝ!» አሉት።ምርቃታቸው እያንዳንዱ ፍሬ እንዳያመልጠው ከስር ከስር በ«አሜን» እየለቀመ ቆየና፤ «አባብዬ… እንደው ይሄ አትጣ አግኝ ብለው የመረቁኝ ነገር ምኑን ነው?» አላቸው። እርሳቸውም ነገሩ ጨዋታ መስሏቸው ፈገግ ብለው፤ «ምንስ ቢሆን የኔ ልጅ? ሰላምም ቢሆን ጤና፤ ፍቅርም ቢሆን አንድነት፤ በጎውን የልብህን መሻት ሁሉ እንድታገኝ ነው ምርቃቴ» አሉት።እርሱ ግን ፊቱን ቅጭም አድርጎ፤ «እንደው ወደላይ አስፈጻሚዎች ጋር ሲደርስ ለመምረጥ እንዳይቸግራቸው፤ «ትራንስፖርት አግኝ…ታክሲ አትጣ!» ብለው ለይተው ቢጠቅሱልኝ ብዬ ነው» አላቸው። ነገሩ ቀልድ ነው ተብሎ በዛን ሰሞን በሰፈራችን እንደ ጉድ ተሳቀ። እርሱ ግን ከልቡ ነበር፤ ተማሯላ!\nባለፉት ቀናት የነዳጅ መጥፋት ድፍን አዲስ አበባ እንዴት የገበያ ማዕከሏን መርካቶን እንደመሰለች አላያችሁም? ግን እኔ የምለው፤ ለነዳጅ እንዲህ ከሆንን…ሰላም ጨርሶ የጠፋች ቀን ምን ሊውጠን ነው። ነዳጅና ሰላም ምን አገናኛቸው እንዳትሉኝ። ሰዎች! ሁሉም ነገር ፖለቲካ መሆን የለበትም። ግን አንዳንዴ አርቆ ማሰብ ያስፈልጋል ብዬ ነው። አርቀሽ አስበሽ ልብሽ ውልቅ ብሏል! በሉኛ! ይሁን እተወዋለሁ።\nግን እውነቴን ነው፤ አትጡ! አግኙ። ለምን? በትራንስፖርት ማጣትና ማግኘት መካከል ያለውን ሰፊ ልዩነት ስትመለከቱ ራሳችሁን ታያላችሁ። ባለመኪና ከሆናችሁ ደግሞ እኛን መኪና አልባዎቹን ታዩናላችሁ። ለምሳሌ አሁን በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ቀን ረዥም ዘንዶ የሚያስንቅ ሰልፍ ይዘን አውቶብስ ጥበቃ ላይ ታድመናል።ከስንት አንዴ የሚመጣውን ባስ «ሰለፉ ከእኔ ነው የሚጀምረው» በሚል ንትርክ ጥቂት አቆየነው። ከዚህ ቆይታ በኋላ ሰላማዊና ሰልፋዊ ግፊያ ተደርጎ ተሳፈርን። ማን እንደመረቀኝ ባላውቅም ወንበር አገኘሁ። እማማ አፍሪካ! በየክፍሏ ለወንበር የሚራኮትባት መቼስ ብዙ ነው። ብቻ እድሜው ገፋ ያለ፤ «ኧረ እርስዎ ይቀመጡ» የሚባል ዓይነት ሰው በአካባቢዬ ስላልነበር ተደላድዬ ሃሳቤን ጥዬ ተቀመጥኩ።\nታዲያ ከገባን በኋላ፤ «እዛጋ ተጠጉ…እዚህ ጋር አለፍ በሉ» ልመና ጀመረ፤ ውጪ ያለው ተሰላፊ። «ከዚህ በላይ ወዴት ልጠጋ?» ንጭንጭ ያሰማል ተሳፋሪ። «ቆይ ሰው ሌላ ባስ አይጠብቅም እንዴ? ሞልቶ እያዩት እዚህ ተፋፍኖ ለመሄድ መጋፋት ምንድን ነው?» ይላል፤ ለባሱ መጨረሻኛ ሆኖ የገባው ሰው። ሁሉም ብቻ የየራሱ የሆነ አስተያየት ይሰጣል።ብቻ መሙላት አይቀርም ባሱ ሞልቶ ተንቀሳቀሰ። ልክ ሲንቀሳቀስ ባሱን የተሳፈረ ሁሉ በመስኮቱ አሻግሮ የተሰለፈውን ሰው እያየ ከንፈሩን መምጠጥ ይጀምራል። «በስመ አብ ሰልፍ! አሁን ስንት ሰዓት ነው ይህ ሁሉ ሰው ቤቱ የሚገባው?» ይላል። ተጋፍቶና ተጣልቶ በባሱ የተሳፈረው ሰው፤ ለገፋውና ለታገለው ለጣለውም ሰው መልሶ ያዝናል።እናላችሁ! መቼም ሀብታም ሰው ነው ለምስኪን ደሃ ሲያዝን የሚያምርበት፤ እኛ ቀንቶን የተሳፈርን ሰዎችም ገና ሰልፍ ላይ ላሉት ሀዘን ገባን። እኔም ራሴ አዘንኩ፤ እውነት እላችኋለሁ ሰልፉ ላይ እኔ የነበርኩ እስከማይመስለኝ ድረስ ነው የተሰለፉት ሰዎች ያሳዘኑኝ። አሃ! እኔ አገኘሁኛ! ይሄኔ ይህ ተከታዩ ሃሳብ ብልጭ አለልኝ፤ ለካ መተሳሰባችንን የሰረቀው ድህነት ነው። ብዙ አውቶብስ ቢኖረን ኖሮ፤ መንገዱ ቦርቀቅ ቢልልን ኖሮ፤ ከየምንሠራበትና ከየምንማርበት አፈስ አድርጎ ካሰብነው የሚያደርሰን ባለመኪና ዘመድ ቢሰጠን ኖሮ፤ መንገዱን እንጃ እንጂ ራሱ መኪና ቢኖረን ኖሮ፤ ይሄ ሁሉ ይኖር ነበር? አይኖርም።አትጡ አግኙ…አንጣ እናግኝ ያልኩት ለዚህ ነው። በየትራንስፖርቱ ማንነታችን እየታየ ይመስላል። በዛ ቦታ መታገስ የቻለ ትዕግስቱ፣ በዛ ቦታ መሳደብ የቻለ ድፍረቱ፣ በዛ ቦታ መጋፋት የቻለ ጥንካሬው…ሁሉም ቁልጭ ብሎ ይታያል። በቃ! ሰውን የምታውቀው አብረኸው ረጅም ጉዞ ስትሄድ ነው ምናምን የሚሉት ነገር ተለዋጭና አማራጭ አግኝቷል። ወይም «ጓደኛህን ንገረኝና አንተነትህን ልንገርህ» እንደሚባለው፤ «ረጅም የታክሲ ሰልፍ አብሬአቸው ልሰለፍና ስለሀበሾች እነግርሃለሁ» የሚል ብሂል አያይዞ መናገር ይቻላል።«ሰላምም ቢሆን ፍቅርና አንድነት፤ ሊፍት የሚሰጥ ክፉ ያልገጠመው ደግ ባለመኪና፣ ባዶ ታክሲና አውቶብስ፣ ቅድሚያ ለሴት የሚሉ የታክሲ ተራ አስከባሪዎች፣ ስታረፍዱ የማይቆጣ…በጊዜ ስትወጡ የማይከፋው አለቃ፣ መኪና ገዝቶ የሚሰጥ ዘመድ፣ በምትንቀሳቀሱበት መስመር የሚሠራ የምታውቁት የሚያውቃችሁ ሹፌር ወይ ረዳት…የመሳሰሉትን ሁሉ አግኙ፤ ይስጣችሁ። እንዲሁም ጠላት አንዳንዴ ያስፈልጋልና እርሱንም ጠራርጎ አያሳጣችሁ።» የሰፈራችን መራቂ አባት፤ አባባ፤ የጓደኛችን ጥያቄ ቀልድ እንዳልነበረ ከተረዱ በኋላ ነው እንዲህ መመረቅ የጀመሩት። ሰላም!አዲስ ዘመን ጥር 12/2011ሊድያ ተስፋዬ", "passage_id": "09fbcd487380c53fa976508cb2074e7c" }, { "passage": "ዝቅ ማለት ከፍታ ላይ ያደርሳል እንዴ? አንድ ዓረፍተ ነገር ሰምተነው ግራ የሚያጋባን ጉዳይን ከመግለፅ በላይ የሆነን ቁም ነገር የጨበጠ ሆኖ ስናገኘው መመርመር እንጀምራለን። ከፍታ ላይ ለመገኘት ዝቅ ብሎ መጀመር የተሻለ ቦታ ላይ ለመገኘት ቀድሞ የሚያሽልን መጠጋት ግድ ይላል። በነገራችን ላይ ውዶቼ ለማትረፍ ተብሎ ካለ ላይ መቀነስ መሰጠትን ይጠይቃል። ሁሉም እኮ የመስጠት ጣዕምን አይረዳም።\nእራስን አሸንፎ ከስግብግብነት መላቀቅን ከራስ ወዳድነት ስሜት መመንጨቅን ይጠይቃል። ይህ ደግሞ በመሰጠት ውስጥ ባለ መልካምና እራስን\nከሌላው ቀጥሎ ማየትን ቀድሞ ከራስ ሌላ መኖርን ይፈጥራል። አቤት የዚህ ስሜትና ተግባር ጣዕሙ። እራሱን ለሌሎች ደስታ ምክንያት\nበመሆን ጣፋጭ የሆነን ደስታ ማግኘት ምንኛ መታደል ነው።እኛ ጋር ያለ ውዳቂ ነገር ሌሎች ጋር\nየማይገኝና ውድ መሆኑ የማናውቅ ብዙ ነን። እኛ ተርፎን የምነደፋው ምግብ ብዙዎች ሽታው እንኳን እንደራቃቸው የማናስተውል በዝተናል።\nእያለን መስጠትን ካለመድን ስናጣ መቀበል እናውቅበት ይሆን እንዴ? የማይሰጡ እጆች መቀበል ይከብዳቸዋል። መስጠት ቁስን ብቻ አይደለም።\nበጎ ሐሳብ የሚለውጥ ሃሳብ አገር እና ሰውን ሊያቆም የሚችል ሁነኛ በጎ ተግባርም መስጠትን ይገልፃል። በእርግጥ መስጠት ከመቀበል ቢልቅም\nበመስጠት ውስጥ የሚገኘው መንፈሳዊ ጠቀሜታ ተቀባይ ባልጠፋ ያሰኛል። እያለን መስጠትን የራቅነውን ያህል ስናጣ የምንቀበለው ይርቅብናል።\nመስጠት ለመልመድ ከሌለው የሚሰጥ ካጠረው ላይ ቆርጦ ለሌላ የሚለጥፍ ስናይ እራሳችንን እንድናይ እኔስ ምን ላይ ነኝ? ያለሁት የሚል\nጥያቄ እንድናነሳ ያደርገናል። ካለ ላይ መስጠት የሚቀለው ያህል ከሌላ ነገር ላይ ቀንሶ እንካችሁ ማለት ይገዝፋል። ከሌለ ላይ መስጠት\nከባድ ነው፤ ነገር ግን መስጠት ያለው ፋይዳ ላወቀ ይገዝፍበታል። የበጎ ተግባር ያህል ውስጥን ሰላም የሚያስገኝ፤ የመልካም ሥራ\nያህል ውስጥን የሚያድስ ተግባር ከወዴት ይገኝ ይሆን? አንዳንዱ ሰጥቶ የማይጠግብ፣ በጎ ምግብር አድርጎ የማይሰለች ለሰው ኖሮ የማይደክም\nየሆነው የመስጠትን ጣዕም በደንብ ስለገባው ነው።እርግጥ መስጠት ወይም ደግነት እኛ ኢትዮጵያዊያን የማንታማበት ጉዳይ ሆኖ አብሮን ከርሞ አሁን ላይ\nያረጀብን ቢመስልም የበጎነት እርጅና ወደ ሞት እንዳያመራ በአንዳንድ ተንከባካቢዎች ዛሬም ፈክቶ ይታያል። እዚህች አገር ላይ በበጎነት\nስማቸው የናኘ በደግነት ትልልቅ ምግባሮችን የፈፀሙ ኢትጵያዊያን መርሳት ይከብዳል። ደጋግ ልቦች ደጋግ ነገሮች ሁሌም ያሳያሉ። ሰሞኑን በማህበራዊ ገፆች አንድ ጉዳይ ብዙዎች ሲቀባበሉ አንዳንዶችንም ልብ የነካ ተግባር በአንድ\nኬኒያዊ የጎዳና ተዳዳሪ ከሌለው ላይ በመቀነስ ለሰው ህይወት መትረፍ ምክንያት ስለሆነ ታደጊ የተሰራጨው መረጃ በእርግጥም የደግነት\nጥግ የበጎነት ያልተገደበ ድንበር ያመላከተ ነበር። ጉዳዩ እንዲህ ነበር። ምስኪኑ የጎዳና ተዳዳሪ የሰራው ድንቅ ሥራ ይህ ነበር።\nስሙ ጆን ይባላል። የዕለት ጉርሱን ለምኖ በረንዳ የሚያድር ምስኪን ህፃን ነው። ታዲያ ጆን አንድ\nዕለት እንደለመደው ትራፊክ መብራት ላይ መኪኖች ሲቆሙ በመስኮት ሄዶ መለመኑን ተያያዘው። ከበርካታ መኪኖች ገንዘብ ተቀብሎ ወደ\nአንዱ መኪና በመስኮት እጁን ይዘረጋል።ለዚህ ታሪክ መከሰት ዋንኛ ጉዳይም ይሄው ለዕርዳታ የዘረጋው እጁ ያስከተለው ጉዳይ ነበር።ህፃኑ ጆን እጁን ሲዘረጋ የመኪናው መስኮት ሲከፈት ግላዲ ካማዳ ከተባለች ሴት ጋር ፊት ለፊት ይተያያል።\nህፃኑ አንድ ነገር ያያል እናም ግላዲ ካማዳ ያረገችውን የኦክስጅን መተንፈሻ “ምንድነው?” ብሎ ይጠይቃታል። እሷም በሰው ሰራሽ\nመተንፈሻ ኦክስጅን የምትተነፍስ አይኗም በቅጡ የማያይ በእግሯ መንቀሳቀስ የማትችል በየዕለቱ ጤና ፍለጋ ሆስፒታል የምትንከራተት\nመታከሚያ ገንዘብ ያጣች 7 ዓመት ሙሉ በዚህ በሽታ የምትሰቃይ ምስኪን ሴት መሆኗን ትነግረዋለች። ይህንን ያየው የጎዳናው ህፃን ጆን እንባውን መቆጣጠር አቅቶት ለልመና የዘረጋውን እጁን ሰብስቦ እጁን\nዘርግቶ ከሌሎች ያገኘውን ጥቂት ገንዘብ ታከሚበት ብሎ ይሰጣታል። እንባውና ሁኔታው የገረማቸው መንገደኞችም በሁኔታው ተደንቀው የልጁን\nየሃዘን ገፅታ በምስል አስቀሩት። በዚህም አላበቃም የህፃኑ ምስል በፌስቡክ ይለቁታል። ከፎቶው ጋር አብረው ልጁ ምን አይቶ እንዳነባ\nበምን ልቡ እንደተነካ ጽፈው ፎቶውን ያጅቡታል። ድፍን ኬንያ ይህንን ምስል ተቀባበለው። ሁሉም የልጁ ሐዘን አሳዘነው። ይህ ልጅ ምንም ሳይኖረው የዳቦ\nመግዣውን ከሰጠ እኛስ? የሁሉም ጥያቄ ሆነ። ስለ ጉዳዩ ተወራ፤ ስለ ችግርና መፍትሄው ተመከረ፤ በመጨረሻም ለህክምና የተጠየቀችውን\n4 ሚሊዮን ሽልንግ ለመሙላት ሁሉም ያለውን እንካችሁ አለ። ግላዲ በዚህ በጎዳና ህፃኑ ጆን ምክንያት ለህክምና የሚሆናት ገንዘብ በህዝብ መዋጮ ተሟልቶ ወደ ህንድ\nተጉዛ ታክማ ኦክስጅኗን ጥላ ዛሬ በነፃነት፤ በመታገዣ ሳይሆን ተፈጥሮ በሰጣት ትተነፍሳለች፤ ትንቀሳቀሳለች። እንግዲህ እንዲህ ነው፤\nለመስጠት የግድ ሀብታም መሆን አይጠበቅብንም። ልስጥ ብሎ የተነሳም የሚሰጠው ፈፅሞ አያጣም። በጎ ሐሳብም ቢሆን ሌላን የሚያንፅ\nሌላውን የሚያቆም ነውና። እኛ መልካምነትን\nተላምደን ወደ ሌሎች ማስረፅና ለሌሎች መልካም ገጠመኝ ምክንያት እንሆን ዘንድ፤ መልካምን ነገር አቅማችን በፈቀደው መልኩ እንተግብር።\nምን አልባት አቅማችን ለመተግበር ካላበቃን፤ መልካም ነገርን ማዘዝና በበጎ ሐሳብ ጉዳዮች መግለፅ እንልመድ። ለመልካም ተግባር ማነሳሳት\nካልቻልን ቢያንስ መልካም ነገር መመኘት የምናዘወትረው ተግባር ቢሆን ዓለም ምንኛ በቀናች ነበር። ደጋግ ዘመኖች እንዲመጡ በጎዎችን\nያብዛልን አበቃሁ። ቸር ይግጠመን።አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2012 ተገኝ ብሩ", "passage_id": "73bfd82cb831875166f2390a7e012ed6" }, { "passage": "«ጉዳይዎን እንደ እርስዎ በመሆን ላይ ታች ብለን እናስፈጽማለን። ለስራዎ አጋርና አማካሪ የሚያስፈልግዎ ከሆነም ቀን ከሌት ሰርተን የስኬትን ቁልፍ እናስጨብጥዎታለን»፤ እንዲህ ዓይነት ማስታወቂያዎች አዲስ አይደሉም። ገንዘብ በመክፈል ብቻም በተለያዩ ምክንያቶች እኛ መፈጸም ያልቻልናቸውን ጉዳዮች ያለሃሳብ መከወን የሚቻልበት ጊዜ ላይ ቆመናል። በየዕለቱ ፍጥነቷ እየጨመረ በመጣው ምድራችን ኑሮን ለመግፋት ፉክክር ከመግጠም ባሻገር አማራጭ የለም። ለስራ የሚሰጠው\nሰዓት ከፍተኛ በመሆኑም፤ ቤተሰብን ለመምራት፣ የአገልግሎት ሂሳብ ለመክፈል፣ ፍጆታን ለማሟላት፣ ለማህበራዊ ጉዳይ እና ሌሎች ስራዎችን ለመከወን ግብ ግብ ውስጥ መግባታችንንም እያንዳንዳችን ራሳችንን መታዘብ በቂ ነው። ታዲያ ጊዜን ለመቆጠብና እጅግ አስፈላጊ ለሆነው ጉዳይ ቅድሚያ ለመስጠት ሌሎቹን ስራዎች በአደራ ለሌሎች መስጠት አስፈላጊ ነው። የሰው ልጅ በምድር ሲኖር ከሚያስተናግዳቸው ተፍጥሯዊ ባህሪያት መካከል አንዱ ፍቅር ነው። ፍቅር እንደየ አፍቃሪው በተለያየ ሁኔታ ሊከሰት ይችላል፤ እንደ አመጣጡ ለመመለስም የአፍቃሪው ወይም ተፈቃሪው ባህሪው ወሳኝ ነው። አንዳንዱ ደፋር በግልጽ ተናግሮና አሳምኖ አሊያም በተለያየ ሁኔታ ስሜቱን ገልጦ የሚወደውን ሰው ከእጁ ያስገባል። ሌላው ደግሞ በአይናፋርነት መናገር ባለመቻሉ ሲማቅቅና እንደሚመኘው ፍቅሩን በጊዜ ለማጣጣም አይችልም። መቼም እዚያ ስለ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እዚህ ደግሞ ስለ ፍቅር የምታወሪው ምን አገናኝቷቸው ነው ሳትሉኝ አልቀራችሁም። ሁለቱን ጉዳዮች ያገናኛቸው የሰሞኑ የኦዲቲ ሴንትራል ዘገባ ነው። ነገሩ ግራ አጋቢ ቢሆንም ለአንዳንዶች ግን እፎይታን የሚሰጥ አገልጋይ ተቋም በጃፓን በስራ ላይ ውሏል(ለግልጋሎቱ ግን ገንዘብዎን ሆጨጭ ማድረግዎ የግድ ነው)። «ኮኩናቪ» ሁለት የጃፓን ቃላት በጥምረት የፈጠሩት ቃል ሲሆን፤ «በፍቅር ግራ መጋባት» የሚለውን ፍቺ ይሰጣል። ይህንን ትርጓሜ ይዞ የተመሰረተው ኮኩናቪ የተሰኘው ተቋምም፤ አፍቃሪን ከተፈቃሪ የማገናኘት (የተቀደሰ ተግባር ነው መቼም) አገልግሎት ይሰጣል። ጃፓናዊያኑ አፍቃሪዎች በፍቅር የተንበረከኩለት ተፈቃሪ ፊት ደርሰው ስሜታቸውን መግለጥ ከተሳናቸው፤ የሚጠበቅባቸው 260 ዶላር ብቻ መክፈል ነው። ኮኩናቪም እሳት በላሱት ሰራተኞቹ የፍቅር መልዕክቶችን በመላክ፣ ደብዳቤዎችን በመጻፍ እንዲሁም የተፈቃሪዋን/ውን ልብ ለማሸነፍ የሚችሉ ነገሮችን ይከውናል፤ ከተፈቃሪ ለሚሰጥ ምላሽም አፍቃሪውን ወክሎ መልስ ይሰጣል። ገንዘቡን ወደ 530 ዶላር ማሳደግ ከቻሉም ከመልዕክት ልውውጡ በተጓዳኝ አፍቃሪው አይነጥላውን ገፎ ደፋር እንዲሆን የሚረዳው ምክር በባለሙያዎች ይሰጠዋል። እንዲህ ዓይነቱ ስራ ሲከናወንም መረጃዎችን በመመልከት ያሉት ለውጦች ይመዘናሉ፤ በዚህም ስራው ስኬታማ መሆኑ ታይቷል። አገልግሎቱን ያገኙ አፍቃሪዎችም በተቋሙ ይፋዊ ማህበራዊ ድረ ገጾች ላይ ጭምር በድፍረት ስኬታቸውን በመመስከርም አረጋግጠዋል። «እርዳታቸውን ፈልጌ ወደ ኮኩናቪ በማምራቴ ደስተኛ ነኝ፤ ምክንያቱም በፍቅር ግራ መጋባቴ በስኬት አልፏል። በስራቸውም እጅግ ተደንቄያለሁ» ስትል አስተያየቷን የሰጠችው የ23 ዓመቷ ወጣት ናት። በዚህ ወቅትም አገልግሎቱን ለማግኘት ወደ ተቋሙ የሚያመሩ ሰዎች ቁጥር እያደገም ነው ተብሏል። በጃፓን መሰል አገልግሎት ሰጪዎች እየተስፋፉ ሲሆን፤ ከዚህ ቀደም የስራ መልቀቂያ ለማስገባት የአለቃቸውን ዓይን ለማየት ለሚፈሩ ሰዎች አገልግሎት የሚሰጥ ተቋም መኖሩን ድረ ገጹ ዘግቦ ነበር። ኮኩናቪ ግን በመገናኛ ብዙሃን ራሱን ሲያስተዋውቅ «ጭንቀትዎ ጭንቀታችን፤ ፍቅርዎም ፍቅራችን ነው» የሚል አይመስላችሁም?አዲስ ዘመን የካቲት 11/2011ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "65463c851141f31667ae147bceed438e" }, { "passage": "ጥበብ ባለቤትዋን ስታገኝ ትፈካለች።ከጠቢብ ጋር ስትገናኝ እንደ ባቢሎን ወንዝ ጅረቶች ኩልል ብላ በመንቆርቆር ደስታን ታጎናፅፋለች። እርግጥ ግሩም ለትወና ትወናም ለግሩም ተባብለዋል። እርሱና ጥበብ በአጋጣሚ ተገናኝተውና ተሸናኝተው ልዩ ውህደትን ፈጥረዋል።በፈጣሪው ልቦና ተወልዶ፣ በምናብ ፈጠራ ተሰናስሎ የዓለምን ሌላ መልክ ሊገልፅ የተፃፈ የፊልም ጽሑፍ ከግሩም ኤርሚያስን ጋር ከተገናኘ ሕይወት ይዘራል። ወታደር ሆኖ ፊልም ላይተውን ቢባል ወታደሩን ሆኖ የምታገኙት አዲስ አበባ ተክለ ሃይማኖት አካባቢ ተወልዶ ያደረው ግሩም ወታደር ሆኖ ፊልም መስራት ሳይሆን የእውነት ወታደር መሆንን አጥብቆ ይመኘው የነበረ የልጅነት ህልሙ ነበር። ህይወት በራስዋ ዑደት መርታ ዛሬ ትወና ላይ አንግሳው አረፈች። ጥበብ ያማረ ዙፋን የሚሰጣት ስታገኝ በልዩ ግርማ ትነግሳለች።እስዋም ውለታ ቢስ አይደለችምና ስለስዋ ብዙ የሆነን መርጣ፣ የለፋላትን አክብራ፣ ያሳደጋትን ከፍ አድርጋ ልዩ ክብርን ትቸራለች። ፀባየ ሰናዩ አርቲስት ግሩም ኤርሚያስ ከፊልም አለም ስራና ስኬቱ ባለፈ የእረፍት ጊዜ የትና በምን? እንዴትና ከማን ጋር ያሳልፋል? ማህበራዊና ቤተሰባዊ ህይወቱ ምን ይመስላል? … በሚሉት ዙሪያ ገባ ወግ እያወጋን ቆይታ አድርገናል። የስኬት ማሳያዎች ከ20 በላይ ፊልሞች ላይ በትወና ተሳትፎ ባሳየው ድንቅ ችሎታ የተለያዩ ሽልማቶችን የግሉ አድርጓል።ከእነዚህም ውስጥ በአምስተኛው የኢትዮጵያ ፊልም ፌስቲቫል ምርጥ ወንድ ተዋናይ (በትዝታህ)፣ በስምንተኛው የኢትዮጵያ ፊልም ፌስቲቫል ምርጥ ወንድ ተዋናይ (በ400 ፍቅር)፣በሁለተኛው ጉማ አዋርድ ምርጥ ወንድ አክተር ምርጥ አክተር (በጪስ ተደብቄ)፣ በአስረኛው የኢትዮጵያ ፊልም ፊስቲቫልና በጉማ አዋርድ በተመሳሳይ ምርጥ ወንድ አክተር (በላምባ)፣ የአድማጮች የዓመቱ ምርጥ አክተር በተከታታይ በዛሚ 90.7 እና በሸገር ኤፍ ኤም ለዛ አዋርድ ላይ ተሸላሚ በመሆን በፊልም መስክ በተከታታይ የነገሰ የጥበብ ፈርጥ ነው። የመዝናኛ ምርጫ ስመ ጥሩ አርቲስ በናፍቆት የሚጠብቀው ከራስና ከቤተሰቡ ጋር በልዩ ሁኔታ የሚያሳልፈው ልዩ ቀን አለ፤እሁድ።እውቅና ሲጨምር ኃላፊነት ሲበረክት ብዙ ማረፍ ወደ ብዙ ትጋት ይቀየራል።ታታሪው ግሩም በእሁድ አይደራደርም ለራሴና ለቤተሰቤ የምሰጠው ልዩ ቀን ነው።“ከባለቤቴና ከልጆቹ ጋር የማሳልፈው መልካም ጊዜዬ ነውና እጅግ እወደዋለሁ” ይላል። አንዳንዴ ከከተማ ወጣ ያሉ ተፈጥሮዓዊ ቦታዎችና መዝናኛ ስፍራዎች በአብዛኛው ደግሞ ቤት ውስጥ የእረፍት ጊዜውን የሚያሳልፈው ግሩም ልቦለድ መጽሐፍቶችን ማንበብ፣ ፊልሞችን ማንበብ፣ ከሙያው ጋር የተገናኙ ነገሮችን ማገላበጥ ከቤተሰቡ ጋር ጨዋታና ውይይቶችን ማድረግ፤ ከልጆቹ ጋር አብሮ ማሳለፍ የዕረፍት ሰዓቱን ያማረ የሚያደርጉለት ተግባራቶቹ ናቸው። በተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ንቁ ተሳታፊ የሆነው ግሩም በእረፍት ቀኑ ከቤተሰብና ከወዳጆቹ ጥየቃ የሚተርፈው ጊዜ ከልጅነቱ ጀምሮ እጅጉን የሚወደው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማዘውተር ተለምዶዓዊ ተግባሩ ነው።ግሩም ከእውቅናው በፊት የነበረው ማህበራዊ ህይወቱ፣ ባህሪውና የአናኗር ልምዱ አሁንም በዚያው መልክ ያስቀጠለ በዝና ምክንያት ማንነቱን ያልዘነጋ መሆኑን ብዙዎች ይመሰክሩለታል። ምግብና ልብስ የለበሰው ሁሉ የሚያምርበት ግሩም ሲያሻው ጨርቅ ሱሪ ከሸሚዝ ጋር ሲፈልግ ካኔቴራ ከጅንስ ጋር ወቅቱን ባገናዘበ መልኩ ይለብሳል።የልብስ ሳጥኑን ሲከፍት ይህ አሪፍ ነው ብሎ ያመነበትን ይመርጣል።በአለባበስ ሁለገብ ነኝ የሚለው አርቲስቱ ወቅቱን በጠበቀ ልብስ መዘነጥም ልምዱ መሆኑ ይናገራል። ከአያቱ ጋር ያደገው ግሩም ድጋሚ የመፈጠር ዕድል ቢያገኝ ኢትዮጵያዊ እንጂ ሌላ መሆንን ፈፅሞ አይፈልግም። ኢትዮጵያዊ የባህል ምግቦች ደግሞ ምርጫዎቹ መሆኑን ይናገራል።ከልጆቹ ምግብ አብስለህ አብላን ተደጋጋሚ ጥያቄዎች ቢቀርብለትም ሆኖለት አያውቅም።ባለሙያ ሚስቱ እንዳሰነፈችውና በእርስዋ ተከሽኖና ጣፍጦ የሚቀርብለት ምግብ ለምዶ ማብሰል ቀርቶ መሞከር እንኳን እንደሚያዳግተው ይናገራል።ጥሬ ስጋ (ቁርጥ)፣ ሽሮ በቃሪያ አልያም ደግሞ ጎመን በሚጥሚጣ ብቻ ምግቦቹ የሚያቃጥሉ ነገሮች ቀመም ተደርገው ከቀረቡ ግሩም አጣጥሞ የሚመገባቸው መሆኑን ደጋግሞ ይነግሮታል። የአርቲስቱ መልዕክት “እኛ ኢትዮጵያዊያን ውስጣችን የታነፀው በትብብር መንፈስ ነው። አንድነትና ትስስራችን በአብሮነት እንዳይላቀቅ ሆኖ የተጋመደ ነውና አንዳችን ስላንዳችን በመተሳሰብ ይህን ጊዜ ማለፍ ግድ ይለናል።” ምክንያታዊ መሆን እጅጉን የሚያምነው ግሩም “የምታወራው ከሌለህ እጅህን አታውጣ”የሚለው አባባል እነደ ህይወት መርሁ ይጠቀምበታል። አበቃሁ ቸር ይግጠመን። አዲስ ዘመን ግንቦት 9/2012 ተገኝ ብሩ", "passage_id": "dbb6474784e2a96c78f94451d1ce176d" } ]
103544261bbaba6529acf8c34e1db0e4
45ce0bb182143b58cebebdfdf922ef5d
ሹል ሹል !
ሱራ ሽቅብ ሽቅብ ያቃስታል። ግዝፈቱ ያስጨንቀዋል። ልብስ አይበቃውም። የጫማው ቁጥር 48 ነው። የትከሻው ስፋት የሰውነቱ ግዝፈት የቁመቱ ርዝመት የሰማይ ስባሪ አስመስለውታል። አባ ግድየለሽ ሱራ ወግ ጨዋታ ይወዳል። ሰው አያስቀይምም። ውፍረቱ አስፈሪ አስደንጋጭ ነው።የሰፈሩ ሰው ልጆች ሲያለቅሱና ሲረብሹ ዋ ሱራን ነው የምንጠራው ሲባሉ ያውቁታልና በፍርሀት ርደው ጭጭ ነው የሚሉት። ሲደሰትም ሲከፋም ሱራ የአላህ ልጅ፤ የአላህ ወዳጅ የሚለው ነገር አለው። ለወላጆች ምነው ምነው ሕጻናቱ እንዲጠሉኝ እንዲፈሩኝ ባታደርጉ ምን አደረኳችሁ ይላል – ሱራ። በዛ ቁመቱና ውፍረቱ ሲንጎማለል ሲታይ የሞላለት ቱጃር ይመስላል። ጫማ ሰፊው ሱራ በቀን ሰርቶ ከሚያገኘው ውጭ ምንም የለውም። እጁ ሲያጥር ደምበኞቹ ከሆኑት ሴቶች ይበደራል። የድሀ ገንዘብ አታድርገኝ ይላሉ – እማማ ጌጤ። ከቀናት በኋላ ሴቶቹ ከች ይሉና ብር መልስ ይሉታል። አንተ ሱራ ስማ እንጂ የተበደርከውን አታመጣም፤ አላበዛኸውም እንዴ እያሉ ሴቶቹ ወገባቸውን ሲነቀንቁበት ይጨነቃል። ሂጂ እዛው ምን ወገብሽን ትሰብቂያለሽ ይላል ሱራ፤ ሶርሷራው። ተናገር ምንድነው ሂጂ እዛው አንተ አይደለህም እንዴ ስንቱን … ይሉታል። ኧረ በሕግ አምላክ ስሜን አታጥፉ አልደረስኩባችሁም ይላል እንደ ማፈር ብሎ።ጫማው መስፊያ ጎን ያሉት እማማ ጌጤ ይቺ ሙጢ አሁን እውነት ሱራ ቢጠጋት ትተርፋለች፤ ሹል አፍ ሙጢ እንደው መቀላመድ ትወዳለች ልጄ አሉና አጉተመተሙ። የመንደሩ ሴቶቹ የተቦተረፈ ጫማቸውን ይዘው ስፋልን እያሉ የሚወስዱት ለሱራ ነው። ብዙ የሴት ወዳጆች አሉት። አንዳንዶቹ የሚበላው ቋጠር አድርገው ያመጡለታል። አላህ እናንተን ባይጥልልኝ ኖሮ ምን እሆን ነበር ይላል ሱራ። ሱራ የሰማይ ስባሪው ሲሉት እናንተ ኮስማኖች በልታችሁ አይጠጋችሁ፤ ነገር ስትበሉ ውላችሁ ታድራላችሁ ፤ታዲያ ሱራ ምን ያድርጋችሁ ይላል። መኖሪያ ቤቱ የቀበሌ ቤት ነች። ግን ማንንም አያስገባም። ቤት ውሰደን ሱራ ሲሉት ደሞ ምን ቀራችሁ፤ ከእኔ ቤት ምን ጉዳይ አላችሁ ይላል። ቤት እየመጡ እሱ ሲሰራ እየተቀመጡ በዚህ መዘዝ ድሮ ምን እንደመጣበት ሱራ ሲያስታውሰው ይዘገንነዋል። ራሱ አብስሎ ይመገባል። አንዳንዴ በጎርናና ድምጹ ያንጎራጉራል። ሱራ የአላህ ወዳጅ… የአላህ ልጅ እያለ። ተናግረው ሊያናግሩት ሲነካኩት አሁን ከእኔ ምን ታገኛላችሁ ተውኝ ስራ የላችሁም ይላል። ጫማ መስፋቱን ይቀጥላል። ይህን ዝምታ የወረሰው በደርግ ዘመን ከደረሰበት ችግር በመነሳት ነው። በማያውቀው ነገር ሊሞት ነበር። ጫማ የሚሰፋባት አንዲት ክፍል የኪራይ ቤት ነበረችው። ከበውት የሚውሉ የሚያመሹም ነበሩ።ፖለቲካ አይወድም። እሱ ጋ የሚገቡና የሚወጡት ወጣቶች በዛን ዘመን ኢህአፓዎች ነበሩ። ወረቀት የሚበትኑ፤ ግድግዳ ላይ ቀለም የሚቀቡ፤ በቀይ ቀለምና በቀይ ጨርቅ ሀገሩን የሚያሸበርቁ። በፌስታል አምጥተው ሱራ የማያውቀውን እቃ ወረቀት ምናምን አመጣን ሱራየ ይቺ እዚህ ጋ ትቀመጥ ሲሉት ሱራ በመጡ ሰአት ተመልሰው ይወስዱታል እያለ ጫማውን መስፋት ይቀጥላል። የሚያውቀው ነገር የለውም ምስኪኑ ሱራ። እቃቸውን አይነካም። ተጠራጥሮም አይሸፍንም። በል ሲለው ያንጎራጉራል። ሱራ የአላህ ወዳጅ የአላህ ልጅ የምትለዋ ቃል ከአፉ አትጠፋም። በዚህ ይታወቃል። ጊዜው 1969ዓ.ም ነው። አዲስ አበባ መርካቶ አካባቢ። ሀገር ምድሩ ታምሷል። አንድ ቀን ቀበሌው የኢሕአፓ ወጣቶችን እያሳደደ ማሰር ሲጀምር እንዴ እነሱማ ተሰብስበው የሚውሉት ሱራ ጫማ ሰፊው ቤት ነው የሚል ጥቆማ አብዮት ጠባቂዎች ይሰጣሉ። ይታሰር ተብሎ ጠመንጃ ተሸክመው ሱራ ጋ ይሄዳሉ። ሱራ አይሞቀው አይበርደው አባ ግዴለሽ። እንደውም ቤቱ ይከበብ ተብሎ ከውጭ ብዙ ጥበቃዎች ይከቡታል። ሱራ ጫማውን አቀርቅሮ ይሰፋል። መሳሪያ ደግነው ዘው ብለው ገቡ። እጅ ወደ ላይ አሉት። ሱራ የአላህ ወዳጅ አለና ጠመንጃው ምን ያደርጋል ለአንድ ድሀ ጫማ ሰፊ የእኔ እጅ ስራ ይዟል ለምንድነው እጄን ወደላይ የማደርገው በእንጀራዬ ለምን መጣችሁ ይላቸዋል። ና ውጣ አንተ ኢህአፓ አሉት። ሱራ መለሰ ምንድነው ኢሕአፓ አላቸው። እሱንማ አንተ ታውቃለህ በደምብ ትመልሳለህ አሁን እስረኛ ነህ ና ውጣ ቀበሌ እንሂድ አሉት። ተውኝ ቢል ማን ሰምቶት። እያመረሩ ሄዱ። ሌሎች ሱራ ቀበሌ ሂድላቸውና ቃልህን ስጥ ምን ትሆናለህ አሉት። ሱቁን ቆለፈና በብዙ አብዮት ጠባቂዎች ታጅቦ የሠማይ ስባሪው ሱራ ቀበሌ ጽህፈት ቤት ገባ። ግቢው ውስጥ እሱ ጋ ገባ ወጣ ከሚሉት ወጣቶች ውስጥ የታሰሩ እንዳሉ አየ። ጮክ አለና ምን ሰርቃችሁ ነው የተያዛችሁት አላቸው። አብዮት ጥበቃዎቹም ወጣቶቹም ሳቁ። ሱራ ለምርመራ ገባ። ጠያቂዎቹን ያውቃቸዋል። የጫማ ደምበኞቹ ናቸው። ጫማቸው ሲቀደድ የሚሰፋላቸው።ሱራ አንተም አሉት። ተገረመና ምን አላቸው። ኢህአፓ አሉት። ምንድነው የምትሉት እሱን ሰውየ አላውቀውም። ቅድምም አብዮት ጥበቃዎቹ እንደሱ አሉኝ። የእኔ የጫማ ደምበኛ አይደለም። አሰርቶ አያውቅም። እኔም አላውቀውም አላቸው። ሱራ የአላህ ወዳጅ የአላህ ልጅ አለ ሰው በተሰበሰበበት። እስኪጣራ ታስረህ ትቆያለህ አሉት። ክፉኛ አዘነ። አላህ እንደ ስራየ ይስጠኝ፤ በተንኮል ለወነጀሉኝም ፍርዱን ይስጥ አለ- ደገመና። እስር ቤቷ ውስጥ ግዙፉ ሱራ አንገቱን አዝምሞ ገባ። ታሳሪው በተጨናነቀው ቤት ውስጥ ለሱራ ተጣበው ቦታ ሰጡት። ግድግዳውን ደገፍ ብሎ እንደቆየ ድብን አድርጎ እንቅልፍ ወሰደው። ማንኮራፋት ጀመረ።ቢጠሩት መች ሰምቶ። ለሊቱን እነዛን ልጆች ወደማይታወቅ ስፍራ ወስደዋቸዋል። ሲነቃ ልጆቹ የሉም። የሰፈሩ ሰው ሱራ ቀበሌ መታሰሩን ሲሰማ በእጅጉ አዘነ። ከፊሉ አሽሟጠጠ። ደሞ ሱራ ብሎ ፖለቲከኛ እያለ። ጠጅ ቤት መነጋገሪያ ሆነ። ሱራ ታሰረ— ሱራ ታሰረ — ባዩ በዛ። የሰፈሩ ሰው ጫማ የሚሰፋላቸው ሴቶች እየተጋገዙ ምግብ ያቀብሉት ጀመር። ቀለብ የማያገኙት እስረኞች ረሀባቸው ጠፋ። ሱራ ሱራ አሉት አቤት አላቸው። እንኳን ታሰርክ እንዲያውም መውጣት የለብህም አሉት። ተንከትክቶ ሳቀ። አንተ በመታሰርህ እስር ቤቱ ምግብ በምግብ ሆነ ሲሉት ቀበል አደረገና እኔ ፖለቲካ አላውቅም። ጫማ ሰፊ ነኝ። እኔን በሀሰት በወነጀሉኝ ሰዎች ላይ አላህ ፍርድ ይስጥ፤ ሱራ የአላህ ወዳጅ የአላህ ባሪያ አለና አይኖቹ በእምባ ተሞሉ። አይዞህ ሱራ አሉት። አይዞህ አይዞህ ሱራ። ለሊት በቀበሌያቸው አካባቢና ዙሪያ የቀለጠ ተኩስ ተሰማ። እስረኞቹ በተኙበት ይሰማሉ። ሱራ አላህ –አላህ ይላል። የመትረየሱ ድምጽ ተረረረረረም ሲል ሱራ አላህ ድረስ፤ የታሰሩት ልጆች አውጣን አውጣን ሆነ። አይነጋ የለም በጭንቅ ነጋ። ጠዋት ለሽንት ሊወጡ ሲሉ ሱራ ነበር የቀደመው። ያገኛቸውን ሰዎች ምንድነው ጉዱ አላቸው። መጥተው ፈጅተውን ሄዱ፤ አመለጡ አሉት። እነማን ናቸው አላቸው – ሱራ። ኢህአፓዎቹ ናቸዋ አሉት። ሰው ተጎዳ ብሎ ጠየቀ። ምን ሰው ተረፈ ብለህ ነው። በቀደም አንተን ከሱቅህ አስረው ያመጡህ በሙሉ ሞተዋል አሉት። ምን አለ ሱራ ደንግጦ። ደገመና ሱራ የአላህ ወዳጅ የአላህ ልጅ። እቺ ኢህአፓ የምትሏት አላህ ነች እንዴ አለ ሱራ። ሰዎቹ በሳቅ አሽካኩ። ሱራ ሱራ።ወንድወሰን መኮንንአዲስ ዘመን የካቲት 19/2012
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=27990
[ { "passage": " እኛ ሰፈር ብቻ ከሆነ አላውቅም እንጂ መብራት ኃይሎች ፈረቃው ራሱ የተምታታባቸው እየመሰለኝ ነው። አለ አይደለ! የእኛን ሰፈር ያጠፋው ሰውዬ ለምሳ በወጣበት አንድ ሁለት ብሎ ተጫውቶ ሲመለስ የትኛውን ጠፍቶ እንደቆየና የትኛው ሰፈር ተለቅቆ እንደነበር ረስቶት ባለበት የሚተወው። ታድያ ሙሉ ቀን መብራት የሌለው የእኛ ሰፈር ነው ብላችሁ ውሰዱት። «ብለነው ብለነው የተውነውን ነገር!» አትበሉኝና ሰሞኑን ፈረቃውን ሳስብ ነበር። እንደውም ባይገርማችሁ ከስምንት ሰዓት አንዲት ደቂቃ ዝንፍ ብላ ሌላው ቀርቶ አብሮን የቆየው መብራት ካልጠፋ ይከፋኝ ጀምሯል። መቼም በቴሌቭዥን ዜና አልኖርንምና መብራት ቢጠፋ ግድ የለም፤ ኔትወርክ ይኑርልን እንጂ። አዎን! ቴሌም ውሎውን ፈረቃ የሚባል አመል ካወጡ ተቋማት ጋር እንዳያደርግ መምከር ነው። ከምን የዋለች ምን… ምን ነበረ ተምራ መጣች የሚባልላት፤ ብቻ እንዳይጋባብን መጠንቀቅ ነው። አሃ! የሆነውስ ሆኖ አሁንም’ኮ ሁሉ\nነገር በፈረቃ መስሏል። ፍቅርና ጸቡ ራሱ በፈረቃ ሆኗል። መቼ እለት «ኦሮማራ» ሲባል ሰምታችሁ ወር ሳይዘልቅ በሁለት ሰዎች ተራ ግጭት አገር ካልተያዘ ይባላል። ይኸው የፈረቃ ፍቅር ሄዶ ሄዶ «አማራ ትግራይ» ሆነ፤ አልቆየም በጥቂቶች ጸብ መልሶ ግልብጥ። የፈረቃ ትምህርት የቀረ ጊዜ ፍቅራችንን በፈረቃ አድርገነው ተገኘን። እውነት ለመናገር ወቅት ሲፈራረቅ እንጂ ፍቅር ሲፈራረቅ ደስ አይልም። ስላችሁ እየተፈራረቁ የሚወዷችሁ ብዙ ሰዎችን ይስጣችሁ! እያፈራረቁ ከሆነ ግን ዋጋ የለውም። አንድ ቀን እየወደዱ ሌላ ቀን መጥላት ከዛ ደግሞ ድጋሚ መውደድ፤ «ኢትዮጵያ» የሚለውን የጥላሁን ገሠሠን ዘፈን ሲሰሙ በፍቅር አልቅሶ ከአፍታ በኋላ «አይ ይህቺ አገር!» ብሎ በቁጣ ማለቃቀስ ከዛ ድጋሚ በቴዲ አፍሮ «ኢትዮጵያ አገሬ» ማለት፤ ይሄም ያው ፈረቃ አይደለ? በነገራችን ላይ ብልጭ ድርግም የሚል ተፈራራቂ ስሜታችን አምላኩ ይይለትና! አገራችንን የት ባደረስን ነበር። ለምሳሌ ልንገራችሁ፤ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት የነበረውን የኢትዮጵያንና የጣልያንን ጦርነት አስታውሱ። ያኔ ጣልያን የቋጠረው ቂም ፈንድቶ ኢትዮጵያን የወረረ ጊዜ ነበር። በዛ ጊዜ ንጉሡም አቤቱታቸውን ለዓለም መንግሥታት ሁሉ ቢያሰሙም አድማጭ አጡ። በኋላ እነዚሁ አቤቱታውን ሰምተው እንዳልሰሙ ያለፉ አገራት የራሳቸው ጉዳይ ሲገጥማቸው ጣልቃ ሊገቡ ፈቀዱና እንግሊዝ ደረሰች። የአገራችን አርበኞች የአምስት ዓመት መስዋዕትነትና ድካም ላይ የእንግሊዝ ጉልበት ሲጨመር ጣልያን ጨርቄን ማቄን ሳይል ወጣ። ይሄኔ እንግሊዝ ሆዬ ማንም አላወቀባት፤ ወዳጅ መስላ አገር ልትይዝ። ታድያ ንጉሡ ነገሩ ገብቷቸው ስለነበርና የወቅቱ ፖለቲከኞችም ስለባነኑ እንግሊዝም «ውለታዬ አለብሽ» ብላ ኢትዮጵያን ባርያ እንዳታደርግ መላ መላ ብለው ሸኝተዋታል። እና በዛ ሰዓት እነዛ ሰዎች እንደዛሬው ያለ የስሜት ፈረቃ ቢኖርባቸው ከጣልያን ተርፈን የእንግሊዝ ሲሳይ መሆናችን ይቀር መስሏችኋል? በጭራሽ! «እንግሊዝዬ… አንድም ጣልያንን የሸኘነው በአንቺ ምክንያት ነው» ብለን ስንተቃቀፍና ስናቅፋት፤ አጅሪት ምናችንን ታስቀረው ነበር? «ያለሽ መስሎሻል…ተበልተሽ አልቀሻል» እንደተባለለት ጎተራ ሆነን እናርፈው ነበር። ብቻ ግን ይህን ሁሉ የምዘባርቀው በጣም የስሜት ፈረቃ አለብን የሚለው ላይ ለማስመር ነው። አብርቶ ማሳደር፤ አጥፍቶም ማዋል እንደማይችለው መብራት ኃይል፤ ዘግቶ እንደማያከርም ለቅቆም እንደማይዘልቅ ውሃ ልማት አንዳች የፈረቃ አመል አለብን። በምን ፍጥነት የወደድነውን እንደምንጠላ፣ በየትኛው ሌሊት አስተሳሰባችን ሁሉ ተቀይሮ እንደሚያድር፣ በየትኛው ቀን ዘር ቆጥረን ለመስደብ እንደወሰንን፣ በየት በኩል ምርቃት ባዘነበ አፋችን እርግማን እንደሚሞላ፤ ከምኔው ያጨበጨብንለት ላይ ምራቅ እንደምንተፋ አይታወቅም። ድንገት ድርግም! ድንገት ጥፍት! ደግሞ ድንገት ብርት…ፍስስ። በአንዲት ማብሪያና ማጥፊያ እንደሚቆጣጠሩት የእልፍኝ ባልቦላ በአንዲት ጉዳይ ግልብጥ። እንደውም እነ መብራት ኃይል የፈረቃን ጸባይ ከእኛ ሳይሆን ይቀራል የተማሩት!? መድረሻውን የማያውቅ ሰው የሚሄድበትን መንገድ ያልወሰነ ነውና በወሰዱት ሁሉ ይጓዝ የለ? እኛም ልክ እንደዛው «ሆ!» ብሎ\nመውጣት… ግርርርር ብሎ ተስፋ ማድረግ…ተከታትሎ መፍሰስ። ተዓምር በሚሰማባት አገር ላይ እኛም ተዓምር ሆነን ቁጭ! ጉዳዩም ሲፈራረቅ እንደዛ ነው። አንድ ሰሞን የአንዲት ሴት በ«ወድጃት ነው»\nሰበብ መገደልን ስናውለበልብ ቆይተን፤ ጫፉን ሳንይዝ «የቤተመንግሥቱ ራት ላይ አርቲስቷ ተገኘች» ጉዳያችን ይሆናል። አንዱም መቋጫ ሳያገኝ በሰው አክባሪነትና ጨዋነት የተመዘገብን እኛ «ሰው በድንጋይ ተወገረ…» ዜናን እንቀባበላለን። ይህ አንገት አስደፍቶን ሳያበቃ፤ «ፕሮጀክቶቹ» እንደማለዳ ፀሐይ ርዕስ ጉዳይ ሆነው ይጠብቁናል። ብቻ ነገሩ ሁሉ ፈረቃ ነው፤ ርዕሰ ጉዳይም ቀን ይጥለው ጀምሯል። ጉዳዮቻችን ከፍ ካለ የአንድ ሳምንት እድሜ አልያም በአንድ እጅ ጣት የማይቆጠሩ ቀናት ቆይታን ብቻ ያደርጋሉ። በፈረቃ አንዱ ሲጣል ሌላው ይነሳል። ማኅበራዊ ገጾቻችን ደግሞ ለታሪክ የሚበቃ እድሜ ይስጣቸውና «አምና በዚህ ጊዜ እንዲህ ስትሉ ነበር» ብለው አልፈው ያስታውሱናል። የእኛ ፈረቃ መች አሁን ጀመረ? ቆይቶብናልኮ! ይሄ ተፈራራቂነታችን ይበጃል ወይ? አይመስለኝም። የእኛ ስሜት መፈራረቅ «የአሥራ ሦስት ወር ጸጋ» እንደሚባለው፤ በእነዚህ ወራት መካከል እንደሚፈራረቀው የአየር ጸባይ ቱሪስት አይስብ! ፋብሪካ እየተፈራረቁ እንደሚሠሩና እንደሚረካከቡ ባለሙያ ዎች ሥራ አያፋጥን! አያምርብን! አገራችን’ኮ በየቀኑ ሕዝብ\nየምትቀይር እየመሰለን ነው፤ እንደሸሚዝ። አንድ ሰሞን ፈካ ያሉ ተስፈኞች፣ በሰሞኑ ማግስት ጠበብ ያሉ «ተስፋ የለንም» ባዮች፣ አንዳንዴ ዘናጭ ለከረባት የሚስማሙ፣ ሌላ ጊዜ ያላማረባቸው ተዛንፈው የተቆለፉ፤ አገሬ ሕዝብ እንደ ሸሚዝ እየቀየረች ይሆን? ግን እሱስ ቢሆን አያልቅባትም? አይሰለቻትም? እኛስ በየቀኑ ማለዳ ስንነሳ እናት አገራችን «አንተ የትኛው ልጄ ነበርክ?» ብላ ለመለየት ስትቸገር፤ «ዛሬስ ስለእኔ ምን ታስብ ይሆን?» ብላ ስትጨናነቅና ስትሳቀቅ፤ «ዛሬ ደግሞ ሊሰድቡኝ ይሆን ሊያሞግሱኝ» ብላ ስታስብ ስናያት አታሳዝነንም? እንግዲህ ወቅቱም ግራ የገባው ይመስል የሚዘንብበትን ቀን እንኳ መለየት ትቷል መሰለኝ። አልያም እኛ ተኝተን ያለፈን ወቅት ሳይኖር አልቀረም አየሩም ግራ አጋቢ ሆኗል። ዝናቡ ራሱ «ከመጣሁ አይቀርማ ዘንቤ ልሂድ እንጂ» የሚል ነው የሚመስለው። በተረፈ ግን ጊዜውን ጠብቆ የሚሆን ነገር የጠፋ እየመሰለ ነው። እኔ ራሴ አበዛሁ መሰለኝ! ብቻ ፈረቃን ካልወደድንና ከጠላን እኛም ጸባያችን እንደ መብራትና ውሃ ወይም እንደ ወቅት አይፈራረቅ ለማለት ነው። በዛውም! ለባልቦላው ባለቤቶች «ኧረ የእኛ ሰፈር መብራት እየተረሳ ነው መሰለኝ!» በሉልኝ። ሰላም!አዲስ ዘመን ዛሬግንቦት 25/2011 ", "passage_id": "04be8b91048640dbf927b832dfde17a6" }, { "passage": "በሰፈራችን ያገኙትን መመረቅ የሚወዱ አንድ አባት ነበሩ። «ደግሞ ይስመርላችሁ…አምላክም ይስማኝ እንጂ ልጆቼን እናንተን ለመመረቅ ለምን ብዬ እሰስታለሁ?» ይላሉ። ፈገግ ካሉላቸው መመረቅ ነው፣ ዞር ካሉላቸው መመረቅ ነው፣ አቤት ካሏቸው መመረቅ ነው። ነጋዴ አይደሉም፤ ሽበት የተጎናጸፉ፤ እድሜ ያስከበራቸው ደግ አባት ናቸው። እኛ ደግሞ ሲመርቁ እንዳያመልጠን፤ ቶሎ አሜን አሜን ማለት።አንድ ወዳጃችን ታዲያ አብዝቶ ይወዳቸዋል። ምርቃታቸው የሠራለት ነገር ኖሮ እንደሆነ አላውቅም፤ ብቻ እኛ ጓደኞቹ ከምንወዳቸው በላይ ነው እርሱ የሚወዳቸው። እናም ይህን ፍቅሩን ለመግለጽ በዓል አስታክኮ፣ የእኛን ቦርሳና ኪስ በመዋጮ ስም ፈትሾ፤ ነጣ ያለ ጋቢ ገዝቶ አበረከተላቸው። መረቁት! መቼም የእኛ ነገር! ጥቅም ሲያገኙ አብዝተው የመረቁት ይመስለን ይሆናል? ግን አይደለም። እንደወትሮው ሳያደሉ፤ ሳይጨምሩ ወይም ሳይቀንሱ መረቁት። «አትጣ! አግኝ!» አሉት።ምርቃታቸው እያንዳንዱ ፍሬ እንዳያመልጠው ከስር ከስር በ«አሜን» እየለቀመ ቆየና፤ «አባብዬ… እንደው ይሄ አትጣ አግኝ ብለው የመረቁኝ ነገር ምኑን ነው?» አላቸው። እርሳቸውም ነገሩ ጨዋታ መስሏቸው ፈገግ ብለው፤ «ምንስ ቢሆን የኔ ልጅ? ሰላምም ቢሆን ጤና፤ ፍቅርም ቢሆን አንድነት፤ በጎውን የልብህን መሻት ሁሉ እንድታገኝ ነው ምርቃቴ» አሉት።እርሱ ግን ፊቱን ቅጭም አድርጎ፤ «እንደው ወደላይ አስፈጻሚዎች ጋር ሲደርስ ለመምረጥ እንዳይቸግራቸው፤ «ትራንስፖርት አግኝ…ታክሲ አትጣ!» ብለው ለይተው ቢጠቅሱልኝ ብዬ ነው» አላቸው። ነገሩ ቀልድ ነው ተብሎ በዛን ሰሞን በሰፈራችን እንደ ጉድ ተሳቀ። እርሱ ግን ከልቡ ነበር፤ ተማሯላ!\nባለፉት ቀናት የነዳጅ መጥፋት ድፍን አዲስ አበባ እንዴት የገበያ ማዕከሏን መርካቶን እንደመሰለች አላያችሁም? ግን እኔ የምለው፤ ለነዳጅ እንዲህ ከሆንን…ሰላም ጨርሶ የጠፋች ቀን ምን ሊውጠን ነው። ነዳጅና ሰላም ምን አገናኛቸው እንዳትሉኝ። ሰዎች! ሁሉም ነገር ፖለቲካ መሆን የለበትም። ግን አንዳንዴ አርቆ ማሰብ ያስፈልጋል ብዬ ነው። አርቀሽ አስበሽ ልብሽ ውልቅ ብሏል! በሉኛ! ይሁን እተወዋለሁ።\nግን እውነቴን ነው፤ አትጡ! አግኙ። ለምን? በትራንስፖርት ማጣትና ማግኘት መካከል ያለውን ሰፊ ልዩነት ስትመለከቱ ራሳችሁን ታያላችሁ። ባለመኪና ከሆናችሁ ደግሞ እኛን መኪና አልባዎቹን ታዩናላችሁ። ለምሳሌ አሁን በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ቀን ረዥም ዘንዶ የሚያስንቅ ሰልፍ ይዘን አውቶብስ ጥበቃ ላይ ታድመናል።ከስንት አንዴ የሚመጣውን ባስ «ሰለፉ ከእኔ ነው የሚጀምረው» በሚል ንትርክ ጥቂት አቆየነው። ከዚህ ቆይታ በኋላ ሰላማዊና ሰልፋዊ ግፊያ ተደርጎ ተሳፈርን። ማን እንደመረቀኝ ባላውቅም ወንበር አገኘሁ። እማማ አፍሪካ! በየክፍሏ ለወንበር የሚራኮትባት መቼስ ብዙ ነው። ብቻ እድሜው ገፋ ያለ፤ «ኧረ እርስዎ ይቀመጡ» የሚባል ዓይነት ሰው በአካባቢዬ ስላልነበር ተደላድዬ ሃሳቤን ጥዬ ተቀመጥኩ።\nታዲያ ከገባን በኋላ፤ «እዛጋ ተጠጉ…እዚህ ጋር አለፍ በሉ» ልመና ጀመረ፤ ውጪ ያለው ተሰላፊ። «ከዚህ በላይ ወዴት ልጠጋ?» ንጭንጭ ያሰማል ተሳፋሪ። «ቆይ ሰው ሌላ ባስ አይጠብቅም እንዴ? ሞልቶ እያዩት እዚህ ተፋፍኖ ለመሄድ መጋፋት ምንድን ነው?» ይላል፤ ለባሱ መጨረሻኛ ሆኖ የገባው ሰው። ሁሉም ብቻ የየራሱ የሆነ አስተያየት ይሰጣል።ብቻ መሙላት አይቀርም ባሱ ሞልቶ ተንቀሳቀሰ። ልክ ሲንቀሳቀስ ባሱን የተሳፈረ ሁሉ በመስኮቱ አሻግሮ የተሰለፈውን ሰው እያየ ከንፈሩን መምጠጥ ይጀምራል። «በስመ አብ ሰልፍ! አሁን ስንት ሰዓት ነው ይህ ሁሉ ሰው ቤቱ የሚገባው?» ይላል። ተጋፍቶና ተጣልቶ በባሱ የተሳፈረው ሰው፤ ለገፋውና ለታገለው ለጣለውም ሰው መልሶ ያዝናል።እናላችሁ! መቼም ሀብታም ሰው ነው ለምስኪን ደሃ ሲያዝን የሚያምርበት፤ እኛ ቀንቶን የተሳፈርን ሰዎችም ገና ሰልፍ ላይ ላሉት ሀዘን ገባን። እኔም ራሴ አዘንኩ፤ እውነት እላችኋለሁ ሰልፉ ላይ እኔ የነበርኩ እስከማይመስለኝ ድረስ ነው የተሰለፉት ሰዎች ያሳዘኑኝ። አሃ! እኔ አገኘሁኛ! ይሄኔ ይህ ተከታዩ ሃሳብ ብልጭ አለልኝ፤ ለካ መተሳሰባችንን የሰረቀው ድህነት ነው። ብዙ አውቶብስ ቢኖረን ኖሮ፤ መንገዱ ቦርቀቅ ቢልልን ኖሮ፤ ከየምንሠራበትና ከየምንማርበት አፈስ አድርጎ ካሰብነው የሚያደርሰን ባለመኪና ዘመድ ቢሰጠን ኖሮ፤ መንገዱን እንጃ እንጂ ራሱ መኪና ቢኖረን ኖሮ፤ ይሄ ሁሉ ይኖር ነበር? አይኖርም።አትጡ አግኙ…አንጣ እናግኝ ያልኩት ለዚህ ነው። በየትራንስፖርቱ ማንነታችን እየታየ ይመስላል። በዛ ቦታ መታገስ የቻለ ትዕግስቱ፣ በዛ ቦታ መሳደብ የቻለ ድፍረቱ፣ በዛ ቦታ መጋፋት የቻለ ጥንካሬው…ሁሉም ቁልጭ ብሎ ይታያል። በቃ! ሰውን የምታውቀው አብረኸው ረጅም ጉዞ ስትሄድ ነው ምናምን የሚሉት ነገር ተለዋጭና አማራጭ አግኝቷል። ወይም «ጓደኛህን ንገረኝና አንተነትህን ልንገርህ» እንደሚባለው፤ «ረጅም የታክሲ ሰልፍ አብሬአቸው ልሰለፍና ስለሀበሾች እነግርሃለሁ» የሚል ብሂል አያይዞ መናገር ይቻላል።«ሰላምም ቢሆን ፍቅርና አንድነት፤ ሊፍት የሚሰጥ ክፉ ያልገጠመው ደግ ባለመኪና፣ ባዶ ታክሲና አውቶብስ፣ ቅድሚያ ለሴት የሚሉ የታክሲ ተራ አስከባሪዎች፣ ስታረፍዱ የማይቆጣ…በጊዜ ስትወጡ የማይከፋው አለቃ፣ መኪና ገዝቶ የሚሰጥ ዘመድ፣ በምትንቀሳቀሱበት መስመር የሚሠራ የምታውቁት የሚያውቃችሁ ሹፌር ወይ ረዳት…የመሳሰሉትን ሁሉ አግኙ፤ ይስጣችሁ። እንዲሁም ጠላት አንዳንዴ ያስፈልጋልና እርሱንም ጠራርጎ አያሳጣችሁ።» የሰፈራችን መራቂ አባት፤ አባባ፤ የጓደኛችን ጥያቄ ቀልድ እንዳልነበረ ከተረዱ በኋላ ነው እንዲህ መመረቅ የጀመሩት። ሰላም!አዲስ ዘመን ጥር 12/2011ሊድያ ተስፋዬ", "passage_id": "09fbcd487380c53fa976508cb2074e7c" }, { "passage": "ምንድነው እሱ? ምን ተፈጠረ? ነው የምትሉት? ለማረጋገጥ ካልሆነ በስተቀር ዳር ዳርታዬ ሳይገባችሁ ቀርቶ አይመስለኝም፡፡ አዬ ንገረና! ሆዳችንን በሰስፔንስ አትቁረጠው አላችሁ? አዲስ ነገር’ኮ አይደለም የማወራችሁ፤ ያው የምታውቁትና በየጊዜው ኧረ በየቀኑ ማለት ይቻላል፤ እየጨመረ፣ እየወጣ፣ እየተሰቀለ እንደ ኳስ ወደ ሰማይ እየጓነ፣ … የፈለጋችሁትን በሉት፣ የአገልግሎትና የሸቀጦች ዋጋ መናር ነው፡፡ውይይ! ይህን ልትነግረን ነው’ዴ ኡኡታህን የምታቀልጠው? እኛ’ኮ አዲስ ነገር የምትነግረን መስሎን፣ ምን ተአምር ተፈጠረ? ብለን ነበር ሰፍ ያልነው፤ የምትነግረን ይህን ከሆነ፣ በቃህ፣ በቃህ፣ አንተ ቋጣሪ ነህ፡፡ አንተና መሰሎችህ ናችሁ በየሄድንበት እየተከተላችሁን፣ መጠጥ አላስጠጣ፣ ምግብ አላስበላ፣ ጮማ አላስቆርጥ፣ … ያላችሁን፡፡ እንዲያውም ከእናንተ ጋር እንዳንጋፋ ከዚህም በላይ በናረ፡፡ ደግሞ ይንራል፡፡ እንዲህ ካልሆነ ልዩነታችን በምን ይታወቃል? ለምትሉት አይደለም መልዕክቱ፡፡ገቢያችሁ የማይታወቀውን፣ በአየር ባየር (መኒ ላውንደሪ) ኪሳችሁ ላበጠ፣ ካዝናችሁ ለደለበ፣ መጠጥ ቤት ገብታችሁ በየቀኑ ውስኪ ለምታወርዱ፣ ሌሎች የሚያዳምጡትን ሙዚቃ መስማት የሚደብራችሁና እንዲለወጥ ለምታዙና ትዕዛዞች ወዲያውኑ ካልተፈፀመ ማይክራፎን በሽጉጥ ለምትበታትኑ፣ … አይደለም መልዕክቴ፡፡ እንደተባለውም እንደ’ኔ ላሉ ምስኪኖች ነው፡፡የመልዕክቴን ባለቤቶች ከለየሁ፣ ወደ ጭብጡ ልግባ፡፡ አስገራሚና አሳዛኙ ነገር፣ አንዴ ዋጋው የተሰቀለ ነገር፣ ጥሬ ዕቃው ቢረክስ ወይም አቅርቦቱ ቢንበሸበሽ ዋጋው  አይወርድም፣ እንደ ተሰቀለ ይቆይና ትንሽ ቆይቶ ይጨምራል፡፡ የዚያ ጭማሪ ድንጋጤ ሳይለቀን በሳምንቱ ወይም በ15 ቀኑ ሌላ ጭማሪ ይቆለልብናል፡፡ እኔ አልቻልኩም፡፡ ለማን ላመልክት?ከትናንት በስቲያ ወደቤቴ ስሄድ፣ መገናኛ አካባቢ ካለ ታዋቂ ካፌ ገብቼ ማኪያቶ አዘዝኩ፡፡ እዚያ ካፌ የማኪያቶ ዋጋ 5 ብር መሆኑን ነበር የማውቀው፡፡ ሁለት ወር ያህል ቆይቼ የዛሬ ሳምንት ወይም 10 ቀን ቢሆን ነው፣ ማኪያቶ ጠጥቼ 6.50 ከፈልኩ፡፡ ሌላ ጊዜ ጥንቁቅ ነበርኩ፡ ብዙ ጊዜ በትናንት ዋጋ ዛሬ ስለማይሸጡ፣ ዋጋ ሳልጠይቅ አላዝም፡፡ ከትናንት በስቲያ ግን ተሸወድኩ፡፡ እንደበቀደሙ ይሆናል በማለት ማኪያቶ ጠጥቼ 7፡00 ብር አስከፈሉኝ፡፡ተገልጋይ፣ ዋጋ አትጨምሩብኝ ማለት አይችልም - እሺ ይጨምሩ፡፡ እኔ የምለው ቢያንስ ዋጋ ሲጨምሩ ለምን አያሳውቁንም? ነው፡፡ አዲሱን ዋጋ ሰው እስኪለምድ ድረስ የቡና፣ የማኪያቶ፣ የሻይ … ዋጋ ብለው ለምን በትንሽ ወረቀት ግድግዳ ላይ አይለጥፉልንም? እንደዚያ ካደረጉ፣ ዋጋውን አይቶ የተስማማው ይስተናገዳል ያልተስማማው ጥሎ ይሄዳል፡፡ከሦስት ሳምንት በፊት ደግሞ እርር ያልኩበትን ላጫውታችሁ፡፡ ድሃ አይደለሁ… እንግዲህ ጥሎብኝ ጐመን እወዳለሁ፡፡ ሁለት ወር ተኩል ወይም ቢበዛ ሦስት ወር ይሆናል፡፡ እዚያው መገናኛ አካባቢ ጐመን በሥጋ 25 ብር በላሁ፡፡ ዋጋው እንደዚያው ይሆናል ብዬ ከሦስት ሳምንት በፊት ጐመን በስጋ አዝዤ በላሁ፡፡ ሂሳብ ልከፍል ደረሰኝ ስጠይቅ 34.50 መጣልኝ፡፡ እውነቴን ነው የምላችሁ፤ ያን ያህል ይጨምራል ብዬ ስላልገመትኩ በጣም ነው ክው ያልኩት፡፡ አስተናጋጁን“ምንድነው ይኼ?” ብዬ ስጠይቀው፤ ጥርሱን ብልጭ አድርጐ “እንደዚያው ነው” አለኝ፡፡“ከሁለት ወር በፊት 25 ብር ነበር የከፈልኩት፡ መቼ ነው የጨመረው?” አልኩት፡፡“ኧረ ቆይቷል ወር ያልፋል፡፡ ያኔም ቢሆን 28 ብር እንጂ 25 አልነበረም” አለኝ፡፡“እሺ ይሁን! ዋጋ ስትጨምሩ ለምን አታስታውቁንም?” ስለው“የሚያውቁ መስሎኝ ነው” አለኝ፡፡አሁንም ስህተቱ የእኔው ነው፤ ዋጋ ሳልጠይቅ መብላቴ፡፡ ከአሁን በኋላ በምንም ዓይነት ዋጋ ሳልጠይቅ አላዝም፡፡ እናንተም የእኔ ስህተት ትምህርት ይሁናችሁ እላለሁ፡፡ካዛንቺስ አካባቢ አንድ ክትፎ ቤት አለ፡፡ ክትፎው ጥሩ ስለሆነ ብዙ ሰው ይራኮትበታል - በተለይ ፆም መያዣ ወይም መፍቻ ሲሆን፡፡ እኔ ያን ቤት የማውቀው የክትፎ ዋጋ 8 ብር በነበረ ጊዜ ነው፡፡ ከዚያ 10፣ 12፣ 15፣ 17፣ 20፣ 23፣ 27፣ 32፣ …እያለ 40 ቤት ገባ፡፡ የዛሬ ሁለት ዓመት ገደማ“የጥራጥሬ ዋጋ ስለጨመረ መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ አድርገናል” ብለው ለጠፉ፡፡ እዚያ ቤት ደስ የሚለኝ ነገር ዋጋ ሲጨምሩ ያሳውቃሉ፡ መጠነኛ ያሉት 8 ብር ጨምረው ነው፡፡ አስተናጋጁን በቀልድ፣ “እስካሁን ምን ዓይነት ጥሬ ነበር ስታበሉን የነበረው?” ብዬው ከፍዬ ወጣሁ፡፡ 53፣ 66፣ 75…እያለ 80 ቤት መድረሱን ከሰማሁ በኋላ በቅርቡ ደግሞ ስንት ደረሰ? ብዬ ሄጄ ነበር፡፡ “ቅቤ ስለተወደደ ዋጋ ጨምረናል” ይላል እንጂ ትክክለኛ ዋጋውን አይገልጽም፡፡ እኔ ከ48 ብር በኋላ አልበላሁም፤ አድማ አደረኩ፡፡እዚያው ካዛንቺስ አካባቢ 8 ብር ይበላ የነበረ ዱለት፣ 10፣ 12፣ 14፣ 16፣ 19፣…እያለ ዛሬ 25 ብር ደርሷል፡፡ ቀይ ወጥና ቅቅል ደግሞ 12፣ 14፣ 16፣ 19፣ 22፣ እያለ ዛሬ 30 ሆኗል፡፡ ነገ ደግሞ ስንት ይሉን ይሆን? እኔ እዚያ ቤት አድማ የጀመርኩት 19 ብር ሲገባ ነበር፡፡አንድ ወዳጄ እንዳጫወተኝ፣ ካዛንቺስ ያሉ አራት ሉካንዳ ቤቶች ዋጋ የጨመሩት ስብሰባ ተቀምጠው ነው አሉ፡፡ መንግሥት ኪሎ 50 ብር ሽጡ ሲላቸው እነሱ “ከእኛ ነው ከመንግሥት” እያሉ የእኛ የሚሉትን 80 ብር ይሸጡ ነበር፡፡ ለፋሲካ፣ ያን ዋጋ 110 ብር አስገቡት፡፡ በቅርቡ ጨምረው እንደሆን አላውቅም እንጂ ስብሰባ ተቀምጠው 130 ብር እንዳስገቡት ወዳጄ ነግሮኛል፡፡ስለዚሁ የሥጋ ዋጋ ስናወራ ቁርጥ የምትወደዋ የሥራ ባልደረባዬ “አንተ ይህን ትላለህ፣ የናዝሬቱ ባለሥጋ ቤት እዚህ ሥጋ ቤት ከፍቶ አንድ ኪሎ 170 ብር እየሸጠ ነው” አለችኝ፡፡ እኔስ ጥሬ ስጋ አልበላም፤ ይብላኝላችሁ አልኳት፡፡ ሌላዋ ባልደረባዬ ደግሞ “ጥሬ ሥጋ ካልበላህ ኢትዮጵያዊነትህ በምን ይገለጻል? በመታወቂያ ወረቀት?” አለችኝ፡፡ መታወቂያዬም ብሔሬን ነው እንጂ ኢትዮጵያዊነቴን አይገልጽም፡፡ የየት አገር ዜጋ እንደሆንኩ ለራሴም ግራ ገብቶኛል አልኳት፡፡ እሷም “ቀልዴን ነው፤ እኔም ጥሬ ስጋ አልበላም” አለች፡፡እኔ የምለው፤ ይኼ የዜግነት ነገር ኢትዮጵያዊነት ቀርቶ አማራ፣ ትግሬ፣ ጉራጌ፣ ኦሮሞ፣ ወላይታ፣ ሲዳማ፣ …እንደተባለ ቀረ አይደል? ያልገባኝ ነገር የሌሎች አገር ዜጐች በአገራቸው ነው ወይስ በጐሳቸው ነው ዜግነታቸው? ለምሳሌ ናይጄሪያ፣ ኬንያ፣ ሕንድ፣ ብዙ ጐሳ አላቸው፡፡ የእነዚህ አገር ዜጐች፤ ናይጄሪያዊ፣ ኬንያዊ፣ ሕንዳዊ፣ እንጂ በጐሳቸው አይጠሩም፡፡ የእኛ ታዲያ እንዴት በጐሳ ሆነ? የእኔ ነገር የጀመርኩትን ርዕሰ ጉዳይ ትቼ ወደ ሌላ ሄድኩ አይደል? ይቅርታ፡፡እዚህ ላይ ነጋዴ በኪሳራ ወይም በዋናው ብቻ ይሽጥ እያልኩ እንዳልሆነ ይታወቅልኝ፡፡ ማንኛውም ቢዝነስ ለትርፍ እንጂ ለጽድቅ አይሠራም፡፡ ሰው ሠርቶ፣ ነግዶ ማትረፍ አለበት የሚል ጽኑ አቋም እንዳለኝ ይታወቅልኝ፡፡ እኔ እየተቃወምኩ ያለሁት ከልክ ያለፈውን ሸማቹን የሚጐዳውን፣ ሥጋውን በልቶ በአጥንት የሚያስቀረውን ቅጣ ያጣ ትርፍ ነው፡፡ በውጪው ዓለም የሚሠራበት የትርፍ ሕግ አለ፡፡ አንድ ሰው ማትረፍ ያለበት የወጪውን 10 በመቶ፣ ቢበዛ ደግሞ እንደ ዕቃውና እንደሁኔታው 50 በመቶ ቢደርስ ነው፡፡ በእኛም አገር ሕጉ ቢኖርም አይሠራበትም፡፡ አንድ ነጋዴ የወጪውን 100፣400፣ 500…ፐርሰንት ወይም ሺህና 4ሺህ በመቶ ካላተረፈ አይሸጥም፡፡አንድ ተረት ላጫውታችሁ፡፡ ድሮ ነው፤ አንድ ሰው በየቀኑ የወርቅ ዕንቁላል የምትጥል ዶሮ ነበረችው አሉ፡፡ በየቀኑ የወርቅ ዕንቁላሉን መሰብሰብ ትቶ በአንድ ጊዜ ለመክበር “ለምን አርጄያት ሆዷ ውስጥ ያለውን ዕንቁላል አላፍስም?” ብሎ አረዳትና እስከነአካቴው አንዱንም አጣ ይባላል፡፡እኔም የምለው ነጋዴዎቹ ምን አለ ቀስ ብለው ቢከብሩ? እኛ እኮ የትም አንሄድባቸውም፤ አብረን አይደል ያለነው፡፡ ቀስ እያሉ ቢያልቡን ይሻላል እንጂ በአንድ ጊዜ ለመክበር ብለው ካረዱን የሚጐዱት እነሱው ናቸው - እንደ ባለዶሮው ማለቴ ነው፡፡ኳሷ በእነሱ እጅ ስላለች አይደል እንደፈለጉት የሚያደርጉን! ኳሷን ለምን አንቀማቸውም፡፡ እንዴት መሰላችሁ? እናድምባቸው! ለአንድ ቀን፣ ለአንድ ሳምንት፣ ለአንድ ወር ጨክነን ለሽያጭ ያቀረቡትን ነገር “አንገዛም” ብለን እናድም፡፡ ሥጋው፣ ክትፎው፣ ኬኩ፣ ቡናው፣ ማኪያቶው፣ አልሸጥ ብሎ ሲበላሽ ልክ ይገባሉ፡፡ እንዲከስሩ ፈልጌ አይደለም፡፡ በነፃ ገበያ ሥርዓት እንተዳደር ለማለት ነው፡፡ገንዘቤን እንደፈለኩ ባደርግ፣ ብቀደው፣ ባቃጥለው፣ በፈለኩት ዋጋ ብገዛ ምን አገባችሁ? የሚሉትን አይደለም እያነሳሳሁ ያለሁት፡፡ የእነሱ አኗኗሪ የሆኑትን ድሆችን ነው፡፡ ማን ይመራል? የሚለው አያሳስባችሁ፡፡ ሆድ የባሰን እኔም ሌሎችም አለን፡፡ እናንተ ብቻ ባለመግዛት፣ ባለመጠቀም፣ ተባበሩን፡፡ያኔ ብቻ ነው በነፃ ገበያ ሥርዓት መተዳደር የምንጀምረው!ጎበዝ እኔ አድማ ላይ ነኝ! እናንተስ?  ", "passage_id": "198110e30da47491c3529c760ad87155" }, { "passage": "ዓለምን የናጠ የሃያ ደቂቃዎች ስብከት ባለፈው ሐምሌ በኢራቂቱ ሞሱል ታላቁ መስጅድ ተሰማ፤ ድፍን ዓለምን ነጥጥ ውስጥ የከተተ፡፡በማንኛውም መለኪያ - ይላሉ ዛሬ ተንታኞች ስለዚያ እጅግ ደፋር የተባለ ዲስኩር ስናገሩ - ደግሞም በራሱ በእሥልምና ውስጥ በጥባጭና ግልበጣ ጠንሳሽም ነበር፡፡ መላ መካከለኛ ምሥራቅን ወደ ብዙ ደም አፍሳሽ ነውጥና ሽብር ይዞት ዘቀጠ፡፡እራሱን ከአል-ቃይዳ ገንጥሎ የወጣውና ‘እሥላማዊ መንግሥት ነኝ’ ያለው አንጁ መሪ አቡ ባክር አል-ባግዳዲ ካሊፌቱን ወይም የከሊፋ ግዛቱን ያወጀ ጊዜ የተከበሩና ፀንተው የኖሩ የሙስሊሙን ዓለም መሪዎች ምዕራቡንና መሰል ጂሃዳዊያንንም ለግልፅ ጠብና ግብግብ መጥራቱ ነበር፤ ‘ይዋጣልን’ ዓይነት፡፡በኢራቅ ሰማዮች ላይ የአሜሪካ የጦር ድሮኖች እያንዣበቡ ባሉበት የፍልሚያ አውድ ውስጥ ‘ከየት መጣ? ምን ያስባል? ምን ይፈጥር ይሆን?’ የማይባለው የ42 ዓመት ዕድሜው አል ባግዳዲ “ከሊፋ ኢብራሂም ነኝ” አለና በዓለም ዙሪያ ያሉ አንድ ቢሊዮን ሙስሊሞች እርሱን ይከተሉ፣ እርሱ ይመራቸው ዘንድ ደነገገ፡፡አል-ባግዳዲ ‘የዓለም ሙስሊሞች መሪ ነኝ’ ማለቱ ብቻ ሳይሆን በዚህ አዋጁ ከጥቀት ወራት በፊት በስልቶች ወይም ስትራተጂ ጉዳይ ላይ መግባባት ተስኗቸው እና በእርሱም አልታዘዝ ባይነት ተጣልተው ጥሎት የሄደው አል-ቃይዳም ለእርሱ እንዲንበረከክ ፣ ለእርሱ እንዲገዛ ትዕዛዝ ማውጣቱ ነበር፡፡ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡", "passage_id": "7e843384d04a8b3dcc6013962c416a1c" }, { "passage": "የሩቅ ጊዜ እውነተኛ ታሪክ ነው።ምን ለብሼ ልሳቅ የሰውየው እውነተኛ ስሙ አይደለም።በነገር አገደም አግራሞት የሚያጭርበት ጉዳይ ሲያገኝ ከት ብሎ እየሳቀ ምን ለብሼ ልሳቅ ስለሚል ነበር አካባቢው መንደርተኛው በሩቅ የሚያውቁትም ጭምር በዚህ ስያሜ የሚጠሩት።መለያው መጠሪያ ስም ሆኖ ጸደቀለት። አዳሩ\nበዚያን ዘመን ይሰሩ ለነበሩ ቤቶች ከአሰሪዎቹ ከባለቤቶቹ ጋር ተዋውሎ ጭቃውን በጭድ እያቦካ በደንብ በተለያየ ቀናት አገላብጦ ፈርመንትድ ሲሆን (ሲበስል) እንበለው የተማገረውን አዲስ ቤት ደህና አድርጎ በጭቃ ይመርገዋል።በኋላም የልስን ስራ ይሰራል።የእኛ ሀገር የቀደመው ዘመን ሲሚንቶአችን መሆኑ ነው።ዛሬም በስፋት ይሰራበታል፡፡ ብዙዎቹ የሀገራችን ቤቶች\nየሕዝቡ የመሳፍንቱና መኳንንቱ ሳይቀር ምሰሶው ቆሞ ወጋግራው ከተዋቀረና ከተገደገደ በኋላ የሣር ክዳን ይደረግለታል።ዙሪያውን የሚለሰነው ምርጥ ብቃት በነበራቸው የሀገራችን ጭቃ አቡኪና ለሳኞች ነው።ስንቱን ከተማ መንደር ሰፈር አብረው እንደቆረቆሩ፤ ስንቱን ቤት እንደሰሩ፤ የሚናገርላቸው የሚጽፍላቸው ጠፍቶ እንጂ ሰዎቹስ ምርጥ ባለሙያዎችና ባለታሪክም ነበሩ። እነ ምን ለብሼ ልሳቅን የመሰሉ ብዙ ሺዎች ፡፡ ምን\nለብሼ ልሳቅን ለየት የሚያደርገው ለየት ያለ ባህርይና አስገራሚም ስለነበረ ይመስለኛል። ግጥም የለውም። መንደርተኛና ሰፈሩ በአለባበሱ ይደመማል። ትልቁም ትንሹም።ሲመጣ ሕጻናት ይከቡታል። ያውካካሉ።ሱሪ 2 ኮት 3 ሸሚዝ 2 ከረባት 4 ሁልጊዜም መነጽሩ ባዶና መስታወት የሌለው፤ በሸሚዞቹ ኪሶች ላይ የሚሰሩና የማይሰሩ ብዙ እስክሪቢቶዎች የሚደረድር ሰው። ጸጉሩ በዘመኑ ፋሽን ኤልቪስ።ዘመኑም የእነ ኤልቪስ የዝነጣ ዘመን ነበር። በጫማ ላይ ጫማ ስለማይደረግ እንጂ እሱንም ለማድረግ አይመለስም ነበር። በዚያን ዘመን\nእንዲያ ለብሶ ከገጠር መንደር ብዙም በማትለየው የአዲስ አበባ ጥርጊያ መንገዶች ላይ ሽር ብትን እያለ በቄንጥ ሲራመድ የሁሉንም ቀልብ ይስባል።‹‹ኧረ ሳቄ መጣ›› ያሠኛል።እሱ ማንንም ከቁብ አይቆጥርም። ይህ ሰው ማነው ለሚለው ማንም መልስ አላገኘለትም።ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ ወይንም ለመጠላት ወይ ለመወደድ እንዲሉ ሆነና። አዕምሮው ልክ\nአይደለም ባዮች ብዙ ነበሩ።እነሱ እንጂ እሱማ ልክ ነኝ ብሎ ነው የሚኖረው፤ የሚሰራው።የተዋዋለውን ስራ ጭቃ ማቡካቱንና መለሰኑን አሳምሮ ይሰራል።ስራ ሲሰራ ይዘፍናል።ሰው ሰማ አልሰማ ደንታ የለውም።ዘፈኑ ሁሌም ‹‹አንቺ ልጅ›› ነው። ‹‹አሀሀሀ አንቺ ልጅ፡፡›› ምናልባት ምናልባት ይሄ ስለሚሰራው ስራ እንጂ ስለማንነቱ ብዙ የምይታወቀው ሰው ከጀርባው ምን ታሪክ ተሸክሞ ይሆን የሚለው ጥያቄ የብዙዎች ነበር። የት ተወለደ፤ አደገ፤ ተማረ፤ ቤተሰቡስ የት ነበር? ምንም ፍንጭ የለም።ብዙ ሰዎች ለማወቅ ጥረዋል።ሲጠይቁት መልሱ አጭር ነው ምን ለብሼ ልሳቅ ይልና ይንከተከታል።ምናልባት በሰዎቹ በመገረም አሊያም ዓለምን በመናቅ ሊሆን ይችላል።እኛ ያላየነው የማናውቀው የለም በሚል ውስጣዊ ምፀት ይሆናል ከት ብሎ የሚስቀው። አዛውንቶቹ ወጣቱ ሁሉም ሰው ያውቀዋል። አብዝተው ይገረሙበታል። በማይታወቀው ማንነቱ። በዚህ ሰው ማንነት ውስጥ ሌላ የተሰወረ የተደበቀ ማንነት አለ።ግን ለምን እንዲያ ሆነ ቢባል የመልሱ ባለቤት እሱና እሱ ብቻ ነው። ብዙ ሰዎች ደሞ ‹‹ምን ለብሼ ልሳቅ ይላል እንዴ፤ ይሄን ሁሉ የሀገር ልብስ ደራርቦ እየለበሰ›› ይሉና ይሽኮመኮማሉ። የሚገርመው የስራ ልብስ አለው።ለብሶ የሚመጣው ንጹህ ልብሶች ናቸው። ስራውን ሲጨርስ ተጣጥቦ ሲያበቃ ያንኑ ደራርቦ ይለብስና ሽክ ይላል። ‹‹አሀሀሀሀሀሀ አይ ምን ለብሼ ልሳቅ።›› ዛሬ ከስንትና ስንት ዓመታት በኋላ ታወሰኝ በል፡፡ ‹‹በጤናው አይደለም›› ቢሉም ‹‹እኔ እብድ አይደለሁም፤ እናንተ ናችሁ እብድ›› ይላል።‹‹ጤነኛ ነኝ›› የሚል ስንት እብድ እንዳለ መንፈሱ ሹክ የሚለው ይመስላል።ልብሱ፤ ከረባቱ፤ ሸሚዙ ኮቶቹ ይቀያየራሉ።ወይ ሰዎች ይሰጡታል ወይ የራሱ የሆነ የተከማቸ አለው።ለስራ ተዋውሎ ሲመጣ እንጂ መኖሪያው አይታወቅም የምን ለብሼ ልሳቅ።እንደሌሎቹ የእሱን አይነት ስራ እንደሚሰሩት ሰዎች ጠላ፤ ጠጅ፤ አረቄ፤ ቤት አይታይም።ቢሰጡትም አይጠጣም፡፡ አንዳንድ ሰዎች ግን እንደዛው ለብሶ አልፎ አልፎ ግሮሰሪ እንደሚገባ በሥርዓቱ ቁጭ ብሎ አዞ የተወሰነ አልኮል እንደሚጠጣ ይናገራሉ።አንድ ጊዜ ቁምጣ ሱሪውን አድርጎ በባዶ እግሩ ጭቃውን ሲለውስ ከቤታቸው ውሀ ልክ ላይ ቁጭ ብለው ሁለት የተማሩ ወጣቶች ምስጢራቸውን በእንግሊዝኛ ቋንቋ ያወራሉ። ማንም ሰው አይሰማንም ነው ነገሩ።መቼም ምንም ቢያስቡ ሊጠረጥሩ አይችሉም። እሱ ስራውን ይሰራል። ሰማ፤ ሰማ ፤ሰማና መጨረሻ ስራውን ከውኖ ተጣጥቦ ሲያበቃ ያንኑ አስገራሚ ልብሱን ከረባቱን ባዶ መነጽሩን አድርጎ ለማረፍ በሚመስል መልኩ ተማሪዎቹ አጠገብ ቁጭ አለ።እየሳቁ ምን ለብሼ ልሳቅ ታዲያስ አሉት።በተለመደው ሳቁ አውካካ።አይ እናንተ አሁን ምስጢራችሁ እንዳይሰማ ነው አይደል በወፍ ቋንቋ የምታወሩት አላቸው።‹‹ልክ ነህ ማንም እንደማይሰማ እርግጠኞች ነን›› አሉት።የተነጋገሩት ስለአብዮትና ለውጥ ስለንጉሱና ሥርዓታቸው የእኛስ በምን መልኩ ነው መሄድ ያለበት የሚል ነበር፡፡ የወጣቶቹን አፍ ያዘጋ ድንጋጤ ውስጥ የከተተ ድንገተኛ ምትሀት የመሰለ ጉዳይ ተከሰተ።በጠራ እንግሊዝኛ የተወያዩበትን ዘርዝሮ ጥያቄአቸውን በመለሰ መልኩ ነገራቸው ጭቃ አቡኪውና ለሳኙ ምን ለብሼ ልሳቅ።ደነገጡ።ማመን ተሳናቸው።እሱ ነው ሌላ ሰው እስኪሉ ድረስ።መጽሐፍቶችን በስም እየጠራ ይሄን ይሄን አንብቡ ሲላቸው ድንጋጤአቸው ሽቅብ ጎነ።ግን አላቸው ለማንም አትናገሩ ቃል ግቡልኝ። እኔ በዚህ መልኩ የምሰራው የምኖረው የእራሴን ኑሮ ነው።ደስተኛ ነኝ።ዓለምን ንቄ ሰውንም እርቄ ነው ብሎ በረዥሙ ተነፈሰ። እንዴት ብዙ የተማረ ሰው በሌለበት ሀገር የዚህ እውቀት ባለቤት አንዱ ጋ ተቀጥሮ መኖር\nሲችል ይሄንን አይነት ኑሮ ለመኖር መረጠ በሚል ወጣቶቹ በእጅጉ አዘኑ።ተደናገጡ።እሱ ግን አላቸው።ለእኔ አታስቡ አትጨነቁም።በጉልበቴ ሰርቼ እኖራለሁ።ስራ አከብራለሁ።የሰው እጅ አላይም።ልመና አልወድም።ዓለምን ስትረሳት ትረሳሀለች። ሁሉን ከረሳህ በትላንት ውስጥ ካልቆዘምክ ትኖራለህ በሉ ቻው አለና ተነስቶ ግቢውን ጥሎ ወጣ።ጉድ ጉድ ሲሉ ውለው አደሩ።ምን ለብሼ ልሳቅ ማነው።ከአሁኑ ትንሽ መገለጥ በቀር ስለዚህ ሰው ማንም ምንም አያውቅም። ሌላ ሰፈር ሄዶ ያንኑ ጭቃ ማቡካት ሲሰራ እንዲሁ የ11ኛ\nክፍል ተማሪዎች በራፋቸው ላይ ቁጭ ብለው በተሰጣቸው የታሪክ ትምህርት የቤት ስራ ላይ በእንግሊዝኛ እያወሩ ይከራከራሉ።የያኔ ተማሪ ብርቱና የቀለም ቀንድ ነበር።ለወረቀት ሳይሆን ለእውቀት የሚተጋ።ለእውቀት የሚታትር ንብ።አንባቢ፤ተከራካሪ፤ሞጋች።ብርቱ የቀለም ደቀመዝሙርና ካህን።መምህሮቹም በእውቀት የላቁ የረበቡ።እሱ ጭቃውን ጭድ እየነሰነሰ ይለውሳል።ተማሪዎቹ በጥያቄው መልስ ላይ አልተስማሙም።ተነታረኩ።አጠገባቸው ወትሮም የሚያውቁት የሚስቁበት ምን ለብሼ ልሳቅ ብቻ ነበር።ሌላ ሰው የለም። አከራካሪው ጥያቄ በፈረንሳይ አብዮት ላይ ያተኮረ ነው።ምን ለብሼ ልሳቅ አካፋውን ይዞ ጭቃውን እያገላበጠ ይሰማቸዋል። አላስቻለውም። ዝምታውን በድንገት ሰበረና ከት ብሎ ሳቀ።አንዱ ተማሪ ይሄ እብድ ምን ይስቃል ሲል አዎን እብድ ነኝ። ዘመን ያሳበደኝ በራሴ ዓለም የምኖር እብድ አለው። መልሱ ልጁን አስደነገጠው። ምን ለብሼ ልሳቅ ለጠቅ አደረገና በጠራ እንግሊዝኛ ምንድነው የምትጨቃጨቁት ሲላቸው በተቀመጡበት ክው ብለው ቀሩ። እሱ ነው የተናገረው ሌላ ሰው በሚል ጥርጣሬ።ደገመላቸው። የተከራከሩበትን ነጥብ በነጥብ እያነሳ ከመነሻው እስከ መድረሻው አካፋውን ይዞ ቆም እንዳለ አነበነበላቸው።መልሱ ይሄ ነው አለና በረዥሙ ተነፈሰ፡፡ ተማሪዎቹ አብዝተው ተደመሙ።ግን አላቸው ስለእኔ ለማንም አታውሩ ።ስለእኔም አትጨነቁ።አትመራመሩ።እኔ በራሴ የሕይወት መንገድ ደስተኛ ነኝ። ከማንም ምንም እርዳታ አልፈልግም። እስካለሁ በጉልበቴ ሰርቼ እኖራለሁ። ስራዬን አከብራለሁ።እናንተ ግን በርትታችሁ ተማሩ።አንብቡ። ለወረቀት ሳይሆን ለእውቀት ትጉ አላቸው። በተቀመጡበት በድንጋጤ ተመቱ። ከጭቃው ውስጥ ወጥቶ ተጣጥቦ ልብሱን በተለመደው ሁኔታ ለባብሶ ቻው ብሎአቸው መንገዱን ቀጠለ። ግዜው የ1966 አብዮት ዋዜማ\nነበር።ምን ለብሼ ልሳቅ ማነው? እውነተኛ ስሙና ታሪኩስ? ምን ገጥሞት ምንስ ሆኖ ይሄን የሕይወት መንገድ መረጠ? አዲስ ዘመን ሀምሌ 18/2011", "passage_id": "304fd91821603631b9bad2d841cc81b3" } ]
c0955776ed2d1a7532f52f3febdc8ac1
cb3df388848d7e3e3cde1caf920c5062
የአርባ ሰባት ዓመታት ትዝታ የቀሰቀሰው ቀለበት
 ብዙ ጊዜ ጌጣጌጦች ጠፉ ሲባል ቢሰማም ፈልጎ የማግኘቱ ጉዳይ እንደ መግዛቱ ቀላል አይሆንም። በተለይ የወርቅ ጌጣ ጌጥ ጠፍቶ የመገኘት እድሉ ጠባብ ነው።ወርቅ ውድና ተፈላጊ እንደመሆኑ ያገኘውም ሰው ቢሆን የጠፋበትን ባለቤቱን አፈላልጎ ይሰጣል ብሎ መጠበቅ የዋህነት ነው።ሊገኝ የሚችልበት እድል አንድና አንድ ብቻ ነው። ሰው እጅ ያልገባ ከሆነ ብቻ።ይህ ሲሆን ከእለታት አንድ ቀን ሊገኝ ይችል ይሆናል። የጌጣጌጦች መጠን አነስተኛ መሆን ከሚጠፉበት ቦታ ውስብስብነት ጋር ተዳምሮ የመገኘት እድላቸውንም በእጅጉ ያጠበዋል። በዚህም የጠፉት ጌጣጌጦች ከናካቴው ተሰውረው ሊቀሩ አልያም ጥቂት ጊዜ ፈጅተው ባጋጣሚ ሊገኙ ይችላሉ ።ጌጣጌጦች ከጠፉ ረጅም አመታትን አስቆጥረው ሲገኙ ግን ግርምትን ያጭራሉ። ስካይ ኒውስ ከሰሞኑ ከወደ አሜሪካ ይዞት ብቅ ያለው መረጃም ይህንኑ ሃቅ ያረጋግጣል። በ1973 ገና አፍላ ወጣት የነበረችው ዴብራ ሜኬና ብረንስዊክ ሜይን በተሰኘችው የአሜሪካ የባህር ዳርቻ ከተማ በሚገኝ አንድ የእቃ ማስቀመጫ ክፍል ውስጥ ባሏ ያደረገላትን ቀለበት ትጥላለች። ቀለበቱ ከጠፋ ከአርባ ሰባት አመታት በኋላም በቅርቡ በአንድ የብረት ሰራተኛ በፊንላንድ ደን ውስጥ ተቀብሮ ተገኝቷል። ሜኬና በአሁኑ ወቅት 63 ዓመቷ ሲሆን፣ በሞርስ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ እያለች በፖርትላንድ ውስጥ ቀለበቱ እንደጠፋባት ባንጎር የተሰኘው ጋዜጣ በወቅቱ ዘግቦ እንደነበር ድረገጹ አስነብቧል። ትምህርት ቤቱን የሚለይ ምልክት ያለበት ይኼው ቀለበት የቀድሞ የሜኬን ባል በትምህርት ቤትና በኮሌጅ ተገናኝተው ሲያወሩ ያበረከተላት እንደነበር ታውቋል። ባለቤቷ ሻውን ለስድስት አመታት ያህል ከያዘው የካንሰር ህመም ጋር ሲታገል ቆይቶ በ2017 ህይወቱ እስካለፈበት ጊዜ ድረስ ባልና ሚስቶቹ ለአርባ አመታት ያህል በትዳር መቆየታቸውም ተጠቅሷል። ሸዋን የኮሌጅ ትምህርቱን ሳያጠናቅቅ ቀለበቱን ለሜኬን የሰጣት ሲሆን፣ ሆኖም መጋዘን ውስጥ በድንገት እንደጣለችው አስታውሳለች።የብረት ሰራተኛው ቀለበቱን ከተቀበረበት እስካገኘበት ጊዜ ድረስ ተረስቶ እንደነበርም ገልፃለች። የብረት ሰራተኛው ሰማያዊ ፈር ያለውን ብራማ ቀለበት ሲያገኝ የብረት መመርመሪያ ተጠቅሟል፤ ብዙ ጊዜ ያገኝ የነበረው ግን የብረት ኩባያ ወይም ቁራጭ ብረት እንደነበረም የፊንላንድ ሚዲያ ዘግቧል። በቀለበቱ ላይ የተፃፈውን የትምህርት ቤት ምልክትና የምርቃ አመተ ምህረት በመያዝ አልሙኒ ከተሰኘ ማህበር ጋር እንደተገናኘም ሚዲያው ጠቅሷል። በዚሁ መሰረት መኬን ከረጅም አመታት በፊት የጠፋባት ቀለበት እንደተገኘና መውሰድ እንደምትችል በስልክ ሲነገራት እምባ እንደተናነቃትና የወጣትነት የፍቅር ጊዜዋን እንዳስታወሳት ገልፃለች። ‹‹ቀናነት በጎደለበት በዚህ ዘመን እንደዚህ አይነት ሰዎችን ማግኘት በጣም ይከብዳል›› ስትልም ተደምጣለች። ‹‹በአለማችን ጥሩ ሰዎች አሉ፤ ስለዚህ ተጨማሪ ጥሩ ሰዎችን እንፈልጋለንም›› ብላለች። ሜኬና ከጠፋ ረጅም አመታትን ያስቆጠረው ቀለበት እንዴት በፊንላንድ ደን ውስጥ ሊገኝ እንደቻለ ምንም የምታውቀው ምክንያት እንደሌለ አስታውቃለች። ምን አልባት ባለቤቷ ሹዋን በ1990ዎቹ አካባቢ አብዛኛውን ጊዜውን በፊንላንድ ያሳልፍ በነበረበት ወቅት እሱን ብላ ስትሄድ ቀለበቱ አካባቢው ላይ ሳይጠፋ እንዳልቀረ ጠቅሳለች። አዲስ ዘመን የካቲት 17/2012አስናቀ ፀጋዬ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=27863
[ { "passage": "ጊዜው ሁለተኛውን ሲዝን (ክፍል) 'ቺዊንግ ገም' እየፃፈች የነበረችበት ወቅት ነበር። በአንደኛው ቀን መሃል ላይ ከመፃፏ እረፍት ወሰደችና ከጓደኛዋ ጋር አንድ ሁለት ሊሉ ሄዱ።\n\nከዚያም ብዙ ነገሮች ጨለማ ሆኑ።\n\nበነገታው ጥዋት ስትነሳ አንዳንድ ነገሮች እንደ ህልም ትዝ ይሏት ጀመር። መጠጧ ላይ የሚያደነዝዝ ነገር እንደተጨመረበትና እንደተደፈረችም ተረዳች።\n\nይህ ጨለማና ፈታኝ የሆነው አጋጣሚዋን 'አይ ሜይ ዲስትሮይ ዩ' (ላጠፋህ(ሽ) እችላለሁ) በሚልም ፃፈችው። \n\nከመፃፍ በተጨማሪ ወደ ፊልም ቀየረችው፤ ራሷም ተውናበታለች፣ ከሌላ ባለሙያም ጋር በመሆን ያዘጋጀችው እሷ ናት። \n\nበቢቢሲም ላይ የቀረበው ክፍል ብቻዋን የምትተውንበት ነው።\n\n\"ለመፃፍ ሁለት ዓመት ተኩል ወስዶብኛል። በወቅቱም ተጨማሪ ሥራ እየሰራሁ አልነበረም\" በማለት ለሬድዮ ኒውስ ቢት ተናግራለች። \n\n\"በጣም ፈታኝና አስቸጋሪ ወቅት ብቻ ሳይሆን ጥቃቱ በአሁኑ ወቅትም እየተፈፀመብኝ እንዳለ ተሰምቶኝ ነበር፤ ነገር ግን መፃፌ እፎይታን ሰጥቶኛል\" ብላለች። \n\nሬፕ ክራይሲስ የተባለው ድርጅት ባወጣው መረጃ ከአስራ ስድስት ዓመት በላይ የሆኑ 20 በመቶ ሴቶችና 4 በመቶ ወንዶች እንደሚደፈሩ ነው። \n\nይህ መረጃ በእንግሊዝና በዌልስ ያለውን ነው የሚያሳየው።\n\nቢቢሲ ባደረገው የማጣራት ሥራ በጎርጎሳውያኑ 2015 እና 2019 2 ሺህ 600 የሚሆኑ ሰዎች መጠጣቸው ላይ የሚያደነዝዝ ነገር በመጨመር እንደተደፈሩ ነው። ከእነዚህም ውስጥ 72 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች ናቸው። መረጃው የተጠናቀረው ከእንግሊዝና ከዌልስ ነው። \n\n\"ራሳችንን ጥፋተኛ ማድረህ ማንንም አይጠቅምም\"\n\nበፊልሙ ላይ ያለችው የሚኬላ ገፀ ባህርይ አራቤላ በተለያዩ የስሜት ምስቅልቅሎች ውስጥ ትመላለሳለች። በተቻለም መጠን ከደረሰባት አደጋም ለማምለጥ ትቀልዳለች፣ ትስቃለች። ፊልሙ ላይ ያለችው ገፀ ባህርይ አራቤላ የሚኬላ የእውነተኛ ህይወቷም ነፀብራቅ ናት። \n\n\"እንዲህ አይነት አሰቃቂ ክስተተቶች ሲፈጠሩብን እንዲሁም የሚያስታውሱን ነገሮች ሲበዙ በተለያየ መንገድ ለማለፍ እንሞክራለን፤ እንታገላለን። አንዳንድ ጊዜም በማዘን ብቻ አይደለም\" ብላለች።\n\n\"አንዳንድ ጊዜም የደረሰብንን ነገር ለመካድም እንሞክራለን። ሰዎች እንዲያምኑን እየለመንን አይደለም ነገር ግን ሰዎች ስለደረሰብን ነገር በመንገር እንድናምናቸው ይፈልጋሉ\" ትላለች።\n\nበፊልሙ ላይ ያለችው አራቤላ በጓደኞቿ እርዳታ የት እንደተደፈረችና በማን እንደሆነ ትደርስበታለች። \n\nበፊልሙ ላይ የተሳሉት የጓደኞቿ ገፀ ባህርያትም በፍቅር ግንኙነት ወቅት የሚፈልጉትንና የማይፈልጉትን ነገር ለማለት ድምፃቸውን ከማሰማት ጋር ተያይዞ የራሳቸው የተወሳሰበ ታሪክ አላቸው።\n\n\"አጠቃላይ ፊልሙ በወሲብ ግንኙነት ወቅት ፈቃድ ጠቃሚ እንደሆነ ያስረዳል። ምን ያህል ፈቃዳችን እንዴት በሰዎች ጉልበት ሲነጠቅ፤ በራሳችን መወሰን አለመቻላችን የሚፈጥረውን ስሜት ነው የሚያሳየው\" ትላለች ሚኬላ። \n\n\"በደረሰብን ነገር ወደ ራሳችን መጠቆምና ራሳችንን ጥፋተኛ ማድረግ ማንንም አይጠቅምም\" የምትለው ሚኬላ \"ለራሳችን ደግ ልንሆን ይገባል። በማንፈልግበት ወቅት ጮክ ብለን 'አይሆንም' ባለማለታችን ልንፀፀት አይገባም። ለራሳችን ይቅርታ ልናደርግ ይገባል።\" \n\nከዚህ ፊልምም ብዙዎችም እንደሚማሩ ተስፋ አላት። \n\nበተውኔቱ ላይ ያለችው አራቤላ በሰላሳዎቹ እድሜ የምትገኝ ሲሆን በትዊተር አማካኝነት ከፍተኛ እውቅናን አተረፈች። መፅሀፍም ለማሳተም ስምምነት ላይ ደረሰች። እንዲህ እውቅና ላይ ብትደርስም ግራ መጋባቷም የበዛ ነው። \n\n\"የሚሊኒየሙ የዓለም ገፅታ ነው። በማኅበራዊ ሚዲያ ዘመን ሰዎች ህይወታቸውን እንዴት በጥሩ መልኩ እየኖሩ እንደሆነ ማሳየት ይፈልጋሉ።\" \n\n\"ከስልኩ ወይም... ", "passage_id": "236f438da84c6e43a80af328030f9e31" }, { "passage": "‹‹በሰው የሳቁት በራስ ይደርሳል›› ሲባል ሰምቼ ይኸው 24 ሰአት ሴቶችን በሚላከፉት ወንዶች እስቃለሁ፡፡ ግን ‹‹ወፍ የለም›› 1ሺ ሴቶች ብቻ ናቸው የሚከተሉኝ፡፡ (በፌስ ቡክ)\nየቅርብ ጓደኞቼ በዚህ ሁኔታዬ እብድ ይሉኛል፡፡ድርጊቴ እብደት ከመሰላቸው ግን እንደ እነርሱ ሥራ ከመፍታት ይሻለኛል፡፡ ህይወት በየመንገዱ ዳር ዘፍዝፋ ሲጋራና ጫት ከምታስጨብጠኝ ጠበሳ ይሻለኛል፡፡ ይህ ጊዜ የኔ ወርቃማው የጠበሳ ዘመን ነው፡፡ በእርግጥ በአለካከፌ ልብ የለሽ ነገር ግን ‹‹ወንድ ነን›› ከሚሉት ውስጥ አንዱ ነኝ፡፡ ደግሞም ለለከፋ ያህል እንጂ ማንንም ማግባት አልፈልግም፡፡ ወንዶች ጋብቻ ሲነሳብን በራችን ላይ ሳማ የምንተክል ይመስል ግብግብ ያደርገን የለ፡፡እንደለመድኩት የታክሲ ውስጥ ለከፋ ለመጀመር አንድ ወር ሙሉ በሁሉም አቅጣጫ የሚሄዱትን ታክሲዎች ማደን ጀመርኩ፡፡ ምክንያቱም ወቅቱ የኔ ወርቃማው የለከፋ ዘመን ነው፡፡ የምቀመጠው ከኋላ ወንበር ነው፡፡ ታዲያ እኔ ወንበር ከመያዜ በፊት የምትለከፍ ሴት ከኋላ ወንበር ላይ መግባቷን ማረጋገጥ ስለሚኖርብኝ ወደ መስኮቱ ጠጋ ብዬ እመለከታለሁ፡፡ ይህ አይነት የቅንጦት ድርጊት የታክሲ ሰልፍ ባለባቸው አካባቢዎች አይሰራም፡፡ ምክንያቱም እንኳን ከኋላ የተቀመጠውን ሰው አማርጦ በማየት መግባት ይቅርና የትርፍ ትርፍ ላይ የተቀመጠውን ሰው ለማስተዋል እንኳን ጊዜ አይበቃም፡፡ለዛሬ ከፒያሳ መገናኛ በሚጭነው ታክሲ ውስጥ በለመድኩት ቦታ ተቀምጫለሁ፡፡ አጠገቤ ‹‹ከቀሚስ የተሰራ›› አጭርዬ ቀሚስ ለብሳ፣ ከፊቷ የሚበልጥ ስፋት ያለው መነጽሯን አድርጋ፣ ጧ…ጧ…ጧ የሚል የማስቲካ ድምጽ እያሰማች ዘና ብላ የተቀመጠች እንስት አለች፡፡ የምታኝከው ማስቲካ ‹‹ጦር ማስቲካ›› እንድሆነ ከጩኸቱ ማስተዋል ችያለሁ፡፡ ልጅቷን ለማዋራት የመነሻ ቃላት ይሆኑኝ ዘንድ ካነበብኳቸው መጽሐፍት ስለ ፍቅር የሚያወሩትን ባስታውስ ከየት ላምጣው፡፡ከትንሽ ደቂቃ ጉዞ በኋላ የመጣው ይምጣ አልኩና ድፍረት ቢጤ መዘዝ አደረግኩ፡፡ ምክንያቱም ይህ ጊዜ የኔ ወርቃማው የጠበሳ ዘመን ነው፡፡ ጅንጀናውን ለመጀመር ብዬ ወሬ እንደመጀመር ያህል ‹‹ውይ የዛሬው ሙቀት ድንጋይ ያቀልጣል አይደል ቆንጂት?›› ከማለቴ ‹‹ለዚያ ነዋ ያላበህ›› አለችኝ፡፡ በፍርሃት ከግንባሬ የሚፈሰውን ላቤን እየጠቆመችኝ፡፡ አንድ ሁለት ጊዜ ሌሎች ጠበሳ ነክ ቃላትን ወርወር ባደርግላትም ‹‹አንተ ሂድ ከዚህ! በኩርኩም ብዬ ኖርማል እንዳላደርግህ›› ስትለኝ ከዚህ ቀደም ባለማወቅ ካራቲስት ስላከፍ የደረሰብኝን የጫማ ጥፊ መዓትና ለሳምንት ያህል ጎድኔን ስቆጥር መክረሜ ታወሰኝና ፊቴን አዙሬ ተቀመጥኩ፡፡ ልቤ ግን አሁንም ማጉረምረም አልተወም፡፡የኔን የጠበሳ ወርቃማ ዘመን በስኬት ሳልጨርስ ተስፋ አልቆርጥም አልኩና በዚሁ ቀን በአንዱ ታክሲ ውስጥ ሌላ ጉድ ገጠመኝ፡፡ በጣም ቆንጆ የሚል ቃል የማይመጥናት መልከ መልካም ሴት ከኋላ ወንበር አጠገቤ ተቀምጣለች ከልጅቷ በሌላኛው በኩል የተቀመጠው ሌላው የኔ ቢጤ እንቅልፍ እንዳስቸገረው ዓይነት ልጅቷ ትከሻ ላይ በተደጋጋሚ ይተኛል፡፡ በማያገባኝ ነገር ውስጥ ገብቼ በቅናት እርርር አልኩኝ፡፡ሲፈልግ ወገቧ ላይ ሲፈልግ ጉልበቷ ላይ ይጋደማል፡፡ ምርቃና እንዳስቸገረው ሰው ሲቅበዘበዝ ልጅቷ መናገር ፈርታ ኖራ ወደ እኔ ፈቀቅ ስትል የመጥበስ እድሉን ለማግኘት ይበልጥ ተመቸኝ፡፡ ኋላ ላይማ ቀና ብሎ አላይ አለኝ እንጂ በደንብ እንዲደገፋት በዓይን ጥቀሻ ልነግረው ዝግጁ ነበርኩ፡፡ ልጅቷም ከዚህ የኔ እጅ እጅ የሚል የጠበሳ ወሬ፣ ከዚያ ደግሞ ጭነት እንደበዛበት አህያ ያዘነበለ ሰው ሲያስቸግራት በድንገት ረዳቱን ጠርታ ‹‹አባት ቦታ ቀይረኝ የመኪና ትራስ አደረገኝ እኮ›› አለችው፡፡ታክሲ ውስጥ ያሉት ተሳፋሪዎች ከቁጥጥር ውጭ የሆነ ሳቅ አሰሙ፡፡ ንግግሯ እኔን ለሳቅ ባይጋብዝም ሳቁን ለመካፈል ያህል ሰዎቹ ስቀው ሲጨርሱ ብቻዬን አገጠጥኩ፡፡ በዚህ ሁኔታ የተናደደች ልጅት ይቅርታ አሳልፈኝ ልወርድ ነው አለችኝ፡፡ ቦታው ሌላ ትራንስፖርት እንደማይገኝበት ስላወቅኩ አዛኝ መስዬ አብሬያት ወረድኩ፡፡ እናቱ…እናቱ… እያልኩ ጥቂት ተከተልኳት፡፡ በሰከንዶች ሽርፍራፊ ከስፓልቱ ተንጋልዬ የለከፋ ውጤትን ቀመስኩት፡፡ (በተለመደው ካራቴ) ብዙ ሰዎች ከበውኝ ሲስቁብኝ ከቆዩ በኋላ ጎተት አድርገው ከመንገዱ ዳር አስቀመጡኝ፡፡የጠበሳ ወርቃማው ዘመኔን በዝምታ ከማልፍ ብዬ አሁን ላይ አቅሜን መጥኜ መላከፍ ጀምሬያለሁ፡፡ የኔ ቢጤ የሆኑ አንገሽጋሽ ጠባሾች ግን ያለአቅማቸው ፍቅራቸውን በግጥም መግለጽ ይወዳለሉ፡፡\nኃያሉ ፍቅርሽ ————— ያ ኃያል ፍቅርሽ\nጉድ ሰራኝ ቄጠማ ሆነልሽ ክንዴ፤\nውስጥ ውስጤን እያስጨነቀ አልወጣም አለኝ ከሆዴ! ዓይነት ግጥም ለለከፋ ምን ሊረባ ነው፡፡ እንዲህ ተብሎ የተገጠመላት እንስት በእርግጠኝነት ‹‹ለመሆኑ ግጥሙን የጻፍከው መጸዳጃ ቤት ስትገባ ድርቀት አስቸግሮህ ነው እንዴ? አለማለቷን እጠራጠራለሁ፡፡በዚህች ምድር ለጾታዊ ለከፋ ሲሉ ልባቸው የደማ ዕልፍ አዕላፋት ተለካፊዎች መኖራቸው አይካድም፡፡ ሆኖም እውቅና የሚሰጣቸው ቀርቶ የሚናገርላቸው እንኳን የለም፡፡ እንግዲህ ተላካፊዎች በፍቅር ራሳችንን እንድንችል ዋስትና የሚሆኑን የምንለክፋቸው ሰዎች ሳይሆኑ የራሳችን የልብ ቁጥብነት ነው፡፡ የቃላት ተኳሽ የልብ ፊት አውራሪ ጠባቂያችንም ምላሳችን ናት፡፡ እርሷ ካልተቆጠበች የውትወታ አውታሩ ልባችን በሠላም መጓዝ አይችልም፡፡አዲስ ዘመን ታህሣሥ  5/2011አዲሱ ገረመው", "passage_id": "733ff294d7b656ba7cc9c44a38f3cdb4" }, { "passage": "ስትገነባ ሲፈርስባት ደግማ ስትክበው መልሶ ሲናድ … እኔ አንድ ጫማ ሰፍቼ ጨረስኩ። ከመደቧ ላይ ትንንሽ ቋጥኞች አስመስላ እንደየ ዓይነታቸው ማሰናዳት ከጀመረች ቆይታለች፤ ግን አልሆነላትም። አንዱን ደርድራ ስታበቃ ሌላኛው ይፈርስባታል። ድንቹን ያስተካከለች መስሏት ዘወር\nከማለቷ ተደርምሶ ከሽንኩርቱ ይቀላቀላል። እርሱን ለማስተካከል ስትጥር ደግሞ ከወዲያ የከመረቻቸው ሎሚዎች ተዘረጋግፈው ስራዋን ያበዙባታል። ነገሯ «ውሃ ቅዳ፤ ውሃ መልስ» ስለሆነባት አሳዝናኝ እርሷኑ መከታተል ያዝኩ። ይህቺ ሴት ከጎረቤት መደቦች በላይ ስራ እንደሚበዛባት ከኔ በላይ ምስክር አያሻም። በጉሊታችን ከበዛው ወጪ ወራጅ ይልቅ ዓይኔ አዘውትሮ የሚያርፈው እርሷ ላይ ነው። እርግጥ ነው፤ የእኔ ቆጥ ከእርሷ ፊት ለፊት መገኘቱ ሳልፈልግም ጭምር እንዳያት ያደርገኛል። የማያት ግን በምክንያት ነው፤ ነገረ ስራዋ ሁሉ ታሪክ ስላለው። አንገቷን አቃንታ አይኖቿን ስመለከት በስሱ ጭል ጭል ከሚል ዓይነ ውሃዋ ተቀድቶ የማያልቅ ታሪክ አነባለሁ። ከአጥንቷ ከተጣበቀው የጉንጯ ቆዳ ላይ የበለዘው ስፍራም አንዳች የህይወት ካርታ የተሳለበት ይመስለኛል። አሁንም አሁንም በድንችና ሽንኩርት ቁልል መሃል ወዲያ ወዲህ ከሚል የእጇ አይበሉባ የተዘረጉት የደም ስሮቿም መድረሻ የሌለውን አቅጣጫ የሚጠቁሙ ይመስለኛል።ካጠረው ቁመቷ ላይ የከሳው ሰውነቷ ተዳምሮ ወገቧ ሰበር ማለቱን ላስተዋለ፤ አንድ ሃሙስ የቀራት በሽተኛ ትመስላለች። ከመደቧ ስትቀመጥ ኮስሟና ሰውነቷ ከቁልሎቹ አይጎላም፤ በዚያ ላይ ጃንጥላ ስትደርብበት ደግሞ ከነመኖሯም አትታይም። እንዲያም ሆኖ ቀኑን ሙሉ እየካበች የሚፈርስባትን አትክልት በሸክም የማጓጓዝ ብርታት አላት።መኖሯ የሚታወቀው ሁሌም ከእርሷ አቅጣጫ ግርግር ስለማይጠፋ ነው። ብቻዋን የምታሳ ድጋቸው ልጆቿ ቢደርሱላትም እናታቸውን የሚያሳርፉ አልሆኑም፤ ሁሌም የገበያተኛውንና ነጋዴዎችን ቀልብ የሚይዝ ሰቀቀን ይጭሩባታል። እረፍት የሚነሷት ጎረምሳ ልጆቿ ድንገት ደርሰው አንዳች ረብሻ ይፈጥሩባታል። ብዙ ጊዜ የተለያዩ ሰዎች ስሞታ ሲያነሱላት እመለከታለሁ። «ልጆችሽ እንዲህ አድርገው፤ እንዲህ አጥፍተው» እያሉ ይከሱላታል። ይህን ሲሏት በሰቀቀን ከሳሾቹን አሻቅባ ከመመልከት በቀር የምትፈጥረው ነገር ባይኖርም፤ በልጆቿ ፋንታ ይቅርታ ትጠይቃለች። እንደምት ገስጻቸውና እንደሚታረሙም ታስረዳለች። እን ዲህ ሆና ሳያት እንደ ድንቾቿ ሁሉ ከቀለሰችው ጎጆ አንድ ማገር፤ ከገነባችው ህይወቷም ቅንጣት ተስፋ ሲናድ ይታየኛል።ወዲያው ሃሳብ ይይዛታል፤ እንደ ሌሎች ነጋዴዎች ገበያዋን በንቃት አትጠብቅም። ከሳሾቹ ከሄዱም በኋላ አገጯን ከእጇ ላይ አስደግፋ በሃሳብ ጭልጥ ትላለች። እንዲህ ስትሆን ታሳዝነኛለች፤ የእኔም ሃሳብ በእርሷ ላይ ይደረባል። ከትካዜዋ መለስ የምትለው ገበያተኛ ሲመጣ ነው። አፍታም ሳትቆይ ሁለመናዋ እርሷን የማይመስል ሴቷ ልጇ ትመጣለች። ከልብሷም ከመልኳም እንዳማረች እናቷን ትጠጋለች፤ አይናማዋን ልጅ ስመለከት ልቤን ይሞቀዋል። ግን ብዙም አይቆይም፤ ከእናቷ ጋር ከምታደርገው ጥቂት የቃላት መመላለስ በኋላ ስሜቴ በበረዶ ይተካል። እናት አንገቷ ላይ ከምታንጠለጥለው ከረጢት መሰል ቦርሳዋ ከሸጠችው ቆንጥራ ትሰጣታለች። ልጅት ግን ተጨማሪ ካልተሰጣት አትንቀሳቀስም። እርሷን ከመሸኘቷ በዱቤ የቤት ዕቃ የሚሸጠው ነጋዴ ደርሶ ያፈጥባታል። በችርቻሮ የምትለቃቅመው ገንዘብ ከቤቷ ሳታደርስ እዛው ትጨርሰዋለች። እርሷን መከታተል ከጀመርኩ እንስቶ የደሃ መጫሚያዎችን እየጠገንኩ በምገፋው ኑሮዬ ማዘንና ማማረር አቁሜያለሁ። በጊዜ ብዛት ጠረን የፈጠሩት ጫማዎችም ቢሆኑ ለአፍንጫዬ ቤተሰብ ሆነዋል። ቀልቤ ከዚያች ሴት ስለሚሆን፤ ውሎዬን እንድትጋራ የምከፍታትን ሬዲዮንም አድምጫት አላውቅም። ዓይኔን ከወዲያ ጥዬ ቆዳውን ከሶሉ ለማያያዝ ስታገልም ወስፌ ከእጄ ቢሰካም የሚሰማኝ ነገር የለም።አንድ ረፋድ ላይ አንድ ሁለት መደብ እንደ ሸጠች በሚሯሯጡ ሰዎች ትንሿ ጉሊታችን ትረበሽ ጀመር። ከፊት የቀደመው ተባራሪ የመከረኛዋ ሴት ልጅ ነው፤ አባራሪዎቹ ከኋላው ድንጋይና ዱላ ይዘው ሊደበድቡት ይከተሉታል። እናት ለማስጣል ተነሳች፤ እርሱ እንደ ልጅነቱ ከእናቱ ጉያ ሊደበቅ፤ እርሷም ልትሸሽገው ነበር። ግን አልደረሰችበትም ዓይኗ እያየ ደብድበውት ሄዱ። ሰዎች ከአንድ ጥግ አስቀምጠው ሊያረጋግጉት ሞከሩ፤ ለቅሶዋ ግን የሞተ ያህል ነበር። እኔ ብቻ የምመለከተው ምሬቷ አፍ አውጥቶ መናገር ጀመረ። ውስጧ ያለው ብሶት አንድም በእንባ አንድም ሳግ በሚቆራርጠው ሳጓ ሲፈስ ይበልጥ አዘንኩላት። ለምን እንደሆን እንጃ እያንዳንዱ እንቅስቃሴዋ መንፈስን የሚይዝ ታሪክ አለው። አጋሮቿ ከበው ሊያባብሏት ሲሞክሩ፤ ልቤ አብሯት እያነባ ነበር። ከሰው ፊት እንዳላነባ ስለሰጋሁ ወትሮውንም ብከፍት እንጂ የማልሰማውን ሬዲዮ ድምጽ ጨመርኩበት። በአስገምጋሚ ድምጹ ዜና የሚያነበው ጋዜጠኛ «… በተባለ ስፍራ በተቀሰቀሰ ግጭት፤ … ያህል ሰዎች ሲሞቱ … የሚሆኑት ደግሞ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቀሉ» ይላል። ጋዜጠኛው ሃተታውን ሲቀጥል የእኔ ቀልብ መልሶ ከዚያች ደሃ ሴት አርፈዋል። እንባ ያቀረሩት\nአይኖቼ እንባዋን ሲመለከቱ\nአእምሮዬ ጥያቄውን ማዝነብ\nጀመረ። ቀልቧ ከቀልቤ\nለምን እንደተሳሰረ፣ ሳያት\nለምን እንደምፈዝ፣ እያንዳንዱ\nየአካል ክፍሏ ለምን\nታሪክ እንደሚሆብኝ፣ ሁኔታዋ\nሁሉ ለምን አንጀቴን\nእንደሚያላውሰው፣ …።\nየገባኝ ቆይቶ ነው፤\nለካስ በእርሷ ውስጥ\nስመለከት የቆየሁት ስትክብ\nየሚናድባትን፤ ልጆቿ ሁሉ ጎርምሰው\nበግልፍተኝነት ችግር የሆኑባትን\nሃገሬን ነበር።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 14/2011", "passage_id": "488890826ed8f2f69f2c6648b8d0c7a5" }, { "passage": "ቤቴልሄም ጌታቸው ገና አፍላ ሳለች የአምስተኛ ክፍል ተማሪ ሆና የሚኒ ሚዲያ ክበብ አባል እንደነበረች ታስታውሳለች። ያኔ \"መጥፎ ጓደኛ\" የሚል የእራሷን ድርሰት ፅፋ በልጆች ዓለም የሬዲዮ ፕሮግራም ላይ ማቅረቧን ትናገራለች። \n\nቤቲ ድምጿ ወፍራም ስለሆነ በድርሰቱ ላይ ወንድ ሆና ነበር የተወነችው። ከዚያ በኋላ ደግሞ ፈርጥ የቲያትር ቡድን ውስጥ ከድምፃዊ አብነት አጎናፍር ወንድም ካሳሁን አሰፋ ጋር መተወን ጀመረች። \n\nመርካቶ - \"አንድ ህልም ለ20 የሚታይበት ሰፈር\"\n\nቤቲ ልጅነቷን ስታስታውስ ተወልዳ ያደገችበት ሰፈርን አትረሳም። ለሙያዬ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል የምትለው ይህ ሰፈር ችምችም ያሉ ቤቶች የሚገኙበት፣ ማህበራዊ ህይወቱ የተሟሟቀ ነው። \n\n• ባህልን በኤሌክትሮኒክ ሙዚቃ የቀመመው ሮፍናን\n\n• ስለኢትዮጵያ የቤተ ክርስቲያን ስዕሎች ምን ያህል ያውቃሉ?\n\n• ተፈጥሮን በብሩሽ የሚመዘግበው መዝገቡ\n\n• “ከወጡት ስራዎቼ ይልቅ ገና የሚወጡት ናቸው ትልቅ ቦታ ያላቸው” አለማየሁ ገላጋይ \n\nከአዲስ አበባ የትኛውም አቅጣጫ ሰው ወደ መርካቶ ይፈሳል። ከሀገሪቱ የትኛውም አቅጣጫ ሰው ይጎርፋል። መርካቶ ሞላሁ አትልም፤ ሁሉንም ተቀብላ ማህበራዊ ህይወቷን አዛንቃ ለልጆቿ ታቀብላለች። እንደ ቤቲ ከሆነ ሕይወት በመርካቶ ፈዝዛ አታውቅም። ከነሙሉ ወዟ ትገማሸራለች። \n\nመርካቶ ለሐሜት አትመችም ትላለች ቤቴልሔም። ስሟን በክፉ ከማንሳት በጥበብ ማነሳሳት ይቀላታል። በዚች ትንሿ ኢትዮጵያ ድራማ ያልሆነ ነገር አይታያትም። ትራጀዲ ገጥሞት የሚንሰቀሰቅ አልፎ ሂያጅ መንገደኛ፣ የሚያፍነከንክ ገጠመኝ ያለው የጎረቤት ልጅ በአውቶብስ ተራ አይጠፋም ባይ ናት።\n\nበመርካቶ ሕይወት ሚስቶ ናት ። የተለያዩ ክልል ሰዎችን አነጋገር ለመቅዳት፣ ኢትዮጵያን ሳይዞሩ ደጃፋቸው ድረስ መጥታ ለመመልከት መርካቶዎች የታደሉ መሆናቸውን ትመሰክራለች። \n\nጥበብ ናት መርካቶ፣ ጥበበኞችም ሞልተውባታል የምትለው ቤቲ ዋኖስ ኮመዲን እንጀራዬ ያለችው ፕሮ ፕራይድ ውስጥ ነው። ፕሮ ፕራይድ የተሰኘው ግብረ ሰናይ ድርጅት የከተማ ድህነትን ለመቀነስና የፀረ ኤች ኤይቪ ስራዎችን ለመስራት መርካቶ ውስጥ እግሩን ሲያስገባ ቤቲ የባህል ቡድኑ አባል ሆና ተቀላቀለች። \n\n\"ያኔ እኔም ደምሴም ብቻችንን ነበር የምንሰራው\" ትላለች ቤቴልሄም። የሁለቱ ኮመዲያን ለየብቻ መስራት ግን ቡድኑን ያስተባብር ለነበረው ነብዩ ለሚባል ጓደኛቸው አልተዋጠለትም። ሁለቱ ቢጣመሩ አዲስ ነገር እንደሚሆንና ለእነርሱም የሙያ እድገት፣ ለተመልካቾችም አዲስ ነገር ማቅረብ እንደሆነ ተሰማው። እንዲጣመሩ ሀሳብ አቀረበ፤ ሀሳቡን ተቀበሉት።\n\nዳቦ ባይቆረስም ዋኖሶቹ ተባሉ። \"ዋኖስ የወፍ አይነት ናት ሌሎችን ወፎች የምታዝናና\" ትላለች ቤቲ። \n\nበ1993 የአለም የኤድስ ቀን እንደ አዲስ አመት ነበር የሚከበረው ትላለች ጊዜውን ስታስታውስ። ትልልቅ ዝግጅቶች በየአዳራሹ፣ ድንኳኖች በየቀበሌው ተጥለው፣ ግድግዳዎች በተለያዩ ፖስተሮች አጊጠው፣ ቲሸርት፣ ኮፍያ ተዘጋጅቶ ሙዚቃ፣ ጭውውት እየቀረበ ይከበር ነበር። \n\nእርሷ ታዲያ ያኔ ፕሮፕራይድ ባዘጋጀው መድረክ ላይ ከሽመልስ በቀለ ጋር መድረክ የመምራት እድል አገኘች። ሽመልስ አደነቃት። በፊትም የጥበብ ጥሪ አለኝ ብላ በየመድረኩ ላይ መክሊቷን ትፈልግ ነበር የዛን እለት አገኘችው። ኮመዲያን ቤቴሊሄም ጌታቸው በኮሜዲ አለም ስሟን ፃፈች። \n\nቀጣዩ ስራ የተፃፈው ስሟ በጊዜ ድሪቶ እንዳይደበዝዝ ተግቶ መስራት ነው። ለዚህ ደግሞ የዋኖሶች አዲስ ጥምረት አገልግሏታል። የዋኖሶችን አዲስ ጥምረት በትርኢት መካከል መፈተን ሲፈልጉ ደግሞ ሜጋ የኪነጥበባት ማዕከል መድረክ አገኙ። \n\n19 94 አ.ም የዘመን መለወጫ በዓል ምሽት ዋኖሶቹ አዲስ የኮመዲያን ጥንዶች... ", "passage_id": "5f6ea437b431d54f5baa8a0ed2ca681a" }, { "passage": "\"ከዚያማ የምሽቱ ህይወት ይጀመራል። ሙዚቃው ያለማቋረጥ ይንቆረቆራል። እኛም በምናውቀው ሩምባ፣ ቡጊውን ለመደነስ እንወናጨፋለን\" ይላሉ። \n\nቯልስ ለመደነስ ሙከራ ቢያደርጉም መጠጋጋትን ስለሚሻ በጊዜው የነበሩ ሴቶች ይመርጡት እንዳልነበር ሲያስታውሱ ይስቃሉ።\n\nየዱሮ አራዳ የሚባሉት የውቤ በረሃ አድማቂዎች እንደነበሩ አያልነህ ትውስ ሲላቸው በተለይ በጊዜው \"ጀብደኛ\" ይባል የነበረውና በቅፅል ስሙ ማሞ ካቻ ተብሎ ይጠራይ የነበረው ግለሰብ ስም ከአዕምሯቸው አይጠፋም። \n\nወደ ውቤ በረሃ መዝለቅ የጀመሩት ገና ምኒልክ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪና የ16 ዓመት አፍላ ጎረምሳ እያሉ ነበር።\n\nበዚያን ጊዜ 1 ብር ይሸጥ የነበረውን ቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ መጠጣት አቅማቸው ስለማይፈቅድ በ25 ሳንቲም ጠጃቸውን ጠጥተው ማስቲካ እንደሚያኝኩ እየሳቁ ይናገራሉ። \n\nይሄ ትዝታ እድሜ በጠገቡት ሰዎች ብቻ ሳይሆን በእድሜ ባልገፉት እንደ ታዋቂው ሙዚቀኛ ፍሬው ኃይሉ ልጅ ባሉትም የሚታወስ ነው። ዳዊት ፍሬውም ከትውልድ ትውልድ ተላልፎ በእሱ እድሜ በኮንጎ ነፃነት ታጋይ ስም ፓትሪስ ሉሙምባ የተሰየመውን የውቤ በረሃ ክለብን ያስታውሳዋል።\n\nከኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ጋር ተያይዞ ደጃች ውቤ ብዙ አስተዋፅኦ እንዳደረገ የሚናገረው ዳዊት \"በከተሜነት\" ዙሪያም ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አካባቢዎች አንዱ እንደሆነ ይናገራል።\n\nበኢትዮጵያ የዘመናዊነት ታሪክ ትልቅ ስፍራ ያለውና በ1960ዎቹ የሥነ-ፅሁፍ፣ ሙዚቃና ጥበብ ትልቅ ቦታ ያለው ውቤ በረሀ ታሪካዊው አሻራው ላይመለስ ፍርስራሽ ሞልቶታል።\n\nየአካባቢው የመፍረስ ዜና ሲሰማ ብዙዎችን እንዳስደነገጠ የሚናገረው ዳዊት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘንም የገለፀው ለውቤ በረሃ በማዜም ነው። \n\nየሚኖረው ሰሚት አካባቢ ቢሆንም ዘወትር ወደ የደጃች ውቤ ያቀናል። የደጃች ውቤ ትዝታ አይለቅምና።\n\n\"ስምህ በወጭ ወራጁ የሚታወቅበትና ሁሉም እጁን ዘርግቶ የሚቀበልህ ቦታ ነው\" ይላል።\n\nበተለይም የአኮርድዮን ሙዚቃ መሳሪያን በመጫወት የሚታወቀውን አባቱን በማስታወስም ሲያልፍ፣ ሲያገድምም \"ያባቱ ልጅ ውቤን ገዛሽው\" ይሉት እንደነበር ያስታውሳል።\n\nዳዊት የውቤ በረሃ መፈራረስን ሲመለከት ደርግ ስልጣን በተቆጣጠረበት ወቅት ከተማ መኮንን የዘፈነው \"አፈረሱት አሉ ዉቤ በረሃን\" ለአሁኑ የውቤ በረሃ መፈራረስ ትንቢት እንደሆነ ይሰማዋል። \n\nበጊዜው በሰዓት እላፊ ምክንያት በደጃች ውቤ አካባቢ ዘፈን እንዳይዘፈን በመደረጉ \"አፈረሱት አሉ\" እንደተዘፈነ ይናገራል። ደጃች ውቤ ሰፈር ከፈረሰ በኋላም ብዙዎች ይህን ዘፈን የስልክ መጥሪያ እንዳደረጉ በሀዘን ይገልፃል። \n\nከአዲስ አበባ መልሶ ማልማት ፕሮጀክት ጋር ተያይዞ ጥንታዊው ደጃች ውቤ ሰፈር (ውቤ በረሃ) የመፍረስ ዜና ሲሰማ ብዙዎችን አስደንግጧል። \n\nበዚህም ታሪካዊ የሚባሉ ቤቶች የፈረሱ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ እንደ አድዋ ሆቴል፣ የታዋቂው ሙዚቀኛ ፍሬው ሀይሉ ቤት፣ በአፄ ምኒልክ ዘመነ-መንግሥት ከቱርክ መሳሪያ ያመጣ የነበረው አርመናዊው ቴርዚያን ቤትና የአፈ-ንጉሥ ተክሌ ቤት ይገኙበታል።\n\nሰፈሩ አሁን የሚገኝበትን ሁኔታ በማየት ምን ያህል የደመቀ ስፍራ እንደነበር መገመት ይከብዳል።\n\n\"ምሽቱ አይነጋም\" የተባለለት የዚህ ሰፈርን ዝና በጊዜው ያልነበሩት የሚናፍቁትና ሁሉም የእኔ የሚለው ዓይነት እንደሆነ ብዙዎች ይመሰክራሉ። ቦታው ባንድም ይሁን በሌላ ከብዙ ሙዚቀኞች ትዝታ ጋርም የተቆራኘ ነው።\n\nሙዚቀኞች ብቻም ሳይሆኑ አንቱታን ያገኙ የኢትዮጵያ ፀሀፊዎችና ገጣሚዎች ይህን ቦታ በሥራዎቻቸው ገልፀውታል። \n\nከእነዚህም አንዱ የስብሃት ገብረ-እግዚአብሔር በ\"ሌቱም አይነጋልኝ\" መፀሃፉ በሰፈሩ ያለውን የሴተኛ አዳሪ ህይወትና ሰቀቀኑን፣ ድህነትን፣ ሙዚቃውን እንዲሁም የማህበራዊ ህይወት... ", "passage_id": "33f1225e33f982dafa413016a57e93e1" } ]
e5b9bea8a620314d538c9dea92964481
b04d8a4613cbc6c23257e0e4a3ac13dd
ኮሮና ቫይረስን በአሻንጉሊት
የኮሮና ቫይረስ በተለያዩ የአለም ክፍሎች እየተስፋፋ መምጣቱን ተከትሉ ህዝቦች በከፍተኛ ስጋት ውስጥ ወድቀዋል። አለም አቀፍ የሰዎች እንቅስቃሴም እንደወትሮው ሊሆን አልቻለም። በተለይ ደግሞ የቫይረሱ መገኛ በሆነችው ቻይና ሰዎች ቫይረሱ እንዳይዛቸው በተቻላቸው አቅም ሁሉ ራሳቸውን ለመከላከል ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ። ከሰሞኑ በሀገሪቱ ደቡብ ምእራብ ሲሽዋን ግዛት በሚገኝ አንድ ሆስፒታል ህሙማንን ለመጎብኘት የመጣችና ስሟ ያልተጠቀሰ አንዲት ወይዘሮ ራሷን ከኮሮና ቫይረስ ለመከላከል ያደረገችው ጥረት ግን ብዙዎችን አስፈግጓል ሲል ኦዲቲ ሴንትራል በድረገፁ አስፍሯል። በማህበራዊ ትስስር ገፅ በተለቀቀው በዚህ አጭር ቪዲዮ ወይዘሮዋ ከፊትለፊት ለማየት የሚያስችል አነስተኛ የመስታወት መስኮት ያለው ግዙፍ የቀጭኔ ቅርፅ ያለው የፕላስቲክ አሻንጉሊት ልብስ ለብሳ በሆስፒታል ውስጥ ስትንቀሳቀስ ትታያለች። ‹‹ለምን ይህን ግዙፍ የፕላስቲክ ቀጭኔ አሻንጉሊት ልብስ ለበሽ? የሚል ጥያቄ ይቀርብላታል። ወይዘሮዋ የኮሮና ቫይረስ በቻይና ከመከሰቱ በፊት አባቷ በመተንፈሻ አካል ችግር በሆስፒታሉ ብዙ ጊዜ ህክምና ሲከታተሉ አጥብቃ ትጠይቃቸው እንደነበር አስታውሳ፣የኮሮና ቫይረስ ከተከሰተ በኋላ አባቷን መጠየቋን አቁማ መቆየቷን ተናግራለች። በቅርቡ ግን ይህች ወይዘሮ አባቷን ለመጠየቅ ወደ ሆስፒታሉ ትመጣለች። በወቅቱም ሃኪሞች ፊቷን እንድትሸፍንበት የህክምና ጭምብል ይሰጧል።እሷ ግን ጭምብሉ የአገልግሎት ጊዜው ያለፈበት ነው በሚል ስጋት የኮሮና ቫይረስን በአስተማማኝ መልኩ ለመከላከል ግዙፉን የቀጭኔ አሻንጉሊት ልብስ ለመልበስ እንደወሰነች ገልፃለች። ‹‹ሃኪሞቹ የሰጡኝ የህክምና ጭምብል የአገልግሎት ጊዜ ያለፈበት ነው። በገበያ ላይም እንደልብ አይገኝም። በመሆኑም አሻንጉሊቱን ለመልበስ ተገድጃለሁ›› ስትልም ወይዘሯዋ ተናግራለች። ይህን እንግዳ ድርጊት የታዘቡት የሆስፒታሉ ሰራተኞችም ቪዲዮ በመቀረፅና በማህበራዊ ትስስር ገፅ በመልቀቅ በርካታ ቻይናውያን ፈገግ አሰኝተዋል። አዲስ ዘመን የካቲት 17/2012አስናቀ ፀጋዬ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=27860
[ { "passage": "አሜሪካዊው ተዋናይ ድዋይን ጆንሰን ወይም ዘሮክ በኮሮናቫይረስ ወረርሸኝ ምክንያት ለተቸገሩ ሰዎች ገንዘብ ይሰጣል የሚል መረጃ በሺዎች በሚቆጠሩ ማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ዘንድ ተጋርቷል።\n\nከፍተኛ ገንዘብ እንደሆነም የተገለፀ ሲሆን በበርካታ ቋንቋዎችም ተተርጉሟል። አንዳንዶቹ ቪዲዮዎችም ሆነ ፎቶዎች እንደገና በማስመሰል ጥበብ ወይም በፎቶ ሾፕ የተሰሩ ናቸው።\n\n•በቺካጎ የኢትዮጵያውያን ማኅበር መስራች አቶ መንግሥቴ አስረሴ በኮሮናቫይረስ ህይወታቸው አለፈ \n\n•\"ሞትን ተሻገርኳት\" ከኮሮናቫይረስ ያገገመች ሴት \n\nይህንንም ገንዘብ ለማሸነፍ ውድድር ተዘጋጅቷል የሚል መረጃም አብሮ የወጣ ሲሆን፤ ተሳታፊዎች ከሽልማቱ ዝርዝር ውስጥ ከስማቸው የመጀመሪያ ፊደል ጋር የሚመሳሰል መምረጥ ይኖርባቸዋል።\n\nአንዳንዶች በአስገራሚ ሁኔታ የባንክ መረጃዎቻቸውን በፌስቡክ አስተያየት መስጫ ያሰፈሩ ሲሆን፤ ለእርዳታም የተማፀኑም አልታጡም።\n\nሽልማቶቻችሁን ኑ ውሰዱ በሚል የቀጠለ ሲሆን አንደኛው ቪዲዮ ላይ አንድ ግለሰብ ከፍተኛ ገንዘብ ሲቀበል ያሳያል። ይህንንም ቪዲዮ አራት ሚሊዮን ሰዎች ተመልክተውታል።\n\nነገር ግን ቢቢሲ ማረጋገጥ እንደቻለው ቪዲዮው የሮክ አይደለም፤ የገንዘብ ሽልማቱም ማጭበርበር ነው።\n\nበፕሬዚዳንቱ ኮሮናቫይረስን ይፈውሳል የተባለው መድኃኒት \n\nየአለም አቀፉ የጤና ድርጅት እስካሁን ባለው መረጃ መሰረት የኮሮናቫይረስን የሚከላከል ወይም የሚያድን መድኃኒት የለም ቢልም የማዳጋስካሩ ፕሬዚዳንት ግን ኮሮናቫይረስን የሚከላከል መፈወሻ አግኝቻለሁ ብለዋል።\n\nከዕፅዋት ተገኘ የተባለው መድኃኒት ከአርቲሜዥያ ወይም በኢትዮጵያውያን ዘንድ አርቲ ከሚባለው ተክል ነው። \n\nይህ እፅ የወባ በሽታን የሚፈውሱ ንጥረ ነገሮችንም በውስጡ አካቷል። ፕሬዚዳንት አንድሪ ራጆሊና ታዲያ ይህንን የአርቲ ተክል ከሌሎች እፅዋት ጋር በመቀላቀል መድኃኒት እንደተሰራና፣ ሙከራም ተካሂዶ ፈዋሽነቱ ተረጋግጧል ብለዋል። ሁለት በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎችንም ማዳኑንም ይፋ አድርገዋል። \n\nመድኃኒቱ ስለ ፈዋሽነቱ ምንም አይነት ማስረጃ ያልቀረበ ሲሆን የምርምር ተቋማትም ማረጋገጥ አልቻሉም። ፕሬዚዳንቱ ግን አልሰማም ብለዋል፤ ሃገሪቱ ጥላው የነበረውንም አስገዳጅ የቤት መቀመጥ ውሳኔም በከፊል አንስተዋል። \n\n•በሴቶች የሚመሩ አገራት ወረርሽኙን በተሳካ ሁኔታ እንዴት ተቆጣጠሩት? \n\n•ከሚስታቸውና ከልጃቸው ጋር ከኮሮናቫይረስ ያገገሙት የአዳማ ነዋሪ ወደ ቤታቸው ተመለሱ\n\nየሃገሪቱ ሚዲያ እንደዘገበው ከአንድ ሺህ በላይ ወታደሮች በመዲናዋ አንታናናሪቮ ተሰማርተው መድኃኒቱን እያከፋፈሉ ነው።\n\nህዝቡም ለመቀበል የተሰለፈበት ቪዲዮም ወጥቷል። አቅማቸው ለማይፈቅደው ማህበረሰብ በነፃ የሚከፋፈል ሲሆን ለሌላው ግን በትልልቅ መደብሮች መሸመት ይችላሉ።\n\nየጀርመኑ ማክስ ፕላንክ ተቋም በአርቴሚዥያ (አርቲ) ኮሮናን ለመፈወስ ያስችላል ወይ በማለት ምርመራ የጀመረ ሲሆን ውጤቱ አልታወቀም። ኮንጎም በአትክልቱ ላይ የምርምር ስራዎችን ጀምራለች።\n\nየብርቱካን ልጣጭ ፈዋሽነት \n\nከሰሞኑ ሙቅ ውሃ፣ የብርቱካን ልጣጭ፣ ቪክስ ተብሎ የሚጠራው ቅባትን በመቀላቀል መጠጣት ቫይረስንም ሆነ ባክቴሪያን ይገላል፣ ሁሉንም ፀረ ተህዋሲያንንም ከሰውነት ያስወግዳል የሚለው ቪዲዮ በከፍተኛ ሁኔታ መነጋገሪያ ሆኗል። ወደ 1.6 ሚሊዮንም ሰዎች በቲክቶክ ተመልክተውታል። \n\nቲክቶክ ቪዲዮውን ከገፁ ላይ ካወረደው በኋላም ቪዲዮው በኢንስታግራም ላይ ወጥቶ አንድ ሚሊዮን ሰዎች ተመልክተውታል። ኢንስታግራምም ቪዲዮውን ከገፁ አጥፍቶታል።\n\nሙቅ ውሃም ሆነ ሲትሪክ አሲድ ያለባቸውን ፍራፍሬዎች መመገብ የኮሮናቫይረስን ለማዳናቸው ምንም መረጃ የለም።\n\nበቪዲዮ ተጠቃሚዎች ዘንድ ዝነኛ በሆነው ቲክቶክ የተለያዩ... ", "passage_id": "30605d932047466bfe7d6f0535ccbb2c" }, { "passage": "የአይፎን ሞባይል ቀፎ የሚገዛበት ገንዘብ ለማግኘት ሲል፣ ሴት ልጁን በተወለደች በ18ኛው ቀን በድረ-ገጽ አማካይነት ሽጧል በሚል ሰሞኑን በፖሊስ በቁጥጥር ስር የዋለው አ ዱኣን የተባለ ቻይናዊ፣ የ3 አመት እስር እንደተፈረደበት ዘ ኢንዲፔንደንት ዘገበ፡፡ነዋሪነቱ ፉጂያን በተባለቺው የቻይና ግዛት እንደሆነ የተነገረለት ግለሰቡ፣ ኪውኪው በተባለው የአገሪቱ ታዋቂ ማህበራዊ ድረገጽ ላይ ልጁን ለመሸጥ ያወጣውን ማስታወቂያ የተመለከተ ግለሰብ ልጅቷን ለመግዛት 2ሺህ 500 ፓውንድ መክፈሉን ዘገባው ገልጧል፡፡አባትዬው ልጁን በመሸጥ ያገኘውን ገቢ አይፎንና ሞተር ብስክሌት ለመግዛት ሊያውለው አስቦ እንደነበር የተነገረ ሲሆን፣ ልጅቷ የተረገዘቺው ያለ እቅድ እንደነበረና አባትዬውም ሆነ እናትዬው የ19 አመት ዕድሜ ያላቸው ወጣቶች እንደሆኑ ዘገባው አስረድቷል፡፡እናትዬው ዢያኦ ሚ የተለያዩ ስራዎችን በመስራት ገቢ ታገኝ እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፣ አባትዬው በበኩሉ አብዛኛውን ጊዜውን በኢንተርኔት ካፌዎች ተጎልቶ የሚያሳልፍ ስራ ፈት እንደነበረና ልጁን ለመሸጥ የወሰነውም ለማሳደጊያ የሚሆን በቂ ገንዘብ የለኝም በሚል ስጋት እንደሆነ አብራርቷል፡፡ልጁን የሸጠው ይሄው ግለሰብ በቁጥጥር ስር የዋለው እናትዬው ለፖሊስ በሰጠቺው ጥቆማ መሰረት እንደሆነም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡", "passage_id": "d37eb17c9ad0f6170a032e67ee1446c7" }, { "passage": "አቶ ታደሰ መላኩ የተባሉ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ ከኮቪድ 19 ወረርሽኝ በሽታ እራሳቸውን ለመጠበቅ አፍና አፍንጫቸውን በአፍ መሸፈኛ (ጭምብል) ሸፍነዋል። ከተጠቀሙት በተጨማሪ ለመግዛትም ጭምብሎቹን ከሚሸጠው አንድ ወጣት ጋር በዋጋ ሲከራከሩ ነበር ያገኘኋቸው።\nለምን ከመንገድ ላይ እንደሚገዙም ጠየኳቸው፤ በመንገድ ላይ ውጭ ሌላ የመሸጫ ቦታ ስለመኖሩ አያውቁም። መርጠው መግዛታቸውን እንጂ ከጥራት ጋር በተያያዘ ሊከሰቱ ስለሚችል ችግሮች ግንዛቤም የላቸውም። የሌሎች ያነጋገርናቸው ጭምብል ተጠቃሚዎች ምላሽም ከአቶ ታደሰ የተለየ አይደለም።\nለበሽታው መከላከያ ቅድመ ጥንቃቄ የሚውለው የአፍ መሸፈኛ (ጭምብል) እና የእጅ ንጽህና መጠበቂያ ሳኒታይዘር በስፋት እየቀረበ ያለው በመንገድ ላይ ንግድ በተሰማሩ መደበኛ ባልሆኑ ነጋዴዎች ነው። የንግድ ፈቃድ አለን ብለው ወረቀት እያሳዩ ቤት ለቤትም እያዞሩ የሚሸጡም እየታየ ነው። በተለይ በጋራ መኖሪያ ቤት። ጤናን ለመጠበቅ ተብሎ ሌላ የጤና ጠንቅ መሸመት እንዳይሆን ? ከአቅርቦቱ ጎን ለጎን የጥራቱ ጉዳይ እንዴት እየታየ ነው ስንል ባለሙያ አነጋግረናል ።\nየአለርት ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ናቸው። ዶክተር ይሄይስ ፈለቀ ይባላሉ። የአፍ መሸፈኛ (ጭምብል) እና የእጅ ንጽህና መጠበቂያ ሳኒታይዘር ለህዝብ እየቀረበ ያለበትን መንገድ አይደግፉም። ጭምብል ከህክምና መገልገያዎች አንዱ በመሆኑ ቁጥጥር ተደርጎበት በህክምና መገልገያ መሸጫ መቅረብ አለበት ይላሉ።\nእንደእርሳቸው ማብራሪያ በሽታን ለመከላከል የሚደረገው ጭምብል ደረጃው ይለያያል። በጣም ጥቃቅን የሆኑ ቫይረሶችን የማያሳልፍ ጭምብል እንዳለ ሁሉ የማይከላከልም ይኖራል። ይሄ የሚሆነው ጭምብሉ የሚሰራበት ግብአት ጥራት መጓደል ነው። ስለዚህ ጭምብል ቫይረስን የሚከላከል መሆን አለበት። ጥቅም ላይ ሲውልም መሸጥ ባለበት ትክክለኛ ቦታው መሆን ይኖርበታል።\nበጉዳዩ ላይ በተመሳሳይ መልኩ ያነጋገርናቸው የአዲስ አበባ ከተማ ምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተር አቶ ዓለማየሁ ሁዱማ ናቸው። እሳቸው እንደሚሉት ባለስልጣኑ የአፍ መሸፈኛ (ጭምብል) እና የእጅ ንጽህና መጠበቂያ ሳኒታይዘር ለህዝብ እየቀረበ ስላለበት ሁኔታ ጥቆማ እና አስተያየት ከተለያዩ አካላት ደርሶታል።\nአንዳንዶችም በፊታቸው ላይ የጤና ችግር እያስከተለባቸው እንደሆነም አሳውቀዋል። ምርቱ ከምን እንደሚሰራም ባለስልጣኑ አያውቅም። እስካሁንም በባለስልጣኑ ጭምብል እንዲሸጡ ፈቃድ የሰጣቸው አካላት የሉም። በሽታውን ለመከላከል ጭምብሉን መጠቀም እንደሚያስፈልግ ባለስልጣኑ ያምናል። ነገር ግን አሁን ባለው አሰራር ጥቅም ላይ እየዋለ ስላለው ጭምብል ተጠቀሙም አትጠቀሙም ለማለት አልቻለም። እርምጃ ለመውሰድም የሚያስችል የተቀመጠ አሰራር የለም። \nጥያቄዎቹ በመብዛታቸው እና ምርቱም አስፈላጊ በመሆኑ ባለስልጣኑ የዓለም ጤና ድርጅትን መስፈርትና የተለያዩ ሀገሮችን ተሞክሮ መሰረት በማድረግ የምርቱ ግብአት ምን መሆን እንዳለበት ወይም ተስማሚነቱን፣ የማምረቻው መሳሪያና የማምረቻ ቦታን ጨምሮ ደረጃዎችን አዘጋጅቷል። የተዘጋጀው ደረጃም ለፌዴራል ምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን መቅረቡንም አቶ ዓለማየሁ ገልጸዋል።\nሳኒታይዘርም በተመሳሳይ መደበኛ ባልሆኑ ነጋዴዎች በመንገድ ላይ መቅረብ አለበት ብለው አያምኑም። ባለስልጣኑ ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ ከነጋዴዎቹ በመቀማት እየተከላከለ መሆኑን አመልክተዋል።\nበምርቶች ደረጃ ጉዳይ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የአልመዳ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ የአዲስ አበባ ከተማ ቅርጫፍ ሥራ አስኪያጅ አቶ አማኑኤል ግርማይ እንደሚሉት፣ የአፍ መሸፈኛ ማምረት የጀመሩት ከትግራይ ክልል ምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን ፍቃድ አግኝቶ ነው። ምርቱንም ባለስልጣኑ ባወጣው መስፈርት መሰረት እያመረተ መሆኑን፤ ምርቱም መቶ በመቶ በጥጥ ግብአት እንደሚመረትና ከእጅ ንክኪ ውጭ እንዲሆንም አርባ ፍሬ በአንድ ላይ በማሸግ ለገበያ እየቀረበ መሆኑን አመልክተዋል። እንደ አቶ አማኑኤል ማብራሪያ ፋብሪካው በሽታው ከተከሰተ ጀምሮ እስከ ቅርብ ጊዜ ያመረተውን የአፍ መሸፈኛ በድጋፍ ሲሰጥ ቆይቷል። አሁን ግን ወደ ገበያ ገብቶ በመሸጥ ላይ ነው። በቀን እስከ 50ሺ ለማምረት እቅድ ይዞ ወደ ሥራ ገብቷል።\nየአፍ መሸፈኛ ለማምረት የሚያስችለው ደረጃ ሰሞኑን እንደደረሳቸውና ይህንኑም ለአባላቶቻቸው ማሳወቃቸውን የገለጹልን ደግሞ የኢትዮጵያ ጨርቃ ጨርቅና አልባሳት አምራቾች ማህበር ፕሬዚዳንት አጋዚ ገብረየሱስ ናቸው። እርሳቸው እንዳሉት አምራች ኢንዱስትሪዎቹም ማህበራዊ ኃላፊነት የመወጣት ግዴታ አለባቸው። በመሆኑም የማህበሩ አባላት መስፈርቱ እስኪወጣ ድረስ ምርት ውስጥ አልገቡም። በአሁኑ ጊዜም 35 በላይ ፈቃደኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች በቀን ከአንድ ሚሊዮን በላይ የአፍ መሸፈኛ አምርተው ለማቅረብ ተዘጋጅተዋል።\n አዲስ ዘመን ሚያዝያ 22/2012\nለምለም መንግሥቱ", "passage_id": "99eda4a01614d8f580f036993585b4be" }, { "passage": " “ይህንን ማንም ሰው ሊተነብየው አይችልም!”  ከትናንት በስቲያ ከወደ ጄኔቫ አንድ ነገር ተሰማ…“ኮሮና ቫይረስ ፈጽሞ ላይጠፋ ይችላል… አብረውን እንደሚኖሩት ሌሎች በሽታዎች ሁሉ፣ ኮሮናም አብሮን ሊቀጥል ይችላል” በማለት እቅጩን ተናገሩ - ዶ/ር ሪያን፡፡የአለም የጤና ድርጅት የአስቸኳይ ጊዜ ጉዳዮች ዳይሬክተር ዶ/ር ማይክ ሪያን ከትናንት በስቲያ በተካሄደ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ “ቫይረሱ መቼ ከአለማችን ላይ ሊጠፋ ይችላል?” ተብለው ሲጠየቁ የሰጡት ምላሽ ብዙዎችን ያስደነገጠ፣ ተስፋ ያስቆረጠና ግራ ያጋባ ነበር፡፡በተለያዩ የአለማችን አገራት ከ100 በላይ የሚሆኑ የኮሮና ቫይረስ ክትባት ምርምሮች እየተደረጉ እንደሚገኙ የጠቆሙት ዶ/ር ማይክ ሪያን፤ አለም በለስ ቀንቷት ክትባቱን ብታገኝ እንኳን ኮሮናን ላታጠፋው እንደምትችል ተናግረዋል - የመከላከያ ክትባት ከተገኘለት ረጅም ጊዜ ያለፈውንንና አሁንም ድረስ ከአለማችን ያልጠፋውን የኩፍኝ በሽታ እንደ አብነት በመጥቀስ፡፡ጥቂት ቆይቶ ግን፤ አለቃቸው ሌላ የተሻለና የሚያጽናና ነገር ተናገሩ…“ኮሮና ቫይረስን ማጥፋት ባይቻል እንኳን፣ እስከ መጨረሻው የአቅማችንን እንጥፍጣፊ ተባብረን ከጣርን፣ የሆነ ጊዜ ላይ ልንቆጣጠረው የምንችለው ነው” አሉ፤ የአለም የጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም፡፡የዶክተር ቴዎድሮስ ንግግር በተወሰነ መልኩ ቢያጽናናም፣ “መቼ ነው ያ የሆነ ጊዜ?... እስከ መቼ ነው ቫይረሱ በዚህ ሁኔታ የሚቀጥለው?” የሚል ጭንቀትና ስጋት የወለደው ጥያቄን ማጫሩ ግን አልቀረም፡፡ኮሮና ቫይረስ መላውን አለም በቀውስ ማዕበል እየናጠ፣ ሚሊዮኖችን ወደ አልጋ፣ በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩትን ወደ መቃብር እየሸኘ፣ ኢኮኖሚውን እያንኮታኮተ፣ ማህበራዊ ግንኙነትን እየበጣጠሰ፣ እልፎችን በፍርሃት እያራደና በየቤታቸው አድፍጠው እንዲቀመጡ እያስገደደ የሚቀጥለው እስከ መቼ ነው፣ መቼስ ነው በቁጥጥር ስር የሚውለው ብለው የሚጠይቁ ብዙዎች ናቸው፡፡“ኮሮና መቼ ነው በቁጥጥር ስር የሚለውለው?” የሚለውን ይህንን የብዙዎች ጥያቄ ለመመለስ፤ ብዙ ርቀት መጓዝ ወይም ብዙ ማብራሪያ መስጠት አላስፈለጋቸውም - ዶ/ር ሪያን፡፡“ይህንን ማንም ሰው ሊተነብየው አይችልም!” ሲሉ እቅጩን ተናገሩ፡፡ቀጥሎ የሚመጣው እስካሁን ከሆነው ሁሉ የባሰ እንደሚሆን ብዙዎች እየተናገሩ ቢሆንም፣ ኮሮና ቫይረስ ግን በየደቂቃው በመላው አለም ብዙዎችን ማጥቃቱን፤ ቁጥሮችም በየአንዳንዷ ደቂቃ ማሻቀባቸውን ተያይዘውታል፡፡እስከ ትናንት በስቲያ አመሻሽ ድረስ…ኮሮና ቫይረስ በመላው አለም ከ4 ሚሊዮን 477 ሺህ በላይ ሰዎችን እንዳጠቃና 300 ሺህ የሚሆኑትንም ለህልፈተ ህይወት እንደዳረገ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥርም ከ1 ሚሊዮን 680 ሺህ ማለፉ ተነግሯል፡፡ እስከተጠቀሰው ጊዜ ድረስ ከ1 ሚሊዮን 435 ሺህ በላይ ሰዎች የተጠቁባትና ከ86 ሺህ በላይ ሰዎች ለሞት የተዳረጉባት አሜሪካ፣ አሁንም በኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎችና ሟቾች ቁጥር ከአለማችን አገራት በቀዳሚነቷ ቀጥላለች፡፡ስፔን በ272 ሺህ 700፣ ሩስያ በ252 ሺህ 300፣ እንግሊዝ በ233 ሺህ 200፣ ጣሊያን በ220 ሺህ 200 ያህል የቫይረሱ ተጠቂዎች እስከ አምስተኛ ያለውን ደረጃ ሲይዙ፣ እንግሊዝ በ33 ሺህ 700፣ ጣሊያን በ31 ሺህ 200፣ ስፔን በ27 ሺህ 400፣ ፈረንሳይ በ27 ሺህ 100 ያህል ሟቾች ከአሜሪካ በመቀጠል እስከ አምስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡በኮሮና ሳቢያ የሚጠቁትም የሚሞቱትም ቁጥራቸው ማደጉን ቀጥሏል፤ የአለም ሳይንቲስቶች ደግሞ ደግሞ ለዚህ የጥፋት ማዕበል ማቆሚያ የሚሆን አንዳች መላ ፍለጋ በየቤተ ሙከራው ደፋ ቀና ማለታቸውን ቀጥለዋል፡፡ ከአለም ዙሪያ ከቀረቡ 100 በላይ የሚሆኑ በምርምር ላይ ያሉ የኮሮና ቫይረስ የክትባት አይነቶች ውስጥ የተሻሉና ውጤታማ እንደሚሆኑ የታመነባቸው 8 ያህሉ ተመርጠው እየተሰራባቸው እንደሚገኝና ስራው እየተፋጠነ መሆኑን የአለም የጤና ድርጅት ባለፈው ማክሰኞ ዕለት አስታውቋል፡፡የኮሮና ቫይረስ መከላከያ ክትባት የማፈላለግ ስራውን ለማፋጠን ከተለያዩ አካላት ባለፈው ሳምንት የ8 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ መደረጉን ያስታወሰው ድርጅቱ፤ ያም ሆኖ ግን ይህ ገንዘብ በቂ ባለመሆኑ አገራትና የተለያዩ አለም አቀፍ ተቋማት የሚያደርጉትን ድጋፍ በተፋጠነ መልኩ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርቧል፡፡ሌሴቶ - የመጨረሻዋ አፍሪካዊት አገር ባለፈው ረቡዕ ማለዳ…ሁሉንም የአፍሪካ አገራት አዳርሶ አንዲት አገር ብቻ ቀርታው የነበረው ኮሮና ቫይረስ፣ በስተመጨረሻም የመጨረሻዋ መዳረሻው ወደሆነችውና በአገር ተከብባ ወደምትኖረው ደቡባዊ አፍሪካዊት አገር ሌሴቶ ሰተት ብሎ መግባቱ ተሰማ፡፡ከተቀረው የአፍሪካ አገር በተለየ መልኩ በኮሮና ሳትደፈር ይህን ያህል ጊዜ መቆየቷ በብዙዎች ዘንድ መነጋገሪያ አድርጓት የሰነበተችውና  በአህጉሩ በኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር ቀዳሚነቱን በያዘችው ደቡብ አፍሪካ ዙሪያዋን ተከባ የምትገኘው ሌሶቶ፤ ከውጭ አገራት በመጡ መንገደኞች ላይ ባደረገችው ምርመራ አንደኛው በቫይረሱ መጠቃቱን ማረጋገጧን ይፋ አድርጋለች፡፡በመላው አፍሪካ በዚህ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት ከኤች አይ ቪ ኤድስ ጋር ተዛማጅ በሆኑ ምክንያቶች ሳቢያ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለሞት ሊዳረጉ እንደሚችሉ የአለም የጤና ድርጅት ባለፈው ማክሰኞ በሰጠው መግለጫ ማስጠንቀቁን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ በተደረገ የዳሰሳ ጥናት፤ በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት በአፍሪካ ለ6 ወራት የፀረ-ኤች አይ ቪ መድሐኒት አቅርቦት ቢቋረጥ፣ ከኤድስ ጋር በተዛመዱ በሽታዎች የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር እንደሚጨምር መነገሩን የጠቆመው ዘገባው፣ ከሰሃራ በታች ያሉ የአፍሪካ አገራት መንግስታት ለጉዳዩ ትኩረት ካልሰጡት እስከ መጪው የፈረንጆች አመት ድረስ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ሰዎች በኤድስና ተዛማች በሽታዎች ሳቢያ ሊሞቱ እንደሚችሉ ድርጅቱ ማስጠንቀቁንም አክሎ ገልጧል፡፡የአለም የጤና ድርጅት ሳይንሳዊ መንገድን ተከትሎ ያልተሞከረና ደህንነቱ ያልተፈተሸ መድሐኒት ለጤና አይበጅምና ከመውሰድ ተቆጠቡ ብሎ በአደባባይ የተቃወመውን ባህላዊ የኮሮና ቫይረስ መድሃኒቷን በግዛቷ ውስጥ በገፍ መሸጧን የተያያዘችው ማዳጋስካር፣ ይህንኑ መድሓኒቷን ታንዛኒያ፣ ጊኒ ቢሳዎ እና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን ጨምሮ ወደተለያዩ የአፍሪካ አገራት “ኤክስፖርት” በማድረግ ተጠምዳ ነው ሳምንቱን ያገባደደችው፡፡ማዳጋስካር “ፍቱን መድሐኒት አግኝቻለሁ፤ ከአሁን በኋላ ቫይረሱ ወደ ዜጎቼ ድርሽ አይልም” ብላ ብትምልም፣ የአገሪቱ ጤና ሚኒስቴር ግን ከትናንት በስቲያ ባወጣው መግለጫ 18 ተጨማሪ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ፣ አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ወደ 230 ከፍ ብሏል፡፡በአፍሪካ የወረርሽኙ መስፋፋት ከፍተኛ ደረጃ ላይ የሚደርስበት አደገኛው የጥፋት ጊዜ ገና እንደሆነ ባለሙያዎች እያስጠነቀቁ ቢሆንም፣ በርካታ የአፍሪካ አገራት ግን ለሳምንታት ተግባራዊ ሲያደርጉት የነበረውን የእንቅስቃሴ ዕገዳ ከሰሞኑ ማላላት መጀመራቸው እየተነገረ ነው፡፡ የበሽታውን መስፋፋት ለመቆጣጠር ሲሉ ጥለዋቸው የነበሩ የእንቅስቃሴ ገደቦችና እገዳዎች ኢኮኖሚያቸው ላይ ከፍተኛ ጫና መፍጠር መጀመሩን በማየት ተግባራዊ ሲያደርጓቸው የነበሩ ገደቦችንና እገዳዎችን ለማላላት እየወሰኑ ያሉ የአፍሪካ አገራት እየተበራከቱ መሆናቸውን የዘገበው ቢቢሲ፤ ጂቡቲ፣ ማሊ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ጋቦን፣ ኒጀር እና ኡጋንዳ ለማላላት ያወጡትን ዕቅድ ይፋ አድርገዋል ብሏል።በጊኒ የኮሮና ቫይረስን ስርጭት ለመግታት መንግስት የጣላቸው የእንቅስቃሴ ገደቦች ለሙስናና ተገቢ ያልሆነ ጥቃት ዳርጎናል ያሉ ዜጎች ባለፈው ማክሰኞ አደባባይ ወጥተው ባደረጉት ተቃውሞ፣ ከፖሊስ ጋር በተፈጠረ ግጭት  ስድስት ሰዎች መገደላቸውን አልጀዚራ ዘግቧል፡፡በኮሮና ተጽዕኖ በቀን 6 ሺህ ህጻናት ሊሞቱ ይችላሉ በማደግ ላይ ባሉ አገራት ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ መከላከል በሚቻሉ በሽታዎች ሳቢያ የሚከሰተው የህጻናት ሞት በመጪዎቹ ስድስት ወራት በ45 በመቶ ያህል ሊጨምር እንደሚችልና በየዕለቱ በመላው አለም 6 ሺህ ያህል ከአምስት አመት ዕድሜ በታች ያሉ ህጻናት ለሞት ሊዳረጉ እንደሚችሉ የተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት ዩኒሴፍ አስጠንቅቋል፡፡በአገራቱ የሚገኘው ውስን የጤና ሃብትና ቁሳቁስ ከነባር በሽታዎች ወደ ኮሮና ቫይረስ መከላከል ከመዞሩ ጋር በተያያዘ በተለይ በአፍሪካ፣ እስያና ላቲን አሜሪካ ድሃ አገራት በ6 ወራት ውስጥ ተጨማሪ 1.2 ሚሊዮን ህጻናት እንዲሁም 57 ሺህ ያህል እናቶች ለሞት ሊዳረጉ እንደሚችሉም ድርጅቱ አስታውቋል፡፡ ድርጅቱ በተጠቀሰው የ6 ወር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያለው የህጻናት ሞት ሊከሰትባቸው ይችላል ብሎ የጠቀሳቸው ቀዳሚዎቹ አስር አገራት ባንግላዴሽ፣ ብራዚል፣ ኮንጎ፣ ኢትዮጵያ፣ ህንድ፣ ኢንዶኔዢያ፣ ናይጀሪያ፣ ፓኪስታን፣ ኡጋንዳ እና ታንዛኒያ ናቸው፡፡ኢኮኖሚው እንዴት ሰነበተ?ባለፉት ሶስት ወራት የአለማችን ንግድ በ3 በመቶ ያህል እንደሚቀንስ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የንግድና የልማት ተቋም ባለፈው ረቡዕ ባወጣው መረጃ አስታውቋል:: የንግድ መቀነሱ በቀጣዮቹ ሶስት ወራትም ተጠናክሮ ሊቀጥልና ከሚያዝያ እስከ ሃምሌ ወራት 27 በመቶ ሊደርስ እንደሚችል የጠቆመው ተቋሙ፣ ባለፈው መጋቢት ወር የሸቀጦች ዋጋ በአለማቀፍ ደረጃ በ20 በመቶ መቀነሱንም አስታውሷል፡፡ዘ ጋርዲያን በበኩሉ፣ አለማቀፍ የመኪኖች ሽያጭ በ2020 የፈረንጆች አመት በ20 በመቶ ያህል እንደሚቀንስ መነገሩን ከሰሞኑ ለንባብ ባበቃው ዘገባው አመልክቷል፡፡ የአለማችን ኢኮኖሚ በፈረንጆች አመት 20202 በ3.2 በመቶ ያህል ቅናሽ እንደሚያሳይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከሰሞኑ ባወጣው መግለጫ ያስታወቀ ሲሆን፣ ከ300 በላይ የአለማችን ህግ አውጪዎች አለማቀፉ የገንዘብ ተቋምና የአለም ባንክ የድሃ አገራትን ዕዳ እንዲሰርዙ ጥሪ ማቅረባቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ የህንድ መንግስት የኮሮና ቫይረስ በአገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ለመቋቋምና በወረርሽኙ ሳቢያ የንግድ እንቅስቃሴያቸው የተጎዳባቸውንና ስራቸውን ያጡ ዜጎችን ለመደጎም በማሰብ የ264 ቢሊየን ዶላር የኢኮኖሚ መታደጊያ በጀት መመደቡን ባለፈው ረቡዕ ሲያስታውቅ፣ ጣሊያንም የ59.6 ቢሊዮን ዶላር የኢኮኖሚ ማነቃቂያ በጀት ማጽደቋን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ኮሮና ቫይረስ ያን ያህል ተጽዕኖ እንዳልፈጠረባት በሚነገርላት አውስትራሊያ የሥራ አጥ ዜጎች ቁጥር ወደ 6.2 በመቶ ማደጉና ከ6 መቶ ሺህ በላይ የአገሪቱ ዜጎች ለስራ አጥነት መዳረጋቸው መነገሩን ቢቢሲ ዘግቧል:: በአገሪቱ ከመንግሥት ድጋፍ እየተደረገላቸው የሚገኙ ዜጎች ቁጥር ከ6 ሚሊዮን በላይ መድረሱን የጠቆመው ዘገባው፣ 1 ሚሊዮን አውስትራሊያውያን ደግሞ ሥራ አጥ ስለሆንን ድጋፍ ይደረግልን የሚል ማመልከቻ ለመንግስት ማቅረባቸውን አመልክቷል፡፡መክፈትና መዝጋት፣ ማላላትና ማጥበቅነገሩ አላምር ሲላቸው የእንቅስቃሴ ገደቦችንና ዕግዶችን ከጣሉ ከሳምንታት በኋላ፣ ተዘግቶ መቀመጥ ከቀጣዩ የኢኮኖሚ ቀውስ እንደማያስጥል የታያቸውና ገደቦችን ያነሱ አገራት፣ ከቀናት በኋላ ደግሞ ቫይረሱ በፍጥነት መሰራጨቱ ክፉኛ ሲያስደነግጣቸው መልሰው ገደቦችን መጣላቸው እየተዘገበ ይገኛል፡፡ቫይረሱን በቁጥጥር ስር አውያለሁ ብላ ህጎቿን ባላላች በሳምንት እድሜ ውስጥ የተጠቂዎች ቁጥር እንደገና ያሻቀበባት ሊባኖስ፣ በፍጥነት ያላላችውን ህጎች መልሳ አጥብቃለች:: የወረርሽኙን ስርጭት ለመግታት በማሰብ የጣለችውን የእንቅስቃሴ ገደብ ከሰሞኑ ማላላት የጀመረችው ፓኪስታን፣ በአንዳንድ ግዛቶች ከፍታው የነበረውን የንግድ እንቅስቃሴ የማህበራዊ እርቀት ደንቦች አልተከበሩም በሚል ከጥቂት ቀናት በኋላ መልሳ መዝጋቷ ተነግሯል፡፡ያላሏቸውን ህጎች መልሰው ካጠበቁና የእንቅስቃሴ ገደቦችን እንደ አዲስ ተግባራዊ ማድረግ ከጀመሩ ሌሎች የአለማችን አገራት መካከል ህንድና ኢራን እንደሚገኙበት ተነግሯል፡፡ በአንጻሩ ደግሞ የእንቅስቃሴ ገደቦችን ማላላትና ዜጎቻቸውን ወደ መደበኛው እንቅስቃሴ ለመመለስ የመረጡ ህንድ፣ ሩስያ፣ አሜሪካና ሲንጋፖርን የመሳሰሉ በርካታ አገራት መኖራቸውን መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል፡፡እንግሊዝ በቤታቸው ሆነው ስራቸውን መስራት የማይችሉ የተወሰኑ ሰራተኞች ወደ ቢሮ እንዲገቡ ለመፍቀድ ማሰቧን ስትገልጽ፣ ሜክሲኮ የተወሰኑ የመኪና አምራች ኩባንያዎችን ከሰሞኑ እንደምትከፍት አስታውቃለች:: የጣሊያን ትምህርት ሚኒስቴር በመጪው መስከረም ሁሉም የተዘጉ ትምህርት ቤቶች እንደሚከፈቱ ማስታወቁን የዘገበው ሮይተርስ፣ አውስትራሊያና ጀርመን ለ2 ወራት የዘጉትን ድንበራቸውን በመጪው ሰኔ ለመክፈት መስማማታቸውን ገልጧል፡፡በቀን 18 ሚሊዮን ኮሮና ተኮር ሃሰተኛ ኢሜሎች ይላካሉየኢንተርኔት አጭበርባሪዎች ለጂሜይል ተጠቃሚዎች በየዕለቱ 18 ሚሊዮን ያህል ሃሰተኛ የኢሜል መልዕክቶችን እንደሚልኩ ታዋቂው የቴክኖሎጂ ኩባንያ ጎግል ከሰሞኑ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ከኮሮና ቫይረስ ስርጭት መስፋፋት ጋር በተያያዘ መሰል ሃሰተኛ ኢሜይሎች በከፍተኛ ሁኔታ መጨመራቸውን የጠቆመው ጎግል፣ ባለፈው ሳምንት ብቻ መሰል ከ100 ሚሊዮን በላይ መልዕክቶችን ማገዱንና 20 በመቶ ያህሉ ከኮሮና ቫይረስ ጋር የተያያዙ መሆናቸውን በመግለጽ፣ አጭበርባሪዎች በእነዚህ ሃሰተኛ መልዕክቶች አማካይነት የተጠቃሚዎችን የግል መረጃዎች እንደሚመነትፉ አመልክቷል፡፡በኤርትራ 1 ታማሚ ሲቀር፤ በፔሩ ግማሽ ያህሉ ሃኪሞች ኮሮና ይዟቸዋልበኤርትራ በኮሮና ቫይረስ ከተጠቁት 39 ሰዎች መካከል 38ቱ ከሆስፒታል አገግመው መውጣታቸውንና በህክምና ላይ የሚገኘው አንድ ሰው ብቻ መሆኑን የአገሪቱ የጤና ሚኒስቴር ባለፈው ሰኞ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡በሌላ ዜና ደግሞ፣ የፔሩ መንግስት በኮሮና ቫይረስ በከፍተኛ ሁኔታ በተጠቃችው ኢኩቶስ የተባለችው የአገሪቱ ከተማ ውስጥ የህክምና አገልግሎት በመስጠት ላይ ከነበሩ 350 ዶክተሮች መካከል 189 የሚሆኑት በቫይረሱ መጠቃታቸውን እንዳስታወቀ ዘ ጋርዲያን ዘግቧል፡፡ሲጋራ ከኮሮና አያስጥልም፤ ይልቁንም የበለጠ ያጋልጣልከሳምንታት በፊት ከወደ ፈረንሳይ የወጣ አንድ ጥናት፣ ሲጋራ አጫሾች ከማያጨሱት ጋር ሲነጻጸር በኮሮና ቫይረስ የመጠቃት ዕድላቸው ዝቅ ያለ እንደሆነ ጠቁሞ ነበር፡፡ የአለም የጤና ድርጅት ግን ይህን እና ሌሎች መሰል ጥናቶችን ይፋ የሚያደርጉ አሳሳች ሳይንቲስቶችን “የማይመስል ነገር እየመከራችሁ ሰውን አታሳስቱ” ሲል ከሰሞኑ ማስጠንቀቁንና በአንጻሩ ሲጋራ ማጨስ ለኮሮና የማጋለጥ ዕድሉ ከፍ ያለ እንደሆነ መግለጹን አናዶሉ ኤጀንሲ ዘግቧል፡፡አጫሾች በኮሮና ቫይረስና በሌሎች የመተንፈሻ አካላት በሽታዎች የመጠቃት እድላቸው ከማያጨሱት የበለጠ ከፍ ያለ መሆኑን ድርጀቱ በሳምንቱ መጀመሪያ ይፋ ባደረገው መረጃ ማስታወቁን የጠቆመው ዘገባው፣ ማጨስ ሳንባን በመጉዳት ሰውነታችን ኮሮናንና ሌሎች በሽታዎችን የመከላከል አቅሙ አነስተኛ እንዲሆን እንደሚያደርግ መጠቆሙንም አክሎ ገልጧል፡፡", "passage_id": "fc420cc17f501abe433b660e38ac82f4" }, { "passage": "የሁነቶችን እንቅስቃሴ መቅረፅ የሚያስችል ካሜራ አሰራር እንዲሁም አነስተኛ ብርሃንን ማሻሻል የሚችሉ ሌንሶች የእነዚህ ስልኮች መለያ ነው።\n\nእንደ አውሮፓውያኑ በ2017 የሳምሰንግ ሽያጭ ጨምሮ የነበረ ቢሆንም እንደ ሌሎቹ ተቀናቃኝ የቻይና ኩባንያዎች ግን ሽያጩ በጣም አልጨመረም።\n\nኤክስፐርቶች እንደሚሉት አሁን ምርቶቹ ላይ የተደረጉት ማሻሻያዎችም ቀላል እንጂ ጉልህ የሚባሉ አደሉም።\n\nይሁንና የs9 ቅርፅ ከ s8 ጋር እጅግ የሚመሳሰል መሆኑ ለአዲሶቹ ስልኮች ሽያጭ ችግር ሊሆን እንደሚችልም ይናገራሉ። S9+ ብቻ ከ S8+ በደንብ ይለያል።\n\nሁለቱ የካሜራ ሌንሶች የተያዩ እይታዎችን ይሰጣሉ፤ ትኩረት ከሚደረግበት ነገር ውጭ ያለን ነገር ገፅታንም እንደተፈለገው ለማድረግ ያስችላሉ።\n\n\"የተደረጉት ማሻሻያዎች ሰዎች ስልካቸውን ለመለወጥና አዳዲሶቹን ለመግዛት የሚገፋፉ አይመስለኝም\" ይላል አይዲሲ በተሰኘው ኩባንያ የገበያ ጥናት ኤክስፐርት የሆነው ፍራንሲስኮ ጀሮሚዮ።\n\nየስልኮቹ ካሜራ መሻሻል በርካቶች አዲሶቹን ስልኮች እንዲገዙ ሊያደርጉ ቢችሉም ይጠብቅ የነበረው ማሻሻያ ከዚህ የበለጠ እንደነበር ኤክስፐርቱ ያስረዳል።\n\nከጠበቃቸው ማሻሻያዎች መካከል ለምሳሌ የኢንተርኔት ቀጥታ ትርጉም አንዱ ነበር። በተቃራኒው አዲሱ የቺፕ ቴክኖሎጂያቸው ምስጋና ይግባውና ያለ ኢንተርኔት ቃላት የሚተረጉሙትን የህዋዌ አዳዲስ ስልኮች ያደንቃል።\n\n ", "passage_id": "dab1df1cfa5cf57ea4ae9e63657b89e6" } ]
8d11d66d39146c8a53e7d6864d45a265
9140e7e676cf0bc5533f32535b36f7d7
ዝም ስንል
አቶ አንድአርጋቸው የ75 አመት እድሜ ባለፀጋ ነበሩ። እኝህ አዛውንት ደስተኛ ሆነው የሚኖሩና በጣም የሚያስቀና ቤተሰብ ያላቸው ሰው ነበሩ። ከብዙ አመታት በኋላ ልጆቻቸው አድገው የራሳቸውን ኑሮ በመመስረት ወደ ተለያየ አካባቢ ሄዱ። ባለቤታቸው እና የልጆቹ እናት ከብዙ አመታት በፊት በሞት ስለተለየቻቸው በመንደሩ ውስጥ በብቸኝነት እና በሀዘን ብዙ ጊዜያቸውን ያሳልፉ ጀመር። አቶ አንዳርጋቸው አብዛኛውን ጊዜያቸውን በብቸኝነት ቢያሳልፉም፤ የልጅ ልጆቻቸው በአመት በአል እና በእረፍት ጊዜያቸው አያታቸውን ሊጠይቁ ይመጡ ነበር። በዚህ ወቅት እጅግ ደስተኛ እና ተጫዋች ይሆኑ ነበር። በአንደኛው እለት አቶ አንዳርጋቸው ቀጣዩን ቀናቶች ደስተኛ ሆኖ የሚያሳልፉበት ጊዜ ተፈጠረ። ምክንያቱም አራቱ የልጅ ልጆች ሊጠይቋቸው የሚመጡበት ወቅት በመሆኑ ነበር። የልጆቹን መምጣት በጉጉት ሲጠብቁ የነበረው አዛውንት ቤቱን ማፅዳት፣ እቃዎቹን በአዲስ መልክ ማስተካከል፣ የአትክልት ስፍራዎቹን ማሰማመር ጀመሩ። ምክንያቱም እነሱን ሊጠይቋቸው የሚመጡት ልጆች ደስተኛ እንዲሆኑ ስለሚፈልጉ ነበር። የልጅ ልጆቹ የሚወዱትን የምግብ አይነትም አዘጋጅተው ይጠብቋቸው ነበር። በዚህ ጊዜ ሚስቱ ከመሞቷ በፊት የሰጠችውን «የእጅ ሰአት» ባጋጣሚ ጣሉ። ሆኖም ግን ሰአቱን ከእጃቸው ላይ መጥፋቱን ማስተዋል አልቻሉም። ሚስታቸው ከሞተች በኋላ ሰአቱን በጣም ነበር የሚወዱት ከእጃቸው ላይም እንዳይጠፋ በጣም ይጠነቀቁ ነበር። በልጅ ልጆቻቸው መምጣት በጣም ደስተኛ የሆኑት የእድሜ ባለፀጋ የሰአቱን ከእጃቸው ላይ መጥፋት ሳያስተውሉ ለቀጣዮቹ ሁለት ቀናት በደስታ እና በጨዋታ አሳለፉ። በሶስተኛው ቀን ግን ሰውነታቸውን ለማፅዳት መታጠቢያ ቤት ሲገቡ ከእጃቸው ላይ እንደሌለ ተገነዘቡ። በጣም በማዘንም እንደ አይናቸው ብሌን የሚሰስቱትን ሰአት በመጣላቸው ተበሳጩ። ለመጨረሻ ጊዜም የት ቦታ አድርገውት እንደነበር ለማስታወስ ሞከሩ። ቤቱን ለማፅዳት ሲሞክሩ ሊጠፋ እንደሚችልም ገመቱ። በግቢው ውስጥ የሚገኝ የእቃ ማከማቻ ቤት ውስጥ ሊሆን እንደሚችልም ጠርጥረው እዛው ለመፈለግ ወሰኑ። በአያታቸው ግራ መጋባት እና መናደድ የተገረሙት ልጆች፤ ምን እንዳጋጠማቸው ጠየቋቸው። እሳቸውም « ከአያታችሁ የተሰጠኝን እና በህይወቴ ትልቅ ግምት የምሰጠውን ሰአቴን ጣልኩት፤ ልክ ልቤን እንደጣልኩት ነው የሚሰማኝ። ይመስለኛል እቃ ማከማቻ ቤት ውስጥ የጣልኩ ይመስለኛል » በማለት ነገራቸው። ልጆቹም በሁኔታው ማዘናቸውን በመግለፅ፤ በፍለጋው እንደሚተባበሩ ገለፁላቸው። ልጆቹ እና አያታቸው አላስፈላጊ እቃ በብዛት የሚከማችበት ቤት ውስጥ ሊገኝ እንደሚችል ወስነው ፍለጋቸውን ቀጠሉ። ሰአቱን ለማግኘት ሁሉንም እቃ ለማየት ሙከራ አደረጉ። ሆኖም ግን የጠፋውን የእጅ ሰአት ሊያገኙት አልቻሉም። ያረጁ መፅሀፍት፣ ወንበር፣ ጠረጴዛ እንዲሁም በርካታ ቁሳቁሶች በቤት ውስጥ ተከማችቶ ስለነበር ፍለጋቸውን አስቸጋሪ አድርጎባቸው ነበር። ለ ሁለት ሰአታት ያክል ሲፈልጉ ቆይተዋል። በሁኔታው እጅግ ያዘኑት አቶ አንዳርጋቸው የልጅ ልጆች ፍለጋቸውን ማቆም እንደሚኖርባቸው አስረዷቸው። ውዱን ሰአት ከእንግዲህ ሊያገኙ እንደማይችሉ ተገንዝበው ነበር። ልጆቹም በሁኔታው በጣም አዘኑ። ሆኖም ግን አያታቸው በተፈጠረው ሁኔታ እንዳያዝኑ በተቻላቸው መጠን ሊያፅናኑን ሞከሩ። ከልጅ ልጆቹ አንደኛዋ የሆነችው እና ፅጌ የምትባለዋ አስተዋይ ልጅ፤ አስቀድመው ሁሉም የእጅ ሰአቱን ሲፈልጉ የነበረበት ቤት ተመልሳ ትሄዳለች። በሁኔታው የተገረሙት አያቷ እና ወንድሞቿ ይህንን ለምን እንደምታደርግ ይጠይቋታል። ምክንያቱም እስኪሰለቻቸው ድረስ ሰአቱን ለማግኘት ሙከራ አድርገው አልተሳካላቸውም ነበር። ፅጌም ወንድሞቿ እና አያቷ ወደ እቃ ማከማቻው ቤት ሲሄዱ እንዳይከተሏት ነግራቸዋለች። ምንም አይነት ድምፅም እንዳያሰሙ ታስጠነቅቃቸዋለች። በሁኔታው የተገረሙት ወንድሞቿ እና አያቷም ፍላጎቷን ለማሳካት ይስማማሉ። ፅጌ በዝግታ ወደ እቃ ቤቱ አመራች። በሩን ከፍታም ወደ ቤቱ አንደኛው ጥግ በማምራት ያገኘችው መቀመጫ ላይ ለ25 ደቂቃዎች በቤቱ ውስጥ ከተቀመጠች በኋላ አያቷ እና ወንድሞቿ ወደሚገኙበት አካባቢ አመራች። ሁሉም ግን ከፊት ለፊታቸው በሚያዩት ነገር ተገርመው ነበር። ምክንያቱም ፅጌ ለሁለት ሰአት ያክል ለፍተው ሲፈልጉት የነበረውን የአያታቸውን ሰአት ማግኘት ችላ ነበር።አቶ አንዳርጋቸው በፍቅር የሚወዷት ባለቤታቸው የሰጠቻቸው ሰአት በመገኘቱ እጅግ በጣም ደስተኛ ነበሩ። አገኘዋለሁ ብሎም አልገመተም። ከምንም ነገር በላይ የባለቤታቸው ስጦታ እስከ ህይወታቸው ፍፃሜ እንዲቆይ ፍላጎታቸው ነበር። በሁኔታው በጣም የተደሰቱት አያቷም፤ ፅጌን ሰአቱን እንዴት እና የት ቦታ ላይ እንዳገኘችው ጠየቋት። ፅጌ ለአያቷ እንዲህ ስትል መለሰች «አያቴ በበጋ ወራት ትምህርት ቤት በጣም የምንወደው አስተማሪያችን ሁል ጊዜ ዝም የማለት ጥቅሞችን ይነግረናል። ሁሌ ባይሆንም አንዳንድ ወቅት ዝምታ አስፈላጊ መሆኑን ያስረዳናል። ለምሳሌ እሱ ሲያስተምር በጥሞና እንድናዳምጠው ይመክረናል» በማለት መለሰችለት። አያቷም ግራ በመጋባት መንፈስ « ታዲያ ይሄ ከእጅ ሰአቱ መገኘት ጋር ምን አገናኘው?» ሲሉ ጠየቋት። ፅጌ ለአያቷ ጥያቄ በድጋሚ ምላሽ ሰጠች «አያቴ የእጅ ሰአቱን ስንፈልግ እየተጯጯህን እና እቃዎችን ከወዲያ ወዲህ እያንኳኳን ነበር። ትንሽ በመሆኑም የት ቦታ ተደብቆ እንደነበር ለማወቅ አልቻልንም። ሆኖም ግን እኔ ለሁለተኛ ጊዜ ስሄድ ብቻዬን ነበርኩ። እቃዎቹን በማንኳኳትም ልፈልገው አልሞከርኩም። ቁጭ ነበር ያልኩት። ምክንያቱም የእጅ ሰአቱ ሲቆጥር «ቲክ… ቲክ… ቲክ…» የሚል ድምፅ ያሰማ ነበር። ዝም በማለቴም ይህንን ድምፅ መስማት ችያለሁ» በማለት በፈገግታ በመሞላት አስረዳቻቸው። አያቷም በሁኔታው በመደነቅ አቅፈው ግንባሯን በመሳም አመሰገኗት። በዝምታና በጥሞና ነገሮችን መከታተል፤ ረጋ ብሎ ሁሉንም ነገር ማየትና መመርመር ትክክለኛ ውሳኔ ላይ ለመድረስ እንደሚያስችልም ለሁሉም አስተማረች። አሁን በሀገራችን ያለው ሁኔታም ይሄንን የሚጠይቅ ነው። አዲስ ዘመን የካቲት 15/ 2012  ዳግም ከበደ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=27792
[ { "passage": "እኩለ ቀን ነው ፤ አማራጭ ስለሌለኝ አናት በምትበሳ ፀሐይ መሀል አንድ ወዳጄን ለማግኘት እየተጓዝኩ ነው። እኔ የምለው? ለጸሐይ ቀርበን ነው ወይስ እሷ ወደ እኛ ቀርባ ? ሀይሏ ከመክበዱ የተነሳ ሰውነት የሚያዝል ፣ሃሳብ የሚያስረሳ ነው ብል ማጋነን አይሆንም ብቻ ይህን ሁሉ ውርጅብኝ ተቋቁሜ አይደርሱ የለ የቀጠርኩትን ሰው ወደማገኝበት ቦታ ደረስኩ። በአካባቢው ወደሚገኝ ካፌ ገብቼ አረፍ አልኩ። ብዙም ሳልቆይ አንዲት መልከ መልካም ወጣት ወደ እኔ ቀርባ ምን እንደምፈልግ ጠየቀችኝ። ብዙም ማሰብ ሳያስፈልገኝ ‹‹ውሃ ታመጭልኝ›› እርሷም ቃጠሎዬ ገብቷታል መሰል ለዛውም የቀዘቀዘ አቀረበችልኝ። ጠጣሁት፤ ነብሴ ተመለሰች። ዋናው ነገሬ እንኳን ስለ ፀሐይዋ ማውጋት አልነበረም። እግረ መንገዴን ያስተዋልኩትን እንዲሁ ለመንገር\nያክል እንጂ! የዛሬው ቁምነገሬ ይህን ይመስላል… ለረጅም ጊዜ ተለያይተን ከነበረው ወዳጄ ጋር በቀጠሮ ሰዓት ተገናኝተናል። ከአጭር\nሰላምታ በኋላም ሊያማክረኝ ወደ መጣበት ጉዳይ … እንዲያው ሊያማክረኝ አልኩ እንጂ ያጋጠመውን ሊነግረኝ ወደፈለገው ሃሳብ በቀጥታ\nገብተን መጨዋወት ጀመርን፡፡ ‹‹እኔ የምልህ›› ብሎ ወጉን ሲጀምር በአይኔ ተከትልኩት፤ ቀጠለና ‹‹ውሸት ለካ የእውነት ድምቀቷ\nናት!›› የሚል ጭውውቱን ሲጀምር፤ በተዝናኖት ከተቀመጥኩበት እግሬን፣ እjyንና ቀልቤን እየሰበሰብኩ የወዳጄ አፍ አቅራቢያ ተጠጋሁ፤\nቀጠል አድርጎ ‹‹ባለፈው የሽርክና ስራ ለመስራት አብሬያቸው ጥምረት የመሰረትነውን ልጆች ታወቃቸዋለህ አይደል?›› ሲል ጥያቄውን\nአስከተለ። አንገቴን በአዎንታ እየነቀነኩ እንደማውቃቸው ገለፅኩለት። ‹‹ታዲያ ከሶስታችን መካከል አንዱ ይህንን የስራ ጥምረት አልወደደው\nነበር›› በማለት በዚህም ምክንያት ሊበትናቸው ፣ ጠቅላላ የስራ ግንኙነታቸውን ሊያጠፋው ያላደረው ነገር ያልፈነቀለው ድንጋይ እንዳልነበር\nአረዳኝ…። ‹‹ይህንን\nሰይጣናዊ ምግባሩን ለመከወን ያልተፈጠረ የሃሰት ስንቁን ይዞ ወጣ›› ወጉን እየሰማሁ መሆኔን ለማስረዳት ‹‹እሺ›› ብዬ ቀጣዩን\nበጉጉት እየጠበኩ… ‹‹የማህበራችንን ስም ለማጥፋት ዕቃ የምናቀርብላቸውም የተለያዩ ድርጅቶች እና ከዚህ በኋላ ይሄዳሉ ብሎ ወደሚያስባቸው\nድርጅቶች ጋር በመሄድ የሚሰሩት እንዲያ ነው… እንዲህ ነው … የእነሱ ስራ ችግር አለበት›› እያለ ብቻ ብዙ ስማቸውን እንዳጠፋ\nበንዴት አጫወተኝ። በዚህ ሁሉ የልጁን ወሬ የሚሰሙ ድርጅቶች ለማጣራት በሚል ወደ ምርት ማምረቻችን መምጣታቸውን ገለፀልኝ። ታዲያ\nየሰሙት እና ያዩት ነገር የተቃረነ በመሆኑ ከዚህ በፊት አይተውት በማያውቁት ሁኔታ በደንበኛ ብዛት እንደተጨናነቁ ነገረኝ። ታዘው\nየማያውቁትን ያክል ከአቅማችን በላይ ትዕዛዝ መቀበላቸውን በሃሴት ነገረኝ። ብቻ ምን አለፋችሁ ሊያዋርዳቸው አስቦ ቆንጆ ማስታወቂያ\nሰርቶ እንዳከበራቸው ነገረኝ። የሚገርመው በቅርቡ መኪና ሊገዙ ነው ! በውሸት ሊያጠፋቸው አስቦ መጥቶ ይልቁን አበለጸጋቸው፡፡ በዚህ\nየወዳጄ ጨዋታ መሃል ነው ያነበብኩትን የማስቀመጥበትን አድባር ቦርሳዬን (ፎልደር) ውስጥ ያለ አንድ ጽሑፍ ትዝ ያለኝ።የህዝብ ስነ\nቃሎችን በማደራጀት እንደመማሪያ የሚያቀርብ “ተረት ተረት” በሚል ስሙ የሚጠራው የማህበራዊ የትስስር ገጽ ያገኘሁትን ነው፤ አወጣሁት፤\nተረቱ ሳነበው ወዳጄ ከነገረኝ ጉዳይ ጋር ተዛምዶ አየሁት ፤ ስነ ቃሉ እንዲህ ነው… እሳት፣ ውሃ፣ እውነትና ሃሰት ጓደኞች ነበሩ።ነገር\nግን ሃሰት በዚህ ጥምረት ደስተኛ ስላልነበረ አንድነታቸውን ማበላሸት ፈልጎ እንዲህ አለ “ለምን ወደ አንድ ስፍራ ተጉዘን እያንዳንዳችን\nየራሳችንን ግዛት አንመሰርትም? ስለዚህ ተነስተን አብረን እንጓዝ፡፡”ሁሉም\nበሃሳቡ ተስማምተው ሲሄዱ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ሀሰት ወደ ውሃ ጠጋ ብሎ “እሳት ሣሩን፣ ደኑንና ቁጥቋጦውን የሚያቃጥል ቀንደኛ ጠላታችን\nስለሆነ ለምንድነው ከእርሱ ጋር ግዛት ፍለጋ የምንሄደው?” አለው።ውሃም “ታዲያ ምን ብናደርግ ይሻላል?” አለ።ሃሰትም ቀበል አድርጎ\n“ልንገድለው እንደሚገባ ግልፅ ነው።እሳትን የማጥፋት ብቸኛ ኃይል ያለህ ደግሞ አንተ ነህ።እናም ቁጭ ሲል ጠብቀህ እላዩ ላይ ራስህን\nበመርጨት አጥፋው፡፡” አለው።ውሃም “ራሴን መሬቱ ላይ ከረጨሁ ተመልሼ ውሃ መሆን አልችልም፡፡” አለ፡፡ ሀሰትም\n“ችግር የለውም፤ ተረጭተህ እንዳትበታተን የተወሰኑ ድንጋዮች በዙሪያህ አኖርና በኋላ እሰበስብሃለሁ።” አለው።በዚህ ጊዜ ያልጠረጠረው\nእሳት መጥቶ ቁጭ ሲል ውሃው አንድ ጊዜ በላዩ ላይ ሲረጭ ሃሰት ድንጋዮች ዙሪያውን አድርጎ ውሃውን ከሰበሰበውና እሳትን ካስወገዱ\nበኋላ አብረው መጓዝ ጀመሩ።ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ሃሰት ውሃውን “ለምን እዚህ ገደል አፋፍ ላይ ቁጭ ብለህ በተፈጥሮ ውበት አትዝናናም?”\nአለው፡፡ ውሃም\nአፋፉ ላይ ቁጭ ሲል ሃሰት ቀስ ብሎ ተነስቶ ውሃ የተቀመጠባቸውን ድንጋዮች ከስሩ ሲለቅማቸው ውሃው በመፍሰስ ተበታትኖ ጠፋ።በመጨረሻም\nሃሰት እውነትን ማጥፋት ነበረበትና ወደ አንድ ትልቅ ተራራ በተቃረቡ ጊዜ ሃሰት እውነትን ከተራራው ግርጌ ቁጭ በል ብሎት ከተራራው\nአናት ላይ ትልቅ አለት ቁልቁል በመልቀቅ እውነትን ሊጨፈልቀው ሲል እውነት ቀልጠፍ ብሎ ማምለጥ በመቻሉ አለቱ ተንከባሎ ሲፈረካከስ\nከውስጡ አልማዝ፣ ወርቅና ልዩ ልዩ የከበሩ ማዕድናት ወጡ።ሃሰትም የእውነትን አስከሬን ሊመለከት በመጣ ጊዜ እነዚህን ሁሉ የከበሩ\nድንጋዮችን አየ፡፡እናም\n“እነዚህ ሁሉ ከየት መጡ?” ብሎ ጠየቀ። እውነትም “ እላዬ ላይ እንዲወድቅ ከላከው አለት ነው የወጡት፡፡” አለው።በዚህ ጊዜ ሃሰት\n“አሁን ደግሞ እኔ ከተራራው ግርጌ ልቀመጥና አንተ አለቱን በላዬ ላይ ልቀቅብኝ፡፡” አለው፡፡እናም\nእውነት ወደ ተራራው ጫፍ ወጥቶ ትልቅ አለት ወደታች በለቀቀ ጊዜ የሃሰት አናት ላይ አርፎ ጨፈላልቆ ገደለው፡፡አየህ\nወዳጄ !ምን እንኳ ሃሰት ቀን የወጣላት፣ የአሸነፈች፣ የተሳካላት ብትመስልም ለጊዜው የተወሰነ ጥፋት ታደርሳለች እንጂ እውነት አትጠፋም።\nይልቅ እውነት በሃሰት የጥፋት መሳሪያ ትለመልማለች ብሎም የመበልጸጊያ መንገዶች ከሃሰት ታገኛለች። ይህ የማህበረሰብ ስነ ቃል ቀድሞ ከወዳጄ ጋር ካነሳሁት\nጉዳይ ጋር እንዴት ይገናኛል? ብለህ ከጠየከኝ፤ ስነ ቃሉም ሆነ ገጠመኜ የሚያሳየው እውነት ፈተና ቢገጥመውም በመጨረሻ አሸናፊ መሆኑን\nየሚያሳይ እንደሆነ እነግርሀለሁ። ሰላም!አዲስ ዘመን ታህሳስ 12/2012አብርሃም\nተወልደ", "passage_id": "ffe9d4c079fd0fdee3604d5f86efc207" }, { "passage": "የዛሬ ሳምንት የሸኘነው ሰኞ ዛሬም ተመልሷል፤ የሳምንቱ ማክሰኞም ነገ ሊመለስ ቀጠሮ ይዟል። ከአስር ወራት በፊት የሸኘው ክረምትም ወራቱን ሲያካልል ቆይቶ እነሆ በሰኔ «ግም» ብሏል። ማታ የተረከብነውን ጽልመት ንጋት ላይ ለጸሃይ ብናስረክብም ደግሞ ሰዓታትን ቆይቶ ዳግም ከተፍ ይላል። እድሜም እንዲሁ ነው፤\nበደካማ አካላት ህይወት ይጀመራል። ጉርምስናና ጥንካሬውም ጥቂት ዓመታትን ቢያስቆጥር ነው። ጉልምስናው እርጅናውን እየጎተተ አምጥቶ በድካም ያሳርፈዋል። ህይወት ዙረት ናት ይባላል፤ ዳሩ መሬቷም ክብ አይደለች? አዙሪቱ ሞት ከወሰደው በቀር የሄደውን መልሶ ማምጣት ሃቁ ነው። «ዞሮ ዞሮ ከቤት፤ ኖሮ ኖሮ ከመሬት» ያሉት አበውም ይህንኑ ተገንዝበው ነው። እኔ\nየምለው ግን ሳይንስ የነገረን የዓለማችን መሽከርከር በጸባያችን ላይም ተጽእኖ ያሳድር ይሆን እንዴ? «ተውነው» ያልነውን እየመላለስን፤ «ተግባባን» ያልነውን እያፈረስን፣ የረሳነውን እያስታወስን፣ የተረዳነውን እየዘነጋን፣… እንዴት እንዘልቀው ይሆን? በልጅነቴ የሰማሁትን አንድ\nቀልድ ላካፍላችሁ፤ በአንድ የአእምሮ ህሙማን ማእከል የሚገኙ የጤና ባለሙያዎች ህመምተኞቹ ተሽሏቸው እንደሁ ለማጣራት ይነሳሉ። ከዚያም ቴሌቪዥን ከሚመለከቱበት ክፍል አቧራ ያለባቸውን ወንበሮች ደርድረው ሲያበቁ፤ ህሙማኑን አንዳንድ ወረቀት እየሰጡ እንዲታደሙ ይጋብዟቸዋል። የጤና\nባለሙያዎቹ ሲመለሱም ሁሉም አቧራማው ወንበር ላይ ተቀምጠው ቴሌቪዥን ሲመለከቱ ያገኟቸዋል። ከመካከላቸው አንዱ ግን ወረቀቱን ከአቧራው ላይ አንጥፎ ነበር የተቀመጠው። ባዩት ነገርም በመደሰትና ለውጥ እንዳለው በማመን፤ «ለምን ወረቀቱን ከወንበሩ ላይ አነጠፍክ?» ሲሉ ይጠይቁታል። እርሱም «ከፊት ለፊቴ የተቀመጠው ሰው ስለከለለኝ ከፍ እንዲያደርገኝ ነው» ሲል ነበር የመለሰላቸው። ከሁሉ ይበልጥ ተስፋ ቢጣልበትም የታየው ግን ተቃራኒውን ነው። እኛም ያው ሆነናል፤ የገነባነውን መልሰን እናፈርሳለን፣ ያስተካከልነውን እናበላሻለን፣ ብንሄድም እንመለሳለን፣ ያወገዝነውን እናከብራለን፣ የሰቀልነውን ደግሞ እናወርዳለን፣ አልፈን አናልፍም፤ መልሰን ከዚያው ነን። እንዲህ ለማለት ምን አነሳሳሽ አትሉኝም? ተግባራችን ነው። ከሰሞኑ ከአዲስ አበባ አንዱ ስፍራ በእግር ጉዞ ላይ ሳለሁ፤ አንድ ወጣት ተጠግቶኝ «ዶላር ነው፤ ምንዛሬ?» እያለ ይከተለኝ ጀመር። ከወራት በፊት በዘመቻ ይህ የጥቁር ገበያ የገንዘብ ምንዛሬ እንዲቀር መደረጉን አስታውሳለሁ። እንዲያውም ይህንን ህገወጥ ተግባር የሚያከናውኑ ሱቆችም መታሸጋቸው የአንድ ወቅት ዜና ነበር። ከቆይታ በኋላ ግን ዳግም አንሰራርቷል ለማለት ይቻላል፤ ምክንያቱም ወጣቱን ጥቂት አለፍ እንዳልኩ ሌላኛውም በተመሳሳይ «ምንዛሬ?» ብሎኛላ። ስደትም ሌላኛው አዙሪት ነው። «ስደት ይብቃ» የሚል መፈክር ይዘን ነበር ቅርብ ጊዜ፤ ስለ ስደት መጥፎነትም ብዙ ተሰብከን በብዙ ኮንነናል። አሁን ደግሞ ዳግም ማሻሻያ ተደርጎበት በጋዜጣ እና ሌሎች መንገዶች በገንዘብ እያስተዋወቁና እየደለሉ ወደ ስደት ለማጋዝ በአዲስ መልክ እንቅስቃሴ ተጀምሯል። ምን ይሄ ብቻ፤ ሌላም አለ። ከወራት በፊት ከአዲስ አበባ ምድር የጎዳና ተዳዳሪነትን ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እናስወግዳለን ተብሎ በከተማዋ ሲደረግ የነበረው ሽር ጉድ የጉድ ነበር። ከተመረጡ ክፍለ ከተሞችም የጎዳና ተዳዳሪዎችን ወደ ማሰልጠኛና ማገገሚያ የመውሰዱ ተግባር ተጀመረ። ለጊዜው የተመረጡት ክፍለ ከተሞች ፀዱ። አሁንስ? ያው የአዙሪታችን ጉዳይ ሆነና “ፀዱ” የተባሉት ክፍለ-ከተሞች ተመልሰው እዛው ገብተዋል። ለአንድ ሰሞን ታትረን ብንሰራም ድካማችን ቅርብ ነው። ላንደግመው ምለን ተገዝተን የተውነውን ስንፍና፣ መጥፎ እሳቤ፣ መከፋፈል፣ መጠላለፍ እና መሰል ነገሮች ውለን ስናድር እርግፍ አድርገን እንተዋቸዋለን። ግለታችን ንፋስ ሲነካው ወዲያው ቀዝቅዞ ወደ ነበርንበት ይመልሰናል። ሌሎችም አሉ፤ ትናንት ጥያቄ አንስተው እንደተመለሰላቸው ዘንግተው ዳግም መሰል ጥያቄ ያነሱ። ከአንድ የሙያ ዘርፍ ለተነሳ ጥያቄ የተሰጠ ምላሽ፤ መሰል ጥያቄ ላለው ሌላ ሙያም እንደሚያገለግል እየታወቀ መልሶ ለጥየቃ መነሳትን ምን ይሏል? ከስፖርቱ መድረክም አንድ ምሳሌ ላንሳላችሁ፤ እግር ኳሳችንና ደጋፊዎቹን። ከስታዲየሞቻችን እስከ ጨዋታ ሜዳዎች፤ መሰዳደቡ፣ ለጠብ መፈላለጉ አልፎም ተርፎ ድብድብና ሁከቱ ጠንክሮ ነበር በአንድ ወቅት። በመንግስታዊ አካላትም ምክክር፣ ተግሳጽ እና ቅጣት ሲተገበሩም ጥቂት መሻሻል ታየ። ኧረ እንዲያውም «ስፖርታዊ ጨዋነት ቀንሷል» ተብሎ ነበር። ግን አፍታም አልቆየም፤ መልሶ አገረሸና ጭራሽ «ጨዋታውም ይቅር» ተባለ። የህይወትን አዙሪት\nመጋፋት አይቻል ይሆናል፤\nይኼኛው አዙሪት ግን\nከድክመታችን ይመነጫል። በየደረስንበት\nእየተማማልን መልሰን እዚያው\nከሆንን እርምጃችን ሁሉ\n«ባለህበት እርገጥ» ኑሯችንም\nውል አልባ መሆኑን\nእያየን ነው። ግን\nአዙሪቱ ነው መሰል፤\nከጥፋታችን አልተማርንም።አዲስ ዘመን ሰኔ3/2011 ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "6e08b001336110c76c332700f30de5a0" }, { "passage": "“እ…አብይ ይወርዳል? የትኛው ነብይ ወይም ሟርተኛ ነህ አንተ ደግሞ!” እንዳትሉኝ። ቸኩላችሁ እንዳትበይኑ፤ ጥሎብን ችኩል ፈራጆች ሆነናል። ነገሩን በጥሞና ተመልክቶ መዳኘትና ሚዛናዊ ፍርድ መስጠት ብርቃችን ሆኗል አይደል!? የምናስበውን እንጂ እውነታውን ቀርበን መመርምር ሰልችተናል። አቤት ስንቶችን ባልተገኙበት አውለን ያለተግባራቸው ስም ሰጥተን፣ ያላሰቡትን አስበንና ያላዩትን ቀለም ቀብተን በችኩልነታችን ችካል ሆነንባቸው ይሆን? ዛሬ ዛሬማ እንደልማድ በስሚ ስሚ “ተደረገ” እና “ተባለ”ን ተከትልን የምንነጉድ በመሆናችን ተወራ ብለን መበየን ተክነንበታል። እንዴት ከኛ አርቀን ማስተዋልን ጭራሽ ዘንግተን እርግጠኛ ባልሆንበት ጉዳይ የመንጋ ብያኔ መስጠት ቀልሎናል። ለዛሬ ችኮላችንን የሚያሳይ አንድ ገጠመኜን ላካፍላችሁ ወደድኩ። ጠዋት የመጽሀፍ\nመደርደሪያዬን ተጠግቼ አንድ መጽሀፍ ስፈልግ ጊዜ ወሰደብኝ። ተራ በተራ ከተደረደሩት መካከል ማግኘት አልቻልኩም። ደግሜ ከላይ እስከታች\nፈለግሁ፤ የለም። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መጽሀፍ ማዋስ መተው እንዳለብኝ እየተሰማኝ ነው። አንዳንድ ሰው መጽሀፍ ለማንበብ ተውሶ መመለስ\nአይወድም። አሊያም ደግሞ መዋሱን ይረሳዋል መሰለኝ መልስ ካላሉት በራሱ እንደ ጨዋ አመስግኖ የሚመልስ እየጠፋ ነው። እኔ ደግሞ\nየፈለኩትን/የነበረኝን መጽሀፍ ከመደርደሪያዬ ላይ ሳጣ ያናድደኛል። ዛሬም የፈለኩት መጽሀፍ የለም። ማን እንደወሰደው ማስታወስ አልቻኩም።\nበወሰደው ሰው ሳላወቀው አኮረፍኩ። ለስራ በጣም ስለፈለኩት በመጨረሻ አማራጭነት መግዛት እንዳለብኝ ከራሴ ጋር ተስማማሁ። ቁርሴን\nእንደ ነገሩ ቀመስ አድርጌ ከቤቴ ወጣሁ። መጽሀፉ ቆየት ያለ ስለሆነ ይገኛል ብዬ ወዳሰብኩበት ለገሀር አካባቢ ወዳለ መጻሕፍት ቤት\nለማምራት የሜክሲኮን ታክሲ ያዝኩ። ቡልጋሪያ ማዞሪያ ስደርስ አንዲት በዕድሜ ገፋ ያሉ እናት የተሳፈርኩበት\nታክሲ  አስቁመው፤ ባለ 25 ሊትር ቢጫ\nጀሪካን በረዳቱ አጋዥነት ወደ ታክሲው አስገቡ።  በእጆቻቸው በሩንና\nወንበር በመያዝና ዕድሜ የተጫናቸውን እግሮቻቸውን እየጎተቱ፤ በከፊል ተደግፈው ገብተው ከጎኔ አረፍ አሉ። እንደገቡ ሹፌሩ ያውቃቸዋል\nመሰል “እማማ እንዴት አደሩ ሰላም ነዎት? ከየት ነው?” አላቸው። እሳቸውም ቀና ብለው ወደ ሹፌሩ ተመልክተው በፈገግታ፡- “አብደላ\nአንተ ነህ እንዴ? ደህና ነህ አለህ ለመሆኑ …እሰይ! እሰይ! ልጄ በርትተሀላ እቺን ገዛህ፤ ላዳዋን ትተህ፤ ጎበዝ ልጄ እግዛብሄር\nይባርክልህ” ምርቃቱን አከታተሉለት።  እኔም በውስጤ ምርቃቱ ቅቡልነት\nእንዲኖረው ተመኘሁ። ከትላልቅ ሰዎች የሚገኝ ምርቃት የመንፈስ ምግብ አይደል! ደስ ሲል፤ቀጠሉ እማማ፡ “ከየት አልከኝ ልጄ ውሀ ልቀዳ ሄጄ። ይሄው\nአስራ አምስት ቀናችን ውሀ ከጠፋ እነዚህ ሙሰኞች በየቀበሌና በየወረዳው የተሰበሰቡ የመንግሥት ሹመኞች አስቸገሩን። ቆይ መስሎዋቸዋል\nገና ዶ/ር አብይ ይወርዳል። ሹመት ላይ ዘላለም የሚቀመጡ መስሎዋቸው እኮ ነው ሰውን የሚያንገላቱት…” ሰትዬዋ በሚናገሩት ተሳፋሪው\nሁሉ ጆሮ ሰጥቶ ያደምጣቸዋል። በአብዛኛው ተሳፋሪ ትኩረት የተሰጠው አንድ አረፍተ ነገር በተለይ ደጋገሙት “ዶ/ር አብይ ይወርዳል።”\nተሳፋሪው ድምጽ በማውጣት ጭምር አጉረመረመ “…እ..እ..”  በጥያቄ መልክ መሆኑ ነው። ሰው መሪውን ሲወድድ ደስ ይላል። ጠቅላይ ሚኒስትራችን\nበህዝቡ ዘንድ፤ በሰው ዘንድ ያስወደዳቸው ሁሉም ባንድነት የተቀበላቸው የዘመኑ ምርጥ መሪ ስለመሆናቸው ማሳያ የሴትየዋን “ዶ/ር\nአብይ ይወርዳል” የሚለውን ዓረፍተ ነገር መሰማት ተከትሎ በተቀየረው የተሳፋሪዎች የፊት ገጽታ ይበልጥ ተደመምኩ። ሴትዬዋ ቀጠሉ፡ “የወረዳው ሰራተኞች ስራ አይሰሩም። በማይረባ\nወሬ ነው ቀናቸውን የሚጨርሱት፤ ቧንቧ ተበላሸ እባካችሁ ስሩልን ብለን መመላለስ ከጀመርን 10 ቀን አለፈ። አልሰራ ብለውን በስተርጅና\nጀሪካን ተሸክመን እንዞራለን። እንቢ አሉ። የተነገራቸውን መስማት አቁመዋል። ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዶክተር አብይ ይወርዳል! አብያችን\nቀበሌ ድረስ ወርዶ ሁሉንም ያስተካክላል። እስከዚያ እንዳሻቸው ያድርጉን፤ ጉዳቸው ማሾፋቸው እስኪታወቅ ነው አብያችን መቶላቸዋል፤ለካስ ይወርዳል፤ እስከ ቀበሌ ድረስ፤ የሚሉት የጠቅላይ\nሚኒስትሩን አዲስ አሰራር ነው። ተሳፋሪው ከስልጣን ይወርዳል ብለው እሱን እየዘለፉ መስሎት ጆሮውን አቁሞ በቅሬታ እየገላመጣቸው\nእንዳላዳመጠ ነገሩ ሲገባው በፈገግታ እርስ በእርሱ ይተያይ ጀመር። ሴትዮዋ ቀጠሉ፤ ሁሉም ተሳፋሪ በፈገግታ እሳቸውን ነው የሚሰማው፤\n“ የሚናገረውን አልሰማህም ልጄ? ህዝብን አገልግሉ፤ ሀገራዊ ኃላፊነታችሁን ኢትዮጵያዊ አደራችሁን ተወጡ ሲል፤ እሱ የተባረከ ነው!\nቃሉም ተግባሩም የሚያጠገብ፤” እሳቸው የሚያወሩት ሹፌሩን እየተመለከቱ ነው ሌላውን ተሳፋሪ ቁብ ሰጥተው አላዩትም።“አይ እኛን በነገር ካስረጁን ዕድሜያችን ከገፋ በኋላ\nለእናንተ ምርጥ መሪ መጣ። እኛማ ጃጀን። በዚህ ዕድሜያችንም ቢሆን ይሄን ሀገር ወዳድ መሪ ስለሰጠን አምላክን እናመሰግነዋለን።”\nየሴትዮዋ የሰላ ንግግር ጆሮ ያስጥዳል። በመሀል ሹፌሩ ረዳቱን “እንዳትቀበላቸው የሳቸው ተከፍሏል” አለው። ረዳቱ የተቃውሞ ምላሽ\nሠጠ፡-“ኧ ዴች ነው። አብዲ ተቀብያለሁ። ብዙ ነው እስከነ ጀሪካናቸው” አለ። አስር ብር ማለቱ ነበር። ሴትዮዋ፡- “የምን ቋንቋ\nመቀየር ነው ግብዣ ከፍ ሲል ነው የሚጥመው፤ መልስላት ተባልክ መልስ!” ሲሉ በታክሲው ውስጥ የነበርነው ሁላችንም ተሳፋሪዎች በሳቅ\nተንከተከትን።በነገራችን ላይ የቋንቋ አጠቃቀማችን ብዙ ያስተዛዝባል\nአይደል፤ በእርግጥ የረዳቱ ከሹፌር ወይም መሰል የሙያ ባልደረቦቹ ጋር መግባባት የሚችሉበት ቋንቋ መፍጠራቸው ችግር ባይኖረውም፤\nከማንና እንዴት መጠቀም እንዳለባቸው አለመረዳታቸው ተግባቦትን ያፋልሳል። “አራዶች” የኛ የሚሉት ካራዶቹ ጋር ካልሆኑ ከኔ ቢጤው\nጋር ሊያግባባቸው አይደለም በወጉ ሊያጋጫቸውም ይከብዳል። በየሆቴሉ መዝናኛና አቅጣጫ አመላካች የሆኑ ቦታዎች ላይ የሚለጠፉ ማህበራሰቡን\nወይም ነዋሪውን የዘነጉ የቋንቋ አጠቃቀሞች አብዛኞቹ በእኛ አገር እና ለኛ የተዘጋጁ እኛን ግን የማያግባቡ መሆናቸው ወደፊት የምናየው\nይሆናል።የረዳቱ ከሹፌሩ ጋር የተነጋገረበት የራሱ ቋንቋ እናታችን\nበሰጡት የመልስ ምት ድል ሆነና ሹፌሩ በድጋሚ እንዲመልስላቸው ነግሮት መለሰላቸው። በመጨረሻ ሜክሲኮ ኬኬር ህንጻ አጠገብ ሲደርሱ\nለሹፌሩ እንዲያቆምላቸው ነግረው የምርቃት መዓት አዥጎድጉደውለት ወረዱ። የምን አስር ብር ነው ይህን ምርቃት ለማግኘት ምንስ ቢሰጥ፤\nእናም ወረዳ ምናምን ላይ ያላችሁ አስፈጻሚዎች፤ እባካችሁ በእናንተ አቅም የሚፈታውን የህዝቡን ጥያቄ  እየለያችሁ ፍቱ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ እናንተ ዘንድ ከመድረሱ\nበፊት እባካችሁ እናንተ ወደ ህዝቡ ዘንድ ውረዱና አድምጡት፤ ብለዋችኋል እናታችን፤አዲስ ዘመን የካቲት 6/2011", "passage_id": "0b406825e05019e01f1fe5967b35c23c" }, { "passage": "“በአንድ ወቅት በአንድ ስፍራ የሚኖር ቤተሰብ ነበር። በቤተሰቡ ውስጥ አንድ አባወራና ባለቤቱ ከሴት ልጃቸው ጋር ይኖራሉ። ነገር ግን ሦስቱም መስማት የተሳናቸው ነበሩ። ከዕለታት አንድ ቀን አመሻሽ ላይ አባወራው አህያውን ውሃ ሊያጠጣው ፈልጎ እየነዳ ወደ ወንዝ ወረደ። ወንዙ አጠገብ እንደደረሰም ሌሎች ብዙ እረኞች ከብቶቻቸውን ውሃ እያጠጡ ነበር። እነእርሱም “ሰማህ አንተ ሰው? ከብቶቻችን እየጠጡ ነው። ያንተ ግን አህያ ስለሆነ ከብቶቻችን ቀድመው ይጠጡ፤” አሉት። ሰውዬውም “ይቅርታ አህያዬ የሚሸጥ አይደለም” አላቸው። \nእረኞቹም “ሰውየው እብድ ነው እንዴ?” ብለው ጥለውት ሄዱ። ሰውዬውም አህያውን አጠጥቶ ወደ ቤቱ ተመለሰ። ቤት እንደደረሰም ወደ ኩሽና ሄዶ ባለቤቱን እንዲህ አላት፤ “ይገርምሻል! ዛሬ ነጋዴዎችን መንገድ ላይ አግኝቼ ‘አህያህን ካልሸጥክልን’ ብለው ሲያስቸግሩኝ የሚሸጥ እንዳልሆነ ነገርኳቸው። ” ሚስቱም ቀና ብላ አይታው “እንግዲያውማ ልትፈታኝ ከወሰንክ አንድም ቀን ካንተ ጋር ማደር ስለማልፈልግ ወደ ቤተሰቦቼ እሄዳለሁ” ብላ፤ ዕቃዎቿን እየሰበሰበች እያለች ልጃቸው ወደ ቤት ስትገባ እናት ቀና ብላ አይታት “ይገርምሻል! ከእነዚያ ብዙ የትዳር ዓመታት በኋላ አባትሽ ሂጂልኝ አለኝ” አለቻት። ልጅቷም የሃፍረት ፈገግታ አሳይታ ቀና ብላ እንግዲህ “እናንተ ወላጆቼ ናችሁ። ልትድሩኝ ከፈለጋችሁ በሃሳባችሁ እስማማለሁ፤” አለቻቸው ይባላል። \nዛሬ በአገራችንም ከኮሮና ቫይረስ ጋር ተያይዞ እንዲህ አራምባና ቆቦ የሆኑ ያለመደማመጥ ችግሮችን በየቦታው እናስተውላለን። በተለይ ወረርሽኙን ለመከላከል መንግሥት ዘርፈብዙ ጥረቶችን እያደረገ ባለበት በአሁኑ ወቅት ለቫይረሱ መስፋፋት ምክንያት የሆኑ ተግባራት እዚህና እዚያ መስተዋላቸው እውነትም መስማት የተሳናቸው ሰዎች መኖራቸውን ያሳያል። \nለምሳሌ በአገራችን በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከተቀመጡ ክልከላዎች ውስጥ አንዱ ከሦስት በላይ ሆኖ አንድ ላይ መሰብሰብ ወይም መገናኘትን ነው። ከዚህ አንፃር ሕጉን የሚያከብሩ በርካታ ዜጎች ቢኖሩም ጥቂቶቹ ግን ይህን ችላ ብለው በየገበያ ቦታው፣ በተለያዩ የመጠጥና የመመገቢያ ስፍራዎች፣ በመጫወቻ ስፍራዎች እንዲሁም በመንገድ ላይ ይታያሉ። \nከዚህ አንፃር በተለይ በመርካቶ ገበያ አካባቢ ያለውን የህዝብ ስብስብ ለተመለከተ አዋጁ ስለመኖሩ ሊጠራጠር ይችላል። ከዚህም ባሻገር በተለይ አሁንም አንገት ለአንገት ተቃቅፈው የሚጓዙ ወይም ተሰብስበው የሚያወጉ ወጣቶችን ማየት እንግዳ አይደለም። ታዲያ መንግሥት ከዚህ በላይ ምን ማድረግ አለበት? የግድ የእያንዳንዱን ሰብኣዊ መብት በሚጥስ አግባብ በፀጥታ አካላት አማካኝነት ሰዎችን መበተን አለበት። አዕምሮ የተሰጠው የሰው ልጅስ እንዴት እንዲህ አይነት ራስን የሚጎዱ ተግባራትን በራስ ላይ ይፈፅማል? \nበተደጋሚ እንደተነገረው የኮሮና ቫይረስን ለመቆጣጠር ዋነኛው መንገድ አካላዊ ርቀትን መጠበቅ ነው። ይህንን በአግባቡ ተግባራዊ ያላደረጉ የበለፀጉ አገራት ጭምር ምን እየደረሰባቸው እንደሆነ በየዕቱ ከዓለም አቀፍ ሚዲያዎች እየሰማን ነው። ቫይረሱ በአገራችን ከተስፋፋ ደግሞ መቆጣጠር ከማንችለው ከፍተኛ አደጋ ውስጥ እንደሚከተን ይታወቃል። ታዲያ ከዚህ አንፃር ለራሳችን ጤንነት ሲባል እንድናከብራቸው የተነገሩንን ሕጎች ማክበር ለምን ተሳነን? ወይስ የምንሰማው መስማት የምፈልገውን ብቻ ነው። \nአንዳንዶቻችን ደግሞ ፈጣሪ ኢትዮጵያን ብቻ ለይቶ እንደፈጠረ ሁሉ “እኛ ፈጣሪ ይጠብቀናል፤ ስለዚህ ኮሮና ምንም አያደርገንም” በሚል አስተሳሰብ ራሳችንን ስናታልል እንታያለን። እንዲህ የሚሉ ሰዎች ደግሞ ስለእምነት እውቀት የላቸውም ለማለት ያስደፍራል። ምክንያቱም የሃይማኖት አባቶች እንደሚያስተምሩት ፈጣሪ የሚረዳን እኛም የበኩላችን ሃላፊነት ስንወጣ ብቻ ነው። ለዚህ ነው የሃይማኖት አባቶችም የህክምና ባለሙያዎችን ምክር ተግባራዊ እንድናደርግ በተደጋጋሚ የሚነግሩን። \nእናም መስማት እንደተሳነው ቤተሰብ ውስጣችን ወይም እኛ ለራሳችን የነገርነውን ብቻ ከምንሰማ የባለሙያንና የመንግሥትን እንዲሁም የሃይማኖት አባቶችን ምክር በመስማት ራሳችንን ከኮሮና ቫይረስ እንከላከል። ይህ ሳይሆን ቀርቶ በራሳችን መንገድ የምንነጉድ ከሆነ ግን ኋላ ማጣፊያው ያጥረናልና ከወዲሁ እንጠንቀቅ። አዲስ ዘመን ሚያዝያ 16/2012", "passage_id": "75552930559a4aca74edbbff13367ad7" }, { "passage": "ከዩኒቨርሲቲ ተመርቄ ሦስት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የሦስት መስሪያ ቤቶችን ጓዳ አንጎዳጎድኩ። እነዚህ ተቋሞች አንድ ነገር እንደሚያመሳስላቸው ታዝቤያለሁ፡፡ ዜጎች በዩኒቨርሲቲ፤ በመስሪያ ቤቶችና መኖሪያ መንደሮች አካባቢዎች ሰብሰብ ብለው ስለ አንድ ጉዳይ በተለይ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ ሃሳቦችን በመሰንዘር እንደሚወያዩ ይታወቃል። በዚህም በሁለት ከፍ ሲልም በሦስት ጎራ ተከፍሎ መከራከርም የተለመደ ነው፡፡ \nበየሰፈሩም ቢሆን ሰብሰብ ተብሎ እስከ ምሽት ሦስት እና አራት ሰአት ድረስ ትኩረት ስለሚስቡ ጉዳዮች መወያየት በወጣቶችም ሆነ በተለያየ የእድሜ ክልል ላይ በሚገኙ ሰዎች አዲስ ነገር አይደለም። በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጊቢ ውስጥ ከዋናው ጉዳይ ውጪ ስለፍቅር የሚወራበት፣ ሴቶችና ወንዶች ሰብሰብ ብለው የሚያወጉበት፣ ፖለቲካ የሚፈጭበት እና የችከላ ቦታዎች በስፋት አሉ፡፡ \nበእርግጥ እነዚህን ለምሳሌነት አነሳሁኝ እንጂ ሌሎችም አይጠፉም፡፡ ሁሉም ደስ ወዳለው እየሄደ ሃሳብን በሃሳብ ይመለክታል፤ አንዱ ለሌላው ያዋጣል። ይህ ደግሞ በየእለቱ ከአዲስ ሰዎች ጋር ለመተዋወቅ እድልን ይፈጥራል፡፡ ከፍ ሲልም ሊያወዳጅ ይችላል፡፡ ጉዳዩ የሰው ልጆች ባህል መሆኑን ለማመላከት ከጥንት ጀምሮ እንደሚፈፀም በርካታ መረጃዎችን በማንሳት ማሳየት ይቻላል። \nየዛሬ ምልከታዬ በዋናነት በአገራችን በተለይ ደግሞ በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት መዝናኛ ክበብ ውስጥ ክርክር ስለሚደረግበት አንድ ቦታ ማውሳት ነው፡፡ በዚህ ስፍራ ደንበኞች የሚስተናግዱባቸው ቦታዎች የራሳቸው የሆነ መለያ ቁጥር ተሰጥቷቸዋል፡፡ አስተናጋጆችም አንድ፣ ሁለት እና ሦስት ወዘተ. የሚል የመለያ ቁጥር አላቸው፡፡ በዚህ መሰረት ደንበኞቻቸውን ያስተናግዳሉ፡፡ \nቁጥር ከተሰጣቸው ቦታዎች መካከል አስተናጋጆች በቅፅል ስሙ ‹‹ሲጋራ ተራ›› ብለው ይጠሩታል፡፡ እኔ ግን ወሬ ማጨሻ ቢባል የተሻለ ይመስለኛል፡፡ መጠሪያውን ያገኘው በቦታው ላይ ከሚቀመጡ ሰዎች ባህሪ አንፃር ነው፡፡ በብዛት የሚያዘወትሩ ሰዎች ሲጋራቸውን ማግ እያደረጉ ወሬ የሚያጨሱ ናቸው፡፡ ነገር ግን ቡና እየጠጡ እና ቁርሳቸውን እየበሉ የሚሳተፉም ሆነ የሚታዘቡም በስፍራው ይታደማሉ፡፡ \nከዚህ ቀደም የዚያ ሰፈር ደንበኛ ስላልነበርኩ፤ በርከት ያሉ ሰዎች ተሰብስበው ድምፃቸውን ከፍ እያደረጉ ሲያወሩ ብሰማም ትኩረት ሰጥቼው አላውቅም ነበር። አንድ ቀን ግን የቦታውን ሁኔታ ከሚያውቅ ጓደኛዬ ጋር ሄደን ቁጭ አልን፡፡ አረፍ ከማለቴ ብዙ ነገሮች ሲወሩ (እየተነሱ ሲጣሉ) ሰማሁኝ፡፡ በስፍራው ተገኝቶ የራስን ሃሳብ አለመሰንዘር ከባድ ነው፡፡ ድንገት እራስን ከአንዱ ሃሳብ ጋር አዛምዶ አመክንዮን ሲወ ረውሩ ያገኙታል። \nበወሬ ማጨሻ ስፍራዋ ፖለቲከኞቻችን ስልጣናቸውን ለማስጠበቅ ሲሉ ‹‹ፖለቲካንና ኤሌክትሪክን በሩቅ ነው›› እያሉ የሚያስፈራሩባት አባባል ቦታ ካለማግኘቷም በላይ ቃሏ ትዝ የምትለው ተከራካሪ የለም፡፡ እየተመረጠ እሳት እሳቱ ይወራል፡፡ በእርግጥ ‹‹ጋዜጠኞች›› በመሆናቸው ለሻይ አረፍ ሲሉ ይህን መሰል ሃሳብ መሰንዘሩ የሚጠበቅ ነው፡፡ \nብዙ ዝምተኛ የሚመስሉ የስራ ባልደረቦቼ በሲጋራ ተራ ወሬ ለማጨስ ማርሽ ቀያሪዎች ናቸው፡፡ ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ በጥቅሉ ማህበራዊ ጉዳዮች ይወራሉ፡፡ በስፋት ይተነተናሉ፡፡ አንድ ወሬ ይወለዳሉ፤ በፍጥነት ያድጋሉ፤ ይሞታሉ፡፡ በጥቅሉ ለማውራት ‹‹እኛ እና እነሱ ›› ብሎ መፍራት የለም፡፡ በሀያሏ አሜሪካ በቅርብ እስከተዋለደችው ደቡብ ሱዳን ድረስ የማይንኳኳ በርና የማይነሳ ሀሳብ አይገኝም፡፡ የሚጎነተለው ተተንኩሶ፤ የሚብጠለጠለው ይጎሻሸማል። የሚወደሰውም እንደዛው፡፡ \nስለ አገራችንም ፖለቲካ አንዱ ብድግ ብሎ አሁን ያሉ ችግሮች ሁሉ በቅርብ እንደሚፈቱና ከወቅታዊ ችግር በዘለለ ዘላቂ ችግር እንዳልሆነ ሲናገር ፤ በሌላ ጎራ የተሰለፈው ቡድን ደግሞ የኢትዮጵያ እድሜ ከአንድ ቀን የጸሀይ ውሎ እንደማይበልጥ በማስረጃ ‹‹እውነት ነው እንዴት?›› እስክትል ድረስ አስረድቶ ሊያሳምንህ ይሞክራል፡፡ በወሬ ማጨሻ ቦታ የአገራችን ፖለቲከኞች ምን እንደሚባሉ ቢሰሙ ብዬ ልከትበው አሰብኩና ከዚህም በላይ ሃሳብ በሃሳብ እንደሚደባደብ ሲገባኝ አለፍኩት። \nከላይ ካነሳሁላችሁ መነሻ አመክንዮ በተጨማሪ እንዲህ አይነት ክርክር እና ውይይት የማውቀው በመፅሐፍ ላይ የ1960ዎች ትውልድ እየተባሉ የሚጠሩ ተማሪዎችን ነው፡፡ ካፒታሊዝምን ጠልተው ሶሻሊዝምን አምልከው የእነ ሌሊን መፅሐፍትን እንደሕይወት መርህ ቆጥረው የሚከራከሩት ማለት ነው፡፡ \nበዚህ ስፍራ ከታደምኩ ወዲህ እንዲያውም የአገራችን ፖለቲከኞች ከስሜታዊነት ነፃ ሆነው ክርክር ማድረግ ከፈለጉ ወደ ኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጎራ ቢሉ ከወቀሳ ይተርፋሉ የሚል እምነት አሳድሮብኛል። ጥሩ ልምድም እንደሚያገኙም አልጠራጠርም፡፡ ያው አለ አይደል ልምድ ልውውጥ ጥሩ ነው መቼም። በመደማመጥ ላይ የተመሰረተ ውይይት ከመልመድም፤ የአንድን ሰው እውነት ከማጣጣልና ከመንቀፍ ይልቅ፤ ሃሳብን በሃሳብ የመመከት ጥሩ ል ምድ መቅሰም ነው፡፡ \nእናማ ሃሳቤን ከማጠቃለሌ በፊት በመጨረሻ ይሄን ሃሳብ ጣል ለማድረግ ወደድኩ። ችግሮችን በክርክር የመፍታት ልምዱ ደካማ ለሆነ ማህበረሰብ ‹‹የወሬ ማጨሻ›› ተብላ እንደተሰየመችው ስፍራ በተመሳሳይ በተለያዩ ቦታዎች እንዲህ ያሉ የበረከቱ ጉሊቶች መኖር አለባቸው የሚል ሃሳብ አለኝ፡፡ በተለይ ደግሞ በመስሪያ ቤት፣ በትምህርት ቤት እና በመዝናኛ ቦታዎች ቢዘወተሩ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች ይኖራቸዋል፡፡ በተለይ ሃሳብን በነፃነት ለመተንፈስ። \nአንዳንድ ወዳጆች በአጋጣሚ አልያም አስበውበት ወደ አራት ኪሎ ብቅ ካሉ ‹‹ወሬ ማጨሻ›› ጎራ በማለት፤ በአምስት ብር ቡና እየተጎነጩ ዋጋ የማይወጣለትን ሃሳብ እንደሚያዋጡ በሚስጥር ሹክ ማለት እወዳለሁ። ሰላም!\nአዲስ ዘመን ግንቦት 16/2012ሞገስ ፀጋዬየጋዜጠኛው ቅኝትከእርሶ ለእርስዎአዲስ ዘመን ግንቦት 16/2012ተገኝ ብሩ", "passage_id": "ab6790cc0fcb18ad800bde45ea316503" } ]
fd4c1bcfdaa8448b23a6dbab94df4514
83fd508b17a12bd06e0c4b273852a71a
አማራጭ ሃሳብ አምጡ!
ከብዙ ጊዜያት በፊት በአንድ አገር ውስጥ የሚኖሩ ማህበረሰቦች ነበሩ። እነርሱንም የሚያስተዳድር አንድ ንጉሥም ነበር። ይህ ንጉሥ የሚያስተዳድራቸውን ነዋሪዎች በደስታ ያኖራቸው ነበር። በእሱ የአገዛዝ ዘመን ሁሉም ነዋሪዎች በነፃነት ተገቢውን ነገር በማድረግ በሰላም ኑሯቸውን ይመራሉ። ንጉሣቸው እርሱ በመሆኑም በጣም ደስተኞች ነበሩ። በአንድ ወቅት ንጉሡ በአገሪቷ ላይ የሚገኙ ታሪካዊ ቦታዎችን፣ የአምልኮ ስርዓት የሚፈፀምባቸው ቤተክርስቲያናትን እንዲሁም እርሱ በአገዛዙ ወቅት ያልተመለከታቸውን እና በርቀት ያሉ አካባቢዎችን ለመመልከት ይወስናል። እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው እርሱ የሚያስተዳድራቸውን ቦታዎች ለማወቅ እና ሁሉም ስፍራዎች ምቹ እና የማህበረሰብ ክፍሎችም በሰላም እና በተድላ መኖራቸውን ለማረጋገጥ ስለፈለገ ነበር።ንጉሡ ጉብኝቱን በእግሩ በመጓዝ ለማድረግ ይወስናል። አገልጋዮቹን እና አብረውት የሚጓዙ ቤተሰቦቹንም ከእርሱ ጋር በእግራቸው እንዲጓዙ አደረገ። ንጉሡ ይህንን ለማድረግ የወሰነበት ምክንያት በቀላሉ የሚያስተዳድራቸውን የማህበረሰብ ክፍሎች እንዲያገኝ ስለሚያስችለው ነበር። በዚህ የተነሳ እርሱ ጉብኝት በሚያደርግባቸው አካባቢዎች የሚያገኛቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ንጉሣቸውን በማግኘታቸው እና ከእርሱም ጋር በማውራታቸው ፍፁም ደስተኛ ሆኑ። እነርሱ በዚህ ንጉሥ ስር ስለሚተዳደሩ እና ቅን ልቦና ያለው መሪ ስላላቸው ደስተኞች ሆኑ። ይህ ቅን ንጉሥ በርካታ የአገሩን አስደናቂ ቦታዎች መመልከት ቻለ። ታሪካዊ ቦታዎችን፣ የእምነት ስፍራዎችን በተፈጥሮ የተዋቡ አካባቢዎችን እንዲሁም በርካታ ባህል ያላቸው የማህበረሰብ ክፍሎችን ማግኘት በመቻሉ በጣም ደስተኛ ሆነ። አገሩ እጅግ የበለፀገች በመሆኗም የሚያምነውን አምላክ አመሰገነ። ይህ ንጉሥ በሚደርስበት አካባቢ ሁሉ እጅግ በከበረ ሁኔታ አቀባበል ይደረግለት ነበር። ነዋሪዎቹም ቅን እና ለማህበረሰቡ ከልቡ አሳቢ በመሆኑ እጅ እየነሱ ያመሰግኑታል። ከብዙ ቀናት የጉብኝት ቆይታ በኋላ ጉብኝቱን አጠናቀቀ ወደ መኖሪያ ስፍራውም ደስተኛ ሆኖ ተመለሰ። እርሱ የሚያስተዳድራቸው ሰዎች በተድላ እና በደስታ መኖራቸውንም በዓይኑ አይቶ መመስከር ቻለ። ሁሉም ነዋሪዎች ኑሯቸውን ያለምንም ችግር ይመሩ ነበር። አብዛኞቹ በግብርና ሥራ፣በከብት ማርባት እና በብረታብረት ምርት ላይ አድርገው ነበር። ኑሯቸውን የሚያቀልላቸው አዳዲስ ማሽኖች ይፈጥሩ እና ይገለገሉባቸውም ነበር። ነገር ግን ይህ ንጉሥ በጉብኝቱ ወቅት አንድ ያዘነበት እና ቢስተካከል ብሎ ያሰበው ጉዳይ ነበር። ረጅም ርቀት በመጓዝ ጉብኝት ባደረገበት ወቅት እግሩን በጣም ታሞ ነበር። እግሩን የሚከላከልለት ምንም ነገር ስላልነበረም በጣም ለሚያስጨንቅ ህመም ተዳርጓል። የውስጥ እግሩም ቆስሎ መሬት ለመርገጥ በጣም ተቸግሮ ለትንሽ ጊዜም ቆየ። ባለሟሎቹ እና ቤተሰቦቹ በተፈጠረው ነገር በጣም በማዘን በቶሎ እንዲያገግም ዕርዳታ ያደርጉለት ጀመር። ከህመሙ እንዳገገመ አንደኛውን ሚኒስትሩን በመጥራት ስለተፈጠረው ነገር አናገረው። እንዲህም አለው «አገሪቷ ላይ ያሉትን ታሪካዊ፣ ተፈጥሯዊ እና ሃይማኖታዊ ስፍራዎች በመመልከቴ በጣም ደስተኛ ነኝ። ህዝቦቼም በተድላ እና በደስታ በመኖራቸው እረክቻለሁ። ነገር ግን አንድ ጉዳይ አላስደሰተኝም። ይህም የተጓዝንበት መንገድ በጣም የማይመች እና ኮሮኮንቻማ ነበር። ጠጠር እና ሹል ድንጋዮችም ይበዙበት ነበር። እኔ ለጥቂት ግዜያት በእነዚህ አካባቢዎች ስጓዝ ይህ ችግር አጋጥሞኛል። ነገር ግን ሁል ጊዜ በእነዚህ መንገዶች የሚገለገሉት ህዝቦቼ ምን ያክል ይሰቃያሉ? ይህ ጉዳይ ለህዝቤ ምቾትን የሚቀንስ እንደሆነ ተረድቻለሁ። ነገሩ በጣም አሳስቦኛል» አለው። ለሚኒስትሩ ይህን ካለው በኋላ እንዲህ በማለት ትዕዛዝ ሰጠ « በሁሉም መንገዶች ላይ የበሬ ቆዳዎችን አንጥፉ። በዚህ ምክንያት ህዝቦቼ እንዲሰቃዩ አልፈልግም። ይህን ቆዳ ካነጠፋችሁ ግን ሁሉም ሰው በምቾት መንቀሳቀስ ይችላል» አለው። ሚኒስትሩ ንጉሡ ይህን ሲል በመስማቱ በጣም ግርምት እና ጥያቄ ተፈጠረበት። ምክንያቱም የንጉሡን ትዕዛዝ በማክበር እነዚህ ቆዳዎች እንዲነጠፉ ቢደረግ በጣም በብዙ መቶ ሺ የሚገመቱ ከብቶች መሞት ይኖርባቸዋል። ይህ ደግሞ አርሶአደሩ ለወተት ምርት እና ለግብርና ሥራ የሚጠቀምባቸውን ከብቶች ሊያጣ ይችላል። በመንገዶቹ ላይ ቆዳውን ለማንጠፍ ደግሞ በጣም ብዙ ገንዘብ የሚጠይቅ እና ከባድ ነበር። የአገሪቷን ሀብትም በቀላሉ የሚያጠፋ ነበር። በዚህ የተነሳም ከንጉሡ ትዕዛዝ ሲቀበልና ሲወያይ የነበረው ሚኒስትሩ ለሥራ አጋሮቹ ሃሳቡን አጋራቸው። እነሱም በእርሱ ስጋት ተስማሙ። በርካታ ገንዘብ እና በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ከብቶች መጥፋቱ አሳሳቢ ሆነባቸው። ሚኒስትሮቹ በጉዳዩ ላይ በጣም ተጨንቀው መፍትሔ በማፈላለግ ላይ ሳሉ፤ ከመካከላቸው የነበረ አንድ ብልህ ሚኒስትር ሃሳብ እንዳለው ተናገረ። ይህን መፍትሔም ለንጉሡ ማቅረብ እንዳለባቸው ተስማምተው ሰውዬው ወደ ንጉሡ ዘንድ ሄደ። ሚኒስትሩ አማራጭ ነው ብሎ ያቀረበውን ሃሳብ ንጉሡ ጠየቀው። ሚኒስትሩም እንዲህ በማለት መለሰለት «ንጉሥ ሆይ መንገዱን በቆዳ ከመሸፈን ይልቅ፤ ለምን በእግር ልክ ተስተካክሎ የተቆረጠ ቆዳ ሁሉም ሰው አያደርግም። ይህ ሲሆን አንድ ቆዳ ብዙ የእግር ሽፋኖችን መሥራት ይችላል» በማለት መለሰለት። ይህ ብልህ ሚኒስትር ባቀረበው ሃሳብ ንጉሡ በጣም ተገረመ። ሃሳቡም በጣም ትክክል እና በቶሎ መተግበር ያለበት ጉዳይ እንደሆነ ተናገረ። ለሚኒስትሩ አድናቆት እና ሽልማት አበረከተለት። በቶሎም ለራሱ ሁለት ከቆዳ ላይ የተቆረጡ መሸፈኛ ጫማዎችን አዘዘ። ህዝቦቹም ልክ እርሱ እንዳደረገው ጫማ እንዲያደርጉ እና እራሳቸውን ከጉዳት እንዲጠብቁ ጠየቃቸው። ህዝቦቹም ንጉሣቸው ከልቡ እንደሚያስብላቸው በማወቃቸው እና የቀረበላቸውን ሃሳብ ስላስደሰታቸው በሃሳቡ ተስማሙ። ከዚያን ጊዜ ጀምሮም ህዝቡ በተለያየ ፋሽን ጫማዎችን ማድረግ እና እግሮቹን ከጉዳት መከላከል ጀመረ። የተሻለ አማራጭ ሃሳብ ያለው ሁልጊዜም ተመራጭ ነው።አዲስ ዘመን የካቲት 22/2012ዳግም ከበደ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=28167
[ { "passage": "ያሉበት ሁኔታ - የጤና እና የኑሮ ብርቱ ፈተናዎች ያስጨንቁዎታል? .. ብቻዎን አይደሉም! የኮረናቫይረስ መዛመድ የከሰተውን አሳሳቢ ሁኔታ ተከትሎ በእርስዎና በቤተሰብዎ፤ በወዳጅ የዘመዶችዎ አለያም በጉዋደኞችዎ፤ ብሎም በወገኖችዎ ጤና እና ደህንነት ጉዳይ ሃሳብ ገብቶዎታል? በኑሮዎ ላይ እያሳደረ ያለው ሊያሳድር የሚችለው ጫና እና መቃወስ ለጭንቀትና ለምን ይመጣ ይሆን ስጋት ዳርጎዎታል? ጭንቀትዎም ይሁን ስጋትዎ ምክኒያታዊ ነው።አንዳንዴም ከዚህ አልፎ ግራ ግብት ይልዎ ይሆናል። አሳሳቢው ፈተናዎች መላ ፍለጋ በሃሳብም በአካልም የቻሉትን ያህል ደክሞም ቢሆን መፍትሄ በመሻት እና ለመንፈስ መረበሽ በመዳረግ መሃከል ግን ትልቅ ልዩነት አለ።በእርግጥ እንዲህ ግራ የሚያጋባው ነገር በበዛበትና ሰማይ የተደፋ በሚመስልበት ጊዜ ራስን ከከፋው አደጋ ለመታደግ የሚያስችልና በተጨባጭ ሊደረግ የሚችል ነገር ይኖር ይሆን? ሁለት ታዋቂ የአንጎል ህክምና ባለሞያዎች ጋር በምናደርገው ደርዝ ያለው ወግ የችግሮቹን ተፈጥሮና መንሴዎች፡ ብሎም የተሻሉ አማራጮች በትልቀት እና በዝርዝር እንፈትሻለን። ከዚያም ሻገር ብለን የመጭውን ዘመን የነገውን ዓለም ህይወት ገጾች እንገልጣለን።ተከታታይ ክፍል ውይይቶቹን ከዚህ ያድምጡ።", "passage_id": "3bdba401bfae09bcb41ea239b792204d" }, { "passage": "ወረርሽኙ የበርካቶችን የሕይወት አቅጣጫ ለውጧል። ጊዜ ለማሳለፍ ሲሉ ቋንቋ መማር፣ ቤት ውስጥ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መሥራት ወይም ምግብ ማብሰል መለማመድ የጀመሩ አሉ።\n\nአዳዲስ ነገር የመሞከር ተነሳሽነት ሁሌም አብሮን ይዘልቃል ማለት ግን አይደለም። አንዳንዴ በከባድ ስንፍና ሳቢያ ትንሽ ነገር እንኳ መፈጸም ይሳነናል።\n\nበዚህ ወቅት ራሳችንን ዳግመኛ ማነሳሳት የምንችልባቸውን ጥቂት መንገዶች እንመልከት።\n\nአዲስ ነገር መሞከር\n\nተነሳሽነት ለራስ የሚጠቅም ተግባር ማከናወን እንዲሁም ለሌሎች መትረፍንም ያካትታል።\n\nሰውን መርዳት የሚሰጠው ሀሴት ወይም በሚሠሩት ሥራ መደሰት ተነሳሽነትን ይጨምራሉ። እንደ ገንዘብ እና ሽልማት ያሉ ማበረታቻዎችም ያነሳሱናል።\n\nኮሮናቫይረስ ብዙዎችን ሥራ አልባ አድጓል። ማኅበራዊ ሕይወትንም አላልቷል። እናም በርካቶቻችን ተነሳሽነታችን ጠፍቶ ስንፍና ቢጫጫነን አይገርምም።\n\nየአሜሪካ የሥነ ባለሙያዎች ማኅበር ዋና ዳይሬክተር ሊን ቡፍካ እንደሚሉት፤ አዕምሯችን መልካም ነገሮች ላይ እንዲያተኩር በማድረግ ተስፈኛ ለመሆን መሞከር ያስፈልጋል።\n\nለምሳሌ ስለወደፊቱ ስናስብ የተሻሉ ቀኖች ሊመጡ እንደሚችሉ በማሰብ ተነሳሽነታችንን መጨመር እንችላለን።\n\nበዚህ ምድር ላይ ልንለውጣቸው የምንችላቸው ነገሮች ላይ ማተኮር እና ከአቅማችን በላይ የሆኑትን መረዳትንም ይመክራሉ።\n\nበሕይወታችን የምናገኛቸው ስኬቶች ትንሽም ቢሆኑ ዋጋ መስጠት ያስፈልጋል። አዕምሮ ውስጥ የሚፈጠሩ አሉታዊ ድምጾችን በአወንታዊ ለመቀየርም ይረዳል።\n\nበየጊዜው አዳዲስ ነገር ማድረግን የሚመክሩት ደግሞ ጊዜን በአግባቡ የመጠቀም አማካሪዋ ኤልዛቤት ግሬስ ሳውደርስ ናት።\n\n\"እስኪ ሞክረው የማያውቁትን ምግብ ያብስሉ። በእግርዎ ይንሸራሸሩ። አዲስ ቋንቋ ይማሩ።\" ትላለች።\n\nየሚፈልጉትን ማወቅ\n\nበኒው ዮርክ ዩኒቨርስቲ የሥነ ልቦና መምህር ጋብርኤል ኦቲንገን እንደሚሉት፤ የሁሉም ነገር መጀመሪያ የሚፈልጉትን ማወቅ ነው። ከዚያም የሚፈልጉትን ነገር እንዳያገኙ የሚያግዱ መሰናክሎችን መለየት።\n\nአንድ ነገር ማድረግ ሲፈልጉ፤ ምን ውጤት አገኝበታለሁ? ብሎ በመጠየቅ ተግባርን ከውጤት ጋር ማስተሳሰርን ባለሙያዋ ይመክራሉ።\n\nለምሳሌ በቀን ለ30 ደቂቃ ለመሮጥ ቢወስኑ ለአካልዎ እንዲሁም ለአዕምሮዎ የሚያስገኘውን ጥቅም አብረው ማሰብ ይችላሉ።\n\n\"ስፓርት ከሠራሁ በኋላ ሰውነቴ ይፍታታል፣ ጤናማ እሆናለሁ፣ የተሻለ ቀን አስባለሁ ወዘተ ብለው ያስቡ\" ይላሉ የሥነ ልቦና መምህሯ።\n\nበማንኛውም ሁኔታ ውስጥ መሰናክሎች እንደሚገጥሙ ይጠበቃል። መፍትሔው ግን መሰናክል ፈርቶ መቆም ሳይሆን ችግሩን እንዴት ልለፈው? ወደሚል ስልት መሸጋገር ነው።\n\nየሥነ ልቦና ባለሙያዋ እንደሚሉት፤ \"አንድ ነገር ለማድረግ ሲወጥኑ ዝም ብሎ በምኞት ከመዋኘት ምን ችግር ሊገጥመኝ ይችላል ብሎ በብልሀት መጀመር ያዋጣል።\"\n\nከዚያም እቅድ አውጥቶ ወደ ተግባር መግባት።\n\nወዳጆች ማፍራት\n\nባለሙያዎች እንደሚሉት፤ ስንፍናን ለማስወገድ በሐሳብ ከእርስዎ ጋር ከሚመሳሰሉ ሰዎች ጋር ትስስር መፍጠር መልካም ነው።\n\nበብሪትሽ ኮሎምቢያ ዩኒቨርስቲ የሚያስተምረው ስቲቨን ቴይለር \"አንድ ነገር የግል ህልም ከሚሆን የጋራ ግብ ሲሆን ተነሳሽነትን ይጨምራል። የእኔ ከሚለው ስሜት ይልቅ የእኛ የሚለው ስሜት ይበልጣል\" ይላል።\n\nከሌሎች ጋር መደጋገፍ መሰናክልን በቀላሉ ለማለፍም ያግዛል።\n\nጥናቶች እንደሚያሳዩት ለራሳችን አንዳች ነገር ከማድረግ ይልቅ ለሰዎች ማድረግ ይቀለናል። ስለዚህም አንድን ተግባር ግላዊ ሳይሆን ማኅበራዊ ማድረግ ይመከራል።\n\nበእርግጥ በአንድ ጀንበር ስንፍናን ማስወገድ አይቻልም። ከዓመት ዓመት ተነሳሽነት ያለዎ ሰው ይሆናሉ ማለትም አይደለም።\n\nሆኖም ግን የሚፈልጉትን ማወቅና... ", "passage_id": "9f5ea99d0fdf339844790eda82a4e05c" }, { "passage": "አዲሱ ገረመውበቅርብም፣ በሩቅም (እነ ዲያስፖራ) ያላችሁ ወዳጆቼ እንዴት ሰነበታችሁ? ሠላም ነው! ሰበር ዜናው፣ ማለቴ ቅዝቃዜው እንዴት ይዟችኋል? የሚመች ነገር ቢኖርም ባይኖርም ይመቻችሁ! ስሙኝማ ይልቅ የሙያ ቅጥር የሚባለው ገበያው ሲቀዘቅዝ ለአቅመ ሹመት የደረሱት ገበያውን እየተቆጣጠሩት ነው አሉ። እውነት ይሆን እንዴ?ለነገሩ በዘመነ ኢህአዴግ ገበያው ይሄው ሆኖ ነው የቆየው። የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የተማረ ሰው እየተረሳ ነው፤ የሚሾመው ሌላ ሌላው ነው ሲባሉ ምን ብለው ነበር የመለሱት። የኢህአዴግን አላማ/አብዮታዊ ዴሞክራሲን ማለታቸው መሰለኝ/ እስከ አሳካ ድረስ የፈለገንን እንሾማለን ምን ትሆኑ አይነት ነገር ተናግረው ነበር።በዚህ አያያዝ እድገታችን ወደ ሦስት አሀዝ/ዲጂት/ ሊያሻቅብ ይችላል የሚል መላ ምት (መላ ለምን ይመታል ግን) ብናስቀምጥስ? “ወይ ጣሊያን!” አለች ምዕራብ ጀርመን! እንዲህ እንዲህ እያልን እንተንፍስ እንጂ። አንዱ ወዳጄ የሰሞኑን የአሜሪካውን አመጽና ሰልፍ አይቶ፣ እኛና አሜሪካ አንድ ነን፤ ሁለታችንም ዴሞክራት፤ ሁለታችንም ጋር የኑሮ ውድነት አለ፤ ሁለታችንም ጥጋብ አንወድም፤ ልዩነቱ እነሱ ተቸገርን ብለው በበላ አፋቸው በአደባባይ ሲጮሁ እኛ በአደባባይ ቀርቶ በባዶ ሆዳችን ተቸገርን ብለን ማሰብ አንችልም፤ አለኝ።እኔ ግን ተቃውሞዬን ገለጽኩለት። እኛ አገር አሁን ላይ እንኳን ጮሆ መናገር፣ ጮክ ብሎ መፃፍም ይቻላል አልኩታ። ለዚህ አይደል ታዲያ እኔስ ዳርዳር ማለቴ። እናላችሁ አገራችን በሹመት እምርታ አሳይታለች። ለዚህም በሹመት ቦታ መሙላት ምክንያት የባለሙያው መድረሻ ማጣትና እንግልት ምስክር ነው። ወዳጄ በቅርቡ ሥራ ስቀጠር በመጀመሪያው ወር ደመወዜ ማኪያቶ እጋብዛሃለሁ ያልከኝን አስታወስክ? ለካ እያሽሟጠጥክ ኖሯል? ግድ የለም ሹም ስትሆን ጋብዘኝ። ቅጥሩማ በየት በኩል። የስላቅ ሰፈሩ ወዳጄ የተጠበብክባት የማኪያቶ ግብዣ ስላቅ ግን ታስገርመኛለች እኮ። ሥራ ልትቀጠር ሄደህ ሹመት በሩን ዘጋብህ አይደል? እንግዲህ እኔ አልፈርድልህ፤ እርሱ አንድዬ ይመልከትህ እንጂ። ስሙን መጥቀስ የማልፈልገው አንድ የመንግስት ተቋም ሰሞኑን ሽርጉድ በዝቶበታል። ሹመት የሚያገኙ አዳዲስ ሰዎች መኖራቸውን ተከትሎ ራሳቸውን ከአመራር ተርታ የሚመድቡት ሲዶልቱ ነው የሚውሉት። ወሬው ሁሉ “እከሌ የት ቦታ ሊመደብ ይችላል?፤ እነ እከሌ እንኳን እነ እከሌ እያሉላቸው ምንም አይሆኑም” የሚል ሆኗል። ለዛሬው ይህችን አጭር መጣጥፍ ለመጻፍ መነሻ የሆነኝም ይኸው ነው። ሹመት በነፃ ገበያ ቢወዳደር ቅጥር ከሚያወጣው ዋጋ ያንስ ነበር። አንዳንዴ ተሿሚዎች ራሳቸውን ዝቅ አድርገው ከባለሙያዎች ጋር ለሥራ ቢወዳደሩ ሌላኛው ችግር በደንብ ይገባቸው ነበር እላለሁ። ተሿሚ ደመወዙ ስንት እንደሆነ የሚያውቀው በዓመት አስልቶ እንጂ በወር ባንክ ቤት ተሰልፎ አይደለም። የወንበር ከሚለው ጀምሮ የነዳጅ፣ የቤት፣ የስልክ፣ የጉዞ፣ የማትግያ ወዘተ ተብለው በተሿሚዎች ቋንቋ ብቻ የሚታወቁ ጥቅማ ጥቅሞች አስክረውት በየት በኩል ደመወዙን ይቁጠር። በዚህ ላይ በትንሽ በትልቁ ከከተማ የሚያስወጣ ስብሰባና የመሳሰለው አለ፤ አበል የሚታጨድበት። ከእርሱ እኩል ተምረው እኩል የስራ ልምድ ኖሯቸው እንደውም በልጠው የሚገኙ ሰዎች ደግሞ ይህ ሁሉ ለእነርሱ ህልም ነው።ምን ህልም ብቻ ቅዥትም ነው። በነገራችን ላይ ሹመት የሚሰጠው፤ በዋነኛነት ለትልልቆቹ አመራሮች ባለው ቀረቤታ ላይ ተመስርቶ ነው። ትልልቆቹ አመራሮች ከወደዱህ፤ አንተ ብትማር፤ በፖለቲካ ብትበስል ባትበስል፤ ችግር የለውም። ካንተ የሚጠበቀው ትልቁ መስፈርት የነሱ አሸርጋጅ መሆን ነው። በዚህ መልኩ፤ እጅግ ብዙ አመራር ወደ ስልጣን መጥቷል። ወደ ስልጣን የመጣ አሸርጋጅ ከብሯል። የቪላና ፎቅ ቤት ባለቤት ሆኗል። ቪ ኤይት መኪናን ሲያሻው በሾፌር አሊያም በራሱ እጅ እንደልቡ አሽከርከሯል። አሁን እንዲህ አይነት ሰዎች፤ የህዝብን አጀንዳ ወደ ጎን ትተው፤ ቀን ከሌት ስለ ራሳቸው ጉዳይ ቢጨነቁ ምኑ ይገርማል? ለዚህ እኮ ነው ሹመት ቅጥ ይኑረው የምለው። እንደዚህ አይነት ሰዎች፤ በሆነ አጋጣሚ እንኳን ከሀላፊነት ቢነሱ፤ ምርጥ የተባለ ቦታ ተፈልጎላቸው ይመደባሉ፤ ይህ ምርጥ ቦታ ከጠፋም፤ በህግ ያልታወቀ / በመስሪያ ቤቱ መዋቅር የስራ መደብ የሌለ/ የስራ መደብ ይፈጠርላቸዋል፤ በዚህም መሰረት ተዘፍዝፈውበት ከከረሙት ስልጣን በሆነ አጋጣሚ ቢነሱ እንኳን፤ ሰናይ ኑሯቸውን እንዲገፉ ይደረጋል። ይሄ አሰራር በተለይም ለእነዚያ 27 ዓመታት ሲተገበር የኖረ ነው። ይሄን ሁሉ የተበላሸ አካሄድ ደግሞ፤ ህዝብ አንጀቱ እያረረ በአንክሮ ሲከታተልና ሲታዘበው ከርሟል። በአሁኑ ወቅት ለህዝባችን የሚያስፈልገው የሿሚ አገልጋይ ሳይሆን በውድድር ወደ ሥልጣን የሚመጣ አገልጋይ ነው።በሹመት ርዕዮተ ዓለም የበላይነት እሳቤ የቱንም ያህል የተማርክ ብትሆን፤ በአመራርና በፖለቲካው ብትበስል፤ እውነት ብትናገር ወዘተ. አንተ ለታላላቆቹ አመራሮች፤ እስካልተመቸሃቸው ድረስ ዋጋ ቢስ ነህ። ስለሆነም ሰበብ ተፈልጎልህ ከሥራ እንድትሰናበት ሁሉ ልትደረግ ትችላለህ። ያኔ ልክ ለእነሱ አሸርጋጆች እንደሚደረገው ሁሉ፤ ላንተ ጥሩ ቦታ ተፈልጎልህ የምትመደብ እንዳይመስልህ፤ ይልቁንስ ለሲቪል ሰርቪስ ቢሮ፤ በሚመጥነው ቦታ መድቡት ተብሎ ደብዳቤ ይጻፍልሀል። ሂድ አትበለው እንዲሄድ አርገው አይነት ስራም ይፈጥርልሃል። የሲቪል ሰርቪስ አመራርም፤ ቀድሞ ስለሚነገረው፤ ከወደደህ፤ እንደ ምንም ቦታ ፈላልጎ፤ በሚመጥንህ ይመድብሀል፤ ከደበርከው ደግሞ፤ ቦታው ስለሌለኝ፤ አንድ ደረጃ ዝቅ ብለህ ተመደብ ይልሀል፤ አንተም ደሀ ነህና እየቆዘምክ ትቀበላታለህ። ይህ ብዙዎች የተማሩ ሰዎች የገጠማቸው እጣ ፈንታ ነው። ይሄንን ኢ-ፍትሀዊ አሰራርም እስከመቼ በትዝብት እንመልከተው?ከዚህ ቀደም ዩኒቨርሲቲዎች ብቃትን ሳይሆን ፖለቲካዊና ዘውጋዊ ማንነትን ባማከለ መልኩ በተሾሙ የገዥው ፓርቲ እንደራሴዎች እንዲመሩ ተፈርዶባቸው ነበር። የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ይሾሙ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። አሁን ላይ የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንት በተቋሙ ተልእኮና በዓለም አቀፍ መልካም ልምድ መሰረት፣ አካዳሚያዊ ነጻነት እንዲኖረው ተደርጎ ከሹመት ተኮር ይልቅ ውድድር ተኮር ሆኖ ተሻሽሏል። ይህ መልካም ጅማሮ በሌሎች የመንግስት ተቋማት ላይም ሊተገበር ይገባል። ይህ የዩኒቨርሲቲዎች ተሞክሮ እየተቀመረ ወደ ሌሎች ተቋማት መውረድ ይኖርበታል። ምህንድስናን የተማረ ሰው በውድድር ቢመራ መንገዶቻችን ባልጎረበጡን፤ ፖለቲካው በዘርፉ ትምህርት ባለው ቢመራ ኖሮ አገራችን በፖለቲካዊ ቀውስ አትናጥም ነበር። የኢኮኖሚውን ጉዳይ የሚመራ ባለሥልጣን በዘርፉ ተምሮና ተወዳድሮ ቢመራ የእድገት ዲጂቱም ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ይሆን ነበር። ሹመት የሚለው አሰራር ጎርበጥ ያደርጋል። እንደ ማህበረሰብ የሞራል ልዕልና ሰርቶ ጥሮ ግሮ በማግኘት የሚያምን ትውልድ መፍጠር ያስፈልጋል።ፖለቲካውን ማሳለጥ ከቻለ ከየትኛውም የህብረተሰብ ክፍል አምጥተን እንሾማለን የሚለው ኢህአዴጋዊ መርህ አላረመደምና ቀስ በቀስ ልክ እንደ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶቹ ስልጣን በውድድር የሚያዝበት ወቅት እንዲመጣ እንፈልጋለን። ", "passage_id": "14a4bb7b7f1b430d9c0164172f05c326" }, { "passage": "ባለፈው ሳምንት “ስማርት” ስለተባሉት የቢዝነስ መመሪያዎች ስንነጋገር፣ በአሁኑ ወቅት ሕይወትም ሆነ ቢዝነስ ያለእቅድና ግብ አይመራም ብለን ነበር። በዚህ ሳምንት ቀጣዩን ክፍል ነው የማቀርበው፡፡ ለሕይወታችንና ለቢዝነስ የምንቀርፃቸው ግቦች በሁለት ይከፈላሉ፡፡ አንደኛው ግብ በአብዛኛው ከአሁን ቀደም የሰራነውና የምናውቀው ስለሆነ 95 በመቶ ይሳካል ብለን የምንቀ  ርፀው ነው፡፡ ሌላኛው ደግሞ ቀደም ብለን በፍፁም ያልሞከርነውና የማናውቀው ስለሆነ ያለመሳካት ዕድሉ 95 በመቶ ሊሆን ይችላል፡፡ ግን ልንሰራውና ልንሞክረው እንፈልጋለን፡፡ ዝርዝር ውስጥ ባንገባም ሁለቱም የቢዝነስ ግቦች በራሳቸው መንገድ ጠቀሜታ አላቸው፡፡ የግብ ዕቅድ በማንኛውም መንገድ ሊዘጋጅና ሊፃፍ ይችላል፡፡ የዚህ ጽሑፍ መጠነኛ ትኩረት ግብ ቀረፃ ላይ ቢሆንም በአብዛኛው ግን፣ ግቡን በመፈፀም ሂደት ላይ የበለጠ ያተኩራል ይላሉ፤ ሚ/ር ስኮት ሃልፎርድ፣ በጁን በታተመው ኢንተርፐሪነር መጽሔት ላይ ባቀረቡት ዘገባ፡፡ ጸሐፊው በማከልም “የቀረፃችሁት ግብ በእርግጥ ጠቃሚ ሊሆን ይችላል፡፡ ነገር ግን ሊሳካ የሚችልባቸውን አንዳንድ ሁነኛ የስኬት ምክንያቶች ብትመርጡ እመርጣለሁ፡፡ ምክንያቱም ለዓላማና ግባችሁ ጠንካራና ጎበዝ መሆናችሁን ታዩበታላችሁ። የሰው ልጅ አዕምሮ፣ እርግጠኛ ሆነው ይሳካል ብለው ያመኑበትን ግብ ለማሳካት የተቃኘ ነው” ብለዋል፡፡ ስለዚህ በንግድ ሥራ ለመመንደግ ወይም ቢዝነሱን ወደ አዲስ ከፍታ ለማምጠቅ ከፈለጉ፣ ጸሐፊው ለከፍተኛ ስኬት ያበቃሉ ያሏቸውን ሰባት ነጥቦች እነሆ! የተነቃቃ ሕልም ለትልቅ ግብ - ቤት፣ መኪና፣ ትምህርት፣… ማለም ጥሩ ነው፡፡ ነገር ግን እርግጠኛ ሆነው ተግባራዊ የሚያደርጉት ከሆነ ለዚያ ሥራ የሚያተጋ (የሚነቃቃ) ነገር ያስፈልጋል፡፡ የመጀመሪያው ነገር፣ ሕልሙ ላይ ለመድረስ የሚያነሳሳ ምክንያትና ጥልቅ ፍላጎት ነው፡፡ ግብዎ ጋ የሚያደርሰው መንገድ አሰልቺ፣ ችግርና መሰናክሎች የተጋረጡበት ሊሆን ይችላል፡፡ ካሰቡበት ህልም እንዳይደርሱ የሚጋረጡ በርካታ አጋጣሚዎች (ችግሮች) ሊኖሩና ሊፈጠሩ ይችላሉ፡፡ በዚህ ጊዜ ሊረዳዎትና ሊያጠነክርዎት የሚችለው ግቡ ላይ ለመድረስ ያነሳሳዎትን ምክንያት ማሰብ ነው፡፡ የሚከወኑትን ነገር ለ24 ሰዓት ይከፍላሉ፡- ግብዎ ከክብደትዎ 10 ኪሎ መቀነስ ከሆነ አዕምሮዎ የሚያውቀው በ24 ሰዓት 10 ኪሎ መቀነስ ሳይሆን በወሰኑት ጊዜ ውስጥ 500 ግራም መቀነስዎን ነው፡፡ ስለዚህ፣ ግብዎን አዕምሮዎ እንዲረዳ አድርገው ይቅረፁ፡፡ ሕልምዎ ሀብታም መሆንና መኪና መግዛት ከሆነ፣ እንዴት አድርገውና በምን ያህል ጊዜ ውስጥ ሀብታም እንደሚሆኑ (በየወሩ እቁብ እየጣሉ፣ ንብረት ሸጠው፣ ውርስ ተካፍለው፣ ደሞዝ አጠራቅመውና ተጨማሪ ገቢ ፈጥረው፣… በአንድ፣ በሁለት፣ በአምስት ዓመት፣ …) ተብሎና ተዘርዝሮ መቀመጥ አለበት፡፡ በጊዜ የተከፋፈለችው ትንሿ ግብ፣ ምክንያታዊና ቀጣይነት ያላት መሆን አለባት፡፡ በየወሩ ከደሞዜ 1000 ብር እየቆጠብኩ በዓመት 12 ሺ ብር ይኖረኛል፡፡ በአምስት ዓመት ደግሞ 60 ሺ ይኖረኛል፡፡ ተጨማሪ ሥራ በመስራት በወር 10ሺ ብር፣ በዓመት 120 ሺ ብር፣ ከአምስት ዓመት በኋላ 600ሺ ብር፣… ተብሎ ግብ ከተበጀ፣ በምንም ዓይነት ምክንያት ከዕቅዱ መዛነፍ የለበትም ማለት ነው፡፡  በየቀኑ የሆነ ነገር ይሥሩ፡- ካሰቡት ግብ ላይ ለመድረስ፣ በየቀኑ ከሚያደርጉት የሥራ ድግግሞሽና ፍጥነት የበለጠ ምንም ዓይነት ነገር ወደ ግብዎ አያቀርብዎትም፡፡ ይህ ሲባል ግን ታምመው ቢተኙ እንኳ ከዕለታዊ ሥራዎ መቅረት የለብዎትም ማለት አይደለም፡፡ ከአቅም በላይ የሆነ ነገር ሲያጋጥም ወይም ሲደብርዎት ሊያቋርጡት ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ግብዎ ጋ ለመድረስ የመጀመሪያዎቹን 30 ቀናት በሚገባ ካልተጠቀሙና የአካሄድዎን ፍጥነት ካልለኩ 90 ከመቶ ግብዎን እንደማያሳኩ ማረጋገጫ ይሆናል፡፡ ስለዚህ፣ የመጀመሪያዎቹ 30 ቀናት ቁርጠኛ እንደሆኑ አዕምሮዎን ለማሳመን እጅግ ወሳኝ ናቸው፡፡ መቀየርና ማስተካከል (Adapt and Adjust)፡- ትልቁ ግብ ላይ ለመድረስ የሚችሉበትን ትንሿን የዕለት ተዕለት ግብ ሲተገብሩ፣ አመቺ ያልሆነ አስቸጋሪ ሁኔታ ሲያጋጥም፣ ሁኔታውን ማስተካከል ያስፈልጋል፡፡ የየዕለቱ ትንሿ ግብም በጣም ቀላል ከሆነች ጥሩ አይደለም። አተገባበሩ በጣም ቀላል ከሆነ የበለጠ ከበድ ያድርጉት፡፡ በአጠቃላይ፣ ወዳሰቡት ግብ ለመድረስ የሚደረገው ትግልና ጥረት ከባድ ከሆነ ደግሞ ቀለል ያድርጉት፡፡ የሰው አስተያየትና ሽልማት (Feedback and Reward)፡- የሰው ልጅ አዕምሮ፣ አዲስ ነገር ለመማርና አዲስ ባህርይና እውቀት ለመቅሰም ሁለት ነገሮች ያስፈልጉታል፡፡ አንደኛው አስተያየት (Feedback) ሲሆን፣ ሌላኛው ሽልማት (Reward) ነው፡፡ ግብዎን ለማሳካት ሲንቀሳቀሱ፣ የሌሎች አስተያየት ምን እንደሆነ ለመጠየቅ ድፍረት ይኑርዎት፡፡ “ይኼን ነገር እንዴት አየኸው? ምኑ መስተካከል አለበት ትላለህ/ትያለሽ?...” ብሎ መጠየቅ፣ ስህተትን አውቆ ለማስተካከል በጣም ጠቃሚ ነው፡፡ የሰዎች አስተያየት ጥሩ ከሆነና ወደ ግብዎ ለመድረስ ትክክለኛ መስመር ላይ ከሆኑ ጥሩ ነው፣ በየዕለቱ ትንሿን ግብዎን ያለስህተት ስላከናወኑ፣ እውቅና እንዲሆንዎ ራስዎን ይሸልሙ፡፡ ውጤታማ ሥራ ባከናወኑበት ቀን፣ ትንሽ ወርቃማ የኮከብ ምልክት የሚያደርጉበት ቀን መቁጠሪያ ቢኖርዎ ለበለጠ ለትጋት የማነሳሳት አቅም እንዳለው በጥናት ተረጋግጧል፡፡ ትክክለኛ ሥራ እያከናወኑ መሆኑን መገንዘብ ለአዕምሮ በቂ ሽልማቱ ነው፡፡  በትኩረት ያልሰሩበትን ጊዜ ይለዩ (Schedule Slop Time):- ላቀዱት ግብ ትኩረት ያልሰጡበትን ወይም ራስዎን ያታለሉበትን ወይም ጭራሽ ያልሰሩበትን ጊዜ መዝግበው ይያዙ፡፡ ምክንያቱም፣ ያንን የባከነ ጊዜ ተመልሰው ስለሚሰሩ፣ ለጊዜው ተግባርዎን ያለመወጣትዎ ሊያሳዝንዎትና ሊያሸማቅቅዎት አይገባም፡፡ ግን ልማድ እንዳይሆን በጣም ይጠንቀቁ፡፡ መሰልቸት እንዳለ ይወቁ፡- አንድን ነገር በየቀኑ ትንሽ ትንሽ መሥራት ሊያሰለች ይችላል። ቢሆንም ግን አያቋርጡ፡፡ ምክንያቱም፣ ያቀዱት ግብ ላይ መድረስ፣ በየቀኑ የደስታ ሻምፓኝ የመክፈት ሥነ-ሥርዓት ያህል ቀላል አይደለም፡፡ ብዙ ጊዜ በየቀኑ ጥቃቅን ነገሮች ላይ አጣብቆ የሚያውል አሰልቺ ነገር መሆኑ መታወቅ አለበት፡፡ ይህን ነገር ተገንዝቦ በየቀኑ ትንሽ ጠንከር አድርጎ ደጋግሞ መስራት ያስፈልጋል፡፡ ምክንያቱም ግባቸውን የሚያሳኩ ሰዎች፣ ነገሮች ከባድና አሰልቺ ሲሆኑባቸው ብዙ ጊዜ የሚያደርጉት እንደዚያ ነውና፡፡  ", "passage_id": "b30a265834bf6cde280981d8600a2bfc" }, { "passage": "መጨባበጥ ከሰው ልጅ ባሕል ጋር እንደተጨባበጠ እነሆ ስንት ዘመኑ!\n\nሰዎች አዲስ ሰው ሲተዋወቁ ይጨባበጣሉ፤ ከሚያውቁት ሰው ጋር ይጨባበጣሉ። ቢሊየነሮች የንግድ ሥምምነት ተፈጣጥመው ይጨባበጣሉ። አጫራች አሸናፊውን ተጫራች ማሸነፉን የሚያውጅለት እጁን በመጨበጥ ነው። መንግሥታት በጦርነት ከተቋሰሉ በኋላ \"ይቅር ለእግዜር\" የሚባባሉት በመጨባበጥ ነው።\n\nመጨባበጥ እንደ መተንፈስ ያለ ነው። ሕይወታችንን ተቆጣጥሮታል።\n\nእንኳንስ እኛ የአሜሪካ ፕሬዝዳንትም የነጩ ቤተ መንግሥት የግዛት ዘመኑን ሩብ የሚያጠፋው በመጨባበጥ ነው። \n\nአንድ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት በዓመት በአማካይ ስንት ሰው የሚጨብጥ ይመስልዎታል? 65 ሺህ ሰዎችን!\n\nታዲያ ከመጨባበጥ ጋር በቀላሉ የምንፋታ ይመስልዎታል?\n\nለመሆኑ ማን ጀመረው?\n\nእንዴት ይታወቃል ይሄ? አይታወቅም። ኾኖም መላምቶች አሉ። \n\nጥንታዊ ግሪኮች መሣሪያ ይሸከሙ ስለነበር አንዱ ሌላውን ለማጥቃት እንዳልመጣ ለማሳየት ይጨባበጡ ነበር። \n\nአውሮፓዊያንም ጀምረውት ይሆናል። ድሮ በመካከለኛው ዘመን በነፍስ የሚፈላለጉ የመሳፍንትና የመኳንንት ቤተሰቦች እርስ በርስ የሚጨባበጡበት ዋናው ምክንያት አንዱ ሌላውን ሊጎዳ የሚችል መሣሪያ እንዳልታጠቀ እጁን በማርገፍገፍ ለማጣራት ነበር።\n\nመጨባበጥን እንደ የኮይኮር ክርስቲያኖች ያስፋፋው ግን የለም። ኮይኮሮች በ17ኛው ክፍለ ዘመን የነበሩ የክርስቲያን ወንድማችነት ማኅበር አባላት ናቸው። ማንኛውም መልክ ያለው ጦርነትን ይጸየፋሉ።\n\nእነርሱ በሰው ልጆች እኩልነት ከማመናቸው ጋር ተያይዞ ይሆናል ከማጎንበስ ይልቅ መጨባበጥ እኩልነትን ይገልጣል ብለው ያስባሉ። እንዲያ በማመናቸው ነው ሰመል መጨባበጥን አጠናክረው ገፉበት። \n\nክርስቲን ላጋር በቴክሳስ ኦስተን ዩኒቨርስቲ የሥነ ልቡና ሳይንስ ፕሮፌሰር ናት።\n\nመጨባበጥ የሰው ልጆች ትሁትነት የሚገለጥበት፤ ልብ ለልብ መናበባቸውን በጥቂቱም ቢሆን የሚንጸባረቅበት ጥበብ ነው። \n\n\"የሰው ልጅ በጊዜ ርዝማኔ እንዴት ማኅበራዊ ፍጡር እየሆነ እንደመጣም ማሳያ ነው\" ትላለች ፕሮፌሰር ክሪስቲን። በተለይም ሰው በንክኪ ራሱን የሚገልጽ እንሰሳ ስለመሆኑም ሌላ ማረጋገጫ ነው።\n\nመጨባበጥ የብዙ ዓለም ጥግ ረቂቅ ቋንቋ ነው። ለዚያም ነው አቁሙት ስንባል ግራ የገባን። ለዚያም ነው በእግር ተጨባበጡ ሲባል ፌዝ የሆነብን። ለዚያም ነው መሪዎች ስንት ጊዜ መመሪያ እየረሱ ሲጨባበጡ የነበረው። ለዚያም ነው በክርን ተጨባበጡ ሲባል \"እረ ወዲያ!\" ያልነው።\n\nፕሮፌሰር ላጋር እንደምትለው \"መጨባበጥ ብቻም ሳይሆን መነካካት ጠንካራው የስሜታችን ቋንቋ ነው፤ ልናጣው አንፈልግም።\"\n\nበሳይንስ እኛን ይቀርባሉ የሚባሉት \"አጎቶቻችን\" እነ ቺምፓዚም ከእኛ የባሱ ናቸው። እጅግ ይተቃቀፋሉ። ሰላምታ ሲሰጣጡ አጠገባቸው ያለውን ዛፍም ቢሆን ያቅፉታል እንጂ የእግዜር ሰላምታን ቸል አይሉም። አንዳንዴ ከመተቃቀፍም አልፈው ይሳሳማሉ። \n\nበ1960ዎቹ ምርምሩን ይፋ ያደረገው አሜሪካዊው የሥነ ልቦና ሳይንስ ሊቅ ሃሪ ሀርሎ የዝንጀሮ ልጆች ለዕድገታቸው እጅግ አስፈላጊ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ መነካት አንደሆነ ደርሶበታል። መተሻሸት፣ መታቀፍ። \n\nቀጭኔዎችም እንደኛው ናቸው። ሁለት ሜትር በሚረዝመው መቃ አንገታቸው አንዱ የአንደኛውን አንገት ይጨብጣል።\n\nመጨባበጥን ለምን አንተካውም?\n\nይሄ መጨባበጥ የሚሉት ነገር ምንም ያህል ወሳኝ የስሜት መግለጫችን ቢሆንም አማራጭ አልባ አይደለም። \n\nለምሳሌ ሁለት መዳፎቻችንን በማገናኘት እጃችንን ከደረታችን አስደግፈን ከወገብ ሸብረክ ብንልስ? ደስ አይልም? ሕንዶች \"ናመስቴ\" ይሉታል።\n\nወይም ደግሞ እንደ ሳሞአ ደሴት ነዋሪዎች በዓይን ጥቅሻ ሰላም ብንባባልስ? እነዚህ ከአውስትራሊያ ማዶ በትንሽ ደሴት የሚኖሩ ሕዝቦች... ", "passage_id": "0b5461fbdb15a47076f44024d576c6fc" } ]
1dc366a9969be64642dd9a02872e5b34
f5fd5f8429954acd23718946efefed41
ደንበኞች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ያልተጠቀምንበትን የታሪፍ ክፍያ እያስከፈላቸው መሆኑን አመለከቱ
– አገልግሎቱ በደንበኞች የሚቀርቡ ማናቸውንም ቅሬታዎች ለመፍታት ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ በጋዜጣው ሪፖርተሮች አዲስ አበባ፡- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ያልተጠቀሙበትን የኤሌክትሪክ አገልግሎት እያስከፈላቸው መሆኑን የአዲስ አበባ ነዋሪዎች አመለከቱ። አገልግሎቱ በበኩሉ በደንበኞች የሚቀ ርቡ ማናቸውንም ቅሬታዎች ለመፍታት ዝግጁ መሆ ኑን አስታወቀ። የጋዜጣው ሪፖርተር በሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን ቁጥር ሁለት አገልግሎት መስጫ ማዕከል ያነጋገራቸው የአገልግሎቱ ደንበኛ ምንተስኖት ፍሬው፣ “ቤቴ የንግድ አይደለም፤ ነገር ግን በየወሩ የምከፍለው ከአንድ ሺህ ብር በላይ ነው።አሁን ደግሞ እጥፍ ጨምሮ መጥቷል። ይህ ሁሉ ያልተጠቀምኩበት ነው። ሰሞኑን ብመላለስም ደረሰኝ አልመጣም እያሉ ከሥራዬ እያስተጓጎሉኝ ነው።ችግራችንን ለመናገር የሚሰማን ሰው የለም።በተከታታይ አራት ቀን መጥቼ መፍትሔ አላገኘሁም፤ መስተንግዶው ደካማ ነው።መንግሥት ይህንን ተቋም እታች ድረስ ወርዶ መቆጣጠር አለበት።ክፈል ከተባልክ መክፈል ነው፤ ከዚህ ውጪ ሰሚ የለም” ሲሉ ምሬታቸውን ያስረዳሉ።ከዚህ በፊት አምስት ሺህ ብር ቆጠረ ተብዬ ዋናው መስሪያ ቤት ስሄድ አምስት ሺ ብሩ ስህተት ነው የቆጠረው ሰባት ሺህ ብር ነው ተብዬ ከስድስት ሺህ ብር በላይ ከፍያለሁ። በየወሩ አስር አስር ብር ሲቆጥር ሄጄ ሳመለክት ቀደም ሲል ከዚህ እላፊ ከፍለህ ስለሆነ አሁን የቆጣሪ ግብር ብቻ ነው የምትከፍለው ተባልኩ።መጨረሻ ላይ ግን ውዝፍ ክፍል አሉኝ።ከዚያ በኋላ የምከፍለው ብር በጣም ያማርራል ይላሉ።ይመርመርለኝ ስል ብር ክፈል ተብዬ ከፈልኩ፤ ከዚያ ብመላለስ ብመላለስ መፍትሔ በማጣቴ ተውኩት።እንደገና ቆጣሪ ይቀየርልኝ ብዬ ሳመለክት ከቀበሌ አጽፍ ተባልኩ፤ አጽፌ ስሄድ ከነጭራሹ ያንተ ፋይል የለም ብለው አናስተናድህም አሉኝ፤ የምሄድበት አካል አጥቼ ተቸግሬ ነው ያለሁት ብለዋል። በዚያው ጣቢያ ሌላኛው ቅሬታ አቅራቢ ሃምሳ አለቃ መስፍን ተሾመ ፣የችግሩን አሳሳቢነት እንዲህ ሲሉ ይገልጻሉ፤ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚተዳደርበት ህግ ያላቸው አይመስለኝም።ጠይቀን የሚያስረዳንም አካል የለም።መቁጠሩ ብቻ ሳይሆን አለመተላለፉ ሌላኛው ችግር ነው።ተሯሩጠን እያደርን ጊዜያችን ያለ አግባብ እየባከነ ነው።ቆጣሪው ቆጥሮ ወደ ሲስተም አልተላለፈም በማለት በራሳቸው ችግር ምክንያት መጥተው አገልግሎት እንዳናገኝ እና የተለያዩ ቅጣቶችን ይጥሉብናል ብለዋል። ለመንግሥት ብር ለመክፈል ለምነን መሆን የለበትም፤ መጥተው በትክክል አንብበው ተገቢውን ክፍያ ሊጥሉብን ይገባል። ቀድም ሲል ሁለት መቶ ብር ይቆጥር ነበር፤ አሁን ምክንያቱን ሳናውቀው በዕጥፍ እንድንከፍል ተደርገናል።የተከሉትን ቆጣሪ በትክክል አይቆጣጠሩትም፤ አያነቡትም ሲሉ ቅሬታቸውን ይገልጻሉ።ላለፉት ሁለትና ሦስት ወር አልተነበበልኝም የሚሉት ስማቸው እንዲጠቀስ ፍቃደኛ ያልሆኑ ቅሬታ አቅራቢው ሳምንቱን ሙሉ ሥራ ፈትቼ ብመላለስም ቅሬታዬን መርምሮ መልስ የሚሰጠኝ አካል አላገኘሁም ብለዋል።በየወሩ የሚቆጥረው እየጨመረ ነው፤ ነገር ግን ለማን ማመልከት እንዳለብን ጠፍቶኝ በግራ መጋባት ውስጥ ነኝ።ከሥራ ገበታችን እየተስተጓጎልን ተሰልፈን ብንውልም ምክንያት ፈጥረው ሳንስተናገድ እንባረራለን። መንግሥት መፍትሔ ካልፈለገልን ችግሩ አሳሳቢ ከመሆኑም በላይ ሳንጠቀም በግዴታ እንድንከፍል እየተደረግን ሲሉም ምሬታቸውን ገልጸዋል፡፡ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡን የኢትዮጵያ ኤሌከትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ እንዳሉት ተቋሙ ከ2011 ዓ.ም ታህሳስ ጀምሮ ለተከታታይ አራት ዓመት የሚቆይ የታሪፍ ማስተካከያ እያደረገ ሲሆን፤ በቅርቡም በታህሳስ ወር ሦስተኛውን ዙር ማስተካከያ አድርጓል።ይህ ደግሞ አገልግሎቱን ለማሻሻል ወሳኝ ነው። አገልግሎቱ አሁንም ቢሆን የሚያስከፍለው ታሪፍ ከሌሎች አገራት ጋር ሲነፃፀር በጣም አነስተኛ ነው ያሉት አቶ ሽፈራው፤ ለአብነትም ይህንን ማስተካከያ ስናደርግ አንድ ኪሎ ዋት ሃወር ኤሌክትሪክ የመሸጫ ዋጋ 1ነጥብ 8 የኤሪካ ሳንቲም እንደነበርና በወቅቱ ግን ኬንያ ለአንድ ኪሎ ዋት ሃወር 15 ሳንቲም ታስከፍል እንደነበር ጠቅሰዋል፡፡በሌላ በኩል አገልግሎቱ ታሪፍ ማሻሻያ እያደረገ ቢሆንም የአገልግሎት ማሻሻያ ሥራዎች ገና ብዙ ሥራ እንደሚቀራቸው የጠቀሱት አቶ ሽፈራው ሆኖም የአገልግሎት ጥራት ለማምጣት እየተሠራ ነው ብለዋል።ለዚህም በዘንድሮ በጀት ዓመት ለጥገናና ለአቅም ማሻሻያ አንድ ቢሊየን ብር የሚጠጋ በጀት ተመድቦ እየተሠራ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡በሌላ በኩል አንዳንድ ደንበኞች የማይገባ ክፍያ መጠየቃቸው ትክክል አለመሆኑን አቶ ሽፈራው ጠቁመው፤ የይጣራልኝ ጥያቄ ሲያቀርቡም በቅድሚያ ክፈሉ የሚል አሠራር አለመኖሩን ተናግረዋል።ነገር ግን እንዲህ የሚያደርጉ ካሉ ተቋሙ ለማስተካከል ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አቶ ሽፈራው እንደጠቆሙት ቆጣሪ በየወሩ መነበብና በዚያ መሰረት ክፍያ መፈፀም አለበት።ይህ ካልሆነ ግን ደንበኞች በየደረጃው ቅሬታቸውን ማቅረብ አለባቸው።ከዚህ ውጪ ግን የተጠራቀመ ሂሳብ እንዲክፈሉ ማድረግ ትክክል ባለመሆኑ እንዲህ ዓይነት ችግሮች ካሉ መታረም አለባቸው ብለዋል፡፡ተቋሙ ከደንበኞች ለሚነሱ ማናቸውም ቅሬታዎች በየደረጃው ተገቢውን ምላሽ ለመስጠትና ችግሮች ካሉ ለመፍታት ዝግጁ ነው ያሉት አቶ ሽፈራው ለዚህም ህብረተሰቡ ህጋዊ አሠራርን ተከትሎ ለሚያጋጥሙ ችግሮች እስከ ማዕከል ድረስ ቅሬታውን ማቅረብ እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡ አዲስ ዘመን ጥር 5 ቀን 2013  ዓ.ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=39377
[ { "passage": "የዜግነት ጉዳዮች መምርያ ክፍያ የዘገየው በአዲሱ አደረጃጀት ምክንያት ነው ብሏልበፀጥታና በደኅንነት ሥራዎች የተመደቡ ሠራተኞች ሰሞኑን በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ላይ በሙስና ምክንያት በሚካሄደው ማጣራት ሳቢያ፣ ወርኃዊ የደመወዝ ክፍያ እንደዘገየባቸው በመግለጽ ቅሬታቸውን አሰሙ፡፡ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የፀጥታ ሠራተኞች እንደገለጹት፣ በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ሥር በሚገኙ ልዩ ልዩ ክፍሎች ተመድበው በኤርፖርትና በሌሎችም ተቋማት ውስጥ በጥበቃ ሥራ ላይ ቢሆኑም፣ ከተለመደው የክፍያ ጊዜ ከአራት ቀናት በላይ ደመወዝ ዘግይቶባቸዋል፡፡ የክፍያው መዘግየት አግባብ አለመሆኑ ብቻም ሳይሆን፣ እስኪጣራ በሚል ሰበብ ደመወዛቸው ሳይከፈል ለሳምንት ያህል  መዘግየቱን ሠራተኞቹ አልተቀበሉትም፡፡ ጉዳዩን በተመለከተ ሪፖርተር በስልክ አነጋግሮአቸው ምላሽ የሰጡት የኢሚግሬሽንና የዜግነት ጉዳዮች መምርያ ምክትል ዳይሬክተር አቶ መንግሥቱ አልማ፣ የደመወዝ መዘግየቱ በሠራተኞቹ እንደተጠቀሰው ከወቅቱ ዕርምጃ ጋር አይገናኝም፡፡ ይልቁንም ግፋ ቢል ለሦስት ቀናት መዘግየት የታየው በመሥሪያ ቤቶች ውስጥ በሚደረገው የተቋማት ማዘዋወር ሒደት ሳቢያ ነው ብለዋል፡፡ ቀደም ሲል የጥበቃ መምርያን ጨምሮ የዜግነትና የኢሚግሬሽን ጉዳዮችን የሚከታተለው ተቋም ተጠሪነቱ ለብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ነበር፡፡ በአዲሱ የተቋማት አወቃቀር ግን የዜግነትና የኢሚግሬሽን መምርያ የፌዴራል ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲን ተቀላቅሏል፡፡ በተቋማቱ መካከል መከናወን የሚገባቸው የኦዲትና የሒሳብ ማወራረድ ሥራዎች የደመወዝ ክፍያውንና የተወሰነ የፔቲ ካሽና የመጠባበቂያ ክፍያን ለጥቂት ቀናት ቢያዘገዩትም፣ መላውን ሠራተኛ ያካተተ የደመወዝ መዘግየት እንዳልተፈጠረ አቶ መንግሥቱ ገልጸዋል፡፡ የመጀመርያው ሩብ ዓመት የበጀት ኦዲት እየተካሄደ እንደሚገኝ ጠቁመው፣ በአብዛኛው የደመወዝ መክፈያ ጊዜም በወሩ መጨረሻ ቀናት ከ24 እስከ 25 ባሉት ውስጥ እንደሚፈጸም አስረድተዋል፡፡ ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዋናው መሥሪያ ቤት ሠራተኞች ለመረዳት እንደተቻለው፣ የደመወዝ ክፍያ ቀደም ሲል ዘግይቶባቸው እንደማያውቅና በአብዛኛውም ወር በገባ ከ23ኛው ቀን ጀምሮ ክፍያ እንደሚፈጸምላቸው ነው፡፡ ከሁለት ወራት ወዲህም ክፍያቸው በባንክ በኩል እየተፈጸመ እንደሚገኝም አስረድተዋል፡፡", "passage_id": "f99762bf0a119deb65ba145ddf68d00b" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- አፍሪ ኸልዝ የቴሌቪዥን ጣቢያ መብታቸውን በመጠየቃቸው ደመወዝ እንደከለከላቸው የተቋሙ ሠራተኞች ቅሬታቸውን ገለጹ፡፡በአፍሪ ኸልዝ የቴሌቪዥን ጣቢያ የካሜራ ክፍል ኃላፊ አቶ ሀብታሙ በየነ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጸው፤ እርሱን ጨምሮ ሰባትየሥራ ባልደረቦቹ ደመወዝ ሳይከፈላቸው ሁለት ወራት ከሰባት ቀን አሳልፈዋል፡፡ ከዓመት በላይ በድርጅቱ በቆየባቸው ጊዜያትም ደመወዝ በወቅቱ ተከፍሏቸው እንደማያውቅ ጠቅሶ፤ የሰኔ ወር ደመወዝ ሳይከፍላቸው የሐምሌ ወር መውሰጃ ጊዜ በመድረሱ ሠራተኞችን ለከፍተኛ ቅሬታ መዳረጋቸውን፣ ሁኔታው ግራ ያጋባቸው ሠራተኞችም ልመና በተሞላበት ሁኔታ ተደጋጋሚ ቅሬታ ቢያቀርቡም ደመወዛቸው ሊከፈላቸው እንዳልቻለ አስረድቷል፡፡ከዚህ\nቀደምም መሰል ችግሮች ሲያጋጥሙ ፊርማ እያሰባሰቡ ይጠይቁ እንደነበርና መብታቸውን በመጠየቃቸው ብቻ የተባረሩ ሠራኞች እንደነበሩ አቶ ሀብታሙ አስታውሶ፤ ተቋሙ ሥራውን በጀመረበት አካባቢ በነበሩ መዘግየቶች ዋና ሥራ አስኪያጇ ገንዘብ አጥሯቸው በመዘግየቱ ይቅርታ ይጠይቋቸው የነበር ቢሆንም በሰኔ ወር ላይ በተፈጠረው መዘግየት ቤተሠብ አስተዳዳሪ እንደሆኑና ችግር ላይ እንደወደቁ ለተቋሙ ቢያሳውቁም ምንም ምላሽ ሊያገኙ እንዳልቻሉ፣ ከሠራተኞች መካከል ከቤት አከራዮቻቸው ቤት እንዲለቁ የተነገራቸው እንዳሉም ቅሬታ አቅራቢዎቹ ጠቁመዋል፡፡ዋና\nሥራ አስኪያጇ ቅሬታዎች ሲበረቱና ጉዳዩ ለሕዝብ ጆሮ ሲደርስ የሰኔ ወርን ከሐምሌ ወር ጋር አንድ ላይ ለመክፈል ከገንዘብ ከፋይ ጋር በመቀመጥ ቅሬታውን ለመገናኛ ብዙሃን ለማድረስ የሄደና ያልሄደውን በመለየት ላልሄዱት ሲከፍሉ፤ መገናኛ ብዙሃን ዘንድ መሄዳቸውን ያመኑ ሰባት ሠራተኞች ከደመወዛቸው የአምስት ቀናት ተቆርጦ እንደሚሰጣቸው እንደገለፁላቸው አስረድተዋል፡፡ ቅሬታ\nአቅራቢዎቹ ሁኔታው ንዴት ፈጥሮባቸው ደመወዛቸውን ላለመቀበል ወስነው ከሄዱ በኋላ ካለባቸው ችግር አንፃር የአምስት ቀናቱ ተቆርጦ እንዲሰጣቸው ዳግም ቢጠይቁም ልዩ ልዩ ምክንያቶችን በመደርደር የሁለት ወራት ደመወዝ ሳይከፈላቸው ሰባት ቀናት እንዳለፋቸው ገልጸው፤ አሁንም ሥራቸውን እየሠሩ እንዳሉ፣ ቤተሠቦቻቸውም ለችግር መጋለጣቸውን ተናግረዋል፡፡በአፍሪ ኸልዝ ቴሌቪዥን ጣቢያ የሕግ አማካሪና ጠበቃ አቶ ሞገስ ናደው፤ የደመወዝ መዘግየት አጋጥሞ እንደነበር አምነው መዘግየቱ እንደ ማንኛውም በአገሪቱ እንዳሉ ድርጅቶች ሊያጋጥም ይችላል፡፡ ሠራተኞቹ ቅሬታቸውን በማቅረባቸው በተቻለ አቅም ክፍያው እንዲፈፀም ተደርጓል፡፡ አቤቱታ አቅራቢዎቹ ሁሉም ሠራተኛ ላይ ቅሬታ እንዳለ አስመስለው የሚያቀርቡት ትክክል አይደለም በማለት አስተባብለዋል፡፡አቶ\nሞገስ ፤ የዘገየው የሰኔ ወር ደመወዝ ሲሆን፤ ከሐምሌ ወር ጋር እንዲከፈል ተደርጓል፡፡ ተቋሙ ተሯሩጦ ክፍያውን በ30 ቀናት ውስጥ ከከፈለ ይህን ያክል አደጋ ተደርጎ ሊወሰድ አይገባም፡፡ በአሰሪና ሠራተኛ አዋጅ 377/96 መሠረት ደመወዝ የሚከፈለው ለተሠራ ሥራ ብቻ እንደሆነ አንቀጽ 54 ንዑስ ቁጥር 1 ይደነግጋል፡፡ ዘግይቷል፤ መዘግየቱ ግን ድርጅቱ ባጋጠመው የገንዘብ ችግር ምክንያት ነው፡፡ ሥም ለማጥፋት ካልተፈለገ በስተቀር አንድ ወር ደመወዝ በመዘግየቱ በዚህ ደረጃ መቅረቡ ትክክል አይደለም ብለዋል፡፡ተቋሙ\nከ50 በላይ ሠራተኞች ያሉት ሲሆን፤ ደመወዝ በመዘግየቱ ምክንያት ሰባቱ ሠራተኞች የሥራ ገበታቸው ላይ አልተገኙም፡፡ የቅርብ የሥራ ክፍል ኃላፊም ለአምስት ተከታታይ የሥራ ቀናት እንዳልተገኙ አቅርቧል፡፡ ማሕደራቸው ሲታይም የጎላ ችግር ስላልነበረባቸውና ደመወዝ ዘግይቶ ስለተሰጣቸው ምንም እንኳ ጥፋታቸው የሥራ ውል እስከማቋረጥ የሚያደርስ ቢሆንም ለአምስት ቀናት በመቅረታቸው ያልሠሩበት ሊከፈላቸው ስለማይገባ ተመላሽ ይደረግ በሚል መወሰኑን ጠበቃው አስረድተው፤ መፍትሄ የሚሆነውም ሥራቸውን አክብረው በመገኘት ቅሬታ ሲያቀርቡ ተቋሙ ችግሩን ተመልክቶ ተገቢው ውሳኔ ለማስተላለፍ ዝግጁ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ጠበቃ፣ የሕግ አማካሪና መምህር አቶ ዳኛቸው መኮንን ሲያብራሩ፤ አሠሪው በወቅቱ ደመወዝ የመክፈል ግዴታ አለበት፡፡ ከደመወዝ ጋር የተያያዙ ነገር ግን እንደ ደመወዝ የማይቆጠሩ ሌሎች ክፍያዎችም በውላቸው መሠረት አብረው መከፈል ይኖርባቸዋል፡፡ ሠራተኛው በቀን የሚያገኘው አማካኝ ደመወዝ በውል ስምምነቱ መሠረት የተወሰነ ሆኖ በአገሪቱ መነሻ ወለል አልተቀመጠም፡፡ በቀጣሪና በተቀጣሪ ስምምነት መሠረት በቀን የሚከፈለው አማካኝ ደመወዝ በሣምንት አልያም በወር ተሰልቶ በወቅቱ ሊከፈል ይገባል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የውሎ፣ የትርፍ ሰዓት፣ የበረሃና የመጓጓዣ ክፍያዎችና ሌሎች እንደየ መሥሪያ ቤቱ የሚከፈሉ ሁሉ በደመወዝ መክፈያ ቀን ሊከፈሉ ይገባል፡፡በስምምነታቸው መሠረት መከፈል በሚገባው ቀን ክፍያ ካልተፈፀመ አሠሪው ግዴታውን አልተወጣም ማለት ነው፡፡ አሠሪው ግዴታውን ሳይወጣ ሲቀርም በሕግ ተገድዶ ደመወዛቸውንና ወጪያቸውንም አስልቶ በክርክሩ ሒደት ደመወዝ መከፈል ከቆመበት እስከሚወሰንበት ድረስ ያለው ጊዜ ወለድ ታስቦ እንዲከፍል ይደረጋል፡፡ የሥራ ውሉ ሳይቋረጥ ከሆነ ደመወዝ እንዲከፍልና በዚህ ምክንያት የተጉላሉበት ነገር ካለ ተካክሶ እንዲከፈል ይደረጋል፡፡ ከዕዳዎች ሁሉ በቅድሚያ መከፈል ያለበት የሠራተኛ ደመወዝ መሆን እንደሚጠበቅበትም አቶ ዳኛቸው አሳውቀዋል፡፡በኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ገብረጊዮርጊስ ኣብርሃ እንደሚናገሩት፤ በአገሪቱ የተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ሲቋቋሙ ብሮድካስቱ ጥልቅ ክትትል ያደርጋል፡፡ ክትትሉም ድጋፍን መሠረት ያደረገ ሲሆን፤ መገናኛ ብዙሃኑ ሲቋቋሙ ማሟላት ያለባቸው አስፈላጊ ግብዓቶች ይታያሉ፡፡ በሒደትም መጀመሪያ ባስገቡት የፕሮጀክት ጥናት መሠረት ስለማንቀሳቀሳቸው ቁጥጥርና ክትትል ይደረጋል፡፡ ወደ ተግባር ከገቡ በኋላም ያሏቸውን መርሃ ግብሮች የሚያሻሽሉ ከሆነ በየጊዜው ይፈተሻል፡፡ የኤዲቶሪያል ለውጥ ካደረጉም ለባለሥልጣኑ ያሳውቃሉ፡፡ በዚህ መሠረትም ክትትል ይደረጋል፡፡ ነገር ግን መገናኛ ብዙሃኑ ከሰራተኞቻቸው ጋር የሚኖራቸውን ግንኙነት አስመልክቶ ለባለሥልጣኑ የቀረበ ቅሬታ የለም፡፡ ተቋማቱ በየራሳቸው መተዳደሪያ ደንብ የመምራት መብታቸው የተጠበቀ በመሆኑ አለመግባባቶች ሲፈጠሩ የማየት ሥልጣን የለውም፡፡አዲስ  ዘመን ነሃሴ 8/2011ፍዮሪ ተወልደ", "passage_id": "4d3627b6eeb99808a4eacbe7e6416614" }, { "passage": "የቦሌ ክፍለ ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጸ/ቤት  የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ቅሬታ እንዳላቸው ተገልጋዮች ለዋልታ ቴሌቪዥን ገልጸዋል፡፡እንደ ተገልጋዮች ገለጻ  በጽህፈት ቤቱ ከተገልጋዮች ጋር ፊትለፊት የሚገናኙት ባለሙያዎች ከፍተኛ የሆነ የስነ-ምግባር ችግር ይስተዋልባቸዋል ብለዋል፡፡በዚህም ጽ/ቤቱ ለተገልጋይ የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመሥጠት መቸገሩን ነው ተገልጋዮቹ የገለጹት፡፡በተጨማሪም የተገልጋዮች ፋይል በአግባቡ ስለማይያዝ በተለያዩ አጋጣሚዎች ፋይላቸው እንደሚጠፋም ጠቁመዋል፡፡ጽ/ቤቱ በበኩሉ ችግሩ እንደነበር አምኖ ባለፉት ሶስት ወራት ባለአንድ ገጽ የእቅድ ሰሌዳ በማዘጋጀት ችግሩን ለመቅረፍ እየሠራ መሆኑን ጠቅሷል፡፡በዚህም መሠረት የዲሲፒሊን ችግር የታየባቸውን 18 ሠራተኞች ከስራ ያሰናበተ ሲሆን 100 በላይ ለሚሆኑት ደግሞ ማስጠንቀቂያ ሠጥቷል፡፡የቦሌ ክፍለ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ እንዳለ ኮርንሳ እንደገለጹት በክፍለ ከተማው ከ58 ሺህ በላይ ግብር ከፋዮች የሚገኙ በመሆኑ ጫናው ተፈጥሯል፡፡በመሆኑም ጫናውን ለመቀነስ ይቻል ዘንድ የአገልግሎት አሠጣጡን ለማስፋት ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡", "passage_id": "219fabddd3b7bbea03bdd1ca6c850f5a" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 2፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አዲስ የድህረ አገልግሎት ክፍያ ስርዓት ሊዘረጋ መሆኑን አስታወቀ።አገልግሎቱ ከደንበኞቹ የሚሰበስበውን ወርሃዊ የፍጆታ ሂሳብ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኩል ለማድረግ ዝግጅቱን አጠናቋል።አዲሱ ስርዓት አሰራርን ከማዘመን በተጨማሪ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል ታልሞ መዘጋጀቱም ነው የተገለፀው።ተቋሙ በቅርብ ተግባራዊ ያደረገውን የኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒንግ የአሰራር ስርዓት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲስተም ጋር በማስተሳሰር የኤሌክትሪክ ፍጆታ ክፍያውን ከ1 ሺህ 585 በላይ በሚሆነው የባንኩ ቅርንጫፎች መክፈል የሚያስችል አምስት አማራጮችን ዘርግቷል።እነሱም በንግድ ባንክ ቅርንጫፍ በአካል በመሄድ የሚፈፀም የጥሬ ገንዘብ ክፍያ፣ ከቀጥታ ሂሳብ ተቀናሽ ተደርጎ የሚፈፀም ክፍያ፣ በእጅ ስልክ አማካኝነት እና በኢንተርኔት እና ሞባይል ባንኪንግ የሚከፈሉ ናቸው።ከሚቀጥለው ሳምንት ረቡዕ ጀምሮም ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ነው የተባለው።በለይኩን ዓለም", "passage_id": "465a20a490a4f76c9430df7f0e9a26fc" }, { "passage": "ሰሞኑን በአዲስ አበባ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደንበኞች በኤቲኤም ማሽን ገንዘብ ማውጣት ባለመቻላቸው፣ በአጭር የመልዕክት ጽሑፍ ገንዘብ ማውጣታቸውን በሚገልጸው መልዕክት ከፍተኛ መደናገጥ እየተፈጠረባቸው ነው፡፡ ባንኩ በበኩሉ በጊዜያዊ ገንዘብ ዝውውር የኔትወርክ ችግር ያጋጠመ ቢሆንም፣ የገንዘብ ኪሳራ እንደማይገጥማቸው ገልጿል፡፡በከተማዋ የተለያዩ የባንኩ ቅርንጫፎችና በንግድ ተቋማት አካባቢ በተተከሉ የኤቲኤም ማሽኖች ደንበኞች ገንዘብ ለማውጣት ቢሞክሩም፣ ሙከራቸው አለመሳካቱን ከማሽኑ የመረጃ ሰሌዳ እየተገለጸላቸው መሆኑንም እየገለጹ ነው፡፡ ሪፖርተርም ይኼንኑ ችግር በተለያዩ ቦታዎች ተዟዙሮ አይቷል፡፡ በተለይ ደንበኞች ሙከራው እንዳልተሳካላቸው ዓይተው ከሄዱ በኋላ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ሞክረው ያልተሳካላቸውን የገንዘብ መጠን ማውጣታቸውን የሚገልጸው መልዕክት ሲደርሳቸው፣  ድንጋጤና ግራ መጋባት ተፈጥሮባቸዋል፡፡ነገር ግን ከቆይታ በኋላ የተጠቀሰውን የገንዘብ መጠን ወደ አካውንታቸው መመለሱን የሚያሳይ መልዕክት ከባንኩ እንደሚደርሳቸውም ለመረዳት ተችሏል፡፡ ይኼንን በተመለከተ መገናኛ፣ አራት ኪሎ፣ ካዛንቺስና ቦሌ አካባቢዎች የሚገኙ የባንኩ ቅርንጫፎች ሪፖርት በሚያደርጉ ደንበኞች ተጨናንቀው መሰንበታቸውን ለማየት ተችሏል፡፡ በአንዳንዶቹ ቅርንጫፎች ደንበኞች በምሬት ከባንኩ ሠራተኞች ጋር ሲጨቃጨቁም ተስተውለዋል፡፡የባንኩ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ኤፍሬም መኩሪያ በተወሰኑ ቅርንጫፎች አካባቢ ባሉ ማሽኖች ችግሩ መስተዋሉን አምነው ችግሩ ከኔትወርክ መቆራረጥ ጋር የተያያዘ መሆኑን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ከቴክኖሎጂው ጋር ለመራመድ በሚደረገው ጥረትም ችግሮች እንደሚከሰቱ ጠቁመዋል፡፡ችግሩ የተከሰተው በዝውውር (Transfer)  አለመሟላት ምክንያት ቢሆንም፣ በማዕከል ቋት አማካይነት የሚተላለፍ በመሆኑና ጥብቅ ክትትል ስለሚደረግበት፣ ደንበኞች ሥጋት ላይ ሊወድቁ እንደማይገባና በፍጥነት ሊስተካከል እንደሚችል አቶ ኤፍሬም ጨምረው ገልጸዋል፡፡ሆኖም ደንበኞች እንዲህ ዓይነት ችግር በሚገጥማቸው ወቅት በአቅራቢያቸው በሚገኙ ቅርንጫፎች ወይም ኤቲኤም ካርዱን ያወጡበት ቅርንጫፍ በመሄድ ሪፖርት እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የባንኩን ነፃ የስልክ መስመር በሆነው በ950 በመደወል ጥያቄ ሊያቀርቡ ይገባልም ብለዋል፡፡የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመላው አገሪቱ ከ650 በላይ የኤቲኤም ማሽኖች  አሉት፡፡ በአዲስ አበባ ብቻ ከ250 በላይ መትከሉን ከባንኩ የተገኘው መረጃ ያሳያል፡፡", "passage_id": "5b6b9f24b231e12759a1ec68196ef209" } ]
ffd8355d6b5840699a9ce61fc8199c2f
83ed0d6fb8409ceca5bffbd47834e8fa
በአማራ ክልል ከ328 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የሚሸፍን የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ተጀመረ
ሰላማዊት ውቤ አርማጮሆ፦ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት በዘንድሮ የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች በሚገኝ ከ328 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ተግባራዊ እንደሚሆን የአማራ ቤሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ግብርና ቢሮ አስታወቀ። በሥራው 4 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዜጎች እንደሚሳተፉ ገለጸ። በቢሮው የተፈጥሮ ሀብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም ዳይሬክተር ተወካይ እስመለዓለም ምህረት ለጋዜጣው ሪፖርተር እንዳስታወቁት ከትላንት ጀምሮ እንደ አካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ ከ20 እስከ 30 ለሚደርሱ ቀናት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራው በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች በሚገኙ ከ328 ሺህ ሄክታር በላይ በሆኑ የማሳ፣ የቦረቦር መሬቶችና የተራራ ሥፍራዎች ስነ ሕይወታዊ ሥራዎች ይከናወናሉ።በተጨማሪም በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች ከ1 ነጥብ 6 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተፈልተው ከ182 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የመትከል የስነሕይወታዊ ሥራ የሚሠራ መሆኑን የጠቆሙት ተወካዩ ፣ በሥራው 4 ነጥብ 6 ሚሊዮን የክልሉ አርሶ አደሮች፣ ባለሙያዎች፣ ባለድርሻ አካላትና የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ይካፈላሉ ብለዋል።የተፈጥሮ ሀብት ሥራ ከዚህ ቀደም የግብርና ሥራ ተደርጎ ይወሰድ እንደነበረ የጠቀሱት ኃላፊው፣ ሥራው የሁሉንም ርብርብ የሚጠይቅ በመሆኑ ይሄ ዓይነቱ አስተሳሰብ መቅረት እንዳለበት አሳስበዋል። ባለሀብቱ በእርሻ መሣሪያም ሆነ መኪናውን ለሥራው የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ለማጓጓዝ እንዲውሉ በመፍቀድ እንዲተባበርና የራሱን አስተዋፅኦ እንዲያደርግም ጥሪ አቅርበዋል።የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራው ስነ አካላዊ፣ ስነ ሕይወታዊ፣ ዘላቂነትና ተጠቃሚነትን ያካተተ እንደሆነና የሥራው የመጨረሻ ግብም አፈር መቆለል፣ድንጋይ መካብና ጉድጓድ መቆፈር ሳይሆን ተጠቃሚነትን ማምጣትና የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ እንደሆነ አመልክተዋል። ሥራውን ለማከናወን ባለፉት ወራቶች ሥራው የሚሠራባቸውን አካባቢዎችና ከ8 ሺህ 300 በላይ ተፋሰሶች የመለየት፣ ክፍተት ያለባቸውን ባለሙያዎች የማሰልጠንና ለሥራው የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን የማዘጋጀትና ሕብረተ ሰቡን የማወያየት ሥራዎች ሲሠሩ መቆየታቸውን አስታው ሰዋል። የተፈጥሮ ሀብት ልማት ጥበቃ ሥራ መነሻው ታች ከተፋሰስ መሆኑን የጠቀሱት ተወካዩ ፣ ይሄው ዝግጅት እስከ ቀበሌ መውረዱን አስታውቀዋል። ባለፈው ሳምንት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድርና የግብርናው ዘርፍ ኃላፊዎች ባሉበት መግባባት ላይ ተደርሶ የጋራ መደረጉንና ትላንትና በይፋ መጀመሩን ጠቁመዋል። ቀደም ሲል ቦረቦር የነበሩ፣የተራቆቱ መሬቶችና ተራራዎች የነበሩና በተፈጥሮ ሀብት ሥራው በመለወጥ አትክልትና ፍራፍሬ፣ የእንሰሳት መኖ፣ለማገዶ እንጨት የሚውሉ ዝሪያዎች የለሙባቸውና የእንሰሳትና የንብ እርባታ እየተካሄደባቸው የሚገኙ ሥፍራዎች በፌዴራል፣ በክልል፣በዞንና ከተለያዩ አካባቢዎች በመጡ አመራሮችና ባለሙያዎች ተጎብኝተውና ልምድ ተቀስሞባቸዋል ብለዋል።“ሥራው ዓመቱን ሙሉ የሚሠራ ነው›› ያሉት ተወካዩ፣ በአማራ ክልል የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ በተደራጀና በንቅናቄ መልማት የጀመረዉ በ2003 ዓ.ም መሆኑን አስታውሰዋል።›› ‹‹ከንቅናቄው በፊት የክልሉ የደን ሽፋን 6 ነጥብ 5 በመቶ ነበር›› ያሉት ተወካዩ እስከ አሁን በተሠራዉ ሥራም የክልሉ የደን ሽፋን ወደ 14 ነጥብ 6 በመቶ ከፍ ማለቱን ተናግረዋል። ዕድገቱን ዘላቂ ለማድረግ የዘመቻ ሥራው ከተጠናቀቀ በኋላም የተገኘውን ተሞክሮ በመቀመር በቀጣይ በግል ማሳና በሌሎች አካባቢዎች በቋሚነት ተጠናክሮ የሚሠራ መሆኑን አመልክተዋል። የተፈጥሮ ሀብት ልማት ጥበቃ ሥራ እንደ ሀገር ከጥር 1/2013 ጀምሮ በይፋ መጀመሩና እንደ አካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑ ይታወቃል።የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር በተገኙበት በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ላይ አርማጭሆ ወረዳ ችራ ቀበሌ በሶኒ ተፋሰስ ነው። በሥነ-ሥርዓቱ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሳኒ ረዲ ጨምሮ ሌሎች የፌዴራል፣ ክልልና ዞን ከፍተኛ አመራሮችም ተገኝተዋል። አዲስ ዘመን ጥር 5 ቀን 2013  ዓ.ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=39389
[ { "passage": "አዲስ አበባ፡- በ2012 በጀት አመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት 95 ነጥብ 4 ሄክታር ከይገባኛል የፀዳና የለማ መሬትን ማዘጋጀቱን የመሬት ልማትና ከተማ ማደስ ኤጀንሲ አስታወቀ። የኤጀንሲው የኮሙኒኬሽን ባለሙያ አቶ አብዮት ታዬ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት ፤የከተማ አስተዳደሩ ሊገነባ ላሰበው አምስት መቶ ሺህ የጋራ መኖሪያ ቤቶችና በአስሩም ክፍለ ከተሞች ለተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማት የሚውል ከይገባኛል የፀዳ 95 ነጥብ አራት ሄክታር የለማ መሬት አዘጋጅቷል፡፡ኤጀንሲው፤ እጅግ የተጎሳቆሉና ወደ ኋላ የቀሩ የከተማዋን አካባቢዎች መልሶ ለማልማት፤ የልማት ተነሺዎችን ፍላጎት መሰረት በማድረግ ምትክ ቦታ፣ የጋራ መኖሪያ ቤት፣ እንዲሁም የቀበሌ ቤትና የካሳ ክፍያ በመክፈል ቦታዎቹን ነጻ ማድረጉንም ጠቁመዋል።መንገዶች በሚሰሩበት ወቅት በግራና በቀኝ የሚገኙ ቦታዎችን ከይገባኛል ነፃ በማድረግ የወሰን ማስከበር ስራ ተሰርቷል፤ ለአብነትም ለኢትዮ ቴሌኮምና ለኤሌክትሪክ ሀይል አገልግሎት የዋሉ ምሰሶዎችን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የማንሳትና መንግስታዊና መንግስታዊ ላልሆኑ ተቋማት ለማህበራዊ አገልግሎት፣ ለሊዝ ወዘተ… የለማ መሬትን እያዘጋጀ ያስተላልፋል።ኤጀንሲው በከተማዋ በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ አምስት ፕሮጀክቶችንም ወደ ስራ ለማስገባት በአካባቢው ለሚገኙ ነዋሪዎችና ተቋማት ለባለ  ይዞታዎች ምትክ ቦታ የመስጠትና ካሳ የመክፈል ስራ እየሰራ ይገኛል። ከነዚህም ውስጥ የለገሀር መልሶ ማልማትና ፑሽኪን አደባባይ ወደ ስራ የገቡ ሲሆን፤  ሂልተን ጀርባ የሚገኘው የቤተመንግስት ማስፋፋያ ፕሮጀክትም ወሰን የማስከበር ስራው ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ቦታው ለልማት ክፍት ሆኗል። ከዚህ በተጨማሪም በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥረት የተጀመረውና ጎተራ አካባቢ የሚገኘው ሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ በይዞታ ላይ የሚገኘውን ንብረት ሙሉ ለሙሉ አንስቶ ቦታው ለመልሶ ማልማቱ ዝግጁ ሆኗል። ከዚህም በላይ የዲዛይን ስራው የተጠናቀቀና የግንባታው ወጪም ሙሉ በሙሉ የሚከናወነው በቻይናው ኤግዚን ባንክ በተገኘ ድጋፍ መሆኑን አቶ አብዮት ጨምረው ገልፀዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2012ፍሬህይወት አወቀ ", "passage_id": "8def1dbc9769db9ea431d2cfacaa535a" }, { "passage": "በአማራ ክልል ከ9 ሺህ ቶን በላይ የማር ምርት መገኘቱን የአማራ ክልል እንስሳት ሀብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ አስታወቀ።\nየአማራ ክልል ለንብ ማነብ ተስማሚ የሆነ የአየር ፀባይ እና የመልክዓ ምድር አቀማመጥ እንዳለው ይነገራል፡፡", "passage_id": "0a63248a7f84f119255f0f8d3ca7bfd7" }, { "passage": "ባሕር ዳር፡ ግንቦት 11/2012 ዓ.ም (አብመድ) ከ60 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት ለአዲስ አልሚዎች ለማስተላለፍ ዝግጅት ላይ መሆኑን የክልሉ ገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ቢሮ አስታወቀ።የተለያየ አፈጻጸም ችግር ያለባቸውን በመንጠቅ አዲስ ለሚያለሙ ባለሀብቶች ለማስተላለፍ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የአማራ ክልል ገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ቢሮ ኃላፊ ግዛት አብዩ ተናግረዋል።በእርሻ ኢንቨስትመንት የተሰማሩ ባለሀብቶች ምርታማነቸውን እንዲጨምሩ ሰፊ ሥራ እየተሠራ መሆኑንም አንስተዋል።መሬት በጨረታ፣ በጊዜያዊነት፣ በመደበኛ የሊዝና በጨረታ በጊዜያዊነት መርቶ በማቅረብ በኩልም እየተሠራ ስለመሆኑ ኃላፊው አመልክተዋል። በመጪው የመኸር ወቅት በምዕራብ ጎጃም፣ አዊ ብሔረሰብ አስተዳደር፣ ምሥራቅ ጎጃም፣ ምዕራብና ማዕከላዊ ጎንደር በሰፊው ለማልማት ታስቧል።የእርሻ ወቅት ከመድረሱና ከኮሮና ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ ምርትና ምርታማነት እንዳይቀንስ ማምረት የሚችል የገጠር ኢንቨስትመንት መሬት ጾም እንዳያድርና የውጭ ምንዛሬ ለማስገኘት ከ60 ሺህ ሄክታር በላይ የኢንቨስትመንት መሬት በውድድር ማስተላለፍ እንዳስፈለገ ነው የክልሉ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ቢሮ የገለጸው።", "passage_id": "25a159fbe1b026adfaafdbdb27356fa5" }, { "passage": "በሀገራችን የተለያዩ ክልሎች የተራቆቱ  መሬቶች እንዲያገግሙ ለማድረግ 30 ሺሕ ሄክታር ሰው ሰራሽ ደን ለማልማት እየሰራ መሆኑን የአከባቢ ደን ልማትና የአየር ንብረት ለውጥ ሚኒስቴር አስታወቀ ፡፡በሚኒስቴሩ የደን ዘርፍ ልማት ዓቅም ግንባታ ፕሮግራም አስተባባሪ ዶክተር ተፈራ መንግስቱ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለጹት፤ በአማራ ፣በትግራይና በደቡብ ክልሎች በሚገኙ ዘጠኝ ወረዳዎች በ3 ሺሕ ሄክታር መሬት ላይ የችግኝ ተከላ ስራ ባለፈው ክረምት ተጀምሯል፡፡በቀጣይ ክረምትም ሰው ሰራሽ ደኑን ከ6 ሺሕ ሄክታር በላይ ለማድረስ መታቀዱንም ዶ/ር ተፈራ  ጠቁመዋል።ሚኒስቴሩ ከተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም በጋራ እየሰራ መሆኑንና ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ 22 ሚሊየን ዶላር  መመደቡን ነው ያስታወቁት ፡፡በወረዳዎቹ የሚገኘው ህብረተሰብ በስፋት እየተካፈለ ሲሆን በወረዳዎቹ አከባቢዎች የነጻ ጉልበት ተሳትፎው ከ50 እስከ 80 በመቶ ይደርሳል ነው ያሉት ፡፡የፕሮጀክቱ ዓላማም የደን ዘርፉን ዓቅም ማጠናከር ነው ያሉት አስተባባሪው ፤ በደን ዘርፍ በሙኮራ ደረጃ በተወሰኑት ወረዳዎች መሬት ላይ ስራ ለመጀመር መሆኑን አስረድተዋል ፡፡እንደዚሁም በዘርፉ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት በመቀናጀት የምርምርና የስልጠና  ስርዓቱን ማጠናከር ላይ ማተኮሩንም ገልጸዋል ፡፡በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት 150 ሺ ሄክታር የተጎዱ ቦታዎችን መልሰው እንዲያገግሙ እንደሚደረግም አስታውቀዋል ፡፡እንደዚሁም ያገገሙ ቦታዎችን ደግሞ እስከ 60ሺ ሄክታር ከልለው የልማት ሰራዎችን ለመስራት መታሰቡን ገልጸዋል ፡፡በነዚህ አከባቢዎች ላይ ህብረተሰቡ በንብ ማነብ ስራ ፣በተሻሻሉ ምድጃዎች ስራ ፣በችግኝ ጣቢያ ስራ እና በሌሎች የደን ልማት ስራዎች ላይ ለ7ሺ 359 የስራ ዕድል መፈጠሩን ዶክተር ተፈሪ አስታውቀዋል ፡፡በተጨማሪም ስራውን ከየወረዳ መስተዳድሮች ጋር በመሆን የሚያስተባብሩ 90 ሰዎች ተቀጥረው እየሰሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል ፡፡በዓቅም ግንባታም ረገድ በደን ዘርፉ የትምህርት ስርዓቱን ለማጠናከር ካሪክለሙ በመከለስ  ተማሪዎች የተሻለ ዕውቀትና ክህሎት ይዘው እንዲወጡ ለማድረግ እንደሚሰራም ገልጸዋል፡፡ፕሮጀክቱ ሐምሌ 2007 ዓመተ ምህረት መጀመሩን ከአስተባባሪው ገለጻ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ", "passage_id": "2811d6ae101ea4504c16a8c8a0d24234" }, { "passage": "የግብርና ሚኒስቴር 2 ነጥብ 7 ሚሊየን ሄክታር መሬት በመስኖ ለማልማት አቅዶ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።የሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ታረቀኝ ፅጌ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለፁት፤ እቅዱን ለማሳካትም እያንዳንዱ ቤተሰብ ቢያንስ አንድ የውሃ ባንክ እንዲኖረው የሚያደርጉ አማራጮች ተለይተው 70 ከመቶ የሚሆነው ቤተሰብ የውሃ ባንክ እንዲኖረው ይደረጋል።እቅዱን ውጤታማ ለማድረግም የተደራጀ የልማት ሰራዊት መገንባትና የአነስተኛ መስኖ አውታሮችን በማስፋፋት ላይ ትልቅ ድርሻ ያለውን የአርሶ አደር ጉልበት በስፋት ለመጠቀም የሚያስችል የህዝብ ንቅናቄ ለመፍጠር መታቀዱን ጠቁመው፤ የህዝብ ንቅናቄውን በመፍጠር የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ስራዎችን በሁሉም ምዕራፎች መከናወን የሚገባቸውን ስራዎች በሙሉ በተደራጀ አግባብ መፈፀም ያስፈልጋል ብለዋል።እንደ አቶ ታረቀኝ ገለፃ በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱ በተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ስራው የተቀመጠውን ግብ ከወዲሁ ለማሳካት የተቻለ መሆኑን ጠቁመው፤ በቀጣይም በተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ስራ አዲስ ግብ በማስቀመጥ የሚከናወን ይሆናል ሲሉ ተናግረዋል።እንዲሁም የተለያዩ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች የሚካሄድባቸው የማህበረሰብ ተፋሰሶችን ከ3 ነጥብ 77 ሚሊየን ሄክታር በሚቀጥለው ዓመት ወደ 7 ነጥብ 78 ሚሊየን ሄክታር ከፍ ለማድረግ መታቀዱን ጠቁመው፤ ባለፉት ሶስት የእቅድ አመታት 13 ነጥብ 7 ሚሊየን ሄክታር ማልማት መቻሉን ገልፀዋል።የአፈር ለምነትን የሚያሻሽሉ ቴክኖሎጂዎች ተግባራዊ እንደሚደረጉ የገለፁት አቶ ታረቀኝ ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያላቸው 5 ነጥብ 1 ቢሊየን ችግኞችም ይዘጋጃሉ ብለዋል።አስፈላጊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችም በአብዛኛው አካባቢዎች ከጥር ወር ጀምሮ እየተከናወነ መሆኑን አቶ ታረቀኝ መናገራቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።", "passage_id": "c5bb21ac3075bcca329cf5e4028113d6" } ]
918c97b690f491d299ad7888f081c39c
0daf9551c748ce6e92c3f36b7beb2d94
የጁንታው ከፍተኛ አመራሮች መያዝ የህግ የበላይነትን በተግባር ያረጋገጠ መሆኑ ተገለጸ
ሞገስ ተስፋ አዲስ አበባ፡- የጁንታው ከፍተኛ አመራሮች መያዝ የህግ የበላይነትን በተግባር ያረጋገጠ እንደሆነ አዲስ ዘመን ያነጋገራቸው አንዳንድ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።ለተንኮል ሸራቢ አካላትም ትልቅ ትምህርት የሰጠ መሆኑን አመለከቱ፡፡ አዲስ ዘመን ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ነዋሪ የሆኑት አቶ ጌትነት ደምሌ እንደገለጹት፣ በቁጥጥር ስር የዋሉ የጁንታው ከፍተኛ አመራሮች ለ27 ዓመታት ሀገርን እመራለሁ በሚል አምባገነናዊ የአገዛዝ ቀንበራቸውን በህዝብ ጫንቃ ላይ በግድ በመጫን ህዝብን በዘር፣ ኃይማኖት እና በጎሳ እያጋጨ ሀበት ሲመዘበሩ የነበሩ የጥፋት መሃንዲሶች ናቸው። በስልጣን ዘመናቸው ዜጎቿ በየቦታው የሚገደሉባት፣ በቋንቋ የሚጋጩባት፣ አንዱ ብሔር አንዱን በጥላቻ እንዲያይ ያደረገ ክፉ አረም የዘሩ መሆናቸውን ጠቁመው፣ እነዚህ የሀገር ቀንደኛ ጥላቶች ከስልጣን በተገፉ ማግስትም ከኛ ውጪ ሀገርን የሚመራ ኃይል የለም በሚል እብሪት በአደባባ ሲደነፉ የነበሩ ናቸው። የእነሱ መያዝ የዘሩትን በተግባር እንዲያጭዱ የሚያደርግ ትልቅ ትርጉም ያለው ክስተት ነው ብለዋል፡፡ ‹‹ሥራ ለሠሪው›› እንደሚባለው የለኮሱት እሳት ራሳቸውን አቃጥሏቸዋል ያሉት አቶ ጌትነት ፣ የእኩይ ተግባር ቀያሾቹ መያዝ ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ለውጥ ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል። ቀጣዩ ዘመን የህግ የበላይነት በተግባር የሚታይበት፣ ሀገር የምትለወጥበት ፣ በግለሰብ ደረጃም የተሻለ ኑሮ ለመኖር፣ ሠርቶ ለማደግ እና ለመለወጥ ለሚፈልግ ዜጋ ትልቅ የዕደገት እና የለውጥ ዘመን እንዲሆን የተሻለ ዕድል የሚፈጥር እንደሚሆን አመልክተዋል። እንደ አቶ ጌትነት አስተያየት፣ መንግሥት የህግ ማስከበር ዘመቻውን በታላቅ ሀገራዊ ወኔ እና ትብብር በተሞላበት ሁኔታ የሰላማዊ ዜጎችን ደኅንነት በመጠበቅ፣ ብዙ ንብረት ሳይወድም በትንሽ መስዋዕትነት በድል መወጣቱ ትልቅ ስኬት ነው።ለዚህ ስኬት ቀጣይነት ደግሞ መንግሥት ብቻ ሳይሆን ሁሉም ዜጋ ባቅሙ ጠንክሮ በመሥራት የጎደለውን በመሙላት ሊንቀሳቀስ እንደሚገባ ጠቁመዋል። መንግሥት ህግን ለማስከበር እየወሰደ ያለውን ዕርምጃ የሚመጥን ትክክለኛ መረጃ በመገናኛ ብዙሃኑ ለህዝቡ እንዲደርሱ መደረጉ በራሱ ትልቅ ስኬት መሆኑን አመልክተው ፣ የህግ ማስከበር ዘመቻው ሀገርን በቁማር እና ተንኮል መምራት የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ተጠያቂነት ማስከተሉ እንደማይቀር ያስተማረ ነው። ጁንታዎች በሠሯቸው ሥራዎች ኪሳራ እንጂ ትርፍ አላገኙም። ይህም ሀገርን ካለችበት ማማ ለማውረድ ለሚሠሩ ትልቅ መማሪያ እንደሆነ ገልጸዋል። ሌላኛዋ የአዲስ አበባ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ገነት አለማየሁ በበኩላቸው ፣ የጁንታው ከፍተኛ አመራሮች ለበርካታ ዓመታት በህዝብ ላይ ያስከተሉት ጥፋት ሳያንስ ከስልጣን ከተገለሉ ማግስት ነፃነቱን እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ተገፎ ከቆየው የትግራይ ህዝብ ጉያ ገብተው በሰላም መቀመጥ አቅቷቸው ለዳግም ጥፋት የደገሱት የጥፋት ድግስ ራሳቸውን እንዳጠፋቸው አመልክተዋል። ጁንታው በስልጣን በቆየባቸው ዓመታት በተለይም በሴቶች ላይ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈፀሙን አመልክተው ፣ የጥፋት ቡድኑ በቁጥጥር ስር መዋሉ የጊዜ እንጂ የቡድን ጀግና እንደሌለ በተጨባጭ ያሳየ ነው ብለዋል። የህግ የበላይነት ምን ማለት እንደሆነም ለቡድኑ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች ትምህርት የሰጠ መሆኑን ገልጸዋል። አቶ ስዩም ይሁኔ የተባሉት ልላኛው መዲናዋ ነዋሪ ፣በሀገሪቱ ያሉ ስልጣን ለመያዝ እውቅና የተሰጣቸው ፓርቲዎችም ከጁንታው አመራሮች ትምህርት በመያዝ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ እና የህዝብ ጥቅም መረጋገጥ ቢሠሩ ቀጣይነት ላላው ሰላም መስፈን ትልቅ ዋጋ ይኖረዋል ብለዋል።ከጀርባ ሆነው ግጭት ለመፍጠር ነገር በመጥመቅ፣ በማስታጠቅ ሀገሪቱ የተረጋጋች እንዳትሆን አቅደው ሲሠሩ የነበሩ የህዝብ ጠላቶች መያዛቸው ለህዝብ ሰላም መረጋገጥ እና ቀጣይነት ያለው የሀገር ዕድገት ለማስመዝገብ ትልቅ መደላ ድል እንደሆነ አስታውቀዋል። ሀገርን ሲያውኩና መጥፎ ሥራ ሲሠሩ የቆዩት አመራሮች መያዝ የህግ የበላይነት ያረጋገጠ ፣ ማንም ሰው ከህግ በላይ ላለመሆኑ ማሳያ ነው ያሉት አስተያየት ሰጪው፣ መንግሥት በቀጣይ ለሚወስደው የህግ ማስከበር ዕርምጃ የህዝብ ድጋፍ ወሳኝ በመሆኑ ለትክክለኛ ፍትህ ዘብ በመሆን ከስጋት ተላቀን ልማቱን እንድናስቀጥል መንግሥት እና ከህዝብ ከቀደመው በተሻለ ተቀራርበው መሥራት እንዳለባቸው አሳስበዋል። አዲስ ዘመን ጥር 5 ቀን 2013  ዓ.ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=39385
[ { "passage": "አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በህወኃት ውስጥ ያለው ቡድን የሀገር መከላከያ ጦር ጄት መትቼ ጥያለሁ ሲል የገለጸው ፍጹም ሀሰት መሆኑን የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ኢንዶክትሪኔሽን ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል መሐመድ ተሰማ ገለጹ።ሜጀር ጄኔራል መሐመድ አየር ኃይሉ አሁንም ቢሆን የተመረጡ ቦታዎችን ማጥቃቱን አጠናክሮ ቀጥሏል ነው ያሉት።የጥፋት ቡድኑ በመከላከያ ኃይል እየደረሰበት ባለው ጥቃት በርካታ ይዞታዎችን እየለቀቀ መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡ሜጀር ጄኔራሉ በርካታ የክልሉ ልዩ ኃይልና ሚሊሻዎችም በሰላም እጃቸውን እየሰጡ እንደሚገኙ ኢዜአ ዘግቧል። ", "passage_id": "8d3deb8793cb12b60d010b9fba6a847e" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ህዳር 18፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በመተከል ዞን እየተወሰደ ያለው ህግን የማስከበር ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የመተከል ዞን ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢ ኮሎኔል አያሌው በየነ ገለጹ።ካለፈው ሃምሌ ወር ጀምሮ እስካሁን 280 ጸረ ሰላም ሃይሎች ላይ እርምጃ መወሰዱንም ነው የገለጹት።የጁንታውን ተልዕኮ በማስፈጸም በዞኑ ውስጥ ዜጎችን በመግደል፣ በማፈናቀልና ንብረት በማውደም የተሰማሩ ቡድኖችን ለማጽዳት እርምጃው ይቀጥላል ብለዋል ኮሎኔል አያሌው ።ቀጠናው የአጎራባች ሃገራት አዋሳኝ ስለሆነ ለጠላት ሰርጎ ለመግባት አመቺ መሆኑና የጸረ ሰላም ሃይሎች ከህብረተሰቡ ጋር በመቀላቀላቸው ለይቶ ለማውጣት የአንዳንድ አመራሮች ቁርጠኝነት ማነስ ሁኔታውን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማረጋጋት አስቸጋሪ እንዳደረገውም ተናግረዋል።ይሄን የጥፋት ተልዕኮ ለመደምሰስ የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የፌደራል ፖሊስና የክልሉ ልዩ ሃይል ፖሊስ በመቀናጀት የዘመቻ ስራዎች እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው ህብረተሰቡ ጠላትን አጋልጦ እንዲሰጥ የፖለቲካ አመራሩ እየሰራ ይገኛልም ነው ያለው።ቀጠናውን ወደ ነበረበት ሰላም ለመመለስ አጥፊዎችን በመደምሰስ እንዲሁም በጉዳዩ በአንድም ይሁን በሌላ መልኩ የተሳተፉ አካላትን ወደ ህግ በማቅረብ የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡ባለፉት ሁለት ቀናት ህግን ለማስከበር በተደረገው የተቀናጀ ዘመቻ በማንዱራ 17፣ በዳንጉር 4 እና በጉባ 2 በአጠቃላይ 23 ጸረ ሰላም ሃይሎች ላይ እርምጃ መወሰዱን ከመተከል ዞን ኮሙዩኒኬሽን ያገነነው መረጃ ያመለክታል፡፡ ", "passage_id": "e6f5e5dd40c34ed6b1d53f2e8ff9354e" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ህዳር 20 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀገር መከላከያ ሰራዊት በትግራይ ክልል እያካሄደ የነበረውን ህግን ማስከበር ዘመቻ አጠናቆ እና ህዝቡን በማረጋጋት ወደ ቀየው መመለስ መጀመሩን ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ አስታወቁ።የራያ ግንባር አዛዥ ሌተናል  ጄኔራል ባጫ ደበሌ ህግን በማስከበር እርምጃው በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል።ሌተናል  ጄኔራል ባጫ ደበሌ በመግለጫቸው የመከላከያ ሰራዊቱ ሶስተኛ ምዕራፍ ህግን የማስከበር ዘመቻውን  አጠናቆ በደህንነት ስጋት ምክንያት ከቀያቸው ተፈናቅለው የነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ወደ መመለስ ተሸጋግሯል ብለዋል።ሰራዊቱ የፀጥታ ስጋት የሚታይባቸውን አካባቢዎችን በማረጋጋት ህብረተሰቡ ወደ መደበኛ ህይወቱ እንዲመለስ የሚደረገውን ጥረት እያገዘ ነው ብለዋል።ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን የጁንታው ቡድን በተለያዩ ከተሞች ሊፈፀማቸው የሚችሉ የአጥፍቶ መጥፋት ጥቃቶችን ለመከላከል ሰራዊቱ በተጠንቀቅ ላይ ይገኛል ነው ያሉት።በትናትነው ዕለት የፅንፈኛው ቡድን አባላት  ሌተናል  ጄኔራል ባጫን  ማርከናል የሚል መረጃ ሲነዙ እንደነበር በመግለጫቸው ላይ ያነሱት ሌተናል ጄኔራሉ በጉዳዩ ዙሪያ በሰጡት መግለጫ እየፈረጠጠ ያለው ቡድን ምንም አይነት የመማረክ አቅም ብለዋል።ከተማረክንም በህወሃት ጁንታ ሳይሆን በኢትዮጵውያን እና በኢትዮጵያዊነት ነው ሲሉ በመግለፅ የጦር ኃይሎች ምክትል ኢታማዦር ሹም ሌተናል ጄኔራል አበባው ታደሰ ጋር  በጋራ በመሆን መግለጫ እንደሚሰጡም ጠቁመዋል።የጁንታው ቡድን አባላትን ለህግ ለማቅረብ የሚከናነው ስራዎች እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።በፋሲካው ታደሰ", "passage_id": "1c2caf827252d4f65b0c85792808c635" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) መንግሥት በጥንቃቄና በፍጥነት እየወሰደ የሚገኘው ህግ የማስከበር እርምጃ በስኬት ታጅቦ ወሳኝ የድል ምዕራፍ መቀዳጀቱን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ገለፁ።ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በፌስቡክ ገፃቸው ባወጡት መልእክት፥ “ውድ የሃገራችን ህዝቦች! እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን” ብለዋል።“እነሆ ዛሬ! በሃገር መከላከያ ሰራዊታችን በሳል የውጊያ ጥበብ እና የትግል ወኔ የህውሃት ጁንታ ቡድን የከተመባትን የመቀሌ ከተማ ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሯል” ብለዋል።መንግሥት በክልሉ በጥንቃቄ እና በፍጥነት እየወሰደ የሚገኘው ህግ የማስከበር እርምጃ በስኬት ታጅቦ ወሳኝ የድል ምዕራፍ መቀዳጀቱንም ገልፀዋል።“ለዚህ ዘመን ተሻጋሪ ድል ላበቁን ለጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችን፣ ለአማራ ክልል ልዩ ሃይል እና ሚሊሻዎች ታላቅ ምስጋና እና ክብር ይገባቸዋል” ብለዋል አቶ ደመቀ።“በዚህ ህግ የማስከበር ዕርምጃ በኢትዮጵያዊነት ለአፍታ ለማይደራደረው የትግራይ ክልል ህዝብ ለመከላከያ ሰራዊታችን ብርቱ ደጀን በመሆን ለተጫወተው ታሪካዊ ሚና ልዩ ክብር እና ምስጋና ይገባዋል” ብለዋል በመልእክታቸው።በመቀጠል የጁንታውን ቡድን አድኖ ለህግ የማቅረብ ተልዕኮ በተቀጣጠለው የድል ስሜት እስከመጨረሻዋ ሰዓት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።መንግሥት በደረሰበት ወሳኝ የድል ምዕራፍ ዜጎችን ከጥቃት የመጠበቅ እና የመከላከል ተግባሩን በጥንቃቄ፣ በንቃት እና በሃላፊነት ስሜት የሚወጣ መሆኑንም ገልፀዋል።በቀጣይ በትግራይ ክልል እና በአከባቢው ፍፁም ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን አስፈላጊውን ሁሉ በመንግስት በኩል ተፈፃሚ ይደረጋል ብለዋል።በአጭር ሂደት በትግራይ ክልል በጁንታው ቡድን ሴራ የፈራረሱ መሰረተ ልማቶችን መልሶ የመገንባት እና የማቋቋም እንዲሁም በሂደት በክልሉ ዘላቂ ሰላም እና ልማት የማረጋገጥ ስራዎች በትኩረት እንደሚከናወኑም አስታውቀዋል።“በጠንካራ የአመራር ጥበብ የተመራው ህግ የማስከበር እርምጃችን መሪ ዓላማ የጁንታውን ቡድን ካለበት ለቅሞ ለህግ ማቅረብ ተልዕኮ በመሆኑ፤ አሁንም እስከመጨረሻው ድረስ ለዓላማው የተሟላ ተፈፃሚነት የትግራይ ክልል ህዝብ ወንጀለኞችን ከተደበቁበት ፈልፍሎ የማጋለጥ ታሪካዊ ሃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪዬን አቀርባለሁ” ብለዋል።", "passage_id": "b6e76b9372909d2407322eb6c9b715f8" }, { "passage": "እፀገነት አክሊሉ አዲስ አበባ፦ የኢትዮጵያ ህዝብ በጉጉት ሲጠብቅ የነበረው ይህንን ነው አሁንም የቀሩትን በመያዝ የልቡን ለማድረስ ሠራዊቱ ዝግጁ ነው ሱሉ ከምሥራቅ እዝ 25ተኛ ክፍለ ጦር መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ አስታወቁ። አባይ ወልዱ እና ዶክተር አብረሀም ተከስተን ጨምሮ ዋነኛ የጁንታው አመራሮች እንደ ጃርት ቆፍረው ከተደበቁበት ጉርጓድ አውጥቶ ለፌዴራል ፖሊስ ማስረከቡን ገለጹ፡፡ መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ ትላንት ማምሻውን በቁጥጥር ስር የዋሉ የጁንታውን ሲቪልና ወታደራዊ አመራሮችን ይዘው አዲስ አበባ በገቡበት ወቅት እንዳስታወቁት፣ ሰዎቹ እጅግ አስቸጋሪ በሆነ ሁኔታ የጃርት ጉድጓድ ቆፍረው ቢደበቁም ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ሌት ተቀን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል በፈጸመው ተጋድሎ በቁጥጥር ስር ሊያውላቸው ችሏል፡፡ ሠራዊቱ በከፍተኛ ወኔ ቁጭትና ተነሳሽነት ሌት ተቀን ግዳጁን ለመፈጸም ሲሠራ እንደነበር ገልጸው፣ እነዚህንም ትልልቅ የጁንታውን አመራሮች በቁጥጥር ስር ያዋለው በዚህ ትጋቱ መሆኑን ገልጸዋል፡፡በቀጣይም የተቀሩትን አገር ለማተራመስ ሲጥሩ የነበሩ የጁንታው ከፍተኛ አመራሮች ከተደበቁበት ጉድጓድ አድኖ ለመያዝ ከፍተኛ ሥራ እየተሠራ መሆኑን ጠቁመው ፣ በተለይም ህብረተሰቡ የከዚህ ቀደም ድጋፉን አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡“የኢትዮጵያ ህዝብ በጉጉት ሲጠብቅ የነበረው ይህንን ነው አሁንም የቀሩትን በመያዝ የልቡን ለማድረስ ሠራዊቱ ዝግጁ ነው” ብለዋል፡፡ አገርን ለመበታተን አቅደው በመከላከያ ሠራዊት ላይ ዕርምጃ እንዲወሰድ ካደረጉ አሸባሪዎችና ዋነኛ የጁንታው አመራሮች መካከል፡-1-አቶ አባይ ወልዱ – የቀድሞ የክልሉ ፕሬዚዳንት የነበሩ፣2-ዶክተር አብርሃም ተከስተ – የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት የነበሩ፣ 3-ዶክተር ረዳኢ በርሄ – የክልሉ ኦዲተር ኃላፊ የነበሩ፣4-ዶክተር ሙለጌታ ይርጋ- የክልሉ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ ኃላፊ የነበሩ፣ 5-አቶ ዕቁባይ በርሄ – የሃይማኖት ጉዳይ ክትትል ኃላፊ የነበሩ፣ 6-አቶ ጌታቸው ተፈሪ – የክልሉ ፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤትና የሠላምና ደህንነት ኃላፊ የነበሩ፣7-ወይዘሮ ኪሮስ ሃጎስ – የክልሉ ማህበራዊ ጉዳይ ኃላፊ የነበሩ፣ 8- ንጋቱ አንገሶም ፣9- አምደማርያም ተሰማ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል። የመከላከያ ሠራዊት ኃይል ስምሪት መምሪያ ኃላፊ ብርጋዴል ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው ከትናንት በስቲያ፣ አገርን ለመበታተን አቅደው በመከላከያ ሠራዊት ላይ ጥቃት እንዲደርስ ያደረጉ አሸባሪዎችና ዋነኛ የጁንታው አመራሮች መካከል ፣1ኛ- አቶ አባይ ወልዱ፡- የቀድሞ የክልሉ ፕሬዚዳንት የነበረ፤2ኛ- ዶክተር አብርሃም ተከስተ- የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት የነበረ፤3ኛ- ዶክተር ረዳኢ በርሄ፡- የክልሉ ኦዲተር ኃላፊ የነበረ፤4ኛ ዶክተር ሙሉጌታ ይርጋ፡- የክልሉ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ ኃላፊ የነበረ፤5ኛ- አቶ ዕቁባይ በርሄ- የሃይማኖት ጉዳይ ክትትል ኃላፊ የነበረ፤6ኛ- አቶ ጌታቸው ተፈሪ፡- የክልሉ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤትና የሠላምና ደህንነት ኃላፊ የነበረ፤7ኛ- ወይዘሮ ኪሮስ ሃጎስ፡- የክልሉ ማህበራዊ ጉዳይ ኃላፊ የነበረች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ፣ ከመከላከያ ከድተው ጁንታውን የተቀላቀሉ ፣1ኛ-ኮሎኔል\nገብረእግዚአብሄር አምባዬ \n2ኛ- ኮሎኔል ትርፏ አሰፋ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን፤የአገር መከላከያ ሠራዊቱን በማስከዳት ተግባር ላይ ተሰማርተው የነበሩና በጦርነቱ ከሠራዊቱ ከድተው ጁንታውን የተቀላቀለ፣ 1ኛ- ሜጀር ጄኔራል ኢብራሂም አብዱልጀሊል፡- ቀደም ሲል የመከላከያ ሎጂስቲክ ኃላፊ የነበረና አሁን የጁንታው ሎጂስቲክ ኃላፊ የነበረ፤2ኛ- ብርጋዴል ጄኔራል ገብረኪዳን ገብረማርያም፡- የመከላከያ ኢንዶክትሪኔሽን ኃላፊ የነበረና በጡረታ ከተሰናበተ በኋላ ጁንታውን የተቀላቀለ፤3ኛ- አስር ከፍተኛ መኮንኖች፤4ኛ – ሁለት መስመራዊ መኮንኖች፤5ኛ- የክልሉ ረዳት ኮሚሽነር የነበረና ከፖሊስ ከድቶ ወደ ጁንታው የተቀላቀለ በውጊያ ላይ እያሉ እርምጃ እንደተወሰደባቸው ማስታወቃቸው ይታወሳል ።", "passage_id": "ee5b4eff33302708d1b84648ffca3c82" } ]
8bf8cf5d1350c71e1264a4c325c9b10b
2723cab26f2297cdd7111d40f5e92159
የኮሮና ቫይረስን በቃሪያና በርበሬ?
ዓለም ሰሞኑን ከቻይና ተነሳ በተባለው ኮሮና ቫይረስ መታመስ ይዛለች። ዓለም አቀፉ ሚዲያ በስፋት እየዳሰሰውም ይገኛል። ኮሮና ቫይረስ የዓለማችን ቁጥር አንድ አሸባሪ ቫይረስ ሆኖ ተከስቷል። እንደ አልቃይዳ፤ አልሻባብ፤ ዓለምን ማሸበሩን ቀጥሏል።‹‹የጨነቀ ነገር መላው የጠፋ፤ ደሞ ምን ጉድ አመጡብን?›› አሉ አዛውንቷ እማማ አለሚቱ። ‹‹ከዚህ ከሚወራው መአት አምላክ ይጠብቀን እንጂ ምን ሊባል ይችላል›› አሉ በፍርሀት ጎብጠው። ‹‹ደሞ በትንፋሽ፣ በንክኪ ይተላለፋል የሚሉት ነው እኮ የበለጠ የሚያሸብረው። እንዴት እንዴት ልንሆን ነው። የእኛ ኑሮ እንደሁ በጣም የተቀራረበ፣ የተነካካ አንዱ ከሌላው መራቅ የማይችልበት ነው፤ ብቻ እሱ ይሰውረን›› አሉና አማተቡ። ቤታቸው ውስጥ ከጎናቸው የተቀመጡት ባለቤታቸው አቶ ደቻሳ ‹‹መቆየት ደጉ ስንት ጉድ አየን፤ የባሰ አታምጣ ማለት ይሻላል አለሚቱ›› አሉ። ‹‹እኛስ እሺ። ገና ምኑንም ያላዩት ሕጻናት ወጣቶች እንዴት ሊሆኑ ነው የእነሱ ያሳስበኛል›› አሉ ደቻሳ። ልጆቻቸው በሙሉ ባህር ማዶ ከተሻገሩ ዓመታት ተቆጥረዋል። አውሮፓና አሜሪካ ይኖራሉ። እዛው ከተለያዩ ሀገራት ዜጎች ጋር ተጋብተው ወልደው ከብደዋል። እንደው እንዴት ይሆኑ ይሆን ምን ይሻላል በሚል አባትና እናት ተጨንቀዋል። እናትና አባት ቶሎ ቶሎ ስልክ ወደ አውሮፓ ይደውላሉ። አቤት እማዬ፤ አቤት አባዬ፤ ሲሉ ከወዲያ እንዴት ናችሁ ለመሆኑ ይሄ አዲሱ ተውሳክ ከምን ደረሰ ይሉና ይጠይቃሉ። እኛ እኮ አሸባሪ ብለነዋል። እማዬ ምን ሆንሽ እዚህ ምንም የለም መንግስት እየተቆጣጠረው ነው ሰላም ነው›› ሲሏቸው ‹‹እልል እሰየው እመብርሀን የት ሄዳ ልጆቼን ትጠብቃለች›› ይላሉ። አቶ ደቻሳም እንዲሁ። ‹‹ጎረቤታቸው ያሉት አዛውንት ይሄን የሰሞኑን የአዲስ በሽታ ወሬ ሰምተው በፍርሀት ተውጠዋል። የእሳቸው ልጆች ሀገር ውስጥ ናቸው። ‹‹ማን አላችሁት የበሽታውን ስም›› አሉና ለመጥራት ለመስማትም ፈሩ። በየትና እንዴት አድርጎ እንደሚመጣ ነቅተው የሚጠብቁ ይመስላሉ። ‹‹በዱላ አይመታ፤ ሂድ ውጣ አይባል፤ ምን ጉድ መጣብን›› አሉ እነ አቶ ደቻሳና ወ/ሮ አለሚቱ። ቤታቸው ብቅ ያሉት አቶ ዘበርጋም ይናገራሉ። ዘበርጋ ቀጠሉ ‹‹የት አባቱንስና ኮረና ፎረና የለም። እኛ እኮ እግዚአብሔር የሰጠን ብዙ መድሀኒት አለን። ነጭ ሽንኩርት፤ ዝንጅብል፤ ቃሪያ ፤ፌጦ፤ ጥቁር አዝሙድ፤ ጤና አዳም ወዘተ›› እያሉ ዘረዘሩት። ‹‹ምናባቱንስና ደሞ ለቻይና በሽታ ማን ይሸበራል፤ ድምጥማጡን ነው የምናጠፋው፤ ደፍሮ እኛ ሀገር አይገባም ኤድያ አትሸበሩ ካለ መድኃኒዓለም›› አሉ ጭንቀታቸውን ትተው በልበሙሉነት። ‹‹የእኛ የአበሻ አረቄም እኮ ለእንዲህ አይነቱ የተስቦና የመጋኛ በሽታ ፍቱን መድኃኒት ነው፤ በእሱ እናቃጥለዋለን፤ የምን መረበሽ ነው አሉ።›› አቶ ደቻሳ ነገሩ ከትከት አድርጎ አሳቃቸው። ‹‹እንግዲህ እስከዛሬ የጠበቀን አምላክ ያውቃል። መቼም የማያመጡብን የማንሰማው መአት የለም። ኤድስ የመጣብን ከፈረንጅ ሀገር ነው። ሌላ ሌላም። በቴሌቪዥን ኢቦላ እንዲህ አደረገ ሰው ፈጀ ደም አስተፋ ሲሉ ሁሉ እንሰማለን። ይኸው ደግሞ አዲሱ በሽታ በትንፋሽ በጉንፋን በትኩሳት ወዘተ ይለያል ይላሉ።››‹‹የት ሄደን እንኑርላቸው እስቲ ሰው በገዛ ሀገሩ መኖሪያ ያጣል እንዴ?›› አሉ ወ/ሮ አለሚቱ። አቶ ደቻሳ ቀጠሉና ‹‹ውጭ ያሉት ልጆቼ አንድ ጊዜ በዚህ ጉዳይ ሲያወሩ ፈረንጆቹ በሽታ የሚያመርት ፋብሪካ አላቸው ሲሉ ጆሮዬን ጣል አድርጌ ሰምቼአለሁ። ይሄ ነገር ያሳስበኛል። ዓለምን ለማጥፋት ቆርጠው የተነሱ ነው የሚመስለኝ ዝም ብዬ ባልተማረ ህሊናዬ ሳስበው አሉና ዝም አሉ። እኔም ቀልድ መስሎኝ እንጂ ሰምቼአለሁ›› አሉ ወይዘሮ አለሚቱ። ዘበርጋ ቀጠሉና የሁሉም በሽታ መነሻ እንስሶቹ ናቸው። ሊቀመላእክቱ ችግሩን አጥፍቶ ቢገላግለን ምን አለበት›› አሉ በጣም ተበሳጭተው። ‹‹በእኛ ዘመን ድሮ እንዲህ አይነት ጉድ አይተን ሰምተን አናውቅም። የጠና በሽታም አናውቅ። ግፋ ቢል ደማከሴውን፤ ጤና አዳሙን፤ ነጭ ባሕር ዛፉን አረግሬሳውን ቆርጠን ታጥነን ቶሎ መዳን ነበር። የበሽታው መብዛት አይነቱ ስሙ ጉድ ያሰኛል። ይህን ሁሉ ጉድ ድሀ እንዴት ይችለዋል። ሰውም በጣም ተሸበረ›› እያሉ ሲያወጉ ጎረቤታቸው ማንችሎት ሞቅ ብሎት እንዴት ናችሁ? ብሎ ገባ። እርስ በእርስ ተያዩና አመሉን ስለሚያውቁ የታፈነ ሳቅ ሳቁ። አባግድየለሽ ነው ማን ችሎት። ‹‹አዳሜ የምን መፍራት ነው ሞት እንደሁ አይቀር አላቸው። ሁሉም ደነገጡ። አዲስ መጣ ያሉት በሽታ ነው የሰው ሁሉ ወሬ። ጠጅ ቤቱን ጠላ ቤቱን ሰፈሩን መንደሩን ሁሉ የሞላው። እኛና እሱ እንተዋወቃለን። አይነካንም። አንንነካውም። መድኃኒቱ ጠጅና አረቄ መጠጣት፤ ቃሪያና በርበሬ አብዝቶ መብላት ብቻ ነው አዳሜ ትጨነቂያለሽ ምንም የለም›› አላቸው።‹‹ምን ትጨነቃላችሁ እናንተ ዘጠና ዓመት ውስጥ ናችሁ ለምኑ ብላችሁ ነው አላቸው። ወይዘሮ አለሚቱ የእድሜ ነገር ሲነሳ አይወዱም። አዋልደሀል አሉት። ምን ማዋለድ ያስፈልጋል እናንተ እኮ ሉሲ ስትወለድ የነበራችሁ ናችሁ›› አላቸው። አዲስ ዘመን ጥር 28/2012ወንድወሰን መኮንን
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=26779
[ { "passage": "የመገናኛ ብዙሃኖቻችንን ሳስባቸው ሞልቶላ ቸው ግብር የሚያበሉ ደጋሽ ይመስሉኛል። በዓይነ ህሊናችሁ ሳሉት፤ ከዳስ የሞላው እድምተኛ ከቀረበው እየተቋደሰም ከሌሎች እድምተኞች ጋር ሲያወጋና ሲጨዋወት። ደጋሽ በየመሃሉ ብቅ ብለው «ብሉ እንጂ፤ ኧረ እየጠጣችሁ» እያሉ ሲጋብዙ። ደግሞ «ተጫወቱ» ብለው ለወጋቸው ትተዋቸው ወደ ሌላው ሄደው ከቆይታ በኃላም «አፈር ስሆን ይህቺን ብቻ» እያሉ ሲያግደረድሩ። ከራዲዮ አሊያም ቴሌቪዥን ያላችሁን ካሰኛችሁ አንድ ጣቢያ ላይ አድርጋችሁ አዳምጡት(ከትህትና ጋር)። ዜናም በሉት ማህበራዊ ጉዳይ፣ ፖለቲካዊም ሆነ መዝናኛ፣ ስፖርት ወይም የዘፈን ግብዣ፣… የትኛውም መሰናዶ እየተስተናገደ ይሆናል። ታዲያ እያዳመጣችሁ ሳለ ከመሃል ከአማላይ ሽልማቶች ጋር «ጠጡ» የሚል ግብዣ ይቀርብላችኃል (በነጻ ይጠጣ ይመስል)። የእናንተን ባላውቅም ለእኔ ግን አብዛኛው ሰውና የመገናኛ ብዙሃኑ እየተመሳሰሉብኝ ነው። ምነው ቢሉ መዳረሻቸው አንድ ነዋ፤ መጠጥ። ይህንን ለማረጋገጥ ለምን አንድ ዳሰሳዊ ጥናት አንሰራም፤ ከመተግበራችን በፊት ግን በህሊናችን እንሞክረው። የአንድ ተቋም ሰራተኞች ስራቸውን ጨርሰው ሲወጡ ወደየት ይሄዳሉ የሚለውን እናጣራ። እንበልና 20 ሰራተኞች ካሉት ተቋም ምን ያህሉ፤ ወደ ቤታቸው፣ ወደ ትምህርት ቤቶች፣ የሃይማኖት ተቋማት፣ የመዝናኛ ቦታዎች፣… ይሄዳሉ? መቼም ከልምዳችሁ ተነስታችሁ ዋናውንም ባይሆን ተቀራራቢውን ምላሽ መስጠት ትችላላችሁ። እንደ እኔ ከሆነ በዛ የሚሉት በስራ የደከመ አካላቸውን ከቤታቸው ሳይሆን ከመጠጥ ጠርሙስ ነው የሚያሳርፉት። አንዳንዱማ ልማድ ስለሚሆንበት፤ የጠርሙስ አንገት ካልጨበጠ የኖረም አይመስለው። ኧረ እንዲያውም እስከ ቢራ ሰዓት ትጉህ የነበረው ሰራተኛ የሚበላሸው የመጠጥ ቤትን ደጃፍ ከመርገጡ ነው። ያው ሁሉም ነገር ደረጃ አለው አይደል፤ መጀመሪያ ጠጪው ጽዋውን ያነሳል፤ ከዚያ ጽዋው ሌላ ጽዋ ይጋብዛል፣ ሲደጋገምም መጠጡ ራሱ ጭልጥ አድርጎ ወደ ማይታወቅ ስፍራ ይወስዳል። እናማ የምታስበውን፣ የምትናገረውን፣ የምትሰራውንና የምትሆነውን አታውቅም፤ ከጸጸት ጋር እስኪነጋ ማለት ነው። ግን ከ፦ቱ በኃላ መገኛቸው እዚያው መሸታ ቤት ይሆናል፤ የሚገርመው ነገር እንደሚጎዳቸው እኮ ያውቃሉ፤ ነገር ግን ሱስ ስለሚሆንባቸው የሚያቆሙት መጠጡን ሳይሆን ስለመጥፎነቱ ማሰቡን ነው። የመገናኛ ብዙሃኑም የየዝግጅታቸው መዳረሻ የአልኮል መጠጦች ማስታወቂያ ነው። ጥሩ ጥሩውን ሲያቀብሉንና መረጃ ሲያስኮመኩሙን ቆይተውም አይደል መዝጊያቸውን «ጠጡ» የሚያደርጉት(ለዚያውም ከእነ ቤተሰባችን በምንከታተላቸው ጣቢያዎች)። እናሳ አይመሳ ሰሉም? አሁን እንኳን የብዙዎቻችን ፍላጎት የተሟላ ይመስለኛል (ለተወሰነ ሰዓት ጠጡ አትበሏቸው ተብለዋላ)። አዋጁን እንደ አዲስ ልነግራችሁ ፈልጌ አይደለም፤ በዚህ ላይ የታዘብኩትን ላካፍላችሁ በሚል እሳቤ እንጂ። ከሰሞኑ ለስራ ጉዳይ ጥቂት ኪሎ ሜትሮችን አቆራርጬ ነበር፤ ታዲያ በጉዟችንም ሆነ በመልሱ ከመኪናችን ውስጥ የደራ ክርክር ሲደረግበት የቆየው ጉዳይ አዋጁ ነበር። ለእኔ የሚገርም ለሆነብኝ ተቃውሞ እንደ መከራከሪያ ሲነሳ የነበረው ደግሞ፤ የመገናኛ ብዙሃኑ እና የስፖርት ክለቦች (ብሔራዊ ቡድንን ጨምሮ) በስፖንሰር እጥረት ሊዳከሙ እንደሚችሉ እንዲሁም ተጠቃሚው ስለ ራሱ ያውቃልና ነጋሪ አያሻውም የሚል ነው። ግን ግን ማስታወቂያው ለተወሰነ ሰዓት አይተላለፍ በመባሉ ይህ ሁሉ ነገር ከተወራ እንዲያውም አልኮል የተባለ ነገር እንዳይሸጥ የሚያደርግ ህግ ቢወጣ ምን ሊኮን ይሆን? እንዴት ይህንን ዓይነት ጉዳይ ተቃውሞ ሊነሳበትና የክርክር አጀንዳ ሊሆን እንደቻለ ግን አሁንም ድረስ ሊገባኝ አልቻለም። ስለ መዳከም የተነሳው እውነትነት ያለው ቢሆንም ትውልድን ከማዳን የበለጠ ሊሆን ግን አይችልም። ሰካራም ትውልድ ፈጥረን ሃገሪቷን ለማን ልናስረክብስ ነው? የማስታወቂያ ማጀቢያዎችን ሲዘምሩ («… ሳብ ግጥም» የሚሉ ህጻናት አልገጠማችሁ ይሆን?) የሚውሉና ማስታወቂያውን ቃል በቃል የሚሸመድዱ ህጻናትና ታዳጊዎችን የተመለከተ ለዚህ መደራደሪያ ያቀርባል ተብሎም አይጠበቅም። «እኛም ካልጠጣን» ብለው የሚያለቅሱ እና የተቀዳውንም ሰው «አየን፤ አላየን» ብለው የሚጨልጡም እኮ አሉ። የቀረበለትን ከማግበስበስ ባለፈ «የቱ ይጠቅማል፤ የትኛውስ ይጎዳል?» የሚለውን የመለየት አቅምም ሆነ ፍላጎት ያለው ትውልድ ገና አልተፈጠረም። ለዚህም ነው የአስገዳጅ አዋጅ አስፈላጊነት፤ «ተጠቃሚው ለራሱ ይወቅበት» የሚል ፍርጃ ግን ኃላፊነት የጎደለው ነው። እናማ ወገን በቆርኪ ልክ ማሰባችንን ትተን እይታችንን ማስፋት እንልመድ። አንድን ነገር «ተከለከልኩ» ብሎ ከማላዘንም ሌላ አማራጭ መፈለግ ጉብዝናችንን የሚለካ ይሆናል።አዲስ ዘመን የካቲት 11/2011ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "05de6fd054df8f259d5c1f9c8d10fa62" }, { "passage": "በተለምዶ እንቁላል ፋብሪካ ተብሎ የሚጠራው አካባቢ በመኪና ገበያነት ይታወቃል። ሰሞኑን ግን “ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው” እንዲሉ፤ የአካባቢው የመኪና ነጋዴዎች አዲሱ የኤክሳይዝ አዋጅ ረቂቅ ለተወካዮች ምክር ቤት ከቀረበ ጀምሮ “ባልተረጋገጠ እሳቤ ምክንያት ሽያጭ ከቆመ ወራት አስቆጥረናል::” ይላሉ። ከመሸጫዎቹ በአንዱ የአንዲት\nቶዮታ ቪትስ የኋላ\nበር ተከፍቶ በዕቃ\nማስቀመጫው ውሃ ተቀምጦበታል።\nአራት ወጣቶች እና\nሁለት ጎልማሶች ክፍት\nከተተወው የኋላ በር\nፊት ለፊት ከብበው\nተቀምጠው የያዙትን ውሃ\nእየተጎነጩ ያወራሉ። ስለገበያው\nሁኔታ ሲጠየቁ ቀደም\nሲል በሃዘን ስሜት\nሲነጋገሩ የነበሩት ሁሉም\nአንድ ላይ በቁጣ\nይናገራሉ:: “ገበያው\nሞቷል፤ በፊት አንድ\nመኪና ይሸጥ ከነበረበት\nበ40 እና በ50\nሺህ ብር ቅናሽ\nለመሸጥ ብንሞክርም እንኳን\nደፍሮ የሚገዛ የለም”\nይላሉ። የመኪና አስመጪው አቶ መሃመድ አወል እንደሚናገሩት፤ መኪና ሻጭ ብዙ ቢሆንም መኪና ገዢ ጠፍቷል። ቀድሞ የመኪና ማስገቢያ ግብር ጨመረ ተብሎ ሲወራ፤ እነርሱም በመኪና ዋጋ ላይ ጨምረው ነበር። አሁን ደግሞ “አዲስ ያልተነዳ መኪና የማስገቢያ ቀረጥ ቀንሷል” መባሉ ገበያውን አበላሽቶታል። በተጨማሪ ገዢው ህዝብም ሆነ የመኪና ነጋዴው ግብሩ በምን ያህል ቀነሰ ወይም ጨመረ የሚለው በትክክል አልገባውም፤ በዚህ ሳቢያ ገበያው ተበላሽቷል። ከራስ ደስታ ሆስፒታል የእንቁላል ፋብሪካን አደባባይ አልፈው ሲሄዱ በስተቀኝ ባለው የተንጣለለ ግቢ ውስጥና የዛፎች ጥላ ሥር ከ500 ያላነሱ መኪናዎች ተደርድረዋል። አብዛኛዎቹ ለአዲስ አበቤዎች የትራንስፖርት አገልግሎት መስጫነት የሚያገለግሉት “ስሪ ኤል” እና “ፋይፍ ኤል” የተባሉ ሚድ ባስ የቶዮታ ምርቶች ናቸው:: ሌሎቹ ወደ ክፍለ አገር በሚደረጉ ጉዞዎች ላይ በፍጥነት የሚሽከረከሩት “ሃይሩፍ” እና “ዶልፊን”፤ እንዲሁም ሌሎችም ዘመነኞቹ ብርማ ቀለም የተቀቡ መኪናዎችም ተደርድረዋል። በግቢው ውስጥ ከበር እንደገቡ ስምንት ሰዎች በሸራ የተወጠረች የጀበና ቡና ማፍያ መጠለያ ውስጥ ተቀምጠው፤ ገሚሱ የእጅ ስልኩን እየነካካ አንዳንዱ ፎቶ። አንዳንዱ ደግሞ ፌስቡክ ይመለከታል። የተወሰኑት እርስ በርሳቸው ያወራሉ። ፂመ ሸበቶው አለሙ\nበቀለ (ስማቸው የተቀየረ)\nእንደሚናገሩት፤ 500 መኪናዎችን\nይዟል ተብሎ የሚገመተው ግቢ የሚታወቀው መኪና ገዢ ሲመላለስበት ነበር። አሁን ግን እንኳን ገዢ ጠያቂ ጠፍቷል። በፊት መኪና ሲሸጥ የመኪና አስመጪው ብቻ ሳይሆን የቴክኒክ ፈታሽ፤ የመኪና ወንበር ነጋዴዎች፣ አሻሻጭ ወጣቶች እና ከሽያጩ ጋር ተያይዘው የሚመጡ የታክሲ አሽከርካሪዎች እና ረዳቶች ሳይቀሩ ስራ ያገኙ ነበር። አሁን እነዚህ ሰዎች ሁሉ ስራ አቁመዋል። “በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች ሰዎች በትራንስፖርት ችግር ይሰቃያሉ” የሚሉት የመኪና ሻጩ፤ እነርሱ ግቢ ውስጥ ያሉ 500 መኪናዎች በስራ ላይ ቢውሉ ችግሩን በማቃለል በኩል ከፍተኛ አስተዋፅኦ ሊኖራቸው ይችላል በማለት ይጠቁማሉ። ጨምረውም “እነዚህ መኪናዎች ከውጭ የገቡት ቡና ተሽጦ በተገኘ የውጭ ምንዛሪ ነው። የአገር ሃብት ናቸው። አገልግሎት መስጠት እያለባቸው ገበያ አጥተው ፀሃይ ላይ ተሰጥተው መዋላቸው ለአንድ ነጋዴ ብቻ ሳይሆን ለአገርም ኪሳራ ነው” በማለት ይናገራሉ። በተንጣለለው ግቢ ውስጥ ከተደረደሩት መኪናዎች በስተግራ ጉብ ባለው የድንጋይ ቤት ውስጥ በጠራራ ፀሃይ ገመድ እየዘለሉ ራሳቸውን ለማዝናናት ከሚሞክሩት የመኪና ነጋዴዎች መካከል አንዱ ወጣት ሙሉጌታ አወል ነው። እርሱ እንደሚናገረው፤ በመኪና ላይ “ግብር ሊጨምርም ሆነ ሊቀንስ ነው” ተብሎ መወራት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ገበያው ተቀዛቅዟል። ምንም እንኳን የአዋጁ አላማ ‘የአካባቢ ብክለትን ለመከላከል እና አገር ለመጥቀም ነው’ ተብሎ የተገለፀ ቢሆንም፤ ገበያውን ከማቀዛቀዝ አልፎ የመኪና ነጋዴዎችን እና ከመኪና ሽያጭ ጋር ተያይዞ የሚሰሩ ሰዎችን በሙሉ ጎድቷቸዋል። ጉዳቱ በዚህ የሚያቆም ብቻ ሳይሆን ወደፊትም ይቀጥላል የሚል ስጋት አለው። ወጣት ሙሉጌታ እንደሚናገረው፤ አዋጁ እና የግብር ማሻሻያው በደንብ ሲታይ የአገሪቱን ሁኔታ ያገናዘበ አይመስልም። አሁን ላይ የኢትዮጵያ መኪና አስመጪዎች “አዳዲስ መኪናዎች” ብለው የሚያስመጧቸው በዓለም አቀፍ ገበያ ብዙም ተፈላጊነት የሌላቸውን ነው። እነዚህ መኪናዎች ቶሎ ከጥቅም ውጪ የሚሆኑ እና የመለዋወጫ ዕቃ እጥረት የሚያጋጥማቸው ናቸው። መኪናዎቹ ከኢትዮጵያ የመንገድ ስሪት አንፃር ቶሎ የማርጀት ዕድል የሚያጋጥማቸው ከመሆናቸውም ባሻገር የሚገዙበት ዋጋም ቀላል ባለመሆኑ ዜጎች መኪና የመግዛት አቅም አይኖራቸውም። የተገዙትም ለጥቂት ዓመት አገልግለው ይቆማሉ። ይህ ደግሞ መኪና ገዢውን ብቻ ሳይሆን አገርንም የሚያከስር ነው።“ህዝቡ ያልተረዳው አንድ ነገር አለ:: በመሰረታዊነት መኪናን እያስወደደ ያለው የኤክሳይዝ ታክስ ሳይሆን ቅድሚያ የሚከፈለው የ35 በመቶ ቀረጥ ነው።” የሚለው ወጣት ሙሉጌታ፤ መኪናውን ሌላ አገር ሄዶ መግዛት ብቻ ሳይሆን የማስጫኛ፤ የመርከብ ማጓጓዣ፤ ጅቡቲ ላይ የተቀመጠበትም ሆነ ኢትዮጵያ ከገባ በኋላ የሚከፈሉ ክፍያዎች፤ ቢሮክራሲው እና አዲስ አበባ ላይ የመሸጫ ቦታ ኪራይ፤ እንዲሁም የአሻሻጭ ሰራተኛ እና ሌሎች ተደራራቢ ወጪዎች ዋጋውን የሚያንሩት መሆኑን ይናገራል። ዝርዝር የመተግበሪያ ደንብና መመሪያ ሳይወጣለት እንዲህ ያለ ለውጥ ያመጣው የኤክሳይዝ አዋጅ በሌላ ጎኑ የነጋዴዎቹን ስራ ገድሎባቸዋልና፤ “መንግስት አዋጁን ከመውጣቱና ወሬው ከመነዛቱ በፊት በጉዳዩ ላይ የመኪና አስመጪ ነጋዴዎችን ማወያየት እና የሚናገሩትን ማዳመጥ ነበረበት። ‘ነጋዴ ጥቅሙን ብቻ የሚያይ ነው’ ብሎ መደምደም አይገባም። ነጋዴም ዜጋ ነው። መንግስትን ጨምሮ ሌሎችም ሊያስቡለት ይገባ ነበር” ይላሉ።አዲስ ዘመን የካቲት 16/2012ምህረት ሞገስ", "passage_id": "9c7df9b5f57e88e70f6b80129e8dba33" }, { "passage": "ወቅቱ የበዓላት ሰሞን ነው። የአዲስ አበባ ጎዳናዎች ጭምር በድንኳን ጎጆዎችና በሐበሻ አልባሳት ደምቀዋል። የገናና የጥምቀት በዓላት መጣሁ መጣሁ ማለት ቀድመው የሚያበስሩ ይመስላሉ። ነፍሳችሁ በሐሴት ይሞላል። የማህበረሰባችን የደስታ ፍልቅልቅ ስሜት ሁሌም ሊያዩት ይናፍቃል፤ ያጓጓልም። ምነው ሁሌም በዓል በሆነ ያሰኛል። በዚህ ድባብ ውስጥ ሆነን ሽሮ ሜዳ ተገኘን። እኛም በዚሁ ስፍራ ተገኝተን በጥበብ አልባሳት የተንቆጠቆጡት የባህል ሱቆች የባህሉን ድባብ ከኢትዮጵያዊ ወግና ባህል ጋር አዋህደው የግብይት ሥርዓቱን እንዴት እያስኬዱት እንደሆነ፣ የሚስተዋለውን የገበያና የሸማች አቅም ሁኔታ እንዲሁም የባህል አልባሳቱን እየጎበኘን ነው።“ከአምስት ዓመት በፊት ጀምሮ ጥምቀት ሲደርስ ጥበብ እገዛለሁ። በማንኛውም ጊዜ አስቤበት መግዛት ትዝ ብሎኝ አያውቅም። ምናልባትም በልጅነቴ እናቴ ልብስ የምትገዛልኝ ሁሌም ለጥምቀት እንደነበረ ትዝ ይለኛል” ያሉት በሽሮ ሜዳ የባህል አልባሳት መሸጫዎች በሸመታ ላይ ያገኘናቸው ወይዘሮ ኤልሳቤጥ አለሙ ናቸው። ወይዘሮ ኤልሳቤጥ እንደሚሉት፤ በየዓመቱ የገበያው ሁኔታ ብቻ ሳይሆን የዲዛይኑም ሁኔታ ከሚጠበቀው በላይ ይለያያል። የሚገዙትን የጥበብ ቀሚስ አይነት ከቤታቸው ወስነው መጥተው ገዝተው አያውቁም። እዚያው መርጠው ቀልባቸው የወደደውን ነው የሚገዙት።አምና የገዙት የአበሻ ቀሚስ ዋጋው 4800 ብር ሲሆን ዘንድሮ ደግሞ 5300 ብር ነው የገዙት። ‹‹አውጥተው እስኪ እየው፣ ምርጥ ነው፤ እጃቸውን ክፉ አይንካው›› ሲሉ መርቀዋል። ‹‹ካየኋቸው ብዙ የጥበብ ሱቆች ውስጥ ዋጋቸው ብዙም የሚራራቅ አልገጠመኝም። ግን እኮ ሰው ብዙ አይለብስም። የአበሻ የጥበብ ቀሚስ ከሚለብሰው የ‹ቻይና ሱሪ የሚለብሰው በዝቷል›› ይላሉ ወይዘሮ ኤልሳቤጥ።‹‹በደመቁት የሐበሻ ቀሚሶች መካከል ተገኝቶ የማይደምቅ የለም›› የሚለው ‹‹አበበና ጓደኞቹ የባህል አልባሳት መሸጫ› ውስጥ በመሸጥ ላይ ያገኘነው አቶ ባህሩ ቀለመወርቅ ነው። አቶ ባህሩ እንደሚለው፤ በበዓላት ሰሞን የባህል አልባሳት መጠነኛ ጭማሪ ማሳየታቸው የተለመደ ነው። ዘንድሮም እስከ ሁለት ሽህ የሚደርሱ ጭማሪዎች በነባር የጥበብ ቀሚስ ዲዛይኖች ላይ የሚስተዋል ሲሆን ካለፉት ዓመታት አንፃር ብዙም አልጨመረም። ጤፍ የጨመረውን ያህል ግማሽ ጭማሪ የሐበሻ ልብሶች ላይ አለመታየቱን በንፅፅር የሚናገረው አቶ ባህሩ፤ በበዓላት ወቅት ብዙ አዳዲስ ዲዛይኖች ስለሚወጡ የእነሱ ዋጋ በጣም ከፍተኛው እስከ 30 ሺህ ብር እንደሚደርስ ተናግሯል። በማንኛውም ጊዜ እስከ አስራ አምስት ሺህ ብር ድረስ የሚገዙ ኢትዮጵያውያን አሉ።ነገር ግን ሰው የጥበብ ቀሚስንም ሆነ በአጠቃላይ የሐበሻ አልባሳትን የመግዛትም ሆነ የመልበስ ባህሉ አነስተኛ ነው። አሁን አሁን በተወሰነ ደረጃም ቢሆን መነቃቃቶች ይታያሉ። ለምሳሌ ባህላዊ የቡና (የጀበና ቡና) ቤቶች እየተበራከቱ በመምጣታቸው የሐበሻ ቀሚስም በአስተናጋጆች በኩል እየተለመደ ይመስላል። የባህል ኤግዚቢሽንና ባዛሮችም ጥሩ የትውውቅ አጋጣሚዎችን ይፈጥራሉ። ወደዘርፉ የሚገቡ በፈለጉት መንገድ የሐበሻ አልባሳትን የሚያዘጋጁ ወጣት ዲዛይነሮችም መኖራቸውን ወጣት ባህሩ አስረድቷል።‹‹ኢትዮጵያ የተዘጋጁ የባህል አልባሳት ችርቻሮ›› ሱቅ ውስጥ ደንበኞቿን በማስተናገድ ላይ ያገኘናት ወይዘሮ አለምነሽ ከበደ እንደተናገረችው፤ የባህል አልባሳት ሥራ ወቅታዊ ነው። የማህበረሰቡ የመጠቀም (የመልበስ) ልምድም እንደዚያው ወቅታዊ ነው። ለዚያ ሰሞን ግን አለ የተባለውን ምርጥ ሥራ ይዘን ለመቅረብ ጥረት እናደርጋን። አዳዲስ ፋሽን የሐበሻ ቀሚሶችን ከ20 እስከ 25 ሺህ ብር እና ዝቅተኛው ደግሞ እስከ ሁለት ሺህ ብር ድረስ እንደሚሸጡ ተናግረዋል። ወይዘሮ አለምነሽ እንደሚሉት የዲዛይኖቹ ብዛት በጣም በርካታ ነው። ሆኖም አዘውትሮ ስለማይለበሱ ሰዎች የሚስባቸውን ይመርጣሉ። የሚወዱት የቀለም ምርጫም አለ። በዋጋ ላይ የሚታዩት ጭማሪዎችም የተለመዱ ናቸው። በሌላ በኩል እነዚህ አልባሳት የኢትዮጵያዊ መገለጫዎቻችን በመሆናቸው በጋራ ማስተዋወቅ አለብን ይላሉ። መንግሥትም ከዚህ በተሻለ ደረጃ ዘመናዊ የስፌት ማሽኖችን በማቅረብ የጥልፍና የሽመና ባለሙያዎችን አሠራር ማሳደግ ቢችል ዋጋቸው ተመጣጣኝ ይሆናል፤ ባህላችንም ሳይደበዝዝ ይቀጥላል ብለዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 24/2012ሙሐመድ ሁሴን", "passage_id": "84537e7964ea52cfe079e2727720358b" }, { "passage": " ኧሯ! እንዴት ሆኖ እንዴት ሆኖ እኛንማ አይደፍርም! ብለን ነበር ደፈረን። በሩቅ ሆኖ የሰማነው ዜና ገስግሶ መጥቶ አጠገባችን ከደረሰ የወራት እድሜን አስቆጠረ። በሰው ሀገር ሲነገር፤ ሲወራ እኛ ዘንድ የማይደርስ መስሎን ተዘናግተንማል። እኛ ሀገር አይገባም ፤ ጥቁሮችን አይነካም በማለት እራሳችንን በማይሆን ተስፋ እያታለልን ቆይተናል። ቁርጡ ቀን ደርሶ በሀገራችን የቫይረሱን መገኘት እውነታ ሲነገር ሰምተን ላለማመን ያመነታነው ስንቶቻችን እንሆን? ታዲያ አስፈሪ ዝናውን አስቀድሞ በርካቶቻችንን ኮርኩሮ ሃሳብ በማሰንዘር ፤ ከሃሳባችን መደምደሚያ ሳንደርስ ከች ብሎ ጉድ ያደረገን እሱም አይደል ወይ ኮሮና። ስለ ቫይረሱ ያለን እውቀት እንደ ግንዛቤ የሚለያይ ነው። አንዳንዱ ህይወቱ ግድ ሰጥቶ ለራሱ ኖሮ ሌላውን ለማትረፍ የሚጥረው ነው። ሌላው ደግሞ ለራሱም ሆነ ለሌላው ግድ የሌለው ቢነገረው ቢዘከር ሰምቶ እንዳልሰማ አይቶ እንዳላየ የሚሆን ነው። ራሱን በመኖርና ባለመኖር መካከል ከቶ በደመነፍስ እንደሚኖር ሰው ቫይረሱ ምንም እንደሚያመጣ የሚናገርም ዛሬ ድረስ አልጠፋም። ሰውን ለማዳን ራሱን ያልሰሰተውን ተመልክተን እሰየው በርታልን ጓድ እንዳላልን ሁላ ፤ በግዴለሽነት የሚኖረውን ደግሞ በትዝብት እያየን ከማለፍ ለመምከር የሞከርን እንኖራለን። የሚጠነቀቀውም ሆነ ግዴለሹ፤ የአንዱ ጤንነት የሌላው መኖር ዋስትና ነው ። የሰው ልጅ በምድር ላይ የሚኖረው ለራሱ ብቻ አይደለም፤ ለሌሎችም ነው። አንዱ ከሌለ የሌላው መኖር ትርጉም አልባ ነውና ። ህይወት ጣዕም የሚኖራት በመኖር ነው። መኖር ትርጉሟ ሙሉ የሚሆነው አንዳችን ለአንዳችን በሚኖረን አብሮነት ፤ መረዳዳትና መደጋገፍ ነው። ለዚህ ዋንኛው ደግም የኔ ጤንነት ሲጠበቅ የጎረቤት፤ የአካባቢዬ ፤ የሀገር፤ የሁሉም ጤና መሆን ግድ ይላል ። ታዲያ አለመታዘዛችን ከምን የመነጨ ይሆን? ለመኖር ራሳችን ከመጠበቅ ሌላው አማራጭ ይኖር ይሆን። ታላላቆቻችን፤ አባቶቻችን ማድመጥ፤ መደማመጣችንን እሴቶቻችንን ማን ነጠቀን? ለምን ረሳነው? በራሳችን ፈርደን በሌሎችም የመጨከን አባዜን ከየት አመጣነው? የሰውን ልጅ ሳይመርጥ ከምድረ ገጽ እያጠፋ ያለው ይህ ጨካኝ ቫይረስን እንዴት ልባችንን ሊያደነድን ቻለ። ሰው የሚችለውን ነውና የሚታዘዘው እራሳችንን እንመርምር ለመለወጥ መትጋት አለብን። የማንችለውን ትተን የምንችለውን መምረጥ ፤ ዛሬን መኖር ለነገ ተስፋ ነው። የእኛ ጥንቃቄ ለወገን መሆኑ ማመን አለብን። ነጭ፤ ጥቁር፤ ዘመድ፤ ባዕድ እያልን ራሳችንን ሳንከፋፈል ከስጋት ራስን ጠብቆ በማስመለጥ አብሮ ማምለጥ ይቻላልና ነው። ካለበለዚያ ግን “ከኑግ ጋር ያለህ ሰሊጥ አብረህ ተወቀጥ” ከሆነ ጉዳይ የታሪክ ተወቃሽ መሆናችን አይቀርም። መቼም ቫይረስ በሀገራችን ከተከሰተ ማግስት ጀምሮ ብዙ ለውጦችን፣ አዳዲስ ነገሮችን ታዝበናል። ለመከላከል የሚረዱን እጅን በሳሙና ቶሎ ቶሎ በደንብ መታጠብን ፤ ፊት በእጅ አለመንካት፤ አካላዊ ርቀትን መጠበቅ በዋናነት ከህክምና ባለሙያዎች የሚሰጡትን ምክሮች ተግባራዊ ለማድረግ ተሞክሯል። ለራሱ ያለ ራሱ ተጠንቅቆ ሌላውን ለማዳን እየጣረ እየተጋ ታይቷል። ይገርማችኋል! ለዛሬ ትዝብቴ መነሻ የሆኑት ይህንን የሰሙ የማይመስሉ የሰፈሬ ወጣቶች ናቸው። በከተማችን የሚገኙ በርካታ ወጣቶች በጎ ተግባራት ላይ በመሳተፍ ከወገናቸው ጎን የቆሙበትን አይተናል፤ ሰምተናልም። የነገ የሀገሪቱ ተስፋዎች መሆናቸውንም አስመስክረዋል። የኔ ሰፈር ወጣቶች ግን ቫይረስ መኖሩን አልሰሙም!! በአንድ ላይ በጋራ በመሆን መጠጥ ይጠጣሉ ፤ ጫት ይቅማሉ፤ መንገድ ዳር ተዛዝለው በሚባል ሁኔታ ሆነው ያወጋሉ። የቫይረሱ የተከሰተ ሰሞን አልነበሩም፤ ጠፍተው ነበር ። እሰየው አልኩኝ፤ ራሳቸውን ለመከላከል ወስነው ቤት ለመቀመጥ የከተሙ መስሎኝ። አልሰሜን ግባ በለው አሉ። ለካ የቦታ ለውጥ በማድረግ ከሰው አይን ዞር ብለው ነበር። ታዲያ እኔም የግዴታዬን ለመወጣት ወደእነሱ አመራሁ። በእግዜር ስላምታ ተቀላቀልኳቸው። ስለቫይረሱ አስከፊነት የነሱ መጠንቀቅ ለሚወዷቸው ሁሉ ፤ ለወላጆቻቸው፤ ለሰፈራችን ሁሉም እንደሆነ አስረዳኋቸው። ለማዳመጥ ፈቃደኛ ባልሆነ ጆሮ ሰሙኝ ። መልስ አልሰጡኝም። አንደኛው እሺ አለኝ ቀልድ በተሞላበት ፌዝ ። በእውነት አመመኝ። ለምን አትተሳሰቡም እርስ በርሳችሁ እንኳን አትዋደዱም አልኳቸው። እሺ ሌላው ቢቀርስ ለምን አትታዘዙም አልኩት? አቀርቀረው ስልካቸውን መጎርጎር ተያያዙት ። ትቻቸው ስሄድ መታዘዝ ከመሰዋዕትነት ይበልጣል አልኩ ሰምተውኛል፤ ግን ዝምታን መርጠዋል። ለብቻዬ እንዳስብበት የቤት ስራ የሰጡኝ ወጣቶች ዞር ብዬ በማየት ጉዞዬን በሃሳብ ቀጠልኩ። “ለምን ይሆን የተከለከለ ነገር የሚያምረን?” አልኩኝ ለራሴ ። ወደ አፈጣጣራችን ተመለስኩ ለካ አዳምን ከገነት ያስባረረው አታድርግ የተባለው በማድረጉ ነው። እኛም ዛሬ ለመቅጽበት ለሚያልፍ ቀን ብለን አታደርጉ የተባልነውን በማድረግ በጎ ተግባር እንደፈጸመ ጀግና በየአደባባዩ እንታያለን። ማንንም መስማት አንፈልገም፤ እራሳችንን ብቻ ካልሆነ በስተቀር ፤ ራሳችንን በቅጡ አውቀን ብናዳምጥ ጥሩ ነው። በዓለም ያሉ ሀገራት እንደኛ አይነት ተው ተብለው የማይሰሙ ዜጎች በመያዛቸው ነው። ዛሬ ለመስማት የሚቀፍ ዜና እየሰማን የምንገኘው። እነሱ ቢጸጸቱም ወደ ኋላ ሊመልሱት የማይችሉት ነገር ሆኖባቸዋል። ለኛ ትምህርት መሆን አለባቸው። እኛ ላይ በቅድሚያ ያልተፈጸመብን መሆኑን እያመሰገን ከሰማነው፣ ካየነው ቀድሞ መገኘት የግድ ይለናል። ጊዜው ፈጣን ነው ፤ ዛሬ ላይ እንኳን ቆመን ነገን ለማየት በተሰጠን መልካም እድል መጠቀም አለብን። ያለመታዘዛችን ዋጋ እንዳያስከፍል መበርታት ያስፈልገናል። ለዚህም ቀኑ ዛሬ እንጂ ነገ አይደለም። የቤት ስራን ከወዲሁ በመፈጸም ለወገን አለኝታነታችን በመግለጽ እራስን ሆኖ መገኘት፤ ታዝዞ መታዘብ ማስተማር ፤ቀዳሚ ሆኖ ለሌሎች አርአያ በመሆን መስመሩን በመጥረግ ከመስመሩ ያፈነገጡትን መመለስ ይገባል። የዛሬ ሁላችንም አብሮነትና ትብብርን አንዱ ለአንዱ መኖር ግድ ይሆናል። ታላላቆቻችንን በማስቀደም እነሱን አድምጠን ከዚህ አስከፊ አደጋ ማምለጥ ይኖርብናል። አብረን ስንሆን፣ ስንተባበር፣ ስንደማምጥ፤ ስንረዳዳ ያምርብናል። ባህሩን አቋርጠን መሻገር እንችላለን። የሰው ልጆችን እየጠረገ ያለውን አስከፊ ወረርሽን ለመከላከል ወኔ አቅም ጉልበት ይኖረናልና ። መጪው ጊዜ መልካም ዜና የምንሰማበት ጊዜ ይሁንልን ። አዲስ ዘመን ሚያዝያ 19/2012 ወርቅነሽ ደምሰው", "passage_id": "d7ff0b5545f060e154c21078eb959f90" }, { "passage": "የአመላችን\nነገር አመላም ያበቅላል፤ አይጣል ነው። አሁን አሁንማ ከሰው (ከመሰሎቻችን) ጋር አላስኖር ሊለን ደርሷል፡፡ መሬት ጠበበችኝ ሊልም ይዳዳው ይዟል፡፡ አመል ሆኖብን ምን ቢዋብ፣ ቢሽቀረቀር፣ ቢለፋ፣ ቢታትር በዓይናችን አይሞላም፡ ፡ ፈጣሪ ይቅር ይበለኝ እንጂ ከአመል ጎዶሎነት የአካል መጉደል በስንት ጣዕሙ ይሻላል እቴ፡፡ እንደውም እኮ «የእኔ ብቻ ሸጋ» በሚያሰኝ ልክፍት የአመል በሽታ ታማሚዎች ሆንን እንጂ የዚችን አገር ጸጋ በልኩ ላይቋደስ የመጣ ያለ አይምሰላችሁ። ሆሆይ በል ጥናትክን አቅርብ እንዳትሉኝ፤ ተጠንቶ ተጀምሮ፤ በጥናቱ የሚጠናቀቅ ለውርርድ አታገኙም፤ አትሰቡት፡፡ «ላያስችል\nአይሰጥም» ነው ወይስ ላያስችል አይፈጥርም፡፡ አሁን ለመሬት የሚባለው፡፡ አዎ! ቻይማ ባትሆን የእኛ አመል ገመና ለስቅላት ይዳርገን ነበር። ይች ቻይ መሬትማ ሁልጊዜም የምትሆነው በልኳ ነው፡፡ በልካችን ያልተቃኘው የእኛ አመል፣ ልካችንን ያልተረዳነው እኛ ምስቅልቅል እያደረግናት እንጂ እሷማ የምትሆነውን አሳምራ ታውቃለች፡፡ ከልኳ በላይ የሆንባት የእኛው ጉድ ነው፡፡ አልክ አትበሉኝ እንጂ፤ እንደ እውነታው ከሆነ ካለ ልኩ የተፈጠረ የለም፡፡ ያለ ልኩ የሚኖርም ማንም የለም። ልኩን ማጤን ግን ተስኖታል፡፡ አመላችንን መዛኝ፣ ልካችንን ነጋሪ መስሪያ ቤት ባለመኖሩ እንጂ እኛማ ለጉድ የበቃን ነን፡፡ የሰው\nአመላችንን ክደን በውሻ (ለዚያውም በእብድ ውሻ) አመል ተክተናል፡፡ ውሾች ሆነናል ብል በስድብ ናዳ መዝገብ ላይ አታስፍሩት፡፡ እንደ ውሽልሽል የድንጋይ ካብ አመላችን ሊንደን መቃረቡን መፈተሽ ግን ደግ ነው፡፡ አዎ! ጥርጥር የለውም ማንነታችን ሊናድ ዘሟል። ኧረ እንደውም ሰውነታችንን የካድን «እባቦች» ሆነናል የሚል በአጽንኦት የታዘበ አይጠፋም። በሚያመዝነው ባህሪያችን ተሰልቶ እንስሳነታችን ይመደባል፤ ይፈረጃል፤ ቢባል ጉዳችን እስከ አናታችን ድረስ ነው፡፡ ፍርጃ ነው። ግንቦት 7 እና ኦነግ የተሟሹበትን ፈርጀ ብዙውን አፈራረጅ አላልኩም፡፡ «በፕሮፌሰር\nእከሌ፣ በዶክተር እከሌ ጥናት እንደተረጋገጠው» ብለህ ምንጭ ጥቀስ የሚል ስለራሱ አመል ነጋሪ የሚናፍቅ አይጠፋም፡፡ ኧረ የተጸውኦ ስማቸውን ባታነሳም በወል ስማቸው እንኳን «የዘርፉ አጥኚዎች» እንዳሉት ብለህ በእነሱ የብዕር አንደበት የእኛን አመል ንገረን የሚልም ይኖራል። ብዙ ነገር እኮ ተዛንፎብናል ጎበዝ!፡፡ በዓይናችን የምናየውንና በየዕለቱ የምንሆነውን ተግባር መዝነን ቆም ብለን በሰውኛ አስተሳሰብ ከማጤን ይልቅ በጆሮ በኩል የመጣን ወሬ ያለአንዳች ልኬት ፍጹም እውነት አድርጎ ማሽሞንሞን የምንወድ አመላሞች ብዙ ነን፡፡ አመላችን\nየደረሰበትን የክፋት ጥግ መርምሮ ለመረዳት የተሻለ የአመል ሊቅነት አይጠይቅም። ወደ ሰውነት መመለስ በቂ ነው፡፡ ሰው ስንሆን ሰው ይታየናል። (ታላቁ ሙፍቲ እንዳሉት) አጃኢብ የሚያሰኘው ደግሞ በሕዝብ አገልጋይነት ካባ ውስጥ ተጠቅልለን የምንጦር የመንግሥት ሠራተኞች ሺ አመለኛ መሆን ነው፡፡ በእኛ የአመል ክፋት ስንቱ ግዑዝ የመስሪያ ቤት ሕንፃ ጭምር አመላም ሆኗል፤ በአመላምነቱ ታውቋል፡፡ ሠራተኛው በአመላምነቱ እስከ «አንቱ» ክብር ሾልኮ የተቆናጠጠ ብዙ ነው፡፡ የበርካታው ሺህ አመላምነት ግን «አይ አመል እቴ!» ተብሎ የሚታዘንለትና መሳለቂያነትን ያተረፈ ነው፡፡ ክፉ አመላምነት፡፡ በተከፈተችው ጉሮሮው የሚወረውርባት ቁራሽ ያጣ እስኪመስለው ድረስ በፍርኃት ተንጦ ነፍሱን ማሸነፍ ተስኖት አመል ያበቀለ ቀዥቃዣ አመላም፡፡ የዚህ\nዓይነቶቹ «ሰው መሳይ በሸንጎ» የአመል ምድብተኞች ተርታ ውስጥ ይሰለፋሉ፤ ይካተታሉ፡፡ ባልታወቀው ደረጃ መዳቢ እንደተገለጸው ተብሎ ይታወቅልኝ፤ ይዘገብልኝ፡፡ በእርግጥ ለሌሎች የነፍስ ከፍታ የራስን ነፍስ ከማሳነስና ከማሸነፍ በላይ መስዋዕትነት የለም፡፡ ያኔ ሚዛኑ ሰውነት ይሆናል፡፡ ሰው መሆን እንልመድ፡፡ ለሩብ ምዕተ ዓመት ያህል ከመንግሥት ሥራ ተጣብቶ የኖረ አንድ «ሞዴል አገልጋይ» የሲቪል ሰርቪስ ተሸላሚ ባልደረባዬ ሹክ ያለኝን ሀሜት አስታወሰኝ፡፡ «በሞቴ ንገረን የሚል ከመካከላችሁ አንድ ሰው እንኳን አይታየኝም?» ተውት፡፡ እኔም\n«ከዓይን ይልቅ የጆሮ አመላም» ስለሆንኩ የተሰማችሁን ስሜት ነገ እሰማዋለሁ፡፡ ወሬ ዬን ግን ቀጠልኩ፤ ደግሞ ለማውራት ማን አህሎኝ፡፡ ሰውዬው ምን አለኝ መሰላችሁ ‹‹ ከሺ ባለ ማዕረግ ፤ ሺ አመለኛ ሰው ሥጋውና ጎጆው የደነደነ ነው›› አትሞኝ። ብሎ የራስ ጸጉሬን አሸት አሸት አደረገኝ፡፡ አዎ! ሺ አመልን ተላብሶ ከአመለኞች ጋር መራመድ ይቻ ላል፤ተችሏልም፡፡ ግን ሰው መሆን አያስች ልም፤ ሰው መሆንንም አይሰጥም፡፡ ሥጋ ሰውነትን ያስክዳል። ሰውዬው ይሄን የታዘበ በት ያ ወቅት ብዙ ዲግ ሪዎች ለመደርደር መማሰን አለበለዚያም በበርካታ ዘርፎች መመረቅ ገንዘብ አያስገኝም፡፡ ይልቁንስ የበርካታ አመሎች ባለቤት መሆን ተሽሏል ነው ነገሩ፡፡ አዎ! አመላችን ሰውነታችንን አስክዶናል። ያባይሆንም እንዲህ እርስ በእርስ መናከሳችን፣ መተማማታችን፣ መቋሰላችን እና መጋደላችን እየበረታ ባልሄደ ነበር፡፡ የሰው ሕይወት መጥፋት ኖሮበት አይሳቅም እንጂ እኮ የአመላችን ጣጣ በሰላሳ ሁለት ጥርስ የሚያንከተክት ነው። እንጂማ ሰው እንሁን፤ ሰውነትን እንላበስ ብለው ሆነው የተገኙ መሪ ከዶክተሩ በላይ ሰውነት ላሳር ነው። ነገሩ\n‹‹ፈረስ ያደርሳል እንጂ አይዋጋም›› ነው፡፡ ‹‹ነገርን ነገር ያነሳዋል›› ነውና የአበው ብሂል የተከበሩት ታላቁ የእስልምና እምነት መሪ ሙፍቲ ሐጅ ዑመር ኢድሪስ ከተናገሩት አስገራሚ ነጥብ ላካፍላችሁ ወደድኩ፡፡ ‹‹የሕዝብ መሪዎች ያለወቅታቸው፣ያለ ጊዜያ ቸው፣ያለሰው ብቻቸውን ምጡቅ ሆነው ይፈጠራሉ። የዚህ አይነት ክስተት ሲገጥም ምርጫቸው መምከር፣ ተው ማለት፣ መለመን፣ መታገስ፣ መቻልና ብቻቸውን ማልቀስ ይሆናል እጣቸው›› ይላሉ፡፡ በእሳቸው\nእምነት ዶክተር አብይ አህመድ በዚህ ረገድ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ የእሳቸው አይነት ሰው የሆነ መሪ ከዚህ በፊት አላየሁም፤ ከዚህ በኋላም ይመጣል ብዬ አላስብም። ከሁሉም በፊት ‹‹ሰውነት ይቀድማል፤እስኪ ሰው እንሁን›› ብለው ከንግግራቸው እኩል እንባቸው በጉንጫቸው ኮለለለለለ…ልል ብሎ ሲወርድ በአይኔ በብረቱ የተመለከትኩት መቼም አይረሳኝም፡፡ እናም ሰው እንሁን፡፡ የማያሳፍር ሰውነት ይኑረን፡፡አዲስ\nዘመን  ግንቦት 1/2011በሙሐመድ\nሁሴን", "passage_id": "5ddd4414eb73e0b983be98a89125d8f4" } ]
7ca6dd1f1e94a2f4b788a5c0fee8e87c
184c06230b785507685899e472310128
ልጃገረድነትን ማስመሰል የቻለው የ40 ዓመት ጎልማሳ
ስለ አንድ ነገር አይቶ መናገር ይቻላል፤ ሰምቶም እንዲሁ። አንዳንዴ ግን ያዩትንም የሰሙትንም ማመን ይከብዳል። ኦዲቲ ሴንትራል በቅርቡ ይዞት የወጣ መረጃ እንዳመለከተው፤ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት የጃፓን ልጃገረድ የሚመስል ሰው፣ በመካከለኛ እድሜ ላይ የሚገኝ አባወራ ነው። በዊኪፒዲያ ላይ እንደተጠቀሰው፤ ታኩማ ታኒ የተባለው ይህ ጃፓናዊ ድምጻዊ የተወለደው እኤአ በ1977 ነው። ይህ መረጃ ግን ይህን ሰው በፍጹም አይገልጸውም። ሁሉም የግለሰቡ ምስሎች ተማሪ ልጃረገድ ነው የሚመስሉት። ታኩማ ከወጣትነቱ አንስቶ ለኪነጥበብ ከፍተኛ ዝንባሌ ነበረው። ገና በህጻንነት እድሜውም ፓያኖ እና የድምጽ መሳሪያዎችን አጥንቷል። በመለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ የትምህርት እድሜውም ግጥም መጻፍ ጀማምሯል። በ28 ዓመቱ ደግሞ ድምጻዊ በመሆን በተዋቂ የጃፓን ባንድ ውስጥ ሰርቷል። ታኩማ በ34 ዓመቱ ደግሞ ልጃገረድ ተማሪ ለመምሰል ይወስናል። ከዚያም ጊዜ አንስቶ ይህን ማስመሰሉን በሚገባም ያደርገዋል። የ40 ዓመት ጎልማሳ በሆነበት በአሁኑ ወቅት ሳይቀር ልጃገረድ መምሰል በሚገባ ችሏል። በዚህም ብዙዎችን በማህበራዊ ሚዲያ እስከ ማደናገር ደርሷል። በህይወቱ ስኬታማ ከሆነባቸው ክንውኖቹ መካከል ልጃገረድ በመምሰል ያከናወናቸው ይበልጣሉ ያለው መረጃው፣ 1 ነጥብ 62 ሜትር እንደሚረዝም፣ 47 ኪሎ ግራም እንደሚከብድ፣ የጫማ ቁጥሩም በአማካይ ከሚታወቀው ቁጥር ያነሰ መሆኑን ያብራራል፤ ይህም ልጃገረድ ለመሆን ያደረገውን ጥረት እንዳሳካለት ይጠቁማል። መረጃው እንዳመለከተው፤ ታኩማ ልጃገረድ ለመምሰል ሲል ሜካፕ መጠቀሙ እንዲሁም ፎቶ ግራፎቹ እጅ ስራ ያያቸው መሆናቸው የማይካድ ቢሆንም፣ ለተላበሰው የልጃገረድነት ባህሪ የዓመታት ልምዶቹ ከፍተኛ ስፍራ የሚሰ ጣቸው ናቸው። አመናችሁም አላመናችሁ ይህ ጥረቱ፣ የ40 ዓመት ጎልማሳውን ታኩማ የተለያዩ ሙያዎች ባለቤት እንዲሆን አስችለውታል። ያለው መረጃው፣ በዚህ የልጃገረድነት ገጸ ባህሪው በጃፖን የቴሌቪዥን ጣቢያዎች በተደጋጋሚ ለመታየት እንዲሁም የፉጂ ቲቪ ቫይኪንግ የአልባሳት ውድድር ሽልማትን በማሸነፍ ለመሸለም በቅቷል። ሙዚቀኛ ብቻ አይደለም። አቱኮስቬት ቶክዮ የተሰኘ የሴቶች ልብስ ፋሽን በመመስረትም ስራ ፈጠሪ መሆን ችሏል፤ ልብሶቹን በማስተዋወቅም በሞዴልነት ይሰራል። ልጃገረድ መመሰል መቻሉ በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነት እንዲያገኝ አስችሎታል። በዚህ የተነሳም ብዙዎች ታኩማን የ40 ዓመት ሰው እንዲሁም ባለትዳር አርገው እንዳይቀበሉት አርጓል። እኤአ በ2016 ተማሪነት በተላበሰው መስሉ ህጻን አቅፎ የተነሳውን ፎቶ እና ‹‹እኔ አባት ነኝ›› የሚል መልእክት በማያያዝ በኢንተርኔት የለቀቀው መረጃም ብዙዎችን አስደንግጧል። ‹‹በህይወት ዘመንህ ምን መስራት እንዳለብህ ለሰዎች እያሳየሁ ነው›› ያለው ታኩማ፣ ‹‹ሌሎች ስለአንተ አለባበስና ስለመሳሰሉት ምን ይላሉ ብለህ እንዳትፈራ›› ሲልም ያሳስባል። የምትለብሰው ከእድሜህና ከጾታህ ጋር የሚሄድ እና የማይሄድ ስለመሆኑም ብዙም ትኩረት አትስጥ ያለው ታኩማ፣ ህይወትን በመሰለህ መንገድ ምራ ሲልም ያስገነዝባል። አዲስ ዘመን ጥር 26/2012
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=26632
[ { "passage": "የፖለቲካ ትንተና አላዋጣህ ስላለኝ የፍቅር ትንተና ልገባ ነው (ፍቅር ገራገሩ ማንም እንደፈለገው የሚተነት ነው!) ‹‹ግን የፖለቲካ ተንታኝ ነበርክ እንዴ?›› የሚል ካለ፤ አዎ የፖለቲካ ተንታኝ ነበርኩ! ‹‹ደግሞ አንተ ምኑን አውቀኸው!›› ብሎ ጥያቄ የሚያስከትል ካለ፤ ወዳጄ ፌስቡክ ላይ ፖለቲካ ለመተንተን ምንም እውቀት አይጠይቅም ነው መልሴ! ለማንኛውም አሁን አውቄም ይሁን ሳላውቅ ፖለቲካ አልተነትንም! በቃ ከዚህ በኋላ ጅንጀና ነው የምተነትን። በነገራችሁ ላይ ጅንጅና እና ፍቅር ይለያያል (ክፋቴ ግን ልዩነቱን አላብራራም) ትንታኔው ተጀምሯል። በነገራችሁ ላይ እልም ያልኩ ውሸታም ነኝ። ያቺንም ስጀነጅን ሚስት የለኝም፣ ያቺንም ስጀንጅን ሴት አናግሬ አላውቅም፣ ያቺንም አንቺ ነሽ የመጀመሪያዬ ነው የምላቸው (አቤት ቢተዋወቁ እንዴት ጉዴ ይፈላ ነበር)። ችግሩ ሼል ለሰሪው ሆነና ከሁሎችም ጋር አልፀናልኝም (ድሮስ አጭበርባሪ ሊፀናለት ነበር!) ለነገሩ ይሄ በእኔ\nብቻ ያለ ችግር\nአይደለም። ራሳቸው በምጀነጅናቸው\nሴቶችም ያየሁት ችግር\nነው። እንዲያውም አንዱን\nገራሚ አጋጣሚ ልንገራችሁ።ውይ! ለካ አሁንም የኔው አጭበርባሪነት ይቀድማል። በመጀመሪያ ለማጭበርበሪያ ብየ በስሜ ያልሆነ ሀሰተኛ የፌስቡክ አካውንት ከፈትኩ። ለነገሩ ይሄንንም ያደረኩት ወድጄ አይደለም። በትክክለኛው ስሜና በራሴው ፎቶ እምቢ ስላሉኝ ነው (የደረስኩበት ነገር እነርሱም ውሸታምና አጭበርባሪ እንደሚወዱ ነው) በትክክለኛው አካውንቴ ሳወራ አይመልሱልኝም፤ አንዴ ቢመልሱልኝም አይደግሙትም። በማጭበርበሪያው አካውንቴ የሚከተለውን ምርጥ የስለላ ሼል ሠርቸበታለሁ። አንዲት ቆንጂዬ ልጅ በትክክለኛው አካውንቴ መጀንጀን ጀመርኩ። ባል አለኝ ብላ እምቢ አለችኝ። ሌላኛዋ ደግሞ ፎቶዬን ካየች በኋላ ‹‹ሂድ ወደዚያ ምን ይመስላል! ቆረቆንዳ!›› ብላ ሰደበችኝ። በተለይ በዚችኛዋ የከፋ ቂም ያዝኩባት! ሁለቱንም በማጭበርበሪያው አካውንት\nመጀንጀን ጀመርኩ። ስሳደብ\nይስቁልኛል፣ ነውር የሆነ\nነገር ሳወራም ይስቁልኛል።\nአሁንስ ብሎክ አደረጉኝ\nብየ በጣም ነውር\nየሆነ ነገር ስልክላቸው\nበጣም ይስቁልኛል። ይሄ\nነገር እንዴት ነው?\nበጨዋነትና በቁም ነገር\nሳወራ ዝም ይሉኛል፤\nእንዲያውም ይባስ ብሎ\n‹‹እስኪ አትጭቅጭቀኝ!›› ብለው\nኩም ያደርጉኛል። ከዚያ\nነገሩን ስገምት ለካ\nየሚያውቁትን ሰው ስለሚያፍሩ\nእንጂ እንዲህ አይነት\nነውር ነገር ያስቃቸውዋል\nማለት ነው አልኩ።\nለነገሩ ስለማያውቁኝ ምን\nይጃጃላል እያሉ እየሳቁብኝም\nይሆናል። እስኪ ነገሩን\nበቁም ነገር ልሞክረው\nብየ ደግሞ ሞከርኩትበዚህ ውስጥ ያጠናሁት የአገራችንን ፖለቲካም ጭምር ነው። ከትክክለኛ ነገር ይልቅ የማስመሰል ነገር የበለጠ ተከታይና ተወዳጅነት አለው። ከተረጋገጠ ወሬ ይልቅ አሉቧልታ ተፅዕኖ ፈጣሪ ነው። ማነው፣ ምንድነው፣ እንዴት ነው… ብሎ የመጠየቅ ባህል የለንም። ውይ! የተውኩትን ፖለቲካ\nገባሁበት አይደል? እናላችሁ\nከአንደኛዋ ጋር እልም\nያለ ፍቅር ውስጥ\nገባን። ይቺ በማጭበርበሪያው\nአካውንቴ እልም ያለ\nፍቅር ውስጥ የገባችዋ\nልጅ በትክክለኛው ስሜና ፎቶዬ ‹‹ባል አለኝ›› ያለችኝ ናት። በማጭበርበሪያው አካውንቴ እንዳወራነው ገና አላገባችም፣ ኧረ እንዲያውም ‹‹ወንድ ሚባል ነገር አላውቅም›› ነው ያለችኝ። ቆይ ይቺን እዚህ ላይ ያዝ አርጓትና ሌላ ገጠመኝ ላስገባ (ይቅርታ ድንገት ትዝ ስላለኝ ነው) በትክክለኛው አካውንቴ ጓደኛ አለኝ ያለችኝ ሌላኛዋ ደግሞ በሀሰተኛው እያወራን ምንም ጓደኛ የለኝም፤ ወንድ የሚባል አላውቅም አለችኝ፤ ‹‹እና ታዲያ ድንግል ነሽ ማለት ነው›› እላታለሁ ‹‹ሰገጤ ፋራ!›› ብላኝ ብሎክ አደረገችኝ። በዚችኛዋ ስለተቀጣሁ ድጋሜ እንዲህ አይነት ጥያቄ ጠይቄ አላውቅም። ያቺን ነገር ይዛችሁ\nቆያችሁኝ? እናላችሁ ባለትዳር\nነኝ ካለችኝ ልጅ\nጋር ምን አይነት\nወንድ ትወጃለሽ? ምን\nአይነት ሴት ትወዳለህ\nስንባባል ቆየን። እልም\nያለ ፍቅር ውስጥ\nገባን። ስለትዳር ማውራት\nተጀመረ። ሁለታችንም የማጭበርበር\nልምዱ ስላለን የምናወራው\nበጥንቃቄ ነው። እንዲህ\nእንዲህ እያልን ቤቴ\nነይ፣ ቤትህ ልምጣ\nየመባባል ደረጃ ላይ\nደረስን። እዚህ ላይ\nግን አንድ ምክር\nመለገስ አማረኝ (የምር\nይቺኛዋን ምክር ግን\nበቁም ነገር ያዙልኝ) ብዙ ፍቅረኛሞች ከተዋወቁ በኋላ ወደ እሱ ቤት ወይም ወደ እሷ ቤት መሄድን አይፈልጉም። ከሴቶች እንደምሰማው ወንዶች ቤታቸውን ማሳየት አይፈልጉም ነው የሚባል፤ ከወንዶች እንደምሰማው ደግሞ ሴቶች ለመግደርደር ሲሉ ቤት መሄድ አይፈልጉም ነው። ቤቴ መጣች ይለኛል ብሎ ከመፍራት ይመስላል። እዚህ ላይ ግልጽ መሆን አለባቸው። ግደለሽም ሳትፈሪ ‹‹ቤትህ እንሂድ›› በይው። አይ ቤቴማ አንሄድም ካለሽ ይሄ ሰው ቤቱ ሚስት አለው ማለት ነው፤ ወይም ሌሎች ሴቶች ስለሚያመላልስ ጎረቤትና አከራይ ምን ይለኛል ብሎ ይፈራል ማለት ነው። አንች ብቻ ብትሆኝ ኖሮ ግን እንዲህ አይጨነቅም! እርግጥ ነው ቤት መሄድ የመተማመን መጨረሻ አይደለም! ኧረ የራሳችሁ ጉዳይ ወደራሴ ገጠመኝ! በትክክለኛው አካውንቴ እምቢ ብላ በማጭበርበሪያው እሺ ካለችኝ ልጅ ጋር ተጃለስን (አራዳነኛ ለምን ይቅርብኝ) እላችኋለሁ። ፍቅራችን ተጧጧፈ፤ እንዲያውም በኋላማ ስንበላ ስንተኛ ሁሉ መፃፃፍ ሆነ። ‹‹የኔ ማር ቤት ገባክ?›› አዎ ገብቻለሁ ‹‹የኔ ማር ራት በላክ?›› አዎ በላሁ ‹‹የኔ ማር\nተኛክ?››….. የተጠየቅኩትን\nሁሉ አዎ ነው።\nፍቅራችን እንዲህ ተጧጡፎ\nልንገናኝ ተቀጣጠርን፤ ትዝ\nቢለኝ ለካ በትክክለኛው\nአካውንቴ ታውቀኛለች። ጎበዝ ይሄን ነገር በቁም ነገር መቋጨት ይሻላል። በዚህ ዘመን ፍቅር የለም ለምትሉ ፍቅርን ያጠፋው ፌስቡክ ነው። መተማመን ጠፍቷል፤ ሁሉም እንደራሱ እየመሰለው ሌላውንም አያምንም። በዘጠኝ አካውንት የሚያጭበርብር ሰው ሌላውን ሊያምን አይችልም። በትዳሩ ላይ የሚወሰልት ወንድ ሚስቱን ሊያምን አይችልም፤ በትዳሯ ላይ የምትወሰልት ሴት ባሏ ጸሎት ቤት ቆይቶ ቢመጣ ልሹ ከመጠጥ ቤት ነው የመጣህ ብላ ድርቅ ልትል ትችላለች። ልሹ ታማኝ ያልሆነ ሰው ሌላውን አያምንም!አዲስ  ዘመን  ቅዳሜ\nመጋቢት 21/2011በዋለልኝ አየለ ", "passage_id": "e54af5cdac9a3b0abdd8e9a1a4fa22a6" }, { "passage": "የወንጀል ዓይነቱ የብዛቱን ያህል ሰፊ ነው፡፡ ሰዎች በሰሯቸው ወንጀሎች ምክንያት ተገቢውን ፍርድ አግኝተው ዘብጥያ ሲወርዱ ጥቂት የማይባሉት ደግሞ በሰሩት ወንጀል ከህሊናቸው ጋር ሙግት ገጥመው ተሸሽገው ይኖራሉ፡፡ ዞሮ ዞሮ ግን ፕላኔታችን ከቤት ሰብሮ ስርቆት እስከ ገንዘብ ዝርፊያ፣ ከአስገድዶ መድፈር እስከ ግድያ፣ በርካታ ወንጀሎችን አሁንም ማስተናገዷን ቀጥላለች፡፡ይሁን እንጂ አንዳንድ ጊዜ የወንጀል ድርጊቶች በአሰቃቂነታቸው ወደር የማይገኝላቸው በመሆኑ በርግጥም በሰው ልጅ ስለመፈፀማቸው የሚያ ጠራጥሩ ሲሆን፣ ሌሎች የወንጀል ዓይነቶች ደግሞ ያልተጠበቁና እስካሁን ተፈፅመዋል ተብለው የማይታሰቡ በመሆናቸው የሰዎችን ትኩረት ይስባሉ፡፡ ከሰሞኑ በአገረ ቻይና ተፈፅሞ የተገኘው የወንጀል ዓይነትም ይህንኑ የሚያረጋግጥ ይመስላል፡፡\nኦዲቲ ሴንትራል ከሰሞኑ ባወጣው መረጃ መሰረት የ41 ዓመት ዕድሜ ያለው ቻይናዊ ዋንግ ፌንግ ሳይማር ሆነ እንጂ ፖሊስ የመሆን የረጅም ጊዜ ህልም ነበረው፡፡ ጎልማሳው ሳይማር ፖሊስ የመሆን ህልሙ ከንቱ ሆኖ አልቀረም፡፡እንደዘገባው ከሆነ የዋንግ ፖሊስ የመሆን ህልም እውን የሆነው ከ12 ዓመታት በፊት ወንድሙ በገባበት የብድር ዕዳ ፍርድ ቤት ቀርቦ ጠበቃ በፈለገበት ጊዜ ነበር፡፡ በወቅቱ የወንድሙ ጠበቃ ዋንግ ፍርድ ቤት እንዲቀርብና ለወንድሙ ምስክር እንዲሆን ይጠይቀዋል፡፡ ዋንግ ጠበቃውን በፍርድ ቤት ካገኘው በኋላ ፖሊስ እንደሆነና በአገሪቱ በሚገኝ አንድ ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ እንደሚሰራ በሃሰት ይመሰክራል፡፡ ማታለሉ ሰርቶለት ይህንኑ የማታለል ተግባር በሌሎች ሰዎች ላይም መሞከር ይጀምራል፡፡ ለጓደኞቹና ለሚቀርባቸው ሁሉ ፖሊስ እንደሆነ በመንገር የተሳሳተ የፖሊስ የደምብ ልብስ በመግዛት፣ ካቴና በመያዝና መታወቂያም ጭምር በማዘጋጀት የፖሊስነት ሙያውን ሀ ብሎ ይጀምራል፡፡ዘገባው እንደሚለው በ2011 እ.ኤ.አ ዋንግ በኋላ ሚስቱ ከሆነችው ከ ዢያ ሉ ጋር ይቀ ራረባል፡፡ ዋንግ በጓደኛው አማካኝነት ጂያዢንግ በተሰኘው የወንጀል ምርመራ ቢሮ እንደሚሰራ ይነግራታል፡፡ እርሷም ዋንግ በሚነግራት ልብ አንጠልጣይ የወንጀልና የፖሊስ ምርመራ ታሪኮች መመሰጥ ትጀምራለች፡፡ ዋንግ ምንአልባትም በምክትል የፖሊስ ኃላፊነት ቦታ ላይ ሳይሆን እንዳልቀረም ታምናለች፡፡ይሁን እንጂ ግንኙነታቸው እያደረ ሲጠነክር ቤተሰቦቿ ዋንግን መጠርጠር ይጀምራሉ፡፡ ከአክስቷ ልጅች ውስጥ አንዱ ዋንግ በፖሊስ ሙያ ስለመመረቁ ለማረጋገጥ የቻይና የፖሊስ አካዳሚን ቢጠይቅም ስለዋንግ አንድም መረጃ ሳያገኝ ይቀራል፡፡ ዋንግ ታዲያ በምላሹ በቻይና ወንጀል ፖሊስ አካዳሚ ትምህርት እንደጀመረና ሌላ መታወቂያ እንደቀየረ ለሚስቱ ይነግራትና አምናው ሚስቱ ለመሆን ትስማማለች፡፡በጋብቻው ቀን አንድ የዋንግ ቤተሰብና የሥራ ባልደረባ ብቻ መገኘት ያስገረማቸው የሙሽሪት ቤተሰቦች ይህ ለምን እንደሆነ በጥርጣሬ ዋንግ እንዲያብራራላቸው ይጠይቁታል ይላል ዘገባው ሲቀጥል፡፡ ዋንግም ከረጅም ዓመታት በፊት አብዛኛው ቤተሰቡን በሞት እንደተነጠቀ፣ በአሁኑ ወቅት ከቀሩት ቤተሰቦቹ ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት እንደሌለውና ሁሉም የሥራ ባልደረቦቹ በሌላ ከፍተኛ የሰርግ ሥነ ሥርዓት ላይ ለመታደም እንደሄዱ በመግለጽ እውነታውን ይሸመጥጣል፡፡ ከሠርጉ በኋላም ዋንግ ጥብቅ የሆኑ የወንጀል ምርመራ ጉዳዮችን እንደሚመረምርና ይህን ለማንም እንዳትናገር ለባለቤቱ አስረግጦ ይነግራታል፡፡ዋንግ ሁሌም የፖሊስ የደምብ ልብሱን በመልበስ ወደሥራ ስለሚሄድ፣ ያለማቋረጥ ስለወንጀል ጉዳዮች ስለሚያወራና በተደጋጋሚ ግዳጅ አለብኝ በሚል ለቀናት ቆይቶ ስለሚመለስ ሚስት ይህ ሁሉ እንግዳ ነገር መስሎ አልታያ ትም፡፡ እንዳውም ፖሊስ በተጨማሪ ሰዓትም ጭምር ግዳጅ ተሰጥቶት ይሰራል ሲባል ስለምትሰማና የዋንግ ድርጊትም ከዚህ የተለየ ባለመሆኑ በእርሱ ድርጊት ብዙም አልተደነ ቀችም፡፡ የዋንግ ሚስት የማታወቅው ነገር ቢኖር ሰውዬው ለዓመታት በሙያው ሲያጭበርብር መቆየቱንና በዚህ ቆይታው ሰፊ ልምድ መያዙን ነው ይላል ዘገባው፡፡\nዋንግ የሀሰት ፖሊስነቱን ለ12 ዓመታት በሚገባ ለማስጠበቅ ከመቻሉም በላይ ሙያውን በመጥፎ መንገድም ተጠቅሞበታል የሚለው ዘገባው፤ ለአብነትም ከሦስት ዓመታት በፊት የሚስቱ የአክስት ልጅ በስርቆት ወንጀል ተጠርጥሮ ፍርድ ቤት ሲቀርብ የልጁ ቤተሰቦች ዋንግ የያዘውን የፖሊስነት ሙያ ተጠቅሞ እርዳታ እንዲያ ደርግላቸው በጠየቁት መሰረት ከጠበቃ ጋር በመሆን የልጁ ክስ እንዲቀነስለት አድርጓል፡፡ የልጁ ቤተሰቦችም የዋንግ ድጋፍ እንደነበረበት አምነዋል፡፡በርካቶች ዋንግ በ12 ዓመታት የፖሊስ ሙያ ቆይታው በፖሊሳዊ ግዳጅ ላይ ያለ ቢመስላቸውም፤ የወንጀል ምርመራዎችን ያለ እረፍት እያካሄደ ነው ብለው ቢያስቡም ወይም ደግሞ ወንጀለኞችን ከያሉበት እያደነ ነው ብለው ቢገምቱም ዳሩ ሰውየው አብዛኛውን ጊዜውን ሲያሳልፍ የነበረው በሆቴል ውስጥ እና ብዙም ትርፋማ ባልሆነው አነስተኛ የህትመት ቢዝነስ ውስጥ ተሰማርቶ እንደነበር ታውቋል፡፡ ሀሰተኛ የፖሊስነት ሙያውን ሽፋን በማድረግ ቢዝነሱን ለመታደግ በሚልም በርካታ ገንዘብ ከግለሰቦች የተበደረ ቢሆንም ብድሩን ግን መክፈል አልቻለም፡፡\nዘገባው ሲያጠቃልልም ከ12 ዓመታት በኋላ በቅርቡ ዋንግ በእውነተኛ ፖሊስ በቁጥጥር ሾር ውሏል፡፡2 ሚሊዮን የቻይና ዮዋን ወይም 290 ሺ ዶላር ዕዳ እንዳለብትም ፖሊስ ለማረጋገጥ ችሏል፡፡ጥቂት የማይባሉ አበዳሪዎችም ለዋንግ ያበደሩትን ገንዘብ ለመቀበል በመጠባበቅ ተሰላችተው እንደነበርና ወደ ህግ ለመሄድ በዝግጅት ላይ እንዳሉ ነው ዋንግ በፖሊስ ቁጥጥር ሼር የዋለው፡፡ ፖሊስ የዋንግን መኖሪያ ቤት ሲፈትሽ በውስጡ ሀሰተኛ የደምብ ልብስና መታወቂያ፣በእጅ የተፃፈ መለማመጃ የፖሊስ ሪፖርትና ካቴና ማግኘቱን አስታውቋል፡፡ዋንግ በፖሊስ ቁጥጥር ሾር ከዋለ በኋላ ይህን የማታለል ተግባር ለመፈፀም ምን እንዳነሳሳው ሲጠየቅ ‹‹ ሁሌም ፖሊስ የመሆን ፍላጎት ነበረኝ፤ በተለይ ከ12 ዓመት በፊት ወንድሜን ለመርዳት ስል የገባሁበት ጣጣ ሃሰተኛ ፖሊስ እንድሆን አስገድዶኛል፡፡ ለጓደኞቼና ለማውቃቸው ሁሉ ፖሊስ ሆኜያለሁ ብዬ ከተናገርኩ በኋላ ያገኘሁትን ክብር ላለማጣትም በማታለሉ ተግባር እስካሁን ልገፋበት ችያልሁ›› ሲል መልሷል ይላል ዘገባው፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 23/2011አስናቀ ፀጋዬ", "passage_id": "bc88cf7fbfbddb7948586afa3d5ca935" }, { "passage": "ልሹ የ50 አመት እድሜ ባለፀጋ መሆኑ ደግሞ አግራሞትን ፈጥሯል። \n\nክሌር ለተባለው መፅሄት በሰጠው ቃለ መጠይቅ በዚህ እድሜ ክልል ያሉ ሴቶች \"አዛውንትና በዕድሜያቸው የገፉ ናቸው\" ብሏል። \n\n\"በዕድሜያቸው አነስ ያሉ ሴቶችን እመርጣለሁ። የ25 አመት ሴት ሰውነት የሚያስደምም ሲሆን፤ በአንፃራዊው 50 አመት የሞላቸው ሴቶች ሰውነት አይደለም\" ብሏል። \n\n•\"ኢትዮጵያዊ ታሪኮችን ወደ ዓለም አቀፍ የፊልም መድረክ ማምጣት ፈታኝ ነው\" ዘረሰናይ መሐሪ\n\n•''አዝማሪዎቻችን የሙዚቃ ሳይንቲስቶች ናቸው\"\n\nአስተያየቱም በማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ዘንድ ቁጣን ቀስቅሷል። \n\nማሪና ፎይስ የተባለች የፈረንሳይ ኮሜድያን በትዊተር ገጿ ላይ እንዳሰፈረችው አሁን ወደ 49ኛ አመቷ ልትሸጋጋር ስለሆነ ከደራሲው ጋር ግንኙነት ለመመስረት ያሉኝ \"አንድ አመት ከአስራ ቀናት ነው\" በማለት በፌዝ ሸንቆጥ አድርጋዋለች። \n\nሌላኛው የትዊተር ተጠቃሚ በበኩሉ ከአምሳ አመት በላይ እድሜ ያላቸው ሴቶች \"በእፎይታ እየተነፈሱ\" ነው በማለት አስተያቱን ችሮታል። \n\nሌላ አስተያየት ሰጪ በበኩሉ \"ከአምሳ አመት በታች ያሉ ሴቶችስ የማይታዩህ ሁኔታ ሊፈጠር አይችልም\" ወይ በማለት ቀልዷል። \n\nከዚህም በተጨማሪ ከአምሳ አመት እድሜ በላይ ያሉ ሴቶችም አስተያየቱን በመቃወም ፎቷቸውን አጋርተዋል። \n\nኮሎምቤ ሽኔክ የተባለች ጋዜጠኛ በበኩሏ በኋላ በሰረዘችው ፎቶ ላይ \"የ52 አመት ሴት መቀመጫ ይህንን ይመስላል። ይህንን ነው ያጣኸው ነፈዝ\" በማለት አስተያየቷን ሰጥታለች። \n\nሌሎች ደግሞ አምሳና ከአምሳ አመት በላይ የሆኑ የሆሊውድ ተዋንያን እነ ሀሊ ቤሪ፣ ጄኔፈር አኒስተንን ፎቶ በመለጠፍ የደራሲው አስተያየት ስህተት እንደሆነ ለማሳየት ሞክረዋል። \n\nአን ሩማኖፍ የተባለች ሌላኛዋ ፈረንሳያዊ ኮሜዲያን አውሮፓ 1 በታባለ ሬድዮ ጣቢያ \" ፍቅር በሁለት ሰዎች መካከል ያለ ጥልቅ ግንኙነት እንጂ ሰውነት ብቻ አይደለም። አንድ ቀን ይህንን እንደሚረዳው ተስፋ አደርጋለሁ\" ብላለች። \n\nሞይክስ በፅሁፎቹ ሽልማትን ያሸነፈ ደራሲ ሲሆን በአስተያየቶቹ ውዝግብን በማስነሳት ይታወቃል። \n\n• የቀድሞዋ ሶቭየት ህብረት ትውስታዎች በኢትዮጵያውያን ዓይን\n\nበዛው መፅሄት ላይ ከእስያ የመጡ ሴቶችን በተለይም ከኮሪያ፣ ከቻይናና ከጃፓን እንደሚመርጥ መናገሩም ከፍተኛ ወቀሳን ፈጥሮበታል። \n\nየተቀሰቀሰውንም ቁጣ ተከትሎ ስለሚመርጣቸው ሴቶች ኃላፊነት እንደማይወስድ ገልፆም \" የምወደውን እወዳለሁ። በምርጫየ ላይ ሰዎች መግባት የለባቸውም\" ያለ ሲሆን እሱም ይህን ያህል ቆንጆ የሚባል እንዳልሆነ በቀልድ መልኩ ጣል አድርጓል። \n\n\"የአምሳ አመት ሴቶች እኔን አያዩኝም። ቀኑን ሙሉ በመፃፍና በማንበብ ጊዜውን የሚያሳልፍ ያልተረጋጋ ሰው ምን ያደርግላቸዋል? ጊዜያቸውን በጠቃሚ ጉዳዮች የሚያሳልፉ ይመስለኛል። ከኔ ጋር መሆን ቀላል አይደለም\" ብሏል። \n\n ", "passage_id": "e59c128265a9fbbce628c7b50b170423" }, { "passage": "ቤተልሔም ነጋሽ በማኅበራዊ ብዙኃን መገናኛዎች ሲወራ የሰነበተውን የ12 ዓመት ታዳጊ የ“ጋብቻ” ፎቶ እንዲሁም በሰሜን ጎንደር ያለ መምህር ያደረሳቸው እና በሚያስተምርበት ትምህርት ቤት ያሉ፣ በቤተሰባቸው ሊዳሩ የተፈረደባቸው ነገር ግን ዕድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች የሆኑ 7 ተማሪዎችን ዝርዝር መነሻ አድርገው የሚከተለው ትዝብት ያስነብቡናል።  የሰኞ (27 ጥር 2011) ቀን የፌስቡክ ውሎ ጅምር እንደሌላው የተለመደ ቀን አልነበረም። ጠዋት እንደልማዴ ከሥራ በፊት ፌስቡክና ትዊተር “ምን አሉ?” ብዬ አየት ባደርግ በአንድ የፌስቡክ ወዳጃችን ከአንዲት ወዳጄ ጋር በጋራ ሥሜ ተነስቶ አየሁ። የተመለከትኩት “ኧረ ሴታዊት (ፌሚኒስቶች) ይህቺን ሕፃን አስጥሉ” ከሚል መልዕክት ጋር የተያያዘ ፎቶ ነበር። ወዳጃችን ያጋራን ፎቶ ኋላ የ12 ዓመት ልጅ እንደሆነች የምንረዳት ሕፃን እና የፌስቡክ ገጹ 18 ዓመት እንደሞላው የሚያመለክተው ወጣት በቤተክስርቲያን የተክሊል ጋብቻ ልብስ ለብሰው የተነሱት ፎቶ ነበር። ሁለቱም የጋብቻ ቀለበት አድርገው፣ ካባና ቆብ ደፍተው ይታያሉ። ታዳጊዋን “የሚያገባት” ወጣት ፎቶውን ፌስቡክ ላይ ሲያጋራ በትግርኛ የጻፈው መልዕክት “አስቤው ሳይሆን ተሰጥቶኝ ነው” የሚል ነበር።ፎቶው ላይ የልጅቷ ሕፃንነት በግልጽ ይታወቅ ስለነበር፥ በሠርግ ልብስ ሆና ስትታይ በጣም የሚያስደነግጥ ብቻ ሳይሆን አስቀያሚ ነገርም ነበረው። ወዲያው የትግራይ ክልል ነዋሪዎችን የሚያውቁና ከዚያም አካባቢ የመጡ ጓደኞቻችንን ስንጠራ ጉዳዩ ታውቆ በክልሉ ያሉ የመብት ተሟጋቾችና ታዋቂ ሰዎች እንደያዙት ሰማን። ትክክለኛ ቦታውን ለማወቅም ርብርብ ተደርጎ በመጨረሻ ተገኘ። የክልሉ ሴቶች ጉዳይና ፖሊስ ቆላ ተንቤን ወረዳ ውስጥ “በሚቀጥለው ሳምንት ሊካሔድ ነበር” የተባለውን ሠርግ ማስቆሙን፣ ወረዳውም ትብብር ማድረጉን የሚገልጸውን የመጨረሻውንና ምሽት ላይ የተበሰረውን ይህንን ዜና እውነት እንደሆነ አረጋግጠን ቀኑን ስንጨርስ ትልቅ እፎይታ ነበር። ዳግም የማኅበራዊ ብዙኃን መገናኛን ጉልበት ያየንበት፣ ለበጎ ሲውል የታዘብንበት ክስተትም ሆኖ አልፏል።ስለ ትዝብት ከተወራ አይቀር፣ ይህ መረጃ ሲዘዋወር በነበረበት ወቅት ድርጊቱን ካወገዙት ባላነሰ ሊባል በሚችል ደረጃ፥ ለድርጊቱ ድጋፍ ሲሰጡ የነበሩ የፌስቡክ ተጠቃሚዎችን አስተያየት ማንበብ ፎቶውን ከማየት ባላነሰ የሚያሳዝን ብቻ ሳይሆን የሚያሳፍርና ተስፋ የሚስቆርጥ ገጠመኝ ነበር። በበኩሌ የሴቶች እኩልነት ጥያቄ ጉዳይ ለብዙዎች የማይዋጥላቸው ነገር መሆኑን ባውቅም፣ በግልጽ ሕፃንነቷ የሚታይ ልጅ ታግባ አታግባ የሚለው ጉዳይ አከራካሪ ሆኖ ማየት “እንዲህ ሆነን፣ ይህን አመለካከት ይዘን ነው ለውጥ የሚመጣው” የሚል ጥያቄ ያስነሳል።ለምሳሌ ያህል “ይሄ ምርጥ ሊበረታታ የሚገባው ነው”፣ “ተውት ያሳድግበት፣ በሕግ ለተክሊል የምትሆን ሚስት ማግኘት አይችልም”፣ “ልጁ ዲያቆን ሊሆን ስለሚችል የ18 ዓመት ድንግል ከየት ያገኛል”፣ “…ይህ ዓይነት ሠርግ በተክሊል ተጋቢዎች ዘንድ የተለመደ ነው። እንደ ማሸነፊያ የሚቀርበው አካለመጠን እስክትደርስ ቤተሰብ ኃላፊነት እየወሰደ እንደሚያጋባ ነው”፣ “ሲጀመር እነሱ ያገኙትን ዕድል እግዚአብሔር የመረጣቸው ብቻ ናቸው የሚያገኙት ስለዚህ እግዚአብሔር ትዳራቸውን የአብርሃምና የሳራ ያድርግላቸው።…” የሚሉ ሲገኙበት፣ ትዊተር ላይ ደግሞ “ምን ነክቶአቸው ነው?” ብሎ ለሚጠይቅ “ምንም አልነካቸው፣ አለማወቅ ነው” ብሎ የሚከራከር አለ። ሌላው “ፌስቡክ የሚጠቀም ወጣት ሕፃን ልጅ ማግባት ወንጀል ብቻ ሳይሆን ትክክል አለመሆኑን አያውቅም?” ሲባል “ቢያውቅ ፌስቡክ ላይ አይለጥፍም” ይላል መልሶ።ድርጊቱ ክፉኛ ያሳዘናቸው ደግሞ በዚህ ጉዳይ የእምነት ቤቶችም ጭምር ከሕግ ተጠያቂነት ማምለጥ እንደሌለባቸው ሲያሳስቡ ነበር። የአገሪቱ ሕግ የጋብቻ ዕድሜ 18 ዓመት መሆኑን ደንግጎ ሳለ የ12 ዓመት ልጅ ካባ አልብሶ መዳር ትንሽ ሊከብድ ይገባ ነበር። ፈቅጃለሁ እንኳን ብትል ዕድሜዋ 18 ዓመት ያልሆነ ልጅ ማግባት አይደለም የግብረስጋ ግንኙነት ለማድረግ ፈቃድ መስጠት አትችልም።ከድጋፍና ተቃውሞ አስተያየት ባለፈ አንድ በልጅነቷ ተድራ በጉዳቱ ውስጥ ያለፈች ሴት የጻፈችው ምስክርነት የሚያሳዝን ነገር ነበረው።\n“…እኔስ የኔን ቀን አስታወሰኝ። ለመድኃኒያለም ማኅበር ብለው ደግሰው በልጅነቴ ሲድሩኝ። ብዙ ዓመት ዝም ብዬ ነበር። ማሳቀቁ፣ የሚነጥቀው ነገር ብዛቱ፡ የእያንዳንዱ ቀን ሕመም። የዛሬውን ፎቶ ሳይ ወደረሳሁት ወደዛ ጨለማ ጊዜ ተመለስኩ። ዛሬ ልጄን ሳያት 13ኛ ዓመቷን ደፍና፣ ለዛውም ከእኔ ልጅነት ሲተያይ የእሷ ዕድገት የበለጠ ሆኖ ‘በዚህ ዕድሜዬ ነበር ጨክነው የሞሸሩኝ፤ በዚህ ዕድሜዬ ነበር’ እላለሁ። እህቱ ብትሆን ለምን ሰው አየሽ? ብሎ የሚሸልል ሁሉ፥ የጨቅላ ጭን መሐል በባሕል አሳቦ ለመግባት ትንሽ ያዝ አያደርገውም።…”ጽሑፌን ስደመድም የችግሩን ስፋት በሚመለከት መረጃ በመስጠት በግልጽ ሊታወቅ የሚገባውን የሕፃናት ጋብቻ በልጆቹም፣ በአገርም ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት በመግለጥ ነው።\nበተለምዶ ያለዕድሜ ጋብቻ እየተባለ የሚጠራው የሴት ሕፃናት/የልጆች ጋብቻ ማንኛውም ከ18 ዓመት በታች ባለች ሴት ልጅ ላይ የሚፈፀም ጋብቻ ነው። ይህም ልጅቷ በአካልም፣ በሥነ ልቡናም፣ በሰውነትም ልጅ ለመውለድና የትዳርን ኃላፊነት ለመሸከም ዝግጁ ባልሆነችበት ወቅት የሚፈፀም ነው። የተባበሩት መንግሥታት ሕፃናት አድን ድርጅት መግለጫ እንደሚያስረዳው፥ ይህ ድርጊት የብዙ ሰብኣዊ መብቶችን ጥሰት በውስጡ የያዘ ነው። የማኅበራዊ ፍትሕ መጓደል ምልክትም ነው።\n“ሙሽሮች ሳይሆኑ ልጆች” (Girls not Brides) የሚለው ዓለም ዐቀፍ የልጆች ጋብቻን የማስቀረት ዘመቻ ድረገጽ ዩኒሴፍን ጠቅሶ እንዳስቀመጠው በ2017 እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በተደረገ ጥናት የተገኘው መረጃ በኢትዮጵያ ከታዳጊ ሴት ልጆች 14 በመቶ የሚሆኑት 15 ዓመት ሳይሞላቸው ያገቡ ሲሆን፥ 40 በመቶው 18 ዓመት ሳይሞላቸው ያገባሉ። በዓለም ዐቀፍ ደረጃም አገራችን ሕፃናትን በመዳር 16ኛ ደረጃ ይዛ ትገኛለች። በዚህ መሠረት ከአምስት ሴት ልጆች ኹለቱ፣ 18 ዓመት ሳይሞላቸው ትዳር ይዘዋል፤ ከአምስቱ አንዷ ደግሞ 15 ሳይሞላት ለትዳር ተሰጥታለች። ሥርጭቱ በየክልሉ የሚለያይ ሲሆን፥ አማራ ክልል ከፍተኛውን ቁጥር በመያዝ 45 በመቶ ሴት ልጆች በልጅነታቸው የሚዳሩበት ክልል ነው።\nመረጃዎች እንደሚሉት የግዴታ ጋብቻ እና ልጆችን መዳር በብዙዎቹ የአፍሪካ አገራት “ባሕል” እና “ልማድ” ተደርጎ ተይዟል። በአገራችንም ከላይ የተጠቀሱት አስተያየት ሰጪዎችን ጨምሮ ብዙዎች “እዚያ አካባቢ እንዲህ ማድረግ የተለመደ ነው። በተክሊል ጋብቻ ይኼ የታወቀ ነው” የሚል አስተያየት ሲሰጡ ይደመጣል። የማደጎ ጋብቻም ይሁን ሌላ መቅረት ያለበትና እየቀነሰም የመጣ “ባሕል” ለዚህ ዋና ምክንያት ነው።ብሔራዊ የልጆች ጋብቻን የማስወገድ ጥምረት በተሰኘው ቡድን አማካኝነት በሴቶችና ሕፃናት ሚኒስቴር መሪነትና በዩኒሴፍ ድጋፍ የተደረገ ጥናት ግኝት እንደሚለው ድህነት ልጆችን በለጋነታቸው ለመዳር ዋና ምክንያት አይደለም።ወላጆች በከፋ ድህነት መኖራቸው ሳይሆን ይልቁንም በማኅበራዊ መደብ ደረጃ ለማሳየት፣ እንዲሁም የሆነ የመደብ ደረጃ ላይ ያሉ ኹለት ቤተሰቦችን የማዛመድና የማቀላቀል ጉዳይም ነው። ይህ በየቦታው የተለያየ መሆኑ ግምት ውስጥ መግባት ይኖርበታል።ዋናው ጉዳይ ግን “ሴት ልጅ አጎጠጎጤ ካወጣች መዳር ነው፣ ትባልጋለች” የሚል ባሕል እና ልማድ ነው። “የተፈጠረችው ልትዳር፣ ልትወልድ ነው፤ በጊዜ ትጠናቀቅ” ብሎ የሚወስን ልማድ። የቤተሰብን ክብር የማስጠበቅ “ንፁህ” ሆኖ የመገኘት ግዴታን የማረጋገጥ ብቸኛ መንገድ በሕፃንነት መዳር ነው ተብሎ ስለሚታሰብም ጭምር ነው ይህ የሚሆነው።\nየጤና ሚኒስቴር ባለፈው ወር የተከበረውን የጤናማ እናትነት ወርን አስመልክቶ ያወጣው መረጃ እንደሚያመለክተው በኢትዮጵያ ከ33 በመቶ በላይ የኅብረተሰቡን ክፍል የሚወክሉት ወጣቶችና አፍላ ወጣቶች ሲሆኑ፣ ከእነዚህ 40 በመቶዎቹ በ18 ዓመታቸው ያገባሉ።20 በመቶ ያህሉ ደግሞ 18 ዓመት ሳይሞላቸው የሚያረግዙ ሲሆን፣ ለተለያዩ የጤና ችግሮች ተጋላጭነታቸውም የጎላ ነው። የአፍላ ዕድሜ እርግዝና በአብዛኛው የሚከሰተው በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ በሚገኙ፣ ዝቅተኛ የትምህርት ደረጃ ባላቸውና በገጠር አካባቢ በሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎች ነው።\nበአብዛኛው እርግዝናው የሚከሰተው በጋብቻ ምክንያት መሆኑን የጠቆመው መረጃው፣ እርግዝናው የሚያስከትላቸውንም ችግሮች አስፍሯል።\nየአፍላ እርግዝና፣ ለከፍተኛ ደም ግፊትና ደም ማነስ፣ ቀኑ ያልደረሰ ሕፃን ለመውለድ፣ ንፅሕናውን ላልጠበቀ የፅንስ ማቋረጥና ለተወሳሰበ ምጥና ፊስቱላ ለመጋለጥና ከማኅበራዊ ሕይወት ለመስተጓጎል ምክንያት ነው።\nከላይ የጠቀስነውን የአመለካከት ችግርና የተግባራዊነቱን ስፋት ስንጠቅስ የመጣ ለውጥ የለም ወይም ተስፋ የለም ለማለት አይደለም። በመንግሥትና በአጋሮች በተለያየ መልኩ የሚደረገው ዘመቻ ውጤት አምጥቷል። በዚህም በቀደሙት ዓመታት 60 በመቶ የነበረው የልጆች ጋብቻ ወደ 40 በመቶ ወርዷል። ይህም በዓለም ከፍተኛ ለውጥ ካስመዘገቡ አገሮች ቀዳሚ ሆኖ ተመዝግቧል፤ 40 በመቶ ቀላል ቁጥር አለመሆኑ ባይረሳም።\nየሚታየው ለውጥ የመጣው ሴት ልጆች ትምህርት ቤት እንዲቆዩ ዘመቻ በማድረግ፣ ወላጆችን በማስተማር፣ መምህራን የለውጡ አስፈፃሚና ተቆርቋሪ እንዲሆኑ በማድረግ በመሆኑ ይህን ማስቀጠል ያስፈልጋል።ሌላው ዋናው ለሴት ልጅ ቦታ የማይሰጥ ባሕል የሚቀየርበትን ሒደት የማፍጠን ብቻ ሳይሆን ሴት እንደ አምራች ለአገር ዕድገት አስተዋፅዖ ማበርከት የምትችል፣ በራስዋ ሕይወት መወሰን ያለባት፣ ከትዳርና ልጅ መውለድ ውጪ ራዕይ ሊኖራት የሚችል፣ መሆኑን ማስተማርና ማስረፅ፣ ተከታታይ ዘመቻ ማድረግ፣ ልጆች ተድረው ሲገኙ በድርጊቱ ተሳታፊዎችን በወንጀል መጠየቅ ያስፈልጋል።ዋነኛው የመፍትሔው አካልም በተለይ የክልል መንግሥታት ጉዳዩን ቀዳሚ አጀንዳ ሊያደርጉት ይገባል። አጥፊዎች ላይ እርምጃ በመውሰድ የማኅበረሰቡን ግማሽ አካል ሰብኣዊ መብቶች የጣሰ ዕድገት ሊኖር እንደማይችል፣ የሕፃን ልጅ ሕይወት ዳግም እንዳይበራ አድርጎ ለዘላለም የሚያጨልም፣ ከትምህርት ገበታ የሚያስቀር፣ ለጨዋታና ለማደግ ዕድል ያላገኘ ያልጠና አካሏን ለግንኙነትና ለእርግዝና መዳረግ፣ በወሊድ ምክንያት ለሚከሰት ሞት አልያም በአገራችን በስፋት ለሚታየው የፊስቱላ ችግር የሚዳርግ “ባሕል” ተቀባይነት እንደማይኖረው ሊያሳዩ ይገባል።ቤተልሔም ነጋሽ የፖለቲካ ተግባቦት ባለሙያ ናቸው።\nበኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ሊገኙ ይችላሉ።ቅጽ 1 ቁጥር 13 የካቲት 2 ቀን 2011", "passage_id": "33ddf451c19b03da38e0c45cc4e53529" }, { "passage": " ቀደም ሲል ስለጋዜጠኝነት ሙያ ሥልጠና ለመውሰድ ወደ ቻይና ሄጀ በነበረበት ወቅት የጠላት መከላከያ ምሽግ የሆነውን ታላቁን የቻይና ግንብ ለመጎብኘት እኔና ጓደኞቼ እድል አግኝተን ነበር። ቦታውን ስንጎበኝ የአፍሪካ ቱሪስቶች መሪና አስተርጓሚ ሆና ትሠራ የነበረችው ሆው ሉዊስ (ኢትዮጵያውያን ጓደኞቼ ጫልቱ የሚል ስም የሰጡዋት ) ወጣት ከቻይና ሥነቃል ተነሥታ ሾለ ታማኝቱ አፍቃሪ ሾለ ሚንግ ጂያንግ፤ ሾለ ባለቤቷና በታላቁ የቻይና ግንብ ሼል ስለነበረው ተሳትፎ አጫውታን ነበር። ሉዊስ እንደተረከችልን ቆንጆይቱ ሚንግ ጂያንግ በቻይና ሾለ ታላቁ ግንብ ከሚነገሩ ታሪኮች ውስጥ አራተኛው ሥነ ተረት ተደርጎ ይታያል። ይህ ከ2200 ዓመት በላይ እድሜ ያለው፤ በኲዊን ሥርዎ መንግሥት ዘመን የታወቀና በአፈ ታሪክ ላይ የተመሠረተ ሥነ ተረት ነው። ሥነ ተረቱ የተገኘው በብራና ላይ (ማኑስክሪፕት) በእጅ ተጽፎ ነው። ወይዘሪት ሉዊስ እንዳለችው ሚንግ በመልካም እንክብካቤ ያደገች፤ እጅግ በጣም ቆንጆ፤ ሙዚቃ የመድረስና ግጥም የመግጠም ችሎታን የታደለችና የፈላስፋው የኮንፊሺየስ ዓይነት አስተሳሰብ የነበራት ወጣት ናት። ከዕለታት በአንዱ ቀን ከሰዓት በኋላ ሚንግ ጂያንግ በቤተሰቦቿ ግቢ ውስጥ በሚገኝ የአጸድና አትክልት ቦታ ውስጥ አበቦችን ተመስጣ በማየት ላይ እንዳለች በአጸዱ አጥር በኩል ያያት በነበረ አንድ ወጣት ስሜቷ ተሰረቀ። ወጣቱ ዋን ጂሊያንግ እንደሚባልና ታላቁን ግንብ ይገነባ ከነበረው የመጀመሪያው ንጉሥ አምልጦ የመጣ ሠራተኛ እንደሆነ ነገራት። በረሀብና በችግር በጣም እንደተሠቃየም ገለጸላት። ቆንጆይቱ ሚንግና ቤተሰቦቿ ወጣቱ እንግዳ ዋን ጂሊያንግ አብሯቸው እንዲቆይ ፈቀዱለት። በእውነትም ወጣቱ የተማረና መልካም ሥነ ምግባር ያለው ሰው ነበር። ቆይቶ እጅግ በጣም ቆንጆ የሆነችው ሚንግና ወጣቱ ዋን ጂሊያንግ በፍቅር ወደቁ። የሚንግ ቤተሰቦች ተወዳጇ ልጃቸው ትዳር ለመመሥረት እጮኛ ስላገኘች በእጅጉ ተደሰቱ። ወዲያውም ጋብቻ መሠረቱ። ነገር ግን በሰፈሯ በውበቷ የተነደፈ ሌላ ሰው ጋብቻዋን በምቀኝነት ተነሣሥቶ ለማደናቀፍ ስለፈለገ በአካባቢው ወደሚገኙ ባለሥልጣኖች ዘንድ ሄዶ አቤቱታ አቀረበ። በሠርጋቸው ቀንም የወደፊት ባለቤቷ ዋን ጂሊያንግ ተይዞ በሰሜን ቻይና የታላቁ ግንብ ወደሚገነባበት ቦታ ተላከ። ወጣቷ ሚንግ ጂያንግ ያገባችው አዲሱ ባለቤቷ ወደእርሷ እንዲመለስላት ቀንም፤ ሌትም ትጠብቀው ጀመር። የበጋው ወቅት ገብቶ እስኪያልፍ ድረስ በጉጉት ስሜት ሆና ስለእርሱ ብታስብና ብትጨነቅም ምንም ዓይነት ቃል፤ አንዳችም መልእክት ከዋን ጂሊያንግ ሊመጣላት አልቻለም። ለብዙ ቀናት በሐሳብ ስትሰቃይ ከቆየች በኋላ በመጨረሻ ክረምቱ ሲገባ ለባለቤቷ የሚበረከቱ የክረምት ልብሶችን አዘጋጅታ እስካለበት የታላቁ ግንብ ፕሮጀክት ድረስ ሄዳ ዓይኑን ለማየት ወሰነች። ቤተሰቦቿ ግን እንዳትሄድ ቢቃወሟትም የእነርሱ ተቃውሞ ምንም ዓይነት ቁብ ሳይሰጣት ተራራዎችንና ወንዞችን እያቆራረጠች የታላቁ ግንብ እስካለበት ቦታ ድረስ ተጓዘች። እዚያም ስትደርስ ወፈ ሰማያት የሆነ የቀን ሠራተኛ በበዛበት መሃል ዋን ጂሊያንግን ፈልጋ ለማግኘት በማትችልበት ሁኔታ ውስጥ ሆና ላይ ታች ትባዝን ጀመር። በመጨረሻ ስታጠያይቅ ባለቤቷ ዋን ሒሊያንግ በታላቁ ግንብ ሼል ብዙ ሥቃይና እንግልት ከደረሰበት በኋላ በዚሁ የሥራ ጫና ምክንያት እንደሞተ መርዶ ተነገራት። እሪ ብላና ራስዋን ስታ ወደ መሬት ወደቀች። ራሷን ስታውቅ ኀዘኑ ልቧን ይበላው ጀመር። ዕንባዋም እንደ ጎርፍ እየወረደ ትጮህ ጀመር። የት እንደተቀበረና ዐፅሙ የት እንዳረፈ ለማወቅ ተቸገረች። በዚህ ዓይነት ለሦስት ቀናት ያህል ስታለቅስ ቆይታ እስከታላቁ ግንብ ጫፍ ድረስ በእግርዋ ወጣች። በድንገትም ተአምራዊ ነገር ይፈጠራል። ይኸውም የግንቡ 800 ማይል የሆነው ክፍል በታላቅ ፍንዳታ ተሰባብሮ ይወድቃል። በወደቀበት ሰዓትም የእርሷን ባለቤት ጨምሮ የበርካታ ሰዎች ነጫጭ ዐፅሞች ከድንጋይ ስብርባሪና ከአቧራ ጋር በላይና በውስጥ እየሆኑ መታየት ጀመሩ። ዐፅሞችን ስትመለከት በበለጠ ከጭንቀት ላይ ወደቀች። ወዲያው ጣቶቿን አደማችና «ይህ የምመለከተው ባለቤቴ ከሆነ ደሜ ወደ መሬት ሰርጎና የባለቤቴን ዐፅም ሰርሾሎ እንዲገባ ምኞቴ ጥልቅ ነው Âť ብላ ጸለየች። የሙታን ልሾ ቅሎችንም ተመልክታ ወደየቤተሰቦቻቸው መልእክት ለማድረስ ትችል ዘንድ ጠየቀቻቸው። የራስ ቅሎችም ለጥያቄዋ በግጥም እንዲህ ሲሉ መለሱላት። በፀደይ በክረምት እንዲሁም በበጋ፤ በቢጫማው ዐፈር በአሽዋው መሬት ላይ ተኝተናል ባልጋ። በይ ቃል አድርሽልን ጽንዓት ቢሆናቸው፤ ለየሚስቶቻችን ለተለየናቸው። መዝሙር አሰሚልን ለየነፍሶቻቸው ፤ የእኛ መሥዋዕትነት መድኅን ቢሆናቸው። ዋን ጂሊያንግ ሲሞት ሰውነቱ ከታላቁ ግንብ ጋር ተጣብቆ የግንቡ አካል ሆኗል። ነፍሱ በአየር ላይ እየተቅበዘበዘች ባለቤቱን ሚንግን እንዲህ ትላለች። ÂŤ ከመሬት ውስጥ የምገኘው እኔ አንድ ድሃ ወታደር ለምን ጊዜም አልረሳሽም ከድንጋይ ክምር ጋር ስዋደቅ ነው የወደቅሁት»። ባለቤቱም ይህንን ስትሰማ «አሁን አባትና ምንም ዓይነት ዘመድ የለኝም፤ ባል ልጅ የለኝም፤ የምሄድበት ቦታም የለኝም የምፈልገው እንዳንተ እዚሁ መሞት ብቻ ነው»። ይህ ስለታላቁ የቻይና ግንብ የሚነገረው ሥነ ተረት በይዘትም በቅርጽም እየተሻሻለና በጥናትና ምርምር እየዳበረ ከመምጣቱ ባሻገር በብዙ የዓለም ቋንቋዎች ተተርጉሟል። በኢትዮጵያ ቋንቋዎች ግን ገና የተተረጎመ አይመስልም። የቻይና የኪነ ጥበብ ሰዎች የሚንግንና የዋን ጂሊያንግን ፍቅር መነሻ አድርገው «የወጣቷ ሚንግ ያንግ የ12 ወራት አበባዎች» በሚል ሳቢና ማራኪ በሆነ መንገድ ኅብረ ዝማሬ ሠርተውላቸዋል። የመጀመሪያው ውቅት የአበባ፤ ሁለተኛው የፍቅርና የተስፋ ፤ ሦስተኛው የድንጋጤና የጥርጣሬ… እያለ አስከ አሥራ ሁለተኛው ወር ይደርሳል። ይህ ወር ለሚንግ የመከራና የጭንቀት ጊዜ ሆኖ ተሥሏል። ሚንግ ለብቻዋ ሆና «ሁሉም ቤተሰብ ከደስታ ብዛት የተነሣ በየቤቱ ቀይ መብራት እያበራ ነው፤የጎረቤቶቼ ባለቤቶች ወደቤታቸው በሰላም ተመልሰው ከፍቅረኞቻቸው ጋር ተገናኝተዋል፤የእኔ ባለቤት ብቻ ታላቁን የቻይና ግንብ እገነባለሁ ብሎ እንደወጣ ቀረብኝ፤ ዐፅሙ ከግንቡ ጋር ተላትሞ ግድግዳ ሆነ፤ ደሙ አሸዋና ሲሚንቶ ሆኖ ግንቡን አጸናው፤» እያለች ስታለቅስ፤ ስታዝንና ስትተክዝ ትታያለች። ነፍሱ ከቦታ ቦታ እየተዘዋወረች በደሏን በመናገር« ውድ ባለቤቴ ሆይ እኔ ድሃው ባለቤትሽ ሞቼና ተቀብሬ ከመሬት በታች ብሆንም ለምን ጊዜም አልረሳሽም» ስትል ትሰማታለች። ወጣቷን ለከፍተኛ ኀዘንና ሰቆቃቀው የዳረጋት በኵይን ሥርዎ መንግሥት የመጀመሪያ የነበረው ጨካኙና አምባገነኑ ንጉሥ ነው። የመሠረተውን አዲስ መንግሥት ከጠላት ለመከላከል ሲል በርካታ የቻይና ወጣቶችን እያስገደደና እያዘዘ ታላቁን ግንብ እንዲገነቡ፤ ለሕይወታቸው ሳይጨነቅ እንደባሪያ ሌትም ቀንም ያለዕረፍት እንዲሠሩ ያደርጋቸው ነበር። ከዚህም ተነሣ በርካታ ወጣቶች በናዳ፤ በመሬት ነውጥና በእሳት ቃጠሎ፤ በተስቦ በሽታ አልቀዋል። ጭካኔ በተሞላበት የግንባታ ሼል ልጆቻቸውን፤ ዘመዶቻቸውን፣ ባለቤቶቻቸውንና ልጆቻቸውን ካጡና እድለቢስ ከሆኑ ወጣት ሴቶች ውስጥ አንዷ ሚንግ ሆነች። ቻይናውያን ለሚንግ ማስታወሻ እንዲሆን በኪንግሁዋንግ የደሴት ከተማ ቤተመቅደስ ሠርተውላታል። ቻይናዊው ንጉሠ ነገሥት የሞተ ባለቤቷን እያስታወሰች እንደምትጨነቅ ስለሚያንግ ሁኔታ በሰማ ጊዜ ወደእርሱ ዘንድ እንዲያመጧት አዘዘ። ወደ እርሱ ዘንድ መጥታ ባያት ጊዜ በውበቷ ተማረከና ሊያገባት ወሰነ። ሚንግም ንጉሡ ሦስት መሠረታዊ ነገሮችን ካሟላላት ልታገባው እንደምትችል ተስማማች። የጠየቀቻቸው ሦስት ነገሮች አንደኛ ለሟች ባለቤቷ ክብር ሲባል ለ49 ቀናት የመታሰቢያ በዓል እንዲደረግለት፤ ሁለተኛ ንጉሠ ነገሥቱና ባለሥልጣኖቹ በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ እንዲገኙ እንዲደረግላት፤ ሦስተኛ ለሞተው ባለቤቷ መሥዋእት ለማቅረብ እንድትችል በወንዙ ዳር 49 ሜትር ርዝመት ያለው ሰገነት ( ማማ) እንዲሠራላት የሚል ነው። ንጉሠ ነገሥቱን ኲይን\nሺ ሁዋንግዱም ወጣቷ\nየጠየቀቻቸው ሦስት መሠረታዊ\nነገሮች በአንድ ጊዜ\nእንደሚፈጸሙላት ማለላት። በመሐላው\nመሠረትም የጠየቀችውን ሁሉ\nፈጸመላት። ሁሉ ነገር\nከተዘጋጀ በኋላ ከሰገነቱ\nላይ ወጥታ ደካማነቱንና\nጨካኝነቱን እያነሣች ንጉሠ\nነገሥቱን ኲይንን በኃይለ\nቃል ትዘልፈውና ታወግዘው\nጀመር። ይህንን ከተናገረች\nበኋላ ከማማው ላይ\nዘልላ ወደ ባሕሩ\nራስዋን በመጣል ጠልቃና\nሰምጣ ሞታለች።አዲስ ዘመን ነሐሴ 26/ 2011  ታደለ\nገድሌ ጸጋየ ዶ/ር", "passage_id": "3fc9c739854e91f291341c966b0f3d82" } ]
9e7683a6602fe9b07d7c83a6895dc8c9
2cd9675413e4de66d828b2a3a1ee5e47
ኮሚሽኑ ስኬታማ ሥራ ማከናወኑን አስታወቀ
የኮሮና ወረርሽኝ (ኮቪድ 19) በየዘርፉ የተለያዩ ተጽእኖዎችን ማድረሱ ግልጽ ነው። ከእነዚህ ዘርፎች መካከል አንዱ የሆነው ስፖርት ሲሆን፤ ጠቅላላ እንቅስቃሴው ተገቶ እንዳልነበር ለመሆን ተገዷል።በርካታ ስፖርታዊ ውድድሮች፣ ስልጠናዎች፣ ጉባኤዎችና ሌሎች ክንዋኔዎች በቫይረሱ ስጋት ምክንያት ሲሰረዙና ሲራዘሙ መቆየታቸው ይታወቃል። ነገር ግን የተለያዩ አገር አቀፍና ዓለም አቀፍ የስፖርት ተቋማት ለተቋረጡት ስፖርታዊ ኩነቶች አማራጮችን በመፈለግ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ቆይተዋል።እንደ መፍትሄ ባስቀመጧቸው ሃሳቦች ታግዘውም ክፍተታቸውን ሲሸፍኑ ሰንብተዋል፡፡ይህ በመላ ዓለም ጥላውን ያጠላው ወረርሽኝ ወደ ኢትዮጵያ መግባቱ ከተረጋገጠበት ጊዜ አንስቶም በርካታ እርምጃዎች በስፖርቱ አካባቢ ሲወሰድ ተስተውሏል። ስልጠናዎች፣ የውድድር ዝግጅቶች፣ ውድድሮች፣ ስብሰባዎችና ሌሎች ጉዳዮች መቋረጣቸው የግድ ቢሆንም፣ ስፖርቱን በበላይነት የሚመራው የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን እና ጥቂት የስፖርት ማህበራትና ተቋማትም በሌላ አቅጣጫ ከተለመዱት ኩነቶች ውጪ የሆኑ ተግባራት ላይ አተኩረው ቆይቷል፡፡ነገር ግን በወቅታዊው ችግር ተቋማቱ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ባስቀመጡት መርሐ ግብር መሰረት ያከናወኗቸው እንዲሁም ያልሸፈኗቸው እቅዶች መኖራቸው አይቀርም።ኮሚሽኑ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዱቤ ጂሎ ይገልጻሉ። በተለይ በትኩረት ሲከናወን የቆየው የስፖርቱን ሁለንተናዊ ችግር ሊቀርፍ የሚችለውን ጥናት ወደ ተግባር በመቀየር ላይ ነው። ሃገር ዓቀፉ የስፖርት ሪፎርሙን ለመተግበር በሚያስችል ሁኔታ ግብረ ኃይል በማቋቋምና እቅዶችን በማውጣት በውድድር፣ በስልጠና፣ በማዘውተሪያ ስፍራና አደረጃጀት ዙሪያ ያሉ ችግሮችን በመገምገም ስራዎች በዓመቱ ውስጥ ተከናውነዋል። የስፖርት መተዳደሪያ ደንቦችን እንዲሁም ስታንዳርዶችን በማዘጋጀት፣ የስፖርት ማህበራት ያሉበትን ደረጃ የማውጣት፣ ስፖርቱ የሚመራበት አደረጃጀት ላይ ዶክመንት የማዘጋጀት፣ የስፖርት ማህበራት አደረጃጀት ላይ ክለሳ ማድረግም በበጀት ዓመቱ ተችሏል።በመንግሥት በኩል ከፍተኛ በጀት ተመድቦለት በመካሄድ ላይ የሚገኘው ብሄራዊ ስታዲየም ግንባታ፣ የካፍ እግር ኳስ ማሰልጠኛ ማዕከል እድሳት እንዲሁም በሲኤምሲ በሚገኘው ቦታ ላይ የማዘውተሪያ ስፍራ የመስራት እቅድ ላይም ኮሚሽኑ ሲሰራ መቆየቱንና ይህም ስኬታማ እንደነበር ምክትል ኮሚሽነሩ ያብራራሉ።በዓመቱ በርካታ ስራዎች ቢከናወኑም በአንጻሩ ከወረርሽኙ ጋር በተያያዘ በታቀደው መሰረት ለመፈጸም ያልተቻሉ ጉዳዮችም መኖራቸው አልቀረም።ይኸውም የዓለም፣ አህጉርና ሃገር አቀፍ ውድድሮችን ማካሄድ እና በክልሎች የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ለመገምገም አለመቻል ነው።ከጥቂት የእግር ኳስ ሊጎች በቀር በዓለም ደረጃ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ዝግ መሆናቸውይታወቃል።በኢትዮጵያም የተሻለ እንቅስቃሴ የሚያደርጉት የእግር ኳስና አትሌቲክስ ስፖርቶች እንደቀደመው በመርሐ ግብራቸው መሰረት መስራት አልቻሉም።ሃገሪቷ የምትታወቅበት አትሌቲክስ ኦሊምፒክን ጨምሮ በርካታ ዝግጅት ሲያደርግ ቢቆይም፤ በወቅታዊው ሁኔታ ብሄራዊ ቡድኑን ለመበተንና ስልጠናዎችን ለማቋረጥ ተገዷል። በእግር ኳስም ተመሳሳይ ሁኔታ ያለ ሲሆን፤ ከማህበር ባለፈ በግላቸውም ስፖርተኞች ከቀደመው ጊዜ ገቢያቸው እንዲቀንስ አድርጓል። ነገር ግን በአንጻራዊነት ሲታይ በእነዚህ ስፖርቶች ያለው እንቅስቃሴ የተሻለ ሊባል የሚችልና ተጓዳኝ ስራዎችን እያከናወኑ መሆኑን ምክትል ኮሚሽነሩ ይጠቁማሉ።ቀድሞም እምብዛም እንቅስቃሴ ያልነበራቸው ሌሎች ስፖርት ማህበራት ደግሞ በዚህ ወቅት ይበልጥ ተዳክመዋል።በመሆኑም የስፖርት ኮሚሽን ዋነኛው ሥራ እነዚህን ማጠናከር ይሆናል።አብዛኛዎቹ ፌዴሬሽኖች ከላይ እስከ ታች ያለውን አደረጃጀት ማስተካከል አይደለም የውስጥ ውድድራቸውንም በትክክል መምራት ያልቻሉበት ሁኔታ መኖሩን በግምገማ ተለይቷል። በመሆኑም በአዲሱ በጀት ዓመት ስፖርቱን ከሚመሩት የጽህፈት ቤት ኃላፊዎች ጀምሮ በትኩረት ለመስራት እቅድ ተይዟል።እንደሚታወቀው ለፌዴሬሽኖቹ በመንግሥት በኩል የሚመድበው ዓመታዊ ድጎማ እጅግ አነስተኛና ለሚሰሯቸው ስራዎች በቂ ባለመሆኑ ለመንግሥት ጥያቄ በማቅረብና ጭማሪ በማድረግ በአቅም እንዲጠናከሩ ይሰራል።በኢትዮጵያ ስፖርት መርሐ ግብር መሰረት ይህ የክረምት ወቅት ስልጠናዎችና ውድድሮች ተጠናቀው የታዳጊ ወጣት ፕሮጀክቶች ስልጠና የሚመዘንበት እንዲሁም ክለቦችና የማሰልጠኛ ተቋማት ደግሞ ምልመላ የሚያደርጉበት ነበር።ታዲያ በዚህ ውድድር ማካሄድ በማይቻልበት ወቅት ከታዳጊዎች ምልመላ ጋር በተያያዘ በኮሚሽኑ የታሰበ አማራጭ መንገድ ስለመኖሩም ምክትል ኮሚሽነሩ ማብራሪያ ሰጥተዋል።ሃገር አቀፉ የስፖርት ሪፎርም ምልመላን በተመለከተ የተለዩ ስፍራዎች መኖራቸውን ያመለክታል።እንደየስፖርት ዓይነቶቹ የተሻለ ችሎታ የሚገኝባቸው ስፍራዎች በጥናት ላይ ተሞርክዞ ተቀምጧል። በመሆኑም ከቫይረሱ ጋር በተያያዘ የመንግሥትን ውሳኔና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በመመልከት በባለሙያዎች ስራው የሚከናወን ይሆናል።የኮሮና ወረርሽኝ የስፖርቱን ዘርፍ ሙሉ በሙሉ ጎድቷል፤ እንቅስቃሴዎችንና ውድድሮችን ገድቧል።በስፖርተኞችና ሃገራትም ላይ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ችግሮችን አስከትሏል፤ ይህም አደጋ ነው።ነገር ግን ይህ ጊዜ ያልፋል በሚል ተስፋ ሁሉም በአንድነት እየተጠባበቀ ይገኛል።መንግሥትም ሁኔታዎችን በማገናዘብ ምላሽ ይሰጣል የሚል ተስፋ አለ፤ ይህን ወቅት በመሻገርም ስፖርቱን ወደነበረበት የስፖርት ቤተሰቡም ወደ ተመልካችነቱ የሚመለስበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም።በመሆኑም ይህንን ጊዜ በጋራ ለማለፍ ራስን ከቫይረሱ መጠበቅ እንዲሁም የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማድረግ እንዲቆዩም ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርበዋል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 13/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=35740
[ { "passage": "የኢትዮጵያ የሥነ-ምግባር እና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አየልኝ ሙሉዓለም ለቢቢሲ እንደተናገሩት የሙስና ወንጀል በአገር ላይ እያስከተለ ያለውን ኪሳራ ለመከላከል የተደራጀ እና ንቃተ ህሊናው ከፍ ያለ ማኅብረሰብ ለመፍጠር እንዲሁም ጥፋተኞችን ተጠያቂ ለማድረግ፤ የሥነ-ምግባር እና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን፣ ፖሊስ እንዲሁም አቃቤ ሕግ በጥምረት ከመቼውም በላይ እየሰሩ ይገኛሉ ብለዋል። \n\nከለውጡ ጋር ተያይዞ የጸረ-ሙስና ኮሚሽን ከመቼውም በላይ የተነቃቃበት እና የተለወጠበት ደረጃ ላይ ነው የሚገኘው የሚሉት ኮሚሽነሩ፤ እርሳቸው የሚመሩት ኮሚሽን ግን ከዚህ ቀደም የነበረውን አይነት ተጽእኖ መፍጠር እንደማይችል ይስማማሉ።\n\n• \"የኤክሳይዝ ታክስ አዋጁ ላይ የሚለወጡ ነገሮች ሊኖሩ ይችላሉ\" የጠ/ሚ የኢኮኖሚ አማካሪ \n\n• የኢትዮጵያን አፈር ለማከም የሚመራመረው ዶ/ር መሐመድ አባኦሊ\n\nየኮሚሽኑ ከዚህ ቀደም የነበሩት ኃላፊነቶች እንዲቀሩ መደረጉ የነበረውን ተደማጭነት እና ተጽዕኖ ፈጣሪነትን እንዳሳጣው ኮሚሽነሩ ለቢቢሲ ተናግረዋል።\n\nኮሚሽኑ ከፖሊስ እና ከአቃቢ ሕግ ጋር በቅርበት ስለሚሰራ እንደተቋም ተዳክሟል ማለት አይቻልም የሚሉት ኮሚሽነር አየልኝ፤ \"ወደፊት ግን ሥነ-ምግባር እና ጸረ-ሙስና ተብሎ እስከተቋቋመ ድረስ ያለ ምርመራ ጠንካራ ሆኖ ለኅብረተሰቡ ችግር ምላሽ መስጠት የሚችል አይሆንም\" ብለዋል።\n\nጸረ ሙስና ኮሚሽን ቀደም ሲል ሙስናን የመከላከል፣ የሙስና ወንጀል የመመርመርና ሕግ የማስከበር ኃላፊነቶች እንደነበሩት አስታውሰው፤ አሁን ግን ለሙሰና ተጋላጭ የሚያደርጉ አሰራሮችን ማሻሻል፣ ተቋማትን ማጠናከር እና መደገፍ፣ እንዲሁም ሙስናን የሚጠየፍ ኅብረተሰብ ለመፍጠር ትኩረት አድርጎ እየሰራ እንደሚገኝ ለቢቢሲ አስረድተዋል።\n\nጸረ-ሙስናን የሚያጠናክር እና አቅም እንዲኖረው የሚያስችል አሠራር ቢዘረጋ መልካም ነው የሚሉት ኮሚሽነሩ፤ \"ሙስና የሚፈጸምባቸው የወንጀል አይነቶች እየተራቀቁ እንደመምጣታቸው ወንጀሉን የመከላከል እና የመመርመር ሥራው ተጣምሮ አቅሙ ባላቸው ብቁ ሠራተኞች ቢከናወን ውጤታማ መሆን ይቻላል\" ሲሉም ይጠቁማሉ። \n\nኮሚሽነሩ 2007 እና 2008 አካባቢ ኮንትሮባንድን ጨምሮ በኢትዮጵያ በተደራጀ መልኩ ሕገ-ወጥ ንግድ የተስፋፋበት ዓመት እንደነበረ ይናገራሉ። \n\n\"የመንግሥት ሃብት እና ንብረት በተደራጁ ኃይሎች ምዝበራ የተካሄደበት፣ ሜጋ ፕሮጀክቶች በታሰበላቸው ሰዓት ካለመጠናቀቃቸው ባሻገር ተጨማሪ ሃብት እንዲወጣባቸው የተደረገበት፣ ጨረታ ከግልጽ አሰራርነት ይልቅ በትውውቅ ሲከናወኑ የቆዩባቸው ዓመታት ነበሩ\" የሚሉት ኮሚሽነር አየልኝ፤ ይህ የተንሰራፋው የሙስና ወንጀል ህዝቡን አስመርሮ በኢትዮጵያ የታየውን አይነት የፖለቲካ ለውጥ እንዲመጣ ማስቻሉን ይናገራሉ።\n\n• የኢትዮ-ኤርትራ ድንበር መከፈትን መነሻ ያደረገው ፌስቲቫል \n\n• የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስተዳደር እና የሠራተኛ ማህበር እሰጥ አገባ\n\nኮሚሽነር አየልኝ፤ የመንግሥት ባለስልጣናትን ሃብት እና ንብረት የመመዝገቡ ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ የጠቀሱ ሲሆን፤ ከወረዳ ጀምሮ እሰከ የፌደራል ክፍተኛ ባለስልጣናት የሚገኙ የ180 ሺህ ግለሰቦች በላይ ሃብትና ንብረት እንደተመዘገበ ይናገራሉ። \n\nኮሚሽነር አየልኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይም ሆኑ ሌሎች ባለስልጣናት ሀብታቸውን ቀደም ሲሉ ቢያስመዘግቡም በወቅቱ የማሳደስ ክፍተት መኖሩን ግን ያስረዳሉ።\n\nአንድ የመንግሥት ሠራተኛም ሆነ ባለስልጣን ሀብቱን ካስመዘገበ በኋላ በየሁለት ዓመቱ ማሳደስ እንደሚኖርበት ያስታወሱት ኮሚሽነሩ ነገር ግን የእድሳት ዘመኑን ጠብቆ ማሳደስ ላይ ክፍተት መኖሩን ተናግረዋል።\n\nኮሚሽነሩ አክለውም እስካሁን ባለው ልምድ እድሳቱን ማከናወንና የግለሰቦችን ንብረት... ", "passage_id": "c2d6d83f94df43d497a00840776dab0a" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ህዳር 22 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሴቶች፣ ወጣቶች እና ማኅበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን የኮቪድ-19 ወረርሺኝን ለመከላከል ያደረገውን ምላሽ አበረታታ፡፡", "passage_id": "4e1a2a7e964d96017a999f7febd30729" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- በአገሪቱ የሚታዩ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለመታገል የሁሉም ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ሥራና ርብርብ እንደሚያስፈልግ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ዶክተር አዲሱ ገብረአግዚአብሔር አስታወቁ።", "passage_id": "277888dc642a062550ed451ece4b3665" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን የሚያጣራና የሚመዘግብ የባለሙያዎች ቡድን ማሰማራቱን አስታወቀ። ከአርቲስ ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ በኋላ በተከሰተው የጸጥታ ችግር በሕይወትና በንብረት ላይ የደረሰውን ጉዳት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በቅርብ መከታተል መቀጠሉን አስታውቋል። በዚህም መሠረት የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን የሚያጣራና የሚመዘግብ የባለሙያዎች ቡድን ወደ ሥራ ማሰማራቱን እና በወንጀል ተጠርጥረው የተያዙ ወይም የተከሰሱ ሰዎችን ሰብዓዊ መብቶች አጠባበቅን በተመለከተ ስልታዊ ክትትል እያደረኩ እገኛለሁ ብሏል።ኢሰመኮ የሚያደርገው ምርመራ ውጤት የደረሰውን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ዓይነት፣ መጠን፣ የአጥፊዎችን ተጠያቂነት ለማረጋገጥ፣ የተጎዱ ሰዎች የሚካሱበትና መልሶ የሚቋቋሙበት እንዲሁም ይህን የመሰለ ጥሰት ድጋሚ ከመከሰት ለመከላከል ስለሚያስችሉ እርምጃዎች ተገቢ ግብዓት እንደሚሆን እምነቱን በመግለጫው ላይ አስፍሯል። የተፈጠረውን ሁከት ተከትሎ በወንጀል ተጠርጥረው ከተያዙት መካከል አቶ ጃዋር መሐመድ፣ አቶ በቀለ ገርባ፣ አቶ እስክንድር ነጋ እና ኢንጅነር ይልቃል ጌትነትን ጨምሮ ሌሎች ታሳሪዎችም የሚገኙበትን የእስር ሁኔታ በተከታታይ መመልከቱንም አስታውቋል።በተለይም እነ አቶ ጃዋር መሐመድ እና አቶ እስክንድር ነጋ በመጀመሪያ ላይ ታስረው ይገኙ የነበረበትን በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ስር ያለውን እስር ቤት፣ እንዲሁም አሁን የሚገኙበትን በፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል ምርመራ ቢሮ ከሚገኘው እስር ቤት በተጨማሪም በተለምዶ እንቁላል ፋብሪካ የሚባለው አካባቢ የሚገኘውን ጊዜያዊ የእስር ቤት ኮሚሽኑ መጎብኘቱን እና ታሳሪዎችንና ኃላፊዎችንም ማነጋገሩን ጠቅሷል።ኮሚሽኑ የእነ አቶ እስክንድር ነጋ የእስር አያያዝ ላይ እንዲሻሻል ምክረ ሀሳብ የሰጠባቸው ጉዳዮች ተግባራዊ መደረጋቸውን፣ እንዲሁም በዋስትና መብት ሊለቀቁ ስለሚገባቸው የተወሰኑ ታሳሪዎች የሰጠው ምክር ሃሳብም በሚመለከታቸው የፍትሕ አስተዳደር አካላት ተግባራዊ መደረጉን በመልካም እርምጃነት እውቅና እሰጣለሁ ብሏል።አቶ ጃዋር መሐመድ፣ አቶ በቀለ ገርባ፣ አቶ እስክንድር ነጋ እና አቶ ስንታየሁ ቸኮልን ጨምሮ ስድስት ታሳሪዎች አሁን የሚገኙበት በፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል ምርመራ ቢሮ በሚገኘው እስር ቤት ውስጥ መሆኑን ገልጿል።ጨምሮም ንጽህናው የተጠበቀ፣ የተፈጥሮና የኤሌክትሪክ ብርሃን የሚያገኝ፣ ታሳሪዎቹ ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ ከቤተሰብ አቅርቦት የሚቀበሉበትና ለመተያየት የሚችሉበት፣ በአጠቃላይ አነጋገር ተቀባይነት ደረጃ ያለው ሲሆን፤ በተወሰነ መልኩ ከወቅቱ የአየር ጸባይና ከሕንጻው ባሕሪ የተነሳ የመቀዝቀዝ ጠባይ ያለው በመሆኑ ቅዝቃዜውን ለመቀነስ የሚያስችል ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ተመልክተናል ብሏል ኮሚሽኑ። ኮሚሽኑ ጨምሮ እንዳለው፤ ከታሳሪዎች ከቤተሰብ ጋር በተገቢው መጠን ተቀራርቦ ለመተያየት አለመቻላቸው፣ የክፍሎቹ መቀዝቀዝ፣ የፀሐይ መቀበያ ጊዜ ማጠር፣ የመብራት መቋረጥ የመሳሰሉ ቅሬታዎች ደርሰውኛል ብሏል። ኮሚሽኑ በዚህ ጉዳይ ላይ ከሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት ማድረጉን እና አፈጻጸሙንም በቅርበት እንደሚከታተል አስታውቋል። በተለምዶ እንቁላል ፋብሪካ በሚባለው አካባቢ በሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ጊዜያዊ ማቆያ ጣቢያ ከሚገኙ ታሳሪዎች መካከል የኦኤ.ምኤን ጋዜጠኞች አቶ ጉዮ ዋርዮ እና አቶ መሀመድ ሲራጅ፣ የኦፌኮ አባል አቶ ደጀኔ ጣፋ እንዲሁም ሦስት ትውልደ ኢትዮጵያዊ የሆኑ የውጭ አገር ዜጎችን ኮሚሽኑ መጎብኘቱን አስታውቋል። አብዛኛዎቹ ታሳሪዎች ተገቢ ያልሆነ አያያዝ እንዳልተፈጸመባቸው ተናግረው ለኮሮናቫይረስ ተጋላጭ ልንሆን እንችላለን የሚል ሥጋት እንዳደረባቸው ተናግረዋል ብሏል። የውጪ አገር ዜጎቹን ጨምሮ የተወሰኑ ሰዎች እስካሁን ከቤተሰብ አባላት ጋር አለመገናኘታቸውን እንደገለጹለት ኮሚሽኑ በመግለጫው ጠቅሷል። ኮሚሽኑ ከበርካታ ታሳሪዎች የተነሳለት ቅሬታ፤ እስካሁን ቃላቸውን ለመርማሪ ፖሊስ አለመስጠታቸው እና በተደጋጋሚ የጊዜ ቀጠሮ የተጠየቀባቸው መሆኑ ነው። ኮሚሽኑ የፍትሕ አካላት ውስን በሆነ አቅም በርካታ ጉዳዮችን በማጣራት የሥራ ጫና ያለባቸው ቢሆንም በተቻለ መጠን የምርመራ ሥራውን እንዲያቀላጥፉ ኮሚሽኑ ጠይቋል።በሌላ በኩል የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን በቁጥጥር ስር ያዋላቸውን ታሳሪዎች በሚመለከት ኮሚሽኑ በቅርቡ ለመመልከት በዝግጅት ላይ ያለ ቢሆንም፤ ብዙ ታሳሪዎች ቤተሰቦቻቸው ያሉበትን ቦታ በተሟላ ሁኔታ ያለወቁ በመሆኑ ሁሉም ታሳሪዎች ለቤተሰቦቻቸው ያሉበትን ቦታ በስልክ እንዲያስታውቁ እንዲደረግ ምክረ ሀሳብ ሰጥቼያለሁ ብሏል።የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) የታሳሪዎች ጉዳይን በሚመለከት በሰጡት አስተያየት \"አሁን ባለው የሰላምና መረጋጋት እንዲሁም የኮሮናቫይረስ ሁኔታ፤ ፖሊስና ዐቃቤ ሕግ በቅድሚያ ትኩረት ሊያከናውኑ የሚገባቸው ያላቸውን ጉዳዮች ጠቅሷል።በዚህም መሰረት ሁሉም ታሳሪዎች ቤተሰቦቻቸውን በስልክ በማናገር ያሉበትን ቦታ ማሳወቃቸውን ማረጋጥ እና በተፋጠነ ምርመራ በዋስትና መብት ወይም በነጻ ሊፈቱ የሚገባቸውን ታሳሪዎች በመለየት በአፋጣኝ መለቀቃቸውን ማረጋገጥ መሆኑን አመልክቷል። ", "passage_id": "bee2a899d94dcb20d2f9a2c8d0e76ddf" }, { "passage": "የወቅቱ የዓለም ራስ ምታት በሆነው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች አንቀላፍተው ቢቆዩም ከሰሞኑ የአውሮፓ ሊጎች ወደ ልምምድ መመለስን ተከትሎ የስፖርቱ ኢንዱስትሪ መነቃቃት ጀምሯል። አሁንም የኮሮና ወረርሽኝ (ኮቪድ 19) ስጋት እንዳለ ቢሆንም ጥንቃቄን በተላበሰ መልኩ ወደ ቀድሞው መደበኛ ሁኔታ ለመመለስ ጥረቶች እየታዩ ነው። በዚሁ ምክንያት ተቀዛቅዞ የቆየው አበረታች ቅመሞችን መከላከልና የመቆጣጠር ሥራ ነው። ይህ ስፖርትን በተፈጥሯዊው መንገድ ብቻ እንዲካሄድ የማድረግ ጥረት ሊቀዛቀዝ የቻለው በዓለም አቀፍ ደረጃ ውድድሮች መቋረጣቸውን ተከትሎ ነው። ይሁን እንጂ ከዓላማው አንጻር ረጅም ጊዜ መውሰዱና መዘናጋቱ ዋጋ ሊያስከፍል ይችላል። \nበመሆኑም ዓለም አቀፉ የጸረ አበረታች ቅመሞች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ በስሩ ለሚገኙት ብሔራዊ ጽሕፈት ቤቶች መመሪያ ማዘጋጀቱን ከሰሞኑ በድረገጹ አስነብቧል። ይህም በየሀገራቱ የሚገኙ የጸረ አበረታች ቅመሞች ተቆጣጣሪ ጽሕፈት ቤቶች ወደ ቀደመ ሥራቸው እንዲመለሱ የሚያስችል ርምጃ ነው። ኤጀንሲው በወረርሽኙ ምክንያት በዓለም ዙሪያ ሲሰሩ የቆዩት ናሙና የመውሰድና ምርመራ የማድረግ ሂደቶችን የቀነሰና አንዳንድ ሥራዎችንም በጊዜያዊነት ማቋረጡን በዘገባው ተጠቁሟል። ነገር ግን አሁን ወደ ሥራ ለመመለስ እንቅስቃሴ መደረግ እንዳለበት የኤጀንሲው ፕሬዚዳንት ዊቶልድ ባንካ ይገልጻሉ። በኤጀንሲው ስር ካሉ ተቋማት ጋር ከወቅታዊው ጉዳይ ጋር በተያያዘ በቅርበት ሲሰሩና ድጋፍ ሲያደርጉ ቆይተዋል። አሁን ግን ሥራው እንደቀድሞው መቀጠል ያለበት በመሆኑ፤ በቴክኖሎጂ በታገዘና የናሙና አወሳሰዱን በአዲስ መንገድ ማካሄድ ተገቢ መሆኑን ያመላክታሉ። ለዚህ ደግሞ በጸረ አበረታች መድኃኒት ቁጥጥር ላይ የሚሰሩ አካላት አዲስ ነገር ለመፍጠር ርብርብ ላይ ይገኛሉ። \nየተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ኦሊቨር ኒግሊ በበኩላቸው፣ በዚህ ወቅት ናሙናዎችን ከአትሌቶች ለመውሰድ አዳጋች መሆኑን ነው የሚጠቁሙት። ምርመራው መቀጠል የሚገባው አስፈላጊው የጤናና ንጽህና ሁኔታ የተስተካከለ ሲሆን ብቻ ነው። የአትሌቶችና በዙሪያቸው ያሉ አካላት ጤናም ኤጀንሲው ትኩረት የሚሰጠው ቀዳሚ ጉዳይ ነው። ተቋሙ የአትሌቶችን ናሙና በመውሰድ አበረታች መድኃኒት ተጠቃሚነታቸውን በምርመራ መለየት ብቻም ሳይሆን የጤና ግለ ታሪካቸውንም መመዝገብ ሌላው ተግባሩ ነው። ንጹህ ስፖርት ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት ግንዛቤ ማስጨበጥም እንዲሁ። በመሆኑም በቀጣይ ሳምንታት ከብሔራዊ ተቋማቱ ጋር በመሆን ሥራው በምን መልኩ መቀጠል ይገባዋል በሚለው ላይ መፍትሄ በማፈላለግ ወደ ሥራ የሚመለስ እንደሆነ አብራርተዋል።\nየሯጮቹ ሀገር ኢትዮጵያም የኤጀንሲው አባል ሀገር በመሆን ንጹህ ስፖርት እንዲካሄድ ሚናቸውን ከሚወጡት መካከል ትጠቀሳለች። ተሞክሮውን ለሌላው ዓለምም ማጋራት የቻለና በሥራው ምስጉን የሆነ ጽሕፈት ቤትም በአጭር ጊዜ ለማቋቋም መቻሉ ይታወቃል። በመላው ዓለም ባጠላው በዚህ የወረርሽኝ ወቅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የጸረ አበረታች ቅመሞች ተቆጣጣሪ ጽሕፈት ቤት እንቅስቃሴውን በምን መልኩ እያከናወነ ይገኛል? የሚለውን የጽሕፈት ቤቱ ዳይሬክተር አቶ መኮንን ይደርሳል ያስረዳሉ። የተቋሙን ውስጣዊና ውጫዊ እንቅስቃሴ በሁለት የሚከፍሉት ዳይሬክተሩ፤ የኮሮናን ቫይረስ በመከላከል ረገድ ሠራተኞችን የመቀነስና የንጽህና ቁሳቁስን የማዘጋጀት ሥራዎች መከናወናቸውን ይጠቁማሉ። \nሁለተኛውና ከተቋሙ ውጪ ከአትሌቶች ጋር በመገናኘት የሚከናወነው ደግሞ ከአበረታች መድኃኒት ቁጥጥር ጋር የተያያዘው ሥራ ነው። ይሁን እንጂ ከአትሌቶች ናሙና መውሰድ በእጅጉ ለንክኪ የሚያጋልጥ በመሆኑ አትሌቶችንም ሆነ በምርመራው ተሳታፊ የሆኑ ባለሙያዎችን ለቫይረሱ ተጋላጭ እንዳይሆኑ በማሰብ ለጊዜው ገታ ተደርጓል። \nነገር ግን ሥራውን ሙሉ ለሙሉ ማቆም የማይቻል በመሆኑ ለቫይረሱ አጋላጭ ይሆናሉ የሚል ስጋት ያሳደሩ ሥራዎችን ፎርማት ለመቀየር መሞከሩን ዳይሬክተሩ ይገልጻሉ። በዚህም መሠረት አበረታች ንጥረ ነገር ተጠቃሚ የሆኑ አትሌቶችን የማጋለጥ፣ አትሌቶች ባዮሎጂካል ፓስፖርት ፕሮግራም ሥራን የማጠናከር እንዲሁም ሌሎች ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። በዚህ ጊዜ ውድድሮች የተቋረጡ ቢሆንም ስፖርተኞች ግን በየግላቸው በቤታቸው ውስጥ እንቅስቃሴ ማድረጋቸውን አላቆሙም። ይህንን ተከትሎም ከውድድር ውጪ የሚወሰዱ አበረታች ንጥረ ነገሮችን ከመውሰድ እንዲቆጠቡም ያሳስባሉ። በጥቅሉ በጊዜያዊነት ንክኪ ካለባቸው ሥራዎች በቀር ሌሎች ሥራዎች እንደቀጠሉ ሲሆን፤ የአድራሻ ምዝገባቸውን በመደበኛ መልኩ የሚያደርጉ በመሆኑ በዚህ ላይም መዘናጋት አይገባም።\nዓለም አቀፉ የጸረ አበረታች መድኃኒቶች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ በመግለጫው ባመላከተው መሠረት፤ ጽሕፈት ቤቱም እንደቀደመው የአትሌቶችን ናሙና ወደመውሰድና መመርመር ሥራው ለመመለስ የሚያስችለውን ሁኔታ እያጠና ይገኛል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ ከሆነም ስፖርተኞች ከባለሙያዎች ጋር የሚኖራቸውን ንክኪ በሚቀንስና ለበሽታው አጋላጭ በማይሆን መልኩ መፍትሄ እንደተገኘ በቀጥታ ምርመራው የሚጀመር ይሆናል። በብሔራዊ ቡድን፣ በክለብ እና በማሰልጠኛ ተቋማት የተያዙ አትሌቶች እንዲሁም በቡድን ሆነው የሚሰሩ ሰልጣኞች በዚህ ወቅት ልምምድ አቋርጠው በቤታቸው ይገኛሉ። ምንም ዓይነት የቡድን እንቅስቃሴ የማይፈቀድ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ አትሌቶች በያሉበት አነስተኛ ልምምድ ብቻ የሚያደርጉ ይሁን እንጂ አሁንም እንደ ተቋም አስጊ ሁኔታዎች መኖራቸው አልቀረም። \nይህም ወቅታዊውን ሁኔታ ሽፋን በማድረግ የተከለከሉ ንጥረነገሮችን የመጠቀም አዝማሚያ ሊኖር ይችላል የሚል ስጋት ነው። እስካሁን በተጨባጭ የተገኘ መረጃ ባይኖርም በዓለም አቀፍ ደረጃም ሆነ እንደ ተቋም ስጋቱ አለ። ከአትሌቶች ባሻገር ከጀርባ በመሆን አጋላጭ የሆኑ አካላት አበረታች ቅመሞችን እንዲጠቀሙ በመገፋፋትና በማሳመን የሕግ ጥሰት የመፈጸም አዝማሚያ ሊኖር ይችላል የሚል ግምት አለ። በመሆኑም ስጋቱን ለመቅረፍ የሚያስችሉ ሥራዎች በመከናወን ላይ ነው የሚገኙት። \nበስፖርተኞች በኩል ስለ ጉዳዩ ያለውን ግንዛቤ ለማስፋትም በመገናኛ ብዙኃን በመታገዝ መልዕክቶች በመተላለፍ ላይ ይገኛሉ። በተመረጡ መገናኛ ብዙኃን ላይም የማስታወቂያ እንዲሁም የማንቂያ ሥራዎች እየተካሄዱ መሆኑን የሚጠቁሙት ዳይሬክተሩ በጽሕፈት ቤቱ ድረገጽም መረጃዎችን እያስተላለፉ ይገኛል። ይህም አትሌቱ በሚመቸው መንገድ መረጃ እንዲያገኝ ያስችለዋል። በቀጣይም በመደበኛነት ማስታወቂያዎቹ የሚተላለፉባቸውን የመገናኛ ብዙኃን ቁጥር ለመጨመር ታቅዷል። ሌላው ጽሕፈት ቤቱ በትኩረት እየሄደበት ያለው የሕግ ማዕቀፍ የማሻሻል ሥራ ነው። ኤጀንሲው የጸረ አበረታች ቅመሞች ሕግን ጨምሮ ሌሎች ዓለም አቀፍ ስታንዳርዶችን አሻሽሏል፤ በመሆኑም በጽሕፈት ቤቱ በኩል እአአ በ2021 ተግባራዊ የሚሆኑ የተለያዩ የሕግ ማዕቀፎችን ለመከለስ በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። \nበመጨረሻም ዳይሬክተሩ ስፖርተኞችም ሆኑ ሌሎች የሀገሪቷ ዜጎች የሕክምና ባለሙያዎችን ምክር በመተግበር በዓለም ላይ ከተከሰተው ወረርሽኝ ራሳቸውን እንዲጠብቁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ስፖርተኞች፣ የስፖርት ባለሙያዎች፣ የስፖርት አመራሮች እንዲሁም ሁሉም ባለድርሻ አካላት በበኩላቸው በአበረታች ንጥረ ነገር መከላከልና መቆጣጠር ሥራው ለአፍታ የቆመ ባለመሆኑ መዘናጋት እንዳይኖር ዳይሬክተሩ ያሳስባሉ። ዓለም አቀፉ ኤጀንሲም ሆነ የዓለም አትሌቲክስ ይህ ጊዜ ሲያልፍ ስፖርቱ አደጋ ላይ እንዳይወድቅ በጥንቃቄ እየተመለከቱት ነው። በዚህ መሠረት የሚመለከታቸው አካላት ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው። ተጠቃሚነታቸው ከተረጋገጠም ጽሕፈት ቤቱ አስፈላጊውን አስተዳደራዊ እንዲሁም የወንጀል እርምጃ ከመውሰድ ወደኋላ የማይል በመሆኑ ስፖርተኛው በመደበኛ ጥንቃቄው መቀጠል እንዳለበት ዳይሬክተሩ አስቀምጠዋል።አዲስ ዘመን ግንቦት 10/2012ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "01f73fe2dd71eb57e86861f0d6e6addf" } ]
39ae17924d00962075166fbaa4e196a8
2a4280ce4a5d321ea7ebe75a0df75e0c
ቶማስ ባኽ ተጨማሪ ዓመታት የመቆየት ፍላጎት አላቸው
ዘጠነኛው የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ቶማስ ባኽ በቀጣይ ዓመት በሚካሄደው የኮሚቴው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አስታወቁ። ላለፉት ስምንት ዓመታት ኮሚቴውን የመሩት የ66 ዓመቱ ባኽ በድጋሚ የሚመረጡ ከሆነም ለቀጣይ አራት ዓመታት በፕሬዚዳንትነታቸው የሚቆዩ ይሆናል። በህግ ትምህርት የዶክትሬት ዲግሪ ያላቸውና በስፖርቱ ዓለምም የተዋጣላቸው ቶማስ ባኽ ኮሚቴውን መምራት የጀመሩን እአአ በ2013 ነበር።በምዕራብ ጀርመን የተወለዱት ቶማስ ባኽ በትምህርት ከፍተኛ ደረጃ የደረሱ ቢሆንም ሀገራቸውን በሻሞላ ስፖርት በታላቁ የኦሊምፒክ መድረክ (እአአ 1976 በተካሄደው የሞንትሪያል ኦሊምፒክ) የወርቅ ሜዳሊያ በማጥለቅ ሊያስጠሩ ችለዋል።በሦስት የዓለም ቻምፒዮና ተሳትፎዎችም አንድ የወርቅ ፣አንድ የብር እና አንድ የነሃስ በድምሩ ሦስት ሜዳሊያዎችን ለሃገራቸው አስገኝተዋል።ከስፖርቱ ወደ አመራርነት የገቡት እአአ 2006 ሲሆን፤ የጀርመን ኦሊምፒክ ስፖርት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት በመሆንም ነበር። ከዚያ በሂደት ዓለም አቀፉን የኦሊምፒክ ኮሚቴ በመቀላቀል በተለያዩ ሃላፊነቶች አገልግለዋል። እአአ በ2013 በተካሄደው 125ኛው የኦሊምፒክ ኮሚቴ ጠቅላላ ጉባኤ ወቅት የፕሬዚዳንትነት ምርጫ ላይ ተሳታፊ ሆነዋል።በምርጫውም አብረዋቸው የቀረቡትን አምስት እጩዎች በሰፊ የድምጽ ልዩነት በማሸነፍ የፕሬዚዳንትነት መንበሩን ሊቆናጠጡ ችለዋል።ለቦታውብቁ ሆነው በመገኘታቸውም ተጨማሪ አራት ዓመት ተሰጥቷቸው ለስምንት ዓመታት ሊያስተዳድሩ ችለዋል፡፡በቀጣዩ ዓመት በሚካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ላይም ከኮሚቴው አባላት ተጨማሪ እድል የሚሰጣቸው ከሆነ ለማስተዳደር ፈቃደኛ መሆናቸውን ሮይተርስ በድረገጹ አስነብቧል። ‹‹የኮሚቴው አባላት በድጋሚ የፕሬዚዳንትነት እድል የሚሰጡኝ ከሆነ የምንወደውን ኦሊምፒክ ለማገልገል ዝግጁ ነኝ›› ሲሉም ማረጋገጫ ሰጥተዋል። ከኮሚቴው አባላት በስልጣን እንዲቆዩ ጥያቄ የቀረበላቸው መሆኑን ደግሞ ኢንሳይድ ዘ ጌምስ የተባለው ድረገጽ አስነብቧል።ፕሬዚዳንቱ አክለውም ‹‹እገዛችሁ ለቀጣይ ሥራ የሚያነሳሳኝ ይሆናል›› ብለዋል። ባኽ ከሌሎች ፕሬዚዳንቶች ልዩ የሚያደርጋቸው በኦሊምፒክ ተሳታፊና ውጤታማ በመሆናቸው ሲሆን፣ በስልጣን ዘመናቸው ካሳለፏቸው አስቸጋሪ ሁኔታዎች መካከል በዋናነት የሚጠቀሰው በመንግሥት ጭምር የሚደገፈው የሩሲያ አትሌቶች የአበረታች ቅመሞች ተጠቃሚነት ቅሌት ሩሲያ በኦሊምፒክ መድረክ እንዳትሳተፍ ማድረጋቸው ግንባር ቀደሙ ነው።ሌላኛው ደግሞ በዚህ ወቅት በመላው ዓለም በተከሰተው የኮሮና ወረርሽኝ ሳቢያ ተራዝሞና ተሰርዞ የማያውቀውን ኦሊምፒክ ለአንድ ዓመት እንዲራዘም ማድረግ ነው።አዲስ ዘመን ሐምሌ 13/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=35754
[ { "passage": "የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ የብሔራዊ ፀጥታ አማካሪያቸውን ሊቀይሩ ነው። ፕሬዚዳንቱ አስተዳደሩን ከተረከቡ ባለፈው የአንድ ዓመት ከሁለት ወር ጊዜ ብዛት ያላቸው ከፍተኛ የአስተዳደሩ ባለሥልጣናት ተሰናብተዋል።የብሔራዊ ፀጥታ አማካሪው የጦር ሠራዊት ጀነራል H R McMastern ቀድሞ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር የነበሩት ጃን ቦልተን እንደሚተኳቸው ሚስተር ትረምፕ ትናንት ሃሙስ ማታ በትዊተር አስታውቀዋል። ቦልተን በአሁኑ ወቅት በወግ አጥባቂው ፎክስ ቴሌቨዥን ጣቢያ ተንታኝ ናቸው።አንድ የዋይት ኃውስ ባለሥልጣን እንደተናገሩት ጄነራል ሜክማስተር ሥራቸውን ለቀው በጡረታ እንዲገለሉ ሚስተር ትረምፕ ተስማምተውበት ነው።", "passage_id": "c54912632cac91a76dfe0b304a047243" }, { "passage": "በማሊ የእርቀ ሰላም ስምምነቱ ከተፈረመ ከአንድ ዓመት በኃላም ፈተናዎች አሉ። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተጨማሪ ወታደሮችን በመላክና ሃገሪቱ ከአሸባዊዎች ጋር በምታካሂደው ውግያ ለመርዳት በዚህ ሳምንት ቃል ገብቷል።ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ። ", "passage_id": "86a2a16eb936613aeb3e3f0eef46991d" }, { "passage": "ረጅም ጊዜ በወሰደውና አነታራኪ በሆነው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ሪፖብሊካኑን ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕን ማሸነፋቸው የተነገረላቸው ዲሞክራቱ ጆ ባይደን ከወዲሁ የአስተዳደር ርክክብ ዝግጅታቸውን ፈጥነው ጀምረዋል።በመጪው እአአ ጥር ሃያ ቃለ መሃላ ፈጽመው ሲረከቡ ቁልፍ የሆኑ የትረምፕ ፖሊሲዎችን እንደሚቀለብሱ ተጠቁሟል።ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ባይደን በጠባብ አጠቃላይ ድምጽ የመራጭ ተወካይ ድምጾችን ባሰነፉባቸው ክፍለ ግዛቶች የተፈጸሙ የድምጽ ቆጠራ መዛባቶች ሲፈተሹ ውጤቶቹ ተቀልብሰው አሸናፊ እኔ እሆናለሁ በማለት ክሶች መስርተዋል።ተመራጩ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን እና ምክትላቸው ካማላ ሃሪስ ትናንት የሽግግር ዌብሳያታቸውን ከፍተዋል።አፋጣኝ ትኩረታቸው የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ፤ በወረርሽኙ ምክንያት የደቀቀው ኢኮኖሚ የአየር ንብረት ለውጥና የስርዓታዊ ዘረኝነት ጉዳይ እንደሚሆን አሳውቀዋል።ባይደን በቀድሞ የምግብ እና መድሃኒት አስተዳደር ኮሚሺነር ዶ/ር ዴቪድ ኪስለር እና በዬል ዩኒቨርስቲ ተባባሪ ፕሮፌሰር ዶ/ር ማርሴላ ኑኔዝ ስሚዝ የሚመራ አስራ ሦስት አባላት ያሉት የኮሮናቫይረስ ምክክር ኮሜቴ አቋቁመዋል።ፕሬዚዳንት ትረምፕ በምርጫው መሸነፋቸውን ለመቀበልም ሆነ ለጆ ባይደን ቴሌፎን ደውለው ለማነጋገር ፈቃደኛ አልሆኑም።", "passage_id": "baac689eb9f7f2985207661ecb96852d" }, { "passage": "ፕሬዚደንቱ በቫይረሱ መያዛቸውን ተከትሎ ራሳቸውን ለይተው ማቆየት ስላለባቸው ወደየትም ለመጓዝ አይችሉም። ከፕሬዚዳንታዊ ምርጫው ተፎካካሪያቸው ከጆ ባይደን ጋር የሚያደርጉትሁለተኛው ክርክር የታቀደው እ.ኤ.አ ለጥቅምት 18 ነበር። ፕሬዚደንቱ እሳቸውናባለቤታቸው ቫይረሱ እንድተገኘባቸው ይፋ ያደረጉት በዋሽንግተን ሰዓት ከሌሊቱ ሰባትሰዓት ሊል ሲል ነው። በትዊተር ገጻቸው\" እኔና ቀዳማዊት ዕመቤት ኮቪድ 19 እንደያዝንተረጋጋጡዋል፥ካሁን ጀምረን ራሳችንን ለይተን በመቆየት የማገገም ሂደት እንጀምራለን\" ብለዋል።ፕሬዚደንቱ ይህን ካሉ ከ11 ደቂቃ በሁዋላ ዋይት ሃውስ ቤተ መንግስት የፕሬዚደንቱ ሃኪም ዶክተር ሾን ኮንሊ መግለጫ አውጥተዋ። ፕሬዚደንቱና ሚላንያ ቫይረሱእንደተገኘባቸው ያረጋገጡት ዶክተሩ በሁኑ ወቅት በደህና ሁኔታ ላይ ናቸው።በዋይትሃውስ መኖሪያቸው ተወስነው ሊያገግሙ ታቅዷል ብለዋል፥ በዚሁ ወቅትም ስራቸውንያለምንም እክል ማከናወናቸውን ይቀጥላሉ ብዬ እጠብቃለሁ ብለዋል ዶክተሩየፕሬዚደንት ዶናልድ ትረምፕና ባለቤታቸው ን በኮሮና ቫይረስ መያዝ ዜና ተከትሎምክትል ፕሬዚደንት ማይክ ፔንስ በትዊተር ባወጡት የመልካም ምኞት መግለጫ \" ከኬረን ጋር ሆነን ለውዶቹ ጉዋደኞቻችን ለፕሬዚደንት ትረምፕ እና ለቀዳማዊት እመቤት ሚላንያ ፍቅራችንን እንገልጻለን፥ እንጸልያላቸዋለን ፥ በመላዋ አሜሪካ ከሚሊዮኖች ጋርሆነን በፍጥነት እንድታገግሙና ሙሉ ጤንነታችሁ እንዲመለስ እንጸልያለን፥ እግዚአብሄርፕሬዚደንቱንና ቀዳማዊት እመቤትን ከነቤተሰባችሁ ይባርክ \"ብለዋልየምክትል ፕሬዚደንቱ የፕሬስ ጸሃፊ ዴቪድ ኦማሊ በትዊተር ገጻቸው ባወጡት ቃል ደግሞምክትል ፕሬዚደንቱና ባለቤታቸው ተመርምረው ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸው መረጋገጡንተናግረዋል። በክሮዌስያ ጉዞ ላይ ያሉት የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፔዎ በበኩላቸው ተመርመረው ኮቪድ 19 እንዳልተያዙ አብረዋቸው ለተጓዙ ጋዜጠኞች አረጋግጠዋል።አስከትለውም “ፕሬዚደንቱና ባለቤታቸው ፈጥነው እንዲያገግሙ ጸሎቴ ነው” ብለዋል።በመጪው ምርጫ የዲሞክራቲክ ፓርቲው የፕሬዚደንቱ ተፎካካሪ የቀድሞው ምክትልፕሬዚደንት ጆ ባይደንም በትዊተር ገጻቸው ለፕሬዚደንቱና ለቀዳማዊት እመቤት ሚላንያመልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል \"እኔና ጂል ፕሬዚደንት ትረምፕና ቀዳማዊት እመቤት ሚላንያ በቶሎ እንዲያገግሙ መልካም ምኞታችንን እንገልጻለን ፥ ለፕሬዚደንቱናለቤተሰባቸው ጤናና ደህንነት እንጸልያለን” ብለዋል።", "passage_id": "e1d20915a1f7d178f6b921eb98a2c1a9" }, { "passage": "የቀድሞው የላይቤሪያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አጊስቲም ናጋፉና ለ2017ቱ ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ለመወዳደር እንደሚፈልጉ ትናንት ማክሰኞ ይፋ አደረጉ።በዚሁ መሠረት፣ ለምዕራብ አፍሪቃዊቷ አገር ፕሬዚደንትነት ከሚወዳደሩት ከወቅቱ ምክትል ፕሬዚደንት ጆሰፍ ቦካይ ከታዋቂው ኳስ ተጫዋችና የዲሞክራሲያዊ ለውጥ ኰንግሬስ ፓርቲው ጆርጅ ማኔ ዋህ ከ ሊበርቲ ፓርቲው ቻርልስ ብሩምስኪን እና የቀድሞው ፕሬዚደንት ቻርልስ ቴይለር ወዳጅ ከሆኑት ነጋዴ ከበኖኒ ዩረይ ጋር ሊገጥሙ ነው ማለት ነው። በፕሬዚደንት ኤለን ጆንሰን ሲርሊፍ አስተዳደር የገንዘብ ሚኒስትርም የነበሩት ናጋፉና ለአሜሪካ ድምጽ የአፍሪቃ አገልግሎት በሰጡት ቃል፣ በሕዝብ አስተዳደርም ሆነ በአመራር እረገድ በቂና አኩሪ ልምድ፣ ከጥሩ ስም ጋር ያላቸው እንደሆኑ ተናግረዋል።", "passage_id": "3d929e8b54146646e3dabcd30281ef87" } ]
3cac16e6b6fd2fca6a297657ce7db907
e102093a75b3fa4bfed30677a5eeb468
“ከፍተኛ የክብር ኒሻን ሽልማቱ ከጀነራል ብርሃኑ ጁላ አልፎ ለአገርም ትልቅ ትርጉም ያለው ነው” – ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ ሀብተማርያም የህብረተሰባዊት ኢትዮጵያ የጀግና ሜዳይ ተሸላሚ
 እፀገነት አክሊሉአዲስ አበባ፦ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀነራል ብርሃኑ ጁላ ከጅቡቲ መንግሥት የአገሪቱን የመጨረሻ ደረጃ ከፍተኛ ኒሻን መሸለማቸው ከግለሰቡ አልፎ ለአገርም ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን የህብረተሰባዊት ኢትዮጵያ የጀግና ሜዳይ ተሸላሚ ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ ሀብተማርያም ገለጹ።ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ ሀብተማርያም ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት፣ ሽልማት ማለት አንድ ሰው ለሠራው ሥራ ላበረከተው አስተዋጽዖ እውቅና መስጠት ነው፤ በተለይም እንደዚህ አይነት የእውቅና ሽልማቶች ሲበረከቱ ለግለሰቡ ብቻ ሳይሆን ለአገርም የሚኖራቸው ክብር በጣም ትልቅ ነው። በውትድርና ዓለም ላይ ላሳለፍን ሰዎች የእውቅና ሽልማት ማለት ለአገርም ለራስም ምን ዓይነት ትርጉም እንዳለው በሚገባ እንረዳለን ያሉት ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ፣ ስሜቱ በጣም ከባድ የሚጥለው ኃላፊነትም ትልቅ ነው ብለዋል። እውቅናው በሰራዊቱ ላይ የሚያሳድረው ተነሳሽነት ከፍተኛ ከመሆኑም በላይ የሞራል ድጋፍ እንደሆነም አስታውቀዋል። ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ብርሃኑ ጁላን የክብር ኒሻን ሽልማት ማግኘታቸውን መስማታቸው እጅግ እንዳስደሰታቸው የገለጹት ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ፣ ከደስታም አልፈው በአገራቸው መከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ ኩራት እንዲሰማቸው እንደሆኑም አመልክተዋል። ሠራዊቱ በተለይም በህግ ማስከበር ዘመቻ ላይ ከፍተኛ የሆነ የህይወትና የአካል መስዋዕትነትን ከፍሏል፤ በጣምም አስደናቂ ጀግንነት በአጭር ጊዜ በትንሽ ወጪ አሳይቷል ፤ ከዚህ አንጻር ሽልማቱ ቢያንስበት እንጂ የሚበዛበት አይደለም ብለዋል። የጎረቤት አገር ጅቡቲ መንግሥት በዚህ መልኩ ሠራዊታችንን ሲያከብርና እውቅና ሲሰጥ የኢትዮጵያ መንግሥትም ዝም ማለት የለበትም ያሉት ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ፣ ለእነዚህ ጀግኖች የሚገባቸውን ክብርና እውቅና መስጠት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። ይህ ሽልማት ሠራዊቱ የህይወት የአካል የደምና የላብ መስዋዕትነት የከፈለበት፣ የዚህ ሁሉ ውጤት ነው፤ እርሳቸውም ለሰጡት አመራር ላወጡት እቅድ የሚገባቸው ነው ፤ ግን ደግሞ የሳቸው ሽልማት የሠራዊቱ ብሎም የኢትዮጵያ ነው። ሽልማቱ እንኳን በቦታው ላይ ሆነው ተጋድሎ ለፈጸሙ ቀርቶ እኛ ጡረቶኞቹን ያስደሰተ ልባችንን ያሞቀ እንኳን ኢትዮጵያዊ አልፎም ወታደር ሆንን ያስባለ ነው ብለዋል። ይህ ዓይነቱ ስጦታ የተለመደ አይደለም የሚሉት ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ ከዚህ አንጻርም ከፍተኛ ክብር የሚገባው ሠራዊቱንም ለበለጠ ሥራ ትጋት ቆራጥነትና አገር ወዳድነት የሚያነሳሳ ስለመሆኑም ተናግረዋል።የጁንታው መሰሪ አካሄድ በዚህ ዓይነቱ ጀግንነት መስመር ማስያዝ ባይቻል ኖሮ ችግሩ ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጎረቤቶቻችን ይተርፍ ነበር ።ህንንም ጠንቅቀው ያውቃሉ ፤ ከዚህ አንጻርም ሽልማቱ “የእኛን ችግር ፈታችሁልን፣ እናንተ ሰላም ስትሆኑ ነው እኛ በሰላም መኖር የምንችለው “ የሚል መልክዕክትም ያለው ነው ብለዋል። ሠራዊቱ በጎረቤት አገራት እየተዘዋወረ በሚያደርገው የሰላም ማስከበር ሥራ ከፍተኛ እምነት እንዳደረባቸውም ማሳያ እንደሆነ ገለጸዋል። “ብላቴ ላይ አየር ወለድና ኮማንዶዎች ሲመረቁ በክብር እንግድነት ተገኝቼ ነበር ፤ በወቅቱም ባየሁት ነገር በአመራሮቹ ብቃት፣ በሙያዊ ክህሎታቸው፣ በስነ ስርዓታቸው እጅግ ከመደሰቴና ከመኩራቴም በላይ ሠራዊቱን የሚበግረው ምንም ኃይል እንደማይኖር ተናግሬ ነበር።አሁንም ጁንታው ለረጅም ዓመታት የተዘጋጀበትን ምሽግ ንዶ ይህንን የመሰለ ውጤት ማምጣቱ የግምቴን ትክክለኝነት አሳይቶኛል “ ብለዋል። ኢትዮጵያ አሁን የገጠማትን ዓይነት ችግር ምን ጊዜም ሊገጥማት እንደሚችል ታሳቢ በማድረግ ሠራዊቱን አሁን ካለው አቋም እንዳይለቅ ከዚህም በላይ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እንዲታገዝ ማድረግ ያስፈልጋል፤ ይህንን ማድረግ ከቻልን ምንም የሚገታን ኃይል አይኖርም ሲሉም ተናግረዋል። አዲስ ዘመን ጥር 5 ቀን 2013  ዓ.ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=39376
[ { "passage": "ለቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም ደሳለኝ እና የቀድሞዋ ቀዳማዊ እመቤት ሮማን ተስፋዬ ላበረከቱት አስተዋጽኦ የወርቅና ከፍተኛ የክብር ዲፕሎማ ተበረከተላቸው፡፡ ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያምና ባለቤታቸው ትናንት በብሄራዊ ቤተመንግስት በተደረገ የሽኝት ፕሮግራም ነው ሽልማቱ የተበረከተላቸው፡፡በስነስርዓቱ ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ የሀገሪቱን እድገት በማስቀጠልና በተለያዩ ሀገራዊና አለማቀፋዊ መድረኮች በመገኘት የሃገሪቱን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ማጠናከራቸውን አስታውቀዋል፡፡ለአፍሪካ ምሳሌ በሚሆን መልኩ ሰላማዊ የስልጣን ርክክብ  በማድርጋቸውም  አድናቆታቸውን  ገልጸዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ  ˝አቶ  ኃይለማሪያም ደሳለኝ ማገልገልን ያወረሱን ታላቅና ጀግና መሪ ናቸው˝ ብለዋል፡፡አቶ ኃይለማሪያም በበኩላቸው ለተደረገላቸው የምስጋናና የሽኝት ፕሮግራም ለኢትዮጵያ ህዝብ፣ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለካቢኔ አባላቶቻቸው፣ ለመንግሰት ሰራተኞችና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ምስጋና አቅርበዋል፡፡የተጀመረው የለውጥ እንቅስቃሴ ወደኋላ እንዳይቀለበስ ህብረተሰቡ ለአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር  አብይ ድጋፍ እንዲያደርግ እና ጊዜ እንዲሰጣቸው ጥሪ አቅርበዋል፡፡(ኢዜአ) ", "passage_id": "1788b09c57e28c03476cba0db5e7cb15" }, { "passage": "የኅብረተሰብዓዊት ኢትዮጵያ ጀግና ሜዳይ ተሸላሚ የነበሩት ብሪጋዲየር ጄነራል ተፈራ ለገሠ ዛሬ አረፉ፡፡ብሪጋዲየር ጄነራል ለገሠ አሜሪካ ውስጥ በሕክምና ሲረዱ መቆየታቸውን ለቤተሰቡ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለቪኦኤ ገልፀዋል፡፡ብ/ጄነራል ለገሠ ተፈራ ከሃረር የጦር አካዳሚ በ1959 ዓ.ም ተመርቀው የኢትዮጵያ አየር ኃይልን መቀላቀላቀላቸውንና የጄት አብራሪና መምህር ሆነው ማገልገላቸውን የሕይወታቸው ታሪክ ይናገራል፡፡የዚያድ ባሬ ሶማሊያ ጦር በ1960ዎቹ መጨረሻ ኢትዮጵያን በምሥራቅና በደበቡብ ምሥራቅ በኩል ወርሮ በነበረ ጊዜ የዘጠነኛው ስኳድሮን ባልደረባ የነበሩት ተዋጊ ጄት አብራሪ ጄነራል ለገሠ ተፈራ አምስት የሶማሊያ ጦር አይሮፕላኖችን በአየር ላይ ውጊያ መትተው መጣላቸው ይነገርላቸዋል፡፡ጄነራል ለገሠ ተፈራ በጦር እሥረኛነት ለአሥራ አንድ ዓመታት ሶማሊያ ውስጥ ከቆዩ በኋላ ወደ ሃገራቸው ሲገቡ ወደ ኢትዮጵያ አየር ኃይል ተመልሰው በበረራ አስተማሪነት አገልግለዋል፡፡ግንባር ላይ ለፈፀሙት ጀብዱም የጦር ሜዳ ጀብዱ ሜዳይና የኅብረተሰብዓዊት ኢትዮጵያ ጀግና ሜዳይ በወቅቱ የኢትዮጵያ መሪ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ተጠልቆላቸዋል፡፡ብሪጋዲየር ለገሠ ተፈራ ኮ/ል መንግሥቱ ኃይለማርያምን ከሥልጣን ለመገልበጥ የተሞከረው የ1983ቱ ኩዴታ ሲከሽፍ ወደ አሜሪካ ተሰድደው እስከ ሕልፈታቸው እዚያው ኖረዋል፡፡ብሪጋዲየር ለገሠ ተፈራ ሦስት ልጆችን አፍርተዋል፡፡", "passage_id": "769b29a3c1cb3a91fdffeedf4ccc8093" }, { "passage": "በኢትዮጵያ በየዓመቱ የሚካሔዱ የሽልማት መርሃ ግብራት ጥቂት ናቸው። እነዚህም በሙዚቃ፣ በፊልም እንዲሁም በመጻሕፍት ሕትመት ሥራዎች ላይ ያተኩራሉ። ሁለገብ የሆኑ የመመሰጋገኛና የማመስገኛ መድረኮች ግን ብዙም አልተፈጠሩም። በዚህ መካከል ነው ከሰባት ዓመታት በፊት የበጎ ሰው ሽልማት በሚል ሥያሜ የተጠራ ዓመታዊ የሽልማት መርሃ ግብር የተጀመረው። ሽልማቱ በአክሱም ሆቴል በአምስት የሽልማት ዘርፎች በማካሔድ የጀመረው ጉዞ ዛሬ ላይ ዐሥር የሚጠጉ ዘርፎችን አካትቶና በቅርቡም በበጎ አድረጎት ድርጅትነት ተመዝግቦ ሰባተኛውን መርሃ ግብር ለማካሔድ ዋዜማው ላይ ይገኛል።የበጎ ሰው ሽልማት የየዓመቱን ተሸላሚዎች በሚያወሳበት ዓመታዊ መጽሔት መግቢያ ተከታዩ ሐሳብ ተከትቦ በየዓመቱ ይነበባል፥ “…አገራዊ ኀላፊነት ወስደው ትውልድን የሚጠቅም፣ የአገርን ዕድገት የሚያስመነድግ፣ ለሌሎች አርዓያ የሚሆን፣ የታሪክን ማርሽ የሚለውጥ ሥራ የሠሩትን… የማበረታታት፣ የማድነቅ፣ የመሸለምና ዕውቅና የመስጠት ባሕል እምብዛም የለንም። ከዚህ ይልቅ የመተቻቸትና የመናናቅ፣ የመመቀኛኘትና የመጓተት ልማዶች ጎልተው ይታያሉ። ይህንን ልማድ ለመቅረፍና አገራዊ ጀግኖችን ለማውጣት፣ ለመሸለምና ትውልዱ እንዲያውቃቸው ለማድረግ መሥራት የመንግሥት ብቻ ኀላፊነት አይደለም። ኢትዮጵያዊ ዜጋ ሁሉ ሊፈጽመው የሚገባ የዜግነት ግዴታው ነው።”በዚሁ መሰረት የ2011 የበጎ ሰው ሽልማት በሥነ ጥበብና ኪነጥበብ ሥር ዘንድሮ በያዘው የፎቶግራፍ ዘርፍ እጩ ከሆኑት መካከል፤ በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ፎቶ አንሺ በመሆን ለበርካታ ዓመታት ያገለገለው ፎቶግራፈር ዳኜ አበራ አንዱ ነው። ከአዲስ ማለዳ ጋር ባደረገው ቆይታ ለሽልማቱ እጩ ከመሆኑ በፊት ስለሽልማቱ የሚያውቃቸው ጥቂት ነገሮች እንደነበሩ ገልጾ፤ ይልቁንም በሙያቸው ውለታ የዋሉ፣ ጥሩ ነገር ያበረከቱ ነገር ግን የተዘነጉ ሰዎችን የሚያስታውስ ነው ሲል ጠቅሷል።ዳኜ ከራሱ መታጨት ባሻገር ዘርፉ ትኩረት ማግኘቱ እጅግ አስደስቶታል። “ሙያውን በሽልማት ዘርፍ ማካተቱ ቀላል የሆነላቸው አይመስለኝም፤ ብዙ ትግልን እንደጠየቃቸው አምናለሁ። ምክንያቱም ብዙ ሰዎች ሙያውን በስፋት አያውቁትምና ጥቆማ ለማግኘትም ያስቸግራል” ሲልም አስተያየቱን ሰጥቷል። በጎ ሰው ሽልማት ዘርፉን ማካተቱ ከሱም አልፎ ሙያው ላይ ላሉ በቅርበት ለሚያውቃቸው ባለሙዎችም ጭምር መነቃቃትን የፈጠረ እንደሆነ አስታውሷል።በአሁኑ ወቅት ሁሉም ሰው በተንቀሳቃሽ ስልክ ካሜራ ይዞ በሚንቀሳቀስበት ጊዜ የፎቶግራፍ ባለሙያ መታወሱም ቀላል እንዳይደለ ዳኜ በአጽንዖት ለአዲስ ማለዳ ያነሳው ነጥብ ነው። ዳኜም መታጨትን በራሱ እንደ ሽልማት ቆጥሮት፤ ከወዲሁ መታሰቢያነቱንም በባድመ ጦርነት ሕይወቱን ላጣውና በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ባልደረባው ለነበረ ፎቶግራፈር ዘውዱ ጥላሁን ይሁንልኝ ብሏል።የበጎ ሰው ሽልማት አዘጋጆች “እኛ የምችለውን እንሥራ፤ በዐቅማችን እንወጥነው” ብለው የጠነሰሱት የበጎ ሰው ሽልማት በአሁኑ ሰዓት መምህርነት፣ ቅርስና ባሕል፣ ሳይንስ፣ መንግሥትና የሥራ ኀላፊነት፣ ንግድና ሥራ ፈጠራ፣ የበጎ አድራጎት ሥራዎች፣ ኪነጥበብ /ፎቶግራፍ/፣ ሚድያና ጋዜጠኝነት እንዲሁም ልዩ ተሸላሚ ዘርፎችን ይዟል። ማኅበራዊ ጥናት ዘርፍ በተለያዩ ምክንያቶች ዘንድሮም ሳይካተት የቀረ ሲሆን ለኢትዮጵያ መልካም የሠሩ የውጪ አገር ዜጎች የተሰኘው ዘርፍም ለአገራቸው መልካም የሠሩ በውጪ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በሚል ዘርፍ ተተክቷል።የበጎ ሰው ሽልማት ዘንድሮ የያዘው አዲስ ዜና አለ፤ ይህም ለዓመታትና በተደጋጋሚ ሲያቀርብ የነበረው ጥያቄ መልስ አግኝቶ፤ በበጎ አድራጎት ማኅበራት ኤጀንሲ መመዝገቡ ነው።የበጎ ሰው ሽልማት በበጎ አድራጎት ድርጅትነት መመዝገቡ በአንድ ወገን አስተዳደራዊ ጥቅሞችን እንደሚያስገኝ የቦርድ አባልና ገጣሚ አንዷለም አባተ (የአጸደ ልጅ) ይጠቅሳል። ይህም የተደራጀ ቢሮና ቋሚ አድራሻ እንዲኖረው፣ የሰው ኀይል ቀጥሮ ለማሟላትና መሰል ተያያዥ ሁኔታዎችን ለማካተት ያስችላል። ያም ብቻ አይደለም የስብሰባ ቦታንና የአባላቱን መገናኛ ቋሚ በማድረግ በኩል በብዙ ያግዛል።ከዛ ባሻገር ወደፊት ከሽልማት ውጪ ያሉ በጎ አድራጎቶችን በማንቀሳቀስና ከሚመለከታቸው ሁሉ ጋር ተባብሮ ለመሥራት ይህ የመጀመሪያው እርምጃ መሆኑን ነው አንዷለም ለአዲስ ማለዳ የገለጸው። በየዓመቱ በሚያዙ ዕቅዶች መሠረትም ሥራዎችን ለማከናወን ያግዛል ብሏል። በእርግጥ የበጎ ሰው ሽልማት የበጎ አድራጎት ድርጅትነት ሳይሰጡት በፊትም ምክንያት ሆኖ ያስገኛቸው መልካም ውጤቶች ነበሩ። አንዱም የተሸላሚዎች እውቅና ማግኘት ነው። ይህም ተሸላሚዎች በኅብረተሰቡ ዘንድ መልካም ሥራዎቻቸውና ምሳሌ የሚሆኑ ጥረቶቻቸው እንዲታወቁና ክብርም እንዲያገኙ ማስቻሉ ነው።ሽልማቱ በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነት እያገኘ መሔዱንም አንዷለም አስታውሷል። ለዚህም የሰዉ ተሳትፎ ከጊዜ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱና ጥቆማዎች ከአገር ዳር እስከዳር እንዲሁም ከባሕር ማዶ ጭምር መቅረባቸው ማሳያ ነው። “ዘንድሮ ድርጅቶችም ከሠራተኞቻቸው መካከል መጠቆም ጀምረዋል” ሲል አንዷለም አክሏል። ዘንድሮ በድምሩ 291 ሰዎች በእጩነት የተጠቆሙ ሲሆን በወራት የመለየት ሥራም አሁን ላይ በድምሩ 27 እጩዎች ቀርበዋል።የማኅበራዊ ዘርፍ ባሳለፍነው ዓመት የበጎ ሰው ሽልማት እንዲሁም በዘንድሮው ሳይካተት የቀረበትን ምክንያትም አንዷለም አስረድቷል። ይህም የሆነው ጠቋሚዎች ለዘርፉ ብለው የሚልኳቸው ሰዎች በአብዛኛው በሌሎች ዘርፎች ይልቁንም በመምህርነት ሊካተቱ የሚችሉ እየሆኑ በመገኘታቸው ነው። ጠቋሚዎች እጩዎችን ሲያቀርቡ አያይዘው ስለማንነታቸው አጠር ያለ መግለጫ ማኖራቸው ሥራውን ያገዘ ቢሆንም በጎ ሰውን ሽልማት እንደወትሮ አሁንም ያጋጠመው ችግር አለ። ይህም ሰዎች ታሪካቸውን ሰንደው የማስቀምጡ ልመድ የሌላቸው መሆኑ ነው።“እጩዎች ከተለዩ በኋላ ለምዘና በሚያበቃ መልኩ ለማውጣት የሚደረገው ትግል ሁሌም ፈታኝ ነው። ሥራዎቻውንና አስፈላጊ ሰነዶችን ማግኘት ያስቸግራል” ሲል አንዷለም ለአዲስ ማለዳ ሌላው ተግዳሮት መሆኑን ጠቅሷል። የመገናኛ ብዙኀንን ሚና ደግሞ በበጎ ጎን አንስቷል። ይህም የበጎ ሰው ሽልማት አዳዲስ መረጃዎችን ለሕዝቡ ከማድረስ ጀምሮ ጥቆማ እስከ ማድረግ ድረስ በመገናኛ ብዙኀን በኩል ከወትሮው የተለየ እንቅስቃሴ መታየቱ ነው። ይህም ሽልማቱ የሁሉም እንዲሁም የጋራ መሆኑ እየታወቀ መምጣቱን ያሳያል።“አሁንም ግን በተለይ ጥቆማን በተመለከተ ከሕዝብ ብዙ የሚጠበቅ አለ። ዋናው ጠቋሚ ሕዝብ ነው፤ አሁንም በየዘርፉ ያልደረስንባቸው በርካቶች ስለሚሆኑ የሕዝቡ ጥቆማ የበለጠ ሊሻሻል ይገባዋል ብለን ነው የምናስበው” ሲልም አንዷለም ተናግሯል።ዘንድሮ ሰባተኛው የዓመቱ በጎ ሰው ሽልማት ከሳምንት በኋላ እሁድ፣ ነሐሴ 26 በኢንተርኮንቲነንታል ሆቴል ይካሔዳል። በዚህም ለዓመቱ የቀረቡት 27 እጩዎች ሁሉ ለበጎ ሰው አሸናፊ መሆናቸውን እንደወትሮው አዘጋጆቹ ይገልጻሉ። አንዷለም “ከጣት ጣት ይልቃል እንዲሉ እንጂ 27ቱም ለእኛ በጎ ሰዎችም አሸናፊዎችም ናቸው” ብሏል።የበጎ ሰው ሽልማት በጎ አድራጎት ድርጅት፤ “በሥራ ክፍተት ይኖራልና ይህን ተጋግዞ መሙላት ያስፈልጋል። በጎ ሰው ሽልማት በብሔር፣ በሃይማኖት፣ በቋንቋ ወይም በመደብ የተመሠረተ አይደለም፤ ከእነዚህ በላይ ሆኖ ነው የሚሠራው” ሲል በአንዷለም በኩል ለአዲስ ማለዳ አንባብያን መልዕክቱን ልኳል።አዲስ ማለዳም ለዘንድሮ የበጎ ሰው ሽልማት እጩዎችም መልካም ዕድልና ምኞቷን ታስተላልፋለች። በዘንድሮ የበጎ ሰው ሽልማት በትሩ አድማሴ፣ ዶ/ር አሚር አማን እና ግርማ ወንዳፍራሽ በመንግሥታዊ የሥራ ኀላፊነት ዘርፍ፤ ኦባንግ ሜቶ፣ ታማኝ በየነ እና ጸጋዬ ታደሰ (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ዕድገት አስተዋጽዖ ያበረከቱ በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ዘርፍ፤ ዳንኤል መብራቱ፣ ክቡር ገና እና ነጋ ቦንገር በንግድን ሥራ ፈጠራ፤ በልሁ ተረፈ፣ አማረ አረጋዊ እና አንድነት አማረ በሚድያ እና ጋዜጠኝነት፤ ሽታዬ ዓለሙ (ፕሮፌሰር)፣ ሕይወት ወልደመስቀል እና መስከረም ለቺሳ (ዶ/ር) በመምህርነት፤ ለገሠ ነጋሽ (ፕሮፌሰር)፣ሰብስቤ ደምሴ (ፕሮፌሰር) እና ታደለች አቶምሳ (ዶ/ር) በሳይንስ፤ ሚካኤል ጸጋዬ፣ በዛብህ አብተው እና ዳኜ አበራ በኪነጥበብ (ፎቶግራፍ) ዘርፍ፤ ጀንበር ተረፈ (ዶ/ር) ፣ አብዱላዚዝ መሐመድ (ዶ/ር) እና ላሌ ለቡኮ በበጎ አድራጎት፣ አበዱልፈታ አብደላ፣ አድማሴ መላኩ እና ሳሙአል መኮንን በቅርስና ባሕል ዘርፍ የታጩ በጎ ሰዎች ናቸው።ቅጽ 1 ቁጥር 42 ነሐሴ 18 2011", "passage_id": "e826d06d9d45d018a5bfb92584a87d54" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ህዳር 8 ፣2013 (ኤፍ ቢ ሲ) “ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ” መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ፡፡የዩኒቨርሲቲው ማህብረሰብ በያሉበት በመሆን ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ያላቸውን ክብር እና አጋርነት ገልጸዋል፡፡ዩኒቨርሲቲው ለመከላከያ ሰራዊቱ 1 ሚሊየን ብር በጥሬ እንዲሁም 2 ሚሊየን 286 ሺህ ብር የሚያወጡ የተለያዩ የምግብ ቁሳቁሶችን ድጋፍም አድርጓል፡፡የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ደረጀ እንግዳ ህግ የማስከበር ሂደቱን ተከትሎ ለቀረበው ሃገራዊ ጥሪ ምላሽ ለመስጠት ዩኒቨርሲቲው እንደተቋም የሚጠበቅበትን አስተዋፅዖ ለማበርከት መወሰኑን ተናግረዋል፡፡የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት በመከላከያ ሰራዊት ላይ የተቃጣው ጥቃት እኩይ ተግባር በመሆኑ እንደሚያወግዙት እንዲሁም መንግስት እየወሰደ ያለውን ህግ የማስከበር እርምጃ እንደሚደግፉና የሚጠበቅባቸውን አስተዋፅዖ ለማበርከት ዝግጁ መሆናቸውን ነው የገለጹት፡፡የተቋሙ የአካዳሚክ ዘርፍ ሰራተኞች የደመወዛቸውን 10 በመቶ እንዲሁም የአስተዳደር ዘርፍ ሰራተኞች ደግሞ የደመወዛቸውን 5 በመቶ ለሰራዊቱ ድጋፍ እንዲደረግ ቃል ገብተዋል።", "passage_id": "1b448ce269be7348dfe44d8c8860d238" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ህዳር 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) “ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ” መርሃ ግብር በተለያዩ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችና የፌደራል ተቋማት ተካሄደ።መርሃ ግብሩ በሰላም ሚኒስቴር መስሪያ ቤት የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚልን ጨምሮሚኒስትር ደኤታዎች እና የተቋሙ ሰራተኞች በተገኙበት ተካሂዷል።የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት፥ ክብርና አድናቆት ለሚገባው አርማችንና መከታችን ለሆነው ለመከላከያ ሰራዊታችን ክብራችሁንና ፍቅራቸውን ለገለጹ የሰላም ቤተሰቦች ከልብ ምስጋና አቅርበዋል”።ወይዘሮ ሙፈሪሃት፥ “መከላከያችን ህዝቡን አምኖ እራሱን ሰጥቶ ጀርባውን ሳይሆን ግንባሩን ስለሀገሩና ስለህዝብ ሲል የተሰለፈ ሀይል ነውና ከክብር፣ ከምስጋና ከፍቅር ውጭ አይገባውም ነበር” ብለዋል።በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርም የሚኒስቴር መስያ ቤቱ አመራሮች እና ሰራተኞች በዛሬው እለት በተካሄደው “ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ” መርሃ ግብር ላይ በመሳተፍ ለመከላከያ ሰራዊት ድጋፋቸውን ገልፀዋል።በትራንስፖርት ሚኒስቴርም “ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ” መርሃ ግብር የትራንስፖርት ሚኒስትር ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስን ጨምሮ ሚኒስትር ዴኤታዎችና የተለያዩ የሥራ ክፍል ሓላፊዎች እንዲሁም አጠቃላይ ሠራተኛው በተገኙበት ተካሂዷል።በኢፌዲሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴርም መርሃ ግብሩ የባህልና ቱሪዝም ሚንስትር ዶክተር ሂሩት ካሳውን ጨምሮ ሚንስትር ዲኤታዎች፣ አመራሮች እና ሰራኞተኞች ተካሂዷል።የጤና ሚኒስቴር የስራ ሃላፊዎችና ሰራተኞች የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በተገኙበት፥  “ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ” በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው መርሃግብር ለጀግናው የመከላከያ ሰራዊት ያላቸውን ክብርና ድጋፍ ገልጸዋል።የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አመራሮችና ሠራተኞችም “ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ” በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው መርሃ ግብር ላይ የተካፈሉ ሲሆን፥ “ለመስዋዕትነታቸሁ ክብር ሰጥተናል፣ ወኔያቸሁና ጀግንነታችሁ አኩርቶናል፣ እናመሰግናለን፣ ሁሌም ከጎናችሁ ነን” የሚል ምልእክት አስተላልፈዋል።የግብርና ሚኒስቴር እና የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት አመራሮች እና ሠራተኞችም “ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ” መርሃ ግብር ለመከላከያ ሰራዊታ ያላቸውን ክብር ገልፀዋል።የትምህርት ሚኒስቴርም “ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ክብር እቆማለሁ” ጥሪን ተቀብሎ የሁለት ደቂቃ የድጋፍ ስነ ስርዓት አካሂዷል።የሚኒስትሩ አመራሮች እና ሰራተኞች ለአንድ ደቂቃ ቀኝ እጃቸውን ደረታቸው ላይ በማድረግ እና ለአንድ ደቂቃ ደግሞ በማጨብጨብ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ያላቸውን አጋርነት ገልፀዋል።የሳይንስና ከፍተኛ  ትምህርት ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎችና  ሰራተኞች   “ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ክብር እንቆማለን” በሚል መሪ ቃል “ መከላከያ  ጥቃት የኛ ጥቃት ነው፣ የተቃጣውን ጥቃት እናወግዛለን፣ መከላከያ ሠራዊታችንን በምንችለዉ ሁሉ  እንደግፋለን”  በማለት ድጋፋቸውን ገልጸዋል።የኢፌድሪ ማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞችም “ለሃገሬ የመከላከያ ሰራዊት ክብር እቆማለው!” ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ያላቸውን ክብርና ድጋፍ ገልጸዋል።የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ አመራርና አባላት “ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ” መርሃ ግብር ላይ በመሳተፍ ለጀግናው የመከላከያ ሰራዊት ያላቸውን ክብርና ድጋፍ ገልጸዋል።የኢትዮጵያ አየር መንገድ አመራሮች እና ሰራተኞችም በመርሃ ግብሩ ላይ በመሳተፍ ለመከላከያ ሰራዊት ያላቸውን አጋርነት እና ክብር አሳይተዋል።", "passage_id": "3672ffcdc8edb699d5191ee6d3ec1cb1" } ]
9cacab0912af9a3a346a38e919da73be
d3790d6356985a77292a210004ae3d28
ከሌሊሶ ሜዳ እስከ ማልታ ደሴት
በደቡብ ክልል ከምባታ ጠምባሮ ዞን ዋና ከተማ ዱራሜ ነው የተወለደችው። ሰባት ልጆች ላፈሩት እናት እና አባቷ አምስተኛ ልጅ ስትሆን፤ ከልጅነቷ ጀምሮ ነበር በኳስ ፍቅር የወደቀች። የእግር ኳስ መሰረቷን የጣለችው ተወልዳ ባደገበችበት ዱራሜ ከተማ በሰፈር ውስጥ ነው። ከሰፈር የተነሳው የኳስ ህይወት ከሀዋሳ ከተማ አንስቶ በደደቢት እና ብሔራዊ ቡድን በግብ አስቆጣሪነት ስሟ እስከመነሳት የደረሰም ነበር፤ የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድንና በማልታ ቢርኪርካራ እግር ኳስ ቡድን አጥቂ ሎዛ አበራ። የሎዛ የእግር ኳስ ህይወቷ ሀ፣ሁ ከሌሊሶ ሜዳ ይጀምራል። የዱራሜዋ የትናነቷ ታዳጊ ባደገችበት ሠፈር ካሉ ወንድ እኩዮቿ ጋር እየተጋፋች በመጫወት ነበር የጀመረችው። ከወንዶች ጋር ሴት ሆና መጫወቷና ብቃቷ ለብዙዎች ግርምት ከመፍጠር ባሻገር ከሠፈሯ ‘ሌሊሶ’ ሜዳ አሁን ያለችበት ትደርሳለች ብለው ብዙዎች አልገመቱም። ሎዛ በኳሱ ወንዝ ተሻጋሪ ታሪክ መስራትን እንደምትችል በልቧ የነበረውን መሻትና ወኔ በአንድ ወቅት ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዲህ ብላ ነበር ። «በእግር ኳስ ሃገሬን ወክዬ ዓለም አቀፍ መድረክ ላይ መጫወት የልጅነት ህልሜ ነው። ይሄንኑ ህልሜን እውን ለማድረግ እልህ አስጨራሽ ፈተናዎችን በመጋፈጥ እውን አድርጌዋለሁ» ስትል ገልፃለች። በሎዛ የልጅነት የኳስ ህይወት ውስጥ የነበሩት ማህበራዊ ተጽእኖዎችን ትልቁ ፈተና ፈጥሮባታል። ኳስ ያላት የበዛ ፍላጎት በቤተሰቦቿ ዘንድ ይህ የተወደደ አልነበረም። «ትምህርትሽን አጥብቀሽ መያዝ ነው ያለብሽ»የሚል ምክር አዘል ቁጣ አስከትሎባታል። «ከምንም ነገር በፊት ፍላጎት ይቀድማል። እግር ኳስ መጫወት ከሆነ ፍላጎታችን፤ ያንን ፍላጎታችንን ለማሳካት ሳይደክሙ መሥራት። ሌላም ከሆነ እንደዚሁ። ተስፋ ሳይቆርጡ እደርሳለሁ ያሉበት ቦታ እንደሚደረስ ሁሌም ለአእምሮ መናገር፤ ራስን ማሳመን፤ ሥራን ማክበር ማለትም አንድ ሙያ የሚጠይቀውን ዲሲፕሊን መከተል ያስፈልጋል» የምትለው ሎዛ ትምህርቷን ሳትለቅ ኳሱን ጠበቅ ማድረጉን አማራጭ አድርጋ ገፋችበት። በኳሱ የነበራት ተሳትፎ የከንባታ ዞንን ወክላ የመጫወት አጋጣሚን ፈጠረላት። ይህም የሎዛን ከልጅነት ህልሟ የሚያደርሷት ባቡር ውስጥ መግባቷን ያረገገጠ ነበር። የመጀመሪያ ፕሮፌሽናል ኳስ ተጫዋች ነት የተጀመረበት ይህ አጋጣሚ፤ ወደ ክልል አሻገራት። ደቡብ ክልልን ወክላ ለመላው ኢትዮጵያ ውድድር እንድትሳተፍ ሆነ። ለዱራሜዋ ህልመኛ በአደማ የተካሄደው ውድድሩ የባቡሩ ጉዞ ሃዲዱን ጠብቆ እየተጓዘ መሆኑን ያመላከተ ነበር። ሎዛ በመላው ኢትዮጵያ የነበራት እንቅስቃሴ በሐዋሳ ሴቶች እግር ኳስ ቡድን አሠልጣኝ የሆነው ዮሴፍ ገብረወልድ እይታ ውስጥ አስገብቷታል። ከሌሊሶ ሜዳ የተነሳው የኳስ ህይወቷ መዳረሻውን በሐዋሳ እግር ኳስ ክለብ አደረገ። ፈጣኑ የሎዛ ጉዞ ኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ላይ ታሪክ መስራቱን ተያያዘው። ሎዛ ከሐዋሳ ጋራ ዋንጫ ባታነሳም በቆየችባቸው ሁለት ተከታታይ ዓመታት የክለቡ ኮከብ ጎል አስቆጣሪ ነበረች። በሐዋሳ የፈነጠቀው የኳስ ህይወት ታሪክ፤ ቀጣይ ማረፊያውን ደደቢት ላይ አደረገ። ሎዛ በኢትዮጵያ የሴቶች እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ በርካታ ክዋክብቶች የሚገኙበት ክለብን መቀላቀሏ በፍጥነት የበለጠ ጎልታ የመውጣት እድልን አስገኘላት። በደደቢት ቤት ክለቡ እስከፈረሰበት ጊዜ አራት ዓመታትን ቆይታ አድርጋለች። በእነዚህ ዓመታት በተከታታይ ኮከብ ጎል አስቆጣሪ መሆን ችላለች። ክለቧን ለሶስት ተከታታይ ዓመት ደግሞ የሴቶች ፕሪሚዬር ሊግ ሻምፒዮና እንዲሆን አስችላለች። የሎዛ የኳስ ህይወት ከፈረሰው ደደቢት ባህር ማዶ በመሻገር ሲውዲን አርፏል። ከብሔራዊ ቡድኑ የቀድሞ አምበል ቱቱ በላይ ጋር አብራ ወደ ሲውዲን አቅንታ፤ የሁለት ወር የሙከራ ልምምድ ማድረግ ጀመሩ። በሲውዲን የሚገኙ ሮዘንጋርድ እና ፒቲያ አይ ኤፍ ለአራት ወራት ያክል ቆይታ ማድረግ ቢችሉም፤ ሳይሳካ በመቅረቱ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል። የዱራሜዋ ባለህልም ወንዝ የተሻገረው ህልሟ ከቆይታ በኋላ መዳረሻውን በማልታ ደሴት ከፍተኛ ሊግ ላይ ለሚሳተፈው ቢርኪርካራ አድርጓል። ከሠፈሯ ‘ሌሊሶ’ ሜዳ አሁን ያለችበት ትደርሳለች ብለው ብዙዎች ያልገመቷት ሎዛ፤ በማልታ ደሴት አዲስ ታሪክ መስራት ጀምራለች። በአውሮፓ የምትጫወት የመጀመሪያዋ ሴት ኢትዮጵያዊት እግር ኳስ ተጫዋች መሆን የቻለችው ሎዛ፤ በጥበበኛ እግሮቿ ሌላ ታሪክ በመስራት ነበር የውድድር ዓመቱን ያጠናቀቀችው። የግብ አዳኟ ሎዛ አበራ የኳስ ህይወት ከሌሊሶ ሜዳ እስከ ማልታ ደሴት የተሻገረ ስኬት ማስመዝገብ ችሏል። በእግር ኳሱ ተስፋ ሠንቀው እየተንቀሳቀሱ ለሚገኙ ለሀገራችን ሴት እግር ኳስ ተጫዋቾች ላይ ከፍተኛ የሆነ መነቃቃት ይፈጥራል ባይነን።አዲስ ዘመን ሐምሌ 14/2012 ዳንኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=35843
[ { "passage": "ከሀገር ቤት ተነስቶ ሱዳን ሊብያ በርሃና ባህር አውሮፓ ድርስ ሰንሰለት የፈጠረው የህገወጥ አሸጋጋሪዎች ድብቅ እጅ ብዙዎችን ለሞትና ለጉስቁልና ዳርጓል፡፡ሴቶች፣ ህፃናት ወጣቶች በረሃ ውስጥ በውኃ ጥምና ርሃብ ህይወታቸውን ያጣሉ፤ ሴቶች ይደፈራሉ፤ ላልፈለጉት እርግዝና ተዳርገው በሊብያ እስር ቤቶችና በየጎዳናው በስቃይ ላይ የሚገኙ በርካቶች መሆናቸውን ገልፀውልናል። ", "passage_id": "22e20ee0b8e13837ca7f815cc36e4a48" }, { "passage": " ወደ አውቶቡስ ተራ ያቀናሁት እግር ጥሎኝ አልነበረም። አውቶቡስ ተራ ከወትሮው በተለየ የጉዞ መጨናነቅ እንዳለ ሰምቼ ነው። መነሻውን ከአራት ኪሎ ያደረገው ጉዞዬ፤ አትክልት ተራን አልፎ ጎጃም በረንዳን እስከሚያልፍ ከወትሮው በተለየ የገጠመኝ ነገር አልነበረም። ከጎጃም በረንዳ በኋላ ምነው ታክሲው በቀረብኝና በእግሬ በሄድኩ ያሰኛል። አለፍ ሲልም መመኘት ብቻ ሳይሆን ከታክሲው ለመውረድ ያስገድዳል። ጉዞዬን በእግሬ ተያያዝኩት። የባቡር ትኬት መቁረጫውን እንዳለፍኩ\nለወትሮው የተለመደው የረዳቶች ልብሴን ይዘው ‹‹የት ነህ›› ዛሬ የለም። ዛሬ የልመና ተራው የተጓዡ ነው። ተጓዥ ብሆን ኖሮ በጣም\nእንደምቸገር ገባኝ። የሄድኩበት ጉዳይ ለመስቀል በዓል ወደ ጉራጌ የሚሄዱ ሰዎችን ለማነጋገር ስለነበር ትኩረቴ በሙሉ ተጓዦች ጋር\nመድረስ ነው። ወደ ጉራጌ ሀገር የሚሄድ ተሽከርካሪ በአይኔ ብቃኝም የቱ ወዴት እንደሚሄድ በቀላሉ ለመለየት ያዳግታል። ረዳቶች ደግሞ\nበደራ ገበያ ውስጥ ስለሆኑ እነሱን ከመጠየቅ መንገደኛውን መጠየቅ ይቀላል። ከሬዲዮ ይሁን ከፍላሽ ባላውቅም በአንደኛው ሚኒባስ ውስጥ የአበባ ደሳለኝን ‹‹መስቀል ጉራጌ›› ዘፈን\nሰማሁ። ወደ ጉራጌ የሚሄድ ይሆናል ብዬ ስጠጋ ወደ ፍቼ የሚሄድ ሚኒባስ ነበር። በፌርማታው ውስጥ ያሉት አብዛኞቹ ተሽከርካሪዎች ወደ ደቡብ አካባቢዎች የሚሄዱ ናቸው። ተጓዡም ረዳቱም\nየተዋከበ ነው። የሚጫኑ ዕቃዎች ይበዛሉ። መንገደኛ እና ረዳት በሚጫነው ዕቃ ዋጋ ይከራከራሉ። አንድ ሰው ሁለትና ሦስት ቦርሳዎች\nይዟል። መጠኑ ትልቅ የሆነውን ረዳቱ እጭናለሁ ይላል ፤ባለቤቱ ደግሞ ዋጋውን በመፍራት ይዠው እቀመጣለሁ ተወኝ እያለ ይጨቃጨቃሉ።\nከቦርሳ ውጪ ያሉ በፌስታልና በሌሎች ነገሮች የተቆጣጠሩ ዕቃዎች የተሽከርካሪውን ወለል መረገጫ አሳጥተውታል። ይህ ወደ ወልቂጤ የሚሄደው\nተሽከርካሪ ነው። በጉዞው ላይ ያገኘሁት ወጣት ስንታሁ ጥበቡ እንደሚለው፤ የቱንም ያህል የትራንስፖርት ችግር ቢኖር\nየጉራጌ ተወላጅ ከመስቀል በዓል ሊቀር አይችልም። እንኳን የትራንስፖርት ችግር ከሥራ ትባረራለህ ቢባል እንኳን አይቀርም። ለመስቀል\nበዓል ዓመቱን ሙሉ ነው ዝግጅት የሚያደርገው። እንደ ስንታየሁ ገለጻ፤ አዲስ አበባ ውስጥ የሚኖሩ ጉራጌዎች እንዲያውም ዕድለኞች ናቸው። ትራንስፖርት\nያገኛሉ፤ ቀኑ ሲቃረብም መሄድ ይችላሉ። ሩቅ አካባቢ የሚኖሩ ግን በጣም ይቸገራሉ። የጉራጌ ተወላጅ ደግሞ ለመስቀል በዓል ከየትኛውም\nየኢትዮጵያ ጫፍ ይመጣል እንጂ መቅረት አይታሰብም። እንኳን ኢትዮጵያ ውስጥ እያለ ከውጭ አገርም ይመጣል። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ወጣት አስቻለው ተስፋዬ ይባላል። እንደ አስቻለው ገለጻ፤ ለመስቀል በዓል\nየጉራጌ ተወላጅ እንኳን አገር ውስጥ እያለ ከውጭ አገርም ቢሆን ይመጣል። ከቤተሰቡ አባል ውስጥ አንድ ሰው ከቀረ ከፍተኛ ሀዘን\nነው። ልጆችም የቤተሰቦቻቸውን እርግማን በመፍራት ከየትም ቢሆን ይመጣሉ።አንዳንዶችም ልጅ እንደሞተባቸው ሁሉ ሀዘን ይቀመጣሉ። ‹‹እናትና አባት እንዴት ልጃቸውን ይራገማሉ?›› ለአስቻለው የቀረበለት ጥያቄ ነበር። ‹‹እርግማኑ\n‹እንዲህ ያድርግህ!› በማለት በአፍ መናገር አይደለም። ልጃቸው ካልመጣ ከፍተኛ ሀዘን ይሰማቸዋል። ውስጣቸው ይረበሻል፤ ያንን ነው\nልጆች እንደ እርግማን የሚቆጥሩት›› የአስቻለው መልስ ነበር። ልጆችም ከቀሩ የስነ ልቦና ጭንቀት ነው የሚይዛቸው። የጎረቤት ቤተሰብ\nሞልቶ የእነርሱ አንድ ልጅ ቢቀር ወላጆች ቅር ይላቸዋል፤ የቀረው ልጅም ቅር ይለዋል። በአንፃሩ በመስቀል በዓል የሚያገኙት ምርቃት\nደግሞ የስነ ልቦና ጥንካሬ ነው የሚሰጣቸው። በመስቀል በዓል ላይ የጉራጌ አባቶችና ቤተሰቦች ይመርቃሉ። የመስቀል በዓል መገለጫ\nከሆኑት ምርቃት ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ነው። አስቻለው እንደሚለው፤ ለመስቀል በዓል ወደ ቤተሰብ የሚሄዱ የጉራጌ ተወላጆች የዓመት ዝግጅት ነው\nየሚያደርጉት። የዚህኛው የመስቀል በዓል ካለፈ ዕለት ጀምሮ ለሚቀጥለው ዓመት ይዘጋጃሉ። ልጆች ገንዘብ ያጠራቅማሉ፤ ወላጆች በሬ\nያደልባሉ። በሥራ ምክንያት በአዲስ አበባ እና በሌሎች አካባቢዎች የሚኖሩ ልጆች ከበዓሉ አስቀድመው ለወላጆቻቸው ገንዘብ ይልካሉ።\nበጉራጌ የመስቀል በዓል ላይ ሙስሊምና ክርስቲያንን መለየት\nእንደማይቻል የሚናገረው\nደግሞ ወጣት አብርሃም ካሳሁን ነው። የጉራጌ ሙስሊም ማህበረሰብ ከክርስትና እምነት ተከታዮች ያላነሰ ነው የመስቀል በዓልን በጉጉት\nየሚጠብቀው። በጨዋታው፣ በምርቃቱና በሌሎች ክዋኔዎች ሁሉ አብሮ ነው የሚሳተፈው። ከምርቃቱ ባሻገርም የመስቀል በዓልን ተናፋቂ የሚያደርገው\nይህ የአብሮነት ስነ ሥርዓቱ ነው። የተነፋፈቀ ዘመድ አዝማድ ሁሉ የሚገናኘው በመስቀል በዓል ነው። «አዳብና»\nበጉራጌ ልዩ ቦታ የሚሰጠው በመስቀል በዓል የሚደረግ ባህላዊ ሥነ ስርዓት ነው። የመስቀል በዓል አከባበር ሲጀምር በመጀመሪያው ቀን\nየጎመን ክትፎ ይበላል፤ በሚቀጥለው ቀን ለእርድ የቀረበ ሰንጋ ይታረዳል፤ ቁርጥ ሥጋ ይቀርባል፤ በዚያን ዕለት የጨፊ የሚባል ነገር\nአለ። ጨፊ ከቅቤ፣ ከሚጥሚጣ እንዲሁም ሃሞት ጋር ተቀላቅሎ ጥሬው ስጋ የሚበላበት ነው። ይህ ጥሬ ስጋ የመብላት ሥነሥርዓት የበዓሉ\nማሟሻ ነው፤ ጥሬው ስጋ ከተበላ ከሰዓታት በኋላ እንደየፍላጎት የክትፎ መብላት ሥነሥርዓቱ ይቀጥላል። ከአንድ ሳምንት በኋላ የተራረፈው\nስጋ፣ ተዘልዝሎና ደርቆ፣ ቋንጣ ሆኖ፣ ቋንጣው ተቀቅሎና በእጅ እንደ ክትፎ ተከትፎ በሚጥሚጣና በቅቤ ልክ እንደ እርጥብ ክትፎ ተለዉሶ\nይቀርባል። ይህ የተቀቀለ ቋንጣ የሚበላበት ቀን ‹‹አዳብና›› ይባላል።አዲስ ዘመን መስከረም 17/2012 ዋለልኝ አየለ", "passage_id": "28a0816fc4ddb2206614df148a0b384c" }, { "passage": "ኤርትራዊያንና ሌሎች አምባገነን መሪዎቻቸው ፊታቸውን ያዞሩባቸው ዜጎች በተመሳሳይ ጸጥታውን ተገን አድርገው ይሻገራሉ፤ በዝምታ። እንግሊዝ ባሕር ሰርጥን. . . ።\n\nየእንግሊዝ ባሕር ሰርጥ፤ ዩናይትድ ኪንግደምንና ፈረንሳይን የሚያገናኘው አጭሩ የባሕር ላይ አቋራጭ ነው።\n\nይህ ስፍራ ወደ እንግሊዝ ለመሻገርና አዲስ ኑሮ ለመጀመር ላቆበቆቡ ስደተኞች ተመራጩ ነው። ለምን?\n\nአንደኛ ይህ የባሕር ሰርጥ በርካታ የመርከቦች እንቅስቃሴ ያለበት በመሆኑ ትኩረት አይስብም። ሁለተኛ አየሩ ምቹ ነው። አየሩ ምቹ ሲሆን የባሕሩ ወጀብ ዝግ ያለ ነው።\n\nየኬንት ነዋሪዎች ጠዋት ሲነሱ ባሕር ዳርቻው አካባቢ ቤሳቤስቲ የሌላት እርጉዝ ሴት ያገኛሉ። ከወጀቡ ተገፍታ የወጣች ሴት።\n\nመሽቶ በነጋ ቁጥር ስደተኞችን የሚተፋው ይህ ባሕር በርካታ በጦርነትና በድህነት ከሚታመሱ አገሮች የሚነሱ ስደተኞችን አስተናግዷል። \n\nከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዚሁ መንገድ ከአውሮፓ አገራት ወደ ዩናይትድ ኪንግደም ገብተው አዲስ የጥገኝነት ጥያቄ የሚያቀርቡ ሰዎች ቁጥር እያሻቀበ ነው።\n\nቁጥሮች በራሳቸው ብዙ ይናገሩ ይሆናል።\n\nበዚህ ዓመት ብቻ 4ሺህ ሰዎች በሦስት መቶ ትንንሽ ጀልባዎች ቁጢጥ ብለው ተሻግረዋል። \n\nባለፈው ሐሙስ ዕለት ብቻ 235 ሰዎች ተመዝግበው እንግሊዛዊያን ጉድ እያሉ ነበር። እንዲህ ዓይነት ቁጥር በአንድ ቀን ተመዝግቦ አያውቅም።\n\nበነገራችሁ ላይ የፈንሳይ የባሕር ተቆጣጣሪዎች አደን ስለሚወጡና ጀልባዎችን በአካባቢው ስለሚያስቆሙ እንጂ ከዚህ ቁጥር እጥፍ የሆኑ በርካታ ጀልባዎች በየቀኑ ኬንት በደረሱ ነበር።\n\nብዙዎቹ ጀልባዎች በጣም ትንንሽና ለአደጋ የሚያጋልጡ ሆነው በዚያ ላይ በሕጻናትና አቅመ ደካሞች ይታጨቃሉ። \n\nበዚያ ላይ ያ መስመር እጅግ ብዙ መርከቦች የሚመላለሱበትና አደገኛ ነው።\n\nበዓለም አቀፍ የባሕርና የውቅያኖስ ሕግ በባሕር ላይ ሕይወታቸው አደጋ ላይ ያለ ሰዎችን ከአደጋ መታደግ ለአገሮች ግዴታ ነው።\n\nባለፈው የፈንጆች ዓመት ወደ ዩናይትድ ኪንግደም የገቡ የውጭ ዜጎች (ለሥራና ለትምህርት) 677ሺህ ናቸው።\n\n49 ሺህ ሰዎች ደግሞ የጥገኝነት ጥያቄ ማመልከቻ አስገብተዋል። ከዚህ ቁጥር ውስጥ በእንግሊዝ የባሕር ሰርጥ (English Channel) በጀልባ ተሳፍረው የመጡት አንድ እጅ ቢሆኑ ነው።\n\nነገር ግን የጥገኝነት ጥያቄ ከዩናይትድ ኪንግደም ይልቅ በሌሎች የአውሮፓ አገራት ይበዛል። \n\nለምሳሌ ያለፈውን ዓመት አሐዝ ብቻ ብንመለከት 165ሺህ 600 ሰዎች በጀርመን የጥገኝነት ጥያቄ አቅርበዋል። \n\nበፈረንሳይ ደግሞ 129ሺህ የተለያዩ አገራት ዜጎች አስጠጉን ብለዋል። በስፔን ደግሞ 118ሺህ ሰዎች ተመሳሳይ ጥያቄ አቅርበዋል።\n\nከዚህ አንጻር ዩናይትድ ኪንግደም ጥብቅ ድንበር፣ ጥብቅ የጥገኝነት ፖሊሲ እንዳላት መገመት ይቻላል።\n\nአንድ ሰው የእንግሊዝን ምድር ሳይረግጥ የጥገኝነት ጥያቄ ለማሳካት በጣም ፈታኝ ይሆንበታል። ስለዚህ በተገኘው አጋጣሚ ወደ አገሪቱ ለመግባት ይሞከራል።\n\nቀደም ሲል ስደተኞች በከባድ መኪናና በጭነቶች ውስጥ ተደብቀው ነበር ወደ ዩናይትድ ኪንግደም የሚገቡት። \n\nባለፈው ዓመት 39 ቬትናማዊያን እንደ ማቀዝቀዣ በሚያገለግል ከባድ ተሸከርካሪ ውስጥ ታጉረው ወደ አገሪቱ ሲገቡ እዚያው መኪናው ውስጥ ሞተው መገኘታቸው ደንጋጤን ፈጠረ። \n\nክስተቱን ተከትሎ ጥብቅ ቁጥጥር ተጀመረ።\n\nበከባድ መኪና ወደ ዩናይትድ ኪንግደም መግባት እጅግ አደገኛ እየሆነ ሲመጣ ትንንሽ ጀልባዎች አማራጭ ሆኑ።\n\nካለፈው ዓመት ጥር ወር ጀምሮ በጀልባ ወደ ዩናይትድ ኪንግደም ከገቡት ውስጥ ወደመጡበት የአውሮፓ አገር የተመለሱት 155 ሰዎች ብቻ ናቸው።\n\nበቀጣይ 600 የሚሆኑትን በተመሳሳይ ወደመጡበት ለመመለስ ሐሳብ አለ።\n\nዩናይትድ... ", "passage_id": "ab0266028255104821b170cb993f3a97" }, { "passage": "በጣልያን የኮሮና ቫይረስ ሥርጭት ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ገለጹ፡፡የጣልያኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ጁሴፔ ኮንቴ እንደተናሩት በቫይረሱ ሥርጭት የተነሳ ቢያንስ 16 ሚሊዮን ሰዎች በሎምባርዲ ክልል እና በሌሎችም 14 ግዛቶች በየቤታቸው ተገልለው እንዲቆዩ ትዕዛዝ ተላልፏል፡፡ ሰዎቹ ራሳቸውን አግልለው እንዲቆዩ ትዕዛዝ የተላፈው በቫይረሱ እንዳይጠቁና የተጠቁት ወደ ሌሎች እንዳያስተላልፉ ጥንቃቄ ለማድረግ ሲባል ነው፡፡ጣልያን በፍጥነት እየተዛመተ ያለውን የኮሮና ቫይረስ ሥርጭት ለመግታት የስፖርት ማዕከላት፣ የመዋኛ ገንዳዎች፣ የጉብኝት መዳረሻ ሙዚዬሞች እና ሰዎች የሚበዙባቸው መናፈሻዎች እንዲዘጉ አዝዛለች፡፡ የቀብርና የሠርግ ዝግጅቶችም እንዳይከናወኑ ክልከላ ተላልፏል፡፡", "passage_id": "41ed311e1f31d843fde740bbc4c3020d" }, { "passage": "ከሰጠመው ጀልባ የመጣ እንደሆነ የታመነበት የአደጋ ጊዜ ጃኬት በሊቢያ የባህር ዳርቻ ተገኝቷል\n\nበምዕራብ ሊቢያ ከምትገኘው ሳብራታ የተነሳው ጀልባ ቢያንስ 100 ሰዎችን ጭኖ እንደነበር የአካባቢው ኃላፊዎች ለቢቢሲ ተናግረዋል።\n\nጀልባው ከመስጠሙ በፊት በገጠመው ችግር ለቀናት ያለቁጥጥር መጓዙና በመጨረሻም በዙዋራ ከተማ አቅራቢያ ባለፈው ረቡዕ መታየቱ ተዘግቧል።\n\nእስካሁን 35 ሰዎች ከአደጋው ሲተርፉ 8 አስክሬኖችም መገኘታቸውን ኃላፊዎቹ ገልጸዋል። \n\nየሊቢያ የባህር ኃይል ቃል አቀባይ እንዳስታወቁት የተረፉት ተጓዞች ሁሉም ከሰሃራ በታች ካሉ የአፍሪካ ሃገራት የመጡ ናቸው።\n\nየተባበሩት መንግስታት እንደሚለው በዚህ የአውሮፓውያን ዓመት 100,000 ስደተኞች ሚዲትራኒያን ባህርን አቋርጠው ወደ ጣሊያን ሲሻገሩ ከ2400 በላይ የሚሆኑት ደግሞ በመንገድ ላይ ሞተዋል።\n\nበሊቢያ የሚያዙ ስደተኞች ደግሞ በትሪፖሊ ብዙዎች በአስቸጋሪ ሁኔታ ወደታጨቁባቸው ማቆያዎች ይወሰዳሉ።\n\n ", "passage_id": "25fef1823c8cb99934a02345aa8b499a" } ]
f073e10a1cf2fbbbb92cec4f67594636
8f817826468f39d01148b9da266bd2a8
ዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ከአቶስ ጋር ውሉን አራዘመ
 ዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ከግዙፉ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ኩባንያ አቶስ ጋር ያለውን የስፖንሰርሺፕ ስምምነት ማራዘሙን ገለፀ። አዲሱ ውል እስከ 2024 እንደሚዘልቅም ሁለቱ ተቋማት ባለፈው ሳምንት ስምምነት ላይ መድረሳቸው ታውቋል። ኮሚቴውና ኩባንያው እኤአ ከ1989 ጀምሮ አብረው እየሰሩ እዚህ ደርሰዋል። የፈረንሳዩ አቶስ ኩባንያ የዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ግንባር ቀደም ስፖንሰር በመሆን 2014 ላይ ለስድስት ዓመታት የሚዘልቅ ውል ማሰሩ የሚታወስ ነው። የሁለቱ አካላት አዲስ ስምምነት ለ2022 የቤጂንግ የክረምት ኦሊምፒክና ለ2024 የፓሪስ የበጋ ኦሎምፒክ ውድድሮች የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶችን ማሟላትን ያካተተ መሆኑ ተነግሯል። ይህ የስፖንሰርሺፕ ስምምነት የቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ መራዘሙን ተከትሎ ዓለም አቀፍ ኮሚቴው ከገጠመው ኪሳራ በጥቂቱም ቢሆን ሊያገግምበት የሚችል መልካም አጋጣሚ እንደሆነ ተጠቁሟል። ‹‹በዚህ አስቸጋሪ ወቅት የዓለም አቀፍ አጋሮቻችን ድጋፍና በራስ መተማመን ከምን ጊዜውም በላይ አስፈላጊ ነው›› በማለት ቶማስ ባኽ አስተያየት ሰጥተዋል። ፕሬዚዳንቱ አክለውም ዓለም አቀፍ ኮሚቴው የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ኩባንያ የሆነው አቶስ ውድድሮችን ዘመኑ በሚፈቅደው ቴክኖሎጂ በማገዝ የሚያደርገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልፀዋል። ቶማስ ባኽ የአቶስ ኩባንያ ከኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አጋርነቱ ባሻገር የኦሎምፒክን መርህ በዓለም ሕዝብ ዘንድ ለማስረፅ በሚደረገው እንቅስቃሴ አጋር ሆኖ በመዝለቁም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ኩባንያው የኦሎምፒክን እንቅስቃሴ እኤአ ከ2001 ጀምሮ እየደገፈ እንደሚገኝ ይታወቃል። በፓሪስ ሰሜን ምዕራብ ቢዞንስ አካባቢ በሚገኘው የአቶስ ኩባንያ ተገኝተው የውል ስምምነቱን የፈረሙት ቶማስ ባኽ በፈረንሳዩ ፕሬዘዳንት ኢማኑኤል ማክሮን አቀባበል ተደርጎላቸዋል። የፓሪስ 2024 ኦሎምፒክን እንዲሁም የወቅቱ አሳሳቢ የጤና ጉዳይ የሆነው ኮቪድ 19 ዙሪያም ምክክር ማድረጋቸው ታውቋል። የአቶስ ኩባንያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኤሊ ጂራርድ ከዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ጋር ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት በአጋርነት ሲሰሩ ቆይተው ውላቸውን በማራዘማቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል። ዋና ስራ አስፈፃሚው አክለውም ኦሊምፒክንና የኦሊምፒክ ጨዋታዎችን በቴክኖሎጂ በማገዝ ወደ ፊትም ኩባንያው ጠንክሮ እንደሚሰራ አብራርተዋል። በሁለቱ አካላት መካከል የታደሰው ውል የዓለም አቀፉ ፓራኦሎምፒክ ኮሚቴንም የሚያካትት ነው። አቶስ ኩባንያ በርካቶቹ የኦሎምፒክ ስፖንሰሮች ፓራኦሎምፒክ ኮሚቴውን ለመደገፍ ሲያመነቱ 2018 ላይ ስፖንሰር ለመሆን ፍቃደኝነቱን ማሳየቱ ይታወሳል። አቶስ ኩባንያ በ2018 ፒዮንግያንግ የክረምት ኦሎምፒክ ወቅት ‹ክላውድ› የተባለ ቴክኖሎጂ ይፋ በማድረግ ስራ ላይ ያዋለ ሲሆን በተራዘመው የቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክም ይህን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ይጠቀማል ተብሎ ነበር። ባለፈው ሰኔ ዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ የቶኪዮ ኦሎምፒክ በመራዘሙ ስድስት መቶ ሃምሳ ሚሊየን ዶላር ኪሳራ እንደሚገጥመው የተነገረ ሲሆን ይህን ኪሳራ ለማካካስ እንደ አቶስ ያሉ አጋሮቹን ድጋፍ ከምን ጊዜም በላይ ይፈልጋል። የቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ ለአስራ ስድስት ወራት በመራዘሙ ምክንያት የአዘጋጅ አገሯ ጃፓን መንግስትና የዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ገና ከጅምሩ በርካታ ውስብስብ ችግሮች ውስጥ መዘፈቃቸው ሲነገር ቆይቷል። የኦሎምፒክ ውድድሩ በዓለም ላይ ከፍተኛ ስጋት በፈጠረው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ጋር ተያይዞ ወደ ቀጣዩ ዓመት መራዘሙ ግድ መሆኑ ከታመነበት ወቅት አንስቶ አዘጋጆቹ በርካታ ፈተናዎችን መጋፈጣቸው የማይቀር ሆኗል። በተለይም ላለፉት ሰባት ዓመታት የበለጠ ዝግጅት ሲደረግበት የቆየው የኦሎምፒክ ውድድር መራዘሙ ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ ማስከተሉ የአዘጋጆቹ ራስ ምታት እንደሚሆን ቀድሞም የታወቀ ነው።ይህ ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ የጃፓን መንግስትንም ይሁን ዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴን በእጅጉ ሊፈትን እንደሚችል በባለሙያዎች አስተያየት ሲሰጥበት የቆየ ሲሆን ሁለቱ አካላት ኪሳራውን ለማካካስ እንደሚደጋገፉና ሌሎች ባለድርሻ አካላትም ለዚህ እንዲዘጋጁ ጥሪ ሲያቀርቡ ቆይተዋል።የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እንዲህ አይነት ችግሮች ሲገጥሙት ትልቅ ተቋም እንደመሆኑ የመድህን ዋስትና እንዳለው ይታወቃል። አሁን የገጠመው ግን ካለው የመድህን ዋስትና አቅም በላይ በመሆኑ ነው እዚህ ችግር ውስጥ የተዘፈቀው። ስለዚህ የመድህን ዋስትናው በሕጉ መሰረት የሚሸፍነው ኪሳራ እንዳለ ሆኖ ተጨማሪ ኪሳራውን የሚያካክስበት አንድ ነገር መፈጠሩ የግድ ይሆናል፡፡አዲስ ዘመን ሐምሌ 16/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=35901
[ { "passage": "ለ2021 የሴቶች ከ20 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ የማጣርያ ጨዋታዎች ከተቋረጡበት ይቀጥላል በማለት ካፍ ቢያሳውቅም በኢትዮጵያ በኩል እስካሁን ምላሽ አላገኘም።በ2020 ሊደረግ ታስቦ የነበረው የዓለም ዋንጫው ጥር 2021 ላይ በኮስታሪካ እና ፓናማ አዘጋጅነት እንደሚካሄድ የሚጠበቅ ሲሆን በቅድመ ማጣርያ የቡሩንዲ አቻዋን 7-1 በሆነ ድምር ውጤት አሸንፎ ወደ አንደኛ ዙር ያለፈው ከ20 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በቀጣይ ዙር ከዚምባብዌ ጋር ግንቦት ወር ላይ ለመጫወት መርሐ ግብር ቢወጣለትም በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙ የሚታወስ ነው።ካፍ ማጣርያው የሚቀጥልበትን አዲስ መርሐ ግብር የላከ ሲሆን ከነሐሴ 28-30 የመጀመርያው ጨዋታ፤ የመልሱ ጨዋታ ደግሞ ከጳጉሜ 5-መስከረም 2 እንደሚሆን ለኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ካሳወቀ አስራ አምስት ቀናት አስቆጥሯል። ሆኖም ፌዴሬሽኑ በስሩ የሚገኙ ብሔራዊ ቡድኖች አሰልጣኝን ውል እንደማያራዝም አሳውቆ የነበረ ቢሆንም ከ20 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ የውድድር መርሐግብርን ካፍ ማሳወቁን ተከትሎ የቡድኑ አሰልጣኝ ፍሬው ኃይለገብርኤል እና ረዳቶቹ ምናልባትም ውላቸው ሊታደስላቸው እንደሚችል ከዚህ ቀደም መዘገባችን ይታወቃል።ምንም እንኳን ፌዴሬሽኑ በአሰልጣኞቹ የውል ማራዘም ጉዳይ ላይ የተለየ ነገር ባይኖረውም ጨዋታው የሚደረግበት ጊዜ አንድ ወር እየቀረው አምስት ወር ከሜዳ የራቁትን የብሔራዊ ቡድኑ አባላት ወደ ትክክለኛው አካል ብቃታቸው ለመመለስ የስድስት ሳምንት የዝግጅት ጊዜ እንደሚያስፈልገው እየታወቀ እስካሁን ቡድኑ ዝግጅት አለመጀመራቸው እና ፌዴሬሽኑ በዚህ ጉዳይ ላይ ዝምታ መምረጡ የብሔራዊ ቡድኑ ጨዋታን ፌዴሬሽኑ ሰረዘው ወይ? የሚል ጥያቄ አስነስቷል።የብሔራዊ ቡድኑ ሁኔታን አስመልክቶ ምላሽ እንዲሰጡን የፌዴሬሽኑን ዋና ፀኃፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን ጠይቀናቸው ተከታዩን ሀሳብ ሰጥተውናል።“ውድድሩን ለማድረግ የሚያስችል ፍቃድ ለማግኘት ለመንግሥት እና የሚመለከታቸው አካላት ጥያቄ ካቀረብን ረጅም ቀናት አስቆጥሯል። በትናንትናው ዕለት ምላሽ እንደሚሰጡን ቀጠሮ ቢይዙልንም ተገቢውን ምላሽ አላገኘንም። የውድድሩ ቀን እየተቃረበ መምጣቱን እንረዳለን፤ በቅርቡም ከመንግስት ምላሽ\nእናገኛለን የ።” ብለዋል።ኢትዮጵያ ዙሩን ካለፈች በሁለተኛው ዙር ጥቅምት ወር ላይ ከቦትስዋና እና ደ/አፍሪካ አሸናፊ የምትጫወት ይሆናል።", "passage_id": "43a4a4e74cb0b632d402260a2fae5972" }, { "passage": "በተለያዩ መንገዶች ከሚሰሙ መረጃዎች ውጭ ይፋዊ በሆነ መንገድ እስካሁን በዲኤስቲቪ እና የሊግ ኩባንያው መካከል የተደረሰው የውል ስምምነት ለምን ይፋ ሳይሆን ቀረ?  የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አክሲዮን ማኅበር የሊጉን የቴሌቪዥን ስርጭት መብት መግዛት የሚፈልጉ ተቋማትን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ DStv’ም ከተወዳዳሪዎቹ የተሻለ ፋይናንሻል እና ቴክኒካል ፕሮፖዛል በማቅረብ መብቱን መግዛቱ ከተሰማ ቆይቷል። ሆኖም በተለያዩ መንገዶች ከሚወጡ መረጃዎች ውጭ የስምምነቱ ዝርዝር ነጥቦች እና ሌሎች ጉዳዮችን በተመለከተ በጋዜጣዊ መግለጫ ይፋዊ ነገሮች አልተገለፁም። በዚህም የተነሳ የተለያዩ አጠራጣሪ ነገሮች ሲነሱ ቆይተዋል። ይህን ተከትሎ ባደረግነው ማጣራት እስካሁን የዘገየበት ምክንያት አንዳንድ በቅድሚያ ሊሟሉ የሚገቡ ቅድመ ሁኔታዎችን ለማስተካከል በወሰደው ጊዜ እንደሆነና በቅርቡ ሁሉም ዝርዝር ነገሮች በይፋዊ ጋዜጣዊ መግለጫ ለስፖርት ቤተሰቡ መረጃ እንደሚሰጥ ሰምተናል። በሌላ ዜና ሦስቱን የትግራይ ክልል ክለቦች ዙርያ አሁን ባለው ወቅታዊ ሁኔታ አንፃር ሊጉ ለተወሰኑ ቀናት ሊራዘም ይችል ይሆን በማለት ባደረግነው ማጣራት የሊግ ኩባንያው አክሲዮን የቦርድ አመራር በቀጣይ የሚወስኑት የተለየ ነገር ከሌለ በስተቀር ውድድሩ በተባለለት ጊዜ እንደሚጀምር ሰምተናል።©ሶከር ኢትዮጵያ", "passage_id": "d2384c65ac80c385f3bf812dead3c571" }, { "passage": "የአፍሪካ እግርኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባዔውን በአዲስ አበባ ለማድረግ ቀጠሮ ቢይዝም ሃሳቡን መቀየሩ ታውቋል።በአሁኑ ሰዓት በፊፋ የአምስት ዓመት ዕግድ ተጥሎባቸው የነበረው የካፍ ፕሬዝዳንት አህመድ አህመድ ከወራት በፊት በአዲስ አበባ ትራንዚት ሲያደርጉ ኢትዮጵያ የካፍን ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ እንድታስተናግድ መመረጧን ለፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት ገልፀው እንደነበር ይታወሳል። ይህንን ተከትሎ ከታኅሣሥ 1-10 ድረስ በአዲስ አበባ ይደረጋል ተብሎ ይታሰበውን ይህን ጠቅላላ ጉባኤ ለማስተናገድ ፌዴሬሽኑ የተለያዩ ሥራዎችን እየከወነ ቢገኝም ጉባኤው አዲስ አበባ ላይ እንደማይደረግ ተገልጿል።የካፍ ኢመርጀንሲ ኮሚቴ እንደገለፀው ከሆነ ተቋሙ ይህንን ውሳኔ የወሰነው በሜዲካል ኮሚቴው በቀረበለት ምክረ ሃሳብ እንደሆነ አስረድቷል። በተለይም በአህጉሪቱ ያለውን የኮቪድ-19 ስርጭት ታሳቢ በማድረግ ጉባዔውን በአካል በመገናኘት ማከናወን አስጊ እንደሆነ በማሰብ ውሳኔው መወሰኑ ተብራርቷል። ከኮቪድ በተጨማሪ በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ ያለው ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታም እንደ ተጨማሪ ምክንያትነት እንደተያዘ ተጠቁሟል። ይህንን ተከትሎ ፊፋ ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባዔውን እንዳከናወነው ካፍም ጉባኤውን በቪዲዮ ኮንፍረንስ ለማከናወን ወስኗል።© ሶከር ኢትዮጵያ", "passage_id": "d3368bf15b4e6abb70ff5af0027b2a89" }, { "passage": "አትሌት ቀነኒሳ በቀለ\n\nአትሌት ቀነኒሳ በቅርቡ ለቶኪዮ ኦሎምፒክ የማራቶን ምርጫ ጋር በተያያዘ ላቀረብኩት ቅሬታ በቂ ምላሽ የማይሰጠኝ ከሆነ በግል የዓለም አቀፉን የኦሎምፒክ ባንዲራ ወክዬ ልወዳደር እችላለሁ ሲል ለቢቢሲ ተናግሯል። \n\nየኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ሥራ አስፈፃሚ ሚያዝያ 19/2013 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ በመጪው የቶክዮ ኦሊምፒክ ላይ የሚሳተፉ አትሌቶች ተወዳድረው እንደ አዲስ እንዲመረጡ ወስኖ ነበር።\n\nፌዴሬሽኑ አትሌቶችን አወዳድሮ መምረጥ አስፈላጊ መሆኑ በፌዴሬሽኑ የቴክኒክ ኮሚቴ፣ በአሰልጣኞች እና በአትሌቶች ጭምር በጋራ የተወሰነ ውሳኔ መሆኑን ገልጿል። \n\nበዚህም መሰረተ ፌዴሬሽኑ ሚያዚያ 28 በሰበታ ከተማ ለሚካሄደው ወድድር አትሌት ቀነኒሳ በቀለን ጨምሮ ለ12 ወንድ እና ለ8 ሴት አትሌቶች ጥሪ አቅርቦ ነበር። \n\nውድድሩም በታቀደለት ቀን ተካሂዶ በሁለቱም ጾታ ከ1-5ኛ የወጡ አትሌቶችን ፌዴሬሽኑ ይፋ አድርጓል። \n\nየቀነኒሳ ቅሬታ ምንድነው? \n\nአትሌት ቀነኒሳ በቀለ ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት 2020 ሊካሄድ ታቅዶ በነበረው የቶኪዮ ኦሎምፒክ ለመወዳደር በአትሌቲክስ ፌዴሬሽኑ ተመርጦ እንደነበረ ያስታውሳል። \n\nይሁን እንጂ ፌዴሬሽኑ በቅርብ ጊዜያት ውድድር ስላልተካሄዱ የአትሌቶችን ብቃት ለመለየት የአገር ውስጥ ውድድር በማካሄድ ለመምረጥ ማሰቡ በአትሌት ቀነኒሳ ዘንድ ቅሬታን ፈጥሯል። \n\nአትሌት ቀነኒሳ ለቢቢሲ ሲናገር፤ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የነበረው ሕግ በመቀየር በአገር ውስጥ ውድድር የማራቶን ተወዳዳሪዎችን ለመመርጥ መወሰኑ አግባብ አይደለም። \n\nአትሌት ቀነኒሳ ከእርሱ በተጨማሪ ሌሎች አትሌቶችም በዚህ የፌዴሬሽኑ ወሳኔ ላይ ደስተኛ አለመሆናቸውን ገልጸዋል ይላል። \n\n\"ሌሎች አትሌቶችም ቅሬታ አቅርበዋል። ስብሰባውን ረግጠው የወጡ ልጆችም ነበሩ። ነገር ግን የእነርሱ ቅሬታ አልተሰማም። ለምንድ ነው በምርጫ የምታደርጉት ብለው ደስተኛ አለመሆናቸውን ተናግረው ነበር። ለኦሊምፒኩ ቀጥታ የምትመርጡን ከሆነ እንመጣለን፤ አሁን የማጣሪያ ውድድር ለማድረግ ስላልተዘጋጀን ማጣሪያው ላይ መሳተፍ አንፈልግም ብለው የወጡ ልጆች አሉ\" በማለት ያስረዳል። \n\nአትሌት ቀነኒሳ በዓለም አቀፍ መድረክ በማራቶን ውድድር ያስመዘገበው ሰዓት የዓለማችን ሁለተኛው ፈጣን ሰዓት መሆኑን ያስታውሳል። በጥሩ ጤንነት እና አቋም ላይም እንደሚገኝ ጨምሮ ተናግሯል። \n\nአትሌት ቀነኒሳ በጥሩ ብቃት እንደምትገኝ ካመንክ ለምን ፌዴሬሸኑ ባዘጋጀው የማጣሪያ ውድድር ላይ አልተሳተፍክም ተብሎ ለቀረበለት ጥያቄ ሲመልስ፤\n\n\"ሲጀመር ውድድሩ መደረጉ በራሱ ፍትሃዊ አይደለም። እኔ የተወዳደሩት አትሌቶች ውጤት ያልተገባ ነው ማለቴ አይደለም። ውድድሩን ላደረጉትም ላላደረጉትም ክብር አለኝ። ነገር ግን እንደሚታወቀው ባለፈው ዓመት በሰዓታችን መሠረት ስድስት አትሌቶች ተመርጠናል። አሁን አዳዲስ አትሌቶች ተጨምረው ነው ውድድሩ የተደረገው። ይህ ራሱ ፍትሃዊ አይደለም\" ይላል። \n\nአትሌት ቀነኒሳ፤ በኢትዮጵያ ለማራቶን ውድድር የአገር ውስጥ ማጣሪያ ከተደረገ በርካታ አስርት ዓመታት ማለፋቸውን ገልጾ፤ ይህ ውድድር የ2020 ኦለምፒክ ነው። ውድድሩ ወደ 2021 ስለተዘዋወረ እንደ አዲስ ውድድር ሊታይ አይገባም ይላል። \n\nበተጨማሪም \"ውድድሩ ሶስት ወራት ቀርተውት እያለ ለምን ማጣሪያ ማድረግ አስፈለገ? ሕጉ ለምን ተቀየረ? ይህን የማድረግ ሐሳብ ካላቸው ለምን ከዓመት በፊት አላደረጉትም። ይህ ማራቶን ነው። 10 ሺህ ወይም 5 ሺህ አይደለም። የትራክ ሩጫ አይደለም\" ብሏል። \n\nአትሌት ቀነኒሳ በቀለ\n\nየዓለም ሻምፒዮናው አትሌት ቀነኒሳ ጥቂት ወራት ለቀሩት ወድድር አሁን ላይ ሌላ የማራቶን ማጣሪያ ማድረግ ጉዳት ሊያስከትል እንደሚችል ያስረዳል።... ", "passage_id": "69cdba366926a76b7b51292d44074423" }, { "passage": "የኮሮና ቫይረስ(ኮቪድ 19) በዓለም ላይ በከፍተኛ ፍጥነት መሰራጨቱን ተከትሎ የሁሉም ዓለም አቀፍ የስፖርት መርሐግብሮች እንዲቋረጡ አድርጓቸዋል። የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱ ተከትሎ የስፖርቱ ዓለም ካለፉት ሁለት ወራት በላይ ተቋርጦ እንዲቆይ አድርጎታል። የውድድሮቸ መቋረጥና መርሐ ግብሮች መራዘማቸውን ተከትሎ የስፖርቱን ኢንዱስትሪ ክፉኛ እንደጎዳው ዓለም አቀፍ ጥናቶች ከወዲሁ ያመላክታሉ። ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በመቆማቸው ምክንያት የሚደርሰውን ኪሳራ በመጠኑም ቢሆን ለማዳን ውድድሮችን በዝግ ስታዲየም ማድረግ አማራጭ ተደርጓል። ከቫይረሱ ስጋት ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆን ባይችሉም ታላላቆቹን አውሮፓ እግር ኳስ ሊጎች ጨምሮ አንዳንድ አገራትም ስፖርታዊ ውድድሮቻቸውን ከሰሞኑ አስጀምረዋል። ውድድሮችን በዝግ ስቴድየሞች በማድረግ የውድድር ዓመቱ ከመጠናቀቁ በፊት መርሐግብሮቻቸውን ለማጠናቀቅ ጨዋታዎችን እያደረጉ ይገኛሉ። \nበአውሮፓ እግር ኳስ ሊጎች የተወሰደውን መፍትሔ የዓለም አቀፍ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተግባራዊ ሊያደርገው እንደሚችል ቢቢሲ ዘግቧል። የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሰባስቲያን ኮዬ ፤ የአትሌቲክስ ስፖርት ሲመለስ በባዶ ሜዳዎች ሊካሄድ እንደሚችል ማስጠንቀቃቸውን መሰረት ያደረገው ዘገባው፤ «በታላላቆቹን አውሮፓ እግር ኳስ ሊጎች ከሰሞኑ እንደተመለከትነው ዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድሮችም በቅርቡ ሊመለሱ ይችላሉ »ሲል አስነብቧል የዓለም አቀፍ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የአትሌቲክስ ስፖርት ሲመለስ በባዶ ሜዳዎች ሊካሄዱ እንደሚችሉ ከማስገንዘብ በተጨማሪ ፤ውድድሮች ስለሚመለሱባቸው ሁኔታዎች በተመለከተ ሃሳብ መስጠታቸውን አመልከቷል። በዚሁ ላይም «ዓመታዊው የዳይመንድ ሊግ እንዲሁም የተለያዩ የአትሌቲክስ ውድድሮች ሁኔታዎች ከተገመገሙ በኋላ በመጪው ነሐሴ አጋማሽ እንዲካሄዱ እቅድ ተይዟል። በነሐሴ እንዲካሄዱ እቅድ የተያዘላቸው አስራ አንዱ የተለያዩ የአትሌቲክስ ውድድሮች በዝግ ሜዳ ይሆናሉ » ሲሉ መናገራቸውን ጽፏል። \nቢቢሲ በዘገባው ፕሬዚዳንቱ በተለይ ጌምስ ለተባለው ድረገፅ በሰጡት ማብራሪያ «በመጪዎቹ ቅርብ ጊዜያት የሚካሄዱ ውድድሮች ላይ ለደህንነት ስንል ልንደራደርባቸው የማይገቡ ጉዳዮች አሉ። በተደጋጋሚ በጤና ባለሙያዎችም ሆኑ በአካባቢው ማህበረሰብ የተነገረንን ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ ያስገባና ችላ የማንላቸውም ናቸው። ሁላችንም ቢሆን ይህ የረዥም ጊዜ መፍትሔ ነው ብለን አናስብም። ስፖርታዊ ውድድሮች ያለታዳሚ ይጠፋሉ። ሆኖም በአሁኑ ወቅት የአትሌቲክስ ውድድሮችን ለመመለስ መክፈል ያለብን መስዋዕትነት ይሄ ነው» ሲሉ መናገራቸውን በዘገባው አካቷል።አዲስ ዘመን ግንቦት 11/2012ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "7880ef43a81ab343f810d54366a6043d" } ]
eaadc85c63a9af3a8bf54f41f46060f8
66c5d001c1953acb5f324e83aafebc9d
የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና እና ተስፋው
ጽጌረዳ ጫንያለው የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ለአፍሪካውያን ትልቅ ተስፋ የሚሰጥ መሆኑን የምጣኔ ሀብት ባለሙያው ይናገራሉ::የአፍሪካ ነፃ ንግድ ሰነዱም ይህንኑ የሚያረጋግጥ ነው::በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት መምህሩ ዶክተር ዳዊት ሀዬሶ እንደሚናገሩት፤ በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና አስፈላጊ የሚሆንበት ዋናው ምክንያት እንደ አህጉር የእርስ በእርስ ንግድ ትስስሩ በጣም ዝቅተኛ በመሆኑ እና ይህንን ወደ ከፍታ ለመመለስ ነው::ከዚያም ባሻገር ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር፣ ሰፊ የገበያ አማራጭ ለመፍጠር፣ ጥራት ያለው ምርት ለማግኘትና ለማቅረብ፣ ተጨማሪ ገቢ ለሠራተኛው፣ ለባለሀብቱና ለሸማቹ ለማስገኘት ይጠቅማል::በሌላ በኩል ሕገወጥ ንግድን ይቀንሳል፤ ግብር የሚከፍሉ ነጋዴዎችን ያበራክታል::ንግዱን ነፃ እንቅስቃሴ እንዲኖረው በማስቻል ተመጣጣኝ ዋጋ ገበያው ላይ እንዲኖርም ያደርጋል::በተለይ በአፍሪካ አገራት ያለውን የሰው ሃይል ከመሸጥ አኳያ ከፍተኛ ፋይዳ አለው::ይህ ማለት በሁለት መልኩ ሊሆን ይችላል::አንዱ የሥራ ዕድል በመፍጠር ሲሆን፤ ሁለተኛው በምርታማነት ደረጃ ሌሎች የሚገዙበትን ዕድል ይሰጣል::እንደ አፍሪካ ያለው ችግር ተመሳሳይ በመሆኑም አንዱ ከአንዱ ጋር ተመጋጋቢ ሆኖ ከላይ ወደታች ያለውን አሠራር ያስቀራል ይላሉ::ከአፍሪካ ጥሬ ዕቃ ሄዶ አውሮፓ ወይም እስያ ላይ ተመርቶ መልሶ በዝቅተኛ ታክስ ለአገር ውስጥ ይቀርባል::ይህ ነፃ የንግድ ቀጣና ተግባራዊ መደረጉ አምራቹ ሳይቀር አፍሪካ ላይ እንዲፈጠር ያደርጋል::የቁጠባ ባህልን ከፍ በማድረግ የውጭ ምንዛሬን ዝውውር ያፋጥናል::የውጭ ምንዛሬ እጥረትንም የሚቀንስ መሆኑን ይናገራሉ::እንደ አየር ትራንስፖርት ላሉ አገልግሎቶችም የሚሰጠው ጥቅም ከፍተኛ እንደሆነ የሚጠቁሙት ዶክተር ዳዊት፤ ከገበያ፣ ከእውቀት ሽግግር፣ ከውጭ ንግድ ዕድገት አንፃርም ጠቀሜታው ከፍተኛ መሆኑን ያነሳሉ::የነፃ ቀጣናው ስምምነት መረጃ እንደሚያሳየው ደግሞ፤ የዓለም ንግድ ድርጅት ከተመሰረተ እ.ኤ.አ ከ1994 በኋላ አሁን የተመሰረተው የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ትልቁ ሲሆን፤ 54 አገራትን አቅፏል። 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ሕዝብን ይይዛል፤ 3 ነጥብ 4 ትሪሊየን ዶላር በአጠቃላይ ምርት ይዞ አህጉሩን እርስ በእርስ ያስተሳስራል::በዚህ ሁሉ የማደግ ሁኔታን ያመቻቻል::የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጡን ከነበረበት 16 በመቶ ወደ 33 በመቶ ያሳድገዋል ተብሎ ይታመናል::የንግድ ሚዛን ጉድለቱንም ከ50 በመቶ በታች ይቀንሰዋል::ለአህጉሩ 2 ነጥብ 8 ቢሊዮን ዶላር በዓመት የተጣራ ገቢ ያስገኛል ::እንደ መረጃው ከሆነ፤ የሸማቾች ገንዘብ ወጪ የማድረግ አቅምን 2036 ነጥብ 7 ትሪሊየን ዶላር እንዲደርስ ያደርገዋል::ይህ ሆነ ማለት የገንዘብ ዝውውሩ የተረጋጋ እንዲሆን ያግዛል::በዚህም ምርትና ምርታማነት በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራል::የታሰበው የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ውጤታማ እንዲሆን ብዙ ተግባራት መከናወን እንዳለባቸው የሚገልፁት ዶክተር ዳዊት፤ የኢትዮጵያ የንግዱ ማህበረሰብን ተወዳዳሪ ለማድረግ በተለይም አብዛኛው ምርት የግብርና በመሆናቸው የኢንዱስትሪው ዘርፍ ላይ መሥራት ያስፈልጋል::ውጤታማ የምንሆንባቸውን ምርቶች ወደገበያ ለማቅረብ የማያስችሉ ልማዳዊ አሠራሮች ወይም ቢሮክራሲዎችን መቀነስ ይገባል::ያለንን ሀብት ማውጣት ላይም መሠራት አለበት::እንደ አፍሪካ የንግድ ሕጉን ማሻሻል፣ ተመሳሳይ የታክስ ታሪፍ ማስቀመጥ፣ ለነጋዴዎች የነፃ ቪዛ ሂደቱን ማስተካከልም አስፈላጊ መሆኑን ይናገራሉ::እ.ኤ.አ በ2018 የወጣ መረጃ እንደሚያመላክተው፤ የአፍሪካ አገራት የእርስ በእርስ የንግድ ትስስር ከአጠቃላይ የንግድ ልውውጡ 19 በመቶ ብቻ ነው::ይህ ሲታይ ከ80 በመቶ በላይ የንግድ ልውውጡ የሚደረገው ከአፍሪካ ውጭ እንደሆነ ያመላክታል::የአውሮፓ አገራት የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ 69 በመቶ ይሸፍናል::እስያውያንም እንዲሁ 59 በመቶ የእርስ በእርስ ንግድ ልውውጥ ያደርጋሉ::አፍሪካ ውስጥ ግን በጣም ዝቅ ያለ በመሆኑ የንግድ ሚዛን ጉድለት ያስከትላል::ስለዚህም አህጉሩ እነዚህንና መሰል ችግሮችን ለመፍታት አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናዎችን መመስረት አስፈልጓቸዋል::ሁኔታው በሚገባ ከተሰራበት በቀጣይ እንደ አገርና አፍሪካ ብቻ ሳይሆን እንደ አለምም በንግዱ ዘርፍ ታዋቂና ኃያል የሆኑ አገራት ይወጣሉ::የሕዝብ ተጠቃሚነትም በዚያው ልክ ይረጋገጣል::ከድህነት የመላቀቁም ሁኔታ ይመቻቻል::
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=39249
[ { "passage": "እውነቱ ግን በአሁኑ ወቅት አፍሪካ፤ በውጪ ለሚኖሩ የብዙ ባለሃብቶች ትልቅ ኢንቨስትመንት ማዕከል መሆኗ ነው። \n\nዶክተር ሓርነት በክረጽዮን አፍሪካውያኖች ይህን ዕድል በደንብ እንዲጠቀሙበት የሚያስችል 'አፍሪካ ቢዝነስ ጃምፕስታርት' የተሰኘ ፕሮጀክት በመንደፍና ተግባራዊ በማድረግ ብዙዎች ወደ አህጉሪቱ እንዲመጡ ለማድረግ ተግታ እየሰራች እንደሆነ ትገልፃለች።\n\n\"የአፍሪካ ቢዝነስ ጃምፕስታርት ዋና ዓላማ በተለይም በአሜሪካና አውሮፓ የሚኖሩ አፍሪካውያን በተለያዩ ዘርፎች በአህጉሪቱ እንዲሰማሩ ለማበረታታትና ስልጠና ለመስጠትም ነው\" ትላለች ዶከተር ሃርነት። \n\nስልጠናዎቹና የንግድ ዕድሎቹ አፍሪካ ውስጥ ለሚኖሩም ጭምር ክፍት መሆኑን ገልጻለች። \n\nበአሁኑ ወቅት ንግድና ኢንቨስትመንት በአፍሪካ እያደገ መሆኑን በመጠቆም፤ አፍሪካውያን ታዛቢ ብቻ ከመሆን አልፈው በተፈጠረው ዕድል ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ በር መከፈቱን ዶክተር ሓርነት በአፅንኦት ትናገራለች። \n\nአፍሪካ ቢዝነስ ጃምፕስታርት የአፍሪካውያንን ዕውቀት በኢንቨስትመንት ዘርፍ ለማሳደግ ዋነኛና መሰረታዊ ዓላማው አድርጎ በመስራት ላይ ይገኛል።\n\nእስከ ዛሬ ይደረግ የነበረው የኤርትራዊያንና የኢትዮጵያዊያን ኢንቨስትመንት ተሞክሮንና ጥናትን መሠረት ያደረገ እንዳልነበረ ዶክተር ሃርነት ይገልፃሉ።\n\n\"ኤርትራውያንና ኢትዮጵያውያንን ስንመለከት በፊት የነበሩትን ሃበሾች ዱካ በመከተል በአንጎላ፣ በደቡብ ሱዳን ወይም በኡጋንዳ መነገድ ነው የሚወዱት።\"\n\nሆኖም ግን እንደ አንጎላና ደቡብ ሱዳን ያሉት ሃገራት ውስጥ ንግድና የኢንቨስትመንት ዋስትና የሌለውና ለአደጋ የተጋለጠ ነው። በማለት ዶክተር ሓርነት በተነፃፃሪ ዋስትና ያላችው ሃገሮችን ጠቅሳለች።\n\n\"እንደታንዛኒያ፣ ሩዋንዳ፣ ቦትስዋናና ጋናን የመሳሰሉ ሃገራት የተሻለ ዕድልና ዝቅተኛ ስጋት ያለባቸው ናችው። ስለዚህ አስፈላጊ ጥናት በማካሄድ ከአንጎላና ከደቡብ ሱዳን የተሻለ አማራጭ አለ።\"\n\nበኤርትራና በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ሁኔታ በሚመለከት ደግሞ፤ በተለይ ኤርትራ ውስጥ ለንግድ የሚመች ሁኔታ የሌለ መሆኑን የምትገልፀው ሓርነት የንግድ ፈቃድም እንደማይሰጥ አመልክታለች።\n\nበተመሳሳይ ኢትዮጵያ ውስጥም በቀላል መንገድ ንግድ መጀመር አይቻልም። ምክንያቱም የንግድ ፍቃድ በቀላሉ ስለማይገኝ። በተለይ ደግሞ ኢትዮጵያዊ ዜግነት ለሌላቸው ሰዎች የሚታሰብ አይደለም። እንደ እርሻ፣ የውጭ ንግድና ማምረት በመሳሰሉ አንዳንድ ኢንዳስትሪዎች በኩል ግን ብዙ ዕድል እንዳለ ትናገራለች።\n\nላለፉት 4 ዓመታት አፍሪካ ቢዝነስ ጃምፕስታርት ብዙ ሰዎችን በአንድነት በማሰባሰብ ሩዋንዳ ውስጥ የጥናታዊ ጉዞ እንዲያደርጉና ሃገሪቱ ውስጥ ያሉትን ዕድሎች በቅርብ እንዲዳስሱ አድርጓል።\n\n\"ከእኔ ጋራ የተጓዙ ኤርትራውያንና ኢትዮጵያውያንን በጣም ነው የተገረሙት። ምክንያቱም ከዚህ በፊት የነበራቸው ተሞክሮ አንጎላ ወይም ደቡብ ሱዳን ብቻ በመሆኑ ነው።\" \n\n\"በሩዋንዳ ንግድ መክፈት በጣም ቀላል ነው። በ24 ሰዓታት ውስጥ የንግድ ፍቃድ ያለችግር ማግኘት ይቻላል። ሰለዚህ ሩዋንዳ ለመላው አፍሪካ ምሳሌ መሆን ትችላለች።\"\n\nዶክተር ሓረነት ጀርመን ተወልዳ ያደገች የሁለት ልጆች እናት ስትሆን በምግብ ዋስትናና የገጠር ዕድገት ዘርፍ ምሩቅ ነች። \n\nለ13 ዓመታት በተባበሩት መንግሥታትና የአውሮፓ ህብረት እንደዚሁም በኦክስፋም ውስጥ የበላይ አማካሪ በመሆን በታላቋ ብሪታንያ፣ በኤርትራ፣ በሱዳንና በጀርመን ሰርታለች። \n\nአሁን ደግሞ የአፍሪካ ያልተነካ ሃብት ጥቅም ላይ ለማዋል በሚል ሃሳብ ነው ትኩረትዋን ወደ አፍሪካ ያደረገች። \n\n ", "passage_id": "3efd88b33a1edbc73b177f340e54856d" }, { "passage": " ለምለም መንግሥቱ አዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያ\nከጅቡቲ ጋር ሙሉ ለሙሉ የፈጠረችውን\nየንግድ ግንኙነት ተደራሽነቷን\nወደሌሎችም በማስፋት የአፍሪካ\nነፃ የንግድ ቀጣና ተጠቃሚነቷን ማሳደግ እንዳለባት አንድ የፖሊሲ ባለሙያ አስታወቁ። የፖሊሲ ባለሙያው ዶክተር ቆስጠንጢኖስ በረኸተስፋ ዛሬ የሚጠበቀውን ‹‹አፍሪካ ኮንቲኔታል ፍሪ ትሬድ›› የተሰኘው ጋና አክራ ላይ የተከፈተውን ጽሕፈትቤት ይፋ የማድረግ ሥነሥርዓት አስመልክቶ አዲስዘመን ጋዜጣ ላቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል በማደራጀት፣መንገድ በመዘርጋት፣በአጠቃላይ በመሠረተልማት ዝርጋታ ትልቁን ድርሻ ወስዳ ከጎረቤት ሀገሮች ጋር ለመገናኘት እያደረገች ባለው እንቅስቃሴ ከጅቡቲ ጋር ሙሉ ለሙሉ የንግድ ግንኙነት ፈጥራለች። በአሁኑ ጊዜም ለጅቡቲ ኤልክትሪክ ታቀርባለች። ጅቡቲም ለኢትዮጵያ ወደብ ሆና ታገለግላለች። እንዲህ ያለው ግንኙነት ከአንዳንድ የአፍሪካ ሀገራት ጋርም ጅምር እንቅስቃሴዎች ቢኖሩም የበለጠ በማስፋት የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ተጠቃሚነቷን ማሳደግ ይጠበቅባታል ብለዋል። ኢትዮጵያ በመሰረተልማቱ ትልቁን ዕርምጃ ወስዳ በመንቀሳቀስ ላይ መሆኗን የጠቆሙት የፖሊሲ ባለሙያው፤ ከመካከለኛውና ከምዕራብ አፍሪካ በተሻለ በምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ማመንጫና ማሰራጫና መንገድ በመሥራት እንዲሁም የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት በማከናወን የተሻለ ሥራ መሥራቷን አመልክተዋል። የበለጠ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ ቴክኖሎጂ፣ባለሙያና ሀብት ያላቸው ኩባንያዎችን መፍጠርና ዘመናዊ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋት እንደሚጠበቅ አመልክተዋል። ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ የእርሻ መሬትና የውሃ ሀብት በአግባቡ ከተጠቀመችና በመገንባት ላይ ያለችውን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ካጠናከረች ወደፊት ሱዳን፣ኬኒያ፣ጅቡቲና ሌሎችም ጎረቤት ሀገሮች ከተለያዩ ሀገሮች የሚያስገቡትን ምርት በማቅረብ ተጠቃሚ ልትሆን የምትችልበት ዕድል ሰፊ እንደሆነ ገልጸዋል። ተጠቃሚ ሀገራትም ከሌሎች ሀገሮች በሚያስገቡት አገልግሎቶች የሚጣልባቸውን ቀረጥ እንደሚያስቀርላቸው ጠቁመዋል። የንግድ ትስስሩ በመካከላቸው\nበድንበርና በተለያየ መንገድ የሚነሳው አላስፈላጊ\nንትርክ ጠብቦ የዲፕሎማሲ\nግንኙነታቸው ወደ መልካም ነገር እንዲለወጥ\nበማገዝ ሀገራቱ ዘርፈብዙ\nጥቅሞችን ያስገኝላቸዋል ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት 50ኛ የምሥረታ በዓሉን ሲከበር ከ50 ዓመታት በኋላ እኤአ በ2060 አፍሪካ አንድ የንግድ ቀጠና ትሆናለች የሚል ውሳኔ ተላልፎ እንደነበር ያወሱት የፖሊሲ ባለሙያው፤የንግድ ልውውጡን ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲሸጋገር ከተፈለገ ሀገራቱ መሠረተ ልማት ማስፋፋት፣ግጭቶችን ማቆም ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና የንግድ ትሥሥርን ብቻ የሚያጎለብት የተለያዩ ግንኙነቶችን ለማጠናከር የሚያግዝ እንደሆነ አመልክተዋል። የአፍሪካ ህብረት ብዙ አዋጆችን ማውጣቱት ያወሱት የፖሊሲ ባለሙያው ትልቁ ችግርና ክፍተት ተፈጻሚ አለማድረግ እንደሆነ ጠቁመዋል። እኤአ በ2009 በመሰረተ ልማት፣ በኢኮኖሚ፣በሰብዓዊ ድጋፍ ሥራዎች አሥራአንድ የአፍሪካ ሀገሮችን ለማስተሳሰር ጥናት ተጠንቶ ለሥራዎቹ ማስፈፀሚያ የሚውል ወደ 21 ቢሊየን ዶላር ገንዘብ ባለመገኘቱ አለመተግበሩን፣እኤአ በ2015 እንዲሁም 69 ቢሊየን ዶላር የሚያወጣ ሥራ እንዲሠራ በጥናት ቢለዩም ሳይከናወኑ መቅረታቸውን ጠቁመዋል። ሥራዎች በእነዚህ ሁሉ ፈተናዎች ማለፋቸውን አስታውሰዋል።አዲስ ዘመን  ታህሳስ 23/2013", "passage_id": "305101002c2599dce926cad0a82c8383" }, { "passage": "የሚኒስትሮች ምክር ቤት የኢትዮጵያን የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ስምምነት አባልነት አፀደቀ።ምክር ቤቱ ስምምነቱን ዛሬ ባካሄደው ስብሰባው ያጸደቀ ሲሆን ስምምነቱ የዓለም የንግድ ድርጅት ከተመሠረተ ትልቁ የንግድ ስምምነቶች አንዱ ሲሆን፥ በአፍሪካ አንድ ገበያ ለመፍጠር ሙከራ ያደርጋል።ውሳኔው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከሚያራምዱት አዕምሮን ለሃሳብ መንሸራሸርና ገበያዎች ለትስስር በመክፈት በአፍሪካ ክልላዊ ውህደትንና ጥብቅ ጥምረት እንፍጠር ከሚለው ራዕይ ጋር ይጣጣማል።የኢትዮጵያ ውሳኔና የፓን አፍሪካን እሳቤ የመደገፍ ታሪካዊ ልምድ የአፍሪካን ውህደት በተሻለ ሁኔታ ወደ እውነታነት ያስጠጋል። (ምንጭ፡- የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት)", "passage_id": "aef81ad6947966324dd1252f46a2132d" }, { "passage": "የፋብሪካው ግንባታ በተያዙለት ሁለት ደረጃዎች ሙሉ በሙሊ ሲጠናቀቅ አጠቃላዩ መዋዕለ-ነዋይ ከ230 ሚሊየን ብር በላይ እንደሚሆን ተነግሯል።ደሴን ከምዕራብ ወረዳዎች ጋር በሚያገናኘው ገራዶ ሜዳ ላይ የቆመው ይህ ፋብሪካ ለግብርናና ለግንባታ ሥራዎች ግብዓት የሚሆኑ ምርቶችን የሚያወጣ ሲሆን እስከአሁን በሃገር ውስጥ የማይሠሩ ውጤቶችንም ለገበያና ለተጠቃሚዎች እንደሚያቀርብ ተገልጿል።በሌላ የንግድና ምጣኔ ኃብት ዘገባ፤ የዩናይትድ ስቴትሱ የአፍሪካ የዕድገትና የተጠቃሚነት ዕድሎች ድንጋጌ /አጎአ/ ተጠቃሚ ሃገሮች የያዝነው የአውሮፓው 2019 ዓ.ም. የምክክር መድረክ በምዕራብ አፍሪካዪቱ አይቮሪ ኮስት የአትላንቲክ የንግድ መናኸሪያ ከተማ አቢዦን ላይ ተካሂዷል።በዚህ ዕሁድ፤ ሐምሌ 28/2011 ዓ.ም. ተጀምሮ ማክሰኞ፣ ሐምሌ 30/2011 ዓ.ም. በተጠናቀቀው 18ኛው የአጎአ ጉባዔ ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ የዕድሉ ተጠቃሚ የሆኑ ከሰሃራ በስተደቡብ ያሉ ሃገሮች የንግድና የዲፕሉማሲ ባለሥልጠናትና እንዲሣተፉ የተጋበዙ፣ እንዲሁም የዩናይትድ ስቴትስ የንግድና የውጭ ጉዳይ ከፍተኛ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።ይህ በልማት ወደኋላ የቀሩ የአፍሪካ ሃገሮችን ለመድገፍና ምርቶቻቸወን ያለቀረጥ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ገበያ ማስገበት እንዲችሉ ታስቦ የዛሬ 19 ዓመት የወጣ ሕግ ከዚህ ቀደም ለሁለት ጉዜ የተራዘመ ሲሆን የአሁኑ የተቃሚነት ጊዜ የሚያበቃው በመጭዎቹ ስድስት ዓመታት ውስጥ ነው።በአፍሪካዊያንና በአሜሪካዊያን ባለሙያዎች፣ ባለሥልጣናትና ታዛቢዎች ዕምነት አፍሪካ ከግዙፉና ከካብታሙ የአሜሪካ ገበያ እንድትጠቀም የተሰጣትን ዕድል በአግባቡ ሳትጠቀምበት ቀርታለች። ", "passage_id": "245e2d8e68ca23fecd68dce7e112314a" }, { "passage": "የአፍሪካን የአየር ትራንስፖርት አውታር ወደፊት እንደሚያራምድ የታመነበት የአፍሪካ የጋራ የአየር ትራንስፖርት ገበያ ምሥረታ ተቃውሞ ገጠመው፡፡ የአፍሪካ የአየር ትራንስፖርት ገበያ በክልከላ የተተበተበ በመሆኑ የአፍሪካ የአየር መንገዶች ዕድገት ፈታኝ እንዳደረገው ሲገለጽ ቆይቷል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት የገበያ ክልከላን በማስቀረት የአፍሪካ አየር መንገዶች አፍሪካ ውስጥ በነፃነት ከአገር አገር እንዲበሩ የሚያስችል የአፍሪካ የጋራ የአየር ትራንስፖርት ገበያ ምሥረታ፣ ጥር 20 እና 21 ቀን 2010 ዓ.ም. በአዲስ አበባ በተካሄደው 30ኛው የኅብረቱ የመሪዎች ጉባዔ በይፋ አውጇል፡፡ ሰኞ ጥር 21 ቀን በተካሄደው የመሪዎች ጉባዔ የአፍሪካ የጋራ የአየር ትራንስፖርት ገበያ መመሥረቱን ያወጁት አዲሱ የኅብረቱ ሊቀመንበር የሩዋንዳ ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ ናቸው፡፡ ፖል ካጋሜ የአፍሪካ የጋራ የአየር ትራንስፖርት ገበያ ምሥረታ ለአፍሪካ የአየር ትራንስፖርት ዕድገት ትልቅ ዕርምጃ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ፖል ካጋሜ፣ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙሳ ፈቂ ማሃማትና የቶጎ ፕሬዚዳንት ፋውሬ ናሲንግቤ ለጋራ ገበያው ምሥረታ የተቀመጠውን የማስታወሻ ድንጋይ መርቀው ከፍተዋል፡፡ በጉባዔው መክፈቻ ላይ ፖል ካጋሜ የጋራ ገበያ ምሥረታውን አስመልክተው ንግግር ካደረጉ በኋላ፣ የኡጋንዳ ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ አስተያየት ለመስጠት ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ ሊቀመንበሩ ፖል ካጋሜ በጋራ የአየር ትራንስፖርት ገበያ ላይ ማንኛውም መሪ አስተያየት እንዲሰጥ በፕሮግራሙ ላይ የተቀመጠ ነገር ባይኖርም፣ ለፕሬዚዳንት ሙሴቬኒ ዕድሉን ሰጥቷቸዋል፡፡፡ ፕሬዚዳንት ሙሴቬኒ የአፍሪካ የጋራ የአየር ትራንስፖርት ምሥረታ ላይ ሥጋት እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡ የጋራ ገበያ ምሥረታው የሚጠቅመው የተወሰኑ የአፍሪካ አየር መንገዶችን እንደሆነ የገለጹት ሙሴቬኒ፣ እነዚህ የአፍሪካን ሰማይ የተቆጣጠሩት አየር መንገዶች ወደፊትም የአፍሪካን ገበያ እንዲቆጣጠሩ የሚፈቀድ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ‹‹ይህ ጥሩ አይደለም›› ያሉት ሙሴቬኒ፣ ገበያውን ክፍት ከማድረግ በፊት የአፍሪካ አገሮች በየክልላቸው የጋራ አየር መንገድ ቢያቋቋሙ ተመራጭ እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡ የአፍሪካ ሲቪል አቪዬሽን ኮሚሽን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ የሙሴቬኒ ንግግር በዕውቀት ላይ ያልተመሠረተ ነው፡፡ ‹‹ኡጋንዳ ገበያዋን ለአፍሪካና ለሌሎች አየር መንገዶች ክፍት ያደረገች አገር ናት፡፡ ወደ ኢንቴቤ የማይበር አየር መንገድ የለም፡፡ ሙሴቬኒ በጉባዔው ያንፀባረቁት ሐሳብ ግር የሚያሰኝ ነው፤›› ብለዋል፡፡ በሙሴቬኒ ተቃውሞ ላይ አስተያየታቸውን ለሪፖርተር የሰጡት የቀድሞ የአፍሪካ አየር መንገዶች ማኅበር ሊቀመንበርና የአፍሪካ አቪዬሽን ሰርቪስስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሚስተር ኒክ ፋዱግባ፣ የአፍሪካ አገሮች እ.ኤ.አ. በ1999 የአፍሪካን የአየር ትራንስፖርት ገበያ ክፍት ለማድረግ የያማሱክሮ ውሳኔ በመባል የሚታወቀውን ሰነድ ያፀደቁ መሆኑን አስታውሰው፣ የአፍሪካ አገሮች የማይተገበሩትን ውል ለምን ይፈርማሉ ሲሉ ተችተዋል፡፡ የአፍሪካ የጋራ የአየር ትራንስፖርት ምሥረታን የተቃወሙት ሙሴቬኒ ብቻ አይደሉም፡፡ በናይጄሪያ የሚገኙ የግል አየር መንገዶችም ተቃውሞአቸውን አሰምተዋል፡፡ የናይጄሪያ አየር መንገዶች በማኅበራቸው አማካይነት ባወጡት መግለጫ ናይጄሪያ ለጋራ ገበያ ምሥረታው ዝግጁ አለመሆኗን በመግለጽ፣ መንግሥታቸው ውሉን ተግባራዊ እንዳያደርግ ጠይቀዋል፡፡ አንዳንድ የአፍሪካ አየር መንገዶች የጋራ የአየር ትራንስፖርት ገበያ መመሥረት የሚጠቅመው እንደ ደቡብ አፍሪካ፣ ኬንያና ኢትዮጵያ ላሉ ትልልቅ አየር መንገዶችን እንደሆነ በመግለጽ ትንንሽና ደካማ አየር መንገዶችን እንደሚጎዳ ያላቸውን ሥጋት ይገልጻሉ፡፡ የአፍሪካ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣናት የተሰነዘረውን ተቃውሞ አጣጥለውታል፡፡ የአፍሪካ ሲቪል አቪዬሽን ኮሚሽን ዋና ጸሐፊ ሚስስ ሶሶና ኢያቦ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የጋራ የአየር ትራንስፖርት ገበያው የሚጠቅመው ትልልቅ አየር መንገዶችን ብቻ ነው የሚለው የተሳሳተ አስተያየት ነው፡፡ የጋራ ገበያው ትልቅ ትንሽ ሳይል ሁሉንም አየር መንገዶችና አገሮች የሚጠቅም እንደሆነ የገለጹት ሚስስ ሶስና አፍሪካን በአየር ትራንስፖርት በማስተሳሰር፣ የመንገደኞች ቁጥር በመጨመር፣ የአቪዬሽንና ተያያዥ ዘርፎችን ሁሉ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አስረድተዋል፡፡ ‹‹በፍርኃት ውስጥ የምትኖር ከሆነ ለውጥ ማምጣት አትችልም፡፡ እነዚህ አየር መንገዶች ከፍርኃት ተላቀው የጋራ ገበያ ምሥረታው የሚያመጣውን ዕድሎች ተመልክተው በዕድሎቹ ለመጠቀም መሥራት ይኖርባቸዋል፤›› ብለዋል፡፡ ናይጄሪያዊቷ ሚስስ ሶስና ናይጄሪያ የጋራ የአየር ትራንስፖርት ገበያ ምሥረታ ካፀደቁት የመጀመርያ አሥራ አንድ አገሮች አንዷ መሆኗን ጠቁመው፣ የናይጄሪያ መንግሥት ማየት የቻለውን የጋራ ገበያው የሚፈጥረውን ዕድል የናይጄሪያ አየር መንገዶች ገና ማየት እንዳልቻሉ ተናግረዋል፡፡ የአፍሪካ አየር መንገዶች ማኅበር ዋና ጸሐፊ ሚስተር አብዱራህማን በርቴ በበኩላቸው፣ ትንንሽ አየር መንገዶች በትልልቅ አየር መንገዶች እንዋጣለን የሚል ሥጋት እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡ አነስተኛ የሆኑ የአፍሪካ አየር መንገዶች ከትልልቅ የአፍሪካ አየር መንገዶች ጋር መተባበር እንዳለባቸው ሚስተር አብዱራህማን ጠቁመዋል፡፡ ‹‹ትልልቆቹ አየር መንገዶች ሁሉም ቦታ መብረር አይችሉም፡፡ ትልቅ የሚባሉት አየር መንገዶች ረዥም በረራዎች ሲሸፍኑ አነስተኛ አየር መንገዶች አጭር በረራዎችን ማካሄድ ይችላሉ፡፡ መፍትሔው ተባባሮ መሥራት ነው፤›› ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ የጋራ ገበያው የሚመራበት ሕግና ሥርዓት ያለው በመሆኑ አየር መንገዶች ፍርኃት ሊሰማቸው አይገባም ብለዋል፡፡ ‹‹የለውጥ ባቡር በመገስገስ ላይ ነው፡፡ ማስቆም አይቻልም፡፡ የሚሻለው ተባብሮ መሥራት ነው፤›› ብለዋል፡፡ ሚስተር ኒክ ፋዱግባ በበኩላቸው፣ ገበያ ሲከፈት አሸናፊና ተሸናፊ እንደሚኖር ጠቁመው፣ ‹‹ስኬታማ የሆነውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከመውቀስ ይልቅ እንደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ጠንክሮ መሥራት ያስፈልጋል፡፡ ቶጎ፣ ማላዊና አሁን ደግሞ ዛምቢያ እንዳደረጉት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በሽርክና መሥራት ይጠቅማል፤›› ብለዋል፡፡የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረ ማርያም አፍሪካ ውስጥ ትንሽና ትልቅ የሚባል አየር መንገድ እንደሌለ ተናግረዋል፡፡ ‹‹ሁላችንም ትንሽ ነን፡፡ አሁን የተባለው ነገር ሁለት ራሰ በረሃ ሰዎች ለማበጠሪያ እንደሚሻሙት ዓይነት ነገር ነው፤›› ያሉት አቶ ተወልደ፣ የጋራ ገበያው ለአፍሪካ አየር መንገዶች ብቻ ሳይሆን የአፍሪካን አገሮች እርስ በርስ ግንኙነት በማጠናከር ንግድ፣ ኢንቨስትመንትና ቱሪዝም በማስፋፋት የሚኖረውን ጠቀሜታ በዝርዝር አስረድተዋል፡፡ የአፍሪካ የጋራ የአየር ትራንስፖርት ምሥረታ የአፍሪካ ኅብረት 2063 የልማት አጀንዳ አንዱ አካል ሲሆን፣ 23 አገሮች በፊርማቸው ሲያፀደቁ አራት አገሮች ግን በሒደት ላይ ይገኛሉ፡፡ አቪዬሽን አፍሪካ ውስጥ ስምንት ሚሊዮን የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፣ ለአኅጉሪቱ አጠቃላይ ብሔራዊ ምርት 80 ቢሊዮን ዶላር አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡ ", "passage_id": "d365a4acb0402302eb3416af01ec8981" } ]
f5dd16666ec0062def5e1fca7e69bd09
2f5409753f23bd86990d6fe50dba82a4
የጁንታው መያዝ መንግስት እየወሰደ ላለው የሕግ ማስከበር ትልቅ ስኬት እንደሆነ ተገለፀ
ሞገስ ተስፋ አዲስ አበባ፡- የጁንታው ቁንጮ አቦይ ስብሃት መያዝ መንግስት እየወሰደ ላለው የሕግ ማስከበር ትልቅ ስኬት እንደሆነ አንዳንድ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ።ኢትዮጵያ በሴራ እና ተንኮል እንደማትፈርስ በተግባር ያረጋገጠ እንደሆነም አመለከቱ ።አዲስ ዘመን ያነጋገራቸው አቶ ውብሸት ጌታሁን እንዳሉት፣የጁንታው ቁንጮ የሆኑት አቶ አቦይ ስብሃት ኢትዮጵያ ልትፈርስ ነው እያሉ በመንግስት መገናኛ ብዙሃን ሳይቀር ሲሰብኩ የነበሩ ናቸው::ነገር ግን በሴራ እና በተንኮል ኢትዮጵያ እንደማትፈርስ አይተዋል ያሉት አቶ ውብሸት፣ የግለሰቡ መያዝ ብለዋል::የመከላከያ ሰራዊት እየወሰደ ያለው ሕግን የማስከበር ዘመቻ ፣ የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ለሚዳፈሩ እና ለወንጀለኞች ትልቅ ማስተማሪያ እንደሆነም አመልክተዋል ። ጁንታዎቹ በሥልጣን ዘመናቸው እጃቸው በብዙ ንጹሃን ደም የተጨማለቀ ቢሆንም መንግሥት ወደ ብቀላ ሳይገባ በሕግ የበላይነት በመተማመን እና በሕገ መንግሥቱ መመራት እየወሰደ ያለው ሕግ የማስከበር እርምጃ ለሕግና ለሕገመንግስታዊ ሥርዓት ያለውን ታማኝነት ማሳያ መሆኑን ገልፀዋል:: ጁንታዎች አልመው ኢትዮጵያ ትፈርሳለች ብለው ሲናገሩ የማያፍሩ ሰዎች ናቸው የሚሉት አቶ ውብሸት፣ ሕዝብ ሲኖር ባለሥልጣን ይኖራል፣ ባለሥልጣን ሆኖ ለመኖር ደግሞ ሕዝብ መኖር አለበት::ሀገር ማለት ደግሞ ሌላ ነገር ሳይሆን ሰው ማለት ነው ብለዋል::እነዚህ ጁንታዎች ሥልጣን ተቆናጠው በኖሩበት ዘመን አብዮታዊ ዲሞክራሲ በሚል አንዱ ከአንዱ ጋር በሰላም እንዳይኖር አቅደው በጥላቻ ሲሰሩ እንደነበር አስታውሰው ፣ከስልጣን ከተወገዱ ማግስትም እኛ ስልጣን ካልያዝን በስተቀር ሀገር ትፈርሳለች ብለው በድፍረት ከመናገር በዘለለ አቅደው በተግባር ሀገር ለማፍረስ ሲሰሩ እንደነበር ጠቁመዋል ::እንደ አቶ ውብሸት ገለፃ ፣ጁንታው ‹‹ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል›› በማለት ሀገርን ለመበተን ቢሰራም ህልማቸው ሳይሳካ ቀርቷል::ለስልጣናቸው ማራዘሚያ በተደጋጋሚ ትልልቅ የሀገሪቱ ብሔሮችን በማጋጨት ሲጥሩ ነበር ::ይህ ሁሉ ሳይሳካላቸው ከዚህ በፊት የዘሩትን እያጨዱ ነው ብለዋል ::የጥፋት ቡድኑ በአብዮታዊ ዲሞክራሲ ጭንብል ሲንቀሳቀስ ቢቆይም ፣ በዲሞክራሲ በፍፁም የማያምን ፣ በጥፋት የተተበተበ መሆኑን በመከላከያ ሰራዊት ላይ የወሰደው አሳፋሪ ጥቃት ትልቁ ማሳያ እንደሆነ ገልጸዋል::ሌላኛዋ የአዲስ አበባ ነዋሪ ወይዘሮ ትህትና በላይ በበኩላቸው ፣ኢትዮጵያን ለማፍረስ ከውጪም ከውስጥም ብዙ ሴራዎች ተሸርበዋል፣ ነገር ግን በቁርጥ ቀን ልጆቿ እና በፈጣሪዋ ታግዛ የቆየች ሀገር መሆኑዋን አመልክተዋል ::አሁንም መንግስት የወሰደው የደህንነት ተቋማትን የማጠናከር እርምጃ ተቋማቱ በሙሉ እግራቸው እንዲቆሙና የሕግ የበላይነትን እንዲስከብሩ ማድረግ የሚስችል አቅም እንደፈጠረላቸው በተጨባጭ ማየት እየቻልን ነው ብለዋል::በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል እየተወሰደ ባለው የህግ ማስከበር እርምጃ አንጋፋው የተንኮል ቀያሽ እና ስትራቴጂስት መያዙ ትልቅ ድል ነው ያሉት ወይዘሮዋ፣ ይህም በተለይም ሕግ የሚያስከብሩ ተቋማት እንደሀገር እየተጠናከሩ መምጣታቸው አመላካች እንደሆነ ጠቁመዋል :: የሀገርን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ሲሰሩ የነበሩ ቁልፍ አመራሮች በሕግ ቁጥጥር ስር መዋላቸው በሕግ ማስከበሩ ዘርፍ ትልቅ ስኬት እንደሆነ የገለፁት ፣የአዲስ አበባ ነዋሪው አቶ ይሁኔ ገበየሁ፣ በጁንታው የተንኮል ሴራ በርካታ ኢትዮጵያውያን በአሰቃቂ ሁኔታ እንዲገደሉ መደረጉን አስታውሰዋል::የጥፋት ቡድኖችን መልምለው፣ በማሰልጠን ፣ በማስታጠቅ እና ለጥፋት ስምሪት በመስጠት ዋነኛ ተዋንያን እንደነበሩ ገልጸው ፣ የጁንታው አድራጊ ፈጣሪ እና የተንኮል ቁልፍ ቀያሽ መያዙ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ጥፋቶችን ሲያደርሱ የነበሩ ቡድኖች እንዲጠፉ ያደርጋል ብለዋል። ቀሪዎቹን የጁንታው ተፈላጊ አባላት ለቃቅሞ ለሕግ ማቅረብ ጥልቅ አቅም ይፈጥራል ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ በመላው ሀገሪቱ ሰላምን ለማረጋገጥ የግለሰቡ መያዝ ወሳኝ ድል እንደሆነ ገልፀዋል::አሁን ተረኝነት የሚያስከትለውን መዘዝ ያየንበት ጊዜ ነው፣ ተረኛ ነኝ ብሎ ሀገር ላይ ማሴር፣ የሀገሪቱን ሕዝቦች መከፋፈል፣ ከሕግ አግባብ ውጪ ዜጎችን መቅጣት ውጤቱ ምን እንደሆነ በተጨባጭ ያየንበት በመሆኑ ከዚህ መማር ያስፈልጋልም ብለዋል ::ስልጣን ያዝኩ ብሎ አንዱን ጠቅሞ ሌላውን መጉዳት ውጤቱ ኪሳራ እንጂ ትርፍ እንደማያስገኝ በማሰብ ለአንድነት፣ ለዲሞክራሲ ለሕግ የበላይነት እና ለፍትህ ያለምንም አድሎ መስራት ከመሪዎች እንደሚጠበቅም አሳስበዋል::
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=39248
[ { "passage": "የኢትዮጵያ መንግሥት በሰሜኑ የሃገሪቱ ክፍል እያካሄደ እንዳለ የሚገልፀው የህግ ማስከበር ዘመቻ ፍፃሜውን ሊያገኝ መዳረሱን አስታወቀ። የዘመቻው ማጠናቀቂያ በሆነችው መቀሌ ከተማና ነዋሪዎቿ ላይ ጉዳት እንዳይደርስ የሚቻለው ጥንቃቄ ሁሉ እንደሚደረግም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለፁ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የፌዴራል መንግሥት በተቆጣጠራቸው የትግራይ ክልል አካባቢዎች ሰብዓዊ ድጋፍ እየቀረበ እንደሆነ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አመለከተ።\n", "passage_id": "5a3b98e8c450799ecdaadbb099ae0276" }, { "passage": "በትግራይ ክልል የተካሄደው የህግ ማስከበር ዘመቻ ህገ መንግሥታዊ ስርዓትን ተከትሎ በብቃትና በውጤታማነት የተከናወነ ነው ሲሉ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አደም ፋራህ አስታውቀዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በትግራይ ክልል ስላለው አጠቃላይ ሁኔታ በቀጣይ ለምክር ቤቱ ሪፖርት እንደሚያቀርቡም አፈጉባኤው ጠቅሰዋል።የዘንድሮው የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀንም ለዓመታት በብሔር ብሔረሰቦች ሲነግድ ከከረመው የህወሓት ቡድን ሽንፈት ማግስት መከበሩ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።\n\n", "passage_id": "79a37faaf9ee5e7eb0e7392a19f2894a" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ሕዳር 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በመከላከያ ሰራዊት ላይ የጽንፈኛው ሃይል የአገር ክህደት ተግባርና ጥቃት ማድረሱን የጁንታው አባል የሆኑት ሴኮቱሬ ጌታቸው መሰከሩ።", "passage_id": "2b1248d35a3e23babb9e35a55968de44" }, { "passage": " አዲስ አበባ፡- የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልን ከሚያዋስኑ አገሮች ድንበር ጥሰው ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ አካላት የሚጠብቃቸው የጤና ምርመራና ድንበር በመጣሳቸው ደግሞ የህግ ተጠያቂነት መሆኑን የክልሉ ግብረ ኃይል ጸሐፊና የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መሀመድ ሀምደኒል ገለጹ፡፡ ወረርሽኙን እንደ ትልቅ መሳሪያ በመጠቀም ጥቃት እንዳይኖርም እየተንቀሳቀሱ መሆናቸውን ተናገሩ፡፡ኮሚሽነር መሀመድ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ ድንበር ጥሶ የሚገባ አካል ምርመራ የሚደረግበት በሁለት መልኩ ነው፡፡ የመጀመሪያው ሰውዬው በኮሮና ቫይረስ መያዝ አለመያዙን ለማረጋገጥ የሚያስችል የጤና ምርመራ ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ደንቡን በመጣሱ ተጠያቂ ማድረግ ነው፡፡ ለዚህ ዋና ምክንያቱ የወረርሽኙ ጉዳይ እየከፋ በመምጣቱ ዋጋ እንዳያስከፍል ህጉን ጠበቅ ለማድረግ ታስቦ ነው፡፡እንደ ኮሚሽነሩ ገለጻ፤ በግልጽ በህግ የተቀመጡ መግቢያ ኬላዎች አሉ፡፡ እነዚህም ሶስት ሲሆኑ፤ በተለይ ከሱዳን ጋር የሚያዋስኑ ናቸው፡፡ ይሁንና ዝግ በመሆናቸው በፌዴራል ፖሊስ የሚጠበቁ ናቸው፡፡ ከደቡብ ሱዳን ጋር ግን ህጋዊ የሆኑ ኬላዎች ስለሌሉ ሰዎች በአቋራጭ ሊጠቀሙባቸው የሚችሉትን መንገዶች በሰው ኃይል ዝግ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡ ተንጠባጥቦ የሚመጣውን ሰርጎ ገብ ግን ጸረ ሽምቅ ኃይልና ሚሊሻ ስለተቋቋመ ጥበቃው የተጠናከረ በመሆኑ ተጠያቂ በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡ በመሆኑም በተዘጋጀው ለይቶ ማቆያ ይገባሉ፤ በሰሩት የህግ ጥሰት ደግሞ ተጠያቂ ይሆናሉ፡፡ እስካሁን በተደረገው ርብርብ ምንም አይነት ሰርጎ ገብ ድንበር ተሻግሮ አልገባም ያሉት ኮሚሽነር መሀመድ፤ከዛ በፊት ግን ወረርሽኙ በአገራችን ከተገኘ ጊዜ ጀምሮ ወደ 65 ያህል ሰው በህገ ወጥ በመግባቱ በጤናው ጉዳይ ተመርማሪም ተጠያቂም ማድረግ ችለናል ብለዋል፡፡እርሳቸው እንዳሉት፤ ክልሉ ደቡብ ሱዳንና ሱዳን ያዋስኑታል፡፡ ስለዚህም ሰዎች በመውጣትና በመግባት በሽታውን እንዳያመጡ ከሌሎቹ የአገሪቱ የደህንነት ስራ ጋር በማቀናጀት የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ነው፡፡በክልሉ ያለው የመከላከያ ኃይል የግብረ ኃይሉ ሰብሳቢ ሲሆን፤ ከግብረ ኃይሉ ጸሐፊ ጋር በመሆን በየጊዜው የተሰሩ ስራዎችን ለክልሉ ፕሬዚዳንት ሪፖርት ያቀርባሉ፡፡በድንበር አካባቢ ሰው እንዳይገባ የመከላከያ ሠራዊታችንና የክልሉ ፖሊስ ሽምቅ ኃይላችን እንዲሁም ፌዴራል ፖሊስ እና ሚሊሻ በማደራጀት በቋሚና በተንቀሳቃሽነት ስራዎችን በመስራት ላይ እንገኛለን ያሉት ኮሚሽነሩ፤ በተለይ ደግሞ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በክልላችን እየተገነባ ያለ ፕሮጀክት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ህዳሴ ግድባችንን ለማደናቀፍ የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ይህንን ወረርሽኝ እንደ ትልቅ መሳሪያ ተጠቅመው እንዳያጠቁ በጉዳዩ ዙሪያ በጣም በጥንቃቄ እየተንቀሳቀስን ነው ብለዋል፡፡እስካሁን በተንቀሳቀሱባቸው ተግባራት የተወሰዱ እርምጃዎችም መኖራቸውን ጠቁመው፤ የተያዙ ግለሰቦች በገንዘብም በእስርም የተቀጡ መሆናቸውን አስረድተዋል:: ኃላፊነታችን አገርንና ህዝብን መጠበቅ ነው ሲሉም ገልጸው፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ወሳኝ በመሆኑ ህዝቡ ለአዋጁ መከበር ሊተባበር እንደሚገባው ተናግረዋል፡፡ እንደ እርሳቸው ገለጻ፤ በአገር አቀፍ ደረጃ መንግስት እየወሰደ ያለው እርምጃ በጣም ጥሩ ነው፡፡ ጤና ሚኒስቴር የሚያወጣቸውን እና ኮማንድ ፖስቱ የሚያወጧቸውን መመሪያዎችን በተቀናጀ መልኩ በማስከበር ላይ ናቸው፡፡ በክልል ደረጃም የተቋቋመው ግብረ ኃይል እስከ ዞን፣ ወረዳና ቀበሌ ድረስ በጸጥታም ሆነ በህግ ማስከበር ስራ ተሰማርቷል፡፡ ጎን ለጎን ደግሞ ግንዛቤ ሊያስጨብጡ የሚያስችሉ ትምህርቶችም እየተሠጡ ነው፡፡ በእስካሁኑ ካጋጠሟቸው ተግዳሮቶች መካከል ሺሻ ቤቶችና ገበያ አካባቢ የሕግ መጣስና የጥንቃቄ ጉድለት መፈጠር ነው ሲሉ ጠቅሰዋል፡፡ አክለውም ሰዎች በሽታውን የመናቅና አይዘኝም የማለት ነገር እንደሚያንጸባርቁም ተናግረዋል፡፡ ነገር ግን ግንዛቤ እንዲኖራቸው የተለያዩ ስራዎችን መስራታቸውንና ህግ በሚጥሱት ላይ ርምጃ በመውሰድ ላይ መሆናቸውን አመልክተዋል፡፡ በመሆኑም የተሻለ ግንዛቤ በመያዝ ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡አዲስ ዘመን ግንቦት 22 /2012 ዓ.ም አስቴር\nኤልያስ", "passage_id": "7afcb23610aaafd88d2c56046f1b5a5d" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 5 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) መንግስት በትግራይ ክልል የወሰደው ህግን የማስከበር እርምጃ በስኬት መጠናቀቁን በህንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር ዶክተር ትዝታ ሙሉጌታ ገለፁ።አምባሳደሯ ዩናይትድ ኒውስ ኦፍ ኢንዲያ ጋር በነበራቸው ቆይታ ህግ የማስከበር እርምጃው ተጠናቆ ዜጎችን መልሶ ወደ ማቋቋም ስራ መገባቱን ተናግረዋል።ቀሪው ስራም የተደበቁ የህወሓት ቡድን አባላትን በቁጥጥር ስር ማዋልና ለህግ ማቅረብ ነው ብለዋል፡፡ህግን የማስከበር እርምጃው ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ ሁሉንም ዓላማዎች በስኬት ማጠናቀቅ ተችሏልም ነው ያሉት፡፡የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ ከማቋቋም ጋር በተያያዘም የኢትዮጵያ መንግስት ጥሩ ልምድ እንዳለውም አስረድተዋል።በመሆኑም ቀጣይ የመንግስት ስራ ወደ ሱዳን የተሰደዱ እና በሀገር ውስጥ የተፈናቀሉ ዜጎችን ማቋቋም እንደሆነም ገልፀዋል፡፡", "passage_id": "79c1f9ad56346e88367515622dd2ef37" } ]
91b551a776ebef4aae0451c04e846ee1
64fbaacb8f825f1c6038eaf460ace499
በግማሽ የበጀት ዓመቱ ለግድቡ ግንባታ በአዲስ አበባ ከተማ ከ1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ ተሰበሰበ
በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ ፦ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በግማሽ በጀት ዓመቱ ከአዲስ አበባ ከተማ ከ 1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ መሰብሰቡ ተገለፀ:: የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ምስክር ነጋሽ እንደገለጹት÷ በስድስት ወራት በከተማው በቦንድ ግዢ ሽያጭ እና በስጦታ የተሰበሰበው ገንዘብ ባለፉት 8 ዓመታት በድምሩ ከተሰበሰበው የሚበልጥ ነው::ከ2003 ዓ.ም ሐምሌ ወር እስከ 2012 ዓ.ም ሐምሌ ወር ባሉ ዓመታት በከተማዋ የተሰበሰበው 1 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር እንደነበር ጠቁሟል :: ለገቢው ማደግ ምክንያት መንግስት ፕሮጀክቱን በግልፅነት መምራት መቻሉ እንደሆነ አመልክተዋል::ፕሮጀክቱ ላይ የነበሩ ችግሮች ይፋ ተደርገው የማስተካከያ እርምጃ በመውሰድ በሕዝብ እና በመንግስት መካከል መተማመን እንዲፈጠር መደረጉንም አስታውቀዋል::የግድቡ የመጀመሪያ ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት መከናወንም ማህበረሰቡ ከፍተኛ ድጋፍ እንዲያደርግ መነቃቃት መፍጠሩንም ጠቁመዋል::በ2013 ዓ.ም በጀት ዓመት 789 ሚሊዮን ብር እሰበስባለሁ ያለው ከተማ አስተዳደሩ በግማሽ ዓመት ውስጥ 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ መቻሉንም አመልክተዋል ::
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=39247
[ { "passage": "ባለፉት ስድስት ዓመታት ለታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከአዲስ አበባ ከ700 ሚሊየን ብር በላይ ማሳባሰብ እንደተቻለ የአዲስ አበባ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት አስታወቀ፡፡የአዲስ አበባ ሴቶችና ሕፃናት ጉዳይ ቢሮ በበኩሉ ከቦንድ፣ ከቲሸርት ሽያጭና ከሌሎች የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራሞች ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለማሰባሰብ ማቀዱን ገልጿል፡፡የአዲስ አበባ ሴቶችና ሕፃናት ጉዳይ ቢሮና የአዲስ አበባ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት የግድቡ መሰረት የተጣለበትን 6ኛ ዓመትና ማርች 8 ምክንያት በማድረግ በሰጡት የጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተመልክቷል፡፡የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ ዓለምፀሐይ ኤልያስ በዕለቱ እንደተናገሩት የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እውን መሆን በተለይም ሴቶችን በኢኮኖሚያዊና በማህበራዊ ዘርፎች በከፍተኛ ደረጃ ተጠቃሚ እንደሚያደርጋቸውና አሁን ያለባቸውን ጫና በማቃለል ኑሮአቸውን ለመቀየር ያስችላል፡፡ ለበዓሉ የተዘጋጀው ሩጫም ለሕዳሴውን ግድብ ሕብረተሰቡ እያከናወነው ያለውን ጠንካራ ተሳትፎና ሀገራዊ መግባባትን ወደ ላቀ ደረጃ ከፍ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት ለማገዝ ጉልህ ድርሻ እንዳለው ገልጸዋል፡፡በወርሐ ጥር የጀመረውና የካቲት 28 የሚጠናቀቀው ልዩ የገቢ ማሰባሰቢ ፕሮግራም ከ60 ሺህ በላይ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ የተለያዩ አደረጃጀቶችና የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሳተፉ ይጠበቃል ብለዋል።የአዲስ አበባ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ሽታዬ መሐመድ በበኩላቸውሁለቱን ድርብ በዓላት ለማክበር በሚዘጋጁ ፕሮግራሞች ከሴቶች የልማት ቡድን ቁጠባ ከ3 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር፣ ከቦንድ ሽያጭ 10 ሚሊየን ብር በላይ እንዲሁም ከቲሸርት ሽያጭ 6 ሚሊየን ብር  ለመሰብሰብ ታቅዷል፡፡ገቢ ማሰቢሳቢያ ፕሮግራሞች ከምክር ቤቱ አስከ ወረዳ ድረስ የተዘረጉትን የአሰራር ሒደቶችን ይበልጥ ወደ ተግባር በመቀየር ይበልጥ ውጤታማ ሥራዎችን በቋሚነት ለማከናወን ጥረት እንደሚደረግም ተናግረዋል፡፡በመዲናዋ በተዘጋጁ 71 ማዕከላት ባለፉት ሶስት ቀናት ከተሸጠ ቦንድ ከ10 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ታውቋል፡፡ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀንና የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመሠረት ድንጋይ የተጣለበትን 6ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ በመላ ሀገሪቱ ከ650 ሺህ በላይ ዜጎችን የሚያሳትፈው ታላቅ ሩጫ ነገ እሁድ የካቲት 26 ቀን 2009 ዓ.ም. ይካሄዳል፡፡ሩጫው “ጊዜ የለንም እንሮጣለን ለሕዳሴ ግድባችን እንቆጥባለን!” በሚል መርህ እንደሚከናወን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል፡፡ ", "passage_id": "b5ce8a32eb4471b5ef39f94320bb4b89" }, { "passage": "የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት እንዲሰጥ በአንድነት መንፈስ መሰራት እንዳለበት የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ከዚህ በፊት የነበረው ህዝባዊ መነሳሳት እንዲቀጥልና መንግስት በግድቡ ዙሪያ የሚከናወኑ ስራዎችን የተመለከቱ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ማድረስ እንዳለበትም ነዋሪዎቹ ጠይቀዋል፡፡ግድቡም ተጠናቆ አገልግሎት እንዲሰጥና በህብረተሰቡ ዘንድ አመኔታ አንዲኖር መንግስት በትኩረት እየሰራ አንደሆነ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ኃይሉ አብርሃም ገልጸዋል፡፡ከቦንድ አከፋፈል ጋር ተያይዞ የሚነሱ ቅሬታዎችን ጥናት በማድረግ ለመፍታት እየተሰራ መሆኑንም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ግድቡ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ተጠናቆ ኃይል ማመንጨት ባይችልም የግንባታ ስራው አሁን ላይ 65 በመቶ መድረሱ ተገልጿል፡፡በቅርቡ የግንባታውን ስራ ለማስቀጠል ከግንባታ ድርጅቶች ጋር ስምምነት ተደርጎ ወደ ስራ መገባቱ ይታወሳል፡፡የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የተጀመረበት 8ኛ ዓመት በዓል የፊታችን መጋቢት 24 በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል፡፡ ", "passage_id": "7d81ea48f6369884ad06e1ea06075de9" }, { "passage": "ሞገስ ጸጋዬአዲስ አበባ፡- በወቅታዊ አገራዊ ሁኔታዎች ያልተገ ታው የታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ድጋፍ ከምን ጊዜውም በላይ ተጠናክሮ መቀጠሉ እና ባለፉት አራት ወራት ብቻ ከ624 ሚሊዮን ብር በላይ በልማት ባንክ የተረጋገጠ በህዳሴው ግድብ አካውንት ገቢ መደረጉ ተገለጸ።በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልድ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ቀላል የማይባል የህዝብ ለህዝብ የዲፕሎማሲ ሥራ እየሠሩ መሆኑንም ነው የታላቁ የህዳሴ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ያስታወቀው።የጽህፈት ቤቱ የሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ኃይሉ አብርሃም በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ የታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ የህዝብ ተሳትፎ ከወቅታዊ የህግ ማስከበር ሂደት ጋር በተያያዘ የሚዲያው ትኩረት ቢቀንስም አሁንም ድጋፉ ሳይቋረጥ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በዚህም ከመላ ሀገሪቱ ባለፉት አራት ወራት ብቻ በልማት ባንክ የተረጋገጠ ከ624 ሚሊዮን ብር በላይ በህዳሴ ግድብ አካውንት ገብቷልእንደ አቶ ኃይሉ ገለጻ፤ ላለፉት አራት ወራት የነበረው የህዝብ ተሳትፎ እጅጉን ከፍ ያለ ሆኖ ተስተውሏል። ለአብነትም የመጀመሪያው የውሃ ሙሌት ከተጠናቀቀ በኋላ በሀምሌ ወር 119 ነጥብ 9 ሚሊዮን፣ በነሐሴ ወር 152 ሚሊዮን፣ በመስከረም ወር 197 ሚሊዮን እና በጥቅምት ወር 155 ሚሊዮን ብር የተጣራ ገቢ መሰብሰብ ተችሏል።የታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ገቢ በዋናነት ቦንድ በመሆኑ ህብረተሰቡ የቦንድ ግዥን አጠናክሮ እንዲቀጥል እየተሠራ ነው ያሉት አቶ ኃይሉ፤ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በተለያየ መልኩ እያገዙ መሆኑንም ተናግረዋል። በዚህም ዲያስፖራው በግድቡ የሚነሱ ጉዳዮች ላይ በኢትዮጵያ ላይ ተፅዕኖ ለማድረግ የሚሞክሩ ሥራዎችን በመቃወም ከፍ ያለ ኃላፊነት እየተወጡ መሆኑንም ገልጸዋል።‹‹ድምፃችን ለግድባችን›› በማለት በዓለም የሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያውያን ዲያስፖራዎች ከኢትዮጵያውያን ፕሮጀክት ጎን በመሆን ድጋፋቸውን አሳይተዋል። ለዚህም በተለያዩ ክፍላተ ዓለማት 72 ያህል የታላቁ የህዳሴ ግድብ ምክር ቤቶች ያሉ ሲሆን፤ ምክር ቤቶቹም በያሉበት የኢትዮጵያ ማህበረሰቦች በመሰባሰብ ዕርዳታ የሚያሰባስቡባቸው ናቸው። በዚህ ረገድ ዘንድሮ አስረኛ ዓመቱን አስመልክቶ በዓለም ዙሪያ ለሚገኙ ኢትዮጵያ በውጭ ጉዳይ፣ በዲያስፖራ ኤጅንሲና በምክር ቤቶች አማካኝነት በየሀገራቱ እንደሚከበር እና የቦንድ ግዥም እንደሚካሄድ ነው አቶ ኃይሉ የገለጹት።እንደ አቶ ኃይሉ\nገለጻ፤ በውጭ ሀገር\nያሉ ኢትዮጵያውን ቦንድ\nለመግዛት ቢፈልጉም የብር\nማስኮብለል ተደርጎ ስለሚቆጠር\nምቹ አልነበረም። ነገር\nግን የተለያዩ ዘዴዎችን\nበመጠቀም ድጋፋቸውን አጠናክረው\nእየሄዱ ነው። በዚህ\nዓመት ለመምህር ግርማ ወንድሙ ወደ 450 ሺህ ብር በስጦታ መልክ በመላክ የቦንድ ግዥ ፈጽመዋል። ከገንዘብ ድጋፍ በላይ ለሀገራቸው ጠበቃ በመሆን ለማስረዳትም በተለያዩ ጆርናሎች ላይ በመሳተፍ ስለ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ጠቀሜታ በማሳወቅ ላይ ናቸው። በማህበራዊ ሚዲያ ላይም ቀላል የማይባል ሥራ እየሠሩ ይገኛሉ።ሁሉም ኢትዮጵያውያን ወቅታዊ ጉዳይ ሳያዘናጋቸው ዓይናቸውን ከግድቡ ማንሳት እንደሌለባቸው የሚናገሩት አቶ ኃይሉ፤ በዘንድሮው ዓመት የሙከራ የኃይል ማመንጨት እንደሚጀምር፣ ለዚህም አጠቃላይ የቴክኒካል ሥራዎች እያለቁ ስለሆነ በቀጣይ ሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሌት እና አሁን ባለው ሁኔታ የግድቡ አፈጻጸም ወደ 77 በመቶ መድረሱን በመጠቆም፤ እስከ ግድቡ ፍጻሜ ሁሉም በሚችለው ሁሉ ድጋፎችን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 7/2013 ", "passage_id": "e3005ee1aa72de148186ce4d66b5ecad" }, { "passage": "በተያዘው በጀት ዓመት ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሁለት ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱ ተገለፀ፡፡የግድቡን ግንባታ በተያዘለት ዕቅድ ለማስኬድ ገንዝብ የማሰባሰብ ሥራውን ማጠናከር እንደሚገባ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የፋይናንስና ኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪና የመገናኛ እና ኢንፎርሜሽን ሚኒስትር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ለዋልታ ተናግረዋል፡፡‹‹ባለፉት አምስት ዓመታት ከ28 ቢሊየን ብር በላይ ገንዘብ ማሰባሰብ ተችሏል›› ያሉት ሚኒስትሩ በተያዘው በጀት ዓመትም ከሁለት ቢሊዮን ብር በመሰብሰብ ግንባታውን በተያዘው ፍጥነት የማስኬድ ዕቅድ ተይዟል ብለዋል፡፡ገንዘቡን ለማሰባሰብ የተነደፉ ስልቶች አሉ ወይ) በሚል ዋልታ ላቀረበላቸው ጥያቄ ‹‹ 8100 ኤ፣ የቦንድ ሽያጭ፣ የተለያዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ጨዋታዎችና ፕሮግራሞች ተግባራዊ ይደረጋሉ›› ብለዋል፡፡ከገንዘብ ማሰባሰቡ በተጓዳኝ ሠፊና ጠንካራ የዲፕሎማሲ ሥራ እንደሚከናወን ዶክተር ደብረፅዮን ተናግረዋል፡፡ የዳያስፖራውን ተሳትፎ ለማሳደግና ለማጠናከርም ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል፡፡ዶክተር ደብረፅዮን እንዳሉት ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ህዝብ የዲፕሎማሲ ልዑካን በሱዳንና በግብፅ ያካሄዱት ጉብኝት ጥሩ ውጤት አስመዝግቧል፡፡ ባለፈው ዓመት የሱዳን ህዝብ የዲፕሎማሲ ልዑካን በኢትዮጵያ ያደረጉት ጉብኝት የዲፕሎማሲ ሥራ ጥረት ነው፡፡ በቀጣይም የዲፕሎማሲ ጥረቱ ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡‹‹አጠቃላይ የግድቡ ሥራ 54 በመቶ ደርሷል፡፡ 750 ሜጋ ዋት ኃይል የሚያመነጩ ተርባይኖቹን የመግጠም ሥራ በቅርቡ ይከናወናል›› ያሉት  ሚኒስትሩ ተረባይኖቹም የግድቡ ሥፍራ መድረሳቸውን ነው የጠቆሙት፡፡የታላቁ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ብሔራዊ ምክር ቤት ሰሞኑን ባካሄደው 8ኛ መደበኛ ጉባኤ ባለፉት አምስት አመታት ከ28 ቢሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን አስታውሶ ይህም ይህም ቃል ከተገባው 49 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ከግማሽ በላይ መሆኑን ነው ያመለከተው።በ2008 በጀት አመት 12 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ቃል ተገብቶ 8 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን ጠቁሞ ይህም ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ የተሰበሰበበት ዓመት መሆኑን በሪፖርቱ አስረድቷል፡፡ ከዲያስፖራው ማህበረሰብም እስካሁን 2 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር መሰብሰቡ ተመልከቷል፡፡ ", "passage_id": "324113830632b241e96d3fdd9913c064" }, { "passage": " – በሩብ ዓመት ብቻ 168 ሚሊየን ብር ተሰብስቧልአዲስ አበባ፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ለማፋጠን ሲባል ተከፍተው የነበሩ\n4000 የገንዘብ አካውንቶች በአንድ ቋት መካተታቸው ተገለፀ። ህዝባዊ ተሳትፎ እንደቀጠለ ሲሆን በ2012 ሩብ ዓመት ብቻ 168 ሚሊየን ብር መሰብሰቡ ተጠቆመ። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት የህዝብ ግንኙነትና የሚዲያ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ኃይሉ አብርሃም ትናንት በሰጡት መግለጫ፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ለማፋጠን ሲባል በድርጅቶች፣ ተቋማትና ግለሰቦች ተከፍተው የነበሩ ከ4000 በላይ አካውንቶች ለሥራ ያመች ዘንድ በአንድ አካውንት ብቻ እንዲስተናገድ ተደርጓል። እንደ አቶ ኃይሉ\nገለፃ፤ የግድቡ ግንባታ\nበተፋጠነ ሁኔታ የቀጠለ\nሲሆን ህዝባዊ ተሳትፎውም\nአሁንም ተጠናክሮ ቀጥሏል።\nበ2011 በጀት\nዓመት 970 ሚሊየን\nብር የተሰበሰበ ሲሆን\nበ2012 ሩብ\nዓመት ደግሞ 168 ሚሊየን\n953 ሺህ ብር ገቢ\nተገኝቷል። በተለይም በመስከረም\n2012 ዓ.ም 82 ሚሊየን\nብር ተሰብስቧል። በቀጣይም\nበአማካይ በየወሩ 100 ሚሊየን\nብር የመሰብሰብ ውጥን መኖሩን አመልክተዋል። ቀደም ባሉት ዓመታትም ህዝባዊ ተሳትፎ በነበረበት ወቅትም እስከ 100 ሚሊየን ብር ይሰበሰብ ነበር። ከገንዘብ ተቋማት ጋር በመሆን ጽሕፈት ቤቱ በስፋት እየሠራና ቃል የተገቡ ሀብቶች ተሸጠው ብሩ እንዲገባ እየተደረገ ነው። ለህዝብ መረጃ በመስጠት ረገድ ክፍተት መኖሩንም በመጠቆም፣ በዚህ ረገድ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በስፋት እንዲሠሩ ጥሪ ቀርቧል። መሥሪያ ቤቶች ተከታትለው ቦንድ ለገዙ ዜጎች ኩፖን አለመስጠታቸው ሌላው ችግር እንደነበር አስታውሰዋል። የቦንድ ግዥ በተመለከተም በርካታ ቅሬታዎች ነበሩ። በአሁኑ ወቅት ግን ሰባት ማይክሮ ፋይናንስ፣ ልማት ባንክ እና ንግድ ባንክ ጋር በመነጋገር አሠራሩ ፈር እንዲይዝ ተደርጓል። እስከ አሁን ቦንድ ለገዙ ዜጎች ስድስት ቢሊዮን ብር ተመላሽ ሆኗል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ፤\nበግድቡ ግንባታ ዙሪያ\nየኢትዮጵያ አካሄድ ሳይንሳዊና\nየወንዙን የ100 ዓመት\nፍሰትን መሰረት በማድረግ\nየውሃ ሙሌቱን ታሳቢ\nአድርጋ እየሠራች ነው።\nግብፅ ከዲፕሎማሲ ስትወጣ\nመስመር እንድትይዝ እየተደረገ\nመሆኑንም አብራርተዋል። ‹‹እየገነባን\nያለነው ግድብ እንጂ\nስታዲየም አይደለም›› ለዚህም\nግድቡ ውሃ እንዲይዝ\nበሳይንሳዊ መንገድ እንሠራለን ብለዋል። ግብፅ በአባይ ላይ\nእምነት በማጣቷም ሦስተኛ\nአደራዳሪ መፈለጓንም ጠቁመዋል።\nይሁንና የሚደራደሩት ባለሙያዎች\nበመሆናቸው ኢትዮጵያ አሁንም\nበፍትህ አደባባይ አሸናፊ\nትሆናለች፤ ብሔራዊ ጥቅሟንም\nአሳልፋ አትሰጥም ነው\nያሉት። ግብፅ ጉዳዩን በፖለቲካ ዓይን ከማየት በዘለለ ሌላ እይታ እንዲኖረው አትፈልግም። ይሁንና ግድቡ እውን እንዲሆንም የኢትዮጵያም ህዝብና መንግሥት ወሳኝ ሚና እንዳላቸው አብራርተዋል። መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፤ የግድቡ\nመሰረተ ድንጋይ ሲቀመጥ\nበ80 ቢሊዮን ብር ለማጠናቀቅ ታስቦ የነበረ ሲሆን፤ እስካሁን 99 ቢሊዮን ብር ወጪ ተደርጓል። ግድቡን ለማጠናቀቅ ደግሞ 40 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ ወጪ ይጠይቃል። ለግድቡ ግንባታ 15 ከመቶ የሚሆነውን ገንዘብ ከህዝቡ ለመሰብሰብ የታቀደ ሲሆን እስካሁን 13 ቢሊዮን ብር ከህዝቡ መሰብሰቡ ይታወቃል።አዲስ ዘመን ጥቅምት 29/2012 ክፍለዮሐንስ አንበርብር ", "passage_id": "6f585f89273e169671a62cec79934d3d" } ]
87d34fb4ca21656be9b9f5b19d005ad8
238790f6962b11e39b556fdfe12c1add
ስፖርቱ የማገገሚያ ድጎማ እንዲያገኝ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
የኮቪድ 19 ወረርሽኝ የዓለም ወቅታዊው ሁኔታ፤ የሰውን ልጅ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ፣ አስተሳሰብና ልማድ እንዲቀየር ምክንያት ሆኗል፡፡ በዚህ መንስኤነትም አካላዊና አእምሯዊ ጤናን ከመጠበቅና ከማዝናናት ባለፈ ከፍተኛ ገንዘብ የሚዘዋወርበት ስፖርትም በቀድሞ ቁመናው ላይ እንዳይገኝ ሆኗል፡፡ በዘርፉ በዓለም ደረጃ እአአ በ2011 ከተገኘው ገቢ በ45 በመቶ የላቀ ትርፍ ከሁለት ዓመታት በፊት መገኘቱን ወርልድ ኢኮኖሚክ ፎረም ያመላክታል፡፡ ይህ እአአ በ2018 የተገኘው 471ቢሊዮን ዶላር በዚህ ዓመት በእጅጉ ሊያድግ እንደሚችልም አመላካች ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ባልተጠበቀ ሁኔታ ተከስቶ መላውን ዓለም ባዳረሰው የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ምክንያት እንቅስቃሴው ሊገታ ችሏል፡፡ እንደ ሌላው ዓለም ሁሉ የኢትዮጵያ ስፖርትም መዳከም አሳይቷል፡፡ በእንቅስቃሴው መገታት በስፖርተኞች፣ ክለቦች፣ ማሰልጠኛ ማዕከላት፣ አወዳዳሪዎችና ሌሎች ባለድርሻዎች መካከል የነበረው ሰንሰለት በቫይረሱ ተጠቅቷል፡፡ በጥቂት ውድድሮች ሽልማት በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብና የውጭ ምንዛሪ ለሀገር ያስገኙ ከነበሩ አትሌቶች፤ ‹‹ነገ ያልፍልኛል›› በሚል እሳቤ ከኑሮ ጋር እስከሚታገሉት ጀማሪ ስፖርተኞች ድረስ የጉዳቱ ሰለባ ሆነዋል፡፡ ከአቅማቸው በላይ የሆኑትም ከበጎ ፈቃደኞች ተደጓሚ ሆነዋል፡፡ የስፖርት ማህበራትም ከውድድሮችና ስፖንሰሮች ማግኘት የሚገባቸውን ሳያገኙ ቀርተዋል፡፡ ይህንን አሳሳቢ ሁኔታ ያጤነው የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽንም ወረርሽኙ በዘርፉ ላይ ያሳደረውን ጫና በማመዛዘን እንዲሁም በተወሰነ መልኩ የሚያገግምበትን ሁኔታ ለማመቻቸት የሚረዳ ሥራ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ በጉዳዩ ላይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ ማብራሪያ የሰጡት ምክትል ኮሚሽነር ዱቤ ጂሎ፤ ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ እንደ ንግድ ሁሉ ስፖርትም ጉዳት ያስተናገደ ዘርፍ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ስፖርተኞች ቀድሞ የሚያገኙትን ገቢ ማግኘት ባለመቻላቸው፣ ክለቦች የመፍረስ አደጋ የተደቀነባቸው በመሆኑ መሰል ጉዳዮችን ከግምት በማስገባት ከመንግሥት ማገገሚያ የሚሆን የገንዘብ ድጋፍ እንዲለቀቅ ጥያቄ መቅረቡንም ይገልጻሉ፡፡ ኮሚሽኑ ለመንግሥት ያቀረበው የዳሰሳ ጥናት ‹‹ኮሮና ቫይረስ በስፖርቱ ልማት ላይ ያሳደረው ተጽእኖ የማገገሚያ ስልት›› የሚል ሲሆን፤ ጥናቱ የተከናወነውም የሌሎች ሀገራትን ተሞክሮ በመቀመር ጭምር ነው፡፡ በዚህም እንግሊዝ፣ ናይጄሪያ፣ ኬንያ እና የመሳሰሉት ሀገራት በወረርሽኙ ወቅት ለማገገሚያ የተጠቀሙትን ስልት ለመዳሰስ መሞከሩንም አመላክተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ስፖርት ሕዝባዊ መሠረት ያለው እንደመሆኑ በስፖንሰርና በስታዲየም ገቢ ከሚያገኙት ገንዘብ ባለፈ ለከተማ ክለብ ስፖርተኞች ደመወዝ የሚከፈለው ከሕዝብ ከሚሰበሰበው ታክስ ነው፡፡ ይህም ማለት አብዛኛውን ገንዘብ የሚሸፍነው መንግሥት ነው፡፡ ከወቅቱ ነባራዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ውድድሮችን ማካሄድ ባለመቻሉ በዘርፉ ያለው  እንቅስቃሴ አስቸጋሪ ሆኗል፡፡ ይህንን ጊዜ ለመሻገርም ከስፖርት ማህበራቱ ጋር በመተባበር ስትራቴጂ በመንደፍና ጥያቄውን ለመንግሥት በማቅረብ ኮሚሽኑ ምላሽ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ ጥናቱ ስፖርተኞች በምን መልክ ወደሥልጠናና ውድድር ይመለሱ፣ እንዴትስ ፈቃድ ይሰጣቸው የሚለውን በመነሻነት መያዙንም ነው ምክትል ኮሚሽነሩ የሚጠቅሱት:: እንደ ኮሚሽንም ሀገር አቀፍ የስፖርት ማህበራቱ መርሃ ግብራቸውን እንዲያቀርቡም መመሪያ ተላልፏል፡፡ በኢትዮጵያ ስፖርት የሚንቀሳቀሰው የገንዘብ መጠን በውል አይታወቅም፡፡ ይህም መሰል ጥናቶች ላይ ተጽእኖ ማሳደሩ አይቀርም፡፡ ነገር ግን እያንዳንዱ ፌዴሬሽን ይብዛም ይነስም በስፖንሰር የሚያገኙት ገቢ ይኖራል፤ ሆኖም በዓመት ይህን ያህል ይገኛል የሚለው በውል አይታወቅም፡፡ ለአብነት ያህል የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ኢንተርናሽናል እና የሀገር ውስጥ ስፖንሰሮች ቢኖሩትም ከወቅታዊው ሁኔታ ጋር በተያያዘ በትክክል ለማወቅ የሚቻልበት ሁኔታ አዳጋች ነው፡፡ ቢሆንም ቅድመ በግምቶችን በማስቀመጥ ጥናቱ መከናወኑንም ነው ምክትል ኮሚሽነሩ ያስረዱት፡፡ የኮሮና ወረርሽኝ የስፖርቱን ዘርፍ ሙሉ በሙሉ ጎድቷል፤ እንቅስቃሴዎችንና ውድድሮችን ገድቧል፡፡ በስፖርተኞችና ሀገራትም ላይ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ችግሮችን አስከትሏል፤ ይህም አደጋ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ ጊዜ ያልፋል በሚል ተስፋ ሁሉም በአንድነት እየተጠባበቀ ይገኛል፡፡ መንግሥትም ሁኔታዎችን በማገናዘብ ምላሽ ይሰጣል የሚል ተስፋ አለ፤ ይህን ወቅት በመሻገርም ስፖርቱን ወደነበረበት የስፖርት ቤተሰቡም ወደ ተመልካችነቱ የሚመለስበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም፡፡ በመሆኑም ይህንን ጊዜ በጋራ ለማለፍ ራስን ከቫይረሱ መጠበቅ እንዲሁም የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማድረግ እንዲቆዩም ምክትል ኮሚሽነሩ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡አዲስ ዘመን ሐምሌ 15/2012ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=35809
[ { "passage": "ኢትዮጵያ\nካልተጠቀመችባቸው ነገር ግን እምቅ አቅም እንዳላት በባለሙያዎች ከሚጠቆሙ ስፖርቶች መካከል አንዱ የውሃ ዋና ነው። የ«ውሃ ማማ» በሚል የምትጠራው ኢትዮጵያ የዋናተኞች እንዲሁም የውሃ ችግር ሳይኖርባት ለዘመናት በስፖርቱ እንዳትጠራ ሸብቦ ወደኋላ ያስቀራት ችግርም የውሃ ዋና ገንዳ አለመኖር ነው። ለአንድ ስፖርት የማዘውተሪያ ሥፍራዎች መኖር ዓይነተኛ ሚና እንዳለው የሚታወቅ ሲሆን፤ የውሃ ስፖርቶች ፌዴሬሽንም ይህ ሲፈትነው ቆይቷል። አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ ከተሞች ባሉ ሆቴሎች በርካታ የውሃ ዋና ገንዳዎች ይኑሩ እንጂ፤ በአገሪቷ ውስጥ የውድድር ደረጃን የሚያሟሉት የውሃ ዋና ገንዳዎች በግዮን ሆቴል፣ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ ሌሎች ተቋማት እንዲሁም በጊዜያዊነት ለአንድ ውድድር በሚል በየክልሉ የሚገነቡት ብቻ ናቸው። ከዚህ ባሻገር በወጣቶች ስፖርት አካዳሚ የሚገኘው የውሃ ዋና ገንዳ አገልግሎት የማይሰጥ ሲሆን፤ በሌሎች ስፍራዎች የሚገነቡትም በተለያዩ እንከኖች ከተያዘላቸው ጊዜ በእጥፍ የዘገዩ ናቸው። ነገር ግን በዚህ ፌዴሬሽን ተሳታፊ የነበሩ ባለሙያዎች እና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ፌዴሬሽኑ ለገንዳ መገንቢያ የሚሆን ቦታ እንደተሰጠው ያወሳሉ። ፌዴሬሽኑ የራሱ ገንዳ ሊኖረው ይገባል በሚል እንቅስቃሴ የተጀመረው ከ15ዓመታት በፊት እንደ ነበር በ1990ዎቹ ፌዴሬሽኑን በፕሬዚዳንትነት የመሩት አቶ ግርማ ዳምጤ በአንድ ወቅት ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ መግለጻቸውን ማስታወስ ይቻላል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የኦሊምፒክ ደረጃውን የሚጠብቅ ገንዳ የምትገነባ ከሆነም ዓለም አቀፉ ፌዴሬሽን የተለያዩ ቁሳቁሶች ድጋፍ እንደሚያደርግ ቃል ገብቶ እንደነበርም ያስታውሳሉ። ከዚያ በኋላም ፌዴሬሽኑ መሬት አግኝቷል። አዲስ\nዘመን ጋዜጣም ጉዳዩን በመያዝ በሰራቸው ተከታታይ ዘገባዎች ላይ ቦታው ያለ ግንባታ ተዘንግቶ ባዶውን ለዓመታት መቆየቱን ታዝቧል። ግንባታ ያልተጀመረበት መሆኑን ተከትሎም ቦታው በከተማ አስተዳደሩ በኩል ለሌሎች አካላት ሊሰጥ ይችላል የሚል ስጋትም ከባለሙያዎች ዘንድ ሲሰነዘር ቆይቷል። አሁን ግን ይህ ቦታ መኖሩ ተረጋግጦ በድጋሚ በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን የባለቤትነት ማረጋገጫ ማግኘቱ ተሰምቷል። ቦታው ለኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን በ1998 ዓ.ም፤ ለውሃ ስፖርቶች ፌዴሬሽን እንዲሁም ሜዳ ቴኒስ ፌዴሬሽን በጋራ የማዘውተሪያ ስፍራ እንዲገነቡበት በሚል የተሰጠም ነው። ይህ ቦታ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ሃያት ሪሊስቴት አካባቢ የሚገኝ ሲሆን፤ ለውሃ ስፖርቶች 16ሺ ካሬ ሜትር እንዲሁም ለሜዳ ቴኒስ 15ሺ ካሬ ሜትር የተከፈለ ነው። ኮሚሽኑ የቦታውን ካርታ በ2000ዓ.ም ቢያገኝም፤ ምንም ሳይሰራበት ከ10ዓመት በላይ መቆየቱን በኢትዮጵያ ውሃ ስፖርቶች ፌዴሬሽን የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቀልቤሳ ኤባ ይገልጻሉ። አሁን\nፌዴሬሽኑ ባቀረበው ጥያቄ መሰረትም ከኮሚሽኑ የስፖርት ፋሲሊቲ ጋር በመሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቦታውን ለሌላ መስጠት አለመስጠቱን የማጣራት ሥራ ተሰርቷል። ባለሙያዎችም በቦታው ተገኝተው ከተመለከቱ በኋላ መታጠር ስላለበት የግንባታ ፍቃድ ለማውጣት ተችሏል። በዚህም የሁለቱ ፌዴሬሽኖች የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ከኮሚሽኑ ኃላፊዎች ጋር መክረዋል። በምክክሩም ፌዴሬሽኖች የመገንባት አቅም የሌላቸው በመሆኑ በኮሚሽኑ በኩል በ2012ዓ.ም በጀት ተይዞለት የአጥር ግንባታው እንዲጀመር ወደ ፊትም ምን መሆን ይገባል የሚለው በንግግር አቅጣጫ እንዲይዝ ከውሳኔ ላይ ተደርሷል። ኮሚሽኑ በዚህ ወቅት በብሄራዊ ደረጃ ዓለም አቀፍና ዘመናዊ ስታዲየም በመገንባት ላይ የሚገኝ በመሆኑም ገንዳውን ለመገንባት እንደማይቻል እንደ ምክንያት ተነስቷል። ሁኔታዎች\nቢመቻቹና ገንዳው ቢገነባ ፌዴሬሽኑ የማዘውተሪያ ስፍራ የሚያገኝ በመሆኑ፤ ለብሄራዊ ቡድን ስልጠና፣ ለአገር አቀፍ ሻምፒዮናዎች እንዲሁም ሌሎች ዞን አቀፍ ውድድሮችን ወደ አገር ለማምጣት እንደሚረዳ ኃላፊው ይጠቁማሉ። ከዚህ ባሻገር ለፌዴሬሽኑ የገቢ ምንጭ የሚያገኝበት አንድ መንገድ ይሆናል። ዓለም አቀፉ የውሃ ስፖርቶች ፌዴሬሽንም እገዛ እንዲያደርግ ፌዴሬሽኑ ጥያቄ እንደሚያነሳም አስታውቀዋል። ከዚህ ቀደም ለስፖርቱ ልማት እንዲውል የገንዘብ ድጋፍ መደረጉንም ያስታውሳሉ። ቦታው ከግንባታ ውጪ ለዓመታት ሊቀመጥ የቻለው በተለያዩ ፕሮጀክቶች ግንባታ መደራረብ መሆኑን በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን የስፖርት ፋሲሊቲ ዳይሬክተር ኢንጂነር አዝመራው ግዛው ይገልጻሉ። ካርታው የተሰጠው በ2000ዓ.ም ሲሆን፤ በወቅቱ ደግሞ መንግሥት የኢትዮጵያ ወጣቶችና ስፖርት አካዳሚ፣ የጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል፣ የብሄራዊ ስታዲየም ዲዛይን እንዲሁም ግንባታ በእነዚህ ዓመታት ሲከናወኑ ቆይተዋል። እነዚህ ትልልቅ ፕሮጀክቶች ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁ በመሆናቸው ቅድሚያ በመስጠት የውሃ ዋናው እንዲሁም የሜዳ ቴኒስ ሜዳው ግንባታ መዘግየቱን ያነሳሉ። ሁሉንም በአንድ ጊዜ ለመገንባት በበጀት እጥረት ምክንያት አልተቻለም። እንዲያም ሆኖ ሲገነቡ የቆዩት ፕሮጀክቶች ለእነዚህ ስፖርቶች የሚሆኑ ማዘውተሪያዎችን ያካተቱ ነበሩ። ለአብነት ያህል የወጣቶች ስፖርት አካዳሚ የውሃ ዋና ገንዳ እንዲያካትት መደረጉን እንዲሁም የሜዳ ቴኒስም በአንዳንድ አካባቢዎች መኖራቸውንም ዳይሬክተሩ ይጠቅሳሉ። በከፍተኛ ደረጃ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እጥረት አለ፤ በመሆኑም በአግባቡ ማልማትና ሥራ ላይ ማዋል ተገቢ ነው። መንግሥት ስፖርቱን ለማሳደግ በሚያደርገው ጥረት ለስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ መገንቢያ ቦታውን ቢሰጡም፤ ለዓመታት የቆየው ያለ ሥራ ነበር። በወቅቱ ቦታውን ከልሎ ማስቀመጥ ይገባ እንደነበረም አልሸሸጉም፤ እስካሁንም ወደ መሬት ባንክ ሳይገባ እንዲሁ ቆይቷል። አሁን\nግን ካርታውን የማደስ ሥራ የተከናወነ ሲሆን፤ ከዚህ በኋላም አጥር የመከለል እና በአግባቡ እንዲጠበቅ የማድረግ ሥራ እንደሚከናወን ዳይሬክተሩ ይጠቁማሉ። ከማጠሩ ሥራ በተጓዳኝ ስፍራውን በችግኝ የማልማት እንዲሁም መጠነኛ ግንባታ ይከናወናል። ከዚህ ቀደም የተሰሩ ዲዛይኖች በመኖሩ ይህንን የመገምገም አሊያም አዲስ መስራት የሚገባ ከሆነም እርሱን የማወዳደር ሥራዎችም በቀጣይ በጀት ዓመት የሚከናወን ይሆናል። አሁን በግንባታ ላይ የሚገኘው የብሄራዊ ስታዲየም ከፍተኛ ገቢ የሚጠይቅ በመሆኑ ርብርብ የሚደረገው ይህንን ለማጠናቀቅ ነው። የቦታው ፕሮጀክትም በቀጣይ የሚከናወን ይሆናል። ከዚህ በተጨማሪም ዘርፉ የማዘውተሪያ ስፍራዎች ላይ የተለያዩ ሥራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ዳይሬክተሩ ይጠቁማሉ። የስፖርት\nማዘውተሪያ ስፍራዎችን በተመለከተ በ2004ዓ.ም በወጣው አዋጅ ላይ በአንድ ወረዳ ቢያንስ አንድ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ መኖር እንዳለበት ይጠቁማል። በመሆኑም በየትኞቹ አካባቢዎች የማዘውተሪያ ስፍራዎቹ ይገኛሉ በሚል መረጃ ለማጠናቀር በግብረ ኃይል እየተሰራ ይገኛል። ይህ ሲጠናቀቅም የትኞቹ የማዘውተሪያ ስፍራዎች የይዞታ ባለቤትነት ማረጋገጫ አላቸው? በየትኞቹ አካባቢዎችስ ማዘውተሪያ ስፍራዎቹ ይገኛሉ? የሚለውን መረጃ ማግኘት ይቻላል። ከዚህ በኋላም ያሉት የማዘውተሪያ ስፍራዎች ጥበቃ እንዲያገኙና እንዲለሙ የማድረግ ሥራ ይከናወናል። የይዞታ ማረጋገጫ የሌላቸው ስፍራ ዎችም እንዲያገኙ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የሚሰራ መሆኑን ዳይሬክተሩ አብራርተዋል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 28/2011ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "5ad6ee7bc9e1572c707e2675c695047b" }, { "passage": "ሊጉን በ25 ነጥብ እየመሩ ያሉት የሊቨርፑሎች\n\nአልፎም ተጫዋቾችና ወደ ሜዳ የሚገቡ ሌሎች ባለሙያዎችን ለመመርመር 40 ሺህ መመርመሪያ መሣሪያዎች ያስፈልጋሉ። \n\nየ2019/20 ወድድር ዘመን 92 ጨዋታዎች ይቀሩታል። እነዚህን ጨዋታዎች እንዴት እናጠናቅ በሚለው ዙሪያ የሊጉ ክለቦች የቪድዮ ስብሰባ አድርገው ነበር። በስብሰባው ላይ እንደ ሕክምና ባለሙያዎች ያሉ ያገባቸዋል የተባሉ ሰዎችም ተገኝተው ነበር። \n\nክለቦች ሊጉ በቀላሉ ወደ ውድድር እንደማይመለስ መግባባት ላይ ደርሰዋል። የፕሪሚዬር ሊጉ አስተዳዳሪ አካል መንግሥት ይሁንታ ሲሰጥ ብቻ ነው ወደ ሜዳ የምንመለሰው ብሏል። \n\nገለልተኛ ሜዳዎችን መጠቀም ያስፈለገው ደጋፊዎች ከሜዳ ውጪም ቢሆን እንዳይሰበሰቡ በማሰብ ነው ተብሏል። አልፎም የሚመረጡት ሜዳዎች ከፖሊስና የስፖርት ሜዳዎችን ደህንነት ከሚመረምር አካል ይሁንታ ያገኙ መሆን አለባቸው ተብሏል።\n\nየእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ መጋቢት ወር መግቢያ ላይ ነበር በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት እንዲቆም የተደረገው። ሁሉም የሊጉ ክለቦች የቀሩትን 92 ጨዋታዎች ለመጫወት ተስማምተዋል።\n\nየዚህ ዓመት ወድድር ይቋረጥ የሚል ሐሳብ ከየትኛውም ክለብ አልመጣም ተብሏል። \n\nየእንግሊዝ መንግሥት እንቅስቃሴዎች ቀስ በቀስ ወደነበሩበት እንዲመለሱ ካደረገ በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ በዝግ ሜዳ ወደ ውድድር እንደሚመለስ ይጠበቃል። \n\nተጨዋቾች በሳምንት ሁለት ጊዜ የኮሮናቫይረስ ምርመራ ይደርግላቸዋል። በየቀኑ ደግሞ የበሽታው ምልክት ታየባቸው አልታየባቸው የሚለው ይለካል። አልፎም ሜዳዎች በየጊዜው ንፅህናቸው ይጣራል ተብሏል። \n\nተጫዎቾች ከጨዋታ ውጪ ባሉት ጊዜያት ሁሉ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ማድረግ አለባቸው። በውድድር ስፍራዎች ውስጥም ምግብ መብላትም ሆነ ገላን መታጠብ አይችሉም። \n\n ", "passage_id": "35638ef3cd05bbece21e7c4e58dbd314" }, { "passage": "የወቅቱ የዓለም ራስ ምታት በሆነው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች አንቀላፍተው ቢቆዩም ከሰሞኑ የአውሮፓ ሊጎች ወደ ልምምድ መመለስን ተከትሎ የስፖርቱ ኢንዱስትሪ መነቃቃት ጀምሯል። አሁንም የኮሮና ወረርሽኝ (ኮቪድ 19) ስጋት እንዳለ ቢሆንም ጥንቃቄን በተላበሰ መልኩ ወደ ቀድሞው መደበኛ ሁኔታ ለመመለስ ጥረቶች እየታዩ ነው። በዚሁ ምክንያት ተቀዛቅዞ የቆየው አበረታች ቅመሞችን መከላከልና የመቆጣጠር ሥራ ነው። ይህ ስፖርትን በተፈጥሯዊው መንገድ ብቻ እንዲካሄድ የማድረግ ጥረት ሊቀዛቀዝ የቻለው በዓለም አቀፍ ደረጃ ውድድሮች መቋረጣቸውን ተከትሎ ነው። ይሁን እንጂ ከዓላማው አንጻር ረጅም ጊዜ መውሰዱና መዘናጋቱ ዋጋ ሊያስከፍል ይችላል። \nበመሆኑም ዓለም አቀፉ የጸረ አበረታች ቅመሞች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ በስሩ ለሚገኙት ብሔራዊ ጽሕፈት ቤቶች መመሪያ ማዘጋጀቱን ከሰሞኑ በድረገጹ አስነብቧል። ይህም በየሀገራቱ የሚገኙ የጸረ አበረታች ቅመሞች ተቆጣጣሪ ጽሕፈት ቤቶች ወደ ቀደመ ሥራቸው እንዲመለሱ የሚያስችል ርምጃ ነው። ኤጀንሲው በወረርሽኙ ምክንያት በዓለም ዙሪያ ሲሰሩ የቆዩት ናሙና የመውሰድና ምርመራ የማድረግ ሂደቶችን የቀነሰና አንዳንድ ሥራዎችንም በጊዜያዊነት ማቋረጡን በዘገባው ተጠቁሟል። ነገር ግን አሁን ወደ ሥራ ለመመለስ እንቅስቃሴ መደረግ እንዳለበት የኤጀንሲው ፕሬዚዳንት ዊቶልድ ባንካ ይገልጻሉ። በኤጀንሲው ስር ካሉ ተቋማት ጋር ከወቅታዊው ጉዳይ ጋር በተያያዘ በቅርበት ሲሰሩና ድጋፍ ሲያደርጉ ቆይተዋል። አሁን ግን ሥራው እንደቀድሞው መቀጠል ያለበት በመሆኑ፤ በቴክኖሎጂ በታገዘና የናሙና አወሳሰዱን በአዲስ መንገድ ማካሄድ ተገቢ መሆኑን ያመላክታሉ። ለዚህ ደግሞ በጸረ አበረታች መድኃኒት ቁጥጥር ላይ የሚሰሩ አካላት አዲስ ነገር ለመፍጠር ርብርብ ላይ ይገኛሉ። \nየተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ኦሊቨር ኒግሊ በበኩላቸው፣ በዚህ ወቅት ናሙናዎችን ከአትሌቶች ለመውሰድ አዳጋች መሆኑን ነው የሚጠቁሙት። ምርመራው መቀጠል የሚገባው አስፈላጊው የጤናና ንጽህና ሁኔታ የተስተካከለ ሲሆን ብቻ ነው። የአትሌቶችና በዙሪያቸው ያሉ አካላት ጤናም ኤጀንሲው ትኩረት የሚሰጠው ቀዳሚ ጉዳይ ነው። ተቋሙ የአትሌቶችን ናሙና በመውሰድ አበረታች መድኃኒት ተጠቃሚነታቸውን በምርመራ መለየት ብቻም ሳይሆን የጤና ግለ ታሪካቸውንም መመዝገብ ሌላው ተግባሩ ነው። ንጹህ ስፖርት ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት ግንዛቤ ማስጨበጥም እንዲሁ። በመሆኑም በቀጣይ ሳምንታት ከብሔራዊ ተቋማቱ ጋር በመሆን ሥራው በምን መልኩ መቀጠል ይገባዋል በሚለው ላይ መፍትሄ በማፈላለግ ወደ ሥራ የሚመለስ እንደሆነ አብራርተዋል።\nየሯጮቹ ሀገር ኢትዮጵያም የኤጀንሲው አባል ሀገር በመሆን ንጹህ ስፖርት እንዲካሄድ ሚናቸውን ከሚወጡት መካከል ትጠቀሳለች። ተሞክሮውን ለሌላው ዓለምም ማጋራት የቻለና በሥራው ምስጉን የሆነ ጽሕፈት ቤትም በአጭር ጊዜ ለማቋቋም መቻሉ ይታወቃል። በመላው ዓለም ባጠላው በዚህ የወረርሽኝ ወቅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የጸረ አበረታች ቅመሞች ተቆጣጣሪ ጽሕፈት ቤት እንቅስቃሴውን በምን መልኩ እያከናወነ ይገኛል? የሚለውን የጽሕፈት ቤቱ ዳይሬክተር አቶ መኮንን ይደርሳል ያስረዳሉ። የተቋሙን ውስጣዊና ውጫዊ እንቅስቃሴ በሁለት የሚከፍሉት ዳይሬክተሩ፤ የኮሮናን ቫይረስ በመከላከል ረገድ ሠራተኞችን የመቀነስና የንጽህና ቁሳቁስን የማዘጋጀት ሥራዎች መከናወናቸውን ይጠቁማሉ። \nሁለተኛውና ከተቋሙ ውጪ ከአትሌቶች ጋር በመገናኘት የሚከናወነው ደግሞ ከአበረታች መድኃኒት ቁጥጥር ጋር የተያያዘው ሥራ ነው። ይሁን እንጂ ከአትሌቶች ናሙና መውሰድ በእጅጉ ለንክኪ የሚያጋልጥ በመሆኑ አትሌቶችንም ሆነ በምርመራው ተሳታፊ የሆኑ ባለሙያዎችን ለቫይረሱ ተጋላጭ እንዳይሆኑ በማሰብ ለጊዜው ገታ ተደርጓል። \nነገር ግን ሥራውን ሙሉ ለሙሉ ማቆም የማይቻል በመሆኑ ለቫይረሱ አጋላጭ ይሆናሉ የሚል ስጋት ያሳደሩ ሥራዎችን ፎርማት ለመቀየር መሞከሩን ዳይሬክተሩ ይገልጻሉ። በዚህም መሠረት አበረታች ንጥረ ነገር ተጠቃሚ የሆኑ አትሌቶችን የማጋለጥ፣ አትሌቶች ባዮሎጂካል ፓስፖርት ፕሮግራም ሥራን የማጠናከር እንዲሁም ሌሎች ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። በዚህ ጊዜ ውድድሮች የተቋረጡ ቢሆንም ስፖርተኞች ግን በየግላቸው በቤታቸው ውስጥ እንቅስቃሴ ማድረጋቸውን አላቆሙም። ይህንን ተከትሎም ከውድድር ውጪ የሚወሰዱ አበረታች ንጥረ ነገሮችን ከመውሰድ እንዲቆጠቡም ያሳስባሉ። በጥቅሉ በጊዜያዊነት ንክኪ ካለባቸው ሥራዎች በቀር ሌሎች ሥራዎች እንደቀጠሉ ሲሆን፤ የአድራሻ ምዝገባቸውን በመደበኛ መልኩ የሚያደርጉ በመሆኑ በዚህ ላይም መዘናጋት አይገባም።\nዓለም አቀፉ የጸረ አበረታች መድኃኒቶች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ በመግለጫው ባመላከተው መሠረት፤ ጽሕፈት ቤቱም እንደቀደመው የአትሌቶችን ናሙና ወደመውሰድና መመርመር ሥራው ለመመለስ የሚያስችለውን ሁኔታ እያጠና ይገኛል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ ከሆነም ስፖርተኞች ከባለሙያዎች ጋር የሚኖራቸውን ንክኪ በሚቀንስና ለበሽታው አጋላጭ በማይሆን መልኩ መፍትሄ እንደተገኘ በቀጥታ ምርመራው የሚጀመር ይሆናል። በብሔራዊ ቡድን፣ በክለብ እና በማሰልጠኛ ተቋማት የተያዙ አትሌቶች እንዲሁም በቡድን ሆነው የሚሰሩ ሰልጣኞች በዚህ ወቅት ልምምድ አቋርጠው በቤታቸው ይገኛሉ። ምንም ዓይነት የቡድን እንቅስቃሴ የማይፈቀድ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ አትሌቶች በያሉበት አነስተኛ ልምምድ ብቻ የሚያደርጉ ይሁን እንጂ አሁንም እንደ ተቋም አስጊ ሁኔታዎች መኖራቸው አልቀረም። \nይህም ወቅታዊውን ሁኔታ ሽፋን በማድረግ የተከለከሉ ንጥረነገሮችን የመጠቀም አዝማሚያ ሊኖር ይችላል የሚል ስጋት ነው። እስካሁን በተጨባጭ የተገኘ መረጃ ባይኖርም በዓለም አቀፍ ደረጃም ሆነ እንደ ተቋም ስጋቱ አለ። ከአትሌቶች ባሻገር ከጀርባ በመሆን አጋላጭ የሆኑ አካላት አበረታች ቅመሞችን እንዲጠቀሙ በመገፋፋትና በማሳመን የሕግ ጥሰት የመፈጸም አዝማሚያ ሊኖር ይችላል የሚል ግምት አለ። በመሆኑም ስጋቱን ለመቅረፍ የሚያስችሉ ሥራዎች በመከናወን ላይ ነው የሚገኙት። \nበስፖርተኞች በኩል ስለ ጉዳዩ ያለውን ግንዛቤ ለማስፋትም በመገናኛ ብዙኃን በመታገዝ መልዕክቶች በመተላለፍ ላይ ይገኛሉ። በተመረጡ መገናኛ ብዙኃን ላይም የማስታወቂያ እንዲሁም የማንቂያ ሥራዎች እየተካሄዱ መሆኑን የሚጠቁሙት ዳይሬክተሩ በጽሕፈት ቤቱ ድረገጽም መረጃዎችን እያስተላለፉ ይገኛል። ይህም አትሌቱ በሚመቸው መንገድ መረጃ እንዲያገኝ ያስችለዋል። በቀጣይም በመደበኛነት ማስታወቂያዎቹ የሚተላለፉባቸውን የመገናኛ ብዙኃን ቁጥር ለመጨመር ታቅዷል። ሌላው ጽሕፈት ቤቱ በትኩረት እየሄደበት ያለው የሕግ ማዕቀፍ የማሻሻል ሥራ ነው። ኤጀንሲው የጸረ አበረታች ቅመሞች ሕግን ጨምሮ ሌሎች ዓለም አቀፍ ስታንዳርዶችን አሻሽሏል፤ በመሆኑም በጽሕፈት ቤቱ በኩል እአአ በ2021 ተግባራዊ የሚሆኑ የተለያዩ የሕግ ማዕቀፎችን ለመከለስ በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። \nበመጨረሻም ዳይሬክተሩ ስፖርተኞችም ሆኑ ሌሎች የሀገሪቷ ዜጎች የሕክምና ባለሙያዎችን ምክር በመተግበር በዓለም ላይ ከተከሰተው ወረርሽኝ ራሳቸውን እንዲጠብቁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ስፖርተኞች፣ የስፖርት ባለሙያዎች፣ የስፖርት አመራሮች እንዲሁም ሁሉም ባለድርሻ አካላት በበኩላቸው በአበረታች ንጥረ ነገር መከላከልና መቆጣጠር ሥራው ለአፍታ የቆመ ባለመሆኑ መዘናጋት እንዳይኖር ዳይሬክተሩ ያሳስባሉ። ዓለም አቀፉ ኤጀንሲም ሆነ የዓለም አትሌቲክስ ይህ ጊዜ ሲያልፍ ስፖርቱ አደጋ ላይ እንዳይወድቅ በጥንቃቄ እየተመለከቱት ነው። በዚህ መሠረት የሚመለከታቸው አካላት ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው። ተጠቃሚነታቸው ከተረጋገጠም ጽሕፈት ቤቱ አስፈላጊውን አስተዳደራዊ እንዲሁም የወንጀል እርምጃ ከመውሰድ ወደኋላ የማይል በመሆኑ ስፖርተኛው በመደበኛ ጥንቃቄው መቀጠል እንዳለበት ዳይሬክተሩ አስቀምጠዋል።አዲስ ዘመን ግንቦት 10/2012ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "01f73fe2dd71eb57e86861f0d6e6addf" }, { "passage": "ብርሃን ፈይሳበኢትዮጵያ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በስፖርቱ ልዩ ትኩረት ከተሰጣቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ የታዳጊ ወጣቶች ስልጠና ነው። በፕሮጀክቶች የተለዩ ሰልጣኞችን ተቀብለው ወደ ተተኪና ውጤታማ ስፖርተኞች በማሳደግ ረገድም የኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ እና የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የአትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከላት ተጠቃሽ ናቸው። በአትሌቲክስ ስፖርት ውጤታማዋ አትሌት የተሰየመውና በስፖርቱ በርካቶችን ያፈራው አሰላ ከተማ የሚገኘው የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የአትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ሀገር የሚያስጠሩ አትሌቶችን በማፍራት የኢትዮጵያን ዝና ያስቀጥላል በሚል ተስፋ የተጣለበት ነው። ይህ ማዕከል ከወቅታዊው ሁኔታ ጋር ተያይዞ ያለበት ሁኔታ ምን እንደሚመስል የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አመንሲሳ ከበደ ያብራራሉ።የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ተከትሎ ሰልጣኞች ወደየቤተሰቦቻቸው እንዲመለሱ ከተደረገ በኋላ አቋማቸው እንዳይወርድ በርካታ ስራዎች ሲከናወኑ እንደቆዩ ዳይሬክተሩ ይገልጻሉ። ከእነዚህም መካከል አንዱ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ስልጠናውን መቀጠል መሆኑን ጠቅሰው፣ሌላኛው ደግሞ አሰልጣኞች በየክልሉ ወዳሉት ሰልጣኞች በመጓዝ ያሉበትን ሁኔታ ለሁለት ጊዜያት መመልከትና ምክረ ሃሳቦችንም መስጠት ነበር ይላሉ።እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ፤ ማዕከሉ ለአካባቢው ነዋሪ ኳራንታይን ሆኖ ሲያገለግል ቆይቷል፤ ከጥቂት ወራት ወዲህ ግን ለሰልጣኞቹ ጥሪ በማድረግ ሙሉ ለሙሉ ወደ ስልጠናው ተመልሷል። በዚህ ወቅትም ከ200 በላይ የሚሆኑ ሰልጣኞች ምርመራ አድርገው ማዕከሉን እንዲቀላቀሉ በማድረግ በቅርቡ በተካሄደው የኢትዮጵያ አጭር ርቀት የሜዳ ተግባራትና እርምጃ ቻምፒዮና ላይ ጥቂት አትሌቶችን ማሳተፍ ተችሏል። የእግር ኳስ ቡድኑም በተመሳሳይ በፕሪምየር ሊጉ ሰባት ጨዋታዎችን እስካሁን ማድረጉን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።የሰልጣኞች ስፖርታዊ እንቅስቃሴ አካላዊ ንክኪንና የትንፋሽ መለዋወጥን ሊፈጥር እንደሚችል ጠቅሰው፣በዚህ ላይ ሰልጣኞች በካምፕ የሚኖሩ መሆናቸው ወረርሽኙ በማእከሉ የስልጠና ሂደት ላይ ከፍተኛ ጫና ማድረሱን ዳይሬክተሩ ያብራራሉ።እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ፤ ሰልጣኞች በወረርሽኙ ሳቢያ ወደየቤተሰቦቻቸው በተመለሱበት ወቅት ከስልጠናው ጋር ተመጣጣኝ የሆነ የምግብ አገልግሎትና ድጋፍ ማግኘትም አልቻሉም። ወደ ማዕከሉ ከተመለሱም በኋላ በአንድ አሰባስቦ ማሰራት አለመቻልና ዓለም አቀፍ ውድድሮች የተቋረጡበት ሁኔታ በማጋጠሙ የአትሌቶችን ብቃት መመዘን አልተቻለም፤ይህም ወጣት አትሌቶች የሚታዩበትን እድል አዳጋች አድርጎታል። በዚህ ምክንያትም ሰልጣኞች በየጊዜው ምርመራ የሚያደርጉ ሲሆን፤ ስልጠናውን እንደቀድሞው በቡድን ከማካሄድ ይልቅ በግል እንዲሰጣቸው ሆኗል። በአትሌቲክስ ስፖርት በጋራ ልምምድ መስራት ያለው ጥቅም የሚታወቅ ሆኖ ሳለ፣ በቫይረሱ ስጋት ሳቢያ የስልጠና ዘይቤው መቀየር በሰልጣኞች ላይ ውስንነትን አስከትሏል። በማዕከሉ በጀት ላይ የሚያመጣው ተጽእኖም ይኖራል።በአሁኑ ወቅት ማዕከሉ በአጠቃላይ 300 ሰልጣኞች ሊኖሩት እንደሚገባ ጠቅሰው፣ 200 ለሚሆኑት ብቻ ጥሪ በማድረግ አንድ የመኖሪያ ክፍል ለአንድ ሰልጣኝ እንዲሰጥ ተደርጓል ይላሉ። የተቀሩት ደግሞ በርቀት (በቴክኖሎጂ እገዛ) ስልጠናቸውን ቀጥለዋል ይላሉ። በቀጣይ ወደ ማዕከሉ እንዲገቡም ክፍሎችን የማደራጀት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ዳይሬክተሩ ይጠቁማሉ። እንደ ዳይሬክተሩ ማብራሪያ፤ማዕከሉ በ350 ሚሊየን ብር ወጪ ነው የተገነባው።በሃገሪቷ ከኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ ቀጥሎ በዚህ ደረጃ የተደራጀ የስልጠና ማዕከል የአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ብቻ ነው። ያሉትን የስፖርትና የስልጠና ቁሳቁስ ወደ መሬት አውርዶ ስኬታማ አትሌቶች ከማፍራት አኳያ ጥቂት የሚቀረው ቢሆንም፣ ባለበት ደረጃም ቢሆን ሁኔታው ምቹ የሚባል ማእከል ነው። ከሃገሪቷ ነባራዊ ሁኔታ አኳያ ሁለት መሞችን በአንድ የማሰልጠኛ ማዕከል ማግኘት ለስልጠና ምቹ የሚያስብል ነው። አሁን ባለበት ሁኔታ 800 የሚሆኑ ሰልጣኞችን የመቀበል አቅም ቢኖረውም፣ በስልጠና ላይ ያሉት ከግማሽም ያነሱና ማስተናገድ ከሚችለው በታች ነው። ዶክተር አመንሲሳ ቀጣዩ ስራ የሚቀበላቸውን ሰልጠኞች ብዛት ማሳደግና ስልጠናውንም በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ እንዲሆን ማድረግ እንዲሁም የጥናትና ምርምር ስራ ማደራጀትን እንደሚጠይቅ ይጠቁማሉ። ስልጠናው በምርምር የታገዘና ሳይንሳዊ መሆን አለበት ሲሉም ተናግረው፣ አሁን ላይ ክፍተቶች እንዳሉ ነው የሚናገሩት። ሃገራዊ የስፖርት ፍኖተ ካርታውም የሚያስገነዝበው ይህንኑ ነው ይላሉ። አሰልጣኝነት የተለያዩ ሙያዎች ስብጥርና የቡድን ስራ ቢሆንም አሁን ያለው ሁኔታ ግን አንድ አሰልጣኝ በርካታ ሰልጣኞችን የሚያሰለጥንበት ነው ያሉት ዶክተር አመንሲሳ፣የስፖርት ስነልቦና፣ ህክምና፣ እና ሌሎች በተጓዳኝ ሊሰሩ የሚገባቸው የአሰልጣኞች የጋራ ስራ መሆኑን ያመለክታሉ።እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ፤ አንድ አሰልጣኝ በርካታ ሰልጣኞችን በሳምንት እስከ 16 ሰዓት እያሰለጠነ ይገኛል። ስልጠናውም በአንድ አሰልጣኝ ብቻ መቃኘቱ ውጤታማ ሊያደርገው አይችልም። ለዚህ አንዱ ምክንያት በሃገሪቷ ያለው ሙያዊ የስብጥር ሁኔታ ሲሆን፣ ሌላው ግን በገበያ ላይ የሰለጠነ ሰው ኃይል ማግኘት አለመቻል ነው። ለአብነት ያህልም በስፖርት ስነልቦና፣ ቴኳንዶ፣ ቦክስ እና ቅርጫት ኳስ አሰልጣኝነት ስልጠና እንደ ሀገር በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እየተሰጠ አይደለም። ከዓመታት በፊት ከ10 በላይ የሚሆኑ የትምህርት ፕሮግራሞች በኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴርና ስፖርት ኮሚሽን የተቀረጹ ቢሆንም ወደ መሬት ግን መውረድ አልቻሉም። ይህም የሚያሳየው በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ የሙያ መስኮች መኖራቸውን ነው ያሉት ዳይሬክተሩ፣ የሚመለከታቸው አካላትም በዚህ ላይ ሊሰሩ እንደሚገባም ያሳስባሉ።አዲስ ዘመን\nጥር 13/2013", "passage_id": "f5f70a55d228be92f7fa587a5e68ebed" }, { "passage": "የስፖርት ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው በእጅጉ እየጨመረ እንደመጣ ይታወቃል። የዓለም አገራት የስፖርት ሴክተሩን ዘርፈ ብዙ ፋይዳ በመረዳት ብቻ የሚቆሙ እንዳልሆኑ በዘርፉ ያስመዘገቡት ውጤት ማሳያ ነው። በዓለማችን በበርካታ አገራት ከሌሎች ሴክተሮች ባልተናነሰ መልኩ ለስፖርት ልማቱ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይን በማፍሰስ ስማቸውን በዓለም አቀፍ መድረክ ከፍ ብሎ እንዲጠራ ከማድረግ አልፈው ብዙ ማትረፍ ችለዋል፡፡ ለስፖርት ሴክተሩ ትልቅ ትኩረት መስጠት በማህበራዊ ፋይዳው አምራችና ጤናማ ዜጋን በማፍራት\nረገድ ያለውን ውጤት ከመረዳት ይመነጫል። በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚካሄዱ ትላልቅ ውድድሮች በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ከሚገኘው ድል ጀርባ\nለአገር ፖለቲካዊ ትርፍ ማጣጣም ማስቻሉንም መታዘብ ይቻላል፡፡ ስፖርተኞች ከውድድር ድል በኋላ የሚያገኙት ረብጣ የሽልማት ገንዘብና\nየአገር ኢኮኖሚን በማንቀሳቀስ የሚገኘው ትርፍም ቀላል አይደለም፡፡ የስፖርቱን ዘርፈ ብዙ ፋይዳን በጥልቅ በመረዳት የስኬት ማማ\nላይ የወጡ እንደ ጀርመን ያሉ አገራትን ማንሳት ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ለስፖርት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ረገድ ጀርመን\nበግንባር ቀደምነት ተጠቃሽ ናት። ይህች አገር ስፖርቱ በጠንካራ የፋይናንስ መሠረት ላይ ማቆም መቻሏ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ መሠረቱን\nሳይለቅ መጓዝ የቻለ አደረጃጀት መፍጠሯ ለስኬቷ ምክንያት ተደርጎ ይነሳል፡፡ የጀርመን መንግሥት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ከሚያፈስባቸው\nዘርፎች ዋነኛው ስፖርት ሊሆን የቻለውም ለዚህ ነው፡፡ ስፖርት በጀርመን ኢኮኖሚ ውስጥ 2 ነጥብ 2 በመቶ ድርሻ ይይዛል። ስፖርቱን በፋይናንስ\nአቅም እንዲጎለብት ከማድረግ በተጓዳኝ፤ ጠንካራ አደረጃጀት የተዘረጋለት ነው። በጀርመን የስፖርት ዘርፍ ይህን መልክ መላበሱ ከዘርፉ\nየሚገኘው ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ፋይዳ እንዲጎላ ማድረጉ ይነሳል። በኢትዮጵያ ለስፖርቱ ዘርፍ የተሰጠውን ትኩረትና ውጤት\nከሌሎች አገራት አንጻር እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡ በቀደሙት ጥቂት ዓመታት ለስፖርቱ ቅርብ ከሆኑ ሰዎች፣ ከመንግሥትና ከሌሎች\nባለድርሻ አካላት በኩል ኢትዮጵያ ለስፖርቱ ዘርፍ ተገቢ ትኩረት መስጠቷ ይነገራል፡፡ ለስፖርት ዘርፍ በተገቢው ደረጃ ትኩረት ተሰጥቶት\nእየተሰራ አለመሆኑንና የዘርፉ እድገት በቁልቁለት ጉዞ ውስጥ መሆኑም በሌላ ወገን ይነሳል። የስፖርት ሴክተሩ ውጤት አልባ መሆኑ\nግን ሁለቱንም ወገኖች እንደሚያስማማ ለመታዘብ ይቻላል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህም በመንግሥት ደረጃ ይኸው እውነታ ታምኖበት እየተሰራ\nስለመሆኑ በተደጋጋሚ እየተነገረ ይገኛል። በኢፌዴሪ ስፖርት\nኮሚሽን የዕቅድ በጀት ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እንድሪስ አብዱ፤ በአገሪቱ ባለፉት ሁለት የዕድገትና\nትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመናት ዘርፉ ለአገሪቱ ማበርከት ካለበት ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጠቀሜታዎች አንፃር በሚፈለገው\nደረጃ ላይ አለመገኘቱና ውጤቱም በመላ አገሪቱ ተደራሽነት ላይ ክፍተቶች መኖራቸው እንደታመነበት ይናገራሉ:: ለዚህም የስፖርት ሴክተሩን\nመሠረታዊ ችግር በተረዳ መልኩ የ10 ዓመት የስፖርት ሴክተር ስትራቴጂክ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እንዲሆን በኮሚሽኑ በኩል እንቅስቃሴ\nከተጀመረ መሰንበቱን ያስረዳሉ፡፡ ስፖርቱን ወደፊት\nለማራመድ እንቅፋት ከሆኑ መሠረታዊ ምክንያቶች መካከል በዋነኛነት ከአደረ ጃጀት፣ ከፋይናንስ፣ ከሰው ኃይል ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮች\nመሆናቸውን የጠቆሙት የኮሚሽኑ ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ምክትል ዳይሬክተር አቶ እንየው አሊ፤ የ10 ዓመቱ ስትራቴጂክ እቅድ የተጠቀሱትን\nክፍተቶች በጥናት እንዲመልስ ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑን ያስቀምጣሉ፡፡ ስትራቴጂክ ዕቅዱ አገራዊ የስፖርት ሪፎርምን መነሻ በማድረግ\nበስፋት የተዘጋጀ መሆኑንም ይገልፃሉ። በመሆኑም በአገሪቷ ቀጣይ የስፖርት እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ለውጥና ውጤት ማምጣት እንደሚያስችል\nታምኖበታል፡፡ የስፖርት ሴክተሩ ሪፎርም ፕሮግራም ዘርፍን መለወጥ የሚችሉ ብዙ ያመላከታቸው ነጥቦች እንዳሉም ያስረዳሉ። በዚህም\nከአደረጃጀት ፣ ከፋይናንስ፣ ከሰው ኃይልና ሌሎችም ጉዳዮች አንፃር ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት እንደሚቻል ተስፋ የተጣለበት መሆኑን\nይጠቅሳሉ፡፡ በሪፎርሙ ላይ የሴክተሩ ችግሮች የተለዩ ሲሆን በተመሳሳይ መፍትሄዎች መመላከታቸውንም ያክላሉ። ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ\nተግባራዊ የሚደረገውና ከስፖርት ሪፎርሙ የሚቀዳው የ10 ዓመቱ ስትራቴጂክ እቅድ ዘርፍን የተሻለ እንደሚያደርገውም ያላቸውን እምነት\nይገልፃሉ፡፡ አቶ እንድሪስ በበኩላቸው፤\nበቀጣይ ዓመት ተግባራዊ የሚደረገው ስትራቴጂክ ዕቅድ ትኩረት ያደረጋቸው አንኳር ጉዳዮች መኖራቸውን በመጥቀስ በሴክተሩ በቀጣይ\n10 ዓመታት በትኩረት የሚሰራባቸው ተብለው የቀረቡት ቁልፍ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች እንዳሉ ይናገራሉ:: በመጀመሪያ መንግሥታዊ የስፖርት\nአደረጃጀቶችን የመፈፀም እና የማስፈፀም አቅም በማጎልበት፤ የተለያዩ የሕግ ማዕቀፎችን እና የአሠራር ሥርዓቶችን ተግባር ላይ ማዋል\n፤ ሕዝባዊ የስፖርት አደረጃጀቶችን በዓለም አቀፍ እና በአገር አቀፍ መስፈርቶች መሠረት ማደራጀት የስትራቴጂክ እቅዱ ትኩረት መሆናቸውን\nያስቀምጣሉ:: በሁለተኛ ደረጃ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የማሰልጠኛ ማዕከላት ተደራሽነት፣ ሕጋዊነት እና ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን\nመሠረት በማድረግ በጥራት የሚገነቡበትን ስልት ሥራ ላይ ማዋል ትኩረት የሚሰጠው መሆኑን ያስረዳሉ። በአህጉር እና ዓለም አቀፍ የውድድር\nመድረኮች በተፈጥሮ ብቃታቸውን መሠረት በማድረግ አገራችንን የሚወክሉ እና ውጤታማ የሆኑ ተተኪ ስፖርተኞችን በሳይንሳዊ ስልጠናዎች\nማፍራት ትኩረት ተደርጎ የሚሰራበት ጉዳይ መሆኑንም ያብራራሉ፡፡ ስፖርት ለማህበራዊ ልማትና ለአገር ብልፅግና ፣ ለሕዝቦች መቀራረብ\n፣ ለገፅታ ግንባታ እና ለቱሪዝም ዕድገት መሣሪያ ሆኖ እንዲያገለግል ትኩረት ሰጥቶ መስራትም የስትራቴጂክ እቅዱ ቁልፍ ጉዳዮች ናቸው።\nበስትራቴጂክ ዕቅዱ የተጠቀሱትን አንኳር ጉዳዮች መሠረት አድርጎ የተዘጋጀው ግብ ወደ ተግባር መቀየር ከተቻለም የስፖርት ሴክተሩ\nውጤታማ መሆን እንደሚችል እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡የባህልና ቱሪዝም\nሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሀብታሙ ሲሳይ፤ በአገር አቀፍ የስፖርት ፖሊሲ ባለፉት ሁለት አስር ዓመታት የተመዘገቡ በርካታ አበረታች\nውጤቶች ቢኖሩም የአገራችን የስፖርት ዕድገት ከዕድሜው አኳያ ሲመዘን በሚፈለገው ደረጃ ባለማደጉ ብዙ መስራት እንደሚጠበቅ ያመላክታሉ።\nበአሁኑ ወቅት መንግሥት ስፖርቱን እንደ አንድ የልማትና ብልፅግና መሣሪያ አድርጎ በመውሰድ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ እየሰራ እንደሚገኝ\nየሚናገሩት አቶ ሃብታሙ ፤ የስፖርት ዘርፍ በታሪኩ በዚህ ደረጃ ትኩረት ተሰጥቶት እንደማያውቅ ያብራራሉ:: የብሔራዊ የስፖርት ምክር\nቤት በኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ሰብሳቢነትና የበላይ ጠባቂነት መመራቱ መንግሥት ለስፖርቱ ሴክተር የሰጠውን\nትኩረት እንደሚያሳይም ያስቀምጣሉ፡፡ በመሆኑም የስፖርት ዘርፍን ከትናንት በተሻለ መልኩ ዛሬ ትኩረት በማግኘቱ ዕድሉን በአግባቡ\nበመጠቀም ጠንክሮ መስራት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል፡፡አዲስ ዘመን አርብ ጥር 22/2012ዳንኤል ዘነበ\n", "passage_id": "03113203decaadfcc71b27a06362f673" } ]
af6c94b5b4d8e45277d0153e069df19e
8cdd8aa019de0bceb700b83c93bd6f66
የጎደለን…
በአንድ ነገር አምናለሁ። ግራ በገባው ዓለም ላይ አብዛኞቻችን የጎደለን ‹‹ትእግስት›› ነው። ይሄ እኔ የማምንበት ሀቅ ነው። ትእግስት በቀጥታ ከእምነታችን ጋር እንደሚያያዝም አውቃለሁ። ይህ ጉዳይ አንድ ነገር ያስታውሰኛል። አሁን በሕይወት የሌለው አያቴን። ምድር ላይ ያሉ እንቅፋቶችንና መሰናክሎችን በሙሉ አይኔ ማየት እንዲችል አይኔን የገለጠልኝ መሪዬ። የሕይወት መመሪያ ቁልፉን ያቀበለኝ ይህ ታላቅ ሰው በአንድ የተባረከ ቀን የእምነት እና የትግስት ሃያል ቁርኝትን ሊያሳየኝ ቻለ። እምነት ‹‹የማይታየውን ማየት መቻል ሲሆን›› ትእግስት ደግሞ ‹‹በልቦና ያዩትን እውነት እስኪገለጥ የመጠበቅ ሃይል›› እንደሆነ ገለጠልኝ። የበጋው ወር ሲገባደድ ሰማይ የመሬት ንቃቃትን ለመድፈን ‹‹በሕይወት ውሀ›› ምድርን ሲያረሰርስ፤ በእናቴ ግፊት ሁሌም አያቴን ለመጠየቅ ወደ ገጠሩ ክፍል የመሄድ ልምድ አለኝ። ከመኪና ጥሩንባ ጩኸት፤ ከአርማታ ጫካ ተላቅቄ ትክክለኛው የሕይወት ኡደት ከሚከወንባት ውብ የተፈጥሮ ክፍል ጋር የምገናኘው ያን ጊዜ ነበር። ይህ ስሜት ውስጤ እንደቀረ የማስታውሰው አሁን ላይ መለስ ብዬ ለማስተዋል ስሞክር ትዝታው ሲጎሻሽመኝ ነው። ታዲያ ማስተዋል በጎደለው የልጅነት ጊዜዬ ላይ ለአያቴ ቀለል ያሉ ለእኔ ግን ፈታኝ የሆኑ ጥያቄዎችን አከታትልበት ነበር። በአንዱ የክረምት ወቅት እንዲህ ሆነ። አያቴ በጠዋቱ ከመኝታዬ አስነስቶ እርስቱ ወደሆነው ወደ አንድ ሰፊ ሜዳማ ስፍራ ይዞኝ ሄደ። ብቻችንን አልነበርንም። ነገ ዋርካ የሚሆኑ፤ ዛሬ ግን ፍሬ የሚሆኑ በርካታ የዘር ፍሬዎችን ይዞ ነበር። ችግኝ ሆነው ነገ ዛፍ የሚሆኑ። እንደዛሬው ግን የፖለቲካ ትርፍ የሌላቸው የተፈጥሮ ማድመቂያ እፅዋቶች። ሁሌም ይህን የማድረግ ልምድ ቢኖረውን ከእኔ ጋር ግን በዚህ መልክ ፍሬን ከአፈር አዋህደን አናውቅም ነበር። እንዲያው ዘርን ለመበተን ብቻም ወደ ስፍራው እንዳልወሰደኝ ቆየት ብሎ ነበር የገባኝ። በእኔ ለጋና በእርሱ የሰከነ እእምሮ ውስጥ በርካታ ጉዳዮች እየተብሰለሰሉ ፍሬውን ከአፈሩ ጋር አቀላቀልን። በጊዜው ከአያቴ ጋር የነበረኝ ቆይታ አስደሳች ነበር። የዘር ፍሬን ከመሬት ማዋሃድ የሚሰጠው ደስታ ልዩ ነበር። እውነት ለመናገር ደግሞ ከሁሉም በላይ ያጓጓኝ የተከልናቸው ፍሬዎች ከምድር ከርስ ውስጥ እየተፈለቀቁ ሲወጡ ማየት ነበር። ተከላውን ጨርሰን ወደ ቤታችን ተመለስን። እኔ ተመለስኩ ከምል ግን በድኔ ተመለሰ ብል ይቀለኛል። ምክንያቱም ሀሳቤ የነበረው የተከልናቸው ፍሬዎች ላይ ነበር። እንዴት እና መቼ ይበቅሉ ይሆን? ያስጨነቀኝ ጥያቄ ነበር። ከሁለት ሰዓት ቆይታ በኋላ አያቴን ትቼ የተከልናቸው ፍሬዎች ወደሚገኙበት ስፍራ አቀናሁ። ከሜዳው ለመድረስ ልቤ እስኪፈርስ መሮጤን አስታውሳለሁ። በቦታው ስደርስ ግን ከእኔና አያቴ የእግር ጫማ ምልክት፤ ተቆፍረው አፈር ከለበሱ ጉድጓዶች ውጪ ምንም መመልከት አልቻልኩም። ልፋታችን መና የቀረ መሰለኝ። ምንም አረንጓዴ ነገር አልታይህ አለኝ። ተስፋ ቆረጥኩ። ‹‹በቃ የተከልናቸው ፍሬዎቹ አልበቀሉም›› ብዬ ተከዝኩ። ከአንዱ ጉድጓድ ውስጥ አፈር የለበሰውን ፍሬ አውጥቼ ከፀሐይ ትይዩ ካደረኩት በኋላ አንጋጥጬ አየሁት ምንም የበቀለ ነገር አይታየኝም። መልሼ ወደ ጉድጓዱ ተክዬው ወደ ቤት ተመለስኩ። አያቴ ፊቱን ወደ መግቢያው በር አዙሮ፤ ጀርባውን ለጠዋት ፀሐይ ሰጥቶ፤ ኩታውን ደርቦ ከበረንዳው ላይ መጽሐፉን ይኮመኩማል። ልጅ ሆኜ ‹‹ኢትዮጵያ›› እሱን ትመስለኝ ነበር። እውነትም ተፈጥሮን የተረዳ፣ ወግ ባህሉን የጠበቀ ኩሩ ኢትዮጵያዊ ነበር። እንባ ያቀረሩ አይኖቼን ከፊቱ አቅርቤ ‹‹አባባ የተከልናቸው ዛፎች አልበቀሉም። ደርቀዋል›› አልኩት። ቀና ብሎ ሲያየኝ እንባዬን ዘረገፍኩት። አባባ የልጅነት ጭንቀቴን እና ጉጉቴን በተረዳ አንደበት ፈገግ እያለ፤ እንባዬን ከጉንጬ ላይ በመዳፉ እየጠረገ ‹‹ልጄ አትቸኩል። ሂደቱን ለተፈጥሮ ተውላት። ችግኞቹ ይበቅላሉ። ከኛ የሚጠበቀውን አድርገናል። አሁን ተራው የተፈጥሮ ነው›› በማለት ጊዜው ገና መሆኑን ነገረኝ። ‹‹በጥረትህ እምነት ይኑርህ የተከልከው ፍሬ እንደሚበቅል እመን›› ሲልም በውብ አንደበቶቹ አስረዳኝ። ከሳምንት በኋላ አያቴ እንደተለመደው በጠዋት ቀስቅሶ ችግኞቹን ወደተከልንበት ስፍራ ይዞኝ ሄደ። በልጅነት አዕምሮዬ በጊዜው የተመለከትኩት ነገር አስደሳች ነበር። ችግኞቹ አናታቸውን ከቀበረው አፈር ፈልቅቀው አውጥተው ስፍራውን በአረንጓዴ ቀለም ሞልተውታል። ደስ የሚል ትእይንት ነበር። አያቴ ቀጠለ ‹‹አየህ ልጄ ፍሬው ቅጠል ለመሆን የሳምንት ጊዜ ፈጅቶበታል። በሕይወት ውስጥ እንዲሁ ጊዜ የሚፈልጉ በርካታ ጉዳዮች አሉ። ያንተ ድርሻ ሂደቱን ማመን እና የድርሻህን መወጣት ነው። ከዚያ ውጤቱ እስኪመጣ በትእግስት መጠበቅ›› በማለት የሕይወት ክህሎትን አስተማረኝ። በአያቴ አጭር ቋንቋ ሂደቱን ማመን ‹‹ትእግስት›› ማለት ነው። የዘራነውን እንደምናጭድ በልቦናችን ማወቅ ደግሞ ‹‹እምነት››። ለካ አያቴ ሁሌም ያለቦታው ፈጠን ፈጠን ሲሉበት የማይወደው እና ‹‹የጅብ ችኩል ቀንድ ይነክሳል›› እያለ የሚተርተው ወዶ አይደለም። ይሄ የገባኝ ከላይ ያጫወትኳችሁ የችግኙ ጉዳይ ዓመት ከሞላው በኋላ ነበር። ከወዲያኛው ማዶ ስልክ አቃጨለ። አያቴ ነበር ለእናቴ የደወለው። ጥቂት ተጨዋውተው መነጋገሪያውን ለኔ አቀበለችኝ። በስልኩ ውስጥ እንዲህ የሚል ድምፅ ሰማሁ ‹‹ልጄ የተከልናቸው ችግኞች አድገው ትልልቆች ሆነዋል ስታያቸው እንደምትደሰት እርግጠኛ ነኝ››። አያቴ ይህን ሲለኝ ከዓመት በፊት ከጉድጓድ አውጥቼ አንጋጥጬ መብቀል አለመብቀሏን የተመለከትኳትን ፍሬ አስታውሼ ለራሴ ፈገግ አልኩ። ዛሬስ? ጊዜው አልፎ ዓመታት ቢነጉድም የእኔም ሆነ የማህበረሰባችን መሠረታዊ ችግር የትእግስት እና የእምነት ማጣት ነው። የተፈጥሮን ኡደት አለመከተል። በመቸኮላችን ከስጋው ይልቅ ቀንድ መንከስ። ማወቅ ያቃተን አንድ ጉዳይ አለ። የምንተክለው መጥፎም ሆነ ጥሩ ፍሬ ጊዜውን ጠብቆ መብቀሉ እንደማይቀር ማመን አልቻልንም። ሂደቱን አልጠበቅንም! መልካም ፍሬዎች በአንድ ጊዜ አይበቅሉም። የክፋት ፍሬዎችም እንዲሁ። ስኬታማ ሰዎች አይን ባወጣ ሌብነት ካልሆነ በቀር በአንድ ሌሊት ሀብት አያከማቹም። እውቅናም ሆነ እውቀት በአንድ ምሽት አይገኙም። የእኔና የአብዛኛዎቻችን ችግር ይህ ነው። ስኬትም ሆነ ውድቀት በአንድ ቀን ጥረት የሚመጡ ይመስለናል። መች ይሄ ብቻ ሆነ። ዛሬ የስኬት ፍሬ ዘርተን ነገ በቅሎ ማየት እንሻለን። የተፈጥሮን ኡደት መጠበቅ አቅቶን የዘራነውን እየነቀልን በትእግስት ማጣት ወጥመድ ውስጥ እንወድቃለን። ጎጠኞች የዘሩት የክፋት መንገድ በአንድ ምሽት እንደ አረም ተነቅሎ ካልተጣለ ብለን በድብርት ማቅ ውስጥ እንወድቃለን። እምነት እናጣለን። ለዘመናት የበቀለው መልካም የአንድነት ፍሬ በዓመታት የአረም ዳዋ የሚለብስና የሚነቀል ይመስለናል። ፍርሃት ውስጥ እንዘፈቃለን። ማስተዋል አቅቶን ለአያቶቻችን ጆሮ ነፍገን። ሀሳቤን ይህን ጠይቄ ልደምድም። ‹‹ትእግስታችን እስከምን ድረስ ነው?›› በተለይ ደግሞ የማህበራዊ ድረ ገፅ ልክፍት ላይ የወደቅነው ወጣቶች። ዛሬ አስበን ውጤቱ ለነገ የምንጠብቅ። ቀንድ ነካሾች። በአንድ ሌሊት አገር የሚገነባ፤ በንጋታው አገር የሚፈርስ የሚመስለን። በአንድ ወቅት ግርግር በማንነታችን፣ በቤተሰባችን፣በጓደኛችን፣ በአገራችን ፣በሥራችን ፣በጥረታችን እምነት ያጣን። ‹‹የጅብ ችኩሎች፤ ቀንድ ነካሾች›› በተፈጥሮ ሂደት ‹‹ለምን እምነት፤ ለምን ትእግስት አጣን?››!! ሰላምአዲስ ዘመን  ጥር 10/2012ዳግም ከበደ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=25859
[ { "passage": "መቼም ከክረምቱ መግባት ጋር ተያይዞ በርከት ያሉ በረከቶች አይጠፉም። ሁሌም ሰኔ ግም ባለ ቁጥር ብዙ የሚባሉ በጎ ነገሮችን ስናይ ቆይተናል። ማየትም ብቻ ሳይሆን እኛው ራሳችን ተሳትፈን ሌሎችንም ጭምር በማስከተል የድርሻችንን ተውጥተንም ሊሆን ይችላል። ወዳጆቼ! ይህን ጉዳይ ሳነሳላችሁ «ደግሞ ለበጎነት ምንስ ቢሆኑለት ምን አለበትና» ትሉ ይሆናል። እውነት ብላችኋል። ከበጎነት በላይ ምንም የለም። ሁሌም መልካምነትን የያዘ አዕምሮና ልቦና መልካም ፍሬን ለማፈስ የቀረበ ነውና ብዙ ቢባልለት የሚያንሰውና የሚያስገርም አይሆንም። ወደቀደመው ነገሬ ልመለስ። ወደ ክረምቱ በረከት። አዎ! ክረምት ሲታሰብ ሁሌም በረከት አይታጣም። በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አብዛኛውን የሀገሬ ሰው ከልቡ ተነሳስቶ በየቦታው፣ በየጉድባውና በየሸንተረሩ ችግኞችን መትከል ባህሉ እያደረገው ነው። ይህ ደግሞ አሁንም «እሰዬው» የሚያስብል ተሞክሮ ነው። አዎ! ዛሬም ይህን ለሚያደርጉ በጎ አሳቢዎች ሁሉ «በርቱልን ተበራቱልን» ማለትን አንተውም። አንዘነጋምም። ባሳለፍነው ሳምንት በጠቅላይ ሚኒስትራችን አሳሳቢነት መላውን ሀገር ለችግኝ ተከላ የሚያነሳሳ ዘመቻ ተካሂዷል። ይህ ደግሞ ብዙዎችን ለመልካምነት የሚያበረታ ነውና «እሰይ! ይሁን» ከማለት የበለጠ መልካም የሚባል አርአያነቱን ያጎላዋል። ልክ እንዳለፉት ወራት የጽዳት ዘመቻ ሁሉ በመሪ የተመራው የችግኝ ተከላም ውጤታማ የሚባልና የተለየ ሙቀት የነበረው ሆኖ ሰንብቷል። ወዳጆቼ! እስከዛሬም ቢሆን እኮ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሀገር በቀል ችግኞችን በዘመቻ ተክለናል። በተለየ ወኔ ተነስተንም አላማውን አድንቀንና ብዙ ተባብለን ከስምምነት ደርሰናል። ይህ ስምምነት ደግሞ ችግኙ ሞቃታማው አየር ለውጥ፣ ለውሃ መገኛ፣ ለበርሃማነት መቀነሻና ለደን ሀብታችን መጠበቂያ ጭምር መሆኑን አመላክቶናል። ተደጋግሞ ሲነገር እንደምንሰማውና እኛም ሁልጊዜ እንደምንመሰክረው ችግኝ የመትከልን አስፈላጊነት የምንዘነጋው አይደለም። እንዲያውም በአንዳንዶቻችን ተቋማት ዘንድ ይህን የችግኝ መትከያ ጊዜ የዓመቱ የመገናኛና የሠራተኞች ቀን አድርገን በተለየ ስሜት እናስበዋለን። በዚህ ቀን ችግኝ ከመትከል በዘለለ ቀናችንን ብሩህ በማድረግ የዓመቱን ልፋታችን በችግኝ መትከሉ ሰበብ አስውበነው እናልፋለን። «በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ» እንዲሉ የችግኝ ተከላ ቀናት በሌሎች ቁምነገሮች ጭምር ተዋዝቶ ማለፉ እየተለመደ ነው። ይህ መሆኑ ደግሞ አንድም ለአረንጓዴው ቀናችን ሌላም ለዓመቱ ልፋታችን የተለየ ትዝታና ጠቀሜታን አስጨብጦ ያልፋል። ይህ ሁሉ መሆኑ አሁንም ቢሆን «እሰዬው» የሚያስብልና የሚያበረታን ነው።ይህን ቀን አስቦ ደስታን ቢያጭሩና ቁምነገርን ቢገበዩም መልካምነቱን ያጎላል። ዕለቱን በተለየ ትዝታ አስቦም ለከርሞው አረንጓዴነት ቅርስና አሻራን ትቶ ማለፍ ያስችላል። ወዳጆቼ! ለእኔ ግን ይህ ብቻ መሆኑ በቂ ይሆናል አልልም። ችግኞችን መትከሉና አፈር አልብሶ መመለሱም ለተነሳንበት ዓላማ ግብ አይደለም፡፡ ጀምረነዋል ለምንለው የአረንጓዴማነት አካባቢ ማስፋት ማረጋገጫችን አይሆንም። በየዓመቱ ችግኞችን ለመትከል ቦታ መምረጡና አገር ቆርጦ መጓዙም በቂ የሚባል አይሆንም። አሁን ደግሞ እጆቻችንን በእርጥብ አፈር ለውሰን ችግኝ ተክለን መጣን የምንልበት ብቻ አይደለም። እንደዋዛ ከመሬት አገናኝተን በርቀት የምንለያቸው ችግኞችም ታሪካችንና የድርሻችን አሻራ እንዳሳረፍን የምንመካበት ሆኖ ሊሰማንም አይገባም። እውነት ነው! ሁሌም ችግኞችን ከመትከል በዘለለ የተከልናቸው እጽዋት የት ደረሱ ልንል ይገባል። አዎ! ርቀት ተጉዘንና በእግራችን ኳትነን የተከልናቸው የምንላቸውን አሻራዎች በዓመቱ ተመልሰን ስንመጣ ሕይወት ዘርተው፣ በቁመታቸው አድገውና በቅጠላቸው ለምልመው እንደምናገኛቸው እርግጠኞች ልንሆን ይገባል። ይህ ካልሆነ ግን በየዓመቱ ተዘጋጅተው በሚጠብቁን ጉድጓዶች ላይ እንደዋዛ ተከል አድርገን የምንመለሰውን ችግኝ አጸደቅን ለማለት ይቸግረናል። ሁሌም ቢሆን ችግኞቹ ማደግና መብቀላቸውን ካላወቅን ለእኛ በስፍራው ደርሶ አፈር መቆፈሩ ብቻ ምንም ትርጉም አይኖረውም። ለስሙ አደረግነው ብሎ መናገሩም ታሪክና ቅርስ አይሆንም። እንዲህ ማድረግም ለማንም አይበጅም። ችግኞችን በየዓመቱ እየተከሉ የት መድረሳቸውን ያለማወቅ በእኔ ግምትና እሳቤ ወልዶ እንደመጣል ይቆጠራል። ልክ ተወልዶ በአባቱ እንደተካደ፣ አልያም ደግሞ ባልተገባ ግንዛቤና ጭካኔ ከመንገድ እንደተጣለ ጨቅላ ሕፃን ዓይነት። አበቃሁ!አዲስ ዘመን ሰኔ 12/2011 ", "passage_id": "da886cab6b7e2ba0fd1ed12ad6d39a27" }, { "passage": "አንዱ በሌላው ላይ፣ ወገን በወገኑ ላይ ፈጸመ የሚባለውን ጉድና ደባ ሰምቶ ዝም ማለት አልሆንላት ብሎ፤ እውነቷን ነው ማንስ ቢሆን እንዴት ዝም ይላል። ተለጉመው የነበሩ የስሜት ሕዋሳት ነጻነት በተቀዳጁበት ዘመን ላይ ነው የምንገኘዋ። ‹‹የማሰብ ነጻነት፣ የመናገር ነጻነት፣ የመሰብሰብ ነጻነት፣ የመጻፍ ነጻነት….ወዘተ›› አንደኛ ዓመት ክብረ በዓል ብንለውስ? እንደው ማን ይሙት! ልብ ብሎ ለተመለከተን ‹‹ከገመዱ አፈትልኮ የወጣ እንቦሳ›› መስለን አርፈነዋልሳ። በጨዋ ወግና ባህል ተኮትኩቶ ያደገ ኢትዮጵያዊ ሲናገርም ልክ አለው፤ ሲጽፍም ልክ አለው፤ ሲጠላም ልክ አለው፤ ኧረ ሲወድም ልክ አለው። እንዲህ እንደ አሁኑ ልካችን ልኩን ከማጣቱ በፊት ለሁሉም ነገር ከልክ በታች ነበረ አይደል እንዴ? ‹‹አንድ ሰው ነጻነት በሰጠኸው ቁጥር የበለጠ ኃላፊነት በትከሻው እንዳረፈ ይሰማዋል›› ብሎ የተናገረው ምሁር፣ ፈላስፋ፣ ተመራማሪ፣ ሳይንቲስት ማን ነበር? ብዬ ቀና አልኩና ከቅርብ ጓደኛዬ ምስክርነት ተማጸንኩ። እሱም ‹‹ባውቀው ምን አስደበቀኝ ብሎኝ እርፍ!›› ከት ከት ከት ብዬ ሳቅኩኝ። ትናንት የፕሬስ ነጻነትን ልክ ለማስረዘም ረጅም መዘዝ በራሳቸው ላይ ያስከተሉ ሰዎች ቁጥራቸው ቀላል አይደለም። ዛሬ ያስረዘሙትን ነጻነት ወርዱ ከቁመቱ ተስተካክሎ በልክ እንድናምርበት የማድረጉ ኃላፊነት ከእነሱ በላይ ባለቤት የት ይመጣለታል። ካልተመጠነ ለሌላው እንቅፋት መሆኑ የት ይቀራል። እያንዳንዱ ነገር ልክ ከሌለው ለእልክ ይዳርጋል ይላሉ አባቶች ሲመክሩ።መቼም ‹‹ወሬን ወሬ ያነሳዋልና›› የድሮው ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ሚኒስቴር በሕይወት እያለ ‹‹መብትና ግዴታውን ጠንቅቆ የተረዳ፣ የሕዝብ አገልጋይነት መንፈስ መላበስ›› የሚሉ ነገሮች መለጣጠፍ ያበዛ ነበር። እንደው በጥናት የተረጋገጠ ባይሆንም በርካታ ሰዎች ‹‹የአገልጋይነት ሳይሆን የአጎብዳጅነት መንፈስን የተላበሰ›› ሰራተኛ ነው የተፈጠረው ሲሉ ይደመጣሉ። ለዚህ መገለጫው ‹‹መረጃ የማግኘት መብት››ን ብቻ ማየቱ በቂ ማሳያ ነው ይላሉ። ሠራተኛው በራሱ ተማምኖ ሙያው የሆነውን ጉዳይ እንኳን መረጃ ሊሰጥህ አይደፍርም። በሥራው ተማምኖ ከመኖር ይልቅ አጎብድዶ መኖር ጥቅም እንደሚያስገኝ ይነገራል። ስለዚህ ‹‹የአገልጋይነት መንፈስ ተላብሷል›› ሳይሆን ‹‹ክፉ መንፈስ ተዋርሷል›› ቢባል የተሻለ ይሆናል። ያው እንደልብ መተንፈስ ተችሏል፤ በተነፈሱት ልክ ያውም በልጥ አድርጎ ማስተንፈስም ቀርቷል ብዬ ነው የተነፈስኩላችሁ። አለበለዚያማ የተነፈሱትን ትንፋሽ ያስቆጥር ነበር ያ የትናንቱ ክፉ ቀን። እርግጥ ነው ዶክተሩ የመረጃን ዋጋ አሳምረው ያውቃሉ። መረጃ የመሸጥ ጥበብንም ተክነውበታል። በመረጃ ነጻነት ግኡዝ አካሉ ውስጥም ነፍስ ሊዘሩበት እየጣሩ ነው። ከሥልጣን ዕድሜያቸው አኳያ የመገናኛ ብዙኃንና የመረጃ ነጻነትን ከቀብር አፋፍ ታድገውታል። ቁርጠኝነታቸውን አለማድነቅ አይቻልምና። ትናንት ሐሳብ በማፍለቃቸው፣ በመጻ ፋቸው፣ በመናገራቸው ለመከራ የተዳረጉ ወጣቶችና ጋዜጠኞች ብዙ ናቸው። ዛሬ በማጎሪያ ቤት የሉም። የተለየ ሐሳብ ይዞ መምጣት የሚያኮራ እንጂ የሚያሳፍር፣ የሚያሳስር መሆኑ ያከተመ ይመስላል። ዓለም እኛን የሚመለከትበት የተንሸዋረረ ዓይን ወደ መስተካከል ተጠግቷል። ይልቁ ንስ እኛ ራሳችንን የምናይበት ዓይን፣ እኛ ዜጎቻችንን የምንመዝንበት ሚዛን፣ የምናቀ ርብበት የሜትር ልክ መስተካከል ተስኖት እንደተንጋደደ ይሄው እያገዳደለ ቀጥሏል። የነጻነት ልኩን ማወቅ ተስኖን፣ የመናገር ወሰኑ ጠፍቶን ይሄው እርስ በርሳችን የሰላማችን ፀር ሆነናል። ገዳይ ወንድም፣ ሟች ወንድም፣ አፈናቃይ ወንድም፣ ተፈናቃይ ወንድም ሆኖ ቀጥሏል። ዕድሜ ለሚዲያ ነጻነት እንጂ የቀረርቶ፣ የፉከራና የሽለላ ጫካው በእጃችን ላይ ሆኗል፤ ፌስቡክ። ኢትዮጵያ ለረጅም ዘመናት ስሟን ጥላሸት ሲቀቡ የነበሩ ድርጊቶቿ በአንድ ዓመት ከስመዋል። በሰብዓዊ መብት አያያዝ፣ በሐሳብ ብዝሃነት ማስተናገድ፣ በሚዲያ ነጻነት አጠባበቅ ከፍተኛ ለውጥ መታየታቸውን አሁን ላይ መስካሪዎቹ እኛ አይደለንም። ሌሎቹን ለማሳመን የተመናመነ የሃሳብ ጥይት ከመፈለግ ተገላግለናል። ስለ እኛ የሰብዓዊ መብት አያያዛችን ላይ ‹‹እትፍ እትፍ ይልመድባችሁ›› የሚሉ መስካሪዎች ፍለጋ ከጫፍ ጫፍ መኳተንና ማሰልጠን ቀርቷል። አልሆን ሲልም ረብጣ ገንዘብ ለእጅ መንሻ በቀዳዳ ልኮ አፍ ማዘጋት ዛሬ የለም፤ አንዳንድ ያልጠራ ሁኔታ ግን ሊኖር ይችላል። ሆሆይ ጉድ እኮ ነው። አልሰማንም እንዳትሉ! ለሥራ ከምናውለው ገንዘብ በላይ ቆሻሻ አመላችንን አለያም ገመናችንን ለመሸፈን እንከፍል እንደነበር ከውስጥ አዋቂዎች ውስጡን ጠይቁ። እኛ ተንፍሰናል። የመገናኛ ብዙኃን አቅም በማቆጥቆጥ ላይ ነው። በዘርፉ የሚሰማሩ የሚዲያ ሰዎች በሙያዊ ሥነምግባር እንጂ በፖለቲካ ርዕዮት ዓለም የተሞረዱ መሆናቸው ታሪክ ሊሆኑ እየተቃረበ ይመስላል። የሚዲያ ተቋማት መጡልን እንጂ መጡብን በሚል መብቀላቸውን ለማክሰም በጎሪጥ የሚመለከት ባለሥልጣን የለም። ተወዳዳሪነት እንጂ አቋራጭ እርምጃዎች መጥበብ ጀምረዋል። የመንግሥትን ካዝና በማለብ ዕድሜያቸውን የሚያራዝሙ የግል ሚዲያ ጣቢያዎች ልሳናቸው (ደማቸው) ደርቋል። ሕዝብን ረስቶ የፓርቲን እስትንፋስ እየተከተሉ ማላዘን አሁን ላይ ሳንቲም አለመውለድ ላይ ለመድረስ እየተጠጉ ይመስላል። የሚዲያው ባለቤት ባለሥልጣን፣ ጋዜጠኛው ወፍዘራሽ አለያም የእህት ልጅ፣ ፈቃድ ሰጪው አጎት፣ ሸላሚው የሚስት ወንድም፣ የገንዘብ ምንጭ (ስፖንሰር) መንግሥት፣ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚስት ሆነው በሕዝብ ላብ ጅምላ ንግድ አሁን አይሰራ ይሆናል፤ ይህ በሩ እየጠበበ ነው። ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ስለህጸጻችን ምን ያወሩብን ይሆን? ምን ይናገሩብን ይሆን? እያሉ መርበትበት ታሪክ ሊሆን ተቃርቧል። ይልቁንስ የእኛ ሚዲያዎች አቀንቃኝ እነሱ አስወንጫፊ ሆነው አብረው በመዘመር ላይ ናቸው። ኢትዮጵያ እንዲህ የዓለምን ቀልብ ስባ የታየችበት አጋጣሚ ምናልባትም ከአድዋ ድል ቀጥሎ ሁለተኛው ሳይሆን አይቀርም። የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪዎች፣ የዓለም ጋዜጠኞች መብት ተሟጋቾች፣ አክቲቪስቶችና የዓለም ሚዲዎች በኢትዮጵያ መዲና በቅርቡ ይከትማሉ። እንደከዚህ በፊቱ የክስ አቤቱታ ለማሰማት አይምሰላችሁ።ልምድ ለመቅሰም እንጂ። የለውጡ የአንድ ዓመት ፍሬ የሩብ ምዕተ ዓመት ስብራትን መጠገን ችሏል። ኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙሃንና የመረጃ ነጻነት የዓለም የፕሬስ ቀን የዘንድሮ ተሞሻሪ ናት።ከዚህ በፊት በዘርፉ ደረጃ ደልዳዮች ከነበረችበት 150ኛ ደረጃ በአንድ ዓመት ውስጥ 40 ደረጃዎችን ማሻሻል ችላለች። እሰይ ሀገሬ። በዚህ ብቻ የሚወሰን አይምሰላችሁ። እየተውተረተረ ያለው የሚዲያዎቻችን አቅም መለወጥ ይኖርበታል። ጋዜጠኞቻችን ለሙያው ሥነምግባርና ለእውነት የሚቆሙ ብሎም ለህዝብ ጥቅም የሚፋለሙ ሊሆኑ ይገባል። ከግል ሚዲያ ተቋማት እስከ ሕዝብ ሚዲያዎች በጥቅም ትስስር የግለሰቦችን ሥም ለማጥፋት ዘመቻ ይውላሉ የሚሉ አሉባልታዎች ቢነሱም ከአሉባልታ አይዘሉም። በአጠቃላይ የፕሬስ ነጻነቱን በደስታ ስናከብር በምንጠቀምባቸው ሚዲያዎች በኩል የጥላቻ ንግግርን ከማስተላለፍ ብንቆጠብ ከእኛነታችን የሚቀነስ ነገር ይኖር ይሆን? ሁሉም ነገር ትናንትን ስቦ የእኛ ነገር አጃኢብ እንዳያሰኝ ስጋት አለኝ። ምክንያቱም ‹‹ሲለጉሙን እዳ ሲፈቱንም እዳ፣ ተቻችሎ መኖር አሁን ማንን ጎዳ›› እንዳለችው ሴትዮ እንዳይሆንብን ነዋ።አዲስ ዘመን ሚየዝያ 24/2011ሙሐመድ ሁሴን ", "passage_id": "9c3312e8ae66f77e8b451d5187507a91" }, { "passage": "ሰላም ሰዎች እንዴት ነን? መግቢያ ሳላበዛ ቀጥታ የሆነውን ልንገራችሁ! እንዲህ ነው፤ ለምን እንደሚወዷት አላውቅም? ይሯሯጡላታል፣ ይ ጣ\nሉ ላ ታ ል\n፣ ይ ጨ ቃ\nጨ ቁ ላ ታ\nል ፣ ይቧቀሱላታል። «በውበቷ አማላይ፣ በመልኳ ሺህ ገዳይ» የሚሏት ዓይነት ስለሆነች ይሆናል ብዬ አተኩሬ አይቻት አውቃለሁ፤ ቅናት እንዳይመስልብኝ እንጂ ብዙ የምታምር አይደለችም። ቆይ! ልብወለድ መስሏችሁ እንዳይሆን? ታሪክ ነው የምነግራችሁ፤ በመሃል አገር ሸገር አዲስ አበባ የተፈጠረ ታሪክ። እና ይህቺን ልጅ እኔም የማውቃት በርቀት ነው። አንዳንድ ጸባይዋን በድፍረት ለመናገር ያስቻለኝ ከሰው ሰምቼ ወይም ሰው አምቶልኝም አይደለም፤ ያው ሁሌም ስለማያት ነው። መግቢያ መውጪያዬ በእርሷው ቤት በኩል ስለሆነም ነው። ባልወድም በግዴ አያታለሁ። እናላችሁ ከማውቀው ስጀምር፤ የኔን ወንድም ጨምሮ ሁለት ወንዶች ተጣልተውባታል። እንደ አቤልና ቃየን፤ «የእኔ ነው መሆን ያለባት!» ብለው መጋደል ነው የቀራቸው እንጂ ያልተባባሉባት የለም። እርሷ ግን ግድ ያላት አትመስልም፤ እንደው ጊዜ ማሳለፊያዋ እንጂ የማናቸውም መሆኗን ተናግራ አታውቅም። እንደውም በእርሷ ስም አንድ ግጥም ጽፌ ነበር፤ ድሮ ማለት ነው። ግጥሜን ሰብሰብ አድርጌ በአራት ተኩል ስንኝ ሳቀርበው እንዲህ ይላል፤ «…አይ ልጅት መልከኛ ሲጣሉ ታያለች በምኗ እንደሆነ እርሷ የት ታውቃለች? እነርሱም አልተዉ! የእኔ ነች የእኔ ነች ብለው ተጣሉባት ባይገባቸው እንጂ እርሷስ የራሷ ናት…» ደስ ይላል! በብዙዎች መወደድ ጥሩ ነው። እርሷም ለአንዳቸውም «የአንተ ነኝ» ሳትል ለሁሉም እኩል ፈገግታን ትሰጣለች። ስትቀልድላቸው፣ ስትስቅላቸው እኩል ነው፤ ስትስቅባቸው እንኳ አዳልታ አታውቅም። ለእርሷ ቅድሚያ ራሷ ናት እንጂ ሌላ ማንም አይደለም። የመጣውን ተቀብላ ታስተናግዳለች፤ የሄደውን ደህና ሁን ብላ ትሸኛለች። እንደው ግን ወንድሜን ጨምሮ እነዚህ ወዳጆቿ ለአንድ ቀን ፉንጋነቴን ታግሰው ጆሮ ሊሰጡኝ ቢፈቅዱ የምነግራቸው ነበረኝ። በመጀመሪያ ደረጃ እንዴት ብር እንደማይበቃት እያወቁ «የእኔ ነች!» ይላሉ? አሃ! ሰው ለምን ሲል ለወጪ እንዲህ ይራኮታል? «እኔ ወጪ ስለማላስወጣ እኔን ይፈልጉኝ» ማለቴ አይደለም፤ ግን በቃ! ብር አይበቃትማ። ይሄ ፊልሞቻቸን ላይ እንደሚታዩት አይነት የገንዘብ ፍቅር አናውዟቸው እንደተገለጹ ገጸባህርያት አይደለም። እነርሱ በሚመለከት ይህቺን ተወዳጅ ሴት ባካተተ መልኩ «አይወክሉን!» ብለን ሰላማዊ ሰልፍ መውጣት እስኪቀረን ድረስ አይወክሉንም ብለናል። ግን በቃ ኑሮ ነገር ናት! እንዲሰጣት የምትፈልገው ነገር ሁሉ ለእርሷ መሰረታዊ ነው፤ ነገሩ ቅንጦት ባይሆንም ከባድ ነው። ለምሳሌ የኔ ወንድም አብሯት አንድ አካባቢ ስለሚገኝ እንጂ ሌሎቹ ለትራንስፖርት ብለው ብዙ ያወጡላታል። መኪና ሁላ ሳያስፈልጋት አይቀርም። በቃ! ለእርሷ ይሄ መሠረታዊ ፍላጎት እንጂ ቅንጦት አይደለም። «ታክሲ ጥበቃ መሰለፍ ስጠላ!» ካለች አለች ነው፤ በፍጥነት የሆነ እርምጃ መወሰድ አለበት። አለበዚያ ከእርሷ ጋር መኖር አይታሰብማ! የጠየቀችውን ሳያደርጉ «ይኔ ነሽ!» ብሎ ነገር የለማ! አንድ የሰፈር ሰው መቼ እለት ጸበል ጸዲቅ ቅመሱ ብሎ ቤቱ ጠርቶን እርሷም በዛው መጥታ አግኝቻት ነበር። «እንዴ! ፀሐዩ ፀሐይ ነው እንዴ? በዚህ ፀሐይ መሰለፍ ራሱ አስቸጋሪ ነው። ታክሲ ውስጥ ተቀምጦ መቀቀል ደግሞ ደስ አይልም። ባስ ውስጥማ ብገባ በማግስቱ የምታመም ሁላ ይመስለኛል! መኪና ሲኖር ግን በአቋራጭ መንገድም ቢሆን በጊዜ መግባት ይቻላል። መኪና’ኮ መሠረታዊ ነገር\nሆኗል…» አለች። ደመወዙን በተቀበለ በአስራ አምስት ቀኑ «እስቲ ለደሞዝ የምመልሰው ብር አበድሪኝ» የሚለኝ ወንድሜ አፉን ሞልቶ፤ «ልክ ነሽ! አልተሳሳትሽም» ብሎ ፈገግ ይልላታል። ይህን እያወቀ ነው እንግዲህ ከሌሎቹ ቀድሞ የራሱ ሊያደርጋት የሚታገለው። በእርግጥ «ውድ» ከመሆኗ ውጪ እንዲሁም ከማይዋጥልኝ ተወዳጅ ያደረጋት መልኳ ባለፈ፤ ከሁሉ ተግባቢና ተጫዋች እንዲሁም ግልጽና አራዳ መሆኗን እኔም አደንቅላታለሁ። ምን ያለ ፍቅር ነው ግን? እንዴት ቢወዷት ነው «የእኔ ናት!» እያሉ የሚጣሉባት? በቃ! ሲነጋም ሲመሽም የማስበው ይህንን ነው። ነው ወይስ እየተፎካከሩ ነው? መቼም ብዙዎች ተንጋግተው የሚሄዱበት መንገድ ስለሚመቸን፤ «አንዱ የእኔ ናት ያለው አንዳች ነገር ቢያገኝባት ወይም ቢያይባት ነው» ብለው ካልሆነ ጸባይዋንና ችግራቸውን አስተያይተው እርግፍ አድርገው ትውት ሊያደርጓት አይገባም ነበር? ፍቅር ሲበዛ’ኮ አስቸጋሪ ነው።\nታድያ ይህን ታሪክ እንድነግራችሁ ያስገደደኝ በወንድሜና በሌላው እርሷን «የእኔ ናት» ባይ መካከል መስማማት አልመጣ በማለቱ ነው። ከዛም አልፎ ቤታችን ድረስ መጥቶ አባቴ ከአያቱ ያየው ፉከራና ሽለላ ትዝ ብሎት ሰሞኑን ቤቱን በቀረርቶና በፉከራ ግጥም ሞልቶታል። የሌላውም አባት በተመሳሳይ መልኩ ቀን ይጠብቃል፤ ቢችል መሃል ከተማ ላይ ጠልፎ ሊያስወስዳት ሁሉ ይከጅላል። ቢቸግረኝ አስታራቂ ልሆን ተነሳሁ። የወንድሜን አባት ወይም አባቴንም ሆነ የሰፈራችንን ልጅ አባት፤ አልያም ሌሎች «የልጄ ናት!» የሚሉት አባቶች ጋር አልሄድኩም። በቃ! ራሷ ጋር ሄድኩኝ። «የማን ነሽ?» አልኳት፤ ፈገግ ብዬ። ነገሬ ግን በቁጣ ቢሆን ሊያደባድበን ሁላ ይችል ነበር። «የማን ነሽ ይሉኛል የማን ልበላቸው…» አለች በዛወርቅ!፤ አሁን\nትዝታን ራሱን ቀስቅሳ የምትጠራው የምትመስለዋን ድምጻዊት በዛወርቅን ሙዚቃ ብታነጎራጉርልኝ ምን ልል ነው? ደግነቱ እርሷም ነገሩ ገብቷት ፈገግ ብላ ተቀበለችኝ። «ውይ! ምንድን ነው መረጋጋት ያነሳችሁ? ሁሉም የማን ነሽ ይለኛል? ምን አይታችሁብኝ ነው?» አለች። አሁን እንደው እኔን ለማናደድ እንጂ ሳታውቅ ቀርታ ነው? ወንድሞቻችን ሁሉ ጨርቃቸውን መጣል ቀርቷቸው፤ ከምትሰጠው ይልቅ የምትቀበለው ብዙ እንደሆነ እያወቁ እንኳ «የእኔ ናት» እያሉ በመጣላት አባቶቻቸውን በእርጅና ዘመን በከዘራ እያደባደቡ መሆኑ ጠፍቷት ነው? ልታስቀናኝና ልታናድደኝ እንጂ! ተበሳጨሁ። ግን አስታራቂ ልሆን መሄዴ ትዝ ሲለኝ ንዴቴን ዋጥኩት። ለመናደድ እልፍ ምክንያት አለ አይደለ እንዴ? ምን አስቸኮለኝ? «አየሽ ለአንዳቸው ቁርጣቸውን ንገሪያቸው። ማለቴ ሁሉም ስለሚወዱሽ ይሁን ወይም እርስ በእርስ ካለመዋደዳቸው የተነሳ አንቺን ዋንጫ አድርገው እየተጣሉብሽ…እኔ የማውቀው ነገር የለም። ግን በየቤታችን ሰላም እየነሱን ስለሆነ…ቁርጡን ነግረሽ አረጋጊያቸውና እኛም እንረፍበት» አልኳት። ከፊቷ ላይ ፈገግታዋ ሳይጠፋ አየችኝ፤ «እኔ ምን ላድርጋቸው? ያውቁኛል! እንዲርቁኝ ብዬ የኑሮ ደረጃዬን ከፍ ባደርግም፤ ዝብርዝቅርቅ ብዬ ሳልኳኳል ብታይም፣ በሰፈሩ ያሉ እናቶች ባህልና ሥርዓት የማታከብር ምን ዓይነት ሴት ናት እያሉ ከፍ ዝቅ ሲያደርጉኝ ቢሰሙም… በእኔ ከመጣላት የሚያገዳቸው ነገር የለም። እኔ እንደሆነ ከእናቴ ቤት አልወጣ… ቢቻለኝ እርሷን እያገለገልኩና እያገዝኩ ብኖር ነው የምመርጠው። ሲደክማቸው ይተውኛል ተያቸው…ቀስ እያለ ይገባቸዋል።» አለችኝ። የቀደመውን ግጥሜን መዝጊያ «… አልተረዱም እንጂ እርሷስ የእናቷ ናት…» ልበለው ማለት ነው? «እና የማናቸውም የመሆን ወይም ማናቸውንም የማግባት ሃሳብ የለሽም?» አልኳት፤ የባሰ አታምጣ! «ኧረ በጭራሽ! ለጊዜው ደስ ካሰኘኋቸውና እኔንም በሚገባ የሚጠቅሙኝ እስከሆነ ድረስ ከሁሉም ጋር ነኝ። የሁሉም ነኝ በይው! እንጂ የማንም አይደለሁም። የሚሰሙሽ ከሆነ እንደውም የእናቷ ናት በያቸው።» አለችኝ። በዛው ቅጽበት ስልኳ አንዳች ሙዚቃ በማሰማቱ ዝም ልታሰኘውና ደዋዩን ልታናግር ተነስታ ሄደች። መቼም ለእኔ የነገረችኝን ነገር ለወንድሜና መሳዮቹም ነግራቸው ይሆናል’ኮ! ግን\nምንድን ነው የጋረዳቸው? አጠገባቸው ከእርሷ የተሻለ የለምን? ነው ወይስ እውነትም ፍቅር ይሆን? ብቻ ግራ ገብቶኛል። ዛሬ ለወንድሜ ያለችኝን ሁሉ ደግሜ ልነግረውና ላስረዳው ቤት ተመለስኩ። እርቅ ለመፍጠር\nመሄዴን ረስቼ «የዚህች\nልጅ ጓደኛዋ ብሆን\nያዋጣኛል ማለት ይሆን?»\nእያልኩ ሳስብ ነበር።\nየተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞችን\nአገኛለሁ፤ ቢያንስ እርሷን\nብለው ከሚመጡት መካከል\nአንዱን ወዳጅ አደርግ\nይሆናል። ወይም ለትዝብት\nየሚሆን ብዙ መረጃ\nአግኝቼ ልብወለድ ነገር\nእጽፍ ወይም ፊልም\nእሠራ ይሆናል። «ልጅቷ\nየማን ናት?» በሚል\nርዕስ። ወይ ጉድ! የት\nሄድኩ…አሁን ቆይ ለወንድሜ\nታድያ በምን ቋንቋ\nነው የማስረዳው? ሰላም!አዲስ ዘመን ሚያዝያ 6/2011 በ", "passage_id": "b9d24193c02ee113460613cf0a480d57" }, { "passage": "ሰውዬው የታወቀ ነጋዴ ነበር አሉ። ሁሌም በእሱ ሆቴል የሚመገቡ ደንበኞቹ ስፍር ቁጥር የላቸውም። በየቀኑ የሚቆጥረው ገንዘብም ከሌሎች አቻዎቹ በተለየ በርከት የሚል ነው። ይህ ሰው ዘወትር የእንግዶቹን ፍላጎት ለመሙላት ቦዝኖ አያውቅም። ከትላንት በተሻለ ነገን በልጦ ለመገኘት የሚያደርገው ጥረትም የተለየ ነበር። ስመጥሩ ባለሆቴል ታዲያ አንድ ችግር ነበረበት። ምን የተሻለ ቢያገኝና ኪስ ሙሉ ቢያስገባ ግብር መክፈልን ሞክሮት አያውቅም። ነጋዴው ሁሌም የግብርን ጉዳይ መስማት አይፈልግም። ገና ቃሉን ሲያነሱበት ይናደዳል። በእሱ ዕምነት የሚሰራው የራሱ ላብ እንጂ የሌሎች ጭምር መሆን የለበትም። ግብርን ተንተርሰው የሚነሱ ተለምዷዊ ጉዳዮችም ፈጽሞ አይገቡትም። መስማትና ማወቅ ስለማይፈል ግም «ጆሮ ዳባ ልበስ» ሲል ዓመታትን በዋዛ አሳልፏል። ይህ መሆኑ ደግሞ ከሚመለከተው አካል ጋር ሊያግባባው አልቻለም። የግብር መሰብሰቢያ ወቅት በደረሰ ቁጥር ገቢውን ደብቆና እውነታውን ሸሽጎ ለማለፍ የሚሞክረው ባለሀብት በአንድም ይሁን በሌላ ሰበብ ሲሳካለት ቆይቷል። እንዲህ ለመሆኑ ደግሞ ከግብር ሰብሳቢዎቹ መንደር ቀድሞ የሚደርሰው መረጃ አጋሩ ነበር። በውስጥ አዋቂነት የሚያግዙትና ከእጁ ፍርፋሪ የለመዱ አንዳንዶች ሁሌም «አለንህ » እንዳሉት ነው። እነዚህ ሰዎች ስለግብር የታሰበውን ሁሉ ቀድመው «ሹክ ይሉታል። ሚስጥር የተባለውንም አንድም ሳይስቀሩ ይዘረግፉለታል። ይህን ሲያውቅ ታዲያ እንደታሰበው ሆኖ ላለመገኘት ጥንቃቄ በማድረግ የሚያህለው የለም። እንዲያውም የተካነ ነው ማለት ይቻላል። መረጃ ላለመተውም አስቀድሞ ይዘጋጃል። ባለሀብቱ የዕለት ገቢውን ቀንሶ፣ የኑሮ ውድነቱን ከገበያ መጥፋት ጋር አስታኮ ማለቃቀስ ልማዱ ነው። በዚህ የማሳሳት ተግባሩም ተገቢውን ግብር ላለመክፈል ሲንሸራተት ኖሯል። ይህን ሀቅ ሳይሆን ትክክለኛውን እውነታ የሚያውቁት የግብር ሰብሳቢ አካላት በተለያዩ አጋጣሚዎች ስለላ አድርገው ስለማንነቱ ደርሰው በታል። በዚህ ታዋቂ ነጋዴ ሆቴል የሚደራው ገበያ ከሌሎች በተለየ ነው። በተለይም ዕለተ ቅዳሜ ሲሆንና ገበያተኛው ከአዋሳኝ የገጠር አካባቢዎች ወደ መሀል አገር ሲዘልቅ የምርጫው ሚዛን ለዚህ ሰው ያጋድላል። ከገበያ መልስ ሻጭና ገዢው ያሻውን ተገባብዞ የብርሌውን አንገት፤ የብርጭቆውን ወገብ የሚጨብጠው በእርሱ ሆቴል ነው። ዘመድ አዝማድና ወዳጅ ጓደኛም ቢሆን የመገናኛ ቀጠሮ የሚቀናው በእሱ እልፍኝ ሲሆን ነው። በዚህ ቀን አስተናጋጁ ከተጋባዡ ሲተራመስ መዋሉ አዲስ አይደለም። ይሄኔ ወፍራሙ ባለሀብት ከፍ ካለ ስፍራ አረፍ ብሎ ወጪ ገቢውን ያማትራል። ከየአቅጣጫው የሚጎርፈውን ገቢም ከተቀባዩ እየተቀበለ አንድ ሁለት ሲል ይቆጥራል። በማግስቱ ግን የዚህ ሰው ቋንቋ እንደተለ መደው በማለቃቀስ ይተካል። ምንም አላገኘሁ፤ ኑሮ ተወደደ፣ ገበያ ጠፋ፣ አቅም አነሰ… ሌላም ሌላም፤ የዚህ ሰው መለያው ነው። «ዓይን አይቶ ልብ ይፈርዳል» እንዲሉ የሚለው ሁሉ የማይዋጥላቸው ግብር ሰብሳቢዎች መቆጨታቸው አይቀርም፤ ሁሌም ይመክሩበታል። አንድ ቀንም ድንገት ተገኝተው በማስረጃ ሊይዙት ይስማማሉ። በስፍራው ደርሰው ሁሉን ካረጋገጡ በኋላም የበሰለ የተደገሰው በቤት ውስጥ እንዳለ ቤቱን በመላ ለማሸግ ይነጋገራሉ። ይማማላሉ። የማስጠንቀቂያ ደብዳቤውን ከበርና ከመስኮቱ ለመለጠፍ ይስማማሉ። የምክክሩ አካል ከነበረው አንደኛው የነጋዴው የቅርብ ወሬ አቀባይ እንደመሆኑ የተወሰነውን ሁሉ በጥንቃቄ እያዳመጠ በውሳኔው ይተባበራል። ይህ ውሳኔ ለሰውዬው ወሬ በማቀበል ብቻ እንደማይቆም ያውቃል። እንደፍትፍት አጣፍጦ ከሚያጎርሰው እፍታ ባሻገር ለእሱ የሚተርፈው ሲሳይ ቀላል እንደማይሆን እርግጠኛ ነው። እናም ውሎ ሳያድር ከባለ ሆቴሉ ሳሎን ገስግሶ ደረሰ። የያዘውን ሚስጥርና በእሱ ላይ የታሰበውን ዕቅድም አጣፍጦ ነገረው። ባለሀብቱ በዕለተ ቅዳሜ የገበያ ውሎ በሆቴሉ የሚያገኘውን ገቢ አሳምሮ ያውቀዋል። በዚህ ቀን ግብር ሰብሳቢዎቹ ደርሰው እውነታውን ካዩና ጉዳዩን በማስረጃ ካረጋገጡ በህግ እንደሚያስጠይቀው ተረድቷል። ከሁሉም ደግሞ ውስጥ አዋቂው የማስጠንቀቂያ ደብዳቤውን በበርና መስኮቱ ለመለጠፍ ማሰባቸውን አረጋግጦለታል። ያ ከሆነ ደግሞ የበሰለ ምግብ ካለ በሙሉ ይበላሻል። አስቀድሞ ጥንቃቄ አድርጎ ምግብ ካላዘጋጀም የእለቱ ከፍተኛ ገቢ ይቀራል። ለእርሱ ሁለቱም ኪሳራ ነው። ይህን ማወቁ በጉዳዩ ይበልጥ እንዲያስብ እያደረገው ነው። ለእርሱ ማስጠንቀቂያ ደረሰው ማለትም ትክክለኛና ቋሚ ግብር ከፋይ ሆነ ማለት ነው። ልማደኛው ወሬ አቀባይ የሚገባውን ተቀብሎ ከሄደ በኋላ ዝነኛው ባለሆቴል መልሶ መላልሶ ማሰቡን ቀጠለ። በመጨረሻም የሀሳቡ ውጤት ከአንድ ጥግ ሲያደርሰው ልቡ በሀሴት ተሞልቶ ፊቱ በፈገግታ መውዛት ያዘ። ድንገት ከመቀመጫው ፈጥኖ የተነሳው ባለሀብት ሰራተኞቹን በአፍታ ሰብስቦ ትዕዛዝ ለማስተላለፍ ጊዜ አልፈጀም። ይህን ሲያደርግ ልበ ሙሉነት ይነበብበት ነበር ። በተባለው ቀን ግብር ሰብሳቢዎቹ ያሻቸውን አስበው በስፍራው ቢደርሱ ሰውዬው ላይደነቅ ወስኗል። ሁሌም እንደሚያደርገው የልመና ቃላት ማዥጎድጎድ አያስፈልገውም። በድንገ ቴዎቹ እንግዶች መድረስም ተደናግጦ ለመስተ ንግዶ «ሽርጉድ» ለማለት አልፈለገም። እነሱ በዕቅዳቸው ቆርጠዋል። እሱም ቢሆን ያሰበውን አስቧል። አሁን ዕለተ ቅዳሜ ነግቷል። በዚህ ቀን በሰፊው የሆቴል ግቢ ገበያው ይደራል። እንግዶችን በመስተንግዶ የሚያስደስቱት ብርቱ ሰራተኞች እንደተለመደው በስራ ተወጥረው ይውላሉ። ይህ ከመሆኑ አስቀድሞ ግን የታዋቂው ሆቴል ጠንካራ በርና መስኮቶች ወለል ብለዋል። በርና መስኮቶቹ እንደወትሮው አልነበሩም። ክንዶቻቸው ተገንጥለው መዝጊያዎቻቸው ተነቃቅለው ከንፈር እንደሌለው ጥርስ ሆነዋል። ለወትሮው በር አሊያም መስኮት የሚያስብላቸው አካል አብሯቸው አይታይም። መለመላቸውን ቆመው ክንፍ እንደሌለው አሞራ ሆነዋል። የቤት ሳይሆን የዋሻ መግቢያ መስለው ቧ ብለዋል። ገበያው ደርቶ ወጪ ወራጁ በሚተራመስበት የሆቴል አዳራሽ በሰዓቱ የደረሱት ግብር ሰብሳቢዎች የሚያደርጉትን አልዘነጉም። ድንገት በመምጣታቸው የሚደናገጠውን ባለ ሆቴል እያሰቡ በእጅ መንሻ አሊያም በግብዣ እንዳይደልላቸው አስቀድመው ተማምለዋል። የእነሱን ድንገት መድረስ የተመለከተው ሰው ግን እንደታሰበው ሆኖ አልደነገጠም። መሽቆጥቆጥም ሆነ መደናበር አልታየበትም። ሹሞቹን እንደማንኛውም እንግዳ ገርመም አድርጓቸው ወደ ጨዋታው ይመለሳል። እንግዶቹ በዚህ ስሜቱ ቢገረሙም ወደዕቅዳቸው ለመዝለቅ በርና መስኮቶችን ፍለጋ ይዘዋል። የሆቴሉን ዋና መግቢያ እንዳገኙ በሩን በአይኖቻ ቸው መቃኘት ያዙ። ተፈላጊው በር መቃኑ እንጂ ሙሉ አካሉ የለም። አለፍ ብለው የመስኮቶቹን ግራና ቀኝ አሰሱ። እነሱም ቢሆኑ ክንፉ እንደተመታ አሞራ ሆነዋል። ግራና ቀኝ የነበሯቸው መዝጊያዎች አሁን አብረዋቸው የሉም። መለስ ብለው ደግሞ ወደጓሮ በር አመሩ። እሱም ቢሆን መዝጊያው ወላልቆ እርቃኑን ቆሟል። የሆቴሉን ዙሪያ ገባ በጥንቃቄ ሲዞሩ የቆዩት አሳሾች አንድም በርና መስኮት የሚባል እውነት አላገኙም። እናም ምኑን ዘግተው በምን ላይ ወረቀት ለጥፈው ቤቱን አሸግን ይበሉ? በተደበላለቀ ስሜት ተውጠው ወደመጡበት ስፍራ ተመለሱ። ይህ ሁሉ ሲሆን ባለሆቴሉ ከነበረበት ሆኖ በልቡ ይስቅባቸው ነበር። ሰዎቹ አስቀድመው እንዳሰቡት ማስጠንቀቂያውን ለመለጠፍ ያሰቡት በበርና መስኮቶቹ ላይ ነው። ለጊዜው ይህን ለማድረግ ስፍራ ስላላገኙ ተያይዘው ተመለሱ። ይህ የሆነው ለጊዜው ነው። የነገውን እውነት ግን እነሱም ሆኑ ሰውዬው አሳምረው ያውቁታል። ወዳጆቼ! ይህ አጋጣሚ ማንም ቢሆን ከእውነታው ሊርቅ የሚችለው ለጊዜው እንጂ ለዘለቄታው አለመሆኑን ይጠቁመናል። በአብዛኛው እንደሚስተዋለው አንዳንድ ነጋዴዎች ሰርተው በሚከብሩባት፣ ነግደው በሚያተርፉባት ሀገራቸው ከዚህም በላይ የረቀቀ ዘዴ መጠቀማቸው አዲስ አይደለም። ግብር ለማንም ቢሆን የማይቀር ሀገራዊ ግዴታ ነው። ይህ ይሆን ዘንድም ሀይማኖታዊና ታሪካዊ እውነታዎች ጭምር ይጠቁሙናል። ማንም ለሚኖርባት ሀገር ከሚያገኘው ደመወዙ፣ ከሚያፍሰው ምርቱ፣ ነግዶ ከሚያተርፈው ጥሪቱ የሚጠበቅበትን ሊያበረክት ግድ ይለዋል። ግብርን በወቅቱ አስቦ መክፈልም የአዋቂነት ምልክት ነው። ሁሉም ዜጋ በሚከፍለው ግብር ሀገሩን፤ ወገኑንና ራሱን ይጠቅማል። በዚህ ግዴታው ውስጥም መብቱን አስጠብቆ እርሱነቱን ያኮራል። «ግዴታዬን እወጣለሁ፣ መብቴን እጠይቃለሁ» ሲባል ደግሞ በአባባል ላይ ብቻ ተመስርቶ አይደለም። መብትን ለመጠየቅ ግዴታን መወጣት ግድ ሊል እንጂ፤አዲስ ዘመን የካቲት 13/2011መልካምስራ አፈወርቅ", "passage_id": "ab61523fe32855ac06fe325e88fedd36" }, { "passage": "እንዴት\nሰነበታችሁልኝ? እናተዬ የሕይወት ሩጫ ፋታ አይሰጥም አይደል? የሚገርመው ደግሞ ሩጫችን ሲጨምር የምንሮጥለት ነገር እየቀነሰ መሄዱ የሩጫችንን ያህል የሮጥንለት ነገር አለመሙላቱ የስገርማል፡፡ ወይ ጉድ ከሰው ጋር ለየን፤ ከወዳጅ ጋር አራራቀን እኮ፡፡ ግለኝነቱ ጠንክሮ የእርስ በእርስ ግንኙነታችንን ያላላው፤ ማህበራዊ ትስስራችንን ያሳሳውና አብሮነታችንን የሸረሸረው ምን ይሆን? አሁንማ አብረን ቁጭ ብለን የምናወራው መጓጓዣ መኪና ውስጥ ብቻ ሆኗል እኮ ጉድ ነው። ሰብስቦ ሳንፈልግ በጋራ አስቀምጦ የሚያስጉዘን ታክሲ የወጋችን መጠንሰሻ፣ የገጠመኞቻችን መነሻና የትዝብታችን መዳረሻ ሆኗል ታክሲ፤ ከቀናት በፊት ታክሲ ተሳፍሬ ስጓዝ የሰማሁት ገጠመኝ መነሻነት ትዝብቴን እያነሳሁ ላወጋችሁ ወደድኩ፡፡ “እማዬ እኔ ትልቅ ስሆን ቢራ እጠጣና መኪና ይደርሰኛል! ከዚያ ሁሌም አንቺን በመኪናው ይዤሽ ወደፈለግሽበት እወስድሻለሁ፡፡” ታክሲ ውስጥ አንድ የ4 ዓመት ሕፃን ከእናቱ ጋር በሚያደርገው ውይይት መሀል ከልጁ የሰማሁት ለዛሬ ጽሑፌ መነሻ ሆነኝ፡፡ ሐፃን\nነውና እሱን አልታዘብኩትም፤ ለሕፃናት የማያስቡትን ሚዲያዎች ለትውልድ ግድ የሌላቸውን ምርት አቅራቢያዎችና ገቢያቸውን ብቻ የሚያስቡትን የማስታወቂያ ድርጅቶች ታዘብኳቸው እንጂ፤ ይገርማል! እዚህ ሀገር ላይ ህግ አክባሪ ተቋም፣ መመሪያና መተዳደሪያ አክባሪ ሠራተኛ፣ ደንብ አስከባሪ መስሪያ ቤት ጠፍቶ ይሆን እንዴ? ስለኛ ግድ ሳይኖራቸው እዩን የሚሉን በቴሌቪዥን የሚተላለፉ ማስታወቂያዎቻችን ግን ወዴት ይሁን የሚያደርሱን? “ማን ይመለከታል? ምነስ ያስከትላል?” ተዘንግቷል። ይሄ ማህበራዊ ሀላፊነት ይሉት ነገር አፈር ደቼ በልቷል። ምን አገባኝ እኔ ብሩን ልሰብስብ እንጂ በምን መልክ ልሰብስብ አያሳስባቸውም፡፡ በብሄራዊ\nጣቢያዎቻችን ብሄራዊ ስካር ስከሩ እንባላለን፡፡ ወዳጆቼ አባት ከሕፃን ልጁ ጋር ቁጭ ብሎ የሚመለከታቸው ማስታወቂያዎች እናት ከሴት ልጇ ጋር የምትሰማቸው ስርዓት አልባ ምናምናችንን ገዝተው ይጠቀሙ ባዮች ነፃነት ነሱን፤ሃያ አራት ሰዓት ባልተገደበ ሁኔታ እንዳሻቸው የሚያስተዋውቁት ተገቢነት የሌለው ማስታወቂያ ልጁን እንዲህ እንዲያስብ ህልሙ እንዲዛባ አደረገው፡፡ በትንሽ አዕምሮው የሚያስበው የምኞቱ ጥግ ጠጥቶ መሸለም ሆነ፡፡ የሚመጥነው ተለክቶ አልተሰጠውማ ምን ያድርግ ተገኝ ብሩ የሚያየውን የሚሰማውን ተመኘ፤ የሚመኘውንም ተናገረ፡፡ ደሞ እኮ የተገረምኩት ያሳሰበን የልጁ እንደዚያ ማለት ብቻ አይደለም የናትየዋም ምላሽ እንጂ፡፡ የልጁ እናት በተናገሩት ነገር ተከፋሁ። በእነዚያ\nየስካር መንፈስ በሚጣሩ ማስተወቂያዎች የተጸነሰ ህልሙን ለተነፈሰው ልጅ እናቱ የሰጠችው ምለሽ እቅፍ አድርጋ ጉንጩን እየሳመች ጎሽ የኔ አንበሳ አንተ እኮ መኩሪያዬ ነህ! ብትለውስ? እም እሱን ነው የምፈልገው፤ እ… መኩሪያዬ ጉድ! እናት በልጅዋ የስካር ሽልማት መኩራትን ፈለገች፡፡ ልጁ ምን እያሰበ መሆኑ ተዘንግቷት ይሆን? ቆዩኝማ ዕድሜ አያስተምርም? ከፍ ሲባል ከፍ ያለ አተያይ አይለመድም? ዕድሜ ሲጨምር መገሰጫና ማረሚያ አይለይም? እናትነት በራሱ ምንም ሳይጨመር በጎና ክፉ ምኞት አያስለይም? የልጁ እናት ቅር አሰኘችኝ፤ ልጅማ አልኮል ጠጥቶ ከሚያመጣው ድሎት በትምህርት በርትቶ፤ ቀለም ጠጥቶ የሚያወራው ተረት በስንት ጣዕሙ፤ ስካሩ ውስጥ የሞላ የጤና መቃውስ ዘግናኝ አደጋ ሲብስም ሞት እኮ ነው ያለው እናትየዋ አላሰበችውም፡፡ እኔ\nምለው የኛዎቹ መገናኛ ብዙሃን ግን ምን ነካቸው? ለትውልድ አይታሰብም? የሚሠራው ሀገር ለመለወጥ፤ ሀገር ለማነጽ አይደል እንዴ? ኧረ ተው አንተዛዘብ ተው፡፡ የሚገርመው ይሄን ያለ ልክ የሚሰበከውን የአልኮል መጠጥ ማስታወቂያ ያሳሰበው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አንድ አዋጅ አውጥቶ አጽድቋል። ይበል የሚያሰኝ ነው። ያለ ልክ እንዲፈነጩ ተፈቅዶላቸው ከኢትዮጵያዊነት መለያ ከሆኑ እሴትና መልካም ልምዶች ጋር እየቀላቀሉ፣ ከጀግንነት፣ ከአብሮ መኖርና መተሳሰብ ውብ ባህላችን ጋር አዛንቀው ሀበሾች ውብ ናችሁ! ባህላችሁም ደስ ይላል! ስካርም ደንባችሁ ነው፡፡ እያሉን ነው፡፡ ከታሪካችን ጋር እየቀየጡ ለአደጋ ምክንያት ለጤንነት ጠንቅ መሆኑን ረስተው ማዋረዱን ደብቀው አስካሪ መጠጣቸው የደስታና የፌሽታ ምንጭ መሆኑን በተከሸኑና ሲሰሙዋቸው በሚያሰክሩ ቃላት ይሰብኩናል፡፡ ወዳጆቼ የአልኮል መጠጦችን ስያሜ ልብ ብላችሁ ታውቃላችሁ፡፡ በማስታወቂያቸው ስካርን የእኛ ባህል እንዳስመሰሉት ሁሉ ስያሜያቸውንም ከኛ ቀምተዋል፡፡ ሀበሻ ባህሉንና ታሪኩን እንደሚወድ ገብቷቸዋል፡ ፡ በተፈጥሮ ሀብቱ እንደሚማረክ ተረድተዋል፡፡ የጋራችን መጠሪያችንን ቀምተው፤ የተፈጥሮአዊ ሀብቶቻችንን ስም ነጥቀው፣ የታሪካዊ ቦታዎቻችን ስያሜ ወስደው በማን አለብኝነት ለራሳቸው መጠሪያ አደረጉት፡፡ በነገራችን ላይ በቅርቡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሚዲያ በሚታየው የአልኮል መጠጥ ማስታውቂያ አግባብነት ላይ መክሮ ስርዓት ለማስያዝ የሚያስችል አዋጅ አፅድቋል፡፡ በኢትዮጵያ\nየምግብ መድሀኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን ቀርቦ በምክር ቤቱ አባላት በሙሉ ድምፅ የጸደቀው አዋጅ አሁን ላይ በአንዳንድ የሚዲያ ተቋማት ሙሉ በሙሉ መተግበር ባይችልም ቀድሞ ለትውልድ ግድ ሳይሰጣቸው ባሻቸው መልክ ያቀርቡት የነበረውን ማስታወቂያ ሳይወዱ እንዲያቆሙ ተገድደዋል፡፡ ይህንን ተከትሎ ትላንት በአንድ ሬዲዮ ጣቢያ ላይ የአየር ሰዓት ተከራይቶ በመጠጥ ማስታወቂያ ሁለት ሰዓታት ሙሉ ያ …ዬ… ዩ….እያለ አንድ የረባ ቁም ነገር የሌለው ፕሮግራም ሲያቀርብ የነበረ የባህር ማዶ ዘፈን ጋባዥ “በዓለም ላይ የሌለ ህግ ወጣብን…አልኮል አታስተዋውቁ ተባልን፤ የትም ሀገር ተሰምቶም አይታወቅም..” እያለ ወሬና ቁም ነገር የጠፋበት በሬዲዮ ሞገዱ ላይ ድምፁን የሚያስተጋባውን ሰው ስሰማ ይበልጥ አዘንኩበት፡፡ አያችሁ ወዳጆቼ ለሱ መብት ጥያቄ ማለት ያላግባብ ትውልድን በሚያነትብ መልክ የሚቀርበውን ማስታወቂያ እያስተላለፈ ያለገደብ የሚያገኘውን ገቢ ቀነሰ ብሎ መጮህ ነው፡፡ ባይገርማችሁ የዚያን ቀን የሬዲዮ ፕሮግራሙ ሙሉው “እንዴት እንከለከላለን ሌላ ዓለም ላይ የሌለ ህግ ነው” ብሎ ዘራፍ ሲል ነበር ሰዓቱ ያለቀበት፤ እኔ ምለው የትኛው ሀገር ላይ ሰምቶ ይሆን ስርዓት በሌለው መልክ የሚተላለፍ ማስታወቂያ የማያውቁትን መናገር ለዚያውም ለራስ ጥቅም ብሎ፤ አያስተዛዝብም? ወይኔ አሳዘነኝ ይሄኔ እሱ ከራሱ ውጪ የሚመለከተው ዓለም ስለሌለ ይሆናል እኮ ዓለም ላይ የሌለ ህግ ነው ብሎ የተሟገተው፤ ሌላው ዓለም በእንደዚህ ዓይነት ማስታወቂያች ላይ የሚታየውን ጠንከር ያለ ክለከላ ቀድመን ተግብረን ቢሆን ኖሮ ወዳጆቼ ይህ ሰው ፈጽሞ ፕሮግራሙን ለአየር ማብቃት አይችልም ነበር፡፡ ግለሰቡ በራሱ የእነዚህ ማስታወቂያዎች ውጤት ሁሉ ይመስለኛል፤ ለማንኛውም ወዳጆቼ አነሰም በዛ አምላክ ለኛ የፈቀደውን፤ ወደኛም ያቀረበውን መብላታችን በዚያም መኖራችን አይቀሬ ነው። አይደል? በኑሯችን ለወገን አስበን፤ ለትውልድ ተጨንቀን፤ መልካም ነገር ዘርተን ማለፍ መቻል ደግሞ አቻ የሌለው ሰናይ ተግባር ነውና ጉዟችንንና ሥራችንን ሀገር በሚገነባ፤ ትውልድ በሚያንጽ መልኩ ብናደርግ ባይ ነኝ፡፡ ቸር ይግጠመን፡፡አዲስ\nዘመን መጋቢት 4/2011በተገኝ\nብሩ", "passage_id": "de934c4fd3dd07579bfe5067b337820b" } ]
f6511d76b02e901804596169e7dcc89b
b1081c38c755c9c6137ed675d8b2a725
የገዳ ስርዓት – የኦሮሞ ሕዝብ የትልቅነቱ ምልክትም ሀብትም
አስቴር ኤልያስ ስፍራው በተለያዩ የሴቶችና የወንዶች አልባሳት ደምቋል::በአልባሳቱ ላይ ገኖ የሚታየው ነጭ ቀለም በመሆኑም አስተውሎ ለተመለከተው ዙሪያ ገባውን የፈካ ማሽላ አስመስሎታል::በተለያዩ ድንኳኖች ውስጥ ደግሞ የጉጂ የባህል ምግቦች እንዲሁም የተለያዩ ጌጣጌጦችና አልባሳት ለእይታ ቀርበዋል::በዚሁ ስፍራ አምስት የጎጆ ቤቶች በመደዳ ተሰድረው ይታያሉ::ስፍራው በምዕራብ ጉጂ ዞን ቡሌ ሆራ ከተማ የጉጂ ኦሮሞ የባህል ስርዓት የሚካሄድበት ቦሌ ሀገላ ነው ::በዕለቱ የገዳ ስርዓቱን ደረጃ የሚያሳይ ትርዒት በስፍራው የተካሄደ ነው ፣ እነዚህም ደበሌ፣ ቀሬ፣ ኩሳ፣ ራባ፣ ዶሪ፣ ገዳ፣ ባቱ እና ዩባ የተባሉት ናቸው ትርዒቱን ያቀረቡት::በዕለቱ መርሐግብሩን በንግግር የከፈቱት የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ፈርያት መሀመድ እንደሚሉት፤ ኢትዮጵያ የብዙ ባህል ባለቤት ናት::የኦሮሞ ህዝብ ደግሞ ከትውልድ ወደትውልድ ሲያስተላልፍ የመጣው የገዳ ስርዓት አንዱ ነው ፣ ይህም የገዳ ስርዓት እንደ እሬቻ፣ ስንቄ፣ ሞጋሳና ሌሎችንም በርካታ እሴቶችን በውስጡ የያዘ ነው::እነዚህም እሴቶች ለኦሮሞ ብሎም ለአገሪቱ ሕዝቦች ወንድማማችነት እንዲጠናከር የሚያግዙ ናቸው ::የገዳ እሴቶች ውበታቸውንም ጥንካሬያቸውንም ጠብቀው ከትውልድ ወደትውልድ እንዲተላለፉ የሁሉም ድርሻ ነው የሚሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፣ ሚኒስትር መሥሪያ ቤታቸው ከክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመሆን በቅንጅት እንደሚሰራም ነው ያረጋገጡት::የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ከበደ ዴሲሳ በበኩላቸው፤ የገዳ ስርዓት ለኦሮሞ ሕዝብ ሀብቱም ምልክቱም መሆኑን ይናገራሉ::ኦሮሞ በዚህ ሥርዓት ሲተዳደር እንደነበር ሁሉ ዛሬም በመተዳደር ላይ እንደሚገኝም ጠቅሰው፤ በዚህ ሥርዓት ውስጥ መብት እንዳለ ሁሉ ግዴታ መኖሩን ያመለክታሉ::በተለይም ደግሞ ሰላማዊ የሆነ የስልጣን ሽግግርን አጥብቆ ስለሚከተል በዚህም ዓለም እንደሚያውቀው ነው የተናገሩት::እርሳቸው እንዳሉት፤ ይህ ስርዓት ቀደም ሲል በተወሰነ ደረጃ ተዳክሞ ነበር::ይሁንና በተሰሩ ጠንካራ ስራዎች አማካይነት በዩኔስኮ ከመመዝገቡም በተጨማሪ በክልል ደረጃ ከአንድ እስከ ስምንተኛ ክፍል ትምህርት የሚሰጥ ሲሆን፣ በዩኒቨርሲቲ ደረጃም እስከ ሶስተኛ ዲግሪ እየተሰጠ መገኘቱ ይበል የሚያሰኝ ጉዳይ ሆኗል::በመሆኑም ኦሮሞ አሊያም ኢትዮጵያ ብቻ የሚኮራበት ሳይሆን አህጉሪቱ አፍሪካ እንዲሁ የምትኮራበት ስርዓት ነው::የምዕራብ ጉጂ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ከድር ኤሌሞ በበኩላቸው፤ የሕዝቦችን አንድነት ይበልጥ ለማጠናከር ባህልን ማክበር ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ የገዳ ስርዓት ደግሞ የኦሮሞ ሕዝብ የሚተዳደርበት የዴሞክራሲ መሰረት የሆነ በመሆኑ ሊከበርም ከትውልድ ወደትውልድ ለማሸጋገር በሚደረገው ሂደት መተባበርም ተገቢ መሆኑን አስረድተዋል::የዴሞክራሲ መሰረት የሆነውን የገዳ ስርዓት ማጠናከር የሕዝብን አንድነት ለማጠናከር ትልቅ ሚና እንዳለውም ተናግረዋል::በዕለቱ ያነጋገርናቸው ወጣት ነጌቱ ደስታ እና ወጣት ሌሎ ሂርባዬ በየበኩላቸው፤ የገዳ ስርዓትን ለማስቀጠል በመጀመሪያ ግንዛቤን ከፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የተናገሩት::በተለይ የዴሞክራሲ መሰረት ነው የተባለውና በተግባሩም እየታየ የሚገኘው ይኸው ስርዓት በዩኔስኮ መመዝገቡ ብቻ በራሱ የዴሞክራሲን ስርዓት እንደማያስቀጠል ጠቅሰው፤ ስርዓቱን በማስቀጠል ረገድ ከወጣቱ ብዙ እንደሚጠበቅ ነው ያመለከቱት::የገዳ ስርዓት መለያ ምልክታቸው እንደሆነም ይናገራሉ::የገዳ ስርዓት አንደኛውን ትውልድ ከሌላኛው ትውልድ የሚያያዝ መሆኑን የጠቀሱት ደግሞ ሌላኛዎቹ ወጣቶች ጫልቱ ደስታ እና ገመዴ ገናሌ ናቸው::ወጣቶቹ የገዳ ሥርዓት በዩኒቨርሲቲ ደረጃ መሰጠት መጀመሩ ለቅብብሎሽ ትልቁን ሚና የሚጫወት ስለመሆኑም ጠቅሰዋል::እነርሱ የተማሩት ከቤተሰቦቻቸው እንደመሆኑ እነሱም በቀጣይ ለትውልድ ለማስተላለፍ ያላቸውን ቁርጠኝነት ይናገራሉ:: ከትናንት በስቲያ የገዳ ስርዓት ለዓለም ቅርስነት የተመዘገበበትን 4ኛ ዓመት የመታሰቢያ በዓል ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ የገዳ ፓናል ውይይት በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የተካሄደ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን በትናትናው ዕለት ደግሞ የጉጂ ባህልን የሚያመለክቱ የተለያዩ ዝግጅቶች ተካሂደዋል::ወጣቶች የገዳ ስርዓት የኦሮሞ ሕዝብ ሀብትም ምልክትም ነው የሚሉት::
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=39254
[ { "passage": "እሁድ በሚካሄደው የኢሬቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ ከዚህ በፊት ባልተለመደ ሁኔታ የታጠቀ የመንግሥት ፀጥታ አስከባሪ ኃይል እንደማይገኝ በዓሉን እያስተባበረ የሚገኘው የኦሮሚያ አባገዳዎች ምክር ቤት ገልጿል። \n\nበመንግሥት የፀጥታ አስከባሪዎች ቦታም 300 በጎፍቃደኛ ወጣቶች ሥርዓት ያስከብራሉ ሲሉ የምክር ቤቱ ሰብሳቢ የሆኑት አባ ገዳ በየነ ሰምበቶ ለቢቢሲ ተናግረዋል። \n\n''በዘንድሮው በዓል ላይ የትኛውም የመንግሥት አካል ምንም አይነት ድርሻ አይኖረውም፤ የመንግሥት ባለስልጣናትም ንግግር አያደርጉም ።'' ሲሉ ተናግረዋል። \n\n''የመንግሥት ባለስልጣናት እንደማንኛውም ዜጋ በበዓሉ ላይ የመሳተፍ መብት አላቸው። ከዚህ የዘለለ ግን ሌላ ተሳትፎ አይኖራቸውም'' ሲሉ አባ ገዳ በየነ ሰምበቶ አስረድተዋል። \n\nበዓሉ በሚከበርበት ቦታ ያሉ የመግቢያና የመውጫ መንገዶችን የማስፋት ሥራዎች እንደተከናወኑ አባ ገዳ በየነ ተናግረዋል። \n\nከዓመት በፊት በተካሄደው የኢሬቻ በዓል ላይ የፀጥታ ኃይሎች በከፈቱት ተኩስ በርካታ ሰዎች ሲሸሹ ጉድጓድ ውስጥ ገብተውና ተረጋግጠው ህይወታቸው ማለፉ ያታወሳል። \n\nየክልሉ የፀጥታ ጉዳዮች ቢሮ ቃለ-አቀባይ የሆኑት አቶ መለሰ ተፈራ ለቢቢሲ እንደተናገሩት፤ በአባ ገዳዎች የተመለመሉ በጎፍቃደኛ ወጣቶች የበዓሉን ሥነ-ሥርዓት ያስከብራሉ። የኦሮሚያ ፖሊስ ወደ ቢሾፍቱ የሚወስዱ መንገዶችን ብቻ ይቆጣጠራል፤ ያሉት አቶ መለሰ ''መሳሪያ የታጠቀ ፀጥታ አስከባሪ ኃይል በበዓሉ ስፍራ አይገኝም'' ሲሉ አረጋግጠዋል።\n\n''በድንገት''\n\nከዓመት በፊት በኢሬቻ በዓል ላይ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖች በቢሾፍቱ ከተማ በቆመላቸው የመታሰቢያ ሃውልት ላይ ''በድንገት ህይወታችውን ላጡ'' ተብሎ የሰፈረው ጽሁፍ በበርካቶች ዘንድ ቅሬታ ፈጥሮ ነበር። \n\nአባ ገዳ በየነ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ከሆነ ''በድንገት'' የሚለው ጽሁፍ እንዲፋቅ ተገርጓል። በበዓሉ ዋዜማም ህይወታቸውን ላጡት የህሊና ጸሎት እንደሚደረግ ጨምረው አስረድተዋል። \n\nየኢሬቻ በዓል ምንድን ነው? \n\nየቀድሞ የቱለማ አባ ገዳ ነጋሳ ነገዎ ''ኢሬቻ የምስጋና ቀን ነው። ለፈጣሪ የሚሰጥ ምስጋና''። \n\n''ክረምቱን አሳለፍከን፣ ወደ ሌላ ዘመን አሸጋገርከን፣ የዘራነው አሽቷል በማለት የሃይማኖት ልዩነት ሳይገድበን ከሁሉም አቅጣጫ በመሰባሰብ እርጥብ ሳር በመያዝ ለዋቃ ምስጋና እናደርሳለን'' ሲሉ ያስረዳሉ። \n\nየኢሬቻ በዓል በቢሾፍቱ ከተማ በሆር ሃርሰዴ የሚከበር ሲሆን በሚሊዮን የሚቆጠር ህዝብ በበዓሉ ላይ ይሳተፋል። \n\n ", "passage_id": "38ccc74ba287e87078175d6fdae48676" }, { "passage": "የኢሬቻ በዓል በቢሾፍቱ ከተማ ሆራ አርሰዲ ሀይቅ በድምቀት ተከብሯል።በባህላዊ አልባሳት ያሸበረቁ አባ ገዳዎች፣ ወጣቶችና የተለያዩ የህብርተሰብ ክፍሎች ከሌሊቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ወደ ስፍራው በማቅናት  የእሬፈና ወይም የምስጋና ስርዓት አድርሰዋል።የኢሬቻ በዓል በሁለት ቦታና ወቅቶች ተከፋፍሎ ይከናወናል።አንደኛው በክረምቱ  መግቢያ በተራራ ላይ የሚካሔድ ሲሆን ይህም ኢሬቻ ቱሉ የሚል መጠሪያ አለው፡፡ሌላኛው ደግሞ  ክረምት አልፎ ጸደዩ ሲገባ በቢሾፍቱ ሆራ አርሰዲ ሀይቅ የሚፈጸመው ሥርዓት ነው፡፡በኦሮሞ ህዝብ ዘንድ ከጥንት ጀምሮ ከክረምቱ ወደ በጋው ብርሃን  በሰላም መሸጋገርን  ምክንያት በማድረግ በየዓመቱ በመስከረም ወር መጨረሻ የሚከበረው የኢሬቻ በዓል ዘንድሮም በድምቀት ተከብሯል።የኦሮሞ አባ ገዳዎች ህብረት አባላት በስፍራው ተገኝተው የበዓሉን ስርዓት አከናውነዋል።አባ ገዳዎችም ለምለም ቄጠማ ይዘው ምስጋና አቅርበዋል፤ መጪው ጊዜ ለህብረተሰቡ እና ለአገሪቷ የተሳካ እንዲሆን ምርቃት አድርሰዋል።ዘመኑ ሁሉም አንድነቱን ጠብቆ በሰላምና በፍቅር ተከባብሮ የሚኖርበት እንዲሆንም ተመኝተዋል።የበዓሉ ታዳሚዎች በባህሉ መሰረት ባህላዊ ዜማዎችን እያዜሙ፣ የልምላሜ ምልክት የሆነውን እርጥብ ቄጤማና አደይ አበባ በመያዝ ወደ ሀይቁ ወርደው በዓሉን በሰላም አክብረው ተመልሰዋል።የኢሬቻ በዓል ከኦሮሞ ህዝብ ሁለንተናዊ ህይወትና እድገት ጋር ቁርኝት ካላቸው መገለጫዎች መካከል የሚጠቀስና የሰላም፣ የብልፅግና እና የመዋደድ ትርጓሜ ያለው፣ ለአምላክም ምስጋና የሚቀርብበት  ነው።(ኢዜአ)", "passage_id": "c81af60f65a05221e6c513ed9663d157" }, { "passage": " አዲስ አበባ፦ የኦሮሞ ህዝብ ከሌሎች የኢትዮጵያ ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች የተለየ ጥያቄ እንደሌለው በኦሮሚያ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታዬ ደንደአ አስታወቁ ።መላው ህዝብ ይህንን በመረዳት አንድነቱን ማጠናከር እንዳለበት አሳሰቡ ።አቶ ታዬ ደንደአ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት፤ በ1960ዎቹ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ትግል ጀምሮ የኢትዮጵያውያን ሶስት ዋና ጥያቄዎች እንደሚጋሩ አመልክተዋል። ከፊውዳል የመሬት ስሪት ጋር ተያይዞ ‹‹መሬት ላራሹ›› ፤ ሁለተኛው የማንነት ጥያቄዎች፣ በቋንቋ የመማር፣ የመዳኘት፣ የመስራት፣ ባህልን የማሳደግ እና የዴሞክራሲ ጥያቄ አንዱ መሆኑን ተናግረዋል።ጥያቄዎቹ የኦሮሞ ህዝብ\nበየወቅቱ ያነሳቸውን የታገለባቸው\nብዙ ዋጋም የከፈለባቸው\nእንደሆኑ ያመለከቱት አቶ\nታዬ፣ የኦሮሞ ህዝብ\nከዚህ የተለየ ጥያቄ\nየለውም ፤ ኖሮትም\nአያውቅም ፣ እንዳለው\nአድርገው የሚያቀርቡ ኃይሎች\nይህን የሚያደርጉት ሕዝብን\nለማደናገር እንደሆነም አመልክተዋል። ዞሮ ዞሮ የመሬት ጥያቄውም፣ የማንነት ጥያቄዎቹም፣ በተሟላ መልኩ ሊመለሱ አልቻሉም ያሉት ኃላፊው፣ ምክንያቱ ደግሞ የዴሞክራሲ ጥያቄ ባለመመለሱ ነው ብለዋል ። የመንግሥት ባለስልጣናትን ጨምሮ ሁሉም ዜጎች ከህግ በታች ሆነው ለሕግና ለህግ ብቻ በመታመን ፍላጎታቸውን ማንጸባረቅ መቻል ነበረባቸው ፤ ይህ ግን ሊሆን አልቻለም ሲሉም ተናግረዋል ። የመሬት ጥያቄው መልስ ያገኘ ቢመስልም ተመልሶ መሬት የሕዝብ ነው የሚለውን መርህ በመጠቀም አንተ እኮ እንደግል መብት የለህም በማለት አርሶ አደሩን ያላግባብና ያለበቂ ካሳ ማፈናቀል፣ አንዳንዴ ደግሞ በግድ በጉልበት የተፈጸሙ ግፎችም እንደነበሩ አስታውቀዋል። የሰብዓዊ መብቶች፣ የዴሞክራሲ መብቶች ህገ መንግሥቱ ቢያረጋግጥም ማክበር ላይ የከፋ ውስንነት ነበረው። የተዘረጋው የፌዴራሊዝም መዋቅርም ከስም ባሻገር ክልሎች ራሳቸውን በራሳቸው ማስተዳደር አልቻሉም። ከላይ ‹‹ክልል ነህ›› ይባላሉ በውስጥ መስመር ግን አቅም ያለው የፈለገውን ሲያደርግ እንደነበርም አመልክተዋል ።ሰው መግረፍና ማንገላታት ሕገ መንግሥቱ ይከለክላል። ዜጎች እኩል መሆናቸውን ህገ መንግሥቱ በአንቀጽ 25 ያረጋግጣል። ኢትዮጵያ ውስጥ ግን ለአንዳንዶች የተሻለ ዕድል ለሌሎች ደግሞ የከፋ ግፍ ሲፈጸምባቸው እንደነበር ማንም ያውቃል ብለዋል። ግድያ ይፈጸም ነበር፣ ያለጥፋት እስርና መኮላሸት ነበር ይህንን ማንም ሊክድ አይችልም ያሉት ኃላፊው፤ ነጻነት እንዲኖር ህገ መንግሥቱ ይከበር ብለህ ስትጠይቅ ደግሞ በአሸባሪነት ተፈርጀህ የምትከሰስበት ሁኔታ የቅርብ ጊዜ ትዝታ መሆኑንም አስታውቀዋል ። የፖለቲካ ምህዳሩ ሁሉንም በሚያሳትፍ መንገድ መስፋት አለበት፣ ሰብዓዊ መብቶች መከበር አለባቸው በሚል ከፍተኛ መስዋዕትነት ተከፍሏል ያሉት አቶ ታዬ፤ ለእዚህም ሌሎችም መሰል ጥያቄዎች ምላሽ ፍለጋ ወጣቶች በቄሮ በፋኖ፣ በዘርማ፣ በኤጀቶ ተደራጅተውና ተናብበው ታግለው ግፈኛ አሰራር መስመር አስይዘው ለውጥ እንዲመጣ አድርገዋል ብለዋል ። አሁን ትልቁ ለውጥ የዴሞክራሲ ነው። ስለነጻነትና ሰብዓዊ መብት ሲከራከሩ የነበሩና በእዛ ምክንያት የታሰሩ ዜጎች እንዲፈቱ መደረጋቸውን አመልክተው፤በፖለቲካ ምክንያት የተሰደዱ ዜጎች፣ ፖለቲከኞና የፖለቲካ ድርጅቶች አንዳንዶቹ ለ50 ዓመታት አገራቸውን መርገጥ ያልቻሉ ወደ እናት አገራቸው መመለስ እንዲችሉ በር መከፈቱን አስታውቀዋል። ከአቶ አቶ ታዬ ደንደአ ጋር የተደረገውን ቃለ ምልልስ ሙሉውን\nቃል በገጽ ስምንት ይመልከቱ።አዲስ ዘመን ግንቦት 17/2012 ዘላለም ግዛው", "passage_id": "b5453f2d39180db7b0bf27eae049e09d" }, { "passage": "የአንድ ማህበረሰብ ልማድ፣ ወግና ባህላዊ ክዋኔ የብዙ ሰዎችን ተሳትፎ የሚፈልግ ነው፡፡ ስለሆነም ባህል ሰዎችን የማግባባት ሚና አለው፡፡ በመዲናችን የሚከበረው የኢሬቻ በዓል የተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች ተገኝተው የሚያከብሩትና የሚሳተፉበት በዓል ነው፡፡ በዓሉ በአዲስ አበባ መከበሩ ለህዝቦች አንድነት ምን አበርክቶ አለው? ባህል ከሰው ልጆች ጋር ጥብቅ ቁርኝት ያለውና የማንነት መገለጫ\nእንደሆነ የዘርፉ ተመራማሪዎች ያስረዳሉ፡፡ በሲቲ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ኒዎርክ ‹‹The value of culture in peace\nbuilding- ባህል ለሰላም ግንባታ ያለው ዋጋ›› በሚል ርዕስ ጥናት ያደረጉት ዶራታ ፒትሮስካ እንደሚሉት ሰዎች ማንነታቸውን\nከሚገልፁበት መንገድ አንዱ ባህል ነው፡፡ ባህል የማንነት መገለጫ ብቻ ሳይሆን ሰዎችን አቅፎ መያዝ የሚችል ማህበራዊ መዋቅር ነው፡፡\nበኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የቅርስ ጥናት ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ስንታየሁ ቶላ እንደሚያስረዱት ኢሬቻ ለኦሮሞ ህዝብ\nሁሉን ነገር ማለት ነው፡፡ እንስሳትና ዕጽዋትን፣ ሰማይና ምድርን፣ ቀንና ሌሊትን፣ ወዘተ ለፈጠረ ዋቃ/ አምላክ / ምስጋናና ክብር\nየሚያቀርብበት ባህላዊ ሥርዓት ነው፤ ኢሬቻ፡፡ በመሆኑም በዓሉ ሰው ለተሰጠው ፀጋና በረከት፣ ሰላምና ደስታ፣ ጤናና ዕድሜ፣ ፍቅርና\nክብር፣ ምስጋና ያቀርባል፡፡ ዓመቱን ጨርሶ ወደ ቀጣዩ ዘመን ሲሸጋገርም መጪው ዘመን የሰላምና\nየደስታ እንዲሆንለት አምላኩን የሚማፀንበት ባህላዊ ሥርዓት ነው ኢሬቻ፡፡ ወንድ፣ ሴት፣ ህፃን፣ ሽማግሌ ሳይለይና የፖለቲካ አመለካከትና\nየሃይማኖት ልዩነት ሳይኖር፣ የጊዜና የቦታ ርቀት ሳይገድብ ሁሉም በአንድ ላይ ሆኖ የሚያከብረው ባህላዊ ሥርዓት ነው፡፡ አቶ ስንታየሁ እንደሚገልፁት ኢሬቻ ፍልስፍናው ሰላምን፣ ፍቅርን፣\nመቻቻልን፣ ይቅርታን፣ እርቅን የሚሰብክ በመሆኑ በህዝቦች መካከል አንድነትን ይፈጥራል:: በዓሉ በአዲስ አበባ መከበሩም በመዲናዋ\nየሚገኙ በርካታ ብሔረሰቦች ስለ ባህሉ ግንዛቤ እንዲኖራቸውና ከተሳሳተ ትርጉም እንዲወጡ ትልቅ አቅም አለው ይላሉ፡፡ ከኦሮሞ ህዝብ ውጭ ያሉ ማህበረሰቦችም  ይህን ባህል እንደራሳቸው\nእንዲቆጥሩት ይረዳል፡፡ ኢሬቻ በልብ ንጽህና ስለሚከበር ቂም በቀል፣ ጥላቻና ክፋት ቦታ አይኖራቸውም፤ ይልቁንም የተጣሉ ይታረቃሉ፤\nበመሆኑም የታሰበውን ሀገራዊ አንድነትና ሰላም ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ትልቅ እሴት በመሆኑ ሁሉም የማህበር ክፍል የእኔ ብሎ\nሊጠቀምበት እንደሚገባ አቶ ስንታየሁ ያሳስባሉ፡፡ ኢሬቻ የመረዳዳት፣ አንዱ አንዱን የማክበር፣ የፍቅርና የአንድነት መማማርያ መድረክ ነው፡፡ የሰላም፣ የወንድማማችነት፣\nየፍቅር የመተማመንና የመተባበር መንፈስ ኢሬቻ ውስጥ ይገኛል፡፡ ዩኔስኮ የዓለም ሀብትነው ብሎ በቅርስነት ሊመዘግበው ያሰበውን ይህን\nእሴት የኢትዮጵያ ህዝብም የእኔ ሀብት ነው ብሎ ከቱሩፋቱ ሊጠቀም እንደሚገባ አቶ ስንታየሁ ይመክራሉ፡፡ ይህን ፍቅርና ሰላም የሚቀዳበትን\nሀገር በቀል ባህል በመያዝ ህዝቦች ልዩነቶቻቸውን ማጥበብ ይኖርባቸዋልም ብለዋል፡፡ ባለንበት ወቅት ኢትዮጵያ በለውጥ ጎዳና ላይ እንደምትገኝ የገለፁት አቶ ስንታየሁ ወደ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት\nለመሸጋገርና እና በሰዎች መካከል የሚፈጠረውን የርዕስ በርዕስ አለመግባባትን ለማስወገድ ኢሬቻ የሰላም ተስፋን እንደሚያሳይ ተናግረዋል፡፡\nዶራታ ፒትሮስካ በሚለው ጥናታዊ ጽሁፋቸው እናዳስረዱት ‹‹በህዝቦች መካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችንና ግጭችን\nበባህላዊ እሴቶች አማካኝነት ማስወገድ እንደሚቻል ከተለያዩ አገራት ተሞክሮ መረዳት ይቻላል፡፡ ባህላዊ እሴቶች አዎንታዊ አስተሳሰቦች\nእንዲጎለብቱ በማድረግ ማህበራዊ አንድነትን የማጠናከር ሚና አላቸው›› ይላሉ፡፡ የኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ኃይሉ በበኩላቸው እንዳስረዱት የኢሬቻ ሆራ ፊንፊኔ በዓል በመዲናዋ\nአዲስ አበባ መከበሩ በህዝቦች መካከል ጥብቅ ግንኙነት ለመፍጠር አጋዥ ነው:: በዓሉ የኦሮሞ ህዝብ ባህል ቢሆንም ፍቅር፣ አንድነትና\nሰላም ማጠንጠኛዎቹ በመሆናቸው ማንኛውም ሰው በመታደም በረከቱን እንዲቋደስ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በሀገሪቱ የሚገኙ ሌሎች ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦችም በራሳቸው ባህላዊ አለባበስ ደምቀው\nከኦሮሞ ህዝብ ጋር በዓሉን ማክበራቸውን ያስታወሱት ኃላፊው ዘንድሮ በአዲስ አበባ የሚከበረውን በዓል የከተማዋን ነዋሪዎች አሰባስቦ\nስለ ሰላምና ፍቅር ለመዘመር ጥሩ አጋጣሚ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ በዓሉን ለማክበር ወደ ከተማዋ የሚመጡ ታዳሚዎች ለትራንስፖርት ለምግብ፣ ለማረፊያና ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚያወጣው\nገንዘብ ኢኮኖሚውን እንደሚያነቃቃውና የቱሪስቱን ቁጥር እንደሚያሳድገውም ተናግረዋል፡፡ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሺመልስ አብዲሳ እንደገለፁት የኦሮሞ ህዝብ የኢሬቻ በዓልን በአዲስ\nአበባ ከተማ ከኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ጋር ሆኖ ለማክበር መዘጋጀቱ ትልቅ ዕድል ነው:: የሀገሪቱ ህዝቦች ባህላቸውን በነፃነት\nለማስተዋወቅ ያነሱት የነበረው ጥያቄ መልስ ለማግኘቱ አንድ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ቀደምሲል በኦሮሚያ ባህል ማዕከልና በተለያዩ የከተማዋ\nቦታዎች ይህንን በዓል ለማክበር ሙከራ እንደተደረገ የገለፁት ምክትል ርዕሰ መስዳድሩ አሁን እንዲህ ባለ ሁኔታ ለማክበር መብቃት\nትልቅ ስኬት ነው ብለዋል፡፡ ኢሬቻ የአንድነት የሰላምና የፍቅር በዓል በመሆን ለሀገራችን መልካም አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት የተናገሩት\nአቶ ሺመልስ እሴቱን ለዓለም ማስተዋወቅ የተወሰኑ አካላት ድርሻ ብቻ ተደርጎ መታየት እንደሌለበት አስረድተዋል፡፡ እንዲህ ዓይነቱን\nባህል ማጠናከር ከውጭ የሚመጣውን ቱሪስት ብቻ ሳይሆን የሀገር ውስጥ የቱሪስት አቅምንም የሚያበረታታ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ በመጨረሻም የኦሮሞ ህዝብ በዓሉን ሲያከብር አብሮነትን በሚያሳይና ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ባቀፈ መንገድ እንዲከብር\nአሳስበዋል፡፡ በዓሉን ለማክበር የሚታደመው ሁሉም ብሔር ብሔረሰብ የባህል ልብሱን በመልበስ እንዲያከብረውና የትኛውንም የፖለቲካ\nአቋም ከማንፀባረቅ መቆጠብ እንዳለበት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ በአጠቃላይ አስተያየት ሰጪዎቹ እንዳስረዱት አብዛኞቹ ባህላዊ\nእሴቶቻችን በህዝቦች መካከል ፍቅር እንዲደረጅ፣ አንድነት እንዲጎለብት የማድረግ አቅም አላቸው፡፡ ሁሉም ማህበረሰብ ከራሱ ውጭ ላሉ\nባህሎችም ዕውቅና በመስጠት ማህበራዊ መስተጋብሩን ማጠናከር ይኖርበታል፡፡ እንዲህ ሲሆን ማህበራዊ ትስስርና አንድነት ይፈጠራል፤\nቂምና ጥላቻ ከሀገር ጠፍቶ ሰላም ይሰፍናል፤ የሀገር ገጽታ ይቀየራል፤ ብልጽግና ይመጣል፡፡አዲስ ዘመን መስከረም 15  ቀን  2012\nዓ.ም ኢያሱ መሰለ", "passage_id": "b3eb41a86be0df78821f3ae6232a6ed7" }, { "passage": "የኦሮሞ ገዳ ሥርዓት አካል የሆነው የኢሬቻ በዓል በሆራ ፊንፊኔ በገዳ ሥርዓት መሰረት በአባ ገዳዎች ምርቃት ተጀምሮ በድምቀት ተከብሯል፡፡  ከአዲስ አበባ እና ዙሪያዋ እንዲሁም ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ለበዓሉ በባህል አልባሳት ደምቀው ሆራ ፊንፊኔ ላይ የተገኙት የኦሮሞ እና የሌሎች ብሔር ብሔረሰቦች ተወላጆች ኢሬቻውን በአንድነት መንፈስ በጋራ አክብረውታል፡፡በኢሬቻ በዓል የኦሮሞ ሕዝቦች ላገኙት ፀጋና በረከት፣ ሰላምና ደስታ፣ ጤናና ዕድሜ፣ ፍቅርና ክብር፣ ብርሃንና ተሥፋ፣ ከአንድ ወቅት ወደ ሌላ ወቅት በአጠቃላይ ከዘመን ወደ ዘመን በሰላም ላሸጋገራቸው አንድ አምላካቸው – ለዋቃ – ከመዲናዋ እና ከተለያዩ የሀገሪቱ አቅጣጫዎች የተሰባሰቡ ዜጎች በተለያዩ የኦሮሞ ባህላዊ ልብሶች ደምቀው በሆራ ፊንፊኔ ለፈጣሪያቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡በርካታ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችም ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን በዓሉ በሰላም እንዲከበር ጉልህ አስተዋፅዖ ማበርከታቸው ታውቋል፡፡  የገዳ ስርዓት በውስጡ ካቀፋቸው ክንዋኔዎች መካከል አንዱ የሆነው የኢሬቻ በዓል በአዲስ አበባ ከ150 ዓመት በኋላ ዘንድሮ ሲከበር የመጀመሪያው ነው።በዓሉ በተለያዩ ቦታዎች የሚከበር ሲሆን፥ የኦሮሞ ህዝብ የማንነቱ መገለጫ የሆነውን በዓል በአንድ ላይ ተሰብስቦ በየዓመቱ የመስቀል/ጉባ/ በዓልን ተከትሎ ባለው የመጀመሪያ እሁድ ቢሾፍቱ በሚገኘው ሆረ አርሰዲ ያከብራል።ኢሬቻ በዓመት ሁለት ጊዜ ይከበራል፤ በበጋ ወቅት በከፍታ ቦታ ላይ የሚከበር ወይም ኢሬቻ ቱሉ እንዲሁም በጸዳይ ወቅት መግቢያ ላይ በወንዝ ዳር የሚከበረው ወይም ኢሬቻ መልካ በመባል የሚታወቅ ነው።   ", "passage_id": "76f13270fe58a7c681265638181d0af6" } ]
c7605dc8f55917fe288965ab3fbaca16
cd8058a8504575ba62115ec67b27c8ff
ጥምቀትና ሎሚ
ጥምቀት በህብረ ቀለማት ያሸበረቀና በልዩ ልዩ ክንዋኔዎች የተሞላ፤ ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚሳተፍበት፤ እንደሌሎቹ በዓላት በቤት ውስጥ የተገደበ ሳይሆን በአደባባይ የሚከበር ብዙዎች በጋራ የሚታደሙበት ክብረ በዓል ነው። ከሃይማኖታዊ ሥርዓቱ ባሻገር ባህላዊ ወግና ሥርዓቶችን አጣምሮ ያቀፈ፤ ከከተራ አንስቶ እስከ ጥምቀት ዕለቱ የተለያዩ ትዕይንቶች የሚስተናገዱበት ታላቅ በዓል ነው። በተለያዩ የተዋቡ አልባሳት የደመቁ ካህናትና ዲያቆናት በዓሉን ያደምቁታል። «ለጥምቀት ያልሆነ ቀሚስ ይበጣጠስ» እንደተባለው ሁሉ፤ በበዓሉ ለመታደም ከተለያዩ ስፍራዎች የመጡ ምዕመናን ከሌላ ክብረ በዓላት በተለየ መልኩ አዳዲስ አልባሳትን በመልበስ፤ አለበለዚያም ያላቸውን በደንብ አጥበው ለብሰው አምረው፣ አጊጠውና ደምቀው ታቦታቱን ያጅባሉ። በተለያየ የዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ የበዓሉ ታዳሚዎች በቡድን በቡድን ሆነው የተለያዩ ሃይማኖታዊና ባህላዊ ህብረ ዝማሬዎችና ጭፈራዎች ያከናውናሉ። እንደየአካባቢ ባህል የአከባበር ሥርዓቱ ቢለያይም ወጣቶች በአንድነት የሚያሳዩት ትዕይንት፤ ህብረ ቀለማዊ ጨዋታቸው በልዩ ልዩ ቋንቋዎች የሚያቀርቡበት መንገድ ልብ ይማርካል።በዓሉ የሰው አእምሮን በመግዛት ጥሎት በሚያልፍው አይረሴ ትዝታ አጓጊና ተናፋቂ ከመሆኑም ባሻገር፤ ስዕላዊ እይታ ይፈጥራል። ዘፈኖች፣ ጭፈራዎችና ውዝዋዜዎችም ይከወኑበታል። የሌላ እምነት ተከታዮችም ትዕይንቶቹን ለመካፈል ወደ በዓሉ ስፍራ ይነጉዳሉ። ለወጣቶች በትዳር ለመተጫጨት በር ከፋች መሆኑ የሚነገርለት የጥምቀት በዓል፤ ከድሮ ጀምሮ ሲወርድ ሲዋርድ የመጣው የሎሚ ውርወራ ታሪክም ከዚህ ጋር አብሮ መነሳቱ አይቀሬ ነው። በማህበረሰቡ እንደሚታወቀው በአብዛኛው የጥር የጋብቻ ወር ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የመተጫጫው መንገዶች ቢለያይም ጥምቀት ግና ዋነኛው ነው። ጥምቀትና ሎሚ የማይለያዩና አብረው የሚነሱ መሆናቸው ለመተጫጨት በሚፈልጉ ሁለት ጥንዶች መካከል የሚከወኑ ክዋኔዎች አንድ ስለሚያደርጋቸው ነው። ሎሚ ወርዋሪው ጉብል የሚፈልጋትንና ልቡ የከጀላትን ወጣት ካገኘ ይወረውርና ፍቅሩን ይገልጻል። በዕለቱ አምረው የሚገኙት ወጣቶቹ አጋጣሚውን ወደ መልካምነት በመቀየር አብረው ይጫወታሉ፤ ይደሰታሉ። ጥምቀት ላይ ተጫጭተው ለትዳር የበቁ፤ ወልደው የከበዱ፤ ጥንዶች ብዛት ቤቱ ይቁጠረው እንጂ ስለ ብዛቱ ለመተንበይ ጥናት ይጠይቃል። ይህ ባህል በገጠር አካባቢ ትውፊትነቱ በተወሰነ መልኩ ቢቀየርም ዛሬም ድረስ የሎሚ ውርወራና የመተጫጨት ተግባር የሚከወንባቸው አካባቢዎች አሉ። ይህ ባህላዊ የመተጫጫ ክዋኔ የትወናና ስነቃል ወጉን ጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የኖረ ነው። ዛሬ ዛሬ ይህ ደማቅና ተናፋቂ ባህል እየተረሳ፤ የእኛ ባልሆኑ መጤ ባህሎች እየተተካ መሄዱ፤ የአደባባይ ምስጢር ከሆነ ውሎ አድሯል። ይህ ለምን ሆነ? ብሎ የሚጠይቅ ባለመኖሩ በወረርሽኝ ልማዶች የተጠመዱ ወጣቶች ባህላቸውን ረስተው ርቀው ከሄዱ ሰነባብተዋል። የወጣቶች ለትዳር መተጫጨት እንዳለ ሆኖ የተረሳው ግን የሎሚው ጉዳይ ነው። አብዛኞቹ ወጣቶች ስለሎሚ ሲጠየቁ ይህ ‹ቀርቶ ሌላ ዘፈን መጥቶ› ዓይነት ምላሽ ይሰጣሉ። ወጣቱ በሎሚ ፈንታ፤ በአፕል ስልክና በሊሞዚን ቁልፍ እየተተካ መሆኑን ከመናገር ባሻገር አፕሉም ሆነ የሊሞዚን ቁልፉ ሲወረወርና ጥንዶች ሲያስተጫጩ አይታዩም። ሎሚን የቀየረውስ አፕል በምን ተመርጦ ነው? ለሚለው ጥያቄም ወጣቶች ምላሽ ከዘመናዊነት ጋር ከማያያዝ በዘለለ የሚሰጡት አጥጋቢ ምላሽ የለም። ጥምቀት ሲመጣ አሁን አሁን በተለየ መልኩ ወጣቱን ሲማርከው የሚስተዋለው እና ሳይነሳ መታለፍ የሌለበት በአዲስ አበባ በጃንሜዳ የሚታየው የሀርሞኒካ ጭፈራ ነው። ይህንን የሚቃወሙ ቢኖሩም እንዴት እና ከየት መጣ? ቢቀጥልስ ምን ጥቅምና ጉዳት ሊኖረው ይችላል? የሚለውን ለአጥኚዎች እንተወውና ወደ ዋና ጉዳይ ስንመለስ የሎሚ ውርወራንና የጥምቀት በዓልን በማስተሳሰር ሎሚው እና በዓሉ ወደ ፌስቲቫል በማሳደግ፤ ለቱሪዝም መስብህነት በመጠቀም፤ ባህል በማስተዋወቅ፤ የገቢ ምንጮችን ለማሳደግ የሚቻልበትን መንገድ ለመፍጠር መጣር ግድ ይላል። የጥምቀት በዓል በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና ባሕል ድርጅት ዩኔስኮ በቅርቡ በማይዳሰሱ ባህላዊ ቅርሶች ተመድቦ ዓለምአቀፍ እውቅና ማግኘቱና መመዝገቡን ይታወቃል። ይህንንም ተከትሎ የዘንድሮውን በዓል ለማክበርና ለመታደም ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጭ የሚመጡ በርካታ ቱሪስቶች ይኖራሉ። ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም ከሃይማኖታዊ ሥርዓት ባሻገር ባህላዊ እሴትን በማሳደግ እና በማስፋት ለቱሪዝም መስህብነት በማዋል ትርፋማ መሆን ይቻላል በማለት የጠፋው የሎሚ ባህል ተመልሶ የቱሪስት መስህብ ሆኖ ለመገናኘት ያብቃን እያልን በዚሁ እንሰናበታቸሁ በቸር ያገናኝን። አዲስ ዘመን ጥር 11 /2012 ወርቅነሽ ደምሰው
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=25918
[ { "passage": "አዲስ አበባ:- የጥምቀት በዓል አከባበርን፣ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሳይንስ የትምህርትና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) የማይዳሰስ ባህላዊ የዓለም አቀፍ ቅርስነት በወቅቱ እንዲመዘግበው የተጀመረው ጥረት መጠናከር እንዳለበት የበዓሉ ተሳታፊዎች ገልጸዋል።በአዲስ አበባ ጃንሜዳ በተከበረው የጥምቀት በዓል ላይ የተሳተፉ ትውልደ ኢትዮጵያውያን መካከል አንዱ የሆነው አቶ ኪሩቤል ነጋሽ እንደገለጸው፤ እንደ ኢትዮጵያ ዓይነት ትልቅ ጥምቀት ፌስቲቫል በዓለም አይገኝም። በመሆኑም ክብረ በዓሉን በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ ከፍተኛ ጥረት ማድረግ ይገባል።እንደ አቶ ኪሩቤል ገለጻ፤ ጥምቀት በርካታ ህዝብ በአንድነት ወጥቶ በአደባባይ የሚያከብረው እና ሃይማኖታዊ ክንዋኔው ለየት ያለ ነው። በመሆኑም በዓለም ቅርስነት አስመዝግቦ ኢትዮጵያንም ለሌላው ዓለም ይበልጥ በበጎ ጎን እንዲያውቃት ማድረግ ይገባል። ነጮች አንድ ታሪክ እና ስርዓት ካላቸው ያንን ተጠቅመው እራሳቸውን ለማስተዋወቅ የሚያደርጉት ጥረት ከፍተኛ ነው። በኢትዮጵያም ይህን ልምድ በመከተል ጥምቀትን በማይዳሰስ ቅርስነት በማስመዝገብ መጠቀም ያስፈልጋል።በቤተሰቦቹ ኢትዮጵያዊ ደም ያለው አሜሪካዊው ወጣት ናቲና ሊዮ እንደሚገልጸው ደግሞ፤ የጥምቀት አከባበር ለተመልካቹ ሳቢ እና ከሌላው ዓለም ለየት ያለ ስርዓት ያለው ነው። በመሆኑም የበለጠ እንዲታወቅ የሚያደርጉ የቅርስ ምዝገባ ሥራዎች ያስፈልጉታል። ከዚህ ውስጥ ደግሞ የዩኔስኮ ምዝገባ አንዱ በመሆኑ በወቅቱ ጥምቀትን በዓለም ቅርስነት ማስመዝገብ ይገባል። ለዚህ ሥራ አሁን ካለው በላይ በውጭ እና በአገር ውስጥ ያሉ ሰዎችን አስተባብሮ ተጨማሪ ጥረት ማድረግ ይገባል ብሏል።በበዓሉ ላይ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ ባዬ እንደገለጹት፤ጥምቀት ለአፍሪካም ለዓለም ህዝቦች በአግባቡ ሊያውቁት የሚገባ ስርዓትና ባህል ነው። የጥምቀት አከባበርን በዓለም የዩኔስኮ የቅርስ መዝገብ ለማስፈር የሚደረገው ጥረት ታላቅ ድጋፍ ይፈልጋል።በሚቀጥሉት አጭር ዓመታት የጥምቀት የማይዳሰስ ቅርስነት ምዝገባው እውን እንደሚሆን እንተማመናለን ያሉት ረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ፣ «ለዚሁ ሥራ መላው ህዝብ እና የዓለም መሪዎች እንዲሁም የሃሳብ አፍላቂዎች ጭምር ከጎናችን እንዲቆሙ ጥሪ እናስተላልፋለን» ብለዋል።\nእንደ ኃላፊው ገለጻ፤ በአትዮጵያ የጥምቀት በዓል ከጀመረ 1ሺ 600 ዓመት በላይ እንዳስቆጠረ ድርሳናት ያመለክታሉ። በአዲስ አበባ ደግሞ ልክ እንደ አሁኑ ሥርዓት ተበጅቶለት በሃይማኖታዊ ሥርዓት መከበር ከጀመረ 130 ዓመታትን እንዳስቆጠረ ታሪክ ያስረዳል። በበዓሉ ወቅት የሚታዩት ሃይማኖታዊና ባህላዊ ትውፊቶች፤ ስነቃሎች አለባበሶች እና ዝማሬዎች እና ሌሎችም የኢትዮጵያን የዘመናት ስልጣኔ የሚፈትነው ናቸው። የጥምቀት በዓል ሥርዓት ተበጅቶለት እና የኢትዮጵያውያን ትውፊት ሆኖ የዘለቀ ህዝባዊ በዓል ነው። በመሆኑን በዩኔስኮም ለማስመዝገብ የሚደረገው ጥረት ይቀጥላል።የዛሬ ዓመት ልክ በዚሁ ወቅት የጥምቀት በዓል አከባበር በዓለም የማይዳሰሱ ቅርሶች መዝገብ እንዲመዘገብ አስፈላጊውን መረጃዎች ለዩኔስኮ መላኩ ተገልጾ ነበር። በጎንደር፣ በአክሱም፣በላልይበላና በአዲስ አበባ ጃንሜዳ ያለውን የጥምቀት በዓል አከባበርን የሚያሳዩ የፎቶግራፍ፣ የጽሑፍ፣ የተንቀሳቃሽ ምስልና የድምጽ መረጃዎች ተደራጅተው ለዩኔስኮ ገምጋሚ አካል መላካቸው የዛሬ ዓመት የቀድሞው ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ነው።አዲስ ዘመን ጥር 12/2011ጌትነት ተስፋማርያም", "passage_id": "aab1debae6d4858f960e9bf3cd0eed3e" }, { "passage": "በንግስተ ሳባ (አዜብ ዘመነ መንግሥት) ከክርስቶስ ልደት በፊት በ950 ዓመተ ዓለም ቀዳማዊ ምኒልክ የሌዊ ነገድ ከሆኑት 12 ሺህ እስራኤላውያን ጋር በመሆን ታቦተ ጸዮንን በመያዝ በኤርትራ ማይብላ አድርጎ ቀይ ባህርን አቋርጦ አክሱም እንደመጣ ጥንታዊ የብራና መጻሕፍትና የታሪክ ምሁራን በጸሑፋቸው አስፍረዋል። ወቅቱም ‹‹አሸንዳ›› የሚባለው ለታቦት ክብር የሚነሰነስ ከለምለም ሣሮች ሁሉ ረጅምና ሰፋ ያለ የሣር ዓይነት የሚበቅልበት ስለነበር እናቶች በመታጠቅና በመጎዝጎዝ ተቀብለውታል። የአሸንዳ በዓል ጅማሮ ከዚህ እንደሆነም ይነገራል። ታቦቱ አክሱም ከገባበት\nወቅት እስከ 87 ዓ.ም\nድረስ ‹‹አሸንዳ›› በመባል\nይጠራ ነበር። ከቅድስት\nድንግል ማርያም እረፍት\nከዚያም እርገት በኋላ\nበ340 ዓ.ም መታሳቢያነቱን ለማሳየት በወቅቱ ነገስታት በመወሰኑ ምክንያት ‹‹ማርያ›› በመባል ይከበር ጀመር። በአሁኑ ወቅትም በአክሱም ዓይኒዋሪ፣ በኤርትራ ማርያ እንዲሁም በተለያዩ የትግራይ ክልል አካባቢዎች በእነዚህ ስያሜዎችና አሸንዳ በመባል ይከበራል። በትናትናው ዕለትም ከነሐሴ 14 እስከ መስከረም 17 ድረስ በድምቀት በሚከበረው በበዓሉ የአሸንዳ ልጃገረዶች እየጨፈሩ ወደ ሚሌኒየም አዳራሽ ገብተዋል። ልጃገረዶቹ ጋሜና ሌሎች ለበዓሉ የሚሆኑ የጸጉር አሰራር ተሰርተው፣ በላዩ ላይ የተለያዩ ቀለማት ያላቸው ክሮች በመርፌ ቁልፍ አስይዘዋል። በተመሳሳይ በግንባራቸው በተለያዩ ቀለማት የተገመደ ክር(ስንዲድ) አስረዋል። የዓይን ቆባቸው እስከ ቅንድባቸው ከቅቤ ጋር የተለወሰ ስር ኩል ደምቆ ተኩሏል። አንገታቸው ላይ የተለያየ መጠን ያለው መስቀል ያሰሩ ሲሆን፤ ከላይ ዝብጦ ቀጥሎ መካከለኛ ከታች ደግሞ ትልቅ መስቀልን\nበሦስት ደረጃ አስረዋል።\nእጃቸው በአምባር/ ዱከት/\nበአልቦ ያሸበረቀው እግራቸው\nደግሞ ኮንጎ ጫማን\nተጫምቷል። በአንገታቸውና በእጃቸው\nበኩል አሾልከው በተለያዩ\nቀለማት የተገመደ ክር(ድሪ)\nአጥልቀዋል። ጥልፍ ቀሚሳቸው\nላይ ሸብ ባደረጉት\nመቀነት ያሰሩትን አሸንዳ\nከግራ ወደ ቀኝ\nእያወዛወዙ ያዜማሉ።‹‹መጽአት መጽአት አሸንዳ ዕንበብ መጽአትአሸንዳ ናይ ዓሚ ናይ ዓሚየተጋኒና ሎምየ›› እያሉ ሲያዜሙ ይሰማሉ። በአማርኛ ትርጓሜውም አምና ያከበርኩሽ አሸንዳ ዘንድሮም አገኘሁሽ እንደ ማለት ነው። ተነፋፍቀው ያገኟቸውን ጓደኞቻቸውንም ሠላምታ እየተለዋወጡ ወደ ሚሌኒየም አዳራሽ ገብተዋል።‹‹አሸንዳ ለሠላማችን፣ ለአንድነታችና ለልማታ ችን›› በሚል መሪ ቃል በሚከበረው የአሸንዳ በዓል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ አባ ገዳዎች፣ የውጭ አገር ዲፕሎማቶች ተገኝተዋል። ለቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊና ለተሰው ሰማዕታት የህሊና ጸሎት የተደረገ ሲሆን፤ መድረኩም በታዋቂ ድምጻውያን ደምቆ አምሽቷል። የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማ ከትግራይ ሴቶች ማህበር አዲስ አበባ ቅርጫፍ የማስታወሻ ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።ሰናይት ደስታ በዓሉን ለመታደም ከቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ አምስት እንደመጣች ትናገራለች። በዓሉ የተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች በተገኙበት መከበሩ የሠላምና የአብሮነት በዓል ማሳያ ነው። በዚህ ዕለትም ልማቱን ለማስቀጠል ሴቶች ቃል የሚገቡበት እንደሆነ ጠቁማለች።ሌላኛዋ በስፍራው ያገኘናት\nየበዓሉ ታዳሚ መብርሂት ኃይሉ፤ በዓሉ እስከ መስቀል እንደሚቀጥል ትናገራለች። የትግራይ ልጃገረድና ሴቶች የነፃነት ጊዜቸውን የሚያውጁበት የሆነው ይህ በዓል ለዘመናት በጋራ የኖሩ ኢትዮጵያውያን የሚያጋጥማቸውን ችግር በማለፍ ሠላማቸውን የሚጠብቁበት እንዲሆን መልካም አጋጣሚ ነው ትላለች። የአሸንዳ ልጃገረዶች የሠላም አምባሳደር መሆን እንዳለባቸው ገልጻለች።የሠላም ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ አልማዝ መኮንን እንደገለጹት፤ በዓሉ በዚህ መልኩ ደምቆ መከበር የቻለው ተነጻጻሪ ሠላም ስላለ ነው። በመሪ ቃሉ እንደተመለከተው ለአገር አንድነት ወሳኝ የሆኑ ነገሮች የሚገኙት በሠላም በመሆኑ ለሠላም ትኩረት ሊሰጥ ይገባል። በዓሉ ለመልካም ገጽታ ግንባታ ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ በመሆኑ በቀጣይ አገራዊ ልማትና አብሮነት አገርን ለመገንባት ትልቅ አቅም እንዳለው ሚኒስትር ዴኤታዋ ጠቁመዋል። በዚህ በዓል በዋናነት ባለቤት የሆኑት ሴቶች ለቀውስ ቀዳሚ ተጎጂ በመሆናቸው ለሠላም የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።የሴቶችና ሕፃናት ሚኒስትር ወይዘሮ ያለም ፀጋዬና የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር፤ አሸንዳ ሴቶች ነፃነታቸውን የሚያውጁበት ዕለት መሆኑን ተናግረዋል። ለአንድነት ያለው ሚናም ከፍተኛ መሆኑን በመግለጽ፤ ሴቶች በዓሉን ሲያከብሩ የጋራ እሴቶችን በሚያጠናክር መልኩ እንዲሆን ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።አዲስ ዘመን ነሃሴ 27/2011ፍዮሪ ተወልደ ", "passage_id": "b4515ef294937f92333079afd73c38bb" }, { "passage": " ክፍለዮሐንስ አንበርብርጎንደር፡- የጥምቀት በዓል አከባበር፣ ከተራና አጠቃላይ ድባብ ውበት የተላበሰ እና ለቱሪስቶች ምቹ መስህብ መሆኑን ጥምቀትን በጎንደር የታደሙ የውጭ አገር ቱሪስቶች አስታወቁ።የጋዝጣው ዝግጅት ክፍሉ ካናገራቸው የውጭ አገሮች ዜጎች መካከል ከፈረንሳይ እውቅ ከሆኑ መፅሔቶች ሉፊጋ የሚሰራው ጋዜጠኛ ፓስካል ሜት እንዳስታወቀው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ባለው ነባራዊ ሁኔታ ጥምቀትን መታደም አደገኛ እንደነበር ቢነገረውም ጥምቀት በጎንደር ለማክበር መጥቷል፤ በሀገሪቱ ያለው እውነታ በውጭው ዓለም እና በመገናኛ ብዙኃን የተናፈሰውን ያክል እንዳልሆነ መታዘብ ችሏል።‹‹እኔ ጋዜጠኛ ነኝ። መረጃዎችን እጠይቃለሁ፤ አነባለሁ። በዚህም የተነሳ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ ተረድቻለሁ። እስካሁን በሠላም እየተንቀሳቀስኩ ነው፤ የተለየ ነገር አልተመለከትኩም›› ብሏል። የከተራ በዓልና ጥምቀት በዓል ትልቅ የቱሪስት መስብ እንደሆነም ጠቁሟል።ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ የሚሰራው ጋዜጠኛ ሮቢ ኮሪ በበኩሉ፤ ኢትዮጵያ የደማቅ ቅርስ ባለቤት ስለመሆኗ እና ከእነዚህም ውስጥ ጥምቀት አንዱ መሆኑን አመልክቷል። በጎንደር የተከበረው የከተራ እና ጥምቀት በዓል ከሥርዓተ ቅዳሴው እስከ ጥምቅተ ባህር ያለው ሁነት፣ ከባህረ ጥምቀቱ ዙሪያ የቀሳውስቱ ዝማሜ እና በበዓሉ ላይ የሚስተዋለው መንፈሳዊ ሥርዓትና የበዓሉ ታዳሚዎች ሁነት ለፀሐፊዎችና ተመራማሪዎች ብዙ ዕድል የሚሰጥ ነው። ለመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ዘገባም ድምቀት የተሞላበት በዓል መሆኑን መረዳት መቻሉን ጠቁሟል።ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አፍሪካ የመጣችውአሜሪካዊቷ አሽሊ ሄርናንዴዝ፣ የጥምቀት በዓልን በጎንደር መታደሟ ልዩ ስሜት እንደፈጠረባት ገልጻለች። የሕዝቡ በአንድነት መሰባሰብና በህብረ ቀለማት ያሸበረቁ አልባሳት ተውበው ወደ በዓሉ ስፍራ መትመማቸው በእጅጉ አስደናቂ መሆኑንና በሀገረ አሜሪካ ከሚከበሩ ሕዝባዊም ሆኑ ሃይማኖታዊ በዓላት የተለየ መሆኑን ጠቁማለች። ጥምቀት ጥሩ ለዛ ያለው በዓል ሲሆን የልጃገረዶቹ እና ወጣቶች አለባበስ፣ የሥርዓተ ጥምቀቱ ሂደትና አጠቃላይ የከተራ አከባበር የተለየ ስሜት እንደሚሰጥና በርካታ የውጭ አገር ቱሪስቶችን ለመሳብ የሚያግዝ ማራኪ በዓል መሆኑን አመልክታለች። በአሜሪካ በርካቶች ባተሌ ስለሆኑ በዓላትን ከቤተሰቦቻቸው ጋር የማክበር ልምድ እንደሌላቸውና የኢትዮጵያውያን ግን ማህበራዊ ሕይወታቸው የተጠናከረ መሆኑን ተናግራለች። ኢትዮጵያ ከመምጣቷ በፊት ስለ ሀገሪቱ የተሟላ መረጃ እንዳልነበራትና ከመጣች በኋላ ግን የተለየና ጉጉት የሚፈጥር ሕይወት ማየት እንደቻለች አሽሊ አብራርታለች። ፖላንዳዊ ቱሪስት ሚስተር ካሮል ኩስካ፤ ሥርዓተ ጥምቀቱ የሚከናወንበትና የፋሲለደስ ታሪካዊ ግንብና የጥምቀት በዓል መታደሙ ልዩ ስሜት እንደፈጠረበትና ቀጣይ የሰሜን ተራራችን የመጎብኘት እቅድ አለው። በቀጣይ አንድ ሣምንት የተለያዩ የኢትዮጵያ ታሪካዊ እና ባህላዊ እሴቶችን የመጎብኘት ውጥን እንዳለውም ጠቁሟል። በተንቀሳቀሰባቸው አካባቢዎች ፈገግታ የተሞላ ፊት ማየቱ ደግሞ የተለየ ስሜት እንደፈጠረለት አመልክቷል። በቀጣይም ኢትዮጵያን በድጋሜ የመጎብኘትና ጓደኞቹን የመጋበዝ ፍላጎት እንዳለው፤ ስለ ኢትዮጵያም የተቻለውን የማስተዋወቅ ፍላጎት እንዳደረበት ገልጿል።አዲስ ዘመን ጥር 13/2013", "passage_id": "8346729445f3cfd45414739c63bf16ee" }, { "passage": "የቅድስት ማርያም ውቕሮ ገዳም፤ ትግራይ\n\nቅድስት ማርያም ውቕሮ ትባላለች። ወደ አካባቢው ለመድረስ በጣም አስቸጋሪ የጠጠር መንገድና ወንዝ መሻገር የግድ ነው። መኪናችን ወንዙን መሻገር አቅቷት ስትንገዳገድ የተመለከቱት የአከባቢው አርሶ አደሮች ተጠራርተው መንገዱን አስተካክለው አሻግረውናል።\n\nወደ ገዳሙ ቅጥር ግቢ ከተገባ በኋላ መጀመርያ ከአለት የተሰራው ሙዳዬ ምጽዋት ይገኛል። የገዳሙ አስተዳዳሪ ቄስ ዘሚካኤል ወልደጊዮርጊስ ሙዳዬ ምጽዋቱን ከማለፋችን በፊት ጫማችንን እንድናወልቅ ቀጭን ትዕዛዝ አስተላለፉ። \n\nበሰንሰለት ዙርያ ጥምጥም የተቆለፈው የገዳሙን በር ከፍተው አስገቡን። የበሩ መዝጊያ ከአንድ የዛፍ እንጨት ብቻ እንደተዘጋጀ ለመረዳት አይከብድም።\n\nቄስ ዘሚካኤል፤ ገዳሟ መቼና እንዴት እንደተቆረቆረች ይናገራሉ።\n\n\"ይህች ገዳም ንግሥት ማርያም በ333 ጐንደር ላይ ሆነው በህልም ተገልፆላቸው ነበር የታነፀው። ደግሞ የሰው ልጅ በዶማ ቆፍሮ ነው ያነፀው በሉና እመኑ\" ሲሉ አፌዙብን። ብታምኑም ባታምኑም 'አብ ሃነጸ ወልድ መንፈስ ቅዱስ' ራሱ መንፈስ ቅዱስ ነው ያነፃት ብለን ነው የምናምነው\" ይላሉ።\n\nገዳሟ ውስጥ የአንድ ትልቅ የጥድ ዛፍ ቁመት ያላቸው 44 ዓምዶች ይገኛሉ። በሌሎች ገዳማትና አድባራት እንደሚደረገው ሁሉ በቅድስት ማርያምም ወንዶችና ሴቶች ተለያይተው ነው የሚቀመጡት።\n\nበጣሪያው ላይ ሦስት እምነ አድማስ ነበሩ። አንደኛው ወድቆ እንድያውም ጣልያን ለመውሰድ ሞክሮ አልተሳካለትም። ሁለቱ እስከ አሁን ድረስ አሉ። ድንጋዩ ላይ በእብራይስጥ ቋንቋ የተፃፈ ፅሑፍም ይታያል። \n\nእምነ አድማስ ድንጋይን ለመቁረጥና ለመጥረብ ኃይል የተሰጠው የድንጋይ ዘር ነው።\n\nገዳሟ ውስጥ ከሚታወቅ ይልቅ የማይታወቀው ስለሚበዛ ቄስ ዘሚካኤል ያስታወሱትንና የነገሩንን ብቻ አሳጥሬ ልንገራችሁ።\n\nበአንድ የገዳሟ ጓዳ ውስጥ ልጅ መውለድ የዘገየባችው እንስቶች ተቀምጠው ፈጣርያቸውን የሚለምኑበት ከአለቱ ተፈልፍሎ የተዘጋጀ ወንበር ይታያል። ከፊት ለፊቱ ደግሞ መባ የሚያስቅምጡበት መደርደርያ አለ።\n\nበአንደኛው የገዳሟ ክፍል የቅድስት ማርያም መንበረ ታቦት አለ። መንበረ ታቦቱ ራሱ ሙሉ ለሙሉ ከአለት ተፈልፍሎ ነው የተሰራው።\n\nከመንበረ ታቦቱ አናት ላይ 4 ጉልላት ይታያል። ወደ መንበረ ታቦቱ ከካህንና ከዲያቆን ውጪ ምዕመን እንዲገባ አይፈቀድለትም። \n\nገዳሟ ውስጥ የሚገኘው የጨለመው በር ፈለገ ኦር ይባላል። ሊቃውንቱ ጉድጓዱ ቀጥ አድርጐ እስራኤል ነው የሚያስገባው ብለው ያምናሉ። ድሮ ነው አሉ 5 ካህናት ማሾና ጧፍ ይዘው ገብተው በዛው አልተመለሱም ብለውናል።\n\nመሪጌታ ቁጭ ብሎ ወደ ታቦቱ እያየ የሚጸልይበት ዙፋንም ተቀርጾ ይታያል። ዙፋኑ ከላይ ዘውድ አለበት፤ ይህም ከአለት ተፈልፍሎ ነው የተዘጋጀው።\n\nገዳሟ ውስጥ የተለያየ ትርጉም ሊሰጣቸው የሚገቡ 5 ጉልላት አሉ፤ የኮከቦች ተምሳሌት ብለው የሚጠሩዋቸው ቅርፆችም አሉ። \n\nየገዳሟ የበር መዝጊያዎች ከእየሩሳሌም በቀስተ ደመና ተጠፍረው እንደመጡ ይነገራል። ገዳሟ በር የሌላቸው 12 መስኮቶችም አሉት።\n\nልክ እንደ መንበረ ታቦቱ ከካህንና ዲያቆን ውጪ ሌላው ምዕመን የማይገባበት ቤተልሔምም አለ።\n\nበአንድ ትልቅ አለት ላይ ሆኖ ከቅድስት ማርያም በተጨማሪ የቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም አለ። ገዳሟ መወጣጫ አልነበራትም። በቅርቡ አንድ ምግባረ ሰናይ ግለሰብ ከብረት የተዘጋጀ መሰላል አሰርቶላታል። \n\nወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም የሚያስወጣ መሰላል\n\nየቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም መስኮተ አብርሃምን ጨምሮ 6 መስኮቶች አሉዋት። በመስኮተ አብርሃም በኩል አሻግሮ የቅድስት ማሪያም መንበረ ታቦትን ማየት ይቻላል።\n\nሁለቱ ገዳማት ተአምራዊ የጥበብ ሥራ እንዳረፈባቸው ፍንትው ብሎ ይታያል። \n\nእነኝህን... ", "passage_id": "81d596dd0cc87dade71aee8d7221ef00" }, { "passage": "ታቦታቱ የሚያልፉባቸው አውራ ጎዳናዎች በበጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ፀድተው፣ መተላላፊያ መንገዶቹና ዋና ዋና አደባባዮች በባንዲራ አሸብርቀው ይታያሉ። ታቦታት ከየአድባራት በካህናት፣ በዲያቆናት እና በምዕመናን ታጅበው በክብር ይወጣሉ።መተላለፊያ ጎዳናዎች በምንጣፍና በቄጠማ ጉዝጓዝ ደምቀዋል።ታቦታቱ ከየአብያተ ክርስቲያናቱ በምዕመናን ውብ ዝማሬና እልልታ ታጅበው ወደ ጥምቀተ ባህር ይወርዳሉ።  ከተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት ታቦታትን ሊያጅቡ የወጡ ዘማሪያን በተዋበ አልባሳት ደምቀው በስርዓት በተሰደሩ ረድፎች የተዋበ ዘማሬን ያሰማሉ፤ ወጣቶች ተመሳሳይ አልባሳትን በመልበስ በቡድን በቡድን ሆነው ክብረ በዓሉን አድምቀውታል።ጃንሜዳ አሸብርቃለች።ይህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች ዘንድ ከሚከበሩ የአደባባይ ደማቅ ክብረ በዓላት አንዱ የሆነው የከተራ በዓል ልዩ ድባብ ነው፡፡የከተራ በዓል ትላንት\nበመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ\nተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነት\nተከታዮች ዘንድ በመላው ሀገሪቱ በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል። በተለይም በአዲስ አበባ ጃንሜዳ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ ካህናት፣ ቀሳውስት፣ የአድባራትና ገዳማት ተወካዮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ በበዓሉ ላይ ለመገኘት ከተለያዩ ሀገራት የመጡ የአገር ጎብኚዎች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል፡፡የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ\nቤተክርስቲያን ብፁዕ ወቅዱስ\nአቡነ ማትያስ ቀዳማዊ\nፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ\nጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ\nጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ\nዘመንበረ ተክለሃይማኖት፤ በብፁዓን\nአበው  ሊቃነ ጳጳሳት፣ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያው ኃላፊዎችና ሠራተኞች፣ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ በበርካታ ካህናት፣ ምዕመናንና የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ታጅበው ጃንሜዳ ደርሰዋል። በየአመቱ ጃንሜዳና በአካባቢው የሚገኙ የ11 ደብራትና ገዳማት ታቦታት የጥምቀት በዓልን በጋራ የሚያከብሩ ሲሆን፥ ትላንት ከቀኑ ስምንት ሰዓት ጀምሮ ከአድባራትና ገዳማት ጉዞ በመጀመር ምሽት ላይ ጃንሜዳ ደርሰው በክብር ስፍራው አርፈዋል። ታቦታት ወደ ማደሪያቸው ጥምቀተ ባህር ከደረሱ በኋላም አዳራቸውን በዚያው ያደርጉ ሲሆን፥ በካህናትና ዲያቆናት ዝማሬና ሌሎች ሃይማኖታዊ ስነ ስርዓቶች ተከናውኗል።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ብፁእ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ጸሎተ ቡራኬ ሰጥተዋል። ከፀሎተ ቡራኬ በኋላ የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች በየተራ ያሬዳዊ ወረብና መዝሙር አቅርበዋል፡፡በበዓሉ ላይ የተገኙ ምዕመናን የዘንድሮው የከተራ በዓል ልዩ ድምቀት እንዳለው ይገልፃሉ።ወጣት ሙሉጌታ አየለ የአዲስ አበባ ነዋሪ ነው።ጃንሜዳ በዓሉን ለመታደም መገኘቱን ገልፆ በጥምቀት ዋዜማ የሚከበረው የከተራ በዓል ልዩ ሀሴት እንደፈጠረለት ያስረዳል።በአገር ባህል ልብስ ተውበው ክብረ በዓሉ ላይ ተገኝተዋል ወይዘሮ ሮዛ ኩምሳ።“ከተራና ጥምቀት ለኔ ልዩ በዓላት ናቸው፤ ስለዚህ ለኔ ሁሌ ይለይብኛል፤ አሸብርቀን ታቦታተኑ አጅበን በሰላም ስንገናኝ ደስ ይላል” በማለት የበዓሉን ልዩ ድምቀት ይገልፃሉ።በዓሉ ከእምነት ስረዓቱ ባሻገር የባህል ትሩፋቶች ማሳያና የእርስ በርስ ግንኙነት ማጠንከሪያ መሆኑን ይናገራሉ።የእምነቱ ተከታዮችም በዓሉን ሲያከብሩ በመተጋገዝና የሀገራቸው ሰላም በማስጠበቅ ሊሆን እንደሚገባም ይጠቁማሉ።ዛሬ የሚከበረው የጥምቀት በዓል በዘንድሮ አመት በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት /ዩኔስኮ/ በማይዳሰስ የአለም ቅርስነት መዝገቡ ከሌላ ጊዜ ለየት ያለ ድምቀት ያላበሰው መሆኑ በክበረ በዓሉ ላይ የተገኙ ምዕመናን አስተያየት ሰጥተዋል።  አዲስ\nዘመን ጥር 11/2012ተገኝ ብሩ ", "passage_id": "295a1445901bb61504ae2e6f3b63aa87" } ]
74349306f8e6a43fd83bd75413ac64d1
961de908a42148c5a283d1f07e6fd103
ከድጡ ወደ ማጡ
ሰዎችን ከሱስ ለማላቀቅ የማይፈነቀል ድንጋይ የለም። ምክር፣ ህክምና፣ ለደግ ሲባል ማግለል እና የመሳሰሉት ሁሉ ይሞከራሉ። በተለይ ቤተሰብ ቤቱን ቆሌ ያራቀውን ይህን ችግር ለመፍታት ብዙ ይጥራል። ይህ ጥረት ጥቂቶችን ሲታደግ ቢስተዋልም፣ ያደቆነ ሰይጣን ሳያቀስ አይተውም እንዲሉ ይህን ሁሉ አሸንፈው እስከ ህይወት ፍጻሜያቸው ሱሰኛ የሚሆኑ ሰዎች ግን በርካታ ናቸው። ሜክሲኮዊቷ የባሏ መሸተኛነት መሆን በእጅጉ ያስመርራታል። መከረች ዘከረች አልሆን አላት። ቢራ መጨለጡን ሊተው ባለመቻሉ ከዚህ ችግር ሊገላግላት የሚችለውን መላ ማፈላለግን ትመርጣለች። አንድ ቀንም አንድ ሀሳብ ብልጭ ይልላታል። ቢራ እርም እንዲል ያረገዋል ያለችውን መላም ተግባራዊ ለማድረግ ትወስናለች። ሚቼል ኤን የተባለችው ይህች የሜክሲኮ ሲናሎአ ከተማ ነዋሪ፣ ለእዚህ ውሳኔዋ መሳሪያ ይሆኑኛል ስትል ያሰበቸውን ውህድ ከእንግሊዝ ጨውና ከዘይት መሰል ነገር ታዘጋጃለች። ንጥረ ነገሮቹ ቀስ በቀስ ሥራቸውን እንዲያከናወኑ ያስችላል ያለችውን ቅመማም ታደርጋለች። ለእዚህም የተለያዩ ድረ ገጾችን እስከማንበብ ትደርሳለች። ውሳኔዋን ስራ ላይ ለማዋልም ባለቤቷ ጆሴ በራያን ሳያይ ጥቂት ጠብታዎችን በቢራ ጠርሙሶቹ ውስጥ ትጨምራለች። ያህን ያላየው ባለቤቷም እንደ ወትሮው ቢራውን መጨለጡን ይቀጥላል። ቀስ በቀስ ግን ባልተለመደ መልኩ ሆዱን መታመም ይጀምራል፤ ክፉኛ ማስቀመጥም ይጀምረዋል። እሱ ግን ብዙም እንደ ችግር አልተመለከተውም። ሚቼል ግን ተቅማጡ የሆነ አለርጂ ያስከተለው ሳይሆን አይቀርም ስትል ትገልጽለታለች። ችግሩ ምንአልባትም ከአልኮሆል ጋር ሊያያዝ እንደሚችልም ትጠቁመዋለች። እሱ ግን የምትለውን ከቁብ ሳይቆጥር አሁንም እንደ ወትሮው መጠጣቱን ይቀጥላል። ለሆድ ህመሙም ማስታገሻ እየወሰደ መጨለጡን ይቀጥላል። ባለቤቱ ይህ ነገር አይሆንም መጠጣትህን አቁም ትለዋለች፤ተቅማጡ ቢያስቸግረውም መጸዳጃ ቤቱ አጠገቤ እስከ ሆንኩ ድረስ ይህ አያስጨንቀኝም እያለም በባለቤቱ እየቀለደ ይጠጣል። ሚቼል ግን የባለቤቷን ፌዝ ወደ ጎን በመተው አሁንም ሌላ መላ ማፈላለግን ስራዋ ታደርጋለች። በቢራው ውስጥ የምትጨምረውን ንጥረ ነገር መጠን በመጨመርም ቢራውን ማቅረብ ትጀምራለች። በቀጣዩ ቀን የባለቤቷ ተቀማጥ አሳሳቢ እየሆነ ይመጣል። መጸዳጃ ቤት ለመድረስ እንኳ እድል የሚሰጥ አልሆን ይለዋል። እሷም ጉዳዩ በጣም ያሳስባትና በአቅራቢያቸው ወደ ሚገኝ ሆስፒታል ይዛው ትሄዳለች። ጆሴ በምርመራ ወቅት ለሀኪሞች ችግሩ ምናልባትም ከሚጠጣው ቢራ ጋር የተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ይገልጽላቸዋል፤ ከህመሙ ለመፈወስ ሲል ሁለተኛም ቢራ በደረሰበት እንደማይደርስ ያረጋግጥላቸዋል። ቢራው ሆዱን ከማሳመም በተጓዳኝ መቀመጥ እንደከለከለውና ሰላም እንደነሳው ይነግራቸውና አለመጠጣቱን እንደሚመርጥ ይገልጽላቸዋል። ቫንጋርዲያ የተሰኘው የሜክሲኮ ጋዜጣ ጉዳዩን አስመልክቶ እንደሰራው ዘገባ፣ ያቀደችው ያልተሳካላት ይልቁንም ሌላ ጣጣ ያመጣባት ባለቤቱ በሰራችው ድርጊት ትጸጸታለች፤ ባሏ ቢራ እንዲጠላ ለማድረግ በቢራ ውስጥ ባእድ ነገር መጨመሯን በመግለጽ ለተቀማጡ ምክንያቱ እሷ መሆኗን ታስታውቃለች። ጉዳዩ ፖሊስ ዘንድ ይደርስናም ጆሴ ባለቤቱ ከፍታ በምታቀርብለት ቢራ ጠርሙስ ውስጥ አንዳንዴ ባእድ ነገር ይመለከት እንደነበር ለፖሊስ ገልጾ፣እሱ ግን ይህን ያህል ጎጂ ነገር ሊሆን ይችላል ብሎ አስቦም ገምቶም እንደማያውቅም ይናገራል። ፖሊስም ሚቼል በፈጸመችው ድርጊት በተጠ ርጣሪነት በቁጥጥር ስር ያውላታል፤ በእዚህ ድርጊቷም ፍርድ ቤት ቀርባ ቅጣት ሊጣልባት እንደሚችልም ፖሊስ መግለጹን ኦዲቲ ሴንትራል የተሰኘው ድረገጽ መረጃ ያመለክታል። የሚወዱትን ሰው ከችግር ለመታደግ ሲባል የሚወሰድ እርምጃ ሌላ ችግር እንዳያስከትል መጠንቀቅ እንደሚገባ ዘገባው ያመለክታል። አዲስ ዘመን ጥር 12/2012ዘካርያስ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=25947
[ { "passage": " ጠረጴዛ ሙሉ ምግብ በአይነት በአይነቱ ደርድረን ‹‹ኧረ ብሎ! ምነው ብሉ እንጂ በሞቴ! … አፈር ስሆን!›› ብሎ ለምኖ የሚጋብዝ ሰው ከኢትዮጵያውያን ውጪ የትም አገር ላይ ያለ አይመስለኝም:: ይሄ የኛ ማንነት ነው:: ‹‹እንዲያው ለምዶብን ነው ›› እንዳትሉኝ እንጂ እኛ ኢትዮጵያውያን ከሌላው ዓለም የምንለይበት ብዙ ባህሎችና ልምዶች ያሉን ህዝቦች ነን:: መዘመን ሳይከፋ አሁን አሁን ያለ ባህል ወጉ ፈር የለቀቀ ስልጣኔ አለኝ ባዩ በዝቶ ካልሆነ በስተቀር፤ የሚያምርብን ወጉ አብሮ መብላት መጠጣቱ ነው:: ምክንያት ፈልገው አብረናቸው እንድንሆን የሚሹት ቤተሰቦቻችን:: ወላጆቻችን:: ጎረቤቶቻችን:: ጓደኞቻችን… ቤታቸው እስክንሄድ ጉጉቱ ሊገላቸው ነው የሚደርሰው፤ አግኝተውን ነው:: ፍቅር አስገድዷቸው ያለ የሌላቸውን ሁሉ አቅርበው ‹‹ኧረ አፈር ስሆን!›› ይሉናል:: አፈር ስሆን ብሎ ለሚጋብዝ ወዳጅ በወጉ በባህሉ ‹‹ኧረ ጠላትሽ! ለምን አፈር ትሆኛለሽ/ትሆናለህ›› ብለን ቤት ያፈራውን መመገብ ነው፤ እየተገባበዙ መተሳሰቡ:: ያን ጊዜ አቤት ጨዋታው መድራቱ፤ በተለይ ኢትዮጵያዊ ወጉ። እስኪ የዚህን ዘመን የኑሮ ውድነቱን አስቡት። ከዚያ መልስ ወግ ባህላችንን። እውነት ዘመኑ ያገባብዛል? እንዳለው የኑሮ ውድነት፤ ዶሮ በአራት መቶ ብር ገዝቶ ማለቴ ድሮ ሰንጋ በሚጎተትበት ብር። ምን አራት መቶ ብቻ ዶሮ ከነልጆቿ ከነማጠፈጫው የአንድ ሺ ብር ጌታ ሆና ሰው ሁሉ በሩን ዘግቶ መብላት አልነበረበትም ትላላችሁ? ነገሩ ግን ወዲህ ነው። እኛ ኢትዮጵያውያኖች ነን።ባህላችን አይፈቅድም። በር ዘግተን አንበላም። ኑሮ ለምን ከፈለገ ጣሪያ አይነካም። የምን ሰስቶ ቆንጥሮ መመገብ ነው። የኛ ማንነት ይሄ በመሆኑ በራችንን ከፈት አድርገን ‹‹ግቡ… ግቡ ጎራ በሉ:: አረፍ በሉ›› እንላለን። ወዲያው ይከተላል ከምግብ ከመጠጥ በአይነት በአይነቱ። ያቀረብነውን ማእድ እንግዳ እያማረጠ ሲበላ እያየንም አንረካም፤ እንቀጥላለን ‹‹ኧረ ብሉ! አፈር ስሆን… በሞቴ!››። ደስ ብሏቸው እንዲመገቡት ከምግቡም ቀመስ እያደረግን ‹‹ጣፋጭ ነው ‹‹በባለሙያ የተዘጋጀ ነው›› እንላለን። ምክንያቱም እኛ ኢትዮጵያውያን ነን። ብርጭቆውን ሞልተን ቀድተን\nወደ አንደኛው የእጃችን\nመዳፍ ከመጠጡ ፈሰስ\nእያደረግን ‹‹እንዴት ጥሩ\nጠላ›› የማር ጠጅ\nመሰሎት፤ ጠጁ በቤት\nየተዘጋጀ ነው ፤\nጠላው ገብስ ? ለስላሳ\nጉሽ ነው እራስ\nአይነካም›› እያልንም ለጤናም\nዋስትና እንሰጣለን። ባህል\nወግ መከባበራችንን እናሳያለን።\nሁሉም እንዲበላልን፤ እንዲጠጣልን\nበመጓጓት። አቤት ሲያምርብን\nምክንያቱም ባህላችን ነዋ።\nያለውን ሁሉ በአይነት በዓይነቱ አቅርቦ ብሉልኝ በሚል ተማጽዕኖ አድርጎ ብቻ የሚረካ ጥቂቱ ነው። ይሄ ነው የእኛ ባህላችን ግቡልኝ ብሉልኝ ጠጡልኝ ማለታችን። ያለውን ተካፍሎ ተቋድሶ መመገብ ፤ደግሞ መመራረቅ ‹‹ለከርሞ በሰላም ያድርሰን›› ብለን ለቀጣዩ ዓመት መልካም ተመኝተን ‹‹ለሰጫችን ይስጥልን›› ብለን እንለያያለን። እኛም ተራ አለንና ልንጋብዝ እንዘጋጃለን። ይሄ የእኛነታችን ባህል ታዲያ ከወንዝ ወዲህና ከወንዝ ወዲያ አይልም። ብሄር? ቋንቋ? ፆታ? ቀለም? አይጠይቅም። ኑ አብረን እንብላ እንጂ ‹‹አንተ ቆይ ከብሄርህ ጋር ተቀላቀል›› የተባባለበትን ዘመን እኔ በበኩሌ አላስታውስም። ኧረ እንዲያውም የለም። ሁሉም ሰው ጓዳው ሲሞላ በዓል ሲመጣ በአንድ ገበታ መቋደሱ የነበረ ነው። አሁንም ያለ ወደፊትም አጠናከረን የምንቀጥለው። የትም እግራችን እስኪቀጥን ሄደን የማናገኘው ኢትዮጵያዊ ባህላችን ነው። መታወቂያችን! ስለኛ ብዙ ካልኩ አይቀር ባህል ወጋችን ልዩ የሚያደርገን ውብ ማንነታችን መሆኑን ለማሳየት እስቲ አንድ ትዝታዬን ላውጋችሁ። ባህር ማዶ አንድ ወቅት ብቅ ባልኩበት ጊዜ የገጠመኝን ነበር። ሁሌም አስታውሰዋለሁ። ደቡብ አፍሪካ ነው። በቆይታዬ አገሪቷን ከባልደረቦቼ ጋር ዞር ዞር ብለን ከጎበኘን በኋላ ሰብሰብ ብለን እራት ለመመገብ ወደ አንድ ምግብ ቤት ገባን ። እኛ ካዘዝነው ምግብ በቁጥር እንበልጥ ነበር። ከሰው ቁጥር በአንድ የሚያንስ ምግብ አዘዝን። ማይነስ ዋን እንደሚባለው ማለት ነው። አስተናጋጁ ግን ‹‹አንድ ሰው ያላዘዘ አለ›› በሚል ደጋግሞ እንዲታዘዝ ጠየቀ። አንዱን ምግብ ለሁለት\nልንመገበው መሆኑ ሲነገረው\nበጣም ግር አለው።\nኧረ እንዲያውም ገረመው።\nይህን አይነቱን ባህል\nአያውቅምና የታዘዘው አይነት\nተጨማሪ ምግብ እንዲመጣ\nየተነገረው መስሎ ተሰማው።\nአሁንም አለመሆኑ ተነገረው።\nሲመለስ ግን ‹‹ማንም\nየማንንም ምግብ መመገብ\nእንደማይችል ፤ ያዘዘውን\nምግብ በልቶ ካልጨረሰ\nደግሞ አስጠቅልሎ በቴክ\nአዌይ መልክ አስደርጎ\nወደ ቤቱ መውሰድ\nአለበት›› በማለት ሊያስረዳን\nሞከረ። የሆቴሉ ህግም\nሆነ የእነሱ ባህል\nሁሉም የራሱን ይበላል\nእንጂ የሌላውን መካፈል አይችልም የሚል አይነት ነበር። እኛም ተገረምን እነሱም ደነቃቸው። አንድ ሰሀን ላይ በጋራ መመገብ። ለዚያውም እየተጎራረሱ መመገብ ለለመደ ሰው ይሄ በጣም እንግዳ ሊሆን ይችላል። በእኛም ላይ ይሄ ነበር የተፈጠረው። በአንድ ገበታ ላይ ከአምስት ያላነሱ እጆች ተዘርግተው እንደ ፍላጎታችን ጠቅለል አድርገን በመጉረስ ካለማንም ገሳጭ የምንበላው ምግብ ነው። አንድ ምግብ ለሶስት ብንበላስ ማን ከልክሎን። በወቅቱ የሌላውን እና የራሳችንን ባህል እያነፃፀርኩ ተገረምኩ ። አጋጣሚውን ግን የጨዋታ ማድመቂያ አድርገነው ምግባችንን አወራረድን። ‹‹ኧረ ብሉ አፈር ስሆን›› እየተባለ ምግብ ከሚጋበዝበት አገር የመጣን እንግዶች፤ ኢትዮጵያውያን መሆናችንን አላወቀምና አይፈረድበትም። መለስ ብዬ ኢትዮጵያዊነት አስተዳደጋችንን ሳየው አሁንም እኮራለሁ። ቤተሰቦቻችን አንድ በሬ ለአስር ተካፍለው ቅርጫ አብልተውናል። እኛም ዓመት በዓል በመጣ ቁጥር ቅርጫ የለም እንዴ ብለን በጉጉት እንጠብቃለን። የስጋ አምሮታችንን የምንወጣው በጋራ ከምናርደው የዓመት በዓል በሬ ነው። ከልጅነት አእምሮ የማይረሳው አንዱ ቅርጫ ነው። አባቴ ወደ ቅርጫው ቦታ በማለዳ የሚያመራው ‹‹ረፈድ ሲል ዘንቢል ይዛችሁ ኑ›› የሚለውን መልዕክቱን አስቀድሞ ነው። እኛስ ብንሆን አዲሱን ቀሚስ ለማስመረቅ ከጓደኞቻችን ጋር ለመገናኘት ያ ጥሩ አጋጣሚ አይደል? ከተባላው ሰዓት ቀደም ብለን ተጠራርተን ዘንቢል አንጠልጥለን በበሬ ማረጃው ስፍራ ከተፍ ነው። ልጆች አንዳንዴም ሴቶች ዘንቢላቸውን ይዘው ዳር ላይ ቁጭ ብለው ይጠባበቃሉ ምኔ በደረሰ እያሉ። ወንዶቹ ከዚህ ወደዚያ ተፍተፍ ይላሉ። አባቶቻቸውን ይረዳሉ። የእርድ እና የመከፋፈሉ ስራ ሳይጠናቀቅ እንጀራ በትሪ‹› አዋዜ እና ሚጥሚጣ ከች ይላሉ። አዋዜው ካልደረሰም ችግር የለም በርበሬው በአረቄ ተለውሶ አዋዜ ይሆናል። ይሄኔ በስፍራው የተገኘው ሁሉ ጉበት ማወራረድ ላይ ይሳተፋል። ‹‹ግሩም ነው›› ከሚለው ጀምሮ ‹‹ጉበት እኮ ለደም ማነስ ፍቱን መድሃኒት ነው›› እስከሚለው የጉበት ጠቀሜታ ተንታኝ ሆኖ ቁጭ ይላል። ከጉበቱም ከቁርጡም በሚጥሚጣ እየተለወሰ በስራ ለተጠመዱት ከስር ከስር ጉርሻው ይካሄዳል። ወባ እንደያዘው ሰው የሚንቀጠቀጠውን ትኩሱ የበሬ ስጋ እየቆራረጡ መመደቡ ምን ያህል ፍትሀዊነት እንዳለው አስቡት ። በእያንዳንዱ ሰው ላይ ያለው እምነት ሙሉ ነው ።ሚዛን አይጠየቅ፤ የሀይማኖት አባት ወይም ሽማግሌ አይጠራ ብቻ በራስ እጅ ? በአይን ሚዛን እጅ እንዳመጣው ይመደባል። ድልድሉ ሲያበቃ አነስ ያለ ልጅ ይጠራና በወረቀት ላይ ተፅፎ የተጠቀለለውን ስም በየመደቡ ላይ እንዲያስቀምጥ ይደረጋል። ያኔ በቃ ተመራርቆ ምድቡን ማንሳት እንጂ የእከሌ ትልቅ የአያ እከሌ ትንሽ የሚል ፈፅሞ አይነሳም። ከዚህ ብሄር ከዚያ ፆታ ብሎ የሚከፋፍል ቀርቶ በሀሳቡ የሚመጣበት የለም። በጊዜው የቅርጫ እንጂ የብሄር ክፍፍል የማይታሰብ ነው። አንድ በሬ ለአስር ቤተሰብ፤ በአንድ ቤተሰብ አምስት ሰው ቢኖር፤ አንድ በሬ ለሀምሳ ሰው በፍቅር ተካፍለን እንበላለን። ደግሞ እንመራረቃለን፤ ለቀጣዩ ዓመት በሰላም? በደስታ ? በጤና ያገናኘን ብለን። ምክንያቱም እኛ ኢትዮጵያውያን ነንና። ሁላችንም ጎረቤታሞች ስጋውን ተካፍለናል ፤በሁሉም ሰው ቤት ስጋ አለ፤ ስጋ የምለው ለእኛ ትልቁ ክብርም የምንሰጠው ምግባችን ስለሆነ እንጂ በዕለቱ ጠላው? ጠጁ? ዳቦው? ፈንድሻው ? ቡናው… ሁሉ ሳይቀር በእያንዳንዳችን ቤት አለ። ምን ቢሞላ ያለ ሰውና ካለ ጎረቤት አይጥምም። ስለዚህ ‹‹ኑ ቡና ጠጡ›› እንላለን። አብሮ የበላና አብሮ የጠጣ በሀዘን በደስታውም አይተጣጣም እንደማለት ነው ። እናም ምሳ አንዱ ቤት፤ እራት ሌላኛው ቤት። አብሮ ይጫወታል ፤አብሮ ይደሰታል ይሄ ሀሳብ የምንለዋወጥበት መድረክም ነው። የተጣላ ማስታረቂያም ነው። መቼም ከሰው ጋር በተለያየ ምክንያት መጋጨቱ አይቀሬ ነው። በልጅም በውሻም፤ በሌላውም በሌላው ብቻ የጠብ ምንጭ አይጠፋም። ግን ፀቡ አይዘልቅም። ቢሆንም ግን ዘር ማንዘር፣ ብሄር ብሎ አይቆጠርም። ‹‹እገሌና እገሊት ተቀያይመዋል›› ከሚል አያልፍም። ለዚህ ደግሞ ‹‹በዳይ ተበዳይ›› ተለይቶ ይቅርታ እንዲጠያየቁ ይደረጋል። የይቅርታው ማሳረጊያም አብሮ መብላት ይሆናል። አብሮ የበላ ጥርስ አይሳበርም፤ ሰላም ለመንደሩ፤ ሰላም ለቤተሰብ፤ ሰላም ለሁላችን ይሆናል:: ይሄ ነው ኢትዮጵያዊነት\nባህላችን። አብሮ በልቶ፣\nአብሮ ጠጥቶ፣ ሲጣሉ\nታርቆ፣ ደስታና ሀዘንን\nበጋራ ተካፍሎ ማሳለፍ።\nታዲያ ይሄ ሆኖ\nስር መሰረታችን፣ ማንነታችን፤\nዛሬ ላይ በሆነው\nባልሆነው መጎነታተሉን ምን\nአመጣው? በሉ እንግዲህ\nመቼም ‹‹ችግር አይፈጠር››\nሳይሆን ሲፈጠር ባሉን\nባህላዊ እሴት ማረቅ\nእንደምንችል መረዳት ነው\nዋናው ቁምነገሩ። ኑ\nማዕድ ዳር እንሰባሰብ!\nመጎነታተሉን ተወት አድርገን\n‹‹እስቲ በሞቴ አፈር\nስሆን…..ብሉልኝ ጠጡልኝ››\nእያልን አብሮነታችንን እናድስ::\nሰላም!አዲስ ዘመን መስከረም 4/2012 አልማዝ አያሌው", "passage_id": "c47a14e8cef4d702f537d32cadf8a5d4" }, { "passage": "ወይዘሮ የዝና ጨርቆሴ፣ የአዳባ ከተማ ነዋሪ ሲሆኑ፤ ከሰሞኑ ተከስቶ በነበረው ሁከት ቤት ንብረታቸውን ብቻ ሳይሆን ባለቤታቸውን አቶ ዘውዱን እና የልጃቸውን ባል አቶ ሰለሞንን በሞት ተነጥቀዋል። ሌላው ጉዳት የደረሰባቸው ግለሰብ አቶ ካሳሁን ተሾመ በበኩላቸው እንደሚሉት፤ በዕለቱ ንጋት ላይ የጀመረው ሰልፍና ሁካታን ተከትሎ የሰው ንብረት ማውደም መጀመራቸውን የሰሙት ከቤት ሆነው ነበር። ችግሩ እየከፋ መሄዱን ሲገነዘቡም ሆቴላቸውን ሊመለከቱ ይወጣሉ። በስፍራው ሲደርሱ ግን ነገሮች ተቀይረዋል፤ ሆቴሎቻቸውም በእሳት ተያይዘው፣ ግርግሩም በዝቶ አገኙት። በወቅቱም እንኳን እየተቃጠለ ያለውን ንብረታቸውን ሊያድኑ ቀርቶ፤ራሳቸውንም ማዳን እንደማይችሉ በመገንዘባቸው የሚቃጠሉ ሆቴሎቻቸው ወደአመድነት እየተቀየሩ እያዩም ቢሆን አካባቢውን ትተው ይሄዳሉ።ይሄን መሰል ጥቃት ሲደርስባቸው ለሦስተኛ ጊዜ መሆኑን የሚናገሩት አቶ ካሳሁን፤ በዚህኛው የሀጫሉን መገደል ምክንያት አድርገው ወጡ እንጂ አካሄዳቸው አንድም ብሔርን ካልሆነም ሃይማኖትን ተገን አድርገው ኅብረተሰቡን እርስ በእርስ ለማባላት የሚፈጸም የጽንፈኛ አመለካከት ባለቤቶች የሚከውኑት ተግባር መሆኑን አስረድተዋል። በዚህም አሁን ላይ አንድም ንብረታቸው በመውደሙ፤ ሁለተኛም ለህይወታቸው በመስጋታቸው በቤተክርስቲያን ተጠልለው እን ዳሉ በመጠቆምም፤ ይሄን ዓይነት ተደጋጋሚ ጥቃቶች በከተማዋ እየተበራከቱና እየተደጋገሙ በመምጣታቸው ህዝቡ በስጋትና ሰቀቀን እየኖረ እንደመሆኑ መንግሥት መኖሩን በተግባር ሊያሳየን ይገባል ይላሉ። ይህ አካባቢ በተደጋጋሚ የሰላም፣ የህግና ፍትህ ችግር የሚስተዋልበት እንደመሆኑ፤ አሁን በተፈጠረው ችግርም ያንን ማድረግ ባለመቻሉ ህዝቡ ንብረቱን ብቻ ሳይሆን ውድ ህይወቱን በግፍ እያጣ ይገኛል። እናም እነዚህ ወገኖች ችግሮች ተደጋግመው የሚፈጸሙባቸው እንደመሆኑ ከምንም በላይ ድምፃቸውን የሚያሰሙበት የመገናኛ አውታር አብዝተው የሚናፍቁ ናቸው። ምክንያቱም ብዙዎች ተጎድተው የሚያነቡ እንደመሆኑ እንባቸውም ለህዝብና ለመንግሥት የሚያደርስላቸው ይሻሉ፤ ዘወትር በስጋትና በፍርሐት ውስጥ እንደመሆናቸውም ይሄን ጭንቀታቸውን ሰምቶ የሚደርስላቸው የመንግሥት አካል አብዝተው ይናፍቃሉ። በመሆኑም ህዝቦች እንባቸው እንዲታበስ፤ በሰላም ወጥተው እንዲገቡ፤ ሠርተው ንብረት እንዲያፈሩ ብቻ ሳይሆን የንብረታቸው ባለቤትም ተጠቃሚም እንዲሆኑ መንግሥት ጆሮ ሰጥቶ የሲቃ ጩኸታቸውን ሊያዳምጥና ምላሽ ሊሰጥ ይገባል።የአዳባ ከተማ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙስጠፋ ዑመር እንደሚሉት የተፈጠረው ችግር ከባድና ጠላት ተዘጋጅቶበት በቅንብር የተፈጸመ ነው። በወቅቱ ኀዘኑን ለመግለጽ የሚካሄድ ሰላማዊ ሰልፍ የሚመስል ቢሆንም፤ በሂደቱ አቅጣጫውን ሲቀይር ችግሩን ለመከላከል በአገር ሽማግሌና የሃይማኖት አባቶች ጭምር በመታገዝ ጥረት ተደርጓል። ሆኖም ነገሮች ከአቅም በላይ ሆነው በሆቴሎች፣ በሱቆችና በመኖሪያ ቤቶች ጭምር በተፈጸመ ጥቃት ከባድ የንብረት ውድመትና ከአራት ያላነሱ ሰዎችም ህይወታቸው አልፏል። ይህ ከሆነ በኋላ ግን አመራሩም፣ የጸጥታ ኃይሉም በጋራ ተሠርቶ ችግሩን ለመቀነስ የተሞከረ ሲሆን፤ በየቤቱ እየሄዱ በሰዎች ላይ ጥቃት የሚፈጽሙ እንደመሆኑ ችግሩን በሚፈለገው ፍጥነት መግታት አልተቻለም።እንደ አቶ ሙስጠፋ\nገለጻ፤ ይህ ጥቃት\nአንድም ሃይማኖትን፣ ሁለተኛም ብሔርን ለይቶ ለማጥቃት የተፈጸመ ለማስመሰል ተሞክሯል። የተጎዱ ወገኖችን ባሉበት ሁኔታ ለመደገፍም ሆነ የጠፋባቸውን ንብረት ለመተካት የሚያስችሉ ሥራዎች በህብረተሰቡ በራሱ ተነሳሽነት እየተሠሩ ይገኛሉ። ከዚህ ባለፈም አሁን የሆነው ነገር ጠላት አቅዶበት ያደረገው እንደመሆኑ አስተዳደሩ ሳይዘጋጅ የተፈጠረና ውድመትም ሞትም ያስከተለ ነው፤ በዚህ ጥፋት ላይ ተሳታፊ ናቸው ተብሎ የተጠረጠሩ ከ102 ሰዎች በላይ ተይዘዋል። በቀጣይም ህብረተሰቡ ያለበትን ስጋት ለማስወገድና ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲኖሩ ለማድረግ መንግሥት ሙሉ ኃላፊነት ወስዶ እየሠራ ይገኛል።የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት\nአቶ ሽመልስ አብዲሳ\nቀደም ሲል እንደጠቀሱት\nበኦነግ ሸኔ፣ በህወሓት\nጥገኛ ቡድንና በውጭ\nኃይሎች ቅንጅት አርቲስት\nሀጫሉ ሁንዴሳን በሴራ\nበማስገደል በቀሰቀሱት ሁከት\nበመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች\nህይወት ሲያልፍ ከፍተኛ\nግምት ያለው ሀብትና\nንብረትም ወድሟል። ከዚህም\nጋር ተያይዞ አጥፊዎችን\nበህግ ቁጥጥር ስር\nበማዋል ተገቢውን ፍርድ\nእንዲያገኙ የማድረግና የመንግሥት\nመዋቅሩንም በመፈተሽ የማጽዳት\nሥራ እየተሠራ መሆኑን\nመገለጻቸው ይታወሳል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 13/2012ወንድወሰን ሽመልስ", "passage_id": "88bbd09339e9195dd63b91ce8632c840" }, { "passage": "እግር ጥሎኝ ወርቃማ የቅፈላ ሰፈር ከሚባለው አካባቢ ተሰይሜያለሁ፡፡ (ለደህንነት ሲባል የቦታውን ስም አልጠቅስም) ቦታው ላይ ደርሼ የቀጠርኩትን ሰው ጥበቃ አውራ መንገድ ላይ የመብራት ቋሚ ምሰሶ ‹‹ፖል›› ተደግፌ ቆሜያለሁ፡፡ በቅፈላና ሽቀላ ከተሰማሩ ወጣቶች መካከል አንዱ ‹‹አባቴ ታጥበሽ የተቀሸርሽ ደረጃ አንድ የይርጋ ጫፌ ቁጥር አንድ…›› ብሎ ሊያናግረኝ ሲቃጣው በአካባቢው ላይ ያሉት የተዋጣላቸው ቀፋይ መሆናቸውን ተረዳሁ፡፡ በግርግሩ አልበላም ‹‹ነቄ›› ነኝ ብለህ እዚህ ሰፈር ብትመጣ ስርቆት ወደ ዘመናዊ ልመና ይዞርና እያባባሉ ይበሉሃል፡፡ በቅፈላ ሰበብ ቦታ ግብር እየከፈልክ መመለስህ አይቀሬ ነው፡፡ ዘንድሮ ዘመናዊ ልመና የአለማመን ወጉ ተቀይሯል፡፡ በተለይ ሱሰኞች ቀዝቃዛ የስርቆት ትርክት እያቀረቡ፤ አፍዝ አደንዝዝ ወሬያቸውን በማላተም ዘና እያደረጉ፤ በሀዘኔታ ሆዳችንን እየበሉ፤ የአረቄ ቤት ጨዋታዎችን በብዛት በማውጋት ‹‹ቅፈላን›› ከኛ ሌላ ላሳር በማለት ያለምንም ይሉኝታ ድፍን ድፍኑን ይቀበሉናል፡፡ በሌላ ቀን እንዲሁ ብቻዬን በተመስጦ የየመንገዱን ሁኔታ እየቃኘሁ በትዝብት መዝገቤ ውስጥ ማስፈር ያለብኝን እያመረጥኩ ስጓዝ አንድ ነገር ተመለከትኩ፡፡ በተክለ ሰውነቱ ስፖርተኛ የሚመስል በመንገድ ዳር ቆሞ ወጭ ወራጁን ብር የሚቀፍል ጎረምሳ ከመንገዱ ከወዲያ ማዶ በጸሐይ ብርሃን እንዲለበለብ የተሰጣ ቆዳ መስሎ ተቀምጧል፡፡ ረጅም ሰዓት ጸሐይ ላይ ለመቆየቱ ፊቱ ላይ ያለው የድካም ስሜትና ጥውልግልግ ያሉ ዓይኖቹ፣ የደረቁ ከንፈሮቹ ያስታውቃሉ፡፡ ‹‹እናቱ አረ ለዳቦ፣ አባቱ ለምሳ ሙላልኝ፣ ፋዘር አትለፉኝ…›› እያለ ቅፈላውን ያሯሩጠዋል፡፡ አንድ ከፊት ለፊቱ ሸክም ያዘለ ማለቴ ቦርጭ የለጠፈ ሰው መኪናውን አቁሞ በጣቶቹ የመኪናውን ቁልፍ እያሽከረከረ በአስፈሪ አረማመድ መንገዱ ላይ ወዳለው ካፌ ያቀናል፡ ፡ ዓላማዬ አጋጣሚውን\nተጠቅሞ ማንኛውንም የመንገድ ላይ እንቅስቃሴ መታዘብ ስለሆነ ቀፋዩንም ተቀፋዩንም በትኩረት መመልከቴን ተያያዝኩት፡፡ የተሸከመው ቦርጭ\nባለሥልጣን አስመስሎታል፡፡ በነገራችን ላይ ሁሉንም ወፍራምና ቦርጫም የሆኑ ሰዎች ሁልጊዜ እንደ ባለሥልጣን ማየት ልምድ ሆኗል፡፡ አሁን ላይ እኮ ቦርጭ ማውጣት መታወቂያ ከማውጣት በላይ ቀላል ሆኗል፡፡ ዳሩ የደሃ ቦርጭ መጠጥ እስካለ ብቻ ስለሆነች ዘላቂ አይደለችም፡፡ በአንድ ወቅት አውቶቡስ እየጠበቅኩ አጠገቤ የቆመው ቦርጫም ሰውዬ በሰውነቱ ጦር በመሰለው ሌላ ሰው እግር ላይ ቆመ (ሳያስበው) ቀጭኑ ሰውዬም ብዙ ከታገሰው በኋላ በፍራቻ አንደበት ‹‹ጌታዬ ባለሥልጣን ነዎት እንዴ?›› ብሎ ጠየቀው ቦርጫሙ ሰውዬም ‹‹አይደለሁም!›› ሲለው ቀጭኑ እንደ መባነን ብሎ‹‹ ታዲያ ለምን አባክ እግሬ ላይ ትቆማለህ›› ብሎ በቁጣ ገሰጸው፡፡ ወደ ቦርጫሙ ባለመኪና ሰውና ቀፈዩ ልመለስ ሰውዬው ካፌ ውስጥ ሊገባ ጥቂት ሲቀረው ቀፋዩ ሮጥ ብሎ ‹‹ እባክዎ ጋሼ ቢጫ ይቦጭቁልኝ ›› አለው አራዳ ነኝ በሚል የቃላት ጨዋታ፡ ፡ ሰውዬው ቋንቋውን ተረድቶ ኖሮ ‹‹ሳንቲም አልሰጥህም ከፈለግክ ቁርስ ልግዛልህ›› አለው፡፡ ቀፋዩም ምርር ብሎት ‹‹ ኧረ ምንሼ ነው ከነጋ አራተኛውን ቁርስ በልቼ ልፈነዳ ነው እኮ ጨላዋን ቢገጩኝ ይሻላል›› አለ፡፡ ቦርጫሙ ጥሎት ወደ ካፌው ገባ፡፡ በልቤ ተመጽዋች መሆን ካልቀረ የምን ማማረጥ ነው አልኩና ደግሞ ሌላ ክስተት ፍለጋ ጉዞዬን ቀጠልኩ፡፡ ተመጽዋች ሰው ብዙ ልምድ አለው፡፡ ማንን ምን ብዬ ልጠይቅ የሚለው ሀሳብ ብዙ አያለፋውም፡፡ ብቻ ደግ ሰው ይግጠመው፡ ፡ አለበለዚያ በቃላት\nጨዋታ ህሊናን የሚሰብር ንግግር ከውስጣቸው መውጣቱ አይቀርም፡፡ በአንድ ወቅት\nአንድ ጎልማሳ ተመጽዋች ‹‹ጌታዬ ለዕለት ጉርስ የሚሆን ሳንቲም ይስጡኝ›› ብሎ ታዋቂ ሰው ይጠይቃል፡፡ ታዋቂው ሰውም ኪስ ከመግባት ይልቅ ትንሽ አወቅኩ ዓይነት ትዕቢት አብራው ስላለች ምክር ቢጤ ሊሰጥ ቃጣው፡፡ እናም ‹‹ ለኑሮህ የሚበጅ ስራ ለምን አትሰራም ከገንዘብ ይበልጥ የሚያስፈልግህ ጭንቅላት ነው›› አለው ተመጽዋቹን፡፡ ተመጽዋቹም መለሰና ‹‹እርሱስ ልክ ነው ጌታዬ እኔም የጠይቅኮት እርስዎ በደንብ ያልዎትን ነው›› አለው ይባላል፡፡ ከሊቅ እስከ\nደቂቁ የሚቀፍሉት ሰዎች የራሳቸው አይነተኛ መገለጫ አላቸው፡፡ ከፊሉ ተሸቀርቅሮ ‹‹የትራንስፖርት ብር ጎድሎኝ››፣ ሌላው ‹‹ዋሌቴን ቢሮ ረስቼ ወጥቼ››፣ የተቀረው፣ መንገድ ላይ አውቆ ቆሎ በመድፋት አጭር ቴሌቶን በማዘጋጀት ‹‹ቆረጠኝ፣ ፈለጠኝ፣ ያዙኝ ልቀቁኝ›› በማለት ከዚህ ምስኪን ህዝብ ይቀፍላል፡፡ ምን አይነት ዘመን ላይ ደረስን በሚያስብል ሁኔታ አንድ ‹‹ጩጬ›› ምሳ በሚበላበት ምግብ ቤት ገብቶ ‹‹ እማዬ እንዳለቻችሁ…እ እ እ… አጉርሱት›› ማለቱም ልብ ይሏል፡፡ ወገን ዘመድ ከዚህ ሰውረኝ ከማለት ይልቅ ለቅፈላ ለሚመጡ ቀፋዮች የሚሆን አንደበት እንደሚያሻን እንረዳ፡፡አዲስ ዘመን የካቲት 8/2011አዲሱ ገረመው", "passage_id": "fa30537bfebccaf99b2263168f0cda2b" }, { "passage": "የተጠራንበት\nሰዓት እየደረሰ ቢሆንም እስካሁን አልጨረሰችም። ፀጉሯን ስትሰራ፣ ስትለባብስ ከዚያም ስትኳኳል ሰዓቱ ነጉዶ የሙሽሮች መምጫ ደርሷል። መርፈዱን ላሳውቃት ከበር ቆሜ «ኧረ ውጪ» ማለት ከጀመርኩ ደቂቃዎች ተቆጥረዋል። ልጅት ግን የምትጨርስ አልሆነችም፤ አንዱን ለብሳ ጨረሰች ስል «ይሄስ አላማረብኝም» እያለች ሌላውን ታነሳለች። በዚህኛውም ልቧ አይረካም «… ይህ አይሆንም» በሚል ሌላ ፍለጋ ትጀምራለች። ቆሜ መጠበቁ ስላደከመኝ ከአንድ ጥግ ተቀመጥኩ፤ እየቆየች «ጨርሻለሁ …» ትለኛለች። ጥቂትም ሳትቆይ መልሳ «አላማረብኝም» ትላለች፤ በእኔ ዓይን ግን ሁሉም የሚያምርባት ቅንብብ ያለች ቆንጆ ናት። እርሷ ውስጥ ልጅነቴን እመለከታለሁ፣ ለዛ እና ወዘናዬን ወደ እርሷ ያጋባሁ ይመስለኛል። ሰዎች «ቁርጥ አንቺን የመሰለች…» ይሉኛል፤ እኔም ከአባቷ ስሙን ብቻ ከመጋራት በቀር፤ ሁለመናዋ የእኔ ወጣትነት እንዳለበት ነው የሚታየኝ። አሁን አንጋፋነቴ ማርፈዴን አስታወሰኝ እንጂ፤ እኔም በእርሷ እድሜ የሚያሳስበኝ ማማሬ ብቻ ነበር። ቁንጅት ብሎ መታየቱን፣ የሰዎችን ቀልብ መሳቡን፣ ከእኩዮች ጋር የስርቆሽ መተያየቱን፣ መጠቃቀስና መጎነታተሉን፣ መግደርደርና መሽኮርመሙን … ከየትኛውም ጉዳይ በላይ ቦታ የምሰጣቸው ነገሮች ነበሩ። ዕድሜ እያሳሳቀ እንደ ደራሽ ይዞኝ ሳይፈተለክ በፊት፤ ለእኔ የጊዜ ትርጉሙ ከውበት ጋር የተያያዘ ነበር። ከቤት ለመውጣት የሚፈጅብኝ ጊዜም አንድ ሰው ጉዳዩን የሚያጠናቅቅበት ነው። እናቴ ከአንድ ቦታ ይዛኝ ለመሄድ ስታስብ ማርፈዴ ስለማይቀር ቀድማ ታስነሳኝ እንደነበር አስታውሳለሁ። እኔም ደርሶብኛልና የዛሬዋ የልጄ መዘግየት ምክንያቱ አልጠፋኝም፤ ያው በትልልቅ ሰርግ መሃል ትንንሽ ሰርግ አይጠፋም የሚለውን ብሂል ተከትሎ መሆኑ አይቀርም። በየአጋጣሚው እንዲህ መሆኑበእድሜዋ የሚጠበቅ ነው። ታሪክ\nራሱን ይደግማል ይባል የለ፤ እኔም ወደ ትዳር ከመግባቴ በፊት የሆንኩት ትዝ አለኝ። የተዋደደ ሁሉ አብሮ ባይኖር እንኳ ጊዜያዊ ስሜቱ ግን አንዳች ደስታን ይሰጣል። እንዲህ እንደዛሬው እድሜ ቀዝቀዝ ማለት ሲጀምርም ለልባችን ሙቀት መፍጠሩ አይቀሬ ነው። ነገሩ የሆነው እኩያዬ የሆነች አንዲት ዘመዴ መዳሯን ተከትሎ ነው። ሰፈራችን ከሙሽሪት መንደር ብዙም ያልራቀ በመሆኑ፤ ወዲህም ሥራ ለማገዝ፣ ሰርጉን ለማድመቅ፣ ሙሽሪትን እንሶስላ ለመቀባትም፣… መመላለሴ አልቀረም። አመሻሹ ላይም እኛ ሴቶቹ ተሰባስበን «… ሙሽርዬ አይበልሽ ከፋ ሁሉም ያገባል በየወረፋ» እያልን እንጨፍራለን። ከእኛ አንጻር ደግሞ ሰብሰብ ብለው «ሃይሎጋ» ከሚሉት ጎረምሶች አንዱ በዓይን ጎብኘት ሲያደርገኝ ይታወቀኛል። አሁን ከትዝታዬ ማህደር በቀር ወዴት እንዳለ የማላውቀው ወጣት፤ ደማም በመሆኑ ሰርቆ ሲያየኝ ከመከፋት ይልቅ ደስታ ተሰምቶኝም ነበር። የሙሽሪት\nጎረቤት በመሆኑም ሲወጣ እና ሲገባ ቃል ሳናወጣ በዓይን መነጋገሩ እና መጠቃቀሱን ቀጠልን። ታዲያ በሰርጉ ቀን ኃፍረታችን ለቆን ለራሳችን ጥንስስ እንነሳ ይሆናል በሚል ዝግጅቴንየጀመርኩት ከቀናት በፊት ነበር። የምሰራው ሹሩባ፣ የምዋብበት አምባር፣ የምደምቅበት ኩል፣ የምለብሰው ሸማ፣ የምቀባው ሽቶ፣ … ሁሉ ሃሳብ ሆኖብኝ ቆየ። እንዳይደርስ የለም በዕለቱ፤ አሁን ልጄ እንደምታደርገው ሁሉ እናቴን «ጨርሻለሁ…» እያልኩ ሳስጠብቃት ቆይቼ «ያምርብኛል» ባልኩት ራሴን አሰማምሬ ወጣሁ። እናቴ በማርፈዴ እየተቆጣችኝ መንገዳችንን ቀጠልን። እንደ\nዛሬው ድንጋይ ያልተነጠፈበት መንገድ በበልግ ዝናብ መሬቱ የረሰረሰ በመሆኑ ጸዓዳው ልብሴ እንዳይቆሽሽ በጥንቃቄ ነበር የምጓዘው። ግን ምን ዋጋ አለው፤ ከሰርጉ ቤት ለመድረስ ጥቂት ሲቀረን አንድ መኪና፤ መሬቱ ላይ የታቆረውን ውሃ እንደጸበል አጠመቀን። እንዲያ ያለ እንከን የተዘጋጀሁበት ልብስ፣ ያደመቀኝ ጸጉሬ፣ የተኳኳለው ገጼ፣ … ሁሉ በጭቃማው ውሃ ተሸፈነ። ጥፋት አድራሹ መኪናም አለፍ ብሎን ከቆመ በኋላ የሾፌሩ በር ተከፈተ፤ እናቴም ለቁጣ ወገቧን ይዛ አንገቷን ትሰብቅ ጀመር። ለካስ እንዲያ አምሬ እንዲያየኝ ስኳኳልለት የቆየሁት ወጣት፤ ሾፌር ኖሮ ከመኪናው ሲወርድ አንድ ሆነ።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 28/2011ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "c6690e44c3b00939dcb35d30d4515b88" }, { "passage": "ጋዜጠኞች የሙያ አጋሮቼ እንደሚሉት አካባቢን ቀይረው ወደ ሥራ ሲመለሱ ጥሩ ሙድ ወይም መነቃቃት ይፈጠራል፡፡ ወጣ ሲሉ ወጣ ያለ ነገር ይገኛል፡፡ ተስማሚ የሆነ ወይም የሚጎዳ የአየር ፀባይ ያጋጥመዎታል፡፡ አይንዎም እንዲሁ ጥሩም መጥፎም ያያል፡፡ ጆሮም ደግና ክፉውን ይሰማል፡፡ ከሰዎች ባህሪ ጀምሮ ወጣ ብለው አብረው ውለው ሲያድሩ ብዙ ያያሉ። ይታዘባሉ፡፡ በሚታዘቧቸው ነገሮችም ወይ ይዝናናሉ፡፡ ወይም ያዝናሉ፡፡ ወደ\nኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ አምቦ መስመር ነበር ጉዞዬ፡፡ ወደ ጊንጪ መንገድ ይታጠፋል፡፡ ከሙያ አጋሮቼና ከሌሎች ጋር ረፋድ አራት ሰዓት ላይ በዕለተ አርብ ነበር ከአዲስ አበባ ከተማ የወጣነው፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ነበር ወደ ስፍራው ይዞን የሄደው፡፡ በጉዞ\nወቅት ምቾት ከሚነሳው አንዱ የጉዞ ቅድመ ሁኔታ አለመመቻቸት እና የመናበብ ችግር ነው፡፡ የጉዞ አስተባባሪዎች በአንድ ጉዳይ ላይ ተመሳሳይ የሆነ ቋንቋ የላቸውም፡፡ እናቶች እንደሚሉት ‹አረረም መረረም ማህበሬን ተወጣሁት› አይነት ሩጫ ነው የሚታይባቸው። አክብረው የወሰዱትን ባለሙያ አክብረው መመለስ ላይም እንዲሁ ችግር አለባቸው። በዚህ የአንድ ቀን አዳር ጉዞዬ ያነሰኋቸውን ነጥቦች ነበር በባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች ላይ ያስተዋልኩት፡፡ ከተማውን ለቀን\nወደገጠሩ ስንገባ ምድሪቷ የተቀበለችን በልምላሜ፣ በቀዝቃዛ አየርና ዝናብ ነበር፡፡ በአካባቢው ክረምቱ ከገባ የከረመ እንጂ ገና የጀመረ አይመስልም፡፡ ወደ ሥፍራው ያመራነው ሰኔ ግም ሊል አንድ ቀን ሲቀረው ስለነበር ቅዝቃዜ ይኖራል ብዬ አልገመትኩም። በተለይ ‹ጭልሞ› ተብሎ የሚጠራው ደን ‹ውበቴ ቅዝቃዜና ዝናብ ነው› ያለ ይመስላል። ጥቅጥቅ ያለ የተፈጥሮ ደን ነው፡፡ ደኑን አልፈን ስንሄድ ዝናብ አልነበረም፡፡ ከአፍታ ቆይታ በኋላ ስንመለስ ‹ዶፍ› አይነት ዝናብ ነበር የጣለው፡፡ የነበረንን የመንገድ ሥራ ጉብኝት ፕሮግራምም አስተጓጎልብን፡፡ ተፈጥሮን እያደነኩ ወደማሳዎቹ ሳማትር ደግሞ\nለየት ያለ ነገር አስተዋልኩ፡፡ ወይንጠጅና ነጭ ቀለም ያለው አበባ በማሳው ላይ ልዩ ውበት ተጎናጽፎ ትኩረቴን ሳበው፡፡ የአበባ እርሻ ልማት ነው እንዳልል ‹ግሪን ሀውስ› በሚባለው ውስጥ አይደለም፡፡ ጥቂት ከተመራመርኩ በኋላ ምን እንደሆነ ስጠይቅ የድንች ተክል እንደሆነ ነገሩኝ፡፡ እንዲህ ያለ አበባ እንዳለው አለማወቄ ለግብርና ሥራ ምን ያህል እሩቅ እንደሆንኩ ተረዳሁ፡፡ ውስጥ አዋቂ የሆነ ሰው ሲያጫውተኝ በዚህ ወቅት ድንች በአካባቢው በስፋት ይመረታል። ከጥቂት ጊዜ በኋላም ይደርሳል፡፡ ነዋሪው የአካባቢውን ብርድ የሚቋቋመው በድንች ነው። በእንስራ ተቀቅሎ ሰብሰብ ብሎ መብላት የተለመደ ነው፡፡ በአካባቢው ‹ቡትሌ› ተብላ በምትጠራ ጠርሙስ አብሮ አረቄ ይቀርባል። ውስጥ አዋቂው አጣፍጦ ሲያወራኝ እኔም ብርድ ብርድ ያለኝን ለማጥፋት ተመኘሁ፡፡ ምና ዋጋ አለው ድንቹ ገና በአበባ ላይ ነው፡፡ እንዲህ እያወጋን ቅዝቃዜውን ለማምለጥ ብንሞክርም እየመሸ ሲሄድ ቅዝቃዜው ባሰበት። እህል ውሃ ልንል ከሽኩቴ እስከ ጩሉጤ 62 ነጥብ ሁለት ኪሎሜትር የሚሸፍነውንና ሦስት ወረዳዎችን የሚያገናኘውን አስቸጋሪውን መንገድ ለመሥራት በተረከበው ገምሹ በየነ ተቋራጭ ካፕ ጎራ አልን፡፡ ከመመገቢያው አቅራቢያ በሚገኝ ዋርካ ላይ በአሮጌ ቆርቆሮ የተሸፈነ በመካከሉ ደግሞ በነጭ ወረቀት ላይ በትልቅ ፊደል ጽሁፍ ተንጠልጥሏል፡፡ ትኩረቴን ስለሳበው ጠጋ ብዬ ሳነበው ‹እዚህ ውስጥ ኮንዶም ይገኛል› የሚል ነበር፡፡ ማስታወቂያው ከተለጠፈበት አቅራቢም በራሱ ብረት ካልሆነ በእጅ ቢመቱት ድምጽ የማይሰጥ ብረትም ተጠልጥሏል፡፡ ደውል ሳይሆን አይቀርም፡፡ ኃላፊነትን መወጣት እንዲህ ነው፡፡ ‹ዝምታው ይሰበር› ተብሎ ኤች አይ ቪ ኤድስ\nበሽታ ላይ ርብርብ እንዳልተደረገ ዛሬ መልሶ ማሰራራቱ አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ እንደመንገድ ሥራ ባሉ ትላልቅ ፕሮጀክቶች ውስጥ የሚሰሩ ባለሙያዎች ለወራት ጊዜያቸውን የሚያሳልፉት ሥራው ባለበት አካባቢ በመሆኑ ትኩረቱ አስፈላጊ ነውና ይበል የሚያስብል ተግባር ነው፡፡ በነገራችን ላይ ለኤች አይቪ ቫይረስ በጣም ተጋላጭ ከሆኑ የሥራ ዘርፎች ውስጥ በካምፕ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ወይም ባለሙያዎች ይገኙበታል፡፡ በእነዚህ እና መሰል አካባቢዎች የግንዛቤ ሥራው እንዳለ ሆኖ በልቅ የግብረ ሥጋ ግንኙነት የሚመጣውን የቫይረሱን ስርጭት በእንዲህ መልኩ መቀነስ ይቻላል የሚለውን ተሞክተሮ መውሰድ ብልህነት ነው፡፡ ‹‹እዚህ ውስጥ ኮንዶም ይገኛል›› ብሎ የካምፑን ሠራተኞች መንገር ቢያንስ ባስፈለገ ጊዜ እንኳ ‹‹የለም›› ብሎ በመዘናጋት በቫየረሱ ከመጎዳት ይታደጓል፡፡ ለዚህም ነው በካምፑ የተተገበረው ሥራ ይበል የሚያስብል ምርጥ ተሞክሮ ነው ያልኩት፡፡ በዚህ ረገድ ከተሜው በየመዝናኛ ቤቱ ይህን በመሰለ ሁኔታ ሳይሆን በነፃ ጭምር በተለያዩ የሆቴል ኮርነሮችና ኮሪደሮች ቢቀመጥም ‹‹እምቢኝ›› ብሎ አይኑ እያየ ራሱን በቫይረሱ ሲያስለክፍ ማየት በዝቶ ነው ዛሬ መንግሥት ‹‹በቸልተኝነት የኤች አይቪ ቫይረስ ስርጭት ዳግም አገርሽቷል›› ሲል መግለጫም ሆነ ስለጠና ለመስጠት የተገደደው፡፡ እናስ ከእኛ ምን ይጠበቃል ብሎ ራስን መጠየቅ ግድ ነው። በመሆኑም የጎበዘ ራሱን ማቀብ፤ ካልተቻለ ደግሞ መጠቀም ግድ ይሆናል ማለት ነው፡፡ በካምፑ ውስጥ የታዘብኩት ይህ መልካም ሥራ በአቅራቢያው በሳሉ የአርሶ አደሮች መንደር ውስጥ ድረስ መዝለቅ ችሎ ይሆን ስል መየቅ ወደድኩ፡፡ እውነት ነው ቢያንስ እዛው ግቢ ውስጥ ተቀጥረው ያሉ ወጣቶች ለመኖራቸው አልጠራጠርም፡፡ እናም አገልግሎቱ ለእነዚህም የአካባቢው ነዋሪዎችም በሚሆን ልክ እንደሚሆን አምናለሁ፡፡ በአንድ ወቅት በዚህ ካምፕ ሳይሆን በሌላ ሥራ አጋጣሚ ወደ አንድ የገጠር አካባቢ ውስጥ ብዛት ያላቸው ሠራተኞች ያሉበት ካምፕ ውስጥ እንዲሁ ለሥራ እግር ጥሎኝ ነበር፡፡ በካምፑ የደረስነው ፕሮግራሙ ሊከናወን አንድ ቀን ሲቀረው ነበር፡፡ በመሆኑም የተለያዩ ዝግጅቶች እየተደረጉ ባለበት ወቅት ከሥራ ባልደረቦቼ ጋር በመሆን ካምፑን መቃኘት ያዝን፡፡ በአጋጣሚ አንዳንድ በቆርቆሮ በተሠሩ ቤቶች ጥጋጥግ ትላልቅ ካርቶኖች አልፎ አልፎ ተሰቅለው አየን፡፡ በዚያም አካባቢ ስናልፍ፤ አንድ ነጭ ጋወን የለበሰ ሰው ብዛት ያላቸውን ኮንዶሞች ከፌስታል እያወጣ በካርቶኖቹ ውስጥ ያስገባል፡፡ እንደ ድንገት አንድ የጊቢው ሠራተኛ የሚሆነውን ነገር አይቶ ሲገሰግስ መጣና ‹‹ቢሮ ድረስ መጥተን ስንጠይቅ የለም ያልከው ኮንዶም ዛሬ ከየት መጣ›› ሲል አቧረቀበት፡፡ አንድ አንድ ሲሉም ለጠብ ተዳርገው ለማገላገል የደረስንበትን አጋጣሚ አልዘነጋውም፡፡ አንዳንዱ ደግሞ ልክ እንደዚህ ለታይታ ኃላፊ ይመጣል በሚል የሚሠራ ሥራም እንዳለ ማወቅም ይገባል፡፡ ይህን እና መሰል ተያያዥ ሁኔታዎችን እቆዘምኩ ምሽቱ መጣ፤ ድካም ቢጤ ስላለኝ በጊዜ መኝታ ብንፈልግም ከምሽቱ ሦስት ሰዓት በፊት አልተሳካልንም፡፡ በጊዜ ወደ አዳር አለመሄዳችን ሲገርመን ንጋት 11 ሰዓት ላይ ለጉዞ ዝግጁ መሆን እንዳለብን ተነገረን። 60 ኪሎሜትር አባጣና ጎርባጣ መንገድ ስለሚጠብቀን ነበር ጉዞአችን በማለዳ የሆነው። ኪሎሜትሩን በእጥፍ ተጉዘን ነበር ከአቡና ግንደበረት ወረዳ የደረስነው፡፡ እኛ በአንድ ቀን እንዲህ ያለ ስሜት ከተሰማን የአካባቢው ነዋሪዎች ምን ሊሉ እንደሚችሉ መጠየቅ አይገባም፡፡ ከአቡና ግንደበረት እስከ ጊንጭ ድረስ ይሠራል ብለው ሲጠብቁና ሲጠይቁ ዓመታት ተቆጥሯል። ወረዳው በምዕራብ ሸዋ ዞን ከሚገኙ 22 ወረዳዎች አንዱ ሲሆን፣ በሰሜን አባይ፣ በምሥራቅ ሙርጋና ሙገር፣ በምዕራብ ጉደር፣ በደቡብ ደግሞ ቃሌና ቀላጤ በተባሉ ትላልቅ ወንዞች የተከበበ ነው፡፡ ነዋሪው በአንድ\nመንገድ ብቻ ነው የሚወጣውና\nየሚገባው፡፡ ‹በረት ውስጥ\nእንዳለ ከብት ነው ያለነው›\nያሉንም ነበሩ። በመንገድ\nምክንያት የአካባቢው ነዋሪዎች\nለከተማ ባዳ ሆነው\nዘመናትን ማስቆጠራቸውን ነበር\nየሰማነው፡፡ ለአንድቀን እንዲህ\nያማረረን መንገድ እነሆ\nመፍትሄ ሊያገኝ ሁለት\nዓመት ተኩል ጊዜ ተቆርጦለታል፡፡ ዕድሜ ለሰጠው\n2014 ዓ.ም መጀመሪያ ላይ መንገዱ\nአስፓልት ሆኖ አርሶ\nአደሩ ምርቱን ወደ ገበያ\nለማቅረብ እና ከከተማ\nወዳጅ ዘመዱ ጋር እንደልቡ\nለመጠያየቅ ይበቃል፡፡ እኔም\nለመመረቅ እበቃ ይሆናል፡፡አዲስ ዘመን ሰኔ 13/2011 ", "passage_id": "e164961c67becd67e9ab611ce08617fe" } ]
12e255637a899407252ae3f3bbb2e663
75d675f81bcb7e190c21aebd0b8a2bb8
193 አትሌቶች ከዓለም አትሌቲክስ የገንዘብ ድጋፍ ተጠቃሚ ይሆናሉ
የዓለም አትሌቲክስ ከዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር በኮሮና ቫይረስ ሥርጭት ምክንያት ከውድድር በመራቃቸው የገንዘብ ችግር ሊገጥማቸው ይችላል ለተባሉ አትሌቶች ድጋፍ እንደሚያደርግ ባለፈው ሚያዝያ መጨረሻ ማሳወቁ ይታወሳል። የዓለም አትሌቲክስ ለዚሁ ድጋፍ እንዲውል አምስት መቶ ሺህ ዶላር ማዘጋጀቱ የሚታወቅ ሲሆን ይህን ድጋፍ ለአትሌቶች ለማድረስ የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንቱ ሴባስቲያን ኮ በሊቀመንበርነት የሚመሩት የባለሙያዎች ቡድን ተቋቋሞ በስድስት ዞኖች በተከፋፈለው የዓለም አትሌቲክስ አባል አገራት የሚገኙ አትሌቶች የሚያቀርቡት የድጋፍ ጥያቄ ተጣርቶ ዕርዳታው መሰጠት ጀምሯል። በዚህም መሠረት መቶ ዘጠና ሦስት አትሌቶች ተለይተው ድጋፉ እንደደረሳቸው ታውቋል። ዕርዳታው የሚሰጣቸው አትሌቶች ከሃምሳ ስምንት የዓለም አትሌቲክስ አባል አገራት ፌዴሬሽኖች የተለዩ ሲሆን እያንዳንዳቸው በመጀመሪያው ዙር ድጋፍ ሦስት ሺህ ዶላር እንደሚደርሳቸው ተጠቆሟል። የድጋፍ ጥያቄውን ለማቅረብ የተሰጠው ቀነ ገደብ ባለፈው የፈረንጆች ግንቦት ሰላሳ ቀን የተጠናቀቀ ሲሆን ሁለት መቶ ስልሳ አንድ አትሌቶች የድጋፍ ጥያቄውን አቅርበው ጉዳዩን የሚመረምረው የባለሙያዎች ቡድን በተቀመጠው መስፈርት መሠረት አጣርቶ መቶ ዘጠና ሦስት አትሌቶች ድጋፉን እንዲያገኙ ውሳኔ አሳልፏል። የባለሙያዎቹ ቡድን ድጋፉን ለመስጠት በዋናነት ከተመለከታቸው መስፈርቶች መካከል አንድ ድጋፍ የሚሻ አትሌት በቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ አገሩን ለመወከል የተመረጠ መሆን እንዳለበት፣ ለገጠመው የገንዘብ ችግር አሳማኝ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፣ ካለፈው የውድድር ዓመት አኳያ የሚያገኘው ገቢ በእጅጉ የቀነሰና ከአበረታች መድሃኒት ተጠቃሚነት ጋር በተያያዘ ምንም አይነት ክስ ያልቀረበበት መሆን እንደሚገባው ጠቁመዋል። በተጨማሪም በየትኛውም የውድድር አይነት በዓለም አትሌቲክስ የደረጃ ሰንጠረዥ ከአንድ እስከ ስድስት ባለው ውስጥ ስማቸው የሰፈረ አትሌቶች፣ በ2019 በየትኛውም የወርቅ ደረጃ ባለው የጎዳና ላይ ውድድር እስከ ስድስት ባለው ደረጃ ያጠናቀቁ እንዲሁም በ2019 የዳይመንድ ሊግ ውድድሮች እስከ ስልሳ ሺህ ዶላር ድረስ ሽልማት ያገኙ አትሌቶች የድጋፍ ጥያቄያቸው ተቀባይነት እንደሌለው ታውቋል። ድጋፉን የሚያገኙ አትሌቶች ወይም አገራት ስም ያልተጠቀሰ ሲሆን ጥያቄያቸው ተመርምሮ ድጋፍ የሚደረግላቸው አትሌቶች በዚህ ሳምንት መጨረሻ ገንዘቡ እንደሚደርሳቸው ተጠቁሟል። የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንት እንዲሁም የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፋውንዴሽን ሊቀመንበር ሴባስቲያን ኮ ይህን ድጋፍ ለአትሌቶች ለመስጠት እንደታሰበ በሰጡት መግለጫ ወቅት እንዳስቀመጡት፣ የገንዘብ ድጋፉ ባለፉት ጥቂት ወራት ከውድድር በመራቃቸው ምንም አይነት ገቢ አጥተው የገንዘብ ቀውስ ውስጥ ለገቡ አትሌቶች ይውላል። እ.ኤ.አ በ1986 በሞናኮው ልዑል አልበርት ሁለተኛ አማካኝነት በአትሌቲክስ ስፖርት ለሚገጥሙ ችግሮች የበጎ አድራጎት ሥራዎችን ለማከናወን የተቋቋመው የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፋውንዴሽን ካለው በጀት ላይ ቀንሶ አትሌቶች በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ለገጠማቸው ችግር ድጋፍ እንዲውል ማድረጉ ይታወቃል። ድጋፉን ለመስጠት ከተቋቋመው ኮሚቴ መካከል የቀድሞው የኦሊምፒክ የ1500 ሜትር አሸናፊው ሞሮኳዊ አትሌት ሂቻም ኤልግሩዥ፣ የምርኩዝ ዝላይ የዓለም ቻምፒዮኗ ካተሪና ስቲፋኒዲ (የዓለም አትሌቲክስ ኮሚሽንን ወክላ)፣ የዓለም አትሌቲክስ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ሱኒል ሳብሃርዋልና ኤቢይ ሆፍማንና ሌሎችም ተካተዋል። ‹‹ሂቻም ኤልግሩዥ ይህን የድጋፍ ሃሳብ በማቅረቡና ልዑል አልበርት ይህን ፕሮጀክት እውን ለማድረግ ላበረከተው ጠንካራ ድጋፍ ላመሰግናቸው እወዳለሁ›› በማለት ሃሳባቸውን ያሰፈሩት ሴባስቲያን ኮ፣ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ከዓለም አትሌቶች ጋር በተለያየ መንገድ የቅርብ ግንኙነት እንዳላቸው በመጠቆም ዓለም አቀፍ ውድድሮች በመሰረዛቸው በርካታ አትሌቶች የገቢ ምንጫቸው እንደ ደረቀና የገንዘብ ችግር እንደገጠማቸው አብራርተዋል። በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የዓለም አትሌቲክስ ውድድሮች በእጅጉ መጎዳታቸውን ያስታወሱት ኮ፣ አትሌቶች ገቢያቸው ከውድድር የሚያገኙት ሽልማት እንደመሆኑ በዓመቱ መጨረሻ የተወሰኑ ውድድሮችን በማካሄድ ስፖርቱንና አትሌቶቹን እንዳይዳከሙ የማድረግ ተስፋ እንዳላቸው ተናግረዋል። አትሌቶችን ለመደገፍ አሁን ከተያዘው በጀት ባሻገር የስፖርት ቤተሰቡ በሚያደርገው ድጋፍ ተጨማሪ የረድኤት ሥራዎች እንደሚከናወኑም ጠቁመዋል። ልዑል አልበርት ሁለተኛ በበኩላቸው ፋውንዴሽኑን ከመሠረቱ ከሰላሳ አምስት ዓመታት በላይ እንደሆነ በማስታወስ የፋውንዴሽኑ አላማ አትሌቲክስን ማበረታታትና ብሔራዊ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች እንዲሁም አትሌቶች በችግር ጊዜ የገንዘብ ዋስትና እንዲኖራቸው ማድረግ መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህም መሠረት ፋውንዴሽኑ ባለፉት ዓመታት ሰላሳ ሚሊየን ዶላር ለተመሳሳይ አላማ እንዳዋለና አሁንም አትሌቶች በሚቸገሩበት በዚህ ወቅት ሊደርስላቸው በመቻሉ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል። ይህ ድጋፍ አትሌቶች ኦሊምፒክን ጨምሮ ለዓለም አቀፍ ውድድሮች የሚያደርጉትን ዝግጅት እንዳያቋርጡና በገጠማቸው ችግር ውጥረት ውስጥ እንዳይገቡ ሊረዳቸው እንደሚችልም አክለዋል። የቀድሞው የ1500 ሜትር የዓለም ክብረወሰን ባለቤትና የድጋፉ ሃሳብ አመንጪ አትሌት ኤልግሩዤ በበኩሉ፣ የኮሮና ቫይረስ በሁሉም ዓለም ሕዝብ ላይ ትልቅ ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖ እንዳሳደረ በማስታወስ ሁሉም የዓለም ሕዝብ ይህን ችግር ለመጋፈጥ በጋራ የሚቆምበት ወቅት አሁን መሆኑን አብራርቷል። የዓለም አትሌቲክና ፕሬዚዳንቱ የድጋፍ ሃሳቡን በቅንነት ስለተቀበሉትም ምስጋናውን አቅርቧል። ዓለም አቀፍ ውድድሮች በመታገዳቸውም በርካታ አትሌቶች ሊደርስባቸው የሚችለውን የኢኮኖሚ ጫና በማሰብ ይህን በጎ ተግባር መፈፀም እንደሚያኮራም ተናግሯል፡፡አዲስ ዘመን ሰኔ 18/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=35069
[ { "passage": "በኢትዮጵያ አትሌቲክስ አንጋፋውና ያለምንም መቆራረጥ በየዓመቱ ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ማክሰኞ ይጀምራል። ዘንድሮ ለ48ኛ\nጊዜ የሚካሄደው ይህ ውድድር ሁሉንም የአትሌቲክስ እና የሜዳ ላይ ተግባራትን አካቶ የሚከናወን ሲሆን፤ ለዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሚኒማ ማሟላት የሚችሉ አትሌቶችም የሚታጩበት መድረክ ነው። ባለፉት ዓመታት ከዚህ ውድድር በርካታ ብርቅዬ አትሌቶች የፈሩ ይሁን እንጂ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን መቀዛዝ እየተስተዋለበት ይገኛል። በተለይ በውጪ ሃገራት ውድድሮች ላይ ተሳታፊ የሆኑ ታዋቂ አትሌቶች በሃገር ውስጥ ውድድሮች አለመታየታቸው በብዙዎች ዘንድ ወቀሳ እንዲሰነዘርበት ያደርጋል። በመሆኑም በዚህ ዓመት በርካታ ታዋቂ አትሌቶች የተሳተፉ ሲሆን፤ አማን ወጤ፣ ጫላ በዮ፣ ዲኖ ስፍር፣ አንዷምላክ በልሁ፣ አባዲ ሃዲስ፣ የኔው አላምረው፣ ሰለሞን ባረጋ፣ አዲር ጉር፣ … በወንዶች በኩል ተሳታፊ የሚሆኑ አትሌቶች ናቸው። በሴቶች በኩልም፤ ደራ ዲዳ፣ ነጻነት ጉደታ፣ በላይነሽ ጉደታ፣ ሱሌ ኡቱራ፣ ብርትኳን ፈንቴ፣ ህይወት አያሌው፣ ፎቴን ተስፋይ፣ ሰንበሬ ተፈሪ፣ አራያት ዲቦ፣… ከተካፋዮቹ ጥቂቶቹ ናቸው። የዚህ ውድድር ዓላማ፤ ለአትሌቶች የሃገር ውስጥ የውድድር ዕድሎችን ከመፍጠርም ባሻገር በክልሎች፣ ከተማ አስተዳደሮችና ክለቦች መካከል ፉክክር ለመፍጠር እንዲሁም ለብሄራዊ ቡድን የሚሆኑ አትሌቶችን ለመምረጥ ነው። ውድድሩን ለማካሄድ ዝግጅቱ የተጠናቀቀ ሲሆን፤ 2ነጥብ1 ሚሊዮን\nብር በላይ በጀት ተመድቦለታል። ለውድድር የሚሆኑት ቁሳቁሶችና ግብዓቶች ከመሟላታቸውም በላይ ውድድሩን የሚመሩ አደረጃጀቶች መፈጠራቸውንም በፌዴሬሽኑ ጋዜጣዊ መግለጫ በተሰጠበት ወቅት ተጠቅሷል። ማክሰኞ በሚጀመረው ሻምፒዮና ላይም ከዘጠኝ ክልሎችና ሁለት ከተማ አስተዳደሮች  እንዲሁም ከ36 ክለቦች\nየተወጣጡ አንድ ሺ376 አትሌቶች ተሳታፊ ይሆኑበታል። ይህም ካለፈው ዓመት ሻምፒዮና ጋር ሲነጻጸር በ122 አትሌቶች ብልጫ የታየበት ነው። ውድድሩ የሚመራውም፤ በ80የአትሌቲክስ ዳኞች፣ 45 የፌዴሬሽኑ አመራሮችና ባለሙያዎች፣ 3 የህክምና ባለሙያዎችና አንድ አምቡላንስ፣ 32 በጎ ፍቃድ አገልጋዮች እንዲሁም ሌሎች ስራዎችን የሚያከናውኑ ሙያተኞች እንደሆነም ታውቋል። የመክፈቻ መርሃ ግብሩ በቴሌቪዥን የቀጥታ ስርጭት ሽፋን የሚሰጠው ሲሆን፤ የማጣሪያ እና የፍጻሜ ውድድሮችም ይካሄዳሉ። ጠዋት ከሚካሄዱ ውድድሮች መካከል የሴቶች አሎሎ ውርወራ እና የወንዶች ሱሉስ ዝላይ ፍጻሜያቸውን ያገኛሉ። በ800፣\n400እና 100 ሜትር የወንድ እና ሴት የማጣሪያ ውድድሮችም ይካሄዳሉ። በኦሊምፒክ ባህል መሰረት የውድድሩ የመክፈቻ ዝግጅት አመሻሹ ላይ የሚካሄድ ሲሆን፤ ውድድሮችም ይኖራሉ። በዚህም መሰረት የሴትና ወንድ የ10ሺ ሜትር የፍጻሜ እንዲሁም የ100ሜትር\nእና 400 ሜትር የግማሽ ፍጻሜ ውድድሮች በሁለቱም ጾታ ይከናወናሉ። በ42ቱ ውድድሮች አሸናፊ ለሚሆኑ አትሌቶችም የ2ሺ፣ 1ሺ400 እና 1ሺ\nብር ሽልማት እንደየደረጃቸው የሚያስገኝ ይሆናል። ክብረወሰን ለሚያሻሽሉ እና ከሶስት ወርቅ በላይ ለሚያስመዘግቡ አትሌቶችም 6ሺ ብር ተጨማሪ ሽልማት የሚያገኙ ሲሆን፤ ሁለት ወርቅ ለሚያጠልቁ አትሌቶች ደግሞ 5ሺ\nብር ይሰጣቸዋል። በአጠቃላይ አሸናፊ ለሚሆኑት አተሌቶችም 20ሺ፣ 16ሺ\nእንዲሁም 10ሺ ብር ይበረከትላቸዋል። ውድድሩ እስከ መጪው ግንቦት 04 ቀን\n/2011ዓም ለስድስት ተከታታይ ቀናት የሚካሄድ ሲሆን፤ የአትሌቲክስ ስፖርት ወዳዱ ህብረተሰብ በአዲስ አበባ ስታዲየም ተገኝቶ ስፖርቱን እንዲደግፍም በፌዴሬሽኑ ጥሪ ቀርቧል።አዲስ\nዘመን ሚያዚያ 27 ቀን 2011 ዓ.ምብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "c62f6ebc98c2034cb7a51852ca61282a" }, { "passage": "ስለ ኢትዮጵያ ማወቅ የሚፈልግ ማንኛውም ሰው ሰነዶችን ቢበረብር፣ መረጃዎችን ቢያገላብጥ፣ ወይም በይነ መረቦችን ቢያስስ ከተፈጥሮና ሰው መሰራሽ ሀብቶቿ መካከል አንዱ አትሌቲክስ መሆኑን ይገነዘባል። ኢትዮጵያ በዓለም ሕዝብ ዘንድ ከእውቅናም በላይ ከበሬታን እንድታገኝ ካደረጉ ጉዳዮች መካከል በኦሊምፒክ ማራቶን የወርቅ ሜዳሊያ ያጠለቀ የመጀመሪያው ጥቁር አትሌት የአበበ ቢቂላ አገር መሆኗ ትልቅ ድርሻ አለው። መረጃዎች አበበ ቢቂላ በባዶ እግሩን ሮጦ ከማሸነፉም በላይ ከአራት ዓመታት በኋላም ከዓለም ክብረወሰን ጋር ድርብ ድል መቀዳጀቱን ሳያስታውሱ አያልፉም። ስፖርቱን፣ አሸናፊነቱንና ክብሩን ትውልድ እየተቀባበለ ለዘመናት ማኖሩም በወርቅ ቀለም የተጻፈ የታሪክ አካል ነው። አትሌቲክስ ለኢትዮጵያ በቻምፒዮናዎች እና የኦሊምፒክ መድረኮች ላይ በመም፣ በጎዳና ወይም በሀገር አቋራጭ ውድድር ሜዳሊያ የምታስመዘግብበት ዘርፍ ብቻም አይደለም። ከኩራትና የአንድነት ስሜት ምንጭነቱ ባሻገር ሀገር ትለማና ትበለጽግ ዘንድ የበኩሉን በማድረግ እየተረባረበ ነው። ብርቅየ አትሌቶች በሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ፤ የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት፣ በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ፣ በአግሮ ኢንዱስትሪ፣ በኮንስትራክሽን፣ በአውቶሞቲቭና በመሳሰሉት ዘርፎች በመግባት ለወጣቱ የስራ እድል በመፍጠር ረገድ የራሳቸውን አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ። ስፖርቱ መዋዕለ ንዋዩን በማፍሰስ የድርሻውን ከመወጣት ባለፈም ሀገራዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይም ቅድሚያና ቀጥተኛ ተሳታፊ መሆኑም እሙን ነው። በተለያዩ ጊዜያት በፌዴሬሽኑ፣ በአትሌቶችና በሙያ ማህበራት በተናጠልና በቡድን የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ለማውሳትም፤ ከወቅታዊው የኮሮና ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ የተከናወነውን ስራ በምሳሌትነት ማንሳት ይቻላል። የገንዘብና የቁሳቁሰ ድጋፍ ከማድረግም ባለፈ በማዕድ ማጋራት ላይም ፌዴሬሽኑ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከት ችሏል። አሁንም መንግስት በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታና የውሃ ሙሌት ላይ የያዘውን አቋም በጽኑ እንደሚደግፍ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ግንባታው እስኪጠናቀቅ ድረስም የአትሌቲክስ ቤተሰቡ ከመንግስትና ከህዝብ ጎን የሚቆም መሆኑንም በድረገጹ ባወጣው መግለጫ አስነብቧል። ለረጅም ዓመታት ሲጓተት የቆየው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሂደቱ እየተፋጠነና የውሃ ሙሌቱም በተያዘው\nክረምት  የሚጀመር መሆኑን መንግስት ይፋ ማድረጉን ተከትሎ ነው ፌዴሬሽኑ የድጋፍ መግለጫውን ያወጣው። በዚህም የፌዴሬሽኑ አመራሮችና ሰራተኞች፣ አትሌቶች፣ የአትሌት ተወካዮችና አሰልጣኞች፣ የአትሌቲክስ ዳኞች እንዲሁም በስፖርት ቤተሰቡ በቁርጠኝነት እንደሚደግፍ ጠቁሟል። ፌዴሬሽኑ ከዚህ ቀደም ቦንድ በመግዛትና ድጋፍ በማሰባሰብ፣ ከዚሁ ጎን ለጎን የፌዴሬሽኑ አመራሮችና የአትሌቲክሱ ቤተሰብ በስፍራው በመገኘት ግንባታውን መመልከቱ ይታወሳል። ከ40ሺ በላይ ሯጮችን ያሳተፉ የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድሮችን በማካሄድም የግድቡን ግንባታ የሚደግፉ አካላትን የማነቃቃት ስራም አከናውኗል። በቅርቡም ፌዴሬሽኑ ለሕዳሴው\nግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ\nጽህፈት ቤት የገንዘብ\nድጋፍ አበርክቷል። አባይና የህዳሴ ግድቡ ለአትሌቶችና የኢትዮጵያ\nአትሌቲክስ ፌዴሬሽን እንደማንኛውም\nየህብረተሰብ ክፍል የህልውና\nጥያቄ በመሆኑም በአካል በቦታው  በመገኘት፣ ለግንባታው በማስተባበር፣ አቅም የፈቀደውን የገንዘብ አስተዋጽኦ በማድረግ እንዲሁም በግልና በቡድን ለግንባታው የሚያግዙ የዲፕሎማሲ ስራዎችም በተጨማሪነት እየተሰሩ እንደሚገኙም በመግለጫው ተመልክተዋል። ይህ ሂደት የአንድ ወቅት ብቻ ባለመሆኑ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኑ ድጋፉን አጠናክሮ በመቀጠል፤ ስራው እንደ ድል አድራጊ አትሌቶች በጽናትና በቁርጠኝነት እንደሚጠናቀቅም እምነት ተጥሎበታል። ፌዴሬሽኑ ከግድቡ ባሻገር የደም ልገሳና አረንጓዴ አሻራን ለማሳረፍ የችግኝ ተከላ በቅርቡ ለማካሄድም በዝግጅት\nላይ ይገኛል። በዓለምና\nሀገር አቀፍ ደረጃ እየተስፋፋ በሚገኘው\nየኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ\n(ኮቪድ 19) ምክንያት እየተከሰተ\nያለውን የደም እጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት የደም ልገሳ መርሃ ግብር በማዘጋጀት\nፌዴሬሽኑ ለስፖርቱ ቤተሰቦች\nጥሪ አድርጓል። በቀጣይ ሳምንት ሰኔ  16/2012 ዓም ከማለዳው ሶስት ሰዓት ጀምሮ የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት፣ የቢሮ ሰራተኞች፣ አንጋፋ አትሌቶች፣ አሰልጣኞች፣ የአትሌት ተወካይ ማናጀሮች፣ ሁሉም የአትሌቲክስ ማህበራት አመራሮች፣ የክለብ አመራሮች በአጠቃላይ የአትሌቲክሱ ቤተሰብ በፌዴሬሽኑ አስተባባሪነት የደም ልገሳውን ለማካሄድ ቀጠሮ ይዛል። ፌዴሬሽኑ ከኢትዮጵያ ደም ባንክ አገልግሎት ጋር በመተባበር ባዘጋጀው ታሪካዊና አገራዊ ጉዳይ ላይ ሁሉም የድርሻውን እንዲያበረክትም ጥሪውን አስተላልፏል። በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተመናመነ ያለውን የሀገሪቷን የደን ሽፋን እንዲያገግም ለማድረግም ከመንግስት ጎን በመቆም የአረንጓዴ አሻራን በችግኝ ተከላ ለማሳረፍም እቅድ ይዟል። የአትሌቶች የህይወት ምንጭ የሆኑትን የዛፍ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የትና መቼ እንደሚከናወን በቅርቡ እንደሚያሳውቅም ጠቁሟል።  አዲስ ዘመን ሰኔ10/2012ብርሃን ፈይሳ ", "passage_id": "d8d94b43638fd2e8af912cafe5230dad" }, { "passage": "አትሌቲክስ ውድድሩ በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ስታዲየም መካሄድ መጀመሩን ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ባወጣው መረጃ አስታውቋል።በዛሬው እለትም የአሎሎ ውርወራ ማጣሪያና ፍፃሜ፣ የስሉስ ዝላይ ማጣሪያና ፍፃሜ ውድድሮች እንደሚካሄዱ የወጣው መርሃ ግብር ያመለክታል።እንዲሁም ከ100 ሜትር እስከ 800 ሜትር የማጣሪያ ውድድሮች እንደሚካሄዱ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።", "passage_id": "ef0cac2523d80209c971130f6b564b5f" }, { "passage": "በቅርቡ በተጠናቀቀው የዶሃ ዓለም ቻምፒዮና በሴቶች በተካሄደው የማራቶን ውድድር ከተሳተፉት 68 አትሌቶች\nመካከል 28ቱ ውድድሩን ማቋረጣቸው የሚታወስ ነው። ለዚህ ምክንያት የሆነውም በዶሃ የነበረው ከፍተኛ ሙቀትና ወበቅ መሆኑ ተነግሯል።\nከአንድ ዓመት ያነሰ ጊዜ የሚቀረው የቶኪዮ ኦሊምፒክም ከፍተኛ ሙቀት እክል ሊሆንበት እንደሚችል ስጋት ተፈጥሯል፡፡ ይህንን ተከትሎም\nዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ የማራቶን እና የእርምጃ ውድድር ቀደም ብሎ ሊካሄድበት ከታሰበው ከተማ ለውጥ ለማድረግ ማሰቡን አስታውቋል።\nበከባድ ሙቀት ምክንያት በውድድሩ ላይ የሚደርሰውን ተጽእኖ ለመቀነስ ሲባልም በተሻለ መጠን ነፋሻማ\nየአየር ሁኔታ ያለው አካባቢ አስፈልጓል። በመሆኑም ቀድሞ ከታሰበው የኦሊምፒኩ ዋና መዳረሻ ቶኪዮ ወደ አገሪቷ ሰሜናዊ ክፍል ለማሸጋገር\nመታሰቡን የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር በድረ-ገጹ አስነብቧል። በ800ኪሎ ሜትር ርቀት በሆካኢዶ ተራራማ አካባቢዎች\nየሚገኘው ሳፖሮ የተባለው ይህ ስፍራ ውድድሩ በሚካሄድበት ወቅት የአየር ሁኔታው በተሻለ መጠን የሚቀዘቅዝ መሆኑ አትሌቶችን እንደሚረዳቸው\nይታሰባል። ስፍራው እ.አ.አ 1972 የክረምት ኦሊምፒክ የተካሄደበትም ነው። የውድድሩ አዘጋጅ ኮሚቴ፣ የኦሊምፒክ ኮሚቴ እንዲሁም የማህበሩ የጤና ባለሙያዎችና አማካሪዎች እንዳስታወቁት\nኦሊምፒኩ የሚካሄደው በበጋው ወቅት በመሆኑ የቶኪዮ ከተማ የሙቀት መጠን በከፍተኛ መጠን ይጨምራል። ይህም በአትሌቶች ላይ እንዲሁም\nበውድድሩ ላይ ተጽእኖ ማሳደሩ እንደማይቀር አጽንኦት መስጠታቸውን ተከትሎ የቦታ ለውጥ ለማድረግ መታቀዱ ታውቋል፡፡ ሙቀቱ ከማራቶን\nእና እርምጃ ውድድሮች ባሻገር የ5ሺ ሜትር እና 10ሺ ሜትር ውድድሮች እንደተለመደው በቀኑ ክፍለ ጊዜ ሳይሆን ሌሊት ላይ ለማካሄድ\nሊያስገድድ እንደሚችልም ተነግሯል፡፡ ከረጃጅም ርቀት አትሌቲክስ\nባሻገር ላሉ ሌሎች ስፖርቶችም በተመሳሳይ ሙቀቱ አስቸጋሪ ሊሆን ስለሚችል የተለያዩ እገዛዎች እንደሚደረጉም ተጠቁሟል። ይህም መጠለያዎችን\nበማበራከት እንዲሁም የውሃ ማቀዝቀዣ፣ ከፍተኛ የውሃ አቅርቦት እንዲኖርና አትሌቶች ዝግጅት በሚያደርጉበት ወቅት በመረዳት ነው።\nከዚህ ባሻገር በተያዘው የፈረንጆቹ ወር መጨረሻ በሚደረገው ስብሰባ ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን በውድድሩ ስፍራ ለውጥ\nእንዲሁም በኦሊምፒኩ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ለማድረግ ቀጠሮ ተይዟል። የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ\nኮሚቴ ፕሬዚዳንት ቶማስ ባች ባደረጉት ገለጻም «የአትሌቶች ጤና እና ደህንነት ቀዳሚው ጉዳይ ነው። አትሌቶችን ከጉዳት ለመታደግም\nበርካታ ኪሎ ሜትሮችን በመጓዝ ለውጥ ከማድረግ ላይ ደርሰናል፤ ይህም ምን ያህል ትኩረት እንደምንሰጥ የሚያሳይ ነው። ኦሊምፒክ ማለት\nአትሌቶች በህይወት ዘመናቸው የሚያሳኩት ሁነት ነው፤ በመሆኑም ብቃታቸውን ማሳየት አለባቸው። ለዚህ ሥራም እየተባበረን ያለውን ማህበር\nማመስገን ይገባል» ብለዋል። የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ፕሬዚዳንት ሰባስቲያን ኮ\nበበኩላቸው «ከዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እና ከ2020 የቶኪዮ ኦሊምፒክ አዘጋጆች ጋር በቅርበት ስንሰራ ቆይተናል። አትሌቶች\nብቃታቸውን ያሳዩ ዘንድ አስፈላጊውን ሁሉ ልናመቻችላቸው ይገባል፤ በመሆኑም ለማራቶን እና እርምጃ ተወዳዳሪዎች የሚሻል የአየር ሁኔታ\nወዳለው ስፍራ ለውጥ ማድረግ አስፈልጓል» ሲሉ አብራርተዋል። አዲስ\nዘመን ጥቅምት 7/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "7950094d223266e4116e23d57df4ffa9" }, { "passage": "የዓለም አትሌቲክስ በየዓመቱ በሚያዘጋጀው ምርጥ ሴት አትሌቶች ሽልማት ኢትዮጵያዊቷ ለተሰንበት ግደይ እና ኬንያዊቷ ፔረስ ጀፕቺርቺር ከመጨረሻዎቹ አምስት እጩዎች ዝርዝር ውስጥ መግባታቸው ተገለፀ።የዓለም አትሌቲክስ ማክሰኞ እለት በአስሩ ዝርዝር ውስጥ ገብተው ከነበሩ አትሌቶች አምስት ለመጨረሻው ዙር መመረጣቸውን አስታውቋል።ሌሎች ሦስት አፍሪካዊያን አትሌቶች አስሩ ዝርዝር ውስጥ ተካተው የነበረ ቢሆንም 5ቱ ዝርዝር ውስጥ ግን መግባት ሳይችሉ ቀርተዋል። እነዚህ አትሌቶች ኢትዮጵያዊቷ አባበል የሻነህ፣ ኬንያዊያኖቹ ዶ ፌዝ ኪፕየጎን እና ሔለን ኦቢሪ ናቸው። ሌሎቹ በአምስቱ ዝርዝር ውስጥ መካተት ያልቻሉት አትሌቶች ደግሞ የኔዘርላንዷ ፌምኬ ቦል እና እንግሊዟ ላውራ ሙር ናቸው። የዘንድሮው ዓመት የዓለም አትሌቲክስ ሽልማት ሥነ ሥርዓት በቨርቹዋል [ኢንተርኔት] በአውሮፓዊያኑ ታህሳስ 5 የሚካሄድ ሲሆን በማኅበራዊ ሚዲያም በቀጥታ ይሰራጫል ተብሏል።የዓመቱ ምርጥ ሴት አትሌት 5ቱ እጩዎች ለተሰንበት ግደይ በ5000 ሜትር በ14፡06፡62 በመግባት የዓለም ክብረ ወሰንን ሰብራለች። ቫሌንሺያ በተደረገው በዚህ ውድድር በጥሩነሽ ዲባባ ለአስራ ሁለት ዓመታት ተይዞ የነበረውን ክብረ ወሰን አሻሽላለች ተብሏል። የ22 ዓመቷ ሯጭ የገባችበት ሰዓትም 14 ደቂቃ ከ6.62 ሰኮንዶች ሲሆን የጥሩነሸ ደግሞ 14 ደቂቃ ከ11.15 ሰከንዶች ነበር። በሞናኮ በተካሄደው በዋንዳ ዲያመንድ ሊግም 5000 ሜትር ሩጫ በሁለተኛ ደረጃነት አጠናቃለች።ሲፋን ሐሰን 18,930 ሜትር በአንድ ሰዓት ጊዜ በመሮጥ የዓለም ክብረ ወሰን ይዛለች።በ10 ሺህ ሜትር በ29፡36፡67 በማጠናቀቅም የአውሮፓ ክብረወሰን ያስመዘገበች ሲሆን በታሪክ አራተኛዋ ፈጣኗ ሯጭ ተብላለች።የዓለም ግማሽ ማራቶን አሸናፊ ናት። በሴቶች ውድድር 1፡ 05፡34 እና 1፡ 05፡ 16 ሰዓት በመግባት የግማሽ ማራቶን ክብረወሰንን ሁለት ጊዜ ሰብራለች። በቤት ውስጥና ከቤት ውጭ በተደረጉ አራት የርዝመት ዝላይ ውድድሮች አሸንፋለች። በቤት ውስጥ በተካሄደ የርዝመት ዝላይ ውድድር 15.43 ሜትር በመዝለል የዓለም ክብረ ወሰን ሰብራለች።በሰባት የ100 ሜትር ውድድሮች አሸንፋለች። በዓለም መሪነት 100 ሜትር በ10.85 ሰከንድ ሮጣለች።ከእነዚህ እጩዎች አሸናፊውን ለመለየት ሦስት የድምፅ አሰጣጥ መንገዶች አሉ። የዓለም አትሌቲክስ ምክር ቤት እና የዓለም አትሌቲክስ ቤተሰቦች ድምፃቸውን በኢሜይል የሚሰጡ ሲሆን አድናቂዎቻቸው ደግሞ በማኅበራዊ ሚዲያዎች ድምፅ ይሰጣሉ።ከአጠቃላይ ድምፁ የምክር ቤቱ ድምፅ 50 በመቶ ይይዛል። የአትሌቲክስ ቤተሰቦችና የሕዝብ ድምፅ ደግሞ እያንዳንዳቸው 25 በመቶ ይይዛሉ።", "passage_id": "1c9fb30285376b6cc7e0266af37b4de5" } ]
43f84f0643448661baa01e76912a2519
de84553d3b9ca59f08c85d8542247898
ከቤሌር ሜዳ እስከ ቤልጂየም የዘለቀው ኮከብ
በኢትዮጵያ እግር ኳስ አፍቃሪ ልብ ውስጥ በብዙ የሚታወስ ነው። እግር ኳስን ከልጅነት እስከ እውቀቱ ተጫውቷል። አሁንም ቢሆን ከክቧ ኳስ አልራቀም። የቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ የቡድን መሪ ሆኖ አገልግሏል። ባዩ ሙሉ። የመጀመሪያውን የምሥራቅ አፍሪካ የታዳጊዎች ቻምፒዮና ለኢትዮጵያ ዋንጫ ይዘው ከመጡ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ሲሆን በጊዜው የእርሱ ድርሻ ጉልህ ነበር። ከዚህም ሌላ ኬንያ ባዘጋጀችው «የሴካፋ ቻምፒዮና» ላይ ኮከብ ተጫዋች ሆኖ ለመመረጥም በቅቷል። በምሥራቅ አፍሪካ ውድድር ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአገር ውጪ ሩዋንዳ ላይ ዋንጫ ስታነሳ በፍፃሜው ጨዋታ ላይ የማሸነፊያዎቹን ሁለት ግቦች አስቆጥሯል። ባዩ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ዓመት በዋናው ክለብ ተሰልፎ ተጫውቷል። በፕሮፌሽናል ተጫዋችነትም ቢሆን በር ከፋች ነው። በቤልጂየም አገር ለረጅም ጊዜ ለተለያዩ ክለቦች ተጫውቷል። አንጋፋዋ የቀበና ቤሌር ሜዳ ካበቀለቻቸው የአገር ባለውለታዎች ተርታም የሚመደብ ነው። እኛም በዛሬው የስፖርት ማህደር አምዳችን የዚህን ተጫዋች ህይወት በስፋት ለመዳሰስ ወደድን። የልጅነት ትውስታ የቤሌር ሜዳ በኢትዮጵያ በተለይም በአዲስ አበባ ተወላጆች ዘንድ ትልቅ ቦታ አለው። ቀበና መድሀኒ ዓለም ቤተክርስቲያን አካባቢ የሚገኘው ይህ ሜዳ በርካታ አንጋፋ የእግር ኳስ ተጫዋቾችን አፍርቷል። ቤሌር በርካታ አንጋፋ ተጫዋቾች የወጡበት ነው። ሜዳው እግር ኳስን ከንጋት ጀምሮ ሰማዩ ለአይን እስኪይዝ ድረስ የአካባቢው ተወላጆች እና ከሌላ ሰፈር የሚመጡ ታዳጊዎች ዛሬም ድረስ የሚጫወቱበት ነው። የያኔው ታዳጊ ባዩ ደግሞ ከዚህ ሜዳ ጀርባ በሚገኙ መንደሮች ውስጥ ነበር ተወልዶ ያደገው። ጊዜውም 1971 ዓ.ም ነው። ንጉሴ ገብሬን፣ ሰለሞን ሀይለ ማሪያምንና ሲሳይ ሽፈራውን የመሳሰሉ አንጋፋ ተጫዋቾችን ተመልክቶ ኳስ እያቀበለ ነው ያደገው። ባዩ እግር ኳስ በልጅነት ልቦናው ውስጥ ትልቅ ስፍራ እንዲኖረው አንጋፋ ተጫዋቾች ድርሻ ነበራቸው። ለቤሌር ታዳጊዎች እግር ኳስ ከምንም ነገር በላይ ነው። እንደ መዝናኛ፣ ጊዜ ማሳለፊያ እና ተስፋ ያለው ጎበዝ እግር ኳስ ተጫዋች የመሆን ህልምን እንደማሳኪያ ያገለግላል። በዚህ እድል ውስጥ ያለፈው ባዩ በፍቅር ከሚያንከባልላት ኳስ ጋር የእድሜ ዘመን ወዳጅነትን መስርቷል። ከትምህርት ቤት መልስ እንዲሁም በእረፍት ቀን በቤሌር ሜዳ ላይ ከእድሜ እኩዮቹ ጋር ይጫወታል። ውድድሮችን ከሌሎች የአካባቢ ልጆች ጋር ያደርጋሉ። የአካባቢው ሰዎች እና እግር ጥሏቸው በስፍራው የሚያልፉ ሰዎችም ይህን ፍልሚያ ልክ እንደ ስታዲየም በመክበብ ይመለከቱ ነበር። ይህ ደግሞ ለታዳጊው ትልቅ ተጫዋች ለመሆን ህልም ለነበረው ባዩ ትልቅ የሞራል ስንቅ ነበር። አዲስ መንገድ ባዩ የ7ተኛ ክፍል ተማሪ ሆኗል። 12ተኛ ዓመቱንም ይዟል። በሰፈሩ እግር ኳስ ውድድሮችን ቀበሌ ያዘጋጅ ነበር። በዩ እድሜ ደረጃው ቡድኖች ተዋቅረዋል። እሱ እድሜው ገና ቢሆንም የእግር ኳስ ችሎታው ጥሩ ስለነበር በ«ቢ» ቡድኑ ውስጥ ሊመረጥ ቻለ። የእድሜ ልዩነቱ እጅግ ሰፊ ቢሆንም አብሯቸው ልምምድ ያደርግ ነበር። ለአንድ ዓመት ያክል በዚህ ስብስብ ውስጥ ውድድሮችን እና ልምምድ ሲሰራ ቆየ። ሆኖም ግን ቡድኑ በተለያዩ ምክንያቶች ፈረሰ። እነ ባዩም የመበተን አደጋ ገጠማቸው። ነገር ግን የሰፈር ልጆች ተሰባስበው አዲስ ቡድን በግላቸው ጥረት አቋቋሙ። አሰልጣኝ በራሳቸው ሾመው የቀበሌውን ማሊያ ማግኘት ስለቻሉ ልምምዳቸውን ቀጠሉ። ቀይና ሰማያዊው የቤሌር ልጆች መለያ የባዩ የመጀመሪያ ቡድን ሆነ። ከሰፈራቸው እየወጡ ውድድሮችን ማድረግ ጀመሩ። ከ6 ቀበሌ፣ ከላይ ሰፈር ቀበና ልጆች፣ ከአራት ኪሎ እና ከሾላ ልጆች ጋር ውድድር ማድረግ ጀመሩ። ባዩ በወቅቱ የፊት መስመር ተጫዋች በመሆን በጨዋታ ላይ ብዙ ጎሎችን ያስቆጥር ነበር። ያልተጠበቀው አጋጣሚ ጊዜው 1985 ዓ.ም ነበር። ባዩ እና እግር ኳስ እስካሁን የግንኙነታቸው ገመድ አልተበጠሰም። እንዲያውም ወዳጅነታቸው ይበልጥ ጠንክሯል። በሳምንት ሶስት ጊዜ በቤሌር ሜዳ ከጓደኞቻቸው ጋር ልምምድ ያደርጋሉ። አንጋፋውን የጣሊያን ቡድን ጁቬንትስ ስም የያዘ ክለብ አቋቁመዋል። የ14 ዓመት ታዳጊው ባዩ እና ጓደኞቹ እንደተለመደው ልምምድ ለመስራት በቤሌር ሜዳ ተገኝተዋል። በአዲስ አበባ ተወዳጅ ስለሆነ ትልልቅ የእግር ኳስ ክለቦች አልፎ አልፎ በዚህ ስፍራ እየመጡ ልምምድ ያደርጉ ነበር። ክለቦቹ ታዳጊ ልጆችንም ይመለምሉ ነበር። የዚያን እለት ደግሞ ተራው የአንጋፋው እና ተወዳጁ ቅዱስ ጊዮርጊስ ነበር። በአጋጣሚ በስፍራው ተገኝቷል። አሰልጣኝ ስዩም ከበደ የሚያሰራቸው የቅዱስ ጊዮርጊስ የ«ሲ» ቡድን ልጆች ነበሩ። መለማመጃ ሜዳ በማጣታቸው በዚህ ስፍራ ተገኝተዋል። እነ ባዩ ደግሞ በሜዳው ላይ እየተጫወቱ ነበር። በጊዜው ስዩም ሜዳውን ለልጆቹ እንዲለቀቅ ሲጠየቅ ባዩና አንዳንድ ጓደኞቹ ጊዮርጊስ ትልቅ ክለብ ስለነበር ወደ ዳር ወጡ። አንዱ ጓደኛቸው ግን ‹‹አሻፈረኝ »አለ። በወቅቱ ሜዳው ላይ አለመግባባት በመፈጠሩ የባዩ ቡድን እና የጊዮርጊስ ቡድን ግጥሚያ እያደረጉ ልምምድ እንዲያደርጉ ተገደዱ። ይህም አጋጣሚ ደግሞ ያልተጠበቀ ነገር እንዲከሰት አደረገ። ጨዋታው ተጀምሯል። ሜዳውን አንለቅም ያሉት የቤሌር ታዳጊዎች የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብን ታዳጊዎች እየገጠሙ ነው። አሰልጣኝ ስዩም የሚያለማምዳቸው ልጆች ብቻ ሳይሆን ከዚያኛው ወገን ያሉትንም በጥሞና ይመለከታል። በድንገት የአንድ ታዳጊ ኳስ አያያዝ እና አጨዋወት ትኩረቱን ሳበው። ይሄ ታዳጊ ከቤሌር ሜዳ የበቀለው የ14 ዓመቱ ባዩ ነበር። ስዩም ጨዋታውን አቋርጦ ወደሱ እንዲመጣ አደረገው። የመጀመሪያ ጥያቄው «ለክለብ ትጫወታለህ» የሚል ነበር «አረ በፍፁም» በማለት ባዩ መለሰ ። በድጋሚ ወደ ሜዳው እንዲገባ እና እንዲጫወት ጠየቀው። ባዩ አሁንም በተመሳሳይ ድርጊት ማራኪ የእግር ኳስ እንቅስቃሴ አደረገ። ስዩም የባዩን ችሎታ በማድነቅ ለትልቅ ክለብ ይጫወት እንደሆነ በድጋሚ ጠየቀው። እሱ ግን በሰፈር ካቋቋሙት ክለብ ውጪ እንደማይጫወት አስረግጦ ነገረው። አጨዋወቱ ልምድ ያለው እና ታዋቂ ክለቦች ጋር የሚጫወት ይመስል ነበር። በቅዱስ ጊዮርጊስ ታዳጊ ቡድን ውስጥ ለመሰለፍ ጊዜ ያልወሰደበት ባዩ በዚያው ዓመት ቡድኑ ቻምፒዮን በመሆኑ ድሉን ከጓደኞቹ ጋር አጣጣመ። በወቅቱ በነበረው እግር ኳስ ከታዳጊ ቡድኑ ወደ «ቢ» እና ዋናው ቡድን ለማደግ ቢያንስ ከ3 እና ከአራት ዓመት በላይ ይወስድ ነበር። ሆኖም ባዩ ወደ ቢ ቡድን ለመሸጋገር ይህን ጊዜ አልወሰደበትም ነበር። ሁለት የውድድር ዘመን እንዳሳለፈ ለዋናው ቡድን ለልምምድ ተጠራ። በወቅቱ ብሄራዊ ቡድኑ ለኢንተርናሽናል ጨዋታ 9 ልጆችን ከቅዱስ ጊዮርጊስ መውሰዱ ለባዩ ወደ ዋናው ቡድን መሄድ ትልቅ እድል ከፍቶ ነበር። ባዩ ለዋናው ቡድን ቢመረጥም የልምምድ ሰዓቱ ከትምህርቱ ጋር በመጋጨቱ መቅረት ጀመረ። ወቅቱ 1987ዓ.ም ነው። እሱ ደግሞ የ11ኛ ክፍል ተማሪ ሆኗል። የዋናው ቡድን አሰልጣኝ አስራት ሀይሌ በባዩ ብቃት እና ታዳጊነት ተስቧል። እሱን ማጣት ባለመፈለጉም ሙሉ ለሙሉ ካምፕ እንዲገባ ጠየቀው። ባዩ አስራት የሰጠውን እድል ለማመን አልቻለም። ማንም በዚህ ፍጥነት ለዋናው ቡድን ተመርጦ አያውቅም። ለእግር ኳስ ጨዋታ ከፍተኛ ፍቅር ስላለው የአሰልጣኝ አስራትን ጥያቄ በደስታ ተቀብሎም ወደ ካምፕ ገባ። ይህ ደግሞ ከአንጋፋዎቹ ሙሉጌታ ከበደ፣ ተስፋዬ ኡርጌቾ፣አሸናፊ ሲያይ እንዲሁም ዮሴፍ ሰለሞንን ከመመሳሰሉ ተጫዋቾች ጋር እግር ኳስ መጫወት አስችሎታል። በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤት በተቀያሪነት ያገኘው የመሰለፍ እድል ሌላ በር ከፈተለት። የአሰልጣኝ ስዩም አባተ አይኖች በባዩ እግሮች ላይ አረፉ። ወደ ኬንያ ለሚጓዘው ታዳጊ ብሄራዊ ቡድን ተሰላፊ እንዲሆን ተመረጠ። አሁን አገሩን ሊወክል ነው። ይሄ ሂደት የእውነትም ባዩ ለእግር ኳስ መፈጠሩን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነበር። በኬንያ ሞንባሳ በተካሄደው የታዳጊዎች የሴካፋ ውድድር ሁሉንም ጨዋታዎች ላይ በመሰለፍ እንዲሁም በፍፃሜው ጨዋታ ሁለት ግቦችን ከመረብ በማሳረፍ ታሪክ መስራቱን ጀመረ። በ1988 ዓ.ም በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤት ባዩ ሙሉ የመሰለፍ እድል አገኘ። በመሀል ተጫዋችነት እና በግራ መሀል ተከላካይነት ሙሉ ዓመቱን ተጫወተ። በታዳጊ ብሄራዊ ቡድኑ ላይ ያሳየው ምርጥ ብቃት አሰልጣኝ ስዩም አባተን ከማስደሰቱም በላይ ክለቡ እምነት እንዲጥልበት አድርጎ ነበር። የእግር ኳስ ህይወቱም ወደፊት በእድገት መስመር ላይ መክነፉን ቀጠለ። በዚያ ዓመት የኢትዮጵያ ቻምፒዮና፣ የአሸናፊዎች አሸናፊን ጨምሮ የጥሎ ማለፉን ዋንጫ ባዩ ከክለቡ ጋር ለመሳም በቃ። ብሄራዊ ቡድኑን መወከል ቀጥሏል። ኮካኮላ ምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የታዳጊ ዋንጫ ላይ በ1988ዓ.ም መጨረሻ ላይ ተሳታፊ ሆነ። በዚህ ቡድን ላይ ባዩ አምበል ከመሆኑ ሌላ ኢትዮጵያ ቻምፒዮን ስትሆን በኮኮብ ተጫዋችነት ተመርጧል። ውድድሩ ደግሞ ተጨማሪ ሲሳይ ይዞለት ብቅ ብሏል። ባዩ ምን ገጥሞት ይሆን? ያልተሄደበት መንገድ የኮካ ኮላ የምስራቅ እና መካከለኛው አፍሪካ የታዳጊ ዋንጫ ላይ ዓለም አቀፍ ደላሎች ተገኝተው ተጫዋቾችን የመመልመል ስራ ይሰሩ ነበር። ይህ አጋጣሚ የመልማዮችን አይን በባዩ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ይሄ ደግሞ የፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋች የመሆን ህልሙን ያሳካበት ጅምር ነበር። መልማዩ ወደ ቤልጂየም ክለቦች ሄዶ ሙከራ እንዲያደርግ ጥያቄውን አቀረበለት። ከእርሱ ጋር የቡድን አጋሩ ጌትነት ሞት ባይኖር እጩ ተመራጭ ነበር። 1989 ዓ.ም ባለፈው ክረምት ለባዩ የመጣው እድል እውን የሆነበት ነበር። በውድድር ዘመኑ መሀል ላይ ለሙከራ ወደ ቤልጂየም እንዲሄድ ጥሪ ቀረበለት። አስፈላጊውን ጉዳይ አጠናቆም ወደ ቤልጅየም አቀና። በዚያም ለቤልጄሙ ሎክረን ክለብ ፈረመ። ባዩ በወቅቱ እድሜው ትንሽ ነበር። በዚያ ላይ የአገሪቷን ቋንቋ አይችልም። በክለቡ ለአንድ ዓመት ከመንፈቅ ቢፈርምም በወቅቱ የተለያዩ አለመግባባቶች ይፈጠሩ ነበር። ተገቢውን ጥቅማጥቅም አለመክፈላቸው አንዱ ችግር ነው። ይሄ ጉዳይ ተደምሮ በዚያው በቤልጅየም ባዩን የሚፈልግ የ3ተኛ ዲቪዚዮን ክለብ ለመፈረም ቻለ። ባዩ አሁን ላይ ሆኖ የቤልጅየም ቆይታውን ያስታውሳል። የእግር ኳስ ደረጃቸው ከፍተኛ እንደነበር ይናገራል። ዘረኝነትን የመሰሉ አንዳንድ ችግሮች ይገጥሙት እንደነበረ ግን አይደብቅም። ችግሮቹን ተቋቁሞም ፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋችነቱን አሳክቷል። ቤልጅየም ለሶስት ዓመታት ቆይታ ካደረገ በኋላ ለእረፍት ወደ አገሩ የመምጣት እድል ገጠመው። በ1992 ዓ.ም «ፕሮፌሽናል ተጫዋች ለመሆኔ ትልቅ መሰረት ጥሎልኛል» በማለት ሁሌም ከሚያመሰግነው አሰልጣኝ አስራት ሃይሌ ጋር በድጋሚ ተገናኘ። አስራት በወቅቱ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ በመሆን ይሰራ ነበር። ባዩ ብሄራዊ ቡድንን ወክሎ እንዲጫወትም ፍላጎት ነበረው። ሆኖም በጊዜው ብቸኛው ፕሮፌሽናል ተጫዋች መሆኑ እየታወቀ ብሄራዊ ቡድኑን ወክሎ እንዲጫወት ጥያቄ ሲያቀርብ ያገኘው ምላሽ ተገቢ አልነበረም። ፌዴሬሽኑ ባዩን በአገር ውስጥ ባሉ ክለቦች ተጫውተህ መታየት አለብህ የሚል ምላሽ በመስጠት ቅሬታ ፈጥረውበት ነበር። አሰልጣኝ አስራት ሃይሌ ግን የባዩን የእግር ኳስ ክህሎት በሚገባ ያውቅ ስለነበር ቡድኑን እንዲቀላቀል ይፈልግ ነበር። በወቅቱ ፌዴሬሽኑ ለባዩ የሰጠው ምላሽ የአገር ውስጥ ስፖርት ቤተሰብን እና የመገናኛ ብዙሀንን ያነጋገረ ነበር። በነገሩ ቅር የተሰኘው ባዩም ወደ ክለቡ መመለስ ስለነበረበት ወደ ቤልጅየም ተጓዘ። ከአንድ ወር በኋላ ግን ከኢትዮጵያ አንድ የስልክ ጥሪ ደረሰው። ከእግር ኳስ ፌዴሬሽን ነበር። ብሄራዊ ቡድኑ የሴካፋ ውድድር ስላለበት ለውድድሩ መጋበዙ ተገለፀለት። ኢትዮጵያ ሄዶ በነበረ ሰዓት ጉዳዩ በአለመግባባት ቢጠናቀቅም ጥሪውን እንቢ ማለት አልፈለገም። ምክንያቱም አገሩን ወክሎ እንዲጫወት ነው የተጋበዘው። በ1994 ዓ.ም ዋናው ብሄራዊ ቡድን ለሴካፋ ውድድር ወደ ሩዋንዳ ይጓዛል። ባዩም ከፌዴሬሽኑ ጥሪ ደርሶታል። ሆኖም ግን ቡድኑን የተቀላቀለው ጉዞው ሊደረግ አንድ ቀን ሲቀረው ነበር። ከቡድኑ ጋር ልምምድ ባያደርግም ፕሮፌሽናል ልምዱ ከጓደኞቹ ጋር በቶሎ እንዲላመድ አስችሎታል።በአምስት ጨዋታ ላይ አራት ግቦችን በማስቆጠርም ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ዋንጫውን እንድታነሳ የአንበሳውን ድርሻ ተወጣ። በወቅቱ ብሄራዊ ቡድኑ ዋንጫውን ወደ አገሩ ይዞ ሲመጣ በአዲስ አበባ እና በተለያዩ ክልል ከተሞች ከፍተኛ ፈንጠዝያ ተፈጥሮ ነበር። እርሱም ለረጅም ጊዜ አገሩን ወክሎ ስኬታማ መሆን ምኞቱ ስለነበር በውጤቱ የልቡ ደረሰ። ባዩ ሙሉ የሴካፋን ዋንጫ ከአገሩ ጋር ካነሳ በኋላ በተለያየ ጊዜ ጥሪ እየደረሰው ለብሄራዊ ቡድን ተሰልፏል። ከቤልጅየም ወደ የመን በመጓዝም በታይዝ ከተማ የአል ሳከር ክለብን ተቀላቅሎ ለ3ዓመታት ተጫውቷል። የአል ሳከር ክለብ ከ37 ዓመት በኋላ ዋንጫ ሲያነሳ ዮርዳኖስ አባይ ከአሰልጣኝ ስዩም ከበደ ጋር በመሆን ክለቡን ባለታሪክ አድርገውታል። በየመን ቆይታው ስኬታማ ጊዜን ካሳለፈ በኋላ ወደ ቤልጄም በመመለስ ለአር አር ሲ ጌልት ፈርሞ ረዘም ላሉ ዓመታት ተጫውቷል። ቤሌር ሜዳ ላይ የተጠነሰሰው የባዩ የእግር ኳስ ህይወት የግዴታ አንድ ቦታ መጠናቀቅ ነበረበት። በይፋም እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2014 ጫማውን ሰቅሏል። ከተጫዋችነት እራሱን ቢያገልም ሙሉ ለሙሉ ግን ከእግር ኳስ ህይወት አልራቀም። በቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ውስጥ በቡድን መሪነት አገልግሏል። ከቀድሞ ክለቡ ጋር በድጋሚ በሌላኛው የህይወት መስመርም ተገናኝቷል። አዲስ ዘመን ሰኔ 21/2012ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=35264
[ { "passage": "በዚህ ዓመት መጀመርያ ወደ ግሪን ጉልይ ዋና ቡድን ያደገውና ከኢትዮጵያን ቤተሰቦች የተወለደው አዲሱ ባየው የመጀመርያ ጎሉን አስቆጠረ።በአውስትራልያው ሁለተኛው የሊግ እርከን የሚወዳደረው ግሪን ጉልይ ትላንት ከሜዳው ውጭ ኪንግስተን ሲቲን አራት ለባዶ ሲረመርም አዲሱ በ57ኛው ደቂቃ ላይ ግብ ማስቆጠር ችሏል።ባለፉት ዓመታት የታዳጊ ቡድን ቆይታው በርካታ ግቦች በማስቆጠር የሚታወቀው አዲሱ ከ20 ዓመት በታች ውድድር ኮከብ በመባል ዴቪዝ ሆግባን የተሰኘውን ሽልማት ከዚህ ቀደም ተሸልሟል።በዚህ ክለብ ውስጥ ከአዲሱ ባየው ሌላ ዜና ቡጋሊ የተባለ ተስፈኛ ተጫዋች ለሃያ ዓመት በታች ቡድኑ እየተጫወተ ይገኛል።ግሪን ጉልይ እግር ኳስ ክለብ በአውስትራልያ ሁለተኛው የሊግ እርከን ከሚገኙ ስድስት ንዑስ ሊጎች አንዱ በሆነውን ናሽናል ፕሪምየርሊግ ቪክቶርያ የሚሳተፍ ሲሆን 64 ዓመት ያስቆጠረ አንጋፋ ቡድን ነው።", "passage_id": "a0f7af7771a3d812b80f15afbba2af76" }, { "passage": "ቶተንሃም በመጨረሻም ተጫዋች ያስፈርም ይሆን? የማንቸስተሩ አንቶኒ ማርሻል ወደ ሌላ ክለብ ይዘዋወር ይሆን? \n\nበዚህኛው የዝውውር መስኮት ክለቦቻቸውን ሊለቁ የሚችሉ ዘጠኝ የፕሪምየር ሊጉ ተጫዋቾችን እንመልከት። \n\nቶቢ አልደርዌረልድ (ቶተንሃም)\n\nቤልጂየማዊው ተከላካይ ባለፈው ዓመት ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት በቶተንሃም የቋሚ አሰላለፍ ቦታ ለማግኘት ተቸግሮ ነበር። ኮንትራቱ በዚህ ዓመት የሚጠናቀቀው አልደርዌረልድ፤ ስሙ ከማንቸስተር ዩናይትድ ጋር እየተያያዘ ነው። ለተጫዋቹ የቀረበው የመግዣ ዋጋ ደግሞ 75 ሚሊዮን ፓውንድ ነው። \n\n• ጅማ አባጅፋር የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አሸናፊ ሆነ\n\n• ኢትዮጵያዊው ጀማል ይመር በአስር ሺ ሜትር የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ ሆነ\n\n• አወዛጋቢው የእግር ኳስ ዳኞች ማስመሪያ \n\nጃክ ግሬሊሽ (አስቶን ቪላ)\n\nየ21 ዓመቱ እንግሊዛዊ ግሬሊሽ በቻምፒዮንሺፑ አስቶን ቪላ ላደረገው ግስጋሴ ከፍተኛ አስተዋጸኦ አድርጓል። ክለቡ በአሁኑ ሰአት የገንዘብ እጥረት ያጋጠመው ሲሆን፤ በተለይ ደግሞ ቶተንሃሞች ተጫዋቹን የግላቸው ለማድረግ እስከ 20 ሚሊዮን ፓውንድ ለመክፈል ተዘጋጅተዋል። አስቶን ቪላ ግን ቶተንሃሞች ያቀረቡትን ዋጋ እጥፍ እየጠየቁ ነው። \n\nዳኒ ኢንግስ (ሊቨርፑል)\n\nበአንድ ወቅት እንግሊዝ ካፈራቻቸው ምርጥ አጥቂዎች መካከል አንዱ ተብሎ ሲወደስ ነበረው ዳኒ ኢንግስ ሊቨርፑል ባሳለፋቸው ሶስት ዓመታት እጅግ አስቸጋሪ ጊዜ አሳልፏል። በባለፈው የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግም አንድ ጊዜ ብቻ ነው ግብ ማስቆጠር የቻለው።\n\nሊቨርፑሎችም ለተጫዋቹ የ20 ሚሊዮን ፓውንድ መሸጫ ዋጋ ለጥፈውበታል። ተጫዋቹን በጥብቅ ከሚፈልጉት ክለቦች መካከል ደግሞ ክሪስታል ፓላስ የመጀመሪያውን ስፍራ ይዟል። \n\nሃሪ መጓየር (ሌስተር ሲቲ)\n\nበተለይ በአለም ዋንጫው ለእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን ያሳየው ወጥና አስገራሚ አቋም በአሁኑ ሰአት ይህን ተከላካይ ተፈላጊ እንዲሆን አድርጎታል። \n\nየሃሪ መጓየር ዋነኛ ፈላጊ ደግሞ የማንቸስተር ዩናይትዱ አሰልጣኝ ሆሴ ሞሪንሆ ናቸው። ለተጫዋቹም እስከ 56 ሚሊዮን ፓውንድ ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። የተጫዋቹ ባለቤት ሌስተር ሲቲ ደግሞ ለተከላካዮች ሪከርድ የሆነ 80 ሚሊዮን ፓውንድ ጠይቀዋል።\n\nአንቶኒ ማርሻል (ማንቸስተር ዩናይትድ)\n\nከአሌክሲስ ሳንቼዝ ወደ ማንቸስተር ዩናይትድ መምጣት በኋላ አንቶኒ ማርሻል የቋሚ አሰላፍ ቦታ ለማግነት ተቸግሮ የቆየ ሲሆን፤ ለአለም ዋንጫው በብሄራዊ ቡድኑ አለመካተቱ ደግሞ ክለቡን እንዲለቅ ምክንያት ሊሆነው እንደሚችል ተገልጿል።\n\nበሌላ በኩል ተጫዋቹ ሁለተኛ ልጅ ሲወለድለት የቅድመ ውድድር ጨዋታውን ጥሎ ወደ ፈረንሳይ መመለሱ የማንቸስተሩ አሰልጣን ሆዜ ሞሪንሆን ያስደሰታቸው አይመስልም። መሸጫ ዋጋውም እስከ 80 ሚሊዮን ፓውንድ ይደርሳል ተብሏል። \n\nሲሞን ሚኞሌ (ሊቨርፑል)\n\nቤልጂየማዊው ግብ ጠባቂ በሊቨርፑል ቤት የቋሚ አሰላለፍ ቦታውን በካሪየስ ተነጥቆ ነው የቆየው። አሁን ደግሞ ብራዚላዊውን ግብ ጠባቂ አሊሰን ከሮማ ማስፈረማቸው ደግሞ የተጠባባቂውን ቦታ እንኳን እንዳያገኝ ሊያደርገው ይችላል። \n\nበአስገራሚ ሁኔታ የላሊጋው አሸናፊ ባርሴሎናዎች በግብ ጠባቂው ላይ ፍላጎት አሳይተዋል። \n\nአሮን ራምሴ (አርሰናል)\n\nዌልሳዊው አማካይ ራምሴ በአርሰናል ቤት 10 ዓመት የቆየ ሲሆን፤ 300 ጨዋታዎችን ደግሞ ለክለቡ አድርጓል። አዲሱ የአርሰናል አሰልጣኝ ኡናይ ኤምሪ ራምሴን ጠቃሚ ተጫዋች ነው ብለው ቢገልጹትም፤ ከቼልሲ የቀረበላቸው የ35 ሚሊዮን ፓውንድ መገዣ ዋጋ እና የሊቨርፑል ፍላጎት ሃሳባቸውን ሊያስቀይራቸው እንደሚችል ይገመታል። \n\nዊሊያን (ቼልሲ)\n\nይህ የማይደክመው የሚባልለት የክንፍ ተጫዋች በአለም ዋንጫው ለሃገሩ... ", "passage_id": "597d48522393966f48729f6f43f8f324" }, { "passage": "በሙሉ ስሙ ሉዊስ አለማየሁ ቡሽ-ዊኪ ይባላል፡፡ የተወለደበትን ከተማ እና ወላጆቹን የማያውቅ ሲሆን ከተወለደ በኃላ በገበያ ቦታ ተጥሎ በፖሊስ ተገኝቶ ለማዘር ቴሬሳ የህፃናት ማሳደጊያ መሰጠቱን ያስረዳል፡፡ ዴንማርካዊያኑ የቡሽ-ዊኪ ቤተሰብም ከህፃናት ማሳደጊያው በጉዲፈቻ ወስደውት በቤልጅየም እና ዴንማርክ ነው ያደገው፡፡ለዴንማርኩ ብሮንቢ ክለብ ከ19 ዓመት በታች ቡድን የሚጫወተው አለማየሁ ከኢትዮጵያዊያን ቤተሰቦቹ በኢትዮጵያ አቆጣጠር ጥር 8 ቀን 1992 ነበር የተወለደው፡፡ በ16 ወሩም (ግንቦት 18/1993) ለቡሽ-ዊኪ ቤተሰብ በጉዲፈቻ ተሰጥቷል፡፡ አለማየሁ ስለትውልድ እና እድገቱ ለሶከር ኢትዮጵያ እንዲህ ያስረዳል፡፡ “በተወለድኩ በ16 ወሬ ነበር በጉዲፈቻነት ለአሳዳጊዎቼ የተሰጠሁት፡፡ በማደጎ የተወሰድኩት ከአዲስ አበባ ሲሆን ቀጥታ ወደ ዴንማርክ መዲና ኮፐንሃገን ነበር ከቤተሰቦቼ ጋር ያመራሁት፡፡ ነገር ግን የመጀመሪያዎቹን ሶስት ዓመታት የኖርኩት በብራስልስ ቤልጂየም ነበር፡፡ ከሶስት ዓመታት የብራስልስ ቆይታ በኃላ ቤተሰቦቼ ተመልሰው ወደ ኮፐንሃገን መኖርን መምረጣቸው ተከትሎ ሙሉ የልጅነት ጊዜውን (ከ4 ዓመቴ ጀምሮ) በዴንማርክ ነው ያሳለፍኩት፡፡” ይላል አለማየሁ፡፡አለማየሁ ብዙዎች እግርኳስን በሚጀምሩበት መንገድ መጫወት የጀመረ ሲሆን ትምህርት ከጀመረ በኃላ በ2000 (እ.ኤ.አ 2008) ለመጀመሪያ ግዜ ወደ መዲናው ቡድን ቦልድክለብ 1893 (ቢ-93) የታዳጊዎች ቡድን ስር መጫወት ጀመረ፡፡ ከአራት ዓመታት የቦልድክለብ ቆይታ በኃላም በ2004 (እ.ኤ.አ. በ2012) በዴንማርክ ሊግ ለሚወዳደረው የኮበንሀቨን ቦልድክለብ የታዳጊዎች ቡድን ለመቀላቀል በቃ፡፡ ቢሆንም አለማየሁ ከኮበንሀቨን ቦልድክለብ የሁለት አመታት ቆይታ በኃላ ወደ ኃያሉ እና በምዕራብ ኮፐንሃገን ወደሚገኘው ብሮንድባይ በ2006 (2014) አምርቷል፡፡ “እግርኳስን ሁሌም እጫወት ነበር፡፡ በውስጤ ያለነገር ነው፡፡ በታዳጊ ማሰልጠኛ ስገባ ለመጀመሪያ ግዜ የተቀላቀልኩት ቢ-93 በ2008 ነው፡፡ በብሮንድባይ ታዳጊ ቡድን ከመጫወቴ በፊት ለኮበንሀቨን ቦልድክለብ (ኬቢ) ነው የተጫወትኩት፡፡ ከ2014 ወዲህ ግን በብሮንድባይ ታዳጊ ቡድን እየተጫወትኩ ነው፡፡ ለኬቤ ለቀቀኩበት ዋነኛው ምክንያት ክለቡ በተለያዩ የእድሜ እርከኖች ቡድን ቢኖረውም ወደ ሊያሳድገኝ ባለመቻሉ በእግርኳስ ህይወቴ የተሻለ የመጫወት እድልን ለማግኘት ወደ ብሮንድባይ አምርቻለው፡፡”የግራ መስመር አማካይ እና የፊት አጥቂ ሆኖ መጫወት የሚችለው የ17 ዓመቱ አለማየሁ ወደ ባሳለፍነው ነሃሴ ወደ ብሮንድባይ ከ19 ዓመት በታች ቡድን ማደግ ችሏል፡፡ “አሁን ላይ በብሮንድባይ ከ19 ዓመት በታች ቡድን ውስጥ ነው የምጫወተው፡፡ ወደ ቡድኑ ያደግኩት ነሃሴ ወር ላይ ሲሆን አብዛኞቹ የቡድን አጋሮቼ በእድሜ ይበልጡኛል፡፡ ይሁንና በተክለ ሰውነት ረገድ ልዩነት የለንም፡፡”አለማየሁ ስለኢትዮጵያ የሚያስታውሰው የልጅነት ትዝታ ባይኖረውም ስለ ኢትዮጵያ ሲናገር ያለው ስሜት አስገራሚ ነው፡፡ ከትውልድ ሃገሩ ጋር ያለውን የጠበቀ ቁርኝነትን ለማሳየት በስሙ ላይ ጭምር ለውጥ ማድረጉንም ይናገራል፡፡ “ሙሉ ስሜ ሉዊስ አለማየሁ ቡሽ ዊኪ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰዎች ሲጠሩኝ አለማየሁ እንዲሉኝ ነው የምፈልገው፡፡ ስለዚህም በዚህ ስም መጠራቴን እወደዋለሁ፡፡ በነገራችን ላይ ቤተሰቦቼ የሚጠሩኝ በቅፅል ስሜ አለማየሁ ነው፡፡ በጉዲፈቻ ከተሰጠው በኃላ ኢትዮጵያ ሁለት ግዜ የመመለስ እድል አጋጥሞኛል፡፡ ሶስት ዓመቴ እያለሁ እና በ11 ዓመቴ ታናሽ እህቴን (ሳራ) በጉዲፈቻ ቤተሰቦቼ ለማሳደግ ሲወስዱ መጥቼ ነበር፡፡ ኢትዮጵያ ሁሌም ለእኔ የተለየ ቦታ አላት፡፡ ኢትዮጵያ መነሻዬ ነች፤ ለእኔ ሁሉም ነገር የጀመረበት ቦታ፡፡ በቅኝ ግዛት ካልተገዛች፣ የቡና እና የድንቅነሽ (ሉሲ) መገኛ ሃገር በመፈጠሬ ኩራት ይሰማኛል፡፡” የሚለው አለማየሁ ከ20 እና ከ23 ዓመት ብሄራዊ ቡድኖች ጀምሮ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ማልያን መልበስንም ያልማል፡፡ “ከትውልድ ሃገሬ ጋር ያለኝ ጠንካራ ትስስር እና ለእግርኳስ ካለኝ ፍቅር የተነሳ በታዳጊ ደረጃ ኢትዮጵያን ለመወከል አልማለው፡፡” ይላል፡፡የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን እየተከታተለ የሚገኘው አለማየሁ በዴንማርክ እንደማደጉ ከዘረኝነት ጋር የተያያዙ ብዙ አጋጣሚዎች የደረሰበት ቢሆንም በተወሰነ ወልኩ አፍሪካዊ በመሆኑ በተክለሰውነት ረገድ መጠቀሙን ያስረዳል፡፡ ነገሮችን በአዎንታዊ ጎኑ መመልከት ብቻ እንደሚፈልግም ይናገራል፡፡ “ከተወሰኑ የዘረኝነት ችግሮች ውጪ እምብዛም በቆዳ ቀለሜ አድሎ ተደርጎብኝ አያውቅም፡፡ ስላገጠሙኝ ችግሮች በስፋት ማንሳት ብችል አሁን ላይ ደስ ይለኛል፡፡ ነገር ግን ወደ ስላጋጠሙኝ አዎንታዊ ነገር ብናገር እወዳለው፡፡ አንዳንድ የክለብ ጓደኞቼ ከመጡበት ጎሳ ምክንያት መገልል ሲደርስባቸው አስተውያለው፡፡ እንደኔ ግን ትውልደ አፍሪካዊ መሆኔ የጠቀመኝ ጎን አለ፡፡ ሰውነቴ በፍጥነት ነው ያደገው፡፡ በተወሰኑ አጋጣሚዎች ብቻ ነው በፍጥነት የሚበልጡኝን ተጫዋቾች የገጠሙኩት፣ ይህም ከአፍሪካዊነቴ ጋር የተያያዘ ይመስለኛል፡፡”የማንቼስተር ሲቲ ደጋፊ እንደሆነ የሚናገረው አለማየሁ የአርጀንቲናዊው አጥቂ ሰርጂዮ አጉዌሮ እና የቀድሞ የሴኔጋል ከ20 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን እና ሳርስቦርግ ተጫዋች ከርፒን ዲያታ አድናቂ ነው፡፡ በተለይ ዲያታን ሲጫወት መመልከቱ መነሳሳትን እንደፈጠረበት ይናገራል፡፡ “በዚህ እድሜው የተጓዘው ርቀት በጣም ጥሩ የሚባል ነው፡፡ እንደ ሳርስበርግ ያለክለብ መቀላቀል መቻሉም አስገራሚ ነው፡፡ ክረምት ላይ እሱን በመመልከቴ ብቻ የተለየ ነገር ለማድረግ አነሳስቶኛል፡፡”አለማየሁ እምብዛም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን እና የክለብ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ባለማግኘታቸው የመከታተል እድሉን አለማግኘቱን ይጠቁማል፡፡ “እምብዛም የኢትዮጵያን ጨዋታዎች የመከታተል አልቻልኩም፡፡ ግን ባለፉት ግዜያት በቅርበት ለመከታተል ሞክሪያለው፡፡ ብዙም ጨዋታ ባለመመልከቴ የማደንቀው ኢትዮጵያዊ ተጫዋች አሁን ላይ ባይኖርም በቤልጄየም ሌሬስ የተጫወተው ሳላዲን ሰዒድን አደንቃለው፡፡”", "passage_id": "50e280c662f106f4e9535272e37e2983" }, { "passage": "በሀገራችን ከታዩ ምርጥ አጥቂዎችና የችሎታቸውን ያህል ካልተዘመረላቸው ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው። በሀገሪቱ ትልልቅ ክለቦች በዋንጫ የታጀበ የእግርኳስ ዘመን በስኬት አሳልፏል። ብሔራዊ ቡድናችን ካልተጠቀመባቸው አጥቂዎች መካከል አንዱ የሆነው የወቅቱ አሰልጣኝ እና የዘጠናዎቹ ድንቅ አጥቂ ዮሴፍ ተስፋዬ (ቫንባስተን) ማነው?የቅድሞ ድንቅ ተጫዋች ኃይሌ ካሴ ኳስ ሜዳ እና አሸዋ ሜዳ በሚጫወቱበት ወቅት አንድ ወንድሙ የገዛለት የኤሲ ሚላን መለያ አድርጎ ረዥም፣ ቀጭን ታዳጊ ልጅ ሲጫወት ያየዋል። ፍጥነቱን፣ እርሱን ተከላካዮች ለመያዝ ሲቸገሩ፣ የኳስ አመታቱን፣ የጎል አጨራረሱን ሲመለከት ይሄ ልጅ ከሆላንዳዊው ታላቅ አጥቂ ቫንባስተን ጋር አጨዋወቱ ቢመሳሰልበት “ቫንባስተንን ያዙት’ እያለ ሲነግራቸው በዛው ቅፅል ስሙ ሆኖ የቀረው ዮሴፍ ተስፋዬ ትውልድ እና ዕድገቱ የኳሰኞች መፍለቂያ በሆነው መሳለሚያ ኳስ ሜዳ አካባቢ ነው። ኃይሌ ካሴ፣ ፉዓድ አብዱልቃድር፣ ብሩክ እስጢፋኖስ፣ ሰለሞን ቸርኬ እና ጌቱ ከበደን እየተመለከተ ያደገው ዮሴፍ እነርሱ የደረሱበት ደረጃ ለመድረስ የአዲስ አበባ እግርኳስ እንብርት በሆነችው ኳስሜዳ በመጫወት አድጓል።ዮሴፍ የአስራ አንደኛ ክፍል ተማሪ እያለ 1982 እና 83 ባህር ኃይል ቢ ቡድን ተጫውቶ የመንግሥት ለውጥ ሲመጣ ለከፍተኛ ሰባት እና አካባቢው ተጫውቷል። በመቀጠል ተወልዶ ባደገበት አካባቢ ለሚገኘው ለህዝብ ማመላለሻ ለአንድ ዓመት ሲጫወት ቆይቶ በ1987 ጀምሮ ለሙገር ሁለት ዓመት አገልግሏል። በሙገርም ቆይታው የኢትዮጵያ የጥሎ ማለፍ ዋንጫን ካነሳ በኃላ በተለይ አቅሙን አውጥቶ ወደተጫወትበት እና በብዙዎች የስፖርት ቤተሰብ ዘንድ ወደታወቀበት ኢትዮጵያ ቡና በ1989 ሊቀላቀል ችሏል። ለቡና በጉዳት ምክንያት ካልሆነ በቀር በፊት መስመሩ ላይ የአሰግድ ተስፋዬ አጣማሪ በመሆን በአብዛኛው ጨዋታዎች ላይ ተሳትፎ አድርጓል። ኢትዮጵያ ቡና የ1989 የኢትዮጵያ ሻምፒዮና ዋንጫን፣ የአሸናፊ አሸናፊን ዋንጫን እንዲሁም በ1990 የጥሎ ማለፍ ዋንጫ ሲያነሳ ከቡድን አጋሮቹ ጋር አብሮ በመሆን ታሪክ የሠራ ድንቅ አጥቂ ነው። በ1989 ላይ ተከተል ኡርጌቾ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ባጠናቀቀበት ዘመን ጉዳት እየፈተነው አልፎ አልፎ ከሜዳ እራቀ እንጂ ኮከብ ጎል አስቆጣሪ ሆኖ የመጨረስ ዕድል ሰፊ የነበረ ቢሆንም በመጨረሻም ሁለተኛ ከፍተኛ ጎል አግቢ በመሆን ማጠናቀቁ ይታወሳል።ከአጥቂነቱ በተጨማሪ ወደ ኃላ ተመልሶ ኳሶችን አደራጅቶ ወደፊት በመሄድ፣ ሰው ቀንሶ በማለፍ እና ለቡድኑ ጥንካሬ በመስጠት የሚታው ዮሴፍ ከሦሰት ዓመት የኢትዮጵያ ቡና ቆይታ በኃላ 1992 እና 93 ለሙገር እና ለቅዱስ ጊዮርጊስ ለአንድ አንድ ዓመት ተጫውቶ በመቀጠል በ1994–95 ድረስ ሁለት ዓመት ለመድን ሲጫወት ቆይቶ ከ1996–98 ድረስ በሀዋሳ ከተማ የተሳካን ጊዜ አሳልፏል። ከአጥቂነት ባህሪው ወደ ኃላ በመመለስ ከሙሉጌታ ምህረት እና ከበኃይሉ ደመቀ ጋር በአማካይ ስፍራ ላይ የነበራቸው ድንቅ ጥምረት የክልል ቡድን በታሪክ መጀመርያውን የፕሪምየር ሊግ ዋንጫን በ1996 እንዲያነሳ ማድረግ ችሏል። በተለይ በዚሁ ዓመት ኮከብ ተጫዋች ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ በአወዛጋቢ ሁኔታ የመሆን እድሉ መጨናገፉ ይታወሳል።በሀዋሳ ከተማ አብሮት የተጫወተው በኃይሉ ደመቀ ስለ ዮሴፍ እንዲህ ይናገራል “ዮሴፍ ለኔ ኳስን በስሜት ከመጫወት ወጥቼ በአዕምሮዬ እንድጫወት የቀረፀኝ በትክክለኛ ሰዓት ያገኘሁት አስተማሪዬ ነው። አስገራሚ እይታ ያለው ተረጋግቶ በእውቀት የሚጫወት የኔ ምርጡ አማካይ ነው። ስለ መልካምነቱ ቃል የለኝም፤ እጅግ ሲበዛ ባለ ሙሉ ስብእና ባለቤት ነው። ጆሲ (ቫንባስተን) ይችላል” በማለት ተናግሯል።በእግርኳስ ክህሎቱ እና በመልካም ስነ ምግባሩ የሚመሰከርለት ዮሴፍ ከሀዋሳ ጋር የፕሪምየር ሊግ እና የጥሎ ማለፍ ዋንጫን ካገኘ በኃላ ጫማውን እስከሰቀለበት 2001 ድረስ ለሦስት ዓመታት ያህል ለሐረር ቢራ ተጫውቷል። በሐረር ቢራ በነበረውም ቆይታ በ1999 የጥሎ ማለፍ ዋንጫን ቡድኑ እንዲያነሳ የእርሱ ሚና ከፍተኛ ነበር። ብሔራዊ ቡድን ካልተጠቀሙባቸው አጥቂዎች መካከል አንዱ እንደሆነ ብዙዎች የሚመሰክሩለት ዮሴፍ ግብፅ ላይ 5-0 ተሸንፎ እዚህ 5-0 አሸንፎ በፍፁም ቅጣት ምት የወጣው የወጣት ቡድን ውስጥ አባል ነበር።እግርኳስን ባቆመበት ዓመት በፍጥነት ወደ አሰልጣኝነቱ የገባው ዮሴፍ በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ቡና ከ20 ዓመት በታች ቡድን እያሰለጠነ ሲገኝ ባለፈው ዓመት የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ በመሆን ሰርቷል። ይህ የዘጠናዎቹ ወርቃማ አጥቂ ዮሴፍ ተስፋዬ የዛሬው እንግዳችን ነው።“የእግር ኳስ ህይወቴ ስኬት በቡና 1989 እና 90 በነበረው ቡድን ውስጥ የማልረሳው ጊዜ ነው። ቻምፒዮን የሆንበት፣ አል-አህሊን ከውድድር ያስወጣንበት ጨዋታ ለኔ ትልቁ ስኬቴ ነው። ሙገር ሆኜ ደግሞ 1987 ላይ ዋናው በር የከፈተለኝ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ሁለት ግብ አግብቼ ጥሎ ማለፍ ዋንጫ ያነሳንበት ነው። ከሀዋሳ ከተማ ጋር የመጀመሪያው የክልል ቡድን የፕሪምየር ሊግ ዋንጫን አሸናፊ እንዲሆን ያስቻልንበት በእግር ካስ ህይወቴ ውስጥ ትልቅ ቦታ የምሰጣቸውቸው ስኬቶች ናቸው።” የምቆጭበት ነገር ብዙም የለኝም። ከልጅነቴ ጀምሮ የምችለውን ያህል ያለኝ ሰጥቼ 17 ዓመታት ያህል ነው የተጫወትኩት፤ ምንም የሚቆጨኝ ነገር የለም። መቀጠልም መጫወት እችል ነበር። በእግርኳሱ ችክ ማለት አልፈልግም ብዬ ነው ያቆምኩት። ለተተኪዎችም ቦታውን መልቀቅ ያስፈልጋል።“በ1989 የከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ ሆኜ የመጨረስ ከፍተኛ እድል ነበረኝ። ተከተል ኡርጌቾ 12 ጎል አስቆጥሮ ቁጭ ብሎ ነበር። እኔ በቀሪ ጨዋታ ከንግድ ባንክ ጋር እየተጫወትን ሁለት ጎል አስቆጥሬ 11 ጎል ደርሼ ነበር። ሆኖም ተጨማሪ ጎል የማስቆጥርበት አጋጣሚ ቢኖረኝም ዐብይ ሀይማኖት ጉልበቴ ላይ ባደረሰብኝ ጉዳት መጫወት አቅቶኝ ተቀይሬ ወጣው እንጂ ኮከብ ጎል አስቆጣሪ መሆን እችል ነበር።“ወደ አሰልጣኝነቱ የገባሁት 2002 እግርኳስን እንዳቆምኩ ነው። ሳሪስ አካባቢ ነበር የምኖረው፤ ሰለሞን አባተ የሥዩም አባተ ወንድም ተጫውተው ያሳለፉትን ጥሩልኝ ብሎ መልዕክት ልኮብን አንደኛ ደረጃ የአሰልጣኞች ስልጠና ወሰድኩ። ከዛ በኋላ የተለያየ ስልጠናዎችን ስንወስድ ቆይቼ ሲ እና ‘ቢ አጠናቅቄ ከ2008 ጀምሮ በባለሀብቶች እና ተጫውተው ያሳላፉ ኳስ ሜዳ እና አካባቢው የተሰኘ አንድ ቡድን አቋቀምን በማሰልጠን ስልጠናን ጀመርኩ። በ2009 ላይ በዕድሉ ደረጄ ጠቋሚነት ከ20 ዓመት በታች የቡና ታዳጊ ቡድን ም/አሰልጣኝ ሆኜ ተቀጠርኩ። በመቀጠል ሦስት ጨዋታ እንደተጫወትን ዕድሉ ወደ ዋናው ቡድን ሲሄድ እኔ ከ20 ዓመት በታች ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ ሆንኩ ፤ እስካሁንም እየሰራው ነው። 2010 ላይ ዙሩን አሸንፈን ዝዋይ ላይ በነበረው ውድድር ፍፃሜ መድረስ ችለናል። በዚህ መልካም ውጤትም የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ እንድሆን እድሉን አመቻችቶልኛል።“በአሰልጣኝነት ህይወቴ የወደፊት ዕቅዴ እንደመነሻ አሁን ወጣቶች ላይ ነው እየሰራው ያለሁት። እዚህ ላይ ለቡድኔ ጥሩ ጥሩ ልጆችን ማዘጋጀት እና ማቅረብ ነው የማስበው። ወደፊት ራሴን እያዘጋጀው በትልቅ ደረጃ ማሰልጠን እፈልጋለው።“ስለያኔ እና አሁኑ የእግር ኳሱን ሁኔታ ያለው ነገር ለመግለፅ በፊት በጣም ብዙ ጥሩ ተጫዋቾች ነበሩ። ዕድሉን ሳያገኙ ሰፈር ውስጥ የቀሩ በጣም ብዙ ኳስ ተጫዋቾች ነበሩ። አንድ ቡድን ውስጥ ራሱ ዋና እና ተጠባባቂን ለመለየት እስኪያስቸግር ድረስ ማለት ነው። አሁን ላይ እንደዚህ ከሰፈር ከታች የሚመጣ ፉክክር የለም። አሁን እግርኳሱ በተወሰኑ ተጫዋቾች ቁጥጥር ስር ነው ያለው። ከአንዱ ክለብ አንዱ ክለብ እየተዘዋወሩ የሚቆዩበት እንጂ ፉክክር አለ ማለት ይከብደኛል። በፊት አስረኛ ያለው ቡድን አንደኛውን በጣም ነው የሚፈትነው። ወራጁ ቡድን ሊያሸንፍም ይችላል። ቢሸነፍም እራሱ በመከራ ነው። አሁን ዋና ተሰላፊውም፣ አሸናፊውም በቀላሉ ነው የሚታወቀው።“ሁለት ወንድ ልጆች አሉኝ አንደኛው ገና ስምንት ዓመቱ ነው። ወደፊት እግርኳስ ተጫዋች ይሆናል ለማለት ከወዲሁ እንዲህ ነው ብሎ ለመናገር ቢከብድም ፍላጎት አለው። የመጀመርያው ልጄ ቅዱስ ዮሴፍ ይባላል። አስራ ስምንት ዓመቱ ነው። የአስራ ሁለተኛ ክፍል ተማሪ ነው። በአሁን ወቅት ለአፍሮፅዮን ከ17 ዓመት በታች ቡድን ውስጥ በተላካይ ቦታ እየተጫወተ ነው። ያው የአሰልጣኙ እምነት ነው እኔ አጥቂ ሆኜ እርሱ ተከላካይ መሆኑ። ወደፊት ወደ እኔ ቦታ መጥቶ ይጫወት ይሆናል።”", "passage_id": "8cf3d39c8429c7a394e6d555fe398668" }, { "passage": "አዲስ አበባ የተወለደው የመስመር ተከላካይ ኢዮብ ዛምባታሮ የሴሪ ሲ ክለብ የሆነው ሞንፓሊን ተቀላቅሏል፡፡በሴሪ ሲ (ሦስተኛ የሊግ እርከን እየተወዳደረ የሚገኘው ሞኖፖሊ1966 ይፋ እንዳደረገው ከሆነ ተጫዋቹ ክለቡን የተቀላቀለው በውሰት ውል ሲሆን ከዛሬ ጅምሮ ከቡድኑ ጋር ልምምድ ጀምሯል።የ22 ዓመቱ ኢዮብ ለሁለት ዓመታት በአታላንታ ወጣት ቡድን (ፕሪማቬራ) ቆይቶ በ2018 ወደ ፓዶቫ በውሰት ያመራ ሲሆን ከክለቡ ጋር የሴሪ ሲ ዋንጫን አንስቶ ወደ ሴሪ ቢ መሸጋገር ችሎ ነበር። በቀጣዩ የውድድር ዘመን ደግሞ በጣልያን ሁለተኛው የሊግ እርከን 11 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ የተጫወተ ሲሆን በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ወደ አታላንታ ተመልሶ ከግማሽ ዓመት በኋላ ወደ ራቬና በውሰት በመጓዝ ውድድሩ በኮቪድ 19 ምክንያት እስከተቋረጠበት ጊዜ ድረስ አጭር ቆይታ ማድረግ ችሎ ነበር።", "passage_id": "c7dbbc8e9fd893a4ea29c1608ef00be5" } ]
86e48b5c7f4d195ab4aac4f43a133409
4d8d08f10d03419d1741f875a4783d34
የኦሊምፒክ ቀን በወርቃማ ኦሊምፒያኖች
የዓለም ኦሊምፒክ ቀን እ.ኤ.አ ከ1948 ጀምሮ በየዓመቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለያዩ አገራት ይከበራል። ይህም የኦሊምፒክ አባት በሆኑት ፒየር ዲ ኩበርቲን አማካኝነት በአዲስ መንፈስ የተመሠረተውን የኦሊምፒክ ጨዋታ ለማሰብ ይሁን እንጂ በዓሉ ሲከበር ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማከናወን ተፈጥሮዊ መብት በመሆኑ ሁሉም ሰው ዕድሜ ፣ ፆታ ፣ ዘር እና ሃይማኖት ሳይገድበው በሁሉም ቦታ በግል እና በጋራ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በማድረግ በመቀስቀስ እና በማስተማር ጭምር ነው ።የዓለም ኦሊምፒክ ቀን ‹‹ኦሊምፒክ ለሰው ልጆች ጤንነት መልሶ መቋቋም እና ትብብር›› በሚል መሪ ቃል ባለፈው ማክሰኞ በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ቅጥር ግቢ ውስጥ በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሮ ሲውልም ጀግናው አትሌት ሃይሌ ገብረሥላሴና ከማሞ ወልዴ በኋላ በኦሊምፒክ ማራቶን ለኢትዮጵያ ብቸኛውን የወርቅ ሜዳሊያ ሲድኒ ላይ ያስመዘገበው ገዛኸኝ አበራን የመሳሰሉ ወርቃማ ኦሊምፒያኖች ደምቆ ውሏል። እነዚህ የኦሊምፒክ ጀግኖች በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ሳቢያ ከተራዘመው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያን ለመወከል ሲዘጋጁ የነበሩ ወጣት አትሌቶች አስከፊው ጊዜ እስኪያልፍ ራሳቸውን እንዲጠብቁና አቋማቸውም እንዳይወርድ ጠንክረው በመሥራት ከልምምድ መራቅ እንደሌለባቸው ምክራቸውን ለግሰዋል። ያለፉት ሁለት የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮናዎች ላይ በአምስት ሺ ሜትር የነገሰው አትሌት ሙክታር ኢድሪስ እንዲሁም በዶሃው ቻምፒዮና ሙክታርን ተከትሎ በመግባት የብር ሜዳሊያ ያጠለቀው ወጣቱ አትሌት ሰለሞን ባረጋ፣ ሰንበሬ ተፈሪና በወርልድ ቴኳንዶ ለመጀመሪያ ጊዜ በቶኪዮ ኦሊምፒክ ኢትዮጵያን የሚወክለው ሰለሞን ቱፋ የታላላቆቻቸውን ወርቃማ ኦሊምፒያኖች ምክር በሥፍራው ተገኝተው ተቀብለዋል። በክብረ በዓሉ ላይ የተገኙት የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ኤሊያስ ሽኩር፣ የስፖርት ቤተሰቡ የኦሊምፒዝም ፍልስፍናን የዕለት ከዕለት መመሪያው በማድረግ ተግባራዊ ሊያደርገው እንደሚገባ ተናግረዋል። ኦሊምፒዝም ሰላምን፣ ንፁህ ወንድማማችነትን ፣ እርስ በእርስ መግባባትን እና ትብብርን የሚያስተምር በመሆኑ ሁሉም የስፖርት ቤተሰብ የዕለት ከዕለት መመሪያው ሊያደርገው ይገባልም ብለዋል ።‹‹ወቅቱ በጣም አስቸጋሪ እና ፈታኝ በመሆኑ ይህን ክፋ ጊዜ ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር ተባብረን እና ተደጋግፈን የወረርሽኙን ጉዳት መቀነስ ይገባል›› ያሉት ኮሚሽነሩ በመሆኑም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እያደረገ ያለው ድጋፍ ሊመሰገን የሚገባውና ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልፀዋል። ስፖርቱ ወደነበረበት እንዲመለስ እና በወረርሽኙ ምክንያት ለተጎዱ የስፖርት ቤተሰቦች መደገፍ የሚያስችል የማገገሚያ ስትራቴጂ ተዘጋጅቶ ለመንግሥት መቅረቡንም አቶ ኤሊያስ አስታውቀዋል።የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ በበኩላቸው፣ የዘንድሮውን የኦሊምፒክ ቀን ለማክበር የተደረገው ሰፊ ዕቅድ በወረርሽኙ ምክንያት ቢስተጓጎልም ከመቸውም ጊዜ በላይ በዚህ አጣብቂኝ ጊዜ ውስጥ በመሆን በዓሉን ሲከበር ለአትሌቶቻችን ፣ ለአሰልጣኞቻችን እና ለሙያተኞች ያለንንን ክብር የምንሰጥበት ብቻ ሳይሆን የኦሊምፒክ እንቅስቃሴ የተወለደበትን የምናስታውስበት ዕለት መሆኑን አስታውቀዋል።ዶክተር አሸብር አያይዘውም፣ በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት የቶኪዮ ኦሊምፒክ የተራዘመ ቢሆንም ይህን ድል ወደ መልካም አጋጣሚ መቀየር ከተቻለ ለሥራዎቻችን እና ለዝግጅቶቻችን በቂ ጊዜ ይፈጥርልናል ብለዋል ። ኮሚቴው በዓሉን ሲያከብርም 60 ለሚሆኑ የቀድሞ ስፖርተኞች ማለትም ለ41 ቬትራን አትሌቶች እና 19 ከተለያዩ ፌዴሬሽኖች ለተውጣጡ የቀድሞ ስፖርተኞች የዱቄት፣ መኮሮኒ፣ ዘይት እና ሳሙና ድጋፍ አድርጓል። በተጨማሪም ጤናማ ስፖርት እና ስፖርተኛ ሊገኝ የሚችለው ከጤና አካባቢ መሆኑን በማመን የችግኝ ተከላ ሥነ ሥርዓት ተካሂዷል።አዲስ ዘመን ሰኔ 18/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=35067
[ { "passage": "ያልተጠበቁ አስደናቂ አሸናፊዎች፣ ለአሸናፊነት ጥቂት የቀራቸው የሚያስቆጩ ሽንፈቶች፣ አሳዛኝና አስደንጋጭ አጋጣሚዎች፣ በስፖርታዊ ጨዋነት የታጀቡ ክስተቶች፣ ለቀጣዩ ትውልድ ለታሪክ የሚዘልቁ ሁነቶች ባለፉት አስር ቀናት ተስተናግደውበታል። ሁለት ዓመታትን የጠበቀው 17ኛው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ከ10 ቀናት ቆይታ በኃላ ለቀጣይ ሁለት ዓመታት በቀጠሮ ተሰናብቷል። ከጅማሬውም በእስያ መካከለኛው ምስራቅ አቅጣጫ የምትገኘው አገር ከስፔኗ ባርሴሎና እና ከአሜሪካዋ ኦሪጎን ግዛት በልጣ ለዚህ ውድድር መታጨቷ አነጋጋሪ ነበር። በርካታ አስደናቂ ጉዳዮች እና ጥቂት ጉድለቶች ከአስቸጋሪው የአየር ሁኔታ ጋር አጣምሮ ሲካሄድ የቆየው የዶሃው ዓለም ቻምፒዮናም ከትናንት በስቲያ መቋጫውን አግኝቷል። 200 አገራት በሺዎች የሚቆጠሩ አትሌቶቻቸውን ባሳተፉበት ቻምፒዮና፤ 43 አገራት የሜዳሊያ ሰንጠረዡ ውስጥ ሲገቡ 68 የሚሆኑት ደግሞ እስከ 10ኛ ደረጃ ባለው ውጤት ውድድራቸውን አጠናቀዋል። ይህም እ.ኤ.አ በ2017 ለንደን ላይ ከተመዘገቡ ክብረወሰኖች እጥፍ የሚሆኑትም በዶሃ ሊሰበሩ መቻላቸውን ማህበሩ በድረገፁ አስነብቧል። በከሊፋ ስታዲየም በተካሄደው የመዝጊያ መርሀ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ፕሬዚዳንት ሰባስቲያን ኮ የዶሃውን ዓለም ቻምፒዮና በታሪክ ምርጡ እንደነበር መስክረዋል። ኮ በንግግራቸው «ስፖርታችንን ለምትከታተሉና ለስፖርቱ ቅርብ ለሆናችሁ ሁሉ የአትሌቶቻችንን እና አሰልጣኞቻችንን ስኬት በቻምፒዮናው መመዘን ችለናል። በዓለም ላይ ያሉ አትሌቶች ሁሉ በቻምፒዮናው ታሪክ የሚልቀውን አቋማቸውን አሳይተዋል፤ ይህም አስደናቂ ነበር። ለውድድሩ የሚሆነውን ሁሉ ያሟላችው አዘጋጇ አገርም በዚህ መመስገን ይገባታል» ብለዋል። የኳታር ዓለም ቻምፒዮና\nአዘጋጅ ኮሚቴ ምክትል ፕሬዚዳንት ዳሃላን አል ሃማድ በበኩላቸው፤ የቻምፒዮናው አዘጋጅ በመሆናቸው የኳታራዊያን ህልም እንደሰመረ ነው የገለፁት። በአስተያየታቸውም «ለአዘጋጅነት ፍላጎት ያሳየነው ከ1997 ጀምሮ ነበር፤ ለዓመታት ፍላጎታችንን ስናቀርብ ቆይተንም በ2010 የዓለም የቤት ውስጥ ቻምፒዮናን ለማሰናዳት እንዲሁም የዳይመንድ ሊግ አንድ መዳረሻ ለመሆን በቃን። ይህ ጥሩ ቢሆንም መሰል ውድድርን በአገራቸው ሲካሄድ ለመመልከት የሚፈልጉ ትውልድ ላይ በመድረሳችን ለማዘጋጀት በቅተናል» ማለታቸውን ዘገባው ጠቁሟል። በዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር እስካሁን ከተደረጉት የዓለም ቻምፒዮናዎች በተሰጠው ደረጃ መሰረትም ዶሃ ቀዳሚውን ስፍራ መቆጣጠር ችላለች። ለንደን ሁለተኛ ስትሆን፤ የሴቪላ፣ የቤጂንግ እና የበርሊን ቻምፒዮናዎች ከአንድ እስከ አምስት ያለውን ደረጃ ይዘዋል። በዚህ ቻምፒዮና ላይ በርካታ ወጣት አትሌቶች የታዩ ሲሆን የሜዳሊያ ባለቤቶችም ሆነዋል። ከእነዚህ ስኬታማ አትሌቶች መካከል ደግሞ ኢትዮጵያዊያኑ ሰለሞን ባረጋ እና ለሜቻ ግርማ ተጠቃሽ ሆነዋል።አዲስ ዘመን  መስከረም 27/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "e89e3596cf846fe32929f8ef7b64ad76" }, { "passage": "ብርሃን ፈይሳ ጃፓን አስተናጋጅ የሆነችበት የቶኪዮ ኦሊምፒክ ሊካሄድ 192 ቀናት ብቻ ይቀሩታል። ኢትዮጵያም ለዚህ ኦሊምፒክ ከዚህ ቀደም ተደርጎ በማያውቅ ሁኔታ ስምንት ወራትን አስቀድማ ተሳታፊ አትሌቶቿ ወደ ዝግጅት እንዲገቡ አድርጋለች። የምትሳተፈው በአትሌቲክስ፣ ቦክስ እና ወርልድ ቴኳንዶ ስፖርቶች ቢሆንም፤ በተለይ ታዋቂ የሆነችበትና ውጤትም የምታስመዘግብበት አትሌቲክስ ዝግጅቱን አጠናክሮ ቀጥሏል። በመካከለኛና ረጅም ርቀት ለሚካሄደው ውድድር የተመረጡት አትሌቶች ለሁለት ተከፍለው በአሰለፈች መርጊያ እና ሰንዳፋ በሚገኘው ጥሩነሽ ዲባባ ሆቴል መቀመጫቸውን አድርገዋል። አጠቃላይ እየተካሄደ ያለው ዝግጅት ምን ይመስላል በሚለው ላይም አዲስ ዘመን ከፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አትሌቲክስ ክለብ ዋና አሰልጣኝና የቶኪዮ ኦሊምፒክ ረጅም ርቀት ዋና አሰልጣኝና የአሰልጣኞች አስተባባሪ ኮማንደር ሁሴን ሸቦ ጋር ቆይታ አድርጓል። በግዙፏ አህጉር ለሁለተኛ\nጊዜ ጃፓን የምታዘጋጀው\nይህ ኦሊምፒክ የኮቪድ\n19 ቫይረስ በመላው ዓለም\nባሳደረው ተጽእኖ ምክንያት\nለአንድ ዓመት ሊራዘም\nችሏል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ\nብሄራዊ ቡድንም \nዝግጅቱን አቋርጦ በመቆየት ካለፈው ህዳር/2013 ዓ.ም መጀመሪያ አንስቶ ተሰባስቧል። አሰልጣኝ ሁሴን ሸቦም አሰልጣኞችና አትሌቶች በተደረገላቸው ጥሪ መሰረት በሆቴል ተሰባስበው ስልጠና ላይ እንደሚገኙ ይገልጻሉ። በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እና አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በኩልም የሚደረግላቸው ክትትልና ቁጥጥርም በመልካም ሁኔታ እየሄደ መሆኑንም ያመላክታሉ። አሰልጣኝ ሁሴን እንደሚሉት፤ በአሰልጣኞች ቡድን በተያዘው እቅድ መሰረት ስልጠናው የሚሰጠው በምዕራፍ ተከፋፍሎ ነው። በሂደት አትሌቶቹ ለውድድር ብቁ መሆናቸውና የሚያስመዘግቡት ብቃትም እየተመዘነ በመጨረሻ በየርቀቱ አንድ ተጠባባቂ ብቻ በመያዝ 16 አትሌቶች የሚቀሩ ይሆናል። የቡድኑ አባላት አትሌቶች የሚመረጡት ከሁሉም የሀገሪቷ አቅጣጫ መሆኑን ጠቅሰው፣ ከትግራይ ክልል የተመረጡ አትሌቶች በወቅቱ በነበረው ሁኔታ ክለቡን መቀላቀል እንዳልቻሉና ይህም በስልጠናው ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ሊያሳርፍ ይችላል የሚል ስጋት አሳድሮ ነበር ይላሉ። አሰልጣኞች በወቅቱ አትሌቶቹ ያሉበትን ሁኔታ ለማወቅ ሙከራ ማድረጋቸውን አስታውሰው፣ በክልሉ የስልክ አገልግሎት በመቋረጡ ምክንያት መገናኘት አለመቻሉ በዝግጅቱ መጀመሪያ ችግር አጋጥሞ እንደነበር ይናገራሉ። እንደ አሰልጣኙ ገለጻ፤ ኦሊምፒኩ በሚካሄድበት በፈረንጆቹ መጋቢት ወር በጃፓን የሚኖረው የአየር ሁኔታ ሞቃታማ እንደሚሆን ይጠበቃል። በመሆኑም ይህንን ያገናዘበ ስልጠና ከመስጠት አንጻር እየተሰራ ነው። ከዚህ ጎን ለጎን ኦሊምፒኩ ከመካሄዱ አስቀድሞ ለኦሊምፒኩ አጋዥ ሊሆኑ የሚችሉ ውድድሮች ይኖራሉ። እንደ ዳይመንድ ሊግ ያሉ ውድድሮች በተለይ ጠቃሚ ቢሆኑም፤ አሳዛኝ በሆነ መልኩ ዘንድሮ እንደ ቀደሙት ጊዜያት ውድድሮችን በቀላሉ ማግኘት አይቻልም። ለአብነት ያህልም የዓለም ሀገር አቋራጭ ቻምፒዮና የተሰረዘ ሲሆን፤ የዓለም የቤት ውስጥ ውድድሮችም በተመሳሳይ አይካሄዱም። በስፖርት ቤተሰቡም በኩል ከቀደመው ጊዜ በተለየ መቀዛቀዝ በመስተዋሉ ምቾት የሚነሱ ጉዳዮች መኖራቸውን ነው አሰልጣኙ የሚጠቁሙት። የሆነ ሆኖ ግን በዳይመንድ ሊግ ውድድሮች አትሌቶችን በማሳተፍና ሚኒማ እንዲያሟሉ በማድረግ ኢትዮጵያ የለመደቻቸውን የወርቅ፣ ብርና ነሃስ ሜዳሊያዎች ለማስመዝገብ ዝግጅቱ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ይላሉ። አትሌቲክስ የረጅም ጊዜ ስራን የሚፈልግ እንደመሆኑ ስምንት ወራትን ቀደም ተብሎ ዝግጅት መጀመሩ መልካም መሆኑንም ነው አሰልጣኙ ያብራሩት።ባለፉት\nኦሊምፒኮች አትሌቶች በዝግጅት\nላይ ሆነውም ሚኒማ\nእንዲያሟሉ መደረጉ ወጣ\nገባ ማለትን የሚያስከትልና\nስልጠናው ላይም ተጽእኖ\nየሚያደርስ መሆኑን በመጥቀስ\nየስፖርት ቤተሰቡ ስጋቱን\nይጠቅሳል የሚሉት አሰልጣኝ\nሁሴን፣ ለሁሉም አትሌቶች\nየሚሆኑ ውድድሮችን በተመሳሳይ\nጊዜ ማግኘት እንደማይቻል\nነው የሚናገሩት። ለዚህ\nየተቀመጠው መፍትሄ አትሌቶች\nውድድር ሲኖራቸው ቡድኑ\nካለበት ካምፕ ወደ\nውድድሩ ስፍራ ተጉዘው\nከተካፈሉ በኋላ በቀጥታ\nወደ ካምፕ እንዲመለሱ\nማድረግን መሆኑን ያመለክታሉ።\nከዚህ ቀደም በተካሄዱ\nኦሊምፒኮችም መሰል ልምዶች\nእንዳሉ አሰልጣኙ ያስገነዝባሉ።\nውድድሩ\nየአትሌቶች ብቃት የሚለካበት\nመሆኑን ጠቅሰው፣ ቡድኑ\nላይ የሚያሳድረው ተጽእኖ\nእንዳይኖር ይሰራል ብለዋል።\nየኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ\nእና አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም\nበዚህ ረገድ እገዛ\nእንደሚያደርጉም ነው ተስፋቸውን\nያመለከቱት። ማጣሪያን\nበተመለከተም አሰልጣኝ ሁሴን\nከዚህ ቀደም በሄንግሎ\nበሚደረገው የሰዓት ማጣሪያ\nሚኒማውን ማሟላት የቻሉ\nአትሌቶች ይመረጡ እንደነበር\nያስታውሳሉ። በዚህ ዝግጅት\nላይ ግን ተጨማሪ\nማጣሪያ ተዘጋጅቶ የመጀመሪያው\nየዝግጅት ምዕራፍ እንደተጠናቀቀ\nማጣሪያ ማካሄድ ቢቻልና\nአጠቃላይ የቡድን ዝግጅቱ\nከተጠቃለለ በኋላ የተለመደው\nየሄንግሎ ማጣሪያ ቢከተል\nመልካም እንደሚሆንም አሰልጣኝ\nሁሴን ሃሳባቸውን ያቀርባሉ።\nይህንኑ ሃሳብ ለኦሊምፒክ\nኮሚቴና ለፌዴሬሽኑ በማቅረብ\nበጎ ምላሽ እንደሚያገኙም\nያላቸውን ተስፋ ይገልጻሉ።\nአትሌቶች\nበብዛት ውጤት የማያገኙ\nከሆነ በሄንግሎ ብቻ\nተመርጦ በኦሊምፒክ ላይ\nውጤታማ ለመሆን ይቻላል\nማለት አስቸጋሪ ነው\nያሉት አሰልጣኙ፣ ተደጋጋሚ\nልምድና ተደጋጋሚ ውድድር\nበማድረግ ከዚያ መካከል\nነጥረው የወጡትን አትሌቶች\nበአካል ብቻም ሳይሆን\nበስነ ልቦና ረገድ\nኃላፊነትና የሀገር አደራን\nመወጣት እንዲችሉ ለማድረግ\nዘንድሮ ተጨማሪ ውድድሮች\nለማድረግ መታቀዱን ይገልጻሉ።\nእንደሚታወቀው\nአትሌቶች በግል ውድድሮቻቸው\nላይ ይልቁንም በጎዳና\nላይ ውድድሮች ትኩረት\nማድረጋቸው የሀገሪቷ የመም\nውጤቶች እንዲዳከሙ አድርጓል።\nከዚህ ቀደም በተካሄዱ\nኦሊምፒኮች ላይም ይኸው\nምልክት መስተዋሉ በዚህ\nኦሊምፒክም ተመሳሳይ ስጋት\nአሳድሯል። በረጅም ርቀት\nአሰልጣኝነት ከፍተኛ ልምድ\nያካበቱት አሰልጣኝ ሁሴን\nሸቦ ግን በቶኪዮ\nኦሊምፒክ ውጤት ከማስመዝገብ\nአንጻር ስጋት እንደሌላቸው\nነው የሚገልጹት። በእርግጥ\nበሀገሪቷ የኦሊምፒክ ተሳትፎ\nትልልቅ ውጤት የተመዘገበባቸው\nየሲድኒ እና ቤጂንግ\nኦሊምፒኮች ናቸው። አሁን\nዋነኛው ነገር አትሌቶችን\nከጎዳና ላይ ውድድሮች\nማቀብ አስፈላጊ መሆኑ\nነው። በእርግጥ ይህም\nቀላል ስራ ሳይሆን\nከአትሌቶችና ከማናጀሮቻቸው ጋር\nአስቸጋሪ ትንቅንቅ ማድረግን\nይጠይቃል። ነገር ግን\nፌዴሬሽኑ የሚረዳቸው ከሆነ\nበመተጋገዝ አትሌቶችን ከጎዳና\nወደ መም መመለስ\nይቻላል። ይህ ከሆነም\nስጋት እንደማይኖርና ብቃት\nያላቸው አትሌቶች መኖራቸውን\nይጠቁማሉ። በቅርቡ የዓለምን\nክብረወሰን የሰበሩ እና\nአሁንም መስበር የሚችሉ\nጠንካራ አትሌቶች እንዳሉም\nያረጋግጣሉ። በብዙዎች\nዘንድ ያደረው ስጋት\nሊከሰት የሚችለው ካልተሰራ\nእና ባለመስማማት ብቻ\nመሆኑንም ጠቅሰዋል። አትሌቶቸና\nአሰልጣኞች፣ አሰልጣኞችና ፌዴሬሽኑ\nእንዲሁም ኦሊምፒክ ኮሚቴው\nበስምምነትና በመተባበር ከሰሩ\nውጤት በእጃቸው ላይ\nመሆኑንም ይጠቅሳሉ። ሃሳባቸውን\nለማጠናከርም በሪዮ ኦሊምፒክ\nየተጠበቀው ውጤት ላለመመዝገቡ\nምክንያት የሆነው በፌዴሬሽኑ\nውስጥ የነበሩ ሁኔታዎች\nመሆናቸውን አስታውሰዋል። ሁሉም\nሀገራት የተሻለ ዝግጅት\nአድርገው በውድድሩ እንደሚካፈሉ\nእርግጥ ቢሆንም ቡድኑ\nአሁን ባለበት ሁኔታ\nግን ጥሩ የውጤታማነት\nእድል ያለው ከመሆኑም\nባለፈ እስካሁን ከተመዘገቡ\nከፍተኛ ድሎች ያልተናነሰ\nውጤት ሊመዘገብ የሚችልበት\nእድል መኖሩን ይጠቁማሉ። አጀማመሩ\nመልካም የሚባል ከመሆኑም\nባሻገር አትሌቶች ከጎዳና\nላይ ውድድሮች ታቅበውና\nየግለሰቦች ጣልቃ ገብነት\nሳይኖር የሚቀጥል ከሆነ\nእንዲሁም በወጣው ዕቅድ\nመሰረት ስልጠናው ወቅቱን\nጠብቆ ከተካሄደ የተሻለ\nውጤት ሊመዘገብ እንደሚችልም\nነው አሰልጣኙ ተስፋቸውን\nየገለጹት። ከዚህ ቀደም\nየነበረው አትሌቶች በሌሎች\nውድድሮች ላይም ተሳትፎ\nሲያደርጉ ቆይተው ውድድሩ\nሲቃረብ ጉዳት ማስተናገድና\nለህመም መዳረግ ነው\nይላሉ። እንደ አሰልጣኙ ገለጻ፤ ከኮቪድ 19 ጋር በተያያዘ ስልጠናው በጥንቃቄ እየተሰጠ ሲሆን፤ የፌዴሬሽኑ ሃኪሞችም ጥሩ ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ ላይ ናቸው። በዝግጅቱ ማጠናቀቂያ ምናልባትም ቫይረሱ የሚገኝባቸው አትሌቶች ሊኖሩ ይችላሉ። በዚህ ረገድ በአሰልጣኞች የተያዘው እቅድ ከወትሮው ለየት ያለ ነው። ይኸውም ቀድሞ በተወዳዳሪነት ይያዙ የነበሩት አራት አትሌቶች ቢሆኑም አሁን ግን አምስት አትሌቶችን በመያዝ፤ ውድድሩ ሲደርስ ቫይረሱ ተገኝቶባቸው የሚቀሩ አትሌቶች ቢኖሩ በምትካቸው የሚገቡ ይሆናል። የቫይረሱ ባህሪ አስቸጋሪና ሊገመት የማይችል በመሆኑ ወደ ጃፓን የሚኖረው ጉዞ ቀናትን አስቀድሞ እንደመሆኑ ከዚህ ነጻ ሆነው እዚያ ከደረሱ በኋላ የሚያዙ ሊኖሩ ስለሚችሉም ሁለት ተጠባባቂዎችን ይዞ መጓዙ የተሻለ ይሆናል።", "passage_id": "6f952b5709aad40109b500b153b9a670" }, { "passage": "በቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ በእግር ኳስ ለመሳተፍ የአፍሪካ አገራት ሁለተኛውን የደርሶ መልስ የማጣሪያ ጨዋታዎችን ካለፈው ሳምንት ጀምሮ አከናውነዋል። በዋናው ብሔራዊ ቡድን አሠልጣኝ አብርሃም መብራቱ እየተመራ ከሁለት ሳምንት ላላነሰ ጊዜ ሲዘጋጅ የቆየው የኢትዮጵያ ከ23 ዓመት በታች ኦሊምፒክ ቡድን ማጣሪያውን ሳያልፍ ቀርቷል። ባለፈው ሐሙስ የመጀመሪያውን ጨዋታ በሜዳው ከማሊ አቻው ጋር ያደረገው የኢትዮጵያ ከ23 ዓመት በታች ኦሊምፒክ ቡድን አንድ ለአንድ መለያየቱን ተከትሎ ወደ ቀጣዩ ዙር የማለፍ ተስፋው አጣብቂኝ ውስጥ ገብቶ ነበር። እንደ ተሰጋውም ከትናንት በስቲያ ምሽት ወደ ባማኮ አቅንቶ ከሜዳው ውጪ ያደረገውን የመልስ ጨዋታ አራት ለዜሮ ተሸንፏል።በዚህም መሠረት 5ለ1 በሆነ ድምር ውጤት ወደ ቀጣዩ ዙር ሳያልፍ ቀርቷል። እአአ 2004 ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ በኦሊምፒክ እግር ኳስ የተሳተፈችው ማሊ ወደ መጨረሻውና ሦስተኛው ዙር ማጣሪያ ስታልፍ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የመሳተፍ ዕድሏ በጊዜ ከስሟል። ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የማጣሪያ ጨዋታ ሶማሊያን በሜዳዋና በገለልተኛ ሜዳ በሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፋ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፏ ይታወሳል። ማሊን ጨምሮ አስራ ስድስት የአፍሪካ አገራት ቀጣዩን ዙር መቀላቀላቸውን ካለፈው ሰኞ ጀምሮ አረጋግጠዋል። ያለፈው የአፍሪካ ከሃያ ሦስት ዓመት በታች ዋንጫ አሸናፊዋ ናይጀሪያ ቀጣዩን ዙር ከተቀላቀሉ አገራት መካከል ስትገኝ ሞሮኮ ባልተጠበቀ መልኩ በጊዜ ተሰናባች ሆናለች። ሁለተኛው የማጣሪያ ጨዋታ መጠናቀቁን ተከትሎ ያለፉት አገራት በሦስተኛው ዙር የሚገጥሙትን አገር ማወቅችለዋል። በመጨረሻውና ሦስተኛው ዙር የማጣ ሪያ ጨዋታ ደቡብ አፍሪካ ዚምባቡዌን ስትገጥም ዛምቢያ ከኮንጎ ብራዛቪል፣ጋና ከአልጄሪያ፣ካሜሩን ከቱኒዚያ፣ኮትዲቭዋር ከጊኒ፣ ሱዳን ከናይጄሪያ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከማሊ የሚገናኙ ይሆናል። የዓለማችን ትልቁ የስፖርት መድረክ ኦሊምፒክ በሩቅ ምሥራቋ አገር ጃፓን ቶኪዮ ከተማ ሊካሄድ ከሁለት ዓመት ያነሰ ጊዜ ይቀረዋል። በዚህ ኦሊምፒክ ላይ ለመሳተፍ እንደ እግር ኳስ ያሉ የስፖርት ዓይነቶች ረጅም የማጣሪያ ጨዋታዎችን ስለሚሹ ከወዲሁ እየተከናወኑ ይገኛል። በአፍሪካ ዞን ሦስተኛውን የማጣሪያ ጨዋታ የሚያሸንፉ ስምንት አገራት የሚለዩ ቢሆንም በቀጥታ ወደ ኦሊምፒክ አያመሩም። እነዚህ ስምንት አገራት ከዓመት በኋላ ግብፅ ለምታዘጋጀው ከሃያ ሦስት ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ በቀጥታ የሚያልፍ ይሆናል። በዚህ አፍሪካ ዋንጫ ላይ መሳተፍ ብቻ በቶኪዮ ኦሊምፒክ የሚያበቃም አይደለም። በአፍሪካ ዋንጫው ከአንድ እስከ ሦስት ያለውን ደረጃ ይዘው ያጠናቀቁ አገራት በኦሊምፒኩ ተሳታፊ መሆናቸውን ያረጋግጣሉ። የወንዶቹ የኦሊምፒክ ጉዞ እዚህ ላይ ያበቃ ቢሆንም በአሰልጣኝ ሠላም ዘራይ የሚመራው የኢትዮጵያ ሴቶች ኦሊምፒክ ብሔራዊ ቡድን የመጀመሪያ ምዕራፍ ዝግ ጅቱን በማጠናቀቅ ላይ ይገኛል። አሰልጣኝ ሠላም ዘራይ በሁለተኛ ምዕራፍ ዝግጅቷ የአቋም መፈተሻ ጨዋታ ከመሰል ሀገራት ጋር ለማድረግ ያደረገችው ጥረት የተሳካ አይመስልም። ያም ሆኖ የሚቀጥለው ሳምንት ረቡዕ መጋቢት 25 የመጀመሪያ የማጣሪያ ጨዋታቸውን በአዲስ አበባ ስቴዲየም የሚያደርጉት የኦሊምፒክ ሴቶች ቡድን የመልስ ጨዋታቸውን ከሦስት ቀን በኋላ በዩጋንዳ ካምፓላ የሚያደርጉ ይሆናል። እንስቶቹ በደርሶ መልስ ጨዋታ ድል የሚቀናቸው ከሆነም ቀጣይ ተጋጣሚያቸው ካሜሩን እንደምትሆን ካፍ አሳውቋል። ይህ ከሃያ ሦስት ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ በግብፅ ሲካሄድ ለሦስተኛ ጊዜ ሲሆን ውድድሩን ለማዘጋጀት ታጭታ የነበረችው ዛምቢያ ነበረች። ይሁን እንጂ ካፍ ይህን ዕድል 2017 መስከረም ወር ላይ ለግብፅ መስጠቱ ይታወሳል። ናይጄሪያ ያለፈው ውድድር ቻምፒዮን መሆኗም አይዘነጋም። በኦሊምፒክ መድረክ በእግር ኳስ የሚሳተፉ ተጫዋቾች ዕድሜያቸው ከሃያ ሦስት ዓመት በታች የሆኑ ብቻ ቢሆንም አንድ አገር ዕድሜያቸው ከሃያ ሦስት ዓመት በላይ የሆኑ ሦስት ተጫዋቾችን የማሰለፍ ዕድል ይኖረዋል። በሴቶች በኩል ግን በኦሊምፒክ እግር ኳስ ለመሳተፍ የዕድሜ ገደብ አልተቀመጠም። ጃፓን በኦሊምፒኩ የእግር ኳስ ጨዋ ታዎችን ለማስተናገድ በመዲናዋ ቶኪዮ ብቻ ሳትወሰን ሌሎች ከተሞችንም የውድድሩ መዳረሻ ማድረጓ ይታወሳል። ከቶኪዮ በተጨማሪ ኢባራኪ፤ ሴታማ፤ ሳፓሮ፤ ሴንዳይና ዮኮሃማ የእግር ኳስ ውድድሮችን የሚያስተናግዱ ከተሞች ናቸው። ብራዚል ባስተናገደችው የ2016 ሪዮ ኦሊምፒክ በወጣት ቡድኗ አማካኝነት በወንዶች ቻም ፒዮን መሆኗ የሚታወስ ሲሆን ጀርመን በሴቶች ቻምፒዮን መሆን ችላለች።አዲስ ዘመን መጋቢት 19/2011በቦጋለ አበበ", "passage_id": "d6a217a2b323396b881854d75aa583f6" }, { "passage": "የጃፓኗ ቶኪዮ ከ56 ዓመታት በፊት ኦሊምፒክን ለመጀመሪያ ጊዜ አዘጋጀች። እአአ 1964 በተካሄደው በዚያ ኦሊምፒክ ላይም 82 ሀገራት ብቻ በአትሌቲክስ ስፖርት መሳተፋቸው ወቅቱን ታሪካዊ ከሚያደርጉት ሁነቶች መካከል ይጠቀሳል። እንደ አሁኑ100ሜትርን ከ10ደቂቃ በታች መሮጥ የሚችሉ አትሌቶች አልነበሩም። ሴት አትሌቶችም በኦሊምፒክ የሚሳተፉበት ረጅም ርቀት እስከ 800ሜትር ብቻ ነበር። ኢትዮጵያዊው ታላቅ አትሌት አበበ ቢቂላም ለመጀመሪያ ጊዜ ለሀገሩ እና ለራሱ የወርቅ ሜዳሊያውን ያጠለቀው በዚሁ ኦሊምፒክ ላይ ነበር። አሁን ጃፓን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ ሁለተኛውን ኦሊምፒክ ልታዘጋጅ ቀን እየቆጠረች ትገኛለች። ከዘመኑ ጋር የዘመነችው ቅንጡዋ ቶኪዮም የዓለምን ምርጥ አትሌቶች ልታወዳድር መሰናዶዋን በማጠናቀቅ ላይ ትገኛለች። ከከተማዋና ዝግጅቱ ዘመናዊነት ባለፈም ውድድሩ ካለፈው ጋር ሲነጻጸር በበርካታ መልኩ አድጓል። በዚህ ኦሊምፒክ ላይም ስደተኞችና በኦሊምፒክ ኮሚቴ ባንዲራ የሚወዳደሩትን ጨምሮ 200 ሀገራትን የሚወክሉ አትሌቶች ይከትሙባታል። 19 የነበሩት የስፖርት ዓይነቶችም አዳዲሶቹን ጨምሮ 50 ደርሰው ስፖርቶችን ሊያፎካክሩ ተሰናድተዋል። ይህንን ኦሊምፒክ ልዩ የሚያደርገውም ከጠቅላላ ተሳታፊዎች 48ነጥብ2 ከመቶ የሚሆኑት ሴት ስፖርተኞች ከወንዶች እኩል በ165 የውድድር ዓይነቶች የሚያካፈሉ መሆኑ ነው። እአአ በ2020ው የሚካሄደው ይህ ኦሊምፒክ ሊጀመር ዛሬ 353 ቀናት ብቻ ይቀሩታል። የውድድሩ አዘጋጆችም እስካሁን ከተካሄዱት ኦሊምፒኮች ሁሉ የተሻለው እንዲሆን በርካታ ሥራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል። ለውድድር ማካሄጃ የተመረጡት የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችም ወራት እየቀሩት በተያዘው ወር ተጠናቀው ለውድድር ዝግጁ መሆናቸውን ያስመሰክራሉም ተብሏል። በዚህ ሂደትም ይህንን ስኬት ላስመዘገቡት የሀገሪቷ የኦሊምፒክ ዝግጅት ኮሚቴ አባላት ዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ ሽልማት እንደሚያበረክትላቸው ኦሊምፒክ ቻናል የተባለው ድረገጽ አስነብቧል። ውድድሩ ከመካሄዱ አስቀድሞም የማዘውተሪያ ስፍራዎቹ በድጋሚ የሚፈተሹም ይሆናል። በእስያ አህጉር ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ኦሊምፒክን ያዘጋጀችው ጃፓን፤ በድጋሚ የአዘጋጅነት ዕድል ተሰጥቷታል። ለዚህ መሰናዶም በጥቅሉ 15ቢሊዮን ዶላር ማውጣቷ ተዘግቧል፤ ይህም ከዚህ ቀደም ለዝግጅት ከሚወጣው (አስፈላጊ ከሆነው) የላቀ ሆኖ ተገኝቷል። ከዚህም ባሻገር ውድድሩ በርካታ ተመልካቾችን እንዲያገኝ ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል። እስካሁንም 3ነጥብ22 ሚሊዮን ትኬቶች በሀገር ውስጥ ተመልካቾች ተገዝተዋል። ትኬቱን ማግኘት ላልቻሉ ደግሞ በተያዘው ወር በድጋሚ ለሽያጭ ሲቀርብ፤ የተቀረው ደግሞ በክረምቱ ወራት ገበያ ላይ ይውላሉ። በድምሩ 7ሚሊዮን508 ሺ 868 የሚሆኑ ሰዎች የተመዘገቡ ሲሆን፤ እስካሁንም የትኬት መቁረጫው ድረገጽ 24 ሚሊዮን 250 ሺ በሚሆኑ ሰዎች ተጎብኝቷል። የመክፈቻ እና መዝጊያ ትኬቶቹ ዋጋ ከ12ሺ- 300 ሺ የን የተተመነ ሲሆን፤ ሌላው ትኬት ግን 130 ሺ የን የሚያወጡ ይሆናል። ከተማዋ በሁለት በተከፈለ መልኩ መሰናዶዋን ያደረገች ሲሆን፤ አንደኛው ከተማ አትሌቶች ውድድራቸውን የሚያካሂዱበትና ባህሏንም የሚያሳይ ይሆናል። ሁለተኛው ደግሞ ዘመናዊነቷን የሚጠቁምና የአትሌቶች ማረፊያና የመገናኛ ብዙኃንን የያዘ ስፍራ ነው። እአአ በ1964 የመጀመሪያውን ኦሊምፒክ ያስተናገደው ስታዲየሟም የመክፈቻ እና መዝጊያ መርሃ ግብር በማካሄድ ዳግም ታሪክ ይጽፋል ተብሎ ይጠበቃል። በመክፈቻው ዕለት በርካታ ስፖርቶችን በማስጀመርም እስካሁን ከታየው የበለጠ ሜዳሊያዎች እንዲመዘገቡም ታቅዷል። በመዝጊያው ዕለት የሚካሄደው የማራቶን ውድድርም ሀገሪቷ የወርቅ ደረጃ በያዘችበት ታላቁ የቶኪዮ ማራቶን በሚደረግበት መልኩ የሚካሄድ ይሆናል። ውድድሩ በሚካሄድበት ወቅት ሙቀቱ ይበልጥ ተጽእኖ ሊያደርስባቸው የሚችለው በማራቶን አትሌቶች መሆኑ ይታወቃል። ነገር ግን በዚህ ውድድር ላይ የሚሳተፉት አትሌቶች በዶሀ በሚካሄደው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ልምድ ያገኛሉ በሚል ይጠበቃል። ከዚህ ባሻገር ግን በውድድሩ ወቅት በቦታው የሚኖረውን ሙቀት ለመከላከል ባለሙያዎች የዘየዱ ሲሆን፤ ስታዲየሞች በዛፍ የተከበቡ ሆነዋል እንዲሁም ጥላዎችንና የውሃ አቅርቦቶችን በማብዛት ለመቋቋም አስበዋል። በጎዳና ላይ ከሚከወኑት የብስክሌትና የማራቶን ውድድሮች ውጪ ለኦሊምፒኩ ሰባት የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ተዘጋጅተዋል። የአትሌቲክስና የእግር ኳስ ስፖርቶች እንዲሁም የመክፈቻ እና መዝጊያ መርሃ ግብሮች የሚከናውኑበት ትልቁ ስታዲየም 60 ሺ 102 ተመልካቾችን ይይዛል። የእጅ ኳስ ስፖርት መጫወቻ ስፍራው 13ሺ 291 ደጋፊዎችን ሲይዝ፤ የቦክስ ውድድር ማካሄጃው ደግሞ 11ሺ 098 ወንበሮች አሉት። የጠረጴዛ ቴኒስ መጫወቻው 10ሺ፣ ጁዶ እና ካራቴ 14ሺ471 እንዲሁም የክብደት ማንሳት 5ሺ 012 ሰዎችን የመያዝ አቅም ያላቸው የማዘውተሪያ ስፍራዎችም ተሰናድተዋል። ከእነዚህ ውጪ ያሉት ስፖርቶችም በተመሳሳይ እንደየ አስፈላጊነታቸው ከ5ሺ በላይ ተመልካቾችን መያዝ የሚችሉ የማዘውተሪያ ስፍራዎች ተዘጋጅተዋል። የዚህን ኦሊምፒክ አዘጋጅ ኮሚቴ በበላይነት የሚመራው የሀገሪቷ ጠቅላይ ሚኒስትር በሆኑት ዮሺሮ ሞሪ ሲሆን፤ ዝግጅቱን በተመለከተ «ይህ ኦሊምፒክ ከዚህ ቀደም ከታዩት ሁሉ አጓጊ እንደሚሆን አምናለሁ» ብለዋል። ማብራሪያቸውን ሲያጠናክሩም «ከመክፈቻ መርሃ ግብር ሁለት ቀናትን አስቀድሞ ከፉኩሺማ ከሚካሄደው የቤዝቦል ጨዋታ ጀምሮ በወንዶች ማራቶን ውድድሩ እስከሚጠቃለልበት ዕለት ከፍተኛ ዝግጅት ተደርጓል። ከዓለም አቀፍ የስፖርት ማህበራትና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ጋርም አንድ ዓመት ከግማሽ ለሚሆን ጊዜ በቅንጅት ስናቅድ ቆይተናል። ለእስካሁኑ ድጋፋቸው እያመሰገንን ለወደፊትም በመርሃ ግብሩ መሠረት አብረን እንሰራለን» ብለዋል። የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ፕሬዚዳንት ሰባስቲያን ኮ በበኩላቸው በሰጡት አስተያየት «ቶኪዮ ጥሩ ዝግጅት በማድረግ ላይ ትገኛለች። በድጋሚ በተዘጋጀውና እአአ 1664 በተገነባው የቀድሞ ስታዲየም፣ በከተማዋ መንገዶች እና ሌሎች ስፍራዎች ለአትሌቶች ጥሩ ዝግጅት አድርጋለች። የትኛውም ኦሊምፒክ የራሱ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ይኖሩታል፤ ቶኪዮ ግን በዚህ ላይ እየሰራች ትገኛለች። ማድረግ ያለባትን በማድረጓም እኛም ደስተኞች ነን፤ በቀጣይ በሚካሄደው የዓለም ሪሌ ውድድር ላይም ከዚህ በበለጠ እንደምንደመም ተስፋ አደርጋሁ» ብለዋል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 29/2011", "passage_id": "bee74b24b417b56e704874baad26c0db" }, { "passage": "ሰላሳ አንደኛው ኦሎምፒያድ ብራዚል ሪዮ ዲጀኒሮ ላይ ሊጀመር ነው። ነገ አርብ የመክፈቻው ሥነ-ሥርአት ይካሄዳል። ኦሎምፒክስ ብዙ ጊዜ የደስታ የሆታ ጊዜ ነው በእርግጥ በየጊዜው ውዝግብም አያጣውም። የዘንድሮም ከዚህ የተለየ አይደለም።የኦሎምፒክስ ችቦ በጀልባ ሪዮ ገብቷል።የሪዮ ኦሎምፒክ ዝግጅትና በውድድሩ ዙርያ የተከሰቱ ውዝግቦችን ያጠናከረ ዘገባ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ። ", "passage_id": "23c29cd7a595bb132139b11e0fea0ed8" } ]
e1217978fa5b30f06dc81e154898bb93
a05aeb114450545a22415d9f42e50c22
ስፖርት – ሰብዓዊነትን ጋሻ ያደረገ ማኅበራዊ ክዋኔ
ስፖርት የሰላም፣ ፍቅር፣ የአብ ሮነትና የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የወንድማማችነት ልዩ መገለጫ ነው። ስፖርት ዘር፣ ሃይማኖት፣ ፆታና ቀለምን አይለይም። በየት ኛውም ሁኔታ ውስጥ የስፖርታዊ እንቅስቃሴ አስኳል ሃሳብ ወዳጅነትና መተሳሰብ መሆኑ ይታወቃል። በታሪክ ገጾች እንደሰፈረውም በሰው ልጅ ታሪክ ባጋጠሙ በጎም ሆኑ መጥፎ ክስተቶች ስፖርት በአጋርነት ተሳትፏል። ስፖርታዊ ክንዋኔዎች ሰላምንና አንድነትን የሚሰብኩ እንደመሆናቸው በማህበራዊ፣ ፖለቲ ካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች በመግባት ሚናቸውን ሲወጡም ኖረዋል። ስፖርት ሰብዓዊነትን ያነገበ የልግስና ማዕድ መሆኑን የአለም ህዝብ እየፈተነ ባለው የኮሮና ወረርሽኝን ለመዋጋት ሲደረግና እየተደረገ ባለው ርብርብ ላይ በስፖርት ቤተሰቡ በኩል የታየው ተሳትፎ ትልቅ ማሳያ ይሆናል።የኮቪድ -19 ወረርሽኝ የአለም ህዝብን እንደ ቅጠል ከማርገፍ በተጨማሪ በተለያዩ መስኮች ላይ ይህ ቀረሽ የማይባል መቃወስን አስከትሏል።የስፖርት ኢንደስትሪው ደግሞ ዋነኛ ሠለባ ከሆኑ መስኮች በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳል። የቫይረሱ ስጋትነት በዓለም አቀፉ የጤና ተቋም ከተረጋገጠበት ጊዜ ጀምሮ፤ ውድድሮች ተቋርጠዋል፤ ተሰርዘዋል። ይህን ተከትሎ የአለምን ኢኮኖሚ በማንቀሳቀስ ረገድ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ የሆነው የስፖርት ኢንደስትሪውን በአጭር ጊዜ ለከፍተኛ የፋይናነስ ቀውስ ዳርጎታል።በአለም ስፖርት ላይ የተፈጠረው ከፍተኛ መቃወስ ግን የስፖርቱን ማኅበረሰብ የሰብዐዊነት ውሃ ልክ ከመሆን አላደናቀፈውም ነበር።የስፖርት ቤተሰብ በወረርሽኙ ጉዳት ከመቆዘም ይልቅ ,፤ የሰብዐዊነት ጋሻን በማንሳት አለምን ከጭንቅ ለማውጣት በሚደረገው ርብርብ ሰፊ ተሳትፎ ሲያደርግ ነበር፤እያደረገም ይገኛል። በስፖርቱ መስክ ዓለም አቀፍ ዝናን ካተረፉ ግለሰቦች እስከ ዓለም አቀፍ ተቋማት ድረስ ወረርሽኙን ለመመከት እየተደረገ ባለው ርብርብ ሲያደርጉ የነበረው ተሳትፎ ትልቅ ቦታ አጊንቷል።የስፖርቱ ዘርፍ ባለድርሻ የሚባሉት አካላት በተናጠልና ተቋማዊ በሆነ መልኩ ድጋፍ ለሚሹ ድጋፍ በማድረግ እንዲሁም ገንዘብ በማሰባሰብ ወረርሽኙን የመዋጋት ሂደቱን በፊት አውራሪነት ሲመሩ ታዝበናል።በተለያዩ ሀገራት ዓለም አቀፉን ወረርሽኝ ለመዋጋት በስፖርቱ ማኅበረሰብ ዘንድ የታየው ተሳትፎ በሀገራችንም ተመሳሳይ ሲሆን ታዝበናል። በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት ይፋ ከተደረገበት ከወርሃ መጋቢት መጀመሪያ አንስቶ የስፖርቱ ማህበረሰብ ድርሻ ግዙፍ ነው። በስፖርት ዘርፍ የሚገኙ የመንግሥትና የግል ተቋማት፣ የስፖርት ማህበራት፣ ተጫዋቾች፣ አትሌቶች፣ የእግር ኳስ ክለቦችና ተጫዋቾች ወረርሽኙን ለመከላከል የሚደረገውን ርብርብ ተሳትፎ ሲያደርጉ ነበር።በዘመነ ኮሮና የስፖርቱ ማኅበረሰብ ሰብዐዊነትን መሰረት ያደረገው እንቅስቃሴ እንደቀጠለ ይገኛል። በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ስፖርት ኮሚሽን አስተባባሪነት ሚያዝያ 17 ቀን 2012 ዓ.ም የተጀመረውን «ማዕድ ማጋራት» መርሃ ግብር ሶስተኛው ዙር ከትናንት በስቲያ በአዲስ አበባ ትንሿ ስታዲየም ተጀምሯል።የስፖርቱ ማኅበረሰብ ህዝባዊነት የሚያረጋግጥ መሆኑ የተነገረለት ሶስተኛው ዙር ማዕድ የማጋራት መርሃ ግብር ሲጀመር ፤ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ኤሊያስ ሽኩር እንደተናገሩት፤ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት የመደጋገፍ እና የመረዳዳት የቀደመ ባህላችንን የበለጠ እንዲጎለብት አድርጓል።የኮሮና ቫይረስ ወደ ሀገራችን ከገባ ጀምሮ ወረርሽኙን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የስፖርቱ መንግስታዊ እና ህዝባዊ አደረጃጀቶች፣ ታዋቂ አትሌቶች፣ የደጋፊ ማህበራት፣ በአጠቃላይ የስፖርት ቤተሰቡ ህብረተሰቡን በማንቃት እና ኢኮኖሚያዊ ጫናውን ለመቋቋም የሚያግዝ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን በመጣት ላይ ያደረጉትን ተሳትፎ ጠቅሰዋል። የስፖርቱ ማኅበረሰብ ድጋፍ ተጠናክሮ የሚቀጥልና የምገባ መርሃ ግብሩ መጀመር ለዚሁ ማሳያ ይሆናል ብለዋል። የጎዳና ላይ የሚገኙ ወገኖቻችንን በተወሰነ መልኩ ለማገዝ አንድ ወር የሚቆይ የምገባ መርሃ ግብሩ ይሄንኑ ሚና መሰረት ባደረገ መልኩ መጀመሩን የተናገሩት አቶ ኤልያስ፤ በስታዲየም ዙሪያ መርሃ ግብሩ እንዲደረግ የተመረጠበትን ምክንያት መኖሩን አመልክተዋል። «በወቅታዊ የኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ስርጭቱን ለመቆጣጠር ሲባል በተለይ ስታዲየም ዙሪያ የሚገኙ ባር እና ሬስቶራንቶች መዘጋታቸው እና በአካባቢው ያለው እንቅስቃሴ መቆሙ ይታወቃል። ሬስቶራንቶች መዘጋታቸውን ተከትሎ ከሬስቶራንቶች ተመላሽ የሚሆኑ ምግቦችን ይጠቀሙ የነበሩ የጎዳና ተዳዳሪዎችም ሆነ በስታዲየም አካባቢ የተለያዩ ነገሮችን በመሸጥ ይተዳደሩ የነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለከፋ ችግር ተጋልጠዋል። በመሆኑም ጊዜው የከፋ ችግር ላጋጠማቸው የህብረተሰብ ክፍሎች እጃችን የምንዘረጋበት፤ የጋራ መከራችንን በመተጋገዝ የምናልፍበት መሆኑን በማመን እና ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ነው »ሲሉ አብራርተዋል። አቶ ኤልያስ በመጨረሻ የተጀመረው ተግባር የሚቋረጡ ሳይሆን በቀጣይም እነዚህ ወገኖቻችን በዘላቂነት ህይወታቸውን ሊመሩበት በሚችሉ ጉዳዮች ላይ የስፖርት ቤተሰቡ በሙሉ አቅሙ የሚደግፍ መሆኑን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና የቢጂ አይ ኢትዮጵያ አመራሮች በጋራ በመሆን ባስተላለፉት መልዕክት ደግሞ፤ የምገባ መርሃ ግብሩ በቀጣይ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።በስፖርት ኮሚሽን አስተባባሪነት የተጀመረው ማዕድ የማጋራት መርሃ ግብሩ 3ኛ መጀመሩን በዘመነ ኮሮና የስፖርቱ ማኅበረሰብ ሰብዐዊ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን ያመላክታል ተብሏል።ሰኔ 17 ቀን 2012 ዓ.ም የተጀመረው ሶስተኛው ዙር «ማዕድ ማጋራት» መርሃ ግብሩ 300 የጎዳና ተዳዳሪዎችን ለአንድ ወር ያህል እንደሚመገቡ ታውቋል።በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ስፖርት ኮሚሽን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና ከቢ. ጂ አይ ኢትዮጵያ በጋራ በመሆን የመጀመሪያው ዙር ሚያዝያ 17 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ወራት የዘለቀ ነበር።የስፖርት ተቋማቱ ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ያቀረቡትን «የማዕድ ማጋራት ብሄራዊ ጥሪን»ተከትሎ መርሃ ግብሩን የጀመሩት ሲሆን፤ 300 የጎዳና ተዳዳሪዎችን ለአንድ ወር ያህል በመመገብ ሀሳቡን ተግብረውታል።ሁለተኛ ዙር ግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ወር ያህል ተግባራዊ ተደርጎ በመጠናቀቁ ፤ሶስተኛው ዙር መርሃ ግብር ከሰኔ 17 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሐምሌ 16 ቀን 300 የጎዳና ተዳዳሪዎችን በምገባ መርሃ ግብሩ ተጠቃሚ እንደሚደረጉ ታወቋል።በ3ኛው ዙር የምገባ ፕሮግራም የኢትዮጵያ መድን ድርጅት 600 ሺ ብር ድጋፍ በማድረግ የወገን አጋርነቱን ማሳየቱ ተነግሯል። የምገባ መርሃ ግብሩን ለሶስተኛው ዙር ማስቀጠል መቻሉ የስፖርቱ ማህበረሰብ በዘመነ ኮሮና ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ የተጠናከረ ተሳትፎ እያደረገ መሆኑን አመላካች ሆኗል። የመርሃ ግብሩ ተግባራዊነት ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ያቀረቡትን «የማዕድ ማጋራት ብሄራዊ ጥሪን» ወደ መሬት ከማውረድ በተጨማሪ፤ ስፖርት -ሰብዐዊነትን ጋሻ ያደረገ ማኅበራዊ ክዋኔ መሆኑን በተግባር እንዲረጋገጥ ያረጋገጠ መሆኑን ብዙዎች መስክረውለታል።አዲስ ዘመን ሰኔ 19/2012ዳንኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=35130
[ { "passage": "እግር ኳስ በመዝናኛነቱ እንዲቀጥል ሰላማዊ የውድድር መድረክ መፈጠሩ የግድ ነው። ስኬታማ ሊግ ለመመልከት ደግም ጊዜና ገንዘቡን ወጪ አድርጎ፣ ፀሐይና ብርድ ሳይበግረው፣ተስፋ አስቆራጩን ሰልፍ ተቋቁሞ ስታድየም የሚገኘው የስፖርት ቤተሰብ የአደጋገፍ ስርዓትና ስፖርታዊ ጨዋነት ወሳኝነት አለው።ወጥ የውድድር መርሃ ግብር እጦት፤የዳኝነት ውሳኔ አሰጣጥ ችግር እንዲሁም ደጋፊዎች፤ የተጫዋቾችና የአሰልጣኞች ስፖርታዊ ጨዋነት ምግባር ችግር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መገለጫ መሆን ከጀመሩ ዋል አደር ብለዋል።\nየወንድማማችነትና የመግባባት ምሳሌ የሆነው ንፁህ እግር ኳስ ተብክሏል። የስታድየም ድምቀትና ለእግር ኳሱ ውበት ዋና ተዋናይ የሆኑ ደጋፊዎች የአደጋገፍ ስርአት ተለውጧል።ከስታድየሞቻችን የሚሰሙት ህብረ ዝማሬዎች ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እየደበዘዙ በአንፃሩ አፀያፊ ስድቦችና ፀብ አነሳሽ ድርጊቶች ጎልተው ተሰምተዋል፤ታይተዋል።በእግር ኳስ ሁነት ማሸነፍና መሸነፍ ያለና ወደፊትም የሚኖር መሆኑ ተረስቷል።\nይህን ተከትሎ በሚነሱ ግርግሮች ስጋትም ስታድየሞቻችን ለህፃናት፣በእድሜ ለገፉ ሰዎች፣ሴቶችና ለአካል ጉዳተኞች ምቾት የሚነሱ ሆነዋል።አዳዲስ ተመልካችን ለመመልከት እስኪያቅትም የካምቦሎጆው መንደር ለእንግዶቹ በሩን የዘጋ መስሏል።ይሁንና በተለይ ባለፈው ዓመት የፕሪሚየር ሊጉ መገለጫዎች እስኪመስሉ የተስተዋሉና የአገሪቱን እግር ኳስን መቀመቅ የሚከቱ እክሎች በዘንድሮው የሊግ ውድድር እንዳይስተዋሉ ሊጉም ካለፉት ጊዜያት በተሻለ በስፖርታዊ ጨዋናት የታጀበ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ብዙ ደክሟል።\nየኢትዮጵያ እግር ኳስ የፌዴሬሽኑ አዲስ ተመራጭ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጂራ በየክልሉ እየዞሩ ስፖርታዊ ጨዋነትን ማረጋገጥ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ከከተማ አስተዳደሮች ጋር ተወያይተዋል።ክለባትና የደጋፊ ማህበራትም በየፊናቸው የየበኩላቸውን ተወጥተዋል።ክለቦች ተጨዋቾቻቸውን በስነ ምግባርና በእውቀት በማነጽ ረገድ የቤት ስራቸውን እንዲወጡ ተደርጓል። ከሳምንት በፊት በአዳማ ከተማ በስፖርታዊ ጨዋነት ዙሪያ የስፖርት ቤተሰቡን ያሳተፈ ውይይትም ተካሂዶ ነበር ።ይሁንና በስድስተኛው ስምንት የሊጉ መርሃ ግብር ፌዴሬሽኑም ሆነ የስፖርት ቤተሰቡ ጥረት ከንቱ ሆኖ የተለያዩ መድረኮች የተካሄዱ ስብሰባዎችም ፍሬ አልባ ሆነው ታይታል።በእለቱ በቅድሱ ጊዮርጊስና በሃዋሳ ከተማ መካከል ሊካሄድ በነበረው ጨዋታ ቀደም ሲል ለስፖርታዊ ጨዋነት ምክንያት ሆነው የሚቀርቡ ፤የዳኛ ውሳኔ አሰጣጥ ጉድለት፤ አሊያም ዳኞችን ውሳኔ አምኖ አለመቀበል፤ክብር የሚነኩ ዘለፋዎች፣የተጫዋቾችና አሰልጣኞች ለፀብ የሚያነሳሱ ድርጊቶች አልተስተዋሉም።ይልቅስ የስፖርታዊ ጨዋናት ጉድለቱ ጨዋታው ከመጀመሩ ቀድሞ የተከሰተ እንደመሆኑ ሌላ የግጭት መነሾ ተስትውላል። ከጨዋታው መጀመር 25 ደቂቃ ቀድሞ በደጋፊዎች መካከል የተካሄደው አምባጓሮም በርካታ የስፖርት ቤተሰቡን አባላት ለጉዳት ዳርጓል።ክስስቱም ጨዋታውን ለመታዳም ወደ ሜዳ የገቡ ደጋፊዎች ስሜት ክፉኛ አሳዝኗል፣አንገት አስደፍቷል።\nአስር ሰዓት ላይ መጀመር የነበረበት ጨዋታ እስከ ምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት ድረስ ቢጠበቅም የኋላ ኋላ በተለይ ሃዋሳ ከተማዋዎች ጨዋታውን ለማካሄድ ባለመፈለጋቸው ሳይካሄድ ቀርቷል።ከብጥብጡ በኋላ ለክስተቱ ዋነኛ ምክንያት ሆኖ የቀረበው፤ በእለቱ ለእንግዳ ደጋፊዎች የተዘጋጀው የመቀመጫ ስፈራ አናሳ ሆኖ መቅረቡ ነው የተባለ ሲሆን፤ይህ ግን ብቻውን ለክስተቱ አሳማኝና በቂ ምክንያት ነበር ብሎ ለመናገር አያስደፍርም። ምክንያቱም የቦታ ጥያቄ ከሆነም በውይይት መፍታት ሲቻል ድንጋይ የሚያወራውር አንዳችም ምክንያት ይኖራል ተበሎ አይታሰብም።\nምንም እንኳን በእለቱ የግጭቱ ቀስቃሽ የሆኑ ደጋፊዎችን በውል መለየት ቢያስችግርና ቅድሚያ ጥፋተኛ የነበረው ማነው የሚለውን አጣርቶ ውሳኔ የሚያሳልፈው የሊግ ኮሚቴው በእለቱ በስታዲየሙ አንድ አቅጣጫ የተስተዋለው ግጭትና በሜዳው ክልል የነበረው ድብድብ በእጅጉ የሚያሳፍ፤ የኢትዮጵያን ፕሪሚየር ሊግም ስርዓቱን የሚያስጠብቅለት እንደሌለ የሚመሰክር ሆኖ ታይቷል።ከሁሉም በላይ በእንግዳ ክለብ ደጋፊዎች በአግባቡ መለየትና ከአደጋ መከላከል የማያስችል አጥር መኖሩም ጉዳቱን ከባድ አድርጎታል።በተለይ የድንጋይ ውርውራውን ተከትሎ ሸሽተው ወደ ሜዳው ክልል በገቡ የሃዋሳ ደጋፊዎችና በቅዱስ ጊዮርጊስ ስትዋርትቶች መካከል የተፈጠረው ግብ ግብ እጅጉን የሚያሳዝን ሆኖ ታይታል።ይሁንና ስታዲየሙን ከአፍ እስከ ገደፉ የሞሉት የፈረሰኞቹ ደጋፊዎች ከምንም በላይ ለስፖርታዊ ጨዋነት በመገዛት ወደ ፀብ አለመመራትና ሜዳ ወደነበሩት የሃዋሳ ደጋፊዎች አለመግባታቸውም በብዙዎች ዘንድ አድናቆትን አሰጥቷቸዋል።\nየስታድየሙን ፀጥታ ለማስከበር የሚመደቡ የፖሊስ ኃይሎች ቀደም ሲል ከነበረው ታሪክ ጋር ሲነፃፃር ችግሮችን በውይይት ከመፍታት ይልቅ ዱላን አማራጭ አድርገው አለመታየታቸው በብዙዎች ዘንድ አድናቆትን አሰጥቷቸዋል።\nበአጠቃላይ አንድ እርምጃ ፈቀቅ ማለት በተሳነው እግር ኳሳችን መሰል ክስተቶች መመልከት የሚቆመው እንዲሁም ሊጉን ስነስርዓት የማስጠበቅ ኃላፊነት ያለባቸው የስፖርት ቤተሰቦች ይህኑ ተግባራቸውን በአግባቡ የሚወጡት መቼ እንደሆን ለመረዳት አዳጋች ሆኗል።ከሁሉም በላይ በቅዱስ ጊዮርጊስና በሃዋሳ ከተማ መካከል ሊካሄድ ከነበረው ጨዋታ ቀድሞ የተከሰተው የስፖርታዊ ጨዋነት መጓደል ግን ሊጉ ዘንድሮም ስርዓቱን የሚያስከብርለት ማጣቱን አሳይቷል።የሊጉን ስነስርዓት ለማስጠበቅ ከስፖርት ቤተሰቡም በላይ ከባድ ኃላፊነት ያለበት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በተለይም ጠንካራ ህግጋትን በማስተላለፍ ረገድ ከባድ የቤት ስራ እንዳለበት አመላክቷል።\nይህን መሰሉ የስታድየም ብጥብጥና ሁከት በጊዜ መፍትሄ ካልተበጀለት፤ ነገሮች ፈራቸውን ሳይለቁ አስቀድሞ ነገሮችን ማስተካከልና መስመር ማስያዝ ካልተቻለ ከዚህም በከፋ ሁኔታ ወደ መቀመቅ መውረዳችን ሳይታለም የተፈታ ይሆናል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 9/2011ታምራት ተስፋዬ", "passage_id": "a584f5aadc30450c16fe4134c39a5306" }, { "passage": "የአዲስ አበባ ምሽቶች፤ የመጠጥ ቤቶች ማለዳ እንዲሁም ጭፈራ ብቻ የሚስተናገድባቸው መሆንን ከተዉ ከራርመዋል። ከፖለቲካ ይልቅ ማኅበረሰብ ላይ ለውጥ ማምጣትና ተጽዕኖ መፍጠር እንደሚቻላት የሚነገርላት ጥበብ በተለያዩ ሥያሜና ክዋኔዎች ምሽቶቹን ተጋርታለች። ከቴአትርና ሲኒማ ቤቶች ውጪ፤ ወጣቶች ሰብሰብ ብለው በትልልቅ አዳራሽ በሮች ላይ ጥበባዊ ክዋኔን ለመታደም ሲጠባበቁ ማየት እየተለመደ ነው። ያሳለፍነውን ሰኞና ማክሰኞን እንደማሳያ ብንጠቅስ እንኳ ብራና ግጥም በጃዝ እንዲሁም ጦብያ ግጥም በጃዝ የተባሉ ክዋኔዎችን እናገኛለን።በእነዚህ ክዋኔዎች መታደም የቻለችው አዲስ ማለዳ አዳራሽ የሞላውን ታዳሚ እንዲሁም ለቀረቡ ዝግጅቶች ያለውን ግብረ መልስ መታዘብ ችላለች። በአማካይ አንድ መቶ ብር በሚከፈልባቸው እነዚህ ዝግጅቶች ላይ ታዳሚዎች ሳያንገራግሩ፣ የሚያደንቁና የሚያከብሯቸውን ሰዎች ለማየትና ለመስማት በመጓጓት፤ አዲስ ነገር ለማግኘት በአዳራሽ በሮች ላይ ከጥሪው ሰዓት ቀድመው ይገኛሉ። ይህ ከክዋኔዎቹ የወደዱት አንዳች ነገር እንዳለ ያሳብቃል። አዲስ ማለዳ ደግሞ ጠየቀች፤ “እነዚህ ጥበባዊ ክዋኔዎች ምን ፋይዳ አላቸው?” በዛውም ስለክዋኔዎቹ ጠቅላላ ገጽታ ከአዘጋጆች እንዲሁም የሥነ ጽሑፍ ባለሙያዎች ሐሳቦችን ተቀብላለች።ብራና ግጥምን በጃዝ ከወራት በፊት በምንገኝበት ዓመት ቀዳሚው ወር መስከረም ላይ እንደተጀመረ አዘጋጁ ጋዜጠኛ በፍቃዱ ዓባይ አስታውሷል። ዝግጅቱ ሲጀመርም ቀድመው ከሚካሔዱት በተለየ በየወሩ በሚደረገው መርሃ ግብር አንድ ርዕሰ ጉዳይ መምረጥና ሥራዎች በዛ ዙሪያ እንዲሆኑ ማድረግን ይዞ ነበር። መነሻውም ኪነ ጥበብ በሁሉም አገራዊ ጉዳይ ላይ ሚና ሊኖራት ይገባል የሚል ነው።በፍቃዱ በበኩሉ በቀደሙ መድረኮች ካያቸውና ቢሆን የሚመኛቸውን በማካተት ብራን ግጥም በጃዝን እውን እንዲሆን አድርጓል። በኪነ ጥበብ መድረኮች ያልተለመዱ የነበሩና በተለያየ ሙያ ላይ የሚገኙ ሰዎችን ለንግግር መጋበዝም በክዋኔው ተካትቷል። ታድያ እንደ በፍቃዱ ገለጻ እነዚህ ዝግጅቶች ለሥነ ጽሑፍ ወይም ለኪነጥበብ ብቻ ሳይሆን ፋይዳቸው ለአገር ነው።በተለይም ሰዎች የሚቀበሉትንም ሆነ የማይቀበሉትን ሐሳብ ቁጭ ብለው ማድመጥ እንዲችሉና ነገሮችን በተለያየ አንጻር እንዲመለከቱ ያስችላል ባይ ነው። “በዚህም ኪነ ጥበብ ተከታይ መሆኗ ቀርቶ ወደ መሪነት ትሻገራለች” ሲልም ይገልጻል። የክዋኔው ሐሳብም ኪነ ጥበብ ላይ በተለየ ለውጥ ለማምጣት ሳይሆን አገር ላይ ለውጥ ማምጣት ነው።በሙያው ጋዜጠኛ የሆነው ጌታቸው ዓለሙ ‘ሰምና ወርቅ’ የተሰኘ ወርሃዊ ኪነ ጥበባዊ ምሽት ያዘጋጃል። የዚህ ክዋኔ አጀማመር ደግሞ ከቀደመው በተለየ በአዲስ አበባ አማራጭ የመዝናኛና የቁም ነገር ምሽት መሆን ነው። አልፎም መድረክ ያላገኙ አዳዲስ የሥነ ጽሑፍ ባለሙያዎች ዕድል አግኝተውበታል። ጌታቸው እንዳለውም በቅርቡም በመድረኩ ላይ የቀረቡ ሥራዎችና ሌሎች የገጣምያኑ ሥራዎች በመጽሐፍ መልክ ለአንባቢ ይደርሳሉ።ኪነ ጥበብ የማይነካው ነገር የለምና፤ እንደቀደመው ሁሉ በዚህም መድረክ አገራዊ የሆኑ ጉዳዮች ሁሉ ይነሳሉ። ታድያ የእነዚህ ጥበባዊ ክዋኔዎች ፋይዳን በሚመለከት ጌታቸው ሲናገር፤ በአንድ በኩል ብዙ ገጣምያን እንዲጽፉ ማነሳሳት አስችሏል ይላል።ከዛም ባሻገር ሰዎች በሬድዮን እና በትዕይንተ መስኮቶች (‘ቴሌቪዥን’) ብቻ ያይዋቸው የነበሩና የሚያደንቋቸውን ሰዎች በአካል ለማግኘት፣ ሐሳባቸውን ለማካፈልና ለማነጋር ትልቅ ዕድል መፍጠሩንም አስታውሷል። አልፎም አሁን ላይ ለመመረቂያ ጽሑፍ ግብዓት እየሆኑም ነው። ጌታቸው “ጥናት የሚፈልግ ቢሆንም ለዘርፉ ትልቅ አስተዋጽዖ አድርጓል” ብሏል።እነዚህን አዲስ ማለዳ እንደማሳያነት ያነጋገረቻቸው የክዋኔዎቹ አዘጋጆች የሚጋሯቸው ሐሳቦች ደግሞ አሉ። በአንድ በኩል የኪነ ጥበብ ምሽቶች እየተነገደባቸው ነው ከሚለው ሐሳብ አንጻር ነው። ብዙ እንቅስቃሴዎች በራስ ተነሳሽነት ሳይሆን “ያዋጣል” ተብሎ በሚገባት ጊዜ ላይ በዚህ መልክ ሊታዩ የሚችሉ ሁኔታዎች እንዳሉ አዘጋጆቹ ገልጸዋል። ነገር ግን ወረቱን አልፈው መዝለቅ የሚችሉት ጥቂቶች ናቸው።ደግሞም ልፋት ያለው ሥራ መሆኑን ኹለቱም ጠቅሰዋል፣ ከፍ ሲልም በአዲስ አበባ ከተማ ክዋኔዎች በዝተዋል ቢባል እንኳ ካለው ሕዝብ አንጻር ያሉትም እዚህ ግባ የሚባሉ እንዳይደሉ ጠቁመዋል። የቦታ እጥረት፣ በገንዘብ በኩል ደጋፊ ማጣት፣ ሥራዎቻቸውን ለማስደመጥ፤ ሐሳባቸውንም ለማካፈል ፈቃደኛ የሆኑ አቅራቢዎችን እንደልብ ባለማግኘት ምክንያት ተመሳሳይ ሰዎችን በተደጋጋሚ ለማስተናገድ መገደድና የመሳሰሉት ደግሞ እንደተግዳሮት የጠቀሷቸው ናቸው።ከዚህም ባሻገር መድረኮቹ ወቅታዊ ክስተቶች ላይ ከማተኮራቸው ጋር ተያይዞ፤ ለጉዳዮቹ ትኩረት መስጠቱ ቅድሚያ ለሚገባው ቅድሚያ መስጠት ስለመሆኑ አዘጋጆቹ ገልጸዋል። እንደውም በፍቃዱ በንግግሩ “እንደአገር ቅድሚያ የምንሰጣቸው አንገብጋቢ ጉዳዮች አሉ። የመፍትሔ ሐሳብ እንዲቀርብባቸውና መነጋገሪያ እንዲሆኑ ወደ መድረክ ልናወጣቸው ይገባልና ነው” ብሏል።በተመሳሳይ ጌታቸውም ሰው ይተነፍስበት ከኪነ ጥበብ ውጪ ሌላ መሣሪያ የለውም ይላል። ፖለቲከኞች ራስ ወዳድ በሆኑበት ጊዜም ጉዳዮች ላይ በግልጽ ለመነጋገር ከኪነ ጥበብ ውጪ ማን ሊመጣ ነው ሲል ይጠይቃል። “በእነዚህ መድረኮች የአገር ችግር የእኔ ነው ብለው የሚያስቡ ሰዎች ከነሕመማቸው አይቀመጡም፤ ይተነፍሳሉ” ሲል ገልጾታል።ይህ ግን በትውልድ ላይ ስሜታዊነት በመፍጠር ሳይሆን፤ መፍትሔ አመላካች በመሆን ነው። ብዙ ለነፃነት የሚታገሉ የነበሩ ሰዎች አገር ጥለው ሲሸሹና ሲሰደዱ፤ ባሉበት በአቅማቸው እየተጋፈጡ ያሉት ግን የኪነ ጥበብ ሰዎች ናቸው። እናም የፖለቲካ ጉዳዮ እንዲሁም በጠቅላላው ወቅታዊ የማኅበራዊ ጉዳዮች መነሳታቸው በምክንያት እንደሆነ ነው አዘጋጆቹ በተመሳሳይ የገለጹ።በኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር የጥበብ እልፍኝ ሬድዮ ፕሮግራም ላይ የሲሳይ ዳሰሳ አዘጋጅ በመሆን ከአራት ዓመታት በላይ አገልግሏል፤ ደራሲ ገዛኸኝ ሀብቴ። እርሱ በበኩሉ የግጥም ወይም የኪነ ጥበብ ምሽቶች ያበረከቱትን አስተዋጽዖ ለመዘርዘር ጥናት እንደሚያስፈልግ አጠንክሮ ይጠቅሳል። ይሁንና ግን ስምንት ዓመታት ካስቆጠረው ጦብያ ግጥምን በጃዝ አንስቶ በቅርቡ እስከተነሱት ድረስ፣ ጊዜው ረጅም በመሆኑ ብዙ የፈጠሩት ለውጥ እንዳለ ይገልጻል። ለምሳሌም የዚሁ የጥበብ ምሽት ውጤት የሆነውንና በብዙዎች ዘንድ ተወዳጅነት ያለው “እያዩ ፈንገስ” የአንድ ሰው ቴአትርን ይጠቅሳል።ታድያ የእነዚህ ክዋኔዎች አስተዋጽዖ ለሥነ ጽሑፍ ተለይቶ የሚታይ ሳይሆን በጠቅላላው ኪነ ጥበብን የሚያካትት ነው። ይህም እነዚህ ክዋኔዎች ሙዚቃን፣ ተውኔትን፣ ዲስኩርና ወዘተ የመሳሰሉትን ያካትታሉና ነው። በተጨማሪም መድረኮቹን የፈጠሩት የኪነ ጥበብ ሰዎች ይገኛሉ፤ በዛው ልክ የደከሙት እንዳሉ ሆነው ማለት ነው።ግጥምን በጃዝ በሚል መጠሪያ በሚታወቁ ክዋኔዎች ላይ የሚቀርቡ ሥራዎችን በተመለከተ፤ ምሽቶቹ የግጥም ብቻ እንዳይደሉ ገዛኸኝ ይጠቅሳል። እንደውም በአንዳንዶቹ መድረኮች ከግጥሙ ይልቅ ዲስኩር ሲበዛም እንደሚታይ ያነሳል። አልፎም ግጥሞቹ በዜማ ሲታጀቡና የሚቀርቡት ማጀቢያ ዜማዎች ደግሞ የተለመዱና የተወደዱ ሲሆኑ፣ ከግጥሙ ይልቅ ሰው ትዝታውን የማዳመጥ ዕድሉ ሲለሚጨምር፤ ታዳሚ በዜማው እየተደለለ ግጥሞችን ሳያደምጥ እየቀረ እንዳይሆን እንደባለሙያ ሥጋቱን ገልጿል።መድረኮቹ በአንድ ጊዜ ነጻነታቸው ለታፈነ ሁሉ ድምጽና መተንፈሻ በመሆን ማገልገላቸውን የሚጠቅሰው ደራሲ ገዛኸኝ፤መድረኮቹና የሚቀርቡ ሃሳቦች ብዙውን ጊዜ በአገራችን እጦቶችና ሰቀቀኖች ላይ የተመሰረቱ በመሆናቸው ወቅታዊ ጉዳይ አጥተው ሊቀዛቀዙ እንደማይችሉ እምነቱን ይናገራል። በዚህም መሰረት ቀደም ባለው ጊዜ በእነዚህ መድረኮች ሕዝብ የጎደለውና ያጣው በተለያየ ኪነጥበባዊ መንገድ ሲተነፈስ ቆይቶ፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ መንግሥት አጣሁት ያለው እየተንጸባረቀ መሆኑን ጠቆም አድርጓል።ቅጽ 1 ቁጥር 37 ሐምሌ 13 2011", "passage_id": "e70f1c9e0f77cba6fa6ca6c365500000" }, { "passage": "የዓለም ሕዝብ ሁሉ ጭንቀትና ስጋት የሆነው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ከትንሽ እስከ ትልቅ፣ ከሀብታም እስከ ድሃ፣ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ዋነኛ ትኩረቱ እንዲሆን ካስገደደ ስድስት ወራት ተቆጠሩ፡፡ የቫይረሱ ስርጭት በእነዚህ ወራት እንደ ሰደድ እሳት ያላዳረሰው የዓለም ክፍል ስለመኖሩ አጠራጣሪ ሆኗል፡፡ ሀገራት ዓለም በጋራ የገጠማት ጦርነት በድል ለመወጣት የሚያስችል መፍትሄ ለማበጀት ጥረት ማድረጉን ተያይዘውታል። የቫይረሱ ማንነትና፣ ምንነት ፈጣን መፍትሄ ማበጀት የሚያስችል አልሆነም። በእርግጥም የኮሮና ወረርሽኝ በዓለም ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ መስተጋብር ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ብቻ ነውን? በእኔ እሳቤ አዎንታዊ እንዳለው መካድ ንፍግነት ይሆናል! የኮሮና ቫይረስ ዓለምን እንደጎዳት ባለበት ደረጃ ባይሆንም በጎ መልኮችን ይዞ መምጣቱን በድፍረት መናገር ይገባል። ዓለም ከገባችበት የጋራ ማዕጥ ለመውጣት ከሚደረግ ጉዞ የሚቀዳው «ሰውነትን» ያስቀደሙ ደጋግ እጆችን፤ ኅብረተሰቡ ከተጋረጠበት አደጋ ለመታደግ ሰብአዊነትን አርግዘው የሚወለዱ ድጋፎችን በዘመነ ኮሮና ሊበረክቱ ችለዋል። በዓለም አራቱም አቅጣጫዎች ሰብአዊነትን ባስቀደመ መልኩ ሲደረጉና እየተደረጉ ያሉ ድጋፎችን ብሶባቸው ታዝበናል። በተለያዩ መስኮች እንፋሎቱ ሳይበርድ የቀጠለው ልግስና ከስፖርቱ መስክ ያለውን ሁኔታ መመልከቱ ይበጃል።\nስፖርት ሰላም፣ ፍቅር፣ የአብሮነትና የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የወንድማማችነት ልዩ መገለጫ ነው። ስፖርት ዘር፣ ሃይማኖት፣ ፆታና ቀለምን አይለይም። በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ የስፖርታዊ እንቅስቃሴ አስኳል ሃሳብ ወዳጅነትና መተሳሰብ መሆኑ ይታወቃል። በታሪክ ገጾች እንደሰፈረውም በሰው ልጅ ታሪክ ባጋጠሙ በጎም ሆኑ መጥፎ ክስተቶች ስፖርት በአጋርነት ተሳትፏል። ስፖርታዊ ክንዋኔዎች ሰላምንና አንድነትን የሚሰብኩ እንደመሆናቸው በማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች በመግባት ሚናቸውን ሲወጡም ኖረዋል። ስፖርት ሰብአዊነትን ያነገበ የልግስና ማዕድ መሆኑን ዘመነ ኮሮና በተጨባጭ አሳይቶናል። የቫይረሱ ስጋትነት በዓለም አቀፉ የጤና ተቋም ከተረጋገጠበት ጊዜ ጀምሮ፤ ውድድሮችን ከማቋረጥና ከመሰረዝ ባለፈ የስፖርቱ ተዋንያን በተናጥልም ሆነ በተቋማዊ ደረጃ አበርክቷቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። በእግር ኳስ ጠቢብነታቸው ዓለም የመሰከረላቸው ተጫዋቾችና ስመ ጥር አሰልጣኞችም፤ ለደጋፊዎቻቸው መልእክት ከማስተላለፍና ገንዘብ ከመለገስ ባሻገር ሆቴሎቻቸውን ለህክምና አገልግሎት እንዲውሉም ጭምር መስጠታቸው ይታወሳል። በሀገራችን በተመሳሳይ የስፖርቱ ለጋስነትና ሰብአዊነት መገለጫ ያደረጉ ተግባራት ዛሬም እንደ ትናንቱ በዘመነ ኮሮና ከነበረው ብሶበት አለኝታነቱን እያሳየ ይገኛል። የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት ከታወቀበት ከመጋቢት መጀመሪያ አንስቶ በስፖርቱ ማህበረሰብ ጠንካራ እንቅስቃሴ በማድረግ አጋርነቱን በፈጠነና በቀደመ መልኩ ያሳየው። በስፖርት ቤተሰቡ በቡድንም ሆነ በተናጠል ለወረርሽኙ መከላከያ የሚውል የገንዘብ ድጋፍ በማሰባሰብ ከመንግስት ጎን በመቆም ወገን ላይ የተደቀነውን አደጋ በአንድነት ለመመከት ህዝባዊነቱን ማሳየት ችሏል፡፡\nበአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ የድጋፍ መሠባሰብ ጥሪ ተከትሎ የስፖርቱ ማህበረሰብ ተሳትፎ በተጠናከረ መልኩ መቀጠሉን ለመታዘብ ችለናል። ከመከላከያ ስፖርት ክለብ አካባቢ የተሰማው ዜና ይሄንኑ ያስረዳል። የመከላከያ ስፖርት ክለብ አዋቂ ወንዶች እና ሴቶች እግር ኳስ ቡድን እና ኮቺንግ አባላቱ 211 ሺህ ብር ድጋፍ አድርጓል። የስፖርት ክለቡ ለኮረና ቫይረስ መከላከልና መቆጣጠር እንዲውል በከተማ አስተዳደሩ ለተቋቋመ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ኮሚቴ ነበር ገንዘቡን ያስረከበው። «የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባቀረበው የድጋፍ ጥሪ መሠረት የኮቪድ -19 ለመግታት በሚደረገው ርብርብ የበኩላችንን ለመወጣት ነው» ሲሉ ነበር የስፖርት ክለቡ አባላት በስፖርቱን ማህበረሰብ ዘንድ ሰብአዊነትን ባስቀደመ መልኩ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት እየተደረገ ያለውን ተሳትፎ ያመላከቱት። የሀገር ዳር ድንበር ህልውና ከሆነው የስፖርቱ ክለብ በተመሳሳይ፤ በስፖርቱ የሰብአዊነት ልግስናው ተጠናክሮ የመቀጠሉን ሁኔታ የጠዋት ጎህ አትሌቶች የልማት መረዳጃ ተግባርም ይነሳል። በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ድል በማድረግ የሀገራችንን ሰንደቅ አላማ በማወለብለብ ስሟና ዝናዋን ከፍ ባደረጉት አትሌቶች የተቋቋመው ዕድሩ 200 ሺህ ብር ድጋፍ በማድረግ አጋርነታቸውን አስመስክረዋል፡፡\nየአትሌቶቹ የመረዳጃ ዕድር አባላት አስተባባሪዎች ኮማንደር አትሌት ጌጤ ዋሚ፣ አትሌት ተስፋዬ ቶላ፣ አሰልጣኝ ንጋቱ ወርቁ ፣ ዶክተር በዛብህ ወልዴ እና ወይዘሮ አይናዲስ ተስፋዬ ድጋፍ ለማድረግ የመሻታቸውን ሚስጥር በጋራ እንዲህ አጋርተዋል። «ዓለም ብሎም ሀገራችን በጭንቅ ተውጣለች። ህዝባችንም በሲቃ ተኮራምቷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለኮረና ቫይረስ መከላከል ጥሪ ማቅረቡን ተከትሎ እኛም የዜግነት ግዴታችን ለመወጣት የገንዘብ ድጋፍ ልናደርግ ወደናል። ኢትዮጵያዊነታችን የሚደምቀው በዚህ በጭለማና በጭንቅ ወቅት ስንረዳዳና ስንተጋገዝ በመንፈስና በፀሎት አብረን ከማህበረሰባቸን ጎን ስንቆም ነው» \nየኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ከሆኑ አትሌቶች ልግስና ወረድ በማለት እንደ መቋጫ አንድ ክስተት ስንጠቅስ፤ በኢትዮጵያ የወንዶችና የሴቶች ብሔራዊ ቡድኖች አሠልጣኞች እንዲሁም የስፖርቱ ሙያተኞች የተደረገ ልግስና የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ለመከላከል ከስፖርቱ ቤተሰብ በኩል እየተደረገ ያለውን ልግስና የሚያሳየው ሁነት ነው። እነዚህ አካላት ህዝብን ለመታደግ በሚደረገው ርብርብ በየአቅጣጫው 120 ሺህ ብር መሰብሰብ ችለዋል። ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ለኢንጂነር ታከለ ኡማ አስረክበዋል፡፡ ይህ ተግባር በአጠቃላይ ከስፖርት ማኅብረተሰቡ ዘንድ የተንፀባረቁትን ወገናዊ ድጋፎችንና ችግርን በአንድነት ለመመከት እየተደረገ ካለው ጥረት በመነሳት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ከፈጠረውና ካሳደረው አሉታዊ ተጽእኖ ጎን ለጎን የፈጠረው በጎ መልክ ስለመኖሩ የሚያስገነዝብ ይሆነናል። በስፖርት ማኅብረተሰቡ አካላዊ ርቀትን በጠበቀ መልኩ ማኅበራዊ ኃላፊነትን የመወጣት ጉዞ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እሙን ነው።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 9/2012 ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "e10eb64dc6d136aecb7fc5a3a35fdabe" }, { "passage": "ታላቁ የኦሎምፒክ መድረክ ከተለያዩ ሀገራት የሚመጡ በሺዎች የሚቆጠሩ ስፖርተኞች የሚያሳትፉበት የውድድርና የባህል መድረክ ነው። የኦሎምፒክ ጨዋታን «የዓለምን ሕዝብ በአንድ ጥላ ስር የሚያሰባስብ በአራት ዓመት አንዴ የሚመጣ ክስተት» ሲሉ በርካቶች ይገልጹታል። የኦሎምፒክ ጨዋታ ለመጀመሪያ ጊዜ እ.አ.አ በ1896 ግሪክ ላይ ነበር። የዓለምን ሕዝብ ቀልብ በመግዛት ረገድ አቻ ያልተገኘለት ተፀንሶ እስኪወለድ በርካታ ሂደቶች አሳልፏል። እ.አ.አ 1894 በፓሪስ የኦሎምፒክ እንቅስቃሴ ይካሄድ ነበር። በፈረንሳይ ፓሪስ በሚገኘው በሶርቦን ዩኒቨርሲቲ ፔር ደ ኩቨርተ በሚባል አንድ ፈረንሳዊ መምህር የተቋቋመ ነበር። የኦሎምፒክ እንቅስቃሴው ተቋማዊ በሆነ መልኩ ተደራጅቶ በዚሁ ዓመት አቴንስ ላይ ስብሰባ ሊደረግ ችሏል። በፈረንሳዊው ሰው የተፀነሰው ኦሎምፒክ በግሪክ ተወልዶ የመጀመሪያው የኦሎምፒክ ጨዋታ ለመካሄድ በቅቷል። በግሪክ አቴንስ በተካሄደው የመጀመሪያው ስፖርተኞች ብቻ ሳይሆኑ ሰዓሊዎችና መሐንዲሶች የተለያዩ ሥራዎቻቸውን አቅርበው ውድድር አድርገዋል። በዚህም ኦሎምፒክ የስፖርት ብቻ ሳይሆን የባህል መድረክም እንደሆነ በታሪክ ሰነዶች ሠፍሯል። ታላቁን የኦሎምፒክ መድረክ አሳታፊ አለመሆኑ\nብዙዎች በመድረኩ ወደ መሳተፍ የተሸጋገሩት\nዘግይተው ነው። በተለይ በአውሮፓውያን የቀኝ ግዛት ውስጥ በስፋት ወድቀው ለነበሩት የአፍሪካ\nሀገራት ራሳቸውን ችለው በመድረኩ ተሳታፊ ለመሆን ፈታኝ ጊዜያትን አሳልፈዋል።\nየምዕራባውያኑን በዘረኝነት ያበደ እሳቤን አሸንፎ በእኩልነት ለመታደም\nኢትዮጵያ ዘግይታም ቢሆነ መሳተፍ መቻሏ ፈተናውን ያቃለለ እንደነበር ይወሳል። እ.አ.አ 1956 ኢትዮጵያ በሜልበርኑ የኦሎምፒክ አደባባይ አሃዱ ብላ በመግባት የተሰመረውን ግንብ መናድ የቻለች ሲሆን፤ በመቀጠል በሮሙ ኦሎምፒክ ከተሳትፎ የተሻገረ ውጤት መመዝገቡ ለጥቁሮች ዝግ የነበረው ታላቁ መድረክ በሰፊው እንዲከፈት ያደረገ ነበር። በሮም ኦሎምፒክ በኢትዮጵያ የተመዘገቡት ድሎች የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪቃ የጥቁር ሕዝብ የኮራበትን ታሪክ መፃፍ አስችሏል። እ.አ.አ በ1896 በግሪክ አስተናጋጅነት በ11 አገራት ተሳትፎ የተጀመረው የኦሎምፒክ ውድድር አሳታፊ ሳይሆን በርካታ ዓመታትን የተጓዘ ነበር። የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተቀያያሪነትን መስመር ይዞ የተጓዘው ታላቁ የኦሎምፒክ መድረክ ሁሉም የዓለም ሀገራት የሚሳተፍበት ስፖርታዊ ውድድር ወደ መሆን ተሸጋግሯል።«የዓለምን ሕዝብ በአንድ ጥላ ስር የሚያሰባስብ በአራት ዓመት አንዴ የሚመጣ ክስተት» ሲሉ በርካቶች የሚገልጹት ኦሎምፒክን በየ ዓመቱ ሰኔ 23 ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ይከበራል። በብዙ ውጣ ውረዶች ታጅቦ ከዛሬ ደጃፍ የደረሰው ታላቁን የኦሎምፒክ ቀን ደግሞ በየ ዓመቱ ሰኔ 16 ቀን በኢትዮጵያ የሚከበር ሲሆን፤ በኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ አስተባባሪነት የዘንድሮው የኦሎምፒክ ቀን በዛሬው ዕለት በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል። የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የዘንድሮውን የዓለም ኦሊምፒክ ቀንን ሲያከብር ከፕሮግራሞቹ አንዱ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽ ያስከተለው ተፅዕኖ ከግምት ውስጥ በማስገባት ለአቅመ ደካሞች የማዕድ ማጋርት በማድረግ እንደሀነ አስታውቋል። በተጨማሪም በኦሊምፒክ ኮሚቴ ጊቢ ውስጥ ደግሞ የችግኝ መትከል ፕሮግራም እና በግል ስፖርታዊ እንቅስቃሴ እንዲሁም በሌሎች ዝግጅቶት ያከብራል። ከኮሮና ቫይረስ ጋር ተያይዞ በቤት ውስጥ እንዲሁም በእቤት አካባቢ ጥንቃቄ የተሞላበት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ቪዲዮ ውድድር አዘጋጅቶ ነበር። የዓለም የኦሊምፒክ ቀን በሚከበርበት በዛሬው ዕለት ለውድድሩ አሸናፊዎች የተሰናዳውን በዓለምአቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ (IOC) እውቅና ያለው የምስክር ወረቀት እንደሚበረከት ይጠበቃል።አዲስ ዘመን ሰኔ 16/2012ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "06ba9c56a2adc2b1690f830d55fee012" }, { "passage": "ኢትዮጵያ በዘመናዊ ስፖርቶች በዓለም መድረኮች መታየት ከጀመረች ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ ተቆጥሯል። በእነዚህ ዓመት አገሪቱን ሦስት የተለያዩ መንግሥታት መርተዋታል። አንድ መንግሥት የሚከተለው ርዮተ ዓለም በአንድ አገር ላይ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ተጽዕኖ የማሳደሩን ያህል በአንድ አገር ስፖርት ላይም የራሱ የሆነ አሉታዊና አዎንታዊ ተጽዕኖዎችን ማሳረፉ የግድ ነው። አንድ የፖለቲካ ስርዓት በስፖርቱ ላይ ብቻም ሳይሆን የስፖርቱ ዋና ተዋናይ የሆነው ግለሰብ ላይም ተመሳሳይ ተፅዕኖ እንደሚያሳርፍ እርግጥ ነው። የአንድ አገር የፖለቲካ ስርዓት በዲፕሎማሲ፤ በኢኮኖሚ፤ ልማትና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያለው ነባራዊ ሁኔታ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ስፖርቱንና ስፖርተኛውን መንካቱ አይቀሬ ነው። ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት ገደማ አገራችን የምትከተለው የፖለቲካ ስርዓት በአገሪቱ ስፖርት ላይ የተለያዩ አዎንታዊና አሉታዊ ጎኖችን ማሳደሩ አልቀረም። ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት የነበረው የፖለቲካ ስርዓት ለአገራችን ስፖርት ካበረከታቸው አዎንታዊ ጎኖች አንዱ ከዲፕሎማሲ እውነታዎች አኳያ ይቀኛል። አገራችን ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት ከሌሎች አገሮች ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በላቀ መልኩ ማሻሻሏ የሚካድ አይደለም። ይህም በዓለም አቀፍ የስፖርት መድረኮች በተለይም መል ካም ስም ባላት የአትሌቲክስ ስፖርት ኦሊምፒክንና የዓለም ቻምፒዮናን በመሳሰሉ ታላላቅ መድረኮች የነቃ ተሳትፎ እንዲኖራት የራሱን የሆነ አስተዋፅኦ አበርክቷል። ኢትዮጵያ እኤአ ከ1956 ከሜልቦርን ኦሊምፒክ ጀምሮ በኦሊምፒክ መድረኮች ተሳታፊ መሆን ችላለች። ከእዚህ ጊዜ አንስቶ አስራ ሰባት ያህል ኦሊምፒኮች ቢካሄዱም ኢትዮጵያ በሁለቱ ተካፋይ መሆን አልቻለችም ነበር። \nእኤአ በ1984 አሜሪካ ሎሳንጀለስ ባስተናገደችው የኦሊምፒክ ጨዋታ ኢትዮጵያ በወቅቱ የሶሻሊዝም ርዮተ ዓለም ተከታይ ከመሆኗ ጋር ተያይዞ በእዚህ ታላቅ መድረክ መካፈል አልቻለችም ነበር። ከአራት ዓመት በኋላም 1988 ላይ የአፓርታይድ ስርዓትን በመቃወም በሲዎል ኦሊምፒክ ላይ አልተገኘችም። ኦሊምፒክን በመሳሰሉ ታላላቅ የስፖርት መድረኮች በፖለቲካ ርዮተ ዓለም ልዩነት የተነሳ መካፈል አለመቻል አንድን አገር ከሜዳሊያ በዘለለ በርካታ ነገሮች እንደሚያሳጣ አያከራክርም። ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ በሁሉም የኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮናዎች ላይ ቀርታ አታውቅም። በእነዚህ ታላላቅ የስፖርት መድረኮች ሜዳሊያ ከመሰብሰብ ባሻገር መድረኩን ተጠቅማ ገፅታዋን ለመገንባትና ራሷን ለማስተዋወቅ ጠቅሟታልም። በእነዚህ መድረኮች የዘወትር ተሳታፊ መሆኗም የአገሪቱን ስፖርት እንዲነቃቃና ስፖርተኛው ተጠቃሚ እንዲሆን አስችሏል። \nአንድ ስፖርተኛ ራሱን በኦሊምፒክ መድረክ በማሳየት ዓለም አቀፍ ተጠቃሚነትን እንዲያገኝ ከሌሎች አገራት ጋር ያለን መልካም የሆነ የዲፕሎማሲ ግንኙነት እዚህ ጋር ቁልፍ ሚና እንዳለው መገንዘብ ይቻላል። ስፖርተኞቻችን የግል ውድድራቸውን በሌሎች አገሮች ለማድረግ ወደ አንድ አገር በቀላሉ ለመግባት መልካም የዲፕሎማሲ ግንኙነት የሚኖረው አስተዋፅኦ ግልፅ ነው። ይህም ስፖርተኞች በተለይም አትሌቶቻችን በተለያዩ ዓለማት ተዟዙረው በስፖርቱ ያላቸውን ተሰጥኦ ተጠቅመው ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች ወገኖችና ለአገር ሲተርፉ እንድንመለከት አድርጓል። እዚህ ላይ የአገራችን አቪዬሽን ዘርፉ መዘመንና በበርካታ አገሮች ተደራሽ መሆን ለአትሌቶቻችን እንደ ልብ የፈለጉት አገር በረው የትራንስፖርት ጉዳይ ሳያሳስባቸው ጊዜና ገንዘባቸው ሳይባክን ውድድሮች ላይ እንዲገኙ ማስቻሉ መንግሥት በትራንስፖርት ልማቱ ያከናወነውን ተግባር ዋጋ እንድንሰጠው እንገደዳለን። \nስፖርት በዘመናችን ከፍተኛ የገቢ ምንጭ በሆነበት በእዚህ ወቅት አትሌቶቻችን በሌሎች አገሮች ላባቸውን አፍሰው ያመጡትን ገንዘብ አገራቸው ላይ ሠርተው እንዲለወጡበት መንግሥት ቅድሚያ ሰጥቷቸው ሁኔታዎችን በማመቻቸት ወደ ኢንቨስትመንቱ እንዲገቡ አድርጓል። በእዚህም በርካታ አትሌቶቻችን በሆቴልና ሪዞርት እንዲሁም በሌሎች የኢንቨስትመንት ዘርፎች ግንባር ቀደም ተዋናይ ሆነው እናገኛቸዋለን። ይህም ሁኔታ ስፖርተኞቻችን ወደ አደጉት አገራት ለውድድር ወጥተው ከመቅረት ይልቅ ያገኙትን ይዘው ተመልሰው ከራሳቸው አልፈው ለበርካታ ዜጎት እንጀራ ሲከፍቱ እንድንመለከት አድርጓል። \nስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረግ የአንድ ህብረተሰብን አካላዊ እና ስነ ልቦናዊ ጤንነትን በመጠበቅ ረገድ ምርታማነትን የሚያጎለብት፥ ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ቁልፍ ሚና ያለው የዜጎች መሰረታዊ መብት እየሆነ መጥቷል። ይህን ልብ ያለው የ1990 ዓ.ም የተቀረፀው የኢትዮጵያ ብሔራዊ የስፖርት ፖሊሲ በየደረጃው መላውን ህብረተሰብ በስፖርት በማሳተፍ ተተኪ ስፖርተኞችን ማፍራት ቀዳሚ ዓላማው አድርጎታል። ለዚህም መላው ህብረተሰብ በሚኖርበት፥ በሚሠራበት እና በሚማርበት አካባቢ በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል በየደረጃው ምቹ ሁኔታዎችን የመፍጠር ግልፅ አቅጣጫ አስቀምጧል። የዚህን ፖሊሲ አቅጣጫ ስኬታማ በሆነ መልኩ ተፈፃሚ ለማድረግ የመላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ፅንሰ ሃሳብ ለመጀመሪያ ጊዜ በ1996 ዓ.ም በወቅቱ በነበረው የኢፌዴሪ ስፖርት፤ ባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር ነበር የተጠነሰሰው። \nየኦሊምፒክና የመላ አፍሪካ ጨዋታዎችን መርህ መነሻ በማድረግ ህብረተሰቡን በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በስፋት በማሳተፍ እና ተጠቃሚነቱን በማጎልበት የበርካታ ባህልና ትውፊቶች ባለቤት የሆኑ ብሔሮችና ብሔረሰቦች በአንድ መድረክ ተገናኝተው የባህል እና ልምድ ልውውጥ እንዲያደርጉ ታስቦ ፖሊሲው እንደተቀረፀ የመጀመሪያው የጥናት ሰነድ ላይ ተቀምጧል። ይህም አገራችን በምትከተለው የፌዴራሊዝም ስርዓት ህዝቦች የእርስ በእርስ ግንኙነታቸውን በማጠናከር በጋራ መግባባት ላይ የተመሰረተ መተሳሰብ እና መቀራረብ አዲሲቷን ኢትዮጵያ ለመገንባት ዘርፈ ብዙ ጥቅም እንዳለው ታምኖበታል። በዚህም የአገራችን ስፖርት ዜጎችን ተጠቃሚ ከማድረግ አኳያ ተስፋ ሰጪ ምልክቶችን ማየት ተችሏል። ዘመናዊና ግዙፍ ስቴድየሞች በየክልሉ መገንባታቸው፤ አገር አቀፍ የታዳጊ ወጣቶች የስፖርት አካዳሚና በተለያዩ ስፖርቶች የወጣት ፕሮጀክቶች መጀመራቸው የአገራችን ስፖርት ባለፉት ሃያ ስድስት ዓመታት የተጓዘባቸው መንገዶች ናቸው። \nየመላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ለአገሪቱ ትልልቅ መሠረተ ልማቶችን አስገ ኝቷል፡፡ ለውድድሩ ሲባልም ትልልቅ ስታዲየሞች በክልሎች ተገንብተዋል፡፡ በመገንባት ላይም የሚገኙ በርካታ ናቸው፡፡ በባህር ዳር፣ ሐዋሳና መቐለ የተገነቡት ዘመናዊ ስታዲየሞች ከመላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች አልፈው ዓለም አቀፍ ውድድሮችን የሚያስተናግዱ ሆነዋል፡፡ አልፎ ተርፎም ኢትዮጵያ የአፍሪካን ሁለተኛውን ትልቅ የእግር ኳስ ዋንጫ የ2020 አፍሪካን ኔሽን ቻምፒዮን ሺፕ(ቻን) አዘጋጅነት ዕድል እንድታገኝ እነዚህ ስቴድየሞች ካፍን ማሳመን የቻሉበት አጋጣሚ ነበር(ባይሳካም)። ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በየሁለት ዓመቱ የሚካሄዱትን መላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ላይ እያሳዩ ያለው ፉክክር ወደ መጋጋል ደረጃ ለመምጣቱ አንዱ ማሳያ፣ ውድድሮችን ለማዘጋጀትና መሠረተ ልማቶችን አሟልቶ ለመገኘት የሚያደርጉት ሽር ጉድ ለዚህ ተጠቃሽ ነው፡፡ በእነዚህ ስቴድየሞች ግንባታ ሂደትም በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች የሥራ ዕድል ከመፈጠሩ ባሻገር በግንታው ዘርፍ በቢሊየን የሚቆጠር ገንዘብ ሊንቀሳቀስ ችሏል። በዚህም የአገራችን ተቋራጮችን አቅም ከማሳደጉ በተጨማሪ በዘርፉ ትልቅ የእውቀት ሽግግር ሊደረግ ችሏል። ይሁን እንጂ በእነዚህ ስቴድየሞች ግንባታ በብዙ መልኩ የሚነሱ እንከኖች የሉም ማለት አይደለም፡፡ መላ ኢትዮጵያ ጨዋታም ቢሆን ባለፉት ጥቂት ዓመታት የታለመለትን ዓላማ ስቶ ወዳልተፈለገ እኩይ ተግባር መቀየሩና የፖለቲካ መጠቀሚያ መሆኑ የሚካድ አይደለም፡፡ \nበእነዚህ ዓመታት በአገራችን ስፖርት ከታዩ አንኳር የሆኑ አሉታዊ ጎኖች ዋነኛው ከአትሌቲክስ ስፖርት ውጪ ሌሎቹ ስፖርቶች መዳከማቸውና እድገት አለማሳየታቸው ይጠቀሳል። ለእዚህም በርካታ ምክኒያቶች ይቀመጣሉ። ቀደም ሲል አንድ ክለብ ሲቋቋም ያደገ ወይንም ተከታይ ያለው ስፖርት ብቻ ይዞ መቋቋም አይችልም። ይህ ማለት አንድ እግር ኳስ ክለብ ለማቋቋም ሌሎች ከአምስት ያላነሱ ስፖርቶችን ማቀፍ የሚያስገድድ ሁኔታ ነበር። ይህም አንድ ስፖርት ብቻ ተነጥሎ እንዳያድግና ሌሎች ያላደጉ ስፖርቶች ተያይዘው እንዲያድጉ የሚያስችል ነበር። አሁን ላይ ይህ ዓይነቱ አካሄድ በመቅረቱ በርካታ ክለቦች የፈለጉትን ስፖርት ብቻ ይዘው በመጓዛቸው በርካታ ስፖርቶች ሲወድቁ እንመለከታለን። ቀደም ሲል ኢትዮጵያ ከአትሌቲክስና እግር ኳስ በተጨማሪ ቮሊቦል፤ ቅርጫት ኳስ፤ እጅ ኳስና ሌሎች ስፖርቶች ከሌሎች አገሮች ጋር ተፎካካሪ ነበረች። አሁን ላይ ይህ ገፅታ ተቀይሮ ከእግር ኳስና አትሌቲክስ ውጪ ባሉት ስፖርቶች እንኳን ወደ ውጭ አገር ሄደን ጠንካራ ተፎካካሪ ልንሆን በአገር ውስጥም ጠንካራ እንቅስቃሴ ሲደረግባቸው ለማየት ተቸግረናል። \nበስፖርት መሰረተ ልማቶች ትላልቅ ፕሮጀክቶች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ተግባራዊ እየሆኑ ቢመጡም በአገራችን ስፖርት መሰረት የሆኑ የተለያዩ ማዘውተሪያ ስፍራዎች ሕንፃና ቤት ተሠርቶባቸው እናገኛለን። ይህም በምንታወቅባቸው በተለይም በእግር ኳስ ከተለያዩ አካባቢዎች የሚወጡ ተጫዋቾችን እንድናጣ ማድረጉ በርካታ የስፖርት ቤተሰቦች የሚስማሙበት ነው። \nበሌላ በኩል የሚታየው አሉታዊ ጎን ከአገሪቱ የኢኮኖሚ አቅም ጋር ተያይዞ የሚነሳ ቢሆንም ወደ ፊት ትኩረት ተደርጎ ሊሠራበት የሚገባ አብይ ጉዳይ ነው። ለበርካታ ስፖርቶች መዳከም ዋነኛ ምክኒያት የፌዴሬሽኖች የገንዘብ አቅም ማነስ ነው። መንግሥት ለስፖርት ኮሚሽን ከሚበጅተው ገንዘብ ተመፅዋች ሆነው እንደልብ መራመድ የከበዳቸው አገር አቀፍ ፌዴሬሽኖች ጥቂት አይደሉም። እነዚህ ፌዴሬሽኖች ውድድሮችን ለማካሄድ ስፖርቱን ለማሳደግ አንድና አንድ ችግራቸው የገንዘብ አቅም ነው። እነዚህ ፌዴሬሽኖች የመንግሥት እጅ ከመጠበቅ ይልቅ በራሳቸው የገንዘብ አቅማቸውን ለማጠናከር መሥራት እንዳለባቸው ብዙ ጊዜ ምላሽ ይሰጣል። ይሁን እንጂ እነዚህ ፌዴሬሽኖች ራሳቸውን በገንዘብ የሚያጠናክሩበት አቅም እስኪፈጥሩ ድረስ መንግሥት አሁን ከሚበጅትላቸው ገንዘብ በዘለለ ወጥ የሆነ አደረጃጀት ፈጥሮላቸው ዘላቂ የሆነ መስመር በመዘርጋት በኩል ክፍተቶች አሉ። መንግሥት ለፌዴሬሽኖች ዓሣ ከመስጠት ይልቅ ዓሣ የሚያጠምዱበትን ዘዴ ሊያስተምራቸውና መንገዱን ሊያሳያቸው ይገባል። እስከዚያው ድረስም አሁን የተሠሩት መሰረተ ልማቶች ከጋሪው ፈረሱ የቀደመ እንዳይሆኑ ዓመታዊ በጀታቸው ቢያንስ በርካታ ውድድሮችን በዓመት ውስጥ ማስተናገድ የሚያስችላቸውና በኋላ መሰረተ ልማቱ ተሟልቶ ስፖርቱ ኋላ እንዳይቀር በአንድ ላይ መጓዝ የሚያስችል መላ አልተፈጠረም፡፡ የአገራችን ስፖርት ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት ገደማ በእንዲህ ዓይነት የቁልቁለት ጉዞ በመራመድ ዛሬ ላይ ደርሷል። ካለፈው መጋቢት 2010 ወዲህ አገሪቱ በአዲስ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ባሆንም የለውጥ መንገድ ላይ መሆኗ አይካድም፡፡ ይህ የለውጥ ማዕበል በፖለቲካ ውጥረት ውስጥ ገብቶ አገር በማረጋጋት የተጠመደ ከመሆኑም ጋር ተያይዞ ሊሆን ይችላል የስፖርቱን ዘርፍ ትኩረት ሰጥቶ ሲመለከተው አይስተዋልም፡፡ ሁሉም ነገር ወደ መደበኛው እንቅስቃሴ ሲመለስና የፖለቲካ ውጥረቱ ሲረግብ ግን የስፖርቱን የቁልቁለት ጉዞ ሽቅብ እንዲጓዝ የማድረግ ትልቅ የቤት ሥራ እንደሚጠብቀው ከወዲሁ ማስታወስ ግድ ነው፡፡አዲስ ዘመን ግንቦት 16/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "14afffacb7a5601cc006346aab16885d" } ]
96a8e8850782ebabc23f90d7451d46bd
a9d8021a3c08aa13dd1f9158c959625e
የአትሌቲክሱ ዓለም ከወራት በኋላ የሚጠብቀው የዓለም ክብረወሰን
የዓለም ታላላቅ ስፖርት መድረኮች በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ወረርሽኝ ምክንያት ለበርካታ ወራት ከቆሙበት ለመቀጠል ጥረት እያደረጉ እንደሚገኙ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ለመመልከት ተችሏል። የእግር ኳሱ ዓለም ታላላቅ ሊጎች በዝግ ስቴድየምም ቢሆን ጨዋታዎችን እያስቀጠሉ ካንቀላፉበት እየነቁ ይገኛሉ። በዚሁ ወረርሽኝ ሳቢያ ክፉኛ የተጎዳው የዓለም አትሌቲክስ እንቅስቃሴም ከጥቂት ወራት በኋላ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለመመለስ ከወዲሁ እንቅስቃሴ መጀመሩ ለዓለማችን አትሌቶች መልካም ዜና ሆኗል። በተለይም የዓለማችን ኮከብ አትሌቶች በጉጉት የሚጠብቁት ዓመታዊው የዳይመንድ ሊግ ውድድር እንደሚመለስ መገለፁን ተከትሎ ለወራት ከውድድር ርቀው ለተቀመጡት አትሌቶች የምሥራች መሆኑ አይቀርም። በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የተነሳ የዓለም አትሌቲክስ ዓመታዊ መርሃግብሮች በተያዘላቸው ጊዜ ሳይካሄዱ በመቅረታቸው ተዘበራርቀዋል። የዓለም አትሌቲክስ ይህንን ለመካስም በጊዜያዊነትም ቢሆን እንደ ዳይመንድ ሊግ ያሉ ውድድሮች መርሃግብርን ለመከለስ ተገዷል። በብራሰልስ የሚካሄደውም ውድድር ከተከለሱት መርሃግብሮች መካከል የሚጠቀስ ነው። ዳይመንድ ሊጉ ወደ ውድድር ሲመለስ በመጪው የፈረንጆች መስከረም ወር መጀመሪያ እንደሚካሄድ የሚጠበቀው የብራሰልስ ዳይመንድ ሊግ ከወዲሁ ትኩረት አግኝቷል። እንግሊዛዊው የኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮናዎች ጥምር የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤቱ አትሌት ሞሐመድ ፋራህ ከ2017 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ መም ውድድሮች ተመልሶ በብራሰልስ ዳይመንድ ሊግ ተፎካካሪ እንደሚሆን መናገሩን ተከትሎ ውድድሩ ትኩረት ማግኘት ችሏል። የሰላሳ ሰባት ዓመቱ ፋራህ ወደ ውድድር ከመመለሱ በተጨማሪ በ21 ነጥብ 285 ኪሎ ሜትር ፉክክሩን ከአንድ ሰዓት በታች ለማጠናቀቅና አዲስ የዓለም ክብረወሰን ለማሻሻል መዘጋጀቱን ተከትሎ የብራሰልስ ዳይመንድ ሊግ ከወዲሁ በጉጉት እንዲጠበቅ አድርጓል። የርቀቱ ክብረወሰን በጀግናው አትሌት ሃይሌ ገብረሥላሴ የተያዘ ሲሆን ከአስራ ሦስት ዓመታት በፊት እ.ኤ.አ 2007 ኦስትራቫ ላይ ማስመዝገቡ ይታወሳል። በብራሰልሱ ውድድር የአውሮፓ የአስር ሺህ ሜትር የብር ሜዳሊያ አሸናፊው አትሌት በሽር አብዲ ከፋራህ ጋር እንደሚፎካከር የተገለፀ ሲሆን ኢትዮጵያውያንና ኬንያውያን የርቀቱ ፈርጦችም በቅርቡ ውድድሩን እንደሚቀላቀሉ ይጠበቃል። ‹‹ከልምምድ አጋሬ በሽር አብዲ ጋር ውድድሩን ከአንድ ሰዓት በታች በማጠናቀቅ የዓለም ክብረወሰን ለማስመዝገብ እየተዘጋጀን ነው፣ ይህ ለእኔ ትልቅ አጋጣሚ ነው፣ በብራሰልስ ከዚህ ቀደም ባደረኳቸው ውድድሮች ጥሩ ትዝታዎች አሉኝ፣ ብራሰልስ ላይ ፈታኝ ሰዓት መሮጥ ይቻላል፣ ሁሉም ነገር ቀላል ነው›› በማለት ፋራህ ለመገናኛ ብዙሃን አስተያየቱን ሰጥቷል። በተመሳሳይ በሴቶች መካከል በሚካሄደው ውድድር ግን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ተፎካካሪ ከመሆን ባለፈ አዲስ የዓለም ክብረወሰን ለማስመዝገብ መዘጋጀታቸውን የውድድሩ አዘጋጆች ገልፀዋል። በዚህም አትሌት አባብል የሻነህ እና ብርሃኔ ዲባባ ተጠባቂ ሆነዋል። 18 ነጥብ 517 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው ውድድር የዓለም ክብረወሰን የተመዘገበበት ጊዜ ከአስራ ሁለት ዓመታት በፊት እ.ኤ.አ 2008 ላይ ሲሆን ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ድሬ ቱኔ የክብረወሰኑ ባለቤት መሆኗ አይዘነጋም። በዚህ የውድድር ዓመት የዓለም ግማሽ ማራቶን ክብረወሰንን በ1፡04፡31 ሰዓት መስበር የቻለችው አባብል የሻነህ ለአስራ ሁለት ዓመታት ያልተደፈረውን የድሬ ቱኔን ክብረወሰን እንደምታሻሽል ግምት የተሰጣት ሲሆን በማራቶን 2፡18፡35 የሆነ የራሷ ምርጥ ሰዓት ያላት ብርሃኔ ዲባባም ብራሰልስ ላይ ለክብረወሰን ተጠባቂ ሆናለች።አዲስ ዘመን ሰኔ 20/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=35203
[ { "passage": "እአአ\nበ1980 ሞስኮ ባዘጋጀችው ኦሊምፒክ፤ የ5ሺ ሜትር አሸናፊ ኢትዮጵያዊው አትሌት ምሩጽ ይፍጠር መሆኑ ለዓለም አዲስ ታሪክ ነበር። ምክንያቱ ደግሞ በዘመናዊው ኦሊምፒክ ከዚያ ቀደም በተካሄዱት 14 መድረኮች አንድም አፍሪካዊ የወርቅ ሜዳሊያ ሳያጠልቅ መቆየቱ ነው። ርቀቱ በበላይነት የተያዘውም በአውሮፓውያን አትሌቶች ሲሆን፤ በተለይ ፊንላንዳውያን በርቀቱ ነግሰው እንደነበር ታሪክ ያወሳል። በ10ሺ ሜትርም በተመሳሳይ የበላይነቱ በአውሮፓውያን አትሌቶች (ለ11 ኦሊምፒኮች) የተያዘ ነበር። እአአ በ1968 ኬንያዊው ናፍታሊ ተሙ እና ኢትዮጵያዊው ማሞ ወልዴ ተከታትለው የወርቅና ብር ሜዳሊያውን እስኪወስዱት ድረስ። የምስራቅ አፍሪካውያኑ አትሌቶች ድል አድራጊነቱን ከተቀላቀሉ በኋላም የደረጃ ሰንጠረዡን ቀዳሚ ስፍራ ሊቆጣጠሩት ችለዋል። ከኦሊምፒክ ባሻገር ባሉ ውድድሮች ላይ የሚታየው ልምድም ከዚህ የተለየ የሚባል አይደለም። ኢትዮጵያ\nለዘመናት ስሟን ያስጠራችበት ይህ የአትሌቲክስ ውድድር ግን ለመጥፋት ጥቂት ቀርቶታል። በርካታ ጀግና አትሌቶች ድል የነሱበት የ10ሺ ሜትር ርቀት በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና እንዲሁም በኦሊምፒክ ብቻ ከተወሰነ ሰነባብቷል። በዳይመንድ ሊግ ይታይ የነበረው የ5ሺ ሜትር ርቀትም ተመሳሳይ ዕጣ እንደሚደርሰው ዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር በቅርቡ አስታውቋል። ከጥቂት\nአስርት ዓመታት ወዲህ ሙሉ ለሙሉ በምዕራባውያኑ የበላይነት ተይዞ የቆየው ርቀት በምስራቅ አፍሪካውያኑ አትሌቶች ተወስዷል። ሀገራቱ በዚህ ምክንያት ሙሉ ትኩረታቸውን ወደ አጭርና መካከለኛ ርቀቶች እንዲሁም የሜዳ ላይ ተግባራት እንዲያደርጉም ተገደዋል። ስለዚህም በአፍሪካውያን የተወሰደ ክብራቸውን ለማስመለስ ሀገራትን ማዳከም የመጀመሪያው እርምጃቸው መሆኑ ጸሃይ የሞቀው ሃቅ ነው። ውሳኔውን ተከትሎም በርቀቱ በተለይ ውጤታማ የሆኑት ጎረቤታሞቹ ኬንያ እና ኢትዮጵያ ተቃውሟቸውን በማሰማት ላይ ይገኛሉ። ምንም እንኳን በኬንያ በኩል የመወላወል ነገር እየታየ ቢሆንም፤ ኢትዮጵያ ግን በፌዴሬሽኗ፣ በኦሊምፒክ ኮሚቴዋ እንዲሁም በዝነኛ አትሌቶቿ ትግል ማድረጓን ተያይዛዋለች። መታገሉ በህዝቡ ዘንድ እንደ ባህል የሚታየውን ውድድር ወደ ቀድሞ ክብሩ እንዲመለስ ለማድረግ መልካም ሆኖ ሳለ፤ ሌላ የቤት ስራ የሚሰጥ መሆኑ ግን መዘንጋት የለበትም። ይህም ኢትዮጵያን ለመሳሰሉ ሀገራት ይታወቁበት ከነበረው ርቀት ሌላ አማራጭ እንዲመለከቱ የግድ የሚል መሆኑን ነው። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም በረጅም ርቀት አትሌቲክስ የተጣለውን ውሳኔ ከማስቀልበስ እንቅስቃሴው ባሻገር በሌሎች ርቀቶች ላይ የሚገኙአትሌቶችን መመልከት ይኖርበታል። በተለይ ለአጭር ርቀት እንዲሁም ለሜዳ ላይ ተግባራት ምቹ የሆኑ የአካል ብቃት እንዲሁም የአኗኗር ሁኔታ ላይ በሚገኙ አትሌቶች ላይ ትኩረቱን መጨመር እንደሚገባው በትክክልም የሚጠቁም ነው። በውሳኔው\nመሰረት በረጅም ርቀት የሚካፈሉ አትሌቶች ሁለትና አራት ዓመታትን ጠብቀው መወዳደራቸው የግድ ነው። የፌዴሬሽኑ ስጋት ደግሞ አትሌቶች ዓመታትን ከመጠበቅ ይልቅ ፊታቸውን ወደ ጎዳና ሩጫዎች መመለሳቸው ይጎዳቸዋል የሚል ነው። ይህ ስጋት ትክክለኛ ቢሆንም ግን ከማራቶን ባሻገር በመካከለኛ፣ በአጭር፣ በዝላይ፣ በውርወራ እንዲሁም በእርምጃ ወደ ሚካሄዱ ውድድሮች ፊታቸውን እንዲያዞሩ ማድረግ ተገቢ ነው። ኢትዮጵያ ከኬንያ ስትነጻጸር በታላቁ የኦሊምፒክ መድረክ ሜዳሊያ ያስመዘገበችው፤ በ1ሺ 500 ሜትር፣ በ3ሺ ሜትር መሰናክል፣ በ5ሺ ሜትር እንዲሁም በ10ሺ ሜትር ውድድሮች ብቻ ነው። በአንጻሩ ኬንያ ከእነዚህ ርቀቶች ባሻገር በ400 ሜትር፣ በ400 መሰናክል፣ በ400 ሜትር፣ 800 ሜትር እንዲሁም በጦር ውርወራ ሜዳሊያ ማግኘት ችላለች። ይህም ኢትዮጵያ ምን ያህል በአንድ አካባቢ ተወስና እንደቀረች የሚያሳይ ሲሆን፤ ኬንያ በበኩሏ ተሳትፎዋን በማብዛቷ ውጤታማ ለመሆኗ ማሳያ ይሆናል። ኢትዮጵያም ሁሌም ከምትነሳባቸው አራትና አምስት ርቀቶች ያላለፈ ዝናዋን በድጋሚ መገንባት የሚቻልበት መንገድ መኖሩን መዘንጋት አያስፈልግም። ለፌዴሬሽኑ እንዲሁም ለኦሊምፒክ ኮሚቴም አካባቢያቸውን እንዲቃኙ በግልጽ የተቀመጠ ማንቂያ ይሆናል። እንደ ነባራዊው ሁኔታ ከሆነ፤ በኢትዮጵያ ባሉ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ከወረዳ ጀምሮ አያሌ የታዳጊ ወጣት ፕሮጀክቶች ይገኛሉ። በእነዚህ ፕሮጀክቶችም ከእግር ኳስ ስፖርት በሚስተካከል መልኩ የአትሌቲክስ ስፖርት ስልጠና ይሰጣል። ከዚህ ባሻገር በሀገር አቀፍ ደረጃ አራት የስልጠና ማዕከላት እንዲሁም ሁለት አካዳሚዎች ይገኛሉ። በእነዚህም ውስጥ አትሌቲክስ በከፍተኛ ትኩረት ስልጠና የሚሰጥበት ዘርፍ ነው። በተለያዩ አካባቢዎችም በራሳቸው ጥረት እንዲሁም በግል አሰልጣኞች አትሌት ለመሆን የሚታትሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ታዳጊና ወጣቶች ይገኛሉ። ከእነዚህ\nሰልጣኞች የሚልቁት ደግሞ ትኩረታቸውን በረጅም ርቀት አትሌቲክስ ላይ ያደረጉ ናቸው። በሌላ በኩል ኢትዮጵያ በማትታወቅበት የሜዳ ላይ ተግባራት ያለው ሁኔታ፤ በፍላጎት፣ በግብዓት እንዲሁም በቁሳቁስ እጥረት እዚህ ግባ የሚባል አይደለም። ነገር ግን በተለያዩ ጊዜያት ፌዴሬሽኑ ባደረገው ምልከታም ይሁን ባለሙያዎች እንደሚገልጹት በተለይ በአጭር ርቀት፣ ውርወራ እና ዝላይ ውጤታማ መሆን የሚችሉ ታዳጊዎች የሚፈሩባቸው አካባቢዎች ይገኛሉ። በመሆኑም ማሰልጠኛ ማዕከላት ከእነዚህ አካባቢዎች ወጣቶችን በመመልመል፣ ፌዴሬሽኑም አስፈላጊውን ግብዓት በማሟላት እንዲሁም ተገቢውን ስልጠና እንዲሰጥ በማድረግ ውጤታማነትን መመለስ ይችላል። የኢትዮጵያ\nአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከዓመት በፊት በመላ ሀገሪቷ በዚህ ጉዳይ ላይ ትኩረቱን ያደረገ ምልከታ በባለሙያዎቹ ማድረጉ የሚታወስ ነው። ስልጠናው የሚሰጥባቸው ቦታዎች ከባህር ጠለል በላይ የሚገኙበትን በመመልከት እንዲሁም የአኗኗር ሁኔታቸውን በማጥናት ለየትኛው የስፖርት ዓይነት ምቹ ነው የሚለውንም ለይተዋል። በወቅቱ ፌዴሬሽኑ ባስቀመጠው ስታንዳርድ መሰረት አዳዲስ አትሌቶችን የመመልመል ስራዎች መሰራታቸውን ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ አስታውቀው ነበር። በአቅርቦት ላይ የሚታየውን ችግር ለመፍታትም ፌዴሬሽኑ በአነስተኛ ዋጋ ከሚያቀርቡ ከሀገር ውስጥ አምራች ድርጅቶች ጋር በመነጋገር ላይ መሆኑ ተጠቁሞ ነበር። በተለይ እንደየ ሰልጣኙ እድሜ፣ ለውድድርና ለስልጠና በምን ያህል መስፈርት መዘጋጀት ይገባል እንዲሁም ለየክልሎቹ ምን ያህል አቅርቦት ያስፈልጋል በሚለው ላይም ፌዴሬሽኑ ዝግጅት ተደርጓል። በሀገሪቷ\nያሉት አሰልጣኞች ቁጥር ከስልጠናውና ከሰልጣኞቹ ጋር የሚመጣጠን አለመሆኑም ተረጋግጧል። በመፍትሄነትም አሰልጣኞችን ከውጭ ሀገራት ለማስመጣት መታቀዱ በወቅቱ ተገልጾ ነበር። ልምድ ያላቸውን አሰልጣኞች ለማስመጣት በሙከራ መሆኑንና ለኢትዮጵያውያን አሰልጣኞች ልምድና ተሞክሮዎችን እስደሚሰጡም ይጠበቅ ነበር። ይህንን\nስራ ቀድሞ የመጀመሩ አስፈላጊነት አያጠያይቅም፤ ነገር ግን ቀጣይነቱ ላይ ምን እየተሰራ ይገኛል? የሚለው ዋነኛው ጉዳይ ነው። በፌዴሬሽኑ በኩል በዓለም ላይ እየታየ ያለውን ሁነት ተከትሎ መፍትሄ ማበጀት እንዲሁም የጀመሩትን ስራ ከዳር ማድረስ የግድ መሆኑም መዘንጋት የለበትም። ከጥያቄው ባሻገር የተሰጠውን የቤት ስራ ለማከናወን በሙሉ ዝግጁነት መነሳትም አስፈላጊ ነው።", "passage_id": "127551a136af260b2579d72e99514d08" }, { "passage": "በሳምንቱ\nማብቂያ በተለያዩ አገራት በተካሄዱ ውድድሮች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ባለድል ሲሆኑ አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ለሁለት አስርት ዓመታት በሌሎች አትሌቶች ተይዞ የቆየውን ክብረ ወሰን የግሉ ማድረግ ችሎበታል። ዮሚፍ በሳምንቱ መጨረሻ በአሜሪካ ቦስተን በተደረገ የአንድ ማይል የዓለም የቤት ውስጥ ውድድር አሸናፊ ከመሆኑም በላይ ለሁለት አስርት ዓመታት ተይዞ የቆየውን ክብረ ወሰንም የግሉ ማድረግ ችሏል። አትሌቱ ውድድሩን ለማጠናቀቅ የወሰደበት ሰዓት 3ደቂቃ 47 ሰከንድ 1ማይክሮ ሰከንድ ሆኖ ተመዝግቧል። የውድድሩ\nክብረ ወሰን እኤአ1997 በሞሮኮው አትሌትሂሻል ኤልግሩዥ 3:48.45 ሆኖ የተመዘገበ ሲሆን፤ ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ የ21 ዓመቱ ዮሚፍ ይህን ክብረ ወሰን አንድ ደቂቃ ከአርባ አራት ሰከንድ በማሻሻል አዲስ ታሪክ መፃፍ ችሏል። በአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር ሶስተኛው ፈጣን ሰዓት ባለቤት የሆነው ዮሚፍ፤ ከዚህ ቀደም በበርሚንግሃም በተካሄደውና ሳሙኤል ተፈራ ቀዳሚ ሆኖ ባጠናቀቀበት ውድድር ላይ ክብረ ወሰን ለማሻሻል ተቃርቦ እንደነበር ይታወሳል። ከ19 ቀናተ በፊት በአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር ላይ አትሌት ሳሙኤል ተፈራ 3 ደቂቃ፣ ከ31 ሰከንድ፣ ከ04 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት የዓለም የፈጣኑ ሰዓት ባለቤት መሆን መቻሉ ይታወሳል። አትሌቱ ይህ ታሪክ መስራት የቻለው እኤአ በ1997 በሞሮኳዊው አትሌት ሂሻል ኤልግሩዥ ተይዞ የነበረውን ክብረወሰን በ23 ሰከንድ በማሻሻል ነው። ከፈረንጆቹ\n2019 ወዲህ ኢትዮጵያውያኑ የሂሻል ኤልግሩዥን ክብረ ወሰን ለሁለተኛ ጊዜ መስበራቸውና በተለያዩ አገራት በሚካሄዱ ውድድር በአስደናቂ ብቃት አሸናፊ እየሆኑ መታየታቸው የብዙዎችን አድናቆት እያጎረፈላቸው ይገኛል። ከዚህ ውድድር በተጓዳኝ በሳምንቱ መጨረሻ በተካሄደውና በዓለም ዓቀፉ አትሌቲክስ ማህበር የወርቅ ደረጃ በሚሰጠው የቶኪዮ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታ ድል ቀንቷቸዋል። በሴቶች መካካል የተካሄደውን ውድድር አትሌት ሩታ አጋ አሻንፋለች። 2:20.40 ደግሞ ውድድሩን ለማጠናቀቅ የወሰደባት ጊዜ ሆኖ የተመዘገበ ሲሆን፤ በውድድርታሪክም ሶስተኛው ፈጣን ሰዓት መሆኑ ታውቋል። ባለፉት ሶስት የበርሊን ማራቶን ውድድሮች ከአንድ እስከ ሦስት ያለውን ደረጃ ይዛ መፈፀም የቻለችው ሩቲ አጋ በተለይም ባለፈው ዓመት በጀርመን የበርሊን ማራቶን 2፤18፤34 የሆነ ሰዓት ማስመዝገቧ በርቀቱ ታሪክ ስድስተኛዋ ፈጣን አትሌት እንድትሆን እንዳስቻላት ይታወሳል። አትሌቷ ከውድድሩ በኋላ በሰጠችው አስተያየትም፤ የአየር ፀባዩ በተለይ በመሮጫ መንገዷ ላይ የተንጣለለው ውሃ ውድደሩን ከባድ ቢያደርግባትም የኋላ ኋላ ውጤታማ መሆን መቻሏን ተናግራለች። ሩታን ተከትለው ሌላኛዎቹ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ሄለን ቶላ ሹሬ ደምሴም ሁለተኛና ሶስተኛ በመሆን ተከታትለውን ገብተዋል። ይህም በቶኪዮ ማራቶን ታሪክ የመጀመሪያው ሆኖ ተመዝገቧል። በወንዶች መካከል የተካሄደውን ውድድር አትሌት ብርሐኑ ለገሰ በቀዳሚነት አጠናቋል። የ24 ዓመቱ አትሌት ውድድሩን ለማጠናቀቅ የወሰደበት ጊዜም፤ 2፡04.48 ሆኖ ተመዝግቧል። ይህ ሰዓትም እኤአ በ 2017 ኬንያዊው አትሌት ዊልሰን ኪፕሳንግ በቶኪዮ ማራቶን ካስመዘገበው ሰዓት ቀጥሎ ፈጣኑ ሰዓት ሆኖ ተመዘግቧል። አትሌት ብርሐኑ ባሳለፍነው ዓመት ዱባይ ማራቶን፤ ሁለት ሰዓት ከአራት ደቂቃ ከ 48ሰከንድ አሸናፊ መሆኑም ይታወሳል። አትሌቱ ውድድሩን በቀዳሚነት ካጠናቀቀ በኋላ በሰጠው አስተያየትም፤ በውጤቱ በጣም መደሰቱንና በቀጣዩ ዓመት በሚካሄደው የኦሎምፒክ ጨዋታዎች ማራቶን ይህን ድሉን እንደሚደግም ባለሙሉ ተስፋ መሆኑን ተናግሯል። በቶኪዮ ማራቶን ብርሃኑን በመከተል፤ ኬንያዊያኑ ቤዳን ካሮጊና ዲክሰን ቹምባ ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል። የገቡበት ሰዓትም እንደ ቅድም ተከተላቸው2:6:48 እንዲሆን 2:08.44 ሆኗል። በተለይ የአምናውን ጨምሮ የመድረኩ የሁለት ጊዜ ሻምፒዮኖ ቹምባ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁም ብዙዎች ያልጠበቁት ውጤት ሆኖም ታይቷል። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በጃፓን ቶኪዮ በሚካሄዱ ውድድሮች ላይ ከዓመት ዓመት የበላይ መሆናቸው በማስመስከር ላይ ሲገኙ ካለፉት ስምንት ውድድሮች መካከልም በስድስቱ በቀዳሚነት ማጠናቀቅ ችለዋል። በዘንድሮው የጃፓን ማራቶን ከ37 ሺ በላይ አትሌቶች መሳተፋቸው የታወቀ ሲሆን፤የ2012 የኖቤል ሽልማት አሸናፊ ጃፓናዊውን ሳይንቲስት ሺኒያ ያማናካን መድረኩን አድምቀውታል።አዲስ\nዘመን የካቲት26/2011በታምራት\nተስፋዬ", "passage_id": "28a85655ada9c993cc9c428cfc18ef68" }, { "passage": " ውድድር ዓመቱ የዳይመንድ ሊግ ፉክክሮች እየተጋመሱ መጥተው የአሜሪካዋ ዩጂን ከተማ ደርሰዋል፡፡ ዩጂን ዛሬ በተለያዩ ርቀቶች በርካታ ፉክክሮችን ስታስተናግድ በሴቶች መካከል የሚካሄደው የሦስት ሺ ሜትር ውድድር ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጠው ሆኗል፡፡ የኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮኗ ኢትዮጵያዊት አትሌት አልማዝ አያና\nከረጅም ጊዜ ጉዳት በኋላ ወደ ውድድር ተመልሳ የመጀመሪያ ፉክክሯን ዩጂን ላይ ታደርጋለች፡፡ አልማዝ ወደ ውድድር መመለሷ ለፉክክሩ ድምቀት የሰጠው ሲሆን በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በአሜሪካ ምድር በርካታ የዓለማችን ድንቅ አትሌቶች ተሳታፊ እንደሚሆኑ ታውቋል፡፡ ከነዚህም መካከል አልማዝን ጨምሮ ገንዘቤ ዲባባ፣ሔለን ኦቢሪ፣ሲፈን ሃሰን፣ካስተር ሲሜንያና ሌሎችም ድንቅ የመካከለኛና የረጅም ርቀት አትሌቶች ተፎካካሪ እንደሚሆኑ ይጠበቃል። በውድድር ዓመቱ\nአምስት ሺ ሜትርን በበላይነት ተቆጣጥራ የያዘችው ኬንያዊቷ ኮከብ አትሌት ሔለን ኦቢሪ ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት የዳይመንድ ሊግ አጠቃላይ አሸናፊ ለመሆን የምታደርገውን ጉዞ በዩጂን አጠናክራ እንደምትቀጥል ይጠበቃል። የሃያ\nዘጠኝ ዓመቷ ኦቢሪ የዓለም ቻምፒዮን ከመሆኗ ባሻገር በዘንድሮው ዓመት በአገር አቋራጭ ቻምፒዮና ወርቅ ማጥለቅ ችላለች፡፡ ባለፈው ሪዮ ኦሊምፒክ የብር ሜዳሊያ ካጠለቀች ወዲህም በለንደን አትሌቲክስ ቻምፒዮና ወርቅ ማጥለቋ ይታወሳል። ከ1500 ሜትር\nሯጭነት ተነስታ በረጅም ርቀት ኮከብ አትሌት መሆን የቻለችው ኦቢሪ እኤአ 2013 ላይ በዚሁ ዳይመንድ ሊግ ውድድር ድንቅ ብቃት አሳይታለች፡፡ 2014 ላይም በአሜሪካ ምድር የምን ጊዜም ፈጣን ሰዓት የሆነውን 3፡57፡05\nማስመዝገቧ በዛሬው ውድድር ከፍተኛ የአሸናፊነት ግምት እንዲሰጣት አድርጓል፡፡ ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ የኔዘርላንድስ አትሌት ሲፈን ሃሰን 2015 ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ የዳመንድ ሊግ ውድድር አሸናፊ መሆኗ የሚታወስ ሲሆን በ2016 አሜሪካ ፖርትላንድ የቤት\nውስጥ የዓለም ቻምፒዮና ወርቅ ማጥለቅ ችላለች፡፡ ሲፈን ያለፈውን የ2017 ውድድር ዓመትን በተለያዩ ሦስት\nርቀቶች ከምርጥ አምስት አትሌቶች ውስጥ መካተት ችላለች። ከ8 መቶ\nሜትር እስከ 5 ኪሎ ሜትር ድንቅ ብቃት ማሳየት የቻለችው ሲፈን ባለፈው የውድድር ዓመት በ5ኪሎ\nሜትር ሁለተኛና በ1500 ሜትር\nሦስተኛ ሆና ማጠናቀቅ ችላለች፡፡ ዘንድሮም ሲፈን በድንቅ አቋም ላይ የምትገኝ አትሌት መሆኗ በዩጂን ለአሸናፊነት ከሚጠበቁ አትሌቶች አንዷ ለመሆን በቅታለች፡፡ ከፆታዊ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ውዝግብ ውስጥ የምትገኘው ደቡብ አፍሪካዊት ካስተር ሲሜንያ በዩጂን ዳይመንድ ሊግ መካተቷ ውድድሩን በተወሰነ ደረጃውን ከፍ እንዲል አድርጓታል፡፡ የሁለት ኦሊምፒክና ሦስት የዓለም ቻምፒዮና አሸናፊዋ ሲሜንያ በ8መቶ\nሜትር ለሰላሳኛ ጊዜ ያለመሸነፍ ጉዞዋን ማስጠበቅ በመቻሏ አድናቆትን አትርፋለች። ከለመደችው የመወዳደሪያ ርቀት ከፍ ብላ በሦስት ሺ ሜትር\nየምታደርገውን ፉክክርም በተደጋጋሚ ማሸነፍ እንደምትችል ማሳየቷን ተከትሎ ለርቀቱ ኮከቦች ፈተና እንደምትሆን ይጠበቃል፡፡ የ28 ዓመቷ ድንቅ የመካከለኛና ረጅም ርቀት አትሌት ገንዘቤ ዲባባ ከሰባት በላይ የዓለም ክብረወሰኖችን መያዝ የቻለች ሲሆን በዩጂን ባለፉት ሦስት የዳይመንድ ሊግ ውድድሮች የተፎካከረችው በ5 ሺ\nሜትር ነው፡፡ በተለይም 2015 ላይ በዚሁ በ5ሺ\nሜትር 14:19.76 በመሮጥ በአሜሪካ ምድር የምንጊዜም ፈጣን ሰዓት ማስመዝገብ ችላለች። ገንዘቤ ባለፈው ዓመት በዓለም የቤት ውስጥ ቻምፒዮና በ1500ና\n3 ሺ ሜትር ጥምር ወርቅ በማጥለቅ የመጀመሪያዋ የዓለማችን አትሌት መሆን ችላለች። በዘንድሮው ዓመት 1500 ሜትርን 359፡08 አስመዝግባ ማሸነፍ የቻለች ሲሆን\nበ3 ሺ ሜትር ደግሞ በዶሃ ዳይመንድ ሊግ ኬንያዊቷ ኦቢሪን ተከትላ 8:26.20 ሰዓት ሁለተኛ ሆና አጠናቃለች፡፡ ከጉዳት ተመልሳ የመጀመሪያ ውድድሯን የምታደርገው አልማዝ በሪዮ ኦሊምፒክ 10ሺ ሜትርን 29፡17፡45 በሆነ የዓለም ክብረወሰን ሰዓት ማሸነፏ የሚታወስ ሲሆን 2016 ላይ የ5ሺ\nሜትር የዳይመንድ ሊጉ አጠቃላይ አሸናፊ ነበረች። በ2015 የቤጂንግ የዓለም ቻምፒዮና የውድድሩን ክብረወሰን በማሻሻል በ5ሺ ሜትር ስታሸንፍ በ2017 የዓለም ቻምፒዮና በ10ሺ ሜትር ወርቅ ማጥለቋ አይዘነጋም፡፡ ካለፈው አንድ ዓመት በላይ ግን አልማዝ በጉዳት ከውድድር ርቃ ቆይታለች። ይህም በክረምቱ መጨረሻ ኳታር ለምታዘጋጀው የዓለም ቻምፒዮና አትደርስም የሚል ስጋት ፈጥሮ ነበር፡፡ አልማዝ አሁን ልምምዷን በተገቢ ሁኔታ እያከናወነች ሲሆን የዩጂን ዳይመንድ ሊግም ድንቅ ብቃቷን ታሳይበታለች ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በ2015 የቤጂንግ የዓለም ቻምፒዮና የ5ሺ\nሜትር ውድድር በበርካቶች ዘንድ አሁንም ድረስ ይታወሳል፡፡ በዚያ ውድድር አልማዝ አያና ከሦስት ሺ ሜርት\nበኋላ አፈትልካ በመውጣት ውድድሩን በቀዳሚነት ስታጠናቅቅ በሁለተኛነት የማጠናቀቅ ሰፊ እድል የነበራት ገንዘቤ ዲባባ ነበረች፡፡ ይሁን እንጂ ገንዘቤ ውድድሩን ለመጨረስ ከሃምሳ ሜትር ያነሰ ርቀት በቀራት ወቅት ሰንበሬ ተፈሪ ከኋላ መጥታ የብር ሜዳሊያውን ማጥለቋ ይታወሳል፡፡ ሰንበሬ በዩጂኑ ውድድር እነዚሁን የአገሯን ልጆች ጨምሮ ሌሎች ኮከቦች በሚፎካከሩበት ዳይመንድ ሊግ ተካታለች፡፡ ለተሰንበት ግደይና ፋንቱ ወርቁ በዚህ ውድድር ጠንካራ ተፎካካሪ ይሆናሉ ተብለው የሚጠበቁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ናቸው፡፡አዲስ ዘመን ሰኔ 23/2011 ", "passage_id": "186529f7b60d89b46b4ce0fea00acab4" }, { "passage": "በአትሌቲክሱ ዓለም\nረጅም ርቀት ውድድሮች\nየስፖርቱ ድምቀቶች ናቸው።\nበተለይም አምስትና አስር\nሺ ሜትር ውድድሮች\nበዓለም ላይ ከፍተኛ\nተቀባይነትን እያገኙ ለመጡ\nየማራቶን ውድድሮች መሰረት\nናቸው። እንደ አጠቃላይ\nለአትሌቲክስ ስፖርትም ቢሆን\nየጀርባ አጥንቶች ናቸው።\nበታላቁ የስፖርት መድረክ\nኦሊምፒክም ቢሆን የረጅም\nርቀት ውድድሮች የማይረሳ\nታሪክ ያላቸውና ከስፖርት\nቤተሰቡ ምናብ ወደ\nፊትም ቢሆን የማይፋቁ\nናቸው።እአአ 2000 ሲድኒ ኦሊምፒክ ላይ\nጀግናው አትሌት ኃይሌ\nገብረስላሴና ኬንያዊው ድንቅ\nአትሌት ፖል ቴርጋት\nበአስር ሺ ሜትር\nቁጭ ብድግ የሚያደርግ\nግሩም ፉክክር ማን\nይረሳዋል? ይህን ከህሊና\nየማይፋቅ ውድድር ጨምሮ\nበርካታ የአምስትና አስር\nሺ ሜትር ውድድሮች\nየኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮና\nመገለጫዎች መሆናቸውን የሚክድ\nይኖራል ብሎ ማሰብ\nከባድ ነው። በእነዚህ\nውድድሮች ላይ ምሥራቅ\nአፍሪካውያን ፍፁም የበላይነት\nእየጎላ መምጣቱም ለምዕራባውያን ምቾት እንዳልሰጣቸው ምልክቶች መታየት\nየጀመሩት ዛሬ አይደለም።\nለዚህም ጠንክረው ሠርተው\nየበላይነት ከመያዝ ይልቅ\nበሴራ ለማመናቸው በርካታ\nማሳያዎችን ማስቀመጥ ይቻላል።\nእኛ ብቻ በሁሉም\nነገር የበላይ እንሁን\nየሚል ክፉ አባዜ\nየተጠናወታቸው ምዕራባውያን በመጀመሪያ\nየአገር አቋራጭ ሩጫን\nከኦሊምፒክ ድራሹ እንዲጠፋ\nአደረጉ። ቀጥሎም ቀስበቀስ\nየአስር ሺ ሜትር\nየመም(ትራክ) ውድድሮችን\nከገበያ ጋር በማስተሳሰር ‹‹አዋጭ አይደሉም››\nበሚል በዓመት አንድ\nጊዜ እንኳን የሚካሄዱበትን መንገድ ጥርቅም\nአድርገው ዘጉ። በዚህም\nበርካታ የምሥራቅ አፍሪካ\nአትሌቶች በለጋ ዕድሜያቸው\nፊታቸውን ወደ ጎዳናና\nማራቶን ውድድሮች አዙረው\nሮጠው ሳይጠግቡ ከፉክክር\nውጪ እንዲሆኑ አደረጉ።\nየምሥራቅ አፍሪካ አትሌቶች\nአስር ሺ ሜትርን\nእርግፍ አድርገው በጎዳና\nውድድር በተጠመዱበትና በተዘናጉበት ወቅት ግን\nየቤት ሥራቸውን ውስጥ\nለውስጥ ሠርተው በሞፋራህና\nበጋለን ሩፕ አማካኝነት\nስንት የኦሊምፒክና የዓለም\nቻምፒዮና ሜዳሊያዎችን እንደሰበሰቡ የምንዘነጋው አይደለም።\nየሞፋራህና ጋለን ሩፕ\nየጀግንነት ጀምበር እየጠለቀ\nሲመጣም ችላ ብለውት\nየቆየውን አምስትና አስር\nሺ ሜትር ከኦሊምፒክ\nየማስወጣት አጀንዳ ዳግም\nአራገቡት። ‹‹ውጣ አትበለው\nእንዲወጣ አድርገው›› እንደሚባለው አስር ሺ\nሜትርን እንዳኮላሹት ሁሉ\nየቀራቸውን አምስት ሺ\nሜትር ውድድርን ለመቅበር\nከሰሞኑ ሌላ ስልት\nይዘው ከች ብለዋል።\nየዓለም አቀፉ አትሌቲክስ\nፌዴሬ ሽኖች ማህበር\n(አይ.ኤኤ.ኤፍ)\nባለፈው ማክሰኞ ኳታር\nዶሃ ላይ አምስት\nሺ ሜትር ውድድር\nከ2020 ጀምሮ ከዳይመንድ\nሊግ ፉክክሮች እንዲሰረዙ\nወስኗል። ይህ ውሳኔ\nአምስት ሺ ሜትር\nየአስር ሺ ሜትር\nዕጣ ፋንታ እንዲደርሰው የሚያደርግ በመሆኑ\nከአፍሪካውያን የስፖርት ቤተሰቦች\nተቃውሞና ወቀሳ እየቀረበበትም ይገኛል። የኢትዮጵያና ኬንያ አትሌቲክስ\nፌዴሬ ሽኖችን ጨምሮ\nጀግናው አትሌት ኃይሌ\nገብረስላሴ ውሳኔውን ከተቃወሙት\nመካከል ይገኙበታል። ባለፉት\nሁለት ቀናትም አንዳንድ\nየጃማይካ የቀድሞ አትሌቶች\nድምፃቸውን ማሰማት ጀምረዋል።\nይህ ውሳኔ አፍሪካ\nበዓለም አቀፉ አትሌቲክስ\nፌዴሬሽኖች ማህበር ተሰሚ\nየሆነ ወካይ እንደሌላት\nአሳይቶናል። ያም ቢሆን\nረጅም ርቀት ውድድሮች\nየበለጠ አፍሪካውያንን ተጠቃሚ\nየሚያደርጉ በመሆኑ የአፍሪካ\nአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር\n(ሲ ኤኤ)፤\nየአፍሪካ ኦሊምፒክ ኮሚቴ(አኖካ) ውሳኔውን ለማስቀየር\nአልረፈደባቸውም። የአበበ ቢቂላ ታሪካዊ\nድል የኢትዮ ጵያውያን\nብቻ እንዳልሆነው ሁሉ\nይህ ጉዳይ የምሥራቅ\nአፍሪካውያኑ ጎረቤታሞች ብቻ\nአይደለም። አፍሪካውያን በታላቁ\nየኦሊምፒክ መድረክ ሰንደቅ\nዓላማቸው ከፍ ብሎ\nሲውለበለብ፣ ብሔራዊ መዝሙራቸው\nበክብር ሲዘመር ማየት\nከፈለጉ ይህን ውሳኔ\nለማስቀየር በአንድ ላይ\nመቆም አለባቸው። ረጅም ርቀት የአፍሪካውያን ታሪክ በወርቅ\nቀለም የተፃፈበት ዛሬም\nነገም መገለጫቸው ሆኖ\nየሚኖር ህልውናቸው ነው።\nእንደ ኃይሌ ሁሉ\nሌሎች ተፅዕኖ ፈጣሪ\nአፍሪካውያን አትሌቶች ድምፃቸውን\nማሰማት ይኖርባቸዋል። በኬንያዊው\nድንቅ አትሌት ፖል\nቴርጋት የሚመራው የአፍሪካ\nአትሌቶች ኮሚሽንም እዚህ\nጋር አቅሙን ማሳየት\nአለበት።ምዕራባውያኑ እንዲህ ዓይነቱ\nአጋጣሚ በራሳቸው ላይ\nእንዲደርስ ማድረግ አይደለም\nበኦሊምፒክ እንዲስፋፋና የበላይነታቸውን ይዘው እንዲዘልቁ\nያገኙትን ዕድል ከመጠቀም\nወደኋላ አይሉም። አሁንም\nበቀጣዩ የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ እንኳን የነሱ\nፍላጎት ያለባቸው ወይም\nሜዳሊያ ያስገኝልናል ብለው\nያሰቡትን ማንኛውንም እንቅስቃሴ\nየኦሊምፒክ ስፖርት እንዲሆን\nእያደረጉ ነው።በቀጣዩ ኦሊምፒክ ብሬክ\nዳንስ ሳይቀር እንዲካተት\nአድርገዋል። አፍሪካውያንም ከምዕራባውያን ጋር በኦሊምፒክ\nተፎካካሪ ሆነው ለመገኘት\nእንደ አገር አቋራጭ\nሩጫ ዓይነት ውድድሮችን\nከመጠቀም ባለፈ ረጅም\nርቀቶች ላይ ያንዣበበውን አደጋ ለማስቀረት\nበጋራ መጋፈጥ ግድ\nይላቸዋል። የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ፕሬዚዳንትና የቀድሞ የአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር የኦሊምፒክ አሸናፊ እንግሊዛዊው ሴባስቲያን ኮ ወደ ስልጣን ሲመጡ እዚሁ አዲስ አበባ ላይ የረጅም ርቀት የቀድሞ ዝናና ስም ለመመለስ እንደሚሠሩ ቃል ቢገቡም አሁን ቃላቸውን አጥፈዋል። አፍሪካውያን በአንድነት ካሁኑ ካልታገሉም እንደ አገር አቀራጭ ውድድር ሁሉ አስርና አምስት ሺ ሜትር ውድድሮች በቅርቡ ከኦሊምፒክ ላለመሰረዛቸው እርግጠኛ መሆን አይቻልም።አዲስ ዘመን\nመጋቢት 6 /2011ቦጋለ\nአበበ ", "passage_id": "6d6589aa4c0a66d90450b044e54ca629" }, { "passage": "ኡጋንዳዲው ጆሹዋ ቼፕቴጌ በፈረንሳይ ሞናኮ በተካሄደው የዳይመንድ ሊግ ውድድር ለ16 ዓመታት በቀነኒሳ በቀለ ተይዞ የነበረውን የ5000 ሜትር ሩጫ ክብረ ወሰን በሁለት ሰከንድ ማሻሻል ችሏል።የ23 ዓመቱ ወጣት ባላፈው ዓመት በዶሃ የዓለም ሻምፒዮና ላይ የ10 ሺህ ሜትር አሸናፊ በሆነበት ወቅት የ5 ሺህ ሜትር ክብረ ወሰንን ለማሻሻል እቅድ እንዳለው ገልጾ የነበረ ሲሆን በቅርብ ዓመታት ያሳካዋል ተብሎ ግን አልተገመተም ነበር።ነገር ግን በትላንቱ የሞናኮው ውድድር ላይ 5 ሺህ ሜትሩን 12 ደቂቃ 35.36 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በመጨረስ ቀነኒሳን ክብረ ወሰን መስበር ችሏል።ቀነኒሳ በቀለ የዛሬ 16 ዓመት ክብረ ወሰኑን ሲያስመዘግብ ውድድሩን የጨረሰው በ12 ደቂቃ 37 ሰከንድ ከ35 ማይክሮ ሰከንድ ነበር።በሚያስገርም ሁኔታ ቼፕቴጌ በዚህ ዓመት ክብረ ወሰን ሲሰብር ይሄ ሁለተኛው ነው። ባለፈው የካቲት ወር ላይ ደግሞ በተካሄደ የ5 ኪሎ ሜትር ሩጫ ሰዓት ማሻሻል እንደቻለ ተነግሯል። ''ሞናኮ በጣም ልዩ ቦታ ናት፤ የዓለም ክብረ ወሰኖችን ልሰብርባት የምችልባት ከተማ ናት'' ሲል በደስታ ተውጦ ቼፕቴጌ ተናግሯል።''በዚህ ዓመት በእውነቱ ሞራልን ሰብሰብ አድርጎ ለመስራት ትንሽ ይከብዳል፤ ምክንያቱም በወረርሽኙ ምክንያት ሰዎች ከቤታቸው አይወጡም፤ ብዙ ነገሮችም በፊት እንደነበሩት አይደሉም፤ ተቀይረዋል። ነገር ግን በዚህ ሁኔታ ውስጥ በማሸነፌ በጣም ደስተኛ ነኝ።''በሌሎች ውድድሮች የዓለም ሻምፒዮኑ ኖዋህ ሊይስ የ200 ሜትር ውድድሩን በ19 ሰከንድ ከ72 ማይክሮሰከንድ በሆነ ሰዓት በማሸነፍ አይበገሬነቱን አሳይቷል። ታናሽ ወንድሙ ጆሴፈስ ደግሞ በመጀመሪያው የዳይመንድ ሊግ ተሳትፎው እሱን ተከትሎ ሁለተኛ ሆኖ መጨረስ ችሏል።ኖርዌያዊው ዓለም ሻምፒዮን ካርስተን ዋርሆልም ደግሞ በ400 ሜትር መሰናክል ውድድር በአውሮፓውያኑ 1992 በኬቨን ያንግ ተይዞ የነበረውን ክብረ ወሰን መስበር ችሏል።ለብቻው ለማለት በሚያስደፍር መልኩ ሲሮጥ የነበረው ካርስተን ውድድሩን በ47 ሰከንድ ከ10 ማይክሮ ሰከንድ ጨርሷል።ኬንያዊቷ ሄለን ኦቢሪ ደግሞ የሴቶች 5 ሺህ ሜትር ውድድሩን በበላይነት ስታጠናቅቅ ሲፋን ሀሰን ደግሞ ጥቂት ዙሮች ሲቀሩት ውድድሩን አቋርጣ ወጥታለች። 5 ሺህ ብቻ ሰዎች እንዲመለከቱት በተፈቀደው የሞናኮው የዳይመንድ ሊግ ውድድር ላይ ተመልካቾች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማድረግ ግዴታቸው ሲሆን አካላዊ ርቀትም መጠበቅ ነበረባቸው።", "passage_id": "e26d90f548d9640150005c4e6d42bca4" } ]
8f259b6d2721605cf564ddcb7c77428c
18d5a4aa58f61c6bb5aa0567f93afbff
የካፍ አካዳሚ ወደ አገልግሎት የመመለስ ተስፋ
 የኢትዮጵያ እግር ኳስ እድገት ለመቀጨጩ በርካታ ምክንያቶች ሊዘረዘሩ ይችላሉ። ከእነዚህ መካከል አንዱና ትልቁ ምክንያት ሆኖ በተደጋጋሚ የሚነሳው ታዳጊዎችን ለማሰልጠን የሚያበቃ አካዳሚ አለመኖሩ ነው። በእርግጥ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ በአገር አቀፍ ደረጃ በተገነቡ የስፖርት ማሰልጠኛ ማዕከላትና አካዳሚዎች የተለያዩ ስልጠናዎች ደረጃቸውን ጠብቀው በተገነቡ የማሰልጠኛ ማዕከላት መሰጠት ጀምረዋል። ይሁን እንጂ በተገነቡት ዘመናዊ የማሰልጠኛ ማዕከላት እግር ኳሱን ከቁልቁለት ጉዞ ታድጎ አንድ ርምጃ ወደ ፊት የሚያራምድ ፍሬ ማፍራት እንዳልተቻለ ለማንም የተሸሸገ እንዳልሆነ መገንዘብ ይቻላል። የተገነቡትን ዘመናዊ የማሰልጠኛ ማዕከላት ፍሬ እንዲያፈሩ በአግባቡ እንዳልተሰራባቸው አንዱ ማሳያ በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን(ካፍ) የተገነባውና ከአስር ዓመት በላይ አገልግሎት ሳይሰጥ የቆየው የካፍ እግር ኳስ አካዳሚ ነው። በአዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አያት አካባቢ የሚገኘው አካዳሚው ግንባታው የተጀመረው በ1997 ዓ.ም ሲሆን፤ በሶስት ዓመት ለማጠናቀቅ ነበር የታቀደው። ሆኖም ግንባታው በመዘግየቱና ከተጠናቀቀም በኋላ አገልግሎት መስጠት አለመጀመሩ በርካታ መዋዕለ ንዋይ የፈሰሰበትን መሰረተ ልማት አገልግሎት ሳይሰጥ እንዲባክንና ጉዳት እንዲደርስበት ሆኗል። የስፖርት ቤተሰቡ በዚህ የተነሳ ተደጋጋሚ ቅሬታ ሲያቀርብ ቆይቷል። ይህንንም ተከትሎ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተካሄደ እንቅስቃሴ አካዳሚው ስራ አስኪያጅ ተመድቦለትና ለብልሽት ለተዳረጉ ስራዎች እድሳት ተደርጎባቸው ተስፋ ማሳየት ጀምረዋል። ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻም የስፖርት አመራሮች እንዲሁም የስፖርት ማህበራት ኃላፊዎች በቦታው ተገኝተው ጉብኝትና የችግኝ መትከል መርሃ ግብር አካሂደዋል። በወቅቱም አካዳሚው ስላለበትና ቀጣይ እጣ ፈንታው ምን እንደሚሆን ማብራሪያ ተሰጥቷል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጂራ፤ የልህቀት አካዳሚው 15 ዓመት እንደሆነው በማስታወስ፣ ካፍ በአህጉሪቷ የእግር ኳስ ልህቀት አካዳሚውን ለመገንባት ሲነሳ የመረጣቸው አገራት ካሜሩን፣ ሴኔጋል እና ኢትዮጵያ መሆናቸውን ይናገራሉ። በወቅቱ የካፍ ፕሬዚዳንት የነበሩት ኢሳ ሃያቱ ካሜሮናዊ በመሆናቸው በአገራቸው የሚገነባውን ተመሳሳይ አካዳሚ ግንባታ ወደራሳቸው በማድላት በዲዛይኑ መሰረት በጥሩ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ማድረጋቸውን አቶ ኢሳያስ ያስረዳሉ። በዚህ ወቅትም ሁሉም መሰረተ ልማት የተሟላለትና ስፖርተኞችን እያፈራ እንደሚገኝ ይናገራሉ። በሴኔጋል የተገነባው ተመሳሳይ አካዳሚም ቢሆን ከዋና ከተማዋ ዳካር 80 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የአገሪቱ መንግስት ገንዘብ በመመደብና በማደስ ብሄራዊ ቡድናቸውን ያሳርፉበታል። የኢትዮጵያው አካዳሚ እስካሁንም ድረስ ባለበት የቆየ ሲሆን ከወራት በፊት ካፍ የባለቤትነት መብት እንዲሰጥ ለፌዴሬሽኑ ደብዳቤ ጽፎ ነበር። በዚህም መሰረት የሰነድ ርክክቡ ተጠናቆ የውልና ማስረጃ ስራዎች በመከናወን ላይ እያለ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በመከሰቱ ሊቋረጥ ችሏል። ወደፊት ከኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር በመተባበርና ሂደቱን በማጠናቀቅ ህጋዊ ይሆናል ተብሎም ይጠበቃል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ይህን እያደረገ በነበረበት ወቅትም ጎን ለጎን ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ሲያከናውን እንደነበረ ፕሬዚዳንቱ አቶ ኢሳያስ ያስታውሳሉ። የጀርመኑ ክለብ ባየርሙኒክ የአካዳሚውን ሜዳ እንዲያሰራ፣ ጂአይዜድ ደግሞ ሁለት የተፈጥሮና አንድ የሰው ስራሽ ሜዳዎችን ለመስራት ቃል መግባታቸውን ጠቁመዋል። በተለያዩ ደረጃዎች የሚገኙ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድኖችን ለተለያዩ ጨዋታዎች ለማዘጋጀት በሆቴሎች እንዲያርፉ ከፍተኛ ገንዘብ ወጪ እንደሚደረግ ይታወቃል። ከዚህ በኋላ ግን በዚህ አካዳሚ በማሳረፍ ዝግጅታቸውን እንዲያደርጉ ማድረግ እንደሚቻል አቶ ኢሳያስ ተናግረዋል። ከእግር ኳስ ባሻገር ያሉ ስፖርቶችም ብሄራዊ ቡድናቸውን ማሳረፍ የሚችሉበት አጋጣሚ እንዳለ ተገልጿል። ከዚህ ባሻገር በኢትዮጵያ አርፈው ወደ ሌሎች አገራት የሚጓዙ ብሄራዊ ቡድኖች በአካዳሚው እንዲያርፉ በማድረግ ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት እንደሚቻልም ጠቁመዋል። ይህንን ለማድረግ ግን የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችን ማሟላት ያስፈልጋል። ይኸውም የልምምድ ሜዳ እና የጉድጓድ ውሃ መሆኑን ለመንግስት ጥሪ ተደርጓል። ይህ ሲሆንም የፌዴሬሽኑን ጽህፈት ቤት አካዳሚው ወዳለበት ስፍራ ለማዘዋወር እንደሚያመች አቶ ኢሳያስ አብራርተዋል። የቀድሞውም ሆነ የአሁኑ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጽህፈት ቤት የሚገኝበት አካባቢ መሐል ከተማ እንደመሆኑ የእግር ኳስ እንቅስቃሴ ለማድረግ አይታሰብም። አፍሪካን ጨምሮ በሌሎች አገራት ስፖርቱ ሙሉ በሙሉ የሚንቀሳቀሰው በአንድ አካባቢ በተገነባ ዘመናዊ የስፖርት ማዕከል ነው። ይህ አካዳሚ እያለ ግን አገልግሎት መስጠት ሳይጀምር የመፍረስ አደጋ ተጋርጦበት ነበር። የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ባደረገው ጥረትና በመደበው 2 ሚሊዮን ብር ግን በድጋሚ ሊታደስችሏል። በቀጣይም መንግስታዊ አካላት ለትውልድ ሊተላለፍ የሚችለውን አካዳሚ ሊጠብቁ እንደሚገባ አቶ ኢሳያስ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ በበኩላቸው፤ የአካዳሚው ግንባታ የተጀመረው እርሳቸው የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈጻሚ እያሉ መሆኑን አስታውሰው፣ ለዓመታት በዚህ ሁኔታ ውስጥ አልፎ አሁን እድሳት ሲደረግለትም በስፖርቱ ውስጥ መሆናቸውን ተናግረዋል። በመሆኑም ይህ ለእግር ኳስ እድገት እንዲሁም ስፖርተኞችን ለሚያፈራ አካዳሚ ኮሚቴው የሚጠበቅበትን የሚወጣ መሆኑን ጠቁመዋል። የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነሩ ዱቤ ጂሎ፤ ከወራት በፊት አካዳሚውን በጎበኙበት ወቅት አሳዛኝ ሁኔታ መመልከታቸውን ያስታውሳሉ። በወቅቱም ከፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ጋር በመሆን ወደ ስራ መግባት እንደሚኖርበት ተነጋግረዋል። በተከናወነው ስራም አሁን የተሻለ ሁኔታ ላይ ሊገኝ ችሏል። ስለ ስፖርት ሲታሰብ ዋናው ጉዳይ የማዘውተሪያ ስፍራዎች በመሆናቸው ኃላፊነት ያለበት ኮሚሽኑ አካዳሚው ስልጠና እንዲጀምር በትኩረት በመስራት ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። አካዳሚው እንዲገነባ ያደረጉ አካላት ምስጋና የሚገባቸው ቢሆንም ለ15 ዓመታት ያለ ስራ መቀመጡ ግን ጥፋት ነው ሲሉም አቶ ዱቤ ተናግረዋል። በመሆኑም ይህንን ለማረም በቁርጠኝነት መነሳታቸውን አረጋግጠዋል። አካዳሚውን ለማፍረስ ሙከራ ያደረጉትንም የሚቃወሙና ማስተካከያ ማድረግ የሚያስፈልግ መሆኑንም ጠቁመዋል። በእርሳቸው ሃሳብ ላይ ያከሉት የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽነር አቶ ኤሊያስ ሽኩር በበኩላቸው፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ማዕከላትን መንከባከብ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል። ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ለስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መሬት ከመስጠት ባሻገር በቀጣይነት አብሮ መስራት አስፈላጊ ነው። የተገነቡና እየተገነቡ ያሉ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችና የስልጠና ማዕከላት ከተልእኳቸው አንጻር በሙሉ ኃይላቸው እየሰሩ አይደለም። በሌላ መልኩ በየአካባቢው የተገነቡት ማዕከላት ለማህበረሰቡ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት አለባቸው። በመሆኑም በየአካባቢው ያሉ የስልጠና ማዕከላትና አካዳሚዎች ተገቢውን ግልጋሎት እንዲሰጡ ማድረግ ተገቢ ነው። በተለያዩ አካባቢዎች ውድ የሆነው መሬት ለስፖርት እንዲውል ቢሰጥም እንደ ካፍ አካዳሚ ሁሉ ለዓመታት ታጥረው መቀመጥ የለበትም። መንግስት፣ ህብረተሰብ እንዲሁም የስፖርት ቤተሰቡም በስፖርት ስም የተቀመጡ መሬቶችንና ግንባታዎችን ወደ ስራ እንዲገቡ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል። የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው በበኩላቸው፤ አካዳሚው የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ ብቻም ሳይሆን የኢትዮጵያ ህዝብ ሀብት መሆኑን ጠቁመዋል። የአካባቢውን ማህበረሰብም ተጠቃሚ በማድረግ ገቢ ማስገኘት የሚቻልም ይሆናል። እስካሁን አካዳሚውን አለመጠቀም ‹‹ምን ዓይነት እንደሆን ያሳያል›› ያሉት ሚኒስትሯ፤ መንግስት ቦታውን ሰጥቶ መስራት ያለበት አካል በሚገባው ቦታ አለመገኘቱ አሳዛኝ መሆኑን ይገልጻሉ። ቦታውን ከተረሳበትና ከተጎዳበት በማስተካከል አሁን ያለበት ላደረሱ አካላትም ምስጋና ይገባል።አዲስ ዘመን ሰኔ 22/2012 ብርሃን ፈይሳ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=35323
[ { "passage": "ግንባታው ከተጀመረ ዘጠኝ ዓመታትን ያስቆጠረው የሀዋሳ ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተለያዩ ምክንያቶች እየተጓተተ ለምን እስካሁን መጠናቀቅ አልቻለም?በ2004 ግንባታው የተጀመረውና ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ ከ45-50 ሺህ ተመልካቾችን በወንበር እንደሚያስተናግድ የተነገረለት ስታዲየሙ በአራት ዓመታት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ቢጠበቅም በተለያዩ ምክንያቶች እየተጓተተ ዓመታት ተቆጥረው እስካሁን መጠናቀቅ አልቻለም፡፡ በ2008 ለመላው ኢትዮጵያ ውድድሮች ሲባል አፋጣኝ ሥራዎችን ሲከወን የነበረው የዚህ ስታዲየም ፕሮጀክት ከውድድሩ በኋላ ግን ያዘገመ ሥራዎች እየተሰሩበት አሁን ላይ “ቆሟል” የሚባልበት ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ሳትኮም በተባለ የኮንስትራክሽን ተቋራጭ ሲሰራ የቆየው ስታዲየሙ ባልተጠናቀቀበት ሁኔታ ከሀገር አቀፍ ስፖርታዊ ጨዋታዎች አንስቶ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ወላይታ ድቻ ክለቦች አህጉራዊ ውድድሮች ግልጋሎት ሰጥቷል። ስታዲየሙ በውድድር ወቅት በተለይ እንደ ችግር የሚነሳበት የመጫወቻ ሳሩን የመቀየር ሥራ በስድስት ወራት ውስጥ ተፈፃሚ ይሆናል ተብሎ ቢጠበቅም ወቅቱን መጠበቅ ሳይችል ይኸው ድፍን ሁለት ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ የመብራት (ፓውዛ)፣ ስክሪን ገጠማ፣ የሚዲያ ክፍል፣ የመልበሻ፣ የውስጥ ማማሟቂያ እና መፀዳጃ ቤቶች የተሰሩለት ቢሆንም የወንበር፣ የተጠባባቂ ተጫዋቾች መቀመጫ፣ ጥላ፣ መጠነኛ ማሻሻያን የሚሹ የዲዛይን ሥራዎች እንዲሁም የፊኒሺንግ ሥራዎች ይጠብቁታል። ከዚህም በተጨማሪ ከሜዳው ውጪ የሚገኙ ሁለት የእግር ኳስ መለማመጃ ሜዳዎች እና በዲዛይኑ ላይ የተካተቱ የሌሎች ስፖርቶች ማከናወኛ ግንባታዎች ከዚህ ቀደም በጥንድፊያ የተሰሩ በመሆናቸው በዲዛይኑ መሠረት መጠናቀቅ ይጠበቅባቸዋል።የደቡብ ክልል ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ የሺዋስ ዓለሙ ከሶከር ኢትዮጵያ ጋር ባደረጉት ቆይታ ስታዲየሙ አሁን ያለበት ሁኔታ እና እየተሰሩ ያሉ ሥራዎችን በዚህ መልኩ አስረድተዋል።“በመጀመሪያው ዙር ግንባታ በአመዛኙ ትልቁ ስታዲየም መሠረታዊ ሥራዎች እያለቁ ነው። ችግር የነበረበት የሳር ንጣፉ አሁን እየተስተካከለ ነው። ከዛ ውጪ ያለው የቴክኖሎጂ ገጠማው ነው፤ እሱ የኮንስትራክሽን ድርጅቱ ሳትኮም ያመጣው የውጪ ድርጅት ጋር በመሆን አብዛኛዎቹን የቴክኖሎጂ ሥራዎችን ጨርሷቸዋል፡፡ ባለፈው ህዳር እና ታኅሣሥ ላይ የቴክኖሎጂ ገጠማ ሥራው ተሰርቷል፡፡ በሁለተኛ ምዕራፍ የተያዘው የጣራ እና የወንበር ሥራ ነው የሚቀረው። እሱ በኮንትራክተሩ እና በክልላችን ኮንስትራክሽን ቢሮ አማካኝነት አዲስ የተሰራ ዲዛይን ስላለ ዲዛይኑ ላይ ማሻሻያ እንዲደረግ ተብሎ የማሻሻያ ሥራው እየተሰራ ነው። ይህ የዋናውን የስታዲየም ገፅታ የተመለከተ ጉዳይ ነው።“ከዚህ ጋር ተያይዞ ካፍ በተደጋጋሚ የሰጣቸው ኮመንቶች አሉ። በተሰጡን ኮመንቶች መሠረት ከማስተካከል አኳያ አንዳንዶቹ ከመጡት ገምጋሚ ቡድን ጋር ካለ የመረጃ ልውውጥ ችግር ጋር የተያያዘ ነው። ያ ደግሞ ሰነዶች ከታዩ በኃላ ለማስተካከል ተሞክሯል፡፡ የሚቀሩ ክፍሎችን የማደስ መሠረታዊ የሆኑ ሀሳቦች ቀርበዋል። የመጫወቻ ሜዳ፣ የመልበሻ ክፍል፣ የውስጥ ማማሟቂያን በተመለከተ በአመዛኙ በተሰጡት አስተያየቶች መሠረት ለማስተካከል ተችሏል፡፡ ከዋናው ስታዲየም ጋር በተጓዳኝ የማስፋፊያ ሥራዎች ደግሞ አሉ። የመለማመጃ ሜዳ፣ ትንንሽ ሜዳዎች (እንደ ቅርጫት ኳስ ሜዳ እና መሰሎች)፣ ውሀ መዋኛ እና ሌሎች ቀሪ ሥራዎች አሉ። ”ኮሚሽነሩ ሥለ ግንባታው በጊዜው አለመጓዝ ላነሳንላቸው ጥያቄ ማብራሪያቸውን በመቀጠል የበጀት፣ የኮሚቴ መቀያየር፣ ከተቋራጮች ጋር አለመግባባት፣ የፀጥታ ሁኔታ እና ኮሮና ወረርሺኝ ለፕሮጀክቱ መጓተት ምክንያት መሆናቸውን ገልፀዋል።“ሥራውን ከያዘው የኮንስትራክሽን ድርጅት ጋር አለመግባባት እየተፈጠረ በመሆኑ በአማካሪው እና በአሰሪ ቢሮው በኩልም ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶት ነበር፤ ነገር ግን ውጤታማ ባለመሆኑ እያነሳ ያለውም ጥያቄ በአሰራር ደረጃ የማይመለስ በመሆኑ ውሉን ለማቋረጥ እንቅስቃሴ ላይ ነን። የማስፋፊያ ሥራውን የሚሰራው ‘በረከት እንደሻው’ የሚባል ድርጅት ጋር ከ2008 ጀምሮ (የመላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ጀምሮ) ሲሰራ የነበረ ድርጅት ነው። የሚጠይቃቸው ጥያቄዎችን ከተገባው ውል አንፃር ሊመለሱ የማይችሉ ከመሆኑ ባለፈ ያለፉትን 18 ወራት ሥራ ላይም ስላልነበረ ተገምግሞ የመጨረሻ ውሳኔ ላይ እየተደረሰ ነው ያለው፡፡” ከተቋራጩ በተጨማሪ ፕሮጀክቱን የሚከታተለው ኮሚቴ በየጊዜው መለዋወጥ ሥራውን አስቸጋሪ አድርጎታል። ‘የሀዋሳ ስታዲየም የህዝብ ተሳትፎ እና አስተዳደር’ የሚባል ኮሚቴ አለ። እዚህ ክልል በነበረው የአመራር መለዋወጥ እና ሽግሽግ በአብዛኛውም ሥራ አስፈፃሚ ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩም በአጠቃላይ አሁን ስለሌሉ ያን የመተካት ጉዳይ ከክልሉ ባህልና ቱሪዝም እና ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጋር ተነጋግሮ የፈረሰውን ቦርድ መልሶ ለመሰየም እና ለማቋቋም እንቅስቃሴ ላይ ነው ያለነው።” ከዚህ ጎን ለጎን በሁለተኛው ምዕራፍ የሚካተቱ የፊኒሽንግ እና ብዙ ወጪ የሚያስወጣው የጣሪያ፣ የወንበር እንዲሁም ዙሪያ አጥር ግንባታ ለመስራት ባለፈው ክረምት ጨረታ ወጥቶ ነበር። ሆኖም የወጣውን የሚያሟላ አካል ስላልነበር፣ ለዛ የሚረዳ በቂ በጀትም ስላልነበረ በቴክኒክ ውድቅ ተደርጎ ተጨማሪ በጀት ወጥቶ በድጋሚ ጨረታ ለማውጣት ከ200 እስከ 250 ሚሊዮን ያስፈልጋል የሚል መመሪያ ስላለ ያን ለማድረግ በሒደት ላይ ነው ያለነው። ትልቅ ሀገር አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ውድድሮች ሲያስተናግድ የነበረ ሜዳ ቢሆንም በተጠበቀው ልክ ባለፉት ሁለት ዓመታት ሥራ አልተሰራም። ለሥራው የክልሉ መንግሥት በጀት በአግባቡ ሲበጅት ቢቆይም በነበረው የፀጥታ ችግር ጥቅም ላይ ማዋል አልተቻለም። በዚህ ዓመት ለመከናወን ሲታሰብ ደግሞ ለግንባታው የተያዙ አብዛኛው ወጪዎች ወደ ኮሮና ስለዞሩ የበጀት እጥረት አጋጥሟል።“የሳር መቀየር ሥራው እንደተባለው መከናወን ከነበረበት ጊዜ አንፃር በጣም ቆይቷል። ወደ መቀየሩ ሒደት ዘንድሮ ነው የተገባው። ግን ችግሩን በጥልቀት ገምግሞ ከማቅረብ አንፃር መዘግየቶች ነበሩ፡፡ አብዛኛው የሜዳውን ስራ የሚይዘው ይሄን ሳር የመቀየር ነው፡፡ ሳሩን ለመቀየርም በዝርዝር ነው እየተገመገመ የሄደው ለዚህ የሚመች ደረጃው የጠበቀ ኮረት የማስተካከል አፈሩን የማጠብ የፍሳሽ ሥርዓቱን የማስተካከል ጉዳይ አሁን በሚገባ እየሄደ ነው ያለው። ከኮንትራክተሩ ጋር የነበረን ውል በዚህ ሚያዚያ ወር ላይ የሚያልቅ የነበረ በመሆኑ በፍጥነት ነው ሲሰራ የነበረው። አሁን ላይ ያለበት ሁኔታ ጥሩ ነው። ያው የዘገየበት ሁኔታ የአስፈፃሚ አካላት መጓተት አመራሩ በፍጥነት መመሪያ ያለመስጠት ያመጣው ችግር ቢሆንም ዘንድሮ ያን ለማስተካከል ተሞክሯል፡፡ የሳር ንጣፉ በአምስት ወር ለመጨረስ ነው ስምምነት ላይ የተደረሰው። ጥሩ እየሄደ ከኮሮና መምጣት ጋር በተያያዘ ግን ዘግይቷል፡፡ አሁን ግን በፍጥነት ተመልሶ ወደ ስራ እንዲገባ መግባባት ላይ ስለተደረሰ በሁለት ወር የመጨረስ ስራ ላይ እንገኛለን። ችግሩ ተከስቷል፤ ለማስተካከልም ተዘግይቷል። ያም ቢሆን በአጭር ጊዜ ይጠናቀቃል፡፡ ”ስታዲየሙ መቼ እንደሚናቀቅ እና ቀጣይ ሥራዎች በምን መልኩ እንደሚካሄዱ ግልፅ መረጃ ማግኘት አዳጋች ሲሆን ካለው የሀገሪቱ ተጨባጭ ሁኔታ አንፃር በቂ የማጠናቀቂያ በጀት የማግኘቱ ጉዳይ አጠያያቂ ሆኖበታል። በጉዳዩ ላይም ለስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነሩ ጥያቄውን አንስተን ስታዲየሙን ለማጠናቀቅ እየሄዱ ስላሉበት መንገድ እና እቅድ የሚከተለውን ብለውናል።” ከዋናው ስታዲየም ጋር በምዕራፍ ሁለት መካተት ያለበት የጣሪያ እና የወንበር ሥራ የራሱ የሆነ በጀት ስለሚፈልግ ከመስተዳድር ምክር ቤት እና ከክልሉ ምክር ቤት ጋር ተነጋግሮ ማስመደብ፤ በመቀጠል ባለፉት ሁለት ዓመታት የዘገየውን ስታዲየም በምን አይነት መልኩ እናፋጥነው የሚለው ጉዳይ ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተነጋግረን አዲስ ቦርድም ተቋቁሞ ይሄን በበላይነት የሚመራውን ዳግም ለመመለስ በሒደት ላይ ነን።“እንደ ኮሚሽን የመጀመሪያው ምዕራፍ ዘንድሮ መጠናቀቅ አለበት የሚል አቋም ነው የያዝነው። በመጀመሪያው ዙር ቅድም ያልኩት የመጫወቻ ሳሩ ያልቃል፣ የቴክኖሎጂ ገጠማው ያልቃል፣ በዚህ ዙር ተጨማሪ ኮንትራት የተሰጡ የውጪ የማስፋፊያ በአመዛኙ ብዙዎቹ አልቀው የተወሰኑት በኮንትራክተሩ በተፈጠረው ችግሮች የተቋረጡ ቢኖሩም የተሰሩ ሥራዎች ግን አሉ፡፡ ከማስፋፊያ ስራዎች አንፃር 86% ተሰርቷል፡፡ በትልቁ ስታዲየምም ላይ መሰራት ካለበት መሀከል 96% ተሰርቷል፡፡ የማስተካከል እና የለቀማ ስራዎች ሲቀሩ ይሄን ዘንድሮ ለመጨረስም ነው ያሰብነው። የአጥር ግንባታ እና የላንድ ስኬፒንግ ስራ በሚቀጥለው በጀት ዓመት አጋማሽ ላይ እንጨርሳለን የሚል ነው የኮሚሽኑ እቅድ። ”እስከ አሁን 750 ሚሊዮን ብር ፈሰስ እንደተደረገበት የተነገረለት ስታዲየሙን ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ለአዲስ የኮንስትራክሽን ተቋራጭ ጨረታ አውጥቶ በቀጣይ ሥራ የሚጠብቀው ሲሆን ዘንድሮ ወደ ሥራ ለመመለስ 20 ሚሊዮን ብር በጀት ቢመደብለትም በተለያዩ ምክንያቶች መንግስት ከዚህ በጀት ላይ 16 ሚሊዮን ብሩን ለሌላ ስራ አውሎታል ተብሏል፡፡ በቀጣይ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅም ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብን እንደሚጠይቅ ታውቋል።", "passage_id": "e6e7e64ab165afacb36b0ee524cf2e98" }, { "passage": "ካፍ በቅርቡ ባደረገው ግምገማ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ ሜዳዎች ዓለም አቀፍ ውድድሮችን የማስናገድ አቅም ላይ የማይገኙ በመሆኑ የቀጣይ የአፍሪካ መድረክ ጨዋታዎችን በሜዳ የመጫወት ሁኔታ ጥያቄ ምልክት ውስጥ ገብቷል።በኢትዮጵያ ከአዲሱ ሚሌኒየም ወዲህ በመላ ሀገሪቱ ግዙፍ የሚባሉ ስታዲየሞች በመገንባት ላይ ቢሆኑም አንዳቸውም ሙሉ ለሙሉ አልተጠናቀቁም። ከተመልካች መቀመጫዎች እና ውጫዊ ገፅታ ባሻገር የመጫወቻ ሜዳ ጥራት፣ አስፈላጊ ውስጣዊ ግንባታዎች ላይ የሚሰጠው ትኩረት አናሳ መሆኑ ዋጋ እያስከፈለን መጥቷል። በቅርቡ እንኳን በ2020 የቻን ውድድርን ለማስተናገድ በካፍ ተመርጣ የነበረችው ሀገራችን ለሁለት ጊዜያት ሀዋሳ፣ መቐለ፣ ባህርዳር እና አዲስ አበባ የሚገኙ ስታዲየሞችን በካፍ አስገምግማ ያሉበት ወቅታዊ ሁኔታ ውድድሩን ለማስተናገድ ብቁ አይደሉም በሚል የማዘጋጀት ዕድላችንን አሳልፈን ለካሜሩን መስጠታችን ይታወሳል ፡፡በጉዳዩ ዙርያ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ ጂራ ከሶከር ኢትዮጵያ ጋር ባደረጉት ቆይታ “ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ ሜዳዎች አንዳቸውም የካፍን መመዘኛ አያሟሉም ተብለናል፡፡” ሲሉ ይናገራሉ ” የአዲስ አበባ ስታዲየምን ከአሁን በኃላ ካፍ መጠቀም አትችሉም ብሎ በደብዳቤ አግዷል። የመቐለን ለማስመዝገብ ልከናል፤ የባህር ዳን አስቀድመን ስላሳወቅን ብቻ ዕድል ሊኖረን ይችላል። አንድ ተስፋችን ባህርዳር ብቻ ሊሆን ነው።” ሲሉም አክለዋል።እንደ ፕሬዝዳንቱ ገለፃ የሀዋሳ ስታዲየም ሳር በመበላሸቱ በአዲስ ሳር ለመተካት ዕድሳት ላይ የሚገኝ ሲሆን “የአዲስ አበባ ስታዲየም በተለይ የመልበሻ እና የመፀዳጃ ቤቱ እጅጉን የማይመጥን በመሆኑ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን እንዳያስተናግድ ታግዷል።” ብለዋል፡፡የአዲስ አበባ ስታዲየምን በሚመለከት ለጠየቅናቸው ጥያቄ “ለስፖርት ኮሚሽን ደብዳቤ ፅፈናል። ዛሬ ብቻ አይደለም ለስፖርት ኮሚሽን የተፃፈለት። ከኛ በፊት የነበሩት አመራሮች ወቅትም ከአንድም ሦስት ጊዜ ካፍ ይሄ ሜዳ እንዲታደስ አሳስቦ ነበር። ይህ የሀገሪቱ ጉዳይ ነው፤ ፌዴሬሽኑ ሜዳውን ለምን አያድስም የሚል ጥያቄ ሊኖር ይችላል። ነገር ግን ይህ የመንግስት ጉዳይ ስለሆነ ይህንን አሳውቀናል። የፊፋ አባል ሀገር ሆነን ሜዳ የላችሁም መባላችን ለሀገር ውርደት ነው። እኔም ለስራ አስፈፃሚዎቼ እንድታውቁት ብዬ በደብዳቤ አሳውቄያለሁ። በኛ ሀገር ሜዳዎች መሰራታቸው መልካም ቢሆንም በተለይ የመጫወቻ ሜዳዎቹ እጅጉን ደካሞች ናቸው። ” ብለዋል።ፕሬዝዳንቱ ትላንት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በድሬዳዋ ከጅቡቲ ጋር ሲጫወት ተመልካች ስታዲየም ገብቶ ያለመመልከቱ ከዚህ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ያስረዳሉ “የድሬዳዋ ስታዲየም ገና አልተጠናቀቀም። የግንባታ ዕቃዎች እና የአሸዋ ክምር በሜዳ ውስጥ በመታየታቸው በዝግ እንዲሆን ተደርጓል። ይህን ሳናሟላ ለመጫወት መሞከር አዳጋች ነው። ሜዳው ጥሩ ቢሆንም ግንባታው ባለማለቁ ኮሚሽነሩ ያደረጉት ነገር ትክክል ነበር። ይህ በመሆኑ ግን ተከፍቻለሁ”በቀጣይ ጊዜያት በዓለም ዋንጫ፣ ቻን፣ አፍሪካ ዋንጫ እንዲሁም የወጣቶች እና ሴቶች ውድድሮች በርካታ ማጣሪያዎች ያሉባት ኢትዮጵያ በሀገሪቱ ያሉ ሜዳዎች ብቁ ባለመሆናቸው ካፍ ባሳለፍነው ማክሰኞ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ደብዳቤ በመላክ ማስጠንቀቁን ኢሳይያስ ጂራ ተናግረዋል። ” ከአሁን በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚደረጉ ጨዋታዎችን ወደ ጎረቤት ሀገር እንወስድባለኋን ብሎናል። ባለፈው ማክሰኞ ደብዳቤን ልኮልን ካልጨረሳቹ፤ መስተካከል ያለበትን ማስተካከል ካልቻላችሁ ኢንተርናሽናል ጨዋታን በሀገራችሁ አታደርጉም። ወደ ጎረቤት እንወስድባችዋለን ተብለናል። እኛም ለመንግስት ይህን ጉዳይ አሳውቀናል።” ሲሉ ሀሳባቸውን ጠቅልለዋል፡፡", "passage_id": "d60ea67bc244e4fcf8215555804b6250" }, { "passage": "የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ኢንስትራክተር አብርሃም ተክለኃይማኖት በያዝነው ዓመት በመቐለ የእግርኳስ ትምህርት ቤት ለመክፈት በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ ለሶከር ኢትዮጵያ ገልፀዋል።እንደ አብርሃም ተ/ሃይማኖት ገለፃ ከሆነ ትምህርት ቤቱ የታሰበው ልክ እንደ ቀለም ትምህርት ካሪኩለም ተቀርጾለት በክፍል ውስጥ እና በተግባር ስልጠና በመስጠት ተጫዋቾችን ማብቃት ነው። ” በአሁኑ ሰአት በሀገራችን ያለው የስልጠና አሰጣጥ ስርአት በስልጠና ላይ ሳይሆን በውድድሮች ላይ መሰረት ያደረገ በመሆኑ እኛም ይህንን ለመቀየር ብሎም በታክቲክ አረዳድ እና በቴክኒክ የዳበሩ ተጫዋቾች በመፍጠር ከሌላው አለም ተወዳዳሪ የሚሆኑ ተጫዋቾችን ለመቅረፅ በዝግጅት ላይ ነን። ” ሲሉ አክለዋል።በቀጣይ ከመቐለው ትምህርት ቤት ባለፈ በሙሉ ትግራይ ክልል ፕሮጀክቱን በማስፋፋት በ52 የትግራይ ክልል ወረዳዎች 5000 ህፃናትን አቅፎ ለመሥራት የ5 አመት እቅድ መውጣቱን የገለፁ ሲሆን ለዚህ ፕሮጀክት የሚውል 30 ሚልዮን ብር ድጋፍ ከትግራይ ክልል ጠይቀው መልሱን በመጠባበቅ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል።ኢ/ር አብርሀም ተክለኃይማኖት ከ1990ዎቹ መጀመርያ አንስቶ በጉና ንግድ ፣ ኢትዮጵያ ቡና ፣ መተሀራ ስኳር ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና ደደቢት በአሰልጣኝት የሰሩ ሲሆን ከ5 አመት ወዲህ የታዳጊዎች እግርኳስ ስልጠናዎች ላይ ትኩረት አድርገው እየሰሩ ይገኛሉ።", "passage_id": "0d49550a3f443d4bd50e2272ba62db09" }, { "passage": "¬ – የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ  አቅም ለማጠናከርና የቀጣይ ስራዎቹን በይፋ ለማስጀመር  አካዳሚውን በአዋጁ ቁጥር 783/05 እንዲቋቋምና እንዲጸድቅ መደረጉ  የአካዳሚ  ፕሬዝደንት ፕሮፌሰር ደምሴ  ሀብቴ ገልዋል ፡፡የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ በ2002 ዓ/ም በ49 ምሁራን የተመሰረተ ሲሆን የቴክኖሎጂ ዘርፍ በማጠናከርና በማላመድ ችግር ፈቺ የሆኑ የጥናትና ምርምር ስራዎች በመደገፍ የሀገሪቱን ዘላቂ  ልማትና ኢኮኖሚያዊ እድገት ለማገዝ ያለመ ነው ብለዋል፡፡የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ  ፕሬዝደንት ፕሮፌሰር ደምሴ  ሀብቴ በአካዳሚው የሚካሄዱ ሳይንስና ሳይንሳዊ አሰራር  የሀገሪቱን የወደፊት አቅጣጫ የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት የሚያረጋግጥ ነው፡፡የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር አቶ ደሴ ዳልኬ በአካዳሚው የሚደረጉ ምርምሮች በከፍተኛ ትምህርት ፤ምርምር ተቋማትና በኢንዱስትሪ ማእከላት መካከል ጠንካራ ግንኙነት ለመፍጠር ያግዛል፡፡አካዳሚው ከተለያዩ የሳይንስ ምሁራን ተቀቀሞ መንግስት በሳይንስ፡ቴክኖሎጂና አቬሽን  መስኮች ለሚደረገው ጥናት  አጋዥ ሀይል እንደሚሆንም ገልጸዋል፡፡", "passage_id": "f2b59c9bbdcef5631d9264c4ede9c968" }, { "passage": "በመጋቢት 2009 የተመረቀው የይድነቃቸው ተሰማ አካዳሚን እንዲያስተዳድሩለት የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር የተለያዩ የአውሮፓ ሃገራት የእግርኳስ አካዳሚዎችን ካወዳደረ በኃላ ከስፔኑ ሶክስና የእግርኳስ ማህበር ጋር ዛሬ በሸራተን አዲስ የመግባቢያ ሰነድ ውል ተፈራርሟል፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ለሶክስና የአምስት ዓመት ውል የሰጠ ሲሆን 50 ለሚሆኑ ታዳጊዎች ስልጠናውን በመስጠት ማዕከሉ ወደ ስራ እንደሚገባ ተጠቁሟል፡፡ቅዱስ ጊዮርጊስን፣ ሶክስና እና ኢ ፎር ኢ የተባለ የስፔን ድርጅቶች በኢትዮጵያ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የሚያማክር ድርጅት የመግባቢያ ሰነዱን ዛሬ ፈርመዋል፡፡ በፊርማው ስነ-ስርዓት የቅዱስ ጊዮርጊስ የቦርድ ፕሬዝደንት አቶ አብነት ገብረመስቀል እንደተናገሩት የእግርኳስ አካዳሚ መገንባት የክለባቸው የረጅም ግዜ ምኞት እንደነበር ገልፀዋል፡፡ “ ለኢትዮጵያው ቀደምት ክለብ የወጣቶች አካዳሚ መገንባት ሁሌም ህልማችን ነበር፡፡ ይህ ምሽት ለቅዱስ ጊዮርጊስ ታሪካዊ ነው፡፡ ምክንያቱም አካዳሚያችንን ሶክስና እንዲያስተዳድረው የተስማማንበት እለት ስለሆነ፡፡ ይህ ለኢትዮጵያዊያን ታዳጊዎች ወሳኝ የሆነ ኢንቨስትመንት ነው፡፡ በስፔን እና ኢትዮጵያ መካከል ያለውን ጠንካራ ግንኙነትም የሚያስቀጥል ነው፡፡” ብለዋል፡፡የሶክስና የእግርኳስ ማዕከል ምክትል ፕሬዝደንት ዴቪድ ሎፔዝ በበኩላቸው ውሉ የተሳካ እንዲሆን ያስቻሏቸውን አካላት አመስግነዋል፡፡ “በዚህ ጥሩ ግዜ በመገኘቴ በጣም ደስተኛ ነኝ፡፡ ሶክስና የእግርኳስ አስተዳደር ድርጅት ነው፡፡ በስፔን፣ ቻይና እና ሆንግ ኮንግ ቢሮዎች ያሉን ሲሆን አሁን በቅርቡ በኢትዮጵያም ይኖረናል፡፡ ድርጅታችን በታዳጊዎች ስልጠና ፕሮግራሞች ላይ በልዩነት የሚሰራ ነው፡፡ ለእኛ በኢትዮጵያው ምርጥ ክለብ እንዲሁም በአፍሪካ ከምርጥ ክለቦች ተርታ በሚመደበው ቅዱስ ጊዮርጊስ መመረጥ መቻላችን ትልቅ ክብር ነው፡፡ የዚህ አስገራሚ ፕሮጀክት አካል እንድንሆን ያስቻሉንን ሁሉ ማመስገን እፈልጋለው፡፡ ተስጥኦ ሁሉም ቦታ አለ፤ በኢትዮጵያም ተፈልጎ ለመገኘት የሚገባው ብዙ ተስጥኦ እንዳለ እናምናለን፡፡ የእኛም የመጀመሪያ ስራ እነኚህን ተስጥኦ ያላቸው ታዳጊዎች ከሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች ከኢትዮጵያዊያን አሰልጣኞች ጋር በመሆን የመለየት ስራ ነው፡፡ ለቅዱስ ጊዮርጊስ አካዳሚ የሚሆን የአምስት አመት ስትራቴጂም የምንቀርፅ ነው የሚሆነው፡፡”ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሶክስና እንዲገናኙ ከፍተኛውን ሚና የተጫወተው የስፔኑ ኢንቨስትመንት አማካሪ ድርጅት የሆነው ኢ ፎር ኢ ሲሆን የድርጅቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ሁሊዮ ፓዞ  በንግግራቸው ቅዱስ ጊዮርጊስ ለታዳጊዎች ስልጠና የሚረዳውን አጋር ድርጅት ይፈልግ እንደነበረ ጠቁመው ሶክስና ለዚሁ ብቁ ሆኖ በመገኘቱ ይህ ውል ሊፈፀም እንደቻለ አስረድትዋል፡፡በማድሪድ የእግርኳስ ማዕከል ያለው ሶክስና በቻይና የጉዋንዡ ኤቨርንግራንዴ ክለብን አካዳሚን ማስተዳደር ሲችል በአፍሪካ የታዳጊዎች ስልጠና ፕሮግራም ላይ ሲሳተፍ ይህ ለመጀመሪያ ግዜ ነው፡፡ ለ50 ታዳጊዎች ስልጠናው የሚሰጥ ሲሆን በመጀመሪያው አመት 359ሺ ዩሮ ወጪ ይደረጋል፡፡ በሁለተኛው አመት ወጪው ጨምሮ 679ሺ ዩሮ የሚሆን ሲሆን እንደአካዳሚው የቅበላ አቅም ወጪው እየጨመረ እንደሚመጣ ይጠበቃል፡፡ ከአምስት አመት በኃላ የእውቀት ሽግግር ተደርጎ ኢትዮጵዊያን ባለሙያዎች አካዳሚውን እንዲመሩ እንደሚፈልግ አቶ አብነት ተናግረዋል፡፡ በአካዳሚው እና በቅዱስ ጊዮርጊስ ዋና ቡድን መካከል ስለሚኖረው ግንኙት የሶክስና እና የስፖርት ማህበሩ ውይይት እንደሚያደርጉ ሎፔዝ ጨምረው ገልፀዋል፡፡(ከሶክስና ምክትል ፕሬዝደንት ዴቪድ ሎፔዝ እና ኢ ፎር ኢ ዋና ስራ አስኪያጅ ሁሊዮ ፓዞ ለጋዜጠኞች ስለውሉ እና ተያያዥ ጉዳዮች የሰጡትን ሰፋ ያለ አስተያየት አርብ ይዘን እንመለሳለን፡፡)", "passage_id": "af54f753a1831405052d5ca365f37cbb" } ]
e552a119d538e0aee1a4349307d4b7e4
ef81bfce1f9de777e40845c8eb52b3b8
«የስብሃት ነጋ በቁጥጥር ስር መዋል ትልቅ የፖለቲካ ድል ነው» – አቶ መስፍን ደሳለኝ የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር
እፀገነት አክሊሉአዲስ አበባ፦ ለዚህ ሁሉ መሰሪነትና ለጥፋት ስትራቴጂው ህወሓት ጁንታው አገር እንዲያተራምስ በማድረግ የትግራይ ክልልም አሁን ለገባበት ምስቅልቅል የአቶ ስብሃት ነጋ መሰሪነት ትልቁን ቦታ የሚይዝ በመሆኑ የእርሳቸው በቁጥጥር ስር መዋል ትልቅ ፖለቲካዊ ድል መሆኑን የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አስታወቀ። የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አቶ መስፍን ደሳለኝ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት ፣አቶ ስብሃት ነጋ በውሸትና በወንጀል እንዲሁም ለራሳቸው ከሚገባው በላይ ዋጋ ሰጥተው ሕዝቡ ውስጥ የገቡ ፣ከዛም አልፎ አንዳንዶች እስከማምለክ ድረስ የደረሱላቸው ግለሰብ ናቸው፤ መላው ሕዝብ እንደሚያውቀውም ከነቤተሰባቸው እንደውም እስከ ዘር ማንዘራቸው ስልጣንን ተቆጣጥረው ትግራይን እንዲሁም ኢትዮጵያን በእጅ አዙር ሲመሩ ኖረዋል ።ለእርሳቸውና ለዘሮቻቸው ስልጣን ማራዘሚያም የትግራይ ሕዝብ ትልቅ ማጥ ውስጥ እንዲገባ መገደዱን ያመለከቱት አቶ መስፍን ፣ የግለሰቡ መያዝ የፖለቲካዊ ድል ነው እንደውም እግዚአብሔር አገሪቱን ከከፋ ጥፋት ለመታደግ ያሰበም ይመስለኛል ብለዋል።እንደ አቶ መስፍን ገለጻ ፣ የህወሓት የትግል ታሪክ ሲነሳ መልካም ጎን የነበረው ቢሆንም እንደ አቶ ስብሃት ነጋ ያሉ ጽንፍ የያዙ ሰዎች ትግሉን ወዳልሆነ አቅጣጫ በመምራታቸውና በዓለም ላይ መጥፎ የፖለቲካ ታሪክ ያላቸውን የእነ “ስታሊን” ን አካሄድ በመከተላቸው የመጠፋፋት። የመጠላለፍ ፖለቲካ ውስጥ ገብተው የትግራይ ህዝብ ትግል ፍሬ እንዳያፈራ እንዲሁም አሁን ለገባበት ትልቅ ችግር መንስኤ መሆናቸውን አብራርተዋል።ለዚህ ሁሉ መሰሪነትና ለጥፋት ስትራቴጂው የህወሓት ጁንታ አሁን አገርን ለማተራመስ ለገባበት መንገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደነበራቸው የገለጹት አቶ መስፍን፣ አሁን በቁጥጥር ስር መዋላቸው ደግሞ በትግራይም በመላው አገሪቱም የህወሓት ጁንታ ተመልሳ ትመጣለች በማለት በተስፋ የሚጠብቁ ሞኞች ተስፋቸውን ቆርጠው ወደራሳቸው እንዲመለሱና ሥራቸውን እንዲቀጥሉ እንደሚያደርግም ጠቁመዋል።አቶ ስብሃት ነጋ በጣም ተንኮለኛ። በቀለኛ። በሰፈር የሚያስቡ በአምባገነናዊ ዴሞክራሲ የተሸፈኑ ከመሆናቸውም በላይ የህወሓትንም ታሪክ አበላሽተዋል ያሉት አቶ መስፍን፣ ለዚህ ሁሉ ችግርም ዋናው ተጠያቂና ምክንያት እርሳቸው ናቸው።በመካከላቸው አንዳንድ በአስተሳሰባቸው ሻል ያሉ ችግሩ እዚህ ከመድረሱና ወደጦርነት ከመገባቱ በፊት በሰላማዊ መንገድ እንደራደር የሚል ሃሳብን ሲያቀርቡ ተጽዕኖ በማድረጋቸው ምክንያት ይህ ጦርነት ተጀምሮ የሰው ህይወት ጠፋ ፣ ንብረት ወደመ ብለዋል።አቶ ስብሃት የራሳቸው ቡድን። ኃይል ።ሰላይ ያላቸው በሁሉም ቦታዎች በሃይማኖቱም በባህሉም በታሪኩም ላይ ገብተው የፈለጉትን ነገር የማድረግ አቅም የፈጠሩ ናቸው ያሉት አቶ መስፍን፣ ከዚህ የተነሳ ሰውየውን እንደ አንድ ሰው ብቻ ማሰብ በጣም ከባድ ነው።በቁጥጥር ስር መዋላቸውም ትልቅ ነገር የሚሆነው ከዚህ አንጻር እንደሆነም አብራርተዋል። “የትግራይ ህዝብ ለ 17 ዓመት በዱር በገደሉ ያደረገውን ተጋድሎ ። የገበራቸውን ልጆቹን ደም በከንቱ ያስቀሩ፣ ሁሉንም ድካሙን በዜሮ እንዲባዛ ያደረገው የእኚህ ሰው ሴራና ተንኮል ነው፤ አሁን የችግሩ ምንጭ በመነቀሉ ከዚህ በኋላ ክልሉም ሰላም ሰፍኖበት ወደ ልማትና መልሶ ግንባታው ይገባል “ ብለዋል ።አሁን ከባለፈው ታሪካችን ተምረን ብዙ ነገሮችን ማሻሻል መተው የሚገባን መተው ያለብን ይመስለኛል ያሉት አቶ መስፍን፣ ምክንያቱም የሴራ ፖለቲካ የመጠላለፍና ጥሎ የማለፍ አካሄድ ለእነ አቶ ስብሃት ነጋም እንዳልጠቀመ እየታየ ነው፤ በትግራይም ሆነ በመላው የአገሪቱ ክፍል እኛና እናንተ እየተባለ የሚሄድ ፖለቲካ ከዚህ በኋላ ማብቂያው እንደሚሆን አመልክተዋል ።ጊዜያዊ አስተዳደሩም በመተማመን ላይ የተመሰረተ እንደጀመረው ሁሉን አቀፍ የሆነ፣ ማንንም ያላገለለ እና የጋራ ጥቅምን የሚያስጠብቅ ሊሆን እንደሚገባ አመልክተው ፣ ይህ መሆን ከቻለ ፍትህ ማስፈን። ዴሞክራሲን ማምጣት እንደሚቻል ገልጸዋል ። እኛም እንደ ፓርቲ አንድነቷንና እኩልነቷን አስጠብቃ የምትቀጥል አገር እንድትኖር ጠንክረን እንሰራለን ብለዋል።በቀደመው ጊዜ ከፍተኛ የሆነ ብልሽት ከገጠማቸው ተቋማት መካከል መከላከያ ሰራዊት አንዱ ነበር ያሉት አቶ መስፍን ፣አሁን መከላከያ የታነጸበት አካሄድ በጣም አስገራሚ የአጭር ጊዜ ስራ ውጤት የማይመስል የሕዝብ አለኝታ እንዲሆን ማድረግ ያስቻለ እንደሆነ አስታውቀዋል ።በዚህ የሕግ ማስከበር ዘመቻ ላይም ያሳየው አገር ወዳድነት ፣ቆራጥነትና ለመስዋዕትነት መዘጋጀት አስገራሚ ከመሆኑም በላይ እነዚህን ለሁለት ዓመት ሲዘጋጁ የነበሩ የጥፋት ቡድኖችን ከተቀበሩበት ጉድጓድ በዚህ መልኩ እያደነ ማምጣቱ የሚደነቅ ነው ብለዋል ።በቀጣይም የትግራይን ክልል በማረጋጋት ሰላሙን በማረጋገጥ መልሶ ማቋቋም ላይ ከፍተኛ ድርሻውን እንደሚወጣ ጥርጥር እንደሌላቸው ገልጸዋል።የቀሩት የጁንታው ቡድን አባላትም ከዚህ በኋላ ወዴትም መሄድ ምንም ማድረግ እንደማይችሉ ተገንዝበው በሰላም እጃቸውን ሰጥተው ለፍርድ ቢቀርቡ ለእነሱም መልካም ነው፤ አልያ ግን የተዳፈሩት የመከላከያ ሰራዊት በፍጹም ጀግንነት ከተደበቁበት ጉድጓድ ፈልፍሎ እንደሚያወጣቸው መገንዘብ እንዳለባቸውም አመልክተዋል።አዲስ ዘመን ጥር 2 ቀን 2013 ዓ.ም
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=39214
[ { "passage": "ሕወሓት ትጥቅ ትግል በጀመረበት እኤአ እንደ 1975 ዓ.ም ግድም ትግሉን የተቀላቀሉት ታጋይ አስመላሽ፣ የዐይን ብርሃናቸውን ያጡት በቦምብ ፍንዳታ በደረሰባቸው ጉዳት ነበር፡፡ በቦንብ ፍንጣሪ የተመቱት አምባላጌ ተራሮች ምሽግ ውስጥ ነበር፡፡ ያ የትጥቅ ትግል እንደ አውሮጳዊያኑ በ1991 ዓ.ም ዋና ከተማዋን አዲስ አበባ በመቆጣጠር እና ወታደራዊውን ሥርዓት በማስወገድ ተጠናቋል፡፡ \n\nከዚያ በ1998 (እኤአ) ሕወሃት-መራሹ ኃይል ከኤርትራ ጋር ደም አፋሳሽ የድንበር ጦርነት ሲያደርግ፣ አቶ አስመላሽ የግራ እጃቸውን አጡ፡፡ ያን ጊዜ በትግራይ ክልል ዋና ከተማ መቀለ ነበሩ፡፡ የግራ እጃቸውን ያሳጣቸው የኤርትራ የአየር ድብደባ ነበር፡፡ \n\nሕወሃትን ወደ ሽምቅ ተዋጊነት በመለሰው ያሁኑ ጦርነት ደግሞ፣ ታጋይ አስመላሽ ተገደሉ፡፡ የሕወሃት ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና ከፍተኛ አመራር የነበሩት አስመላሽ የተገደሉት ከቀድሞው የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሥዩም መስፍን እና ከቀድሞው የፌዴራል ጉዳዮች ሚንስትር አባይ ጸሐዬ ጋር ነው፡፡\n\nእነዚህ አመራሮች የተገደሉበትን ወታደራዊ ኦፕሬሽን ያዘዙት የ44 ዐመቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ወደ ከፍተኛው የሥልጣን እርከን እስኪመጡ ድረስ በኢሕአዴግ-መራሹ መንግሥት ውስጥ እምብዛም የማይታወቁ አባል ነበሩ፡፡ \n\nአሁን እሳቸው እና ሕወሓት ጠላቶች ሆነዋል፡፡ ወደ ቀይ ባሕር መውጫ የሆነችውን ኤርትራንና ሱዳንን በመዋሰን ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለውን ትግራይ ክልልን ለመቆጣጠርም እየተፋለሙ ነው የሚገኙት፡፡\n\nየኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የኢትዮጵያን ሠራዊት ለማገዝ ወታደሮቻቸውን እንደላኩ ይነገራል፡፡ አንዳንዶች እንደሚሉት ኢሳያስ ወታደሮቻቸውን የላኩት እንደ አውሮጳዊያኑ አቆጣጠር ከ1998 እስከ 2000 ዓ.ም በተደረገው የድንበር ጦርነት በሕወሃት ክንድ የደረሰባቸውን ውርደት ለመበቀል ነው፡፡ በዚያ ደም አፋሳሽ ጦርነት ያለቁት ሰዎች ብዛት እስከ 100 ሺህ ይደርሳል፡፡\n\nሁለቱም መንግሥታት የኤርትራ ወታደሮች በትግራይ መገኘታቸውን ያስተባብላሉ፡፡ ሆኖም ብዙ የትግራይ ዐይን እማኞች፣ ኤርትራዊያን እንዲሁም የአሜሪካ መንግሥት የኤርትራ ወታደሮች በትግራይ ምድር እንዳሉ ነው የሚናገሩት፡፡\n\nዐቢይ አሕመድ በህወሓት ላይ ድል መቀዳጀታቸውን ያወጁት የትግራይ ዋና ከተማ መቀሌ በተያዘች ማግስት ነበር፡፡ ያንን ተከትሎ ጠቅላይ ሚንስትሩ 250 ሺህ ተዋጊዎች እንደነበሩት የሚነገርለትን የሕወሃት አመራሮች አድኖ የመያዝ ዘመቻ እንደሚቀጥል ቃል ገቡ፡፡ \n\nእጅን ታስሮ እና ተጎሳቁሎ መታየት\n\nሁሉም ከ60ዎቹ ዕድሜ በላይ ናቸው፤ አስመላሽ፣ ሥዩም እና አባይ፡፡ በምን አኳኋን እንደተገደሉ ግን በግልጽ አይታወቅም፡፡ አንዳንዶች ተይዘው እንደተረሸኑ ይገምታሉ፡፡ በመንግሥት በኩል የሚነገረው ግን በአንድ ዋሻ አቅራቢያ እጅ ስጡ ሲባሉ አሻፈረኝ በማለታቸው የተወሰደ ርምጃ እንደሆነ ነው፡፡\n\nየእነዚህ ሦስት ታጋዮች መገደል የተሰማው የህወሃት ከፍተኛ አመራሮች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ተከትሎ ነው፡፡ አቶ ስብሐት ነጋ አንዱ ናቸው፡፡ ስብሃት በካሜራ ፊት እጃቸው ታስሮ እና ተጎሳቁለው የታዩበት ሁኔታ፣ እኤአ በ2003 ሳዳም ሁሴን የተያዙበትን የሚያስታውስ ነው፡፡ \n\nአቶ ፈይሳል ሮቤል መቀመጫውን አሜሪካ ካደረገው የሆርን ኦፍ አፍሪካ ስተዲስ ባልደረባ ናቸው፡፡ እርሳቸው እንደሚሉት የዐቢይ ደጋፊዎች ሀገሪቱን ለ3 ዐሥርት ዐመታት ያህል በጠንካራ ክንዱ የመራው የሕወሃት ባለሥልጣናት በገጠማቸው ዕጣ ፋንታ ደስተኞች ናቸው፡፡ ህወሓት መሪነቱን ያጣው በአገሪቱ ተቃዋሚዎች ሰልፍ ማድረጋቸውን ተከትሎ በመጣ ለውጥ ነው፡፡ ለውጡ ዐቢይን ለሥልጣን አብቅቷቸዋል፡፡ \n\n\"ህወሃትን... ", "passage_id": "5875928a4241772eb79778f975b98865" }, { "passage": "በሙስና ተጠርጥረው የታሰሩት ቀድሞው የኢትዮጵያ የኮሚኒኬሽን ሚንስትር የአቶ በረከት ስምኦን እስር ዜና አሁንም እያነገገረ ነው።አቶ በረከት በገዥው ፓርቲ ውስጥ የነበራቸውንና ለረዥም ዓመታት የዘለቀ ከፍተኛ የፖለቲካ ሚናና የመንግሥት ሥልጣን ተንተርሶ የተለየ ትኩረት የሳበው እስራቸው፤ ከተለያዩ አካባቢዎች በርካታ አስተያየትችን ጋብዟል።ከዚህ ቀደም በትዊተር አማካኝነት ባስተላለፏቸው መልዕክቶች “አቶ በረከት ለፍርድ መቅረብ አለባቸው” የሚል አስተያየት የሰነዘሩት የአውሮፓ ፓርላማ አባሏ ሚስ አና ጎሜሽ የቀድሞው የኢሕአዴግ ባለ ሥልጣን እስር ዜና እንደተሰማ እርምጃውን በማወደስ ፈጥነው አስተያየታቸውን ካሰፈሩት ውስጥ ናቸው።ሚስ አና ጎሜሽ በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት አያያዝና የዲሞክራሲያ ጉዳዮች ዙሪያ ጠንከር ያሉ ትችቶችን በማቅረብም ይታወቃሉ። ይህንኑ አስተያየታቸውን መነሻ በማድረግ ከሚስ ጎሜሽ ጋር የተካሄደ ቃለ ምልልስ ዝርዝሩን ይዟል።“የተከሰሱበትን ጭብጥ ሙሉ በሙሉ ባላውቅም .. በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ በደረሰው በደል፣ በበኩላቸው በፈጸሙት ወንጀል ተጠያቂ ይሆናሉ፤ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ።” የሚሉት ሚስ ጎሜሽ - የኢትዮጵያ ሕዝብ ከዚያ ቀደም ታይቶ በማያውቅ ደረጃ ወጥቶ ድምጹን በሰጠበት፣ የአውሮፓ ሕብረትን በመወከል በታዛቢነት በተሳተፉበት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ወቅት ያዩትን ዋቢ አድርገው፤ ከአቶ በረከት ጋር በቀጥታ የተገናኙባቸውን ጊዜያት ያነሳሉ።በኢትዮጵያ በመጣው “እጅግ አሰደናቂ” ባሉት ለውጥ .. ከሀገራቸው ውጭ ይንቀሳቀሱ የነበሩ ተቃዋሚዎች ወደ ሃገር እንዲገቡ መደረጋቸው፣ የሚያምኑትን በግልጽ መናገር መቻላቸው “አሳድሮብኛል” ያሉትን ትልቅ ተሥፋም ሚስ ጎሜሽ ገልጠዋል። ", "passage_id": "a4d509b25f346dd7a152819f2f96c6d5" }, { "passage": "ዳይሬክቶሩ ይህንን የተናገሩት ዛሬ ማለዳ የፌደራል አቃቤ ህግ የመቶ ቀናት የሥራ አቅጣጫ እና ዕቅድ አስመልክተው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።\n\n•ተጠርጣሪዎችን የመያዝ ዘመቻው ብሔር ላይ ያነጣጠረ ነው? \n\n•ሜጀር ጄኔራል ክንፈ: ‘‘ቤት የለኝም፣ መኪና የለኝም፣ ንብረት የለኝም፤ ያለኝ ሰውነቴ ብቻ ነው’’\n\n•ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው የተሾሙት ለህግ ባላቸው ቀናኢነት መሆኑ ተገለፀ\n\nበቅርቡ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረ ሚካኤል መንግሥት ከሰብዓዊ መብት ጥሰትና ከከፍተኛ ሙስና ጋር በተያያዘ የተጀመረው ዘመቻ በማስመልከት በሰጡት መግለጫ ጉዳዩ ከሰብዓዊ መብትና ሙስና ጥያቄዎች ወጥቶ የትግራይ ህዝብን ወደ መምታት የፖለቲካ እርምጃ ሄዷል ማለታቸው የሚታወስ ነው። \n\nከዚህም በተጨማሪ በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ ሜቴክን አስመልክቶ በተሰራው ዘጋቢ ፊልም የፍርድ ቤቱን ሂደት ያዛባል ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ አቶ ዝናቡ ሲመልሱም ከፍርድ ቤቱ የተለየ ነገር እንዳልቀረበና \"የማንም ስም ማጥፋት አንፈልግም\" ብለዋል። \n\nየሙስናው ምርመራ በሜቴክ ብቻ የሚያቆም ሳይሆን በተለያዩ ሜጋ ፕሮጀክቶች ላይ ምርመራ እንደተጀመረና፤ ምርመራው እንደተጠናቀቀም ለህዝብ እንደሚያሳውቁ የተናገሩት አቶ ዝናቡ አሁን ለእስር መነሻ የሆነው የሙስና ምርመራ ሜቴክ ላይ ብቻ ያለመጀመሩን ገልፀዋል።\n\n\"በሙስና ተጠርጥረው እየተመረመሩ ስላሉ ሜጋ ፕሮጀክቶች በአሁኑ ወቅት ምንም መግለፅ አንፈልግም\" ብለዋል። \n\nከዚህም በተጨማሪ ኤፈርትን በመሳሰሉ ኢንዶውመንቶች ላይ ምርመራ ተጀምሮ እንደሆነ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄም አቶ ዝናቡ ሲመልሱ በኢንዲውመንቶቹ ላይ \"የተጀመረ ምንም አይነት ምርመራ የለም። እነዚህ ኢንዶውመንቶች የተመሰረቱበት ክልል ነው በቀጥታ የሚመለከታቸው\" ሲሉ ተናግረዋል።\n\nከተለያዩ አቅጣጫዎች ድንበር አቋርጠው ወደ ሀገሪቱ የሚገቡ ሕገ ወጥ መሳሪያዎች የመያዛቸው መረጃ መሰራጨት ከጀመረ ውሎ አድሯል።\n\n በተለይም ባለፉት ጥቂት ወራት ባልተለመደ መልኩ መዲናዋ አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ ክልሎች ህገወጥ የመሳሪያ ዝውውር መበራከቱ እየተሰማ ነው። \n\nአቶ ዝናቡ የነዚህ ጦር መሳሪያዎች መበራከት ለውጡን ለማደናቀፍ ያለሙ እንደሆነ ገልፀዋል። \n\nከነዚህ ጦር መሳሪያዎች ጀርባም የተለያዩ ሀገራት፣ ቡድኖችና ግለሰቦች ሀብትን ለማካበት እየተረባረቡ እንደሆነ ተናግረዋል።\n\n የህገወጥ የመሳሪያ ዝውውርን ለመቀነስ ከፌደራል አቃቤ ህግ፣ ፖሊስና ሌሎች የደህንነት ቢሮዎች የተውጣጣ ግብረ ኃይል እንደሚቋቋም ተናግረዋል። ዝውውሩን የተመለከተ ህግ በማርቀቅ ላይ መሆኑንም አክለው ግለፀዋል።\n\nየጥላቻ ንግግር እና የህገ ወጥ የሰው ዝውውር ሌሎች ህግ እየተረቀቀላቸው ያሉ ጉዳዮች ናቸው ተብለዋል። \n\nአቶ ዝናቡ ባለፈው ሐምሌ በተደነገገው የምህረት አዋጅ 584 ግለሰቦች ከወንጀል ነፃ የሆኑበትን የምስክር ወረቅት ወስደዋል ሲሉ ለጋዜጠኞች አስረድተዋል።\n\n ", "passage_id": "6ee0f038231bde1ec261788c21ce452f" }, { "passage": "አዲስ አበባ፡- “ለመላው ኢትዮጵያውያን የመጣው ለውጥ ትግራይ እንዳይገባ ለማድረግ ህወሀቶች አፍነው እየሰሩ ናቸው” ሲሉ የቀድሞ የህወሀት መስራች ዶክተር አረጋዊ በርሄ ለአዲስ ዘመን ተናገሩ። ዶክተር አረጋዊ በርሄ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደተናገሩት “አሁን በአገሪቱ የተከሰተው ለውጥ ጥሩና ተስፋ የሚጣልበትም ነው። በአሁኑ ወቅት ያለው አስተዳደር ስሙ ኢህአዴግ ቢሆንም በርእዮተ አለሙና በአሰራሩ ድሮ ከነበረው የተሻለ ነው። ይህን አመለካከት ይዞ የመጣው የለውጥ ኃይል በሩን ለብዙ ነገሮች ክፍት አድርጎታል። ከዚህ ቀደም ህወሀት ኢህአዴግ ነፍጎት የነበረውን ሃሳብን የመግለጽ፤ የመደራጀትና የመንቀሳቀስ ነጻነትን አጎናጽፎናል። ሃሳብን በነጻነት መግለጽም ሆነ መደራጀት አሁን ላይ ተችሏል” ብለዋል።  አዲስ ዘመን መስከረም 23/2012 ራስወርቅ ሙሉጌታ ", "passage_id": "ed732fb5ce6059294592a0e1476170a2" }, { "passage": " ምህረት\nሞገስ አዲስ\nአበባ፡- የጁንታው\nአመራሮች እና ስትራቴጂስቶች\nመያዝ ለትግራይ ህዝብ\nትልቅ የነፃነት ተስፋ\nያነገሰ መሆኑን የትግራይ\nክልል ብልፅግና ፓርቲ\nፅህፈት ቤት ኃላፊ\nአቶ ነብዩ ስሁል\nአስታወቁ፡፡ የትግራይ ህዝብ\nለዓመታት ስርዓቱ የሚገረሰስ\nበማይመስል ደረጃ\nትልቅ ፕሮፖጋንዳ እየተነዛበትና\nአፈና እየተጫነበት መኖሩን\nአመለከቱ፡፡የጁንታው ቁንጮ አመራርና የጥፋት ስትራቴጂስቱ ስብሃት ነጋ፣ አባይ ወልዱ እና ዶክተር አብረሀም ተከስተን ጨምሮ ዋነኛ የጁንታው አመራሮች መያዛቸውን ተከትሎ፤ አቶ ነብዩ ስሁል ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል እንዳስታወቁት፤ አሁን ላይ የትግራይ ህዝብ ስሜት ደስታና ተስፋ የነገሰበት ነው፡፡ በእርግጥ ከነበረው ፕሮፖጋንዳ አንፃር ነገሮችን ለማመን የተቸገረ ሰው ብዛት ቀላል ባይሆንም፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ በተለይም የጁንታው አመራሮች መያዝ ለውጡን በሙሉ ልብ ወደ መቀበሉ እየሄደ እንዳለ የሚያመላክቱ ማሳያዎች እየበዙ መጥተዋል ብለዋል።የህውሓት አጥፊ ቡድን መሪዎች መያዝ መጀመራቸው ብዙ መልዕክት እንዳለው ያመለከቱት አቶ ነብዩ፤ በዋነኛነት ከህግ አንፃር ሊጠቀስ የሚችለው ማንኛውም እና በየትኛውም ደረጃ ላይ ያለ ሰው ህግ ቢጥስ እና ቢያጠፋ በህግ ፊት የሚቀርብ እና ጊዜ ጠብቆ ተጠያቂነቱ የማይቀር መሆኑን የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ለትግራይ ህዝብ በተለይ ለወጣቱ የለውጥ ምዕራፍ ወለል ብሎ መከፈት መጀመሩን ያበሰረ መሆኑን አመልክተዋል፡፡‹‹ስልጣን ማለት ህዝብን ማገልገያ እንጂ የግል ጥቅም ማስጠበቂያ ርስት አይደለም›› ያሉት አቶ ነብዩ፤ ስልጣንን ከዴሞክራሲያዊነት ውጪ በአምባገነንነት መጠቀም የሚያስከትለው ውርደት መሆኑ ግልፅ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ የህውሓት ሥርዓት ቤተሰባዊ እና አፓርታይዳዊ ነበር፡፡ ስርዓቱ በአገር ደረጃ ከፋፋይ እና አፍራሽ ፖሊሲ በመከተል የግጭት እና የቅሬታ ንግድ ላይ የተመሰረተ የሥልጣን አጠባበቅ ስልት በመተግበር አገር የማፍረስ ተግባር ላይ ተሰማርቶ የቆየ እንደነበርም አስታውቀዋል። ሥርዓቱ በትግራይ ህዝብ ላይም ከፍተኛ አፈና እና በደል ሲያደርስ የቆየ እና የትግራይ ህዝብ የታገለለትን በኢትዮጵያዊነት ጥላ ሥር የፍትሐዊ ተጠቃሚነትና የዴሞክራሲ ዓላማዎችን ወደ ጎን በመተው ቤተሰባዊ እና ከፋፋይ ስርዓት ሲገነባ መቆየቱ መዘንጋት የለበትም ብለዋል፡፡ በመጨረሻም ይህ ቡድን እስከ አሁን ላጠፋው ጥፋት በአሁኑ ጊዜ በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ የሞራል እና የህግ ቅጣት እየተቀበለ የሚገኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የፌዴራል መከላከያ ሠራዊት አገርን ለመበታተን አቅደው በመከላከያ ሠራዊት ላይ ዕርምጃ እንዲወሰድ ያደረጉ አሸባሪዎችና ዋነኛ የጁንታው አመራሮች መካከል ስብሐት ነጋ እና አባይ ወልዱን ጨምሮ ከመከላከያ ከድተው ጁንታውን የተቀላቀሉ ኮሎኔሎች እና ጄነራሎችን እየያዘ ለፌዴራል ፖሊስ በማስረከብ ላይ እንደሚገኝ ይታወሳል፡፡", "passage_id": "01437f9ebaad7f4b709b183778f553bd" } ]
d720d09f1dd8bf4ac343b4b0233a5383
bee57edfd11410b782271f076cd56864
‹‹ለሱዳን ትንኮሳ ቸኩለን ምላሽ መስጠት አይገባንም›› -ዶ/ር ኢንጅነር ጥላሁን ኤርዱኖ የታሪክና የጂኦግራፊ መምህር የነበሩና በአሁኑ ጊዜ በአዳማ ዩኒቨርሲቲ የካርታ ምህንድስና መምህር
ማህሌት አብዱል አዲስ አበባ፡- ሱዳን በኢትዮጵያ ግዛት ላይ ላደረገችው የመሬት ወረራ ትንኮሳ ፈጥኖ የኃይል ምላሽ መሥጠት እንደማይገባ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ መምህር ዶክተር ኢንጅነር ጥላሁን ኤርዱኖ አስታወቁ፡፡ዶ/ር ኢንጅነር ጥላሁን ኤርዱኖ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት፤ የሱዳን ጦር በኢትዮጵያ ግዛት ላይ ለፈፀመው የመሬት ወረራ ቸኩሎ የኃይል ምላሽ መሥጠት ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ያመዝናል። በተለይም ውስጣዊውን ችግር በተሟላ ሁኔታ መፍታት ባልተቻለበት በዚህ ወቅት ወደ ኃይል ምላሹ መግባት አገሪቱን ያላሰበችው አደጋ ውስጥ ሊጥላት ይችላል፡፡እንደእርሳቸው ገለፃ፤ ሱዳንም ሆነች ግብፅ በኢትዮጵያ ላይ እያደረጉት ያሉት ትንኮሳ ዋነኛ አላማ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ለማስተጓጎል ነው፡፡ በተለይም ሱዳን የቅኝ ግዛት ውልን በማጣቀስ ያደረገችው ትንኮሳ ግድቡ የሚገነባበትን አካባቢ ሰላም በማወክ ውሃውን ከግብፅ ጋር ብቻ የመጠቀም ፍላጎታቸውን ለማስቀጠል ከመሻት ነው፡፡ ከትንኮሳ በስተጀርባም የግብፅ ወታደራዊ መንግሥት እጅ ያለበትና ከፍተኛ ድጋፍ የሚደረግለት ነው፡፡ ‹‹የሱዳን ዋነኛ ፍላጎት ቸኩለን እንድንገጥማት ነው›› ያሉት ዶክተር ጥላሁን ይህንን ማድረጉ ደግሞ አገሪቱ ካለችበት ፖለቲካዊ ችግር ጋር ተዳምሮ ከፍተኛ ዋጋ ሊያስከፍል እንደሚችል ሥጋታቸውን ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት የትንኮሳውን ዋነኛ አላማ በመረዳት ትክክለኛውን ጊዜ መጠበቅ እንደሚገባው አመልክተዋል፡፡መላው ኢትዮጵያውያንም እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ ለአገራቸው ሰላም በህብረት መቆም እንደሚገባቸው የተናገሩት ዶክተር ጥላሁን ለዚህ ደግሞ በብሔርና በጎሳ ለመለያየት የሚደረገውን የጠላት ኃይሎች ጥረት እንዳይሰምር በጋራ ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ ዶክተር ጥላሁን እንደሚሉት ጠላቶቻችን ሌላ በጣም ጽንፈኛ የሆነ ጠላት ይፈጥሩልናል እንጂ በፍፁም አይተኙልንም፡፡ ይሄ በግርግር መሬት እናስመልሳለን የሚል ቢሆንም ዋነኛ አላማው ግን ኢትዮጵያን ሰላም በማሳጣት የህዳሴ ግድባችንን ግንባታ ማስተጓጎል ነው፡፡ ሱዳን ሁልጊዜ መሆን የምትፈልገው ከአሸነፈው ጋር ነው፡፡ ኢትዮጵያ የፖለቲካ የበላይነቱን ስትይዝ ኢትዮጵያ ያለችውን ትቀበላለች፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ችግር ሲፈጠር ከግብጽ ጋር ነው የምትጎዳን ብለዋል ዶክተር ጥላሁን፡፡ እንደ ዶክተር ኢንጂነር ጥላሁን ገለጻ፤ የግብፅና የሱዳን መንግሥታት ወታደራዊ ናቸው። የሁለቱም አመራሮች ወደ ስልጣን የመጡት በመፈንቅለ መንግሥት ነው፡፡ ወታደራዊ መንግስቱ ኢኮኖሚውን ይዞ ነው ያለው፡፡ ከጎረቤት ጋር በሰላም መኖር አይችሉም፡፡ ሲቪል መንግሥት እንዲኖር አይፈለግም፡፡ ስለዚህ እነዚህ አገሮች ኢትዮጵያ አንድነቷን ካፀናች በምንም ተዓምር አያሸንፏትም፡፡ ግን እጃቸው ረጅም በመሆኑ ለሰላማችን መደፍረስ የሚመጡበት መንገድ አይታወቅም፡፡የውጭ ጠላቶቻችንን ማሸነፍ የምንችልበትና ያለን ብቸኛ መፍትሔ የኢትዮጵያን ሕዝብ አብሮነት መመለስ ነው ያሉት ዶክተር ጥላሁን፤ በቋንቋም ሆነ በብሔር መከፋፈላችንን ማስቀረት ይገባናል ብለዋል፡፡ ምክንያቱም ቋንቋ ከመግባቢያነት ያለፈ ጥቅም ኖሮት አያውቅም ብለዋል፡፡ሁለቱ አገራት በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የተመሰረተ ፖለቲካ አካሂደው አያውቁም፡፡ ስለዚህ የውስጥ የፖለቲካ ችግር ሲፈጠር የሕዝባቸውን ቀልብ ለመስረቅ ሲሉ ችግራቸውን ለኢትዮጵያ ይሰጣሉ። ሁሉንም ነገር ከአባይ ጋር ያያዙታል። በሱዳን በኩልም በዳቦም ሆነ በሌላ መልኩ የሚነሳውን ሕዝባዊ ተቃውሞ ለማስረሳት ሲሉ ተመሳሳይ ድርጊት ይፈፅማሉ ብለዋል ዶክተር ኢንጂነር ጥላሁን፡፡ይሁንና አሁን ከያዙት መሬት በተጨማሪ ገፍተው እንዳይመጡ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በተጠንቀቅ ሊቆምና ዳር ድንበሩን ማስጠበቅ እንደሚገባው ዶክተር ኢንጂነር ጥላሁን አስገንዝበዋል፡፡ በተጨማሪም መንግሥት ግድቡ በሚገነባበት ቤኒሻንጉል ክልል አስተማማኝ ሰላም በመፍጠር የወራሪዎቹ አገር የማተራመስ አጀንዳ ከግቡ እንዳይደርስ ሚናውን እንዲወጣ አሳስበዋል።ከዶክተር ኢንጂነር ጥላሁን ኤርዱኖ ጋር የተደረገውን ሙሉ ቃለምልለስ ገጽ 6 ላይ ይከታተሉ።
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=39157
[ { "passage": "አቶ ውሂብ ኢትዮጵያ ከሱዳን ጋር ያለውን የድንበር አለመግባባት ውዝግብ በውይይት ብቻ ለመፍታት ጥብቅ ፍላጎት እንዳላት ለቢቢሲ ገልፀዋል።\n\nሱዳንም ብትሆን እስካሁን ድረስ በሁለትዮሽ ንግግር የሚል ሃሳብ ብቻ እንዳላቸው የሶስተኛ ወገን አደራዳሪነትን እንዲኖር አለማቅረባቸውን ተናግረዋል።\n\nሁለቱን አገራት ለማስታረቅና ለማሸማገል የተለያዩ አካላትም ጥረት እያደረጉ መሆናቸው የተነገረ ሲሆን ጉዳዩ ያሳሰባት የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ኢትዮጵያና ሱዳን ያላቸውን የድንበር ላይ ውዝግብ በሰላማዊ መንገድና በውይይት እንዲፈቱ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል ባወጣችው መግለጫ ጠይቃለች።\n\nየሰሜን ጎንደር አስተዳዳሪና ነዋሪዎች የሱዳን ሠራዊት ወረራ ፈጽሞበታል ወደ ሚባሉት ስፍራዎች ዘልቆ መግባት የጀመረው በአካባቢው የነበረው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ወደ ትግራይ ክልል መንቀሳቀስ ከጀመረ በኋላ በጥቅምት 29 2013 ዓ.ም እንደሆነ ለቢቢሲ ተናግረው ነበር።\n\nበድንበር አካባቢ ያለውን አለመግባባት በተመለከተ ጉዳዩ በሁለቱ አገራት መንግሥታት አማካይነት በሠላማዊ መንገድ እንደሚፈታና ለዚህም ጥረት እያደረገች እንደሆነ ኢትዮጵያ ስትገልጽ ብትቆይም ሱዳን ግን የያዘችውን መሬት ለቅቃ እንደማትወጣ ገልጻለች።\n\nኢትዯጵያ በበኩሏ ሱዳን በኃይል የያዘችውን መሬት ለቅቃ እስካልወጣች እንድትወጣ ቅድመ ሁኔታ ያስቀመጠች ሲሆን ይህ ተግባራዊ ካልሆነ ድርድር እንደማይኖር መግለጿ ይታወሳል።\n\nየኢትዮጵያና ሱዳንን የድንበር ጉዳይ መፍታት የሚቻለው ሁለቱ ሀገሮች ባቋቋሟቸው መዋቅሮች ብቻ መሆኑን አቶ ውሂብ ገልፀዋል።\n\nየድንበሩ ሁኔታ እስኪፈታ ድረስ ግን ኢትዮጵያና ሱዳን የፈረሟቸው ስምምነቶች ተከብረው መቆየት እንዳለባቸው አቶ ውሂብ አፅንኦት ይሰጣሉ።\n\n\"የኢትዮጵያን ሕልውና የሚጻረሩ ኃይሎች መኖራቸውን እናውቃለን\" ያሉት አቶ ውሂብ \" ሌላ ሶስተኛ አካል ሊኖር ይችላል\" ሲሉ ተናግረዋል።\n\nከኢትዮጵያ በኩል ሶስተኛ አካል ሊኖር ይችላል የሚሉ ንግግሮች ቢሰሙም ሶስተኛ ወግን የተባለው እስካሁን በስም አልተጠቀሰም።\n\nሆኖም እነዚህን ኃይላት በመጋበዝ በዚህ የድንበር ውዝግብ ውስጥ ሚና እንዲኖራቸው ማድረግ ኢትዮጵያ እንደማትፈልግ አክለው ያስረዳሉ።\n\nበተለያዩ ጊዜያት በሁለቱ ሀገራት መካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት እኤአ 1972 የሀሳብ ልውውጥ ስምምነት ተፈራርመው ድንበራቸውን እንደገና ለማካለል መስማማታቸውን አቶ ውሂብ ለቢቢሲ ገልፀዋል።\n\nበስምምነቱ መሰረት ሁለቱ ሀገራት የሚቀበሉት የመፍትሔ ሀሳብ ላይ እስኪደርሱ ድረስ የድንበር ነባራዊ ሁኔታው ባለበት ተከብሮ እንዲቆይ መስማማታቸውን አመልክተዋል።\n\nበ1972 ዓ.ም የተደረሰው ስምምነት በተባበሩት መንግሥታት የተመዘገበ መሆኑን በማንሳት፣ ይኸው ስምምነት ተግባራዊ እንዲሆንና ጦርነት እንደማያስፈልግ ኢትዮጵያ ለሱዳን ማስረዳቷን ይገልጻሉ።\n\n\"የጦር ፍላጎት በኢትዮጵያ ዘንድ የለም\" የሚሉት አቶ ውሂብ ሁለቱ ሕዝቦች በተለያየ ነገር እንደሚተሳሰሩ ተናግረዋል።\n\nየትኛውም ጦርነት ሲያልቅ ወደ ጠረጴዛ ዙሪያ እንደሚመጣ በማስታወስ፣ ከጦርነት አማራጭ ይልቅ ልዩነቶችን በመነጋገር መፍትሔ መስጠት የተሻለ መሆኑን አክለዋል።\n\nበአፄ ኀይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት ኢትዮጵያ ከኬንያ ጋር ያላትን የድንበር ጉዳይ በጋራ መፍታቷን ያነሱት አቶ ውሂብ፣ የድንበሩን አለመግባባት ለመፍታት ሶስተኛ ወገን አስፈላጊ አይደለም ብለዋል።\n\nበድንበሩ አካባቢ አሁንም አልፎ አልፎ ተኩስ እንደሚሰማ የገለፁት አቶ ውሂብ፣ ይህ ጉዳይ እንዲቆም ኢትዮጵያ መናገሯን ገልፀዋል።\n\nአቶ ውሂብ ሁለቱ አገራት የሚያደርጉት ውይይት መች ሊቀጥል ይችላል ተብለው ከቢቢሲ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ሱዳን እና ኢትዮጵያ በድንበር ጉዳይ... ", "passage_id": "6a67688c1ee3632f4b304e16f06a26e4" }, { "passage": "ባሕር ዳር፡ ግንቦት 07/2012 ዓ.ም (አብመድ) የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት እየገጠመው ያለውን ጂኦ-ፖለቲካል ውጥረት ለመፍታት የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲ በተመለከተ አብመድ ከኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዲፕሎማት አቶ ዘሪሁን አበበ ጋር ቆይታ አድርጓል፡፡እንደዲፕሎማቱ ማብራሪያ ኢትዮጵያ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ እየተተገበሩ ያሉ መሠረታዊ መርሆዎችን መሠረት አድርጋ ግድቧን እየሠራች አሁን ካለበት የግንባታ ደረጃ ደርሳለች፡፡ ከድህነት ለመውጣት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ እየገነባች መሆኗን ለዓለም ሕዝብ ስታሳውቅ ቆይታለች፤ አሁንም ማሳወቋን ቀጥላለች፡፡እስካሁን በነበሩት ሂደቶች ግድቡ እውን እንዳይሆን የተለያዩ ጫናዎች ከየአቅጣጫው ሲሰነዘሩ እንደነበርም ዲፕሎማቱ ጠቅሰዋል፡፡ ጫናዎቹ የግድቡን ግንባታ ለአፍታም እንዲቆም አላደረጉትም፤ ይህ የሀገሪቱን የስኬት ጉዞ የሚያሳይ ትልቅ ድል መሆኑን በመጥቀስ፡፡ “ውጤቱ ዝም ብሎ የተገኘ አይደለም፤ በአንድም በሌላ መልኩ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ እየተከተለች ያለችው የዲፕሎማሲ ስልት ያስገኘው ነው” ብለዋል አቶ ዘሪሁን አበበ፡፡እንደዲፕሎማቱ ገለጻ ኢትዮጵያ ቸርም ስለሆነች፣ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋም በመጠቃቀም ላይ የተመሠረተ በመሆኑ “ብቻየን ልልማ” አላለችም፡፡ ከታችኞቹ ሀገራት ጋር በጋራ ለመልማት አማራጭ አስቀምጣለች፡፡ ግብፅ ይህን አላደረገችውም፡፡ የዓባይን ወንዝ ተጠቅማ እስከዛሬ በገነባቻቸው ግድቦች በረሃዋን ወደ ገነት ስትቀይር በድህነት ውስጥ ያለችውን ኢትዮጵያን አላማከረቻትም፡፡ ይህን የዓለም ሕዝብ ጠንቅቆ ያውቃል፤ እንዲያውቅም ለማድረግ እየተሠራ ነው፡፡በመሠረቱ በዓለም ድንበር ተሻጋሪ ወንዝ ያላቸው ሀገራት እየተከተሉት ካለው ስልት አንጻር ሲታይ ኢትዮጵያ ለጋራ ተጠቃሚነት እያሳየች ያለችው የዲፕሎማቲክ ግንኙነት የተሻለ ነው፡፡ ድንበር ተሻጋሪ ወንዝ ያላቸው አብዛኞቹ ሀገራት የየራሳቸውን የቤት ሥራ ነው የሚሠሩት፡፡ ኢትዮጵያ ግን የግድቡን የጥናት ሰነዶች ሁሉ በማጋራት ከተፋሰሱ ሀገራት ጋር እየሠራች መሆኑን አብራርተዋል፡፡ አቤቱታ የሚያቀርቡ ሀገራት ኃላፊነት የተሞላበት የሀገሪቱ የዲፕሎማሲ አሠራር ማሳያ አድርገው ሊውስዱት እንደሚገባም አቶ ዘሪሁን አበበ ጠቅሰዋል፡፡“ኢትዮጵያ ‘ድንበር ተሻጋሪ ወንዝ ያለው ሀገር ፍትሐዊ በሆነ መልኩ ይጠቀም፤ በሌላውም ላይ ጉልህ ጉዳት አያድርስ’ በሚለው የዓለም ልማዳዊ ሕግ መሠረትም ነው ግድቡን እየገነባች የምትገኘው፡፡ በጀመረችው አግባብም ሀብቷን መጠቀም ትቀጥላለች፤ ሀቁ ይህ ነው” ብለዋል አቶ ዘሪሁን፡፡\nበራሷ አቅም፣ ያለማንም የገንዘብ ድጋፍ እየገነባች ያለችውን ግድብ አስመልክቶ ከሁለቱ የግርጌ ተፋሰስ ሀገራት መተማመንን ለማጎልበት ረዥም ርቀት መሄዷንም ጠቅሰዋል፡፡ “በወርኃ መጋቢት 2007 ዓ.ም ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብፅ በመሪዎች ደረጃ በሱዳን ያካሄዱት የጋራ የመሪዎች መግለጫ ስምምነት የጥረቱ ማሳያ ነው፡፡ ስምምነቱን ሁለቱም ሀገራት አውቀውት፣ ጉዳዩን አምነውበት የተካሄደ በመሆኑ የግንባታውን ቀጣይነት ሊያከብሩት ይገባል፡፡ አምነውም ገብተውበታል፡፡ ግንባታ ኮንክሪት መደርደር ብቻ ሳይሆን ሙሌቱንም እንደሚጨምር መረዳት ደግሞ ተገቢ ነው” ብለዋል፡፡\nእንደ አቶ ዘሪሁን ገለጻ የኢትዮጵያ በመጠቃቀም ላይ በተመሠረተ የግንኙነት መርህ፣ ማንም ሳይጎዳ በራስ ሀብት የራስን ችግር ለመቅረፍ እየተደረገ ያለው የዲፕሎማሲ አካሄድ ትክክለኛ ነው፡፡ ኢትዮጵያ በራሷ ግዛት፣ የራሷን ውኃ፣ ለዚያውም ለታችኞቹ ሀገራት ተመልሶ ጥቅም የሚሰጥ የኃይል ማመንጫ ግድብ “አትሞይም” የሚላት ሕግ የለም፡፡የኢትዮጵያ መንግሥት በመጭዎቹ የክረምት ወራትም የመጀመሪያውን ዙር የግድቡን የውኃ ሙሌት እንደሚጀምር አሳውቋል፡፡ የግድቡ ግንባታ ሂደት እስከቀጠለ ድረስ የውኃው ተፈጥሮሯዊ ሂደት በመጭው ሐምሌ ግድቡ በውኃ መሞላቱም አይቀሬ ነው፡፡ዓለም ተገልብጦ ከኢ-ፍታዊነት ጋር እስካልቆመ ድረስ ለኢትዮጵያ ስጋት ነው የሚባል ነገር እንደሌለም አቶ ዘሪሁን ጠቅሰዋል፡፡ “የሚያጋጥሙ ችግሮችም ቢኖሩ ባሉት የሕግ ማዕቀፎች ሁሉም እየተፈቱ መሄዳቸውን ይቀጥላሉ፡፡ ኢትዮጵያም የዓባይን ውኃ በፍትሐዊነት መጠቀሟን ትቀጥላለች” ሲሉ የቀጣይ አቅጣጫዎችን ጠቁመዋል፡፡", "passage_id": "0030f9136354c1ba10518e32146c1301" }, { "passage": "ዋቅሹም ፍቃዱ አዲስ አበባ፦የኢትዮ – ሱዳን ድንበር ግጭት ሱዳን መንግሥትና ሰፊው የሱዳን ህዝብ ፍላጎት እንዳልሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ አስታወቁ። ግጭቱ ለማንም እንደማይበጅ የኢትዮጵያ አቋም መሆኑንም አመለከተዋል።አምባሳደር ዲና ሙፍቲ\nበግጭቱ ዙሪያ በተለይ\nለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት፣\nየኢትዮጵያና የሱዳን ድንበር\n100 ዓመት ያስቆጠረ ቢሆንም\nበሌሎችም የአፍሪካ አገራት\nእንደሚታየው ከቅኝ ገዥዎች\nየተወረሱ ችግሮች መኖራቸውን\nጠቁመዋል። ኢትዮጵያ\nበቅኝ ገዥዎች ባትገዛም\nሱዳን በቅኝ ግዥዎች\nስር ስለነበረች፣ ድንበሩ\nምንም እንኳ ምልክቶች\nቢኖሩትም በዘመናዊ ዘዴ\nበትክክል ባለመካለሉ አንዳንዴ\nበሁለቱም አገሮች የድንበር\nአካባቢዎች መገፋፋቶች ይፈጠራሉ\nብለዋል፡፡ አሁን ያለው ድንበር ባህላዊ መሆኑን ጠቁመው፣ ሰሞኑን የሱዳን ኃይሎች ኃላፊነት በጎደለው መልኩ የኢትዮጵያን መሬት መያዛቸው ስህተት መሆኑ እንዳለ ሆኖ አንዳንድ የሱዳን ሚዲዎችና ባለስልጣናት መሬታቸውን እንዳስመለሱ አድረገው በመግለጫ የሚያሰራጩት መረጃ ተቀባይነት የሌለውና ህገ ወጥ መሆኑ አስታውቀዋል።አንዳንድ የሱዳን ባለስልጣናት\nከኋላ ሆነዉ ጉዳዩን\nለሚያቀጣጥሉ የኢትዮጵያ ጠላቶች\nመጠቀሚያ ሆነው ቢያገለግሉም፣\nየኢትዮጵያ መንግሥት ግን\nግጭቱ የሱዳን ህዝብና\nመንግሥት ፍላጎት ነው\nየሚል መደምደሚያ ላይ\nእንዳልደረሰ ገልጸዋል። ይልቁንስ መጠቀሚያ እየሆኑ ያሉ የሱዳን ባለስልጣናት ድርጊታቸው ሱዳንንም ሆነ ኢትዮጵያን በፍጹም ስለማይጠቅም ያሉትን ችግሮች በሰላማዊና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንዲፈታ የኢትዮጵያ መንግሥት እያሳሰበ መሆኑን ገልጸዋል። ድንበሩም በድንበር ኮሚሽን መርሆዎች ብቻ እንዲፈታም የኢትዮጵያ አቋም እንደሆነም አስታውቀዋል። ግጭቱ የሱዳን መንግሥትና\nየሱዳን ህዝብ ፍላጎት\nእንዳልሆነ የሚገልጹ “እኛ\nከኢትዮጵያ ጋር ፈጽሞ\nወደ ግጭት አንገባም”\nየሚሉ ድምፆች እየጨሩ\nመምጣታቸውን የጠቆሙት አምባሳደር\nዲና፣ ከበስተጀረባው ግን\nየተለያዩ ኃይሎች እንዳሉ\nጠቁመዋል። እነዚህ ኃይሎች ለዘመናት ያልጠቀሟትን ሱዳን ወዳጅ በማስመሰል የጥፋት አጀንዳቸውን ለማሳካት እየታተሩ እንደሚገኙ ጠቁመው ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ለሰላም ወዳዱ የሱዳን ህዝብ እና ባለስልጣናት ፣ እንዲሁም ለሰላም ወዳዱ የአረቡ ማህበረሰብ ፣ ግጭቱ ለማንም እንደማይበጅ በተጨባጭ እያሳወቀች መሆኑን አመልክተዋል። አንዳንድ የሱዳን ወታደሮችና ሚሊሻዎች ሰሞኑን የኢትዮጵያን ድንበር ጥሰው በመግባት የሰው ህይወት ማጥፋታቸውና ንብረት ማውደማቸውን አመልክተው፣ መንግሥትም ጸጥታን ከማስከበር ጎን ለጎን ችግሩ በድርድር እንዲፈታ እየሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ\n25/2013", "passage_id": "06fd77b56a8fea2ddeaf152578413b6c" }, { "passage": "የሱዳን ጦር ቃል አቀባይ አሚን መሀመድ ሐሰን(ዶ/ር) ከኃላፊነታቸው መነሳታቸውን የተለያዩ የሱዳን መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል፡፡\nቃል አቀባዩ ለመገናኛ ብዙሃኑ በላኩት መልእክት በስራቸው ላይ በነበሩበት ወቅት ሚዲያዎች አደረጉልኝ ላሉት ድጋፍ አመስግነዋቸዋል፡፡ ከኃላፊነት መነሳታቸውም የወታደራዊ ስራ ባህሪይ መሆኑን የገለጹት ቃልአቀባዩ “ሁሌም መቀያየር ያለ ነው” ብለዋል፡፡\nከኃላፊነት የተነሱት ቃል አቀባይ “ማንም ሙሉ ሰው የለም፤ ፈጣሪ ብቻ ነው ሙሉ” የሚል መልእክትም አስተላልፈዋል፡፡\nቃል አቀባዩ አሚን መሀመድ ሐሰን(ዶ/ር) ሰሞኑን በኢትዮጵያናሱዳን ድንበር አዋሳኝ አካባቢ ተከስቶ የነበረውን ግጭት አስመልክቶ ተከታታይ መግለጫ ሲሰጡ ነበር፡፡ ቃል አቀባዩ ሰጥተውት በነበረው መግለጫ “የኢትዮጵያ ታጣቂዎች” በመከላከያ በመታገዝ በሱዳን ወታደሮችና በሱዳን ዜጎች ላይ ጥቃት አድርሰዋል የሚል ክስ በከፍተኛ ድምጸት በሀገሪቱ ሚዲያዎች በኩል መግለጫ ሲሰጡ ነበር፡፡\nየቃልአቀባዩ ከስልጣን መነሳት ሰሞኑን ከሰጡት መግለጫ ጋር ይያያዝ ወይንም አይያያዝ የታወቀ ነገር የለም፡፡\nየኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በበኩል ሁለቱን ሀገራት ወደ ግጭት የሚወስድ ምንም ምክንያት እንደሌላ ገልጾ፣ በግጭቱ በሁለቱም በኩል ህይወታቸውን ላጡ ዜጎች ማዘኑን በትናንትናው እለት ገልጿል፡፡\nአሁን ላይ የሁለቱም ሀገራት ህዝቦች ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴያቸውም መመለሳቸውንም ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡\nሱዳን ኢትዮጵያና 1600 ኪ.ሜ የሚረዝም የየብስ ድንበር ይጋራሉ፤ በመካከላቸው ያለው ድንበር መሬት ላይ ተለክቶ አልተካለለም፡፡\n", "passage_id": "f44bc233041783bef73def656d0d1f4f" }, { "passage": "በኢትዮጵያና በሱዳን ድንበር ለዘመናት በቆየው ውዝግብ ምክንያት በሁለቱ አገራት ሠራዊቶች መካከል የሚደረግ ግልጽ ወታደራዊ ግጭት ከዚህ በፊት እምብዛም አጋጥሞ ባያውቅም በቅርቡ በድንበር አካባቢ የታየው ሁኔታ ግን ነገሮች እየተቀየሩ መሆናቸውን ያመለክታል። የቅኝ ግዛት ስምምነቶች 'ድብቅ ስምምነት'ግዛት ይገባኛል ተቃዋሚዎችን መደገፍ ለዚህ ችግር ቀዳሚ ምክንያት የሰሜን ምዕራብ የኢትዮጵያ ግዛት ከሆነው ከአማራ ክልል ጋር በሚዋሰነውና የሱዳን የዳቦ ቅርጫት ተብሎ በሚጠራው የገዳሪፍ ግዛት ውስጥ በሚገኘው አል ፋሻጋ አካባቢ የግዛት ይገባኛል ነው። ሁለቱን አገራት የሚለየው ድንበር መልክአ ምድራዊ አቀማመጦችን በመጥቀስ ከሚገለጸው ውጪ በመሬት ላይ በግልጽ ተለይቶ የተካለለ አይደለም። በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ድንበሮች በጣሙን አወዛጋቢ ናቸው። ከአስርት ዓመታት በፊት ኢትዮጵያ ከሶማሊያ ጋር በኦጋዴን የተነሳ ጦርነት አድርገዋል። እንዲሁም ከ20 ዓመታት በፊት ደግሞ በትንሿ ባድመ ይገባኝል ምክንያት ኢትዮጵያና ኤርትራ ጦርነት ውስጥ ገብተው ነበር። በጦርነቱ 80 ሺህ የሚደርሱ ወታደሮች መሞታቸው የሚነገር ሲሆን በዚህም ምክንያት በሁለቱ አገራት ፍጥጫ ውስጥ ቆይተዋል። በተለይ ደግሞ ዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት ለኤርትራ ከወሰናቸው ግዛቶች ኢትዮጵያ ለመውጣት ፈቃደኛ ባለመሆኗ አለመግባባቱ ለዓመታት ቆይቷል። እነዚህ ቦታዎች በዚህ ዓመት በትግራይ ውስጥ የተቀሰቀሰውን ውጊያ ተከትሎ የኤርትራ ወታደሮች መልሰው ተቆጠጥረዋቸዋል።ከዓመታት በፊት ኢትዮጵያና ሱዳን ለረጅም ጊዜ ተቋርጦ የነበረውን 744 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውን ድንበራቸውን ለይቶ ለማመላከት የሚያስችል ንግግርን መልሰው ጀመሩ።በዚህ መፍትሄ ለመስጠት አስቸጋሪ የሆነው አካባቢ ፋሽጋ የሚባለው ነበር። በ1902 እና በ1907 (እአአ) የነበረው የቅኝ ግዛት ስምምነት መሰረት ዓለም አቀፉ ድንበር ወደ ምሥራቅ ይዘልቃል። በዚህም ሳቢያ መሬቱ ወደ ሱዳን የሚካተት ይሆናል። ነገር ግን ቦታው ኢትዮጵያውያን የሚኖሩበት ሲሆን የግብርና ሥራ በማከናወንም የሚጠበቅባቸውን ግብር ለኢትዮጵያ መንግሥት ሲከፍሉ ቆይተዋል። ሁለቱ አገራት ሲደረጉ በነበረው የድንበር ድርድር አማካይነት በ2008 (እአአ) ላይ ከመግባባት ደረሱ። በዚህም ኢትዮጵያ ለሕጋዊው ድንበር ዕውቅና ስትሰጥ ሱዳን ደግሞ ኢትዮጵያውያኑ በስፍራው ያለችግር ሕይወታቸውን እንዲቀጥሉ ፈቀደች። ይህም አስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በድንበር አካባቢ ያሉ የነዋሪዎችን ህይወት ሳያደናቅፍ ኢትዮጵያ ግልጽ የድንበር መለያ እንዲኖር እስክትጠይቅ ድረስ ቀጥሎ ነበር።በሁለቱ አገራት መካከል ከስምምነት የተደረሰበትን የዚህ የድርድር ልዑክ የተመራው የህወሓት ከፍተኛ ባለስልጣን በሆኑት በአባይ ፀሐዬ ነበር።ህወሓት ከማዕከላዊው መንግሥት ስልጣን ሲወገድ የአማራ ብሔር መሪዎች ከሱዳን ጋር የተደረሰው ስምምነት በአግባቡ ሳያውቁት የተደረገ ድብቅ ውል ነው ሲሉ ተቃውመውታል። በአሁኑ ጊዜ በፋሽጋ አካባቢ ለተከሰተው ግጭት ሁለቱም ወገኖች የየራሳቸውን ምክንያት ያቀርባሉ። ነገር ግን የተከሰተው የሚያከራክር አይደለም፤ በዚህም የሱዳን ሠራዊት ኢትዮጵያዉያኑን ከሚኖሩባቸው መንደሮች ለቀው እንዲወጡ አድርጓል። በቅርቡ ጂቡቲ ውስጥ በተካሄደው ቀጠናዊ የኢጋድ ጉባኤ ላይ የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሐምዶክ ጉዳዩን ከኢትዮጵያው አቻቸው ዐብይ አህመድ ጋር አንስተው ተወያይተዋል። ስለድንበሩ ጉዳይ ድርድር ለማድረግ ቢስማሙም ሁለቱም የየራሳቸውን ቅድመ ሁኔታ አስቀምጠዋል። ኢትዮጵያ በድንበር አካባቢ ጉዳት የደረሰባቸውን ማኅበረሰቦች ሱዳን እንደትክስ ስትጠይቅ፤ ሱዳን በበኩሏ ነገሮች ወደ ነበሩበት እንዲመለሱ ትፈልጋለች። በበርካታ የድንበር ውዝግቦች ውስጥ እንደሚያጋጥመው ሁሉም ወገን የተለያየ የታሪክ፣ የሕግና ለዘመናት የቆዩ ስምምነቶችን እንዴት መተርጎም እንዳለባቸው የየራሱ ትንታኔ አለው። ነገር ግን ይህ የሁለት ጉዳዮች ማሳያ ምልክት ነው፤ ይህም ከጠቅላይ ሚኒስርት ዐብይ የፖሊሲ ለውጥ ጋር የሚያያዝ ነው። በፋሽጋ አካባቢ የሚኖሩት ኢትዮጵያውያን የአማራ ብሔር አባላት ናቸው። ይህም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአገሪቱ ትልቁ ከሆነው የኦሮሞ ብሔር በኩል የነበራቸው ድጋፍ በከፍተኛ ደረጃ በመቀነሱ የፖለቲካ ድጋፍ ለማግኘት ትኩረት ያደረጉበት ማኅበረሰብ ነው። አማራ በአገሪቱ ሁለተኛው ትልቁ ብሔር ሲሆን በአገሪቱ የመሪነት ስፍራም ታሪካዊ ስፍራ አለው። ከወር በፊት የፌደራል መንግሥቱ በትግራይ ክልል በህወሓት ኃይሎች ላይ ድል መቀዳጀቱን ተከትሎ የአማራ ክልል የግዛት ይገባኛል ጥያቄን እያነሳ ነው። የህወሓት ኃይሎች ሽንፈት ሲገጥማቸውና የአማራ ክልል ሚሊሻ ጥያቄ የተነሳባቸውን አካባቢዎች ሲቆጣጠር የራሱን ባንዲራ በመስቀል \"ወደ አማራ ክልል እንኳን ደህና መጡ\" የሚሉ የመንገድ ምልክቶችን አስቀምጧል። ቦታዎቹ በአማራ ክልል ጥያቄ የሚቀርብባቸው ሲሆን ወደ ትግራይ ክልል የተጠቃለሉት ህወሓት ስልጣን በያዘበት ጊዜ ነበር። ምንም እንኳን ጉዳዩ የውስጣዊ የድንበር ጉዳይ ሳይሆን ከጎረቤት አገር ጋር ያለ የግዛት ጉዳይ ቢሆንም፤ የፋሽጋው ግጭትም ተመሳሳይ የግዛት ይገባኛል ጥያቄን የተከተለ ነው። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ የውጭ ግንኙነት የፖሊሲ ለውጥ ችግሩ በሰላማዊ መንገድ እንዳይፈታ ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ ምክንያት ሆኗል። ለ60 ዓመታት የኢትዮጵያ ስትራተጂካዊ ዓላማ ግብጽን መግታት ላይ ያተኮረ ነበር። ነገር ግን ከዓመት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የወዳጅነት እጃቸውን ዘርግተዋል። ኢትዮጵያና ግብጽ የአባይ ወንዝን የህልውናቸው ጥያቄ አድርገው ይመለከቱታል። ግብጽ በቅኝ ግዛት ዘመን ተቀመጡ ስምምነቶችን መሠረት አድርጋ በላይኛው የተፋሰሱ አገራት ውስጥ የሚገነቡ ግድቦች በውሃ ድርሻዋ ላይ የተጋረጡ አደጋዎች እንደሆኑ ትመለከታቸዋለች። ኢትዮጵያ ደግሞ የአባይ ወንዝን ለምታደርገው የኢኮኖሚ ልማት በጣሙን አስፋላጊ ለሆነው የኤሌክትሪክ ኃይል ዋነኛ ምንጭ አድርጋ ትመለከተዋለች። በግዙፉ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ ውዝግብ የተነሳውም በዚህ ሳቢያ ነው። የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለሚያካሂደው የውሃ ዲፕሎማሲ ዋነኛው መሰረቱ በቀሪዎቹ የአባይ ወንዝ የላይኛው ተፋሰስ የአፍሪካ አገራት መካከል ተፈጥሮ የነበረው የትብብር መዋቅር ነበር። ዓላማውም በርካታ አገራትን ያካተተ በአባይ ወንዝ የውሃ ክፍፍል ላይ አጠቃላይ ስምምነት መድረስ ነበር። በዚህ መድረክ ላይም ግብጽ በቁጥር ተበልጣ የበላይነትን ማግኘት አልቻለችም። ህዳሴው ግድብም ጎርፍን በመቆጣጠር፣ የመስኖ ልማቷን በመጨመርና ርካሽ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማግኘት እንደሚያስችላት በመረዳት፤ ሱዳንም ከቀሪዎቹ የአፍሪካ አገራት ወገን ተሰልፋ ነበር። ግብጽ ግን በቅኝ ግዛት ዘመን ስምምነት ላይ የተቀመጠውን አብዛኛውን የአባይ ወንዝን ውሃ ለማግኘት የሚያስችላትን ጥቅም ለማስከበር ቀጥተኛ የሁለትዮሽ ድርድር ፈልጋ ነበር። በጥቅምት ወር 2012 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስርት ዐብይ በሩሲያ አፍሪካ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ወደ ሩሲያ ሶቺ በሄዱበት ጊዜ ከግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱል ፋታህ አልሲሲሰ ጋር ተገናኝተው ነበር። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባለስልጣናት ባልተገኙበት በዚህ ውይይት ኢትዮጵያ በአባይ ውሃ ላይ ከምትከተለው ስትራተጂ ውጪ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፕሬዝዳንት አል ሲሲ የቀረበውን በህዳሴው ግድብ ድርድር ላይ አሜሪካ በአሸማጋይነት እንድትገባ የቀረበውን ሐሳብ ተቀበሉት። በዚህም ሂደት አሜሪካ ከግብጽ ጎን ቆመች። ከኤርትራ ጋር የነበረውን ውጥረት ለማስወገድ የቻሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተመሳሳይ ከግብጽ ጋርም ከስምምነት እንደሚደርሱ አስበው ነበር፤ ግን አልሆነም። እንዲያውም እራሳቸውን አጣብቂኝ ውስጥ አስገቡ። በዋሽንግተኑ ድርድር ላይ የተጋበዘችው አገር ለዓመታት በአሜሪካ ሽብርተኞችን ከሚደገፉ መንግሥታት ዝርዝር ውስጥ ገብታ የገንዘብ ማዕቀብ ስር የቆየችውና ለአሜሪካ ተጽእኖ ተጋላጭ የሆነችው ሱዳን ነበረች። በድርድሩም ሱዳን ከግብጽ ጋር ተስማምታ ቆመች። በኢትዮጵያውያን ዘንድ አሜሪካ ያቀረበችው የስምምነት ሐሳብ ተቃውሞ የገጠመው ሲሆን፤ በዚህም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሐሳቡን ውድቅ ለማድረፈግ ተገደዱ። ይህንንም ተከትሎ አሜሪካ ለኢትዮጵያ ከምትሰጠው እርዳታ የተወሰነውን አገደች። የአሜሪካው ፕሬዝዳንትም ግብጽ የህዳሴውን ግድብ \"ልታፈነዳው\" ትችላለች ሲሉ ያስጠነቀቁ ሲሆን፤ ኢትዮጵያም ግድቡ በሚገነባበት አካባቢ ማንኛውም በረራ እንዳይካሄድ አደረገች። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ በትግራይ ውስጥ ከተከሰተው ግጭትና በሱዳን ድንበር ካለው ውጥረት በተጨማሪ ከግብጽ ጋር ውዝግብ ውስጥ መግባት አይችሉም። ከሱዳን ጋር ያለው የድንበር ችግር በታሪክ ለረጅም ጊዜ የቆየውን ውዝግብ መልሶ እንዲያንሰራራ አድርጎታል። ከአርባ ዓመታት በፊት ሱዳን ህወሓትን ጨምሮ የብሔር ሸማቂ ቡድኖችን ስታስታጥቅ የኢትዮጵያው ወታደራዊ መንግሥት ደግሞ የሱዳን አማጺያንን ይረዳ ነበር። በአውሮፓውያኑ በ1990ዎቹ ሱዳን ታጣቂ እስላማዊ ቡድኖችን ስትደግፍ ኢትዮጵያ ደግሞ የሱዳን ተቃዋሚዎችን ትረዳ ነበር። በትጥቅ የተደገፉ ግጭቶችና አለመረጋጋቶች በብዙ የኢትዮጵያ ክፍሎች ውስጥ በሚያጋጥሙበት በዚህ ጊዜ፤ ሱዳን በቅርቡ የተሟላ ባይሆንም በዳርፉርና በኑቢያ ተራሮች ካሉ አማጽያን ጋር የሰላም ስምምነት ደርሳለች። በዚህ ሁኔታም አገራቱ ወደ ቆየው አንዳቸው የአንዳቸውን ሠላም ወደ ሚያናጋ ተግባር ሊመለሱ ይችላሉ። በሱዳንና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት ከፍተኛ ከሚባለው ደረጃ ላይ ደርሶ የነበረው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ወደ ካርቱም ሄደው አልበሽር ከስልጣን ከተወገዱ በኋላ የዲሞክራሲ መብት ጠያቂ ተቃዋሚዎችና የአገሪቱ ጀነራሎች የሲቪል አስተዳደር እንዲመሰርቱ ድጋፍ ባደረጉበት ጊዜ ነው። የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሐምዶክም ውለታቸውን ለመመለስ በትግራይ ግጭት በተከሰተበት ጊዜ መፍትሄ ለማምጣት ለማሸማገል ሙከራ አድርገው ነበር። ነገር ግን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ኢትዮጵያ ውስጣዊ ጉዳይዋን በራሷ ትወጣዋለች በሚል ሳይቀበሉት ቀርተዋል። ረሃብና አሰቃቂ ታሪክ ያላቸው ስደተኞች ከትግራይ ወደ ሱዳን እየሄዱ ባሉበት ሁኔታ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሽምግልናውን ላለመቀበል የበለጠ አስቸጋሪ ሊሆንባቸው ይችላል። ምናልባትም በሁለቱ አገራት መካከል አዲስ ዙር ድንበር ተሻጋሪ ጠላትነት ሊቀሰቀስ የሚችልበት ስጋት ያለ ሲሆን ይህም የቀጠናውን ቀውስ ሊያባብሰው ይችላል። ", "passage_id": "682ac19305e15a6466d6c48138218ac8" } ]
3b7d5149b588d52a56ab367cd147e716
9526bdf2d33bb41a59c50780d0b1f80b
ከግልባብ ፍሬ
አንድ ገበሬ ናቸው። በዘመናቸው ሮጠው ያሻቸውን አድረገዋል፤ አንሰተው ጥለው እንዳላለፉ ሁሉ ዕድሜ ገሰገሰና ጉልበታቸው ከዳቸው። ጊዜ ሲገፋ አቅማቸው ሲደክም እጅ ሰጡ። በወጣትነታቸው ሌላውን የጦሩት ያህል ተረኛ መሆን ግድ አላቸው። ግን ደግሞ እድለኛ አልነበሩምና ‹‹ጧሪዬ ይሆናል›› ብለው ተስፋ የጣሉበት አንድያ ልጃቸው እስር ቤት ይገባል። ለዚያው ለገበሬ ወሳኝ በሆነው የአዝመራ ወቅት። ይህ ወቅት ገበሬው አቅሙን አሟጦ የሚጠቀምበት ነውና ሽማግሌው መሬታቸው ጦሙ ማደሩን ሲረዱ ሀሳብ ገባቸው። እናም ለልጃቸው ‹‹ልጄ አቅሜ እንደደከመ ጉልበቴ እንደዛለ ታውቃለህ። ዘንድሮ አንተም የለህ መሬቱ ፆሙን ማደሩ ነው። የአንተ መታሰርና ከእኔ መለየትን ሳስብ መጪው ጊዜ አስጨንቆኛል። በርሃብ መሞቴ ነው። መሬቱን ማን ቆፍሮና አለስልሶ አዝመራውን ይዘራልኛል? ችግር ውስጥ ወድቄብሃለሁ።›› በማለት ወደ እስር ቤት ደብዳቤ ላኩ። ልጃቸው የአባቱን መልዕክት አንብቦ ምላሽ ፃፈ። ‹‹አባቴ ዘንድሮ ሌላ ሰው የሚያግዝህ ቢኖር እንኳን የአዝመራውን ቦታ እንዳታስቆፍረው። አይዞህ! አምላክ ሌላ መፍትሄ ያቀርብልናል። የገደልኳቸውን ሰዎች የቀበርኩት እዚያ ቦታ ላይ ስለሆነ በፍፁም እንዳይቆፈር ሌላ ሰው ከቆፈረው ማስረጃ ይገኝብኛል፤ አደራ›› ብሎ መልዕክቱን ይመልሳል። ይህ መልዕክት ከተላከ ከጥቂት ቀናት በኋላ አባት ለልጃቸው በድጋሚ ደብዳቤ ላኩ። ‹‹ልጄ በጣም አመሰግንሃለሁ፤ ባለፈው የላከው ደብዳቤ እኔ ዘንድ ከመድረሱ በፊት ፖሊሶች አይተው ነበርና ማሳውን ሲቆፍሩ ከረሙ። ምንም አይነት ሬሳ ግን አላገኙም፤ ይህንን ያደረከው ቁፋሮው በዘዴ በእነሱ እንዲፈፀም አስበህ መሆኑን ተረድቻለሁ። እናም እነሱ በቆፈሩት ማሳ ላይ አዝመራዬን ዘርቼ እፎይ ብያለሁ። ልጄ እዚያም ሆነህ እገዛህ ስላልተለየኝ እጅጉን አመሰግናለሁ›› አሉት።እናም ምን ለማለት ነው ወዳጆቼ፤ የቀረበንን መጥፎ አጋጣሚ በመላ ብናልፈው አጋጣሚውን በመልካም ብንጠቀመው መልካም ነው። ‹‹የተወረወረብህን ጠጠር ለቅመህ መልሰህ ከመወርወር ይልቅ መሸጋገሪያ ድልድይ ስራበት›› የሚል ምክር ተደጋግሞ ይደመጣል። ልክ ነው። ስለማን ብለን መጥፎ አጋጣሚዎችን መጥፎነታቸው ላይ ብቻ በማተኮር እንቆዝማለን? ይልቅ መጥፎ ገጠመኙን እራሱን መግጠም የተሻለ ነው። በየዕለት እንቅስቃሴያችን የገጠመን አስቸጋሪ ጉዳይ ወደ ጥሩ አጋጣሚና ጥቅም የመለወጥ ልማዳችን ምን ያህል ይሆን? ያሰብነው አልሰምር፤ ያቀድነው አልሳካ ቢለን ፈፅሞ ወደ ተስፋ መቁረጥ መገባት የለበትም። ስንት ነገር ከፊታችን እያለ በአንድ ሙከራ መሳካት አለመሳካት እጅ ከተሰጠማ መነሻችን ላይ ለጉዳዩ የሰጠነው ቦታ ትልቅ መሆኑ እንጂ ገና ስናስበው ላይሳካ እንደሚችል አላስተዋልንም ማለት ነው። በነገራች ላይ ሙከራ የሚሳካው አልፎ አልፎ እንጂ ሁሌም አይደለም፤ የስኬታማ ሰዎች ገጠመኝና የህይወት ውጣ ውረድ ብንመረምር መንገዱ አልጋ ባልጋ ሆኖለት ያለፈ አይገጥማችሁም። በጉዛችን ውስጥ ወደኛ የሚቀርቡን መጥፎ አጋጣሚዎች ወደ መልካም ገጠመኝ መለወጥ እርግጥ የሚያወሩትን ያህል ቀላል አይደለም። ነገር ግን አንዴ ያ መጥፎ አጋጣሚ ወደኛ መጥቷልና ፈጥሮብን የሚያልፈው ጉዳት ከመቀበል ይልቅ ወደ በጎ አጋጣሚ መለወጡ ግድ ይለናል። ብዙ ጊዜ የበጎ ነገሮች አልያም የግኝቶች መነሻ አስቸጋሪ ወይም መጥቶ አጋጣሚዎች ናቸው። እንደውም በችግር ምክንያት የተፈጠሩ መፍትሄዎች የሰው ልጅ ኑሮ ሲያቀሉ በተደጋጋሚ አስተውለናል። ዛሬ ላይ አለም ጭለማን የረታበት ብርሃን ወይም መብራትን የፈጠረው ቶማስ ኤድሰን እጅጉን ጭለማ ይፈራ እንደነበር እናውቅ ይሆን? ጭለማን መፍራት ደግሞ ጭለማን ለመግፈፍ እንዲማስን አደረገውና መፍትሄ ወለደለት።እናም መከራ መፍትሄን ይወልዳል፤ ፍርሃት ማምለጫን ያበጃል። ድህነትን አጥብቆ የሚፈራ ሰው ከድህነት ለመውጣት ብርቱ ጥረት ያደርጋል። እራሱን ለመለወጥ ለሊት እና ቀን ሲማስን እራሱን የተሻለ ቦታ ላይ ለማድረስ ሁሌም ሲፍጨረጨር የተሻለ ቦታ ላይ መገኘቱ አይቀሬ ነው። እየንዳንዱ መጥፎ ገጠመኞቻችንን ወደ እድል እና መልካም አጋጣሚ መቀየር መቻላችን ጥቅሙ ያየለ የሚያደርገው ለዚሁ ነው። ውዶቼ አንድ ነገር ካስተዋልን ብዙ ጊዜ የኛ ስኬት መቃረቢያ የሚሆኑ ጉዳዮች ትኩረት የሰጠንባቸውና እንዳይደናቀፉብን ጠንቃቃ የሆንባቸው ጉዳዮች ናቸው። ስለ ጉዳይ አስልተን መመርምር ጉዳዩን ጠንቅቀን ማወቅና በዚያ ዙሪያ ያለንን ሁኔታ ምቹ ማድረግ እንዳለብን ፍላጎታችን ያስገድደናል። የጀመርነውን ጉዳይ ከዳር ለማድረስ መውተርተራችን ፍሬ ያፈራል። ነገር ግን ስኬትን አልመን የጀመርነው ጉዳይ ዋነኛ እና ወሳኝ ነው። ያመንበትን ሳይሳካልን ቢቀር አለመሳካቱን መነሻ አድርገን ያልተሳካበት ምክንያት መመርመር ተገቢ መሆኑ አያጠያይቅም። ያ ጉዳይ የኛ የመጨረሻ አማራጭ አድርገን መውሰዳችን የመጀመሪያው ስህተት ነው። አለም በብዙ ገጠመኞች የተሞላች ለሰው ልጆች ሰፊ ዕድልን ይዛ የቀረበች ሆና ሳለ የኛ ምልከታ ውስን ይሆንና አንድ መንገድ ላይ ብቻ ችክ እንላለን። ያ መንገድ ደግሞ የሚጓዙበት ብዙዎች ናቸውና የተጣበበ ሆኖ ይጠብቀናል። አስፍቶ መመልከትና ሌሎች አማራጮችን ማየቱ የኛ ልምድ ሊሆን ይገባል። በጥረታችን ውስጥ የሚገጥመንን ጋሬጣ መመንጠር የሚያስችል አቅም ይዞ መገኘትና መፋለም፤ ይህን የማድረግ አቅምን ከፈጠርን ሌላ ዘዴ መዘየድና ችግሩን እራሱ በመፍትሄነት መጠቀሙ ልምድ ብናደርግ መንገዶች ሁሉ ይቀናሉ። አዲስ ዘመን ታህሳስ 20/2012ተገኝ ብሩ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=24906
[ { "passage": "ተማሪዎች ናቸው የምስኪን ቤተሰብ ልጆች። ትምህርታቸውን የሚከታተሉት በመንግሥት ትምህርት ቤት ነው። ጠዋት ማልደው ሲሄዱና ተምረው ሲመለሱ ለተመለከተ በገፅታቸው ላይ የሚታየው ፈገግታ የሌላውንም ልብ ያሞቃል። የተማሏ ያልተቀዳደደ ዩኒፎር ለብሰዋል። ሁሉንም እኩል አንድ የሚያደርግ የትምህርት ቤት ዩኒፎርም፤ በመሐከላቸው ያለው ልዩነት የልብሱ ቀለም ብቻ ነው። ምን አልባት የክፍል ደረጃቸው የተለያየ ስለሆነ ይሆን ? ይሄን በውስጤ ያሰብኩት ነው። የቅድመ መደበኛ ፣ የአንደኛ ደረጃ፣ የመለስተኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ተብሎ የልብሱ ቀለም (ከለር) እንደዛ መልኩ የተለያየ ይሆናል። በትክክል ይሄ ነው ብዬ ልቀበል ምክንያቱም እኔ የተነሳሁት ከልብሱ ቀለም ላይ አይደለም፤ ትኩረቴ በልጆቹ ደስታ ላይ ነው። እኩል ያወራሉ፤ ማለቴ ሁሉም በሚነጋገሩበት ጉዳይ ተሳታፊ ናቸው። ፊቱን ቅጭም አድርጉ፣ አንገቱን ደፍቶ የሚቆዝም አላየሁም።\nይሄ ትልቅ ደስታን ፈጥሮብኛል። የሰው ልጅ ተደስቶ ከማየት የበለጠ ምን ደስታ አለ። ክብር ይግባው ላከበራቸው፤ ምስጋናዬ ከውስጥ\nነው።የሆነ ሆኖ ግን እኔም የ‹‹ምስኪን›› ቤተሰብ ልጆች እንድል የገፋፋኝ የተጫሙት ጫማ ብቻ ነው። የተቆራረጠች ‹‹ኤርጌንዶ››\nነው የለበሱት። እኔ እንጂ እነሱ ይሄንን እንደማያስተውሉት እገምታለሁ ። ምክንያቱም ብዙ ይጉድልባቸው የነበረው ነገረ ዛሬ ከሞላ\nጎዳል ተስተካክሎላቸዋል። ዓለም መቼም ‹‹ሞልታ አታውቅም አይደል›› የሚባለው። ሁላችንም የሚጎልብን ብዙ ነገር አለ። ፍላጎታችን\nእንደ አኗኗራች በመሆኑ። ከሁሉም በላይ ግን ሰው የማይመለከተው “እንዴት ውለህ አደርክ” የማይባለው ሆድ ሰዓቱን ጠብቆ መሙላት\nችሏል። አሁንም እላለሁ ክብር የሚገባቸው ይክበሩ፣ ይመስገኑ።እስክሪብቶ፣ ደብተር፣\nእርሳስ ሳይሉ ሳይጨነቁና ወደ ስርቆትም ሳያመሩ የራሳቸውን የትምህርት መሣሪያ አሟልተው ወደ ትምህርት ገበታ ገብተዋል። ብዙዎቹ\nበችግር ትምህርታቸውን ሲያቋርጡ ሌሎቹ ደግሞ ከትምህርት ቤት መልስ ኑሮን ከቤተሰባቸው ጋራ ለመግፋት ሳንቲም በምታስገኝ ሥራ ላይ\nይሰማሩ ነበር። በጫማ ማሳመር፣ በመላላከ፣ ልጅ በመጠበቅ፣ በቤት ሠራተኛነት… እናም የማጥኛ ጊዜ የላቸውም። ትኩረታቸው ዛሬ ምን\nበልቼ እሄድ ይሆን የሚል እንጂ ዛሬ ይሄንን ትምህርት አጥንቼ፣ ፈተናውን ደፍኜ የሚል አይደለም። ምክንያቱም ቀዳሚው ሆድ ነዋ\n! ሆድ አማርጦ ባይሞላም የተገኘውን መቅመስ ግን የግድ ነው። ብዙ ጊዜ አሁን ሳይሆን\nቀደም ባሉት ጊዜያት ልጆች በየትምህርት ቤቱ ሰልፍ ላይ እየወደቁ ነው፤ ይዝለፈላፋሉ፤ በዴስክ ላይ ይተኛሉ፤ ትምህርት ያቋርጣሉ፣….\nየሚባሉ በርካታ ችግሮች በየትምህርት ቤቱ ይሰማ ነበር። ይሄንን የሰሙ በጋራ ገንዘብ በማዋጣት ለተማሪዎቻቸው አይዝዋችሁ ባናጠገባችሁ\nበቀን አንዴም ቢሆን እንመግባችኋለን ብለው ሲሰሩ ከርመዋል። እነዚህም ሊመሰገኑ ይገባል። መፍትሄ አመላካች ፈር ቀዳጀ ናቸው። እዚህ\nላይ መመስገን አለባቸው ስል የመምህራኖችን ውለታ በመርሳት አይደለም። በተማሪዎቻቸው ላይ ችግር ሲገጥም ገንዘብ አዋጥተው በመመገብ፣\nየራሳቸውን ምሳ አሳልፈው በመስጠት፣ ችግሩን አደባባይ በማውጣት ኧረ አልፈው ተርፈው ቤተ እምነቶች ደጃፍ ብቅ እያሉ ዕርዳታ እንዲያደርጉ\nጭምር ሲማፀኑ የነበሩትን ተመልክቻለሁ። ህዝብ በተሰባሰበበት\nቦታ ላይ ተገኝተው ‹‹ዛሬ የተቸገሩ ተማሪዎች የሁላችን ልጆች ናቸው እርዱ›› ብለው ሲያሳስቡ በጆሬዬ መስማቴን ልመሰክር እችላለሁ።\nእናም የመምህራንን ውለታ ለእነሱ የሚገባውንም ምስጋና ከማንም ይቀድም ይሆናል እንጂ አይታጠፍም። የመምህራኑ ጥረት መልካም አሳቢነት፣\nአስተዋይ አመራር ታክሎበት ዛሬ ለደረሱበት ደረጃ ላይ አድርሷቸዋል። ነገርን ነገር ያነሳዋል\nብዬ እንጂ ለዛሬው ያስተዋልኩት በተማሪዎች ላይ ያየሁትን የተለየ ደስታ ነው። ማስደሰት ያስደስታል፤ ምን ማስደሰት ብቻ የተደሰተ\nሰውን መመልከትም በራሱ ያስደስታል። አንድ የናጠጠ ሀብታም ቤቱ ሙሉ ቢሆን፣ መርጦ አማርጦ መኪና ቢነዳ፣ ፎቅ ቢደረድር፣ በሀገር\nላይ ከሀገር ውጭ ቢንሸራሸር ከአጠገቡ ሁሌ የሚሰማው የሰዎችን ችግር፣ ረሃብ፣ ሰቆቃ፣ ለቅሶ ከሆነ፤ የሚመለከተው ጎስቋሎችን፣ ለልመና\nየሚዘረጉ እጆችን ከሆነ… ደስታው ሁሉ ይጠፋል። ነገር ግን በአጠገቡ ያሉ ሰዎች ሀብታም ባይሆኑም ደስተኛ ከሆኑ፤ ራሳቸውን ለማሸነፍ\nየሚታትሩ ብሎም ሃሴት ከቤታቸውም የማይርቅ ከሆነ እርሱም ይደሰታል። በሰራው ሥራ፣ ባደረገው ጥረት፣ በፈጠረው የሥራ ዕድል የተገኘ\nደስታ ከሆነ ደግሞ ከተደረገላቸውም በላይ የሚደሰተውና የሚረካው እሱ ነው። በእነዚሁ ተማሪዎች\nላይ ሰሞኑን ያየሁትን ፈንጠዝያ ታዲያ ያደረገላቸው አካል ቢያየው በምላሹ ምን ያህል እንደሚደሰት አሰብኩት። ጉዳዩ እንዲህ ነው፤\nተማሪዎች ከትምህርት ቤት ተለቀው ወደ ቤታቸው እየተመለሱ ናቸው። በጀርባቸው አንዳንዶች ደግሞ በደረታቸው የተሸከሙት አዲስ ቦርሳ\nነው። በቦርሳው ውስጥ የተለያየ የመማሪያ ቁሳቁስ አለ። እሱን አንድ በአንድ እያወጡ ይተያያሉ። አንዳንዶቹ ልጆች ይህን አይነት\nቦርሳና የትምህርት መሣሪያ ቁሳቁስ እንኳን በእጃቸው ነክተው፣ በጀርባቸው ተሸክመው በአይናቸው ስለማየታቸውም እጠራጠራለሁ። በጣም\nውድ እና ዘመናዊ ነው። ዛሬ ግን ይሄም ለእናንተ\nይገባል ተብለው እጃቸው መድረሱ ያልጠበቁት እንግዳ ነገር ጭምር ነውና ቀደም ብዬ እንደገለፅኩት በፊታቸው ሙሉ ጥርሳቸው ጭምር ነው\nየሳቀው። ወተት እንደጠገበች ጥጃ እምቦር እምቡር እያሉ የሚሯሯጡትም ቤታቸው ገብተው ለቤተሰቦቻቸው እስከሚያሳዩ በመቸኮል ጭምር\nእንደሆነም አስቤያለሁ። እኔ የዚህ ስጦታ አካል ባልሆንም በተደረገላቸው ተማሪዎች ደስታ በመደሰት አንዱ አካል ሆኜ አምሽቻለሁ።\nመስጠት ‹‹መሰጠት›› ቢሆንም\nለመስጠት ልባችንን በቅንነት ከከፈትን ለብዙዎች እንደርሳለን። ዛሬ በህይወት የሌሉት አለቃዬ በሚሉት ንግግር ሐሳቤን ልቋጭ ‹‹ለሰጫችን\nይስጥልን፤ ለንፉግ ልብ ይስጥልን››። ሰላም!አዲስ ዘመን ህዳር 28/2012አልማዝ አያሌው", "passage_id": "89523c13b0688087ca2c4fd5bee16750" }, { "passage": "አካባቢው\nበረሀማ ቢሆንም፤ ጠንካሮቹ ሴቶች ግን ብዙ ርቀት ተጉዘው ውሃ እየቀዱ የቤት ሥራቸውን እየሰሩና ልጆቻቸውን እያሳደጉ መኖር ለእነሱ ያን ያህል ትልቅ ተግባር አይደለም። በኦሎንጪቲ ከተማ በቦሰት ወረዳ ያገኘናቸው ሴቶች ይህ የዕለት ተዕለት ተግባራቸው ነው፡፡ ዛሬ ላይ ግን ውሃ ከመቅዳት አልፈው፤ የኢኮኖሚ አቅማቸውን አሳድገው ከባሎቻቸው ጥገኝነት ለመውጣት እን ዲሁም ለራሳቸውና ለቤተሰባቸው አስፈላጊውን ሁሉ ለማሟላት በማህበር ተደራጅተው እየቆጠቡ፣ እየተበደሩ እና ባገኙት ገንዘብም የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወኑ ራሳቸውን በመለወጥ ላይ መሆናቸውን ከአንደበታቸው ሰምተናል። በቲሪ ቤሬቴ የንጋት ኮከብ የገንዘብ ቁጠባናብድር የህብረት ሥራ ማህበር ውስጥ አባል እንዲሁም የሂሳብ ባለሙያ የሆኑት ወይዘሮ ባፈና ነዲ እንደሚሉት፤ በ1996 ዓ. ም በተቋቋመው ማህበር ተሳትፎ በማድረግ እስከ አስረኛ ክፍል የዘለቀ እውቀታቸውን በመጠቀም በሂሳብ ባለሙያነት በማገልገል ላይ ናቸው። የስድስት ልጆች እናት የሆኑት ወይዘሮ ባፈና ወደ ማህበሩ ከመቀላቀላቸው በፊት ባለቤታቸው በሚያንቀሳቅሱት የግብርና ሥራ ከመተዳደር ውጪ ተጨማሪ የገቢ ምንጭም ሆነ ቤታቸውን ሊደግፉበት የሚችሉበት ገንዘብ እንዳልነበራቸው ይናገራሉ። ወደ ማህበሩ ከመጡ በኋላ ግን ቤታቸውን እንደሚፈልጉት ማስተዳደር ከመቻላቸውም በላይ ከመሰሎቻቸው ጋር በመገናኘት የተለያዩ ሃሳቦችን በመለዋወጥና ከቤት በመውጣት ትልቅ ጥቅም ማግኘታቸውንም ያብራራሉ። ማህበሩ\nሲመሰረት በእያንዳንዱ አባል ማሳ ላይ በመሄድ እርከን በመስራት የተቦረቦሩ መሬቶችን በመሸፈን እንዲሁም የውሃ ማቆር ተግባሩን በማከናወን ነበር የሚሉት ወይዘሮ ባፈና፤ ይህ መሆኑ ደግሞ የራሳቸውን መሬት እንዴት መጠበቅ እንዳለባቸው በሚገባ ማወቃቸውን ይናገራሉ፡፡ ከዚያም በወር አምስት ብር በማዋጣት ከሚያገኙት አነስተኛ ገቢ ገንዘብ መቆጠብ እንደተማሩም ነው የሚናገሩት። «ሰዎች\nለውጥ ማምጣት የሚችሉት በማህበር ተደራጅተው አንድ መሆን ሲችሉ ነው፤ ምክንያቱም ቀድሞ በአካባቢው አንዲት ሴት ገንዘብ ቢቸግራት የምታደርገው ወደ አራጣ አበዳሪ በመሄድ መበደር ነበር፡፡ ይህ ደግሞ ወለዱ ብቻ ከፍተኛ ስለሆነ በችግር ላይ ችግር መጨመር ነበር፡፡ ከዚህ መጥፎ አካሄድ ለመውጣትም በማህበሩ ገንዘብ ቆጥበን መበደራችን ከፍተኛ ጥቅም አስገኝቶልናል» ይላሉ። እርሳቸውም በየዓመቱ ከማህበሩ ያስቀመጡትን ገንዘብ በመበደር ቤተሰባቸውን እየደገፉ እንዲሁም አንዳንዴም ምርጥ ዘር፣ ማዳበሪያና አርም ማጥፊያን በመግዛት ምርታማነታቸውን እያሳደጉ ስለመሆኑ ተናግረዋል። ዘመኑ ጥሩ ነው የሚሉት ወይዘሮ ባፈና፤ የትኛዋም ሴት ብትሆን እቤት ተቀምጣ የሰው እጅ ከምታይ ለልጆቿ መሟላት የሚገባውን ከምታጎል በማህበር ተደራጅታ ብትሰራ መልካም ነው ሲሉም ተሞክሯቸውን አካፍለዋል። ሌላዋ\nየማህበሩ አባል ደግሞ ወይዘሮ ደብሪቱ በሻህ ናቸው። እርሳቸውም እንደሚሉት፤ በቲሪ ቤሬቴ የንጋት ኮከብ የገንዘብ ቁጠባና ብድር የህብረት ሥራ ማህበር አባል ሆነው በመቀላቀላቸው ባለፉት ሰባት ዓመታት ትልቅ ለውጥ ማምጣታቸውንና ለዚህ ለውጥ መምጣት ዋናው ምክንያት ከሚያገኟት ገንዘብ ጥቂቷን ወደ ማህበሩ አምጥተው መቆጠባቸው መሆኑን ይናገራሉ። «ሴቶች በቤትም በውጪም በርካታ ጫና አለብን» የሚሉት ወይዘሮ ደብሪቱ፣ በዚህ ማህበር አማካይነት ግን የሚያስፈልጓቸውን ነገሮች ከማሟላት አልፈው አባወራቸውን በመደገፍ ላይ ስለመሆናቸውና እርሳቸውም ሁሌም በየዓመቱ ሰኔ ወር ላይ የቆጠቡትን በመበደር ምርጥ ዘርና ማዳበሪያ እየገዙ ማገዝ መቻላቸውን ነው የሚያስረዱት። የሰባት\nልጆች እናት የሆኑት ወይዘሮ ደብሪቱ እራሳቸውን በማነቃቃት ገንዘብ ቆጥበው የኔ የሚሉት ነገር በማስቀመጣቸው፤ አራት ልጆችን ከከፍተኛ የትምህርት ተቋም ማስመረቅ መቻላቸውን እንዲሁም ሌሎቹ በጥሩ ሁኔታ ምንም ሳይጎልባቸው እየተማሩ አልፈው ተርፈው የልጅ ልጅ እያሳደጉ ስለመሆኑ ይናገራሉ። ሴቶች ገንዘብ መቆጠባቸው ራሳቸውን እንዲችሉ ከማድረጉም በላይ ልጆቻቸው የእነሱን ፈለግ ተከትለው ቁጠባን እንዲማሩ ያደርጋቸዋል፤ ይህ ደግሞ እንደ አገርም እድገትን የሚያመጣ ነው ካሉ በኋላ በማህበር የተደራጁም ሆነ ያልተደራጁ ሴቶች እራሳቸውን ከጥገኝነት ለማላቀቅ ትልቁ መፍትሔ ከሚያገኙት ገንዘብ ትንሽም ቢሆን ማስቀመጥ መቻላቸው መሆኑን አብራርተዋል። ዘንድሮ ሴቶች በመንግሥት በኩል እያገኙ ያሉት ትኩረት ጥሩ ቢሆንም፤ በቁጠባ በኩል ስልጠና ቢሰጥ እና የተለያዩ ቁሳቁሶች ቢሟሉ መልካማ መሆኑንም ሀሳባቸውን ሰጥተዋል። ወይዘሮ ዛሊካ አደም በቦሰት ወረዳ ሴቶችና ህጻናት ቢሮ ኃላፊ ሲሆኑ፤ እርሳቸው እንደሚናገሩት፤ በቲሪ ቤሬቴ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ውስጥ ያለው የንጋት ኮከብ የገንዘብ ቁጠባና ብድር የህብረት ሥራ ማህበር ከሌሎች በተሻለ እንቅስቃሴን እያደረገ ነው። ምክንያቱ ደግሞ ባልና ሚስት ተሳስበው በመበደር የጋራ ቤታቸውን እየገነቡ ልጆቻቸውን እያስተማሩ በመሆኑ ነው ይላሉ። በወረዳ ደረጃ ሴቶች ከቤት ወጥተው አደባባይ እንዲውሉ እንዲሁም የእኔ ብለው የሚያዙበት ንብረት ባለቤት እንዲሆኑ በቁጠባና ብድር ማህበራት አማካይነት ትልቅ ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝ የተናገሩት ወይዘሮ ዛሊካ፤ ይህ ጅምር ደግሞ ተጠናክሮ ዩኒየን ደረጃ እንዲደርሱ፤ በሴቶች ላይ ከሚሰሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ጋር በመቀናጀት የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል። አሁን ላይ የሚታይ ሥራ ተሰርቷል ባይባልም እንደ ጅምር ግን ከወርልድ ቪዥን ጋር በመተባበር በማህበር ያልተደራጁ ሴቶች በመንደር ቁጠባ ራሳቸውን እንዲችሉ ሳጥኖች እየታደሉ ይገኛሉ፤ ካሉ በኋላ እነዚህን ሴቶች ደግሞ በሂደት ወደ ማህበር በመቀላቀል ተጠቃሚነታቸውን የማስፋት ሥራ ለመስራት እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ነው የተናገሩት። እንደ ወረዳ ሴቶቹ በሚፈለገው ልክ ተጠቃሚ ሆነዋል ማለት ባይቻልም ዛሬ ላይ እናት ከራሷ መቀነት ፈትታ የምትፈልገው ነገር ለራሷና ለቤተሰቧ ማድረግ ችላለች፡፡ ከዚያም ባለፉ ደግሞ መብትና ግዴታዋን በሚገባ ማወቅ ችላለች ይህ ደግሞ ትልቅ ግብ ነው ማለት ይቻላል ይላሉ ወይዘሮ ዛሊካ።አዲስ ዘመን የካቲት 29/2011በእፀገነት አክሊሉ ", "passage_id": "811d7bfffabed1d6631ade4852f6564e" }, { "passage": "ጃካራንዳ ኢንተግሬትድ አግሮ ኢንዱስትሪ በሚል ስያሜ ይታወቃል አክስዮኑ፡፡ በግብርናና የኢንዱስትሪ ግብአቶች ላይ የሚሰራው ይኸው ድርጅት ከተቋቋመ 3 አመታትን አስቆጥሯል፡፡ በከብት ማድለብ፣ በአሣ እርባታ፣ በንብ ማነብና አትክልትና ፍራፍሬዎችን ማምረትና ወደ ውጪ አገር መላክ ሥራ ላይ እንደተሰማራ የሚናገረው ይኸው ድርጅት ከ2000 በላይ አባላት አሉት፡፡ ማህበሩ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ባኮ ቴፒ ወረዳ ውስጥ ከመንግስት የተረከበውንና በትራክተር አሳርሶ አትክልትና ፍራፍሬዎችን እያመረተ ወደ ውጪ አገር የሚልክበትን የእርሻ ማሣ እንድንጐበኝ ጥሪ ከተደረገላቸው ስድስት የቲቪ፣ የሬዲዮና የህትመት ጋዜጠኞች አንዷ ሆኜ ባለፈው ማክሰኞ ወደሥፍራው ተጓዝኩ፡፡ጉዞአችን የተጀመረው ማለዳ ላይ ቢሆንም 16 ሰዎችን የጫነችውና በኪራይ የተገኘች ሚኒባስ መኪና ረፍት የለሹንና አድካሚውን ጉዞ አጠናቃ ከታለመላት ሥፍራ የደረሰችው ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ተኩል ላይ ነው፡፡ ረሃብና ውሃ ጥሙ ያሰቃየው ጋዜጠኛ ከእርሻው ማሣ ደርሶ የተዘናፈለውን የአትክልትና ፍራፍሬ እስከ ሚያይና ከበሰለው ፍሬ እስከሚቀምስ ቸኩሏል፡፡በትራክተር የታረሰ የተንጣለለ ሜዳ ላይ ስንደርስ ሥፍራው መድረሳችን ተነገረንና ወረድን፡፡ ሁሉም ጋዜጠኛ ግራ መጋባቱ ከፊቱ ላይ ይነበባል፡፡ ጭው ያለውና የተንጣለለው የእርሻ ማሣ ዘር ናፍቆታል፡፡ በትራክተር እየተገመሰ ታርሶ የዘር የለህ በሚለው እርሻ ላይ ተጉዘን የችግኝ ማፍያና ማባዣ ቦታ ነው ወደተባለው ሥፍራ ደረስን፡፡ከሃያ በላይ ዝርያ ያላቸው የተለያዩ የአትክልትና ፍራፍሬ ዓይነቶች በዚህ ሥፍራ እየተፈሉ ወደሌላ ቦታ እንደሚዛወሩ ቢነገረንም በሥፍራው ያየናቸው የቲማቲም፣ የሰላጣ፣ የቃሪያ፣ የቆስጣ፣ የጐመንና የፎሶሊያ ችግኞችን ብቻ ነው፡፡ በመደብ በመደብ እየተከፈሉ እንዲፈሉ የተደረጉት ችግኞች በማህበር በተደራጀ መልኩ የተሰሩ ናቸው ብሎ ለማመን አስቸጋሪ ነው፡፡ የዛሬን አያድርገውና አዲስ አበባ ከተማ እንዲህ ግቢ አልባ ከመሆኗ በፊት በግለሰብ ቤቶች ጓሮ የሚተከሉት የጓሮ አትክልቶች በብዛትም በዓይነትም የተሻሉ ነበሩ፡፡ በአረምና ኩትኳቶ ሥራ ላይ ተሠማርተዋል ተብለው በዕለቱ በሥፍራው ከነበሩ ሴት ሠራተኞች መካከል አንዷን ክንድናና ግር መርጠው ሰጡን፡፡ በዚህ መንገድ ከሚመረጡ ሰዎች ጥሩ መረጃ ማግኘት እንደማይቻል በልምድ የምናውቀው ጉዳይ ነውና እሷን ከሌሎች ትተን የራሳችንን ምርጫ አደረግን በድርጅቱ መሥራት ከጀመረች 12 ቀናት እንደሆናት፣ በቀን የሚከፈላት 20 ብር መሆኑን፣ መኖሪያዋ ከእርሻ ሥፍራው እጅግ የራቀ እንደሆነ ከነገረችን ወጣት ጋር ጥቂት ቆይታ አደረግን፡፡ከተመደቡልን ሰዎች ውጪ ማነጋገራችን እምብዛም ያልተመቻቸው የማህበሩ ሥራ አስኪያጅ ጉብኝቱ እንዲቀጥል ጠየቁ፡፡ የሚጐበኘው ነገር ግራ የገባው ጋዜጠኛ ሥራ አስኪያጁን ነገር ግራ የገባው ጋዜጠኛ ሥራ አስኪያጁን ተከትሎ ጉዞ ጀመረ፡፡ ቢሄዱት ቢሄዱት የማያልቀው የታረሰ መሬት ያታክታል፡፡ አንድ ቦታ ቆም ብለን ሥራ አስኪያጁ ኢንተርቪው እንዲሰጡን ጠየቅናቸው ይህ ጥያቄያችን ሁለት አላማዎችን ያነገበ ነበር፡፡ አንድም ተሠራ ስለሚሉትና በዓይናችን ልናየው ስላልቻልነው ነገር የሚነግሩን ካለ እንዲነግሩን ሲሆን ሌላው ከያዘን ድካም ጥቂት አረፍ ለማለት እንድንችል ነበር፡፡አክስዮን ማህበሩ 2000 አባላት እንዳሉት በከብት ማድለብ ሥራው ለዘጠኝ ዙሮች ወደተለያዩ አገራት የቁም ከብቶችን መላካቸውን፣ በዚህ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርትም ከ3 ወራት በኋላ መላክ እንደሚጀምሩ ገለፁልን፡፡ እንዴ ምኑ ነው የሚላከው? ሁላችንም ጠየቅን፡፡ ችግሮቹ ከሶስት ወራት በኋላ ምርት እንደሚሰጡና ይህም ወደውጪ እንደሚላክ አስረግጠው ነገሩን፡፡ አነጋገራቸው ዝም ብላችሁ የተነገራችሁን ፃፉ የምን ጥያቄ ነው ይመስላል፡፡ ለእርሻ መሬቱ አዋሣኝ ከሆነውና በሕንድ ባለሃብቶች ከተያዘው ቦታ ጋር አለመግባባት መኖሩን፣ ከቦታው ላይ ከተነሱት አርሶ አደሮች ጋር ውዝግብ እንደነበረና ይህ ከምን እንደደረሰ ከጋዜጠኞሀት የቀረበላቸውን ጥያቄ በአግባቡ ለመመለስ ፈቃደኛ ያልሆኑት አቶ ደመላሽ ጉብኝቱን መቀጠሉ እንደሚሻል ነገሩንና የተቋረጠው ጉዞ ተጀመረ፡፡ የተንጣለለ የእርሻ መሬት ማየት የታከተው ጋዜጠኛ ማጉረምረም ጀምሯል፡፡ እንዴ እኛ የመጣነው ወሰን ልንለካ ነው እንዴ? ሁሉም ያጉረመርማል፡፡ ቀስ በቀስ ትዕግስቱ እየተሟጠጠ የመጣው ጋዜጠኛ መሀል የእርሻ ማሳው ላይ ተሰብስቦ ከአንድ ውሣኔ ላይ ደረሰ፡፡ ወደ ኋላ መመለስ፡፡ ይህ ውሣኔ ሥራ አስኪያጁን አላስደሰታቸውም፡፡ ጉብኝቱን እንድንቀጥል ማግባባቱን ተያያዙት፡፡ አልተሣካላቸውም፡፡ ልመናና ማግባባቱ ብቻ በቂ አለመሆኑ የገባቸው ሥራ አስኪያጁ የቲቪ ኦሮሚያ ጋዜጠኞችን ይዘው መጐተት ጀመሩ፡፡ ና ሂድ አልሄድም፡፡ ምንም የሚታይና በካሜራ የሚቀረፅ ነገር በሌለበት ሁኔታ ከዚህ በላይ ለመሄድ አንፈልግም፡፡ ለደቂቃዎች ሙግቱ ቀጠለ፡፡ የቲቪ ካሜራ ማኑ ፊቱን መልሶ ወደመጣበት ጉዞ ሲጀምር ተስፋ ቆረጡ፡፡ መኪናዋ ወደቆመችበት ከ2 ኪሎ ሜትር በላይ ተጉዘን ብንደርስም በውሣኔያችን የተከፉት አቶ ደመላሽ ከቆሙበት አልተነቃነቁም፡፡ በአቅራቢያው ካለ ወራጅ ወንዝ በውሃ ፓምፕ እየተሣበ ወጥቶ የፈሉትን ችግኞችና ጥቂት ፈንጠርጠር ብለው የተተከሉትን የቃሪያ፣ የቲማቲምና የጐመን ተክሎችን የሚያጠጣ የመስኖ ውሃ አለ፡፡ ከአንድ ብርቱ የከተማም ሆነ የገጠር ነዋሪ የጓሮ አትክልት ያልተሻለውንና የሚያኰራ ሥራ ያልተሠራበትን ሥራ ያልተሠራበትን ይህን የእርሻ ሥፍራ እንድንጐበኝ መጠራታችን ለሁላችንም ግራ ሆኖብናል፡፡ ከ3 ወራት በኋላ መላክ ይጀምራል የተባለው አትክልትና ፍራፍሬ ከየት እየመጣ እንደሚላክ የሁሉም ጥያቄ ነበር ያልተመለሱ ጥያቄዎቻችን እንደያዝን ለሰዓታት አቶ ደመላሽን መኪናው ሥር ተቀምጠን መጠበቅ ግዴታችን ሆነ፡፡ እስቲ መኪናውን ነድታችሁ ትሄዱ እንደሆነ አያለሁ ያሉት የማህበሩ ሥራ አስኪያጅ ንዴታቸውን የሚወጡበት አጋጣሚ በማግኘታቸው ደስ ያላቸው ይመስላል፡፡ ከ290 ኪሎ ሜትር በላይ ከፊታችን እንደሚጠብቀን በማወቃችን ምሽቱ እየገፋ ሲሄድ ሥጋታችንም በዛው መጠን ጨመረ፡፡ ከብዙ እልህ አስጨራሽ ጥበቃ በኋላ መጡና የመልሶ ጉዞአችን ተጀመረ፡፡ 45 ኪሎ ሜትር ፒስታ መንገዱን ጨርሰን ጌዶ ስንደርስ ከምሽቱ ሁለት ሰዓት አልፏል፡፡ በመንገዱ ላይ የነበሩትን ጉዳዮች መዘርዘሩ አንባቢውን ላይ የነበሩትን ጉዳዮች መዘርዘሩ አንባቢን ከማሰልቸት ውጪ የሚፈይደው ነገር ባለመኖሩ ባልፈውም ድካም ረሃብና ውሃ ጥም፣ እንዲሁም እንቅልፍ ያደከመው ጋዜጠኛ ድካሙን ለመርሣት ሲያሰማ የነበረውን ህብረ ዝማሬ የድርጅቱ ሠራተኛ የሆነ ወጣት ኃይለ ቃል በተሞላበት ሁኔታ ማስቆሙን ሣይገልፁ ማለፉ ተገቢ ይሆናል ብዬ አላምንም፡፡ ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት አዲስ አበባ በመድረስ የተጠናቀቀው ጉዞ ያስገኘውን ውጤት ረጋ ብዬ ለማሰብ ሞከርኩ፡፡ ምንም አጣሁበት፡፡ ማስታወቂያቸው በቴሌቪዥንና በሬዲዮ በስፋት የሚነገርላቸው የአክስዮን ማህበራት ውስጣቸው በእጅጉ አሣሰበኝ፡፡ ማሞ ሌላ መታወቂያው ሌላ እንዲሉ፡፡  ", "passage_id": "80227ebd174a9e4f154d10305a862e54" }, { "passage": " እንደምን አደራችሁ? እንደምንስ ውላችኋል? ቤተሰቡ፣ ጎረቤቱ፣ ቀዬው፣ ከብቱ፣ አገሩ በአጠቃላይ ሁሉም ሰላም አድሯል? ደግ። ብለው ሲመርቁ አንድ ከጎረቤቴ ያሉ አዛውንት ሁሌ እመለከታለሁ። በየቀኑ ጠዋት ማየቴን እንጂ ልብ ብዬ ትርጉም ሰጥቼ ለማጤን ሞክሬ አላውቅም። 21 ዓመቱን የደፈነ የልጅ ልጃቸውን ‹‹አንተ ጎረምሳ፤ ለምን ሰው ሰላም አትልም? ቆይ የሰላምን ጥቅም ስታጣው ታውቀዋለህ›› ይሉታል። ለካስ በየአካባቢው ሰላም እንዲኖር ከጸሎት እስከ ተግባር መትጋት የሚጠበቅብን ለራሳችን ስንል ኖሯል። የሁላችንም የሠላም ምንጭ በሌሎች ሰላም መዋል ማደር ውስጥ ነው። በየትኛውም ጫፍ ሰላሙ የታወከ አካል ወይም ደግሞ በሰላም አለማደር ሲከሰት መፍትሔ መፈለግ ግድ ይላል። ዝም ብለው ከተመለከቱት ተራ የመጠበቅ ጉዳይ እንጂ ከእያንዳንዱ ሰፈር ደርሶ በሩን ማንኳኳቱ አይቀርም። ስለዚህ የጎረቤትህ፣ የሰፈርህ፣ የከተማህ፣ ብሎም የሀገርህ ሰላም መሆን ለአንተ ሕይወት ዋስትናን የሚሰጥ ነው። ‹‹ሰላም ሳይለኝ ያለፈው ‹የእንትን› ብሔር ስለሆንኩ ነው›› እያለ የተዛነፈ ሒሳብ የሚያሰላ ትውልድ በበዛበት ወቅት የእለት ተግባርን በደስታ፤ በፍቅርና በሰላም መጀመርን የሚያህል ደስታ በዋዛ እንዴት ይገኛል። አዎ፤ የመልካም አስተዳደር ችግር የገጠመው ሰው ውሎው ስኬታማ፣ ለሌሎች ቅን አሳቢ፣ ሰው አማኝ ሊሆን ይቸገራል። እውነት ነው። በተውሶ ጭንቅላት እየታሰበ እንዴት ሰላምና አንድነት ሊገኝ ይችላል። ‹‹ያልበላንን እያከክንስ›› እስከ መቼ እንኑር ጎበዝ። ሆዱ እንጀራ፣ እንጀራ፣ ዳቦ ዳቦ ሲል ለሚያድር ሕዝብ ‹የእንብላ ፣ የእንጠጣ ፓርቲ› እንጂ\nየፖለቲካ ፓርቲ ሲፈለፈል ማደሩ ለራበው ሰው ምን ይፈይድለታል። ቁራሽ ሆኖ ሆዱ የከፈተበትን ጦርነት አይመክት። ተስፋ የጣለበትን ለውጥ በጥርጣሬ እንዲያይ በማድረግ አስተሳሰቡን ለመስረቅ ያለመ ይመስላል። የሌብነት ዘርፎችን ብዛት አያችሁት? ጉድ እኮ ነው። መቶ አስር ሚሊዮን ደረስን ብንለው መቶ ስምንት ሆኖ ለቅርምት መጣ ብሎ መተረቱ ይቀላል። የሸገሮች የሰላም ነፋስ ደግሞ ከአራቱም  የሀገሪቱ ጠርዞች የሚነፍስ ነው። በዚህ የተነሳ አዲስ አበቤው ለቁዘማ ተጋላጭነቱ የሰፋ ሆኗል ይባላል። ሌላው ሁሉ ቢቀር ገንዘቡን ተሰርቆ ሲቆዝም ይውላል ይላሉ ውስጥ አዋቂዎች። እንደው ከተነሳ አይቀር በ‹‹ሰርቆ አደሮችም›› ዘንድ ሪፎርም ተሰርቷል መባሉን ሰምታችኋል? ነገረ ሥራቸው ተቀይሯል ይባላል። እንደ ድሮው ፈራተባ እያሉ ኪስ መዳበስ፣ ስልክ መመንተፍ ቀርቷል። ቦታና አሳቻ ሰዓት መርጦ በደፈጣ የአካል ጥቃት ሰንዝሮ የንብረት ዝርፊያ መፈጸም ለጊዜው ተጠናክሮ ቀጥሏል። ጥሩ ብር መያዙ በተጨባጭ ከተረጋገጠ የሰዓት ገደቡ ግድ አይሰጣቸውም። አሁን ላይ የትኛውም አካባቢ የክልል ከተሞችን ጨምሮ ስርቆት ወደ ዝርፊያ መልኩን ቀይሮ፣ ደረጃውን አሳድጎ ይከወናል። ፅድት ያለ የመደበኛ ሥራ አካል ተደርጎ መቆጠር ጀምሯል። ‹‹እኔኮ ጥሩ ነገር ካልሆነ አልነካካም። ለሥራ ሳውዲ ዓረቢያ አለያም ዱባይ ደርሼ እመጣለሁ›› የሚሉ ዝነኛና ኩሩ ሌቦች መበራከታቸው ይነገራል። የዚህ አይነቶቹ የተለወጡ ሞዴል ሌቦች ወይስ ሞዴል ሥራ ፈጣሪዎች ምን ይባሉ ይሆን? መልሱን ለእናንተ ትቸዋለሁ። ለማንኛውም በእነሱ አጠራር ‹‹ ብቁ ሿሿ›› ይሰኛሉ። ‹‹አዲስ አበባን ማታ ከ1፡00 ጀምሮ ፈረቃው የተቀየረ እስኪመስል ድረስ ከጫፍ ጫፍ ሌቦች ያጥለቀልቋታል›› ሲል ጓደኛችን የታዘበውን አጫውቶኛል። ‹‹በተናጠላዊ ፍተሻ ሳይሆን በተደራጀ አሰሳ የኢኮኖሚያዊ ፍላጎታችንን እናሳካለን›› በሚል መሪ ቃል ንቅናቄውን የሚመራ ይመስላል። በአንበሳ አውቶብስ ተሸከርካሪ ተሳፍረናል። እንደው በስም ብቻ በሩቁ ለምታውቁት በግብሩም አንበሳ አውቶብስ ድንቅ ነው። በነጻነት የማሰብና የመናገር መብት ተከብሯል። የብሔር ፖለቲካ ከባለቤቶቹ በላይ ይፈተፈታል። ምን የማይነሳ አጀንዳ አለ ሁሉም በሽበሽ ነው። ምንጭ ግን ከአንድ ወሬ በላይ አንድን ሰው መጠየቅ አይቻልም። ደጋግመው የወሬ ምንጭ የመጠየቅ አመል ካለብዎ ያስወግዱ፤ ያጣላዎታል። ምክንያቱም በዚህ ወቅት የሀገራችን ወሬዎች የሚጨለፉት ከአንድ ኩሬ ነው ከፌስቡክ። ከአጠገቤ የተቀመጡ አንድ እናት ሲያማርሩ ሰምቼ ቀልቤን ሳቡት። ‹‹ምነው ምን ገጠመዎት እናቴ›› ብዬ\nጠየቅኳቸው። እሳቸውም ‹‹መላዕክቱ መሪያችን እናት እናት ይላሉ። ከታች ያሉት ባለስልጣኖቻቸው ግን ከአይጥ እኩል ቆጥረውናል። እየውልህ ልጄ በዘመመች የቀበሌ ቤት ውስጥ ነው የምኖረው እናም የአይጥ መንጋ ማረፊያ አሳጣኝ። ፍቀዱልኝና በሸራም ቢሆን በአቅሜ ልሸብባት። በቁሜ አይጥ ቀርጥፎኝ፤ የሰው መሳለቂያ መሆኔ ነው ብዬ ብጠይቃቸው ‹አይቻልም፤ አይቻልም፤ ካልሆነዎት ያስረክቡን። ሜዳ ላይ የወደቁት ምን ይበሉ› ብለው አንጓጠው አባረሩኝ። ‹ከላይ አልጋ ከታች ቀጋ› የሆነ\nነገር ገጥሞኛል›› አሉኝ። በሞቴ ጆሯችሁን አውሱኝ ልንገራችሁ፤ እኔ በበኩሌ የአንበሳን ያህል አዛኝ፤ ለአዲስ አበቤ አላየሁም። በአራት ሽልንግ ስንት ሀገርና ወሰን አቋርጦ እንደሚሸኝ የሚያውቀው ያውቀዋል። የዚችን ምስኪን ከተማና ሀገር ቀዳዳዎች ሊሞላ ወፍ ሳይንጫጫ ጀምሮ ይባዝናል፤ ምን ይሄ ብቻ ከባዱ የኑሮ ሸክም አልቃና ብሎ በትከሻቸው ጋልቦ ላጎበጣቸው፣ ከከተማዋ ጫፍ እስከ ጫፍ ቢማስኑም ኪሳቸው አልጠረቃ ላላቸው ለፍቶ አደሮች፣ በእድሜም ሆነ በእክል አቅምና ጉልበት ሊከዳ ለሚዳዳቸው ሁሉ እናት የሆነ ሸካፊ ነው፤ አንበሳ አውቶብስ። ታማኝም ነው። እንደው በዘመኑ ወረርሽኝ ተለክፈን አዕምሯችንም፣ አይናችንም በጎ በጎውን አላስብና አላይ ብሎናል። አንድ ቀን አንበሳ ሳይጭነው ያለፈ ተሳፋሪ የእከሌ ብሔር በመሆኔ ነው ማለቱ የማይቀር ይመስለኛል። ኧረ እንደው እንቅፋት የመታውም ‹‹እንትን በመሆኔ ነው›› ሳይል\nአይቀር። ወገኖቼ ገንዘባችን ብቻ ሳይሆን አስተሳሰባችንም እኮ ለስርቆት ተዳርጓል። እያንዳንዱ ሰው ወደ ተንታኝነት መቀየሩን ሰምታችኋል? ያውም እኮ ፖለቲካ ነው የሚተረትረው። እያንዳንዷ ከአንደበታችን ጠብ የምትል ቃል ፖለቲካዊ ትርጉሟን እንጂ የተተነፈሰችበትን አውድ ማን ከቁብ ይቆጥረዋል። አረማመዳችንም ቢሆን በጥንቃቄ ሒሳብ ተሰልቶ እግራችንን ልናንቀሳቅስና አካባቢያችንን ቃኘት ቃኘት አድርገን አዋሳኙ ሰው አልባ በሆነ ባዶ መሬት ላይ ልናሳርፍ ይገባል። አለበለዚያ በወቅቱ የፖለቲካ ተንታኞች እይታ ውስጥ መውደቃችን የማይቀር ነው። ፍዳም ያስከፍላል ፤ደግሞ ይሄ ምኑ የፖለቲከኛ ተንታኝ አይን ያርፈበታል እንዳትሉኝ። ምክንያቱም እግር አነሳሳችን በቀኝ ከነበረና መሬቱ ላይ ስናሳርፍ ኮቴ ቢጤ ለጆሮ ከበቃ ‹‹አይዞህ፤ እኔን መታህ፤ ጎዳህ›› የምትባል አይምሰልህ። ይልቁንስ አሃ ብሔሬ እንዲህ መሆኑን አውቆ ነው። ዘሬ፣‹‹ብሔሬ…ወዘተ እንትን በመሆኔ እኮ ጠልቶኝ ነው። እንዲህ አድርጎ መርገጥ ነበር ማለቱ እኮ ነው። ንቀውናል እኮ!›› በእነዚህ ላይ እማ ዋጋ ከፍለን ትግል በማድረግ ማሳየት አለብን…ወዘተ። በማለት በፌስቡክ የፖለቲካ ምሩቃን ለትንታኔ እንደሚበቃ ሹክ ልበላችሁ። ኧረ ነገሩስ ከሹክሹክታም በላይ ሆኗል፤ ጸሐይ የሞቀው ሀቅ ከሆነ ዋል አደር ብሏል። ረዘም ላለ ጊዜ በመካከላችን የእሾህ ችግኞች ሲተክሉ የኖሩ እኩዮች እንደነበሩ አይካድም።አሁንም ቢሆን የህዝብን ተከባብሮና ተዋድዶ የመኖር እሴት ጠላሸት በመቀባት ትርፍ የሚያፈነፍኑ መኖራቸው ይነገራል። በዚህ የተነሳ በመካከላችን አስተሳስሮን ለዘመናት የቆየውን አስተሳሰብ በከፋ ደረጃም ባይሆን ሰርቀውናል። ገንዘብህ የተሰረቀ እለት መሳፈሪያ ሊቸግርህ ይችላል። ለድህነት፣ ለረሃብና ለጠኔ ሊዳርግህ ግን ፈጽሞ አይችልም። አስተሳሰብህ ለስርቆት የተዳረግክ ዕለት ግን ተስፋህ ጠላሸት ይቀባል፤ ማንነትህ ይበረዛል፤ ካሳደጉህ ሰዎችና ጎረቤቶችህ በእንትንነትህ ወይም በእንትንነታቸው ትራራቃለህ፤ ትለያያለህ። መለያየትን የሚወልድ ሊጨነግፍና ሊመክን የሚገባው ክፉ በሽታ የወረርሽኝ ያህል መዛመቱን የሚናገሩ በርካቶች ናቸው። ይህ ታዲያ የክፋት ጥግ አይሆንም ትላላችሁ? ሕዝቡ ገንዘቡን ከሚሰርቁት ዘራፊዎች ባልተናነሰ አስተሳሰቡን እያምታቱ በመስረቅ ላይ የተሰማሩትን መከላከል ይኖርበታል ባይ ነኝ። ሰው ሆኖ በተፈጠረበት ብቻ መዋደድና በአንድ ኢትዮጵያዊነት ጥላ ሥር መሰባሰብ ይገባል። ለዚህ ደግሞ ዶክተሩ የተለሙት ትልም ሁነኛ መፍትሔ እንደሆነ በርካታ ዜጎች መስክረውለታል። ‹‹የአንድ\nዓመት ግብራቸው ሺ ዓመት በእጃቸው የዳበሱ ያህል ፈውስ አምጥቷል›› ያሉት የእኛ ዜጎች ብቻ አይምሰሏችሁ በየዓለማቱ ጫፍ ሰው መሆን ያስተሳሰራቸው ፍጡራን ጭምር እንጂ። ለዓለም የሚበቃ አስተሳሰብ ባለቤቶች የሆንን ትልቅ ሕዝቦች በአንዳንድ ፖለቲከኞች የሻገተ አስተሳሰብ ሰብዓዊ ባህርያችንን ለቀን እና አስተሳሰባችንን ተሰርቀን ከሰው ተራ አንሰን ልንገኝ ፈጽሞ አይገባም እንላለን። ቸር እንሰንብት።አዲስ ዘመን መጋቢት 26/2011 ", "passage_id": "4a4ef8a28c91b51f1c9e3a05c2a0fbd1" }, { "passage": "ባሳለፍነው ቅዳሜ ጥቅምት 23/2012 ዓመተ-ምህረት ፤ በዋሺንግተን ዲሲ እና አካባቢዎ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን መካከል የተወሰኑት አዳራሽ ተሰባስበው ነበር።ሀሳብ ለመቀባበል፤እይታን ለመጋራት።መርሐ -ግብሩን ያዘጋጁት አካላት \"ጃንጥላ-የሀሳብ ገበያ\" ሲሉ የሰየሙት ዝግጅት በዚያ ተድርጓል።ሀብታሙ ስዩም በስፍራው ተገኝቶ የተመለከተውን ፤ከስር በሚገኝ ቅኝቱ ያሰማናል።\n", "passage_id": "15e606b2bfae938510f97ee440283ef1" } ]
11f669b5184f7b1335d2efcc647e4a5f
2a1195b85117f85493b54888b566e53e
በድምጽ መስጫ ሳጥን የገባው ቀለበት
በሀገሮች መሪዎችን ለመምረጥ ምርጫ እንደሚካሄድ ይታወቃል። ለእዚህም ዜጎች ድምጻቸውን ይሰጣሉ ፤ ድምጽ በሚሰጥበት ስፍራ ምንም አይነት ሁከት ሊፈጠር አይገባም። በእዚህ አካባቢ ድምጽ በሚሰጡበት ወቅት ወርቅ፣ ገንዘብ ፣ወዘተ ቢጠፋ ያዙኝ ልቀቁኝ ብሎ መጮህ አይቻልም፤ ሊያስጠይቅ ይችላል። ወርቅን ያህል ጠፍቶ ታዲያ እንዴት ዝም ይባላል ትሉ ይሆናል። ያሎት አማራጭ ተረጋግቶ በሰከነ መንፈስ ችግሩን ለሚመለከታቸው አካላት አሳውቆ ድምፁ እስኪጠናቀቅ በትእግስት መጠበቅ ነው።በፈረንጆቹ ባለፈው ታኅሳስ መባቻ በእንግሊዝ ትራፎርድ ምክር ቤት ድምጽ ለመስጠት የተገኘች አንዲት እንግሊዛዊት ከወላጅ እናቷ በስጦታ የተበረከተላትን የወርቅ የጣት ቀለበት ድምጽ ሰጥታ እንደወጣች ከጣቷ ላይ ታጣዋለች። ብዙ ስታፈላልግም ትቆያለች። የቀለበቱ መጥፋት በእጅጉ ያሳስባታል። ለእናቷ ምን ብላ እንደምትነግራትም ግራ ይገባታል። ቻርሎቴ የተባለችው ይህች እንግሊዛዊት ጓደኛዋ በአንድ የፌስ ቡክ ገጽ ላይ በድምጽ መስጫ ሳጥን ውስጥ ቀለበት ስለጣለ ሰው መረጃ መልቀቁን እስከ ገለጸላት ድረስም የት እንደጣለችውም ማስታወስ አልቻለችም። ቻርሎቴ ማንችስተር አቅራቢያ በሚገኘው በክሎቬራል መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ድምፅ እስከሰጠችበት ሰአት ድረስ ቀለበቱ ጣቷ ላይ አንደነበር ታስታውሳለች። ጓደኛዋ መረጃውን እስከላከላት ድረስም ቀለበቱ በድምፅ መስጫ ሳጥን ውስጥ ስለመግባቱም አላወቀችም።ነገሮችን መለስ ብላ ስታሰላስል ድምጽ በሰጠችበት ወቅት ሳንቲም የወደቀባት መስሏት እንደነበር አስታወሰች። ጓደኛዋ የሰጣትን መረጃ መሰረት በማድረግም ድምጽ ወደ ሰጠችበት ትራፎልድ ምክር ቤት ትደውላለች፤ ቀለበት እንደጠፋባትም ትገልጻለች። እነሱም በከተማው መሰብሰቢያ አዳራሽ እንዲቀመጥ ማድረጋቸውን ይገልጹላታል። ቀለበቱ በጠቋሚ ጣቴ ላይ ነበር ፤ ድምፄን ሰጥቼ እጄን ጎትቼ ሳወጣ ሳጥን ውስጥ ወድቆ ሊሆን ይችላል ስትል ትገልጻለች። ቀለበቱ አመልካች ጣቴ ላይ ነበር፤ ጣቴ ላይ ላላ ያለም ነበር፤ ለእዚህም ነው ድምጽ ስሰጥ በቀላሉ ከጣቴ ወልቆ ወደ ድምጽ መስጫ ኮሮጆ ውስጥ የገባው ያለችው ቻርሎቴ ፣በመገኘቱ በጣም መደሰቷን ተናግራለች። ‹‹የእናቴን ፊት እንዴት አያለሁ ብዩ ሳስብ ነበር፤ ለወደፊቱ እንዳይጠፋብኝ በደንብ ተጠንቅቄ እይዛለሁ። ምክር ቤቱ ላደረገልኝ ትብብር አመሰግናለሁ። “ስትል ገልጻለች።አዲስ ዘመን ታህሳስ 21 ቀን 2012 ዓ.ምኃይለማርያም ወንድሙ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=24956
[ { "passage": "ጥንዶቹ ዶሮ እየተመገቡ ሳለ፤ ወንዱ ተንበርክኮ \"ታገቢኛለሽ ወይ?\" ሲል ሴት ጓደኛውን ጠየቀ። \"እዎ!\" ብላም ቀለበት አሰሩ። \n\nኬኤፍሲም፤ \"እኒህን ጥንዶች አፋልጉን\" ሲል ጥንዶቹ ቀለበት ሲያስሩ የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል በማኅበራዊ ሚዲያ የመገናኛ መድረክ ላይ ለቀቀ።\n\n• ትዳር ከባድ የጤና ችግሮችን ለመከላከል\n\nተንቀሳቃሽ ምስሉን 17ሺህ ሰዎች ከተጋሩት በኋላ፤ ጥንዶቹ በኸት ሄክተር እና ኖናሀላና እንደሆኑ ታወቀ። ተንቀሳቃሽ ምስሉን ያዩ ደቡብ አፍሪካዊያንም፤ ጥንዶቹ የተመኙት አይነት ሠርግ እንዲደግሱ ገንዘብ ማሰባሰብ ጀመሩ። \n\nዛካስ ባንቲዊኒ የተባለ ድምጻዊ ሠርጋቸው ላይ በነጻ ለመዝፈን ተስማምቷል። የጫጉላ ሽርሽር ወደሚያደርጉበት ሥፍራ በነጻ ለማድረስ ፍቃደኝነት ያሳዩም አልጠፉም።\n\nድራም የተባለ መጽሔት፤ የጥንዶቹን የፍቅር ታሪክ እንደሚዘግብ አሳውቋል። መጠጥና የምግብ ማብሰያ ቁሳቁሶችን ለማቅረብ ቃል የገቡም አሉ።\n\n• 'ሰልፊ' ለመነሳት ሲሞክሩ የሰመጡት ሙሽሮች\n\nጥንዶቹ ቀለበት ሲያስሩ ቪድዮ የቀረጻቸው ካታካ ማሎቦላ የተባለ ግለሰብ ነው። ፌስቡክና ኢንስታግራም ላይ ምስሉን ከለቀቀ በኋላ በርካቶች ተጋርተውታል።\n\nጥንዶቹም ሊደግፏቸው የፈቀዱ ሰዎችን ባጠቃላይ አመስግነዋል። ጥንዶቹ ከስምንት ዓመት በፊት ጋብቻ መስርተው ነበር። ነገር ግን ሙሽራው በወቅቱ በገዛው ቀለበት ደስተኛ አልነበረም። \n\nስለዚህም ለባለቤቱ ሌላ ቀለበት ለመግዛት ወሰነ።\n\n• ቢዮንሴ በህንድ ለቱጃር ልጅ ሰርግ ዘፈነች\n\n\"ሥራ ስለሌለኝ ኖናሀላና የሚገባተን አይነት ቀለበት መግዛት አልቻልኩም\" ሲል ተናግሯል።\n\nበኸት ሄክተር መላው ደቡብ አፍሪካዊያንን አመስግኖም፤ \"የፍቅር ታሪካችን በዚህ መጠን የብዙዎችን ልብ ይነካል ብለን አላሰብንም ነበር\" ብሏል።\n\n ", "passage_id": "8db2864730439c7fee8dc5971ebe5e9d" }, { "passage": "ደብዳቤዎቹ የተገኙት ቶኪዮ አቅራቢያ ካናጋዋ በሚባለው አካባቢ የሚገኘው የ61 ዓመቱ የቀድሞ ፖስተኛ ቤት በተፈተሸበት ወቅት ነው።\n\nፖስታዎቹን ማድረስ አድካሚ ስለሆነበትና በእድሜ ከእሱ ከሚያንሱ ፖስተኞች ጋር ሲነፃፀር ደካማ ሆኖ ላለመታየት ሲል ፖስታዎቹን ቤቱ እንዳስቀራቸው ተናግሯል ግለሰቡ።\n\n• ጃፓናዊው ቢሊዬነር ወደ ሕዋ አብራው የምትጓዝ 'ውሃ አጣጭ' እየፈለገ ነው\n\n• ጃፓን ከቀበሌ መታወቂያ ያነሰች ሞባይል ሠራች\n\nግለሰቡ የቅርንጫፍ ሃላፊ ሆኖ ይሰራበት የነበረው 'ኮዮዶ ኒውስ' ባለፈው ዓመት ተጠራጥሮ ነገሮችን ለማጣራት ሲሞክር ግለሰቡ ጥፋቱን በማመኑ ከሥራ አባሮታል።\n\nይህን ተከትሎም ግለሰቡ ላይ አንድ ሺህ ፖስታዎችን በማጥፋት ክስ ተመስርቷል። መረጃዎች እንደሚያሳዩት ፖስተኛው ለፉት 17 ዓመታት ፖስታዎችን በቤቱ ሲያስቀምጥ ነበር። \n\nጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ ሶስት ዓመት እስር እና አራት ሺህ ስድስት መቶ ዶላር ቅጣት ይጠብቀዋል እየተባለ ነው።\n\n ", "passage_id": "d500e80f4f8da095936e0b7bf5be72d1" }, { "passage": "ኬብሮን ደጀኔ ከአምባሳደር ካሳ ተክለብርሃን ጋር\n\nእንዳለውም አደረገው። የውክልና ሥርዓቱን በማዘመን የሚወስደውን ጊዜ ከወራት ወደ ደቂቃዎች ለማሳጠር ችሏል። እንዴት? \n\nኬብሮን ደጀኔ 'ሲሊከን ቫሊ' በመባል የሚታወቀው የአሜሪካ ቴክኖሎጂ እምብርት ውስጥ 'ቪዲቸር' የሚባል ድርጅት ካቋቋመ አምስት ዓመት ሊሆነው ነው። አሁን ደግሞ ከኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመሆን የውልና ማስረጃን አሠራር ለማፋጠን ትልቅ ሚና ለመጫወት በቅቷል። \n\nበዛሬው ዕለት በ'ቪዲቸር' የተደገፈው የውክልና አሠራር በዋሺንግተን ዲሲ ባለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ተመርቋል። ለሕዝብ አገልግሎትም ሥራ ላይ እንዲውል ይፋ ተደርጓል። \n\n• በቴክኖሎጂ ኢ-ፍትሐዊነትን የምትታገለው ኢትዮጵያዊት \n\n• ሞባይል ለኢትዮጵያ እናቶችና ህፃናት ጤና \n\nየተጓተተ የውክልና ሂደት\n\nከሁለት ዓመት በፊት ነበር ከውክልና አሠራር ጋር ኬብሮን ግብ ግብ የገጠመው። በኢትዮጵያ ያለን የንግድ ተቋም ዘመድ እንዲያንቀሳቅስለት በማሰብ የውክልና ሂደቱን ቢጀምርም በካሊፎርኒያና በአካባቢው ውክልና የሚጽፍለትም ሆነ የሚያረጋግጥለት ማግኘት ሳይችል ቀረ። ከስድሰት ሰዓታት የአየር ጉዞ በኋላ በዋሽንግተን ዲሲ ሂደቱን አስጀመረ። ውክልና የመስጠት ተግባሩ ግን ቀላል አልነበረም። \n\n11 የተለያዩ ነገሮችን ማሟላት ይጠይቅ እንደነበር እንዲሁም በሕግ ባለሙያ አረጋግጦ ቢያንስ 40 ቀናት መጠበቅ ግድ እንሆነ ይናገራል። ከስንት ወጣ ውረድ በኋላ ኢትዮጵያ የደረሰው የውክልና ወረቀት ስህተት አለበት በመባሉ በድጋሚ ለማሠራት መገደዱንም ኬብሮን ይናገራል። \n\nእንደዚህ ዓይነት ችግሮች መኖራቸውን ከዚህ ቀደም ከብዙ ሰዎች ይሰማ የነበረ ቢሆንም በእርሱ ላይ ከደረሰበት በኋላ አሠራሩን ለመቀየር ቆርጦ እንደተነሳ ይናገራል። በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር እና 'ቪዲቸር' መካከል በተደረሰው ስምምነት መሰረት የውልና ማስረጃን አሠራር ለመቀየርና 'ዲጂታላይዝ' ወይም 'አውቶሜት' ለማድረግም 'ቪዲቸር' ለተሰኘው የኬብሮን ተቋም ፈቃድ ተሰጠ። \n\nየሲሊከን ቫሊ ልጆች ትልቁን ኢትዮጵያዊ የመረጃ ቋት የመፍጠር ህልምን ሰንቀዋል\n\nእነ ፌስቡክ ግላዊ መረጃዎትን ያለአግባብ እንደሚጠቀሙበት ያውቃሉ?\n\nለመሆኑ 'ቪዲቸር' ምንድን ነው? \n\n'ቪዲቸር' ማለት የእንግሊዘኛውን 'ቪድዮ' እና 'ሲግኒቸር' (ፊርማ) ቃላት በማጣመር የመጣ ቃል ሲሆን ስሙ እንደሚገልፀውም እራስን ቪድዮ በማንሳት መፈረም ማለት ነው። \n\n\"በብዕር ጫር ጫር የሚደረገው ፊርማ\" የሰውን ደህንነት ይጠብቃል ብዬ አላምንም የሚለው ኬብሮን፤ አንድ ሰው ውክልና ለሚሰጠው ሰው በሰነዱ መስማማቱን እየገለፀ እራሱን በቪድዮ ይቀርፃል። ቪድዮውም በሰነዱ ይካተታል ስለዚህም ለማረጋገጥ ቀላል ይሆናል ሲል ያስረዳል። \n\n\"ጥሩነቱ ማንኛውም ባለ ጉዳይ ካለበት ሆኖ መተግበሪያውን በስልክ በመጫን ቪድዮውን ቀርፆ መላክ መቻሉ ነው። ለጊዜው ግን በአሜሪካ ላሉ ኢትዮጵያውያን ብቻ ነው የጀመርነው\" በማለት ሂደቱን ያብራራል። \n\n\"በመጀመሪያ ንግግሬን ከአምባሳደር ግርማ ብሩ ጋር ነበር የጀመርኩት ከዚያ በኋላ ከአምባሳደር ካሳ ተክለብርሃን ጋር ወደ ስምምነት አደረስነው። አምባሳደር ካሳም የቴክኖሎጂውን ሃሳብ ወደ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በመላክ ወደ ውሳኔ አደረሰው በማለት ወደ ሥራ እንዴት እንደገባ ያስረዳል። \n\nከውጪ ሃገር ወደ ኢትዮጵያ የሚላክ የውክልና ሂደት ምን ይመስል ነበር?\n\n1) ወካይ በአቅራቢያው ባለ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በማምራት የውክልና ሰነዱን ያጽፋል\n\n2) ኤምባሲው ውክልናውን ተረክቦ ከገመገመ በኋላ ፊርማና ማህተም አስፍሮ ለአመልካች ያስረክባል\n\n3) አመልካች ሰነዱን ከኤምባሲ ተረክቦ ወደ ፈጣን የፖስታ አገልግሎት ወይም ወደ ፖስታ ቤት በመሄድ... ", "passage_id": "b422a6217e3c923dbd959c392f734307" }, { "passage": "ሴትየዋ እነደምትለው የሰርግ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተሳተፈችው በአንድ ድርጅት ውስጥ የሰርግ አዘጋጅ ሆና ለመቀጠር የመጨረሻው ፈተና እንደ ሙሽራ መተወን እንዳለባት ከተነገራት በኋላ ነበር። \n\nበስነ-ስርዓቱ ላይም እሷና እንደ ባል ሆኖ ይተውን የነበረው ባለቤቷ ህጋዊ ፊርማ ተፈራርመዋል። የሆነውን ሁሉ ያወቀችውም ወደ ሆንግ ስትመለስ እንደሆነ ታውቋል። \n\nወዲያው ለከተማው ፖሊስ ብታመለክትም ወንጀል መፈጸሙን እና ተገዳ የፈረመች መሆኑን ማስረጃ ማቅረብ ስላልቻለች ጉዳዩ መፍትሄ ሊያገኝ አልቻለም።\n\n• ትዳር ከባድ የጤና ችግሮችን ለመከላከል\n\nስሟ እንዲጠቀስ ያልፈለገችው ሴት ከሁለት ወራት በፊት በፌስቡክ በወጣ የስራ ማስታወቂያ ላይ ተመዝግባ ነበር። ስራውም ረዳት የሜክአፕ ባለሙያ ቢሆንም፤ ድርጅቱ ለሰርግ አዘጋጅነት እንድትወዳደር እንዳሳመኗት ገልጻለች። \n\nለስራው መመረጧ ከተነገራት በኋላም ለአንድ ሳምንት ስልጠና የወሰደች ሲሆን፤ በመጨረሻው ፈተናም በቻይናዋ ፉዞዉ ግዛት እንደ ሙሽራ ሆና አንድትተውን እንደተነገራት ትገልጻለች።\n\nበየዋህነት ወደ ግዛቲቱ የመንግስት መስሪያ ቤት ሄዳ የፈረመችው የጋብቻ ወረቀትም ህጋዊ ሆኖ ተገኝቷል። ጉዳዩ እስከሚጣራና ያገባችው ሰው ማንነት እስከሚታወቅ ድረስ ላልተወሰነ ጊዜ ባለትዳር ሆና እንደምትቆይም ተነግሯታል።\n\n• የደሞዙን 100 እጥፍ በስህተት የተከፈለው ሰው \n\n• ሽጉጥ ይዘው ለመንቀሳቀስ የተገደዱት ከንቲባ \n\nየሆንግ ኮንግ ፖሊስ እንደገለጸው በየዓመቱ ከ1000 በላይ ቻይናውያን ወደ ሆንግ ኮንግ የሚያስገባቸውን ህጋዊ ወረቀት ለማግኘት ከሆንግ ኮንግ ነዋሪዎች ጋር የውሸት ጋብቻ ይፈጽማሉ። \n\nየ21 ዓመቷ ወጣትም የዚህ ወንጀል ሰለባ ሳትሆን እንዳልቀረች ፖሊስ ገልጿል። \n\n ", "passage_id": "93a9b4ac189377cc29b20f0e048087aa" }, { "passage": "ለረዥም ጊዜያት የት እንደገባ ጠፍቶ የነበረው እሄ የስእል ስራ ባለቤት ጣልያናዊው ሲምባው ወይም ሲኒ ዲ ፒፖ እንደሆነም ኤክስፐርቶች አስታውቀዋል።\n\nእርግጥም ይህ የጥበብ ስራ የዚህ ጣልያናዊ መሆኑን ለማረጋገጥ በኢንፍራሪድ ምርመራም ተካሂዷል።\n\nስእሉ እአአ በሚቀጥለው ወር ለጨረታ የሚቀርብ ሲሆን 6̂.5 ሚሊዮን ዶላር ድረስ ሊያወጣ እንደሚችል ተገልጿል።\n\nዘመናትን የተሻገረውና ከፍተኛ ዋጋ ያለው ይህ ስእልን ያስቀመጡት አዛውንት ስእሉ ትልቅ የጥበብ ዋጋ ያለው ሃይማኖታዊ ስእል እንደሆነ ያምኑ እንደነበርም ተገልጿል።\n\n• የለማ ጉያ ድንቅ የቆዳ ላይ ሥዕሎች\n\n• ስለኢትዮጵያ የቤተ ክርስቲያን ስዕሎች ምን ያህል ያውቃሉ?\n\n ", "passage_id": "86d641ab8dbb02a1713f7285846ba58b" } ]
af521b829f54d23a7afb5934f6e67ad3
133007cdfae8837cce0e4f372ca9c95d
የአሰፋ ሳይንቲስት ውብ ወጎች
 ክፍል ሁለትባለፈው ሳምንት ክፍል አንድ ዝግጅታችን አሰፋ ሳይንቲስትን አስመልክቶ ጥቂት ወጎች ነበሩን። በጨለማው ዘመን የበሩት ፕሮፌሰር አሰፋ በፈረንሳይ ሀገር ኬሚስትሪ ያጠኑ ተመራማሪ ኢትዮጵያዊ ምሁር ነበሩ። እውቀቱ ገፋ ገፋ፤ ከመር ከመር ያደርጋቸው ነበር። ግን እኮ የቤተክህነቱንም ትምህርት ከግእዝ እስከ አራራይ የአማርኛውን ሰምና ወርቅ ጭምር ፈትለው ይገምዱት ነበር። ይሄ ምርምር የሚጠላውን ለማወቅ ጉጉት የሌለውን ደግሞ ‹‹ደናቁርት፤ ደነዝ፤ የሰው አጋሰስ፤ ሰው ነኝ›› ብሎ እኔ አሰፋ ሳንቲስት ሲሉ ካካታና ሳቅ ይበዛል። አሰፋ በተማሪው ዘንድ ምን አሉ? ምን ተናገሩ? እየተባለ እንደ አለቃ ገብረሃናም ፍቅር ዘርፈዋል፤ ይወደዳሉ። ተማሪ መሳቅ፤ መሳቅ፤ አብዝቶ መሳቅ መተረብ በተፈጥሮው ይወዳል። ሲጫወቱ አፍ ያስከድናሉ። በብዛት ወጋቸው ሕልማቸው ሃሳባቸው ሁሉ ሳይንስና ሳይንስ ብቻ ላይ ያተኩራል። ፈረንሳይ ከተማሩ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ጋር ወጋቸው ብርቱ ነው። ለነገሩ ጃንሆይስ አሳምረው ፈረንሳይኛ ይናገሩ አልነበር። ሳባ— ዊ– ሳባ፤ ሲ– መርሲ–መርሲ– ቦኩ እንዲሉ። አሰፋ ሳይንቲስት ነገር ካልመሰላቸው ነቋሪም ነበሩ። ሸንቆጥ፤ ላጥ አድርገው ደርሰው ያጥረገርጋሉ። ሲያሻቸው በቅኔ ይደበድባሉ። በውስጠ ወይራ አማርኛ አያድርስ ነው። ድንዙዝ እንዲሉ መሪጌታ ማን ይፈታዋል ብለህ ነው ምርቃት ይሁን እርግማን ከአዋቂዎች በቀር። ብትሰደብም መሳቅ ነው። አሰፋ ሳይንቲስት የሚያስተምሩበት ስንቱን ታላላቅ ኢትዮጵያዊ ያፈራው የተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት የዘመኑ ካምብሪጅ ነበር። ኮከብ፤ ቀንዲል አውራ።ታላላቅ የጦር መሪዎች ጀነራሎች፤ ፓይለቶች፤ ማሪኖች፤ ሚኒስትሮች፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራን፤ የሕክምናና ሌሎችም ዶክተሮች ወዘተ ተምረው ተመርቀው የወጡበት በዘመኑ እጅግ ታዋቂ ስሙ የገነነ የተጠራ ትምህርት ቤት ነበር፤ ተፈሪ መኮንን። አሰፋ ሳይንቲስት ቁመተ አጭር፤ ቁንን እንደነበሩ የሚያውቁአቸው ይናገራሉ። በዚያ ዘመን ስለሳይንስና ምርምር የሚያውቁ ሰዎች አልነበሩም። ግፋ ቢል የሰይጣን ስራ ነው የሚባልበት ነበር። አጤ ምኒሊክ ከውጭ ፊልም አስመጥተው በግድግዳ ላይ እንዲታይ ሲያስደርጉ የሰዎቹን ምስል በስክሪኑ ላይ ያዩት አያቶቻችን እያማተቡ ‹‹በስመ አብ–ወ– ወልድ ወ–መንፈስ ቅዱስ እነዚህ ሰይጣኖች ናቸው›› በማለታቸው ነበር ፊልም ቤቱ ሰይጣን ቤት የተባለው።መኪናም ስልክም ሲገባ እንዲሁ የሰይጣን ስራ ነው የሚል ተቃውሞው የበረታ ነበር። በዚያም ዘመን ነው አሰፋ ሳይንቲስት የኖሩት፤ የሰሩት፤ ምርምር አድርገው ሮኬት ለማስወንጨፍ የሞከሩት። በራሳቸው ምርምር በሀገር በቀል እቃዎች በመጠቀም ሮኬት ወደ ጨረቃ ለማስወንጨፍ የሞከሩ የመጀመሪያው ኢትዮጰያዊ። ስራቸው የሚታወቀው የሚደመመው ግሩም እምግሩማን አሰፋ ሳይንቲስት የተባለላቸው የተጨበጨበላቸው ሰው። አሰፋ ሳይንቲስት በኢትዮጵያ የጠፈር ምርምር ታሪክ ውስጥ አንድ ቀን ብርሃን ሆነው ይገለጣሉ። ታሪካቸው አምሮ ይጻፋል። ምርምራቸው ዶክመንቶቻቸው ቢፈተሹ አንድ ቦታ ሊያደርሱ ይችላሉ። ‹‹አሴ፤ አሰፋ ሳይንቲስት›› እያሉ ነው ራሳቸውን የሚጠሩት። ሌሎችም እንዲሁ። ለዛ ያለው ወግ አዋቂ ስለነበሩ በእርሳቸው ንግግር ተማሪው ይመሰጣል፤ ይደመማል፤ ያውካካል። ሲያሻቸውም ይጨምሩበታል። አለማድነቅ አይቻልም። ግሩም ድንቅ ።አንድ ጊዜ አሰፋ ሳይንቲስት ክፍል ውስጥ ገብተው ማታ ሕልም ማየታቸውን ይናገራሉ። ተማሪው እንደተለመደው አፉን ከፍቶ ያዳምጣል። ተኝተው ከአልጋቸው ግርጌ ታላቁና ኃያሉ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል የተንቆጠቀጠ ወርቅ ልብሱን ለብሶ ሰይፉን እንደያዘ ቆሞ ‹‹አሰፋ ሳይንቲስት ሲለኝ በመደንገጥ ተርበትብቼ አቤት ብዬ ተነሳሁ። እንካ ይሄ የአቶሚክ ቦምብ መስሪያ ፎርሙላ ቀመር ነው ተጠቀምበት አለኝ። በድንጋጤ ተውጬ እንደተቀበልኩ ተሰወረብኝ።›› እሺ አለ ተሜ አፉን ክፍቶ። ‹‹ይሄን ሚስጢር ለመከላከያ ሚኒስትርና የፈረንሳይ ተማሪ (ፍራንኮ ፎን) ለሆነው ለጀነራል አቢይ ወዳጄ ስለሆነ ሄጄ ነገርኩትና እባክህ ጃንሆይ ጋር እንድቀርብ አድርገኝ አልኩት›› አሉ።ጀነራል አቢይ ቀጠሮ አስይዞ አሰፋ ሳይንቲስትን ንጉሱ ዘንድ ይወስዷቸዋል። እጅ ይነሳሉ። ጉዳይህ ምንድነው አሰፋ ሳንቲስት ተብለው ሲጠየቁ በተለመደው ሥርዓት ለጥ ብለው ንጉሰ ነገስቱን እጅ ይነሳሉ። ቀጥለው በሕልማቸው የተነገራቸውን የቦምብ ፎርሙላ ቀመር ይናገራሉ። ‹‹እናሳ›› ሲባሉ ጃንሆይ እንድሰራ ይፈቀድልኝ ይላሉ። አሰፋ ሳይንቲስት አንድ አይናቸው በፈንጣጣ ሕመም በልጅነታቸው ጠፍቷል። በዚህም ትልቅ የአይን መነጽር ያደርጋሉ። ይሄን ንጉሱ ያውቃሉ። ንጉሱ በዙፋናቸው ሆነው ካዳመጡ በኋላ ለአሰፋ ሳይንቲስት መልስ ይሰጣሉ። ‹‹እሺ ልጃችን አሰፋ ሳይንቲስት አንተን ይህን ስራ ብሎ መፍቀድ ለኢትዮጵያ አንድ አይን ነህ፤ አንድ አይናችንን ማጥፋት ነው የሚሆንብን›› የሚል መልስ ሰጡ። አሴ በመጡበት ተመለሱ። ባለቅኔዋ ሀገሬ እንዴት ነሽ። ተማሪው ታሪኩን ሲጨርሱ ቅኔው ስለገባው በክፍሉ ከፍተኛ ሳቅ እየሳቀ አውካካ። አሰፋ ሳይንቲስት በክፍል ሲያስተምሩ ተማሪው የሚናገሩትን ለመስማት በናፍቆትና በጉጉት ይጠብቃል። ቀጠሉ ደግሞ በሌላ ቀን ተማሪዎች ክፍል ገብተው። ‹‹ሰማችሁ ተማሪዎች›› አሉ አሰፋ ሳይንቲስት ። ‹‹ከተማርኩበት ፈረንሳይ ሀገር ፓሪስ ከተማ በሚደረገው የሳይንቲስቶች ጉባኤ ላይ እንድገኝ ደብዳቤ ደርሶኛል›› ካሉ በኋላ ደብዳቤውን ለተማሪዎች እንዲህ ብለው አነበቡ። ‹‹ለተከበርከው ውድ ወዳጃችን ወንድማችን አሰፋ ሳይንቲስት፤ እንደምን ከርመሀል፤ በፈረንሳይ ፓሪስ ከተማ የዓለም ሳይንቲስቶች ስብሰባ ስለሚካሄድ በዚሁ ስብሰባ ላይ እንድትገኝ በክብር ተጋብዘሃል። አክባሪህ ራስቤልድ።›› ብለው የፈራሚውን ታዋቂ የፈረንሳይ ሳይንቲስት ስም ያነባሉ። ተማሪው ፍንድት ብሎ በሳቅ ያውካካል። ያ ፈረንሳዊ ሳይንቲስት የሞተው ከ100 ዓመት በፊት ነበር። በዚያ ዘመን በሕይወት የለማ። አሴን አለማድነቅ አይቻልም። አሰፋ ሳይንቲስት ከትምህርት ቤት መልስ ሁል ጊዜ ማታ ማታ ሲዝናኑ የሚያመሹት ከጥንት ጀምሮ ታዋቂ በሆነው የአራት ኪሎው ቱሪስት ሆቴል ነበር። ተመርቀው ስራ የያዙ ተማሪዎቻቸው በብዛት ቱሪስት ሆቴል ነበር የሚርመሰመሱት። አሰፋ ሳይንቲስት ሲመጡ ወጉ ጨዋታው ይደራል። ተጋብዘው ጠጥተው ሲጨርሱ አሰፋ ሳይንቲስት ተነስተው ውልቅ ብለው ነው የሚሄዱት። አመላቸው ይታወቃል። ሲጀመር ተማሪዎቻቸው ስላሉ ማንም ሂሳብ አያስከፍላቸውም። ከተጋበዙ በኋላ አመሰግናለሁ ፤ ደህና እደሩ የሚል ቃል ከአሴ አፍ አይወጣም። ብለውም አያውቁ። ተማሪዎቹ እርስ በእርስ መከሩና አሰፋ ሳይንቲስት መቼም የሚለው አያጣ ቆይ እስቲ ብለው አንዱ ተማሪያቸው እንዲናገራቸው ተወከለ። አንድ ቀን ምሽት እዛው ቱሪስት ሆቴል እየተዝናኑ እያሉ ‹‹ጋሼ አሰፋ ሁሌ ግዜ እንጋብዝዎታለን ወደቤት ሲሄዱ አመሰግናለሁ እንኳን አይሉም፤ ለምንድ ነው?›› ይላቸዋል። ምን አልክ አሉት። እየሳቀ ደገመላቸው። እዛው አራት ኪሎ ቱሪስት ሆቴል ውስጥ ነበሩ። ‹‹ሰማሁህ ፤ሰማሁህ፤ ና፤ና ተከተለኝ›› ብለው ከሆቴሉ ይዘውት ይወጣሉ። ከሆቴሉ ፊት ለፊት ተኮልኩለው የሚሰሩትን ሊስትሮዎች አየሃቸው ብለው ያሳዩታል። አዎን አየኋቸው ብሎ መለሰ። ‹‹ይኸውልህ እኔ አሰፋ ሳንቲስት ባላስተምርህ ኖሮ እንደነሱ ሆነህ ትቀር ነበር። ስለዚህ የምትጋብዙኝ የልፋቴን ዋጋ ነው። ምስጋና አያስፈልገውም›› ብለው እርፍ። ተመለሱና አብረው ወደ ሆቴሉ ገቡ። ‹‹ምን አለ አሴ?›› አሉ ውስጥ የነበሩት ጓደኞቹ። ‹‹እሱን ማን ይችላል›› አላቸው። በመሃል እንደተለመደው ደህና እደሩም አመሰግናለሁ ሳይሉ አሰፋ ሳይንቲስት ውልቅ ብለው ወደቤታቸው እብስ አሉ። አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 23/2012 ወንድወሰን መኮንን
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=25046
[ { "passage": "የዩናይትድ ስቴትሱ የኢትዮጵያውያን የሽልማት ድርጅት፤ ማኅበረ ግዩራን ዘረ ኢትዮጵያ (በእንግሊዝኛው ምህጻረ-ቃል SEED) እና የዘንድሮ ተሸላሚዎቹ።ለማኅበረሠብ ልዕልና እና መሻሻል ባደረጉት ልዩ አስተዋፅኦ ከተመረጡ ባለ መልካም ታሪኮች ታሪክና ሥራየሙዚቃ ወግ፥ ከእውቁና አንጋፋው ድምጻዊ ሙዚቀኛና የሙዚቃ አቀናባሪ ግርማ በየነ ጋር .. ", "passage_id": "ed6ed5e6979612b1279252c125c3b02d" }, { "passage": "የዩናይትድ ስቴትሱ የኢትዮጵያውያን የሽልማት ድርጅት - ማህበረ ግዩራን ዘረ ኢትዮጵያ - እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር በ2015 ዓም ለክብር ካበቃቸው “የማሕበረሰብ ፈርጦች” አንዱ ነበር።ለዕድሜ ልክ የጥበብ ሥራዎቹ እና ለማህበረሰብ ልዕልና ላበረከተው አስተዋጽኦ ለተሰጠው ለዚህ ሽልማት በሥነ ሥርዓቱ ለመገኘት ወዲህ ወደ ዋሽንግተን ብቅ ባለበት ወቅት ወደ ስቱዲያችን ጎራ ብሎ ስለ ጥበብ እና ስለ ህይወትም ሊያወጋን ዘለግ ቆይታ አድርገናል።\n ", "passage_id": "25cbd6de62267e431919111ba568ecab" }, { "passage": "ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነትን በሥነ ጥበባዊ ገጽታ፣ ብሂልን ከባህል አዛምደው በጥበብ ገበታ ለዓለም ያስተዋወቁ ናቸው፡፡ በሥዕል የለሙ፣ ሥዕልን ያለሙ ሥዕልን በጉያቸው ይዘው ከስድስት አሠርታት በላይ የዘለቁ ናቸው፡፡ በተለይ ከሌሎች ጠቢባን የሚለያቸው በፍየል ቆዳ ላይ የሚነድፏቸው ምስለ አካሎች (ፖርትሬት) በግዝፈት አንግሷቸዋል፡፡  በኩር (ሌጀንድ) ሠዓሊና መምህር የአየር ኃይል ሻምበል ለማ ጉያ፡፡ በደራሲና ተርጓሚ ታደለ ገድሌ (ዶ/ር) የወግ ገበታ ሠዓሊ ለማን እንደገለጻቸው “ከሠዓልያን ሁሉ ለየት ያለ የአሣሣል ጥበብን ይከተላሉ፡፡ በዋነኛነት ትኩረት የሚያደርጉትም ቪዡዋል አርት በሚባለው የአሣሣል ጥበብ ላይ ነው፡፡ ይኸውም የሚታይ፣ የሚዳሰስ፣ የሚጨበጥ የጥበብ ሥራ ሲሆን የሚጠቀሙበት ቁሳቁስ የፍየል ወይም የበሬ ቆዳ፣ የውኃ ቀለም፣ የዘይት ቀለም፣ ከሰል (ቻርኮል) ነው፡፡”ልሒቅ ሥነ ጥበበኛ ለማ ገጸ ታሪካቸው እንደሚያሳየው፣ በቆዳ ላይ መሣል የጀመሩት በኅብረተሰብአዊት ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ ዘመን ጀምሮ መሆኑንና በመጀመሪያ በፍየል ቆዳ ላይ የሣሉትም የቀድሞው የዚምባቡዌ ፕሬዚዳንት ሮበርት ሙጋቤን ሲሆን ከኢትዮጵያ ነገሥታትና መሪዎች መካከል ከአፄ ቴዎድሮስ እስከ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ድረስ የነበሩትን ሠርተዋል። ሥዕላቱ በቢሾፍቱ ከተማ በገነቡት ሙዚየማቸው ውስጥ ይገኛሉ፡፡ የየብሔረሰቡን የአለባበስና የአኗኗር ዘይቤን የሚገልፁ በተለይም የኦሮሞን ሕዝብ ትውፊትን የሚያጎሉ ሥዕሎችን በመሣል ይታወቃሉ፡፡፡በ65 ዓመታት የጥበብ ጉዞአቸው ያፈሩት የጥበብ ሥራ 10,000 እንደሚደርስ ይወሳል፡፡ ሥዕሎቻቸውን በግል በአሥመራ፣ በአዲስ አበባ፣ በደብረ ዘይት በዓውደ ርዕይ ለዕይታ ከማቅረባቸው ባሻገር በውጭ አገሮች በኅብረት ካቀረቡቧቸው መካከል የናይጄርያ መዲና ሌጎስና የሴኔጋሏ ዳካር ይገኙባቸዋል፡፡ በልጃቸው ሠዓሊት ነፃነት ለማ አማካይነትም በአሜሪካ ኒው ዮርክ ከተማ  ያዘጋጁትን ዓውደ ርዕይ የከፈቱት በወቅቱ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ኮፊ አናን ናቸው፡፡የጅማ ዩኒቨርሲቲ በሥነ ጥበብ የክብር ዶክትሬት በ2007 ዓ.ም. በሰጣቸው ጊዜ የአንደኛውን ሥዕላቸውን አንድምታ አንደሚከተለው አቅርቦታል፡- “በተለይ በሕዝብ ዘንድ ትልቅ አድናቆትን የሰጠውና በሹማምንት ልዩ ትርጉምና አቃቂር በማውጣት ከየወቅቱ አዛዦች ጋር እንዲላተም ካስደረጉት የበኩር ሥራዎች ሳትጠቀስ የማታልፈው ቋንጣ የምትባለው ሥዕል ነች፡፡ ቋንጣ የአፍሪካን የሀብት ምዝበራ ወይም ሙስናን ፍንትው አድርጋ ታሳያለች፡፡ በአንድ ቤት ጓዳ ውስጥ ቋንጣ በቀይ መልኩ ተዘልዝሎ ይታያል፡፡ ድመቶች ቋንጣውን መዥርጠው ለመብላት ይታገላሉ፡፡ ጠፍሩ አልጋ ላይ በድምሩ አራት ድመቶች ወጥተዋል፡፡ አንደኛው ግድግዳው በጥፍሩ ቧጥጦ ያወርዳል፡፡ አንዱ ቁመቱ አልደርስ ብሎታል፡፡ አንደኛው ደግሞ በእጁ የገባለትን እንደያዘ ሌላ ለማግኘት አንጋጧል፡፡ በእነርሱ ግፊያና ግርግር ጮጮ ሙሉ ወተት ተደፍቷል፡፡ የወተቱ አወራረድ የዓባይ ፋፏቴን ተመስሎ ቀርቧል፡፡ የመጨረሻው ድመት የሸረሪት ድር የወረሰውን ድብኝት አፍጦ በሸረፋት ድር የተያዘውን ነፍሳት ለመያዝ ያስባል፡፡ ይህ ሁሉ ሲደረግ ግን ከአልጋው ስር አይጥ እሸት በቆሎ ትቀረጥፋለች፡፡ ይህንን ሥዕል ስትመለከቱት የራሳችሁ ፍርድ ትሰጣላችሁ፡፡”ቢቢሲ በአንድ ወቅት ስለ ቋንጣውና ስለድመቶቹ እንዲሁም ስለወተቱ ለማ ጉያ እንዲያብራሩለት ጠይቋቸው ሥዕሉን ከሠሩት 42 ዓመታት ማስቆጠሩንና በዚህ ሥራቸውም አፍሪካና ችግሮቿን ያሳዩበት እንደሆነ ገልጸውለት ነበር። “የአፍሪካ መሪዎችን በድመቶቹ መስለው የሀገራቸውን ሀብት በሙስና ሲመዘብሩ፣ በአልጋው ሥር የሚታዩት የአህጉሪቷ ጠላት አይጦች ደግሞ የአፍሪካን ሀብት ሲቀራመቱ ይታያሉ፡፡ እየፈሰሰ ያለው ወተትም ያለጥቅም ለዘመናት የሚፈሱት የአፍሪካ ወንዞች ምሳሌ ነው።”ከአባታቸው ከአቶ ጉያ ገመዳና ከእናታቸው ከወ/ሮ ማሬ ጎበና በ1921 ዓ.ም. በቀድሞው አጠራር በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አድአ ሊበን ውስጥ ልዩ ስሙ ደሎ ቀበሌ የተወለዱት ሻምበል ለማ ጉያ፣ እንደማንኛውም የኢትዮጵያ እጣ ፈንታው የቆየው እንደ ሌሎቹ የአካባቢው ተመሳሳይ ልጆች ተለምዶአዊው የአባታዊ የሥራ ፈለግ ውርስ ሳይሆን ያልተለመደውን የወ/ሮ ማሬ ጎበናን የዕደ ጥበብ ብቃት ነቅሶ በመያዝ ከዕቃ ዕቃ ጨዋታው በላይና ከሚያዩት የመገልገያ መሣሪያ የሸክላ ውጤቶች ውጪ ከዕድሜያቸው በላይ ወደሠሯቸው ቅርፃ ቅርፆች እንደነበረ ግለ ታሪካቸው ያሳያል፡፡ የመጀመርያ ደረጃ ትምህርታቸውን በአፄ ልብነ ድንግል ትምህርት ቤት ያጠናቀቁ ሲሆን መምህራን ትምህርት ተቋም ለተወሰነ ጊዜ ከተማሩ በኋላ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መልካም ፈቃድ አየር ኃይል በመግባትና በአርሜንት ኮርስ በካዴትነት በመሠልጠን ተመርቀዋል፡፡አገልግሎታቸውንም በሒደት በአስመራ ከተማ በአየር ኃይል መምህርነት ነበር የጀመሩት፡፡ሻምበል ለማ ጉያ ከሠለጠኑበት ሙያ በተጓዳኝ ወደ ጥበቡ የዘለቁበትን ክሂል የቀሰሙት በአስመራ የጣሊያኖች የሥዕል ትምህርት ቤት መማራቸው ነው፡፡ በተለይም በወታደር ቤት እምብዛም የሲቪል ጉዳዮችን ባልተለመዱበት ሁኔታ የሥዕል ዓውደ ርዕይን በማቅረብ በአንድ በኩል በወታደራዊ ትምህርቱ የተሰጣቸውን ግዳጅ እየተወጡ በሌላ በኩል የጥበብ ፍቅራቸውን ሠርተው በማሳየትና ለጥበብ ቀናኢነታቸውን ማሳየታቸው ይወሳል፡፡ “ሥዕል ያለ አስተማሪ” መጽሐፍ አዘጋጅቶ በማሳተምም ተጠቃሽ ናቸው፡፡ባደረባቸው ሕመም ምክንያት  ሕክምና ሲከታተሉ የቆዩት  ሥነ ጠቢቡ ሻምበል ለማ ጉያ በ92 ዓመት ዕድሜያቸው ዜና ዕረፍታቸው የተሰማው ጥቅምት 16 ቀን 2013 ዓ.ም. ነው፡፡ ሥርዓተ ቀብራቸውም ከቢሾፍቱ አቅራቢያ በትውልድ ስፍራቸው በሚገኘው ደሎ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን እንደሚፈጸም ታውቋል፡፡ልሒቁ ሥነ ጥበበኛ ሻምበል ለማ ጉያ ሦስት ሴቶችና ሁለት ወንድ ልጆችን አፍርተዋል፡፡ አምስቱም ልጆቻቸው የአባታቸውን ፈለግ የተከተሉ ሥነ ጠቢባን ናቸው፡፡የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አለ የሥነ ጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት ዲን ሠዓሊ አገኘሁ እንግዳ ሥነ ጠቢቡን እንዲህ ገለጹ፡- “ሻምበል ለማ ጉያ አንጋፋ የሥነጥበብ ሰው ነበሩ፡፡ የሥዕል ማስተማሪያ መጽሐፋቸው ብዙዎቻችንን የሥነጥበብ ‹ሀ ሁ› ያስቆጠረ፣ ተሰጧችንን ፈልገን እንደናገኝ የረዳ ነበር፡፡ ይህን የማይረሳ ውለታቸውን የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሥነጥበብና ጠቢባኑ ሲያስታውሱት ይኖራሉ፡፡ ለሙያው ታምኖና በትጋት ሳያቋርጡ ሠርቶ ስምና ዝና ማትረፍ እጅግ ከባድ በሆነበት በኛ ሙያ፣ ይህን ድልና ገድል መቀዳጀታቸው ያስመሰግናቸዋል፡፡ ጠንካራ ሙያተኛ ነበሩ:: ሻምበል ለማ የሰላም ዕረፍት ይሁንልዎ!!”", "passage_id": "97a71089f1765bba3c7e12e26efadb75" }, { "passage": "የሕክምና ባለሙያው ወደ ትምህርት ቤታቸው መጥተው ለእርሱና ለክፍል ጓደኞቹ የባዮሎጂና የኬሚስትሪ ትምህርቶች ላይ እገዛ ሲያደርጉላቸው ሲያይ ተደንቋል። \n\n• ከአንደኛ ክፍል ዲግሪ እስኪጭኑ ከልጃቸው ጋር የተማሩት አባት\n\nበዋርዴር አጠቃላይ ሆስፒታል ውስጥ ሐኪም የሆኑት ዶ/ር መሐመድ አሊና ዶ/ር አህመድ ናስር አብዱርህማን ዘወትር ቅዳሜና እሁድ ወደ ዋርዴር ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጠመኔ ይዘው ይሄዳሉ።\n\nበትምህርት ቤቱ ውስጥ ስለተላላፊ በሽታዎች፣ ስለንጽህና አጠባበቅ አልያም ስለ ሥነ ተዋልዶ ጤና ለማስተማር ሳይሆን የሚገኙት፤ መደበኛ የትምህርት ሥራውን ለማገዝ ነው።\n\nውለታን የመመለስ ጉዞ\n\nዋርዴር ከጅግጅጋ 520 ኪሎ ሜትሮች ርቃ የምትገኝ ከተማ ነች። ከጅግጅጋ ተነስቶ ወደ ከተማዋ መምጣት የሚፈልግ ቀብሪ በያን፣ ደገሃቡርን፣ ቀብሪ ደሃርን ማለፍ ይጠበቅበታል።\n\nበዚች የገጠር ከተማ በሚገኘው በዋርዴር አጠቃላይ ሆስፒታል ከሚያገለግሉት የሕክምና ባለሙያዎች መካከል ዶ/ር መሐመድ አሊ አንዱ ናቸው። ተወልደው የፊደል ዘር የለዩትም በዋርዴር መጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መሆኑን ይናገራሉ።\n\n• ወላጆች ለልጆቻቸው የሚመኟቸው ኢትዮጵያዊ መምህር \n\nዶ/ር መሐመድ በሚማሩበት ወቅት በትምህርት ቤታቸው የመምህራንና የትምህርት መርጃ መሳሪያ እጥረት በመኖሩ በትምህርታቸው ላቅ ያሉ ተማሪዎች ደከም ያሉትን በመርዳት ያስጠኑ እንደነበር ያስታውሳሉ። \n\n\"እኛን ከሚያስጠኑን መካከል እኮ አንዱ መሐመድ ፋራህ ነው። አሁን በጅግጅጋ ዩኒቨርስቲ ውስጥ መምህር ነው\" የሚሉት ዶ/ር መሐመድ፣ ከዚህ በተለየ ደግሞ በግላቸው ከትምህርት ሰዓት ውጪ የሚያስጠኑ ግለሰቦች ጋርም በመሄድም ያጠኑ እንደነበር ይናገራሉ። \n\nበሶማሌ ክልል ዶሎ ዞን ተወልደው በተለያዩ የሥራ መስኮች የተሰማሩ ምሁራን የአካባቢውን ተማሪዎች መማሪያ ክፍላቸው በመገኘት ሲያበረታቱ\n\nበአንድ ወይንም በሁለት ክፍል ይቀድሟቸው የነበሩ የትምህርት ቤት ጓደኞቻቸው ሒሳብ፣ ፊዚክስ፣ ባዮሎጂና ኬሚስትሪ በማስጠናት በትምህርታቸው እንዲጠነክሩና አሁን የደረሱበት እንዲደርሱ አግዘዋቸዋል።\n\nየሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጥሩ ውጤት አጠናቀው ወደ ጅማ ዩኒቨርስቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ በመግባት ሕክምና አጠኑ። ከተመረቁ በኋላም እንዲያገለግሉ የተመደቡት የቀለም ዘር በለዩበት፣ እጃቸው እስክርቢቶ ጨብጦ ከወረቀት ባገናኘበት ዋርዴር ሆነ።\n\n• ተማሪዎች መገረፍ አለባቸው የሚሉት የታንዛኒያው ፕሬዝዳንት\n\nእርሳቸውና ጓደኞቻቸው ከትንሽ ብላቴናነት ተነስተው ዶክተር እስኪሆኑ ድረስ በፍቅር አቅፋ፣ በእውቀት እንዲጎለምሱ ያደረገችው ዋርዴር እንደቀድሞው ሆና አልጠበቀቻቸውም።\n\nመስኩ፣ ተራራው ትምህርት ቤቱ ያው ቢሆንም አንድ ነገር ግን ተለውጧል።\n\nዶ/ር መሐመድ አንደሚሉት የተለወጠው ነገር ከዶሎ ዞን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም የሚገቡት አፍላ ወጣቶች ቁጥር ከዕለት ወደ ዕለት እያነሰ መሄዱ ነበር። \n\n\"የተወሰን ነው ምህንድስና፣ የተወሰኑት በሂሳብ ሙያ፣ ቀሪዎቻችን ደግሞ ሕክምና አንዳንዶቹም ዩኒቨርስቲ መምህራን ሆነን ሳለ በአካባቢያችን ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ተማሪዎች ቁጥር ማነሱ አሳሰበን\" ይላሉ ዶ/ር መሐመድ። \n\nያለ መፍትሔ የማይመጣው ችግር\n\nከዚያም ሰብሰብ ብለው፤ ለመሆኑ ባለፉት ስድስትና ሰባት ዓመታት ከአካባቢያችን ወደ ዩኒቨርስቲ የገቡ ተማሪዎች ቁጥር ምን ያህል ይሆናል ሲሉ ጥናት አደረጉ። \n\nያገኙት ውጤት ከገመቱት በታች መሆኑን የሚናገሩት ዶ/ር መሐመድ፤ መፍትሄ ያሉትን አስቀመጡ።\n\n ለመሆኑ ተማሪዎቹ ጥሩ ውጤት ላለማምጣታቸው ምክንያታቸው ምንድን እንደሆነ ለያችሁ?\n\nዶ/ር መሐመድ፡ አዎ፤ የትምህርት አሰጣጡ ድክመት፣ የትምህርት መርጃ መሳሪያዎች አቅርቦት... ", "passage_id": "6edbffaa3b45fbae99ca5272a4ee04ee" }, { "passage": "በመንደሩ ብዙ ታዋቂ ሰዎች አሉ:: መገናኛቸው ሰፊ ነው:: በዝክር፣ በአርባ ፣በድግስ በሰርግ፣ በልደት ወዘተ:: ወጋቸው ይደራል:: በተለያየ ዘርፍ ባለሙያዎች አሉ:: ሲደብራቸው እንዴት ነህ እግዜሩ የሚሉም ፈላስፎች አሉበት:: እነሱ ለሕይወት ቅመማ ቅመም ናቸው:: ያጣፍጡልሃል:: እኔ ጥያቄዬ ለእግዜሩ ነው:: እንደው ምን ስትል ፈጠርካቸው አንተዬ ብለው አያገባህም እንደው ሰው በምን ይደበር በምን ያልቅስ በምን ይጩህ በምን ይንከትከት በምን ይትከን ያለኝ መሰለኝ በጆሮዬ:: የባሰ አታምጣ ::ለካስ አንተም የባሰብህ ነህና በል በል ተወኝማ ብዬ በዚያ ቅጥ አምባሩ በጠፋ የመንደር መንገድ ቆዝሜ መራመድ ቀጠልኩ:: ብርቱ የማሪቱ ሽታ ያንን ጥርጊያ የአፈር\nመንገዱንና ሰፈሩን ያምሰዋል:: በነፋስ እየተሞላ ሽው ይላል:: አንድ አዛውንት ከዘራቸውን ይዘው ወገባቸው ጎብደድ ብሎአል በቀስታ\nእየተራመዱ ከበራፉ ሰደርሱ አየሁ:: የማያባራ ጫጫታ:: ሁካታ:: ህብረ ብሄር ጫጫታ:: ብርቱ ጫጫታ:: የማሪቱ ቤት መሆኑ ገባኝ::\nነጋሪም አያሻው:: የሀገሬ ሕዝብ ትልቁ መዝናኛ ማእከል እሱ ነው:: ፊልም ቤት፣ትያትር፣ መዋኛ ፣ባር፣ ሬስቶራንት ብትለው አይሰማህም::\nአሀ እንዴት ብሎ የማያውቀውን ማን ሊሰማህ:: የሰፊው ሕዝብ መድረክ እዛ ነው:: እዛ ነው ፍልስፍናው ለዛና ቁምነገሩ ጨዋታው ያለው::\nአለም የሚቀልጠው፣ነፍስ በሀሴት የምትሞላው\nማሪቱ ቤት ነው:: ነፍሱን ይማረውና አንድ መሪጌታ አጎት ነበረኝ :: ጋይንቴ:: በዚያ ዠርጋዳ ቁመቱ ካባውን ለብሶ ጭራውን እየነሰነሰ\nሰበር ሰካ እያለ ሲራመድ ሲረገረግ ለአፍታ በአይኔ አስታወስኩትና እንባዬ አቀረረ:: መሪጌታ አፈወርቅ ወግ ይችል ነበር:: አንዳንዴ\nሞቅ ብሎት ይመጣል:: አንተ ጠጅቤት ምን ታደርጋለህ መሪጌታ ስለው –ጅሎ ስንቱ ሊቅ ሊቃውንት የተማረው የተመራመረው የሚገኝበትን\nቦታ መናቅህ ነው ይልና በጥያቄ መልሶ ያየኛል:: ገና ከንቢቱ ደጃፍ ስደርስ መሪጌታ መጡ መሪጌታ መጡ ይልና ያ ሁሉ ሰው ብድግ\nይላል፤ መቀመጫው ላይ ሳልቀመጥ በል ንሳ ቀጂ ፤እኔ ለመሪጌታ አንድ፣ እኔ ሁለት፣ አረ እኔ ሶስት ይላል የተቀመጠው ጋባዥ:: ወግ\nይጀመራል፤ ማውካካት ነው:: መሳቅ ነው:: መጫወት ነው አለሜ:: ምኑ ይጠገብ ብለህ የሚለኝ ትዝ ሲለኝ ዳግም እምባ ከጀለኝ::\nዛሬ ሁሉም የሉም::እኒያ ሽማግሌ ጎበጥ ብለው ከዘራቸውን ይዘው ወደ ጠጅ ቤቱ ሲገቡ ሳይ ነው የኋሊት\nወስደው መሪጌታን ያስታወሱኝ:: ደሞስ በእዛ እድሜ ሙሉ ቀን ስንት ወር ከቤት ተቀምጦ እንዴት ይገፋል፤ እንደው ሰው ወዳለበት ሄደው\nይጫወቱ እንጂ ምነው ምነው ታስሮ ወደ መቃብር መውረድ አለ እንዴ አልኩ ለራሴ:: አይ መሪ:: አባ ግርግር:: እሱ ብቻ አይደለም ቤቱ በሙሉ ይሞቀዋል::ሁሉም በሞቅታ ፈረስ ይጋልባል::\nማንም ማንንም አይሰማም:: ሁሉም ተናጋሪ ነው:: ሰሚ፣ አድማጭም የለም:: ኧረ ተደማመጡ ያልክ እንደሁ፤ ኧረ ዲሞክራሲ መብታችን\nእኮ ነው ይልሀል አባ ደፋሩ:: መከረኛው ዲሞክራሲም እየተንቀባረረ ጠጅ ቤት ገባ:: ዲሞክራሲ ሕግና ስርአትን አይጠላም:: የጠጅ ቤቱ ታዳሚዎች ስለዲሞክራሲ ብቻ ሳይሆን ስለ ፓርቲም ደግመው ደጋግመው ሰምተዋል:: ተደምመው\nእነሱም ማቋቋም አለብን ብለዋል:: 137 ፓርቲ በአገር ውስጥ አለ ሲባል እኛስ ለማቋቋም ምን ያንሰናል ብለው ወስነዋል::መጀመሪያ\nስም እናውጣ አሉ በመንጫጫት:: ዝም በሉ ደሞ ስም ለማውጣት ከእኛ ሞልቶ የተረፈ አይደለም እንዴ ምን ትላላችሁ አለ ከጠጅ ቤቱ\nእድምተኛ አንዱ:: እህሳ ደሞ የእድራችንን አይነት መተዳደሪያ ደንብ የፓርቲ ደንብ መጻፍ አለብን ያለሱ አይሆንም ሲባል ሰምተናል\nአሉና አውካኩ:: ተሰብሳቢው የጠጅ ቤቱ እድምተኛ በጠጅኛ ተኝጫጫ:: ዝም በሉ እስቲ :: ደሞ ይሄን ለመጻፍ ጡረታ የወጡት መምህር ቢራራ ይኸው መሀላችን አሉ አይደለም\nእንዴ:: ደግሞም ፍርድ ቤት ማመልከቻ የሚጽፈው አቶ አጎናፍር ደባልቄ አለ አይደለም ወይ ለዚህ አያንስም::ሌሎችም መምህሮች አሉ\nእዚሁ:: መምሬ አለምም ስለቤተክርስቲያን ደንቡ ላይ አንዳንድ ሀሳብ እንዲሰፍር ያደርጋሉ አሉና ዞር ብለው የተወሰኑ ሰዎች አይደለም\nእንዴ መምሬ ይሄ ይከብድዎታል አሏቸው:: መምሬ ጭራቸውን ያሉበት ሁነው በሞቅታ እየነሰነሱ አልቦ ነገር ዘይሰአኖ ለእግዚአብሄር\nአይሉም:: ጉደኛዋ ሀገሬ::ሳቅሽና ፈገግታሽ ሁሌም አይጉደል:: በዚህ መሀል ታዳሚው በሙሉ በጫጫታና ሁካታ ሀሳቡን ከደገፈ በኋላ በሰብሳቢው አማካኝነት ወጉ አልቀረም\nየምትደግፉ፣ የምትቃወሙ ብሎ ሲል የጠጅ ቤቱ አጥር እስኪነቃነቅ ድረስ ጭብጨባው አስተጋባ::ከውጭ ቆማ የነበረች የመምሬ በቅሎ በጭብጨባውና\nበጫጫታው ብዛት የታሰረችበትን ችካል እያስካካች ነቀነቀችው:: በራ ልትሄድ:: ማጨብጨብና መጮህ እንወድ የለ ? ምን ይደረጋል ብለህ\n:: ተረጋጉ ተረጋጉ አንዴ አንዴ አለ በአግዳሚው ወንበር መሀል ላይ የተኮፈሰው ሰብሳቢ:: ምንድነው ተረጋጉ\nየምትለው አሉት ሰዎቹ:: አሁን ለምንመሰርተው ፓርቲ ስም እናውጣ በፍጥነት አሉት:: ምን ገዶን አሉና ቀጠሉልሀ:: ደሞ ስም ለማውጣት\nስም ለመስጠት ማን ብሎን አለ ጀማው እያውካካ:: አንዱ በሞቅታ ብድግ ይልና አንድ ስም ይሰጣል:: ሌላው ይቀጥላል:: ሌላው ይነሳል::\nሌሎችም ባሉበት ሁነው ስም በመስጠት ይጮሀሉ:: አቤት የስሙ መብዛት አቤት የስም ጋጋታ:: ለፓርቲ የሚያስፈልገን እኮ አንድ ብቻ\nስም ነው አለ አንዱ ቆፍጠን ብሎ:: ተው ተው ተው ስንልህ:: አይበቃንም ሁላችንም አንድ አንድ ፓርቲ መፍጠር አለብን አለና አረፈው::\nሀ ሀ ሀ ሀ ሀ የሚል ድምጽና ሳቅ ቤቱን አናጋው:: ድንገተኛ የደስታ ጭብጨባ አስተጋባ:: ማን ፓርቲ መስርቶ ማን ይቀራል:: በቃ\nእያንዳንድሽ ፓርቲ ትመሰርቺያለሽ ማለት ነው:: ነገ እንደተለመደው ከምንጣላ መቼም ባሕሪያችን ክፉ ነውና በግላችን አንድ አንድ\nፓርቲ መስርተን እንገላገል በሚለው ተስማሙ::በሞቅታ\nስሜት ሲጽፍ የነበረው ጉርሜሳ ድምጹን ከፍ አድርጎ ሁሉም እንዲሰማ የተሰጡትን ስሞች አንብብ አሉት:: እናም የታጩት ስሞች በንባብ\nተደረደሩ:: ተናካሽ ፓርቲ ፣ ተንኳሽ ፓርቲ፣ ሰርሳሪ ፓርቲ ፣ ቀምቅም ፓርቲ ፣ ጨልጤ ፓርቲ፣ ጎንጤ ፓርቲ ፣ ፈላጭ ፓርቲ፣ ፈንካች\nፓርቲ ፣ አውልቅ ፓርቲ ፣ አስርግ ፓርቲ፣ አስማጭ ፓርቲ፣ አዝግ ፓርቲ ፣ ድፎ ፓርቲ፣ ድፍድፍ ፓርቲ፣ እያለ ሰውየው በሞቅታ ሲያነብ\nተሰብሳቢው እድምተኛ በከፍተኛ ድምጽና ጭብጨባ አድናቆቱና ደስታውን ገለጸ:: ነገ ማታ ሁልሽም ተገኝተሽ በፊርማሽ ታጸድቂያለሽ አለ\nጸሀፊው:: ለነገ ማታ ያድርሰን እያለ የነገን ጠጅ እየናፈቀ ሁሉም ወደየቤቱ ተፈተለከ:: ጉደኛዋ ሀገሬ ኑሪልኝ !!አዲስ ዘመን ታህሳስ 9/2012ወንድወሰን መኮንን", "passage_id": "a610e2e7fad614af44744a47bc5e5b08" } ]
c61133e77363ceaf2c397876da612b95
ef3f2b6627928ee7b8c29222f3c9de45
የመጸዳጃ ቤት ቆይታን ለማሳጠር
ዘመናዊ መጸዳጃ በሀገራችን ብዙም አልተስፋፋም ቢባል ዋሾ አያሰኝም፤ ይህን እጥረት መንግሥትም በሚገባ ያውቀዋል። ከዚህ አኳያም የመጸዳጃ ቤት አገልግሎትን በከተማ ለማስፋፋት እየተሰራ ይገኛል። በከተሞች የህዝብ፣ የመንግሥትና የሆቴል መፀዳጃ ቤቶች በስፋት የሚስተዋሉ ሲሆን፣ የመኖሪያ ቤቶች መጸዳጃ ቤቶች በስፋት እየዘመኑ ናቸው። በገጠርም በዚሁ ላይ ግንዛቤ በማስጨበጥ ሰዎች ጤናቸውን ለመጠበቅ በመጸዳጃ ቤት እንዲገለገሉ ለማድረግ በተለይ በጤና ኤክስቴንሽን ሰራተኞች በኩል እየተሰራ ነው። በከተሞች በተለይ በህዝብ መጸዳጃ ቤት አጠቃቀም ላይ ግን ተግዳሮቶች ይስተዋላሉ። መጸዳጃ ቤቶችን በንጽህና እና በአግባቡ አለመጠቀም አንድ መሰረታዊ ችግር ነው። መጸዳጃ ቤት ገብቶ ቶሎ አለመውጣት ሌላው ችግር ነው። አንዳንዶች ከጤና ጋር በተያያዘ በተለይ ድርቀት ያለባቸው ናቸው ይባላል መጸዳጃ ቤት እነዚህ ሰዎች መጽሀፍ ፣ጋዜጣ ወዘተ፣ ይዘው በመግባት እያነበቡ ብዙ ይቆያሉ። ሞባይላቸውን ይዘው ገብተው ኢንተርኔት ይሁን ሌላ የሚከታተሉም ጥቂት አይደሉም። ይህ አይነቱ የመጸዳጃ ቤት አጠቃቀም በተለይ በሆቴሎችና በህዝብ መጸዳጃ ቤቶች ተጠቃሚዎች ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ያሳድራል። የእነዚህ ተገልጋዮች ተግባር የራሳቸውንም የሌላውንም ተጠቃሚ ጊዜ ያባክናል። ይህ ችግር የሌሎች ሀገሮችም ችግር ነው። ችግሩ አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱን ተከትሎም አዲስ የመጸዳጃ መቀመጫ ዲዛይን ብሪታኒያ ውስጥ እስከ መስራት መደረሱን ኦዲቲ ሴንትራል ድረ ገጽ ሰሞኑን ይዞት በወጣ መረጃ አስነብቧል። ይህ መቀመጫ ሰዎች መጸዳጃ ቤት ውስጥ ከአምስት እስከ ሰባት ደቂቃ በላይ እንዳይቆዩ የሚያደርግ ነው። ይህ የመጸዳጃ ቤት መቀመጫ እንደ ሌሎቹ መቀመጫዎች ምቾት የሚሰጥ ባለመሆኑም ሰዎች ተቀምጠው እንዲያነቡም ሆነ ሞባይል እንዲነካኩ ብዙም እድል አይሰጥም ይለናል መረጃው። መቀመጫው ዲዛይን የተደረገው በእንግሊዛዊው መሀንዲስ ማሃቢር ጊል ሲሆን፣ ከመደበኛው መጸዳጃ መቀመጫ በ13 ዲግሪ ቁልቁል ያጋደለ ነው፤ ሰዎችም በዚሁ ልክ አጋድለው እንዲቀመጡ የሚያደርግ በመሆኑ ምቾት ይነሳል። ጊል የዚህ መቀመጫ ሃሳብ የተከሰተለት መጸዳጃ ቤት ተጠቃሚዎችን ምቾት ስለሚነሳቸው ቶሎ ጣጣቸውን ጨርሰው እንዲወጡና የኪስ ስልክ እያዩ ጋዜጣ ወይም እያነበቡ እንዳይቆዩ በማሰብ ነው። የተቀጣሪዎችን የሥራ ሰዓት ማስፋት ለሚፈልጉ ነጋዴዎችም መልካም አጋጣሚ መሆኑን ይገልጻል።“በእንግሊዝ ብቻ በአንድ የሥራ ቀን ሰራተኞች አለአግባብ የሚያባክኗቸው ጊዜያት የኢንዱስትሪና የንግድ ባለሀብቶችን በዓመት 4 ቢሊዮን የእንግሊዝ ፓውንድ እንደሚያስወጣቸው ይገመታል።” ሲል ሚስተር ጊል ጠቅሶ፣ አዲሱ የመጸዳጃ ቤት መቀመጫ ሠራተኞቻቸው በመጸዳጃ ቤት አለአግባብ የሚያጠፉትን ጊዜ በማዳን ቀጣሪዎች የበለጠ ሀብት እንዲያፈሩ ያስችላል ይላል።አዲሱ መቀመጫ ለትርፍ ባልተቋቋመው የብሪቲሽ መጸዳጃ ቤቶች ማኅበር ተቀባይነት ያገኘ ሲሆን ፤ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ግን የመጸዳጃ መቀመጫውን ዲዛይን በስላቅ አጣጥለውታል ።በመጸዳጃ ቤት ለረጅም ጊዜ መቆየት አይገባም ሲል በድረ ገፅ ላይ አስተያየቱን የሳፈረው ጊል፣ ለእዚህም ሲል አጨቃጫቂውን የመፀዳጃ ቤት መቀመጫ ዲዛይን መስራቱን ለዊርድ መጽሔት ጠቁሟል። አንዳንዴ ሠራተኞች በመጸዳጃ ቤት ተኝተው እንደሚገኙም ጠቅሶ፣ በሕዝብ መጸዳጃ ቤቶችም ወረፋዎች እየበዙ ተራ የሚጠብቁ ተገልጋዮች ሲቆጡ እንደሚሰማ ይገልጻል። በአገልግሎት ላይ ያለው የመጸዳጃ ቤት መቀመጫ ለተጠቃሚዎች ጤና የሚሰጥ እና ተክለ ሰውነትን የሚያሻሽል እንደሆነ ጊል ቢያምንም ፣ አዲሱ የመጸዳጃ ቤት መቀመጫ ግን ቀጣሪዎችን ከኪሳራ እንደሚታደግም ተናግሯል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 21 ቀን 2012 ዓ.ም ኃይለማርያም ወንድሙ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=24949
[ { "passage": "በየትኛው አቀማመጥ ቢፀዳዱ ጤናማ ይሆናሉ?\\nከሕይወታችን ወደ ስድስት ወር ያህሉን የምናሳልፈው ስንጸዳዳ ነው\n\nበዓመት ውስጥ የአንድ ሰው ሰገራ ሲመዘን 145 ኪሎ ግራም ይሆናል። ይህ ማለት ደግሞ አንድ ሰው በዓመት ሁለቴ ከክብደቱ እጥፍ የሚመዝን ሰገራ ያስወግዳል ማለት ነው።\n\nበሕይወታችን ግዙፍ ቦታ ያለው የመፀዳዳት ጉዳይ ከጤናችን ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አለው። ለመፀዳዳት የምትቀመጡበት መንገድ በጤናችሁ ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የምታውቁ ስንቶቻችሁ ናችሁ?\n\n• መጻሕፍትን ማንበብና መጻፍ ለአዕምሮ ጤና \n\n• ሞባይል ለኢትዮጵያ እናቶችና ህፃናት ጤና \n\nለመሆኑ መፀዳጃ ላይ ስንት ሰዓት ያጠፋሉ?\n\nበ20ኛው ክፍለ ዘመን እኩሌታ ላይ በአፍሪካ ገጠራማ አካባቢዎች የሚሠሩ ሀኪሞች፤ አንዳችም ከ 'ጋስትሮኢንተስታይናል' (ምግብ የመፍጨትና ሰገራ የማስወገድ ሂደት) ጋር የተያያዘ የጤና እክል ያለበት ሰው አልገጠማቸውም ነበር።\n\nነገሩ ሀኪሞቹን አስገርሟቸው ነበር። ከአፍሪካ ውጪ በሌሎች ታዳጊ በሚባሉ አህጉሮችም ምግብ ፈጭቶ ሰገራ ከማስወገድ ጋር የተያያዘ እክል ያለበት ሰው እምብዛም አልነበረም።\n\nመላ ምታቸው የነበረው ነገሩ የአመጋገብ ሥርዐት ውጤት ይሆናል የሚል ነበር። እውነታው ግን ያ አልነበረም። ሀኪሞቹ ለጥያቄያቸው መልስ ያገኙት፤ ከሰዎች ሰውነት የሚወገደው ሰገራ የሚጠራቀምበት የጊዜ ርዝመትና ሰዎች ሲፀዳዱ የሚቀመጡበት መንገድ ነበር።\n\nቁጢጥ በማለት መጸዳዳት የሚቻልባቸው መጸዳጃዎች ቁጭ ብሎ ለመጸዳዳት ከተዘጋጁት በበለጠ ይገኛሉ\n\nምዕራባውያኑ መፀዳጃ ቤት በገቡ ቁጥር ቢያንሰ ከ114 እስከ 130 ሰከንድ ይቆያሉ። በተቃራኒው ታዳጊ በሚባሉ አገሮች አንድ ሰው መፀዳጃ ቤት የሚቆየው ለ51 ሰከንድ ብቻ ነው።\n\nምዕራባውያኑ ቁጭ ተብሎ መፀዳዳት የሚቻልበት መጸዳጃ ሲጠቀሙ፤ ታዳጊ የሚባሉ አገሮች ደግሞ ቁጢጥ ብሎ መፀዳዳት ያዘወትራሉ።\n\nተመራማሪዎች እንደሚሉት፤ ለአጭር ጊዜ መፀዳጃ ቤት መቀመጥ ጤናማ ነው።\n\nስንፀዳዳ መቀመጫችን አካባቢ 90 ዲግሪ ይታጠፋል። ይህም በአካባቢው የሚገኘው ጡንቻ አንጀታችንን እንዲጫነው ያደርጋል።\n\n• ለ10 ዓመታት እጆቹን ያልታጠበው የቴሌቪዥን አቅራቢ\n\n• ዘመናዊውን የመፀዳጃ መቀመጫ የፈጠረው ሰዓት ሠሪ\n\nቁጭ ብሎ ለመፀዳዳት የሚያስችለው ፈጠራ\n\nየመጀመሪያው መፀዳጃ ሥራ ላይ የዋለው ከጥንታዊ ሜሶፖታሚያ ሥልጣኔ ወዲህ እንደሆነ ይነገራል። \n\nከክርስቶስ ልደት 315 ዓመታት በፊት ሮም 144 የሕዝብ መፀዳጃ ነበራት። ሮም ውስጥ የተገነባውና 2,000 ዓመታት ያስቆጠረው መፀዳጃ፤ ጎን ለጎን የተሠሩ 50 የመፀዳጃ ጉድጓዶች የያዘ ነበር።\n\nየሮም የሕዝብ መፀዳጃ\n\nእንደ ጎርጎሮሳውያኑ 1592 ላይ ውሃ የሚያፈስ መፀዳጃ ተፈልስፎ ነበር። 1880 ላይ ደግሞ አንድ እንግሊዛዊ ዓለምን ያስገረመ መፀዳጃ ይዞ ብቅ አለ።\n\nመፀዳጃው ሰዎች ቁጭ ብለው የሚጠቀሙበት ሲሆን፤ ከመፀዳጃ ውስጥ ቆሻሻን ያስወግዳል።\n\nየሚፀዳዱበት መንገድ ጤናዎ ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድረው እንዴት ነው?\n\nብዙዎች ለመፀዳዳት ሲያምጡ ይስተዋላል። ለዚህ ችግር ምክንያት ከሆኑት መካከል የምግብ አለመፈጨት፣ የሰገራ መድረቅና የአንጀት ህመም ይጠቀሳሉ። ተመራማሪዎች እንደሚሉት፤ ልንፀዳዳ ስንል የምንቀመጥበት መንገድም የጤና እክል ያስከትላል።\n\nምዕራባውያን የሚያዘወትሩት የመፀዳጃ አይነት ለጤና እክሉ ምክንያት እንደሆነ ተመራማሪዎች ያስረዳሉ።\n\nበምንፀዳዳበት ወቅት ጉልበታችንን ከ90 ወደ 30 ዲግሪ ከፍ በማድረግ ችግሩን መቅረፍ ይቻላል\n\nበኮርኔል ዩኒቨርስቲ የሚሠሩት ፕሮፌሰር አሌክሳንደር ኪራ፤ ሰዎች ቁጢጥ ከማለት ይልቅ ቁጭ ብለው እንዲፀዳዱ የተሠራው መፀዳጃ የችግሩ ምንጭ እንደሆነ ይናገራሉ።\n\nተመራማሪዎች እንደሚሉት፤ በምንፀዳዳበት ወቅት ጉልበታችንን ከ90 ወደ...", "passage_id": "a73343dec1c64ff85ac0cdd536bdc130" }, { "passage": "አካባቢው ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ጭር ብሏል። ቀድሞ በስፍራው ይስተዋል የነበረው እንቅስቃሴ መጥፋቱ አንዳች ችግር እንዳለ አመላካች ነው። በሆስፒታሉ እንደቀድሞ መግባትም ሆነ መውጣት አይቻልም። ይልቁንም በር ላይ የተቀመጡት የጥበቃ ሠራተኞች በከፍተኛ ጥንቃቄ ገቢ ወጪውን በዓይነ ቁራኛ ይከታተላሉ። ወደ ውስጥ ሲዘልቁ በየግድግዳው ‹‹ርቀትዎን ይጠብቁ››፣ ‹‹መወጣጫ ደረጃዎችን በእጅዎ አይያዙ፤ ከያዙም በአፋጣኝ በደንብ ይታጠቡ›› የሚሉና መሠል መልዕክቶች ተለጥፈዋል። \nየሕክምና ባለሙያዎች በተቻለ መጠን አስፈላጊውን ጥንቃቄ እያደረጉ እንደሆነ በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ተገኝቼ የጽኑ ሕክምና ክፍል አጠቃላይ ሐኪም ዶክተር እስማኤል ሀሰንን አነጋገርኳቸው። መንግሥት ባቀረበላቸው የአፍንጫና አፍ መሸፈኛ ጭንብሎች፣ የንጽህና መጠበቂያ (ሳኒታይዘር) እንዲሁም ሌሎች ቁሳቁሶች በመታገዝ ለሕብረተሰቡ አገልግሎት እየሰጡ ነው። ነገር ግን በሕብረተሰቡ በኩል በጤና ባለሙያዎች እንዲሁም የሚመለከተው አካል እንዲወሰድ የሚነገረውን ጥንቃቄ ችላ ማለትና አለመተግበር እንዳስተዋሉ ገልፀዋል።\nበሆስፒታሉ ለማስታመም የሚገቡትም ርቀትን መጠበቅ እንዲሁም ጭንብሎችን የመጠቀም ሁኔታቸው የላላ እንደሆነ የተናገሩት ዶክተር እስማኤል፤ በሌላ በኩል ቫይረሱ ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ ተብሎ ከታወጀ ጀምሮ በጡረታ ከሥራ የተገለሉ የጤና ባለሙያዎች ሳይቀሩ ጥሪ ተደርጎላቸው ሕዝብን እያገለገሉ ቢሆንም ይህን ሥራቸውን በሚገባ እንዲያከናውኑ የሚረዳቸው ምቹ ሁኔታ አለመፈጠሩን አመላክተዋል። ለዚህም አንዱ ማሳያ በትራንስፖርት አገልግሎቱ ላይ የሚስተዋለው ክፍተት በመሆኑ መንግሥት ይህንን ችግር ተመልክቶ መፍትሔ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።\nበሆስፒታሉ የሚሠሩ ሁለት ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ ነርሶች፤ በተቋሙ ቫይረሱን ከመከላከል ጎን ለጎን ሌሎች ታካሚዎችን በአግባቡ አገልግሎት ለመስጠት የሚደረገው ጥረት አድንቀዋል። ይሁን እንጂ የእጅ ንጽህና መጠበቂያ (ሳኒታይዘር) በ15 ቀናት አንድ እንዲሁም የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብሎች በሣምንት ሦስት ብቻ እንደሚሰጣቸውና እጥረት እንዳለ ነው የጠቆሙት። \nበተጨማሪም ሆስፒታሉ ቫይረሱ እንዳለባቸው ለተጠረጠሩ ሕሙማን የተዘጋጀ ለይቶ ማከሚያ ስፍራ ቢኖረውም ምርመራ ከተደረገላቸው በኋላ ወዲያው እንዲቀላቀሉ ይደረጋል። በለይቶ ማቆያው በቫይረሱ የተጠቃ ሊኖር ስለሚችል ሥራው ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚሻና ነፃ የሆኑትም ከሌሎች ታካሚዎችና የሆስፒታሉ ማሕበረሰብ ጋር ከመቀላቀላቸው በፊት እንዲቆዩ ማድረጉ ጠቀሜታው የጋራ እንደሆነ ጠቁመዋል።\nበየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የሕክምና ጥራት አገልግሎት ዳይሬክተር እንዲሁም ከወቅታዊ ጉዳይ ጋር ተያይዞ በሆስፒታሉ ለኮቪድ 19 ምላሽ ሰጪ የማስተባበሪያ ኮሚቴ የግብዓት አቅርቦት (የሪሶርስ ሞቢላይዜሽን) ቡድን ኃላፊ ዶክተር በረከት ዘላለም እንደገለጹት፤ ቫይረሱ ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ ተብሎ ከታወጀ በኋላ የሠው ኃይል በማጠናከርና ከወትሮው በተሻለ ቫይረሱን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል ዕቅድ ነድፎ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ይገኛል። በጡረታ የተገለሉ የሕክምና ባለሙያዎችም ወደ ሥራ እንዲገቡ ተደርጓል።\nሆስፒታሉ በአሁኑ ወቅት የተሰጠው ኃላፊነት በኮቪድ 19 የተጠረጠሩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን እንዲሁም ከማህበረሰቡ ለሚመጡ ሌሎች ታካሚዎች አገልግሎት መስጠት ነው። በዚህም ሁሉም የጤና ባለሙያዎች ሥራቸውን እያከናወኑ ይገኛሉ። ነገር ግን ቫይረሱን ለመከላከል ወሳኝ የሆኑ የመከላከያ መንገዶች በብዙሃን መገናኛዎች እንዲሁም በተለያዩ ዘዴዎች እየተሰጠ ቢሆንም በሆስፒታሉ ከተቋሙ ቅጥረ ግቢ ውጪ በሕብረተሰቡ ፈቀቅታ አለመጠበቅ እንደሚስተዋል ዶክተር በረከት ተናግረዋል። \nየተለያዩ ታካሚዎች ወደ ሆስፒታሉ እንደሚያቀኑ የገለጹት ኃላፊው፤ ለይቶ ማከሚያ ገብተው ከቫይረሱ ነፃ መሆናቸው ሲረጋገጥ ወዲያው ከሌሎች የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር እንዲቀላቀሉ እንደሚደረግ አምነዋል። ነገር ግን እነዚህ ታካሚዎች የኮቪድ 19 የቅድመ ምርመራ ተብሎ የተቀመጠውን አስፈላጊ የሕክምና ሒደት አጠናቀው ለሌሎች ስጋት አለመሆናቸው ሲረጋገጥ ብቻ ነው ብለዋል። የውጭ የጉዞ ታሪክም ሆነ ከባሕር ማዶ ከመጣ ሠው ጋር ንክኪ እንዳልነበራቸው ከታወቀ ምርመራቸውን እንደጨረሱ ይቀላቀላሉ። በሌላ በኩል የጉዞ ታሪክ እንዳላቸው የተረጋገጠ ታካሚዎች ሕክምናቸውን ቢጨርሱም ወደማቆያ እንዲገቡ እንጂ እንዲቀላቀሉ እንደማይደረግ አረጋግጠዋል።\nበአሁኑ ወቅት በሆስፒታሉ የሠው ኃይል እጥረት ባያጋጥምም የበሽታ መከላከያ ግብዓቶች ተሟልተው እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸው ቫይረሱ እስከመቼ እንደሚቆይ ስለማይታወቅ መንግሥት ከወዲሁ በሰው ሃይል አጥረቱ ላይ የጀመረውን ስራ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው አሳስበዋል።\nአዲስ ዘመን ግንቦት 12/2012ፍዮሪ ተወልደ", "passage_id": "e72385f9e33cfed58e560a7d96b745f9" }, { "passage": "የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የማህበረሰቡን እንቅስቃሴዎች መግታትና እገዳዎች መጣል እንደጊዜያዊ መፍትሔ ተወስዷል። ቫይረሱ ከሰው ወደ ሰው የሚዛመትባቸውን መንገዶችም ለመቀነስ በማሰብ ሰዎች የሚበዙባቸው አብዛኞቹ ቦታዎች እንዲዘጉ ሆነዋል። በዚህ ምክንያት አብዛኞቹ ሰዎች ቤት እንዲውሉ የግድ ሆኗል። የቫይረሱ ሰጋት ከዕለት ወደ ዕለት እየጨመረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የሰዎችን ጭንቀትና ለፍርሐት በማስወገድ የስነ ልቦና ጫና ውስጥ እንዳይገቡ መደረግ አለበት። ገርጂ አካባቢ የግል ሥራዋን እንደምትሠራ የሚትገልጸው ወ/ሮ አዜብ ደመቀ ፤ የዘወትር ተግባሯ ጠዋት ተነስታ ወደ ሥራ በመሄድ ሥራዋን ስትከውን ውላ ማታ ወደ ቤቷ ትመለሳለች። በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ሥራ አለመኖሩን በስሯ ቀጥራ የምታሠራትን ልጅ ጨምሮ እሷ ቤት መዋሏ ድርብ ጫና እንዳሳደርባት ትገልጻለች። ‹‹ሥራ መሥራት ለምጄ ቤት መቀመጥ በጣም ነው የጨነቀኝ፤ ሌሊት እንቅልፍ የለኝም ነገ የሚፈጠር ነገር ያሰጋኛል›› የምትለው አዜብ የቤት ውስጥ ሥራ በመሥራትና ልጆቿን በመንከባከብ ብትሳልፈም፤ውሎ አዳሯ በቤት ውስጥ መሆኑ ከአሁኑ እንደሰለቻትና ፍርሐትና ጭንቀት ውስጥ እንደከተታት ትናገራለች።በኮሮ ቫይረስ ምክንያት ዕረፍት ከተሰጣቸው የመንግሥት ሠራተኞች አንዱ አቶ ጌታቸው መንግሥቱ እንደሚገልጹ፤ ቤት ከመዋሉ በዘለለ ቫይረሱ ምን ያመጣብን ይሆን የሚል ፍርሐትና ጭንቀት እንደሳደረባቸው ይገልጻሉ።‹‹እኔ መጽሐፍት በማንበብ ጊዜዬን እያሳለፍኩ ነው›› የሚሉት አቶ ጌታቸው ፤ባለቤታቸውና ልጃቸው ሥራ ውለው መመለሳቸው ሌላ ተጨማሪ ስጋት እንደሆነባቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ሰዎች ከጨንቀትና ፍርሐት ለመላቀቅ ምን ማድረግ አለባቸው? ስንል ጥያቄ ያቀረብንላቸው የስነልቦናና የማህበራዊ ሳይንስ ባለሙያ ወ/ሮ ዘርትሁን ካሳሁን እንደሚሉት፤ የኮሮና ወረርሽኝ ድንገት የተከሰተ ነው።ሰዎች በሽታው በዓለም ላይ እያስከተለ ስላለው ወድመት ከተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች፤ ከሰዎች የሚሰሟቸውና የሚያዩአቸው አብዛኛውን አሉታዊና የሚያስጨንቁ ነገሮች በመሆናቸው ድንጋጤ ውስጥ ይገባሉ። ጫናው እያደገ ሄዶ ፍርሐት በመፍጠር ጨንቀትና ስጋት አስከትሎ መልስ የማያገኙላቸው ነገሮች ስለሚበዙ ነገን እንዲፈሩ እንደሚያደርጋቸው ያስረዳሉ። \nአብዛኞቹ የምናገኛቸው መረጃዎች የማስፈራ ራት ዓይነት ስሜቶች ያላቸው በበሽታው የተያዙ ሰዎችን ህመሙ እንዴት እንደሚገድልና የሞተው ሰው ብዛት ላይ ያተኮሩ ናቸው የሚሉት ወ/ሮ ዘርትሁን፤ እራሳችንን እንዴት መጠበቅና መከላከል እንደምንችል የሚገልጹ አይደሉም ይላሉ። በዚህ ምክንያት ሰዎች ለጭንቀትና ለፍርሐት ተጋላጭ እንደሚሆኑ ይናገራሉ። እንደ ባለሙያዋ ማብራሪያ ወላጆች ፤ ልጆቻቸው ቤት ውስጥ በማጥናት ፤ መጻሕፍት በማንበብ ፤ ሥዕል በመሳል፤ ስለኮሮናም ሆነ ስለ ሌላ ጉዳይ የሰሙትን እንዲጽፉ ወይም ያዩትን በሥዕል እንዲገልጽ ማድረግ፤ ከቤተሰቦቻቸው ጋር የሚጫወቱበት ዕድል በመስጠት ፍርሐትን ሊቀነስ የሚችል ተግባራዊ የሆነ ልምምድ እንዲያደርጉ ማድረግ እንዳለባቸው ይመክራሉ። ሰዎች ቤት በሚውሉበት ወቅት ጭንቀትና ፍርሐትን ለመቀነስ አዳዲስ የህይወት ልምዶችን በመሞከር ቤት ውስጥ እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው የሚናገሩት ባለሙያዋ፤ ጊዜ ባገኝ ኖሮ ይህን አድርግ ነበር ብለው የሚያስቧቸው ነገሮች ፤ እጅ ሥራ መሥራት ፤ ሥዕል መሳል፤ ቤት ማስዋብ ፤ግቢ ማፅዳት ፤ ስፖርት መሥራት ሊሆን ይችላል። የሚችሉትን የእራሳቸውን እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚገባ ያስረዳሉ።በሌላ በኩል በፍርሐትና በጭንቀት ውስጥ ያሉ ሰዎች እንዳሉ ሁሉ፤ ስለ ቫይረሱ ሰምቶ ምንም አይመጣም ብለው በግዴለሽነት የሚንቀሳቀሱ ሰዎች መኖራቸውን የሚገልጹት ባለሙያዋ፤ ለቫይረሱ ትኩረት ባለመስጠት አሉታዊ ከሆነ መረጃ ምንጭ የሚናፈሱ የተለያዩ ጉዳዮችን በመስማት ‹ እኔን አይነካኝም› በማለት የሚያምኑም እንዳሉ ይናገራሉ።በዓለም የሰውን ልጅ በሙሉ በምንም ሳይለይ ሁሉን እኩል እያጠቃ የሚገኝ በሽታ መሆኑን ማመን ይገባል የሚሉት ወ/ሮ ዘርትሁን፤ በህክምና ባለሙያዎች የሚሰጡ ምክሮችና መረጃዎችን ትክክለኛ ከሆነ ምንጭ በመቀበል ተግባራዊ ማድረግ ይገባል ብለዋል።‹‹ ዛሬ ከማድረግ የታቀብናቸው ተግባራት በህይወት ካለን ነገ ልናደርጋቸው እንችላለንና፤ የነገ ዕድላችንን ዛሬ ማጣት የለብንም። ስለዚህ የምንችለውን ያህል እስከጥግ ድረስ እንጠንቀቅ፤ግዴለሽ ባለመሆን እራሳችንንና ቤተሰባቸውንም መጠበቅ ብንችል ነገ የምንፈልገውን ለማድረግ ሰፊ ዕድል እንዳለ በማስተዋል ህይወትን ማትረፍ ያስፈልጋል›› በማለት ጥሪያቸውን አቅርበዋል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 5/ 2012 ወርቅነሽ ደምሰው", "passage_id": "43e637ec2fd9e29328c33eb188b946e7" }, { "passage": "የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በሰው ዘር በሙሉ እያስከተለ ካለው የጤና እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ባለፈ የስነ ልቦና ጫና እያስከተለ መሆኑ ዕሙን ነው። በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ የዜጎች ማህበራዊ ቁርኝት እጅጉን በጠነከረበት አገር የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ባህሪ እጅግ ፈታኝና አስቸጋሪ ይሆናል። “ሠርግና ሞት አንድ ነው” ተብሎ በሚዜምበትና ለቅሶ የሠርግ ያህል በሚደምቅበት አገር ለቅሶ ከአምስት ባልበለጡ ሰዎች ይከናወን ሲባል እና ሰው የሞተበትን ቤተሰብ እንደወትሮው ሁሉ ከዘመድ አዝማዱ ጋር በመሆን አልቅሶ የመቅበር ዕድል ማጣት አሳዛኝ ከመሆኑም በላይ በሰዎች ላይ የሚፈጥረው የስነልቦናዊ ጫና ቀላል አይደለም። በተለይም አሁን ባለንበት ወርሐ ሚያዝያ በርካታ ጥንዶች የሚሞሸሩበት እንደመሆኑ ዝግጅቱ የሚጀመረው ቀደም ብሎ ነው። ይሁን እንጂ ወቅቱ እንዲህ ያለውን ዝግጅት ለመፈፀም የሚፈቅድ ካለመሆኑ ጋር ተያይዞ በአሁን ወቅት በርካታ የሠርግ ስነስርዓቶች ሊሰረዙ የግድ ሆኗል። ታድያ እንዲህ ያሉና ቀደም ብለው ዝግጅት ሲደረግባቸው የቆዩ የሠርግ ስነ-ስርዓቶች ሲሰረዙ በጥንዶቹም ሆነ በጥንዶቹ ቤተሰቦች ላይ የሚፈጠረውን ስነልቦናዊ ጫና መቀነስ እንዲቻል ምን ይደረግ ስንል የስነልቦና ባለሙያዎችን አነጋገረናል። በተጋቢዎቹም ሆነ በታዳሚዎቹ በተለይም በሚዜና በቤተሰቦች ላይ የሚፈጠር ስነልቦናዊ ጫና መኖሩን የገለጹት በጤና ሚኒስቴር የጤና ክብካቤ ዳይሬክቶሬት አማካሪ ዶክተር የኔነህ ጌታቸው፤ በሌላው ዓለም እንደታየው በርካቶች ለበሽታው ተጋላጭ የሆኑት ሆስፒታሎች ውስጥ እና በቤተ ዕምነቶች አካባቢ እንደመሆኑ ሠርግን የመሰሉ በርካታ ታዳሚዎች በሚገኙበት ቦታም ተጋላጭነት እንደሚኖር ይታመናል። ስለዚህ ተጋቢዎችን ጨምሮ ክርስትና ለቅሶና የተለያዩ ማህበራዊ ክንዋኔዎችን ለጊዜው ተወት ማድረግ ተገቢ መሆኑን ይናገራሉ። በተለይም ወቅቱ የሠርግ እንደመሆኑ ቀድመው የተዘጋጁ ተጋቢዎች ነገሩን በጥልቀት መርምረው ፕሮግራማቸውን ሊሰርዙ የግድ ይላል። በዚህ ጊዜ የሚፈጠርባቸውን ስነልቦናዊ ጫና መቀነስ እንዲችሉም በቅርባቸው ያሉ ሰዎችን ማማከርና መረጃዎችን በሚገባ በመገንዘብ ማብላላት ይጠበቅባቸዋል ያሉት ዶክተር የኔነህ፤ ሰዎች መረጃዎችን በሚገባ ሲረዱ ቫይረሱ ማህበረሰብ ውስጥ ገባ ማለት ምን ማለት እንደሆነና የሆነ ቦታ እንዳለ ይገነዘባሉ። በዚህ ጊዜ ደግሞ ቢያንስ አንድ ሺህ ሰው ጠርተው ሠርጋቸውን ቢያደርጉ ኋላ ትርፉ ፀፀት መሆኑን ጠቁመው፤ መረጃ ወሳኝ እንደመሆኑ መረጃዎችን በሚገባ ተረድተው ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት ችግሩን ሳያቃልሉ መመልከት ከቻሉና ሰዎችን ካማከሩ ህይወት ማትረፍ ይችላሉ። በዚህም ያለሠርግ ፕሮግራም በመጋባት የሚፈጠርባቸውን ስነልቦናዊ ጫና መቀነስ እንደሚቻል እና አሳቢ መሆን ለህይወት ሰፊ ትርጉም መስጠት ተገቢ ነው በማለት ሃሳባቸውን አካፍለዋል። ሌላኛዋ የስነ-ልቦና ባለሙያ ወይዘሮ ራሔል ገብረ መስቀል በበኩላቸው፤ ኮሮና ቫይረስ ወይም ኮቪድ 19 በሁሉም ዓለም ላይ የመጣ እንደመሆኑ ከሌሎች አገራት ልምድ በመውሰድ ችግሩን ለማለፍ ጥረት ማድረግ ይገባል። እርግጥ ነው እቤት ውስጥ ያለሥራ ስንቀመጥ ኢኮኖሚያዊም ሆነ ስነልቦናዊ ጫና ይፈጠራል። ቢሆንም በማንበብ፣ ልጆችን በማስጠናት፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን በማድረግና የመሳሰሉትን ተግባራት በማከናወን ከስነ-ልቦና ጫና መውጣት እንዳለብን ተናግረዋል። “ሁሉም ነገር ከማመን ነው የሚነሳው” የሚሉት ባለሙያዋ፤ በኢትዮጵያ የተለመደ ባህል አለ በተለይም በኀዘናችን ጊዜ የሚያፅናናን በደስታችንም ደስታችንን የምናጋራው ሰው እንፈልጋለን። እርግጥ ነው ሰው የሚያስፈልገን በርካታ ምክንያቶች አሉን። ቢሆንም ዋናው ነገር አዕምሯችንን ማሳመንና ይሄ ነገር ለእኔ ብቻ የመጣ አይደለም ብለን ማመን አለብን። ከዚሁ ጎን ለጎንም የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን በማድረግ፣ በመፀለይና እራስን በተለያዩ ተግባራት መያዝ ያስፈልጋል። ችግሩ ያልፋል እስከዚያው ግን በጤና ለመቆየትና ችግሩን በትንሽ ጉዳት ለማለፍ ጥንቃቄ ማድረግና የምንወዳቸውን ሰዎች ነገ ማግኘት እንድንችል እራሳችንን አግልለን መጠበቅና መጠንቀቅ አለበን ብለዋል። የኮሮና ቫይረስ የሆነ ቦታ ላይ እንዳለ እያሰብን በመጠንቀቅ መንቀሳቀስ እንደሚገባን የገለጹት ባለሙያዋ፤ አሁን አሁን መዘናጋቶች እንዳሉ ይስተዋላልና ልንዘናጋ አይገባም፤ ችግሩ ያልፋል ሁሉም ጉዳዮቻችን ችግሩ ሲያልፍ ልናከናውነው እንደምንችል በማመን ተጠንቅቀን ልንጓዝ እንደሚገባም አሳስበዋል። አዲስ ዘመን ሚያዝያ 29/2012ፍሬህይወት አወቀ", "passage_id": "5a2d6376d426955b17f09814233958c5" }, { "passage": "በዚህ በአፈ-ንጉሥ ነሲቡ መስቀሎ ቤት ውስጥ በርካቶች ይኖራሉ በማንኛውም ሰዓት ቤቱ ሊደረመስ እንደሚችል ባለሙያዎች ያስጠነቅቃሉ\n\nከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተገኙ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከሆነ በከተማዋ ውስጥ ከ230 ያላነሱ በቅርስነት የተመዘገቡ ቤቶች ያገኛሉ። እነኚህ ጥንታዊ ቤቶች ባላቸው ታሪክ፣ የሥነ-ህንፃ ውበት፣ ማህበራዊ ጠቀሜታዎችና ካላችው ረጅም እድሜ አኳያ በቅርስነት የተመዘገቡ ናቸው። \n\nየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የባህልና ቱሪዝም ቢሮም በከተማዋ ውስጥ የሚገኙትን ቅርሶችን የመጠበቅ፣ የመንከባከብና የማሳወቅ ስልጣንና ሃላፊነት ተሰጥቶታል። \n\nነገር ግን ተዘዋውረን እንደተመለከትነው በከተማዋ ውስጥ የሚገኙ የበርካታ ጥንታዊና ታሪካዊ ቤቶች ህልውና አደጋ ላይ ይገኛል። ከነዚህም መካከል ፈረንሳይ ለጋሲዮን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኘው የልዑል ራስ ሥዩም መንጋሻ ቤትና ሳንፎርድ ት/ቤት ጀርባ የሚገኘው የአፈ-ንጉሥ ነሲቡ መስቀሎ ቤት ያሉበት ይዞታ እጅግ አሳሳቢ ነው።\n\n በአሁኑ ወቅት በሁለቱም ቤቶች ውስጥ በርካታ ሰዎች እየኖሩ ይገኛሉ። ከዚህም በላይ አስቸኳይ ጥገና ካልተደረገላቸው የቤቶቹም ሆነ የነዋሪዎቹ ህልውና አደጋ ላይ ይገኛል። \n\nየአምስት ልጆች እናት የሆነችው ወ/ሮ መሰረት ቶላ በአፈ-ንጉሥ ነሲቡ መስቀሎ ቤት ውስጥ ከሰላሳ ዓመትታ በላይ እንደኖረች ትናገራለች። \n\nደርግ ሥልጣን ላይ በነበረበት ወቅት ለወላጆቿ የቤቱ የኋለኛ ክፍል እንደተሰጣቸውና ከዛን ጊዜ ጀምሮ በቤቱ ውስጥ ስትኖር እንደቆየች የምትናገረው ወ/ሮ መሰረት፤ አሁን አሁን ''ዝናብ ሲዘንብ እንቅልፍ የለኝም! ቤቱ በእኔና በልጆቼ ላይ አንድ ቀን ይደረመሳል በሚል ሥጋት ነው የምኖረው'' ትላለች።\n\nበመዲናችን የሚገኙ ጥንታዊ ቤቶችና የነዋሪዎቻቸው ህልውና አደጋ ላይ ነው\n\nበልዑል ራስ ሥዩም መንጋሻ ቤት የሚኖሩ ነዋሪዎች እንደሚሉት ከሆነ፤ ለወረዳቸውና ለአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ተቀያሪ ቤት እንዲሰጣቸው ማመልከታቸውን፤ ይሁን እንጂ እሰካሁን ምንም ነገር እንዳልተፈጸመ ነግረውናል። ነዋሪዎቹ ቤቱ ብዙ ታሪክ እንዳለው ይረዳሉ፤ ቅርሱም ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ ይፈልጋሉ። ይሁን እንጂ እዚህ የሚኖሩት ሌላ አማራጭ ስላጡ እንደሆነና አማራጭ ካገኙ ታሪካዊውን ቤት ለመልቀቅ ፍቃደኛ ናቸው። \n\nየሥነ-ህንፃ ባለሙያና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት ፋሲል ጊዮርጊስ እንደሚሉት ''ጥንታዊ ቤቶቹ የተገነቡት ከእንጨትና ከጭቃ ነው። ከእድሜያቸውና ከአስራራቸው አንጻር ቤቶቹ ብዙ መሸከም አይችሉም። \n\nይሁን እንጂ አሁን በቤቶቹ ውስጥ በርካታ አባዎራዎች እየኖሩ ይገኛሉ። ይህ ማለት ደግሞ በማንኛውም ሰዓት ቤቶቹ ሊደረመሱና ጉዳት ሊያደረሱ ይችላሉ'' በማለት ሥጋታቸውን ይገልፃሉ። ስለዚህ ነዋሪዎቹን ወደ ሌላ ቦታ በማዘዋወር የቤቶቹን ታሪካዊነት መጠበቅ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። \n\nፋሲል ጊዮርጊስ ስለ ጥንታዊ ቤቶች ይናገራሉ\n\nበሌላ በኩል በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የባህልና ቱሪዝም ቢሮ የቅርስ ቁጥጥርና ኢንቨንተሪ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ደርጄ ሥዩም እንደሚሉት ቢሮው በከተማዋ ለሚገኙ ቅርሶች ጥበቃና ጥገና እንደሚያደርግ፤ ይሁን እንጂ ከብዛታቸው የተነሳ ለሁሉም በአንድ ጊዜ ጥበቃና እንክብካቤ ማድረግ አለመቻሉን ይናገራሉ። \n\nአቶ ደረጄ እንደሚሉት ቢሮው ከፍተኛ ጉዳት ላይ የሚገኙ ቤቶችን ለመጠገን የዲዛይን ሥራው እየተጠናቀቀ መሆኑን ተናግረዋል። ቤቶቹን ለማደስ ሥራ ከመጀመሩ በፊት ግን የማጣራትና ለነዋሪዎቹ ተለዋጭ ቤት በማስፈለጉ ረጅም ጊዜ መጠየቁን ገልፀዋል። \n\n ", "passage_id": "d6653a0ea214a6611e0f9cd5609c1ec9" } ]
20f2600b6fd5f853fd36059ef33656a0
92201dc95013bc2bc58c6aee96926667
ፕሬዚዳንቱ ከስልጣን እንዲባረሩ የአሜሪካ ሕገመንግሥት 25ኛው ማሻሻያ እየተጠቀሰ ነው
በኃይሉ አበራከትናንት ወዲያ የዶናልድ ትራምፕ ነውጠኛ ደጋፊዎች የመንግሥት መቀመጫና የሁለቱ ምክር ቤቶች አዳራሾች የሚገኙበትን ግዙፉን የካፒቶል ሒል ህንጻን ጥሰው መግባታቸውን ተከትሎ ከፍተኛ የሴኔት ምክር ቤት አባላት ፕሬዚዳንቱ ከስልጣን እንዲባረሩ እየጠየቁ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧልበዘገባው መሰረት የአሜሪካ ሕገመንግሥት 25ኛው አሜንድመንት ወይም ማሻሻያ እየተጠቀሰ ሲሆን፤ ይህ ማሻሻያ አንድ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት አካላዊ ወይም አእምሯዊ ጤና ከራቀው ምክትል ፕሬዚዳንቱ ቦታውን በተጠባባቂነት ተረክቦ አገሪቱን እንዲመራ ያዛል።ሆኖም ይህ እንዲተገበር የምክር ቤቱ አፈጉባኤ ናንሲ ፔሎሲን ጨምሮ በትንሹ ስምንት የካቢኔ አባላት በጉዳዩ ላይ መስማማት አለባቸው። ነገር ግን ይህ የመሆን እድሉ ለጊዜው ጠባብ ነው ተብሏል።የትራምፕ ነውጠኛ ደጋፊዎች ካፒቶል ሒልን ጥሰው ሲገቡ ታህታይና የላዕላይ ምክር ቤት አባላት የባይደንን መመረጥ ከግዛት ተወካዮች የማረጋገጥ ሥነ ሥርዓት ላይ ተገኝተው ይህንኑ በማካሄድ ላይ ነበሩ። አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲና ምክትል ፕሬዚዳንት ማይክ ፔንስም በሸንጎ ላይ ተገኝተው ነበር።ይህንን ለአሜሪካ እንግዳ የሆነ ድርጊት ተከትሎ የሕግ መምሪያ ምክር ቤት አፈ ጉባኤዋ ናንሲ ፔሎሲ 25ኛውን የሕገ መንግሥት ማሻሻያ በመጥቀስ ትራምፕ አሜሪካንን ለመምራት ብቁ ስላልሆኑ ከዋይት ሐውስ እንዲባረሩ ጥያቄ አቅርበዋል።ይህን ጥያቄ በርካታ ዲሞክራቶችና ጥቂት ሪፐብሊካኖች ጭምር ድጋፍ ሰጥተውታል። የሴኔት ዲሞክራት ተጠሪ ቸክ ሹመር ትራምፕ አመጽ በማቀጣጠላቸው ከሥራ ሊባረሩ ይገባል፤ “ምክትል ፕሬዚዳንቱ እና ካቢኔው ይህንን ለማድረግ የማይፈልጉ ከሆነ፣ ኮንግረሱ ዳግመኛ ፕሬዚዳንቱን ከሥልጣን እንዲነሱ ለማድረግ መሰብሰብ አለበት” ብለዋል።ዶናልድ ትራምፕ ከዋይት ሐውስ እንዲወገዱ እንቅስቃሴ የተጀመረ ሲሆን ለድርጊታቸው ክስ እንዲመሰረትባቸውም ናንሲ ፒሎሲ ጥሪ አድርገዋል። ክሱ ተፈጻሚ እንዲሆን ግን ዲሞክራቶች የሪፐብሊካኖችን ድጋፍ ማግኘት አለባቸው። ምክንያቱም ክሱ እንዲፈጸም የምክር ቤቱ ሁለት ሦስተኛው ድምጽ ስለሚያስፈልግ ነው። ይህ የመሳካት እድሉም አነስተኛ ነው።25ኛው አሜንድመንት ፕሬዚዳንቱ ኃላፊነቶቹን መወጣት በማይችልበት ጊዜ ምክትል ፕሬዚዳንቱ ስልጣኑን በጊዜያዊ ፕሬዚዳንትነት ተረክቦ እንዲያስተዳድር ይፈቅዳል። በአሁኑ ሰዓት መነጋገሪያ እየሆነ ያለው የዚህ አሜንድመት አንቀጽ አራት ነው። ይህ አንቀጽ ምክትል ፕሬዚዳንቱ እንዲሁም የካቢኔው አብላጫ አባላት ፕሬዚዳንቱ ኃላፊነታቸውን መወጣት አልቻሉም ብለው እንዲወስኑ እድል ይሰጣቸዋል። ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከሥልጣናቸው እንዲወርዱ ቢደረግ ምክትል ፕሬዚዳንት ማይክ ፔንስ አገሪቱን እንዲመሩ ይደረጋል። ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፊርማቸው ያረፈበትን ደብዳቤ መላክ የሚጠበቅባቸው ሲሆን፣ ሴኔቱም ፕሬዚዳንቱ ሥልጣንና ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ብቁ አይደሉም ሲል ያፀድቃል።ፕሬዚዳንቱ በኮቪድ-19 ተይዘው በነበረበት በጥቅምት ወር ላይ አገሪቱን ለመምራት ሕመማቸው አያስችላቸውም በሚል ተነስቶ ነበር። በዚሁ ወቅት የተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት ናንሲ ፔሎሲ፣ በ25ኛው አሜንድመንት ላይ መሰረት ያደረገ እና የፕሬዚዳንቱን ጤና ለሥራ ብቁ መሆን አለመሆኑን የሚፈትሽ ሕግ አስተዋውቀው ነበር።25ኛው አሜንድመንት በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ1967፣ ጆን ኦፍ ኬኔዲ ከተገደሉ አራት ዓመት በኋላ፣ ፕሬዚዳንቱ በተለያየ ምክንያት ሥልጣንና ኃላፊነታቸውን ባልተወጡ ወቅት ማን ይተካቸዋል የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ በሚል ጸድቋል።በዚህም የተነሳ በርካታ ፕሬዚዳንቶች ይህንን የሕግ ማሻሻያ [አሜንድመንት]፣ በይበልጥ ደግሞ በጊዜያዊነት ሥልጣንን ለምክትላቸው ማስተላለፍ የሚፈቅደውን ክፍል፣ አንቀጽ ሦስትን ተጠቅመውበታል።በ2002 እና በ2007 ፕሬዚዳንት ጆርጅ ደብሊው ቡሽ የአንጀት ህክምና በሚያደርጉበት ወቅት ምክትላቸው እንዲተኳቸው አድርገዋል። ፕሬዚዳንት ሮናልድ ሬገን በ1985 ለካንሰር ህክምና ሆስፒታል በገቡበት ወቅት ተመሳሳዩን አድርገዋል። ነገር ግን እስከ ዛሬ ድረስ 25ኛው አሜንድመንትን በመጠቀም የትኛውም ፕሬዚዳንት ከሥልጣን እንዲወርድ ተደርጎ አያውቅም።አዲስ ዘመን ጥር 01/2013
ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=39204
[ { "passage": "የሪፓብሊካኑ የበላይነት ያለበት የአሜሪካ ሴኔት በኮንግረሱ ጸድቆ የቀረበለትን ሁለቱንም የፕሬዝዳንቱን ክሶች ውድቅ አድርጓል፡፡\nፕሬዝዳንቱ ስልጣንን ያለአግባብ ተጠቅመው ከዩክሬን ጋር ፈጽመዋል የተባለው ክስ 52 ለ 48 በሆነ ድምጽ ሲወድቅ፣ በኮንግረሱ ስራ ጣልቃ ገብተዋል የሚለው ሁለተኛ ክስ ደግሞ 53 ለ 47 በሆነ ድምጽ ነው ውድቅ የሆነው፡፡\nበመሆኑም የፕሬዝዳንቱ ስልጣን በቀጣዩ ህዳር በሚካሄደውና 150 ሚሊዮን ድምጽ ሰጪዎች እንደሚሳተፉ በሚጠበቀው የሀገሪቱ ምርጫ የሚወሰን ይሆናል፡፡\nፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከስልጣን እንዲወርዱ ክስ ከተመሰረተባቸው የአሜሪካ ፕሬዝዳንቶች ለድጋሚ ምርጫ መወዳደር የሚፈልጉ የመጀመሪያው የሀገሪቱ መሪ ናቸው፡፡\nከፕሬዝዳንት ትራምፕ በፊት በአሜሪካ ታሪክ መሰል ከስልጣን የማውረድ ክስ (ኢምፒችመንት) ያጋጠማቸው ሁለት ፕሬዝዳንቶች ብቻ ናቸው፤ ቢል ክሊንተን በ1999 እና አንድሪው ጆንሰን በ1868፡፡ ፕሬዝዳንት ሪቻርድ ኒክሰን ደግሞ በ1974 ከመከሰሳቸው በፊት በፈቃዳቸው ከስልጣን ወርደዋል፡፡\nይሄን መሰል ክስ የመፈጸሙ እድል በጣም ጠባብ ሲሆን ክሱም ከወንጀል ይልቅ በዋናነት ፖለቲካዊ ግብ ያነገበ እንደሆነ ይታመናል፡፡\nፕሬዝዳንቱ አሁን የምርጫ ቅስቀሳቸውን ከዚሁ የክስ ሂደት ጋር በማያያዝ ማካሄድ ጀምረዋል፡፡ የክሱ ሂደት የዲሞክራቶች የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ነገር ግን መቼም አያሸንፉኝም ሲሉ ፕሬዝዳንቱ ዝተዋል፡፡\nምንጭ፡- ቢቢሲ\n", "passage_id": "41a33f6e0e7f46e3ed9fd40642a16898" }, { "passage": "ትራምፕን ከስልጣን ለማውረድና በወንጀል ለመክሰስ ታስቧል ባሳለፍነው ሳምንት በታሪኳ አይታው የማታውቀውን ምርጫ አመጣሽ አመጽና ብጥብጥ ያስተናገደቺው አሜሪካ፣ በቀጣዮቹ ቀናትና በተመራጩ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በዓለ ሲመት ሰሞንም ታጥቀው በሚወጡ የትራምፕ ደጋፊዎችና ጽንፈኛ ቡድኖች ከዳር እስከ ዳር በአመጽ ልትናጥ እና ከፍተኛ ጥፋት ሊከሰት እንደሚችል ኤፍቢአይ አስጠንቅቋል፡፡የጆ ባይደን በዓለ ሲመት እስከሚፈጸምበት ጥር 12 ቀን ድረስ በ50 የአገሪቱ ግዛቶች ውስጥ በሚገኙ የመንግስት መቀመጫዎች እንዲሁም በዋሺንግተኑ የፌዴራል መንግስት መቀመጫ ካፒቶል ሂል በትጥቅ የታገዙ አመጾች በትራምፕ ደጋፊዎችና በጽንፈኛ ቡድኖች ሊቀሰቀሱ እንደሚችሉ የፌዴራሉ ምርመራ ቢሮ ኤፍቢአይ ያስጠነቀቀ ሲሆን፣ በዓለ ሲመቱ በትራምፕ ደጋፊዎች አመጽና ብጥብጥ እንዳይስተጓጎል ለመከላከል ካፒቶል ሂል ዙሪያውን እየታጠረ እንደሚገኝም ቢቢሲ ዘግቧል፡፡የአሜሪካ ምክር ቤት ባለፈው ሳምንት የተሰናባቹ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ደጋፊዎች ከፈጸሙት የአመጽ ድርጊት ጋር በተያያዘ ፕሬዚዳንቱን በ25ኛው የአገሪቱ ሕገ መንግሥት ማሻሻያ መሰረት ከስልጣን ለማውረድና ምክትሉ ስልጣኑን እንዲረከብ ለማድረግ ያሳለፈው ውሳኔ በምክትል ፕሬዝዳንት ማይክ ፔንስ ተቀባይነት ማጣቱን ተከትሎ፣ የአገሪቱ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤቱ ትራምፕን በኢምፒችመንት ከስልጣን ለማውረድና አመጽ በመቀስቀስ ወንጀል ለመክሰስ መዘጋጀቱ ተነግሯል፡፡ትራምፕ ባላመኑበትና ባልተቀበሉት የምርጫ ውጤት ተሸንፈው ከነጩ ቤተ መንግስት ሳይወዱ በግድ ሊወጡ የቀራቸው የቀናት እድሜ ቢሆንም፣ ምክር ቤቱ ግን በአገሪቱ መንግስት መቀመጫ ህንጻ ላይ ደጋፊዎቻቸው የፈጸሙትን ህገወጥ ድርጊት እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም በኢምፒችመንት ከስልጣን ለማስወገድ መጣደፍ የጀመረው ሰውዬው በቀጣይ ምርጫዎች እንዳይሳተፉ ለማድረግ ነው መባሉን ዋሽንግተን ፖስት ዘግቧል፡፡ዲሞክራቶች ፕሬዝዳንት ትራምፕን ጥቂት ቀናት ከቀረው ሥልጣናቸው ለማባረር የሚያደርጉት ጥረት ከሪፐብሊካን ፓርቲ አባላትም ድጋፍ እያገኘ መሆኑን የዘገበው ቢቢሲ፣ ትራምፕ ከሥልጣን እንዲባረሩ የሚጠይቀው ክስ እንዲመሰረትባቸው ድጋፋቸውን ከገለጹት መካከል ከፍተኛዋ የሪፐብሊካን ፓርቲ እንደራሴ ሊዝ ቼኒ እንደሚገኙበትም አመልክቷል፡፡የትራምፕ ደጋፊዎች ባለፈው ሳምንት ረቡዕ በታላቁ የአገሪቱ ተቋም ካፒቶል ሂል ላይ በፈጸሙትና አምስት ሰዎችን ለሞት በዳረገው አጉራ ዘለል የአመጽና የብጥብጥ ድርጊት ተሳታፊ እና ተባባሪ ናቸው ተብለው የተጠረጠሩ በርካታ የፖሊስ አባላት ከስራ መታገዳቸውንና በ15 ያህል ፖሊሶች ላይ ምርመራ እየተደረገ እንደሚገኝ የዘገበው ቢቢሲ፣ ጥፋተኛ ሆነው በተገኙት ላይ ከስራ እስከማባረር የሚደርስ እርምጃ ይወሰዳል መባሉን ገልጧል፡፡ከአመጽ ድርጊቱ ማግስት ጀምሮ የተለያዩ ማህበራዊ ድረገጾች ትራምፕን በቋሚነትና በጊዜያዊነት ማገዳቸውን የገፉበት ሲሆን፣ ፌስቡክ፣ ኢንስታግራምና ትዊተር የትራምፕን አካውንቶች ከዘጉ ከቀናት በኋላ ሰሞኑን ደግሞ ዩቲዩብ ሰውዬውን ለአንድ ሳምንት አዲስ ቪዲዮ እንዳይለቅቁ ማገዱ ተነግሯል፡፡", "passage_id": "ef3dead25936455831fbee87fc2f8e3f" }, { "passage": "ይህንንም ተከትሎ የሃገሪቱ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፀረ-ዘረኝነት ተቃውሞ የተነሳውን አመፅ ለማብረድ የመከላከያ ሠራዊቱን እንደሚያሰማሩ ዝተዋል። \n\nየተለያዩ ግዛቶችና ከተሞች የተቀሰቀሰውን አመፅ ማብረድ ከተሳናቸው የመከላከያ ሠራዊቱንን እንደሚልኩም እየተናገሩ ነው።\n\nሆኖም የተለያዩ ግዛቶች አስተዳዳሪዎች ፕሬዚዳንት ትራምፕ የመከላከያ ሠራዊቱን ለመላክ የግዛቶቹ ፈቃድ እንደሚያስፈልጋቸውና፤ ጣልቃ ገብነትም አይቻልም እያሉ ነው።\n\nፕሬዚዳንቱ ሰራዊቱን በግዛቶቹ ማሰማራት ይችላሉ?\n\nበአጭሩ አዎ ይችላሉ፤ ይህም የሚሆነው ባልተለመዱ ክስተቶች ነው።\n\nበተለያዩ ግዛቶች ላይ በሺዎች የሚቆጠሩ የብሔራዊ ዘብ ወታደሮች ተሰማርተዋል። እነዚህ ወታደሮች የአሜሪካ ሰራዊት ተጠባባቂ ኃይሎች ናቸው። \n\nበአሜሪካ ከሃያ በበለጡ ግዛቶችም ተቃውሞዎችን ለማብረድ በሚል ተሰማርተው የሚገኙ ሲሆን፤ እነዚህ ወታደሮች በከተሞቹ ወይም በግዛቶቹ ጥያቄ የተላኩ ናቸው። \n\nነገር ግን በአስራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን በተደነገገው የአሜሪካ ህግ መሰረት የግዛቶች ጥያቄ ሳያስፈልግ የፌደራል መንግሥቱ ጣልቃ የሚገባባቸውን ሁኔታዎች ዝርዝር ተቀምጧል።\n\nዘ ኢንዘሬክሽን አክት ተብሎ የሚታወቀው ይህ ህግ ግዛቶች የአሜሪካን ህገ መንግሥት ማስከበር በሚሳናቸው ወቅት ወይም የዜጎች መብት በሚጣስበት ወቅት ፕሬዚዳንቱ ያለ ግዛቶች ፈቃድ መወሰን ይችላሉ።\n\nበጎርጎሳውያኑ 1807 የፀደቀው ይህ ህግ \" ቀደምት አሜሪካውያን ጥቃት ሲያደርሱ\" ፕሬዚዳንቱ ያንን ለመከላከል ሰራዊት ማሰማራት እንደሚችሉ የተደነገገ ሲሆን፤ በቀጣይም አመታትም በሃገሪቱ የሚፈጠሩ ረብሻዎችን ለማረጋጋት እንዲሁም የሲቪል መብቶችን ለማስከበር በሚልም ተጨማሪ ሃሳቦች እንዲካተቱበት ሆኗል። \n\nበጎርጎሳውያኑ 1878 ይህንኑ አስመልክቶ ተጨማሪ ህግ የተላለፈ ሲሆን ይህም በሃገር ውስጥ ወታደራዊ ሃይል ለመጠቀም የኮንግረስ ፍቃድ እንደሚያስፈልግ የሚያዝ ነው።\n\n ነገር ግን አንድ የህግ ባለሙያ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ኢንዘሬክሽን አክት በራሱ ፕሬዚዳንቱ ሰራዊት እንዲያሰማሩ ህጋዊ ስልጣን እንደሚሰጣቸው ነው።\n\nባለው የሃገሪቱ ሁኔታ ፕሬዚዳንቱ የግዛቶቹን አስተዳደር ሳይጠይቁ የመከላከያ ሰራዊት የማዝመት ህጋዊ መሰረት እንዳላቸውም ተቀባይነት አለው። \n\nበቴክሳስ ዩኒቨርስቲ የህግ ፕሮፌሰር የሆኑት ስቴፈን ቫልዴክ በበኩላቸው \"በታሪክም ሆነ በልምድም እንደታየው የሃገሪቱ ፕሬዚዳንት የፌደራል ወታደሮችን በተለያዩ ግዛቶች ላይ ለማሰማራት ፈቃድ መጠየቅ እንደማያስፈልጋቸው ነው\" ማለታቸውን የሃገሪቱ ሚዲያዎች ዘግበዋል።\n\nከዚህ ቀደም ይህንን ህግ የተጠቀመበት ይኖር ይሆን?\n\nየኮንግረስ አገልግሎት በሰራው ምርምር መሰረት የኢንዘሬክሽን አክት በሃገሪቷ ውስጥ በበርካታ ጊዜያት ተግባራዊ ቢሆንም በባለፉት ሶስት አስርት አመታት ግን ተፈፃሚ አልሆነም። \n\nለመጨረሻ ጊዜም የተተገበረው በጎርጎሳውያኑ 1992 በፕሬዚዳንት ጆርጅ ቡሽ የስልጣን ዘመት ወቅት ሲሆን፤ ይህም በሎስ አንጀለስ የተካሄደን ፀረ-ዘረኝነት ተቃውሞን ለመቆጣጠር ነው።\n\nበጎርጎሳውያኑ 1950ና 60ዎቹ የሲቪል መብቶች ተጠናክረው በነበረበት ወቅት፣ የግዛቱ አስተዳዳሪዎች ቢቃወሙም የተለያዩ ሶስት መሪዎች ተግባራዊ አድርገውታል። \n\nበጎርጎሳውያኑ 1957 በአርካንሰስ ግዛት ውስጥ ነጮችና ጥቁር ተማሪዎች አብረው ይማሩ የሚለውን ተከትሎ የተነሳውን ሁከት ለማረጋጋት ፕሬዚዳንት ድዋይት አይዘንአወር የመከላከያ ሰራዊት አሰማርተዋል። በወቅቱም ተቃውሞዎች ገጥሟቸው ነበር።\n\nከ1960ዎቹ መጨረሻ በኋላ የዚህን ህግ ተፈፃሚነት በከፍተኛ ሁኔታ ቀንሷል። \n\nየካትሪና አውሎ ንፋስ ያስከተለውንም ቀውስ ተከትሎ ለተለያዩ ግዛቶች ወታደራዊ ድጋፍ እንዲደረግ በሚልም... ", "passage_id": "efdf3132222751d2f71949fa5682a209" }, { "passage": " በኢኮኖሚ ቀውስ ክፉኛ የተመታችውና በህዝባዊ ተቃውሞ ስትናጥ የሰነበተችው ፔሩ፤ 1 ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ 3 ፕሬዚዳንቶችን መቀያየሯን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡በሙስና ወንጀል መዘፈቃቸው የሚነገርላቸውንና ህዝቡ አደባባይ ወጥቶ በተቃውሞ ስልጣን እንዲለቁ የጠየቃቸውን የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ማርቲን ቪዝካራን ባለፈው ሳምንት ከመንበረ ስልጣናቸው ያነሳው የአገሪቱ  ምክር ቤቱ፣ ከቀናት በኋላ የቀድሞውን አፈ ጉባኤ ኢማኑኤል ሜሪኖን በፕሬዚዳንትነት ቢሾምም ሰውየው ሃላፊነታቸውን በአግባቡ አልተወጡም በሚል ሌላ ህዝባዊ ተቃውሞ መቀስቀሱን ተከትሎ፣ ለ5 ቀናት ከቆዩበት ስልጣን አንስቶ፣ ባለፈው ሰኞ ደግሞ ፍራንሲስኮ ሳጋስቲን በጊዜያዊ ፕሬዚዳንትነት ሾሟል፡፡በሙያቸው መሃንዲስ የሆኑት የ76 አመቱ አዲሱ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ፍራንሲስኮ ሳጋስቲ ከአምስት ወራት በኋላ እስከሚካሄደው የአገሪቱ ብሔራዊ ምርጫ ድረስ በስልጣን ላይ ይቆያሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የጠቆመው ዘገባው፣ ከምክር ቤቱ አባላት መካከል ግማሽ ያህሉ ሙስናና የገንዘብ ማጭበርበርን ጨምሮ በተለያዩ ወንጀሎች ተጠርጥረው ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሚገኙም ገልጧል፡፡", "passage_id": "6dae89f3125f686f2a500f761adc2b12" }, { "passage": "በቀድሞዋ በርማ በዛሬዋ ሚያናማር የነበረውን አምባገነናዊ ወታደራዊ መንግሥት ተከትሎ በአሜሪካ ለረዥም ጊዜ ማዕቀብ ተጥሎ ቆይቶ ነበር። \n\nትናንት በሚያንማር የአገሪቱ ጦር መፈንቅለ መንግሥት አከናውኗል። ወታደሮች ሥልጣን መቆጣጠራቸውን ይፋ ያደረጉት የሲቪል መንግሥት አባላትን በቁጥጥር ሥር ማድረጋቸውን ተከትሎ ነው።\n\nየኖቤል ሰላም ሽልማት ተሸላሚዋ ኦንግ ሳን ሱ ቺ እና ሌሎች የፖለቲካ መሪዎች ተይዘው ወዳልታወቀ ሥፍራ ተወስደዋል።\n\nየተባበሩት መንግሥታት፣ ዩናይትድ ኪንግደም እና የአውሮፓ ሕብረት በበርማ የተደረገውን መፈንቅለ መንግሥት አጥብቀው ኮንነዋል። \n\nከእአአ 1989-2010 በእስር ቆይተው የነበሩት ሳን ሱ ቺ በቁጥጥር ሥር ከመዋላቸው በፊት ለደጋፊዎቻቸው በጻፉት ደብዳቤ “መፈንቅለ መንግሥቱን ተቃወሙ” ብለዋል። \n\nሳን ሱ ቺ መፈንቅለ መንግሥቱ በአገሪቱ ወታደራዊ አምባገነናዊ ስርዓትን ያመጣል ሲሉ ጽፈዋል ተብሏል። \n\nበሚያንማር በወታደሩ እና በሲቪል አስተዳደሩ መካከል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ውጥረት ተከስቶ ነበር።\n\nባለፈው ሕዳር በተደረገ ምርጫ የሳን ሱ ቺ ፓርቲ 'ናሽናል ሊግ ፎር ዲሞክራሲ' መንግሥት ለመመሥረት የሚያስችለውን የመቀመጫ ቁጥር ማግኘት ችሎ ነበር። ሆኖም የአገሪቱ ጦር ምርጫው ተጭበርብሯል ሲሉ ቆይቷል።\n\nጦሩ መፈንቅለ መንግሥቱን ካደረገ በኋላ የ11 ሚንስትሮችን እና ሚንስትር ዲኤታዎችን ሹም ሽር አድርጓል። በሌሎች እንዲተኩ ከተደረጉ ሚንሰትሮች መካከል የፋይናንስ፣ የጤና እና የውጪ ጉዳይ ሚንስትሮች ይገኙበታል። \n\nፕሬዝደንት ባይደን ባወጡት መግለጫ የአገሪቱ ጦር የሕዝቡን ፍላጎት ቀልብሶ ስልጣን መቆጣጠሩ አግባብ አይደለም ብለዋል። \n\nአሜሪካ ከ10 ዓመታት በላይ በበርማ ላይ ጥላ የነበረውን ማዕቀብ ያነሳችው አገሪቱ ወደ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት መሸጋገሯን ተከትሎ ነው። ባይደን፤ “በየትኛውም ስፍራ በዲሞክራሲ ላይ ጥቃት ሲደርስ አሜሪካ ወደጎን አትልም” ብለዋል። \n\nይሁን እንጂ የፖለቲካ ተንታኞች የአገሪቱ ጦር መፈንቅለ መንግሥቱን ለማደረግ ሲነሳ አሜሪካ ማዕቀብ እንደምትጥል ቀድሞ ያውቃል። ከአሜሪካ ማዕቀብ ይልቅ መፈንቅለ መንግሥቱን ተከትሎ ቻይና፣ ጃፓን እና ደቡብ ኮሪያ የሚሰጡት ምላሽ ለጦሩ አሳሳቢ ጉዳይ ነው ተብሏል። \n\nከዚህ ቀደም ቻይና የሚያንማር ጉዳይ ውስጣዊ ጉዳይ ነው በማለት ዓለም አቀፍ ጣልቃ ገብነትን ተቃውማ ነበር። በቀጠናው ከሚገኙት አገራት መካከል ካምቦዲያ፣ ታይናላንድ እና ፊሊፒንስ በበኩላቸው የበርማ ጉዳይ የአገሪቱ ውስጣዊ ጉዳይ ነው በማለት ጣልቃ መግባት እንደማይሹ ገልጸዋል። \n\nበሚያናማር ያለው ሁኔታ ምን ይመስላል? \n\nይህ መፈንቅለ መንግሥት በአገሪቷ ዜጎች ዘንድ ከፍተኛ ፍርሃትን ፈጥሯል። በርማ ወደ ዲሞክራሲያዊ ስርዓትእንደምትሸጋገር ተስፋን ሰንቀው ለነበሩት ዜጎች የሳን ሱ ቺ እና ሌሎች ሲቪል ፖለቲከኞች እስር እና መፈንቅለመግሥት የዲሞክራሲ ተስፋን ያጨለመ ሆኖባቸዋል። \n\nአውራ ጊዳናዎች ጸጥ እረጭ ብለው ታይተዋል። በዋና ከተማ ጎዳናዎች ላይ ብዛት ያላቸው የአገሪቱ ጦር አባላትተሰማርተው ታይተዋል። \n\nሰኞ ዕለት ተቋርጦ የነበረው የስልክ እና ኢንተርኔት ግነኙነት ማክሰኞ ንጋት ላይ ተመልሷል። \n\nየአገሪቱ ዋነኛ አየር ማረፊያ ግን አሁንም ዝግ እንደሆነ ነው። \n\nትናንት የሆነው ምን ነበር? \n\nትናንት [ሰኞ] ወታደሮች የአገሪቱን ሥልጣን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠራቸውና መሪያቸውም ኮማንደር ሚነ ኦንግ ሌይንግመሆናቸውን ተናግረዋል።\n\nበርካታ ወታደሮች በአገሪቱ ዋና ከተማ ናይፒታው እና በሌላኛዋ ትልቋ ከተማ ያንጎን ጎዳናዎች በብዛት ታይተዋል። \n\nየሞባይልና ኢንተርኔ አገልግሎት እንዲሁም ስልክ በስፋት የተቋረጠባቸው ዋና ዋና ከተሞች ላይ... ", "passage_id": "8eb8452b89447ea75d7502ea31727b98" } ]
5005d21e101f11eea31d3b268f71230b
ddf2dfea4f72848ef43452421ddeed6e
ወራጅ
ረዳትና ሹፌር የታክሲ የአውቶቡስ ወይም የሌላ መጓጓዣ መሪ ጠምዛዥና መላሽ የበር በረኛ አሳላፊ ናቸው። መገኛቸው እርግጥ እዚህ ፅሁፍ ላይ የወከሉት የወሬያችን ማጣፈጫ የጉዛችን ትዝብት መነሻና ፈጣሪዎች ናቸው። አብዝተው እኛነታችንን ያሳዩናል፤ አግዝፈው ማንነታችንን በእነርሱ ውስጥ ያጎሉልናል። እርግጥ ረዳትና ሹፌር መነሻቸው ማህበረሰብ መድረሻውም ህዝብ ስለሆነ እኛን በደንብ ያውቁናል። እኛም እነርሱ የሚያውቁንን ያህል ባናውቃቸውም በምልከታና በውሏችን በግምትና በሚናገሩት የሆነ ቦታ ላይ መመደቢያ እውቀት አላጣንላቸውም። የትውውቃችን ልዩነት ቢሰፋ አያስገርምም፤ እነርሱ እኛ መተዳደሪያቸው ስለሆንን ያለኛ ህይወት ምናቸውም አይደለም። እርግጥ እኛም በእርነሱ መሪነት መጓዛችን አልቀረምና መንገድ አመላካቻችን ናቸው። የሚቀንሱልን ድካም ሲታወስ ደግሞ እኛም ያለነሱ ህይወት ምን ያህል እንደምትከብድብን አያጠያይቅም። ደጋግሜ ስመለከታቸው ሹፌርና ረዳት አንድ ይመስሉኛል። ረዳቱ ሹፌሩን ሹፌሩ ከረዳቱ ጋር ያላቸው ግንኙነትና ተነጣጥለው ከእኛ ጋር ያላቸው ጉዳይ ሁሉ ከማስበው ጉዳይ ጋር መመሳሰላቸው ይበዛል። አይን አስመልክቶ አዕምሮ አስተውሎ ጉዳችን እየተመነዘረ ሲታይ እውነትም የማይመሳሰል ልዩነት የለም። የቅርባችን የሆኑትን ሹፌርና ረዳትን ሳስብ አንድ ነገር ጋር ተመሳሰሉብኝና ከማለፍ ላጋራችሁ ወደድኩ። ውዶቼ እኔ ረዳትና ሹፌሩ እንትናን እና እንትናን መሰሉኝ አልልም ፅሁፌን ስታነቡ ግን ስለ ማን እያወራሁ እንደሆነ እጅግ ይገባችኋል። በእርግጥም እኔም እናንተም እዚያው ውስጥ ስላለን አንድ መጓጓዣ ውስጥ በምናብ ይዣችሁ ልገባ ነው። ሹፌርና ረዳቱ መነሻዎቼ ተግባርና ስራቸው ደግሞ ማማሰያዎቼ ናቸው። የታሰበኝን በእርነሱ ውስጥ ማሳየት ፈለኩ፤ተከተሉኝ። ፀሀይ ጮራዋን ስትፈነጥቅ ከያለበት በማለዳ ተነስቶ በአጋጣሚ ሁሉም እዚያ ቦታ ላይ ተገኝቷል። እሩቅ ተጓዥ አብሮ ነጓጅ መሆኑን ተረድቶ በጋራ ስምምነት ጉዞውን ለማድረግ በመልካም ፍቃደኝነት አብሮ ለመዝለቅ ተገናኝቷል። መጓዣው ያለ ስጋት የተፈለገበት ማድረስ የሚያስችል አቅም አለው። ሹፌሩ ካልተዘናጋ ረዳቱ የእውነት አጓጓዥ ከሆነ ተጓዡ ስለ መጓጓዣው ካሰበ በእርግጥም ምቹ ነው። ረዳቱ “የሞላ… የሞላ” እያለ ይጣራል። ለካ ሰዎች መሀል የነበረው ሹፌር የሞላው መኪና ላይ ለማሟያነት ተመልቶ ገብቶ ከፊት ቦታውን ይዞ ኖሯል። በሹፌሩ ጠያቂነትና ረዳቱ በሰጠው ምላሽ ሁሉም ተሳፋሪ ቦታውን መያዙ ተሰማ። ተሳፋሪው ልሳነ ብዙ ነው፤ በየራሱ መናገሪያ የጋራ ስለሆነው ጉዳይ ይነጋገራል። ሹፌሩን ተማምኖ ሁሉም መንገዱን ቀጥሏል። ተሳፋሪው እርስ በእርሱ ለመግባባት በጋራ አብሮ የሚያስጉዘውን ተስፋ የጋራ የሆነ አላማን ሰንቋል። ሁሉም ያሰበው እስከ መጨረሻ አብሮ በጋራ መድረስ ነው። መጓጓዣው ወደ ፊት ይሄዳል። መሪው አንዳንዴ ብቻ ከኋላ ድምፅ ሲሰማ ወደ ኋላ እየተመለከተ አብዝቶ ወደፊቱ ብቻ እያየ መጓጓዣውን ይመራል።ጉዞው አድካሚ ነው። መንገዱ ብዙም የተቃና ባይሆንም፤ የተሳፋሪውን የጋራ ጉዞ የሚደናቅፍን ጋሬጣ ግን በመተጋገዝ እያለፍነው ቀጥለናል። የጉዞው ትልቁ ፈተና የሆነው ረዳቱ ነው። በእግጥም ከሹፌሩ ለተሳፋሪ የሚቀርበው ረዳቱ ስለሆነ ለተሳፋሪው ክፉ ሆኖ የሚታየው ብዙውን ጊዜ ረዳቱ ነው። እርግጥ ሹፌሩ ረዳቱን ሿሚ ስለሆነ ከሹፌሩ ጋር ነጥሎ አይጠላውም። ለይቶም አይወደውም። ረዳቱና ሹፌሩ በበለጠ ግንኙነታቸው የጠበቀ ነው። ረዳቱ ከተሳፋሪው አንድም ሳይቀር የሚፈለግበትን ተቀብሎ ለሹፌሩ አስተላልፏል። ግን ደግሞ በየመሃሉ ‹‹ሂሳብ ያልከፈለ አለ›› ብሎ መጠየቁን ቀጥሏል። ያልከፈለ የሚጠበቅበትን ያላዋጣ አንድም እንደሌለ ጠንቅቆ ያውቀዋል። ነገር ግን የያዘውን እያጎደለ የተሰጠውን እየቀነሰ ያልከፈለኝ አለ ወይ የሚለውን ጥያቄውን ይደጋግማል። አጠገቡ ባለው መጮህ በቀረበው ማሳበብ የተለመደ ነውና ሁሉም ረዳቱን ይገላምጣል። ረዳቱ ሲነካ ሹፌሩ ጋር መድረሱ አይቀርም። ጩኸቱ ሲከር ድምፁ ሲጎላ ግን ሹፌሩም ወደ ተሳፋሪው መመልከቱ አልቀረም። ተሳፋሪው በረዳቱ ንግግር በሽቋል። ‹‹እንዴት መክፈላችሁን እያወቀ ያልከፈለ አለ›› ብሎ ይጠይቃል።ተሳፋሪው እርስ በእርሱ ባይጠራጠርም አንዳንዱ ላይ “ያልከፈለ ይኖር ይሆን?” የሚል የተሳሳተ ሀሳብ ወደ አዕምሮው ብቅ ያለ ይመስላል። እራሱ የከፈለ እንጂ ሌላ ያልከፈለ ወይም ያላዋጣ ያለ የሚመስለው ከመሀል አልጠፋም። ደግነቱ አብዛኛው ተሳፋሪ መክፈሉን ያውቃል። የረዳቱ ‹‹ያልከፈለ አለ?›› የሚል ተደጋጋሚ ጥያቄ፤ ያልከፈለ ይኖር ይሆን እንዴ አሰኝቶት እንጂ አንዱ ለሌላው ሌላው ለአንደኛው መክፈሉን ያውቃል።ተሳፋሪው በተለያየ ቋንቋ እያወራ ይግባባል። የተለያየ የባህል ስብጥር ያለው ቢሆንም አይጣረስም። እንደውም አንዱ ባንዱ ሳይዳቀል አንዱ በሌላው ሲሞላ ልዩ ይሆናል። በውይይት በመግባባት ጉዞውን ቀጥሏል። ሹፌሩ የተሳፋሪውን ሁኔታ ለመቃኘት አንዳንዴ ዞር ሲል መጓጓዣው በትክክል መንዳት ይሳነውና ይንገጫገጫል። ያኔ ተሳፋሪው ወደ ሹፌሩ ያማትራል። ‹‹ቀስ ብለህ ንዳ እንጂ፤ በሰላም መግባት እንፈልጋልን።›› የሚለው ይበዛል። ቀስ ሲል ደግሞ ‹‹አይችልም እኮ ለምን መሪውን ለሌላ ሰው አይሰጠውም›› የሚለውም አልጠፋም። “ወራጅ አለ?” የረዳቱ ሌላ ጥያቄ፤ ምን ማለቱ ነው። ተሳፋሪው አልጎመጎመ።የምን ወራጅ ብሎ ጥያቄ ማቅረብ ነው። ሁሉም አብሮ ሊጓዝ ተስማምቶ፤ ሁሉም አብሮ እስከመጨረሻ ሊሻገር ተነጋግሮ፤ ወራጅ አለ ማለት ምንድን ነው። ተው እንጂ ረዳት ቀስ ቀስ..ሹፌሩንም አታደናብር። ህዝቡ በብዙ ይህን ማለት ፈለገ። አንድ ተጓዥ ተናገረ። ይሄን ያለው በሌላው ተደገፈ። ሹፌሩና ረዳቱ ተሳፋሪውን ይዘው ጉዞዋቸውን ቀጥለዋል። አልፎ አልፎ በተሳፋሪው ግራ መጋባት ጉዞአቸው ጋብ እያለ መልሶ እየቀጠለ ወደ ፊት በጋራ መጓዙን ቀጥለዋል። የሹፌሩ መዘናጋት በተሳፋሪው እሪታ እየተቃና የረዳቱ ‹‹ወራጅ አለ›› ማለት ካልበዛ፣ ተሳፋሪው ያልደረሰን ተሳፋሪን ‹‹ውረድ›› ብሎ ካላደናበረ ሁሉም ከዳር በጋራ ለመድረስ ጉዞውን ቀጥሏል። እርግጥም ይህ ከሆነ መንገዱ ይሰምራል። አበቃሁ ቸር ይግጠመን።አዲስ ዘመን ታህሳስ 27/2012 ተገኝ ብሩ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=25216
[ { "passage": "አቶ ሰለሞን ተስፋዬ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ቤቴል አካባቢ ነዋሪ ናቸው። በልማት ኮሜቴ ውስጥ ይሠራሉ። ዘመናዊ የፍሳሽ ማስወገጃ መስመር በአካባቢው ከተዘረጋ አምስት ዓመት እንደሞላው ጠቅሰው፣ ባለሥልጣኑ ቤት ለቤት ሊያገናኝላቸው እንዳልቻለ ይጠቁማሉ። መስመሩ ከመኖሪያ ቤት ፍሳሽ ጋር\nባለመገናኘቱ ነዋሪዎች መቸገራቸውን አመለክተው፣ በተደጋጋሚ ወደ ባለሥልጣኑ ብንመላለስም ችግሩን የሚቀርፍልን አካል ልናገኝ አልቻልንም\nሲሉ ይጠቁማሉ። ቅጥያ የሚባለው ከየቤቱ ወደ ዋናው ፍሳሽ ማስወገጃ የሚያገናኘው መስመር አልተገናኘም ያሉት አቶ ሰለሞን፤ መስመሩ\nእንዲገናኝላቸው ለአምስት ዓመታት ወደ ወረዳና ውሃ ፍሳሽ ወደ ባለሥልጣን መመላለሳቸውን ያስታውሳሉ።የአዲስ አበባ ከተማ ውሃና ፍሳሽ\nባለሥልጣን በቅርቡ ከዘመናዊ ፍሳሽ አወጋገድ ጋር ተያይዞ መሰረተ ልማቱ ከተዘረጋባቸው አካባቢዎች ነዋሪዎች ጋር በራስ ሆቴል በመከረበት\nወቅትም አቶ ሰለሞን ተገኝተዋል። በመድረኩ የተገኘነው በፍሳሽ መስመሩ ተጠቃሚ አድርጉን፣ ቅጥያውንም አገናኙልን ለማለት ሲሉ የገለፁት\nአቶ ሰለሞን፣ ሰው ዘመናዊ የፍሳሽ ማስወገጃ ሥርዓቱን ወዶት መጠቀም ቢፈልግም ምላሽ አልተገኘም ይላሉ። የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ\nነዋሪው አቶ ሽመልስ መርጊያ በአካባቢያቸው ዘመናዊ የፍሳሽ ማስወገጃ መዘርጋቱን ይገልፃሉ። በዚህም ነዋሪው ያለስጋት የአገልግሎቱ\nተጠቃሚ መሆኑን ጠቅሰው፣ እሳቸውም በአገልግሎቱ ዘመናዊነት ርካታ እንደሚሰማቸው ይናገራሉ፤ መፀዳጃ ቤቱ ሞላ ላስጠርግ ብሎ መመላለስ\nየለም፤ ጊዜንና ጉልበትን ማባከን ቀርቶልናል ሲሉ አቶ ሽመልስ ያብራራሉ። ኅብረተሰቡ ዘመናዊ የፍሳሽ ማስወገጃ\nሥርዓት እንዲጠቀም ግንዛቤ ለመስጠት ባለሥልጣኑ ጥረት ማድረግ እንደሚገባው አስገንዝበው፣ ዘመናዊ የፍሳሽ ማስወገጃ ቱቦው ተዘርግቶ\nእያለ በፍሳሽ ማስወገጃ አቅራቢያ የመፀዳጃ ቤት ጉድጓድ የሚቆፍሩ ሰዎች በተደጋጋሚ ማየታቸውን ያመለክታሉ። ይህም ከግንዛቤ ማነስና\nከቤቴ ወደ ፍሳሽ ማስወገጃ ለማስቀጠል ብዙ ክፍያ እጠየቃለሁ ከሚል ሥጋት የመነጨ ሊሆን እንደሚችል ይገምታሉ። የባለሥልጣኑ የፍሳሽ መስመር ቅጥያ\nንዑስ የሥራ ሂደት መሪ አቶ ዘላለም ከተማ በምክክር መድረኩ ላይ እንዳሉት፤ አዲስ አበባን የዘመናዊ ፍሳሽ አወጋገድ ሥርዓት ተጠቃሚ\nለማድረግ በሦስት ቦታዎች የፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያዎችን ግንባታ እየተካሄደ ይገኛል።ከነዚህም መካከል በቀን መቶ ሺህ\nሜትር ኪዩብ የማጣራት አቅም ያለው የቃሊቲ ፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ ግንባታ ተጠናቅቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። 30 ሺህ ሜትር ኪዩብ\nበቀን የማጣራት አቅም ያለው የደቡብ አቃቂ ፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ ግንባታም የተጀመረ ሲሆን፣ በምሥራቅ ተፋሰስ የሚገኘውና ሰማንያ\nሺህ ሜ. ኪዩብ የማጣራት አቅም ያለው ጣቢያም በጥናት ላይ ነው። በከተማዋ በስምንት የጋራ መኖሪያ ቤት ሳይቶች ሃያ ሰባት ሺህ\nሜትር ኪዩብ በቀን የሚያጣሩ 12 ያልተማከሉ ማጣሪያ ጣቢያዎች ተገንብተው አገልግሎት እየሠጡ ይገኛሉ።ፍሳሽ ቆሻሻን በዘመናዊ መንገድ ማስወገድ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው የተናገሩት\nአቶ ዘላለም፣ መፀደጃ ቤት ሞላብኝ የሚል ሥጋት እና ፍሳሽን ለማስወገድ የሚደረግ የተሽከርካሪ ምልልስን በማስቀረት ጊዜና ጉልበትን\nለመቆጠብ እንደሚረዳ ይገልፃሉ። የትራፊክ መጨናነቅ፤ ብክለትና መጥፎ ሽታን ያስቀራል እንዲሁም ፅዱ፣ ውብና ለመኖር የምትመች ዘመናዊ\nከተማን ለመፍጠር ያግዛል ይላሉ።ጠጣር እና ባዕድ ነገሮችን በፍሳሽ መሥመሮችና ማጣሪያ ጣቢያዎች በመግባት\nየሚያደርሱት ጉዳት ከፍተኛ መሆኑን የሚገልፁት አቶ ዘላለም፣ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ መስመሩን ሊጠቀም እንደሚገባም\nያስገነዝባሉ። የባለሥልጣኑ ምክትል ኃላፊ አቶ ተስፋለም ባዩ በቤቴል አካባቢ የፍሳሽ መሠረተ\nልማት ተጠቃሚ ለማድረግ ቀሪ የማገናኘት ሥራዎች እንዳሉ ጠቅሰው፣ በዚህ የተነሳ መስመር የማገናኘቱ ሥራ መጓተቱን ይገልፃሉ። ችግሮቹን\nለማቃለል ጥረት እንደሚደረግ ተናግረዋል። በበጀት ዓመቱ ከ40 ኪሎ ሜትር በላይ የፍሳሽ ማስወገጃ መስመር እንደሚዘረጋ ጠቅሰው፣\nከ12ሺ በላይ ለሚሆኑ ቤቶች ደግሞ የቤት ለቤት ቅጥያ አገናኝተን ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየሠራን ነው ሲሉ አስታውቀዋል። ከአራት ዓመት\nበፊት 10 በመቶ\nብቻ የነበረው\nየዘመናዊ ፍሳሽ\nአገልግሎት ተጠቃሚ\nቁጥር አሁን\n27 በመቶ መድረሱን\nየባለሥልጣኑ መረጃ\nያመለክታል።አዲስ ዘመን መጋቢት 1/2012ኃይለማርያም ወንድሙ", "passage_id": "8f6aba963c0a38ee74bed8097f314e87" }, { "passage": "ወጣት ረሺድ ተሺታ በአንድ ጥግ ላይ በእጁ የያዘውን አነስተኛ ሻንጣ ጉልበቱ ላይ አድርጎ ተንተርሶ ተኝቷል፡፡ አብረውት ያሉት ሶስት ጓደኞቹ ላይም የድካም ስሜት ይነበባል፡፡ ረሺድና ጓደኞቹ ወደ ቤተሰቦቻቸው ሻሸመኔ ለመሄድ ቃሊቲ መለስተኛና አገር አቋራጭ መናኸሪያ ግቢ ውስጥ ሆነው ትራንስፖርት ሲጠብቁ ነው ያገኘኋቸው፡፡ እነርሱ ወደሚፈልጉበት ሥፍራ የሚሄድ የትራንስፖርት አገልግሎት እንደሌለ ቢነገራቸውም ተስፋ አልቆረጡም:: ችግራቸውን እንደነገሩኝ ከአንድ ወር በፊት ተቀጥረው ይሰሩበት የነበረው የህንጻ ግንባታ ሥራውን በማቋረጡ ከሥራቸው ተፈናቅለዋል፡፡ ሥራ ከሌላቸው መኖሪያም ሆነ የዕለት ኑሮአቸውን ለመምራት ይቸገራሉ:: ያላቸው ምርጫ ወደቤተሰቦቻቸው መመለስ ነው፡፡\nእንደ ወጣት ረሺድና ጓደኞቹ በመናኸሪያው ግቢ ውስጥ ብዙ መንገደኞች እንደነበሩ በሥፍራው በነበርኩበት ወቅት ከአንዳንዶች ተረድቻለሁ፡፡ ለወትሮ\n ከመግቢያው በር ጀምሮ ወከባ የነበረበት ግቢ እንቅስቃሴው ተቀዛቅዟል፡፡ በመካከለኛ ሀገር አቋራጭ ወደ ዱከም፣ቢሾፍቱ፣ሞጆ፣ናዝሬት ከሚያጓጉዙት በስተቀር የሀገር አቋራጭ ጉዞ ከሁለት ቀናት በፊት መቆሙን በትራንስፖርት ዘርፉ ካሉት ባለሙያዎች መረዳት ችያለሁ፡፡\nመርካቶ የሚገኘው ከፍተኛ ሀገር አቋራጭ አዲስ ከተማ መናኸሪያ በደረስኩ ጊዜ በግቢው ውስጥ ተሽከርካሪዎች አልነበሩም፡፡ መናኸሪያው ዝግ ነበር፡፡ በመናኸሪያው የክትትልና ስምሪት ሰራተኛ አቶ ታፈሰ በረደድ እንደገለጹልኝ፣ ከትናንት በስቲያ ጀምሮ አገልግሎቱ ተቋርጧል:: ተቸግረው የነበሩ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን መታወቂያቸውን በማየት ትናንት ወደ ባህርዳርና ደብረማርቆስ ሁለት ተሽከርካሪዎች አገልግሎት እንዲሰጥ ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡\nበእያንዳንዱ ተሽከርካሪ ውስጥ 60 ተማሪዎች በታሪፉ አገልግሎቱ እንደተሰጣቸውና ለኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ተጋላጭነቱ እንዳይኖር አስፈላጊው ቅድመ መከላከል በማድረግ እንደተሸኙ አመልክተዋል፡፡ ተማሪዎች በመሆናቸውና\n ሰሞኑንም ወደየ አካባቢያቸው ይሸኛሉ የሚለው መረጃ በመገናኛ ብዙሃን በመተላለፉ በሚደርሱበት ሥፍራ እንደማይጉላሉ ተስፋ አድርገዋል፡፡\nበወትሮው በመናኸሪያው በቀን ቁጥሩ እስከ 80 የሚደርስ ተሽከርካሪ አገልግሎት እንደሚሰጥና እስከ አምስት ሺ የሚደርስ ተገልጋይም እንደሚስተናገድ ይናገራሉ፡፡ በየዕለቱ የሚሰጠው አገልግሎት በዙሪያው ያለው ግርግር በሁለት ቀናት ውስጥ ያ ሁሉ እንዳልነበር መሆኑ እንግዳ ሆኖባቸዋል:: የበሽታው አሳሳቢነትንም እንደሚያሳይ\n ይገልጻሉ፡፡ በሽታው ተወግዶ ወደ ቀድሞ ተግባራቸው ለመመለስ ተመኝተዋል፡፡ ይህ እንዲሆን ከእርሳቸው ጀምሮ እያንዳንዱ ሰው ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ሲሉም ምክራቸውን ለግሰዋል፡፡\nየመናኸሪያዎቹ ሥራ መቀዛቀዝ በዙሪያቸው የምግብና የተለያዩ አገልግሎቶችን በመስጠት የሚተዳደሩና የቀን ሠራተኞችንም ከሥራ ያስተጓጎለ መሆኑም ጉዳቱ ከፍተኛ እንደሆነ መገመት አያዳግትም፡፡ ግን በፍጥነት እየተዛመተ ያለውን ወረርሽኝ ለመከላከል ያለው ቁርጠኝነት እጅግ አናሳ እንደሆነ በአንዳንድ የአዲስ አበባ አካባቢዎች ታዝቢያለሁ፡፡ በተለይ ፒያሳ አካባቢ በሚገኘው አትክልት ተራ በሽታው ስለመኖሩ የሚታወቅ አይመስልም፡፡ ከጥቂት ነገዴዎችና ሸማቾች በስተቀር ግብይታቸው ጥንቃቄ የጎደለው ነው፡፡\nርቀታቸውን ለመጠበቅ ገመድ ያሰሩ ቢኖሩም የገንዘብ እና የዕቃ ቅብብሎሹ በጥንቃቄ ሲከናወን አላየሁም፡፡ አንዳንድ ያነጋገርኳቸው ሸማቾች በሰጡት አስተያየት የሰው ብዛቱ ይኖራል ብለው ከገመቱት\n በላይ ሆኖባቸዋል፡፡ ከወትሮው ይቀንሳል ብለው በማሰብ እንደሄዱም ተናግረዋል፡፡ አንዳንዶቹም በአካባቢያቸው የዋጋ ውድነት በመኖሩ ቅናሽ ፍለጋ እንደመጡ ይገልጻሉ፡፡\nበገበያው ሥፍራ ውሃና ሳሙና በተወሰነ የርቀት ቦታ ቢኖርም የሚያስተውለው ሰው አልነበረም፡፡ ሁሉም የሄደበትን ጉዳይ ሲፈጽም ነው ያስተዋልኩት፡፡ በአካባቢው በጥበቃ ሥራ ላይ ያገኘኋቸው አቶ አረጋ እውነቱ ሸማቹ ለጥንቃቄው ቦታ የሰጠው አይመስልም ይላሉ፡፡ በአካባቢው በድምጽ ማጉሊያ ቅስቀሳ በመደረግ ላይ መሆኑን እና እርሳቸውም በሚችሉት ሁሉ ሰው እንዳይዘናጋ ጥረት ቢያደርጉም የሚፈለገውን ያህል እንዳልሆነ ያስረዳሉ፡፡\nአትክልት እየሸጠ ያገኘሁት ረሺድ ሁሴንም አብዛኛው ሸማች ትኩረቱ የሚገዛው ዕቃ ላይ እንደሆነ ይናገራል፡፡ ረሺድ አፉን ቢሸፍንም ከሸማች ጋር ያለውን ንክኪ የሚከላከልበት የቅድመ ንጽህናም ሆነ የእጅ ጓንት እየተጠቀመ አልነበረም፡፡ ሥራው ለቅድመ ጥንቃቄ ምቹ እንዳልሆነ ነው የገለጸልኝ፡፡\nበስፍራው ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ መሳሪያዎች (ማሽነሪ) መሸጫ ሱቅ ውስጥ ያገኘሁት ፈይሳ ታደሰም ትዝብቱን አካፍሎኛል፡፡ እርሱ እንዳለው፤ በአካባቢው ይቆሙ የነበሩ ተሽከርካሪዎች በሁለት ቀናት ጊዜ ውስጥ አላስተዋለም፡፡ ቀደም ሲል እስከ ረፋድ ሶስት ሰዓት ድረስ በስፍራው የሚቆዩ አትክልት የሚያራግፉ ተሽከርካሪዎችም የሉም፡፡ የሰው ቁጥር ግን አልቀነሰም፡፡ ህዝቡ ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ ትኩረት አድርጓል ብሎ አያምንም፡፡ አካባቢው እንደተባለው ከህዝብ ንክኪ አለመራቁ ብቻ ሳይሆን የጽዳት ጉድለቱም እንዳለ ነው፡፡ ቸልታው እስከ መቼ ይቀጥላል?\nአዲስ ዘመን መጋቢት 24/2012\nለምለም መንግሥቱ", "passage_id": "244f8f05e552760f30bfbf60261931b5" }, { "passage": "አጭሯ ቀጭኗ ባልቴት የሀብተጊዮርጊስ ድልድይ ላይ ቆመው እንደ ሃዘንተኛ አፍና አፍንጫቸውን በነጠላቸው አፍነው ቁልቁል ወደ ወንዙ እያዩ ጭንቅላታቸውን እየወዘወዙ ተክዘዋል። እኛ ደግሞ በአካባቢው ካለው የመተንፈሻ አካል ጸር ከሆነው መጥፎ ጠረን ራሳችንን ለመጠበቅ እየተጣደፍን እናልፋለን። የባልቴቷ ነገር ግራ ስላጋባን ሶስታችንም ተመልሰን ምን ሆነው እንደሆነ ጠየቅናቸው።\nእኔ ምን እሆናለሁ አሉ ኮስተር ብለው። አታዩትም እንዴ ይሄ ወንዝ በነጋ በጠባ እየጠቆረ ይመጣል በዛ ላይ ይይዘው ይጎተተው አንዳች ቆሻሻ አያጣም አሁንማ ብሶበት አረፋውም ይጠቁር ይዟል አሉ።ጸሀዩዋ ትሆን እንዴ አላቸው ጓደኛችን በማሾፍ።\nባልቴቷም በዋዛ አላለፉትም ጸሀይ እሚያጠቁር ቢሆን አንተ ከወንዙ ቀድመህ ሻንቅላ ትሆን ነበር ብለው በዛው ወደ ማጉተምተማቸው ገቡ።\nድሮ ቀረ… ወንዝ ድሮ ቀረ …\nደሞ ወንዝም ድሮ ቀረ ይባላል እንዴ ? ማዘር\nአዎ እውነቴን ነው ድሮ ቀረ መባል ሲያንሰው ነው፡፡ ድሮ ወንዝ ተወርዶ ጽዳት ይጠበቅ ነበር እንጂ እንዲህ እንደዛሬው ወንዝን ጎርፍ ካልመጣ የሚሸሽ አልነበረም። ለማቋረጥ እንኳ ቢፈለግ በዚያው እግራችንን ለቅለቅ ብለን ነበር የምናልፈው። ኧረ ስንት ነገር ነበረ … እዚሁ አዲስ አበባ እንኳ ሲከፋም ሲተከዝም ወንዝ ተውርዶ ነበር የሚንጎራጎረው። ዛሬ እንዲህ ሊያደርጉት።እማማ እዚህ ሽታው ጥሩ አይደለም ያሳምምዎታል። ግን እነማን ናቸው እንዲህ ያደረጉት። ምክሩን ጥያቄ አስከትዬ አቀረ ብኩላቸው።\nከተሜው እንጂ ሌላ ማን ይሆናል? መቼም እስከዛሬ ወንዝ የሚወር ጠላት መጣ ሲባል አልሰማ ንም፤ ይሄ እኮ ወራራ ነው አሉኝ በቆሙበት።\nባልቴቷን ገፋፍተን ካሰናበትን በኋላ አገር ያወራበት ችግር እንዲህ እያደገና እየተስፋፋ የመምጣቱን ነገር የየራሳችንን መፍትሄ በማመ ላከት ከጓደኞቼ ጋር በሰፊው አወጋንበት፡፡ የሶስታችንም ምክንያትና የመፍትሄ ሃሳብ ግን ለየቅል ነበር። የተስማማንበት ነገር ቢኖር በቁጥር የሚታወቁት ዋናዎቹ የአዲስ አበባ ወንዞች ብቻ ሳይሆኑ በየደጃፋችን ከአመት እስከ አመት የሚፈሱትም ቦዮች ያው ጥቁር መሆናቸውን፤ ችግሩ ደግሞ የመጥቆራቸው ብቻ ሳይሆን በአንዳንድ ቦታዎች ያሉት ወንዞችና ቦዮች ከአቅማቸው በላይ ከፈሳሹ ቆሻሻ ይልቅ የያዙት ደረቅ ቆሻሻ መብለጡን እንዲሁም ዛሬ ዛሬ የአዲስ አበባ ጌጥ እየሆነ የመጣውም የውሃ መያዣ ኮዳ (ሀይላንድ) የእነዚህ ትልልቅ ወንዞችም ሆነ ቦዮች የሜዳውና የመንገዱ ሁሉ መለያ ጌጥ እንደሆነ ነበር።በምክንያትና በመፍትሄ ባነሳነው ሀሳብ እኔ የከተማዋ የህዝብ ብዛት ቀን ከቀን እየጨመረ መምጣቱ ዋናው ምክንያት መሆኑን አስቀመጥኩ። ለማስረጃም የእኛን ቤተሰብ በማንሳት፡- እኛ ግቢ ስድስት ቤተሰብ ብቻ ነበር የምንኖረው፣ ለረጅም ዓመታት ተከራይ የሚባል ነገር አልነበረንም፣ የቆሻሻ ማጠራቀሚያው ማዳበሪያ እንኳን የሚሞላው በግድ ነበር። በዛ ለይ በሳምንት አንድ ቀን ቆሻሻ የሚሰበስበው መኪና ሳያቋርጥ ስለሚመጣ ቆሻሻ ብርቅ ነበር። አሁን የእኛ ግቢ እንኳን ድንኳን መጣያ ገመድ መዝለያም ቦታ የለውም፡፡ ከጎረቤት የሚለየን ካልሆነ ግድግዳችንን እንኳ በቅጡ ማየት አይቻልም ቤት ይሰራል ይከራይል ፤ቤት ይሰራል ይከራይል… ትንሽ ቦታ ከተረፈች አንድ ዘመድ ይመጣና ከዛኛው ክፍል ጋር ብትቀላቅላት ይላል አባታችን ተቀብሎ ተግባራዊ ያደርጋል። አሁን እኛ ግቢ በጣራ የማይገናኝ ቤት የለም። ታዲያ ይሄ ሁላ ሰው በሶስት መቶ ካሬ መሬት ላይ በአንድ የቧንቧ ውሃ መስመር፣ በአንድ መጸዳጃ ቤት፣ በአንድ ሻወር እየተጠቀመ እንዴት ቆሻሻው አይበዛም። በመሆኑም መፍትሄ የሚሆነው ወደ አዲስ አበባ የሚደረገውን ፍሰት መቀነስ ብቻ ነው ካልሆነ … ሃሳቤን ዘጋሁ።አይደለም ዘመኑ የፈጠራቸው በካይ ቆሻሻዎች መብዛታቸው እንጂ የሰው መብዛት የቆሻሻ መብዛትን አያመጣም፤ ማንም ፈልጎ ቆሻሻ አይፈጥርም አለ የኔ የሃሳብ ተቃዋሚ የሆነው ጓደኛዬ። ማብራራቱንም ቀጠለና ድሮ ፌስታል አናውቅም ነበር፤ ሀይላንድ የለም ባጠቃለይ ለአካባቢ ብከለት የአንበሳውን ድርሻ የሚወስደው የፕላስቲክ ምርት በብዛት አልነበረም። ከፕላስቲክ ምርት የሚታወቁት ኮንጎ ጫማ፣ ጋዴ ጫማ፣ ቦቲ ጫማ፣ ሳህንና ኩባያ ብቻ ነበሩ። በዛ ዘመን የውሃ ባሊው የብረት ሳፋው የብረት ታንከሩ እንኳ ቢሰቀል የብረት ነበር። ይሄ እንግዲህ ከእኛ በፊት የነበረውን የባዶ እግር፣ የእንቅብና ቁና እንዲሁም የጋንና የማሰሮን ዘመን ትተን ነው።በእኛ የልጅነት ዘመን እንጀራና ዳቦ ሲገዛ በዳንቴል ነበር የሚያዘው፤ አናቶቻችን ገበያ ሲወርዱ ቅርጫትና ዘንቢል ይዘው ነበር። እነዚህ ደግሞ መሬት ጥለህ አፈር ለበስ ብታረጋቸው በወር ውስጥ የሚበሰብሱ ናቸው። ቅርብ ግዜ እኮ ነው ይቺ ኬንያ የምትባል ሀገር በርካታ የፕላስቲክ ምርት ልካ ያበላሸችን። አሁን ደግሞ ቻይና ሁለት ዳቦ የማይዝ ፌስታል እያመረተች በየመንገዱ ስኳሩ ቲማቲሙ ሽንኩርቱ ሁላ ሲበተን ይውላል ይሄ አገልግሎት ተብሎ ደግሞ ወንዙ ሜዳው ሀገሩ ሁሉ በፌስታል ይበከላል፡፡ በዛ ወቅት ከየቤቱ የሚወጣው ቆሻሻ ለመቃጠል እንኳ ጊዜ አይወስድበትም ነበር፡፡ ለኩሰኸው ዞር ስትል አመድ ይሆናል፡፡ አመዱም ሲበተን በቀላሉ አፈር ይሆናል። አሁን እኮ ፕላስቲኩ፣ ጎማው ማይካው አንተ ካለጣፋኸው ሲነድ ውሎ ሲጨስ ያድራል። በዛ ላይ በዚን አርከፍክፈህ እንኳ ብታነደው ሳይበሰብስ የሚኖር የተጨማደደ ልጅ ጥሎብህ ነው የሚጠፋው። ስለዚህ በቀጥታ ወደ ባህላችን ተመልሰን ከፕላስቲክ ምርቶች ካልተፋታን መፍትሄ አናገኝም።በሁለታችንም ሃሳብ ያልተስማማው አባሪያችን (ጓደኛችን) ቅጥ ያጣው የቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓታችንና ራስ ወዳድነታችን እየተስፋፉ በመምጣታቸው የተከሰተ ችግር መሆኑን በማስረጃ በማስደገፍ አቀረበ። የአዲስ አባባ ሰው እንኳን ቆሻሻውን በአግባቡ ሊያስወግድ ይቅርና በመንገድ ዳር የተቀመጡትን የቆሻሻ ማጠራቀሚያዎች እንኳ በአግባቡ አይዝም ብሎ ጀመረ። ሃምሳ ግዜ የሚበሰብስና የማይበሰብስ ቆሻሻ እንለይ እየተባለ ይነገራል፡፡ ህዝቡ ግን የተረፈውን ምግብ በፌስታል ቋጥሮ ይጥላል። ሃምሳ ሳንቲ ሜትር ስፋት የሌለው ቦይ ውስጥ ጆንያ ሙሉ ቆሻሻ ይጥላል። ባዶ ገንዳ ቆሞ ዳር ላይ ቆሻሻውን ዘርግፎ ይሄዳል። አብዛኛው ሰው ወንዞች ለቆሻሻ ማስወገጃነት የተፈጠሩ ይመስል ትንሹንም ትልቁንም ቆሻሻ ይዞ የሚሮጠው ወደ ወንዝ ነው። ለሀቁ ከነዋሪው በላይ አጥፊ የለም ችግሩ ግን በይበልጥ ለጉዳት የሚዳርገው ነዋሪውን ሳይሆን በከተማዋ አጎራባች ያሉ አካባቢዎችን ነው። አዲስ አበባ ሆኖ ከወንዝ ውሃ የሚጠቀም አታገኝም ከከተማዋ ወጣ ስትል ግን ከብቶቹ ሰዎቹ ለንፅህና መጠበቂያና ለሌሎች ነገሮችም ይጠቀሙበታል። በዛ ላይ የገጸ ምድር ውሃ መበከል ለከርሰ ምድሩም መበከል መንስኤ ይሆናል።በፊት ስል በፊት መቼ እንደሆነ እንዳትጠይቁኝ እንጂ በመቅጣት ይታመን ነበር አሉ፡፡ ሰው ሲቀጣ ስለማያጠፋ ተብሎ ማለት ነው። አሁን ደግሞ ማስተማር ይቀድማል በሚል ምልከታ ቅጣቱ ተዘንግቷል እንደኔ ግን ሁለቱም የማይለያዩ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው። ሳያውቅ ያጠፋውን ማስተማር አንድ ነገር ነው እያወቀ የሚያጠፋውን ማስተማር ግን ችግሩን ከማበረታት የዘለለ ፋይዳ የለውም።አባሪያችን ንግግሩን ቀጠለ የነዋሪው ችግር ስል ግን አስተዳደሩንም ያጠቃልላል መቼም በእርግጠኘነት በመንግስት በኩል ወይ በኤጀንሲ አልያም በዳይሬክቶሬት ደረጃ ለዚህ ጉዳይ የተቋቋመ ክፍል መኖሩ አይቀርም። እኛ በትምህርት ቤት ብቻ የምናውቃት «ዳይሬክ ተርነት» ዛሬ ያልገባችበት ጓዳ የለም። ስለዚህ እነሱም ምን እየሰሩ እንደሆነ መጠየቅ አለበት። ለዚህም የተመደበ ገንዘብ ካለ የት እንደገባ መታወቅ አለበት። ማን ያውቃል እነሱስ ወንዝና የወንዝ ዳርቻ እናጽዳ ብለው ቢሯቸውን እያጸዱ ቢሆንስ።በአዳራሽ ጫጫታና በማስታወቂያ ጋጋታ ከተማን ማጽዳት አይቻልም። በዛ ሰሞን እንደ ወረት በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ተሳትፎ ጭምር የተጀመረው የከተማ ጽዳት ለዚህ አንዱ ማሳያ ነው። የዘመቻውን ወሬ ሳንጠግበው ተደበስብሶ ቀረ። በእርግጥ ያኔም ቢሆን ላይ ላይዩን እንጂ የውሃ መውረጃውን ውስጥ ውስጡን አልፈተሸም ነበር። የሚገርመው ሌሎቹም የሀገሪቱ ከተሞች ይሄንኑ እንደ ምርጥ ተሞክሮ ወስደው እየተገበሩት ነው።አባሪያችን ልንመልስለት አቅምም ስልጣንም የሌለንን ጥያቄ ጠይቆን ንግግሩ ገታ። ግን እስከ መቼ ይሆን ይቺ አዲስ አባባና ነዋሪዎቿ የቆሻሻ ፋብሪካ መሆናቸው ሳያንስ በከተማዋ ዙሪያ ያለውን ህዝብ እየበከሉ የሚኖሩት?።ራስወርቅ ሙሉጌታአዲስ ዘመን ጥር 18/2011", "passage_id": "0d449387420fbb096888ce3692e0ae45" }, { "passage": " እንደምን አደራችሁ? እንደምንስ ውላችኋል? ቤተሰቡ፣ ጎረቤቱ፣ ቀዬው፣ ከብቱ፣ አገሩ በአጠቃላይ ሁሉም ሰላም አድሯል? ደግ። ብለው ሲመርቁ አንድ ከጎረቤቴ ያሉ አዛውንት ሁሌ እመለከታለሁ። በየቀኑ ጠዋት ማየቴን እንጂ ልብ ብዬ ትርጉም ሰጥቼ ለማጤን ሞክሬ አላውቅም። 21 ዓመቱን የደፈነ የልጅ ልጃቸውን ‹‹አንተ ጎረምሳ፤ ለምን ሰው ሰላም አትልም? ቆይ የሰላምን ጥቅም ስታጣው ታውቀዋለህ›› ይሉታል። ለካስ በየአካባቢው ሰላም እንዲኖር ከጸሎት እስከ ተግባር መትጋት የሚጠበቅብን ለራሳችን ስንል ኖሯል። የሁላችንም የሠላም ምንጭ በሌሎች ሰላም መዋል ማደር ውስጥ ነው። በየትኛውም ጫፍ ሰላሙ የታወከ አካል ወይም ደግሞ በሰላም አለማደር ሲከሰት መፍትሔ መፈለግ ግድ ይላል። ዝም ብለው ከተመለከቱት ተራ የመጠበቅ ጉዳይ እንጂ ከእያንዳንዱ ሰፈር ደርሶ በሩን ማንኳኳቱ አይቀርም። ስለዚህ የጎረቤትህ፣ የሰፈርህ፣ የከተማህ፣ ብሎም የሀገርህ ሰላም መሆን ለአንተ ሕይወት ዋስትናን የሚሰጥ ነው። ‹‹ሰላም ሳይለኝ ያለፈው ‹የእንትን› ብሔር ስለሆንኩ ነው›› እያለ የተዛነፈ ሒሳብ የሚያሰላ ትውልድ በበዛበት ወቅት የእለት ተግባርን በደስታ፤ በፍቅርና በሰላም መጀመርን የሚያህል ደስታ በዋዛ እንዴት ይገኛል። አዎ፤ የመልካም አስተዳደር ችግር የገጠመው ሰው ውሎው ስኬታማ፣ ለሌሎች ቅን አሳቢ፣ ሰው አማኝ ሊሆን ይቸገራል። እውነት ነው። በተውሶ ጭንቅላት እየታሰበ እንዴት ሰላምና አንድነት ሊገኝ ይችላል። ‹‹ያልበላንን እያከክንስ›› እስከ መቼ እንኑር ጎበዝ። ሆዱ እንጀራ፣ እንጀራ፣ ዳቦ ዳቦ ሲል ለሚያድር ሕዝብ ‹የእንብላ ፣ የእንጠጣ ፓርቲ› እንጂ\nየፖለቲካ ፓርቲ ሲፈለፈል ማደሩ ለራበው ሰው ምን ይፈይድለታል። ቁራሽ ሆኖ ሆዱ የከፈተበትን ጦርነት አይመክት። ተስፋ የጣለበትን ለውጥ በጥርጣሬ እንዲያይ በማድረግ አስተሳሰቡን ለመስረቅ ያለመ ይመስላል። የሌብነት ዘርፎችን ብዛት አያችሁት? ጉድ እኮ ነው። መቶ አስር ሚሊዮን ደረስን ብንለው መቶ ስምንት ሆኖ ለቅርምት መጣ ብሎ መተረቱ ይቀላል። የሸገሮች የሰላም ነፋስ ደግሞ ከአራቱም  የሀገሪቱ ጠርዞች የሚነፍስ ነው። በዚህ የተነሳ አዲስ አበቤው ለቁዘማ ተጋላጭነቱ የሰፋ ሆኗል ይባላል። ሌላው ሁሉ ቢቀር ገንዘቡን ተሰርቆ ሲቆዝም ይውላል ይላሉ ውስጥ አዋቂዎች። እንደው ከተነሳ አይቀር በ‹‹ሰርቆ አደሮችም›› ዘንድ ሪፎርም ተሰርቷል መባሉን ሰምታችኋል? ነገረ ሥራቸው ተቀይሯል ይባላል። እንደ ድሮው ፈራተባ እያሉ ኪስ መዳበስ፣ ስልክ መመንተፍ ቀርቷል። ቦታና አሳቻ ሰዓት መርጦ በደፈጣ የአካል ጥቃት ሰንዝሮ የንብረት ዝርፊያ መፈጸም ለጊዜው ተጠናክሮ ቀጥሏል። ጥሩ ብር መያዙ በተጨባጭ ከተረጋገጠ የሰዓት ገደቡ ግድ አይሰጣቸውም። አሁን ላይ የትኛውም አካባቢ የክልል ከተሞችን ጨምሮ ስርቆት ወደ ዝርፊያ መልኩን ቀይሮ፣ ደረጃውን አሳድጎ ይከወናል። ፅድት ያለ የመደበኛ ሥራ አካል ተደርጎ መቆጠር ጀምሯል። ‹‹እኔኮ ጥሩ ነገር ካልሆነ አልነካካም። ለሥራ ሳውዲ ዓረቢያ አለያም ዱባይ ደርሼ እመጣለሁ›› የሚሉ ዝነኛና ኩሩ ሌቦች መበራከታቸው ይነገራል። የዚህ አይነቶቹ የተለወጡ ሞዴል ሌቦች ወይስ ሞዴል ሥራ ፈጣሪዎች ምን ይባሉ ይሆን? መልሱን ለእናንተ ትቸዋለሁ። ለማንኛውም በእነሱ አጠራር ‹‹ ብቁ ሿሿ›› ይሰኛሉ። ‹‹አዲስ አበባን ማታ ከ1፡00 ጀምሮ ፈረቃው የተቀየረ እስኪመስል ድረስ ከጫፍ ጫፍ ሌቦች ያጥለቀልቋታል›› ሲል ጓደኛችን የታዘበውን አጫውቶኛል። ‹‹በተናጠላዊ ፍተሻ ሳይሆን በተደራጀ አሰሳ የኢኮኖሚያዊ ፍላጎታችንን እናሳካለን›› በሚል መሪ ቃል ንቅናቄውን የሚመራ ይመስላል። በአንበሳ አውቶብስ ተሸከርካሪ ተሳፍረናል። እንደው በስም ብቻ በሩቁ ለምታውቁት በግብሩም አንበሳ አውቶብስ ድንቅ ነው። በነጻነት የማሰብና የመናገር መብት ተከብሯል። የብሔር ፖለቲካ ከባለቤቶቹ በላይ ይፈተፈታል። ምን የማይነሳ አጀንዳ አለ ሁሉም በሽበሽ ነው። ምንጭ ግን ከአንድ ወሬ በላይ አንድን ሰው መጠየቅ አይቻልም። ደጋግመው የወሬ ምንጭ የመጠየቅ አመል ካለብዎ ያስወግዱ፤ ያጣላዎታል። ምክንያቱም በዚህ ወቅት የሀገራችን ወሬዎች የሚጨለፉት ከአንድ ኩሬ ነው ከፌስቡክ። ከአጠገቤ የተቀመጡ አንድ እናት ሲያማርሩ ሰምቼ ቀልቤን ሳቡት። ‹‹ምነው ምን ገጠመዎት እናቴ›› ብዬ\nጠየቅኳቸው። እሳቸውም ‹‹መላዕክቱ መሪያችን እናት እናት ይላሉ። ከታች ያሉት ባለስልጣኖቻቸው ግን ከአይጥ እኩል ቆጥረውናል። እየውልህ ልጄ በዘመመች የቀበሌ ቤት ውስጥ ነው የምኖረው እናም የአይጥ መንጋ ማረፊያ አሳጣኝ። ፍቀዱልኝና በሸራም ቢሆን በአቅሜ ልሸብባት። በቁሜ አይጥ ቀርጥፎኝ፤ የሰው መሳለቂያ መሆኔ ነው ብዬ ብጠይቃቸው ‹አይቻልም፤ አይቻልም፤ ካልሆነዎት ያስረክቡን። ሜዳ ላይ የወደቁት ምን ይበሉ› ብለው አንጓጠው አባረሩኝ። ‹ከላይ አልጋ ከታች ቀጋ› የሆነ\nነገር ገጥሞኛል›› አሉኝ። በሞቴ ጆሯችሁን አውሱኝ ልንገራችሁ፤ እኔ በበኩሌ የአንበሳን ያህል አዛኝ፤ ለአዲስ አበቤ አላየሁም። በአራት ሽልንግ ስንት ሀገርና ወሰን አቋርጦ እንደሚሸኝ የሚያውቀው ያውቀዋል። የዚችን ምስኪን ከተማና ሀገር ቀዳዳዎች ሊሞላ ወፍ ሳይንጫጫ ጀምሮ ይባዝናል፤ ምን ይሄ ብቻ ከባዱ የኑሮ ሸክም አልቃና ብሎ በትከሻቸው ጋልቦ ላጎበጣቸው፣ ከከተማዋ ጫፍ እስከ ጫፍ ቢማስኑም ኪሳቸው አልጠረቃ ላላቸው ለፍቶ አደሮች፣ በእድሜም ሆነ በእክል አቅምና ጉልበት ሊከዳ ለሚዳዳቸው ሁሉ እናት የሆነ ሸካፊ ነው፤ አንበሳ አውቶብስ። ታማኝም ነው። እንደው በዘመኑ ወረርሽኝ ተለክፈን አዕምሯችንም፣ አይናችንም በጎ በጎውን አላስብና አላይ ብሎናል። አንድ ቀን አንበሳ ሳይጭነው ያለፈ ተሳፋሪ የእከሌ ብሔር በመሆኔ ነው ማለቱ የማይቀር ይመስለኛል። ኧረ እንደው እንቅፋት የመታውም ‹‹እንትን በመሆኔ ነው›› ሳይል\nአይቀር። ወገኖቼ ገንዘባችን ብቻ ሳይሆን አስተሳሰባችንም እኮ ለስርቆት ተዳርጓል። እያንዳንዱ ሰው ወደ ተንታኝነት መቀየሩን ሰምታችኋል? ያውም እኮ ፖለቲካ ነው የሚተረትረው። እያንዳንዷ ከአንደበታችን ጠብ የምትል ቃል ፖለቲካዊ ትርጉሟን እንጂ የተተነፈሰችበትን አውድ ማን ከቁብ ይቆጥረዋል። አረማመዳችንም ቢሆን በጥንቃቄ ሒሳብ ተሰልቶ እግራችንን ልናንቀሳቅስና አካባቢያችንን ቃኘት ቃኘት አድርገን አዋሳኙ ሰው አልባ በሆነ ባዶ መሬት ላይ ልናሳርፍ ይገባል። አለበለዚያ በወቅቱ የፖለቲካ ተንታኞች እይታ ውስጥ መውደቃችን የማይቀር ነው። ፍዳም ያስከፍላል ፤ደግሞ ይሄ ምኑ የፖለቲከኛ ተንታኝ አይን ያርፈበታል እንዳትሉኝ። ምክንያቱም እግር አነሳሳችን በቀኝ ከነበረና መሬቱ ላይ ስናሳርፍ ኮቴ ቢጤ ለጆሮ ከበቃ ‹‹አይዞህ፤ እኔን መታህ፤ ጎዳህ›› የምትባል አይምሰልህ። ይልቁንስ አሃ ብሔሬ እንዲህ መሆኑን አውቆ ነው። ዘሬ፣‹‹ብሔሬ…ወዘተ እንትን በመሆኔ እኮ ጠልቶኝ ነው። እንዲህ አድርጎ መርገጥ ነበር ማለቱ እኮ ነው። ንቀውናል እኮ!›› በእነዚህ ላይ እማ ዋጋ ከፍለን ትግል በማድረግ ማሳየት አለብን…ወዘተ። በማለት በፌስቡክ የፖለቲካ ምሩቃን ለትንታኔ እንደሚበቃ ሹክ ልበላችሁ። ኧረ ነገሩስ ከሹክሹክታም በላይ ሆኗል፤ ጸሐይ የሞቀው ሀቅ ከሆነ ዋል አደር ብሏል። ረዘም ላለ ጊዜ በመካከላችን የእሾህ ችግኞች ሲተክሉ የኖሩ እኩዮች እንደነበሩ አይካድም።አሁንም ቢሆን የህዝብን ተከባብሮና ተዋድዶ የመኖር እሴት ጠላሸት በመቀባት ትርፍ የሚያፈነፍኑ መኖራቸው ይነገራል። በዚህ የተነሳ በመካከላችን አስተሳስሮን ለዘመናት የቆየውን አስተሳሰብ በከፋ ደረጃም ባይሆን ሰርቀውናል። ገንዘብህ የተሰረቀ እለት መሳፈሪያ ሊቸግርህ ይችላል። ለድህነት፣ ለረሃብና ለጠኔ ሊዳርግህ ግን ፈጽሞ አይችልም። አስተሳሰብህ ለስርቆት የተዳረግክ ዕለት ግን ተስፋህ ጠላሸት ይቀባል፤ ማንነትህ ይበረዛል፤ ካሳደጉህ ሰዎችና ጎረቤቶችህ በእንትንነትህ ወይም በእንትንነታቸው ትራራቃለህ፤ ትለያያለህ። መለያየትን የሚወልድ ሊጨነግፍና ሊመክን የሚገባው ክፉ በሽታ የወረርሽኝ ያህል መዛመቱን የሚናገሩ በርካቶች ናቸው። ይህ ታዲያ የክፋት ጥግ አይሆንም ትላላችሁ? ሕዝቡ ገንዘቡን ከሚሰርቁት ዘራፊዎች ባልተናነሰ አስተሳሰቡን እያምታቱ በመስረቅ ላይ የተሰማሩትን መከላከል ይኖርበታል ባይ ነኝ። ሰው ሆኖ በተፈጠረበት ብቻ መዋደድና በአንድ ኢትዮጵያዊነት ጥላ ሥር መሰባሰብ ይገባል። ለዚህ ደግሞ ዶክተሩ የተለሙት ትልም ሁነኛ መፍትሔ እንደሆነ በርካታ ዜጎች መስክረውለታል። ‹‹የአንድ\nዓመት ግብራቸው ሺ ዓመት በእጃቸው የዳበሱ ያህል ፈውስ አምጥቷል›› ያሉት የእኛ ዜጎች ብቻ አይምሰሏችሁ በየዓለማቱ ጫፍ ሰው መሆን ያስተሳሰራቸው ፍጡራን ጭምር እንጂ። ለዓለም የሚበቃ አስተሳሰብ ባለቤቶች የሆንን ትልቅ ሕዝቦች በአንዳንድ ፖለቲከኞች የሻገተ አስተሳሰብ ሰብዓዊ ባህርያችንን ለቀን እና አስተሳሰባችንን ተሰርቀን ከሰው ተራ አንሰን ልንገኝ ፈጽሞ አይገባም እንላለን። ቸር እንሰንብት።አዲስ ዘመን መጋቢት 26/2011 ", "passage_id": "4a4ef8a28c91b51f1c9e3a05c2a0fbd1" }, { "passage": " እውነተኛ ታሪክ ነው የምነግራችሁ። እግር ጥሎኝ ሳይሆን እግሬ እስኪነቃ ተመላልሼ ያየሁትን። በተመላለስኩበት የህዝብ “ አገልጋይ “ መሥሪያ ቤት የገጠመኝ “እውነትም የህዝብ አገልጋይ” እንድል አነሳስቶኛል። ወሬዬን ልጀምር ። ሰብሰብ ብለን የተቀመጥነው አንደኛ ፎቅ ላይ የሚገኙትን ሥራ አስኪያጅ ለማግኘት ነው። ከእርሳቸው የሥራ ሰዓት መግቢያ ቀደም ብለን በቦታው ተሰይመናል። ቀደም ብለን የመጣነው ባለጉዳዮች በኮሪደሩ ላይ ተጣብቀው በተቀመጡት የእንግዳ ማረፊያ ወንበሮች ላይ ቁጭ ብለናል። እኔም አንዷ ነኝ። በተደጋገሚ መመላለስ እና ሃላፊው እስኪመጡ ቆሞ መጠበቁ ስለሰለቸኝ በጠዋት ተገኝቼ ያችን የማትሰለች፣ የማትደክም፣ እንደሌላው ባለጉዳይ ኡ…ኡ… የማትል ወንበር ላይ ተቀምጠናል። ይሄ መብራት ሃይል ገርጂ ቅርንጫፍ ተብሎ በሚታወቀው ተቋም ውስጥ ነው። እዛ ታዲያ ያለውን ብሶት ለሰማ፣ በየቀኑ\nየሚመላለሰውን ባለጉዳይ ለታዘበ አይ ሀገር ! አይ አገላጋይ የመንግሥት ሠራተኛ ! አይ አመራር! አይ ለውጥ!… ብሎ አፉን በነጠላው\nይዞ ለማሽማጠጥ ያስነሳል። ግን ምን ዋጋ አለው። በየቀኑ ብሶት በየቀኑ ኡ.. ኡታ መስማት። አንቺስ ካላችሁ እኔማ ሦስት ወር በተደረገ\nያላሰለሰ መመላለስ ሌላም ተጨማምሮበት በሦስት ወሩ ተሳካልኝ። ተሳካላኝ ስላችሁ ታዲያ ቀላል እንዳታደርጉት። ጠዋት ስባል ጠዋት፣\nከሰዓት ስባል በተባለው ሰዓት ከች ብዬ ፤ ሲስተም የለም፣ ባለሙያ አልገባም… የሚሉ ምክንያታችን ሁሉ አልፌ ነው። ሌላው በተለይ\nአቅመ ደካማው ፣ ከአለቃው በስንት መከራ ፈቃድ እየጠየቀ የመጣው ሁሉ ያለ ውጤት ተንገዋሎ ይመለሳል። እግዜር ብሎ ከሃላፊው ከተገናኘ\nደግሞ ባለሙያ አለ መኪና ስለሌለ ነው። ወይ ደግሞ እኛ ምን እናድርግ ወደ በላይ ሂዱና አቤት በሉ የሚል መልስ ያገኛል። ከመብራት\nሃይል አገልግሎት ማግኘት እንዲህ ቀላል አይምሰላችሁ። የአገልግሎት መስጫ ተቋማት ህዝብን ማስለቀስ፣ ማበሳጨት፣ ማሰቃየት ብርቅ\nነው እንዴ። አንቺ የትነበርሽ? የምትሉ ካላችሁ የአሁኑ ባሰ ብዬ እንጂ ቀድሞም ተገልጋይ ነኝ። አውቀዋለሁ በተለይ በመብራት ሃይል\nመስሪያ ቤት በኩል የሚማረር እንጂ የሚደሰት አልሰማሁም። የሰማሁት ሁሉ እውነት ይመስለኛል። ማለቴ ሁሉንም ነገር እውነት ነው ብዬ ባልልም አንዳንድ ነገሮችን\nእውነት ናቸው ብዬ እቀበላለሁ። በተለይ በከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ሲነገሩ እውነት እውነት ይሸቱኝና አምናለሁ። አሁን አሁን\nሳስበው ግን እውነቱ ያለው እውነት ነው ብሎ በተናገረው ሰው አንደበት ላይ ብቻ ነው ። በተግባር ግን ያው እንደተለመደው። ኧረ\nእንዳውም ባስ ባለ መልኩ ህዝብ እየተማረረ ነው። አገልግሎት ለማግኘት የተገለገለበትን ሂሳብ ለመክፈል፣ ለብልሽት ወይም ለሌላ ጉዳይ\nየመጣው ሁሉ ያዝናል! ወዴት ሄደን አቤት እንበል ሲልም ይደመጣል። በዛ ሰሞን አንድ የኢትዮጵያ ቴሌቪዝን ጋዜጠኛ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ\nሃይል የሥራ ሃላፊን ሲያነጋግር ችግሮች እያለ ያነሳቸውን ሀሳብ ከነመረጃው እያቀረበ ሲያፋጥጥ ሳይ ምን አለ ሁሉም የሥራ ሃላፊና\nባለሙያ በዚህ መልኩ የሚያጋልጠው በመጣ ስል የየዋሆች ሀሳብ አሰብኩ። ግን እንደማይሆነ አውቃለሁ። ቢሆንም ይሄ የሀገሪቱ ችግር\nነው። ይሄ ከእኛ በላይ ነው። ዕቃ የለም። ዶላር ስሌለ ነው … የሚባሉ ምላሾች እንደሚበዙም እገምታለሁ ። አንድ በእድሜ የገፉ አዛውንት እናት ከወደ ገርጂ አካባቢ የሚመላለሱ መሆኑን ነግረውኛል። ይሄ ጭውውት\nእዛው በተገናኘንበት የመብራት ሃይል ግቢ ውስጥ ነው። አንድ አይነት ክንፍ ያላቸው ወፎች አብረው ይበራሉ ይባል የለ። እኛም የጋራ\nየሚያደርገን እንግልት አለና በየጊዜው በመገናኘት ተግባብተን የአንቺ የአንተ ችግር ምንድነው ? ምን ያህል ጊዜ ሆናችሁ ? እያልን\nመነጋገሩ መፍትሄ ባይሆንም የውስጥን እንፋሎት ያወጣልና እንወያያለን። እሳቸው ታዲያ እንደነገሩኝ ቆጣሪያቸውን አሁን ካለበት ተነስቶ ወደሌላ ቦታ እንዲዛወርላቸው ነው የጠየቁት።\nይህንን ጥያቄ ባቀረቡበት ወቅት የማስነሻ ክፈይ ተብለው ከፍለዋል። ከአስራ አምስት ቀን በኋላ ይነሳል የሚልም ምላሽ ተሰጥቷቸዋል።\nሆኖም ምላሹ የውሃ ሽታ ቢሆንባቸው በየጊዜው እየተመላለሱ ኧረ አልተሠራልኝም፤ ዝናብ ከዘነበ ቆጣሪው ከተንጠለጠለበት የጭቃ ግድግዳ\nላይ ስለሚወድቅ አደጋ እንዳይደርስብኝ እባካችሁ አንሱልኝ ይላሉ። ታዲያ አንድ ቀን ሃላፊው ባለሙያ ጠርቶ እስኪ የሚቀየርበትን ቦታ\nምንም ምን እንደሚያስፈልገው ተመልከት ብሎ ያዘዋል። ባለሙያውም የራሱ ስልጣን አለ አይደል “መኪና የለም” ሲል ይመልሳል። ይሄን\nጊዜ ሃላፊው ይሄ ፖል የሚጭን መኪና የማያስፈልገው ሥራ ስለሆነ እንዲህ አይነቱን ባለጉዳዩ መኪና እያቀረበ ሥሩ ሲል ያዛል። እርሳቸው\nይሄ ከአንደበቱ ከወጣ ብለው ኮንትራት ላዳ ታክሲ በማቅረብ ባለሙያውን ይዘው ይሄዳሉ። ባለሙያውም እቤት ድረስ ሄዶ ይመለከትና\n“ እማማ ይሄ ቀላል ነው ስምንት መቶ ብር ከከፈሉኝ አሁኑኑ ላንሳሎት” አለኝ። እኔ ደግሞ እንዴ ለመንግሥት ከፍያለሁ ሌላም የለኝ\nአልኩት። እሱም ሳይሰራው ተመለሰ። አሁን ሳስበው መንግሥት መጥቶ ይስራሎት ያለኝ ይመስላል። ይሄው ሁለት ወር ሞላኝ ማን አባ ከና\nይበለኝ። እነሱም ያንገላቱኝ እኔም አልሰለች ብዬ እመላለሳለሁ። አቤት የሚባልበት የለ፤ ተቆጪ የለ ሁሉም አንድ ናቸው ። ሃላፊውም\nየእነሱ አይነት ሳይሆን አልቀረም ባለጉዳይን ከምንም አይቆጥርም። ሰውም አይከብደውም። ብቻ ከወዲያ ወዲህ እያመላለሱኝ ይሄው አለሁ።\nእያሉ የሆዳቸውን ሁሉ ዘረገፉ። ሌላዋ ቀጠለች።\nምን ሁላችን እያየን አይደል ስትል። የአገልግሎት ክፍያ ለመክፈል እንኳን የሚመጡ ባለሆቴል የመሳሰሉት ንግድ ቤቶች ክፍያቸው የሚከፈለው\nበውስጥ ሠራተኞች አማካይነት ነው። ሁሉ ነገር በሙስና ስትል አከለች። አሁን አጠገባችን ለአንዱ የቴክኒክ ባለሙያ በስሙ ጠርቶ ሁለት\nየታሰረ ባለ መቶ ብሮች ሰጥቶ ክፈልና ቀሪው የቁርስ ነው ሲለው በጆሮዬ ሰምቻለሁ፤ በአይኔ አይቻለሁ እያለች የታዘበችውን አከለች።\nሁላችንም ብሶታችንን ብናወጣው ነገር በአህያ አይጫንም እንደሚባለው ይሆንብናልና እንዳው ብቻ ኧረ የተሰጣችሁን ሃላፊነት በአግባቡ\nህዝብን አገልግሉበት ልንል ወደድን።አዲስ ዘመን የካቲት 8/2012 በጋዜጣው ሪፖርተር", "passage_id": "aa4e5b643bf9e5e58081f9ae30812f7f" } ]
f20aa2d6c617f7a664b21ada6e20eda9
443881c7490d28b55c3ddaa3c4b1d122
እንዲህ ቢባል ምን ችግር አለው?
በአውሮፓውቷ አገር ኖርዌይ ለትምህርት ከአንድ ዓመት በላይ ቆይቶ የመጣ አንድ ጓደኛዬ የነገረኝ ነገር ትዝ አለኝ፡፡ በነገራችን ላይ ውጭ አገር ቆይቶ የመጣ ሰው ሳገኝ ቀድሜ የምጠይቀው የህዝቡን ሥነ ልቦና ነው፡፡ እንዲያው ይሄ ርዕስ በርዕስ መነቋቆር የሰለጠኑት አገሮችም አለ ይሆን የሚለውን ለማወቅ ስለምፈልግ፡፡ እናም ይሄ ጓደኛዬ የነገረኝ ነገር በሀገረ ኖርዌይ ያስተዋለው ህዝቡ ሐሜትና መነቋቆር ጉዳዩ እንዳልሆነ ነው፡፡ አለ ከተባለም አድናቆት ነው፡፡ ከከንቲባው ጀምሮ በከተማዋ ውስጥ ያለ የትኛውም ባለሥልጣን ሲሰደብና ሲወቀስ አይወዱም፡፡ ለባለሥልጣኖቻቸው ትልቅ ክብር አላቸው፡፡ ይሄን ነገር በእኛ አገር ቢሆን ብየ አሰብኩት፡፡ አንድ ከሌላ አገር የመጣ ዜጋ ባለሥልጣኖቻችንን ሲያብጠለጥል ብንሰማው በደስታ የሚፍለቀለቀው አይበልጥም? እሰየው አብጠለጠለልን አንልም ነበር? መወቀስ ያለባቸው ቦታ ላይ መወቀስ የለባቸውም እያልኩ አይደለም፡፡ ችግሩ ግን ወቀሳችንም አድናቆታችንም ምክንያታዊ አይደለም፡፡ ሌላውን ሰው የሚያናድድ እየመሰለን ነው፡፡ከሰሞኑ ማህበራዊ ገጽ ላይ ከዳግማዊ አፄ ምኒልክ እስከ ዶክተር አብይ አህመድ ያሉ የአገሪቱን መሪዎች የሚያመሰግን አንድ ፎቶ አየሁ፡፡ ከእያንዳንዱ መሪ ፎቶ ሥር የሚያስመሰግናቸው ሥራ ተጽፏል፡፡ የፎቶው አቀማመጥ በሥልጣን ዘመናቸው ቅደም ተከተል ነው፡፡ በነገራችን ላይ ይሄ ነገር ብርቅ የሆነው ካለው ወቅታዊ ብሽሽቅ አንፃር እንጂ ብርቅ መሆን የነበረበት ሆኖ አይደለም፡፡ ግን ጠዋት ማታ የምናየው አንዱ ሌላውን ሲያጣጥል ነው፡፡ የሚያደንቅም የሚወቅሱትን ለማናደድ ነው፡፡ አንዱን መሪ ለማድነቅ ሌላውን ማጣጣልና መሳደብ ግዴታ መስሏል፡፡ ግን እንዲህ ሁሉንም በሥራቸው ማመስገንም ይቻል ነበር፡፡ ጥፋት ብቻ እናውራ ከተባለ በእያንዳንዱ መሪ ዘመን የተፈፀመ ብዙ ጥፋት አለ፡፡ ግን ምነው የሠሩትን ጥሩ ሥራስ ብናወራላቸው?እዚህ ፎቶ ላይ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድን ‹‹ጠፈርን የደፈረ›› ይላል፡፡ በቅርቡ ኢትዮጵያ ሳተላይት አምጥቃለች፡፡ ሳተላይት ማለት የአንዲት አገር የብልጽና እና የሥልጣኔ ማሳያ ነው፡፡ የመዘመን ምልክት ነው። ኢትዮጵያ ደግሞ በኋላቀርነትና በድህነት ስሟ ሲጠራ የቆች አገር ናት፡፡ ስለዚህ የዚች አገር ስም በእንዲህ አይነት ነገር ሲጠራ ጀግንነት ነው፡፡በአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ፎቶ ሥር ‹‹ሥልጣኑን በሰላም የለቀቀ›› ይላል፡፡ እንደሚታወቀው የአፍሪካ አገራት ስማቸው ተደጋግሞ የሚጠራው በምርጫ ማጭበርበርና በ‹‹ሥልጣን አልለቅም!›› ጦርነት ነው፡፡ የአፍሪካ መሪዎች የሚታወቁት የሥልጣን ሽግግር በተደገረ ቁጥር አሻፈረኝ ሲሉና ግጭት ሲቀሰቀስ ነው፡፡ የራሷ የኢትዮጵያ የዘመናት ታሪክም ይሄው ነው፡፡ ሥርዓቶች ሁሉ የተቀያየሩት በጦርነት ነው፡፡ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ግን በራሳቸው ፈቃድ ሥልጣን ለቀቁ። አቶ ኃይለማርያምና ዶክተር አብይ ተቃቅፈው የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ተረካከቡ፡፡ ይሄ አቶ ኃይለማርያምን ጀግና ያሰኛቸዋል፡፡በአቶ መለስ ዜናዊ ፎቶ ሥር ‹‹ዓባይን የደፈረ›› ይላል። ለዘመናት የዘፈንና የፉከራ ምንጭ ሆኖ የኖረው ዓባይ የኃይል ምንጭ ሊሆን የመሰረተ ድንጋይ የተቀመጠለት በአቶ መለስ ዜናዊ ነው፡፡ በርሃብና በድህነት የምትታወቅ አገር ከዓለም ግዙፍ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነውን የህዳሴ ግድብ ጀመረች፡፡ ኢትዮጵያዊ የአገር ፍቅር ታየበት። የማይደፈር የመሰለውን ዓባይ መገደብ ተጀመረ፡፡ ይሄ አቶ መለስ ዜናዊን ጀግንነት የሚያሰኝ ነው፡፡ በኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ፎቶ ሥር ‹‹የሀገርን ዳር ድንበር ያስጠበቀ›› ይላል፡፡ የደርግ ዘመነ መንግሥት ስሙ የሚነሳው በጨቋኝነቱና በጨፍጫፊነቱ ነው፡፡ በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን የኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያምን የሀገር ፍቅር ብዙዎች የመሰከሩት ነው፡፡ የደርግ ሥርዓትን ታግሎ ያሸነፈው ኢህአዴግ መሪ የሆኑት ራሳቸው አቶ መለስ ዜናዊ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያምን ‹‹በሀገሩ ጉዳይ አይደራደርም›› ብለው ነበር፡፡ ደርግ በዘመኑ የነበሩ ወረራዎችን ተቋቁሞ የአገሩን ዳር ድንበር አስጠብቋል፡፡ ይሄም ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያምን ጀግና ያሰኛቸዋል፡፡ በዳግማዊ አፄ ምኒልክ ፎቶ ሥር ‹‹ጣሊያንን የደፈረ›› ይላል፡፡ አንዲት አፍሪካዊት አገር አንዲት አውሮፓዊትን አገር ትደፍራለች ብሎ የማይታሰብበት ዘመን ነበር፡፡ የአውሮፓ ኃያልን ማን አለብኝ ብለው የአፍሪካ አገራትን ልክ እንደ ሸቀጥ መከፋፈል ጀመሩ፡፡ ኢትዮጵያ ላይ ሲደርሱ ግን አልተሳካም። ኃያልን አገራት ያልጠበቁት ሽንፈት አጋጠማቸው፡፡ ነጭ በጥቁር ተሸነፈ፡፡ ታሪክ ተቀየረ፡፡ የአፍሪካ ጥቁር ህዝቦች ‹‹ለካ ነጭን ማሸነፍ ይቻላል›› አሉ፡፡ እነሆ ኢትዮጵያን አይተው የአፍሪካ አገራትም ነፃ ወጡ፡፡ ይሄ ዳግማዊ አፄ ምኒልክን ጀግና ያሰኛል፡፡አንድ ነገር ልብ ይባልልኝ፡፡ የተጠቀሰው ጀግንነታቸው ይሄ ብቻ ሆኖ አይደለም፡፡ በፎቶ ተቀነባብሮ ያየሁትን መነሻ አድርጌ ስለሆነ እንጂ፡፡ ማህበራዊ ገፆች ላይ እንዲህም ማመስገንና ማድነቅ ይቻላል የሚለውን ለማሳየት እንጂ የመሪዎች ሥራ ይሄ ብቻ ሆኖ አይደለም፡፡ በሌላ በኩል ይሄኛው ሥራቸው ነው መቅደም ያለበት የሚል ሐሳብም ሊነሳ ይችላል፡፡ ግን እንዳልኩት ነው፡፡ መነሻዬ ፎቶው ላይ ያየሁት ነው፡፡ ያደረገው አንድ ግለሰብ ሊሆን ይችላል፤ በፓርላማ የፀደቀ ወይም የምሁራን ውይይት የተደረገበት አይደለም፡፡ እንደ ምሳሌ ነው የተነሳ፡፡ ጀግና የሚያሰኙ ሥራዎች አሏቸው ለማለት ነው፡፡ የጀግና ችግር የለብንም፡፡ ያለብን የራስን የሆነ ነገር የማክበር ችግር ነው፡፡ የመሪዎቻችን፣ የሳይንቲስቶቻችን፣ የአርቲስቶቻችን ጀግንነት የሚታየን ፈረንጅ ሲሸልማቸው ነው፡፡ የመሪዎቻችን ነገር ጭፍን የፖለቲካ አስተሳሰብ ስለተጫነው የክርክርና የጭቅጭቅ ምክንያት ሆኗል፡፡ የሚያሳዝነው እኮ ደግሞ የዋናዎቹ የመገናኛ ብዙኃንም አጀንዳ ይሄው መሆኑ ነው፡፡ የሚያሳዝነው እኮ ትልልቅ ሰዎች ራሱ አጀንዳቸው ይሄው መሆኑ ነው፡፡ የማህበራዊ ገፆች ብቻ ቢሆን እኮ ቀላል ነበር፡፡ የተራ ሰዎች ብቻ ቢሆን እኮ ይሻል ነበር። ትልልቅ የሚባሉ ሰዎች ራሱ ንግግር የሚያደርጉት አንዱን ለማመስገን አንዱን በመሳደብ ነው፡፡ አቶ ዕገሌን ለማመስገን የግድ አፄ ዕገሌ መሰደብ አለበት፡፡ አፄ ዕገሌን ለማድነቅ የግድ አቶ ዕገሌ መሰደብ አለበት፡፡ ይሄው ነው የፖለቲከኞቻችንም ሆነ የምሁራኖቻችን ትንታኔ፡፡ እስኪ ማድነቅና ማመስገንንም እንልመድ! አፄ ዕገሌን ሳንሳደብ አቶ ዕገሌን ማድነቅ ወይም አቶ ዕገሌን ሳንሳደብ አፄ ዕገሌን ማድነቅ እንቻል! መልካም በዓል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 26/2012ዋለልኝ አየለ
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=25183
[ { "passage": " 10 መማር ከሚያስገኛቸው ጥቅሞች አንዱ ማመዛዘን መቻል ነው። እውነታውም ቢሆን የተማረ ሰው በቀላሉ የመኖርና ህይወቱን የመምራት ብልሃት ይኖረዋል። ለሕጎች ተገዥ መሆንን ጭምር ያካትታል። ለመንግሥት አስተዳደር በጥቅሉ ለሕጎች ተገዥ ከመሆን በላይ ለመንግሥት ጠቃሚ ሀሳብ በማቅረብ ሀገርን ይረዳል። ነገር ግን በእኛ ሀገር ይህን እየተመለከትን አይደለም። ኮቪድ -19 የዓለም ሥጋት ከሆነ ሰንበትበት ቢልም የኛ ሀገር ሰው ግን ድንግጥም ያለ አይመስልም። የመንግሥትን መመሪያና የህክምና ባለሙያዎችን መልዕክት ባለመስማት ለበሽታው ተጋላጭ በሆኑ ቦታዎች ላይ የሚውለው በአብዛኛው የተማረው የሕብረተሰብ ክፍል ነው ብል ማጋነን አይሆንብኝም። የተማረው ላልተማረው አርአያ ከመሆን ይልቅ ቸልተኝነትን የሚያስተምሩ ይበዛሉ። ሁሉም ሰው ሳይዘናጋ ከኮቪድ -19 ለመከላከል ከሦስት አካላቶች መጠንቀቅ አለበትት። መጀመሪያ እራሳቸውን ከሚያታልላቸው ከራሳቸው ህሊና መጠንቀቅ ከቀሪ ሁለት አዘናጊ አካላት በመጠንቀቅ ሕይወታቸውን መታደግ ይችላሉ። አማኝ ነኝ የሚለው ሰው የእምነት አባቶችን መልዕክት አልሰማም ብሎ በግድ በሽታው ካልያዘኝ ማለት እብደት ነው። ከዚህ በፊት በርካታ ጊዜ ወረርሽኝ ተነስቶ በሚሊየንና በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እንደ ሞቱ መረጃዎች ያስረዳሉ። እና ያኔ ፈጣሪ የለም? አማኝስ? መልሱ አያከራክርም። ነገር ግን ከጥንቃቄ ማነስ የተነሳ ክቡር ህይወታቸውን አጥተዋል ማለት ነው። ህሊናችን በሃይማኖት እያሳበበ ተዘናግተን እንድንሞት እንዳያደርገን እንጠንቀቅ። እንደውም እኮ ጠንካራ እምነት ያለው ሰው በቀላሉ የመሪውንና የባለሙያዎችን ትዕዛዝ መቀበል ነበረበት። ሁሉም የዕምነት ተቋሞች ለመሪዎቻችንና ለታላላቆቻችን መታዘዝ እንዳለብን ያስተምራሉ። ታዲያ አሁን አድርጉ የተባልነውን ዘንግተን ከኮሮና ጋር መፋጠጣችን ትዕዛዝ አለማክበር አይሆንም? በፈጣሪ ከሚያምን ሰው ይህ ይጠበቃል? ነፍሳችንስ ተጠያቂ አናደርጋትም? ህሊናችንን በውሸት እየሸነገልን ነው። አሁን በሀገራችን እየተስተዋለ ያለው በተማረውና ባልተማረው ሰው የአስተሳሰብ ልዩነት መጥፋቱ ነው። እንዴት ሰው በአንድ ህይወቱ ይቀልዳል? ‹‹ሐበሻ ሞት አይፈራም›› ሲባል ትኩረት ሰጥቼው አላውቅም ነበር ነገር ግን ሰሞኑን የምናየው ነገር የዚህን አባባል እውነታነት የሚያረጋግጥ ነው። ግን እንደሚገባኝ ሐበሻ ሞት አይፈራም ሲባል በሀገሩ ጉዳይ፣ በሚስቱና በእናቱ ጉዳይ ነው። ለጠቀስናቸው ሲሉ መሞት የጀግና ሞት ነው። ነገር ግን በጥንቃቄ ጉድለት በወረርሽኝ መሞት ጀግናውን የኢትዮጵያን ህዝብ ክብር የማይመጥን ሞት በመሆን ልንጠነቀቅ ግድ ይላል። ‹‹ደፋርና ጭስ መውጫ አያጣም›› እያልን የራሳችን ህሊና ለኮሮና አሳልፎ እንዳንሰጥ እፈራለሁ። ይህ የሀገራችን ቢሂል ለኮሮና ወረርኝ አይሰራም። እርግጥ ነው አዳዲስ ነገሮችን ለመሞከር ይረዳ ይሆናል። ከዚህ ይልቅ በአሁኑ ወቅት የሚጠቅመን ‹‹ፈሪ ለእናቱ ጀግና ነው›› የሚለውን የፈሪ ማበረታቻ ሥነ ቃላችን ነው። አንዳንድ ሰዎች ቤት ውስጥ መዋል ለወንድ ልጅ አይመጥንም ቢሉም ክፉ ቀንን ተደብቆ ነፍስን ማትረፍ ጀግንነት የሚሆንበት ቀን እሩቅ አይሆንም። እምነት ካለን ሊያታልለን የሚሞክረውን የገዛ ህሊናችንን ባለመስማት ህይወታችንን እናትርፍ። ፈጣሪም እኮ በመጨረሻው ዘመን ፈተናዎች ይበዛሉ ብሏል። ይህ ማለት እኮ ችግሮች ሲከሰቱ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል ማለት ነው። አንዳንድ ሰዎች መጠንቀቅን ፈጣሪ የለም እንደማለት አድርጎ በመቁጠር እየተዘናጉ ነው። ሁሉም ሰው በሁለተኛ ደረጃ እራሱን ከአንዳንድ ፖለቲከኞች መጠበቅ አለበት። የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ብለው የመንግሥትን መመሪያን ካለማክበርም በላይ ኮሮና መንግሥት በሚለው ልክ አስጊ አይደለም እያሉ ህዝብ እንዳይጠነቀቅ የሚያደርጉ ብዙዎች ናቸው። እንደ መንግሥት መግለጫ ቢሆንማ ኑሮ እስካሁን የኢትዮጵያ ህዝብ ያልቅ ነበር ሲሉ ይደመጣሉ። መንግሥት ምርጫ እንዳይካሄድ እየተጠቀመበት ነው በማለት ይመርጠናል የሚሉትን ህዝብ እየተሳለቁበት ነው። ህይወቱን እንዲነጠቅ ጉልበትና ድፍረት እያደሉት ይገኛሉ። መንግሥት ደጋፊዎቼን አሰረብኝ፤ እንዳይሰበሰቡ እያደረገብኝ ነው ብሎ ኮሮናን መወንጀል ቀላል ስላልሆነ መጠንቀቁ ይበጃል ባይ ነኝ። ፖለቲከኞች ስልጣን ለመያዝ ህዝብ እንደሚያስፈልግ የተገነዘቡት አይመስልም። ሀገርን መምራት ማለት ምድሩን አይደለም የሰውን ልጅ ነው። ስለዚህ የሰው ልጅ በበሽታ እንዳያልቅ ቀድሞ ማሰብ የብልሆች መንገድ መሆን አለበት ብዬ አስባለሁ። ተሳስቼ ከሆነ ግን ሞግቱኝ ካጠፋሁ እማራለሁ። አሁን ጊዜው ተማሩ እንማር የሚባልበት እንጂ ዘራፍ የሚዘፈንበት አይደለም። ሕይወቱን የሚወድ ሰው በሦስተኛ ደረጃ የሀሰተኛ ነቢያቶችን የማዘናጊያ መልዕክት መስማት ዋጋ እንደሚያስከፍለው ማወቅ አለበት። ሀሳቡን ከመፅሔት ላይ ያገኘሁት ሲሆን እንዲህ ይላል፤ ‹‹ከነገ ጀምሮ ኮሮና የሚባል በሽታ ከምድር ላይ እንዲጠፋ አዘዝኩ›› እያለ የሚጮህ ሀሰተኛ ነቢያት ሞልተዋል። ዙሪያውን የከበበው ህዝብ እሱን ተከትሎ ‹‹አሜን›› እያለ ይጮሀል። ከገረመኝ ነገር ግን በዚህ ጭንቅ ወቅት እንኳን ‹‹ነብዮች›› በቴሌቪዥን ቻናል የዘነጠ ፎቷቸውን አስቀድመው ‹‹ኮሮና ከኢትዮጵያ መቼ እንደሚጠፋ ፈጣሪ የነገራቸውን ነቢይ ነገ ለህዝብ ስለሚያስተላልፉ ይጠብቁ›› የሚል ማስታወቂያ ማስነገራቸውን አለማቆማቸው ነው። በቤቱ ተቀምጦ እልልታውን እያስተጋባ ከጥንቃቄ የሚርቅ በርካታ ምዕመናን እንደሚኖሩ አልጠራጠርም። እንዲህ ብሎ ህዝብ እንዳይጠነቀቅ ማድረግ በፈጣሪ ያስጠይቃል። ህዝቡም ራሱን ከነዚህ አዘናጊዎች መጠበቅ አለበት። እኔን የሚገርመኝ መጪውን መከራ መተንበይ ቀርቶ መገመት ያልቻለ ‹‹ነቢይ›› በመከራው ሰዓት እጁን ለፈውስ በድፍረት ዘርግቶ መቆሙ ነው። በዚህ የከፋ ዘመን እንዲህ እያወጁ ይሄ የዋህ ህዝብ ራሱን እንዳይጠብቅ ማዘናጋት ምን ይሉታል? ፈጣሪስ ይወደዋል? ህዝቡ በወረርሽኝ ላለመያዝ የሚያደርጉትን እንቅስቃቄ ከፈጣሪው ጋር እየተጣላ እንዲመስለው የሚያደርጉ ሀሰተኛ ነቢያቶች ለመዋሸትም ህዝብ እንደሚያስፈልግ አስበው ከማደናገርና ከማዘናጋት ሊቆጠቡ ይገባል። መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹በመከራ ወቅት ብትላላ ኃይልህ ትንሽ ስለሆነ ነው።›› የሚል ቃል አለ። ህሊና ላለው ሰው ይህ ቃል በቀላሉ በመከራ ጊዜ ጥንቃቄ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ይጠቁማል። ሳይጠነቀቁ ቀርቶ መሞት ምን የሚሉት ሞት ነው? ይሄ ለኔ የእምነት ሳይሆን በተለይ ደግሞ ክብርን ለሚወደው የሀገሬ ህዝብ የውርደት ሞት ነው። አዲስ ዘመን ሚያዝያ 4/2012 ሞገስ ፀጋዬ", "passage_id": "4070f2792c8a5a915a5cb59f93ebdef3" }, { "passage": "ኢትዮጵያውያን በምን እንታወቃለን የተባለ እንደሆነ ከዓለም እንደቀደመ በምናምነው ስልጣኔ ብቻ አይደለም፡፡ የእኛ በሆኑ ሰዋዊ ሀብቶችም ጭምር ነው፡፡ ለምሳሌ ትህትና፣ ለሰብአዊ ፍጡር የሚሰጥ አክብሮት፣ በማንነት ኩራትና ክብር እንዲሁም ታዛዥነት የኢትዮጵያዊ መገለጫዎች ሆነው ይጠቀሳሉ፡፡ አሁንስ? አሁንማ ሁሉም ነገር ውድ በሆነበት ጊዜ ይኸው እነዚህም ውድ ሆነውብናል፡፡ነገሩን እንደልብ አንጠልጣይ ፊልም ግነት አበዛሁበት መሰለኝ፡፡ እሺ ሳላጋንን፤ «ታዛዥነት ወዴት ገባች?» የሚል መጽሐፍ ይዘጋጅ ይሆን? በጣም ውድ ከሆኑና እየጠፉብን ካሉ ሀብቶቻችን መካከል መታዘዝ አንዱ ይመስለኛል። በአገራችን ያለውን ሁኔታ እያንዳንዱን ስናይ መነሻውም አለመታዘዝ ነው፡፡ አንዱ ጅብ ሌላው ውሻ ሆኖ፤ መንገዱን ባለመታዘዝ እየቀደዱ መሄድ ብቻ፡፡ይሄ ሁሉ ለአገሩ የማይታዘዝ ሰው ግን ቤቱ ገብቶ ልጆቹ እንዲታዘዙት ይፈልጋል? ሰሞኑን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስብሰባ ስም የሚወጣው ወጪ አስደንጋጭ እየሆነ መምጣቱንና እንዳላቆመ ተዘግቦ ነበር፡፡ እነዚህ ሰዎች ስብሰባ ቀንሱ፤ ደንበኛ እናንተን ብሎ መጥቶ በስብሰባ ሰበብ እንዳያጣችሁ፤ ከተሰበሰባችሁም በእረፍት ቀን አድርጉት ሲባሉ፤ ለካ «በአንድ አፍ!» ብለዋል፡፡ከዛ ቅዳሜና እሁድ «ዊኬንድ»ን ከአዲስ አበባ ወጣ ብለው፤ አዳማ ላይ መሰብሰብ፡፡ «ለምን?» አጋጣሚውን ለመጠቀምና አገር ለመጎብኘት፤ የአገር ውስጥ ቱሪዝምን ከፍ ለማድረግ ማለት ነው። የሆነው ሆኖ እንደተቋምም አለመታዘዝ እንዳለ ተገልጾልኛል፡፡ ነገሬ ለምን ከከተማ ተወጣ ሳይሆን፤ በዚህ አካሄድ የአንድ ለአምስት ሳምንታዊ ግምገማ የሚባለው የስብሰባ ዓይነትም ከከተማ ወጣ ተብሎ ይከናወን በሚል ሰበብ፤ ጉዞው እለታዊ እንዳይሆን በመስጋት ነው፡፡ጥሩ! መዋዕለ ነዋይን ከከተማ ወጣ ብሎ ማፍሰስ ተገቢ ነው፡፡ እንግዲህ ወይ ለብቻው በጀት መመደብ ነዋ! አስታውሳለሁ ከዓመት ወይም ከሁለት ዓመት በፊት የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች አንዳንድ አላስፈላጊ ወጪዎችን እንዲቀንሱ ተብሎ የኮፍያ፣ ካላንደር ወዘተ የመሳሰሉ የህትመት ወጪዎች እንዲሁም ድግሶች እንዲቀሩ ተብሎ ነበር፡፡ ይህን ባዩ ደግሞ ገንዘብና ኢኮኖሚውን የሚከታተለው ሚኒስቴር ነው፡፡\nተቋማቱ ለዚህ ትዕዛዝ ታዛዥ ነበሩ ወይ? አልነበሩም፡፡ በእርግጥ በጣም ቆጣቢ ይሁኑና፤ እንደእኛ መሥሪያ ቤት በአሥራ ዘጠኝ ሰማንያዎቹ መጨረሻ የተቋማቸውን ዓርማ ይዞ በታተመ ማስታወሻ ደብተር ይጠቀሙ እያልኩኝ አይደለም፡፡ ግን ቢያንስ በጥቂቱ መታዘዝ ጥሩ ነበር፡፡ጭራሽ ስብሰባ ቀንሱ ሲባል ወጪ መጨመር? ጉድ!\nበብዙ እንቅስቃሴዬ መገናኛ የሚሉትንና አንድ ወዳጄ ‹‹መጠፋፊያ እንጂ መገናኛ ሊሆን አይችልም!›› የሚለውን ሰፈር ሳልረግጥ አላልፍም፡፡ እውነቱን ነው! ብዛታችን ቁልጭ ብሎ የሚታየው እዚህ አይደለም እንዴ? ታድያ በዚህ መንገድ ትልልቅ ሰዎች፤ የሚገራው እንደሚፈልግ እንደ ትንሽ ልጅ ሲሆኑ ሳይ ብስጭት እላለሁ፡፡ ይህን ‹በጎ ፈቃደኛ የመንገድ ትራፊኮች› ይናገሩት፡፡ጠዋት ቀድመው የሚወጡትና ጸባያችንን አውቀው ሳይሰለቹ የሚያስተናግዱት እነዚህ ወጣቶች ስንቱን አይተዋል? እንዴት ነፍስ ያወቀ ሰው፤ «መኪና ይበላሃል! አሁን የመኪኖች ተራ ነው፤ ጥቂት ታግሰህ ቁምና ታልፋለህ» ሲባል፤ አሻፈረኝ ይላል? በመስመር ሂዱ፣ ወደዳር አትውጡ፣ እያያችሁ ተሻገሩ፣ ተረጋጉ፣ ስትሻገሩ ዜብራውን የባለስልጣን ቢሮ ምንጣፍ እንደረገጠ ሰው አትጠንቀቁለትና ራመድ በሉ… ይላሉ አስተናባሪዎች፤ ሰሚ ግን የለም፡፡ታዘቡን! ራሳችንን ታዘቡ! መሥሪያ ቤት ቢሄዱ ቁጭ ብሎ እስክርቢቶ እየበሉ የሻይ ሰዓት ለመጠበቅ ነው፤ ከፍ ካለ ለመሰብሰብና ፊርማ ሳይነሳ ለመድረስ፤ ወዲህ ደግሞ ቆም ብለው ከወዳጅ ጋር «እገሌ ፖስት ያደረገውን አየሽ? እንትና ያለውን ሰማሽ?» ሲባባሉ እልፍ የሚለውን ሰዓት ማንም ልብ አይልም። መንገድ ላይ ግን ሯጭ ነን፡፡ ሰዓት እንደረፈደበት፤ ጊዜውን በአግባብ እንደሚጠቀም ሰው «አሁን ደግሞ እኛ እንለፍ እንጂ ምንድን ነው፤ ሰዓት ገደላችሁብንኮ!» ይላል፤ መንገድ አስተናባሪውን እየተቆጣ፡፡ሌላው ቀርቶ ቅጣት እንኳ አይመልሰንም፡፡ እንደልጅ መቆጣትና ተዉ ማለት አንድ ነገር ነው፡፡ መንገዱ ስርዓት እንዲኖረው የሚደክሙት በጎ ፈቃደኛ ትራፊኮች ዱላ ይዘው ‹ዋ!› እያሉ ቢያስፈራሩ እንኳ ሰዉ የሚታዘዝ አይመስለኝም፡፡ ትልቅ ሰው ግን ድሮም እንዲህ ያስቸግራል!?\nበቀደም በኢትዮጵያ ሆቴል በኩል ሳልፍ ‹‹ዝርዝር ነው?›› አለኝ አንድ ወጣት፡፡ ‹‹እናንተ! አላችሁ እንዴ?›› አልኩት…በልቤ፤ ራሴን በአሉታ ነቅንቄለት እያለፍኩ፡፡ አንደኛ ምን ሆኖ ነው እኔን በዝርዝር የጠረጠረኝ? ዝርዝር ፈላጊ እመስላለሁ? ነው ወይስ አስዘርዛሪዎች እንደእኔ ዓይነት ሰው ልከው ነው የሚያዘረዝሩት? የሚለው ጥያቄ ተፈጠረብኝ፡፡ሁለተኛ ደግሞ ድፍረታቸው ገረመኝ፡፡ እንዴት ሰው በቅጣት አይመለስም? ይህን «እንቢ ባይነት» አርበኞች አገርን ለጠላት አንሰጥም ያሉ ጊዜ ያሳዩት ነው፡፡ «ብትገድሉንም ንቅንቅ አንልም፤ አገራችንን ለባንዳና ጠላት አንተውም» ብለው እስከመጨረሻው ታግለውና ሞተው አገር አትርፈዋል፡፡ እነዚህ ወንድሞችና እህቶቻችን ደግሞ ገንዘብ ለማትረፍ «እንቢ» ብለዋል፡፡አሁን የገባኝ ታዛዥነት የሚባል ኢትዮጵያዊና ሰዋዊ ሀብታችን መቀበሩ አልያም መሰረቁ ነው፡፡ የሚገርመው ደግሞ ልጆች ጋር ሳይጠፋ አዋቂዎች ጋር ነው ድራሹ የሌለው፡፡ መንገድ ላይ ተረጋጋ ሲባል፤ ያውም ለራሱ ጥቅም አልሰማ ያለ ጎልማሳ፤ አውቶቡስ ተሳፍሮ ወጣት ልጅ ለትልቅ ሰው ከወንበሩ ካልተነሳ ቁጣው ለጉድ ነው፡፡ ነገሩን አልኩኝ እንጂ በእርግጥ፤ እሾህን በእሾህ ብሎ የማይታዘዝን ባለመታዘዝ መቅጣት ልክ አይደለም፡፡\nግን ትልቅ ሰዎች ምን ነካችሁ ማለት ፈልጌ ነው፡፡ አንድ ሰው ነፍስ ካወቀና ራሱን መግዛት የሚችልበት ደረጃ ከደረሰ፤ ትልቅ ሰው ይባላል፡፡ እና እነዚህ ሰዎች ብርቅዬ ሊሆኑብን ይሆን? አሁን ስለመታዘዝ ለልጅ እንጂ ለትልቅ ሰው የሚነገር መስሎን ያውቃል? ድንቅ የሚለው ግን ረባሽና አስቸጋሪው ትልቅ ሰው መሆኑ ነው፡፡ ይሄኔ ነው ልጅነት ንፍቅ የሚለው፡፡ ሰላም!አዲስ ዘመን ጥር26/2011", "passage_id": "223d5326bf719c41d9c4c667363cf26a" }, { "passage": "በሽታም የማፈናቀልና የማሳደድ፤ የማስጋትና መበተን አቅሙን ያሳድጋል ጃል፤ ድሮ ድሮ ወረርሽኝ ሲከሰት ቸነፈር አገር ሲመታ አኮፋዳውን ጠቅሎ ቅሉን አንጠልጥሎ የመጀመሪያው ተበታኝ የቆሎ ተማሪ ነበር፤ ለዚህም ተስቦና ሌሎች ተዛምተው የነበሩ ተቀጣጣይና ተላላፊ ገዳይ በሽታዎች ምሥክሮቼ ናቸው።አሁን እኛ በዘመናችን እንሆ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቻችን በወረርሽኝ ሥጋት ምክንያት ወደየመጡበት ሲበተኑ ዓየን።መቼስ ይሁን፤ በዚህ ይማርና!\nአንድ መርከብ ውስጥ ነው አሉ፡- በመርከቧ ውስጥ አንድ ክፍል ለተከራዬ ፕሮፌሰር አንድ አስተናጋጅ ይቀጠርለታል።ታዲያ አስተናጋጁ ሻይና ቡና እንዲሁም ሌሎች ነገሮችን ለፕሮፌሰሩ ባደረሰ ቁጥር ፕሮፌሰሩ አስተናጋጁን አንድ ጥያቄ ይጠይቀዋል “ሥነ ሕዋ አጥንተሃል?” አይ አላጠናሁም ፕሮፌሰር፤ መልስ ካስተናጋጅ።የህይወትህን ሩብ አጥተኽዋላ ታዲያ- ፕሮፌሰሩ።\nሌላ ቀን አስተናጋጁ የተለመደ ተግባሩን ሊያከናውን ወደ ፕሮፌሰሩ ክፍል ገብቶ ሲወጣ አሁንም ፕሮፌሰር ጥያቄ ጠየቁት፡- “ሥነምድር አጥንተሃል?” \nአስተናጋጅ፡- ኧረ በምን ዕድሌ ፕሮፌሰር፤ \nፕሮፌሰር፡- ሥነሕዋም ካላጠናህ ሥነምድርም ካላጠናህማ ግማሹን የህይወት ክፍልህን እንደተነጠቅህ ቁጠረው፡፡\nአሁንም ሌላ ቀን\nፕሮፌሰር፡- አስተናጋጅ፣ ሥነሕይወት አጥንተሃል?\nአስተናጋጅ፡- አላጠናሁም ፕሮፌሰር\nፕሮፌሰር፡- የሕይወትህን እሩብ ጉዳይ አጥተሃል፡፡\nበማግሥቱ አስተናጋጅ የተለመደ ሥራውን ለማከናወን ወደ ፕሮፌሰሩ ቢሮ ሲያመራ መርከቧ በማዕበል መናጥ ጀመረች፤ ያኔ ጠያቂው\n አስተናጋጁ ነበረ።“ፕሮፌሰር፣ ሥነ ዋና (ስዊሞሎጂ) አጥንተዋል?” \nፕሮፌሰር፡- እንደሱ የሚባል ሳይንስ አለ? ኧረ አላጠናሁም አስተናጋጅ፡፡\nአስተናጋጅ፡- ማእብለ መረከቧን እየናጣት ነው፤ ዋና ካልቻልክ ሙሉ ሕይወትህን አጥተሃል።አለው ይባላል፡፡\nበኛ ወግ እንቀይረው እስኪ፤ እርስዎ አካላዊ ርቀት መፈፀም ይችላሉ? ካልቻሉ … ሕይወትዎን አጥተዋል ማለት ነው።እጅዎን በተደጋጋሚና በአግባቡ እየታጠቡ ነው? እያደረጉ ካልሆነ … ሕይወትዎ ለሞት ተጋልጧል ማለት ነው።ምክንያቱስ? ምክንያቱም ያው እንደሚያውቁት መርከቧ በኮቪድ 19 ማእበል እየተናጠች ነውና፡፡\nግን አንዳንድ ወረርሽኝ ብዙ ሕይወት የሚቀጥፈውንና አገርን በክርኑ አቅም እስክታጣ የሚደቁሰውን ያህል ብዙ አስተምሮ ያልፋል።በበኩሌ እኛ ሰዎች ምን ያህል ግብዞች እንደሆን የታዘብኩበት አጋጣሚ ነው። ተው እንጂ ጎበዝ፤ መከላከያው ሩቅ ቢሆን ምን ሊውጠን ነው? በእጃችን እያለ እንደዚህ ከሆን።ቆይ እስኪ ከበሽታ ጋር ለዚያውም ከብርሐን ፍጥነት በእጥፍ የመሰራጨት አቅሙን ካሳየ ወረርሽኝ ጋር ምን የሚሉት ትክሻ መለካካት ነው?\nበእኔ እምነት ከኮቪድ 19 በፊት ለዚህኛው ትምክህታችን መድኃኒት ቢገኝለት መልካም ነው ባይ ነኝ።የመቀመጫ ቤት መኖር አለመኖሩ እንዳለ ሆኖ እቤትህ ተቀመጥ – እንቢ፤ ታጠብ – እንጃልህ፤ ሳኒታይዘር ተጠቀም – ኧረ ንክች እያልን አስቸገርን እኮ።የለት ጉርሳቸውን በዕለት ካልወጡ ማያገኙት ቢሆኑ አጥጋቢ ምክንያት አላቸው እንበል፤ ከራብ ጦር ይሻላል አይደል ብሂሉስ።\nተው እንጂ ሰዎች፤ በሀገሪቱ ፕሬዚደንት እና ጠቅላይ ሚኒስትር፤ በአገሪቱ ቁንጮ አርቲስት እና ከንቲባ በይፋ እየተለመኑ አልሰማሁም ማለት ጤነኝነት ነውን? እዚህ ጋ በማህበራዊ ድረ ገፅ ያየሁት አንድ መልዕክት ትዝ አለኝ፤ ወደ ጎን ሁለት ሜትር\n አካላዊ ርቀት ይኑርህ ስትባል ካልሰማህ ወደታች ሦስት ሜትር ትርቃታለህ የሚል መልዕክት ሲዘዋወር ነበር።አዎ! ሲመክሩት ያልሰማ ቢቀልቡት አይድንም ነውና አካላዊ ርቀት መጠበቅ ካቃተህ ትሞታለህ ማለቱ ነው፡፡\nወዳጆቼ! እስኪ ዛሬ አንድ ዕውነት ላይ እንስማማ።“በሽታ አይናቅም” የሚል ሃቅ ላይ አንድ እንሁን። ኮቪድ 19 ደካማ ቫይረስ ነው ሲባል ሰምታችኋል አይደል? አዎ ደካማ ሊሆን ይችላል።ደካማ ቢሆንም ቅሉ ለመግደል ግን አላነሰም። ሁለት ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎችን ሲይዝ ጭስም ሆነ ነበልባሉ በዓይን አልታየም።በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ግብዓተ መሬት ሲፈፅምም ድምፁን የሰማው አልነበረም።እጅግ ማራኪና ልዕልና ያለው የጤና ተቋምና የጤና ሥርዓት ያላቸውና የዓለማችን ቀዳሚ የሚባሉ ሀገራትን አንገት ሲያስደፋ ከእጅ ጣት ያነሱ ሳምንታት ብቻ ናቸው የተቆጠሩት።\nአዎ! በሽታ አይናቅም።የቫይረስ ደካማም የለውምና አትዘናጉ።ሥጋ ደዌን ታውቁታላችሁ? እጅግ ልፍስፍስ በሆነ ደካማ ባክቴሪያ የሚተላለፍ በሽታ ነው። ይህ በሽታ መድኃኒቱ ተገኝቶ እንኳን እስካሁን ድረስ በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ብሎም በዓለም ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ የሚገኝ በሽታ ነው።ባክቴሪያው ደካማ ይባል እንጂ ከክርስቶስ ልደት በፊት ጀምሮ ይሄው አሁንም ድረስ አለ፤ እና እንዴት በሽታ ይናቃል?\nእንዴት እዚህ ዘመን ላይ ያለ ሰው እጆችህን በአግባቡ ታጠብ ተብሎ ይመከራል፤ እሺ ይመከር እንዴት እጆችህን ታጠብ ተብሎ ይለመናል፤ እሺ ይለመን እንዴት ላለመታጠብ ምክንያት ይደረድራል።በሉ ወዳጆቼ እጆቻችሁን ታጠቡና ለእጥበት አገልግሎት ካልሆነ በስተቀር ከፊታችሁ ጋር አጣሏቸው።ብዙ ጊዜ እንደሰማነው እጆቹን ወደ ዓይን፣ አፍንጫ እና አፍ በላክ መጠን የመጀመሪያ ተጋላጭ ያደርገናል፤ ቀጥሎ አጠገባችን ያሉ እነዛ የምትወዳቸው፡፡\n አረቄና ነጭ ሽንኩረት፤ ፌጦና ዝንጅብል፤ ጥቁር አዝሙድና ሰናፍጭ፤ እፆችና ሎሚ ያድነኛል እያልክ ራስክን አታታል።እነዚህን በአግባቡና በልክ የሠርክ ምግብህ አድርገህ ተጠቀምባቸው።የተጠቀሱት ነገሮች በሽታን የመከላከል አቅማቸው እና ፈዋሽነታቸው የተመሠከረ ነው፤ ግን ድሮ ከበሽታው በፊት ታዘወትራቸው ከነበረ ብቻ ሊረዱህ ይችላሉ።ህይወት ግን በግምትና በዘልማድ አትመራም፤ አስይዘሃት ቁማር ተጫውተህ ታውቃለህን? አታደርገውም።\nበመገናኛ ብዙኃን ማህበራዊ ሚዲያን ጨምሮ እንደተመለከታችሁልኝ ያ ሁሉ ሕዝብ በሞት የተትረፈረፈባት ቻይና በማግስቱ ሳይቀር ስካሩና ሀንጎቨሩ የማይለቅና ቀምሳችሁት ቀርቶ አሽታችሁት ስንፋጤው በአካል ላይ ሁሉ ያሉ ፀጉሮችን የሚያቆም ‘ኦልድ ቻይኒዝ’ የሚባል አረቄ ነበራት።እንደሚታሰበው ቢሆን ቻይና ሕዝቧን ሰብስባ አረቄዋን እየጋተች ሕዝቧን ታተርፍ ነበረ።\nእናም እላለሁ።እባካችሁ ተጠንቀቁ፤ አንተ ባትሞት የምትወዳቸውን ትገድላለህ፤ የምትወዳቸው ባይሞቱ የምትወዳቸው የሚወዷቸውን አጥተው ይሰበሩብሃል።በቸልታ፣ በእንዝህላልነትና በግዴለሽ አስተሳሰብ መደረግ የሚችለውን ጥንቃቄ በመተው ፈጣሪህን እንዳትፈታተነው አደራ እልሃለው።በሙሉ ልብህ ፈጣሪህን አምነህ ፀልይ፤ አንተ እያወቅህ የጣልከውን ራስህን ግን ማንም እንደማያቀናልህ ጠንቅቀህ ተገንዘብ።\nያው እንደሰማኸው ከሰዎች ጋር ያለህን አካላዊ ርቀትም ጠብቅ፤ መተቃቀፍ ካማረህ በመንፈስ ተቃቀፍ። ምንም እንኳን መንበረ ሥልጣንን በፈቃድህ ባታቆናጥጠኝም፣ እኔ ይህን ሕግ አንተ ላይ አወጅኩኝ፤ ይህን አዋጅ በሌላ አዋጅ እስክሽረውም አደራ ያለመዘናጋትና ያለመታከት ተግብር።እንኳን በሽታውን ተከላክሎልህ ይቅርና ብታደርገው ስለማይጎዳህ ነገር ቀንድህን አቁመህ ስትከራከር ባይህ እታዘብሃለው፤ ለነገሩ እንደኔ ባይነግሩህ እንጂ ሰዎችም በዚህ ጉዳይ ብዙ ጊዜ ታዝበውሃል።\n አዲስ ዘመን ሚያዝያ 26/2012ውብሸት ሰንደቁ", "passage_id": "564c32c45465b8f146e247b9bce947e1" }, { "passage": "የሌላውን ሀገር ባላውቅም በእኛ ሀገር  ግን የማንተገብራቸው በርካታ አባባሎች አሉን። ምሳሌ ጥቀስ ካላችሁኝ ከመነሻዬ ሀሳብ ጋር ከሚቀራረቡት መካከል ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ፣ ሳይቃጠል በቅጠል፤ አስሬ ለካ አንዴ ቁረጥ፤ ሰዶ ማሳደድ ቢያምርህ….. ፤ ቀድሞ ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ…..የሚሉት ከብዙ ጥቂቶቹ ናቸው። ብዙ አልተጠቀምንባቸውም  እንጂ   በየመስኩ በየጉዳዩ ብዙ ተረቶች ብዙ አባባሎችና ወጎች  አሉን።ያለሁት ኮተቤ  ከአንድ የዘመዴ ቤት ነው የታመመች ልጇን ለመጠየቅ። ልጅቱ ደግሞ እግሯን  በጀሶ ጠቅልላ መሬት ላይ የተነጠፈ ፍራሽ ላይ ተኝታለች። እንዴ?  ምን ተፈጥሮ ነው? ጠየቅኩ፤ «ወለም ብሏት» ስትይኝ ቀላል መስሎኝ ነበር አልኩ ደንገጥ ብዬ። «እንዳትደነግጡ ብዬ ለሁሉም እንዲሁ ነው ያልኩት። ለነገሩ ዶክተሩ አጥንቷ ብዙም አልተጎዳ፤ በዛ ላይ ልጅ ስለሆነች ቶሎ  ይስተካከላል ብሎኛል» አለች።  ለመሆኑ ምን ሆና ነው?እናቲቱ « አልሰማ ብላ» በማለት ጀምራ ባጭሩ ታሪኩን አወጋችኝ። በአካባቢው ረጅም ጊዜ የወሰደ ሰፊ የመንገድ ሥራ እየተከናወነ ነው። እናም በየቀኑ ወይ ይቆፈራል ወይ ይናዳል ይሄ ሲሆን ግን መንገዱ  በከፊል ለመኪና ይዘጋል። እግረኛው በአንድ ጎን  የግለሰብ አጥር በሌላ  በኩል ደግሞ ገደል በሚያዋስኑት ጠባብ የግራና ቀኝ መንገዶች እየተጠባበቀ ነው የሚጓዘው። አንዳንድ ቦታ ገደሉ ረጅም ስለሚሆን እናት ልጇን በዛ መንገድ እንዳትሄድ  ርቀት ቢኖረውም በአስፋልት ዞራ እንድትመጣ በተደጋጋሚ መክራት ነበር፤ ግን አልሆነም። ከጓደኞቿ መለየት ያልመረጠችው ልጅት ከጓደኛዋ ጋር እንደተያያዙ  ተንሸራተው ከአንዱ ገደል ይወድቃሉ። እንደተነገረኝ ከሆነ ሁለቱም ለከፋ ጉዳት ባይዳረጉም ለቀናት ከትምህርት ገበታቸው መለየታቸው ግን አልቀረም።እንደኔው ሊጠይቁ የመጡ አንዲት እናት «አሁንማ አስተካከሉት እኮ ትናንት የእከሌ አባት አሉ  ስም እየጠሩ ወድቀው ላይሞቱ ነው የተረፉት፤  ዛሬ በደንብ አስተካክለውታል» አሉ በማፅናናት አይነት። ምን ዋጋ አለው ፈጣሪ ባይደርስላት ሞታ አልነበር። ስንት ሰው  በቀን በማታ መከራውን ሲያይ ምን ሰሩ?  ድሮም አንድ ሰው ሞተ፣ መኪና ተገለበጠ ካልተባሉ እንደማይሠሩ ይታወቃል፤ የህዝቡን አቤቱታ መች ሰምተውን ያውቃሉ አለች ዘመዴ ምርር ብላ። እነሱ ወሬያቸውን ቀጠሉ እኔ በሀሳብ ነጎድኩ ግን እውነት እስከ መቼ እሳት እያጠፋን እንኖራለን ?።ተሰናብቼ ወጥቼ ከሃሳቤ ሳልላቀቅ መገናኛ አካባቢ ስደርስ ሻይ ቡና ለማለት መተባበር ህንፃ ላይ ባለ አንድ ካፌ ውስጥ ተቀመጥኩ። ቁልቁል የባቡሩን አካፋይ የቀለበት መንገድ ስመለከት ትኩረቴንም ስሜቴንም የሚስብ ተመሳሳይ  ነገር አስተዋልኩና በጥሞና መከታተል ጀመርኩ። አካባቢውን በደንብ አውቀዋለሁ፤ የጎዳና ላይ ንግድ የተጧጧፈበት ነው። በተለይ አመሻሽ ላይ ያለው ገበያና የሚቀርበው ሸቀጥ «ንግድ ፈቃድ፣ ግብር፣ ቤት ኪራይ» ለምኔ  የሚያሰኝ ነው።  ይሄ ታዲያ  ለወጣቶቹ ነጋዴዎች ከጠባቂዎች ጋር የሚደረገውን  የድብብቆሽ ጨዋታ  በየቀኑ ማሸነፍ ይጠይቃል።  እነዚህ ነጋዴዎች አብዛኞዎቹ በወጣትነት እድሜ ክልል ያሉና ከአዲስ አበባ ውጪ የመጡ በመሆናቸው ባንድ እጃቸው ዱላ በአንደኛው ደግሞ ኮፍያቸውን ይዘው ለሚያሯሩጧቸው የሸገር ጠባቂዎች  የሚረቱ አይደሉም። እንዲያውም አንዳንዶቹ ያንን ኮተት ይዘው እንደዚያ መሮጥ ከቻሉ በዱላ ቅብብል ውድድር ቢሳተፉ እላለሁ።እንግዲህ ልብ በሉ መንግሥት የጎዳና ላይ ንግድን የሚያበረታታ ባይሆንም ወደ ህጋዊ ሥርዓት ለማስገባትና ነባራዊውን ሁኔታ ከግምት በማስገባት በመንገድ ዳርቻ እንዲሸጡ የተፈቀደላቸው ህግ አክባሪ የጎዳና ላይ ነጋዴዎች በየቦታው አሉ። በዚሁ አካባቢ እንኳ ከአደባባዩ  ሁለት መቶ ሜትር ባልሞላ ርቀት አምቼ አጥር ስር በተፈቀደላቸው ቦታ ተወስነው የመኪናና የእግረኛ እንቅስቃሴ ሳያግዱ የሚሠሩ የጎዳና ላይ ነጋዴዎች ቢኖሩም እቃቸውን የሚገዛ  ሸማች የሚደርሳቸው  በአደባባዩ ከሚሯሯጡት  ህገ ወጥ ነጋዴዎች የተረፈው ብቻ ነው። ከታች የምገልጽላችሁ ትእይንት ደግሞ እጣ ሳያወጡ፣ አቦሰም  ሳይጣጣሉ  ጠባቂዎቹና ነጋዴዎች እንዴት  የአባሮሹን ጨዋታ እንደሚጀምሩ ነው።አዲስ አበባ መንገዶች ባለሥልጣን እግረኛውንና አሽከርካሪውን ለመለየት በከለለው  ብረት ላይ  ደማቅ ሰማያዊ ቀለም ያለው ባለ አርማ ዩኒፎርም የለበሱ የቦሌ  ክፍለ ከተማ ደንብ አስከባሪዎች ሦስት ሆነው ተደግፈው ያወራሉ። የሚያወሩት ደግሞ ስለ ኑሮ ውድነት ነው። ፎቅ ላይ ሆነህ እንዴት ይሄን አዳመጥክ የሚለኝ ካለ ግምቴ መሆኑን በማስቀደም ለግምቴ መነሻ የሆነኝን  ምክንያት አቀርባለሁ።ከፌስ ቡክ እንደተማርኩት ከሆነ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ሰብሰብ ብለው ከታዩ ድንጋይ ውርወራ ሊጀመር በመሆኑ ከአካባቢው መራቅ አልያም ኮፍያ ብጤ ጣል ማድረግ ከተማሪዎቹ ንረታም ሆነ  ሰላማዊና አጥፊን ሳይለዩ ከሚቀጡት ህግ አስከባሪዎች  ራስን ለመታደግ ይረዳል። ተማሪዎቹ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ከሆኑ ስለፍቅር ጓደኛቸው እንደሚያወሩ የሚገመት ሲሆን፣ የመጀመሪያ ደረጃ ተማሪዎች ከሆኑ ስለ ፊልም እንደሚሆን እንገምት። ወደ መንግሥት ሠራተኛው ሲመጣ ጉዳዩ የሚወሰነው በእድሜ አልያም በክፍል ደረጃ ሳይሆን በደመወዝ ይሆንና ባጭሩ ዝቅተኛው ተከፋይ ስለኑሮ ውድነት መካከለኛው ተከፋይ ስለሥልጣንና እድገት ፣ ከፍተኛው አመራር የየእለት ጭውውቱ በፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ያጠነጠነ መሆኑ በዚሁ ፌስ ቡክ ማየት ችያለሁ። የፖለቲካው ነገር ግን ደመወዝም ዕድሜም የሚገድበው አይደለም፤ በተለይ አሁን አሁን።እጅና አፍ አይጠፋፉም ብዬ ከግማሽ ሰዓት ላላነሰ ጊዜ እጄን ከብርጭቆዬ አገናኝቼ ወደ አስፋልቱ ባደረግሁት ማፍጠጥ እነዚያን ስለ ኑሮ ውድነት የሚያወጉ የደንብ አስከባሪዎች የጎዳና ላይ ነጋዴዎቹ እንደ ቀልድ ባጠገባቸው ያልፏቸው ይዘዋል፤ ትንሽ መጠንቀቅ የሚመርጡት ደግሞ ጣደፍ ጣደፍ እያሉ ያልፋሉ፤ ለነገሩ ከአስፋልት ማዶ  የሚያልፉ  ጥንቃቄ  የሚያበዙ  ነጋዴዎችም አሉ።ይህን ጉድ ሳላይ አልነሳም ብዬ ለአንድ ሰዓት ከቆየሁ በኋላ አስራ አንድ ሰዓት ተኩል ሲሆን በርከት ያሉ ደንብ አስከባሪዎች ከየአቅጣጫው በመምጣት ባጠገባቸው እያለፉ ወደ አደባባዩ ገብተው እቃቸውን ከዘረጉት የጎዳና ላይ ነጋዴዎች ጋር የዘወትር አባሮሻቸውን ቀጠሉ። አንዳንዶቹ ሊይዟቸው የሚፈልጉ አይመስሉም ፤ በፍጥነት መሮጥ ይጀምሩና ሊደርሱባቸው ሲሉ ፍጥነታቸውን ይቀንሳሉ።  ለነገሩ «ከልብ ካለቀሱ» የሚለውን አባባላችን  መነሻ  አድርገን ካየነው ምንስ ፈጣን ቢሆን   እቃ ተሸክሞ የሚሮጥን በባዶ ሮጦ መያዝ አለመቻል ተቀባይነቱ እዚህ ግባ የሚባል አይሆንም።  ግን እነዚህ ደንብ አስከባሪዎች የሚሰጣቸው ሥልጠና ምንድነው? ቤት ተሠርቶ፣ አጥር ታጥሮ ሲያልቅ ማፍረስ በአጭሩ መቅጨት የሚችሉትን ለግጭትም ለንትርክም ምክንያት ሲሆን ይታያል።ከዓመታት በፊት አንድ የመኪና ጥገና  የሚሠራ ጓደኛዬ የነገረኝ « የወረዳችን አስተዳደር  21 ዓመት በጋራዥነት ሲያገለግል የነበረውን ግቢ  ከስፋቱ  ጀምሮ ደረጃ አያሟላም ብሎ  እንዲያስፋፉ የማስተካከያ ጊዜ ይሰጣቸዋል።  አስተዳደሩ ምንም እንኳ በህግ የተቀመጠ ነገር ቢናገሩም  በሦስቱም አቅጣጫ በግለሰብ መኖሪያ ቤቶች የተከበበችው  ቦታ ወዴትም እንደማትሰፋ በእርግጠኝነት ያውቁ ነበር። እናም ቀኑ ደርሶ ጋራዡ መስፋት ባለመቻሉ  ተዘጋ» የኔ ጓደኛና ባልደረባው  ከባድ መሳሪያ የማያስፈልጋቸውን ጥገናዎች በየቤታቸውና በየመንደሩ መንገድ እየዘጉ መሥራቱን ቀጠሉበት።  በዛ ሰሞን  እንዴት ነው ያዋጣል? ብዬ ላቀረብኩለት ጥያቄ የሰጠኝ ምላሽ እንዲህ የሚል ነበር  « እኛና መንግሥት ከጋራ ተጠቃሚነት ወደ የጋራ ተጎጂነት ተሸጋግረናል፤ እኛ በጠራራ ጸሀይ በየጎዳናው እየተሽከረከርን ለመሥራት ተገደናል መንግሥት ደግሞ ብታንስም መሰብሰብ የሚችለውን ግብር አጥቷል፤ ድሮ ማወራረድ ስላለ ብዙ ነገሮችን ስንገዛ በደረሰኝ ነበር፤ አሁን ህጋዊ ነጋዴዎች ጋር የሚያስኬደን ጉዳይ የለም፣ ነገሩ ሁሉ አየር በአየር ሆኗል»።  አለኝ እያዘነም ፤እየተናደደም።ምንም እንኳ ህግ መከበር ቢኖርበት  ሰው ከሰላማዊ መንገድ ተገፍቶ ሲወጣና አማራጭ ሲያጣ  ወዴት እንደሚያመራ የሚያሳየን ይመስለኛል። እነዚህ በየታክሲው ላይ የምናያቸው እቤትዎ ድረስ መጥተን ፍሪጅ እናድሳለን፣ ቴፕ፣ ቴሌቪዥን  እንጠግናለን የሚሉ ማስታወቂያዎችም የዚሁ ውጤት ይመስሉኛል። ይሄን ሳይ  ህግና ሥርዓት አክብረው የሚንቀሳቀሱትን  አለመደገፍና አለመንከባከብ ህገ ወጦችን  ማበረታታት፤ ህጋዊው መንገዱንም መግፋት ይሆንብኛል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 20/2011", "passage_id": "89f5dae4825b4812f1864181eed9151f" }, { "passage": "ስንት አይነት ዓመል አለ ? እንዲሁ ብድግ ብሎ ነጠላዬን አቀብሉኝ የሚል። ማለቴ ለነገር ማን ነው? ብሎ እንቧ ባይ፤ በፉከራ። ዛቻ። ማስፈራራት እንዳው ደርሶ ሰውን ለማሸማቀቅ መሞከር፤ ኧረ ብዙ አለ። ይሄ ታዲያ ወንዶች ላይ ብቻ እንዳይመስላችሁ ሴቶችም በተመሳሳይ ይታይባቸዋል። ‹‹የቤትሽን አመል እዛው›› የሚል የታክሲ ላይ ጽሁፍ ሳይ ታዲያ ምን ያህል በነገር ተጠብሰው ይሆን ስል አሰብኩ። ይህን ስል ግን እንዲህ አይነት ጽሁፍ የህዝብ አገልጋይ በሆነ መኪና ውስጥ መለጠፉ ተገቢ ነው እያልኩ እንዳልሆነ ይያዝልኝ። ምክንያቱም አገልጋይ ‹‹ተገልጋይ ክቡር ነው›› የሚለውን መቀበል አለበታ፤ እንዳውም ‹‹ደንበኛ ክቡር ነው›› የሚለውን በትልቁ ማስነበብ ይጠበቅበታል። ደንበኛ ከሌለ ገንዘብ የለም፤ ሥራ የለም። ስለዚህ ሁልጊዜ ደንበኛ መከበር አለበት። አገልጋይስ ካልን ተመሳሳይ ነው። ደንበኛም ካለአገልገይ ምንም መሆን አይችልም። ማን ምን ማድረግ ይችላል? ማለቴ የአንድ ቦታ አገልጋይ የሌላ ቦታ ተገልጋይ መሆኑ አይዘንጋ። ይሄን ወደ ፈላጊና ተፈላጊ እናምጣው። አርሶ የሚያበላን ገበሬ መቼም የምንሰጠው ትልቅ ቦታ አለ፤ ህይወታችንን የያዘው እሱ በመሆኑ ማለት ነው። ግን እኮ እኛም ለእሱ ስንት እንደምናገለግል በየዘርፉ ሆነን አስሉት። ብዙ ነው እንዳው ዝም ብለን ብቻ እንከባበር፣ እንተጋገዝ … በሚለው እንስማማ። አንዱ ሌላው፤ ሌላውም ለአንዱ አስፈላጊ ነዋ። ከዚህ የተለየ ሀሳብ ያለው ካለ መድረኩ ክፍት ነው ጻፉ፣ ሞግቱን። ስንት አይነት አመለኛ አለ መሰላችሁ? “አመልሽን እንዳለው ሁሉ አመልክን …” መባል ያለበት። በመንገድም ዘወርወር ሲባል የሚያጋጥም አጀብ የሚያሰኝ ሞልቷል ብቻ እንዲህ አይነቱ አይግጠማችሁ። አንድ ዕቃ ድንገት አይኔ ይገባል። ነገሩ አሁን ለመግዛት ባላስበውም የሚያስፈልገኝ ዕቃ በመሆኑ እገዛዋለሁ ብዬ ዕቅዴ ውስጥ ገብቷል፤ እናም አንድ ቀን መንገድ ዳር ለሽያጭ ቀርቦ አየሁትና ኪሴን የሚመጥን ከሆነ ለመውሰድ ጎንበስ አልኩ። እያገላበጥኩም ደህንነቱን ማረጋገጥ፤ ቀጥሎ የሚመጣው የዋጋ ውጣ ውረድ፣ ክርክር አይደል ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አመራሁ። እናም በዛው መስመር ላይ ነን። ዋጋውን ደጋግሜ ጠየቅኩ እሱ ግን ምን በወጣው መልስ አይሰጥም፤ ለጠየቀው ሁሉ መመለስ ደክሞት ወይ ሰልችቶት ይሆን እንደእኔው እያገላበጠች የምትመለከተውን እና ከእኔ ቀደም ብላ የነበረችውን ቀስ ብዬ ስንት ይላል? አልኳት። መለሰች ” እሱ አልነገረኝም ሰዎቹ (እንደ እሷ ሊገዙ ዕቃ የሚያገላብጡት) ግን እንዲህ ብለውኛል አለች በሽክሹኩታ ። ዋጋው ከኪሴም ሆነ ከዕቃው ጋር አልጣጣም ስላለኝ ለምን አትናገርም ዋጋውን አልኩ። ተነፈሰ፤ ሴትየዋ እንዳለችኝ ነው። ስለዚህ ልገዛው አልችልም። በእጄ የያዝኩትን ዕቃ አስቀምጬ መንገድ ስጀምር እሱ ደግሞ ስድቡን ቀጠለ። ካልገዛሽ ምን አስጠየቀሽ በሚመስል መልኩ። ብቻ ያወርደዋል፤ በነፃ ውሰጃ፣ ሌላም ሌላም… ብቻ የማይወረወሩ ቃላቶች የሉም። ዋጋውን ለመናገር የደከመ የመሰለው ምላስ ለስድቡ ጊዜ ረዘመ “ጉልበተኛ ይዘዝብህ!” ትልቅ ምርቃቱ ነበር ። ኮቴዬ\nእስኪጠፋ ድረስ የእሱን ድምጽ አዳምጣለሁ የሚለውን በትክክል ባልሰማውም ያው የተለመደው የስድብ ውርጅቢኝ እንደሚሆን መገመት አልቸገረኝም። እኔም እንደ እሱ ወገቤን ብይዝስ ኖሮ ብዬ በገበያው መሀል የሚፈጠረው ሁሉ ተሰማኝ፤ አቤት ስንት አይነት ነገረኛ አለ? ትዝብቴን አጠናከርኩ። ይሄ ነው” አመልክን እዛው” ማለት። ያለ ዕቃው ዋጋ ሰጥቶ ካልገዛችሁ ማለት አይናችሁን ጨፍኑና ተታለሉ እንደማለት ነው። ግን እኮ የእኛ አገር የገበያ ስርዓት የመንገሪያና የመሸጫ ዋጋው ሀቅና እውነታ ላይ የተመሰረተ ባለመሆኑ ነው እንጂ እንደሌሎች አገሮች የመሸጫ ዋጋው የተወሰነ መሆን ነበረበት። ይሄ ማንም በዋጋም በጥራት ሳይታለል ሳይጭበረበር ግብይት ያካሄድ ነበር። በነገራችን ላይ ከዚህ በመነሳት ነው በመንግሥት እና በንግዱ ማህበረሰብ መካከልም መተማመኑ የማይታየው። የሚነገደውና የሚያቀርበው ፤… አራንባና ቆቦ\nየሚሆነው። ይሄንን ስል ምን ትዝ አለኝ? የድሮ ሰፈራችን እማማ ብርቄ ማንም ባይናገራቸው እንኳን ደሞ ይሄ ይቺ ብለው የንግግር መጥፎ ይዘረግፋሉ። ምን አደረጉ? ቢባሉ በእርግጠኝነት መልስ አይኖራቸውም ብቻ አዩኝ። አንጓጠጡኝ። እንዳው ሳስበው ሳስበው የውስጣቸውን ችግር። ድህነቱን የሚገፉበት እየመሰላቸው ይሆናል? ማንም ዞር ብሎ አይዞወት እንኩ ይቺን አይለማ። ያለውም የሌላውም ዝም ጭጭ ከሆነ የተቸገረው ምሬቱን በመጥፎ ንግግር በስድብ ማውጣቱ አይቀርም። እኛም አመለቢስ የሚለውን ስም ሰጥተን ግን ደግሞ የችግሩ መሰረት ምን ይሆን ብለን ብንነሳ መፍትሄው እኮ በእጃቸን መዳፍ ሥር ይሆናል፤ ደግሞም ነው። ነገርን ቀለል ቀለል የሚያደርጉ ደግሞ አሉ፤ እነሱን ያድርገኝ ማለት ጥሩ ፀሎት ነው። ማን ለነገር ጭንቅላቱን በነፃ ያከራያል? እንዳው ቢሆን ቢሆን ኧረ ደግሞ ይሆናል ክፉ ነገርን ሰምቶ እንዳልሰሙ መሆን፤ ነገርን ቀለል አድርጎ ማየት ለእያንዳንዱ ችግር ምክንያት በመፍጠር ራስን ነፃ ማውጣት ከምንም በላይ ትልቅ ዋጋ አለው። አብሮ ለመኖር ከቤት ውስጥ እስከ ውጭ የሥራ ቦታ በጎረቤት ብቻ ሁሉን ችሎ አቻችሎ መኖር ጥሩ የሚባል ይሆናል። ካልሆነስ ካላችሁ ካልሆነማ ጭንቀት፤ ስኳር፤ ደም ግፊት…መሰል ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን መጥራት ይሆናል። ይሄንን ስል ግን ሁሉም ህመምተኛ በዚህ ምክንያት የታመመ ነው ለማለት እንዳልሆነ ይያዝልኝ። ዋናው ግን እንዳው የስነልቡና ባለሙያዎች እንደሚሉት ትልቁ ጉዳይ አዕምሮን ሥራ አለማሳጣት ነው። ሰው ቁጭ ሲል የሆነ ያልሆነው ሲያስብ ሌላውም ሌላውም ሲጨማመርበት አዕምሮው ለፈጠራ ለሥራ መሆኑ ይቀርና ለፀብ። ለለከፋ፣ ለተንኮል፣ ሰውን ለማጣላት… ብቻ ለክፋት ይውላል። እንዲህ አይነት ሰው ከዕለታት አንድ ቀን ቢሆንም ፀባይ ማረሚያ ጎራ ማለቱ አይቀርም። አዎ! ጎራ ማለት አለባቸው። የሕግ የበላይነትን ካለወቁ በሕግ አምላክ ቢባሉም ጆሮ ዳባ ይሆናል። እሱ ብቻ አሸናፊ የሆነ ይመስለዋል፤ መሳደብ፣ መበጥበጥ ትክክለኛ ነገር ሊመስለው ይችላል:: እናም ሁሌም እሱ ልክ መሆኑን ለራሱ ያስረዳል። ለራሱ ትክልል የሆነ ቢመስለውም ትክክል አለመሆን ሕግ እንዲያሳውቀው ቢደረግ እሱ ከጥፋቱ ተምሮ ለሌላውም የሕግን የበላይነት የሚሰብክ አይመስላችሁም? ይሄንን ስል ምን ትዝ አለኝ። ሁለት ልጆች ኳስ ይጫወታሉ። እኔ ደግሞ በዳኝነት ላገለግል ተመርጫለሁ። እናም ጨዋታው ሕግ ወጣላት ከህጉ አንዱ መበሻሻቅ አለ የሚል ነው። ሁለቱም በዚህ ሀሳብ ተስማሙ፤ መበሻሸቅ የማንንም መብት ሳይነኩ በሚለው መቋጫ ጨዋታው ቀጠለ ። እንደሚያሸንፍ በራሱ\nየተማመነው እንዳሰበው ሳይሆን ጎል እየገባበት ተቃራኒው ደግሞ ጎሉን እያስቆጠረ ጨዋታው ደራ። አሸናፊና ተሸናፊ ተለይቶ ጨዋታው ይጠናቀቃል። በቤት ውስጥ ሕጉ መሰረት በችሎታው ባልተማመነው ተጫዋች ጨዋታው ተጠናቀቀ። እናም የብሽሽቁ ሰዓት ደረሰና አሸናፊው ብዙ ጊዜ ጎል አግቢዎች የሚደንሱትን ዳንስ በመደነስ እይተገለባበጠም ደስታውን ገለፀ። ይሄን ጊዜ ንዴቱን አልችል ያለው ተቃራኒ ቡድን ዘሎ አናቱ ላይ ጉብ አለ። ይሄ እንግዲህ በንዴት መሆኑ ነው ተገላገሉ ልጁም ተቀጣ፤ ከዛ እንዴት እመታለሁ ብሎ ቡራ ከረዩ አለ፤ ለማስረዳትም ለመረዳትም እልሁ አለና በዕለቱ በቅጣት ታለፈ ። በተገቢው ቦታ ተገቢው\nቅጣት ጥሩ ፍሬ ያፈራል\nእና ተኝቶ ሲያስበው\nጥፋቱ ፀፀተውና በማግስቱ\nሁሉንም ሰው ይቅርታ\nጠየቀ። ሁሉም ነገር\nበተገቢው መልኩ ቅጣት\nከተሰጠው የጎበጠው ይቃናል።\nይሄ ብቻ አይደለም፤\nየራስም ችግር ይታያል\nወደ መስመር መግባትም\nይኖራል። መስመሩን የሚያውቅ\nደግሞ የወደፊቱንም ያያል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 28/2011 ", "passage_id": "181d7940fa201141f5473195294d613a" } ]
e972d49758e31f60d8cbc8ea81d2a40a
20daf983e9542986441cf79b0053d6bd
ኢትዮጵያ በአፍሪካ መድረክ ተሳታፊ ክለብ የሌላት ብቸኛ አገር ሆናለች
የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ወረርሽኝ እንደሌሎቹ ማህበራዊ፣ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ኩነቶች ሁሉ የዓለምን ስፖርት ውጥንቅጡን አውጥቶታል፡፡ ታላላቅ የዓለማችን ሊጎች የሚይዙትን የሚጨብጡትን አጥተው ከርመዋል፡፡ ከሳምንት በፊት አንስቶ ግን የዓለማችን ታላላቅ ሊጎች ወደ ውድድር እየተመለሱ ስፖርቱም እያገገመ ይመስላል፡፡ ወትሮውንም ችግር የማያጣት አፍሪካ የዚህ ችግር ገፈት ቀማሽ መሆኗ ነገሩን በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንደሚያደርግባት ቀድሞም የተገመተ ቢሆንም የአንዳንድ አገራት የእግር ኳስ መሪዎች አስቸጋሪውን ወቅት በብልሃትና በበሰለ አመራር ሰጪነት ለመሻገር ጥረት ማድረጋቸው አልቀረም፡፡ የቡርኪናፋሶ እግር ኳስ ተሞክሮም ለዚህ ጥሩ ምሳሌ መሆኑን መመልከት ይቻላል፡፡ ቡርኪናፋሶ እንደሌሎቹ የዓለማችንም ይሁን የአፍሪካ አገራት ሰሞንኛ ማህበራዊ ሁኔታዋ ጤነኛ አልነበረም። አፍሪካ ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ የኮሮና ቫይረስ ያጠቃቸው ፖለቲከኞች ተመዝግበውባታል። የቡርኪናፋሶ መንግሥት ይህ ቫይረስ ተስፋፍቶባቸዋል ብሎ ካወጀባቸው ቦታዎች መካከል የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎች ይገኙበታል፡፡ ጅምናዚየም ፣ የኳስ መጫወቻ ሜዳዎች ለዚህ ተጠቃሽ ከሚባሉት ቦታዎች ውስጥ ይገኛሉ። ስለዚህ ይህንን አደጋ ለመቀነስ እና ለማህበረሰቡ ዋስትና ለመስጠት ሊጉን ሰርዞ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ የዘንድሮው የውድድር ዓመት እንደማ ይጠናቀቅ እና በዚሁ ውጤት እንደሚያልቅ፣ ሁሉም ክለቦች በውል ውስጥ የሚገኙ ተጫዋቾቻቸውን ውል እንዲያከብሩላቸው እና እስከውል ማለቂያው ድረስ ደመወዝ እንዲከፍሉ፣ ማንኛውም ክለብ ያለምንም በቂ ምክንያት ምንም አይነት የክለብ አባላት ቅነሳ እንዳያደርግ፣ የትኛውም ተጫዋች ተበደልኩ ቢል ለፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት እንዲያመለክት፣ ከሁሉም በላይ በዘንድሮ 2019 የውድድር ዘመን በኢንተርናሽናል መድረክ አገሪቱን የወከሉት ቡድኖች ማለትም (ራሂሞ ኤፍ ሲ) እና (ሳሊታስ) የተባለው ክለብ በክለቦች ኮንፌዴሬሽን ጨዋታ በሚመጣው ዓመት አገሪቱን እንዲወክሉ አድርጓል። ይህንን ያደረገውም የዘንድሮ ልፋታቸው ሽልማት እንኳን ቢሆን ብሎ በማሰብ ነው ። አሱማ ሲሪማ የቡርኪናፋሶ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ናቸው፡፡ ይህንን ውሳኔ ሲወስኑ ሁሉንም እንደሚያስማማ በማሰብ መሆኑን ተናግረዋል:: ቡርኪናፋሶን የወከሏት ቡድኖች የተገኙት አምና ባስመዘገቡት ውጤት ነው ። ይህ አንዳንዴ የተቀመጠን ህግ እና አሰራር ወቅቱ በሚፈቅደው ነገር እንደሚጠመዘዝ ማሳያ ነው ። የኢትዮጵያ ሊግ ካምፓኒ ምንም አይነት ቡድን ኢትዮጵያን በኢንተርናሽናል ውድድር አይወክልም የሚል ውሳኔ ከወር በፊት አስተላልፏል። ይህ እንደ አገር በድጋሚ ሊጤን የሚገባው ውሳኔ እንደሆነ በርካቶች አስተያየት ሰጥተውበታል፡፡ ውሳኔው ስህተት መሆኑን ወሳኞቹ አካላት ቢያምኑም የተወሰደ ርምጃ የለም፡፡ ይህንንም ተከትሎ ኢትዮጵያ በአፍሪካ መድረክ ተሳታፊ ክለብ የሌላት ብቸኛ አገር ሆናለች፡፡ የደቡብ አፍሪካው ሱፐር ስፖርት ከቀናት በፊት ‹‹ኮሮና እና የአፍሪካ ሊጎች›› በሚለው ሰፊ ዘገባው በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ከሶስት ወራት በላይ ተቋርጦ የነበረውን የአፍሪካ አገሮች ወረርሽኙ ባይጠፋም የሊግ ውድድሮች ቀስ በቀስ ከተቋረጠበት እያስጀመሩ እንደሆነ አስነብቧል። ሱፐር ስፖርት በሰፊ ዘገባው አያይዞም ኢትዮጵያ ከሌሎች አገሮች በተለየ መልኩ ሊጓን ሙሉ ለሙሉ መሠረዟን እና በሯን መዝጋቷን አስነብቧል። በዚህም ኢትዮጵያ በቀጣይ ዓመት ክለቦቿ በአፍሪካ ውድድር ባለመሣተፍ ብቸኛዋ አገር መሆኗ ተረጋግጧል:: በኢንተርናሽናል ውድድሮች ኢትዮጵያን ወክለው የሚሳተፉት ቡድኖች ከየትም ወገን ይምጡ የሚወክሉት ሊጉን ነው ። ሊጉ ደግሞ በድግግሞሽ በየዓመቱ ኢትዮጵያን በጥራት የሚወክሉ ቡድኖችን ይፈልጋል። ይህንን ጥራት ለማምጣት ደግሞ የቡድኖችን የኢንተርናሽናል ተሳትፎ መንገድ መቁረጥ ሌላ ፈተና ይዞ እንደሚመጣ ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ ይህን መቁረጥ በአንድ ዓመት የኢንተርናሽናል ልምድ በጥሩ ብቃት ላይ የሚገኝን ተጫዋች ራሱን የማሳየት ተስፍ ማጨለሙ አይቀርም፡፡ የክለቦችን የአስተዳደራዊ ዝግጅት ደረጃ ከፍ የማድረግ ልምድ ማሳነስም ሌላኛው ኪሳራ ነው፡፡ እንደ ላይቤሪያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ቡርኪናፋሶ ያሉ የአፍሪካ አገራት የዘንድሮ ፕሪሚየር ሊግ ውድድራቸውን ቢያቋርጡም በአፍሪካ ውድድሮች ላይ የሚወክሏቸው ክለቦች አሏቸው። በዚሁ ወረርሽኝ ሳቢያ ከአፍሪካ ክፉኛ ተጎጂ የሆነችው ግብፅም ብትሆን ሊጓን ሙሉ በሙሉ ለመዝጋት አልተጣደፈችም፡፡ እንዲያውም ከትናንት በስቲያ የአገሪቱ ስፖርት ሚኒስትር አሽራፍ ሶቢሂ ሁሉም የእግር ኳስ ክለቦች ከአንድ ሳምንት በኋላ ልምምድ እንዲጀምሩ ማሳሰባቸው እየተዘገበ ይገኛል፡፡ አዲስ ዘመን ሰኔ 11/2012ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=34598
[ { "passage": " ቦጋለ አበበ ምዕራብ አፍሪካዊቷ አገር ኮትዲቯር የ2023 አፍሪካ ዋንጫን ለማስተናገድ የምታደርገው ዝግጅት በሚፈለገው ደረጃ ቀጥሏል።የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ባለፈው ዓመት ከተከሰተ ወዲህ በርካታ የዓለማችን አገራት ስፖርታዊ ውድድሮችን ከማቆም ባለፈ ዓለም አቀፍና አህጉር አቀፍ ውድድሮችን ለማስተናገድ የሚያደርጉት ዝግጅት ተስተጓጉሏል።የ2023 አፍሪካ ዋንጫን ለማስተናገድ ዕድሉ የተሰጣት ኮትዲቯር ግን ወረርሽኙ ሳያግዳት ዝግጅቷን በተገቢው መንገድ እንደቀጠለች ኢንሳይድ ዘጌምስ አስነብቧል። የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የግምገማ ቡድን ከሳምንት በፊት ወደ ኮትዲቯር አቅንቶ አገሪቱ እያደረገች የሚገኘውን ዝግጅት የተመለከተ ሲሆን ምዕራብ አፍሪካዊቷ አገር ለአፍሪካ ዋንጫው ተገቢውን ዝግጅት በማድረግ ሂደት ላይ እንደምትገኝ አሳውቋል።በዝግጅት ግምገማ ቡድኑ ውስጥ የካፍ ምክትል ዋና ፀሐፊ አንቶኒ ባፎይ፣ የውድድር ዳይሬክተሩ ሳምሶን አዳሙ፣ የብሔራዊ ቡድን ውድድሮች ማኔጀሩ ኢስማሊ ዋሊ እንዲሁም የአገልግሎትና የጉዞ ዋና ሃላፊው ራንዳ ሚትዋሊ ተካተው ወደ ስፍራው አቅንተዋል። የግምገማ ቡድኑ ከኮትዲቯር ከተመለሰ በኋላ ለኢንሳይድ ዘጌምስ አስተያየታቸውን የሰጡት ምክትል ዋና ፀሐፊው ባፎይ ምንም እንኳን የኮቪድ-19 ወረርሽኝ የዓለም ሕዝብ የጤና ቀውስ በመሆን ቢቀጥልም ያሳደረውን ጫና ተቋቁማ ኮትዲቯር በጥሩ ሁኔታ ዝግጅቷን እንደቀጠለች ማረጋገጫ ሰጥተዋል። ‹‹ጉብኝቱ በደንብ የታሰበበት ነው፣ በጉዟችንና የውድድሩ አዘጋጆች እየሠሩ በሚገኙት ሥራ ረክተናል›› ያሉት ባፎይ አብዛኛው ለውድድሩ የሚገነቡት ስቴድየሞች በ2021 አጋማሽ እንደሚጠናቀቁ ጠቁመዋል።ይህም አዘጋጆቹ እስከ ውድድሩ ድረስ በቂ ጊዜ እንዳላቸው የሚያሳይ ሲሆን ለሙከራ የተለያዩ ጨዋታዎችን የማካሄድ ዕድልም እንደሚኖራቸው ባፎይ አብራርተዋል። የውድድሩ አዘጋጆች በዕቅዳቸው መሰረት እየተመሩ ትክክለኛ ሰዎችን በትክክለኛው ቦታ በማሰራት ተጨባጭ ነገር እንዳሳዩ የጠቆሙት ባፎይ‹‹ ሁሌም የምናገረው ነገር አንድ ነው፣ ትክክለኛውን ሰው በትክክለኛው ቦታ ማስቀመጥ›› በማለት አዘጋጆቹን አድንቀዋል።ኮትዲቯር እ.ኤ.አ 2014 ላይ የ2021 አፍሪካ ዋንጫን እንድታዘጋጅ ዕድሉን ያገኘች አገር መሆኗ ይታወሳል።ይሁን እንጂ የ2019 አፍሪካ ዋንጫን ለማዘጋጀት ዕድሉ የተሰጣት ሌላኛዋ ምዕራብ አፍሪካዊት አገር ካሜሩን 2018 ላይ ውድድሩን ለማዘጋጀት የምትገነባቸው ስቴድየሞች በመጓተታቸውና በወቅቱ በአገሪቱ የነበረው የፖለቲካ አለመረጋጋት ከደህንነነት አኳያ ስጋት ስለፈጠረ የአዘጋጅነት ዕድሉ ለግብጽ ተሰጥቷል።ካሜሩንም በምትኩ የ2021 አፍሪካ ዋንጫን እንድታዘጋጅና ኮትዲቯር የ2023 አፍሪካ ዋንጫን እንድታሰናዳ ሽግሽግ ተደርጓል። በዚህም መሰረት ኮትዲቯር የአፍሪካን ትልቁ የስፖርት መድረክ በተሳካ ሁኔታ ለማዘጋጀት በቂ ጊዜና ዕድል ማግኘት ችላለች።ውድድሮቹንም ከ2023 ሰኔ ወር መጨረሻ አንስቶ በመዲናዋ አቢጃን፣ ቦኬ፣ ኮርሆጎ፣ ሳን ፔድሮ እና ያሙሱክሮ ከተሞች እንደ ምታከናውን ይጠበቃል።", "passage_id": "949e7538c3640ef47ac37addfddefb84" }, { "passage": "የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በአገር ውስጥ ሊጎች የሚጫወቱ ተጫዋቾች ብቻ የሚሳተፉበትን የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮን ሺፕ / ቻን/ እኤአ በ2020 ለማስተናገድ ከካፍ ኃላፊነቱን ከተረከበ ዓመታት ተቆጥረዋል። ለዚህም ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ በርካታ ስታዲየሞች በሀገሪቱ መገንባታቸው ተቀባይነትን ለማግኘት ዋና ምክንያት ሆኖ ተመዝግቧል። የካፍ ፕሬዚዳንት ማዳጋስካራዊው አህመድ አህመድ ወደ ተመረጡባት ኢትዮጵያ ብቅ ባሉበት ወቅት፤ አገሪቱ በስፖርት መሰረተ ልማት በተለይም ለእግር ኳሱ ዕድገት ከፍተኛ ወጪ መድባ የምታከናውናቸውን የተለያዩ ተግባራት አድንቀዋል። ኢትዮጵያ አህጉራዊ ውድድሮችን የማዘጋጀት ፍላጎቷንም በስኬት የማድመቅ ተስፋ እንዳላት ጭምር ምስክርነት ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ፤ ለቻን አዘጋጅነት ከመታጨቷም በላይ እያደረገች ያለውን ዝግጅት አስመልክቶ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጪ መገናኛ ብዙሀን ሰፊ ዘገባዎች ሲሰራጩ ቆይተዋል። የኋላ ኋላ ግን እየተሰሩ ያሉት ስራዎች ውድድሩን ኢትዮጵያ በብቃት ስለማስተናገዷ ጥያቄን አስነስቷል። በተለይም ሀገሪቱ ለመስተንግዶ የምታደርገው ዝግጅት ሲፈተሽ በሚፈለገው ፍጥነት መጓዝ እንዳልቻለ ታይቷል። ውድድሩን ያስተናግዳሉ ተብለው የተለዩት ስታዲየሞችም አጠቃላይ ለውድድሩ የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች መሟላት አለመሟላታቸው ከካፍ በተላኩ ባለሙያዎች ባሳለፍነው ወር መጀመሪያ ተጎብኝቷል። በጉብኝቱም የተገኘው ውጤት ኢትዮጵያ ውድድሩን ለማዘጋጀት ያደረገችው ጥረት እንዳልተሳካና መከናወን ያለባቸው በርካታ ስራዎች በአግባቡ እንዳልተከናወኑና አጥጋቢ ስራዎችም እንዳልተሰሩ በሪፖርት ቀርቧል። ኢትዮጵያ ያገኘችው የአስተናጋጅነት ዕድል ጥያቄ ውስጥ የወደቀ ቢሆንም በብሄራዊ ፌዴሬሽኑ በኩልም ሆነ ከመንግስት ምንም ዓይነት ማረጋገጫ ሳይገኝ ቆይቷል። ይሁን እንጂ ከሰሞኑ ግን ድብብቆሹ ማክተም እንዳለበት በማመን እውነታው ለህዝብ ይፋ ተደርጓል። በመሆኑም የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የስፖርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ፤ መንግስት ለውድድሩ ዝግጅት አስፈላጊውን ወጪ ለመሸፈን ዝግጁ አለመሆኑን በምክንያትነት ጠቅሰው ኢትዮጵያ በ2020 እንድታሰናዳ በአፍሪካ እግር\nኳስ ኮንፌዴሬሽን የተሰጣትን የአፍሪካ አገሮች ዋንጫ (ቻን) እንደማትቀበል አስታውቀዋል። የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን (ካፍ) ፕሬዚዳንት አህመድ አህመድ የኢትዮጵያ መንግስትን የዘገየ ውሳኔን መሰረት በማድረግ የ2020 የቻን\nዋንጫን በአጭር ዝግጅትና ፍጥነት በተሟላበት ሁናቴ ማስተናገድ ለሚችል አገር ለማስተላለፍ በካይሮ መምከር ግድ ብሏቸዋል። በመሆኑም የአዘጋጅነት ዕድሉን ለምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሩን ተላልፏል። ካሜሩን ውድድሩን በተሻለ ሁኔታ ማስተናገድ እንደምትችል እምነታቸውን ገልፀዋል። በ2022 ለማዘጋጀት እድል\nየነበራት ካሜሩን አሁን ያገኘችውን እድል ተጠቅማ ለውድድሩ ዝግጅቷን አጠናክራ በመቀጠል የተሳካ መድረክ ትፈጥራለች ተብሎ እንደሚጠበቅም አስታውቀዋል። የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ባሳለፈው ውሳኔ መሠረት የአስተናጋጅነት ዕድሉን ከኢትዮጵያ የተቀበለችው ምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሩን በደስታ መረከቧን ቢቢሲ ጽፏል። ከኢትዮጵያ እጅ ያመለጠው የቻን አዘጋጅነት በካሜሩን ቤት እንደ መልካም አጋጣሚ የታየም መሆኑን አስፍሯል። ከኢትዮጵያ መዳፍ ውስጥ ፈለቅቃ ከወሰደችው ከካሜሩን ቤት የ2019 የአፍሪካ ዋንጫን የማስተናገድ ዕድሉን አግኝታ የነበረ ቢሆንም፤ በተቀመጠው ጊዜ\nዝግጅቷን የማጠናቀቅ አቅሟ ጥያቄ ውስጥ መግባቱን ተከትሎ ለግብፅ መሰጠቱ አስታውሶ፤ በከፍተኛ ደስታ አጋጣሚውን ለመጠቀም የምትሰራ መሆኑን የሚያሳይ አስተያየት መሰጠቱንም አስነብቧል። የአፍሪካ አገሮች\nዋንጫ (ቻን) በአገር\nውስጥ ሊግ ብቻ የሚጫወቱ\nተጫዋቾችን ብቻ የሚያሳትፍ\nየውድድር መድረክ ሲሆን፤\nበሁለት ዓመት አንዴ\nይደረጋል። እኤአ 2009 የተጀመረው\nቻን የመጀመሪያዋ ዋንጫ\nኮትዲቯር ስታዘጋጅ፤ 2ኛውና\nበ2011 የተካሄደውን ደግሞ\nሱዳን አዘጋጅታለች። በ2014 ደቡብ\nአፍሪካ ሶስተኛውን ስታስተናግድ፤\nበ2016 ሩዋንዳ 4ኛውን\nአዘጋጅታለች። በ2018 በሞሮኮ\nአዘጋጅነት ለ5ኛ ጊዜ\nየተካሄደ ሲሆን፤ 6ኛውና\nበ2020 የሚካሄደው የቻን\nዋንጫ ደግሞ ወደ ምዕራብ\nአፍሪካ በመጓዝ ካሜሩን\nቤት መግባቱ ተረጋግጧል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 9/2011", "passage_id": "65d2f2d45a66722aee9fbc21e9dbdac8" }, { "passage": "በውድድር ጊዜው እንዲሁም በተሳታፊ ሃገራቱ ብዛት ላይ ለውጥ በማድረግ እየተካሄደ ያለው 32ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ዛሬ አራተኛ ቀኑ ላይ ደርሷል። ዛሬ በሁለት ምድቦች ጨዋታዎች የሚከናወኑ ሲሆን፤ ምድብ አራት ኮትዲቯርን ከደቡብ አፍሪካ ያገናኛል። ከምድብ አምስት ደግሞ ቱኒዚያ ከአንጎላ እንዲሁም ማሊ ከሞሪታኒያ የሚጫወቱ ይሆናል። ከምድብ\nአራት ኮትዲቯርና ደቡብ አፍሪካን ለሚያገናኘውም ጨዋታ ከፍተኛ ግምት ተሰጥቷል። ይህንን ውድድር ለማዘጋጀት ፍላጎት አሳይታ ያልተሳካላት ደቡብ አፍሪካ በአፍሪካ ዋንጫ መድረክ ስኬትን ያስመዘገበችው አንድ ጊዜ ብቻ ነው። እአአ በ1996 ባስተናገደችው ውድድር ዋንጫውን በሃገሯ ካስቀረች ወዲህም ሻምፒዮን ልትሆን አልቻለችም። ዝሆኖቹ በበኩላቸው እአአ በ1992ቱ የሴኔጋል እንዲሁም እአአ በ2015ቱ የኢኳቶሪያል ጊኒ የአፍሪካ ዋንጫዎች ላይ አሸናፊ በመሆን ከተጋጣሚያቸው የተሻለ ውጤት አላቸው። ሁለቱ ቡድኖች\nከዚህ ቀደም የተገናኙባቸው ሁለት ጨዋታዎች በአቻ ውጤት እንዲሁም በደቡብ አፍሪካ የበላይነት የተጠናቀቀ ቢሆንም፤ የዚህ ጨዋታ የአሸናፊነት ቅድመ ግምት ግን ወደ ዝሆኖቹ አድልቷል። የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ በካይሮ በሚገኘውና 30ሺ ሰዎችን በሚይዘው አልሰላም ስታዲየም የሚከናወን ይሆናል። በአውሮፓ\nክለቦች በሚጫወቱ ወጣቶች የተዋቀረው የኮትዲቯር ብሄራዊ ቡድን ዘንድሮ ለዋንጫ ይደርሳል የሚል ቅድመ ግምት ባያገኝም ጠንካራ ከሚባሉት ቡድኖች መካከል ይጠቀሳል። የመጨረሻ የወዳጅነት ጨዋታቸውን ከዩጋንዳ ጋር ያደረገው ቡድኑ 1ለ0 በሆነ ውጤት ነበር የተረታው። ሆኖም በዛሬው ጨዋታ አሸናፊ ለመሆን የሚጫወቱት ዝሆኖቹ ዋንጫውን ወደ ሃገራቸው ለመመለስ አቅደው ተሳትፏቸውን እያደረጉም ይገኛሉ። ባፋና ባፋናዎች\nእአአ 2015 እና 2017 የአፍሪካ ዋንጫዎች ላይ ዝቅተኛ ውጤት ያስመዘገቡ መሆኑን ተከትሎ በዚህ ውድድር የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የሚጫወቱ መሆኑን የቡድኑ አባላት ይገልጻሉ። ሞሮኮ፣ ኮትዲቯርና ናሚቢያ ከተደለደሉበት ምድብ የሚገኘው ቡድኑ የረጅም ጊዜ የዋንጫ ረሃባቸውን ለማስታገስ ወደ ግብፅ እንደተጓዙም አስታውቀዋል። በቤልጂየም በሚገኘው ክለብ የሚጫወተው ፔርሲ ታኡ ከቢቢሲ ባደረገው ቆይታ፤ ምድቡ ጠንካራ የሚባል ቢሆንም ቡድናቸው ግን ከዚህ ቀደም ካስመዘገበው ውጤት የተሻለ ነገር ለማስመዝገብ የሚጫወት መሆኑን ጠቁሟል። አሰልጣኝ\nስትዋርት ባክስተር ቡድኑን ከተቀላቀሉ በኋላም በቡድኑ የራስ መተማመን ስሜት እንደጎለበተም ተጫዋቹ ጠቅሷል። እኛም የአሰለጣጠኑን እንዲሁም አጨዋወቱን ተከትለን በመጫወት የተሻለ ውጤት እንደምናስመዘግብ እናምናለን። እርሱ ቡድኑን ከያዘ ጀምሮም ቡድኑ ለውጥ በማሳየት ላይ ይገኛል ሲልም አክሏል። በምድብ\nአምስት ሁለት ጨዋታዎች የሚደረጉ ሲሆን፤ ቱኒዚያ ከአንጎላ እንዲሁም ማሊ ከሞሪታኒያ ይገናኛሉ። በዚህ ምድብ የተሻለ ግምት የሚሰጠው ብሄራዊ ቡድንም የቱኒዚያ ነው። የካርቴጅ ንስሮች በሚል መጠሪያ የሚታወቀው ቡድኑ እአአ በ2004 ዋንጫውን በሃገሩ ማስቀረቱ የሚታወስ ነው። አንጎላ በመድረኩ የሚጠቀስ ውጤት የሌላት ከመሆኑ ባሻገር በምድቡ አስፈሪ ሊባል የሚችል ቡድን ባለመኖሩ ቱኒዚያ በቀላሉ ከምድቧ ማለፍ እንደምትችል ይጠበቃል። በፊፋ ማስጠንቀቂያ\nሲሰነዘርባት የቆየችው ማሊም በመድረኩ አዲስ ገቢ የሆነችውን ሞሪታኒያን ታስተናግዳለች። እአአ 1972 ለፍጻሜ የደረሰችው እንዲሁም 2012 እና 2013 ሦስተኛ በመሆን ውድድሯን ያጠናቀቀችው ማሊ አዲሲቷን ሃገር በቀላሉ ልትረታ እንደምትችልም ይገመታል። በነገው ዕለትም የምድብ ስድስቶቹ ሻምፒዮናዋ ካሜሩን ከጊኒ-ቢሳዋ እና ጋና ከቤኒን የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል።አዲስ ዘመን ሰኔ 17/2011 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "48e3deeca13a23c29b78b84459da045a" }, { "passage": "ሞሮኮ የቶታል አፍሪካ ሃገራት ቻምፒዮንሺፕ (ቻን) ያሸነፈች የመጀመሪያዋ አዘጋጅ ሃገር ሆናለች፡፡ ሞሮኮ በፍፃሜው ናይጄሪያን 4-0 በሆነ ሰፊ ውጤት በመርታት ነው የውድድሩን ዋንጫ ያነሳችው፡፡ የፍፃሜው ጨዋታ ጋምቢያው ባካሪ ፓፓ ጋሳማ የመራ ሲሆን ኢትዮጵያዊው አርቢትር ባምላክ ተሰማ አራተኛ ዳኛ ነበር፡፡የሞሮኮው አሰልጣኝ ጀማል ሰላሚ በ4-2-3-1 የጨዋታ አቀራረባቸው በፍፃሜም የተገበሩ ሲሆን ለማጥቃት በማሰብ የናይጄሪያው አሰልጣኝ ሳሊሱ የሱፍ 4-3-3 ተጠቅመው ነበር፡፡ ሆኖም ካዛብላንካ በሚገኘው ስታደ መሃመድ አምስተኛ በተደረገው ጨዋታ ሞሮኮ ተጋጣሚዋ ላይ የጨዋታ ብልጫን ወስዳለች፡፡ ዛካሪያ ሃድራፍ ሞሮኮን በ45ኛው ደቂቃ መሪ ሲያደርግ አመቻችቶ ያቀበለው አብደልጃሊል ጅቢራ ነበር፡፡ ሱፐር ኢግልሶች ከእረፍት መልስ ኢንጂ ሞሰስ በሁለት ቢጫ ከሜዳ በመውጣቱ ይበልጥ ጨዋታው እንዲከብዳቸው አድርጓል፡፡ የዋይዳድ ካዛብላንካው የአጥቂ አማካይ ዋሊድ ኤል ካርቲ በ61ኛው ደቂቃ መሪነቱን ወደ ሁለት ሲያሰፋ ከሶስት ደቂቃዎች በኃላ ሃድራፍ ሶስተኛው አክሏል፡፡ ልማደኛው አጥቂ እና ለውድድሩ ፍፁም ልዩ የነበረው አዩብ ኤል ካቢ በ73ኛው ደቂቃ የማሳረጊያ ግቡን ከመረብ አዋህዷል፡፡ቅዳሜ ሱዳን ሊቢያን በመለያ ምት 4-2 በማሸነፍ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቅ ችላለች፡፡ አንድ አቻ በተጠናቀቀው መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ግዜ ሱዳን በዋለልዲን መሃመድ የ8ተኛ ግብ ለረጅም ግዜ ስትመራ ቆይታለች፡፡ በሁለተኛው አጋማሽ ተጋጣሚያቸውን ላይ ጫናን አሳድረው የተጫዋቱት ሊቢያዎች የሱዳኑ ግብ ጠባቂ አክራም ኤል ሃዲ ያመለጠውን ኳስ ሳልም አብሎ በግንባሩ ገጭቶ በማስቆጠር ሃገሩን በ84ኛው ደቂቃ አቻ አድርጓል፡፡ አሸናፊው ለመለየት በተሰጠው የመለያ ምት በሱዳን በኩል ሙሃናድ ጣሂር ኦስማን፣ አታሂር ኤል-ጣሂር፣ አህመድ አደም መሃመድ እና መአዝ አብደልራህማን ሲያቆጥሩ ሙፍታህ ታክታክ እና አብደልሰላም አል-ፊቶሪ በሊቢያ በኩል የተሰጠውን የመለያ ምት ወደ ግብነት ቀይረዋል፡፡ ነገር ግን ኤል መህዲ አል ማስሪ እና ሳለም አብሎ መለያ ምቶቻቸውን አምክነዋል፡፡ የሱዳኑ ግብ ጠባቂ ኤል ሃዲ የአብሎን ምት በማዳን ሃገሩን አሸናፊ አድርጓል፡፡አዩብ ኤል ካቢ የውድድሩ ኮከብ ግብ አስቆጣሪ (በ9 ግቦች እንዲሁም) እና ተጫዋቾች ሆኖ መርጧል፡፡ ለአምስተኛ ግዜ በተዘጋጀው ቻንም እንደቀደሙት ውድድሮች ሁሉ አዲስ አሸናፊ ከመገኙቱ አልፎ አዘጋጅ ሃገር ለመጀመሪያ ግዜ ዋንጫውን አሸንፏል፡፡ በካዛብላንካ፣ ታንገ፣ ማራካሽ እና አጋድር ጨዋታዎቹን ሞሮኮ በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ ችላለች፡፡ያለፉት 100 ቀናት ለሞሮኮ ልዩ ነበሩ ማለት ይቻላል፡፡ የሞሮኮ ክለብ የሆነው ዋይዳድ ካዛብላንካ የቶታል ካፍ ቻምፒየንስ ሊግን ከ25 ዓመታት በኃላ ሲያሸንፍ የአትላስ አንበሶቹ ኮትዲቯርን ከሜዳቸው ውጪ በመርታት ከ1998 ወዲህ ለመጀመሪያ ግዜ የዓለም ዋንጫ ተሳትፏቸውን አረጋግጠዋል፡፡ ከዚህም በላይ በጥር ወር የ2026ቱን የዓለም ዋንጫ ለማስተናገድ ጥያቄ ካቀረቡ ሃገራት መካከልም ናቸው፡፡ኢትዮጵያ በ2020 የሚስተናገደውን ቻን ለማስተናገድ የካፍ አርማን ከፕሬዝደንት አህመድ አህመድ እጅ የፌድሬሽኑ ፕሬዝደንት ጁኒይዲ ባሻ ተቀብለዋል፡፡", "passage_id": "e70dea75fdded3b1899240649bd095f4" }, { "passage": "ሰሜን\nአፍሪካዊቷ አገር ሞሮኮ በቅርቡ ለምታዘጋጀው መላ አፍሪካ ጨዋታዎች ለመሳተፍ ኢትዮጵያ በተለያዩ ብሔራዊ ስፖርት ፌዴሬሽኖቿ አማካኝነት ዝግጅት ከጀመረች ሰንብታለች በተለይም ዓመቱን ሙሉ በመርሐግብር መሰረት የሊግ ውድድሮችን የማያደርጉና የማጣሪያ ውድድር የማያስፈልጋቸው ብሔራዊ ፌዴሬሽኖች ባለፈው ወር የኢትዮጵያ ቻምፒዮናን በተናጠል በማካሄድ ወደ ሞሮኮ ይዘው የሚጓዟቸውን የብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች መርጠው በዝግጅት ላይ ናቸው በዓመታዊ መርሐግብር የተለያዩ ውድድሮችን የሚያካሂዱ ፌዴሬሽኖች የብሔራዊ ቡድን\nተጫዋቾችን ለመምረጥ ስለማይቸገሩ የውድድሮች ቀን ሲቃረብ ዝግጅት መጀመራቸው የተለመደ ነው ከእነዚህ ብሔራዊ ፌዴሬሽኖች መካከል የኢትዮጵያ ቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽን አንዱ ነው ፌዴሬሽኑ ለመላ አፍሪካ ጨዋታ ዝግጅቱን ለመጀመር የማጣሪያ ውድድር ማድረግ ይጠበቅበታል ለዚህም እቅድ አውጥቶ የሚያስፈልገውን በጀት እንዲፈቀድለት ለሚመለከታቸው የኢትዮ ጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴና የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን ያቀረበው ጥያቄ እስካሁን ምላሽ እንዳላገኘ የፌዴሬሽኑ የፅሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ይመር ሃይሌ ለአዲስ ዘመን አስታውቀዋል እንደ\nአቶ ይመር ገለፃ፣ የቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽን የመላ አፍሪካ ጨዋታን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴና ከፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን ጋር ስብሰባ ባደረገበት ወቅት ስፖርቱ በአገሪቱ ሰፊ እንቅስቃሴ እየተደረገበት የሚገኝ በመሆኑ ኢትዮጵያ በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች ከምትሳተፍባቸው ስፖርቶች አንዱ ሆኖ ተመርጧል በተመረጠበት ማግስትም የውድድሩ ቀን ባይደርስም የፌዴሬሽኑ የቴክኒክ ኮሚቴ አሰልጣኞችን መርጦ እንዲያሳውቅ በማድረግ ማስታወቂያ አውጥቶ አሰልጣኞች ተቀጥረዋል አሰልጣኞቹም ተጫዋቾች እንዲመርጡና እቅዳቸውን እንዲያቀርቡ ተደርጓል ፌዴሬሽኑ በዚህ ሂደት ውስጥ እያለ መላ አፍሪካ ጨዋታ ላይ ከመሳተፉ በፊት የአፍሪካ ዞን አምስት የቅርጫት ኳስ የማጣሪያ ውድድር መሳተፍ ስለሚኖርበት ከዞን አምስት በደብዳቤ ጥያቄ መጥቶለታል የዞን አምስት የማጣሪያ ውድድሩ ከአስር ቀናት በኋላ ተጀምሮ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ሲሆን በዚህ ውድድር ለመሳተፍ ፌዴሬሽኑ እቅዱን ከዞን አምስት ከመጣለት ደብዳቤ ጋር አያይዞ የሚያስፈልገውን ወጪ እንዲሸፍኑ የውድድሩ ባለቤቶች ለሆኑት የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴና የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን አቅርቧል ያም ሆኖ ከሚመለከታቸው አካላት እስካሁን ምንም አይነት ምላሽ እንዳላገኘና የተመረጡት አሰልጣኞችም ተጫዋቾች መልምለው ዝግጅት ለማድረግ እንዳልቻሉ አቶ ይመር ይናገራሉ የማጣሪያ ውድድሩ ሊጀመር ጥቂት ቀናት በቀሩበት በዚህ ወቅት የኦሊምፒክ ኮሚቴና የስፖርት ኮሚሽን አገርን ወክለው በማንኛውም ውድድር ላይ የሚሳተፉ ብሔራዊ ቡድኖችን ወጪ መሸፈን እንዳለባቸው አቶ ይመር ያብራራሉ ‹‹በፌዴሬሽኑ በኩል የምናደርገው ይሄ ነው፣አገራዊ ውድድሮች ላይ ስንሳተፍ ወጪውን መሸፈን ያለባቸው እነዚህ አካላት ናቸው፣ ተተኪ ወጣቶችን በስፖርቱ ለማግኘትም ሆነ አገር ለማስጠራት እንዲሁም ክለቦች የሚጠናከሩበትን መን ገድ ለመፍጠር እንደ መላ አፍሪካ አይነት ጨዋታዎች ላይ መሳተፍ አለብን፣ ካለበለዚያ ፌዴሬሽኑ መኖሩ ትርጉም የለውም›› ይላሉ ፌዴሬሽኑ ደብዳቤ አስገብቶ እስካሁን መልስ አላገኘም ማለት የሚያዘጋጃቸው ብሔራዊ ቡድኖች እንዳይወዳደሩ ማለት ነው ሲሉ ያስረዳሉ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር አቶ ታምራት በቀለ በበኩላቸው፤ ብሔራዊ ፌዴሬሽኖች አገርን ወክለው በዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ ለመወዳደር በቅድሚያ የማጣሪያ ውድድሮችን በራሳቸው ማድረግ እንዳለባቸው ይናገራሉ ማጣሪያውን ማለፍ ከቻሉ ግን ሙሉ ሃላፊነቱን ኦሎምፒክ ኮሚቴና ስፖርት ኮሚሽን ይረከባሉ እነዚህ ፌዴሬሽኖች የማጣሪያ ውድድሮችን በሚያደርጉበት ወቅት አቅም ካነሳቸው ድጋፍ የሚጠይቁበት ሁኔታ መኖሩን ያመለክታሉ ከቅርጫት ኳስ ጋር በተያያዘ መላ አፍሪካ ጨዋታዎች ላይ ሦስት በሦስት በሚባለው ውድድር ለመሳተፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እቅድ ውስጥ መካተቱትን ይጠቅሳሉ ቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽን የዞን አምስት ውድድርን በተመለከተ ያነሳው ነገር እንደሌለም ይጠቁማሉ ወደ ፊት ድጋፍ የሚጠይቁ ከሆነ ግን በኮሚቴው ሥራ አስፈፃሚ በኩል የሚታይ መሆኑን ያስገነዝባሉየፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን የኮሙ ኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ናስር ለገሰ እንደሚሉት፤ ብሔራዊ ፌዴሬሽኖች ለዓለም አቀፍ ውድድሮ በሚያደርጉት የማጣሪያ ጨዋታዎች ኦሎምፒክ ኮሚቴም ይሁን ስፖርት ኮሚሽን ወጪያቸውን ይሸፍናል ተብሎ የተቀመጠ ነገር የለም ፌዴሬሽኖች ከኮሚሽኑ የሚያገኙትን የድጎማ በጀት አብቃቅተው የሚጠቀሙበት ሁኔታ አለ እጥረት ሲገጥማቸው ግን ተጨማሪ ድጋፍ ይጠይቃሉ ጥያቄው አሳማኝና ውጤት ይመዘገብበታል ተብሎ ሲታመንም ተጨማሪ ድጎማ ይደረጋል ፌዴሬሽኖች ስፖርቱን እንዲመሩ እስከ ተቋቋሙ ድረስ በጀቱንም መምራት ይኖርባቸዋል አገርን ወክለው ሲወዳደሩ ሃላፊነቱን መውሰድ አለባቸው በሌላ በኩል ግን እግር ኳስ፣ አትሌቲክስና ሌሎችም አገርን ወክለው ሲወዳደሩ በራሳቸው በጀት ነው የሚንቀሳቀሱት ‹‹ስፖርት ኮሚሽን ሃያ ዘጠኙም ፌዴሬሽኖች ውጪ ሄደው የማጣሪያ ውድድር ሲያደርጉ ወጪ የቻልንበት አጋጣሚ የለም›› ያሉት አቶ ናስር፣ ማጣሪያውን ማለፋቸው ሲረጋገጥ ግን ከዝግጅት ጀምሮ ሙሉ ድጋፍ እንደሚ ደረግላቸው ይገልፃሉ የማጣሪያ ውድድር የማያስፈልጋቸው ነገር ግን ውጤት ይመጣባቸዋል ተብሎ የታመነባቸው እንደ አትሌቲክስ፣ ቦክስና ወርልድ ቴኳንዶ አይነት ስፖርቶች ለመላ አፍሪካ ጨዋታዎች ሆቴል ገብተው ዝግጅት እያደረጉ ይገኛሉ ኦሊምፒክ ኮሚቴና ስፖርት ኮሚሽን የማጣሪያ ውድድር ማድረግ የሚጠበቅባቸው የኳስ ስፖርቶች ማጣሪያውን ማለፋቸውን ካረጋገጡ በኋላ ወደ ሆቴል ገብተው ዝግጅት ያደርጋሉ የሚል እምነት አላቸው በጉዳዩ ላይ አንድ ወጥ የሆነ መተዳደሪያ ደንብ ባለመኖሩ ሦስቱ አካላት ማለትም ፌዴሬሽኑ፣ ኮሚቴውና ኮሚሽኑ የጋራ ስምምነት ላይ በቅርብ ቀን መድረስ ይችላሉ ማለት ከባድ ነው እነዚህ አካላት በቅርብ ቀን ተግባብተው መስራት ቢችሉ እንኳን በቅርጫት ኳስ የማጣሪያውን ጨዋታ ለማድረግ ከቀረው ቀን አንፃር የማይቻል ነው ቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽን ከኦሊምፒክ ኮሚቴና ስፖርት ኮሚሽን የበጀት ድጋፉን በቅርብ ቀን አግኝቶ፣ አሰልጣኞች በቀሪው አስር ቀን ውስጥ ተጫዋች መልምለውና ተዘጋጅተው በማጣሪያ ውድድሩ ምን አይነት ውጤት ሊያስመዘግቡ ይችላሉ? የሚለው የስፖርት ቤተሰቡ ጥያቄ ነው የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት\nዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ\nየኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ\nፕሬዚዳንት በመሆናቸው ጉዳዩን\nበቅርበት ያውቁት እንደሆነ\nበስልክ ለማነጋገር ብንሞክርም\nሊሳካልን አለመቻሉን መግለፅ\nእንወዳለንአዲስ ዘመን ቅዳሜ ሰኔ 8/2011", "passage_id": "38b1b6c715f12794fec8e2adb8be35e8" } ]
a9d9b59c6268b73757d0058a47ba97a5
ed1349c7a3a3792606c14c89ef1f693d
የለንደን ማራቶን ሊሰረዝ ይችላል
በቀጣዩ መስከረም ሊካሄድ ቀጠሮ የተያዘለት ‹‹የግሬት ኖርዝ ረን›› ግማሽ ማራቶን ውድድር መሰረዙን ተከትሎ ጥቅምት ላይ እንደሚካሄድ የተነገረው የለንደን ማራቶንም ሊሰረዝ እንደሚችል ጥርጣሬ ፈጥሯል:: በእንግሊዝ አገር ከሚካሄዱ የጎዳና ላይ ውድድሮች መካከል ትልቁን ስፍራ የሚይዙት ሁለቱ የማራቶንና ግማሽ ማራቶን ውድድሮች ከኮሮና ቫይረስ(ኮቪድ 19) ወረርሽኝ ስጋት ጋር በተያያዘ ቀደም ብሎ ከሚካሄዱበት ወቅት እንዲራዘሙ ተደርጎ በቀጣዩ መስከረምና ጥቅምት ወር ሊካሄዱ ቀጠሮ ተይዞ ነበር፡፡ ዘንድሮ አርባኛ ዓመቱን የያዘው ‹‹ግሬት ኖርዝ ረን›› የግማሽ ማራቶን ውድድር ከመሰረዙ አስቀድሞ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ስልሳ ሺ ተሳታፊዎችን በመያዝ በብሪታኒያ ትልቁ የጎዳና ላይ ውድድር መሆን ችሏል፡፡ ከሰላሳ አንድ ሚሊዮን ዶላር በላይ ከውድድሩ በመሰብሰብ ለበጎ አድራጎት እንዲውል ለማድረግ ታስቦ የነበረ ቢሆንም በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ሳቢያ እንዳልተቻለ አዘጋጆቹ ገልፀዋል፡፡ ይህንንም ተከትሎ ውድድሩ ሊሰረዝ እንደቻለ የሮይተርስ ዘገባ ያመለክታል:: ውድድሩ ለኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የሚደረገውን ጥንቃቄ ከግምት በማስገባት እንዲካሄድ አዘጋጆቹ ከጤና ባለሙያዎች እንዲሁም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀናጅተው በመስራት ጥረት ቢያደርጉም እንዳልተሳካ አሳውቀዋል፡፡ በዚህ ታላቅ ውድድር ባለፈው ዓመት እንግሊዛዊው የኦሊምፒክ ጥምር የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት የሆነው አትሌት ሞሐመድ ፋራህ ለስድስተኛ ተከታታይ ጊዜ ሲያሸንፍ ኬንያዊቷ የማራቶን ባለክብረወሰን ብሪጊድ ኮስጌ የውድድሩን ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር ማሸነፏ ይታወሳል፡፡ ይህ የግማሽ ማራቶን ውድድር መሰረዙን ተከትሎ ጥቅምት ላይ ሊካሄድ የታሰበው ትልቁ የለንደን ማራቶንም ሊሰረዝ እንደሚችል ተገምቷል፡፡ የለንደን ማራቶን እንደወትሮው ቢሆን ባሳለፍነው ሚያዚያ ላይ የዓለማችን የርቀቱ ኮከቦችን ያፋልም ነበር፡፡ በተለይም በወንዶች የማራቶን ባለክብረወሰኑ ኬንያዊው ኢሉድ ኪፕቾጌና የርቀቱ ሁለተኛው ፈጣን አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በዚህ ውድድር የሚያደርጉት ፉክክር በብዙዎች ዘንድ በጉጉት ሲጠበቅ ነበር፡፡ ውድድሩ መሰረዝ አለመሰረዙን ግን አዘጋጆቹ የገለፁት ነገር የለም፡፡ በርካታ የማራቶን የዓለም ክብረወሰኖች የሚ ሻሻሉበት የበርሊን ማራቶን በዚህ ዓመት የመሰረዝ ወይም የመራዘም እድል ያልገጠመው ብቸኛው ውድድር ነው ማለት ይቻላል፡፡ ይህ ታላቅ የማራቶን ውድድር የኮሮና ቫይረስ በዓለም ላይ ከመከሰቱና ከመስፋፋቱ አስቀድሞ መስከረም ወር ላይ በመካሄዱ የሌሎቹ ታላቅ ውድድሮች እጣ ፋንታ ሳይገጥመው ቀርቷል፡፡ ያም ሆኖ የኮሮና ቫይረስ ስርጭት እስካሁን የሚያቆመው ባለመኖሩና ወደ ፊትም መፍትሄ ማግኘቱ አጠራጣሪ እየሆነ በመምጣቱ በቀጣዩ መስከረም የበርሊን ማራቶን የመካሄዱ ጉዳይ አጠራጣሪ ሆኗል፡፡ የውድድሩ አዘጋጆች ባለፈው ወር እንደጠቆሙትም፣ ውድድሩን በተለመደው ወቅት ለማካሄድ እስካሁን ውሳኔ ላይ መድረስ አልቻሉም፡፡ ውድድሩን ለማካሄድ ወይም ለማራዘም ውይይት እየተደረገ ሲሆን ውሳኔ ላይ ለመድረስ ጊዜ እንደሚያስፈልጋቸው አሳውቀዋል፡፡ የጀርመን መንግስት በኮሮና ቫይረስ ስጋት እስከ መጪው ጥቅምት ወር መጨረሻ ከአምስት ሺ ሰው በላይ የሚሰበሰብባቸው ማንኛቸውም መርሐግብሮች ማገዱን ተከትሎ የውድድሩ አዘጋጆች ውሳኔ ላይ ለመድረስ እንደተቸገሩ ጠቁመዋል፡፡ እንደ በርሊን ማራቶን ሁሉ ዋነኞቹ የዓለማችን የማራቶን ውድድሮች ከሆኑት አንዱ የቦስተን ማራቶንም በተመሳሳይ ምክንያት መካሄድ ከነበረበት ወቅት የመራዘም እድል እንደገጠመው ይታወሳል፡፡የበርሊን ማራቶን አዘጋጆች ውድድሩ ካለው ስፋትና ከሚያሳትፈው የሰው ብዛት አኳያ የሚካሄድበት እድል መኖር አለመኖሩን በማጥናት ላይ የሚገኙ ሲሆን ውሳኔ ላይ ለመድረስም የተወሰነ ጊዜ እንደሚያስፈልጋቸው አሳውቀዋል፡፡ ለዚህም የውድድሩ አዘጋጆች አሁን ላይ በቫይረሱ ስጋት የተነሳ በሙሉ ኃይላቸው ተገናኝተው መስራት አለመቻላቸው አንዱ እንቅፋት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በርካታ የዓለም ክብረወሰኖች የሚመዘገቡበት የበርሊን ማራቶን 2018 ላይ ኬንያዊው ኢሉድ ኪፕቾጌ 2፡1፡39 የሆነ አዲስ የዓለም ክብረወሰን በርቀቱ እንዳስመዘገበበት ይታወሳል፡፡ ባለፈው መስከረም ደግሞ ቀነኒሳ በቀለ ይህን ክብረወሰን ለማሻሻል በሁለት ሰከንድ የዘገየ ሰዓት ማስመዝገቡ አይዘነጋም፡፡ አዲስ ዘመን ሰኔ 11/2012 ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=34601
[ { "passage": "ነገር ግን የድል ዜናው ቦታውን ቀይሮ በተገናኙባቸው ውድድሮች ኬንያዊው አትሌት የርቀቱ ፈጣን ተሰኘ፡፡ በጉዳት ምክንያት ከውድድር ርቆ የቆየው የሃገር አቋራጭ ንጉሱ ቀነኒሳም በርቀቱ ያለውን ተስፋ ከማሳየት በቀር ለሁለት ዓመታት ውጤት አላስመዘገበም ነበር፡፡ እአአ 2016 ግን የፓሪስ ማራቶንን በማሸነፍ በጠባብ የደቂቃዎች ልዩነት ሁለተኛው የርቀቱ ፈጣን አትሌት ለመሆን ችሏል፡፡ በቀጣዩ ዓመት በለንደን ማራቶን ያስመዘገበው ሰዓት ከፈጣኑ የዘገየ መሆኑ በርቀቱ ያለውን ተስፋ አጠራጣሪ አድርጎት ነበር፡፡ ምክንያቱ ደግሞ በ5 እና 10ሺ ሜትር የሶስት ጊዜ የኦሊምፒክ ቻምፒዮኑ ቀነኒሳ የባት ፣ የቁርጭምጭሚት፣ ተረከዝ፣ ሽንጥ እና ቋንጃ ጉዳቶች ጋር ትግል ሲያደርግ በመቆየቱ ነው፡፡ የአትሌቱ የረጅም ጊዜ ማኔጀር ጆስ ሄርሜንስም ስለ ቀነኒሳ ከሰሞኑ በዓለም አትሌቲክስ ድረ ገጽ አጠቃላይ መረጃ ሰጥቷል፡፡ አሰልጣኙ አትሌቱ የነበረበትን ሁኔታ ሲገልጽም ‹‹በአዲስ አበባ ያለው ህይወቱ ውጥረት የበዛበት በመሆኑ ለልምምድ እንዲሁም ለማገገም የተመቸ ጊዜ የለውም፡፡ ከሩጫው ባሻገር በቢዝነስ ስራዎችም ላይ ተሳታፊ እና የልጆች አባት እንደመሆኑም አብዛኛውን ጊዜውን በዚህ ያሳልፋል፡፡ በዚህ ሂደትም ጊዜውን ያለእረፍት እያሳለፈ ነበር›› ሲልም ይገልጻል፡፡ ‹‹የማራቶን ሁለተኛውን ሰዓት ካስመዘገበበት የበርሊን ማራቶን ሁለት ወራት አስቀድሞም ለጥቂት ጊዜ ከውጥረት መላቀቅ እንዳለበትና ጥሩ የማገገሚያ ጊዜ እንደሚኖረው አስረዳነው›› ይላል ማኔጀሩ፡፡ ይህን ማሳመን ቀላል ባይሆንም በመጨረሻ ግን ከቤተሰቦቹ ተለይቶ ለሁለት ወራት በሆላንድ በምትገኝ አንዲት ከተማ ለማሳለፍ የግድ ሆነ፡፡ አትሌቱም የሩጫ ህይወቱን ከማቋረጡ አስቀድሞ በማራቶን አንድ ታሪክ ማስመዝገብ የሚፈልግ በመሆኑ ከጉዳቱ በቶሎ አገግሞ ወደ ልምምድ እንዲገባ የቻሉትን ሁሉ ማድረጋቸውን ማኔጀሩ ያስታውሳል፡፡ ክብደቱ በመጨመሩም በሆላንዳዊው የስነ ምግብ ፕሮፌሰር አርማንድ ቤቶንቬል እገዛ የአመጋገብ ሁኔታውን ማስተካከል ተችሏል፡፡ በአዲስ አበባ ቆይታው የአመጋገብ ሁኔታው የተጠና አልነበረም፤ አብዛኛውን ጊዜ የሆቴል ምግብ የሚያዘወትር ከመሆኑ ጋር በተያያዘ እንደ አትሌት በሚጠበቅበት ሁኔታ ላይ አልነበረም፡፡ በባለሙያዎቹ አማካኝነትም ፕሮቲን፣ ሩዝ እና ድንች በተሻለ ሁኔታ እንዲያገኝ ተደርጓል፡፡ ስልጠናውንም በአግባቡ ነበር የሚከታተለው፡፡ ወደ ዋናው ስልጠና ከገባም በኃላ በሳምንት እስከ 50 ኪሎ ሜትር በመሸፈን ጥሩ የሚባል ጊዜ አሳልፏል፡፡ የመልካም አስተሳሰብ ባለቤት በመሆኑም ከታሰበው በተሻለ ፍጥነት መሻሻል ሊያሳይ ችሏል፡፡ ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በኃላም በአሰልጣኝ ሃጂ አዲሎ ስር በመሆን ስልጠናውን ሳያዘባ ሲሰራ ስለ ነበር በጥቂት ጊዜ ወደ ቀደመ አቋሙ ሊመለስ ችሏል፡፡ ዝግጅቱ በርቀቱ ከፈጣኖች ተርታ ከሚሰለፈውና ከዓለም ቻምፒዮኑ አትሌት ሌሊሳ ዴሲሳ ጋር መሆኑም የተሻለ ነገር አስገኝቶለታል የሚል እምነት እንዳላቸው ኸርሜንስ ይናገራሉ፡፡ በእርግጥ ስልጠናውን በሚያደርግበት ወቅት አዲስ አበባ ዝናባማ የአየር ሁኔታ ነበራት፤ ይህም አስቸጋሪ ስለነበር ስልጠናውን በበፊቱ ልክ ማከናወን አንዳልተቻለም አልዘነጉም፡፡ ‹‹ውድድሩ ሲቃረብም በአትሌቱ ብቃት ሁላችንም ከመተማመን ላይ ደርሰን ነበር፡፡ እኛ በስልጠናው ወቅት ሲያሳይ በቆየው ብቃት ከፍተኛ ተስፋ ስንሰንቅ እርሱ ደግሞ በጥሩ ውጤት ማጠናቀቅን አላማው አድጎ ነበር፡፡ ከሚታመነው በላይ ጠንካራ አትሌት ነው፤ በውድድሩ ላይ ኬንያዊው አትሌት ከያዘው ክብረወሰን በሁለት ሰከንዶች ብቻ ዘግይቶ ገብቷል›› በማት አ ድ ና ቆ ታ ቸ ው ን ይገልፃሉ፡፡ እውቅና ያልተሰጠውና ሰው ሰራሽ በሆነ መንገድ ቢሆንም የሰው ልጁ 42ኪሎ ሜትሮችን ከ2ሰዓት በታች መግባት ይችላል የሚለው ሙከራ በኬንያዊው ኪፕቾጌ እውን ከተደረገ በኃላም የስፖርት ቤተሰቡ ጥያቄ ተመሳሳይ ሆኗል፡፡ ‹‹ቀጣዩ ምንድነው?›› የሚለው ፤ ምላሹም ቀነኒሳን ከማየት የተሻለ አለመኖሩን የሚያሳይ ነው፡፡ ቀነኒሳ ማራቶንን በተለመደው መንገድ ሮጦ በቴክኖሎጂ ሳይታገዝ ከ2፡00 በታች መሮጥ እንደሚችል በቅርቡ አብሮ እየሰራ የሚገኘው አሰልጣኙ ሃጂ አዲሎም በቅዳሜው እለት እትማችን ባደረጉት ቃለ ምልልስ መግለፃቸው ይታወቃል፡፡ አሰልጣኙ ሃጂም ‹‹ ቀነኒሳ ሩጫ ከማቆሙ አስቀድሞ ማራቶንን ከ2፡00 በታች ይሮጣል፣ በየትኛው ውድድር እንደሚሆን ግን መናገር አይቻልም›› ይላሉ፡፡ ቀነኒሳ ምናልባትም ይህን ለማሳካት የቀጣዩን ዓመት የበርሊን ማራቶን መታገስ ላይጠበቅበት ይችላል፡፡ በቀጣዩ ሚያዝያ በለንደን ማራቶን ለመሳተፍ በሆላንድ አገር የሚያደርገው ዝግጅት በታሰበው ልክ ከሄደ ህልሙን በቅርቡ እውን ሊያደርግ እንደሚችል ይጠበቃል፡፡አዲስ ዘመን ኅዳር 15/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "fa3b2da7adfb2e87723b00e9316e3be8" }, { "passage": "የውድድር ዓመቱ የዳይመንድ ሊግ ፉክክሮች ሰባተኛ መዳረሻ ከተማ በሆነችው ስታንፎርድ ከሳምንት በኋላ ይቀጥላሉ፡፡ በዚህ ውድድር በርካታ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በተለያዩ ርቀቶች ተፋላሚ እንደሚሆኑም ይጠበቃል፡፡ ከሁለት ሳምንት በኋላ በስዊዘርላንድ መዲና ሉዛን የዓመቱ ስምንተኛው የዳይመንድ ሊግ ፉክክር ሲካሄድ በወንዶች መካከል የሚደረገው የአምስት ሺ ሜትር ፉክክር ከወዲሁ ትኩረት ስቧል፡፡ ይህ ውድድር የዓመቱ ምርጥ የአምስት ሺ ሜትር ፍልሚያ የሚል ስያሜም ከወዲሁ ተችሮታል፡፡ይህን\nውድድር ትኩረት እንዲያገኝ ያደረጉት ምክንያቶች መካከል በዋናነት ሁለቱ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ጥላሁን ሃይሌና ሰለሞን ባረጋ ሲሆኑ በውድድር ዓመቱ በርቀቱ ፈጣን ሰዓት ያስመዘገቡ አምስት አትሌቶች መካተታቸው በጉጉት እንዲጠበቅ አድርጎታል፡፡በረጅም ርቀት ኢትዮጵያ ተስፋ ከጣለችባቸው አትሌቶች መካከል ግንባር ቀደም የሆነው ጥላሁን በዘንድሮው የውድድር ዓመት 5ሺ ሜትርን 12፡52፡98 በመሮጥ ስሙ በቀዳሚነት የተቀመጠ ፈጣን አትሌት ነው፡፡ ጥላሁን በሉዛኑ ውድድር ከሦስት ሳምንት በፊት ሮም ላይ በጠባብ ልዩነት ያሸነፈውን ሰለሞን ባረጋን ዳግም ይገጥማል፡፡ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የ5ሺ ሜትር ውድድሮችን እየተቆጣጠረ የሚገኘው ሰለሞን ሮም ላይ 12:53.04 ሰዓት አስመዝግቦ ለጥቂት በጥላሁን መሸነፉ ይታወሳል፡፤እንግሊዛዊው ሞፋራህን ከበርካታ ዓመታት በኋላ ከ5ሺ ሜትር ንግስናው ያወረደው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሙክታር ኢድሪስ በሉዛኑ ውድድር የሚጠበቅ ሲሆን ትውልደ ኢትዮጵያዊው የባህሬን አትሌት ብርሃኑ ባለው በፉክክሩ ውስጥ ተካቷል፡፡ ሮም ዳይመንድ ሊግ ላይ ጥላሁንና ሰለሞን ተከታለው በገቡበት ፈጣን ውድድር 12:56.48 የሆነ ሰዓት ያስመዘገበው አባዲ ሃዲስ እንዲሁም የኦሊምፒክ የብር ሜዳሊያ ባለቤቱ ኬንያዊ ፖል ቼሊሞ ፉክክሩን ከሚያደምቁ አትሌቶች መካከል ይገኙበታል፡፡አዲስ ዘመን ቅዳሜ ሰኔ 15/2011", "passage_id": "251f89ff7764667782d8fe7005257607" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ከለንደን ማራቶን ውጪ መሆኑን አስታወቀ፡፡ቀነኒሳ በቀለ ከውድድሩ ውጪ የሆነው በግራ ባቱ ላይ ባጋጠመው ጉዳት እንደሆነ ተናግሯል፡፡አትሌቱ ይህን አስመልክቶ በማህበራዊ ትስስር ገፁ እንዳሰፈረው ውድድሩን ባለመሳተፌ በጣም አዝናለሁ ብሏል፡፡ለውድድሩ ዝግጅት እንዳደረገ የገለፀው አትሌቱ በመጨረሻዎቹ የዝግጅት ሳምንታት ውስጥ በግራ ባቱ ላይ ያጋጠመው ጉዳት እንቅፋት እንደሆነበት ተናግሯል፡፡", "passage_id": "2363b78b89566b8da7247b878b51094a" }, { "passage": "የ2019 ውድድር ዓመት በማራቶን ወርቃማው ዘመን እንደነበር የዓለም አትሌቲክስ ተንታኞች የውድድር ዓመቱን መገባደድ ተከትሎ በርካታ ማሳያዎችን በማስቀመጥ ተጠምደዋል፡፡ ይህን የውድድር ዓመት ወርቃማ ካስባሉት ቁልፍ ማሳያዎች መካከል ግንባር ቀደሙ ኬንያዊው የርቀቱ የክብረወሰን ባለቤት ኢሉድ ኪፕቾጌ በቬና ማራቶን ርቀቱን በአርባ አንድ አሯሯጮችና በዘመናዊ ጫማ ታግዞ ከ2፡00 በታች ማጠናቀቁ ነው፡፡ ከኪፕቾጌ አስደናቂ ብቃት ባሻገር የ5ና 10 ሺ ሜትር የዓለም ክብረወሰን ባለቤቱ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ከረጅም ጊዜ ጉዳት በኋላ ወደ ውድድር ተመልሶ ባለፈው በርሊን ማራቶን 2፡01፡41 የሆነውን ሁለተኛ ፈጣን ሰዓት ማስመዝገቡ የውድድር ዓመቱን ወርቃማ ካሰኙት ምክኒያቶች አንዱ ነው፡፡ ከ5 ና 10ሺ ሜትር የመም(ትራክ) ውድድሮች ጀምሮ በኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮናን\nበመሳሰሉ ታላላቅ መድረኮች ባለፉት ሃያ ዓመታት በረጅም ርቀቶች ተፎካካሪ የሆኑት ቀነኒሳና ኪፕቾጌ አሁን ላይ በማራቶን የዓለማችን\nቁጥር አንድና ሁለት ናቸው፡፡ ኪፕቾጌ ከዓመት በፊት የርቀቱን ክብረወሰን በበርሊን ማራቶን 2፡01፡39 በሆነ ሰዓት ሲያስመዘግብ\nከእሱ ሌላ ይህን ክብረወሰን የሚደፍረው አትሌት እንደማይኖር የበርካቶች ግምት ነበር፡፡ በተቃራኒው ቀነኒሳ ባለፈው መስከረም ከረጅም\nጊዜ ጉዳት በኋላ ወደ ውድድር ተመልሶ በበርሊን ማራቶን ሲሳተፍ ፈጣን ሰዓት ያስመዘግባል ብሎ የገመተ አልነበረም፡፡ ያም ሆኖ ሦስት\nየኦሊምፒክ ወርቆችን መሰብሰብ የቻለው የሰላሳ ሰባት ዓመቱ ቀነኒሳ ከኪፕቾጌ የዓለም ክብረወሰን በሁለት ሰከንድ ብቻ የዘገየ ሰዓት\nበማስመዝገብ የዓለም ክብረወሰን የማሻሻል አቅም እንዳለው አስመስክሯል፡፡ ኪፕቾጌ በማራቶን የዓለምን አንደኛ ፈጣን ሰዓት በእጁ ይዞ ቀነኒሳም በሁለት ሰከንድ\nየዘገየ ሁለተኛውን ፈጣን ሰዓት ይዞ በዘንድሮው የውድድር ዓመት ብቻ በሁለት ታላላቅ የውድድር መድረኮች የሚፋለሙበት አጋጣሚ ሰፊ\nእንደሚሆን ሰሞኑን የወጡ መረጃዎችን ከግምት በማስገባት መገመት ይቻላል፡፡ ኪፕቾጌ ከትናንት በስቲያ በለንደን ማራቶን እንደሚሳተፍ\nማሳወቁን ተከትሎ ከቀነኒሳ ጋር የሚፋለምበት አጋጣሚ በመጪው ሚያዝያ እውን እንደሚሆን ታውቋል፡፡ ቀነኒሳ ከበርሊን ማራቶን አስደናቂ\nድሉ በኋላ በለንደን ማራቶን ለመሳተፍ ትልቅ ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ ይህም ሁለቱ አትሌቶች የጤና ወይም ሌላ የተለየ\nችግር ካልገጠማቸው ለንደን ላይ የዓለም ህዝብ በጉገት የሚጠብቀው ትልቅ ፉክክር እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡ ሁለቱ አትሌቶች\nበለንደን ማራቶን ከዚህ ቀደም እንደመፎካከራቸው የዘንድሮውን ምን ልዩ ያደርገዋል? የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችላል፡፡ ሁለቱ አትሌቶች\nከዚህ ቀደም የለንደን ማራቶንን ጨምሮ በሌሎች የጎዳና ላይ ውድድሮች የተገናኙባቸው አጋጣሚዎች ቢኖሩም ቀነኒሳ በጥሩ አቋም ላይ\nአልነበረም፡፡ ይህም የሁለቱን የረጅም ርቀት ፈርጦች ፉክክር በሚጠበቀው ደረጃ እንዳይገኝ አድርጎታል:: አሁን ላይ ሁለቱም ኮከቦች\nበድንቅ አቋማቸው ላይ እንደመገኘታቸው መጠን ዘንድሮ ሊያደርጉት የሚችሉት ፉክክር የተለየ እንደሚሆን ከወዲሁ መገመት አይከብድም፡፡\nኪፕቾጌ ቬና ላይ 1፡59፡41 በመሮጥ የሰው ልጅ የብቃት ጥግ ገደብ እንደሌለው ካሳየ በኋላ በጥሩ የስነ ልቦና ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡\nቀነኒሳ ደግሞ በሁለት ሰከንድ ምክኒያት ባመለጠው የዓለም ክብረወሰን ቁጭት ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ይህን ቁጭቱን ለመወጣት በከፍተኛ\nተነሳሽነት ጥሩ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል፡፡ኪፕቾጌ ባለፉት አራት ዓመታት በለንደን ማራቶን ነግሷል፡፡ የቦታው ክብረወሰንም በእጁ\nይገኛል፡፡ ቀነኒሳ በጥሩ አቋም ላይ ባልነበረበት ወቅት ለንደን ላይ ከአንዴም ሁለቴ የተራበውን ድል ማሳካት አልቻለም፡፡ ዘንድሮ\nግን ከበርሊን ማራቶን ጣፋጭ ድሉ በኋላ ይህን ውድድር የማሸነፍ ጉጉቱ አይሏል፡፡ ሁለቱ ፈርጦች በዚህ አይነት ደረጃ ላይ መገኘታቸው\nለስፖርት አፍቃሪው የምስራች ሲሆን ለስፖርቱም እድገት አንድ ርምጃ ነው፡፡ ምናልባትም በዚህ ፉክክር መካከል በቴክኖሎጂ በመታገዝ\nከ2፡00 በታች መጠናቀቅ የተቻለው አርባ ሁለት ኪሎ ሜትር በተፈጥሯዊ መንገድ እውን የሚሆንበት እድል ሊኖር ይችላል፡፡ ይህ ባይሆን\nእንኳን አዲስ የዓለም ክብረወሰን ሊመዘገብ የሚችልበት አጋጣሚ አይኖርም ለማለት አያስደፍርም፡፡ ከለንደን ማራቶን\nባሻገር ሁለቱን ኮከቦች በዘንድሮው የውድድር ዓመት የማየት ሌላ እድል ይኖራል፡፡ ይህም ዓለም በጉጉት የሚጠብቀው ታላቁ የስፖርት\nመድረክ ኦሊምፒክ ነው፡፡ 2020 ኦሊምፒክን ቶኪዮ ለማሰናዳት ዝግጅቷን እያጠናቀቀች ትገኛለች፡፡ ከለንደን ማራቶን በኋላ እዚህ\nኦሊምፒክ ላይ ለመሳተፍ ኪፕቾጌ ፍላጎት እንዳለው መግለፁ ይታወቃል፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በኦሊምፒክና በዓለም ቻምፒዮና\nየሚሳተፉ አትሌቶችን የሚመርጠው አትሌቶች በታላላቅ ውድድሮች ባስመዘገቡት ውጤትና ሰዓት መሰረት እንደመሆኑ መጠን ቀነኒሳ ለቶኪዮ\nኦሊምፒክ የመመረጥ እድሉ ሰፊ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል:: ይህም ሁለቱን ኮከቦች ዳግም በታላቅ የውድድር መድረክ የሚያፋጥጥ አጋጣሚ\nይሆናል፡፡ ሁለቱ አትሌቶች\nኦሊምፒክ ላይ ከተገናኙ የቶኪዮ ድግስ የበለጠ በማራቶን እንደሚደምቅ ግልፅ ነው፡፡ ኪፕቾጌ 2016 ሪዮ ኦሊምፒክ ላይ ቻምፒዮን\nመሆኑን ተከትሎ ለሁለተኛ ጊዜ በዚህ ታላቅ መድረክ ታሪክ ለመስራት ጉጉት ባይኖረው ይገርማል፡፡ ኪፕቾጌ ይህን ድል ካሳካ ከአበበ\nቢቂላ በኋላ በታሪክ ኦሊምፒክ ላይ ሁለት ጊዜ በማራቶን ያሸነፈ አትሌት የመሆን እድል አለው፡፡ ቀነኒሳ ባለፈው ሪዮ ኦሊምፒክ በማራቶን\nኢትዮጵያን ለመወከል ተመርጦ መጨረሻ ሰዓት ላይ ከቡድን ስብስቡ መውጣቱ ይታወሳል፡፡ ዘንድሮ ይህን እድል አግኝቶ መጠቀም ከቻለ\nግን ታሪካዊው አትሌት አበበ ቢቂላ ለሁለተኛ ጊዜ ታሪክ በሰራባት ቶኪዮ ስሙን በወርቅ ቀለም የሚፅፍበት ወርቃማ እድል ከፊቱ ይጠብቀዋል፡፡\nአዲስ ዘመን አርብ ታህሳስ 10/2012ቦጋለ አበበ", "passage_id": "ddafc2a9f40caca7d7d01551f6d8b418" }, { "passage": "የዓለም ታላላቅ ስፖርት መድረኮች በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ወረርሽኝ ምክንያት ለበርካታ ወራት ከቆሙበት ለመቀጠል ጥረት እያደረጉ እንደሚገኙ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ለመመልከት ተችሏል። የእግር ኳሱ ዓለም ታላላቅ ሊጎች በዝግ ስቴድየምም ቢሆን ጨዋታዎችን እያስቀጠሉ ካንቀላፉበት እየነቁ ይገኛሉ። በዚሁ ወረርሽኝ ሳቢያ ክፉኛ የተጎዳው የዓለም አትሌቲክስ እንቅስቃሴም ከጥቂት ወራት በኋላ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለመመለስ ከወዲሁ እንቅስቃሴ መጀመሩ ለዓለማችን አትሌቶች መልካም ዜና ሆኗል። በተለይም የዓለማችን ኮከብ አትሌቶች በጉጉት የሚጠብቁት ዓመታዊው የዳይመንድ ሊግ ውድድር እንደሚመለስ መገለፁን ተከትሎ ለወራት ከውድድር ርቀው ለተቀመጡት አትሌቶች የምሥራች መሆኑ አይቀርም። በኮሮና ቫይረስ\nወረርሽኝ\nየተነሳ\nየዓለም\nአትሌቲክስ\nዓመታዊ\nመርሃግብሮች\nበተያዘላቸው\nጊዜ\nሳይካሄዱ\nበመቅረታቸው\nተዘበራርቀዋል።\nየዓለም\nአትሌቲክስ\nይህንን\nለመካስም\nበጊዜያዊነትም\nቢሆን\nእንደ\nዳይመንድ\nሊግ\nያሉ\nውድድሮች\nመርሃግብርን\nለመከለስ\nተገዷል።\nበብራሰልስ\nየሚካሄደውም\nውድድር\nከተከለሱት\nመርሃግብሮች\nመካከል\nየሚጠቀስ\nነው።\nዳይመንድ\nሊጉ\nወደ\nውድድር\nሲመለስ በመጪው የፈረንጆች መስከረም ወር መጀመሪያ እንደሚካሄድ የሚጠበቀው የብራሰልስ ዳይመንድ ሊግ ከወዲሁ ትኩረት አግኝቷል። እንግሊዛዊው የኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮናዎች ጥምር የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤቱ አትሌት ሞሐመድ ፋራህ ከ2017 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ መም ውድድሮች ተመልሶ በብራሰልስ ዳይመንድ ሊግ ተፎካካሪ እንደሚሆን መናገሩን ተከትሎ ውድድሩ ትኩረት ማግኘት ችሏል። የሰላሳ ሰባት ዓመቱ ፋራህ ወደ ውድድር ከመመለሱ በተጨማሪ በ21 ነጥብ 285 ኪሎ ሜትር ፉክክሩን ከአንድ ሰዓት በታች ለማጠናቀቅና አዲስ የዓለም ክብረወሰን ለማሻሻል መዘጋጀቱን ተከትሎ የብራሰልስ ዳይመንድ ሊግ ከወዲሁ በጉጉት እንዲጠበቅ አድርጓል። የርቀቱ ክብረወሰን በጀግናው አትሌት ሃይሌ ገብረሥላሴ የተያዘ ሲሆን ከአስራ ሦስት ዓመታት በፊት እ.ኤ.አ 2007 ኦስትራቫ ላይ ማስመዝገቡ ይታወሳል። በብራሰልሱ ውድድር የአውሮፓ የአስር ሺህ ሜትር የብር ሜዳሊያ አሸናፊው አትሌት በሽር አብዲ ከፋራህ ጋር እንደሚፎካከር የተገለፀ ሲሆን ኢትዮጵያውያንና ኬንያውያን የርቀቱ ፈርጦችም በቅርቡ ውድድሩን እንደሚቀላቀሉ ይጠበቃል። ‹‹ከልምምድ አጋሬ\nበሽር አብዲ ጋር\nውድድሩን ከአንድ ሰዓት\nበታች በማጠናቀቅ የዓለም\nክብረወሰን ለማስመዝገብ እየተዘጋጀን\nነው፣ ይህ ለእኔ\nትልቅ አጋጣሚ ነው፣\nበብራሰልስ ከዚህ ቀደም\nባደረኳቸው ውድድሮች ጥሩ\nትዝታዎች አሉኝ፣ ብራሰልስ ላይ ፈታኝ ሰዓት መሮጥ ይቻላል፣ ሁሉም ነገር ቀላል ነው›› በማለት ፋራህ ለመገናኛ ብዙሃን አስተያየቱን ሰጥቷል። በተመሳሳይ በሴቶች መካከል\nበሚካሄደው ውድድር ግን\nኢትዮጵያውያን አትሌቶች ተፎካካሪ\nከመሆን ባለፈ አዲስ\nየዓለም ክብረወሰን ለማስመዝገብ\nመዘጋጀታቸውን የውድድሩ አዘጋጆች\nገልፀዋል። በዚህም አትሌት\nአባብል የሻነህ እና\nብርሃኔ ዲባባ ተጠባቂ\nሆነዋል። 18 ነጥብ\n517 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው\nውድድር የዓለም ክብረወሰን\nየተመዘገበበት ጊዜ ከአስራ ሁለት ዓመታት በፊት እ.ኤ.አ 2008 ላይ ሲሆን ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ድሬ ቱኔ የክብረወሰኑ ባለቤት መሆኗ አይዘነጋም። በዚህ የውድድር ዓመት የዓለም ግማሽ ማራቶን ክብረወሰንን በ1፡04፡31 ሰዓት መስበር የቻለችው አባብል የሻነህ ለአስራ ሁለት ዓመታት ያልተደፈረውን የድሬ ቱኔን ክብረወሰን እንደምታሻሽል ግምት የተሰጣት ሲሆን በማራቶን 2፡18፡35 የሆነ የራሷ ምርጥ ሰዓት ያላት ብርሃኔ ዲባባም ብራሰልስ ላይ ለክብረወሰን ተጠባቂ ሆናለች።አዲስ ዘመን ሰኔ 20/2012 ቦጋለ አበበ", "passage_id": "a9d8021a3c08aa13dd1f9158c959625e" } ]
88b836aeb0d8c1e3a9a50dbd9ec4884b
11e63b0d77c5ea376e275c9a8cdf9848
በ «አረንጓዴ አሻራ» መርሃ ግብሩ የስፖርት ቤተሰቡ አሻራ
በኢትዮጵያ የደን ልማት ለማጎልበት የሚያስችለው የዘንድሮ «አረንጓዴ አሻራ» መርሃ ግብር ግንቦት 30 ቀን 2012 ዓ.ም በይፋ መጀመሩ ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ መርሃ ግብሩን ሲያስጀምሩ፤ በዘንድሮ ዓመት የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አምስት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል እቅድ መያዙን ተናግረዋል። ሁሉም ኢትዮጵያዊ ችግኞችን እንዲተክል «አሻራችንን በማኖር ለኢትዮጵያ አረንጓዴ ምንጣፍ እንዘርጋ» ሲሉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብርን አስጀምረዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ጥሪ መሰረት በማድረግ በዘጠኙም ክልሎችና በሁለቱም ከተማ አስተዳደሮች የሚገኙ ተቋማት፣ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጥሪውን በመቀበል አረንጓዴ አሻራቸውን በማሳረፍ ላይ ይገኛሉ። የ2012ዓ.ም አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ተግባራዊ ካደረጉት ተቋማት መካከል ደግሞ የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳል። በ2012 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ 156 ሺህ ችግኞች በመትከል ለሀገር አቀፍ ስኬቱ የበኩሉን ሚና ለመወጣት እቅድ ይዞ ሲንቀሳቀስ ነበር የቆየው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የበጀት ዓመቱን መርሃ ግብር በቅርቡ ማስጀመራቸውን ተከትሎ ፤ ኮሚሽኑ የስፖርት ቤተሰቡንና ማህበረሰቡን የሚያሳትፈውን መርሃ ግብር ሰኔ 10 ቀን 2012 ዓ.ም በይፋ አስጀምሯል። መርሃ ግብሩም «ለስፖርት ልማት አረንጓዴ አሻራችንን እናስቀምጥ» በሚል መሪ ቃል በይፋ ተጀምሯል። ለአረንጓዴ ልማቱ አሻራ የስፖርት ቤተሰቡ አሻራ ለማሳረፍ እድል የሚከፍተው መርሃ ግብሩ በቦሌ ክፍለ ከተማ ሰሚት ኮንደሚኒየም ሁለተኛ በር በሚገኘው የስፖርት ማዘወተሪያ ስፍራ በታላቅ ድምቀት ሊጀመር። በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይም የአዲስ አበባ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ፣ የኢትዮጵያን ባንዲራ በዓለም አቀፍ መድረክ ከፍ እንዲል ያደረጉ አትሌቶች፣ የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች፣ አሰልጣኞችና ደጋፊዎች ተገኝተዋል። በአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን አስተባባሪነት የተሰናዳውን አረንጓዴ አሻራን የማሳረፍ ትግበራው ከሰሚት ኮንዶሚኒየም የተነሳው የተከላ መርሃ ግብሩ በመቀጠል በሌሎች የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ተከናውኗል። ኢንጂነር ታከለ ኡማን ጨምሮ በርካታ የስፖርት ቤተሰቦችን በማካተት የኮረና ቫይረስ ተጋላጭነት በማይኖረው መልኩ እንዲሁም ጥንቃቄ በታከለበት ሁኔታ ችግኝ በመትከል ለስፖርቱ ልማት አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዮናስ አረጋይ በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት ወቅት ፤ ለስፖርተኛውና ለስፖርት ቤተሰቡ የሚያስፈልገው ንፁህ አየርና ጤናማ ለመሆን ችግኝ መትከል አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል። «የስፖርት ማዘውተሪያዎች በኮንክሪት ብቻ ሳይሆን በአረንጓዴ ተክሎችም መዋብ አለባቸው። ስለዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩን በቀሪ ወራትም አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አስገንዝበዋል። «በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ በከተማዋ በሚገኙ የስፖርት ማዘውተሪያዎች ከአንድ ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል ዕቅድ ተይዞ ወደ ተግባር ተገብቷል። በዚህ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 34 የስፖርት ፌዴሬሽኖች የሚሳተፉ ይሆናል» ብለዋል። በከተማዋ የስፖርት እንቅስቃሴው ላይ ተጨባጭ ለውጥና ውጤት በአጭር ጊዜ ውስጥ እየተመዘገበ መሆኑን አክለው የገለጹት አቶ ዮናስ ፤ ለዚህም ስኬታማ ስራዎችን ማከናወን መቻሉን ተከትሎ እንደሆነ ገልጸዋል። ለስፖርቱ ስኬታማነት የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑንና የሚሰሩትን ስራ በአብሮነት በመሆን ሲደክሙ እንደነበር ገልጸዋል። ኢንጂነር ታከለ ኡማ ለመዲናዋ ስፖርት እድገት መነቃቃት እንዲሁም በአረንጓዴ አሻራው መርሃ ግብር ላይ አሻራቸውን በማሳረፍ ላበረከቱትና ወደፊትም ለሚያበ ረክቱት የመሪነት ሚና አመስግነዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በበኩላቸው፤ ስፖርት እና አረንጓዴ ቦታ እንደማይነጣጠሉ ተናግረዋል። ይህን በመገንዘብ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን ለማኖር የተገኙ ስፖርተኞችን አመስግነዋል። «በአረንጓዴ አሻራ ላይ የስፖርት ቤተሰቡ ችግኝ በመትከል በመንከባከብና በማሳደግ ከተማችንን ማስዋብ ፣ ማሳመርና ንፁህ አየር በማግኘት ውጤታማ ስፖርተኛ እንዲሆኑ መትጋት ይኖርባቸዋል» ብለዋል። የስፖርት ቤተሰቡና ማህበረሰቡ በከተማዋ ሁለንተናዊ ለውጥ ላይ እያደረጉት ያለውን አስተዋፅኦ እና ርብርብ አጠናክረው እንዲቀጥሉም ኢንጂነር ታከለ ለስፖርት ቤተሰቡና ማህበረሰቡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። በተጨማሪም በመርሃ ግብሩ ለይ የተገኙት የኢትዮጵያ ቡናና ቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ተወካዮች አዲስ አበባን አረንጓዴ ለማ ድረግ በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች በቀዳሚነት እንደሚሰለፉ ተናግረዋል። በተመሳሳይ አረንጓዴ አካባቢ ከአትሌቶች የሥልጠና ቦታ ጋር የተቆራኘ በመሆኑ በዛሬው ዕለት አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖራቸው ደስተኛ መሆናቸውን አትሌት ገንዘቤ ዲባባና አትሌት ጌጤ ዋሚ የገለጹ ሲሆን ፤ ችግኝ ከመትከል ባለፈ ተገቢ እንክብካቤ ማድረግ እንደሚገባም አመልክተዋል። አዲስ ዘመን ሰኔ 12/2012ዳንኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=34666
[ { "passage": "በሀገር አቀፉ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ የተሳተፉት የቅዱስ ጊዮርጊስና ኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ደጋፊዎች ‹‹በእግር ኳሱ ሜዳ ያለንን የልዩነትና የጠብን ችግኝ ነቅለን የአንድነትና የፍቅር ችግኝ ተክለናል›› ሲሉ ተናገሩ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማ በተገኙበት የቅዱስ ጊዮርጊስና ኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ደጋፊዎች በመዲናዋ ልዩ ስሙ የሺ ደበሌ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ትናንት ችግኝ ተክለዋል፡፡ በመርሃግብሩ ወቅት አዲስ ዘመን ካነጋገራቸው ተሳታፊዎች መካከል የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊ የሆነው ሳሙኤል ለማ እንደተናገረው፤ ታሪካዊው የአረንጓዴ አሻራ ቀን ተፈጥሮን ከመታደግና አገሪቱን አረንጓዴ ከማድረግ በተጓዳኝ ሕብረተሰባዊ አብሮነትን በማጎልበት ለሀገራዊ ልማትና አንድነት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው፡፡ የሁለቱ ክለብ ደጋፊዎች በዚህ ቀን ተፈጥሮን ከመታደግና አገሪቱን አረንጓዴ ለማድረግ አሻራቸውን ከማስቀመጥ ባለፈ ወዳጅነትም ማጠናከር ችለዋል፡፡ ‹‹በሀገር አቀፉ የአረንጓዴ አሻራ ቀን በእግር ኳሱ ሜዳ የሚያንፀባርቁትን የልዩነትና የጠብ ችግኝ ነቅለው የአንድነትንና የፍቅር ችግኝ ተክለዋል፡፡›› ያለው ሳሙኤል፣ ሁለቱ ክለቦች በዚህ ቀን በአንድነት አላማ በፍቅር መተሳሰራቸው ከአገሪቱ ስፖርት ባሻገር ለአገር ሰላም የሚኖረው ፋይዳ ብዙ መሆኑን አብራርቷል፡፡ ተግባሩ ለሌሎች የአገሪቱ ክለብ ደጋፊዎች ብቻም ሳይሆን ለአጠቃላይ ህዝብም ምሳሌ እንደሚሆን ያመላከተው ሳሙኤል፣ ‹‹ችግኝ መትከል ብቻም ሳይሆን አዕምሯችን ላይ የበቀለውን የዘርና ብሄር ችግኝ መነቃቀል ያስፈልጋል፡፡ ይህን በማድረግም የተሻለችና የበለፀገች ኢትዮጵያን መፍጠር እንችላለን፡፡›› ሲልም ተናግሯል፡፡ የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዋ እስከዳር ይፍሩ በበኩሏ፤ በሀገር አቀፉ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃግብሩ ተፈጥሮን ከመታደግና አገሪቱን አረንጓዴ ከማድረግ በተጓዳኝ የኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ደጋፊዎች ልዩነታቸውን በመናድ አንድነታቸውን መገንባታቸውን ተናግራለች፡፡ ‹‹የሁለቱ ክለብ ደጋፊዎች የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ አገራዊ ጥሪ በመስማት ለአገራዊ አላማ በጋራ በመቆም የጠብን ችግኝ ነቅለው የፍቅር ችግኝ ተክለዋል፤ ለዚህም በመርሀ ግብሩ ላይ ከታየው አንድነትና ፍቅር በላይ ምስክር የለውም፡፡›› ብላለች፡፡ የኢትዮጵያ ቡናው እዮብ ስዩም እና የቅዱስ ጊዮርጊሱ ዳዊት ሽመልስ በየበኩላቸው፤ የሁለቱ ክለብ ደጋፊዎች በአረንጓዴ አሻራ ቀን ከችግኝ በተጨማሪ ፍቅርን ተክለው በፍቅር ማሳለፋቸውን ገልፀዋል፡፡ አንድነትና መተሳሰባቸውንም አሳይተዋል፡፡ ይህ ፍቅርና አንድነታቸውም ወቅታዊ ሳይሆን ዘላቂ ሆኖ እንዲቀጥልና በእግር ኳሱ ሜዳ ላይ ጎልቶ እንዲንፀባረቅ ሁሉም ደጋፊ የበኩሉን እንዲወጣም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ አስተያየት ሰጪዎቹ በአንድነት ተሳስረው የተከሉትን ችግኞች እንደሚንከባከቡ እና መፅደቃቸውንም በየጊዜው እንደሚከታተሉም አስታውቀዋል፡፡ አዲስ ዘመን ሀምሌ 23/2011 ", "passage_id": "6eb76ead2aabc5c1ffafe4dca4048da1" }, { "passage": "‹‹ዛፍ ለሰዎች አልያም ለእንስሳት ጥላነት ከማገልገል ውጪ እንዴት የእግር ኳስ ቡድን ደጋፊ ሊሆን ችላል?›› ይሉ ይሆናል። በርግጥ ዛፍ ሕይወት ያለው ነገር ቢሆንም እንደሰው ትኬት ቆርጦና ስታዲየም ገብቶ የእግር ኳስ ጨዋታዎችን ሊመለከት ይችላል ወይ? ሲሉም አክለው ይጠይቁ ይሆናል።። በርግጥ እውነትዎን ነው። ይሁንና ይህ ዛፍ የእግር ኳስ ቡድን ደጋፊ ሊሆን የቻለው ልክ እንደሰው ትኬት ቆርጦ ስታዲየም በመግባት ሳይሆን በሌላ ምክንያት ነው። ኦዲቲ ሴንትራል የተሰኘው ድረ ገጽ ከሰሞኑ ባወጣው መረጃ መሠረት በኡራጋይ ሁለተኛ ዲቪዥን የሚጫወተው ሬሲስቴኒካ የተሰኘው አነስተኛ የእግር ኳስ ቡድን ደጋፊዎቹ በተቀመጡበት ቦታ ወይም በእኛ ሀገር ስታዲየም አጠራር ካታንጋ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ዛፍ በማብቀል በዓለም የመጀመሪያው ክለብ ሆኗል።። ልክ እንደሌሎቹ የክለቡ ደጋፊዎች ሁሉ ዛፉ በአባልነት እንዲመዘገብና ክለቡ በሜዳው የሚያደርጋቸውን ጨዋታዎች ሁሉ በነፃ እንዲታደም ተደርጓል ሲልም ዘገባው አመልክቷል። ላ ቻቻሪታ የተሰኘው ይኸው እግር ኳስ ደጋፊ ዛፍ ከክለቡ ምስረታ በፊት የነበረ አንጋፋ ዛፍ በመሆኑ ክለቡና ደጋፊዎች ዛፉ የታሪካቸው አንዱ አካል አድርገው ይቆጥሩታል ያለው ዘገባው፤ ክለቡ ከሃያ ዓመት በፊት ለደጋፊዎቹ ተጨማሪ የኮንክሪት መቀመጫዎችን ለመገንባት ሲያስብ አንጋፋ የሆነውን የክለቡ ደጋፊ ዛፍ ለመቁረጥ እንኳን ሃሳብ አልነበረውም። ይልቁንም በወቅቱ ስታዲየሙን ሲገነቡ የነበሩ መሐንዲሶች ዛፉ ሳይቆረጥ የደጋፊዎቹ መቀመጫ ግንባታ እንዲካሄድ ይጠይቃሉ። መሐንዲሶቹም ክለቡ በሜዳው የሚያደርጋቸውን ጨዋታዎች ደጋፊቹ በዛፉ ጥላ ስር በመሆን መከታተል እንዲችሉ የስታዲየም መቀመጫውን በዛፉ ዙሪያ ይገነባሉ። ከዓመታት በፊት አንጋፋው የክለቡ ደጋፊ ዛፍ መቶኛ ዓመቱን ሲያከብር የክለቡ አስተዳደር ዛፉን በማክበር የክለቡ ቋሚ አባል እንዲሆን መወሰኑንና የአባልነት መታወቂያ ካርድም እንዲሰጠው መደረጉንም ዘገባው ገልጿል። ሮቤርቶ ጋርሴቴ የተሰኙት የክለቡ ፕሬዚዳንትም ‹‹ዛፉ እንደ አንድ የክለባችን ደጋፊ ይቆጠራል፤ ሃያ አራት ሰዓታት ሙሉ በስታዲየሙ ስለሚገኝም ታማኙ ደጋፊያችን ነው›› ሲሉ ገልጸዋል። ላ\nቻቻሪታ\nየተሰኘው\nዝነኛ\nዛፍ የ100 ዓመት ዕድሜ ያለው መሆኑ ተነግሯል። በአሁኑ ወቅት 20 ሜትር ርዝማኔ ያለው ሲሆን፣ በስታዲየሙ የኮንክሪት መቀመጫ መካከል በተዘጋጀለት ቀዳዳ አማካኝነት እድገቱንም ቀጥሏል፤ ‹‹ዛፉ ከክለቡ ደጋፊነትም ባሻገር ለሌሎቹ የክለቡ ደጋፊዎች ከፀሐይ መጠለያ በመሆንም ባለውለታነቱን አስመስክሯል›› ሲል ዘገባው አያይዞ ጠቅሷል።አዲስ ዘመን መጋቢት 17/2011 ", "passage_id": "c1d438bae0266682436978799b5bffaf" }, { "passage": "ደንን የመሰለ አንጡራ ሀብት ከሰው ህይወት ነጥሎ ማየት አይቻልም። ዛፍ ለሰው ህይወት ወሳኝ በመሆኑ መቆረጥ የለበትም ፤ መቆረጥ ካለበት ደግሞ በምትኩ እጥፍ ተደርጎ መተከል አለበት። ከከተማው ማህበረሰብ በበለጠ አርሶ አደሩ ከደኑ ዘርፈ ብዙ መገልገያዎችን ይሰራበታል። ለአብነት ያህል እርፍ፣ ሞፈር፣ቀንበርና የመሳሰሉትን የሚያገኘው ከደን ነው። ያለሁበት አካባቢም ከአርሶ አደሩ ጋር ቅርበት ስላለውና እንደ አንድ የኃይማኖት አባት የሚጠበቅብኝን ለአርሶ አደሩ ማህበረሰብ በተለይም ክረምት በመጣ ቁጥር ዛፎችን እንዲተክልና ተንከባክቦ እንዲያሳድ እመክራለሁ። ለተለያዩ አገልግሎት በሚቆርጣቸው ዛፎች ምትክም እንዲተክል አስተምራለሁ። መንግስት ባወጣው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር እኔ እንደ ዜጋ 150 ችግኞችን ለመትከል ተዘጋጅቻለሁ፣ ተከላም ጀምሪያለሁ። ነገር ግን የሀገራችን ህዝብ ዛፉን ከፖለቲካው ጋር እንጂ ከራሱ ህይወት ጋር ማዛመድ አልቻለም። ችግኝ መትከል ግን ለህይወታችን ወሳኝ መሆኑን መረዳት አለበት።  ከዚህ በፊት የምሰራው ስራ አመቺ ባለመሆኑ ችግኝ ተከላ ላይ ተሳትፌ አላውቅም። ነገር ግን ሀምሌ 22 ቀን 2011 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ ሁለት ሚሊዮች ችግኝ የሚተከልበት ቀን በመሆኑ ለመሳተፍ በዝግጅት ላይ ነኝ። ሁሉም ሰው ችግኝ በመትከል ሀገራዊ ሀላፊነቱን መወጣት አለበት። ችግኝ መትከላችን ጥሩና የተመጣጠነ የአየር ፀባይ እንዲኖር ያደርጋል።የአፈር መሸርሸርና በጎርፍ የመጠቃት እድላችንን በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሰዋል። ስለዚህ ችግኝ መትከል አስፈላጉ በመሆኑ ሁሉም ሰው ቢሳተፍ ደስ ይለኛል። ወጣቷ የአስራ አንደኛ ክፍል ተማሪ ናት። እስካሁን ባለው የችግኝ ተከላ ፕሮግራም መሳተፍ ብትፈልግም በምትኖርበት አካባቢ የሚያስተባብር አካል ባለመኖሩ የፈለገችውን ያህል ችግኝ መትከል እንዳለቻለች ትናገራለች። ነገር ግን ሀምሌ 22 ቀን የችግኝ ተከላ ዘመቻ ላይ ለመሳተፍ እየተዘጋጀች ነው። ተማሪ ማዕዶት እንደምትለው የምንተነፍሰውን ንፁህ አየር የምናገኘው ከእጸዋቶች ነው፤ ስለዚህ መንከባከብና የደን ሽፋንን ማስፋት ግዴታችን ነው። የህልውናችን ጉዳይም ነው። አሁን የደን ሽፋን ተመናምኖ ወደ አስራ አምስት ነጥብ ስድስት ብቻ ቀርቷል። ከሰላሳ አመት በፊት ከሰላሳ ፐርሰንት በላይ ነበር። የደን ሽፋኑን ወደ ተሻለ ደረጃ ለመመለስ ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን መንከባከብና ማጽደቅ ይገባናል። “አቅም ኖሮኝ ባለመሳተፌ ቅር ብሎኛል። ነገር ግን ልጆቼ በችግኝ ተከላው ላይ በመሳተፋቸው ደስተኛ ነኝ። ችግኝ መትከል ያስፈልጋል።ስለዚህ ወጣቱ በስፋት መሳተፍ አለበት። ሀገር ያለ ልምላሜ ዋጋ የላትም። በመሆኑም ሀገርን ለማልማት ችግኝ መትከል የማይተካ ሚና አለው።ቤትና የተለያዩ መገልገያ ቁሳቁሶችን የምናገኘው ከእንጨት ነው። እንዲሁም ሁሉም ነገር በፋብሪካ ምርት ሳይተካ እንደ እንጨት የሚያገለግል ነገር አልነበረም። የእንጨት ውጤት የሆኑ ቁሳ ቁሶችን ለማግኘት ችግኞችን መትከል አስፈላጊ ነው።አሁን እየተሰራ ያለው ደግሞ የዚህ ዘመን ታሪክ ነው። ሁሉም በሀይማት፣በዘርና በቀለም ሳይለይይ መሳተፍ አለበት።አዲስ ዘመን ሀምሌ 21/2011", "passage_id": "fc337f5aae9cbcfe992f510193defd5f" }, { "passage": "ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የስፖርት መድረኮች አንገቷን ቀና አድርጋ የምትሄደው በአትሌቲክስ ነው:: ለዚህ ደግሞ የኢትዮጵያዊነት መገለጫ የሆነውን ህብረትና መተሳሰብን ዘመን የማይሽራቸው ጀግኖች አትሌቶች ለተተኪው ጀግና አውርሰው አሳይተውናል:: ድል ድል ነው:: በመደጋገፍና በመረዳዳት ከራስ ጥቅም በላይ አገርን አስቀድሞ የሚመጣ ድል ደግሞ የበለጠ ጣፋጭ ነው:: ጀግኖች አገርን አስቀድመው ለባንዲራ ክብር በሕብረት የሚፅፉት ታሪክ አገርን አንድ ያደርጋል:: ለቀጣዩ ትውልድ አንድነትም ትምህርት ይሆናል:: ይህ የአያሌ አትሌቶቻችን መገለጫ ቢሆንም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ከአገር በላይ ራስን የማስቀደም፣ በሕብረት ታግሎ ጣፋጭ ድል ከማስመዝገብ ይልቅ በግል ታሪክ ለማስመዝገብ የሚደረግ ጥረት በአትሌቶቻችን መካከል እንደሰፈነ የተመለከትንበት አጋጣሚ ብዙ ነው:: የአሁኑ ትውልድ የአትሌቲክስ ጀግኖቻችን በግለኝነት መወቀሳቸው የተደበቀ ነገር አይደለም:: ተደጋግፎ መሮጥና የአረንጓዴ ጎርፍ ታሪክ መፃፍ ከእነ ኃይሌና ቀነኒሳ የአትሌቲክስ ትውልድ ወዲህ እየደበዘዘ የመጣ ይመስላል:: ያም ሆኖ በአሁኑ ትውልድ አትሌቶቻችን መካከል ጠፍቶ እንዳልጠፋ ከትናንት በስቲያ ምሽት ከከፍተኛ ሙቀትና ወበቅ ጋር ታግለው ጣፋጭ ድል በአምስት ሺ ሜትር ያስመዘገቡ የዘመኑ ጀግኖች አስመስክረዋል:: ድላቸውም ሕብረትና መደጋገፍ የታየበት ኢትዮጵያዊ ድል ሆኖ ያለፉትን ጀግኖች ለማስታወስ የሚያስገድድ ሆኗል:: እአአ 2009 በርሊን ላይ ቀነኒሳ የወርቅ ሜዳሊያ ካጠለቀ በኋላ ወደ አገሩ መመለስ ያልቻለው የ5ሺ ሜትር ድል፤ እነሆ ጊዜውን ጠብቆ ለንደንና ዶሃን ለማከታተልም በቃ። በርቀቱ የኢትዮጵያዊያን ታሪክም ብርቱው አትሌት ሙክታር እድሪስ በተከታታይ ለሁለት ዓመታት ያሸነፈ የመጀመሪያው አትሌት አድርጎታል። ረጅም ጊዜ በቆየው ጉዳቱ ምክንያት ተሳታፊነቱ ያጠራጥራል ሲባል የቆየው አትሌቱ የትላንት በስቲያውን ምሽት ያደመቀ ኢትዮጵያዊ ኮከብ ነበር። ከውድድሩ በኋላ ሙክታር በሰጠው አስተያየትም «ለዓመታት ከገጠሙኝ ተደጋጋሚ ጉዳቶች ለማገገም ጥረት ሳደርግ ቆይቻለሁ። እግሬ ላይ ከአንድ ዓመት በፊት ነው ጉዳት ያስተናገድኩት፤ የሆድ ውስጥ ህመምም ነበረብኝ። በዚህም በደንብ አልተንቀሳቀስኩም፤ ነገር ግን ወደዚህ ከመምጣቴ በፊት የህመም ስሜት ስላልተሰማኝ ለድል መፋለም እንዳለብኝ ለራሴ ነገርኩት። በዚህም ደስተኛ ነኝ፤ እንዲህ ዓይነት ደጋፊዎች ሲኖሩ ደግሞ ታሸንፋለህ» በማለት በአረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ ባንዲራ አጊጠው የከሊፋን ስቴድየም በልዩ ድባብ ስላደመቁት ኢትዮጵያውያን ደጋፊዎች አድናቆትና ምስጋናውን ተናግሯል:: በመሰል ድሎች መኩራት ለኢትዮጵያውያኑ አዲስ ባይሆንም የስታዲየሙ ድባብ ተቀዛቅዟል በሚል እየተወቀሰ ያለውን የከሊፋ ስታዲየምንም ወደ ተለመደ ሞቅታው የመለሱት ኢትዮጵያውያን ደጋፊዎች ለመደነቅ አብቅቷቸዋል። አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ባንዲራ የያዙ እና በእነዚሁ ቀለማት የደመቁት የኳታር ነዋሪ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም የብሔራዊ ቡድኑ ልኡክ በስታዲየሙ ተገኝተው ያደረጉት ማበረታቻ ለውጤቱ መገኘት የራሱን ሚና ተጫውቷል። ይህንንም ዓለም አቀፉን ማህበር ጨምሮ ሌሎችንም ያነጋገረ ነው። ውድድሩን ከመነሻው ለተመለከተ የመጨረሻውን የወርቅ እና የብር ሜዳሊያ ብቻም ሳይሆን የኢትዮጵያውያኑ መታወቂያ የመመለሱንም ፍንጭ ያመላከተ ሆኗል። ለ«አረንጓዴው ጎርፍ» ምክንያት የሆነው የቡድን ስራ እንዲሁም የአገር ክብርን በማስቀደም ድልን ለጓደኛ አሳልፎ መስጠት የታየበትም ነበር፤ የወንዶች 5ሺ ሜትር። የኃይሌ ገብረስላሴ እና ገብረእግዚአብሄር ገብረማርያም እንዲሁም የቀነኒሳ በቀለ እና ስለሺ ስህን ጥምረትም ታይቶበታል ለማለት ያስችላል። ሙክታር እድሪስ፣ ሰለሞን ባረጋ እና ጥላሁን ኃይሌ በመፈራረቅ ሲያሳዩ የነበረው እንቅስቃሴ ለሜዳሊያው መገኘት ከፍተኛ ሚና የተጫወተም ሆኗል። በተለይ የመጨረሻው ዙር ላይ ሰለሞን የሌላ አገር ተፎካካሪ አትሌቶችን በመፋለም ቻምፒዮኑ ሙክታር ወደፊት እንዲወጣ ያደረገበት መንገድ ምስጋና አዝንቦለታል:: በቻምፒዮናው ለአገራቸው የመጀመሪያውን የወርቅ፣ ሁለተኛውን የብር እንዲሁም ዲፕሎማ ደረጃ እንዲገኝ ምክንያት ሆነዋል። ይህንን ቻምፒዮና ልዩ የሚያደርገው ካለፈው ቻምፒዮና በአንድ ደቂቃ የፈጠነ ሰዓት የተመዘገበበት መሆኑ ነው። የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤቱ ሙክታር 12:58.85 የሆነ ሰዓት ሲያስመዘግብ፣ ሰለሞን ባረጋ በአንድ ሰከንድ ዘግይቶ 12:59.70 የሆነ ሁለተኛውን ፈጣን ሰዓት አስጽፏል። በኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች መካከል በመግባት የነሃስ ሜዳሊያውን የወሰደው ካናዳዊ አትሌት ሞሃመድ አህመድ የነሃስ ደግሞ13:01.11 ርቀቱን ለማጠናቀቅ የፈጀበት ሰዓት ነው።አዲስ ዘመን መስከረም 21/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "715f41bfa0826ed07aefad2947b8a5c6" }, { "passage": "ባሕር ዳር፡ ግንቦት 28/2012 ዓ.ም (አብመድ) አምስት ቢሊዮን ችግኞች የሚተከሉበት የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ቀን በመላው ኢትዮጵያ ዛሬ ተጀምሯል፡፡ የመርሀ ግብሩን መጀመር አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ባስላለፉት መልእክት ኢትዮጵያ በአራት ዓመታት 20 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖዎችን ለመቋቋም እየሠራች እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡", "passage_id": "6eefe7630edebc54b089be344979df47" } ]
1f99a2af8244cefebeede126afa942fc
10b865936a842ae58ec9b052edf442f2
ላሚን ዲያክ የአራት ዓመት እስር እንዲፈረድባቸው ተጠየቀ
በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ፓሪስ ውስጥ በቁም እስር ላይ የሚገኙት የቀድሞው የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ፕሬዚዳንት ላሚን ዲያክ አራት ዓመት የእስር ቅጣት እንዲተላለፍባቸው ተጠየቀ፡፡ የሰማንያ ሰባት ዓመቱ አዛውንት ላይ ክስ የመሰረቱት የፈረንሳይ አቃቤ የላሚን ዲያክ ልጅ በሆኑት ፓፓ ማሳታ ዲያክ እንዲሁም የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የቀድሞ የማርኬቲንግ አማካሪ ላይ የአምስት ዓመት እስርና የአምስት መቶ ሺ ፓውንድ ቅጣት እንዲተላለፍባቸው ለፍርድ ቤት ጥያቄ እንዳቀረቡ ሮይተርስ ትናንት ዘግቧል፡፡ አዛውንቱ ላሚን ዲያክ እድሜያቸው መግፋቱን ተከትሎ የእስር ቅጣት ከተላለፈባቸው ሕይወታቸው በወሕኒ ቤት ሊያልፍ እንደሚችል በመጠቆም ጠበቆቻቸው ፍርዱ እንዲቀል መጠየቃቸው ታውቋል፡፡ የመጨረሻው የፍርድ ሂደት ላይ የተሰየመው የፈረንሳይ ፍርድ ቤት ውሳኔ ለማስተላለፍም ለመጪው መስከረም ቀጠሮ ይዟል፡፡ እኤአ ከ1999 እስከ 2015 የዓለም አቀፉን አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የመሩት ላሚን ዲያክ መንበረ ስልጣናቸውን ባስረከቡ ማግስት በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በሰማንያ ስድስት ዓመታቸው ነበር ወደ ፓሪስ ባቀኑበት ወቅት በቁጥጥር ስር የዋሉት፡፡ የሃምሳ አራት ዓመቱ ልጃቸው ፓፓ ማሳታም ዓለም አቀፍ ማህበሩን ተገን አድርጎ ህገ ወጥ ገንዘብ ህጋዊ በማድረግና ስልጣናቸውን አላግባብ በመጠቀም እንዲሁም በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው አባት ወህኒ ሲወርዱ ልጅየው ወደ ትውልድ አገሩ ሴኔጋል ተመልሶ የፍርድ ሂደቱን ባለበት እንዲከታተል የተደረገው፡፡ ይሁን እንጂ ፓፓ ማሳታ በመጨረሻው የፍርድ ቤት ውሎ ችሎት ሳይቀርብ ቀርቷል፡፡ ይህም ላሚን ዲያክን እንዳስቆጣ ተዘግቧል፡፡ አባትና ልጅ ቀደም ሲል ከተጠረጠሩበት ወንጀል በተጨማሪ የሩሲያውያን አትሌቶችን የአበረታች ንጥረ ነገር ምርመራ ውጤት በማሸሽ የተጠረጠሩ ሲሆን ጠበቆቻቸው ወደ አገራቸው ሴኔጋል ተመልሰው የክስ ሂደቱን እንዲከታተሉ ያቀረቡት ጥያቄ በፈረንሳይ ፍርድ ቤት ውድቅ ተደርጎ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ፓፓ ማሳታ፣ የቀድሞው የሩሲያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ቫሌንቲን ባላክኒቼቭ እንዲሁም የቀድሞ የሩሲያ አትሌቲክስ አሰልጣኝ አሌክሲ ሜልኒኮቭ እኤአ 2016 ላይ በዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ከስፖርቱ እድሜ ልክ እንዲርቁ ማገዱ ይታወሳል፡፡ ቫሌንቲን ባላክኒቼቭና አሰልጣኝ አሌክሲ ሜልኒኮቭ በዚሁ የክስ ሂደት ውስጥ ጉዳያቸው እየታየ ቢሆንም የፈረንሳይ መንግስት ለረጅም ጊዜ በያዘው ምርመራ ለፍርድ ለመቅረብ ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል፡፡ በክስ ሂደቱ ከአዛውንቱ ዲያክ በተጨማሪ አማካሪያቸው የነበሩት ሃቢብ ሲሴና የቀድሞው የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የአሁኑ (የዓለም አትሌቲክስ) ፀረ አበረታች መድሃኒት ጉዳዮች መሪ የነበሩት ገብርኤል ዶል ጉዳይ እየታየ ይገኛል፡፡ ዲያክ በተጠረጠሩበት ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው ከተገኙ እስከ አስር ዓመት የሚዘልቅ እስር ሊፈረድባቸው እንደሚችልና ቀሪ የእድሜ ዘመናቸውን ወሕኒ ሊያሳልፉ እንደሚችሉ መረጃዎች ወጥተዋል፡፡ የፈረንሳይ የፋይናንስ አቃቤ ህግ ቢሮ እኤአ 2018 ላይ እንዳሳወቀው ዲያክ ስፖርትን ተገን አድርገው በሴኔጋል ለፖለቲካ ቅስቀሳ የሚውል ገንዘብ ከሩሲያ መንግስት ተቀብለዋል፡፡ ለዚህም የሩሲያውያን አትሌቶችን የአበረታች ንጥረ ነገር ምርመራ ውጤት በመሸሸግ ተደራድረዋል፡፡ በዚህ ድርድር ወቅትም ዲያክ ሞስኮ ካስተናገደችው የ2013 የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ቀደም ብለው ውድድሩን ከሚያሰራጩ የቴሌቪዥን ጣቢያዎችና ስፖንሰሮች ጋር በገንዘብ ተደራድረዋል፡፡ አዲስ ዘመን ሰኔ 13/2012ቦጋለ አበበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=34738
[ { "passage": "ኡጋንዳዊው እንደራሴ እና የጥበብ ሰው ቦቢ ዋይን\n\nቦቢ ዋይን ዕለተ ሰኞ ነበር በሃገር መክዳት ክስ ተከሶ ለፍርድ ከቀረበ በኋላ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶት በዋስ የተለቀቀው። \n\nነገር ግን የግለሰቡ ጠበቃ ቦቢ ዋይን ሐሙስ ምሽት ለዳግም እሥር መዳረጉን ለመገናኛ ብዙሃን አስታውቀዋል። \n\nጠበቃ ሮበርት አምስተርዳም ለቢቢሲ እንደተናገሩት «ምንም አንኳ ዳኛው ቦቢ ዋይን ፓስፖርቱን በእጁ እንዲይዝና ከሃገር ቢወጣም ምንም ጉዳት እንደሌለው ቢያሳውቁም ለሕክምና ለመሄድ ሲሞክር ነው አየር መንገድ ውስጥ የተያዘው።» \n\nአክለውም «እየገፈታተሩ ወደ ፖሊስ መኪና አስገቡት፤ የት እንደወሰዱትም አናውቅም፤ ስጋት ላይ አንገኛለን» ሲሉ ቃላቸውን ሰጥተዋል። \n\nበመዝገብ ስሙ ሮበርት ኪያጉላኒ በመባል የሚታወቀው ቦቢ ዋይን ሰኞ ዕለት ፍርድ ቤት በቀረበ ጊዜ በክራንች ድጋፍ ሆኖ ታይቷል። \n\nአጋሮቹ እንደሚሉት ፖሊስ ጣቢያ በነበረበት ወቅት ለፕሬዝደንቱ ቅርብ በሆኑ የጥበቃ ሰዎች ስቃይ ደርሶበታል። \n\nየሃገሪቱ የጦር ኃይል ግን ውንጀላው መሠረተ ቢስ ነው ሲል አጣጥሎታል።\n\n• 'ስቃይ የደረሰበት' ኡጋንዳዊ ፖለቲከኛ ተፈታ \n\nለመሆኑ ቦቢ ዋይን ማን ነው?\n\nአፍሮቢት በተሰኘው የሙዚቃ ስልት ጨዋታ የሚታወቀው ቦቢ ዋይን በኡጋንዳውያን ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይንት ያለው ሲሆን ከሙሴቬኒ መንግሥት ጋር ዓይን እና ናጫ ከሆነ ዓመታት ተቆጥረዋል።\n\nየሙዚቃ ሕይወቱን ትቶ ወደ ሕዝብ ፖለቲካ ዓለም ከመጣ ወዲህም የሕዝብ እንደራሴ ሆኖ በመመረጥ ምክር ቤቱን ሲያስጨንቅ ቆይቷል።\n\nከ75 ዓመት በላይ የሆነው ግለሰብ ለፕሬዝዳንትነት መመረጥ የለበትም በሚልም ሕገ-መንግሥቱ እንዳይነካ ቢታገልም አልተሳካላትም። \n\nየኡጋንዳ መንግሥት ፌስቡክና እና ዋትስአፕን የመሳሰሉ ማሕበራዊ ድር አማባዎች ሊቀረጡ ይገባል ብሎ ያወጣውን ሕግም በፅኑ ሲቃወም ቆይቷል። \n\n• ኡጋንዳዊው ሙዚቀኛ በሃገር ክህደት ተከሰሰ\n\n ", "passage_id": "e1407ee8b8c200ab7642a82a88f67128" }, { "passage": "የሳዑዲ አረቢያ ፍርድ ቤት ታዋቂዋ የሴቶች የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ሉጄይን አል- ሃትሉል ላይ ዛሬ የስድስት ዓመት እስራት ፈረደባት።ከአገሪቱ ብሔራዊ የዜና ምንጭች የወጣው መረጃ እንደሚያሳየው፤ በዛሬው ዕለት በሳዑዲ የተሰየመው የፀረ ሽብርተኛ ችሎት ባስተላለፈው ውሳኔ እ.አ.አ ከ2018 ጀምሮ ከሌሎች በደርዘን ከሚቆጠሩ የሴቶች የመብት ተሟጋቾች ጋር በእስር ላይ የምትገኘው ሉጄይን አል- ሃትሉል የኢንተርኔት መረብን በመጠቀም የውጭ ኃይሎችን አጀንዳ አራምዳለች በሚል ጥፋተኛ ብሏታል።ሉጄይን አል- ሃትሉል ወንዶች በሴቶች ላይ እንዲተገብሩት በሕግ የተሰጣቸው የሞግዚትነት ሥልጣን እንዲነሳ እና ሴቶች መኪና እንዲያሽከረክሩ እንዲፈቀድ ስትወተውትና ስትታገል ቆይታለች። ትግል ስታካሂድ ከቆየችባቸው ነገሮች አንዱ መኪና ማሽከርከር የተፈቀደ ሲሆን እርሷ ግን በእስር ላይ ትገኛለች።የሉጄይን ጉዳይ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ የሰብዓዊ መብቶች ጉዳዮች ባለሞያዎች እና የዩናይትድ ስቴትስ እና የአውሮፓ ሕግ አውጭዎች እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ተቃውመውታል።", "passage_id": "f9773b76e9f30f3d8397bb34540c88ce" }, { "passage": "የአልጀሪያ ወታደራዊ ፍርድ ቤት የቀድሞ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት አብዱላዚዝ ቡተፍሊካ ወንድም ላይ የ15 ዓመት እስር አስተላልፏል።በመንግስት ላይ ሴራ በመጎንጎን እና የሀገሪቱን ጦር ሚና ዝቅ አድርገዋል በሚል የቀድሞ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት አብዱላዚዝ ቡተፍሊካ ወንድም ሰይድ ቡተፍሊካ  እስሩ ተላልፎባቸዋል፡፡በተባባሪነት የተጠረጠሩ ሌሎች ሶስት ግለሰቦችም ተማሳሳይ እስር ተበይኖባቸዋል፡፡ለእስር የተዳረጉት ሁለት የሀገሪቱ የቀድሞ የደህንነት መስሪያ ቤት አለቃዎች እና እንድ የፓለቲካ ፓርቲ መሪ ናቸው፡፡ሰይድ ቡተፍሊካ የሀገሪቱ የቀድሞ ፕሬዚዳንት አብዱላዚዝ ቡተፍሊክ በስትሮክ ህመም ከተጠቁበት ጊዜ ጀምሮ ከጀርባ በመሆን የፕሬዚዳንትነቱን ስልጣን በመያዝ ሀገሪቱን ሲመሩ መቆየታው ይታወሳል፡፡ለእስር የተዳረጉትም በሀገሪቱ ላይ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለማወጅና የሀገሪቱን ጦር አለቃ አህመድ ጋይድ ሳላህን ከስልጣን ለማንሳት አሲረዋል በሚል ነበር።ምንጭ፦አልጀዚራ", "passage_id": "d4a000d36fb44ff761c85d92b7ce76ed" }, { "passage": "በተከሰሱበት ከገቢ ግብር ጋር በተያያዘ የወንጀል ድርጊትና የንግድ ፈቃድ ሳይኖራቸው ለኢትዮጵያውን ብቻ በተፈቀደ ሥራ ላይ ተሠማርቶ መገኘት ወንጀል የቅጣት ውሳኔ የተጣለባቸው አንድ ኢትዮጵያዊና ሁለት የሴሪላንካ ዜጎችን፣ ማረሚያ ቤት ከተደጋጋሚ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ በኋላ ፈታ፡፡መጋቢት 7 ቀን 2010 ዓ.ም. በአምስት ዓመታት ጽኑ የእስር ቅጣትና የተለያየ መጠን ያለው የገንዘብ ቅጣት የተጣለባቸው የአካፔ ኢምፔክስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ባለድርሻ አቶ አሸረፍ አወል፣ ሁለት የሲሪላንካ ዜጎች ሄትራጅግ ያጎንታ ሱሬንድሪናታና ፕናንዎታጅ አሲታ ሳራናት ናቸው፡፡ የተወሰነባቸውን የእስራት ቅጣት በአመክሮ (በማረሚያ ቤት የነበራቸው የባህሪና ጠቅላላ ሁኔታ ግምገማ ውጤት) ቅጣታቸውን መጨረሳቸውን ለፍርድ ቤት አመልክተዋል፡፡ በወቅቱ ሳይፈቱ የቀሩት ከሳሽ ዓቃቤ ሕግ በሥር ፍርድ ቤት የተሰጠውን ቅጣት በመቃወም ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ በማቅረቡ ሲሆን፣ ይግባኝ ሰሚው ችሎት ለግንቦት 1 ቀን 2010 ዓ.ም. ቀጠሮ በመስጠቱ ነው፡፡ ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤቱ የሰጠው ትዕዛዝ ፍርደኞቹ ማረሚያ ቤት የሚገኙ መሆኑን ጠቅሶ እንዲቀርቡ እንጂ፣ የእስር ትዕዛዝ ያልሰጠ መሆኑን ለፍርደኞቹ ሚያዝያ 1 ቀን 2010 ዓ.ም. በጻፈው ደብዳቤ አሳውቋል፡፡ ፍርደኞቹ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የጻፈላቸውን ደብዳቤ ይዘው ለሥር ፍርድ ቤት ሲያመለክቱ፣ ፍርድ ቤቱ የታራሚዎች ጥበቃና ደኅንነት አስተዳደር ዘርፍ አስተባባሪ ዋና ኦፊሰር አላምረው ተረፈን ጠርቶ አነጋግሯቸዋል፡፡  ፍርደኞቹ አመክሮ የሚያገኙበት ወይም የሚያስከለክል ችግር እንዳለባቸውና እንደሌለባቸው የተጠየቁት አስተባባሪው፣ የሚያስከለክል እንደሌለ ምላሽ ሰጥተው መፍታት ያልቻሉት ግን ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርደኞቹ ግንቦት 1 ቀን 2010 ዓ.ም. እንዲቀርቡ ትዕዛዝ በመስጠቱ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ በሰጣቸው ምላሽ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ‹‹ይቅረቡ›› እንጂ፣ ‹‹እንዳይፈቱ፤›› የሚል ትዕዛዝ ስላልሰጠ፣ በዕለቱ ሚያዝያ 17 ቀን 2010 ዓ.ም. እንዲፈቱ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር፡፡ ማረሚያ ቤቱ እስከ ሚያዝያ 19 ቀን 2010 ዓ.ም. ባለመፍታቱ የፍርደኞቹ ጠበቆች፣ ደንበኞቻችንን ማረሚያ ቤቱ ሊፈታልንና የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ ሊፈጽም ስላልቻለ፣ በኃላፊዎቹ ላይ ዕርምጃ ተወስዶ ዛሬውኑ እንዲፈቱ ትዕዛዝ ይስጥልን የሚል አቤቱታ ለፍርድ ቤቱ አቅርበዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም ሌላ ትዕዛዝ የሰጠ ቢሆንም፣ ማረሚያ ቤቱ ግን አቶ አሸረፍ አወልን ሐሙስ ሚያዝያ 19 ቀን 2010 ዓ.ም. ከሰዓት በፊት ሊፈታቸው በመቻሉ ትዕዛዙ ቀሪ መሆኑ ታውቋል፡፡ ሁለቱ ሲሪላንካውያን ከአገር እንዳይወጡ ዕግድ የተጣለባቸው ከመሆኑ አንፃር ከእስር ቢፈቱ በምን ሁኔታ መቆየት እንደሚችሉ ከሕግ አንፃር መርምሮ ለመወሰን፣ ለሚያዝያ 23 ቀን 2010 ዓ.ም. የተሰጠው ቀጠሮ እንደተጠበቀ ቀጥሏል፡፡ የሥር ፍርድ ቤት አቶ አሸረፍ አወል አምስት ዓመታት ጽኑ እስራትና 80,000 ብር፣ ድርጅታቸው አካፔ ኢምፔክስ 15,000 ብር፣ ሁለቱ የውጭ ዜጎች እያንዳንዳቸው 100,000 ብርና አምስት ዓመታት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ መወሰኑን መዘገባችን ይታወሳል፡፡   ", "passage_id": "6270653f98d4ae2106b4aff7769d7e7b" }, { "passage": "የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የሃይማኖቶች ነፃነት ኮሚሽን በእነ አቡበከር አህመድ መዝገብ የተከሰሱ ግለሰቦች ላይ የተሰጠው የጥፋተኝነት ብይንና ቅጣት ተገቢነት የለውም አለ፡፡ሐምሌ 27 ቀን 2007 ዓ.ም. የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት በተከሳሾቹ ላይ ከሰባት እስከ 22 ዓመታት ፅኑ እስራት መወሰኑን መዘገባችን ይታወሳል፡፡‹‹ተከሳሾቹ ወንጀለኞች ሳይሆኑ ሰላማዊ የሃይማኖት ነፃነት አቀንቃኞች ናቸው፤›› ያሉት የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ዶ/ር ሮበርት ጆርጅ፣ ‹‹የክስ ሒደቱ የኢትዮጵያ መንግሥት የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችንና ተቃዋሚዎችን ፀጥ ለማድረግ የፀረ ሽብርተኝነት አዋጁን መጠቀም መቀጠሉን ያሳያል፤›› ብለዋል፡፡ኮሚሽኑ የአሜሪካ መንግሥት በጉዳዩ ላይ ተቃውሞውን እንዲያቀርብ ጥሪ አድርጓል፡፡ የኮሚሽኑ አባላት እ.ኤ.አ. በ2012 ኢትዮጵያን ሲጎበኙ የተከሳሾቹ የፍርድ ሒደት ችግሮች እንደነበሩበት መረዳታቸውን፣ ከእነዚህም መካከል አንዱ የእስር አያያዛቸው በሕግ መሠረት የማይከናወን እንደነበር አስታውሷል፡፡በኮሚሽኑ መግለጫ ላይ መንግሥት አስተያየት እንዲሰጥ ጥረት ቢደረግም፣ የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት መግለጫውን እንዳላዩት ገልጸዋል፡፡", "passage_id": "37e14e2955ae40a96d33cefaef8d05c1" } ]
27943446e34b5bd1cddc1e4b2137fc9a
94abbf8e37da82febbb057ee77459c41
ሰብዓዊነትን የታጠቀው የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሀሳብ
ስፖርት ሰላም፣ ፍቅር፣ የአብ ሮነትና የአንድነት፣ የመተሳ ሰብ፣ የወንድማማችነት ልዩ መገለጫ ነው። ስፖርት ዘር፣ ሃይማኖት፣ ፆታና ቀለምን አይለይም። በየት ኛውም ሁኔታ ውስጥ የስፖርታዊ እንቅስቃሴ አስኳል ሃሳብ ወዳጅነትና መተሳሰብ መሆኑ ይታወቃል። በታሪክ ገጾች እንደሰፈረውም በሰው ልጅ ታሪክ ባጋጠሙ በጎም ሆኑ መጥፎ ክስተቶች ስፖርት በአጋርነት ተሳትፏል። ስፖርታዊ ክንዋኔዎች ሰላምንና አንድነትን የሚሰብኩ እንደመሆናቸው በማህበራዊ፣ ፖለቲ ካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች በመግባት ሚናቸውን ሲወጡም ኖረዋል። ስፖርት ሰብዓዊነትን ያነገበ የልግስና ማዕድ መሆኑን ዘመነ ኮሮና በተጨባጭ አሳይቶናል። የቫይረሱ ስጋትነት በዓለም አቀፉ የጤና ተቋም ከተረጋገጠበት ጊዜ ጀምሮ፤ ውድድሮችን ከማቋረጥና ከመሰረዝ ባለፈ የስፖርቱ ተዋንያን በተናጠልም ሆነ በተቋማዊ ደረጃ አበርክቷቸውን ሲወጡ ታዝበናል።በስፖርቱ ዘርፍ ዓለም አቀፍ ዝናን ካተረፉ ግለሰቦች እስከ ዓለም አቀፍ ተቋማት ድረስ ወረርሽኙን ለመመከት እየተደረገ ባለው ርብርብ ከተሳትፎ አልጎደሉም።በተለያዩ ሀገራት ዓለም አቀፉን ወረርሽኝ ለመዋጋት በስፖርቱ ማኅበረሰብ ዘንድ የታየው ተሳትፎ በሀገራችንም ተመሳሳይ ሲሆን ታዝበናል። በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት ይፋ ከተደረገበት ከወርሃ መጋቢት መጀመሪያ አንስቶ የስፖርቱ ማህበረሰብ ድርሻ ግዙፍ ነው።በስፖርት ዘርፍ የሚገኙ የመንግሥትና የግል ተቋማት፣ የስፖርት ማህበራት፣ ተጫዋቾች፣ አትሌቶች፣ የእግር ኳስ ክለቦችና ተጫዋቾች ወረርሽኙን ለመከላከል የሚደረገውን ርብርብ ተሳትፎ ሲያደርጉ ነበር።በስፖርት ማህበረሰቡ በኩል ሰብዓዊነትን መሰረት አድርጎ ህዝባዊነትን በመታጠቅ «ወገን ለወገን » ደራሽነቱን በገንዘብና በቁሳቁስ ድጋፍ ሲደረግ የታዘብንበት ሁኔታ ፤ስፖርት ሰላም፣ ፍቅር፣ የአብሮነትና የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የወንድማማችነት ልዩ መገለጫ የመሆኑን እውነታ በተግባር አስረድቷል።የኮሮና ወረርሽኝ በዓለም ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ መስተጋብር ላይ ያሳደረው ተጽእኖ መዘዙ ዓለም አቀፉን የስፖርት ቁመና የኪሳራ መልክ ያላበሰው ነበር ።በስፖርቱ ላይ የደረሰው ከፍተኛ የሆነ የፋይናንስ ቀውስ የተጽእኖው ሰንሰለት ዛሬ ላይ የሚቆም ሳይሆን እስከ ቀጣዮቹ አስር ዓመታት የሚጓዝ እዳን ያስከተለ መሆኑን ነው ጥናቶች ያመላከቱት።በወረርሽኙ ምክንያት ከፍተኛ መቃወስን ካስተናገዱ መካከል የስፖርት ዘርፍ ዋነኛ ነበር።ይህም በስፖርቱ ማህበረሰብ በኩል ወረርሽኙን ለመዋጋት እየተደረገ በሚገኘው ርብርብ እያደረገ ያለው ተሳትፎ ስፖርት ትልቅ ማህበራዊ ኃላፊነትን የተሸከመ ግዙፍ ተቋም መሆኑን ያመላክታል። በዓለም አቀፍ ደረጃ እንደታዘብነው ሁሉ በሀገራችን የስፖርት ማህበረሰቡ ከነጉዳቱ ትልቅ ተሳትፎ ሲያደርግ ነበር።በዘመነ ኮሮና የስፖርት ቤተሰቡ ሰብዓዊነትን ያነገበ ተግባር በይበልጥ ተጠናክሮ እንደቀጠለ የሚያሳይ መረጃ ከአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አካባቢ የወጣው መረጃ ያመላክታል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በኮሮና ቫይረስ ( ኮቪድ_19) ወረርሽኝ ምክንያት ለተቸገሩ 300 የሁለተኛ ዲቪዚዮን ክለብ አትሌቶች፣ ዳኞችና አሰልጣኞች የሰብዓዊ ድጋፍና ስለ ቫይረሱ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐ ግብር ማዘጋጀቱን አስታውቋል።«ለአትሌቶቻችን እንቁም» በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ ስታዲየም ዛሬ ማለዳ የሚደረገው የድጋፍና ግንዛቤ የማስጨበጫ መርሐ ግብር የስፖርቱ ቤተሰብና ማህበረሰብ ለሰብዓዊነት ተግባር የሚሰጠው ቦታ ምን ያህል ሰፊና ጥልቅ መሆኑን በዘመነ ኮሮና በይበልጥ የሚያሳይበት እንደሚሆን ተጠቁሟል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ቢኒያም ምሩፅ ይፍጠር እንደተናገሩት፤የኮቪድ -19 ወረርሽኝ ስጋት በአትሌቲክሱ ስፖርት እና ስፖርተኞችም ላይ ጥላውን ያጠላ መሆኑን ገልጸዋል ።በመሆኑ ከዚህ ችግር ተሻግረን ነገ የምንፈልገውን ውድድርና ውጤት ለማስመዝገብ ዛሬ መረዳዳት ይኖርብናል።ስለዚህ በሁለተኛ ዲቪዚዮን ክለብ የሚገኙ አትሌቶች፣ አሰልጣኞች፣ የታዳጊ ወጣቶች ፕሮጀክት አሰልጣኞች፣ እና ዳኞች ቁጥራቸው 300 ለሚሆኑ የስፖርቱ ቤተሰቦች በዛሬው እለት የሰብዓዊ ድጋፍ ሊደረግ መሆኑን አመልክተዋል። በኢትዮጵያ አትሌቲክስ የትልቅ ታሪክ ባለቤት ከሆኑት አትሌቶች አንዱ የሆነው ማርሽ ቀያሪው ምሩጽ ይፍጠር ልጅ የሆኑት አቶ ቢኒያም ፤«ነገን እንሻገራለን፣ የምንፈልገውንና የምንወደውን አትሌቲክስ ስፖርታችንን እናስቀጥላለን ዛሬ ላይ በህብረትና በአንድነት ቆመን ልንደጋገፍና ልንረዳዳ ይገባል» ሲሉም ሰብዓዊነትን የታጠቀውን መርሐ ግብር አስፈላጊነት የተናገሩት። የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለአትሌቲክስ የዘወትር አጋር ከሆነው ከሞሐ ለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማህበር ጋር በመተባበር የሰዋዊ ድጋፍና የግንዛቤ ማስጨበጫው የሚከናወን መሆኑንም ነው ያስታወቁት። አዲስ ዘመን ሰኔ 12/2012ዳንኤል ዘነበ
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=34669
[ { "passage": "ከቃለ ምልልሱ አስቀድሞም ስለ ማናጀሩ ጥቂት ነገር እናንሳ። አቶ ተድላ በሰውነት ማጎልመሻ መምህርነት የስራ ዓለምን የተቀላቀሉ ሲሆን፤ በመስኩ በዲግሪ ደረጃ ትምህርት መሰጠት ሲጀምር በኮተቤ መምህራን ማሰልጠኛ ገብተው በ1988ዓ.ም ዲግሪያቸውን ወስደዋል። በቀጣዩ ዓመትም በአማራ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሲሰሩ ቆዩ፤ ከ1996ዓ.ም ጀምሮም በአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን በተለያዩ ኃላፊነቶች አገልግለዋል። በዚሁ ጊዜ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ያጠናቀቁ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የውድድር ዳይሬክተር በመሆን እስከ 2007ዓ.ም ቆይተዋል። ከ2009 ዓ.ም ጀምሮም በፌዴሬሽኑ የክለቦች ህጋዊነት ፍቃድ አሰጣጥ ማናጀር ሆነው እያገለገሉ ሲሆን፤ በስፖርት ማኔጅመንት የሶስተኛ ዲግሪያቸውን ለማጠናቀቅ የመመረቂያ ጽሁፍ በማዘጋጀት ላይ ይገኛሉ። በመጀመሪያ ደረጃ ታሪኩን በደንብ መያዝ ያስፈልጋል፤ እንዴት ነበርን የሚለውን ለማወቅም ከጊዜ ጋር ማነጻጸር ይገባል። የዚያኔ የነበረው የእግር ኳስ እድገት ምን ይመስላል ስንል፤ በወቅቱ ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠው ቢመስልም ከገንዘብ ጋር የተያያዘ አልነበረም። ይልቁኑ ለስፖርቱ ፍቅር፣ ለማሊያ እንዲሁም የወከሉትን አካል ለማስጠራት የሚደረግ ውድድር ነበር፤ አመራሩም በዚህ ውስጥ የተካተተ ነው። አሁን ስፖርቱ ትልቅ ኢንዱስትሪ ሆኗል፤ በመሆኑም ትክክለኛ የስፖርት አመራር ይፈልጋል። ዓለም ተቀይሯል አንድ ወደ መሆኑም ነው፤ ኢትዮጵያም በዚህ መንገድ መጓዝ ይገባታል። 86 የሚሆኑ ክለቦች አሉ፤ እነዚህ ክለቦች በፕሪሚየር ሊግ፣ ከፍተኛ ሊግ እና አንደኛ ሊግ የሚጫወቱ ናቸው። ክልሎች የሚያወዳድሯቸው ሌሎች የዲቪዚዮን ክለቦች አሉ፤ በፌዴሬሽኑ የተመዘገቡት ግን እነዚህ ናቸው። ይህ መሰረታዊ ጥያቄ ሲሆን፤ አንድ ክለብ፤ ክለብ ለመሰኘት አምስት መስፈርቶችን ማሟላት ይጠበቅበታል። እነርሱም የመወዳደሪያ ቦታ መያዝ፣ የወጣቶች ልማት፣ የሰው ሀብት አስተዳደራዊ መዋቅር፣ የፋይናንስ ሥርዓት (የገቢ እና ወጪ ሥርዓት) እንዲሁም ህጋዊነት ናቸው። የትኛውም ክለብ የጸደቀ የልማት ፕሮግራም እንዳለው በቅድሚያ መታየት አለበት። ቀስ በቀስም የሜዳ ባለቤት መሆን ይኖርበታል፤ ካልቻለም በኮንትራት መጠቀም ይገባዋል። ከዚህም ጋር ተያይዞ ጥራት መሰረታዊ ጉዳይ እንደመሆኑ ቢያንስ ሜዳው የተከለለ፣ መልበሻ ክፍሎችና መጸዳጃ ቤቶች ያሉት መሆን አለበት። ይህ ካልሆነ ግን ከመስፈርቱ አፈንግጧል ማለት ነው። የሰው ኃይል አደረጃጀቱ ምን ይመስላል በሚለው ስርም፤ ቋሚ ጽህፈት ቤት፣ ማናጀር፣ የክለብ ኃላፊ፣ የጸጥታ ክፍል፣ … እያለ የሚቀጥል መስፈርት ይገኛል። የክለቡ መተዳደሪያ ምንድነው፤ ወጪና ገቢውስ ምን ይመስላል የሚለውም መታየት አለበት፤ እስካሁንም በፌዴሬሽናችን ያልተሰራበት ነገር ይህ ነው። ክለቦች እንዲጠይቁም ሆነ ተጠያቂ እንዲሆኑ ህጋዊ መሆን ይገባቸዋል። እነዚህን የሚያሟላ ከሆነም አንድ ክለብ አቋሙ የተስተካከለ ነው ለማለት ያስችላል። አሁን በዚህ ላይ እየሰራን ሲሆን፤ የመጀመሪያው የፕሪሚየር ሊግ ክለቦችን ህጋዊ ማድረግ ነው፤ በቀጣይም በየደረጃው ስራው ይቀጥላል። የማያሟሉ ከሆነም ከውድድር እንዲወጡ ይደረጋል። እስከ ሰኔ 30 ድረስ ክለቦች መታየት አለባቸው። ያሉበትን ሁኔታ የማወቅ ስራውም በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል፤ ከ16ቱ የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች አስር የሚሆኑት ታይተው የሚቀሩት ስድስቱ ብቻ ናቸው። አሁን ክለቦቻችን በምን ላይ እንደሚገኙና ምን እንደሚመስሉ በመገምገምና በመፈተሽ ላይ እንገኛለን። የእዚህን ሪፖርትም የመጀመሪያው ውሳኔ ሰጪ አካል ይመለከተውና ሙሉ ፍቃድ ሊሰጠው፣ በገደብ ሊሰጠው አሊያም አይችልም ሊል ይችላል። ይሄ ገና በሂደት ላይ ያለ ነው፤ ነገር ግን የሚያስከፋ አይደለም። ነገ ከነገ ወዲያ ሊሻሻሉ እንደሚችሉም ማሰብ ተገቢ ነው። በአደረጃጀት በኩል ጥሩ ነገር እንዳላቸው ማየት ይቻላል፤ በሜዳ በኩል ከማዘጋጃ ቤት ጋር የተያያዘ ነገር ነው፤ በመንግስት በኩልም ጥሩ ነገር እየተሰራ ይገኛል። ይህ መስፈርት በ2006ዓ.ም ነው ከፊፋ የወረደው፤ የትኛውም የስፖርቱ ተሳታፊ የሆነ አካልም ወስዶ ተግባራዊ ያደርገዋል። ከዚህ ቀደም የክለብ ፈቃድ አሰጣጥ ውይይት ተደርጎበት የፌዴሬሽኑ መተዳደሪያ ደንብ ላይ እንዲካተት ተደርጓል። በእኛ በኩልም ለክለቦች መስፈርቶቹን እንዲያሟሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ እና ቴክኒካዊ ድጋፍም እናደርጋለን በዚህም ደስተኞች ናቸው። ፍቃዱ በየሁለት ዓመቱ የሚታደስ ከመሆኑ ጋር በተያያዘም መሻሻል መኖሩ ተገምግሞ ነው የሚሰጠው። ክለቦች ምን ያህል ገንዘብ አላቸው? ለውድድር ዓመቱስ ይበቃቸዋል? የሚለው በትክክል አለመታወቁ ነው ችግር የሚፈጠረው። አንዳንድ ጥሩ ስራ የሚያከናውኑ ክለቦች አሉ፤ ነገር ግን ይህንን ጠበቅ አድርገው እና በሰነድ አጅበው የሚይዙት ጥቂቶቹ ናቸው። ይህ የሚሆነውም ክለቡን የሚመራው አካል የስፖርት ሳይንስ ባለሙያ ሲሆን ነው። ስራውን አንድን ክለብ ክለብ ለማሰኘት ብለን ሳይሆን፤ ክለቡ በዚህ አደረጃጀት ውስጥ መግባት አለበት ብለን ነው የምንሰራው። ችግሩ ገቢ ሳይኖር እንደ ላሜ ቦራ ገንዘቡን ዝም ብሎ ማፍሰሱ ነው። ስለዚህ ክለቦች የራሳቸውን ገቢ እንዲያመነጩ ማድረግ ይገባል። በእርግጥ በአንዳንድ ክለቦች ገቢ ለማመንጨት እየሞከሩ ነው፤ ነገር ግን በትክክለኛው ሰዓት ሁሉም በዚህ መካተት አለባቸው። በክለቡ፣ በተጫዋቾች በደጋፊዎች እንዲሁም በስፖርቱ ትልቅ ለውጥ ያስከትላል። በትክክል እነዚህ መስፈርቶች ቢተገበሩና በትክክለኛው የስፖርት አስተዳደር ቢመሩ ደግሞ አሁን የሚታየው የክለቦች መፍረስ እና ፖለቲካዊ ችግሩ ባልታየ ነበር። የክለቦች በመንግስት ላይ መንጠልጠል አሁን የጀመረ ባይሆንም አሁን የአመሰራረታቸው ስልት ፈር እየለቀቀ ነው። የክለቦች አሰያየም ትክክል በሆነ አካሄድ ላይ አይገኝም። እንበልና ትግራይ ፖሊስ እና ደቡብ ፖሊስ ተጫውተው አንዱ ሌላኛውን አሸነፈ ቢባል ተሸናፊው ምን ሊሰማው ይችላል? በቀደመው ጊዜ የነበሩ ለአብነት ያህል የመከላከያና የፖሊስ ክለቦች፤ መቻል፣ አየር ኃይል፣ ኦሜድላ፣… የሚል ስያሜ ነበራቸው። ይህ በወቅቱ አመራር የነበሩት አካላ – እስካሁን የውድድር ፈቃድ እንጂ የህጋዊነት ፍቃድ አልሰጠንም። ከዚህ በኋላ ወደዚያ የምንግባ ቢሆንም፤ አሁንም ትልቅ የቤት ስራ አለብን። ክለቦቻችን ምን ዓይነት ስም ይዘው ይምጡ የሚለው በጥናት ላይ በተመረኮዘ አካሄድ አንድ ነገር ላይ እንደሚደርስ ተስፋ አደርጋለሁ። እግር ኳሱ ከፖለቲካ የጸዳ መሆን አለበት፤ እግር ኳስ የሰላምና ፍቅር መድረክ እንጂ በምንም ዓይነት የድብድብ መድረክ መሆን የለበትም። ስፖርቱን የሚመራው አካልም ከዚህ የጸዳ መሆን ይገባዋል። ይህ የኢትዮጵያ እግር ኳስ እንደመሆኑ የኢትዮጵያዊነትን ስሜትን እንዳይነካ ያሉት ህጸጾች በሙሉ መጽዳት አለባቸው። እኔም አመሰግናለሁ፤ በተለይ ክለቦቻችን ምን ይመስላሉ የሚለውን በማንሳታችሁ ደስተኛ ነኝ። ት የተጠቀሙት ስልት\nነው፤ የተመልካችን ስሜታዊነትም ይቀንሳል። አሁን ያለው ስያሜ ግን ስጋት ነው፤ ለፌዴሬሽኑም ትልቅ የቤት ስራ ነው። ዓለም አቀፎቹ\nአካላትም በብሄር፣ በጎሳ፣\nበሃይማኖትና በመሳሰለው የሚመሰረቱ\nክለቦች ተቀባይነት የላቸውም፤\nከኦሊምፒክ መርህም ውጪ ነው።\nበመሆኑም የክለቦች ስያሜ\nከዚህ እሳቤ የጸዳ\nመሆን ይገባዋል። ፌዴሬሽኑም\nእንዲህ ዓይነት ስሞችን\nየሚያስቀር ይመስለኛል። በእኛ\nበኩል ክለቦች ሲመሰረቱ\nእንዲህ ዓይነት ስሞች\nባይሰጡ የሚል ግብዓት\nለጽህፈት ቤቱ እንሰጣለን፤\nልክ እንደ ውጪዎቹ\nክለቦች በከተማ መሰየምም\nይቻላል። ከዚህ ባሻገር\nያለው የጎሳ ስም በመያዝ\nየሚመሰረት ክለብ ትክክል\nአይደለም። ፌዴሬሽኑም በጥናት\nላይ በተመረኮዘ አካሄድ\nመፍትሄ የሚሰጠው ይመስለኛል።አዲስ ዘመን ሰኔ 3/2011 ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "fcdbcafa1ad0d59d9309b9ff2f0aca08" }, { "passage": "የሲድኒ ኦሊምፒክና የኤድመንተን የዓለም ቻምፒዮና የማራቶን አሸናፊው ጀግና አትሌት ገዛኸኝ አበራ በአትሌቲክስ የውድድር ዘመኑ ታሪክ የሚዘክራቸው ገድሎችን ፈፅሟል፡፡ ከሩጫ ሕይወቱ በኋላም በሆቴልና ሪዞርት እንዲሁም በሌሎች የኢንቨስትመንት ስራዎች ተሰማርቶ በአትሌቲክስ የውድድር ዘመኑ የፈፀመውን ጀግንነት ለበርካታ ኢትዮጵያውያን የስራ እድል በመፍጠር ደግሞታል፡፡ ከንግድና\nኢንቨስትመንት ስራው የሚተርፈውን ውድ ጊዜ ሰውቶም የኢትዮጵያን አትሌቲክስ ወደ ፊት ለማራመድ በሚደረገው ጥረት የራሱን አሻራ ለማሳረፍ\nወደ አመራርነቱ መጥቷል፡፡ ከአራት ዓመት በፊት ኃይሌ ገብረስላሴን የመሳሰሉ ጀግና አትሌቶች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን ለመምራት\nወደ ፊት በመጡበት አጋጣሚ የስራ አስፈፃሚ አባል ለመሆን ተወዳድሮ በአንድ ድምፅ ልዩነት ሳይሳካለት ቀርቷል፡፡ ከሦስት\nሳምንታት በፊት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን ሲያካሂድ በተደረገው የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ምርጫ ገዛኸኝ\nስፖርቱን በአመራርነት ለማገልገል እድሉን አግኝቷል፡፡ ጀግናዋ አትሌት ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ሆና በተመረጠችበት\nአጋጣሚ ገዛኸኝም የአዲሱ አመራር አንድ አካል ሆኗል። ለቀጣይ አራት ዓመታትም የፌዴሬሽኑ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንትና የቴክኒክ\nኮሚቴ ሰብሳቢ ሆኖ ያገለግላል፡፡ ገዛኸኝ በቀጣዮቹ አራት ዓመታት አዲሱ የፌዴሬሽን አመራር ሊገጥሙት የሚችሉ እንቅፋቶችን፣ አትሌቲክሱን\nአሁን ካለበት ቁመና የተሻለ ለማድረግ ያሉ ተስፋዎችን እንዲሁም በስፖርቱ ዙሪያ የተለያዩ ሃሳቦችን ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረገው\nቃለ ምልልስ እንደሚከተለው ይናገራል፡፡ አዲስ ዘመን፡- ከአራት ዓመት በፊት ለስራ አስፈፃሚነት ተወዳድረህ በአንድ ድምፅ ሳትመረጥ ቀርተሃል፣ እነ ኃይሌም ተመርጠው ወደ አመራርነት ቢመጡም እንደታሰበው ሳይሆን ቀርቶ ብዙም ሳያገለግሉ ለቀው ወጥተዋል፡፡ ይህን ስትመለከት ዳግም ወደ ምርጫ ለመምጣት ተስፋ አልቆረጥክም?ገዛኸኝ አበራ፡- እውነት\nለመናገር የዛሬ አራት\nዓመት በአንድ ድምፅ\nልዩነት ወደ ፌዴሬሽን\nአመራርነት ሳልመጣ ቀርቻለሁ፣\nያም የሆነበት በፊት\nየተቀመጡ የራሱ መስፈርቶች\nአሉት፣ ክልሎችም እዚህ\nላይ የራሳቸው ስልጣን/ማንዴት;\nአላቸው፣ እዚህ ጋር\nትልቁ ነገር የዓለም\nተሞክሮ በስፖርቱ ውስጥ\nያለፉና ሳይንሱን የተማሩ\nሰዎች ናቸው ፌዴሬሽንና\nኦሊምፒክ ኮሚቴን የሚያገለግሉትና\nየሚመሩት፣ እኛ ይህንን\nለመቀየር ነበር የመጣነው፣\nከዚያ በፊት የአትሌት\nተወካይ በሚል እንጂ\nበሥራ አስፈፃሚነት ፌዴሬሽንና\nኦሊምፒክን ለመምራት ምንም\nአይነት እድል አልነበረም፤\nቀዳዳዎች ጠባብ ነበሩ፡፡\nወደ\nፌዴሬሽን የሚመጡት የፖለቲካ\nሹመኞች ነበሩ፡፡ ክልሎችም\nየሚልኩት እነሱን ነበር፡፡\nይህንን ባህል ለመቀየር\nእኔ ሃይሌ፣ገብረ እግዚአብሄር፣ደራርቱና\nሌሎችም ያደረግነው ጥረት\nበመገናኛ ብዙሃን ጭምር\nእስከ መሰዳደብ የደረሰ\nነበር፣ እኛ\nያሳለፍንባቸው ብዙ ነገሮች\nአሉ፣ እኛ በምንሮጥበት\nወቅት ብዙ ውጣ\nውረዶች ነበሩ፣ በዚያ\nውስጥ ሆነን ታግለን\nነው የአገርን ባንዲራ\nከፍ አድርገን ያውለበለብነው፣\nያ ውጣ ውረድ\nበአሁኖቹ አትሌቶች እንዳይደገም\nብለንም ነው ወደ\nአመራርነት ለመምጣት የወሰነው፡፡\nየትኛውንም\nፌዴሬሽን የሚመራ ከፕሬዚዳንት\nጀምሮ እስከ ታችኛው\nእርከን በመቧደንም በመያያዝም\nእርስበርስ ችግር ነበር፣\nይህን ሰብሮ መግባት\nችግር ከመሆኑም በላይ\nየተቀመጠ ወጥ አሰራር\nአልነበረም፣ አሁንም ቤቱን\nእያስተካከልን ነው ያለነው፣\nሰው ነንና ጉድለቶች\nይጠፋሉ ማለት አይቻልም፣\nእኛ ከአመራር የመጣን\nሰዎች አይደለንም፣ በርግጥ\nበግል የተለያዩ ተቋማትን\nእንመራለን፣ እነሱም ቢሆኑ\nግን እንደ ባለቤትነት\nከሆነ በሙያ ነው\nየሚመሩት፣ ሙያተኛ ቀጥረንም\nነው እንዲመራቸው የምናደርገው፣\nከራሳችን ተቋም በበለጠ\nግን ፌዴሬሽን ብንመራ\nይሻላል ብየ አስባለሁ፡፡\nፌዴሬሽን\nውስጥ ገብተን ስንመራ\nብቻችንን ሳይሆን በስፖርት\nሳይንስ ተቀጥረው የሚሰሩ\nከጽሕፈት ቤት ኃላፊ\nጀምሮ አሉ፣ በዋናነት\nግን ስራው ምን\nይፈልጋል፣ በቅንነትና በየኔነት\nስሜት ከላይ ሆኖ\nመምራት ያስፈልጋል፣ እኛ\nበስፖርት ውስጥ ስላለፍን\nስፖርቱና አትሌቱ ምን\nይፈልጋሉ፤ እንዴት አድርገን\nነው አትሌቱን ወደ\nፊት ማምጣት ያለብን\nብለን ታች ድረስ\nወርደን ለማየት አንድ\nየፖለቲካ ሹመኛ መጥቶ\nፌዴሬሽን ከሚመራው በበለጠ\nበመርህ ብቻም ሳይሆን\nበተግባር በእርግጠኝነት በስፖርቱ\nውስጥ ያለፈው የተሻለ\nነው፣ ይህ ማለት\nግን ችግሮች አይገጥሙም\nማለት አይደለም፣ ሰው\nበሕይወቱ ውስጥ በሚኖረው\nውጣ ውረድ ውስጥ\nብዙ ተስፋ የሚያስቆርጡ\nነገሮች እንዳሉ ሁሉ\nብዙ ጥሩ ነገሮችም\nአሉ፣ በዚያ ውስጥ\nአልፎ ለትውልድ አንድ\nነገር ጥሎ ማለፍና\nየሚረከበውም ትውልድ አንተ\nያጎደልከውን አስተካክሎ ማስረከብ\nነው ያለበት፡፡ በዚህ ቅብብሎሽ ውስጥ ምንም ተስፋ የሚያስቆርጥ ነገር የለም፣ አንድ ነገር ተስፋ አስቆርጦኛል ተብሎ ሕይወት አይቆምም፣ ይሕን ሕይወት ደግሞ ከኛ በላይ የሚያውቀው አለ ብየ አላስብም፣ በብዙ ውጣ ውረዶች አልፈን እንጀራ የበላንበት፣ ቤተሰብ የመራንበትና ተቋሞችን መስርተን የተለያዩ ስራና ሰራተኞችን ቀጥረን እየሰራን ያለንበት ሙያ ነው፣ ለዚያም ነው ትንሽም ቢሆን አስተዋፅኦ ማበርከት ከቻልን ብለን ወደ አመራርነቱ የምንመጣው፣ እንታገላለን ከዚያም ነገሮችን እናስተካክላለን፣ የቀረውን ደግሞ ሌላ ትውልድ ያስተካክለዋል፣ ስለዚህ ተስፋ የሚያስቆርጥ ነገር የለም፡፡ በግልፅ የወጡ ችግሮች አሉ ብየ አላስብም፣ እነ ኃይሌም ቢሆኑ አሁንም ከፌዴሬሽኑ የራቁ አይምሰልህ፣ አብረን እየሰራን ነው ያለነው፣ በእርግጥ እሱ የራሱን ብዙ ተቋማት ነው የሚመራው፤ ጊዜ የለውም ። ችግሮችን ነቅሶ አለማውጣት አለ፣ ችግሮች አይፈጠሩም ማለት አይቻልም ።ሰውና ተቋም እስከ መራን ድረስ ችግር አይኖርም ብሎ መደምደም ከባድ ነው፣ የምንመራው ተቋምም ሆነ ሰው ቀድሞ የነበረ እንደመሆኑ የተለያየ ፍላጎትና ሃሳብ ሊኖር ይችላል፡፡ ከለውጡ በፊት የነበሩ ችግሮች ስፖርቱ ውስጥ የገቡበት አጋጣሚ አለ፣ ይህንን መንፈስ መቀየር ያስፈልጋል፣ ስፖርት ከፖለቲካ ውጪ መሆን አለበት፣ እኔ ኦሮሞ ሆኜ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያውለበለብኩት የኢትዮጵያን ባንዲራ ነው፣ ሌላውም ከተለያየ ቦታ መጥቶ ተመሳሳይ ነገር ነው የሚያደርገው ወይም ማድረግ ያለበት፣ ይሄ እንዲህ ነው ያኛው እንዲያ ነው ብለን ያሰብንበት ጊዜ አልነበረም፣ ይህ መንፈስ ሙሉ ለሙሉ የለም ብየ አላስብም፣ ችግሮች አሉ፣ እነዚህ ችግሮች ሰዎች የራሳቸውን ፍላጎት ለመፈፀም ሲፈልጉ የሚፈጥሯቸው ናቸው ።መቼም ፈርዶብናል፤ ይሄ የብሔርተኝነት ጉዳይ ሰዎች ጉድለቶቻቸው ሲነገራቸው እንደ ማስተካከል በብሔር የሚሸሸጉበት ሁኔታ አለ፣ በሚዲያውም ረገድ ክፍተቶች አሉ፣ አንድ ነገር ሲፈጠር አንዱን ወገን ብቻ ይዞ ነገሮችን የማራገብ ችግር ይስተዋላል ። እንደዚያ የሚሉ ሰዎች ምናልባት ሥራቸውን ትተው የሌላውን ስራ የሚሰሩ ይሆናሉ ብዬ አስባለሁ፡፡ ከሦስት ከአራት ወራት በኋላ ለማደርገው ውድድር አሰልጣኜ የሚሰጠኝን የቤት ስራ ከራሴ ችሎታና ልምድ ጋር አጣምሬ ለመዘጋጀት ራሴን ነው የማዘው፣ ችግሮች ካሉብኝ ራሴን ፈትሼና የአሰልጣኝ ትዕዛዝ ወስጄ ራሴን በማስተካከል ነው ለውድድር የምቀርበው፣ ስለዚህ ራሴን ነው የምመራው ማለት ነው ።በአመራር ረገድ አላማው አንድ ቢሆንም የተለያዩ ሰዎችንና የተለያዩ ፍላጎት ያላቸውን አትሌቶች መምራት ልዩነቱ ሰፊ ነው፣ ነገር ግን መምራት ማለት የሚያውቁትን ነገር መምራት ነው ወይስ የማያውቁትን ነገር መምራት ነው? የሚለውን ጉዳይ መመልከት አስፈላጊ ነው፣ ለምሳሌ አንድ ሰው የሚመራውን ነገር ተምሮና አውቆ ቢመራው ጥሩ ነው፣ እኛ ስንመራ የምንመራው ሙያውን ነው፣ ሙያውን ስንመራ ደግሞ እናውቀዋለን ብለን ነው፣ አትሌቲክስን ስትመራ የአትሌቱን ስነልቦና ማንበብ አለብህ፣ ብዙ ነገሮቹን ማወቅ ይጠበቅብሃል፣ እኛ በውስጡ ስላለፍን ይህን እናውቀዋለን፣ አንድ በፖለቲካ የተሾመ ሰው ተነስቶ ይህን ሊያውቅ አይችልም፣ በቀላሉ ብዙ ነገሮችን ሊሞኝ ይችላል፣ ውጤት የሚጠፋውም በእንደዚህ አይነት ሂደት ነው፣ መምራት ቀላል ነገር አይደለም፤ይህንን አልክድም፣ አንድ ነገር ሲመራ ግን ስለነገሩ ጠንቅቆ በሚያውቀው ሰው ቢመራ ጥሩ ነው ። አይቸገሩም ማለት አይቻልም፣ ይቸገራሉ ።ፈተናው ትልቅ ነው፣ በስራ አስፈፃሚ ውስጥ ብዙም ባይሆንም የፖለቲካ ሹመኞች አሉ፣ እነሱን አስቀምጠን ሙያዊ ነገር ስናወራ እነሱ አያውቁትም፣ ስለዚህ ወደኛ ሃሳብ ለመምጣት ይገደዳሉ፣ አንድ ሙያዊ ጥያቄ አንስተን የማይመልስልን ከሆነ ሙያውን አያውቀውም ማለት ነው፣ ያለሙያው የገባ ሰው ስለሙያው እንዲህ ነው ብሎ ይከራከራል ብዬ አልጠብቅም ። ቅድም መነሻዬ ላይ እንደ ጠቀስኩት ፌዴሬሽኑ ውስጥ ቡድንተኝነት አለ ፤ግን ፍንትው ብሎ አልወጣም፣ ነገር ግን እኛ ወደ አመራርነት ስንመጣ የእኔነት ስሜት ስላለን ነው፣ ባለፈው ሸራተን ሆቴል የነበረው የሽልማት ስነስርዓት ያልተካተተ አካል አልነበረም ።ተለይቶ የሚደረግ ነገር የለም፣ ደራርቱ ኦሮሞ ስለሆነች የኦሮሚያ አትሌቶችን ለይታ ልትጠቅም አትችልም፤ የነበረው ሽልማት ይሄን መጥፎ የመከፋፈል ስሜት ለማጥፋት የተደረገ አንድ ርምጃ ነው፡፡ ወደ ፊትም ከመዋቅር አንስቶ የተለያዩ ለውጦች ይደረጋሉ የሚል እምነት አለኝ ።አንድ ሰው ፌዴሬሽኑ ውስጥ ገብቶ ስለ አበበ ቢቂላ አንድ ነገር ለመስራት ቢፈልግ በዝርዝር ተሰንዶ የተቀመጠ ሙሉ ነገር የለም፡፡እንዲህ አይነት ችግሮችን ጭምር ለመቅረፍ እየሰራን ነው ።ይሄም ሊሆን ይችላል ትልቁ ፈተናችን ። ምንም ጥቅም አለው ብዬ አላስብም፡፡እኔ የሚመስለኝ ለምሳሌ አንድ የፖለቲካ ሹመኛ ስራ አስፈፃሚ ሆኖ ወደ ፌዴሬሽን ሲመጣ የስፖርት ትጥቅ፣ አትሌቶችን ይዞ ወደ ውጪ አገር መጓዝና ሌሎችም ለእሱ ትልቅ ነገር ሊሆን ይችላል(በእርግጥ እኔም ውጪ ሳልወጣ በፊት ይሄ ትልቅ ነገር ነበር)፣ እኛ አሁን እዚያ ያለነው ሰዎች ይሄ ነገር የሰለቸን ነን፣ ከራሳችን አልፎ እነዚህን ነገሮች ለሌሎች ሰዎች ልናደርግ የምንችል ነን፣ አንዳንድ ጊዜ የግንዛቤ እጥረትም ይመስለኛል። እዚያ ቦታ ላይ ጥቅም ይኖራል ብሎ የሚመጣ ሊኖር ይችላል፣ እኛ አሁን የምናስበው እየተተካካን ፌዴሬሽኑን ማገልገል ነው። ያለፍንበት ፌዴሬሽንና የኢትዮጵያ ሕዝብ ያሳዝነናል፣ ነገሮች ሲበላሹ ከሩቅ የሚመለከት ሁሉ ምናለበት እናንተ በስፖርቱ ያለፋችሁ ሰዎች ብትመሩት ይላል፣ ደግሞም እውነቱን ነው፡፡አዲስ ዘመን፡- ወደ ስራ አስፈፃሚነት ከመጣችሁ አጭር ጊዜ ቢሆንም ፌዴሬሽኑ ውስጥ ይሄ ጥንካሬ አለ፣ ይሄ ደግሞ ድክመት ነው ብላችሁ የለያችሁት ጉዳይ አለ? ገና እየሄድንባቸው ያሉ ጉዳዮች አሉ፣ ለምሳሌ ቴክኒክ የሚመራበት የራሱ የሆነ መመሪያ ማዘጋጀት አንዱ ነው፣ የቴክኒክ ኮሚቴ ሰብሳቢው እኔ እንደመሆኔ ቴክኒክን በተመለከተ ሲሰራባቸው የነበሩ ሰነዶችን እንደመነሻ ፈልጌ ማግኘት አልቻልኩም፣ ይሄን ለመቀየር አሰልጣኙም፣ ውድድሩም፣ አትሌቱና የውጪ ጉዞና ሌሎችም ብዙ ነገሮች የእያንዳንዱ ኃላፊነትና ተጠያቂነት ምን መሆን አለበት የሚለውን ጉዳይ ገና እየፈተሽን ነው ።እያንዳንዱን ባለሙያ በማነጋገርና በጋራ በመስራት ለሁሉም ነገር ሕግና ደንብ ተበጅቶ እስከ ክልል ፌዴሬሽኖች ጭምር የሚመሩበት ሰነድ እናዘጋጃለን፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ማወቅ ያለበት አንድ ነገር አለ፣ ውጤት ለማስመዝገብ ፍላጎትና አቅም መገናኘት አለባቸው ።እነዚህን ለማገናኘት ጊዜ ያስፈልጋል፣ አትሌቶች ወደ አመራር መጥተዋልና ውጤት በአጭር ጊዜ ማምጣት አለባቸው የሚል ካለ ስህተት ነው ።አዳዲስ አትሌቶችን ለማምጣት ወደ ታች ወርደን መስራት አለብን ።እውነት ነው የኢትዮጵያ ሕዝብ አዲስ ፊት ማየት ይፈልጋል፤ እኛም እንፈልጋለን፤ያሉትን አትሌቶች ምክንያታዊ በሆነ መንገድ መርጠን ይዘን እንሄዳለን፣ ይፎካከራሉ ፤ውጤት አይመጣም ይመጣል የምናየው ቢሆንም ባላቸው አቅም ላይ ስነልቦናቸውን ገንብተን እኛ ያለፍንበትን ተሞክሮ በማጋራትና ጠንካራ ዝግጅት በማድረግ በከፍተኛ ክትትል ውጤት እንዲያመጡ እንጥራለን ።ጊዜ ይሰጠን፡፡አዲስ ዘመን፡- ጀግናው አትሌት ገዛኸኝ አበራ ለሰጠኸን ውድ ጊዜ ከልብ እናመሰግናለን ።አዲስ\nዘመን ጥር 01/2013", "passage_id": "d913fe5ff412ed5faeb86a6f662592b3" }, { "passage": "የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አሁንም አለመግባባት ውስጥ ይገኛሉ። በተለይም የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ኮማንደር ደራርቱ ቱሉና የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ መካከል አለመግባባት መፈጠር ከጀመረ የሰነበተ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አለመግባባቱ ከግለሰቦቹ አልፎ ተቋማዊ እየሆነ መጥቷል፡፡ ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ፣ ኦሊምፒክ ኮሚቴው የሚጓዝበት መስመር እና ውሳኔዎች የሚተላለፉባቸው መንገዶች ግልጽ የሆነ አሠራርን የማይከተሉ ከመሆናቸው ባሻገር መመሪያ እና አሠራርን ሳይሆን የግለሰቦች ፍላጎትን ብቻ መሠረት አድርገው የሚካሄዱ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ «ስፖርቱ እውነተኛ ተቆርቋሪ አጥቷል» ሲሉ ቅሬታቸውን ለኦሊምፒክ ኮሚቴው ከትናንት በስቲያ በፃፉት ደብዳቤ አብራርተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ በበኩላቸው «ምንም የተፈፀመ ስህተት የለም» በማለት ትናንት ረፋድ ላይ ለሸገር ስፖርት ተናግረዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ አክለውም ትናንት በአምባሳደር ሆቴል አዲሱ የኦሊምፒክ ኮሚቴ መተዳደሪያ ደንብ ውይይት ሲደረግበት ከአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጋር በተያያዘ የሚነሳውን ቅሬታ እንደሚመክሩበት አብራርተዋል፡፡ በአምባሳደር ሆቴል እንደሚካሄድ ቀጠሮ የተያዘለት አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ወይም ስብሰባ ላይ ተሰብሳቢዎቹ የተጠሩበት ሂደት እና የጉባኤው አጀንዳዎች በግልጽ ምን ምን እንደሆኑ ቀደም ብለው አለመታወቃቸው፡ ከኮሚቴው መተዳደሪያ ደንብ እና አሠራር ጋር አብሮ የሚሄድ እንዳልሆነ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቢልልኝ መቆያ ለልዩ ስፖርት ገልጸዋል፡፡ ደራርቱ ቱሉ ከኦሊምፒክ ኮሚቴ ሥራ አስፈፃሚነት ራሷን ለማግለል ውሳኔ ላይ ደርሳ የነበረች ቢሆንም ሃሳቧን መቀየሯ ይታወሳል፡፡ ደራርቱ በኦሊምፒክ ኮሚቴ የውሳኔ አሰጣጥ ረገድ የምትመለከታቸውን ሕጸጾች ከዚህ በኋላ የማይታረሙ ከሆነ ከኦሊምፒክ ኮሚቴ ሥራ አስፈፃሚነት ራሷን እንደምታገል ማስጠንቀቋ ይታወሳል፡፡ ደራርቱ ባለፈው ነሐሴ በደብረ ብርሃን ከተማ በተደረገው የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ከሥራ አስፈፃሚነት ለመልቀቅ መወሰኗን የተናገረች ቢሆንም በጠቅላላ ጉባኤው በርካታ ሰዎች ውሳኔዋን እንድታጥፍ ግፊት በማሳደራቸው ሃሳቧን ልትቀይር ችላለች፡፡አዲስ ዘመን ጥቅምት27/2012 ቦጋለ አበበ", "passage_id": "3c652ca655f93861775394e54257c746" }, { "passage": "የአፍሪካን አህጉር እግር ኳስ የሚመራው ካፍ ስፖርቱን ለማሳደግ መሰረቱ በታዳጊዎች ላይ መሆኑን ሲናገር ይሰማል። ካፍ ይሄንን መሰረት በማድረግ ታዳጊዎች ላይ መሰረት ያደረገ ተግባር እያከናወነ ይገኛል። ታዳጊዎችንም ማዕከል ያደረጉ የውድድር መርሃ ግብሮችን እየቀረፀ እየሠራ ይገኛል። የካፍ የታዳጊዎች ውድድር ዋና አላማ ዋንጫ ማሸነፍ ሳይሆን ተተኪዎችን ማፍራት ነው፡፡በአፍሪካ ውስጥ ግን የታዳጊዎች ውድድር ውጤት ፍላጋ ላይ ብቻ በማተኮር ፌዴሬሽኖች እና ክለቦች በአህጉሪቱን እምቅ ችሎታ ያላቸውን ታዳጊዎች እንዳይፈሩ እንቅፋት ሆነዋል፡፡ ያም ሆኖ ግን፤ የዕድሜ ማጭበርበር በጉልህ በሚታይበት የአህጉሪቱ እግር ኳስ ውስጥም በታዳጊዎች ላይ ከመሥራት መቦዘን አልፈለገም። ማህበሩ የኮካ ኮላ አፍሪካ አገራት ከ16 ዓመት በታች የእግር ኳስ ውድድርን ይፋ በማድረግ ይሄንኑ አስመስክሯል።ፌዴሬሽኖች እና ካፍ በዕድሜ ማጭበርበር ላይ ያለቸው አመለካከት ስለመቀየሩ የሚተማመኑ ቢሆንም፤ የአዘጋጅነት ዕድሉን ኬኒያ በመውሰድ በሰሜን ምዕራብ ናይሮቢ በምትገኘው ናኩሩ አስተዳደር ከትናንት በስቲያ ውድድሩ ተጀምሯል። የውድድሩ ግብ «አፍሪካን የሚያስጠሩ ኮከብ ተጫዋቾች ማፍራት» ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የአህጉሪቷ የነገ የእግር ኳስ መስታወት የሆነ ውድድር ተደርጎ ተቆጥሯል።የአፍርካን የነገ ተስፋ በመሰነቅ 12 አገራት ማለትም፤ ኬንያ፣ ታንዛኒያ፣ ኡጋንዳ፣ ኢትዮጵያ፣ ሞዛምቢክ፣ ዛምቢያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ጋና፣ ናይጄሪያ፣ ዚምባቡዌ፣ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎና ሴኔጋል በውድድሩ እየተሳተፉ ይገኛሉ። በሰባት የውድድር ቀናት ቡድኖቹ በአራት ምድብ የተከፈሉ ሲሆን በምድብ ሀ አዘጋጇ ኬኒያ ኢትዮጵያ ተደልድለዋል።ውድድሩ ከትናንት በስቲያ በምድብ ሀ በሚገኙት ኬኒያ እና ኢትዮጵያ የተጀመረ ሲሆን፤ አዘጋጇ አገር ኬኒያ በድል በመውጣት ጅማሮውን በሰመረ መልኩ አድርጋለች። የኬኒያ ታዳጊዎች የኢትዮጵያን ብሔራዊ ቡድን አንገት ባስደፋ መልኩ 11 ለ 1 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፋለች። የኢትዮጵያ ከ16 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የደረሰበት አስደንጋጭ ሽንፈት የአገሪቱ ስፖርት ከጊዜ ወደጊዜ እያሳየ ያለውን የቁልቁለት ጉዞ የሚያመለክት ነው። የዚህ ብሔራዊ ቡድን 16 ተጫዋቾች የኮካ ኮላ ኩባንያ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር ባካሄዳቸው የኮፓ ኮካ ኮላ ከ15 ዓመት በታች አገር አቀፍ የታዳጊ ውድድር ላይ የተሳተፉ ናቸው። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የታዳጊ ተጫዋቾቹን ምልመላና መረጣ ያካሄደ ሲሆን የተመረጡት ተጫዋቾችም በአገር አቀፉ ውድድር ላይ ጥሩ ብቃት ያሳዩ ናቸው።በአገሪቱ የእግር ኳስ አቅም አላቸው የሚባሉትን ታዳጊዎች በመመልመል ይህ አይነቱ የሽንፈት ቅሌት መድረሱ የእግር ኳሱ መሰረት እንደተናጋ እንደማሳያ የሚወሰድ መሆኑን የተለያዩ የስፖርት ቤተሰቦች በሰጡት አስተያየት ገልፀዋል። ባለድሎቹ ኬኒያውያኖች በእግር ኳሱ ምስራቅ አፍሪካን ብቻም ሳይሆን በአህጉር ደረጃ ያላቸውን ውጤታማነት ለማሳደግ የሚያስችል ተግባራት እያከናወኑ መሆኑን የትናንት በስቲያው ጨዋታ የሚያመላክት ነው። የምድቡን ሁለተኛ ጨዋታ በዛሬው ዕለት ከቦትስዋና የሚያደርገው የኬኒያ ብሔራዊ ቡድን ካሸነፈ ወደ ግማሽ ፍፃሜ በቀጥታ መቀላቀሉን እንደሚያረጋግጥ ታውቋል።በሌላ በኩል፤ በምድብ ለ የሚገኙት ናይጄሪያ እና ዛምቢያ ጨዋታቸውን አከናውነዋል። በሁለቱ ቡድኖች መካከል በተደረገው ጨዋታ የአፍሪካ እግር ኳስ ክዋክብት መፍለቂያዋ ናይጄሪያ ድል ሳይቀናት አልቀናትም። ይልቁንም የነገው ተስፋዋን ይዛ የቀረበችው ዛምቢያ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት በመርታት ጅማሬዋን አሳምራለች። ጥሩ የእግር ኳስ እንቅስቃሴ በታየበት በዚህ ጨዋታ ለአህጉሪቷ እግር ኳስ ተስፋ ሰጪ ታዳጊዎች መኖራቸውን ያሳዩ መሆናቸውን የተለያዩ የመገናኛ አውታሮች ዘግበውታል።ጨዋታውን በአሸናፊነት ያጠናቀቁት ዛምቢያዎችም ሆኑ ተሸናፊዎቹ ናይጄሪያዎች የምድብ ቀሪ ጨዋታዎችን በተጠናከረ መልኩ ማከናወን እንዳለባቸው የቤት ሥራ ለመውሰድ የተገደደበት ነበር ተብሏል። ከትናንት በስቲያ የተጀመረው ይህ ውድድር አፍሪካን የሚያስጠሩ ኮከብ ተጫዋቾች ማፍራትን ግቡ ማድረጉን ተከትሎ ፤ በአጀማመሬ እንደታየው መድረኩ የአህጉሪቷ የነገ የእግር ኳስ መስታወት ሆኖ መንፀባረቁ ተነግሯል።የኮካ ኮላ አፍሪካ አገራት ከ16 ዓመት በታች እግር ኳስ ውድድር በሰሜን ምዕራብ ናይሮቢ በምትገኘው ናኩሩ አስተዳደር እየተካሄደ እስከ ቀጣዩ ቅዳሜ የሚዘልቅ ሲሆን ዛሬና ነገ የምድብ ጨዋታዎች ይደረጋል።አዲስ ዘመን ታህሣሥ 3/2011ዳንኤል ዘነበ", "passage_id": "efc7799e9c4d27f0e3118fd8744b9181" }, { "passage": "ኢትዮጵያ\nካልተጠቀመችባቸው ነገር ግን እምቅ አቅም እንዳላት በባለሙያዎች ከሚጠቆሙ ስፖርቶች መካከል አንዱ የውሃ ዋና ነው። የ«ውሃ ማማ» በሚል የምትጠራው ኢትዮጵያ የዋናተኞች እንዲሁም የውሃ ችግር ሳይኖርባት ለዘመናት በስፖርቱ እንዳትጠራ ሸብቦ ወደኋላ ያስቀራት ችግርም የውሃ ዋና ገንዳ አለመኖር ነው። ለአንድ ስፖርት የማዘውተሪያ ሥፍራዎች መኖር ዓይነተኛ ሚና እንዳለው የሚታወቅ ሲሆን፤ የውሃ ስፖርቶች ፌዴሬሽንም ይህ ሲፈትነው ቆይቷል። አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ ከተሞች ባሉ ሆቴሎች በርካታ የውሃ ዋና ገንዳዎች ይኑሩ እንጂ፤ በአገሪቷ ውስጥ የውድድር ደረጃን የሚያሟሉት የውሃ ዋና ገንዳዎች በግዮን ሆቴል፣ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ ሌሎች ተቋማት እንዲሁም በጊዜያዊነት ለአንድ ውድድር በሚል በየክልሉ የሚገነቡት ብቻ ናቸው። ከዚህ ባሻገር በወጣቶች ስፖርት አካዳሚ የሚገኘው የውሃ ዋና ገንዳ አገልግሎት የማይሰጥ ሲሆን፤ በሌሎች ስፍራዎች የሚገነቡትም በተለያዩ እንከኖች ከተያዘላቸው ጊዜ በእጥፍ የዘገዩ ናቸው። ነገር ግን በዚህ ፌዴሬሽን ተሳታፊ የነበሩ ባለሙያዎች እና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ፌዴሬሽኑ ለገንዳ መገንቢያ የሚሆን ቦታ እንደተሰጠው ያወሳሉ። ፌዴሬሽኑ የራሱ ገንዳ ሊኖረው ይገባል በሚል እንቅስቃሴ የተጀመረው ከ15ዓመታት በፊት እንደ ነበር በ1990ዎቹ ፌዴሬሽኑን በፕሬዚዳንትነት የመሩት አቶ ግርማ ዳምጤ በአንድ ወቅት ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ መግለጻቸውን ማስታወስ ይቻላል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የኦሊምፒክ ደረጃውን የሚጠብቅ ገንዳ የምትገነባ ከሆነም ዓለም አቀፉ ፌዴሬሽን የተለያዩ ቁሳቁሶች ድጋፍ እንደሚያደርግ ቃል ገብቶ እንደነበርም ያስታውሳሉ። ከዚያ በኋላም ፌዴሬሽኑ መሬት አግኝቷል። አዲስ\nዘመን ጋዜጣም ጉዳዩን በመያዝ በሰራቸው ተከታታይ ዘገባዎች ላይ ቦታው ያለ ግንባታ ተዘንግቶ ባዶውን ለዓመታት መቆየቱን ታዝቧል። ግንባታ ያልተጀመረበት መሆኑን ተከትሎም ቦታው በከተማ አስተዳደሩ በኩል ለሌሎች አካላት ሊሰጥ ይችላል የሚል ስጋትም ከባለሙያዎች ዘንድ ሲሰነዘር ቆይቷል። አሁን ግን ይህ ቦታ መኖሩ ተረጋግጦ በድጋሚ በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን የባለቤትነት ማረጋገጫ ማግኘቱ ተሰምቷል። ቦታው ለኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን በ1998 ዓ.ም፤ ለውሃ ስፖርቶች ፌዴሬሽን እንዲሁም ሜዳ ቴኒስ ፌዴሬሽን በጋራ የማዘውተሪያ ስፍራ እንዲገነቡበት በሚል የተሰጠም ነው። ይህ ቦታ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ሃያት ሪሊስቴት አካባቢ የሚገኝ ሲሆን፤ ለውሃ ስፖርቶች 16ሺ ካሬ ሜትር እንዲሁም ለሜዳ ቴኒስ 15ሺ ካሬ ሜትር የተከፈለ ነው። ኮሚሽኑ የቦታውን ካርታ በ2000ዓ.ም ቢያገኝም፤ ምንም ሳይሰራበት ከ10ዓመት በላይ መቆየቱን በኢትዮጵያ ውሃ ስፖርቶች ፌዴሬሽን የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቀልቤሳ ኤባ ይገልጻሉ። አሁን\nፌዴሬሽኑ ባቀረበው ጥያቄ መሰረትም ከኮሚሽኑ የስፖርት ፋሲሊቲ ጋር በመሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቦታውን ለሌላ መስጠት አለመስጠቱን የማጣራት ሥራ ተሰርቷል። ባለሙያዎችም በቦታው ተገኝተው ከተመለከቱ በኋላ መታጠር ስላለበት የግንባታ ፍቃድ ለማውጣት ተችሏል። በዚህም የሁለቱ ፌዴሬሽኖች የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ከኮሚሽኑ ኃላፊዎች ጋር መክረዋል። በምክክሩም ፌዴሬሽኖች የመገንባት አቅም የሌላቸው በመሆኑ በኮሚሽኑ በኩል በ2012ዓ.ም በጀት ተይዞለት የአጥር ግንባታው እንዲጀመር ወደ ፊትም ምን መሆን ይገባል የሚለው በንግግር አቅጣጫ እንዲይዝ ከውሳኔ ላይ ተደርሷል። ኮሚሽኑ በዚህ ወቅት በብሄራዊ ደረጃ ዓለም አቀፍና ዘመናዊ ስታዲየም በመገንባት ላይ የሚገኝ በመሆኑም ገንዳውን ለመገንባት እንደማይቻል እንደ ምክንያት ተነስቷል። ሁኔታዎች\nቢመቻቹና ገንዳው ቢገነባ ፌዴሬሽኑ የማዘውተሪያ ስፍራ የሚያገኝ በመሆኑ፤ ለብሄራዊ ቡድን ስልጠና፣ ለአገር አቀፍ ሻምፒዮናዎች እንዲሁም ሌሎች ዞን አቀፍ ውድድሮችን ወደ አገር ለማምጣት እንደሚረዳ ኃላፊው ይጠቁማሉ። ከዚህ ባሻገር ለፌዴሬሽኑ የገቢ ምንጭ የሚያገኝበት አንድ መንገድ ይሆናል። ዓለም አቀፉ የውሃ ስፖርቶች ፌዴሬሽንም እገዛ እንዲያደርግ ፌዴሬሽኑ ጥያቄ እንደሚያነሳም አስታውቀዋል። ከዚህ ቀደም ለስፖርቱ ልማት እንዲውል የገንዘብ ድጋፍ መደረጉንም ያስታውሳሉ። ቦታው ከግንባታ ውጪ ለዓመታት ሊቀመጥ የቻለው በተለያዩ ፕሮጀክቶች ግንባታ መደራረብ መሆኑን በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን የስፖርት ፋሲሊቲ ዳይሬክተር ኢንጂነር አዝመራው ግዛው ይገልጻሉ። ካርታው የተሰጠው በ2000ዓ.ም ሲሆን፤ በወቅቱ ደግሞ መንግሥት የኢትዮጵያ ወጣቶችና ስፖርት አካዳሚ፣ የጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል፣ የብሄራዊ ስታዲየም ዲዛይን እንዲሁም ግንባታ በእነዚህ ዓመታት ሲከናወኑ ቆይተዋል። እነዚህ ትልልቅ ፕሮጀክቶች ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁ በመሆናቸው ቅድሚያ በመስጠት የውሃ ዋናው እንዲሁም የሜዳ ቴኒስ ሜዳው ግንባታ መዘግየቱን ያነሳሉ። ሁሉንም በአንድ ጊዜ ለመገንባት በበጀት እጥረት ምክንያት አልተቻለም። እንዲያም ሆኖ ሲገነቡ የቆዩት ፕሮጀክቶች ለእነዚህ ስፖርቶች የሚሆኑ ማዘውተሪያዎችን ያካተቱ ነበሩ። ለአብነት ያህል የወጣቶች ስፖርት አካዳሚ የውሃ ዋና ገንዳ እንዲያካትት መደረጉን እንዲሁም የሜዳ ቴኒስም በአንዳንድ አካባቢዎች መኖራቸውንም ዳይሬክተሩ ይጠቅሳሉ። በከፍተኛ ደረጃ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እጥረት አለ፤ በመሆኑም በአግባቡ ማልማትና ሥራ ላይ ማዋል ተገቢ ነው። መንግሥት ስፖርቱን ለማሳደግ በሚያደርገው ጥረት ለስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ መገንቢያ ቦታውን ቢሰጡም፤ ለዓመታት የቆየው ያለ ሥራ ነበር። በወቅቱ ቦታውን ከልሎ ማስቀመጥ ይገባ እንደነበረም አልሸሸጉም፤ እስካሁንም ወደ መሬት ባንክ ሳይገባ እንዲሁ ቆይቷል። አሁን\nግን ካርታውን የማደስ ሥራ የተከናወነ ሲሆን፤ ከዚህ በኋላም አጥር የመከለል እና በአግባቡ እንዲጠበቅ የማድረግ ሥራ እንደሚከናወን ዳይሬክተሩ ይጠቁማሉ። ከማጠሩ ሥራ በተጓዳኝ ስፍራውን በችግኝ የማልማት እንዲሁም መጠነኛ ግንባታ ይከናወናል። ከዚህ ቀደም የተሰሩ ዲዛይኖች በመኖሩ ይህንን የመገምገም አሊያም አዲስ መስራት የሚገባ ከሆነም እርሱን የማወዳደር ሥራዎችም በቀጣይ በጀት ዓመት የሚከናወን ይሆናል። አሁን በግንባታ ላይ የሚገኘው የብሄራዊ ስታዲየም ከፍተኛ ገቢ የሚጠይቅ በመሆኑ ርብርብ የሚደረገው ይህንን ለማጠናቀቅ ነው። የቦታው ፕሮጀክትም በቀጣይ የሚከናወን ይሆናል። ከዚህ በተጨማሪም ዘርፉ የማዘውተሪያ ስፍራዎች ላይ የተለያዩ ሥራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ዳይሬክተሩ ይጠቁማሉ። የስፖርት\nማዘውተሪያ ስፍራዎችን በተመለከተ በ2004ዓ.ም በወጣው አዋጅ ላይ በአንድ ወረዳ ቢያንስ አንድ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ መኖር እንዳለበት ይጠቁማል። በመሆኑም በየትኞቹ አካባቢዎች የማዘውተሪያ ስፍራዎቹ ይገኛሉ በሚል መረጃ ለማጠናቀር በግብረ ኃይል እየተሰራ ይገኛል። ይህ ሲጠናቀቅም የትኞቹ የማዘውተሪያ ስፍራዎች የይዞታ ባለቤትነት ማረጋገጫ አላቸው? በየትኞቹ አካባቢዎችስ ማዘውተሪያ ስፍራዎቹ ይገኛሉ? የሚለውን መረጃ ማግኘት ይቻላል። ከዚህ በኋላም ያሉት የማዘውተሪያ ስፍራዎች ጥበቃ እንዲያገኙና እንዲለሙ የማድረግ ሥራ ይከናወናል። የይዞታ ማረጋገጫ የሌላቸው ስፍራ ዎችም እንዲያገኙ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የሚሰራ መሆኑን ዳይሬክተሩ አብራርተዋል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 28/2011ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "5ad6ee7bc9e1572c707e2675c695047b" } ]