Dataset Viewer
Auto-converted to Parquet
query_id
stringlengths
32
32
passage_id
stringlengths
32
32
query
stringlengths
2
300
passage
stringlengths
78
8.98k
category
stringclasses
7 values
link
stringlengths
28
740
⌀
negative_passages
listlengths
5
5
608823f9f4635381c68222501123b2ed
465525198bd3bf4e5b137fe927e34ee1
የኦሊምፒክ ማጣሪያ ተሳታፊዎች የሚለዩበት ቻምፒዮና እየተካሄደ ይገኛል
ብርሃን ፈይሳየኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን በየዓመቱ የሚያዘጋጀው የክለቦች ቻምፒዮና በአዲስ አበባ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተሻለ ብቃት ያሳዩ ቦክሰኞች ለቶኪዮ ኦሊምፒክ ማጣሪያ ተሳታፊ እንደሚሆኑም ታውቋል።በቦክስ ስፖርት ከሚካሄዱት ዓመታዊ ቻምፒዮናዎች መካከል አንዱ በክለቦች መካከል የሚካሄደው ነው፤ የዚህ ውድድር የመጀመሪያው ዙር በአዲስ አበባ ከተማ ተጀምሯል። የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን ከአዲስ አበባ ቦክስ ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር በተዘጋጀው በዚህ ቻምፒዮና፤ ከኮቪድ 19 ወረርሽኝ መከሰት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደ ውድድርም ነው። በውድድሩም ላይ አምስት ክለቦች ከአዲስ አበባ (ፌዴራልፖሊስ፣ ፌዴራል ማረሚያ ቤቶች፣ አዲስ አበባ ፖሊስ፣ የኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ እና ኦሞቲክ ቦክስ)፣ ሁለት ክለቦች ከአማራ ክልል (ጎንደር ከነማ እና ደሴ ከነማ) እንዲሁም ድሬዳዋ ከነማ በድምሩ ስምንት ክለቦች ተሳታፊ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያሳያል። በአጠቃላይ ክለቦቻቸውን ወክለውም 12 ሴትና 76 ወንድ ቦክሰኞች በጥቅሉ 88 ተወዳዳሪዎች ተሳታፊ ይሆናሉ። ውድድሩ የሚካሄደው በራስ ኃይሉ ስፖርት ትምህርትና ስልጠና ማዕከል ሲሆን፤ በ10 ክብደቶች በ49፣ 52፣ 57፣ 60፣ 63፣ 69፣ 70፣ 81፣ 89 እና 91 ኪሎ ግራሞች እየተካሄደም ይገኛል። የቦክስ ስፖርት ከንክኪ ስፖርቶች መካከል አንዱ እንደመሆኑ ጨዋታው በሚካሄድበት ወቅት ቦክሰኞቹ አካላዊ ቅርርብ ሊያደርጉ እና ሊነካኩ ይችላሉ። በመሆኑም በዚህ ረገድ ውድድሩ ሙሉ ለሙሉ የኮቪድ 19 ጥንቃቄን በተላበሰ መልኩ እየተካሄደ መሆኑን ነው ፌዴሬሽኑ ያረጋገጠው። ይኸውም ተወዳዳሪዎችና አሰልጣኞች የኮቪድ ምርመራ እንዲያደርጉና ከሌሎች ሰዎች ጋር እንዳይገናኙ በካምፕ እንዲቆዩ በማድረግ ነው። ከዚህ ባሻገር ውድድር የሚደረግበት ሪንግ ቶሎ ቶሎ በኬሚካል እንዲጸዱ እንዲሁም ተመልካቾች ውድድሩ ላይ እንዳይገኙም ተደርጓል። ኮቪድ 19 ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ እንደመሆኑ በመላው ዓለም ስፖርታዊ ውድድሮች ተቋርጠው መቆየታቸው የሚታወስ ነው። ከእነዚህ ውድድሮች መካከል ለቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ የቦክስ ስፖርት ማጣሪያ የሚካሄደው ውድድር ይጠቀሳል። ውድድሮች ወደ እንቅስቃሴ መግባታቸውን ተከትሎም ማጣሪያው የሚቀጥል ይሆናል። ኢትዮጵያም በዚህ ቻምፒዮና (በመጀመሪያው ዙር) የተሻለ ብቃት ያሳዩ ቦክሰኞችን በማጣሪያው የምታሳትፍ መሆኑ ታውቋል። ቻምፒዮናው አራት ዙሮች ያሉት ሲሆን፤ ሁለተኛው ዙር ከአማራ ክልል ቦክስ ፌዴሬሽን ጋር በመሆን ጎንደር ላይ፣ ሶስተኛውን ከደቡብ ክልል ቦክስ ፌዴሬሽን ጋር በመሆን ወላይታ እንዲሁም የመጨረሻውና የማጠቃለያው ውድድር አዲስ አበባ ላይ የሚካሄድም ይሆናል። ቻምፒዮናው ጥር 4/2013 ዓም የተጀመረ ሲሆን እስከ ጥር 7/2013 ዓም ድረስም ይቆያል።
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=39481
[ { "passage": "12 ኛው የመላ አፍሪካ ጨዋታ ከነሐሴ 13 እስከ 25 ቀን 2011 ዓ.ም በሞሮኮ ራባት ከተማ የሚካሄድ ሲሆን ኢትዮጵያም ተሳታፊ ከምትሆንባቸው 13 የስፖርት አይነቶች አንዱ ካራቴ ነው። በውድድሩ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ካራቴ ብሄራዊ ቡድን ልኡክ ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅቱን እያደረጉ እንደሚገኙና በውድድሩም ጥሩ ውጤት ያስመዘግባሉ የሚል እምነት መያዙ ተጠቁሟል። ተሳታፊ ስፖርተኞችም ውጤታማ ለመሆን እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ካራቴ ፌዴሬሽን ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሠፋ አንጀሎ ዝግጅቱን አስመልክተው እንደተናገሩት ፤ ለውድድሩ ትኩረት በመስጠት ከግንቦት ወር ጀምሮ ዝግጅት መጀመሩንና ሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተሳተፉበት ሻምፒዮና በማካሄድ ውጤታማ ሊሆኑ ይችላሉ ተብሎ የታመነባቸው 25 ወጣት ስፖርተኞች ዕጩ የብሔራዊ ቡድን አባል የማድረግ ስራ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡ ከተመለመሉት ዕጩ የብሔራዊ ቡድን አባላት ውስጥም አስፈላጊውን ማጣሪያ በማድረግ 3 ሴትና 6 ወንድ ስፖርተኞች ለውድድሩ ተመርጠዋልⵆ ስፖርተኞቹም በቀን 2 ጊዜ የስልጠና መርሃ ግብር ወጥቶላቸው ዝግጅታቸውን በማድረግ ላይ ሲሆኑ መንግስትም በቂ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ በውድድሩ የተሻለ ውጤት እንደሚመዘገብ ፍላጎት ማሳየቱን ተናግረዋል። እገዛው ጥሩ ቢሆንም ብሄራዊ ቡድኑ በተወሰነ መልኩ ውስንነቶች እንዳሉበት ጠቁመዋል። ከውስንነቶቹ መካከል ዓለም አቀፉ የካራቴ ፌዴሬሽን ያረጋገጠው የመወዳደሪያ ልብስ “ቲሞኖ” በሀገር ውስጥ አለመኖሩ ነው ያሉት አቶ አሰፋ ይህን ችግር ለመፍታትና ለውድድሩ ሙሉ ሆኖ ለመገኘት ከአንዳንድ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመጻጻፍ ላይ ነን ብለዋል፤ ጥረቱ ተሳክቶም ለውድድሩ እንደሚደርስ ያላቸውን እምነት ጠቁመዋል። የብሄራዊ ቡድኑ ዋና አሠልጣኝ ኢንስትራክተር ዮሴፍ ተበጀ በበኩላቸው ዝግጅቱ ጥሩ መሆኑን ተናግረው ተወዳዳሪ ስፖርተኞች የሚሰጣቸውን ስልጠና በአግባቡ እየተቀበሉ መሆኑን እና በስነ ልቦና ፣ በታክቲክ እና በቴክኒክ በመዘጋጀት ሙሉ የማሸነፍ አቅምም መፍጠራቸውን ተናግረዋል ፡፡ ኢንስትራክተር ዮሴፍ እንደሚሉት ቡድኑ እየተደረገለት ያለው ድጋፍ ከወትሮው የተለየ ነው ተወዳዳሪዎችም በድጋፉ ልክ ውጤት ለማስመዝገብ ጥረት እያደረጉ መሆኑን ገልፀዋል ፡፡ በዝግጅቱ ዙሪያ አስተያየቱን የሰጡት የነጠላ ካታና የቡድን ካታ ተወዳዳሪ የሆኑት ሄዋን እና ሰለሞን እንደገለፁት ፤ በፌዴሬሽኑ እየተደረገ ያለው ድጋፍ እና በአሠልጣኙ እየተሰጣቸው ባለው ስልጠና ደስተኞች መሆናቸውን በመግለጽ ለሀገራቸው ውጤት በማስመዝገብ አዲስ ታሪክ ለመስራት መዘጋጀታቸውን አብራርተዋል፡፡ በሞሮኮ\nራባት በሚካሄደው 12ኛው መላ አፍሪካ ጨዋታ በካራቴ ስፖርት ኢትዮጵያ በ 3 ሴት በ 6 ወንድ ስፖርተኞች ተወክላ የምትሳተፍ ሲሆን በነጠላ ካታ እና ኩምቴ (fight) በወንድ እና በሴት እንዲሁም በቡድን ካታ በወንድ ትካፈላለች ፡፡አዲስ ዘመን ነሃሴ 2/2011", "passage_id": "41c10d66bddeabdcf4513522a4366d4a" }, { "passage": "በተያዘው ዓመት መጨረሻ በሚካሄደው የቶኪዮ ኦሊምፒክ ዝግጅት አካል የሆነው ችቦ የመለኮስ ስነ-ስርዓት በመጪው እሁድ የሚጀመር ይሆናል።በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ የሚጀመረው ችቦ ማብራት በዕጣው መሰረት በተለያዩ ክልሎች የሚዘዋወርም ይሆናል፡፡ ለቶኪዮ ኦሊምፒክ ቅድመ ዝግጅት የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ‹‹ከቶኪዮ\nእስከ ቶኪዮ›› በሚል ርዕስ በብሄራዊ ኮሚቴው አማካኝነት ከተለያዩ ባለ ድርሻ አካላት ጋር እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ\nይታወቃል።ከዝግጅቶቹ መካከል አንዱ የኦሊምፒክ ደጋፊ ማህበር አባላትን ማፍራት ሲሆን፣ ለዚህ ንቅናቄም በመላው የሃገሪቷ ክፍል የሚካሄድ\nየችቦ ማብራት ስነስርዓት ከመጪው እሁድ የካቲት 08/2012ዓም ጀምሮ የሚካሄድ ይሆናል። የመጀመሪያው ችቦም በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ የመንግስት\nኃላፊዎች፣ የከተማው ነዋሪዎች፣ ስፖርተኞች፣ ቀጣይ የሃገር ተረካቢ የሆኑት ተማሪዎች እንዲሁም ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት\nየሚበራ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በድረ ገጹ አስነብቧል።ስነ- ስርዓቱ በሌሎች ክልሎችም የሚቀጥል ሲሆን፤ በወጣው\nእጣ መሰረት የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ሁለተኛው ነው።ሶማሌ፣ ትግራይ፣ ጋምቤላ፣ አፋር፣ ሐረሪ፣ ኦሮሚያ፣ አማራ፣ ደቡብ እና ቤኒሻንጉል\nጉሙዝ ክልሎችም የሚዘዋወር ይሆናል። ከዝግጅቱ ጋር በተያያዘም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽነር ዮናስ አረጋይ፤ ከቶኪዮ 2020\nብሔራዊ ዝግጅት ኮሚቴ አባላት ባቀረቡት መርሃ ግብር እና መሪ ዕቅድ ላይ ውይይት በማድረግ ማጽደቃቸውንም በድረ ገጹ ተጠቁሟል።በውይይቱ\nላይም የቀድሞ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤና የብሔራዊ ዝግጅት ኮሚቴ ሰብሳቢው አባዱላ ገመዳ፣ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ\nፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ እንዲሁም የኮሚቴው አባላቶች ተገኝተዋል፡፡ ኦሊምፒክ ለሰው ልጆች የላቀ ቦታ የሚሰጥ፣ አንድ የሚያደርግና ሰላምን የሚሰብክ በመሆኑ ዝግጅቱ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ\nተሳትፎ ይፈል ጋል። በመሆኑም የተለያዩ አካላትን ያካተተ ብሄራዊ የኦሊምፒክ ዝግጅት ኮሚቴ በማዋቀር እንቅስቃሴ ማደረግ የተጀመረው\nቀደም ብሎ ነው።ኮሚቴው ለጃፓኑ ኦሊምፒክ እንዲሁም ሌሎች የልማት ስራዎች የሚውል 1ቢሊየን ብር ለማሰባሰብ፣ ከ12ሚሊየን በላይ\nየሚሆኑ የኦሊምፒክ ደጋፊ ማህበር አባላትን ለማፍራት፣ የአትሌቶች ሽኝትና ሽልማት እንዲሁም በመድረኩ የሃገሪቷን መልካም ገጽታ መገንባትም\nዋነኛ ክንዋኔዎቹ ናቸው። ለዚህ ስራ የሚውል ህዝባዊ ንቅናቄ ችቦ በማብራት የሚጀመር ሲሆን፤ የተለያዩ የገቢ ማሰባሰቢያዎችን ማካሄድም\nበቀጣይ የሚተገበር ይሆናል።ለዚህ ስኬትም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በጋራ በመነሳት አሻራቸውን እንዲያኖሩም ጥሪ ቀርቧል። ሁሉም ኢትዮጵያዊ\nበጋራ በመነሳት አሻራውን በኦሊምፒክ ላይ እንዲያኖር ጥሪ ቀርቧል፤አዲስ ዘመን ረቡዕ የካቲት 4/2012  ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "8a04d224c4328a24ad6a906e9d2e6856" }, { "passage": "የዘንድሮውን ከ20 ዓመት በታች የዓለም ሻምፒዮና በኬንያ ናይሮቢ ከመካሄዱ በፊት ውድድሩ በሚካሄድበት አካባቢ ያለው የአየር ጥራት እንደሚለካ የዓለም አትሌቲክስ ተቋም አስታውቋል፡፡\nባለሙያዎቹ ፈረንሳይ ሞናኮ ከሚገኘው ዋና መስሪያ ቤቱ ትናንት ኬንያ መግባታቸውን ያስታወቀው ተቋሙ “ኩናክ” የተሰኘ የአየር ጥራት መለኪያ መሳሪያ ሻምፒዮናው በሚካሄድበት የካሳራኒ ስታዲየም መተከሉንም ገልጿል፡፡\nመሳሪያው ባለፈው ዓመት በአዲስ አበባ ተተክሎ ነበር፡፡\nይህን ያስታወሰው ሲ.ጂ.ቲ.ኤን አፍሪካ የናይሮቢው የታዳጊዎቹ ሻምፒዮና የአየር ጥራት የሚለካበት የመጀመሪያው ዓለም ቀአፍ ውድድር መሆኑን ዘግቧል፡፡\nሻምፒዮናው በመጪው ሰኔ ወር መጨረሻ የሚካሄድ ነው፡፡\nኬንያ ከሶስት ዓመታት በፊት በዚሁ በካሳራኒ ስታዲየም ከ17 አመት በታች የዓለም ሻምፒዮናን ማስተናገዷ የሚታወስ ነው፡፡\n", "passage_id": "5812a107b5ae2f1f1f7b1c4b2bd0509d" }, { "passage": "የዓለም ታላቁ ስፖርታዊ ውድድር ኦሊም ፒክ፤ በየወቅቱ አዳዲስ የውድድር ዓይነቶችን በማካተት ይታወቃል። ፓሪስ\nበታሪኳ ለሶስተኛ ጊዜ እአአ በ2024 በምታስተናግደው ኦሊምፒክ ላይም አዳዲስ ውድድሮች የሚጨመሩ መሆኑ ታውቋል። የመጀመሪያው በማራቶን\nስፖርት ላይ መሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውንም ሰው ማካተት ሲሆን፤ «ብሬክ» በመባል የሚታወቀው ዳንስ፣ በ«ስኬት ቦርድ» መንሸራተት፣\nበውሃ ላይ መንሳፈፍ እንዲሁም ተራራ መውጣት የኦሊምፒኩ የውድድር ዓይነቶች ናቸው።ከአትሌቲክስ ስፖርቶች ረጅሙን ርቀት የሚሸፍን ውድድር እንደመሆኑ ከፍተኛ ጽናትና ጥንካሬን ይጠይቃል፤ ማራቶን።\n42ኪሎ ሜትር መሸፈኑ ከባድ ቢያደርገውም በተለያዩ የዓለም ከተሞች በየሳምንቱ የሚካሄድ የውድድር ዓይነት በመሆኑ ብዙዎች ይሳተፉበታል።\nበተለይ በዚህ ርቀት እንደ ኦሊምፒክ ባሉ የውድድር መድረኮች ተሳትፎ የሜዳሊያ ባለቤት መሆን ከፍተኛ ክብርን ያስገኛል። በዚህም\nምክንያት በኦሊምፒክ የርቀቱ ተካፋይ የሚሆኑት፤ ታዋቂና ልምድ ያላቸው አትሌቶች ናቸው። በፓሪስ ኦሊምፒክ ላይ ግን የትኛውም መሮጥ የሚፈልግ ሰው ተካፋይ መሆን እንደሚችል የዓለም ኦሊምፒክ ኮሚቴ\nአስታውቋል። ይህንን ዜና ተከትሎም የኦሊምፒኩን አስተባባሪ ኮሚቴ በፕሬዚዳንነት የሚመሩት ቶኒ ኢስታንጉዌት «ውድድሩን ልዩ ለማድረግ\nአንድ እርምጃ ተራምደናል። በርካቶችን የሚያሳትፉ የተለያዩ ውድድሮችም እንዲካተቱ አድርገናል። ተሳ ታፊዎች በየትኛውም ደረጃ ላይ\nቢገኙም በኦሊምፒኩ የተለየ ልምድ እንዲኖራቸው ማድረግ እንፈልጋለን» ሲሉ ገልጸዋል።በአሜሪካዋ የኒው ዮርክ ከተማ እአአ ከ1970 እንደተጀመረ የሚነገረው «ብሬክ» የተባለው የዳንስ ዓይነት፤\nባሳለፍነው ዓመት በቦነስ አይረስ በተካሄደው የወጣቶች ኦሊምፒክ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደ አንድ የውድድር ዓይነት ተካሂዶ ነበር።\nይህንን ተከትሎም በዋናው የኦሊምፒክ ውድድር ላይም ለማካተት መወሰኑን ፕሬዚዳንቱ ይጠቁማሉ።  ሊቀመንበሩ አክለውም\nከዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እንዲሁም የስፖርት ማህበራት ጋር በመስራት ላይ እንደሚገኙና ልምዱ በሌሎች ስፖርቶችም እንዲንጸባረቅ\nእንደሚሹም ገልጸ ዋል።አዲስ ዘመን የካቲት\n18/2011ብርሃን ፈይሳ __\n  ", "passage_id": "f353ba31d75c252e4f49b91071931a2d" }, { "passage": "የዓለም የዩኒቨርሲቲዎች ቻምፒዮና የእግር ኳስ ውድድር ትናንት በቻይናዋ ጂንጃንግ ከተማ ተጀምሯል።አፍሪካን በመወከል በውድድሩ ላይ የሚካፈለው ብቸኛው የኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲም ትናንት ከታይላንድ አቻው ጋር የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል፡፡ባለፈው ዓመት በመቐለ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት 9ኛው የአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ቻምፒዮና መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን በቻምፒዮናው ላይ በእግር ኳስ ስፖርት አሸናፊ የነበረው የኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ በመሆኑ አፍሪካን በመወከል በዓለም ቻምፒዮናው ላይ ለመሳተፍ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ወደ ቻይና አቅንቷል።በዚህ ቻምፒዮና ላይም ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች የተውጣጡ 16 የወንድ ቡድኖች እንዲሁም አራት የሴት ቡድኖች ይካፈላሉ፡፡በወንዶች በኩል ጨዋታው በአራት ምድብ ተከፍሎ የሚካሄድ ሲሆን፤ በምድብ አንድ የቻይና፣ አውስትራሊያ፣ ጀርመን እና ስፔን ዩኒቨርሲቲዎች ተደልድለዋል።በምድብ ሁለት ደግሞ ኢትዮጵያ፣ ከታይላንድ፣ ከቻይና እና ከሜክሲኮ ጋር ተደልድላለች።በሦስተኛው ምድብ ብራዚል፣ ኮሪያ፣ ዩክሬን እና ጣሊያን እንዲሁም በመጨረሻው ምድብ ላይም ክሮሺያ፣ ሩሲያ፣ ሆንግ ኮንግ እና ኡራጓይ ይገኛሉ።በሴቶች ደግሞ ቻይና፣ ብራዚል፣ አውስትራሊያ እና ስዊዘርላንድ በመጀመሪያው ምድብ የተካተቱ ሲሆን፤ ታይላንድ፣ ቻይና፣ ሩሲያ እና ፈረንሳይ በሌላኛው ምድብ ተደልድለዋል።ኢትዮጵያን እና አፍሪካን የሚወክለው ኮተቤም ለዚህ ውድድር ሁለት አሰልጣኞችንና 18ተጫዋቾችን በመያዝ ዝግጅት ሲካሄድ ቆይቷል።ቡድኑ በዋና አሰልጣኙ ዶክተር ወገኔ ዋልተንጉስ እየተመራ በኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ ልምምዳቸውን ሲያደርጉ የቆዩ ሲሆን፤ በተለያዩ የስፖርት አመራሮች ማበረታቻ ሲደረግላቸው ቆይቷል።ቡድኑ ወደ ቻይና ከማቅናቱ አስቀድሞም በብሔራዊ ቤተመንግሥት የባንዲራ ርክክብና ሽኝት ተደርጎላቸዋል።ጂንጃንግ በደቡባዊው የቻይና ክፍል የምትገኝ ሲሆን፤ በተለይ በእግር ኳስ ስፖርት ታዋቂ ከተማም ናት።በከተማዋ 14 እግር ኳስ ስታዲየሞች የሚገኙ ሲሆን መሰል ውድድሮችን ለማሰናዳትም ተመራጭ ናት። አዲስ ዘመን ኅዳር 12/2012 ብርሃን ፈይሳ", "passage_id": "477a78e354a95820c0fc37ac8e747437" } ]
65a4d23f1b9eedcdc2e06f1f3c9c4718
8cbcc5f269b0b8b7a519f07006145508
አዲስ ዘመን ድሮ
 የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ቀደምት ዘገባዎች በእጅጉ ተነባቢ ዛሬም ላገኛቸው በእጅጉ ተነባቢ ናቸው።እኛም ከእነዚህ ዘገባዎች ጋዜጣው በ1950ቹ ያስነበባቸውን ወጣ ያሉ ዘገባዎች ለዛሬ ይዘንላችሁ ቀርበናል። በዛሬው የአዲስ ዘመን ዱሮ አምዳችን አዲስ ዘመን ጋዜጣ በ1950ዎቹ ይዟቸው ከወጣ ዘገባዎች በአዘጋገባቸውና በይዘታቸው ተነባቢ ናቸው ያልናቸውን እና ሌሎች አስደናቂ ዘገባዎችን ይዘን ቀርበናል። ማገጃ ምልክት ይሰጠውማንኛውም የሥራ ድርጅት በብዙ ድካም ከተቋቋመ በኋላ አስፈላጊው ጥንቃቄ ካልተደረገለት የተሠራው እንዳልተሠራ የነበረው እንዳልነበር መሆኑ የማይጠረጠር ነው።በሲዳሞ ጠ/ግዛት ዋና ከተማ ይርጋዓለም የቴሌኮሙኒኬሽን ቦርድ ያቋቋመው ከፍተኛ መሥሪያ ቤት ይገኛል። የተቋቋመውም በትልቁ መኪና መንገድ አጠገብ ስለሆነ ፤ተሽከርካሪዎች የሚመላለሱበት ቦታ ነው።አንዳንድ ጊዜም ከባድ ጭነት የያዙ መኪናዎች ለምሳሌ አውቶቡስን የመሳሰሉት በሁለተኛው መንገድ እንዲያልፉ የሚታዘዙበት ቀን ስለሚያጋጥም በተጠቀሰው መሥሪያ ቤት አደባባይ የሚገኙትን ሽቦዎች ሳይመለከቱ ለማለፍ ሲሞክሩ በብዙ መጯጯህ ስልኩ ሽቦ ከመጣስ የዳነበትና መኪናውንም ለመመለስ የቻለበትን ጊዜ ለማታወስ የማይችል የለም፤ ታናናሽ መኪናዎችን ለማሳለፍ የቦታው ስፋት ይፈቅዳል።ስለ ታላላቅ መኪናዎች ግን የክፍሉ ባለሥልጣን የማገጃ ምልክት ቢያደርግበት የሚሻል መሆኑን አስታውሳለሁ። አቧራ አዋዜ አይደለም። በዚሁ ከተማ ትልቁን መንገድ በመከተል አልፎ አልፎ በሚገኙት ሰፈሮች ብዙዎች የልኳንዳ ሥጋ የተሰቀለባቸውና   ፉርኖ ይህንንም የመሳሰሉት ምግቦች የተደረደረባቸው ቤቶች ይገኛሉ። ሥጋው የሚገኝበት ብዙ ቦታ በረንዳ ስለሆነ ማናቸውም ተንቀሳቃሽና ይልቁንም በማይቋረጠው የመኪና ኃይል ከመንገዱ ላይ የሚነሳው አቧራ በሥጋውና በማናቸውም ምግብ ላይ ሲሰፍርበት ይታያል።ለማስረጃ ያህል በመንገዱ ዳር የሚገኘውን የቡና የሌላውንም ቅጠል የተመለከትን እንደሆነ በአንዱ ቅጠል ላይ ብቻ አንድ ጥርኝ የሚሞላ አቧራ ስለምናገኝ በየቀኑ በያንዳንዱ ብልት ሥጋ ላይ ተደባልቆ ወደ ሆድ የገባውን አቧራ ለመገመት እንችላለን። ስለዚህ ሥጋና ፉርኖ ይህንንም የመሳሰለ ምግብ የሚያሰናዱ ነጋዴዎች ለዚሁ አገልግሎት በዘመናዊ ዕቅድ በተሰናዳው መስታወት ውስጥ ማኖር ይገባቸዋል።ይህም ባይቻል አቧራ ወደሌለበት ሁለተኛው መንገድ እንዲዛወሩ ማድረግ ስለሚገባ ፤ሥራው የሚመለከተው ባለሥልጣን ያስብበት ዘንድ ሳስታውስ በትሕትና ነው። መመሳሰል ይገባዋልበዚሁ ከተማ የሚገኘው የጠቅላይ ግዛቱ በጅሮንድ ጽ/ቤት በሦስት ቦታ ተከፋፍሎ የሚገኝ ከመሆኑም በላይ ቤቱም በጠላት ጊዜ የተሠራ አሁን መፍረስ የጀመረ ነው።ስለ የውስጥ ዕቃውም አጠባበቅ ከቤቱ ይልቅ ዘበኞቹንና ካዝናውን ማመን ግድ ሳይሆን አይቀርም። ይኸውም ሆኖ ለሥራው የተመጠነ ስፋት ያለው አይደለም። በአካባቢው የሚገኙት ቢሮዎች በአማረና በጥሩ ሕንፃ የተሠሩ ሲሆኑ፤ የተጠቀሰው መሥሪያ ቤት እርጅና የእነሱን ውበት ግርማ አሳንሶታል።ስለዚህ ጓደኞቹን እንዲመስል የክፍሉ ባለሥልጣን ይተጋበት ዘንድ ማሳሰብ የጋዜጣው ፋንታ ነው። የሲዳሞ ጠ/ግዛት አዣንስ ኃይለ መስቀል ወልደየስ (የካቲት 20 ቀን 1951 የወጣው አዲስ ዘመን) ሁለት ወንዶች ልጆችእናት በአስር ቀን ልዩነት ሁለት ወንዶች ልጆች ወለደች። በወቅቱ ዜናው ጋዜጣችን ላይ ሲወጣ ርዕሰ ዜናው ከላይ እንደተጠቀሰው ሁለት ወንዶች ልጆች ብቻ ነበር የሚለው በሚከተለው መልኩ ተዘግቦ ስለነበር እንድታነቡት እንጋብዛለን። በደብረ ታቦር ከተማ ዙሪያ ቃናት ማርያም ከተባለው አገር የአቶ መኰንን ካሳ ባለቤት ያልጋነሽ አድማሱ የተባለችው ፤ጥር 22 ቀን 51ዓ.ም ከሌሌቱ 8 ሰዐት ሲሆን አንድ ወንድ ልጅ ከወለደች በኋላ 10 ቀን ቆይታ የካቲት 2 ቀን 1951 ዓ.ም ከጥዋቱ 1 ሰዐት ሲሆን አንድ ወንድ ልጅ ደግማ መውለዷንና ሁለቱም ልጆች እስካሁን በሕይወታቸው መኖራቸውን የነዚሁ ልጆች አባት አቶ መኰንን ካሳ አስታውቀውናል። የደብረ ታቦር ከተማው ዙሪያ ምክትል ገዥ ባላምባራስ ኃይሌ ታምራት በቁጥር100/1951የካቲት 10 ቀን በተጻፈ ደብዳቤ አረጋግጠውልናል።እኒህ የምክትል ወረዳ ገዥ እንደዚህ ያለው ሁኔታ በጋዜጣ እንዲገለጥ በቶሎ ለአውራጃው ግዛት አዣንስ ጽ/ቤት በማስተላለፋቸው እናመሰግናለን። ሌላዎችም ምክትል ገዥዎች የርሳቸውን አርአያ ተከትለው ይህን የመሰለ ጉዳይ ሲያጋጥማቸው በፍጥነት የሚያስታውቁን ቢሆን ከፍ ያለ ምስጋና የሚያገኙበት መሆኑን እንገልጻለን።የደብረ ታቦር አውራጃ አዣንስ አሰፋ ረታ (የካቲት 17 ቀን 1951 የወጣው አዲስ ዘመን)
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=38334
[ { "passage": "መኳንንት ጌጡ በከብት ንግድ ላይ ከተሰማራ ከአሥር ዓመት በላይ አልፎታል። በጎችና ፍየሎችን ከገበሬዎች እየገዛ ለአዲስ አበባ ነጋዴዎች የሚያከፋፍለው መኳንንት በሥራው ላይ ብዙ ጊዜያትን ቢያሳልፍም፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ገበያው ተገማች ባለመሆኑ ኪሳራ ውስጥ እየወደቀ መሆኑን ይናገራል። ለአብነትም ባለፈው የአዲስ ዓመት በዓል ገበያ ይኖራል በሚል ዕሳቤ በከፍተኛ ዋጋ በጎችና ፍየሎችን ከገበሬዎች ገዝቶ የነበረ ቢሆንም፣ ሸማቾች ዋጋ በመወደዱ እንዳልገዙት ያስታውሳል። ‹‹ገበሬዎች ዋጋ በመጨመራቸው የተነሳ እኔም ይህንን ማካካስ ነበረብኝ፤›› የሚለው መኳንንት፣ ዋጋ በመጨመሩ ምክንያት ሸማቾች ፍላጎት የነበራቸው ቢሆንም፣ ሊገዙት እንዳልቻሉ፣ ምንም እንኳን በጎቹን ከበዓል በኋላ በአነስተኛ ዋጋ ቢሸጣቸውም፣ ከፍተኛ ኪሳራ ደርሶበት እንደነበር ያወሳል። ታዲያ ለዘንድሮ ገና በዓል ከአዲስ ዓመት ገጠመኙ ትምህርት በመውሰድ ረከስ ባለ ዋጋ ከገበሬዎች ቢገዛም፣ የሸማቾች ፍላጎት በጣም ወርዷል ይላል። ‹‹ከጊዜ ወደ ጊዜ ገበያውን መገመት አዳጋች እየሆነ ነው፤›› የሚለው መኳንንት፣ በተለይ በአገሪቱ የሚስተዋለው አለመረጋጋት ሸማቾች በተረጋጋ መንፈስ እንዳይሸምቱ እንዳደረጋቸው ምልከታውን ያጋራል። የገና ገበያ ምን ይመስላል?በዘንድሮ የገና በዓል ገበያ ከአዲስ ዓመት አኳያ የምግብ ምርቶች ዋጋና የአቅርቦት መረጋጋት ቢያሳዩም፣ የሸማቾች ቁጥር ብዙም ጭማሪ አለማሳየቱን ነጋዴዎች ይናገራሉ። የሪፖርተር ዘጋቢዎች በቦሌ፣ ሾላ፣ መርካቶና ቄራ በሚገኙ ገበያዎች ባለፉት ሁለት ቀናት ያደረጉት ዳሰሳ እንደሚያሳየው፣ በተለይም የዶሮ፣ የበግና የፍየል አቅርቦት ካለፈው በዓል አንፃር ጭማሪ አሳይቷል። በአዲስ ዓመት ወቅት እስከ 550 ብር ሲሸጥ የነበረው የዶሮ ዋጋ በገና ወደ 400 ብር የወረደ ሲሆን ከወላይታ፣ ከአርባ ምንጭ እንዲሁም በአዲስ አበባና ዙሪያ ከተሞች የዶሮዎች ቁጥር መጨመሩ እንደ ምክንያት ተነስቷል። ከበግና በፍየል ገበያ መረጋጋት ታይቷል። ‹‹ባለፈው በዓል (አዲስ ዓመት) ከኦሮሚያ አንዳንድ ከተሞች ይመጡ የነበሩ በግና ፍየሎች በነበረው አለመረጋጋት የተነሳ ቁጥራቸው ቀንሶ የነበረ ሲሆን፣ በገና በዓል ይህ ችግር ተቀርፏል፤›› የሚለው በቄራ አካባቢ የሚሠራው ሰዒድ መሐመድ የተባለ ነጋዴ ነው፡፡ ይህም ዋጋ እንዲረጋጋ ትልቅ ሚና እንደተጫወተ አስረድቷል። የሸማቾችም አስተያየት ከዚህ ብዙ የተለይ አይደለም። ‹‹በአዲስ ዓመት ሁሉ ነገር ተወዶ ነበር፤›› የሚሉት ተመሥገን ቢተው የሚባሉ ሪፖርተር በቦሌ አካባቢ ያገኛቸው ሸማች፣ የበግና የፍየል ዋጋ ከፍተኛ ቅናሽ ማሳየቱንና የተሻሉ አማራጮቹም በዘንድሮ በዓል መታየታቸውን ተናግረዋል።በአዲስ ዓመት ወቅት እስከ 6,000 ብር ሲሸጥ የነበረው መካከለኛ መጠን ያለው በግ በዘንድሮ ገበያ ወደ አራት ሺሕ ብር ዝቅ ያለ ሲሆን፣ ሙክት የሚባል የሰባ በግ ከ9,000 ብር ወደ 6000 ዝቅ እንዳለ ነጋዴዎች ተናግረዋል። በተመሳሳይ ከፍተኛው የፍየል ዋጋ ከ12,000 ብር ወደ 8,000 ብር ዝቅ ማለቱን፣ አነስተኛ ክብደት ያለው የፍየል ዋጋ ከአንድ ሺሕ ብር በላይ ቅናሽ በማሳየት በ3,000 ብር ሲሸጥ ተስተውሏል። እንደ ገበያው ቅርበት ቢለያይም በአዲስ አበባ ሲሸጡ የነበሩ ፍየሎችና በጎች በብዛት ከደብረ ብርሃን፣ ከዱበር፣ ከጊንጪ፣ ከደሴና ከጅማ የመጡ ናቸው፡፡ ሠንጋዎች በአብዛኛው ከምሥራቅ ኦሮሚያ በተለይም ሐረርጌ ዞን ውስጥ ከሚገኙ አነስተኛ ከተሞች የመጡ እንደሆኑ ሪፖርተር በከተማው ያደረገው ዳሰሳ አመላክቷል። በተጨማሪ ቅልብ ሠንጋዎች በአብዛኛው ከአዳማ፣ ከባሌና ከአርሲ የገቡ ሲሆን ከጎንደርና ከወለጋ የመጡ ሠንጋዎች ቁጥር ላይ ቅናሽ መታየቱን ለማወቅ ተችሏል። በግና ፍየል ላይ የታየው የዋጋ መቀነስ ሠንጋዎች ላይ የታየ ሲሆን፣ እስከ 5,000 ብር የሚደርስ ቅናሽ ተስተውሏል። የሐረር ሠንጋዎች ከ34,000 ብር አንስቶ እየተሸጡ የነበረ ሲሆን፣ ዝቅተኛ ዋጋ ያላቸው ሠንጋዎች ደግሞ ከ10,000 ብር እስከ 12,000 ብር ድረስ ሲሸጡ ተስተውሏል። ያላቸው ክብደት መካከለኛ የሚባሉት ሠንጋዎች ደግሞ ከ12,000 ብር እስከ 18,000 ብር ሲሸጡ ተስተውሏል። ይሁን እንጂ በአዲስ አበባ በቅርጫ ሠንጋ የመግዛት ልማድ እየቀነሰ በመምጣቱ፣ በብዛት ሠንጋዎችን የሚገዙት ልኳንዳዎች መሆናቸውን ማወቅ ተችሏል። በሌላ በኩል ከአቅርቦት አኳያ ከአዲስ ዓመት መሻሻል ቢታይም፣ የገዥዎች ቁጥር ላይ እምብዛም ለውጥ እንዳልታየ አሸናፊ ሽፈራው የተባሉ የከብት ነጋዴ ለሪፖርተር ተናግረዋል። ለዚህም እንደ ምክንያት ያነሱት፣ ‹‹በዓሉ በሐሙስ ቀን መዋሉን›› ሲሆን፣ በማግሥቱ የፆም ቀን በመሆኑ የገዥዎች ፍላጎት ቀንሷል ብለዋል፡፡ የሠንጋ ዋጋ መረጋጋት ቢያሳይም ልኳንዳ ቤቶች በሥጋ ዋጋ ላይ ቅናሽ ማድረጋቸው አልታየም። በአንዳንድ አካባቢዎች ከወዲሁ ጭማሪዎች እየታዩ ሲሆን፣ በአሁኑ ጊዜ የአንድ ኪሎ ሥጋ ዋጋ ከ200 ብር እስከ 600 ብር እየተሸጠ መሆኑን ሪፖርተር ያደረገው ዳሰሳ ያሳያል፡፡  በሌላ በኩል በዓልን ተከትሎ በስፋት በጥቅም ላይ ከሚውሉ ምርቶች መካከል የሆነው ቅቤ ዋጋ ላይ እስከ 20 ብር ጭማሪ የታየ ሲሆን፣ በመርካቶና በሾላ ገበያዎች በኪሎ እስከ 290 ብር ሲሸጥ ተስተውሏል። ከአቅርቦት አኳያ ካለፈው በዓል አንፃር የተሻለ ሁኔታ እንደነበር ነጋዴዎች ተናግረዋል። በተመሳሳይ በኮረሪማ አቅርቦት ላይ መሻሻል መታየቱን ተከትሎ ከአዲስ ዓመት አኳያ እስከ 80 ብር የሚደርስ ቅናሽ ታይቷል። በሾላና በመርካቶ ሪፖርተር ባደረገው ዳሰሳ በኪሎ እስከ 170 ብር ሲሸጥ ተስተውሏል። በአዲስ ዓመት ወቅት እስከ 38 ብር ሲሸጥ የነበረው የሽንኩርት ዋጋ ወደ 17 ብር የቀነሰ ሲሆን፣ የነጭ ሽንኩርት ዋጋም ከ160 ብር ወደ 100 ብር ወርዷል፡፡በምግብ ምርቶች ላይ የታየው መረጋጋት ምግብ ነክ ያልሆኑ ምርቶች ላይ ሊታይ አልቻለም። ለአብነት አልባሳቶችን ማንሳት ይቻላል።በመርካቶ፣ በፒያሳና በሃያ ሁለት አካባቢዎች የሪፖርተር ዘጋቢ ባደረገው ዳሰሳ መሠረት፣ ከውጭ የሚገቡ ሱሪዎች ላይ ከ100 ብር እስከ 200 ብር የሚደርስ ጭማሪ የታየ ሲሆን፣ የወንድና የሴት ጫማዎች ላይ ከ50 ብር እስከ 150 ብር ጭማሪ ታይቷል። ከቻይና የሚገቡ ምርቶች በውጭ ምንዛሪ እጥረት የተነሳ አቅርቦታቸው መቀነሱ እንደ ምክንያት ተወስቷል። በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከውጭ ከሚገቡ አልባሳት ውስጥ 90 በመቶ ከቻይና በመሆናቸው፣ ያለው የአቅርቦት ችግር ካልተፈታ የታየው የዋጋ ጭማሪ ከፍተኛ ሽያጭ ይኖራል ተብሎ በሚገመትበት የጥምቀት በዓል ላይ የበለጠ ሊጨምር እንደሚችል፣ አብሽሮ አወል የተባሉ በልብስ ንግድ ላይ የተሰማሩ ነጋዴ ተናግረዋል። ባለፉት ሦስት ወራት የታየው የምርት እጥረት በዓይነቱ የከፋ መሆኑን ሪፖርተር ያነጋገራቸው ነጋዴዎች የተናገሩ ሲሆን ከዱባይ የሚገቡ ምርቶች ላይ የሚጣለው ቀረጥ ከፍ ማለቱም ለታየው የዋጋ ጭማሪ ምክንያት እንደሆን አስረድተዋል፡፡የታየው የዋጋ ግሽበት በዚህ አያበቃምበአገር ውስጥ የሚመረቱ ጫማዎች የችርቻሮ ዋጋ ላይ እስከ 100 ብር የሚደርስ ጭማሪ ታይቷል። በተለይም ጫማ ለማምረት የሚውሉ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች አቅርቦት በመቀነሱና የፋብሪካዎች የማምርት አቅም በመውረዱ የጫማ ዋጋ ሊጨምር እንደቻለ፣ አማኑኤል መንግሥቱ የተባሉ በአመዴ አካባቢ የጫማ ንግድ ላይ የተሰማሩ ነጋዴ ተናግረዋል። የሸማቾች ልበ ሙሉነትበኢትዮጵያ በተደጋጋሚ የሚታየው አለመረጋጋት፣ የሸማቾች ልበ ሙሉነት (consumers’ confidence) ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚያሳድር ግልጽ ነው። በተለይም አለመረጋጋቶች በሚከሰቱ ጊዜ ሸማቾች የምግብ ምርቶች ይጠፋሉ በሚል ፍራቻ በብዛት ሲገዙ ማየት የተለመደ ሲሆን፣ በእንዲህ ዓይነት ወቅቶች እንደ አልባሳት ላሉ ምግብ ነክ ላልሆኑ ምርቶች ያለው ፍላጎት ሲቀንስ ይስተዋላል። በገና በዓል የዋዜማ ገበያ ላይ የታየው ከዚህ የተለየ እንዳልሆነ ነጋዴዎች ያስረዳሉ፡፡ በአገሪቱ ያለው አለመረጋጋት በከፋ ቁጥር ሸማቾች ልበ መሉነታቸው ስለሚቀንስ የሚያወጡት ገንዘብ ይቀንሳል የሚሉት የጫማ ነጋዴው አማኑኤል፣ አለመረጋጋቶች በተከሰቱ ቁጥር የሽያጭ ገቢያቸው ወዲያውኑ እንደሚቀንስ ይናገራሉ፡፡ የኮሮና ወረርሽኝ የተከሰተ ሰሞን ሸማቾች በመደናገጣቸው ምግብ ነክ ያልሆኑ ምርቶችን መግዛት አቁመው እንደነበር ያወሱት አማኑኤል፣ ከዚያም የሃጫሉን ሞት ተከትሎ በተከሰተው የፖለቲካ አለመረጋጋትና በትግራይ በነበረው ግጭት የተነሳ ተመሳሳይ ችግር ገጥሟቸው እንደነበር ተናግረዋል። ይሁን እንጂ አሁን በአገሪቱ አንፃራዊ ሰላም እየታየ በመሆኑ የሸማቾች ልበ ሙሉነት ስለጨመረ የንግድ እንቅስቃሴው የተሻለ መሆኑን የሚናገሩት አማኑኤል፣ በገና በዓል ገበያ ከአዲስ ዓመት የተሻለ ሽያጭ ማስመዝገባቸውን አውስተዋል። በሌላ በኩል በአገሪቱ አንፃራዊ ሰላም ቢታይም ሸማቾች ከፍተኛ ገንዘብ ለማውጣት ያላቸው ፍላጎት ብዙም አላደገም የሚሉት በከብት ንግድ ላይ የተሰማሩት መኳንንት፣ አሁንም መንግሥት ይህንን ለመቅረፍ መሥራት እንደሚገባው አውስተዋል። በተመሳሳይ የሸማቾች ልበ ሙሉነት ወሳኝነት እንዳለው የሚናገሩት የምጣኔ ሀብት ባለሙያው አቶ አየለ ገላን ሲሆኑ፣ ለኢኮኖሚ ዕድገት ሞተር በመሆን እንደሚያገልግል ያስረዳሉ። ‹‹ሸማቾችና ነጋዴዎች በምጣኔ ሀብት ላይ ያላቸው መተማመን የተሻለ ሲሆን፣ የኢኮኖሚው ዕድገትም የተሻለ ይሆናል። ይህንን ማድረግ ካልተቻለ ደግሞ አገሪቱ የምታሳየው ዕድገት ይቀንሳል፤›› በማለት፣ የሸማቾች ልበ ሙሉነት ለኢኮኖሚ ዕድገትና መረጋጋት ያለውን የማይተካ ሚና የመንግሥት የፖሊሲ አውጪዎች ሊረዱት ይገባል ሲሉ አቶ አየለ ሐሳባቸውን ለሪፖርተር አጋርተዋል። በሳምሶን ብርሃኔ", "passage_id": "a5b7e6e5832e7a77d46647633ddc3e72" }, { "passage": "የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ተመስገን ጥሩነህ የ2012 አዲስ ዓመት ዋዜማ ልዩ ዝግጅት መልዕክትሙሉ መልዕክቱን ያንብቡትየተከበራችሁ የአማራ ክልል ህዝቦች፤የተከበራችሁ መላው የአገራችን ህዝቦች፤ክቡራን የሃይማኖት አባቶች፤የተከበራችሁ የፌዴራልና የክልል የስራ ኃላፊዎች፤የተከበራችሁ የዞን፣ የከተማ፣ የወረዳና የቀበሌ አመራሮች፤ክቡራን የባህር ዳር ነዋሪዎች፤ክቡራን ጥሪ የተደረገላችሁ ምሁራንና ባለሃብቶችክቡራትና ክቡራንበቅድሚያ ሁላችንንም እንኳን ከዘመን ዘመን በሰላም አሸጋገረን፡፡ መልካም አዲስ ዓመት፤ እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን ለማለት እወዳለሁ፡፡ በዚህ አይነቱ ለየት ባለ ሁኔታ በተዘጋጀ የአዲስ ዓመት ዋዜማ ዝግጅት ተገኝቼ መልዕክት ማስተላለፍ በመቻሌ የተሰማኝ ደስታ እጥፍ ድርብ መሆኑን እየገለፅኩ ‹‹ማቅ አውልቀን፤ ግምጃ እንልበስ›› በሚል መሪ ሃሳብ በተዘጋጀው በዚህ የዋዜማ ክብረ በዓል ላይ ጥሪ ስናስተላልፍላችሁ ፈቅዳችሁ የአዲስ ዓመት ዋዜማ ክብረ በዓላችን ተካፋይ ለመሆን በመምጣታችሁ በክልሉ መንግስት፣ በህዝቡና በራሴ ስም ላቅ ያለ ምስጋናዬን እያቀረብኩ የአማራ ክልል ርዕሰ መዲና ወደ ሆነችው ውቢቷ ከተማችን ባህር ዳር እንኳን ደህና መጣችሁ ለማለት እወዳለሁ፡፡ክቡራትና ክቡራን፡-ኢትዮጵያ የፍጥረታት ሁሉ መነሻ ምድረ ቀደምት፣ የጥንታዊ ታሪክ ባለቤት፣ የገናና ስልጣኔ አምባ፣ የአኩሪ ተጋድሎ እና ድል ባለቤት ሀገር ስትሆን ኢትዮጵያዊነት ደግሞ የኩራት ምንጭ ነው፡፡ ኢትዮጵያዊነት የኩራት ምንጭ ነው ስንል ሀገሪቱ ጥንታዊነት እና የገናና ስልጣኔ ባለቤት የነበረች መሆኑ ብቻ ሳይሆን የበርካታ ውብ ባህሎች ሀገር በመሆኗም ጭምር ነው፡፡ የኢትዮጵያውያን ባሕሎች ዘርፈ ብዙ እና ውቦች ናቸው፡፡ ከባሕላችን መገለጫዎች መካከል አንዱ የበዓል አከባበር ስርዓታችን ነው፡፡ በዓላት ለእኛ ለኢትዮጵያውያን ልዩ ቦታና ትርጉም አላቸው፡፡ በተለያዩ በዓላቶቻችን እንደ ሕዝብ ትዝታችን ተጽፎባቸዋል፤ ህብረታችን ታትሞባቸዋል፣ ማህበራዊ ትስስራችን ተገምዶባቸዋል፤ ተስፋችን ተበስሮባቸዋል፡፡ የዘመን መለወጥን ማብሰሪያው የአዲስ ዓመት በዓልም ሁላችንም ኢትዮጵያውያን በጋራ የምናከብረው፤ ከከረምንበት ጭጋጋማ ብርዳማ ክረምት፣ ተስፋን ወደምትፈነጥቀው የጸደይ ፀሀይ፤ ማብሰሪያ ወቅት የሚከበር በመሆኑ፤ ልዩ ስሜት ይሰጣል፤ ለዚህም ነው ብዙዎቻችን የአዲስ ዓመት በዓል ትዝታ የሚናፍቀን፡፡አገራችን ኢትዮጵያ የተገነባችበት ሁኔታ፤ እንደ ታሪኳ ሁሉ ረዥም ጊዜ የፈጀ፣ በጥልቅ ጥበብ የተበጀ ነው፡፡ ይህቺ ድንቅ አገር የተገነባችው በቅድመ አያቶቻችን ብርቱ ታታሪነት፣ደም እና አጥንት ነው፡፡ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስከበር እና ክብሯን ለማስጠበቅም፤ የአማራ ክልል ሕዝቦች ከሌሎች እህት እና ወንድም ኢትዮጵያውያን ጋር በመሆን ሳይሰስቱ ፊት ለፊት ግንባራቸውን ሰጥተዋል፡፡ ለዚህም ቅዱስ ተግባራቸው ለዘላለም ስናከብራቸው፣ ስናመሰግናቸው እና ስንመካባቸው እንኖራለን፡፡ዓለም የሚመሰክረው እኛም የምናውቀው ሀቅ የአማራ ክልል ሕዝቦች መነሻ እና መድረሻቸው፤ የኢትዮጵያ ጥንካሬ እና ታላቅነት ነው፡፡ ይህም ዕውን የሚሆነው፤ በሁሉም የኢትዮጵያውያን ሕብር እና እኩልነት እንደሆነ በጽኑ ያምናሉ፡፡ የአማራ ክልል ሕዝቦች፤ በኢትዮጵያ አገር ግንባታ ሂደት ውስጥ የተለያዩ ፈተናዎችን አልፈዋል፡፡ በተለይም ኢትዮጵያን ለማፍረስ የፈለገ ጠላት ሁሉ፤ የመጀመሪያ ኢላማ አድርጎ ግፍና መከራ የሚያደርስበት፣ ባህሉን ለማጥፋት የሚረባረብበት፤ ወጉን ለማኮስመን የሚታትርበት የአማራ ክልል ሕዝቦችን ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ይህ የሆነበት አበይት ምክንያ የአማራ ክልል ሕዝቦች ለኢትዮጵያ እና ለህብረ ኢትዮጵያዊነት ቀናኢ በመሆናቸው ነው፡፡በመሆኑም ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን ለመካድና ለመርሳት ወይንም ለመጥራት እና በውስጣቸው ለመኖር መስጋት፤መጠራጠር፤ መዘንጋት ለሚሹ አካላት ከላይ የጠቀስኳቸውን የኩራት ምንጮች የሆኑ ውብ የአባቶቻችን ባህል፣ ወግ፣ ወኔና ጀግንነት አለማወቅ፤ ወይንም እያወቁ ሆነ ብሎ ማጥፋት በመሆኑ የእንዲህ አይነት አባዜ የተጠናወታቸው አካላት ሁሉ፤ በአዲሱ ዓመት ፈጣሪ ቅን ልቦና እንዲሰጣቸው እንመኛላቸዋለን፡፡ክቡራንና ክቡራት፡-ባለፉት በርካታ ዓመታት በመጣንበት ጉዞ ውስጥ ያጋጠሙ ፈተናዎች እና ሳንካዎች እጅግ ብዙ እና ውስብስብ ቢሆኑም ከፊሉን ተገዳድረን እያለፍን ብዙውን ግን በአሸናፊነት እየተወጣን እዚህ ደርሰናል፡፡ በየጊዜው ያጋጠሙንን ፈተናዎች እንዴት ማለፍ እንደቻልን ልምድ እና ተሞክሮ ያለን ህዝቦች ስለሆን፤ ባለፉት ጊዜያት በአገራችን በተለይም በክልላችን ያጋጠሙንን ፈተናዎችም፤ በአሸናፊነት መወጣት ጀምረናል፡፡ ችግር ሲያጋጥመን እንዴት መፍታት እንዳለብን የተማርነው፤ ከቀደምት አባቶቻችን ነው፡፡ እኛ የጠበብት አባቶች ልጆች ነን፡፡ አይደለም በጥንታዊቷ ይቅርና በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እንኳ የኢትዮጵያንም ሆነ የአማራን ሕዝብ በእጅጉ ህልውናውን የሚፈታተኑ፣ አያሌ ጉድጓዶች ተምሰዋል፡፡ ይሁንና፤ በፈተና ወቅት ወደ ኋላ መንደርደር ማለት ለባለ ራዕይ ወደ ፊት እንዴት እንደሚያስወነጭፍ አባቶቻችን አስተምረውናል፡፡ እኛም የአባቶቻችን ልጆች ነንና፤ ዛሬም ብዙ የችግር አረንቋዎች አልፈን እዚህ ደርሰናል፡፡ አበው እንደሚሉት ችግር ሲገጥመው የሚደነግጥ ከዚህ ቀደም ያለ ችግር የኖረ ሰው ነው፡፡ በብዙ ችግር ያለፈ ሰው ግን የሚያጋጥመውን ፈተና በብቃትና በአሸናፊነት ይወጣዋል፡፡ እኛም እንደ ሕዝብ የብዙ ተግዳሮቶች ውል የሚፈታበትን ጥበብ የያዝን ስለሆነ ባለፈው ጊዜ በክልላችነ አጋጥሞን የነበረውን አስጨናቂና ከባድ ጊዜ ተቋቁመን ይኸው እዚህ ደርሳል፡፡ ይህ ክስተት ያደረሰብን የህይወት የንብረትና የስነ ልቡና ጉዳት ከባድ ቢሆንም በደረሰብን ሀዘን እየቆዘምን እንደ ዶሮ አንገት ደፍተን መሬት ስንጭር የምኖር ደካሞች አይደለንም፡፡ክቡራንና ክቡራት፡-አጋጥሞን የነበረው ጉዳት ጥልቅ ሀዘን ውስጥ ቢያስገባንም ለሕዝባችን ስንል ከሀዘን ቶሎ መውጣት ነበረብን፡፡ ሀዘን ማብዛት ትረፉ የበለጠ ለችግር መጋለጥ ነው፡፡ መሪ በደስታ ጊዜ ብቻ ሳይሆን በሀዘን ጊዜም ጭምር ሕዝቡን እየመራ ማሻገር አለበት፡፡ በሀዘን በመቆዘም የምናተርፈው ነገር የለም፡፡ የሚሻለን የወንድሞቻችንን ህልም እውን ማድረግ ነው፡፡ ስለሆነም ያጋጠመን ጉዳት ወደ ባሰ ችግር ሳይሸጋገር ከሕዝባችን ጋር ሆነን በጥበብ በመወጣት ከማቅ ወደ ግምጃ ከምንሻገርበት ቀን ደርሰን፤ ይኸው ዛሬ በእናንተ ፊት ግምጃ ለብሰን መቆም ችለናል፡፡የማያሳፍረንና የማያሳንሰን የክልላችን ሕዝብ፤ ከጎናችን ሁኖ ስለደገፈን በሕዝባችን አይዞህታ ተረጋግተንና ተበረታተን፤ ይኸው ዛሬ ማቅ አውልቀን ግምጃ ለብሰን ለተጨማሪ ተስፋ እና ድል ወደ መጪው ብሩህ ዓመት እንሸጋገር ዘንድ ቆርጠን ተነስተናል፤ አዲሱን ዓመት ስንቀበል ከሕዝባችን ጋር ጣትና ጥፍር ብቻ ሳይሆን ደምና የደም ስር ሆነን የምናከናውናቸውና ውጤት የምናስመዘግብባቸው በርካታ ተግባራት ሰንቀናል፡፡ በአዲሱ ዓመት “ማቅ አውልቀን ግምጃ እንለብሳለን” ስንል ከመቼውም ጊዜ በላቀ መንገድ ለሁለንተናዊ ልማትና ለፍትሃዊ ተጠቃሚነት እንሰራለን ማለታችን ነው፡፡በመሆኑም በመጪው ዓመት የተስፋ ግምጃችንን ለመልበስ ጠንካራ የመንግስትና የፓርቲ አደረጃጀትና ተቋማዊነት እንፈጥራለን፡፡ ህግን የማስከበርና የሕዝብን ደህንነት ዋስትና የሚሰጥ የፀጥታ እና ፍትህ መዋቅሮችን ተደራሽና ጠንካራ እናደርጋለን፡፡ ለዘመናት ስር ሰዶ ያለውን ድህነት የመቀነስ ትግል አጠናክረን የልማትና የኢንቨስትመንት ተግባራትን ከምንጊዜም በተሻለ ቁርጠኝነት ለማሳካት እንረባረባለን፤ ግብርና ትልቁ የትኩረት ማዕከላችን ይሆናል፤ የሥራ ዕድል ፈጠራ በሁሉም ዘርፎች በተለይም ደግሞ በግብርና ኢንቨስትመንት፣ በቱሪዝም ዘርፎች በተለየ ሁኔታ ትኩረት ሰጥተን እንሰራለን፤ በመጪው ዓመት ክልላችንን ብቻ ሳይሆን ሀገራችንንም ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያላቸው ፋብሪካዎችን ስራ ለማስጀመር ጥረት ይደረጋል፤ በእነዚህም ትርጉም ያለው የሥራ ዕድል ለመፍጠር በትኩረት እንቀሳቀሳለን፡፡ ከክልል ውጭ የሚኖሩ የአማራ ክልል ተወላጆች ሁለንተናዊ መብታቸው እንዲከበር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራና በትብብር እንሠራለን፡፡ በአገራችንና መላው ዓለም ከሚገኙ ምሁራን ባለሀብቶችና ከመላው ሕዝብ ጋር በመቀራረብና በመመካከር የልማት የሰላምና የዴሞክራሲ ትግላችንን በትብብር ለመሥራት ከምንጊዜውም በላይ እንተጋለን፤ በተለያዩ አካባቢዎች የሚነሱ የማንነትና የአስተዳደር ወሰን ጥያቄዎች የሕዝባችንን ደህንነት እና ሕገ መንግስታዊ መብት በሚያረጋግጥ ሕጋዊና ዴሞክራሲያዊ አግባብ የሕዝቦችን ፍትሐዊ ተጠቃሚነት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ እና አገራዊ አንድነት ለመፍጠር እየተሠራ ነው፡፡ክቡራትና ክቡራን፡-በዚህ ልዩ የዋዜማ ዝግጅት በሀዘናችን ወቅት ከጎናችን ለነበሩ ሁሉ ምስጋናና በእግረ መንገዱም አደራ አቀርብ ዘንድ እንድትፈቅዱልኝ እጠይቃለሁ፤እናንት የእውነተኛ ህብረ መገለጫ የሆናችሁ የአማራ፣ የአገው፣ የኦሮሞ፣ የአርጎባ፣ የቅማንት በጥቅሉ የክልላችን ሕዝቦች፣ በተለይም ደግሞ የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዎች በዚያ የማቅ ወቅት ከጎናችን ባትሆኑ ኖሩ ዛሬ ለዚህ ግምጃ አንደርስም ነበር፡፡ ለአስተዋይነታችሁና ለአርቆ ተመላካችነታችሁ ክብር ይገባችኋልና የክልሉ መንግሥት በእጅጉ ያመስግናል፡፡ እናንተን ይዘን የማናሳካው እቅድ አይኖረንም፡፡ በመሆኑም መላው የክልላችን ሕዝቦች ከክልሉ ወጪና በተለያየ የዓለም አካባቢ የምትኖሩ ወገኖቻችን እኛ ህልማችን በሁለንተናዊ መልኩ የለማና ያደገ ሕዝብና ከባቢ መፍጠር ነውና፤ ለዚህ እውን መሆን ከመቼውም በላይ ቆርጠን እንደተነሳን አውቃችሁ ከጎናችን በመሆን እንድታግዙን ስንደክም እንድታበረቱን ስንሳሳት እንድታርሙን በዚህ አጋጣሚ ጥሪ ለማቅረብ እወዳለሁ፡፡ እናንተ የዕምነት ተቋማት የሃይማኖት አባቶች፤ የአገር ሽማግሌዎች ያለ እናንተ ተግሳፅና ምክር፤ ያለ እናንተ ቡራኬና ፀሎት፤ እንዲሁም ያለ እናንተ ግልግልና እርቅ አገር አይረጋም፡፡ በሃገራችን ያሉ ሁሉንም ሃይማኖቶች አስተምህሮ ስንመረምረው ሁሉም ሰላምን፣ ፍቅርን፣ መቻቻልን፣ መተባበርንና አንድነትን የሚያስተምሩ ናቸው፡፡ የኛ ህዝብ እንኳን የሰው ሊወስድ የወደቀ ቢያገኝም አንስቶ ለባለቤቱ የሚሰጥ፣ ጠብ ቢያጋጥመው በህግ አምላክ የሚል፣ እንግዳ ቢመጣበት እግር አጥቦና ከአልጋው ወርዶ የሚያስተናግድ፣ ምን ይሉኝ የሚገደው ሆኖ የዘለቀው በእናንተ አስተምህሮ ነው፡፡በተለይም የክርስትናም ይሁን የእስልምና አስተምህሮት በሀገራችን ኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ትውልድን በጥሩ ስነ ምግባር በመኮትኮትና በማሳደግ ፊደል ቀርፆና ብራና ፍቆ አሁን ለደረስንበት ዘመናዊ ትምህርት መሰረት የጣለ ሃገራችን ኢትዮጵያ በተለያዩ ጊዜ በገጠማት የውጭ ወረራም ይሁን የውስጥ ችግሮች ለሃይማኖታቸውና ለሃገራቸው ክብር ሲሉ ክርስቲያኖች መስቀላቸውን፣ ሙስሊሞች ኪታባቸውን ይዘው ተፋልመዋል፡፡ አኩሪ መስዋዕትነትና ገድል ፈፅመዋል፡፡ በመሆኑም ሃገራቸውንና ሃይማኖታቸውን ለዚህ ትውልድ አስረክበዋል፡፡ ይህ ሃይማኖትንና ሃገርን የመከፋፈል ጥቃት በተለያዩ ጊዜያት በውስጥም ይሁን በውጭ ሴራ ተሞክሮ የከሸፈና ያልተሳካ የደካሞች እኩይ ዕቅድና ድርጊት ነው፡፡ ባሳለፍነው ወርም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ የተቃጣው ሃይማኖትን የመከፋፈል ሴራ ፈፅሞ ተቀባይነት የሌለው እና መንግስት ከእምነቱ ተከታዮችና ከመላው የኢትዮጵያ ህዝቦች ጋር በመሆን በጋራ ልንመክተው የሚገባ ጉዳይ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ ባሳለፍነው ከባድ ወቅትም በፀሎትና በምክር ከጎናችን እንዳልተለያችሁን ሁሉ መጭው ዘመን ያሰብነውን የምንተገብርበት ይሆንልን ዘንድ ፀሎታችሁ፣ ምክራችሁ፣ አይዞህ ባይነታችሁ እንዳይለየን፣ በትህትናና በታላቅ አክብሮት እጠይቃለሁ፡፡የክልላችን ሆነ የአገራችን የዛሬም ሆነ የነገ ተስፋ የሆናችሁ ወጣቶቻችን፣ እኛ ከእናንተ የምንፈልገው ነገር እንዳለ ሁሉ፣ እናንተም ከእኛ ብዙ ነገር እንደምትፈልጉ እናውቃለን፡፡ የእናንተ ፍላጎት አቅም በፈቀደ መጠን ለሟሟላት፣ ሌት ከቀን እየሰራን እንደሆነ አውቃችሁ፣ ለእቅዶቻችን ስኬት ግንባር ቀደም ሆናችሁ ተሰለፉ እኛንም ደግፉን፡፡ ምክንያታዊ ሆናችሁ ሞግቱን እንጂ አታደናቅፉን፡፡ እናንተ ክፍተቶቻችንን ማሳየት አንዳንዱን ደግሞ እናንተም መሙላት ይጠበቅባችኋል፣ ለእናንተ በተለይም ለመላው ህዝባችን ህልውና ብለን፣ ህግና ስርአት ለማስከበር በምንንቀሳቀስበት ጊዜ፣ ለሰላም ስትሉ አግዙን እንጂ አታስተጓጉሉን፡፡ ይልቁንስ ተከባብረን ስለነጋችን በመነጋገር እና በመመካከር የክልላችንን ብሎም የአገራችንን ልዕልና በማስጠበቅ ወደ ተሻለ ምዕራፍ የማሸጋገር ታሪካዊ ኃላፊነታችንን እንድንወጣ ምክሬን እለግሳለሁ፡፡የክልላችን አርሶ አደሮች፣ በአዲስ አመት አዲስ ተስፋ ሰንቃችሁ፣ አርሳችሁ እና አለስልሳችሁ የዘራችሁት ሰብል መልካም ቡቃያ እያያችሁ፣ በምትገኙበት በዚህ ጥሩ ወቅት ላይ ትገኛላችሁ፡፡ እናንተ ምንጊዜም ከእርሻ ስራችሁ ማንም አይነጥላችሁም፣ ሊነጥላችሁ የሞከረም አልተሳካለትም ፤ አሁንም ይህን ተግባራችሁን አጠናክራችሁ እንደምትቀጥሉ እምነቴ የጸና ነው፡፡ በመጪው አመት ግብርናን ለየት ባለ የአሰራር ሁኔታ በሙከራ ደረጃ በአንዳንድ አካባቢዎች ለመጀመር አቅደናል፡፡ ይህ አሰራርም ስኬታማነቱ ከተረጋገጠ ደረጃ በደረጃ የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን ይረዳል፡፡ በትንሽ መሬት ብዙ ማምረት እና ሰፊ ገቢ ማግኘት የሚያስችል ፕሮጀክት በመሆኑ ለልጆቻችሁም መልካም የስራ እድል አማራጭ ሆኖ ያገለግላል፡፡በአትክልት እና ፍራፍሬ እንዲሁም የእንስሳት ሀብት ላይ ያተኮረ በመሆኑ የአመጋገብ ስርዓታችንንም ለማሻሻል ይረዳናል፤ ሰላማችሁን ነቅታችሁ ጠብቁ፡፡ አዳዲስ የአሰራር ዘዴዎችን ጠቃሚነት ተረድታችሁ ተግብሩ፡፡ የመንግስት ድጋፍ በመጪው አመት ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ አደራ የምላችሁ ነገር ትርፍ አምርቱ፤ እናተ እያላችሁ ክንዳችሁ ሳይዝል ኢትዮጵያውያን መራብ የለባቸውም፡፡እናንት የአማራ ክልል ምሁራን፡- የክልላችንን ኢኮኖሚያዊ፣ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎችን ለመደገፍ የምሁራን ሚና የማይተካ መሆኑን እንረዳለን፡፡ ስለሆነም የክልሉን ሁሉን አቀፍ እንቅስቃሴ እንድትደግፉ ፣ችግር ፈቺ የሆኑ ጥናት እና ምርምሮችን እየሰራችሁ ፣ሳይማር ያስተማረ ወገናችሁን ወደ ብልጽግና ለማሻገር፣የመፍትሔ አካል ሆናችሁ እንድታገለግሉና የማህበረሰብ አገልግሎት ኃላፊነታችሁን በተግባር እና በቅርበት እንድትወጡ ጥሪ አቀርብላችኋለሁ፡፡የክልላችን ባለሀብቶች፣ ዳኞች፣ የፍትህ እና የጸጥታ አካላት፣የመንግስት እና የግል ዘርፍ ሙያተኞች፣የሚዲያ አካላት፣ የሲቪክ ማህበራት፣ባለጥበቦች፣የማህበረሰብ አንቂዎች፣ተማሪዎች በጥቅሉ ሁላችሁም ወገኖቻችን በየተሰማራችሁበት ሙያ በኃላፊነት መንፈስ ፣ በንጹህ ሰብዕና፣በተቆርቋሪነት እና በቁጭት ለሰላም፣ለዕድገት እና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ታገለግሉ ዘንድ ጥሪ አቀርብላችኋለሁ፡፡ በምታደርጉት ህግ እና ስርዓትን የተከተለ እንቅስቃሴያችሁ ሁሉ ለሚያጋጥማችሁ ተግዳሮት የክልሉ መንግስት በየትኛውም ቦታና ሰዓት ከጎናችሁ መሆኑን ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ፡፡ክቡራት እና ክቡራን፡-የአማራ ህዝብ ከጥንት ጀምሮ በየትኛውም የኢትዮጵያ አካባቢዎች በብዛት እንደሚኖር ይታወቃል፡፡ ተጋብቶ እና ተዋልዶ እንደጠፍር አልጋ ከሁሉም ጋር ተጋምዶ ይኖራል፡፡ ይህን አጋጣሚ ተጠቅሜ ጥሪ ማቅረብ የምፈልገው ለመላው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ብሔረሰቦች እና ህዝቦች የአማራ ህዝብ በየአካባቢያችሁ የሚኖረው አንድም ሀገሩ ስለሆነ እንደ ኢትዮጵያዊነቱ፣ በሌላ በኩል ደግሞ እናንተ ወንድሞቹ እና እህቶቹ ስለሆናችሁ፣ እንደ ትናንቱ ነገም አብራችሁ ተሳስባችሁ በፍቅር እንደትኖሩ፣ በመካከላችሁ የሚገባውን አሜካላ ጊዜ ሳትሰጡ እንድትነቅሉ እያሳሰብኩ ከእናንተ በላይ ስለእናንተ መስተጋብር የሚያውቅ እና የሚረዳ የሌለ መሆኑን ተረድታችሁ በቆዬው የኢትዮጵያዊነት መንፈስና ስሜት በሰላም እንደትኖሩ ጥሪዬን አቀርብላችኋለሁ፡፡", "passage_id": "573ce324b398d83369010f3754f91d8f" }, { "passage": "አንዱ በሌላው ላይ፣ ወገን በወገኑ ላይ ፈጸመ የሚባለውን ጉድና ደባ ሰምቶ ዝም ማለት አልሆንላት ብሎ፤ እውነቷን ነው ማንስ ቢሆን እንዴት ዝም ይላል። ተለጉመው የነበሩ የስሜት ሕዋሳት ነጻነት በተቀዳጁበት ዘመን ላይ ነው የምንገኘዋ። ‹‹የማሰብ ነጻነት፣ የመናገር ነጻነት፣ የመሰብሰብ ነጻነት፣ የመጻፍ ነጻነት….ወዘተ›› አንደኛ ዓመት ክብረ በዓል ብንለውስ? እንደው ማን ይሙት! ልብ ብሎ ለተመለከተን ‹‹ከገመዱ አፈትልኮ የወጣ እንቦሳ›› መስለን አርፈነዋልሳ። በጨዋ ወግና ባህል ተኮትኩቶ ያደገ ኢትዮጵያዊ ሲናገርም ልክ አለው፤ ሲጽፍም ልክ አለው፤ ሲጠላም ልክ አለው፤ ኧረ ሲወድም ልክ አለው። እንዲህ እንደ አሁኑ ልካችን ልኩን ከማጣቱ በፊት ለሁሉም ነገር ከልክ በታች ነበረ አይደል እንዴ? ‹‹አንድ ሰው ነጻነት በሰጠኸው ቁጥር የበለጠ ኃላፊነት በትከሻው እንዳረፈ ይሰማዋል›› ብሎ የተናገረው ምሁር፣ ፈላስፋ፣ ተመራማሪ፣ ሳይንቲስት ማን ነበር? ብዬ ቀና አልኩና ከቅርብ ጓደኛዬ ምስክርነት ተማጸንኩ። እሱም ‹‹ባውቀው ምን አስደበቀኝ ብሎኝ እርፍ!›› ከት ከት ከት ብዬ ሳቅኩኝ። ትናንት የፕሬስ ነጻነትን ልክ ለማስረዘም ረጅም መዘዝ በራሳቸው ላይ ያስከተሉ ሰዎች ቁጥራቸው ቀላል አይደለም። ዛሬ ያስረዘሙትን ነጻነት ወርዱ ከቁመቱ ተስተካክሎ በልክ እንድናምርበት የማድረጉ ኃላፊነት ከእነሱ በላይ ባለቤት የት ይመጣለታል። ካልተመጠነ ለሌላው እንቅፋት መሆኑ የት ይቀራል። እያንዳንዱ ነገር ልክ ከሌለው ለእልክ ይዳርጋል ይላሉ አባቶች ሲመክሩ።መቼም ‹‹ወሬን ወሬ ያነሳዋልና›› የድሮው ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ሚኒስቴር በሕይወት እያለ ‹‹መብትና ግዴታውን ጠንቅቆ የተረዳ፣ የሕዝብ አገልጋይነት መንፈስ መላበስ›› የሚሉ ነገሮች መለጣጠፍ ያበዛ ነበር። እንደው በጥናት የተረጋገጠ ባይሆንም በርካታ ሰዎች ‹‹የአገልጋይነት ሳይሆን የአጎብዳጅነት መንፈስን የተላበሰ›› ሰራተኛ ነው የተፈጠረው ሲሉ ይደመጣሉ። ለዚህ መገለጫው ‹‹መረጃ የማግኘት መብት››ን ብቻ ማየቱ በቂ ማሳያ ነው ይላሉ። ሠራተኛው በራሱ ተማምኖ ሙያው የሆነውን ጉዳይ እንኳን መረጃ ሊሰጥህ አይደፍርም። በሥራው ተማምኖ ከመኖር ይልቅ አጎብድዶ መኖር ጥቅም እንደሚያስገኝ ይነገራል። ስለዚህ ‹‹የአገልጋይነት መንፈስ ተላብሷል›› ሳይሆን ‹‹ክፉ መንፈስ ተዋርሷል›› ቢባል የተሻለ ይሆናል። ያው እንደልብ መተንፈስ ተችሏል፤ በተነፈሱት ልክ ያውም በልጥ አድርጎ ማስተንፈስም ቀርቷል ብዬ ነው የተነፈስኩላችሁ። አለበለዚያማ የተነፈሱትን ትንፋሽ ያስቆጥር ነበር ያ የትናንቱ ክፉ ቀን። እርግጥ ነው ዶክተሩ የመረጃን ዋጋ አሳምረው ያውቃሉ። መረጃ የመሸጥ ጥበብንም ተክነውበታል። በመረጃ ነጻነት ግኡዝ አካሉ ውስጥም ነፍስ ሊዘሩበት እየጣሩ ነው። ከሥልጣን ዕድሜያቸው አኳያ የመገናኛ ብዙኃንና የመረጃ ነጻነትን ከቀብር አፋፍ ታድገውታል። ቁርጠኝነታቸውን አለማድነቅ አይቻልምና። ትናንት ሐሳብ በማፍለቃቸው፣ በመጻ ፋቸው፣ በመናገራቸው ለመከራ የተዳረጉ ወጣቶችና ጋዜጠኞች ብዙ ናቸው። ዛሬ በማጎሪያ ቤት የሉም። የተለየ ሐሳብ ይዞ መምጣት የሚያኮራ እንጂ የሚያሳፍር፣ የሚያሳስር መሆኑ ያከተመ ይመስላል። ዓለም እኛን የሚመለከትበት የተንሸዋረረ ዓይን ወደ መስተካከል ተጠግቷል። ይልቁ ንስ እኛ ራሳችንን የምናይበት ዓይን፣ እኛ ዜጎቻችንን የምንመዝንበት ሚዛን፣ የምናቀ ርብበት የሜትር ልክ መስተካከል ተስኖት እንደተንጋደደ ይሄው እያገዳደለ ቀጥሏል። የነጻነት ልኩን ማወቅ ተስኖን፣ የመናገር ወሰኑ ጠፍቶን ይሄው እርስ በርሳችን የሰላማችን ፀር ሆነናል። ገዳይ ወንድም፣ ሟች ወንድም፣ አፈናቃይ ወንድም፣ ተፈናቃይ ወንድም ሆኖ ቀጥሏል። ዕድሜ ለሚዲያ ነጻነት እንጂ የቀረርቶ፣ የፉከራና የሽለላ ጫካው በእጃችን ላይ ሆኗል፤ ፌስቡክ። ኢትዮጵያ ለረጅም ዘመናት ስሟን ጥላሸት ሲቀቡ የነበሩ ድርጊቶቿ በአንድ ዓመት ከስመዋል። በሰብዓዊ መብት አያያዝ፣ በሐሳብ ብዝሃነት ማስተናገድ፣ በሚዲያ ነጻነት አጠባበቅ ከፍተኛ ለውጥ መታየታቸውን አሁን ላይ መስካሪዎቹ እኛ አይደለንም። ሌሎቹን ለማሳመን የተመናመነ የሃሳብ ጥይት ከመፈለግ ተገላግለናል። ስለ እኛ የሰብዓዊ መብት አያያዛችን ላይ ‹‹እትፍ እትፍ ይልመድባችሁ›› የሚሉ መስካሪዎች ፍለጋ ከጫፍ ጫፍ መኳተንና ማሰልጠን ቀርቷል። አልሆን ሲልም ረብጣ ገንዘብ ለእጅ መንሻ በቀዳዳ ልኮ አፍ ማዘጋት ዛሬ የለም፤ አንዳንድ ያልጠራ ሁኔታ ግን ሊኖር ይችላል። ሆሆይ ጉድ እኮ ነው። አልሰማንም እንዳትሉ! ለሥራ ከምናውለው ገንዘብ በላይ ቆሻሻ አመላችንን አለያም ገመናችንን ለመሸፈን እንከፍል እንደነበር ከውስጥ አዋቂዎች ውስጡን ጠይቁ። እኛ ተንፍሰናል። የመገናኛ ብዙኃን አቅም በማቆጥቆጥ ላይ ነው። በዘርፉ የሚሰማሩ የሚዲያ ሰዎች በሙያዊ ሥነምግባር እንጂ በፖለቲካ ርዕዮት ዓለም የተሞረዱ መሆናቸው ታሪክ ሊሆኑ እየተቃረበ ይመስላል። የሚዲያ ተቋማት መጡልን እንጂ መጡብን በሚል መብቀላቸውን ለማክሰም በጎሪጥ የሚመለከት ባለሥልጣን የለም። ተወዳዳሪነት እንጂ አቋራጭ እርምጃዎች መጥበብ ጀምረዋል። የመንግሥትን ካዝና በማለብ ዕድሜያቸውን የሚያራዝሙ የግል ሚዲያ ጣቢያዎች ልሳናቸው (ደማቸው) ደርቋል። ሕዝብን ረስቶ የፓርቲን እስትንፋስ እየተከተሉ ማላዘን አሁን ላይ ሳንቲም አለመውለድ ላይ ለመድረስ እየተጠጉ ይመስላል። የሚዲያው ባለቤት ባለሥልጣን፣ ጋዜጠኛው ወፍዘራሽ አለያም የእህት ልጅ፣ ፈቃድ ሰጪው አጎት፣ ሸላሚው የሚስት ወንድም፣ የገንዘብ ምንጭ (ስፖንሰር) መንግሥት፣ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚስት ሆነው በሕዝብ ላብ ጅምላ ንግድ አሁን አይሰራ ይሆናል፤ ይህ በሩ እየጠበበ ነው። ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ስለህጸጻችን ምን ያወሩብን ይሆን? ምን ይናገሩብን ይሆን? እያሉ መርበትበት ታሪክ ሊሆን ተቃርቧል። ይልቁንስ የእኛ ሚዲያዎች አቀንቃኝ እነሱ አስወንጫፊ ሆነው አብረው በመዘመር ላይ ናቸው። ኢትዮጵያ እንዲህ የዓለምን ቀልብ ስባ የታየችበት አጋጣሚ ምናልባትም ከአድዋ ድል ቀጥሎ ሁለተኛው ሳይሆን አይቀርም። የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪዎች፣ የዓለም ጋዜጠኞች መብት ተሟጋቾች፣ አክቲቪስቶችና የዓለም ሚዲዎች በኢትዮጵያ መዲና በቅርቡ ይከትማሉ። እንደከዚህ በፊቱ የክስ አቤቱታ ለማሰማት አይምሰላችሁ።ልምድ ለመቅሰም እንጂ። የለውጡ የአንድ ዓመት ፍሬ የሩብ ምዕተ ዓመት ስብራትን መጠገን ችሏል። ኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙሃንና የመረጃ ነጻነት የዓለም የፕሬስ ቀን የዘንድሮ ተሞሻሪ ናት።ከዚህ በፊት በዘርፉ ደረጃ ደልዳዮች ከነበረችበት 150ኛ ደረጃ በአንድ ዓመት ውስጥ 40 ደረጃዎችን ማሻሻል ችላለች። እሰይ ሀገሬ። በዚህ ብቻ የሚወሰን አይምሰላችሁ። እየተውተረተረ ያለው የሚዲያዎቻችን አቅም መለወጥ ይኖርበታል። ጋዜጠኞቻችን ለሙያው ሥነምግባርና ለእውነት የሚቆሙ ብሎም ለህዝብ ጥቅም የሚፋለሙ ሊሆኑ ይገባል። ከግል ሚዲያ ተቋማት እስከ ሕዝብ ሚዲያዎች በጥቅም ትስስር የግለሰቦችን ሥም ለማጥፋት ዘመቻ ይውላሉ የሚሉ አሉባልታዎች ቢነሱም ከአሉባልታ አይዘሉም። በአጠቃላይ የፕሬስ ነጻነቱን በደስታ ስናከብር በምንጠቀምባቸው ሚዲያዎች በኩል የጥላቻ ንግግርን ከማስተላለፍ ብንቆጠብ ከእኛነታችን የሚቀነስ ነገር ይኖር ይሆን? ሁሉም ነገር ትናንትን ስቦ የእኛ ነገር አጃኢብ እንዳያሰኝ ስጋት አለኝ። ምክንያቱም ‹‹ሲለጉሙን እዳ ሲፈቱንም እዳ፣ ተቻችሎ መኖር አሁን ማንን ጎዳ›› እንዳለችው ሴትዮ እንዳይሆንብን ነዋ።አዲስ ዘመን ሚየዝያ 24/2011ሙሐመድ ሁሴን ", "passage_id": "9c3312e8ae66f77e8b451d5187507a91" }, { "passage": "የሩቅ ጊዜ እውነተኛ ታሪክ ነው።ምን ለብሼ ልሳቅ የሰውየው እውነተኛ ስሙ አይደለም።በነገር አገደም አግራሞት የሚያጭርበት ጉዳይ ሲያገኝ ከት ብሎ እየሳቀ ምን ለብሼ ልሳቅ ስለሚል ነበር አካባቢው መንደርተኛው በሩቅ የሚያውቁትም ጭምር በዚህ ስያሜ የሚጠሩት።መለያው መጠሪያ ስም ሆኖ ጸደቀለት። አዳሩ\nበዚያን ዘመን ይሰሩ ለነበሩ ቤቶች ከአሰሪዎቹ ከባለቤቶቹ ጋር ተዋውሎ ጭቃውን በጭድ እያቦካ በደንብ በተለያየ ቀናት አገላብጦ ፈርመንትድ ሲሆን (ሲበስል) እንበለው የተማገረውን አዲስ ቤት ደህና አድርጎ በጭቃ ይመርገዋል።በኋላም የልስን ስራ ይሰራል።የእኛ ሀገር የቀደመው ዘመን ሲሚንቶአችን መሆኑ ነው።ዛሬም በስፋት ይሰራበታል፡፡ ብዙዎቹ የሀገራችን ቤቶች\nየሕዝቡ የመሳፍንቱና መኳንንቱ ሳይቀር ምሰሶው ቆሞ ወጋግራው ከተዋቀረና ከተገደገደ በኋላ የሣር ክዳን ይደረግለታል።ዙሪያውን የሚለሰነው ምርጥ ብቃት በነበራቸው የሀገራችን ጭቃ አቡኪና ለሳኞች ነው።ስንቱን ከተማ መንደር ሰፈር አብረው እንደቆረቆሩ፤ ስንቱን ቤት እንደሰሩ፤ የሚናገርላቸው የሚጽፍላቸው ጠፍቶ እንጂ ሰዎቹስ ምርጥ ባለሙያዎችና ባለታሪክም ነበሩ። እነ ምን ለብሼ ልሳቅን የመሰሉ ብዙ ሺዎች ፡፡ ምን\nለብሼ ልሳቅን ለየት የሚያደርገው ለየት ያለ ባህርይና አስገራሚም ስለነበረ ይመስለኛል። ግጥም የለውም። መንደርተኛና ሰፈሩ በአለባበሱ ይደመማል። ትልቁም ትንሹም።ሲመጣ ሕጻናት ይከቡታል። ያውካካሉ።ሱሪ 2 ኮት 3 ሸሚዝ 2 ከረባት 4 ሁልጊዜም መነጽሩ ባዶና መስታወት የሌለው፤ በሸሚዞቹ ኪሶች ላይ የሚሰሩና የማይሰሩ ብዙ እስክሪቢቶዎች የሚደረድር ሰው። ጸጉሩ በዘመኑ ፋሽን ኤልቪስ።ዘመኑም የእነ ኤልቪስ የዝነጣ ዘመን ነበር። በጫማ ላይ ጫማ ስለማይደረግ እንጂ እሱንም ለማድረግ አይመለስም ነበር። በዚያን ዘመን\nእንዲያ ለብሶ ከገጠር መንደር ብዙም በማትለየው የአዲስ አበባ ጥርጊያ መንገዶች ላይ ሽር ብትን እያለ በቄንጥ ሲራመድ የሁሉንም ቀልብ ይስባል።‹‹ኧረ ሳቄ መጣ›› ያሠኛል።እሱ ማንንም ከቁብ አይቆጥርም። ይህ ሰው ማነው ለሚለው ማንም መልስ አላገኘለትም።ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ ወይንም ለመጠላት ወይ ለመወደድ እንዲሉ ሆነና። አዕምሮው ልክ\nአይደለም ባዮች ብዙ ነበሩ።እነሱ እንጂ እሱማ ልክ ነኝ ብሎ ነው የሚኖረው፤ የሚሰራው።የተዋዋለውን ስራ ጭቃ ማቡካቱንና መለሰኑን አሳምሮ ይሰራል።ስራ ሲሰራ ይዘፍናል።ሰው ሰማ አልሰማ ደንታ የለውም።ዘፈኑ ሁሌም ‹‹አንቺ ልጅ›› ነው። ‹‹አሀሀሀ አንቺ ልጅ፡፡›› ምናልባት ምናልባት ይሄ ስለሚሰራው ስራ እንጂ ስለማንነቱ ብዙ የምይታወቀው ሰው ከጀርባው ምን ታሪክ ተሸክሞ ይሆን የሚለው ጥያቄ የብዙዎች ነበር። የት ተወለደ፤ አደገ፤ ተማረ፤ ቤተሰቡስ የት ነበር? ምንም ፍንጭ የለም።ብዙ ሰዎች ለማወቅ ጥረዋል።ሲጠይቁት መልሱ አጭር ነው ምን ለብሼ ልሳቅ ይልና ይንከተከታል።ምናልባት በሰዎቹ በመገረም አሊያም ዓለምን በመናቅ ሊሆን ይችላል።እኛ ያላየነው የማናውቀው የለም በሚል ውስጣዊ ምፀት ይሆናል ከት ብሎ የሚስቀው። አዛውንቶቹ ወጣቱ ሁሉም ሰው ያውቀዋል። አብዝተው ይገረሙበታል። በማይታወቀው ማንነቱ። በዚህ ሰው ማንነት ውስጥ ሌላ የተሰወረ የተደበቀ ማንነት አለ።ግን ለምን እንዲያ ሆነ ቢባል የመልሱ ባለቤት እሱና እሱ ብቻ ነው። ብዙ ሰዎች ደሞ ‹‹ምን ለብሼ ልሳቅ ይላል እንዴ፤ ይሄን ሁሉ የሀገር ልብስ ደራርቦ እየለበሰ›› ይሉና ይሽኮመኮማሉ። የሚገርመው የስራ ልብስ አለው።ለብሶ የሚመጣው ንጹህ ልብሶች ናቸው። ስራውን ሲጨርስ ተጣጥቦ ሲያበቃ ያንኑ ደራርቦ ይለብስና ሽክ ይላል። ‹‹አሀሀሀሀሀሀ አይ ምን ለብሼ ልሳቅ።›› ዛሬ ከስንትና ስንት ዓመታት በኋላ ታወሰኝ በል፡፡ ‹‹በጤናው አይደለም›› ቢሉም ‹‹እኔ እብድ አይደለሁም፤ እናንተ ናችሁ እብድ›› ይላል።‹‹ጤነኛ ነኝ›› የሚል ስንት እብድ እንዳለ መንፈሱ ሹክ የሚለው ይመስላል።ልብሱ፤ ከረባቱ፤ ሸሚዙ ኮቶቹ ይቀያየራሉ።ወይ ሰዎች ይሰጡታል ወይ የራሱ የሆነ የተከማቸ አለው።ለስራ ተዋውሎ ሲመጣ እንጂ መኖሪያው አይታወቅም የምን ለብሼ ልሳቅ።እንደሌሎቹ የእሱን አይነት ስራ እንደሚሰሩት ሰዎች ጠላ፤ ጠጅ፤ አረቄ፤ ቤት አይታይም።ቢሰጡትም አይጠጣም፡፡ አንዳንድ ሰዎች ግን እንደዛው ለብሶ አልፎ አልፎ ግሮሰሪ እንደሚገባ በሥርዓቱ ቁጭ ብሎ አዞ የተወሰነ አልኮል እንደሚጠጣ ይናገራሉ።አንድ ጊዜ ቁምጣ ሱሪውን አድርጎ በባዶ እግሩ ጭቃውን ሲለውስ ከቤታቸው ውሀ ልክ ላይ ቁጭ ብለው ሁለት የተማሩ ወጣቶች ምስጢራቸውን በእንግሊዝኛ ቋንቋ ያወራሉ። ማንም ሰው አይሰማንም ነው ነገሩ።መቼም ምንም ቢያስቡ ሊጠረጥሩ አይችሉም። እሱ ስራውን ይሰራል። ሰማ፤ ሰማ ፤ሰማና መጨረሻ ስራውን ከውኖ ተጣጥቦ ሲያበቃ ያንኑ አስገራሚ ልብሱን ከረባቱን ባዶ መነጽሩን አድርጎ ለማረፍ በሚመስል መልኩ ተማሪዎቹ አጠገብ ቁጭ አለ።እየሳቁ ምን ለብሼ ልሳቅ ታዲያስ አሉት።በተለመደው ሳቁ አውካካ።አይ እናንተ አሁን ምስጢራችሁ እንዳይሰማ ነው አይደል በወፍ ቋንቋ የምታወሩት አላቸው።‹‹ልክ ነህ ማንም እንደማይሰማ እርግጠኞች ነን›› አሉት።የተነጋገሩት ስለአብዮትና ለውጥ ስለንጉሱና ሥርዓታቸው የእኛስ በምን መልኩ ነው መሄድ ያለበት የሚል ነበር፡፡ የወጣቶቹን አፍ ያዘጋ ድንጋጤ ውስጥ የከተተ ድንገተኛ ምትሀት የመሰለ ጉዳይ ተከሰተ።በጠራ እንግሊዝኛ የተወያዩበትን ዘርዝሮ ጥያቄአቸውን በመለሰ መልኩ ነገራቸው ጭቃ አቡኪውና ለሳኙ ምን ለብሼ ልሳቅ።ደነገጡ።ማመን ተሳናቸው።እሱ ነው ሌላ ሰው እስኪሉ ድረስ።መጽሐፍቶችን በስም እየጠራ ይሄን ይሄን አንብቡ ሲላቸው ድንጋጤአቸው ሽቅብ ጎነ።ግን አላቸው ለማንም አትናገሩ ቃል ግቡልኝ። እኔ በዚህ መልኩ የምሰራው የምኖረው የእራሴን ኑሮ ነው።ደስተኛ ነኝ።ዓለምን ንቄ ሰውንም እርቄ ነው ብሎ በረዥሙ ተነፈሰ። እንዴት ብዙ የተማረ ሰው በሌለበት ሀገር የዚህ እውቀት ባለቤት አንዱ ጋ ተቀጥሮ መኖር\nሲችል ይሄንን አይነት ኑሮ ለመኖር መረጠ በሚል ወጣቶቹ በእጅጉ አዘኑ።ተደናገጡ።እሱ ግን አላቸው።ለእኔ አታስቡ አትጨነቁም።በጉልበቴ ሰርቼ እኖራለሁ።ስራ አከብራለሁ።የሰው እጅ አላይም።ልመና አልወድም።ዓለምን ስትረሳት ትረሳሀለች። ሁሉን ከረሳህ በትላንት ውስጥ ካልቆዘምክ ትኖራለህ በሉ ቻው አለና ተነስቶ ግቢውን ጥሎ ወጣ።ጉድ ጉድ ሲሉ ውለው አደሩ።ምን ለብሼ ልሳቅ ማነው።ከአሁኑ ትንሽ መገለጥ በቀር ስለዚህ ሰው ማንም ምንም አያውቅም። ሌላ ሰፈር ሄዶ ያንኑ ጭቃ ማቡካት ሲሰራ እንዲሁ የ11ኛ\nክፍል ተማሪዎች በራፋቸው ላይ ቁጭ ብለው በተሰጣቸው የታሪክ ትምህርት የቤት ስራ ላይ በእንግሊዝኛ እያወሩ ይከራከራሉ።የያኔ ተማሪ ብርቱና የቀለም ቀንድ ነበር።ለወረቀት ሳይሆን ለእውቀት የሚተጋ።ለእውቀት የሚታትር ንብ።አንባቢ፤ተከራካሪ፤ሞጋች።ብርቱ የቀለም ደቀመዝሙርና ካህን።መምህሮቹም በእውቀት የላቁ የረበቡ።እሱ ጭቃውን ጭድ እየነሰነሰ ይለውሳል።ተማሪዎቹ በጥያቄው መልስ ላይ አልተስማሙም።ተነታረኩ።አጠገባቸው ወትሮም የሚያውቁት የሚስቁበት ምን ለብሼ ልሳቅ ብቻ ነበር።ሌላ ሰው የለም። አከራካሪው ጥያቄ በፈረንሳይ አብዮት ላይ ያተኮረ ነው።ምን ለብሼ ልሳቅ አካፋውን ይዞ ጭቃውን እያገላበጠ ይሰማቸዋል። አላስቻለውም። ዝምታውን በድንገት ሰበረና ከት ብሎ ሳቀ።አንዱ ተማሪ ይሄ እብድ ምን ይስቃል ሲል አዎን እብድ ነኝ። ዘመን ያሳበደኝ በራሴ ዓለም የምኖር እብድ አለው። መልሱ ልጁን አስደነገጠው። ምን ለብሼ ልሳቅ ለጠቅ አደረገና በጠራ እንግሊዝኛ ምንድነው የምትጨቃጨቁት ሲላቸው በተቀመጡበት ክው ብለው ቀሩ። እሱ ነው የተናገረው ሌላ ሰው በሚል ጥርጣሬ።ደገመላቸው። የተከራከሩበትን ነጥብ በነጥብ እያነሳ ከመነሻው እስከ መድረሻው አካፋውን ይዞ ቆም እንዳለ አነበነበላቸው።መልሱ ይሄ ነው አለና በረዥሙ ተነፈሰ፡፡ ተማሪዎቹ አብዝተው ተደመሙ።ግን አላቸው ስለእኔ ለማንም አታውሩ ።ስለእኔም አትጨነቁ።አትመራመሩ።እኔ በራሴ የሕይወት መንገድ ደስተኛ ነኝ። ከማንም ምንም እርዳታ አልፈልግም። እስካለሁ በጉልበቴ ሰርቼ እኖራለሁ። ስራዬን አከብራለሁ።እናንተ ግን በርትታችሁ ተማሩ።አንብቡ። ለወረቀት ሳይሆን ለእውቀት ትጉ አላቸው። በተቀመጡበት በድንጋጤ ተመቱ። ከጭቃው ውስጥ ወጥቶ ተጣጥቦ ልብሱን በተለመደው ሁኔታ ለባብሶ ቻው ብሎአቸው መንገዱን ቀጠለ። ግዜው የ1966 አብዮት ዋዜማ\nነበር።ምን ለብሼ ልሳቅ ማነው? እውነተኛ ስሙና ታሪኩስ? ምን ገጥሞት ምንስ ሆኖ ይሄን የሕይወት መንገድ መረጠ? አዲስ ዘመን ሀምሌ 18/2011", "passage_id": "304fd91821603631b9bad2d841cc81b3" }, { "passage": "የ2009  ዓም  የአዲስ  ዘመን  መለወጫ  በዓል በሰላም፣ በደስታና በድምቀት እየተከበረ መዋሉን  የተለያዩ   የአዲስ አበባ  ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ ።   \nዋኢማ ተዘዋውሮ ያነጋገራቸው የተለያዩ የአዲስ አበበ ከተማ ነዋሪዎች እንደገለጹት የ2009 የአዲስ  ዘመንን  በሰላም ፣ በደስታና በፍቅር  ማክበራቸውን ።\nአዲሱ ዘመን ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የደስታ፣ የሰላም፣ የፍቅርና የመከባባር   እንዲሆንለት መልካም  ምኞታቸውን ገልጸዋል ።  \nበከተማዋ  የካራ ቆሬ አካባቢ ነዋሪ የሆኑት አቶ ወይሳ ጥርአይሎ እንደገለጹት ከዋዜማው አንስቶ  የአዲስ ዘመን  መለወጫ በዓሉን ለማክበር ዝግጅት ሲያደርጉ መቆየታቸውንና በሰላም ማክበራቸውን ገልጸው አዲሱ ዓመት  ለኢትዮጵያና ህዝቦቿ የሰላም ፣ የደስታና የዕድገት እንዲሆን ተመኝተዋል።  \nወጣት ዳናዊት  ለምለም በበኩሏ  አዲሱን ዓመት ካለፉት ዓመታት በህይወቷ ላይ የተሻለ ለውጥ  በማምጣት የምትጥርበት መሆኑን ጠቁሟ   ወጣቶች  እራሳቸውን  በመለወጥ  ለአገር ዕድገት  አስተዋጽኦ የሚያበረክቱበት ዘመን እንዲሆን ተመኝታለች ።\nበአዲስ አበባ ከተማ የኮልፌ ቀራንዮ አካባቢ  ነዋሪ  የሆነው ከበደ እሸቱ የዘንድሮ የአዲስ ዓመት በዓል በአዲስ መንፈስ  እንደተቀበለው በመግለጽ ሁሉም  ዜጋ  በአዲሱ ዓመት ለሰላም ፣ ለዴሞክራሲና ለልማት  የሚቆምበት  እንዲሆን ተመኝቷል ።\nሌላዋ  የአዲስ አበባ ከተማ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ነዋሪ  የሆነቺው  ዓለም  ተሰማ   አዲሱን  ዓመት  የምትቀበለው   ከባለፉት ዓመታት  በተሻለ  መልኩ ኑሮዋን  የማሻሻል  የያዘችውን ዕቅድ ለማሳካት ከልብ በመነሳት ነው ብላለች ።   \n   ", "passage_id": "6d19e2aa379bbdaeddf54c58376df9e3" } ]
524ddf103c1b646d02bab34958c46ee4
e3564bee4dc397f060bc0d8c4a9a3ed4
የአረንጓዴ ጎርፍ በጎ አድራጎት አምባሳደሮች ተሰየሙ
ቦጋለ አበበየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽን ከኢትዮጵያ አረንጓዴ ጎርፍ የአትሌቲክስ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር‹‹የገና በዓልን ከአንጋፋ አትሌቶች ጋር እናሳልፍ›› በሚል ትናንት በኢትዮጵያ ሆቴል በተዘጋጀው የእውቅናና የሽልማት መድረክ የበጎ አድራጎት ድርጅቱ ሁለት አምባሳደሮች ተሰይመዋል፡፡ በዚህም ከሴት ፈር ቀዳጇ የአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር የቀድሞ ኮከብ አትሌት ኮማንደር ቁጥሬ ዱለቻ የተሰየመች ሲሆን በወንድ ፋና ወጊው የኦሊምፒክ የሦስት ሺ ሜትር መሰናክል የነሐሴ ሜዳሊያ ባለቤትና የርቀቱ አሰልጣኝ ሻምበል እሸቱ ቱራ የዕውቅና አምባሳደርነት የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።አምባሳደሮቹ በተሰየሙበት መርሃግብር በህይወት ዘመናቸው ለኢትዮጵያ ስፖርት የላቀ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ግለሰቦች የዕውቅናና የምስጋና ካባ እንዲሁም የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል፡፡ አንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ሐኪም ዶክተር አያሌው ጥላሁን እንዲሁም አንጋፋው የስፖርት ጋዜጠኛ ሰለሞን ገብረእግዚያብሔር የዕውቅናና የምስክር ወረቀት ከተቀበሉ በኋላ በሞሀ ለስላሳ መጠጦች እንዱስትሪ አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጌታቸው ቢርቦ የክብር ካባ ተጠልቆላቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ጎርፍ አትሌቲክስ የበጎ አድራጎት ድርጅት መስራችና ዋና ስራ አስኪያጅ አትሌት መልካም ተገኝ፣ ‹‹መረዳዳት በህይወት›› በሚል ሀሳብ ለአገራቸው የሰሩ፣ የለፉ ፣ የደከሙና ለአገር ክብር የተጉ አትሌቶችንና ቀጣይ ተተኪዎችን በማንኛውም ማህበራዊ ህይወታቸው ለመታደግ በጎ አድራጎት ድርጅቱ መመስረቱን ጠቅሰው ለዚህ የተቀደሰ አላማ ሁሉም አካላት ትብብር እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽነር በላይ ደጀን በበኩላቸው ‹‹መረዳዳት በህይወት›› የሚለው መሪ ቃል በጎ አድራጎት ድርጅቱን እንደሚወክል በመግለፅ፣ ለአገራቸው ክብር ፣ ህዝብና ባንዲራ የለፉ አንጋፋ አትሌቶችና ጋዜጠኞች እንዲሁም ሌሎች ባለሙያዎች በዚህ ደረጃ ዕውቅና ማግኘታቸው ተገቢ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡ በቀጣይ በጎ አድራጎት ድርጅቱ የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን በጋራ እንደሚሰሩም ቃል ገብተዋል፡፡ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ዱቤ ጅሎ በበኩላቸው ይህን በጎ አላማ እውን ላደረጉና መርሃግብሩን ላዘጋጁና ለዚህ ያበቁ የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን አመራሮችን አመስግነዋል። በርካታ አንጋፋ አትሌቶች በመርሃግብሩ ታድመውም የእውቅናና የምስክር ወረቀት ተቀብለዋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 28/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=39010
[ { "passage": "የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስቴር የአንደኛ ዓመት መታሰቢያ አስመልክቶ በተካሄደው ችግኝ ተከላ ላይ የንግድ ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋማት የሆኑት የኢትዮጵያ እህል ንግድ፣ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለሥልጣንና የንግድ አሠራርና ሸማቾች ጥበቃ ባለሥልጣን ተካፍለውበታል፡፡የንግድ ሚኒስትር አቶ ከበደ ጫኔ ለዋልታ እንደተናገሩት ተከላው በአንድ በኩል የሃገሪቱን ልምላሜ የሚያመጣ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ የመለስ ራዕይን በሁሉም ሰራተኛ ውስጥ በማስረጽ የእድገትና ተራንስፎርሜሽን እቅዱን ለማሳካት በቁርጠኝነት ለመንቀሳቀስ አጋጣሚ ይፈጥራል፡፡ተከላው ለዚሁ ዓላማ ሲባል በጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በተመረጠው የውንጌት ቀለበት መንገድ አደባባይ ላይ በሚገኙ የአረንጓዴ ስፍራዎች ላይ ሲሆን በእለቱ በ350 ሰዎች ተሳትፎ እስከ 1 ሺህ 100 ችግኞች ተተክለዋል፡፡ ", "passage_id": "d08c3d48c61da21fbd75ee90af19bead" }, { "passage": "አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 14 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የጤና ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት  ጋር  በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ- ግብር በአገር አቀፍ ደረጃ 6 ነጥብ 5 ሚሊዮን ችግኞችን እንደሚተክል አስታወቀ።በዚህም ሚኒስቴሩ ዛሬ በሥሩ ያሉ ተጠሪ ተቋማት ሠራተኞች ጋር በመሆን በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ 5ሺህ ችግኞችን በመትከል መርሃ ግብሩን  አስጀምሯል።መርሃ ግብሩም “ከኮሮና ቫይረስ ራሳችንን እየተከላከልን አረንጓዴ አሻራችንን እናሳርፍ” በሚል መሪ ሃሳብ እንደሚከናወን ነው የተገለጸው።በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ  ላይ የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያን ጨምሮ የስራ ሃላፊዎች እና ሰራተኞች በመሳተፍ አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል፡፡የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በዚህ ወቅት÷መርሃ-ግብሩ አካበቢን ከመጠበቅ በተጓዳኝ ለማህበረሰብ ጤና ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል።ችግኞች በሚተከሉበት ወቅት የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚወሰዱ ጥንቃቄዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም ዶክተር ሊያ ታደሰ  ጥሪ አቅርበዋል።በመርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፉ አመራሮች እና ሰራተኞች  የሚተከሉ ችግኞች የአየር ንብረትን በመጠበቅ  ለዜጎች ጤና  ያላቸው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡በመለሰ ምትኩ#FBCየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።", "passage_id": "2c5cd5aac652a11c6f96537a7d7129a0" }, { "passage": "ዓምና በተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ በአንድ ጀምበር ከ350 ሚሊዮን እንዲሁም በክረምቱ መርሃግብር ከአራት ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል በሕንድ ተይዞ የነበረውን የዓለም ክብረ ወሰን ኢትዮጵያ መስበሯ ይታወሳል። ይህንኑ ተግባር በዚህ ዓመት በተሻለ መነቃቃት እና ነገን ታሳቢ ባደረገ ጥንቃቄ ለመድገምም ቅድመ ዝግጅቶች ተጠናቀው እነሆ በዛሬው እለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በአገር አቀፍ ደረጃ የሚከናወነውን የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር በደቡብ ክልል ያስጀምራሉ። በዚህ ዓመት በመላው አገሪቱ አምስት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል በችግኝ ዝግጅቱም በአስተሳሰብም በተግባርም በቂ ቅድመ ዝግጅት መደረጉ ተነግሯል።በዚህም የአገሪቷን አረንጓዴ ሽፋን ከማሳደግ ባለፈ የአርሶ አደሩን ህይወት መለወጥ የሚችሉ የፍራፍሬ ዛፎች በስፋት መዘጋጀታቸውን የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ኡመር ሁሴን ገልጸዋል። ከአምስት ቢሊዮኑ ችግኞች 60 በመቶ የሚሆኑት ለምግብነት ሊውሉ የሚችሉ የአትክልትና የፍራፍሬ ተክሎች መሆናቸውን ያስታወቁት ሚኒስትሩ፤ ከቀሪው 40 በመቶ ውስጥ ደግሞ ትልቁ ድርሻ ያላቸው የአገር በቀል ተክሎች መሆናቸውንም ጠቁመዋል። ለዚህም በአገር አቀፍ ደረጃ ከተዘጋጁት 24ሺ የችግኝ ጣቢያዎች በትግራይ ክልል አንድ በመቶ፤ በአማራ ክልል 32 በመቶ፣ በኦሮሚያ ክልል 42 በመቶ እንዲሁም በደቡብ ክልል 25 በመቶ እንደሚሸፍን ተናግረዋል። በችግኝ ተከላ ወቅት የኮቪድ 19 ተጽእኖ ተግዳሮት ሊሆን እንደሚችል የጠቆሙት አቶ ኡመር፤ ሂደቱም ችግኝ በመጫንና በማውረድ፤ አካላዊ ርቀትን በመጠበቅ ራስን የመጠበቂያ መሳሪያዎችን በማቅረብና በብዛት ወጣቶችን ተሳታፊ በማድረግ እንደሚካሄድ ገልጸዋል። አቶ ኡመር፤ ችግኝ ለፈጣን ልማት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት፤ የህዝቡን ኑሮና ለማሻሻል እንዲሁም አገርን ለማበልጸግ እንደሚረዳና ከዛሬው የአረንጓዴ አሻራ ይፋዊ የችግኝ ተከላ ዕለት ጀምሮ ተመሳሳይ የችግኝ ተከላ ዘመቻዎች እንደሚካሄዱና ለዚህም በቂ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል። የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ በበኩላቸው ችግኞቹ አገሪቷን በግብርና ኢኮኖሚ መጥቀም የሚችሉ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ እያንዳንዱ ሳይት ላይ ምን ያህል አለ የሚለው በቴክኖሎጂ በመታገዙ ለመንከባከብ እንደሚያግዝና ይህም አምስት ቢሊዮን የመድረሱን ዓላማ ለማሳካት ውጤታማ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።ህዝቡ በየዓመቱ የሚያከናውነው የችግኝ ተከላ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ እንዳይተላለፍ በሚያግዝ ስልት መንግስት ተገቢውን ዝግጅት ማድረጉን የጠቆሙት ሚኒስትሩ፤ ከይፋዊው የተከላ እለት ጀምሮ እስከ ሀምሌ ወር መጨረሻ ተግባራዊ ክንዋኔው እንደሚቀጥል ተናግረዋል። በመሆኑም ዝናብን ሳይጠብቁ በመስኖ በማልማት ምርታማነትን ማስፋፋትና አገሪቷ ወደ ኋላ በቀረው ግብርናዋ በዘመናዊ መንገድ ታግዛ ውጤታማ እንድትሆን ማድረግ እንደሚገባም ሚኒስትሩ ገልጸዋል። “ችግኝ ከተፋሰስ አጠባበቅ አኳያ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። አገር በቀል የሆኑ የዛፍ አይነቶች ቢተከሉ ምርት ሊሰጡ የሚችሉና አፈሩን መንከባከብን የሚችሉ ስላሉ የዝናብ መጠንን ለመጨመር ያስችላል። ይህም የውሃ በጀት እንዲያድግ ያደርጋል። ከዚህም ባሻገር ደለል በወንዞች ውስጥ አልፎ ወንዞች እንዳይሞሉ ይከላከላል። የተሻለ የምንጭና የከርሰ ምድር ክምችት እንዲኖር ያግዛል። የአካባቢንና የዓለም ሙቀትን ለመቀነስም ያስችላሉ” በማለት ችግኝ ከዛፍነቱ ባሻገር ብዙ ሚና እንዳለው አብራርተዋል። የአረንጓዴ አሻራ ብሄራዊ ኮሚቴ አባል አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ፤ በችግኝ ማፊያ ማዕከላት የሚታዩት ተግባራት ጥሩ ደረጃ ላይ መሆናቸውንና ከዚህም በላይ ብዙ ሥራ እንደሚጠበቅ፤ ጅማሮው ያማረ እንደሆነ ሁሉ በዘላቂነት የሚከናወነው ተግባርም እንዲሁ ታሳቢ መደረግ እንዳለበት ተናግሯል። ምርት በተገቢው ሁኔታ ለማግኘት በባለቤትነት እንክብካቤ ማድረግ እንደሚገባና ምርቱን ለተፈለገው ዓላማ ለማዋል ከፍተኛ ጥረት እንደሚያስፈልግ አመላክቷል። የተራቆቱ አካባቢዎችን በማልማት አዳዲስ ምርቶችን የማስተዋወቅ ሥራው ቀጣይነት ያለው እንዲሆን የአረንጓዴ አሻራ ብሄራዊ ኮሚቴ አባላት በሚገባ መስራት እንዳለባቸው አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ተናግሯል። ድምጻዊ ስለሺ ደምሴ (ጋሽ አበራ ሞላ) “በባለሙያዎች አማካኝነት የተደረገው ችግኝ የማፍላት ሥራው በመስክ ጉብኝት መልካም ነገሮችን አይተናል። በተለይ የሚተከሉ ችግኞች በዓይነት መብዛታቸው ደግሞ የማህበረሰቡን የአኗኗር ባህሪ መሠረት ያደረጉ በመሆናቸው የአካባቢን ስነምህዳር ከመጠበቅ አልፈው በፋይናንስ በኩል ከፍተኛ ጠቀሜታ ይሰጣሉ። ለመትከል የታሰበውን ቁጥር ለማሳካት ተክሎች ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆኑ በአእምሮ ውስጥ ቀድሞ መትከል ይገባል’’ ይላሉ። እርሳቸውን ጨምሮ ያሉ የኮሚቴ አባላት እንዲሁም ታዋቂ ግለሰቦች ይህንን ግንዛቤ ለህብረተሰቡ ማድረስ እንዳለባቸው ድምጻዊ ስለሺ ደምሴ ተናግሯል። በተከላው ላይ የሚደረገው ዘመቻ ኃላፊነት ወስዶ በመንከባከብም ሊቀጥል እንደሚገባ ያመላክታሉ። አዲስ ዘመን ግንቦት 28/2012 አዲሱ ገረመው", "passage_id": "b2464022e5e0160a67da350cc00c734f" }, { "passage": "ለኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ውጥኖች ስኬት የደን ሽፋን መጨመርና የተራሮች ወደ አረንጓዴነት መለወጥ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው የአካባቢ የደንና የአየር ንብረት ለውጥ ሚኒስቴር አስታወቀ።የሚኒስቴሩ ሠራተኞች የዛሬውን \"የአረንጓዴ ልማት ቀን\" በአዲስ አበባ-አዳማ የፍጥነት መንገድ ላይ የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ አክብረዋል።ከአዲሱ ዓመት መቀበያ ዝግጅቶች አንዱ የሆነው ዕለቱ \"የአረንጓዴ ልማት ጠበቆች ነን\" በሚል መሪ ሃሳብ ነው የተከበረው።ሚኒስትሩ ዶክተር ገመዶ ዳሌ የአረንጓዴ ልማቱን ቀጣይነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።በዓሉ በየክልሉና በየተቋማቱ የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብና አካባቢን በማፅዳት እየተከበረ መሆኑን ገልፀዋል።የችግኝ እንክብካቤና የአካባቢ ፅዳት ስራው ዓመቱን ሙሉ ሊሰራ እንደሚገባም አሳስበዋል።በተጨማሪም የደኖችን ቁጥር በመጨመር ኢትዮጵያ ላላት የአረንጓዴ ልማት ጥብቅናና ታዳሽ ኢኮኖሚ ስኬት አስተዋፅኦ ማድረግ ይገባል ብለዋል።የደን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ከበደ ይማም በበኩላቸው ደኖችን ማልማት ወደ ታቀደው የኢኮኖሚ አማራጭ ለመሰማራት ቅድሚያ የሚሰጠው ስራ መሆኑን አስረድተዋል።ደኖች ሲለሙና የደን ሽፋኑ በተራሮች አካባቢ ሲበዛ የአፈር መሸርሸርን ከመከላከል ባለፈ ውሃ በብዛት እንዲታቆር ያደርጋል ብለዋል።ይህም ለእርሻ ልማትና አገሪቱ እንደ ትልቅ አማራጭ እየተጠቀመችበት ያለውን በውሃ የሚመነጭ ኃይል ለመፍጠር ያስችላታል።የኃይል አቅርቦቱ ደግሞ ለተጀመረው የኢንዱስትሪ ልማት አቅርቦት ይሆናል ሲሉ አስረድተዋል።የደን ልማቱ ከኢትዮጵያ አልፎ ለጎረቤት አገራት የውሃ ፍላጎትና ተስማሚ የአየር ንብረት ምክንያት በመሆኑ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ እንደሆነም ነው የተናገሩት።የኢትዮጵያ የፍጥነት መንገዶች ኢንተርፕራይዝ ስራ አስኪያጅ አቶ ሙስጠፋ ከድርም የአገሪቱን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ለማሳካት ኢንተፕራይዙ የበኩሉን ድርሻ በመወጣት ላይ መሆኑን ገልፀዋል።ኢንተርፕራይዙ በቀን በአማካይ ከ21 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችን የሚያስተናግድ ሲሆን ከእነሱ የሚወጣውን የጭስ ልቀት ለማካካስ ዘንድሮ 21 ሺህ ችግኞችን ተክሎ በመንከባከብ ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።ኢትዮጵያ በ2025 አገራዊ የደን ሽፋኗን 20 በመቶ ለማድረስ እየሰራች ትገኛለች-ኢዜአ)። ", "passage_id": "4efbd148f29894ee6c5d2b11c326aed8" }, { "passage": "ሰኞ ሐምሌ 22 ቀን 2011 ዓ.ም. በመላ አገሪቱ 200 ሚሊዮን ችግኞች የሚተከሉበት መርሐ ግብር ተይዟል፡፡ ‹‹አገራዊ የአረንጓዴ ልማት ድርጊት መርሐ ግብር›› በመባል በሚታወቀው አረንጓዴ አሻራ የማኖር ሥነ ሥርዓት፣ በችግኝ ተከላ የዓለም ክብረ ወሰን ለመስበር ዕቅድም ተይዟል፡፡ በመላ አገሪቱ በአጠቃላይ አራት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታስቦ እስካሁን 2.7 ቢሊዮን ችግኞች መተከላቸውን የውኃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር በቅርቡ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡፡ ለማኅበራዊ ምርታማነት፣ ተጋላጭነትን ለመቋቋም፣ ለአየር ንብረት ተፅዕኖ መቀነስና መላመድ፣ ጤናን ለማሻሻል፣ ለዱር እንስሳት ከለላ፣ ለብዝኃ ሕይወት ከለላ፣ ለውኃ ማንፃትና ከለላ፣ እንዲሁም ለኢኮኖሚ ጠቀሜታ (ደንና ግብርና) ሲባል በሚከናወነው መርሐ ግብር በመላ አገሪቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ይሳተፉበታል ተብሏል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ለችግኝ ተከላው 2.8 ሚሊዮን ጉድጓዶች መዘጋጀታቸው ተገልጿል፡፡ ነዋሪዎች በ116 ወረዳዎች በችግኝ ተከላው የሚሳተፉ ሲሆን፣ ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡም የመትከያ ቦታ መዘጋጀቱ ታውቋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በተለያዩ ጊዜያት ችግኞችን ሲተክሉ መሰንበታቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ከተለያዩ የውጭ አገር እንግዶች ጋርም ሲተክሉ ነበር፡፡ ሰኞ ሐምሌ 22 ቀን 2011 ዓ.ም. ደግሞ በደቡብ ክልል በወላይታ ዞን በሶዶ ከተማ ዳሞት  ተራራ ላይ፣ ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ችግኝ እንደሚተክሉ ታውቋል፡፡ በምሥሉ ላይ የሚታየው የዳሞት ተራራ ሲሆን፣ ችግኞቹ ደግሞ በሶዶ የደንና ዕፅዋት ልማት ፕሮጀክት የፈሉ ናቸው፡፡", "passage_id": "c7d304018c47a16935952018ba248631" } ]
841356db06403e817a5278c53afc2643
01c3a5732d6f5bdd77714d572c7bdf9f
የሊጉ በቢዝነስ ሞዴል መመራት አበረታች ጅምር መሆኑ ተገለጸ
ብርሃን ፈይሳአዲስ አበባ፡- የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ በሼር ካምፓኒ እንዲተዳደር መደረጉና የቴሌቪዥን ሽፋን ማግኘቱ ለሌሎች ስፖርቶችም አበረታች ጅምር መሆኑ ተገለጸ። በብሄራዊ ስፖርት ምክር ቤት የ2013ዓም የስፖርት ዘርፍ አፈጻጸም ሰነድ ላይ እንደተመለከተው፤የሃገሪቷ ስፖርት በቢዝነስ ሞዴል እንዲመራ በማድረግ ረገድ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሪሚየር ሊጉን (ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ) በሼር ካምፓኒ እንዲመራ ማድረጉ መልካም ጅማሬ ነው። በአጭር ጊዜ ውስጥ የተደራጀው ካምፓኒው ውድድሩን የቴሌቪዥን መብት እንዲያገኝ እና የውድድር ስያሜውንም መሸጥ መቻሉ በስፖርት ላይ ትልቅ ተስፋን እና መነቃቃት ፈጥሯል። የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር፤ ሃገር አቀፍ የስፖርት ማህበራት ስፖርቱን በቢዝነስ ሞዴል ከመምራት አንጻር ሰፊ ስራ መሰራቱን ጠቅሰው፣ ለእዚህም በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሊግ ካምፓኒው መቋቋም ተጠቃሽ መሆኑን አመላክተዋል። የውድድሩ መሸጥ በተለይ ክለቦች በገቢ ራሳቸውን እንዲችሉ የሚያደርግ፣ ለተጫዋቾችም መልካም ዕድል የፈጠረና የሃገርን ገጽታ ለመገንባት ትልቅ አስተዋጽኦ ያደረገ ነው ነው ያሉት ኮሚሽነሩ፣በተመሳሳይ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብም ወደ አክሲዮን የተለወጠበት ሁኔታ ሌሎች ክለቦች ልምድ የሚወስዱበት ነው ብለዋል። ይህም በቢዝነስ ሞዴል ከመመራት አንጻር የተጀመሩ ስራዎች እንዳሉ ማሳያ መሆኑንም ጠቅሰዋል።የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው በበኩላቸው፤ በዓመቱ (2012ዓም) የሊግ ኮሚቴ በመፍጠር እግር ኳስ የስፖርታዊ ጨዋነትና የስፖርት መርህን የሚያከብር ዘርፍ እንዲሆን መደረጉ መልካም መሆኑን ጠቁመዋል። የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ራሱን መቻልም ለሌሎች እንዴት ራስን በገቢ መቻል ይቻላል የሚለውን ያሳየ መሆኑን ተናግረው፣ ጥሩ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ጠቋሚ ነው ብለዋል። ይህንንም አጠናክሮና ተባብሮ ማስኬድ ከተቻለ በስፖርቱ የሚነሱ ጥያቄዎችና ችግሮች ይቀረፋሉ ሲሉም ተስፋቸውን አንጸባርቀዋል። ብሔራዊው የስፖርት ሪፎርም ክለቦችና የስፖርት ማህበራት በገቢ ራሳቸውን ችለው ከመንግስት ድጎማ እንዲላቀቁ እንዲሁም ሃብት እንዲያፈሩ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ያመላክታል። እንደ ኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን የአፈጻጸም ሪፖርት፤ መንግስት እስካሁን ከክልል እስከ ፌዴራል ባለው ደረጃ 163 ሚሊዮን 177ሺ 165 ብር ድጋፍ አድርጓል። ይህንን ለመቅረፍም ሃገር አቀፍ የስፖርት ማህበራት ያሉበት ሁኔታና ቁመና ለማወቅ ቅኝት በማድረግ ያሉበትን ደረጃ ለመለየት ጥረት ተደርጓል። የስፖርት ማህበራት ስፖርቱን በቢዝነስ ሞዴል በመምራት ከድጎማ የሚላቀቁበትና የራሳቸውን አቅም በማጎልበት የ10 ዓመቱን የስፖርት ልማት እቅድ ግቦች የሚያሳኩበትን ቁመና መፍጠርም በተያዘው ዓመት የኮሚሽኑ እቅድ መሆኑም ተጠቁሟል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 28/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=39011
[ { "passage": "የ2011 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከወትሮው በተለየ አጨቃጫቂ ሁኔታ፣ በተደጋጋሚ መቆራረጥ እንዲሁም በአሰልቺ የውድድር መርሐ ግብር ተጠናቋል፡፡ የዘንድሮው የፕሪሚየር ሊግ ከዚህ ቀደም ይታዩ ከነበሩ ስፖርታዊ ባላንጣነት ይልቅ ‹‹ብሔር ተኮር›› መጠቃቃቶችና ግጭቶችን አስተናግዶ አልፏል፡፡ በሊጉ በተፈጠሩ አለመግባባቶች ምክንያት በተለይ የአዲስ አበባ ክለቦች የተለየ አቋም እንዲይዙ አድርጓል፡፡ አንጋፋው ቅዱስ ጊዮርጊስ የሊጉን የመጨረሻ ሦስት ጨዋታዎች ሳያከናውን የውድድር ዓመቱ መርሐ ግብር ተጠናቋል ቢባልም፣ የክለቡ ቀጣይ ዕጣ ፋንታ እንዴት ሊሆን ነው? የሚለውና ሌሎች ከስፖርት መርህና ባህል ባፈነገጠ መልኩ ሲሰጡ የነበሩ ውሳኔዎች፣ ፌዴሬሽኑ ከፊት ለፊቱ የተደቀኑበት ጥያቄዎችን ሳይፈታና የሊጉን ቀጣይ አካሄድ እንዴት እንደሚሆን ሳይወስን የ2012 ዓ.ም. የውድድር ዘመን በወርሃ ጥቅምት አልያም ህዳር ለመጀመር ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ሽር ጉድ እያለ መሆኑን እየተሰማ ይገኛል።ከአዲስ አበባ ክለቦች በኩል የተያዘው አቋም ገፍቶ መሄድ የፕሪሚየር ሊጉ ህልውና ጥያቄ ውስጥ መሆኑን ምልክት እያሳየም ይገኛል። ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ የሊጉን አደረጃጀት እንዲቀየር አጥብቀው ሲጠይቁና ሲሞግቱ የሰነበቱት ክለቦቹ ይህንን መንገድ በመተው በራሳቸው በመጓዝ ውጤታማ ለመሆን ከጫፍ ደርሰዋል። ከብሄራዊ እግር ኳስ ፌዴሬሽኑ በኩል ቅቡልነት ያጣው የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጥያቄም ጥናትን መሰረት በማድረግ ተቀብሎ ተግባራዊ ሊያደርገው መሆኑ ታውቋል። የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በኢትዮጵያ እግር ኳስ የሚታየውን የሊግ ውድድር የአደረጃጀት ችግሮች በመለየትና የመፍትሔ ሀሳቦች በማስቀመጥ ላይ ያተኮረ የአውደ ጥናት መድረክ ከትናንት በስቲያ በሸራተን ሆቴል አዘጋጅቷል።በመድረኩ ላይ\nዋነኛ ትኩረት የነበረው የሊግ አደረጃጀት ጉዳይ ሲሆን፤ «በኢትዮጵያ አሁን ያለው የሊግ አደረጃጀት በፋይናንስ ረገድ ክለቦች ላይ ያለው ተጽእኖ ምንድ ነው? » በሚል ጥናታዊ ጽሁፍ ቀርቦ ነበር። የጥናቱ አቅራቢ የአዲስ አበባ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ሥራ አስኪያጅ አቶ ገዛኸኝ ወልዴ እንዳሉት በኢትዮጵያ የሊግ ውድድር ፕሪሚየር ሊግ፣ ከፍተኛ ሊግና አንደኛ ሊግ ናቸው፤ በእነዚህ ውድድሮች ላይ በየዓመቱ ሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር ወጪ ይደረጋል። አብዛኞቹ ክለቦች የከተማ ቡድኖች በመሆናቸው ከዚህ ውስጥ 95 በመቶ ከመንግስት ካዝና ወጪ የሚሸፈን ነው። ገንዘቡም ለተጫዋቾች ወርሃዊ ደሞዝ፣ ለምግብ፣ ለመኝታ፣ ተዟዙሮ ለመጫወትና ለትራንስፖርት እንደሚውል ተናግረዋል።የወጪውን ከፍተኝነት ከትራንስፖርት ጋር ተያይዞ ያለውን ሁኔታ አቶ ገዛኽኝ ሲገልጹ ፤ « በዋናነት ተዟዙሮ መጫወት በሁሉም እርከኖች ለትራንስፖርት ብቻ\nግማሽ ቢሊዮን (490 ሚሊዮን 800 ሺህ) ብር በየዓመቱ ወጪ ይሆናል። ይህ ሁሉ ወጪ ወጥቶ አንድ በፕሪሚየር ሊግ ውድድር የሚሳተፍ ቡድን ሲያሸንፍ 150 ሺህ ብር የገንዘብ ሽልማት ያገኛል። ከዚህ አኳያ ወጪና ገቢው የማይመጣጠን የገንዘብ ቀውስ ያለበት የሊግ አደረጃጀት እንደሚገኝ ማሳያ ነው» ሲሉ ተናግረዋል። የጥናቱ አቅራቢ እንዳሉት የፊፋ የክለቦች ፈቃድ የሚለው በምንም መንገድ የአንድ ክለብ ወጪና ገቢ መበላለጥ የለበትም ነው፤ ሆኖም በኢትዮጵያ ያለው ነባራዊ ሁኔታ ይሄንን የሚያሳይ አለመሆኑን ገልጸዋል።ሌላው የሊግ አደረጃጀቱ ከጸጥታና ደህንነት፣ ከፋይናንስ አኳያ ያለበት ሁኔታ ምን እንደሚመስል ያቀረቡ ሲሆን ችግሮች መኖራቸውን አስረድተዋል። የሊጉ አደረጃጀት ስፖርታዊ ጨዋነት እንዲጓደል በር ከፋች መሆኑን አመላክተዋል። አሁን ያለው የሊግ አደረጃጀት ከክልሎችና ከከተማ አስተዳደሮች ተሳትፎ አንጻር ሲመዘን ሁሉንም ውድድር የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጠቅልሎ የያዘ መሆኑ አቅም ያላቸው ተጫዋቾች እድል እንዳይኖራቸው አድርጓል። የክልሎችን የውስጥ ውድድር አዳከሟል ሲሉ አደረጃጀቱ በሌላ ማዕዘን ያለበትን ክፍተት በጥናቱ አስረድተዋል። በአጠቃላይ የኢትዮጵያ እግር ኳስ የሊግ አደረጃጀት ከፋይናንስ አንጻር ሲታይ ከፍተኛ ችግር ያለበት፣ የመንግስትን ገንዘብ ጥቅም በሌለው መንገድ የሚያስወጣ፣ ስፖርታዊ ጨዋነትን በአጉል መንገድ እንዲጓዝ ያደረገም በመሆኑ ያሉትን ክፍተቶች መስመር በማስያዝና የወደቀውን እግር ኳስ ለማዳን አዲስ የሊግ አደረጃጀት ተግባራዊ ማድረግ አስፈላጊ እንደሚሆን አሳስበዋል።በአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የቀረበውን ጥናትና የሊጉ አደረጃጀት እጣ ፈንታ መሰረት በማድረግ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማኅበር ቦርድ ሊቀመንበር አቶ አብነት ገብረመስቀል እንዳሉት የአዲስ አበባ ክለቦች እስከ ዛሬ ድረስ በየክልሉ ስንሄድ ያልደረሰበን ዛቻና ድብደባ የለም። የእኛ አንድ አለመሆንና ምስቅልቅሉ የወጣ ስራ አስፈጻሚ መምረጣችን ነው ዋጋ እየከፈልን ያለው በመሆኑም ከዚህ በኋላ የአዲስ አበባ እግር ካስ ፌዴሬሽን ከጎናችን ቆሞ አንድ መሆንና ያለው የውድድር አደረጃጀት (ፎርማት) መቀየር አለብን ብለዋል ። “እንደ አዲስ አበባ አንድ ሆነን በራሳችን ውድድር እናካሂድ። በዚህ ምክንያት ጉሮሯቸው የሚዘጋ ጥቅማቸው የሚቀር ግለሰቦች የተለያየ ስም ሊሰጡን ይችላሉ። እኛ የፖለቲካ እና የብሄር ቡድኖች አይደለንም። ለሃገራችን ሰላም የሚጠቅመውን እያሰብን ነው ያለነው” ብለዋል።የኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ መሥራችና የቦርድ ሰብሳቢ መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ በበኩላቸው፤ ባለፉት ጊዜያት የተለያዩ ውይይቶችን ስናደርግ ቆይተን አሁን ወሳኝ ጊዜ ላይ ደርሰናል። እስከ ዛሬ የሊግ አደረጃጀት ( ፎርማት) የኢትዮጵያ እግር ኳስ ውስጥ ከፍተኛ ሃብት ያካበቱ ግለሰቦች ምን አይነት ሀብት እንዳፈሩ ከነመረጃው በጥናት የምናቀርብ ይሆናል ብለዋል። መቶ አለቃ ፈቃደ አክለው፤ እነዚህ ግለሰቦች የራሳችንን ውድድር ስናካሂድ ከፍተኛ ጥቅም ስለሚቀርባቸው ቡናና ጊዮርጊስ የራሳቸውን ውድድር ብቻቸውን ያድርጉ እያሉ ይሳለቃሉ። አሁን ጉዳዩ የቡናና የቅዱስ ጊዮርጊስ ብቻ አይደለም። የኢትዮጵያን እግር ኳስ ከውድቀት፣ ከሞት የማዳን ነው። ከዚህ በኋላ ለአንድ ቀን ማደር አንችልም። ይህን የመግባቢያ ሰነድ መፈረም አለብን ሲሉ በተደጋጋሚ ጥያቄን ሲያቀርቡበት የነበረውን የሊግ አደረጃጀት እንዲሻር ተማጽኖን አቀረቡ። በመድረኩ ላይ ተሳትፎ ያደረጉ 22 የአዲስ አበባ ክለቦችም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ህልውና በአዲስ የሚቀይረውን የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተቀበሉ። ከፌደራል ፖሊስ ክለብ በቀር በስብሰባው ላይ የተገኙ ለእግር ኳሱ እድገት ሆነ አላግባብ የሚወጡ የመንግስት የገንዘብ ወጪን ለማስቀረት በሚል ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ስር በመሆን ለመወዳደር በጋራ ተስማምተው ተፈራርመዋል። ስምምነታቸውም የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለሚመለከተው አካላት በሙሉ እንዲያደርስ ወስነው ጉባኤው ተጠናቋል።የዚህ አይነቱ\nየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ህልውና\nመንታ መንገድ ላይ እንዲቆም\nያደረገው ሆኗል። በጉዳዩ\nላይ ከብሄራዊ እግር\nኳስ ፌዴሬሽኑ በኩል\nምንም አይነት ምላሽም\nሆነ አስተያየት ያልቀረበ\nሲሆን፤ የአዲስ አበባ\nክለቦችን ውሳኔ ተከትሎ\nሌሎች ክልሎችም ተመሳሳይ\nአቅጣጫን እንደሚከተሉ ይጠበቃል።አዲስ ዘመን ነሃሴ 1/2011ዳንኤል ዘነበ ", "passage_id": "daaac1af515db4246ce68f63ca0bff14" }, { "passage": "አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 13/2006 (ዋኢማ) – ሁሉንም የልማት ሃይሎች አቀናጅቶ በመንቀሳቀሱ የ2006 በጀት አመት የድርጅትና የመንግስት እቅድ አፈጻጸም ውጤታማ መሆኑን የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አስታወቀ።የኢህአዴግ ም/ቤት ጽ/ቤት ለዋልታ በላከው እንዳስታወቀው ኮሚቴው በዛሬው እለት  ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው እንደገመገመው  በገጠርና በከተማ የልማትና መልካም አስተዳደር ስራዎች በድርጅት መሪነት ስኬቶችን ማስመዝገብ ተችሏል።በገጠር ልማት  ከአካባቢ አካባቢ  አንጻራዊ ልዩነት መኖሩን የጠቆመው መግለጫው በተለያዩ መስኮች ያለው የሰራዊት ግንባታ እድገት ማሳየቱንም ገልጿል።የለማውን ተፈጥሮ ሃብት ጥቅም ላይ በማዋልና ችግኞችን በመትከልም ሆነ   በመንከባከብ ረገድ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለማስወገድ  ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው አሳስቧል፡፡በ2006/2007 የምርት ዘመን የሰብል ልማት ምርትን ከ20 በመቶ በላይ ለማሳደግ የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም መግለጫው ጠቁሟል።በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ልማት ሰፋ ያለ እንቅስቃሴ የተደረገ ቢሆንም ኢንተርፕራይዞች በማኑፋክቸሪንግ መስክ በስፋት በማሳተፍና  የተፋጠነ ሽግግር እንዲያካሂዱ በማድረግ በኩል የታዩ  ክፍተቶችን ለመሙላት ርብርብ እንደሚደረግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ገልጿል።በገጠር  ለ2 ነጥብ 2 ሚሊየን ወጣቶች  የሥራ እድል ለመፍጠር ታቅዶ 85 በመቶ መከናወኑን የጠቆመው መግለጫው በከተሞችም ከ2 ሚሊዮን 600 ሺሕ በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሮላቸዋል።በትምህርት፤ በጤናና ሌሎች ማህበራዊ ዘርፎች የአመቱ አፈፃፀም ስኬታማ እንደሆነም ስራ አስፈጻሚው ተመልክቷል። ", "passage_id": "75dcf9ddf12343c9d3ad1772ca70eaab" }, { "passage": "በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ባለው የመካከለኛ አመራር ጥልቅ ተሃድሶ የውይይት መድረክ ላይ ሊቀመንበሩ እንደገለጹት በክልሉ የሚስተዋሉ ዋና ዋና ችግሮች በመፍታት የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን ማጠናከር ይገባል።\"በጥልቅ ተሃድሶው ድርጅቱ ያለውን አሰራር፣ ጥንካሬና ድክመትን በመገምገም የህብረተሰቡንና የአካባበውን ነባራዊ ሁኔታ ለመረዳትና ከወቅቱ ሁኔታ ጋር እራሱን እያመዛዘነ ለማስተካከል እጅግ አስፈላጊና ተገቢ ነው \"ብለዋል።ድርጅቱ የመጀመሪያውን ተሃድሶ ሲያደርግ 15 ዓመታት ማስቆጠሩን ጠቆሙት አቶ ለማ በዚህ ጊዜ ውስጥ በርካታ ለውጦች መገኘታቸውን ተናግረዋል።በእዚኒህ ዓመታት እየጨመረ የመጣውን የህዝብ ቁጥር ታሳቢ በማድረግ በልማት ዘርፉ አንፀባራቂ ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰው \"የወጡ ፖሊሲዎች፣ህጎችና የምንሰራቸው የየእለት ስራችን ከህዝብ ፍላጎት ጋር በማነፃፀር እንዲገመገሙ ይደረጋል\" ብለዋል ።ጥልቅ ተሃድሶው የህዝብን ጥቅም በማስከበር ረገድ ያሉ ጉድለቶችንና መልካም ነገሮችን በመመርመር መስተካከል የሚገባቸውን በዚሁ አግባብ ተፈጻሚ ለማድረግ ዓይነተኛ መሳሪያ ነው።ባለፉት ሦስት አምስት ዓመታው በህብረተሰቡ ውስጥም በርካታ ለውጦች እንዳሉ የተናገሩት ሊቀመንበሩ የህዝብ የልማት ፍላጎት መጨመሩን፣የመንግስት ስራ መስፋቱንና ውስብስብ ከመሆኑ ነባራዊ ሁኔታ አንፃር እየታየ የውስጥ አቅምን መለካት የተሃድሶው ዋነኛ ማጠንጠኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ከዚህ በመነሳት የህዝቡን ፍላጎት አሁን ያለው አቅም፣ ስፋትና ሀብት እንዲሁም የህዝቡን ጥያቄ ለመመለስና ለማሳካት ድርጅቱ ራሱን ለመፈተሽ መዘጋጀቱ ተገቢ መሆኑን ጠቁመዋል።የድርጅቱ ሊቀመንበር እንዳመለከቱት ከጥልቅ ተሃድሶው በፊት የተሰሩ ማህበራዊ፣ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊ ለውጦች ቢኖሩም በዚያው ልክ የሚታዩ ጉድለቶች ስላሉ ህብረተሰቡን ለቅሬታ ዳርገውታል፡\"ቅሬታው የተባላሹ ነገሮች እንዲስተካከሉለት ከመፈለግ የመነጨ በመሆኑ እንደ ድርጅትና እንደ መንግስት ተስተካክለን እንድንገኝ የሚያግዝ ነው \"ብለዋል ።ፍትህ በገንዘብ ሳይሆን በአግባቡ ለዜጋ እንዲሰጥ ከመፈለግ የመነጨ ቅሬታ በመሆኑ ድርጅቱ አንድ በአንድ ችግሮቹን ነቅሶ በማውጣት የማስተካከል እርምጃ እንደሚወስድ አቶ ለማ ተናግረዋል፡፡ ሥርዓቱን ለማስቀጠል የመልካም አስተዳደርና የኪራይ ሰብሳቢነት አደጋን እልባት መስጠት ተገቢ መሆኑን ጠቁመው \" ሁላችንም ቆም ብለን ራሳችንን እያየን ልንፈትሽ ግድ ነው \"ብለዋል።ድርጅቱ አስፈላጊውን አስተዳደራዊና ህጋዊ እርምጃ ጭምር ለመውሰድ አቋም ወስዶ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ መግባቱንም አስታውቀዋል።የህዝቡን ጥያቄ በጋራ በመነጋገርና በመመካከር ለመመለስ ታስቦ የተዘጋጀ ተሃድሶ መሆኑን ያመለከቱት አቶ ለማ “እኛው በእኛው ህዝብ ላይ የፈጸምናቸውን በደሎች አመራሩ አንድ በአንድ እያነሳ ሂስና ግለ ሂስ ያደርጋል” ብለዋል።\"የጀመርነውን ተሃድሶ እስከ ታች በማውረድ ህብረተሰቡ ተሳታፊ እንዲሆን ካደረግን የገባንባቸው ችግሮች አስተካክለን የተሻለና ተስፋ ያለው ስራ እንሰራለን ብለን እንጠብቃለን\" ብለዋል።ከጥቅምት 25 እሰከ ሕዳር 3/2009 ዓም ድረስ በአዳማ፣ ሀረር፣ ሻሸመኔ፣ ነቀምትና ጅማ ከተሞች እየተካሄደ ባለው የጥልቅ ተሃድሶ መድረክ ላይ ከ5 ሺህ 350 በላይ መካከለኛ አመራሮች እየተሳተፉ ናቸው። የመድረክ ዋና አላማ በክልሉ የተጀመረውን የመስመር ማጥራት እርምጃ ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋር ያለመ መሆኑም ቀደም ብሎ ተገልጿል -(ኢዜአ) ።", "passage_id": "1fa552c1beb0dcdd2259d3c930a94cd3" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ስኬታማ ያደረጉትን ሚስጥሮች በሌሎችም ትላልቅ የአገሪቱ ፕሮጀክቶች ላይ መድገም ይቻል ዘንድ ተሞክሮውን እንዲያሰፋ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ አሳሰቡ።የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በዛሬው እለት ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚገኘውን የመንገደኞች ማስተናገጃ (ተርሚናል) ጨምሮ የተለያዩ የአየር መንገዱ የሥራ እንቅስቃሴዎችን ጎብኝተዋል።በጉብኝቱ ላይ የተገኙት የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ እና የምክር ቤቱ አባላት በሰጡት አስተያየት፤ የአየር መንገዱ የአፍሪካና የዓለም ኩራትነቱን አጠናክሮ መቀጠል መቻሉን ማረጋገጣቸውን ተናግረዋል።ይህ ታላቅ ስኬት ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በሚያንቀሳቅሱ የሀገሪቱ የተለያዩ የልማት ተቋማት ላይም መጠቀም ይቻል ዘንድ የስኬት እውቀቱ ወደሌሎችም የሚተላለፍበትን መንገድ አየር መንገዱ እንዲዘይድ አፈ ጉባኤው ጠይቀዋል።የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረማሪያም በበኩላቸው ኩባንያው እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር እስከ 2025 ድረስ ለማሳካት ይዞት የነበረውን ህልም ከወዲሁ እውን ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።በአሁኑ ወቅት የኢትጵያ አየር መንገድ ደንበኞችን በማጓጓዝም ሆነ በካርጎ ጭነት ማመላለስ በአፍሪካ ከሚገኙ አየር መንገዶች ሁሉ ቀዳሚው እንደሆነ ጠቁመዋል።አክለውም አየር መንገዱ በተጠናቀቀው የአውሮፓዊያን ዓመት 12 ሚሊየን መንገደኞችንና ከ432 ሺህ ቶን በላይ ዕቃዎችን አጓጉዟል ሲሉም አስረድተዋል።በዚህ አገልግሎቱም በዓመቱ አራት ቢሊየን ዶላር ማስገባት መቻሉንም ይናገራሉ።በማንኛውም የፖለቲካ ሁኔታ ጣልቃ አለመግባቱ፤ እስከ አሁን ሀገሪቱን የመሩ መንግሥታትም በአየር መንገዱ አሠራር ላይ ጣልቃ አለመግባታቸው አየር መንገዱ ስኬታማ እንዲሆን ካስቻሉት ምክንያቶች መካከል ናቸው ብለዋል።የማኔጅመንቱ ተጠያቂነትንና ግልጸኝነትን መሰረት ያደረገ የአሠራር ሥርዓት መከተሉም ለስኬቱ ቁልፍ እንደሆነ ጠቁመዋል።የምክር ቤቱ አባላት በአየር መንገዱ የአሠራር ሥርዓትና የስኬት ሚስጥር ላይ ጥያቄና ማብራርያ ጠይቀው ከዋና ሥራ አስፈጻሚው መልስ ተሰጥቶባቸዋል።ምክር ቤቱ አየር መንገዱ ለያዘው ቀጣይ ስኬት እውን መሆን አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም አባላቱ ቃል ገብቷል።የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአምስት አህጉራት ከ127 በላይ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎች ላይ የሚበር ሲሆን፤ በሳምንት ከ2 ሺህ በላይ መንገደኞችን ያስተናግዳል፤ በየቀኑ ደግሞ ከ300 በላይ በረራዎችን እንደሚያደርግም በዚሁ ጊዜ ተጠቅሷል።ምንጭ፦ ኢዜአ", "passage_id": "7b15b00c0009147fb4a8ff827f6108b2" }, { "passage": "የኢህአዴግ ም/ቤት ጽ/ቤት ለዋልታ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ለእቅዱ እንደ መነሻ የተቀመጠውን የመጀመሪያውን የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ያለፉት አራት አመታት አፈጻጸም ከእቅዱ አላማዎች፣ አቅጣጫዎችና እና ዋና ዋና ግቦች አኳያ ገምግሟል፡፡የእቅድ አፈጻጸሙም በኢኮኖሚ እድገት፣ በመሰረተ ልማት፣ በማህበራዊ ልማት፤ በአቅም ግንባታና በመልካም አስተዳደር እንዲሁም በባለብዙ ዘርፎች ዙሪያ የህዝቦችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስኬታማ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው ብሏል፡፡ በእቅዱ የትግበራ ሂደት ቁልፍ በሆኑ ሀገራዊ የልማት ጉዳዮች ዙሪያ ከፍተኛ ህዝባዊ መነሳሳት የተፈጠረበት እንደነበረና ይህም ለቀጣይ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች የተደራጀና የተጠናከረ አቅም እንደሚሆን ኮሚቴው አስምሮበታል፡፡በመጀመሪያው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ከተቀመጡት ግቦች ውስጥ በመሰረታዊ አማራጭ በየአመቱ በአማካይ የ11.2 በመቶ እድገት ማስመዝገብ አንዱ የነበረ ሲሆን ያለፉት አራት አመታት አፈጻጸም ሲታይም ኢኮኖሚው በአመት 10.1 በመቶ በማደግ ባለሁለት አሃዝ የኢኮኖሚ እድገቱን አስቀጥሏል፡፡ አፈጻጸሙ ከተቀመጠው ግብ አኳያ የተወሰነ ጉድለት ቢኖረውም የአለም ኢኮኖሚ ከፍተኛ ችግሮችና ውጣ ውረዶች በነበሩበት ወቅት ችግሩን በመቋቋም በዚህ ደረጃ ማደጉ በጣም ከፍተኛ እድገት እንደሆነ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ገምግሟል፡፡በአገራችን የተመዘገበው እድገት በተመሳሳይ ወቅት ከሰሃራ በታች ባሉ አገሮች ከተመዘገበው የ5 በመቶ እድገት አኳያ ሲታይም በጣም ከፍተኛና ፈጣን እድገት እንደሆነ ታይቷል፡፡ እድገቱ አገራችንን በአለም አቀፍ ደረጃ እጅግ ከፍተኛ ፍጥነት ካስመዘገቡ ጥቂት አገሮች አንዷ እንድትሆን ያደረገ የትክክለኛ መስመርና ፖሊሲ ውጤት መሆኑም ተመላክቷል፡፡ ኮሚቴው ከግምገማው በመነሳት ፈጣንና ተከታታይ እድገቱን አጠናክሮ ማስቀጠል የሁለተኛው እድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱ አንዱ የትኩረት አቅጣጫ እንደሚሆን አስምሮበታል፡፡ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው በመጀመሪያዊ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱ አፈጻጸም የነበሩ ስኬቶችን፣ እጥረቶችንና ፈታኝ ሁኔታዎችን እንዲሁም የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን በዝርዝር ከፈተሸ በኋላ ለሁለተኛው የእድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅድ እንደ መነሻ እንዲሆኑ አስቀምጧል ፡፡ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ለሁለተኛው የአምስት አመት የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱ በተቀመጡ አቅጣጫዎችና ግቦች ላይ ከተወያየ በኋላ ዝርዝር እቅዱ እንዲዘጋጅ የሚያስችሉ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው እለት ማጠናቀቁን የኢህአዴግ ም/ቤት ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡ ", "passage_id": "e998294aa8798f32a7283a0938bf1bd4" } ]
9f0d6f3852caca37e94c2b2a90b869e7
8f8010b037e30c19d8f3afa6d45e4f21
የኦሊምፒክ ሥራ አስፈፃሚው እስከ ቶኪዮ ኦሊምፒክ ማግስት ይቀጥላል
ቦጋለ አበበ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አርባ አምስተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ባለፈው እሁድ በሐዋሳ ከተማ ሲያካሂድ የተለያዩ ውሳኔዎች ተላልፈዋል፡፡ ባለፉት አራት ዓመታት ሲያገለግል ቆይቶ ዘንድሮ ይጠናቀቅ የነበረው የኮሚቴው የስራ አስፈፃሚና የፕሬዚዳንት የስልጣን ዘመን በመጪው ክረምት እስከሚካሄደው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ማግስት ድረስ እንዲቀጥል ጉባዔው ወስኗል፡፡ የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ባለፈው ዓመት ሊካሄድ የነበረ ቢሆንም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ለአስራ ስድስት ወራት ተራዝሞ በመጪው ክረምት ሊካሄድ ቀን ተቆርጦለታል፡፡ ኮሚቴውን ሲመራ የነበረው ሥራ አስፈፃሚ በኦሊምፒኩ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የተለያዩ ዝግጅቶችን ሲያደርግ የቆየ ሲሆን ዘንድሮ የስራ ዘመኑን አጠናቆ በጠቅላላ ጉባዔ ምርጫ ይካሄድ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ኦሊምፒኩ በመራዘሙ ሲዘጋጅ የቆየው ስራ አስፈፃሚ የልፋቱን ውጤት እንዲመለከት እስከ ኦሊምፒኩ ማግስት እንዲቀጥል ጠቅላላ ጉባዔው ውሳኔ አስተላልፏል፡፡ ጉባዔውን በንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ፣ ኢትዮጵያ የአኖካን ጉባኤ ባስተናገደችበት ማግስት አስረኛ ክልል ሆኖ እንደ አዲስ በተዋቀረው የሲዳማ ክልል ጉባዔው መካሄዱ ልዩ እንደሚያደርገው ገልፀዋል፡፡ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ግዜ የአፍሪካ ወጣቶች ኦሊምፒክን በ2022 ለማስተናገድ እድል ባገኘችበት ማግስት በሲዳማ ክልል ዘንድሮ የኢትዮጵያ ወጣቶች ኦሊምፒክ ጨዋታ እንደሚካሄድም ጠቁመዋል፡፡ ኮሚቴው በቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ የአበበ ቢቂላን የ1964 የቶኪዮ ኦሊምፒክ ገድል ለመድገም በምትዘጋጅበት ወቅት ጉባዔውን ማካሄዱና በኮቪድ-19 ስጋት ውስጥ ሆኖ መከናወኑ ጉባዔውን የተለየ እንደሚያደርገውም ተናግረዋል፡፡ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው፣ ስፖርት የማህበራዊና ተፈጥሯዊ ሳይንስ ዘውግ መሆኑን ጠቅሰው ማህበራዊ ትስስርን በእጅጉ የሚፈጥር በመሆኑ ህብረተሰቡ ስፖርትን ባህሉ እንዲያደርግ የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል። እስካሁን ድረስ በስፖርት ዘርፍ የተፈጠረው ተወዳዳሪነት ዝቅተኛ መሆኑን በመጥቀስም በአትሌትክስ ስፖርት ኢትዮጵያ ያስመዘገበችው ውጤት በሌሎችም እንዲደገም መሠራት እንዳለበት አብራርተዋል። ሚኒስትሯ የህብረተሰብ ስፖርትንም ለማስፋፋት በትምህርት ቤትና በስራ ቦታ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ መሠራት እንዳለበት ገልፀዋል። የኢፌዲሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሸነር ኤሊያስ ሽኩር በበኩላቸው፣ 45ኛው የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የተካሄደው በስፖርት ህብረተሰቡ ዘንድ መነቃቃት በተፈጠረበት ወቅትና በብሔራዊ የስፖርት ምክር ቤት መደበኛ አንደኛ ስብሰባ ትላልቅ ውሳኔዎች በተላለፈበት ወቅት መሆኑን አስታውሰዋል፡፡ የአኖካ ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ የተካሄደ መሆኑን ጠቅሰውም ሠላማዊና አስተማማኝ ሁኔታ በኢትዮጵያ መኖሩን አኖካ በማረጋገጡ ቀጣይ ስብሰባዎችን በራሱ ሙሉ ወጪ በኢትዮጵያ ለማካሄድ መነሳሳት እንዳሳየ አብራርተዋል። ለቶኪዮ 2020 የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ዝግጅት ማድረግ በተጀመረበት ወቅት ላይ ጉባዔው በስፖርት ምክር ቤት በተቀመጡ ወሳኔዎችና አቅጣጫዎች መሠረት በጥልቀት መምከር እንዳለበት አስረድተዋል፡፡ ስፖርት ለሠላም፣ ለወዳጅነት፣ ለአንድነት፣ለወንድማማችነትና ለብልፅግና መሆኑን በመገንዘብ ጠቃሚ ውይይት እንዲደረግ አሳስበዋል፡፡ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ፕሬዚዳንት አቶ ደስታ ሌዳሞ ጉባኤውን በንግግር የከፈቱ ሲሆን፣በዕለቱ በስፖርት ላይ በመስራት እውቅና ለተሰጣቸው ፈርጦች ምስጋና አቅርበዋል። በጉባኤው በስፖርት አመራርነት በፌደራልና በክልል ደረጃ አገልግሎት ሲሰጡ ቆይተው በአሁኑ ጊዜ በተለያዩ አመራር ቦታዎች ላይ ለሚገኙ አካላት የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።ከነዚህም መካከል የቀድሞ የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትር የነበሩትና በአሁኑ ወቅት የደቡብ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ርስቱ ይርዳው፣ የቀድሞ ወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትር ዴዔታ ወይዘሮ ሃቢባ ሲራጅ፣ የቀድሞ ወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትር ዴዔታ የነበሩትና አሁን የደቡብ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆን እያገለገሉ የሚገኙት አቶ ተስፋየ ይገዙ፣ የቀድሞ የኢፌዴሪ ምክትል ስፖርት ኮሚሽነርና አሁን የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ ጌታቸው ባልቻ የእውቅና ሽልማት ከተበረከተላቸው መካከል ዋነኞቹ ናቸው። ጠቅላላ ጉባዔው የ44ኛው መደበኛ ጉባኤ ቃለ ጉባኤ ፣ የ2012 ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርትና የውጪ ኦዲተር ሪፖርት መርምሮ ያፀደቀ ሲሆን የ2013 ዓ.ም ዕቅድና የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ቀጣይ 46ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔን በተመለከተ መክሮ ውሳኔ አስተላልፏል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 28/2013
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=39012
[ { "passage": "የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ለአስራ ስድስት ወራት በመራዘሙ ምክንያት የአዘጋጅ አገሯ ጃፓን መንግሥትና የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ገና ከጅምሩ በርካታ ውስብስብ ችግሮች ውስጥ መዘፈቃቸው ሲነገር ቆይቷል። የኦሊምፒክ ውድድሩ በዓለም ላይ ከፍተኛ ስጋት በፈጠረው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ጋር ተያይዞ ወደ ቀጣዩ ዓመት መራዘሙ ግድ መሆኑ ከታመነበት ወቅት አንስቶ አዘጋጆቹ በርካታ ፈተናዎችን መጋፈጣቸው የማይቀር ሆኗል። በተለይም ላለፉት ሰባት ዓመታት የበለጠ ዝግጅት ሲደረግበት የቆየው የኦሊምፒክ ውድድር መራዘሙ ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ ማስከተሉ የአዘጋጆቹ ራስ ምታት እንደሚሆን ቀድሞም የታወቀ ነው። \nይህ ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ የጃፓን መንግሥትንም ይሁን ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴን በእጅጉ ሊፈትን እንደሚችል በባለሙያዎች አስተያየት ሲሰጥበት የቆየ ሲሆን ሁለቱ አካላት ኪሳራውን ለማካካስ እንደሚደጋገፉና ሌሎች ባለድርሻ አካላትም ለዚህ እንዲዘጋጁ ጥሪ ሲያቀርቡ ቆይተዋል። \nየዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እንዲህ ዓይነት ችግሮች ሲገጥሙት ትልቅ ተቋም እንደመሆኑ የመድህን ዋስትና እንዳለው ይታወቃል። አሁን የገጠመው ግን ካለው የመድህን ዋስትና አቅም በላይ በመሆኑ ነው እዚህ ችግር ውስጥ የተዘፈቀው። ስለዚህ የመድህን ዋስትናው በሕጉ መሠረት የሚሸፍነው ኪሳራ እንዳለ ሆኖ ተጨማሪ ኪሳራውን የሚያካክስበት አንድ ነገር መፈጠሩ የግድ ይሆናል። ይህንን ተጨማሪ ኪሳራ የጃፓን መንግሥት እንደሚሸፍን ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ ቀደም ሲል በተለያዩ አጋጣሚዎች መስማማታቸው ቢገለፅም አሁን የሃሳብ ለውጥ እንዳደረጉ የሚጠቁሙ መረጃዎች መውጣታቸውን ተከትሎ ውዝግቦች ተነስተዋል። \nየዓለም አቀፍ ኮሚቴው ፕሬዚዳንት ቶማስ ባኽ ሰሞኑን ከአንድ የጀርመን ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቃለምልልስ እንደጠቆሙት፣ ዓለም አቀፍ ኮሚቴው ከጃፓን መንግሥት ጋር በተስማማው መሠረት ለሚደርሰው በመቶ ሚሊዮን ዶላሮች የሚገመተውን ኪሳራ ለመሸፈን የራሱ ድርሻ አለው። ተጨማሪ የተባለውን ኪሳራ የመሸፈን ግዴታ ያለበት ደግሞ የጃፓን መንግሥት ነው። ይህን ስምምነት ሁለቱ አካላት እአአ 2013 ላይ እንዳደረጉ ቢገለፅም የጃፓን ካቢኔ አባላት ዋና ፀሐፊው ዮሺሂዴ ሱጋ ስምምነቱ እንዳልተደረገ አስተባብለዋል። \nይህንንም ተከትሎ በሁለቱ አካላት መካከል ውዝግብ የተፈጠረ ሲሆን ተጨማሪ የተባለው ኪሳራ እስከ ሦስት ቢሊዮን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል የጃፓኑ ክዮዶ ኒውስ ዘግቧል። የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ አዘጋጅ ቃል አቀባይ ማሳ ታካያ በበኩላቸው የጃፓን መንግሥት፣ የኦሊምፒኩ አዘጋጅ ኮሚቴና ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ውድድሩ በመራዘሙ ሊገጥሙ የሚችሉ እንቅፋቶችን በጋራ እንደሚወያዩና መፍትሄ እንደሚያስቀምጡ ተናግረዋል። \nኦሊምፒኩ በመራዘሙ ብቻ የጃፓን መንግሥትን ጨምሮ በርካታ ባለድርሻ አካላት ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ ውስጥ እንደሚገቡ ቀደም ሲል ተዘግቧል። የጃፓኑ ኦሊምፒክ አዘጋጅ ኮሚቴም ገና ከመጀመሪያው ከፍተኛ ኪሳራ ሊገጥም እንደሚችል መናገሩ ይታወሳል። ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ለዚህ ኪሳራ ስጋት ሰላሳ ሦስቱንም ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኖች የሚመለከት መድህን የገባ ቢሆንም በቂ እንደማይሆን ታምኖበታል። ፕሬዚዳንቱ ቶማስ ባኽም ኦሊምፒኩ መራዘሙን በገለፁበት ወቅት ከባድ ኪሳራ እንደሚኖር በማመን ሁሉም ባለድርሻ አካላት መስዋዕትነት መክፈል እንደሚጠበቅባቸው ለመጠቆም ሞክረዋል። ከባዱን መስዋዕትነት ማን እንደሚከፍልና ጫናው በየትኛው ወገን ትከሻ ላይ ሊወድቅ እንደሚችል ግን ከመጀመሪያውም ግልፅ አልነበረም። አሁን ላይ ገና ኦሊምፒኩ አስራ አምስት ወራት ገደማ እየቀሩትም ሁለቱ አካላት ውድድሩ በመራዘሙ የገጠማቸውን ውስብስብ ችግሮች ከመፍታት ይልቅ ከገንዘብ ጋር በተያያዘ ባለው ጉዳይ ላይ መነታረ ክ ጀምረዋል። \nየተለያዩ ተንታኞች እንደሚናገሩት ከሆነ የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በዓለም ላይ ሙሉ ለሙሉ እስከ ቀጣዩ ዓመት በቁጥጥር ስር ካልዋለ ኦሊምፒኩ በተራዘመበት 2021ም ላይካሄድ ይችላል። ከዚህም በዘለለ የመሰረዝ ዕድል ሊገጥመው ይችላል። ኦሊምፒኩ በመራዘሙ ብቻ በሚገጥመው ኪሳራ ትልቅ ውዝግብ የሚነሳ ከሆነ ከነጭራሹ ከተሰረዘ የሚገጥመው ኪሳራም በቀላሉ የሚሰላ እንደማይሆን ይታመናል። አዲስ ዘመን ሚያዝያ 17 / 2012 ቦጋለ አበበ", "passage_id": "c6132eb1ae8632b1cb425d11c6f98a83" }, { "passage": "የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ወራት ብቻ ለሚቀሩት የሪዮ ኦሊምፒክ በአፋጣኝ ወደ ስልጠና ለመግባት ሁኔታዎች እንደሚመቻቹ አመለከተ፡፡ ፌዴሬሽኑ በዝግጅቱ ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ምክክር አድርጓል፡፡ ጃፓን አስተናጋጅ የሆነችበት የቶኪዮ\n2020 ኦሊምፒክ ሊካሄዱ የቀሩት ከስድስት ወራት ያነሰ ጊዜ ብቻ ነው፡፡ በመሆኑም ካለፉት የሪዮ ኦሊምፒክና የዶሃው የዓለም አትሌቲክስ\nቻምፒዮና ተሞክሮ በመውሰድ ስልጠና እንዲታቀድና በአፋጣኝ ወደ ትግበራ እንዲገባ ሁኔታዎች እንዲመቻቹ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡ ለተግባራዊነቱም\nፌዴሬሽኑ ለሚያወጣው የምልመላና የስልጠና ዝግጅት ሚናውን እንደሚወጣ አስታውቋል፡፡ ለውድድሩ ታስበው የሚከናወኑ እንዲሁም ታቅደው\nየሚመሩና የሚፈጸሙ እንዲሆኑ ጥብቅ ክትትልና የድጋፍ ስርዓት ተዘርግቶ ችግሮች ሲያጋጥሙ በወቅቱ ተቀራርቦና ተረባርቦ መፍታት የሚያስችል\nቀልጣፋ ስርዓት እንዲዘረጋና እንዲተገበርም ፌዴሬሽኑ አሳስቧል፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከቶኪዮ\nኦሊምፒክ ጋር በተያያዘ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ትናንት ባደረገው የምክክር መድረክ ላይ ከኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን፣ ከኢትዮጵያ\nኦሊምፒክ ኮሚቴ፣ የክልልና ከተማ አስተዳደር ፌዴሬሽኖች፣ አንጋፋ አትሌቶችና የሙያ ማህበራት፣ ክለቦች፣ ማሰልጠኛ ተቋማት፣ አሰልጣኞች፣\nማናጀሮች እንዲሁም የማናጀር ተወካዮችና ሌሎችም ባለሙያዎች ተሳታፊ መሆናቸው ታውቋል፡፡ በውይይቱም ላይ አገሪቷ በተለይ በኦሊምፒክ\nውጤታማ በሆነችበት የአትሌቲክስ ስፖርት እንደተለመደው ውጤት በማስመዝገብና የአገርን መልካም ገጽታ በመገንባት ላይ ያጠነጠኑ ሃሳቦች\nተነስተዋል፡፡ የምልመላ፣ የስልጠና የአሰራር፣ ቅንጅት፣ ተግባቦት፣ ትብብር፣ ተፈጥሯዊና ንጹህ ውድድር ማድረግ እንዲሁም\nከግል ፍላጎት ይልቅ የአገርን ክብር ማስቀደም የሚሉ ሃሳቦችም ጎልተው ተንጸባርቀዋል፡፡ ትግበራውም በፌዴሬሽኑ መሪነትና አስተባባሪነት\nከባለ ድርሻ አካላት ጋር ተግባብቶና ተቀናጅቶ በመስራት ረገድ የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ የአቋም መግለጫ በማውጣት የምክክር\nመድረኩ ተጠናቋል፡፡ በአቋም መግለጫው የአትሌቶችና አሰልጣኞች ምላመላ በተሻሻለው የፌዴሬሽኑ የውስጥ አሰራር መመሪያ መሰረት\nግልጽ፣ ፍትሃዊና ተጠያቂነት የሰፈነበት እንዲሆንና ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እንዲከናወን ተጠቁሟል፡፡ አትሌቶች ዘመናዊና\nሳይንሳዊ ስልጠና ከመስጠት አንጻር የሚመረጡ አሰልጣኞች ወቅቱንና ሁኔታው የሚጠይቀውን የስልጠና ዕቅድ እንዲዘጋጅ፣ በአፈጻጸሙም\nላይ በተገቢው መንገድ ክትትል እንዲደረግበትና የማስተካከያ እርምጃዎችም በወቅቱ እንዲወሰዱ እንዲሁም የቶኪዮን የአየር ሁኔታን ያገናዘበ\nስልጠና እንደሚካሄድም ቃል ተገብቷል፡፡ ፌዴሬሽኑ ከኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጋር በመተባበር የገንዘብና የግብዓት አቅርቦት ወቅቱን ጠብቆ\nእንዲቀርብና በሥራ ላይ እንዲውልም ከስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡ ስለ አበረታች ቅመሞች ግንዛቤ ያለውና ንጹህ የሆነ አትሌት እንዲሁም\nበዓለም አቀፉ ጸረ አበረታች ቅመሞች ኤጀንሲ መመሪያ መሰረት ምርመራ ሂደቱን በአግባቡ የሚያልፉ አትሌቶች በመድረኩ እንደሚካፈሉም\nተረጋግቷል፡፡ ከዚህ ባሻገር ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለውጤታማነት እንደሚሰራም ተጠቁሟል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፣ አዲስ ዘመን ረቡዕ ጥር 27/2012 ብርሃን\nፈይሳ", "passage_id": "2bd802a362001fb9b97203a341d7206b" }, { "passage": "አዲስ አበባ፣ መጋቢት 15፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ የ2020ቱን የቶኪዮ ኦሎምፒክ ውድድር በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ለአንድ ዓመት እንዲራዘም የቀረበውን ምክረ ሃሳብ መቀባሉ ተገልጿል። ", "passage_id": "af985e57b58d499356918c60d0f8bb43" }, { "passage": "ለአንድ አገር ስፖርት ውጤታማነት ማንሰራሪያና የትንሳኤ ማብሰሪያ መላና ምክንያት ከሆኑት ውስጥ በተለይ በዋና ከተሞች የሚካሄዱ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ተጠቃሾች ናቸው። የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን በአዲሱ ዓመት – የዓመታት ቁጭቴን በእርካታና በተስፋ ለመሙላት እንዲሁም ለስፖርቱ ትንሳኤ የምችለውን ለማከናወን ቆርጬ ተነስቻለሁ” ብሏል፡፡ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል ጋር ቆይታ ያደረጉት አቶ ዮናስ አረጋይም የኮሚሽኑን ተግባራትና መፃኢ ተስፋ አብራርተዋል፡፡ አዲስ ዘመን፡- የከተማ አስተዳደሩ\nበ2011 ዓ.ም በስፖርቱ ዘርፍ ካከናውናቸው ተግባራት መካከል እንደ ስኬት ያስመዘጋባቸው ምን ምን ጉዳዮች ነበሩ? አቶ ዮናስ፡- በስኬት ደረጃ ያስቀመጥናቸው አምስት ጉዳዮች ናቸው፡፡ የመጀመሪያው አጠቃላይ መዋቅሩን ከታች እስከ ላይ እንዲለወጥ\nአድርገነዋል፡፡ የማያስፈልጉ መዋቅሮችን አስነስተናል፡፡ የተሻሉ መዋቅሮችን ደግሞ ወደፊት እንዲሄዱ አድርገናል፡፡ ለምሳሌ፤ የማያስፈልገው\nአንዱ የኮንስትራክሽን ዘርፉ ነው፡፡ እሱን አንስተን ኮንስትራክሽን ቢሮ ይመለከተዋል ብለን ሰጥተነዋል፡፡ ስፖርት ኮሚሽኑ የማዘውተሪያ\nስፍራ ያስፈልገናል የሚል ጥያቄ ማቅረብ እንጂ፤ መሐንዲስ በሌለበት የማዘውተሪያ ግንባታ ማካሄድ አይደለም፡፡ ኮሚሽኑ በስፋት የስፖርት ከፍተኛ ባለሙያዎች አልነበሩትም፡፡ ስለዚህ\nከሚሽኑ በሚያስተዳድራቸው እንደ ራስ ኃይሉ፤ አበበ ቢቂላ፤ ጃንሜዳ፤ አራት ኪሎ ሥልጠና ማዕከላት ሁለት ሁለት ከፍተኛ ባለሙያዎች\nእንዲመደቡ አድርገናል፡፡ እነዚህ ማዕከላትም አብዛኞቹ ስፖርትንና የስፖርትን ሥራ ትኩረት አድርገው እንዲሰሩ ሆኗል፡፡ ይህም በተሻለ\nደረጃ ተተግብሯል፡፡ የማያሰሩ ማነቆዎች የተባሉትን በጠቅላላ በባለሙያ በተደገፈ ጥናት ፈትሸን ለማየት ጥረት አድርገናል፡፡ ከዚህ\nጋር ተያይዞ ለውጥ ባደረግንበት ልክ የሰው ሃይላችንን የመደልደል ሥራም ሠርተናል፡፡ የዚህ ውጤትም የስፖርት ኮሚሽን ከዚህ በፊት\nየነበረውን እንደ ልብ እንዳይሠራ ያደረገውን አሠራር ለማረምና አዲስ አበባ ያጣቸውን የስፖርት ማዕከልነቷን ለመመለስ ነው፡፡ ይህንን\nትኩረት አድርገን ስንሰራም በመዋቅሩ ዙሪያ ምን መደረግ አለበት ብለን ከፍተኛ ግምገማ አድርገናል፡፡ ሌላኛው፤ እንደ መንግሥትም ሊበራታታ የሚገባው ጉዳይ በቀደመው አደረጃጀት የወጣቶች ጉዳይና ስፖርት በጋራ የነበረ\nሲሆን፤ ስፖርት ራሱን ችሎ ይሂድ የሚል መዋቅር የመጣውም በዚህ ዓመት ነው፡፡ ሁለተኛው፤ የስኬት ተግባር የማዘውተሪያ ሥፍራን የተመለከተ ነው፡፡ ምንም እንኳን የአዲስ አበባን ጥያቄ በሚመጥን\nመልኩ ተመልሷል ባይባልም ትናንት የነበሩትንና ያደሩትን ውዝፍ ሥራች ግን ማገባደድ ችለናል፡፡ ለምሳሌ፤ የአበበ ቢቂላ ስታዲየም\nየረጅም ጊዜ የግንባታ ችግር ነበረበት፡፡ የማስፋፊያ ችግር ነበረበት፡፡ ከተማዋንም የሚመጥን አልነበረም፡፡ አሁን ግን ከተማዋን\nበሚመጥን መልኩ የወንበር፤ የትራክና የጣራ ሥራዎች ተጠናቅቀው አጠቃላይ ሥራው ወደ 95 በመቶ ያህል አልቋል፡፡ ከ105 ሚሊዮን\nብር በላይም ወጭ ተደርጎበታል፡፡ ከህዳሴ ግድብ እኩል የተጀመረው የሜዳ ቴኒስና የዓለም አቀፍ መዋኛ ገንዳውም በአጭር ጊዜ ውስጥ ቀንና ሌሊት\nእየተሠራ እንዲጠናቀቅ ተደርጓል፡፡ የቀረን ውሃ መሙላትና መሞኮር ብቻ ነው፡፡ ሁለቱም የመዋኛ ስፍራዎች፤ ማለትም የህፃናቱም የአዋቂውም\nተጠናቅቀዋል፡፡ ይህም ከ500 ሚሊዮን በላይ ወጭ ተደርጎበታል፡፡ ከዚህ በፊት የተጀመሩትን ሥራዎች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ ከማድረግ\nአኳያ በርካታ ሥራዎች የተሰሩበት ወቅት ነበር፡፡ እዚህ ላይ ሊታሰብ የሚገባው ቁምነገር ግዙፍ የሆኑ ሜጋ ፕሮጀክቶችን መሥራት አይደለም\nትልቁ ነገር፤ ዋናው ነገር ተደራሽ በሆነ ሁኔታ አነስ አነስ ያሉ ማዘውተሪያ ቦታዎችን መሥራት ነው የሚያዋጣው፤ በመሆኑም፤ በ2012\nዓ.ም የምንሰራቸው እንዳሉ ሆነው በአፈጣኝ ግን በ117ቱም ወረዳዎች የጥርጊያ ሜዳ መሥራት አለብን ብለን ተነስተን 61 ቦታዎች\nተሳክተውልናል፡፡ አዲስ አበባ የነበራትን ነባር ሜዳ በማጣት ነው እንጂ የምናሳልፈው አዲስ ሜዳዎች ሲጨመሩ ብዙም የተለመደ አልነበረም።\nይህ በሁለተኛው የዕቅድና ትራንስፎርሜሽን ዘመን ያልሠራነውን ነው በዚህ ዓመት ማሳካት የቻልነው፡፡ ከዚህ ውጭ 63 ቦታዎች የይዞታ\nማረጋገጫ ካርታም አስወጥተናል፡፡ አንዳንዱ ቦታ ካርታ ስለሌለው ማንም ባዶ ቦታ ሲያይ መጥቶ ይገነባል፡፡ ይህ እንዲቀርም ተደርጓል፡፡\nሦስተኛው፤ የታዳጊዎችን ፕሮጀክቶች ከአዲስ አበባና\nከኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በዝርዝር እንዲገመገሙ አድርገናል፡ ፡ ገልለተኛ አካላቱ ፕሮጀክቱን ሲያጠኑ እስከዛሬ\nበነበረው አሠራራችን ላይ ችግር እንደነበር አመላክተዋል፡፡ በእርግጥ የተወሰኑ ፕሮጀክቶች የተሻሉ መሆናቸውም ታይቷል፡፡ በድምር\nውጤቱ ግን በአዲስ መንገድ መሄድ እንዳለብን ያመላከቱ ናቸው፡፡ ወደ 132 የሚሆኑ ጣቢያዎች ላይ በነበሩ እንቅስቃሴዎች ከአራት\nሺህ አምስት መቶ  በላይ ልጆች የታቀፉበት ሥራ ግን በስኬት\nየሚታይ ነው፡፡ እነዚህም አጠናክረን እንቀጥላለን፡፡ ስለዚህ ታዳጊዎች ላይ በአዲስ ዓመት አዲስ ሐሳቦች ተግባራዊ ይደረጋሉ፡፡\nበተመረጡ ቦታዎች ላይ ብቻ ለመስራት ነው ዕቅድ የተያዘው፤ በዚህ ዓመት በዘጠኝ የስፖርት ዓይነቶች እስከ ሦስት ዓመት ድረስ ካልሰራን\nመወዳደሩ አይጠቅምም የሚል አቋም ላይ ነን፡፡ በነገራችን ላይ፤ አዲስ አበባ ላለፉት ስድስት ዓመታት ከስፖርት ማዕከልነቷ ወጥታ\nበአገር አቀፍ ውድድሮች ስድስተኛና ሰባተኛ ደረጃ ነበር ይዛ የምታጠናቅቀው፤ ስህተታችንን ስላወቅን በትክክል በሰራነው ላይ ብቻ\nበመሳተፍ ያልሰራነውን በመተው ጥራት ላይ ት ኩረት ማድረግ ጀምረናል፡፡ በአራተኛ ደረጃ፤ ለአጠቃላይ ባለሙያዎች ሠፋፊ ዓለም አቀፍ ይዘታቸውን\nየጠበቁ ሥልጠናዎች ተሰጥተዋል፡፡ የመጨረሻና ትልቁ ሥራ ደግሞ የማስ ስፖርትን የማጠናከሩ ተግባር ነው፡፡ ስፖርት መሰረቱ ማስ ስፖርት\nነው። ይህም በኢትዮጵያ የስፖርት ፖሊሲ ላይ በግልጽ ተቀምጧል፡፡ ማስ ስፖርት ባህል ሆኖ እንዲቀጥልም የተሻለ ሥራ ተሠርቷል፡፡\nአዲስ ዘመን፡- እነዚህን\nስኬታማ ተግባራት ስታከናውኑ ምንም ሳንካ አልነበረም ማለት ነው? አቶ ዮናስ፡- ቀላል የማይባሉ ችግሮች ነበሩብን፡፡ መዋቅር ሲስተካከል በክፍለ ከተማ ላይ በስፖርት የሰለጠኑ ብቻ ናቸው የስፖርት\nዘርፍ ዳይሬክተር መሆን ያለባቸው ስንል በማኔጅመንትና በኢኮኖሚክስ የጨረሱ ነበሩ የተመደቡት፤ ይህንን ለማስተካከል ችግር ፈጥሮ\nነበር፡፡ በሌላ በኩል፤ ታዳጊዎች ላይ አሁንም ቀላል የማይባሉ ማነቆዎች አሉ፡፡ ለምሳሌ፦ አንዱ ችግር የእድሜ ማጭበርበር ነው፡፡\nአሾልኮ የሚያስገባውም የሚገባውም ትስስር ያላቸው ናቸው፡፡ ልምምድ በአግባቡ ያለመስራት፤ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በተሻለ ፍጥነት\nየፍፃሜ ሥራዎችን አለማከናወን፣ በቢሮ በኩል ደግሞ ትጥቅ አለማድረስ፤ አበልና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞችን ማዘግየት፤ እልፍ ሲል ደግሞ\nየጥራት ጉድለቶችም እንዳሉ አስተውለናል፡፡ በፈፃሚዎች መካከል ያሉ ድክመቶችም ተስተውለዋል፡፡ ከዚህ ውጭ አዲስ አበባ ላይ የማዘውተሪያ\nሥፍራ ችግር ቀላል አይደለም፡፡ በተለይ በልማት ምክንያት ተነሽ በሆኑ አካባቢዎች አንድ ስንዝር መሬት እንኳን ማግኘት ችግር ነበር፡፡\nማስ ስፖርቱን ቁልፍ ጉዳይ አድርጎ አለመግምገም እንዲሁ እንደ ክፍተት የሚታይ ነው፡፡ እንደ ካርኒቫልና ፌስቲቫል ከማየት በዘለለ\nበእያንዳንዱ ወረዳ ላይ እንዲተገበር በማድረግ ረገድ ችግር አለ፡፡ የመጨረሻው አንዱ ችግር የአዲስ አበባ ስታዲየም ጉዳይ ነው፡፡ እንደሚታወቀው ሁሉም ክልሎች ስታዲየም አላቸው፡፡\nበፌዴራል የሚተዳደር ስታዲየም የላቸውም፡፡ የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን መሥራት ያለበት በስትራቴጂክ ጉዳዮች ላይ ነው እንጂ ክልሎች\nበሚሰሩት ጉዳዮች ላይ መካተቱ ስፖርቱን ያዳክመዋል የሚል እምነት ነው ያለኝ፤ እኛም የአዲስ አበባ ስታዲየም ሜዳው ይሰጠን ብለን\nአመልክተናል፡፡ ይህንን እየጠበቅን ነው፡፡ በተለይ በስታዲየሙ ዙሪያ ያለው የአልኮል መጠጥ ንግድ ቤቶች በስፖርቱ ላይ ከፍተኛ ማነቆ\nእንዲፈጠር አድርገዋል፡፡ በመሆኑም ስታዲየሙን ተረክበን አልምተን ለከተማዋ ማህበረሰብ አገልግሎት እንዲሰጥ እናደርጋለን፡፡ ይህ\nሲሆን ደግሞ የሚገጥመውን የፋይናንስ ችግር ለመቅረፍ ያግዛል፡፡ አዲስ ዘመን፡- ወርሐዊው\nየማስ ስፖርት ተሳትፎ ለፖለቲካ ፍጆታ እንጂ ስፖርታዊ መሠረት የለውም የሚሉ አካላት አሉ። አርስዎ በዚህ ጉዳይ ላይ ምን ይላሉ?\nስፖርታዊ ክንዋኔውስ ከታለመለት ዓላማ አንፃር ምን ያህል ውጤታማ ነበር? አቶ ዮናስ፡- በመሰረቱ ስፖርት ከዘር፤ ከሃይማኖትና ከፖለቲካ የፀዳ ነው፡፡ የኦሊምፒክ ውድድሮችን ብዙ ጊዜ በከተማችን ውስጥ\nስናካሄድ ቆይተናል፡፡ ስፖርትን የሚያጠናክረው ሠላም ነው፤ የሚያፈርሰውም የሰላም እጦት ነው። አገራችን ውስጥ በሚፈጠር ችግር የስፖርቱ\nቤተሰብ ለሰላሙ አቅም ካልሆነ ስፖርት ምንም አይጠቅመንም፡፡ ስፖርት ለአገራችን አንድነትና ፍቅር ጠንካራ የሆነ መሠረት መፍጠሪያ\nነው፡፡ ኦሊምፒክን የመሰረተው እኮ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት የፈጠራቸው ችግሮች ናቸው፡፡ በነገራችን ላይ ኦሊምፒክ ውድድር አይደለም።\nአሁን አሁን የውድድር መልክ ያዘ እንጂ አንድነትና ፍቅር የሚገለፅበት መድረክ ነበር፡፡ ስለዚህ የማስ ስፖርቱ በህዝባችን ውስጥ\nእንዲሰርፅ ማድረግ አንድነትን ማጠናከሪያ እንጂ በሌላ እይታ የሚታይ አይደለም፡፡ ስፖርቱ ያቀራርባል እንጂ የፖለቲካ ተልዕኮ አይደለም፡፡\nበአሁን ወቅት በስፖርት ቤት የገባው አንዱ ነገር ዘረኝነት ነው፡፡ ለዚህ ነው “ዘረኝነት ይብቃ” የሚል መሪ\nቃል/ሞቶ እየተጠቀምን ያለነው፤ ስፖርት የፖለቲካው ትኩሳት ጥሩ ሲሆን ጥሩ የምንሆንበት፤ መጥፎ ሲሆን መጥፎ የምንሆንበት አካሄድ\nአይደለም፡፡ ፖለቲካው ጥሩም ሳይሆን ወደ ሠለም መመለሻ አቅም መሆን አለበት፡፡ ስፖርት ሠላም ነው ካልን ሰላም የሚያደፈርሱ ሃይሎችንም\nከእኩይ ተግባራቸው የሚያወጣ ነው፡፡ ትኩሳትን የሚያበርድ እንጂ ለመንግሥትና ለህዝብ ራስ ምታት መሆን የለበትም፡፡ ከዚህ አንፃር፤ ምንም የፖለቲካ አጀንዳ የለውም። የፖለቲካ አመራሮች በማስ ስፖርት ላይ ተገኙ ማለት አጀንዳው\nፖለቲካ ነው ማለት አይደለም። መቀራረብና መፈቃቀር ግን አጀንዳው ነው፡፡ ሁሉም ተጋግዘው ነው እየሠሩ ያሉት፤ የሚተላለፈው መልዕክት\nእንዴት መሥራት እንዳለብን የሚጠቁም ነው፡፡ የስፖርት ቤተሰቡም የመገኘትም ያለመገኘትም መብት አለው፡፡ የማስ ስፖርት መርሐ ግብር ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ዓላማውን እያሳካ ነው፡፡ በማህበረሰቡ ዘንድ\nመቀራረብ ፈጥሯል፡፡ ሰዎች በጉጉት እንዲጠብቁት ሆኗል፡፡ የተሳታፊዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል። ከጤና አኳያም ብዙ\nሰው ባህል አድርጎት እየተሳተፈበት ነው፡፡ የማስ ስፖርት ከጀመርን በኋላ 21 ወረዳዎች በተጠናከረ መልኩ እየሠሩ ይገኛሉ፡፡ አዲስ ዘመን፡- በመዋቅር ለውጡ ስፖርት ኮሚሽን ራሱን ችሎ\nእንዲቆም ቢደረግም ተጠሪነቱ ግን ለወጣቶችና በጎ ፈቃድ ማስተባሪያ ቢሮ መሆኑ አሉታዊ ተጽዕኖ አይኖረውም? አቶ ዮናስ፡- ክልሎች የተለያየ አደረጃጀት ይኖራቸዋል፡፡ አዲስ አበባ ላይ አሁን ባለው ሁኔታ ለስፖርቱ ትልቅ ትኩረት ከተሰጠው\nተጠሪነቱ ለከንቲባው መሆን አለበት የሚል እምነት አለኝ። ይህንንም ምክትል ከንቲባው በተገኙበት በዓመታዊ ግምገማ ላይ ተናግሬያለሁ፡፡\nአሁንም ራሱን ችሎ እየሄደ ነው ለማለት ግን የሚጎድለን ነገር የለም፡፡ ቡድን መሪ፣ ዳይሬክተሮችና አመራሩ ነው ወሳኙ፡፡ ሥራውን\nአጠናቅቆ የመሥራት አቅም ካለ የተጠሪነቱ ጉዳይ አያሳስብም፡፡ ስለዚህ በአሁኑ ወቅት ራሱን የቻለ ተቋም ነው ብለን እየመራን ነው፡፡\nከድጋፍ ጋር በተያያዘ ግን ከከንቲባው ጽህፈት ቤት ጋር መሠራት አለበት የሚል አቋም ነው ያለኝ፤ ይህም የሚወሰነው እንደ አመራር\nሚና ይሆናል ብዬ አስባለሁ፡፡ አዲስ ዘመን፡- ኮሚሽኑ በአዲሱ\nዓመት በዋናነት ምን ምን ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ ሊሠራ አቀደ? አቶ ዮናስ፡- ከሚሽኑ የራሱ ስትራቴጂክ ዕቅድ አለው፡፡ ዋና ፍኖተ ካርታውም መነሻው ከዚህ ነው። የስትራቴጂክ ዕቅዱ ዋና\nራዕይ “አዲስ አበባ ላይ ያለው ትውልድ በተክለ ሰውነትም ሆነ በአዕምሮው የዳበረ፤ በአስተሳሰቡ የተሻለ ጠንካራ ዜጋ በስፖርት ዘርፉ\nመገንባት” ነው፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን ደግሞ በአገራዊ ጥሪዎች ላይ ከዓለም የጎላ ተወዳዳሪነት መንፈስን ተግባራዊ ማድረግ ነው፡፡\nበዚህ አዲስ ዓመት የጥርጊያ ሜዳዎቻችንን ማስፋፋት፣ ጥርጊያ ሆነው የተሰሩትን ደግሞ ወደ ሣር ማሸጋገርና ወጣቶችን\nአደራጅተን የተሻለ ሥራ ለመሥራት አቅደናል፡፡ 32 ሦስት በአንድ የሆኑ ሜዳዎችን መስራትም አንዱ ዕቅድ ነው። የተጀመሩትን ፕሮጀክቶች\nሙሉ ለሙሉ እንዲጠናቀቁ ማድረግም ሌላኛው ሥራ ነው፡፡ ሌለኛው ደግሞ የተለዩ የማዘውተሪያ ሥፍራዎችን የመረከብና የማከል ሥራ ነው፡፡\nየማስ ስፖርቱን በተጠናከረ መልኩ በማስቀጠል በሁሉም ወረዳ ተግባራዊ ማድረግ የኮሚሽኑ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ\nነው፡፡ የታዳጊ ፕሮጀክቶችን በተመረጡ ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች ላይ በሚታይና በሚቆጠር ሥራ ላይ ትኩረት እናደርጋለን፡፡ ለዚህም\nለትምህርት ቤቶች በር እንከፍታለን፡፡ ዋናው ነገር በተመረጡ ስፖርቶች ብቻ ውድድር እያደረግን በአዲሱ ዓመት አዲስ አበባ የስፖርት\nማዕከልነቷን እንድትመልስ ማድረግ ነው፡፡ ለዚህም የስፖርቱን ቤተሰብ አቅም ከመገንባት አኳያም የተጀመሩትን ተግባራት እናስቀጥላለን፡፡\nአዲስ ዘመን፡- የከተማ አስተዳሩ በስፖርቱ ዘርፍ ከሌሎች ዓለም\nአቀፍ እህት ከተሞች ጋር ተሞክሮ የመቅሰም ልምድ ካለው ቢጠቅሱልኝ፤ አቶ ዮናስ፡- እስካሁን አለነበረም፡፡ ከአሁን በኋላ ለመጀመር ግን ከተለያዩ አገራት አምባሳደሮች ጋር ተናጋግረናል፡፡\nየአርጀንቲና፣ የጃፓን፣ የፈረንሳይና የኮሪያ ተጠቃሾች ናቸው። ስለዚህ በ2012 ዓ.ም ከእህት ከተሞች ጋር በከተማ አስተዳደሩ አማካኝነት\nትስስር ፈጥረን በማስ ስፖርትና በታዳጊዎች ላይ እንሠራለን፡፡ ከሚበልጡን ለማማር ዕቅድ ይዘናል፡፡ አዲስ ዘመን፡- አዲስ አበባ የአገሪቷ ርዕሰ መዲና ሆና ሳለች\nዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ስታዲየም ማጣቷ ለምንድነው? ወደፊትስ ምን ታስቧል? አቶ ዮናስ፡- ስታንዳርዱ በምን ደረጃ ነው መሆን ያለበት የሚለው ነገር እንዳለ ሆኖ፤ በአጠቃላይ ግን ባዳ መሆናችንን\nያሳያል፡፡ ምክንያቱም “የአዲስ አበባ ስታዲየም ለምንድነው ደረጃውን ያላሟላው?” የሚለውን ነገር አናውቀውም፡፡ ከሚመለከታቸው አካላት\nጋር አብረን ሆነን በምክክር እንዳንሠራ ችግር አለ፡፡ በግብረ መልሶች ላይ ከኮሚሽነሮች ጋር ተቀምጠን አልተወያየንም፡፡ ነግር ግን፤\nበዚህ ዙሪያ በርከታ ሥራ መሥራት እንዳለብን እረዳለሁ፡፡ ችግሩ እንዳይደገምም እየሠራን ነው፡፡ አዲስ ዘመን፡- የባህል ስፖርቶችን በከተማዋ እንዲስፋፉ ለማድረግስ\nምን እየተሠራ ነው? አቶ ዮናስ፡- በቅርቡ አምቦ ላይ በተደረገው የባህል ስፖርት ውድድሮች በከተማ ደረጃ የተሻለ አፈፃፀም ታይቷል፡፡\nበቀጣይም ከባህልና ቱሪዝም ጋር በመተባበር ሥልጠና እንዲሰጥና የባህል ስፖርቱን አጠናክረን መሄድ እንዳለብን ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡\nበአዲሱ ዓመት ከምንሠራቸው ተግባራትም አንዱ ትውልዱ አገሩን እንዲወድ በባህል ስፖርት ላይ ትኩረት ማድረግ ነው፡፡ ነባር የሆኑ\nየባህል ስፖርቶች እንዳይጠፉ ግን በከተማዋ ላይ በርካታ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ነው፡፡ አዲስ ዘመን፡- ለሰጡኝ ሰፊ ማብራሪያ አመሰግናለሁ! አቶ ዮናስ፡- እኔም በጣም አመሰግናለሁ!አዲስ ዘመን መስከረም 2/2011አዲሱ ገረመው ", "passage_id": "a9110a474f2eb59073e6aad97829a75a" }, { "passage": "የአፍሪካ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማኅበር (አኖካ) እ.ኤ.አ. በ 2022 ሌሴቶ እንድታስተናግድ ተወስኖ የነበረውን አራተኛውን የአፍሪካ ወጣቶች ውድድር ከሀገሪቱ ነጥቆ ወደ ኢትዮጵያ አዛውሯል፡፡\nሌሴቶ ለውድድሩ በቂ ዝግጅት እያደረገች ባለመሆኑ ውድድሩ ከማሴሩ ወደ አዲስ አበባ መዛወሩን ማህበሩ ስለማሳወቁ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የቶኪዮ ኦሊምፒክ ብሔራዊ ዝግጅት አባል አራያት ራያ ለአል ዐይን እንዳረጋገጡት ኢትዮጵያ ውድድሩን እንድታስተናግድ የተመረጠች ሲሆን ከአፍሪካ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማኅበር ጋር በወጪ መጋራት እና መሰል ጉዳዮች ላይ ውይይት እየተደረገ ነው፡፡\n“የ 2022 የአፍሪካ ወጣቶች ጨዋታዎች ለኢትዮጵያ አዲስ አበባ ከተማ ተሰጥቷል፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት ይህንን ዝግጅት በጥሩ ሁኔታ ለማስተናገድ ቁርጠኛ ነው” ሲል አኖካ በመግለጫው ይፋ አድርጓል፡፡\nውድድሩን እንድታስተናግድ በ2018 ዕድሉ ተሰጥቷት የነበረችው ሌሴቶ በኢኮኖሚ ችግር ምክንያት ላለፉት 2 ዓመታት ምንም ዝግጅት ሳታደርግ ስለመቆየቷ ነው ማኅበሩ የገለጸው፡፡\nከሁለት ዓመታት በኋላ የሚካሔደውን 4ኛውን የወጣቶች ውድድር የተነጠቀችው ሌሴቶ በምትኩ በቂ ዝግጅት በማድረግ ከአራት ዓመታት በኋላ በ2026 የሚካሔደውን 5ኛውን የአፍሪካ ወጣቶች ጨዋታዎች እንድታስተናግድ ተወስኗል፡፡\nየአፍሪካ ወጣቶች ጨዋታዎች የመላው አፍሪካ ጨዋታዎችን በመተካት በየአራት ዓመቱ በተለያዩ የስፖርት አይነቶች የሚካሔድ ውድድር ሲሆን ከዚህ ቀደም የተካሔዱትን 3 ውድድሮች ሞሮካ ፣ ቦትስዋና እና አልጄሪያ በቅደም ተከተል አስተናግደዋል፡፡\nኢትዮጵያ ከሁለት ወራት በኋላ በአውሮፓውያኑ ታህሳስ 6 የአፍሪካ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማኅበር ጉባዔን እንደምታስተናግድም ከአል ዐይን ጋር ቆይታ ያደረጉት በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የቶኪዮ ኦሊምፒክ ብሔራዊ ዝግጅት አባል አራያት ራያ ተናግረዋል፡፡ ለዚህም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ ነው የገለጹት፡፡\n", "passage_id": "71ae6a3bf08411890767101849fdbfbd" } ]
011166bfa21097cce9355a345d96d1ab
3b9c93b94fd66f9cc1b902020a88e47d
"‹‹ሃገራዊ ችግሮችን ለማረምና አብሮነትን ለማጠናከር ስፖር(...TRUNCATED)
" ብርሃን ፈይሳ አዲስ አበባ፡- እንደ ሃገር እየታዩ ያሉትን ስ(...TRUNCATED)
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=38512
[{"passage":"አዲስ አበባ፡-ወጣቱ የአድዋ ድል ለአገ ራዊ አንድነት (...TRUNCATED)
969a1adb3c275dfcb72c9a19b262ffbc
bd78535bcffacfe1ae1b0f84cba42cf0
"በውድድር ወቅት በወረርሽኙ መከላከያ መመሪያዎች አተገባበር (...TRUNCATED)
"ብርሃን ፈይሳ አዲስ አበባ፡- ስፖርታዊ እንቅስቃሴና ውድድሮ(...TRUNCATED)
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=38515
[{"passage":"አዲስ አበባ፡- በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ (...TRUNCATED)
417d669827e164060f52c003b36785ba
d99a3fe0fff3173d45bf256751d61f8b
ስፖርትን ከፖለቲካ የመለየት ፈተናዎች
"ቦጋለ አበበ‹‹ስፖርትና ፖለቲካ አንድ ናቸው ወይም ጠንካራ (...TRUNCATED)
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=38578
[{"passage":"በእግር ኳሱ የሚስተዋለው ችግር ካልታረመ ውድድርን እ(...TRUNCATED)
fd7e7687d7041a2b2aaf7fbf9e3ab5f6
fa5997abb25501d92753abc953d0c38c
የዓለም አትሌቲክስና 2020 የውድድር ዓመት
"ቦጋለ አበበ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት የዓለም ማህበራዊ(...TRUNCATED)
ስፖርት
https://www.press.et/Ama/?p=38650
[{"passage":"ያልተጠበቁ አስደናቂ አሸናፊዎች፣ ለአሸናፊነት ጥቂ(...TRUNCATED)
3937ddb483244f33d24e7d8e99f63c58
d7ff0b5545f060e154c21078eb959f90
ለራስ ሲባል ሌላውን …
" ኧሯ! እንዴት ሆኖ እንዴት ሆኖ እኛንማ አይደፍርም! ብለን ነበ(...TRUNCATED)
መዝናኛ
https://www.press.et/Ama/?p=31198
[{"passage":"መልካም አስበን፣ መልካም ነገር ሰርተንና መልካም ሆነ(...TRUNCATED)
End of preview. Expand in Data Studio
README.md exists but content is empty.
Downloads last month
62